ኦርቶዶክሳዊ ሕይወት @orthodoxy_life Channel on Telegram

ኦርቶዶክሳዊ ሕይወት

@orthodoxy_life


''ኦርቶዶክስ ክርስቶስ ያሰባት ፣ ሐዋርያት የሰበኳት ፣ አባቶች የጠበቋት'' ቅዱስ አትናቴዎስ https://youtube.com/@orthodoxy_life?si=jhBnTj5VmIcmXlLb

ኦርቶዶክሳዊ ሕይወት (Amharic)

ኦርቶዶክሳዊ ሕይወት የማድረግ የጥንቃቄና የትምህርት ቢኖርበት ላይ ሕይወት ቅዱስ ምንድን ነበረ? ምን ነበር? በዚህ ህገወጥ ይህን ጽሁፍ ለመተግበም የግል አማራጮችን ይረዳሉ. ኦርቶዶክስ ክርስቶስ ያሰባት፣ ሐዋርያት የሰበኳት ፣ አባቶች የጠበቋት፣ እና በርቸ አማራጭዎች ምክንያት አዲሱን ወንጌላዊ ስለሆነ፣ ይህ ምስል በደንብ ሊያመነዝዝ ይችላል. የሆነው ሉባልና ተስፋ በሚጠብቋቸውም ዘርፍ ሰብስቦ ለሁሉም ህዝብ የትኛውን እምነት ለማሳየት እንዝጋ።

ኦርቶዶክሳዊ ሕይወት

02 Feb, 10:26


እውነተኛው የወይን ግንድ

አዳም የሰው ልጆች መነሻ ነው ። አዳም የሰው ዘር ግንድ ነው ። የሰው ልጅ ጉዞ የጀመረው በእርሱ የቀጠለውም ከእርሱ አብራክ በተገኙት ልጆች ነው ። ሔዋንም የተገኘችው ከአዳም ነው ። አዳም የመጀመሪያው አባት ብቻ ሳይሆን የመጀመሪያዋ እናት የሔዋን እናትዋ ነው ። አዳም በኃጢአት በወደቀ ጊዜ ብልየት ወይም እርጅና አገኘው ። ኃጢአት ያስረጃል ፣ የማሰብን አቅም ፣ የመናገርን ብቃት ፣ የመሥራትን ችሎታ ያሳጣል ። በኃጢአት ብልየት ውስጥ ያለ ጽድቅን በነበር ክፋትን በአሁን ያወራል ። አዳም እውነት የሆነውን የእግዚአብሔርን ትእዛዝ እንደ ውሸት ቆጥሮ ሐሰት የሆነውን የዲያብሎስን ቃል እንደ እውነት ተቀበለ ። በዚህ ምክንያት ሐሰተኛ ሆነ ። ሲፈጠር እውነተኛ ግንድ እንዲሆን ነበር ፣ አሁን ሐሰተኛ ግንድ ሆነ ። ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደዚህ ምድር ሲመጣ ዳግማዊ አዳም ተብሎ ነው ። እርሱ ርስት አስመላሽ ፣ ጠላትን ተበቃይ ነው ። ራሱ እውነት ስለሆነ እውነተኛው የወይን ግንድ ነኝ አለ ። ሐሰተኛው የወይን ግንድ መራራ ፍሬ እንድናፈራ ምክንያት ሆነ ። እውነተኛው የወይን ግንድ ግን ጣፋጩን የጽድቅ ፍሬ ለማፍራት አስቻለን ። ግንዱ አዳም ሞቶ ስለነበር ቅርንጫፎቹ የሰው ልጆችም በሞት ተይዘው ነበር ። በክርስቶስ ስናምን ከአሮጌው አዳም ግንድ ተነጥለን በአዲሱ ግንድ በክርስቶስ ላይ እንተከላለን ። ሕይወቱንም እንካፈላለን ። አዳም ልጆችን ለሞት ወለደ ፣ ክርስቶስ ግን በዳግም ልደት ምእመናንን ለሕይወት ወለደ ። የበደለው ቃየን ቢሆን ኖሮ እኛ እንተርፍ ነበር ። የበደለው ግን ግንድ የሆነው አዳም ነውና መትረፍ አልቻልንም ። ከምንጩ የደፈረሰ አይጠራምና ሁላችንም በዚህ ዕዳ ተያዝን ። ክርስቶስም ማሻሻያ በማድረግ ፣ አሮጌውን ግንድ በማከም ሳይሆን ሌላ ግንድ በመሆን መጣ ፣ በዚህም ፍጹም ድኅነትን አገኘን ። በአዳም ውስጥ የጽድቅ ምኞት እንጂ ፍሬው አልነበረንም ፣ በክርስቶስ ግን ለሰማይ የምንኖርበትን አቅም አገኘን ። 

ገበሬው ወይኑን ሁልጊዜ ይገዝረዋል ። ከገበሬው እጅም ስለት አይጠፋም ። እውነተኛው የወይን ግንድ ክርስቶስ ሲሆን ገበሬው እግዚአብሔር አብ ነው ተብሏል (ዮሐ. 15፡1)። እግዚአብሔር አብም ልጁን ለሞት አሳልፎ ሰጥቷል ። ልጁ ካልሞተ ዓለም አይድንምና ። ስለትና ወይን አይለያዩም ፣ ክርስቶስና መስቀልም ለአንድ ቀን ተለያይተው አልታዩም ። ወደ ምድር መውረድ ፣ ከድሀ መወለድ ፣ በበረት መገኘት ፣ በግብጽ መሰደድ ፣ በሰው ሁሉ መጠላት ፣ ቤት አልባ መሆን ፣ የድህነት ኑሮ ፣ በባሪያ እጅ መጠመቅ፣ በሐሰት መከሰስ ፣ በመስቀል ላይ መዋል ፣ በተውሶ መቃብር መቀበር ፣ የሐዋርያት ስደት…. ይህ ሁሉ የመስቀል አካል ነው ። ወይን ስለት ካላገኘው አያፈራም ፣ ክርስቶስም መከራ ባይቀበል ኖሮ እኛን ማትረፍ አይችልም ነበር ። የመስቀሉ ትርፎች እኛ ነን !

አዳም እውነተኛነትን አጣ ። በዚህ ምክንያት በምድር ላይ የውሸት ኑሮ ተጀመረ ። አዳም የምድር ገዥና ትልቁ ንጉሥ ነው ። ውሸት በእርሱ ስለ ተገኘ ከዚያ ጊዜ ጀምሮ የምድር መሪዎች የውሸት አውራ ሠራተኛ ሆኑ ። እውነት የላችሁም ያላቸውንም ባላቸው አቅም የሚያጠፉ ሆነው ተገኙ ። እውነት በነገሥታት ጥቃት ውስጥ ያለማቋረጥ ታልፋለች ። በዛሬው ዓለም ፖለቲካ ተብሎ ሲጠራ ትርጉሙን ውሸት ብሎ ሰው ሁሉ እስኪያስብ ድረስ የአስተዳደር ክብር ወድቋል ። በምድር ላይ ከቤተ መንግሥት እስከ ድሀዋ ጎጆ እውነተኛ ኑሮ እየጠፋ ነው ፣ ብቁ መሪዎች ተደርገው የሚታሰቡም ሕዝብን ማታለል የቻሉት ናቸው ። በወርቅ በአልማዝ ተንቆጥቁጦ የሚወጣው ቆንጆ ውስጡ የተበላሸ ነው ። የራሱ መጨነቅ ሳይደንቀው መጨነቁን ሰው እንዳያውቅበት በብልጭልጭ ይሸፍነዋል ። ብዙ ሕዝብ የሚከተላቸው ዘፋኝና ተዋንያን ሰውን ሲያስደስቱ ራሳቸው ግን ኀዘነተኛ ናቸው ። የውሸት ሳቅ እንዳደከማቸው ይታወቃል ። ባደጉ ከተሞች የቀነጨሩ ሰዎች አሉ ። ባማረ ቤት የሚኖሩ ብዙዎቹ የፈራረሱ ናቸው ። ሕንፃውን አቁሞ ትዳሩ የተበተነበት ፣ ልጆቹ የወደቁበት አያሌ ነው ። ሰዎች በተቃራኒው መኖር ከጀመሩ ቆይተዋል ፣ እንደሚወዱን ሲናገሩ እየጠሉን ሊሆን ይችላል ፣ የጠሉን ሲመስለን ደግሞ በጣም እየወደዱን ነው ። ሰው አድራሻ የለሽ ፣ በቃሉ የማይያዝ ከሆነ ሰንብቷል ። ይህ ሁሉ ከሐሰተኛው ግንድ የተወረሰ ጠባይ ነው ። የሚያሳዝነው የውሸት ኖረን የእውነት መሞታችን ነው ። 

ወይን ከሌሎቹ ተክሎች ልዩ የሚያደርገው ሕይወቱ ያለው ግንዱ ላይ ነው ። ቅጠሉ በጣም ቢያምርም በቅጠሉ ላይ ሕይወት የለም ፤ ፍሬው በጣም ቢያምርና ቢጣፍጥም ሕይወት በእርሱ ላይ ስለሌለ ወስደን ብንተክለው አይበቅልም ። የወይን ግንድ የቅርንጫፉና የፍሬው የሕይወት መገኛ ነው ። ከግንዱ የተለየ ወይን ይከስማል ። ክርስቶስ እውነተኛው የወይን ግንድ ነው ። ምእመናን ቅርንጫፍ ናቸው ። ከእርሱ ተለይተው መኖር አይችሉም ። በራሳቸው ጉልበት ክርስትናን መፈጸም አይችሉም ። አንዳንድ ተክሎች በፍሬአቸው ይበቅላሉ ፣ ሌሎችም በቅርንጫፋቸው ሊበቅሉ ይችላሉ ። ወይን ግን ግንዱ ላይ ሕይወት ስላለ ያለ ግንዱ አይበቅልም ። ያለ ግንዱ ያለ ክርስቶስ ማመንም ፣ ማፍራትም አንችልም ። በፍሬው ግንዱ ይታወቃል ፣ በአማንያን ኑሮም ክርስቶስ ይሰበካል ። 

ከቤተሰቡ በሚመጣው ነገር የሚሰጋ ሰው ብዙ ነው ። ባለሙያዎች ጋ ስንሄድ በቤተሰባችሁ እንዲህ ዓይነት በሽታ ነበረ ወይ  ብለው ይጠይቃሉ ። ቤተሰባቸው በሥልጣን ያሳለፈ ከሆነ ብዙዎች አገር ለቀው ይሰደዳሉ ። አገር የገዙ ሰዎች ለልጆቻቸው አገር እንኳ ማውረስ አይችሉም ። በቤተሰባቸው ባዕድ አምልኮ ያዩ የነበሩ ሰዎች በሚገጥማቸው አለመሳካት ሁሉ ያንን ያስባሉ ። ምናልባት ቤተሰባቸው የሚከተለው ሃይማኖት ከዚያ አላስጣላቸውም ብለው ስለሚያስቡም ለመሸሽ ብለው ሃይማኖት ይቀይራሉ ። ስጋቱ ከፍተኛ ነው ። በክርስቶስ ስናምን ግን እንኳን ከቤተሰብ ከአዳም ግንድነት ተነቅለን በሐዲሱ ግንድ በክርስቶስ ላይ እንተከላለን ። ስለዚህ በዘርማንዘር የሚመጣው ዕዳ ሊያገኘን ፣ ክፉም ሊይዘን አይችልም ። ጦርነቱ አብቅቷል ፣ ጠላትም ተሸንፏል ፣ ነገር ግን አሁን በጦርነት ውስጥ እንዳሉ የሚያስቡ ሰዎች አሉ ። በክርስቶስ ያመነ የቤተሰብ ጣጣ ሊይዘው አይችልም ። ከዚህ በኋላ ለማፍራት ዕድልና አቅም አለውና በጽድቅ መኖር ይገባዋል ። 

እውነተኛው የወይን ግንድ አንተ አንተ ክርስቶስ ነህ ። ከእገሌ ተወለድሁ ፣ ዘራችን ከእነ እስክንድር ይመዘዛል ፣ ከነ ቄሣር ይገናኛል ማለት ሐሰት ነው ። እነዚህ ሁሉ የሞትን ሥልጣን ማሸነፍ አቅቷቸው ወድቀዋል ። ታላቅ ቢባሉም ሎቶሪ ወጥቶላቸው ነው ። ታላቅነታቸውን ሲነጠቁም ፍርድ ቤት ቆመው አልተከራከሩም ። የእነርሱ አይደለምና ፀሐዩ ሲጠልቅ አንሰው ወደ ዋሻ ገቡ ። በባሕርይህ ባለሥልጣን ፣ ጌትነት ገንዘብህ የሆነ አንተ ብቻ ኢየሱስ ክርስቶስ ነህ ። የእገሌ ዘር ነኝ ማለት ለኩራት እንጂ ለጥጋብ አይሆንም ። በአያቱ ድሀ ያልነበረ ባለጠጋ ፣ በአያቱ ባለጠጋ ያልነበረ ድሀ የለም ። ሁሉ ሐሰት ነው ፣ አንተ ብቻ እውነት ነህ ። ጌታ ሆይ የውሸት እየኖርን የእውነት መደሰት እንፈልጋለንና እባክህ ከተኛንበት ቀስቅሰን !

ዲ.አ.መ

ጥር 19 ቀን 2017 ዓ.ም.

ኦርቶዶክሳዊ ሕይወት

23 Jan, 13:06


ቅዱስ ቂርቆስ ሰማዕት

“እኔ ክርስቲያን ነኝ”

በኢትዮጵያ ፣ በቢዛንታየን ፣ በካቶሊክና በኦርቶዶክሳውያን አብያተ ክርስቲያናት የታወቁና ክብር የሚሰጣቸው ቅዱሳን ቂርቆስና ኢየሉጣ በዚህ ቀን ይታሰባሉ ፤ እነዚህ የ4ኛው ክፍለ ዘመን ሰማዕታት በጥንታውያን አብያተ ክርስቲያናት ትልቅ አርአያ ተደርገው ይወሰዳሉ ። ሕፃኑ ቂርቆስም ሠለስቱ ደቂቅን/ሦስቱን ወጣቶች የሚያስታውስ ሐዲስ ሰማዕት ነው ። ቅድስት ኢየሉጣ እግዚአብሔርን በመፍራት የኖረች ሴት ናት ። እግዚአብሔርን መፍራትዋ ከሰማይ ክብርን ሲያስገኝላት በምድር ግን ስደትን አምጥቶባታል ። እርስዋም ዋጋን ከምድር ሳትጠብቅ ከሞቀው ኑሮዋ ከሮም ከተማ ተሰደደች ። በስሜ ትሰደዳላችሁ ያለው ጌታ ቃሉ በእርስዋና በቤተሰብዋ ላይ ሲፈጸም በማየትዋ ዕድለኛ ነኝ ብላ ተደሰተች ። የቅዱሳን ደስታቸው መንገዱ አልጋ ባልጋ መሆኑ ሳይሆን ቃሉ በኑሮአቸው ተዳሳሽ ሲሆን በማየት የሚገኝ ነው ። ሰው ገድለው በሚሸሹበት ዓለም ስለ ክርስቶስ ስደተኛ መሆን ትልቅ ሐሤትን የሚሞላባቸው እውነት ነው ። ስለ እኔ ትሰደዳላችሁ ያለው ጌታ ቃሉ እውነት የሚሆነው በክርስቲያንነት ሲሰደዱ ብቻ ነው ። ስደት ከተማችንን አገራችንን ልቀቁ የሚል የክፋት አዋጅ ነው ። ጌታ ክርስቶስ ፣ ቤት ብቻ ሳይሆን አገርንም የሚለቁለት ፣ አገርን ቢከስሩም አሁንም ትልቅ ማትረፊያ የሆነ ንጉሥ ነው ። እርሱ ክርስቶስ ቤትና የቤት ራስ ፣ አገርና ንጉሥ ነው ። በምድር ላይ ተመላልሶ ያስተማረን ምቾትን ሳይሆን ትግልን ነው ። ደግሞም ሰው በበሽታ ተበጣጥሶ በሚሞትበት ዓለም ስለ እርሱ ሰማዕት መሆን ቅዱሳን ሁሉ ሲለምኑት የኖሩት ዕድል ነው ።

ቅድስት ኢየሉጣ በተሰደደችበት አገርም መኖር አልቻለችም ። ክርስቲያንነትዋ ሊደበቅ አልቻለም ። በተራራ ላይ ያለች ከተማ ልትሰወር አይቻላትምና ። ጴጥሮስን ከቃሉ የተነሣ የክርስቶስ ወገን ነህ እንዳሉት ኢየሉጣንም እንዲሁ አወቅዋት ። ወደ አገረ ገዥው አምጥተው ለጣዖት እንድትሰግድ ቢጠይቋት ዓይን እያለው ለማያይ ፣ ጆሮ እያለው ለማይሰማ አልሰግድም ። የዚህን እውነት የሦስት ዓመቱ ልጄ ቂርቆስ ይንገርህ ብላ አመለከተች ። ቅድስት ኢየሉጣ ለመሰደድ የሚበቃ ቆራጥ የክርስትና አቋም ነበራት ። በገዥዎች ፊትም ለመመስከር የምታምነውን ክርስቶስ የምታውቅ ሴት ነበረች ። ደግሞም ልጅዋን ገና በሕፃንነቱ ስለ ክርስቶስ ጌትነት እየነገረች ያሳደገች ናት ። ከዚህች ቅድስት እናት የምንማረው ብዙ ነገር አለ ። ልጆችን ገና በሕፃንነት ስለ ክርስቶስ ፍቅር እያስተማሩ ማሳደግን ነው ። ልጆች ከተማሩ በኋላ ወደ ኋላ ብንል እንኳ መልሰው ያበረቱናል ። ቅዱስ ቂርቆስ እናቱን ቅድስት ኢየሉጣን “አትፍሪ” እያለ ሲያበረታታት ነበር ። ልጆቻችንን ፣ ደቀ መዛሙርትን ማስተማር በደከመን ጊዜ የሚያበረታታ ለማግኘትም ነው ። በዕለተ ሆሳዕና በአፈ ሕፃናት የከበረው ጌታ በቅዱስ ቂርቆስም አንደበት ጌትነቱ ተመሰከረ ። የሰሙት ሁሉ የዕድሜውን ለጋነትና የሚናገረውን እውነት ማጨባበጥ አልቻሉም ። ቅዱስ ቂርቆስ የሚታወቅበት ንግግሩ “እኔ ክርስቲያን ነኝ” የሚለው ነው ።

ክርስቲያንነት በተራራም በሸለቆም ፣ በከፍታም በዝቅታም የሚሸፈን አይደለም ። ባላፈረብን ክርስቶስ ማፈር አይገባም ። እኛ ወደ ኋላ ብንል እግዚአብሔር ሕፃናትን ያስነሣል ። ልጆቻችንን ለክርስቶስ መኖርን ብቻ ሳይሆን መሞትንም ልናስተምራቸው ያስፈልጋል ። ክርስትና ከሰማዕትነት የተለየ አይደለምና ። ቅዱስ ቂርቆስም በመንፈስ ቅዱስ ረዳትነት ወንጌልን ሰበከ ። የሰሙት ሁሉ አመኑ ። ብርሃናዊ ፊቱንና የሕይወት ቃሉን ሰምተው “በእውነት ክርስቶስ ጌታ ነው” ብለው ሰገዱ ። አገረ ገዥውም አንዲትን ሴት አስክዳለሁ ብሎ ሕዝቡን ሁሉ ከሰረ ። የሮማ ባለሥልጣናት ቄሣሮችንና ጣዖታትን የሚያስመለኩ እንቢ ያለውንም የሚሠዉ ነበሩ ። በዚህ ምክንያት ቅዱስ ቂርቆስ በጥር 15 ቀን ሰማዕትነትን ሲቀበል በማግሥቱ ጥር 16 ቀን እናቱ ቅድስት ኢየሉጣም ሰማዕትነትን ተቀብላለች ። ሕፃኑ እናቱን በሰማዕትነት ቀደመ ። ሕፃናት በፍቅረ ኢየሱስ ካደጉ በሰማዕትነት ይቀድሙናል ። ዛሬ ላሉት ሕፃናት የምንጨነቀው ክርስቶስን እንዲያውቁ ነው ወይስ የፈረንጅ ቋንቋ እንዲያውቁ ነው ? ቅዱስ ቂርቆስን ስናስብ የሕፃናት አገልግሎት ከመቼውም ጊዜ ይልቅ ሊበረታታ እንደሚገባው ነው ። በሕፃንነቱ የገባ እስከ ማታ ይቆያል ። ብንወድም ባንወድም ነገ የዛሬዎቹ ሕፃናት ናት ። ቤተ ክርስቲያን ተተኪ ሕፃናትን ማስተማር ለሰማዕትነትም ማዘጋጀት ይገባታል ። ክርስቶስ የምንኖርለት ብቻ ሳይሆን የምንሞትለትም ነው ።

በዓለ ሰማዕታት የሚዘጋጀው በረከት ለማግኘት ብቻ ሳይሆን ምእመናን የሰማዕትነት ልብ ይዘው ዛሬ ገንዘብን ፣ ነገ ሰይፍን እንዲንቁ ለማድረግ ነው ። ዛሬም ሰማዕትነት በደጅ ደርሶ እያንኳኳ ነው ። ብዙዎች ቀድመውናል ። የማይቀረውን ሞት ለክርስቶስ ሰጥተው ባለ አክሊል ሆነዋል ። ቀጣይ ዘመንም ለቤተ ክርስቲያን ሜዳ ሳይሆን አቀበት ነውና ምእመናን ጣዕመ ዓለምን በመናቅ ፣ ለሰማዕትነት ክብር በመዘጋጀት ሊኖሩ ያስፈልጋል ። በቤዛነት የጀመረው ክርስትና በሰማዕትነት ይቀጥላል ። የምንሰደደው አገራችን በምድር ስላልሆነ ነው ። የማንከበረው ሰው ያለ አገሩ ስለማይከብር ነው ። ዘመነ ሰማዕታት ክርስቲያኖችን የሚያፋቅር ነው ፣ የምቾት ዘመን የሚያጣላ ነው ። በተገፋን ቍጥር ወደ ክርስቶስ እንቀርባለን ። በተገፋን ቍጥር ወደ ሰማይ እናድጋለን ። እሳቱ አፈሩን ይበላዋል ፣ ወርቁን ያወጣዋል !

ለሕፃናት ገና ከአራስ ቤት ጀምሮ ፍቅረ ኢየሱስን እየነገርን ካሳደግን የማያሳፍሩን ፣ እኛን የሚያበረታቱን ቆራጥ አማንያን ይሆናሉ ። ሰማዕታት ሁሉ ሰማዕት የሆኑት ስለ ክርስቶስ በመመስከር ነው ። ሰማዕት ማለት ትርጉሙ ምስክር ማለት ነው ። በቃልም በጽናትም የመሰከሩ ሰማዕታት ተብለው ይጠራሉ ። እኛስ ስለ ክርስቶስ ለመመስከር ፣ ብሎም ስለ እርሱ መከራ ለመቀበል ፈቃደኞች ነን ? ስለ ክርስቶስ መከራ የሚቀበሉ ስማቸው በወርቅ ቀለም ተጽፎ ይኖራል ። የዘመን አቧራ ሊሸፍናቸው በፍጹም አይችልም ። ለዚህም ይህ ቀን ምስክር ነው ። ቤተ ክርስቲያን ለክርስቶስ የተደረገውን አትረሳም !

ከሰማዕቱ ከቅዱስ ቂርቆስ ረድኤት በረከት ያሳድርብን !

ዲ.አ.መ
ጥር 15 ቀን 2015 ዓ.ም.

ኦርቶዶክሳዊ ሕይወት

11 Jan, 10:30


"እውነተኛ ክርስቲያን አባቱ ክርስቶስን ይመስላል፡፡ ይሰደዳል እንጂ አያሳድድም፡፡ ይሰደባል እንጂ አይሳደብም፡፡ የጠፉትን ፍለጋ ይደክማል እንጂ ይባስ ብሎ አይገፈትርም፡፡ በወንድሙ ውድቀት ያለቅሳል እንጂ አይደሰትም፡፡ እንዲህ ካልሆነ ግን አባቱ ሌላ ነው፡፡
ለእግዚአብሔር የምናቀርበው ምስጋና በጊዜውም ያለ ጊዜውም ሊሆን ይገባል፡፡ ባገኘን ጊዜ ብቻ ሳይሆን ባጣንም ጊዜ፤ ባለጤና በሆንን ጊዜ ብቻ ሳይሆን በታመምንም ጊዜ፤ ሲሳካልን ብቻ ሳይሆን ባልተሳካልንም ጊዜ ማመስገን መለማመድ አለብን፡፡ የምስጋናችን ምንጭ የሁኔታዎች መለዋወጥ ሳይሆን ስለ አምላካችን ብቻ ሊሆን ይገባዋል፡፡ ይህን ማድረግ ስንለማመድ በክብር ላይ ክብር ይጨመርልናል፤ እንደ አባታችን ኢዮብ የዲያብሎስን አፍ እንዘጋለን፡፡
ተአምራትን ማድረግ ትፈልጋላችሁን?” እንኪያስ "በዘፈን የደነቆረን ጀሮ መዝሙር እንዲሰማ አድርጉት፡፡ ሴትን በመመኘት የታወረው ዐይን ፈጣሪውን እንዲያይ አድርጉት፡፡ በስርቆት የሰለለ እጅ በምጽዋት እንዲዘረጋ አድርጉት፡፡ ወደ ኃጢአት ቤት በመሄድ ሽባ የሆነውን እግር ወደ እግዚአብሔር ቤት እንዲሮጥ አድርጉት፡፡ ሐሜትን በማውራት ዲዳ የሆነውን ከንፈር መልካም ንግግርን እንዲናገር አድርጉት፡፡ ከተአምራት ሁሉ የበለጠ ተአምር ይሄ ነው፡፡"

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

ኦርቶዶክሳዊ ሕይወት

10 Jan, 12:45


+ ሌላ መንገድ +

ሰብአ ሰገል ወደ ሄሮድስ ሔደው ስለተወለደው የአይሁድ ንጉሥ ጠየቁ:: ከዚያም በኮከብ ተመርተው ወደ ክርስቶስ ደረሱ:: ሔደውም ሰገዱለት:: እጅ መንሻም አቀረቡ::

ከዚያ በኋላ ግን "ወደ ሄሮድስም እንዳይመለሱ በሕልም ተረድተው በሌላ መንገድ ወደ አገራቸው ሄዱ" ማቴ. 2:12

ይህ መልእክት የተነገራቸው ስለ ሁለት ነገር ነው:: የመጀመሪያው ሄሮድስ ሕፃኑን ሊገድለው ስለሚፈልግ ለሄሮድስ መረጃ እንዳይሠጡ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ስለተወለደው የአይሁድ ንጉሥ እየመሰከሩ የመጡበትን መንገድ ትተው አየነው እያሉ በሌላ መንገድ እንዲመሰክሩና የሕፃኑ ንጉሥ ዝና እንዲሰፋ ወንጌል እንዲስፋፋ ነበር::

መልአኩ ወደ ሄሮድስ አትመለሱ አለ እንጂ "ሄሮድስ ሊገድለው ነው" አላላቸውም:: ምክንያቱም ይህን ዜና ቢሰሙ ጦር ይዘው የመጡ ነገሥታት ናቸውና "እኛ እያለን እስቲ ይሞክረን" ብለው ውጊያ ሊያነሡ ይችሉ ነበር:: የሰላም አለቃ የተባለው ህፃኑ ክርስቶስም የውጊያ መነሻ ይሆን ነበር:: ክርስቶስ ግን የምትዋጋለት ሳይሆን የሚዋጋልህ አልፎም የሚወጋልህ አምላክ ነው::

በዚህ መሠረት ሰብአ ሰገል
"ወደ ሄሮድስም እንዳይመለሱ በሕልም ተረድተው በሌላ መንገድ ወደ አገራቸው ሄዱ"

ወዳጄ ክርስቶስን ሳታገኝ በፊት ሄሮድስ ጋር ብትሔድ ችግር የለውም:: ክርስቶስን ካገኘህ በኋላ ግን ወደ ሄሮድስ መመለስ ኪሳራ ነው:: እንደ ሰብአ ሰገል ለጌታ እጅ መንሻ አቅርበህ ፣ ዘምረህ ፣ የከንፈር መሥዋዕት አቅርበህ ነፍስህ መድኃኒትዋን አግኝታ ከተደሰተች በኋላ ሕይወት እንዴት ይቀጥላል?

ወደ ሄሮድስ ልትመለስ ይሆን? እንዳታደርገው! ሄሮድስ ጋር ያለው ኃጢአት ነው:: ሄሮድስ ጋር ያለው ክፋት ነው:: እመነኝ እንደ ሰብአ ሰገል ጌታህን ካገኘህ ወዲህ ወደ ሄሮድስ አትመለስ!

ወዴት ልሒድ ካልከኝ መልሱ እዚያው ላይ አለ :-

"በሌላ መንገድ ወደ ሀገራቸው ሔዱ"

እስቲ ሌላ መንገድ ሞክር! ትናንት ያልኖርክበትን ዓይነት ኑሮ ፣ ትናንት ያልሞከርከው የንስሐ መንገድ እስቲ ዛሬ ሒድበት! ሌላ መንገድ አልነግርህም "መንገድም ሕይወትም እውነትም እኔ ነኝ" ያለህ መድኃኔዓለም ክርስቶስ እርሱ ነው:: በእኔ ኑሩ እንዳለ በእርሱ ኑር:: አደራ ወደ ሄሮድስ እንዳትመለስ!

ዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ
ጥር 2 2017

ኦርቶዶክሳዊ ሕይወት

06 Jan, 19:18


አንኳን ለ2017 ዓ ም ለጌታችን፣ ለአምላካችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረስዎ!

“ስብሐት ለእግዚአብሔር በሰማያት ወሰላም በምድር ሥምረቱለሰብእ፤ በሰማያት ምስጋና ተደረገ በምድርም እርቅ ተወጠነ ‹‹ሰላም ሆነ፡፡›› (ሉቃ. ፪፥፲፬)

በዚህ ዓለም ላይ የሰው ልጆች ነጻነትን ፣ ምድርም ሰላምን ይፈልጋሉ ፤ የምድር ገዥዎች አነዚህን ጸጋዎች እናመጣለ አያሉ ተስፋ የሚሰጡ ቢሆንም በተግባር ማረጋገጥ ስላልቻሱ የሰው ልጆች በሕሊና እስር፣ ምድርም በሁከት አያለፉ ነው ።

አኛ ግን አውነተኛውን ነጻነት አርሱም ለአግዚአብሔር ክብር መኖርን ፤ አውነተኛውን ሰላም ከራስ ጋር መስማማትን አናገኝ ዘንድ በዳዊት ከተማ መድኅን ክርስቶስ ተወልዶልናል።

መልካም በዓለ ልደት ይሆንልዎ ዘጓድ ምኞታችንን ስገልጽ በአክብሮት ነው!

በክርስቶስ ፍቅር!

ኦርቶዶክሳዊ ሕይወት

21 Dec, 07:48


"ክብርና ሥልጣን፥ ሀብትና ንብረት፥ በዚህ ዓለም ላይ የምናገኛቸው ብልጽግናዎች ኹሉ ጸንተው የሚኖሩ አይደሉም። ኹሉም ከወራጅ ውኃ በፈጠነ ፍጥነት የሚያልፉ ናቸው እንጂ ከእነዚህ አንዱስ እንኳን ዘላለማዊ የለም። የሙጥኝ ብሎ ሊልዛቸው የሚሞክር ሰው እንኳን በፍጹም ሊያቆያቸው አይችልም፤ የሚቀረው ባዶውን ነው። መንፈሳዊ ነገሮች ግን እንደዚህ አይደሉም፤ የዚህ ተቃራኒ ናቸው እንጂ፦ እንደ ጽኑ ዐለት የማይንቀሳቀሱ ናቸው፤ ሕልፈት ውላጤ የለባቸውም። ታዲያ ጸንቶ የሚኖረውን እጠፋ እጠፋ በሚለው፥ የማይነቃነቀውን በሚንገዳገደው፥ ዘላለማዊውን በጊዜያዊው ፥ የማያልፈውን በሚያልፈው ፥ ዘላለማዊ ደስታ የሚሰጠውን ዘላለማዊ ስቃይ በሚሰጠው መቀየራችን እንደ ምን ያለ ሞኝነት ነው?"

ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ

ኦርቶዶክሳዊ ሕይወት

20 Dec, 10:10


"የማርን ጥፍጥና ማርን ቀምሶ ለማያውቅ ሰው በመቅመስ እንጂ በቃላት ማስተማር እንደማይቻል ሁሉ የእግዚአብሔርን መልካምነት በቃላት በጠራ መልኩ ማስተማር አይቻልም። ራሣችን ወደ እግዚአብሔር መልካምነት ዘልቀን መግባት ይኖርብናል እንጂ።"

ቅዱስ ባስልዮስ

ኦርቶዶክሳዊ ሕይወት

05 Dec, 16:25


አንዳንዴ በዙሪያዬ የማየው ነገር ልቤን ሲያናውጠው፥ ከመጽሐፍ ቅዱሴ በተጨማሪ መልሼ መላልሼ የማነባቸው መጻሕፍት አሉ። ከጥንቶቹም ከአሁኖቹም፤
ከጥንቶቹ መካከል፥ የቅዱስ አትናቴዎስ በእንተ ሥጋዌ፥ የቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ አምስቱ የነገረ መለኮት ድርሳናት፥ አረጋዊ መንፈሳዊና ማር ይስሐቅ ናቸው። ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ የሕይወቴም የአገልግሎቴ መሪም ነው ሁሉም መጻሕፍቱ አነጋጋሪዎቼ ናቸው።

ከእነዚህ ጋር አብሬ የምደምረው፥ የቅዱስ አውግስጢኖስ ኑዛዜ ( The Confessions of St. Augustine) ነው። መጽሐፉ በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ብቻ ሳይሆን፥ በዓለም ሥነ ጽሑፍ ውስጥ ታላቅ ሥፍራ የሚሰጠው ነው፤ ሁል ጊዜ ራሴን እንድመለከትበትና የእግዚአብሔርን ታላቅነት የእኔን ታናሽነት እንዳይ ያደርገኛል።

በነገረ መለኮት ብቻ ሳይሆን፥ በሥነ ጽሑፍ ዓለም ታዋቂ የሆነው የመጀመሪያው መክፈቻ ምዕራፉን እንዲህ ወደ አማርኛ መልሼዋለሁ፤ ( ትርጉሙ የመጀመሪያ ረቂቅ ስለሆነ ግድፈት አይጠፋውምና ዓይናማዎቹ መሻሻል ያለበትን በኮሜንት መስጫ ላይ አስቀምጡት። )

ጌታ ሆይ፥ አንተ አምሳያ የሌለህ ነህ፤
በመሆኑም ለአንተ የምናቀርበው ውዳሴ ከሰብእናችን ከፍ ያለ ነው።
ኃይልህ ድንቅ ነው፤ ጥበብህ ወሰን የለውም።
እኛ ዝቅተኛ ፍጥረቶችህ አንተን እናመሰግን ዘንድ ተነሳሳን። የሰው ልጅ ምንድነው? የፍጥረትህ ቅንጣት ንጥረ ነገር አይደለምን? እያንዳንዱ ሰው በውስጡ የሚመጣውን ሞት ምልክት ተሸክሞአል። ሟችነቱ የሰውን ኃጢአተኝነት ይመሰክራል። ትዕቢተኛውን እንደምትገሥጸው ለሁሉም ያውጃል።

ነገር ግን ዝቅተኛ ብንሆንም፥ የፍጥረትህ ቅንጣት ንጥረ ነገር ብንሆንም፥ የሰው ልጆች አንተን ለማመስገን እንሻለን። አንተን በማመስገን የሚገኘውን ሐሴት በውስጣችን ትቀሰቅሳለህ። አንተ ለራስህ ሠራኸን፤ በአንተ ዘንድ የዕረፍት ሥፍራውን እስከሚያገኝ ድረስ ልባችን ዕረፍት የለሽ ነው።

ጌታ ሆይ! ከእነዚህ ሁለት ነገሮች የትኛው መጀመሪያ እንደሚመጣ እናውቅ ዘንድ ስጠን። አንተን ከማመስገናችን በፊት አንተን መጥራት አለብን? ወይስ አንተን ከማወቃችን በፊት አንተን መጥራት አለብን? አንተን መጀመሪያ ሳያውቅ፥ አንተን መጥራት የሚችል ማነው? አንተን የማያውቅ፥ አንተ ማን እንደ ሆንኽ የተሳሳተ አሳብ ይዞ ሊመጣ ይችላልና።

ከዚያ ይልቅ፥ አንተን እናውቅህ ዘንድ አንተን እንጥራን? “ የማያምኑትን እንዴት ይጠራሉ? ሳይሰሙስ እንዴት ያምናሉ? ያለሰባኪስ እንዴት ይሰማሉ?”

ስለዚህ እርሱን የሚሹ እንደሚያመሰግኑት፥ እርሱን የሚፈልጉት እንደሚያገኙትና እርሱን የሚያገኙት እንደሚያመሰግኑት እናውቃለን። ጌታ ሆይ፥ አንተን በመጥራት አንተን እሻለሁ፤ አንተን በእውነት እንዳውቅህ በመታመን እጠራሃለሁ፤አንተ ተሰብከሃልና። እምነቴ፥ ጌታ ሆይ፥ አንተን ይጠራሃል፤ አንተ በመጀመሪያ የሰጠኸኝ እምነት። በዚያ እምነት በልጅህ ሰው መሆን በሰባኪው አገልግሎት ሕይወትን እፍ ብለህብኛል።

ጌታ ካልሆነ ጌታ ማንነው?
የእኛ አምላክ ካልሆነ በቀር አምላክ ማነው?
ከፍ ያለው
መልካሙኃያሉሁሉን ቻዩ
መሐሪ ደግሞ ጻድቅ
ሥውር ነገር ግን ለሁሉ የቀረበ
እጅግ ውብ ደግሞ ብርቱ
ቋሚ ነገር ግን የማያቋርጥ። አንተ አትለወጥም ነገር ግን ሁሉን ትለውጣለህ። አንተ አዲስ አይደለህም፤ ነገር ግን አታረጅም። አንተ ሁሉን አዲስ ታደርጋለህ፤ ነገር ግን ትዕቢተኞችን መቅረቡን ሳያውቁ በሽምግልና ድል ታደርጋቸዋለህ።

አንተ ሁሌ ትሠራለህ፤ ነገር ግን ሁሌ በዕረፍት ነህ። አንተ አሁንም ትሰበስባለህ፤ ነገር ግን አንዳች አልጎደለህም። አንተ ሁሉ ያለህ ስትሆን፥ አሁንም ትደግፋለህ፥ ትሞላለህ፥ ትስፋፋለህ፤ አሁንም ትፈጥራለህ፥ ትመግባለህ፥ ታጎለምሳለህ፤ አሁንም ትፈልጋለህ።

አንተ ሳትናፍቅ ታፈቅራለህ፤ ሳታማርር ትቀናለህ፤ ራስህን ሳትገስጽ ጸጸታችንን ትጋራለህ፤ ባህርይ ሳይነዋወጽ ቁጣህን ትገልጣለህ።

ሌሎች ሁሉ ያቀዱትን መፈጸም ሲያቅታቸው፥ ያንተ ዕቅድ ግን አይለወጥም። ያገኘኸውን ነገር ግን ፈጽሞ ያላጣኸውን ትቀበላለህ። በዕጦት አይደለህም ነገር ግን ባገኘኸው ሐሴት ታደርጋለህ። አትመኝም ነገር ግን ገንዘብ ታደርግ ዘንድ እጅግ ዋጋ ትከፍላለህ። ነገር ግን ያንተ ያልሆነ ነገር ያለው ማነው? ምንም ሳይኖርብህ ዕዳ ትከፍላለህ፤ እዳህን በመክፈልህ ግን አንዳችም አይጎድልብህም።

የእኔ አምላክ፥ የእኔ ሕይወት፥ የእኔ ቅዱስ ደስታ፥ አሁን ያልኩት ምንድነው? ስለ አንተ ሲናገር፥ ሟች የሆነ ሰው ምን ማለት ይችላል? ነገር ግን ወዮ ለማይናገረው፤ ዝምታ አስደናቂ ንግግር ነውና።
ኦ በአንተ አርፍ ዘንድ፥
ኦ አንተ በልቤ እንድትገባ እና ልቤ በደስታ ይሰክር ዘንድ፤ የሚያስጨንቀውን ሁሉ እንድረሳውና ብቸኛው የእኔ መልካም አንተን እንድቀርብህ፤ አንተ ለእኔ ምንድነህ? ርኅራኄህን በእኔ አድርግና እንዴት እንደምገልጠው አስተምረኝ። የእኔን ፍቅርና ትኩረት የፈለግህ፥ ካልሰጠሁህ በታላቅ መከራ ልትቀጣኝ የፈለግህ? እኔ ለአንተ ምንድነኝ? እኔ አንተን ባልወድህ ቀላል መከራ አይደለምና፤ ኦ ጌታዬ አምላኬ አንተ ለእኔ ምን እንደሆንህ፥ ምሕረትህ በእኔ ላይ ይሁንና ንገረኝ፤ ለነፍሴ፥ “እኔ የአንቺ ደኅንነት ነኝ” በላት። ትሰማ ዘንድ፥ አሰምተህ ተናገራት።

እነሆ፥ ጌታ ሆይ፥ ልቤ በአንተ ፊት ተገልጦ ተቀምጦአል። የልቤን ጆሮ ክፈትና ለነፍሴ “ እኔ የአንቺ ደኅንነት ነኝ” በላት። አንተ ከተናገርህ በኋላ፥ አንተን እንድይዝህ ፍቀድልኝ። ፊትህን ከእኔ አትሠውር፤ ሞቼ እንዳልቀር እንድሞት አድርገኝ፤
ፊትህን ብቻ እንዳየው ፍቀድልኝ፡ አሜን

ቀሲስ መላኩ ተረፈ

ኦርቶዶክሳዊ ሕይወት

01 Dec, 07:42


የሰው አሳብ
            
  "በሰው ልብ ብዙ አሳብ አለ፤ የእግዚአብሔር ምክር ግን እርሱ ይጸናል።"
       (ምሳሌ  ፲፱ : ፳፩)

አንዳንድ ጊዜ ልባችን የሚፈነዳ እስኪመስለን በአሳብ እንወጠራለን ፣ ሌላ ጊዜ ቀልባችን እንዳይከዳን እንሰጋለን። ጭልጥ ብለን በአሳብ እንጠፋለን፣ አለህ አለሽ ሲሉን ምንተ ህፍረታችንን አለሁ እንላለን። ከሰዎች ጋር እያወራን ካለንበት ጊዜ የሌለንበት ጊዜ ይበዛል፤ በአካል ተቀምጠን በአሳብ እንጠፋለን ። የሚገርመው  ነገር ያንን ሁሉ መንገድ የነዳነው፣ ያንን ሁሉ ዜብራ የተሻገርነው በፍጹም ከአእምሮአችን ውጭ ሆነን ነው። ስንተኛ የሚጠብቀን ጌታ ስንጓዝም ይጠብቀን ነበር።

ግን ይህ ሁሉ ጭንቀት ለምንድነው? ሕይወትን እኛ እንደ ጀመርናት በራሳችን አቅም የምንለካት ለምንድነው? የእኛ ከመጠን በላይ መንቃት አጠገባችን ያሉት እንዲተኙ ፣ አሳብ የለሽ ሆነው እንዲኖሩ ምክንያት አልሆነም ወይ? ሁሉንም ነገር ማስተካከል እችላለሁ ብለን እንዴት አሰብን? ሁሉንም ሩጫ ያሳካ፣ በሁሉ ሙሉ የሆነ ሰው እናውቃለን ወይ? ቤተሰቦቻችንስ የራሳቸውን ሸክም መሸከም የለባቸውም ወይ? ታናሽ ሆነን እንደ ታላቅ እናስባለን። ወላጆች ልጅ ሲሆኑብን ወላጅ ካልሆንኩ እንላለን። ደግሞስ እግዚአብሔር ሁሉን እያየው ከሆነ ፍትሕ ጠፋ ብለን መጨነቃችን ምን ይጠቅማል? ለቀኑ ብልሃት እንዳለው ረስተን ፣ ሲያመጣው ከመቻያው ጋር መሆኑን  ዘንግተን መዋተታችን ለምን አይበቃም? ችግርን መቀነስ እንጂ ማጥፋት እንደማንችል ለምን ረሳን? የድርሻችንን መወጣት እንጂ መረበሽ ጥቅም እንደሌለው ዛሬም አላመንም። የሆኑ ነገሮችን እንዳልሆኑ መመኘት ምን ይፈይዳል? የአቅማችንን ከጣርን ፈንታው የጌታ መሆኑን ለምን አንቀበልም?

በልባችን ብዙ አሳብ አለ። አንዱን ጨረስኩት ስንል ሌላው ይተካል። ችግር ካለቀማ ምድር ገነት ሆኗል ማለት ነው። የሚጠሉን ሰዎች ይረብሹናል። ከሚሸነግሉን ሰዎች የተሻሉ መሆናቸውን ገና አላወቅንም። ምቀኞች ባይኖሩ ጠንቃቃ አንሆንም ነበር። ጠላቶችን መውደድ ያለብን ዕድሜአችን እንዲረዝም ስለሚያደርጉት ነው። ምንም በሽታ የሌለባቸው ሰዎች ያሉት ዝማሬ ላይ ሳይሆን መጠጥ ላይ ነው።  ሰው ችግር ከሌለበት ችግር ይፈጥራል።

ምኞታችን እጅግ ብዙ ነው። ዓለም ለእነ እገሌ ብታልፍም እኛ ጋ ላታልፋ የመጣች ይመስለናል። አንድን ነገር እስክንጨብጠው ያለን ጥረት ብዙ ነው። ከጨበጥነው በኋላ ትርጉም እናጣለን። ሁሉም ነገራችን የችኩላ ነው፣ ለማግባትም ለመፍታትም ፈጣን ነን። በአንድ ጊዜ ሁለት ትምህርት፣ ሁለት ሥራ ፣ ሁለት ሃይማኖት ማራመድ እንፈልጋለን። ሁሉም ነገር ሰልችቶን ደግሞ አስቀምጠነው እንሄዳለን። ዕቅድ በዕቅድ እንሆናለን። ከማማከር በራስ መወሰንን እንደ ጀግንነት እንቆጥረዋለን። እንደሚኖር ብንሠራም እንደሚሞት መዘጋጀት አለብን። የሞቱትን ስናስብ ከሞታቸው ዕቅዳቸው ያስለቅሳል።

አዎ እኛ እውነትም ውሸትም ነን። እውነቱ  አለሁ እያልን ነው፣ ውሸቱ ደግሞ ላንኖር እንችላለን። ለቀጠሮ የማንበቃ፣ እገሌ ይሞታል ብለን እያስታመምን እኛ ልንቀድም የምንችል ፣ እርግጠኛ ባልሆነ ሕይወት ውስጥ ያለን ነን። እርግጡ እግዚአብሔርና የዘላለም ሕይወት ብቻ ነው፡፡ "እርሱ እኮ ልጅ ነው" ስለሚሉን ልጅ አይደለንም። ልጅ አይሞትም ያለው ማን ነው? የማንንም ውድቀት መመኘት አያስፈልገንም ፣ ማንንም ለመበቀል መኖር አያሻንም። ለዕለት የሚበቃ ካለን ማመስገን አለብን። ስለ ታመምን አንሞትም ፤ ጤነኛ ስለሆንን ምንም አይነካንም ማለት አይደለም። ሕፃን ልጅ ወላጆቹ ወደሚያውቁት መንገድ ስለሚጓዝ አይሰጋም። ላመሉ የት ነው? ብሎ ይጠይቃል  ፣ ቢነግሩትም አይገባውም ፤ በወላጆቹ እውቀት ያርፋል። እኛም እንደ አማኙ ሕፃን አንተ ታውቃለህ ብለን ማረፍ አለብን።

አታስቡ አልተባልንም ፣ አትጨነቁ ተብለናል። ኩንታል አሳባችን በሙሉ ግን አይፈጸምም። በአሳባችን ላይ እርሱ ሲያስብበት ብቻ ይሆናል። ትራፊኩ እጁን ወደ ላይ አንሥቶ ቁሙ ሲል መኪናውም ሾፌሩም ይቆማሉ ። የእግዚአብሔር ሥልጣንም የሰዎችን አሳብ፣ ሥልጣንና ኃይል ያስቆማል። ለምንድነው ያስቆምከኝ ብለን ትራፊኩን አንጠይቅም። ለእኛ ደኅንነት ያስቆመንን አምላክ ለምን ? አንለውም። ብቻ ብዙ ብናስብም የሚጸናው ምክረ ሥላሴ ነው!

አምላኬ ሆይ፣
አንተ ያልከው ይሁን። ዛሬ እንኳ ሁሉን ላንተ ልተውልህ! ሁሉን መተው ቢያቅተኝ ነገን እንኳ ላንተ ልተውልህ። ረጅም አስቤ ባጭር የምቀር ነኝ። ልቤ ከፍ ከፍ ያለበትን አሳብ ወዲያው ወርዶ አገኘዋለሁ። ማን ያድነዋል? ሲሉኝ ባንተ ድኜአለሁ፣ እውቀትህ አሳልፎኝ በእውቀቴ እደገፋለሁ። የእኔም የሰዎችም አሳብ  ወጥመድ ነው ። ያንተ አሳብ ግን መንገድ ነው። አዎ አንተ ያልከው ይሁን። ሁሉን ላንተ መተውን፣ በእምነት ማደርን አለማምደኝ። ማጉረምረምን፣ ተስፋ ቢስነትን አሸንፍልኝ። ንቀትን እንድታገሥ እርዳኝ። ቢልልኝ እዚህ እደርስ ነበር ማለትን ከእኔ አርቅ። ያልከው ይሁን ። በሰጠኸኝ ነገር አስደስተኝ ።  አሜን!

ዲ.አ.መ
ኅዳር 20 ቀን 2017 ዓ.ም.
           

ኦርቶዶክሳዊ ሕይወት

03 Nov, 07:56


የተቆራረሰ ልብ

ያላቸው በሌላቸው ጨከኑ፣ አግኝተው ካልሰጡ ከቶ መቼ ሊሰጡ ነው ? ደግሞም የማይሰጥ  ድሀ ማነው ? ለድሀ ጥሩ ቃል መናገር እርሱም ምጽዋት ነው። የአፍ ጮማ መቁረጥ በድU  መሳለቅ፣ በእግዚአብሔር ማፌዝ ነው ። የማይቀበል ሁሉ ያለው ባለጠጋ ማነው? ገንዘብ ሰጥቶ ከድሀ  ደስታ ይቀበላል። ድሀ ማለት ምንም የማይሰጥ ማለት አይደለም፤ ባለጠጋ ማለትም ምንም የማይቀበል ማለት አይደለም። ለመስጠት ሀብተ ሥጋ ፣ ሀብተ ነፍስ ያስፈልጋል። ለመስጠት በሕይወት መኖር ያስፈልጋል። የማይሰጡ እጆች ዛሬ በሰይጣን ተገንዘዋል፡ ነገ በፈትል ይገነዛሉ። መስጠትም ዕድል ነው። ከሚቀበል ይልቅ የሚሰጥ የበለጠ ደስተኛ ነው። ወገን የጨከነባቸው ልባቸው ይቆራረሳል። በበረሃ በውኃ ጥማት እንደ ተሰነጣጠቀ መሬት ይሆናሉ። ያዘኑብን ደስታችንን ይዘውብናል። የእኛን ስንሰጣቸው የእነርሱን ሊሰጡን ተዘጋጅተው የሚጠብቁን አሉ።

እኔ ነኝ ማለት የማይችሉ፣ ራሳቸው ፍሬኑ  እንደ ተበጠሰ መኪና አልቆም ያላቸው፣ ጽድቅን እያዩ ኃጢአትን የሚግጡ፣ ሁልጊዜ እየማሉና ራሳቸውን እየገዘቱ በቆሻሻው ስፍራ የሚገኙ ልባቸው የተቆራረሰ ነው። ራስን ማጣት፣ የሚፈልጉትን አለማወቅ፣ በመንፈሳዊ ድንዛዜ መኖር፣ በእግዚአብሔር ቤት ሆኖ ከእግዚአብሔር መለየት፤ በፍቅር ቤት በቂም ፣ በጸሎት ቤት በትዝብት መኖር ያደከመው ልቦቹ የተቆራረሱ ናቸው ።

ሳይናገር ብልሃት የሚፈልግ ሞኝ፣ የልቤን ለምን አላወቁልኝም? ብሎ የሚጣላ ምስኪን ልቦቹ የተቆራረሱ ናቸው ። በግብጽና በከነዓን መካከል የሚኖር የሕይወት ጥጋብ፣ የነፍስ እርካታ የለውም። መርዛማ አሳቦች ይበክሉታል። ማኩረፍ ዘመዱ፣ ዝምታ አገሩ ይሆናል። ሰዎች አስረድተናቸውም ከተረዱን ዕድለኛ ነን። ሰው የሰውን ችግር ለመረዳት ራስ ወዳድነቱ መሰናክል ይሆንበታል። የሚጮኸው ከራሱ አንጻር ነው ። ከተማ ቢፈርስ ግድ የለውም፣ አጥሩ ሲነካ ግን ያመዋል። ሚሊዮን ሲረግፍ ሰምቶ እንዳልሰማ ያልፋል፣ ልጁ ሲያተኩሰው ግን ሆድ ይብሰዋል። መናገር የማይችሉ፣ በውስጣቸው በማጉረምረም የሚሰቃዩ ልባቸው የተቆራረሰ  ነው።

ፍቅርን ሰጥተው ጥላቻን ያተረፉ የመሰላቸው፣ ልቤን ሰጥቼ ቀልባቸውን እንኳ አልሰጡኝም ብለው የሚያስቡ የተቆራረሰ ልብ ይዘዋል። ይህ ስንጥቅጥቅ የመንፈስ ቅዱስ ዘይት ካልሆነ ምንም ሊያረጥበው አይችልም። የተቆራረሱ ልቦች ሰባራ አንገት፣ ስንኩል ጉልበት ይፈጥራሉ።

ጥላቻ ሰባኪ አላት፣ ጥላቻ ሠራዊት አላት፣ ጥላቻ  ደቀ መዝሙር አላት። በጥላቻ የተወጉ  ሰዎች የማይጣሉት ሰው የለም። የበደላቸውንና ያልበደላቸውን መለየት አይችሉም። እንዴት የቆመ ሰው ከሞተ ሰው ጋር ይጣላል? በጥላቻ የተመረዙ የጅምላ ፍረጃ፣ የጅምላ ፍጅት ያውጃሉ። ሰዎች ስለ ተመረዘው ቃላቸው፣ ስለሚገድል ፍላፃቸው ይጠሏቸዋል። በውስጣቸው የሚያሳልፉትን ስቃይ ግን ማንም አይረዳላቸውም። ካልታመመ የሚያሳምም፣ ባልታወከ የሚያውክ ማንም የለም።  ለሰው ሁሉ ቅን አመለካከት የሌላቸው የተቆራረሱ ልቦችን ይዘዋል።  የተቆረሰ ልብ ለሌላው የሚያዝን ነውና ያረካል፣ የተቆራረሰ ልብ ግን በጥማት ምድረ በዳ የሚያልፍ ነው። 

የተቆራረሱ ልቦች በራስ ሥራ ከማፈር የተነሣ ፣ ራስን ይቅር ካለማለት ይከሰታሉ። የተቆራረሰ ልብ ከሰዎች ብዙ ጠብቆ ጥቂት ባለመቀበል ይከሰታል። የጀመርኩት ሁሉ አይሳካም ፣ የተሳካው ዕድሜ የለውም ብሎ የሚያስብ ሰው የተቆራረሰ ልብ ይይዘዋል። ያን ጊዜ በደመና ውኃ ይጠማዋል። ሆዱን ባሕር ባሕር ይለዋል ። ሆደ ባሻነት ያስለቅሰዋል። የቆሙትን ትቶ የሞቱትን እያስታወሰ  ያዝናል። የተቆራረሰ ልብ መኖሪያውን ከመቃብር ሥፍራ ያደርጋል። የእኔ ነገር የሚል ልቅሶ ያስጀምራል። ሰውም እግዚአብሔርም ትተውኛል የሚል ሹክሹክታ ያመጣል።

የተቆራረሰ ልብ የሚድነው በንስሐ ፣ በእምነት ፣ መለኮትን ብቻ ተስፋ በማድረግ ነው ። አዎ ነገሥታት የመኖሪያ ፈቃድ ይስጡ ይሆናል ፣ የመኖር ፈቃድ የሚሰጥ ግን እግዚአብሔር ብቻ ነው። አንተ ወዳጄ ሆይ በእግዚአብሔር እኖራለሁ በል!

"መኖሪያህ የዘላለም አምላክ ነው፥ የዘላለምም ክንዶች ከአንተ በታች ናቸው፤" ዘዳ. 33፥27

ዲ.አ.መ
ጥቅምት 22 ቀን 2017 ዓ.ም.

ኦርቶዶክሳዊ ሕይወት

24 Sep, 03:39


አዳምጣለሁ (2)

ይቅር በለኝ አዳምጣለሁ ። የሰዎችን ፊት ዓይኔ አትኩሮ ያያል ። ጠንቋይ መዳፍን ሲያነብ ፣ እኔ ፊት እያነበብሁ ራሴን አሰቃያለሁ ። ዛሬ ፊታቸው ጠቆረ ፣ ምን አስበው ነው? እላለሁ ። የምታኖረኝን ትቼ የማያኖሩኝን እፈራለሁ ። መኖሬ በሰው ፍቅር ላይ የተመሠረተ ይመስለኛል ። ዓለሙ ሁሉ ቢያድም አንተ ካልፈቀድህ ማንስ ይነካኛል ? ጌታ ሆይ የሰዎችን የድምፃቸውን መጠን በጆሮዬ እለካለሁ ። ሰላምታቸው ቀዘቀዘ ደግሞ ምን ሊሉኝ ነው ? እላለሁ ። ስሜቴ ከፍና ዝቅ ይላል ። ቋሚ ባልሆኑ ሰዎች ላይ ደስታዬን መሥርቼ ስወጣና ስወርድ እውላለሁ ። አዎ አዳምጣለሁ ይቅር በለኝ ። አንተ በእውነት ስትወደኝ ምንም አይመስለኝም ፣ ሰዎች በሽንገላ ሲያፈቅሩኝ ልቤ ይዘላል ። ቀድሞም ያልወደዱኝ ሲጠሉኝ ግራ ይገባኛል ። የሰው ፍቅር ከሞት አያድንም ፣ “ወዶኛልና አዳነኝ” የተባለልህን አንተን ፣ የነፍስ አብነቴን ችላ ብያለሁና ይቅር በለኝ ። የእግር ኮቴዎች ምን ይዘው መጡ ? የሚል ጥርጣሬ ፣ የስልክ ጥሪዎች ምን ሊሉኝ ነው ? የሚል ስጋት ይጥልብኛል ። ትላንት ሰላም ያሉኝ እንዲህ ብለው ነው ፣ ዛሬ ደግሞ ይህን ቃል ቀነሱ እያልሁ አዳምጣለሁና ይቅር በለኝ ። በብሉይ በሐዲስ ፣ በእውነት ምስክሮች የጸናውን ፣ አንተ ለእኔ ያለህን በጎ አሳብ አቃልያለሁና ይቅር በለኝ ።

አዳምጣለሁ ይቅር በለኝ ። ስሜን ሲያቆላምጡ ደስ ይለኛል ፣ ውለታ መስሎኝ ካልከፈልሁ ያሰኘኛል ። ለስም አጠራሬ የምከፍል ብቸኛ ሰው የሆንሁ ይመስለኛል ። በሙሉ ስሜ ሲጠሩኝ ደግሞ ደስታዬ እንደ ካባ ወደ ኋላ ይወድቃል ። ሰዎች ሥራቸውን ስለ ሠሩ ከማመስገን በላይ ለእኔ ልዩ ውለታ ያደረጉልኝ መስሎ ያሳቅቀኛል ። ቁመናዬ በነፋስ ሽውታ ይነቃነቃል ፣ ቆዳዬ ትንሽ ሲነካ የሚቆስል ስስ ሆኗል ። እንኳን ችግር መጥቶ ፣ ሊመጣ ነው እያለ ይርዳል ። አዳምጣለሁና ይቅር በለኝ ። አንተን ሳይሆን ወደዚህ ዓለም ያላመጡኝን ፣ ከዚህ ዓለም የማይወስዱኝን ፤ እንደ እኔ ፈሪ የሆኑትን አዳምጣለሁና ይቅር በለኝ ። ሰዎች ቃላቸውን ሲያጥፉ ፣ የትላንት ንግግራቸው ከዛሬው ሲዘባረቅ አዳምጣለሁ ፣ ለምን ? ብዬ በቀጭን መርፌ ነፍሴን እወጋጋታለሁ ። አዎ አዳምጣለሁ ሰዎች ለሌላው ሰው መርዛም ዱለታ ሲዶልቱ ፣ እኔን ባይነኩኝም አዳምጣለሁ ። ሲያሙ ቆይተው ፣ ያሙት ሲመጣ አቅፈው ሲስሙት እታመማለሁ ። ወላጅ ቀብረው በሠልስቱ ስለ ውርስ ሲያወሩ አዳምጣለሁ ፣ ስለዚህ እደቅቃለሁ ።

በአካሌ ላይ የሚከናወነውን እያንዳንዱን ነገር አዳምጣለሁና ይቅር በለኝ ። ገና ሞት እያለ መታመምን እፈራለሁ ። በመገናኛ ብዙኃኑ ስለ በሽታ ሲወራ እኔ እንደ ታመመ ሰው እንቅስቃሴ ማድረግ እጀምራለሁ ። አዎ አዳምጣለሁና ይቅር በለኝ ። ትንሣኤና ሕይወት መሆንህን አምናለሁ እያልሁ በሽታን እሰጋለሁ ። ጠቢብ አልቻለም ሲባል በጆሮዬ የምሰማው እግዚአብሔር አልቻለም ብዬ ነው ። አዳምጣለሁና ይቅር በለኝ ። እያንዳንዱን ቃል አጠራለሁ ፣ እንዲህ ያለው እንዲህ ለማለት ፈልጎ ነው እያልሁ አሰላስላለሁ ። እኔ እንደ ልቤ እየተናገርሁ ሰዎች ግን ችሎት ላይ ቆሞ እንደሚናገር ሰው በሰቀቀን እንዲያወሩኝ አደርጋለሁ ። አዳምጣለሁና ይቅር በለኝ ። አሰቡትም አደረጉትም ፣ ተናገሩትም ዝም አሉትም ያው ነው ብዬ አረፋ መትቼ ፣ በሺህ አባዝቼ አዳምጣለሁና ይቅር በለኝ ። በሁለት ጆሮ እየሰሙ ከሰው ጋር መኖር እንደማይቻል ባውቅም ፣ በትዕግሥት ማጣት የካብኩትን ብንድም አሁንም አዳምጣለሁና ይቅር በለኝ ። ምን ይሉኛልን ፈርቼ ሥራዬን ፣ ሐሜትን ተሳቅቄ ራእዬን ትቻለሁና ይቅር በለኝ !

ልጆቼ ስለ እኔ ያላቸውን የፍቅር ሙቀት አዳምጣለሁ ። “ብሞትስ ምን ትላላችሁ” ብዬ የቅኝት ፍተሻ አደርጋለሁ ፣ ገና ሳልሞት አላለቀሱም ብዬ ተስፋ እቆርጣለሁ ። ማዳመጥ አስክሮኝ ብሶትን እወልዳለሁ ። ከሰው ጋር በጨዋታ በሳቅ ውዬ ፣ ወደ ቤቴ ስመለስ የተናገርኩትን ሌሊት ሙሉ ከልሼ አዳምጣለሁ ። አስቀይሜ ቢሆንስ ብዬ እሰጋለሁ ፣ ደስታዬን ሳበላሽ አድራለሁ ። አዳምጣለሁና ይቅር በለኝ ። ስልክ ደውዬ በመጀመሪያው ጥሪ ካልተነሣ አዳምጣለሁ ። የመጀመሪያው ጥሪ በእኔ ትርጉም ፍቅር ነው እላለሁ ፣ ሦስተኛው ጥሪ ላይ ካልተነሣ ስላልፈለጉ ነው እላለሁ ። ደስታዬን ጨቁኜ ለራሴ አለቅሳለሁ ። ባልተጨበጠ ነገር የተጨበጠ ኀዘን ውስጥ እገባለሁ ። ሰዎቹን ሳገኛቸው ያን ጊዜ ስልክ ያላነሣሁት ታስሬ ፣ ታምሜ ነበር ሲሉኝ በራሴ አፍራለሁ ። አዳምጣለሁና ይቅር በለኝ ። ስብከት ስሰማ አዳምጣለሁ ፣ ሰባኪውን ካወቅሁት የእኔን ምሥጢር እያወጣ ነው ብዬ ቃልህን ለመስማት እንኳ እፈተናለሁ ። እኔን ሊናገር ፈልጎ ነው እያልኩ አደባባይህን ፣ የንስሐ ድምፅን እጋፋለሁ ። አዳምጣለሁና እባክህ ይቅር በለኝ ።

ሰዎች የትዳር ውድቀታቸውን ሲናገሩ የእኔም ጉድ ባልሰማው ነው እንጂ ይህን ይመስላል እያልሁ ቤቴን አውካለሁ ። ኑሮዬን አፈርሳለሁ ። ለእልህ ስላደረግሁት አልቆጭም ። ጉልበቴ በማይረባ ነገር ያልቃል ። ቃልህ ተተርጉሞ እንኳ አይገባኝም ፣ የሰዎችን ነጠላ ቃል ግን ተርጕሜ እጣላለሁ ። ትላንት የሰማሁት ቃልህን ረስቼዋለሁ ፣ የሃያ ዓመት ቂም ግን በውስጤ ሕያው ነው ። አዳምጣለሁና ይቅር በለኝ ። ደግ ቃል ቶሎ አይገባኝም ። ትምህርትም ጎበዝ አይደለሁም ። ክፉ ቃል ግን ያለ አስተማሪ ይገባኛል ፣ ፈነካክቼ - አብጠርጥሬ እጋተዋለሁ ። አቤቱ ያን ጊዜ መተንተን ይሆናል ፣ የማይጠቅም መተንተን ነው ፤ ያን ጊዜ ሁሉም ነገር ብልጭ ይልልኛል ፣ የማይጠቅም ብርሃን ነው ። ያን ጊዜ ልቅሶ ይሆናል ፣ የማይጠቅም ልቅሶ ነው ። ማዘንስ ሰዎች ስለበደሉኝ ሳይሆን ሊያስቀይሙህ የማይገባውን አንተን በማሳዘኔ ነው ። አዳምጣለሁና ይቅር በለኝ።

ተፈጸመ

ዲ.አ.መ
የካቲት 28 ቀን 2016 ዓ.ም.

ኦርቶዶክሳዊ ሕይወት

22 Sep, 09:52


አዳምጣለሁ !!!

ይቅር በለኝ አዳምጣለሁ ። ያንተን ቃል አይደለም ፣ አሉታዊ ድምፅን ፣ ከውስጤ የሚያስተጋባውን የአለቀልህን ነጋሪት አዳምጣለሁና ይቅር በለኝ ። ነፋሱ መንቀሳቀስ ፣ ፀሐዩ መፈንጠቅ ፣ ጨረቃ መድመቅ ፣ ከዋክብት መፍካት አቁመዋል የሚለውን የውሸት ድምፅ እውነት ብዬ ስቀበል ያንተን ቃለ ጽድቅ ግን እጠራጠራለሁ ። የማትጠልቅ ፀሐይ ፣ የማትጠፋ መቅረዝ ፣ የሕይወቴ ሕይወት አንተ መሆንህን ቃልህ ሲነግረኝ አላዳምጥም ። አዳምጣለሁ ይቅር በለኝ ፤ ዘመንህ ገሰገሰ ፣ ዕድሜህ ያለ ብልሃት አለቀ ፣ ወራትህ ከሸማኔ መወርወሪያ ይልቅ ፈጠነ የሆንኸውና ያደረግኸው ነገር የለም የሚለኝን የጠላት ድምፅ ሕሊናዬን የተከራየውን የባላጋራውን የቃል ፍላጻ አዳምጣለሁና ይቅር በለኝ ። መሆን ይቀድማል ፣ ተግባር ይከተላል ፤ ካልሆነ ማንነት ተግባር ቢወጣ አይፈውስም ። ከማይራራ ልብ ስጦታ ይወጣል ፣ ወይ ጉቦ ወይ ዝና ፍለጋ ይሆናል ። መሆንን ሰጥቶ ማድረግን የሚያስቀድም እግዚአብሔር ነው ። በገባዖን ሰማይ የቀኑን ሠርክ ማለዳ ያደረገ ፣ ባለቀ ቀን ላይ ቀንን የጨመረ ፣ ተፈጥሮ የሚገዛለት ፣ ጨለማ በእርሱ ዘንድ የማይጨልም ፣ ቀን ቢሉት የማይመሽ ዕድል ፣ ብርሃን ቢሉት የማይጨልም እውነት እግዚአብሔር አለልህ የሚለኝን የመንፈስ ቅዱስ ድምፅ አላዳምጥምና እባክህ ይቅር በለኝ ።

አዳምጣለሁ ይቅር በለኝ ስለ ልደቴ ሳላመሰግን ስለ ሞቴ የሚያስፈራራኝን ፣ እንዴት እዚህ ደረስሁ ? ማለትን ትቼ እንዴት እሆናለሁ ? የሚለኝን ፣ ስለ መኖሬ አስረስቶ ስለ ስኬቴ የሚያዋራኝን ፣ ስለ ጠባቂ መልአኬ አስረስቶ ስለ ከዱ ሰዎች የሚያናግረኝን የጠላቴን ድምፅ አዳምጣለሁና ይቅር በለኝ ።

ጠላቴን በሁለት ጆሮ ፣ አንተን በአንድ ጆሮ አዳምጣለሁና ይቅር በለኝ ። በአንዱ ጆሮ ሰምቼህ በሁለተኛው አፈሰዋለሁ ። ቃልህን በምሰማበት ቦታ አልጋዬንና ትራሴን ልዘርጋ ወይ ? ስሰማህ መልአክ ፣ ስወጣ ሰይጣን ሆኛለሁ ። ጌታ ሆይ አዳምጣለሁና ይቅር በለኝ ። ስለ ታሪክ እጣላለሁ ፣ ስለ ነገ ሰንፌአለሁ ። ጥያቄዬ እያሳሰበኝ የሌሎችን እንቆቅልሽ አናንቃለሁ ። ለመተኛት አልጋ ገዝቻለሁ ፣ እንቅልፍ ግን ያንተ ጸጋ ነው ። ስትነሣ ብትወድቅስ ፣ ስትቆርብ ብታፈርስስ ፣ ስትቀደስ ብትረክስስ ? የሚለውን ድምፅ አዳምጣለሁ ። ኃይልን በሚሰጠኝ በክርስቶስ ሁሉን እችላለሁ የሚለውን ያንተን ቃል ግን አላዳምጥምና ይቅር በለኝ ። እዚህ የደረስኩት በዕድሌ ሳይሆን ባንተ የአሳቢነት ስጦታ ነው ። ራሴን በቤትህ ያገኘሁት በእረኝነትህ ፍለጋ ነው ። የሚበዛውን ወራት በራሴ አልኖርኩም ፣ የቀረውን ትንሽ ዕድሜ በአቅሜ ለክቼ እፈራለሁ ። ጌታ ሆይ ! የምኖረው እስከ ዛሬ ማታ ሊሆን ይችላል ። የምጨነቀው ግን ለሺህ ዓመት ቀለብ ነው ።

አላዳምጥምና ይቅር በለኝ ። አንተ የራስህ ፣ አንተ የወላጆችህ ዕቅድ አይደለህም ። አንተ የማኅበረሰቡ ሎሌ ሳይሆን አንተ ለጌታ ፈቃድ የተሠራህ ነህ ። አንተ የሚመስልህ የሌለ ልዩ ነህ ። አንተ ከስኬት በላይ የእግዚአብሔር ልጅ ተብለህ የምትጠራ ነህ ። አንተ ርካሽ ቦታ ብትገኝም የሠራህ እጅ ውድ ነው ። አንተ ሰዎች ቢጥሉህም ብርና ወርቅ ዋጋህ አይደለም ። አንተ በወልደ እግዚአብሔር በኢየሱስ ክርስቶስ ደም የተዋጀህ ነህ ።

ጌታ ሆይ ! ይህን ድምፅህን አላዳምጥምና ይቅር በለኝ ። ጨው ካልሟሟ ጣዕም አይሆንም ። ድንጋይ ነው ተብሎ ይጣላልና ዋጋውን ያጣል ። ክርስቲያንም ላንተ በመሸነፍ ይከብራል ። ለእኔነቱ በመሞት ጣዕመ ዓለም ይሆናል ። እባክህ ላዳምጥህና ጨው ልሁን ። አሜን !

ይቀጥላል

ዲ.አ.መ
የካቲት 27 ቀን 2016 ዓ.ም.

ኦርቶዶክሳዊ ሕይወት

16 Sep, 07:27


ወደ አንተ እንደተዘረጉ ያረጁ እጆች የተቀደሱ ናቸው።

ኦርቶዶክሳዊ ሕይወት

26 Aug, 18:26


<<Kaleessa isan wajjiin fannifame, Hardha isaan wajjiin kabajame. Kaleessa isa wajjiin awwaalame hardha isa wajjiin du'aa ka'e. Kanaafuu isa nuuf jedhee du'e kaa'eef kennaa yaa keenninu. Yeroo kanan isiniin jedhu kennaa warqee yookiin albuudota mimmiidhagoo yookiin meeshota qaqqaalii harka namaatiin hojjataman yookiin kan kennaa garboonni addunyaa kanaa mootota isaaniitii kennan sana isinitti fakkaata ta'a. Garuu isaa kanaa miti. Ofii keessaniifi laphee keessan qalbii keessanis gooftaadhaaf kennaa. Kabaja nuuf keenname yaa hubannu; isa nu uumeefis galata yaa galchinu. Humna iccitii gooftaan keenya nuuf du'eef yaa hubannu.>>

Qulqulluu Gorgoriwoos
(Jaarraa 2ffaa keessa kan barreefame)

ኦርቶዶክሳዊ ሕይወት

07 Aug, 18:12


በእንተ ማርያም

አእምሮ መልማት ሲያቆም ፣ ያማሩ ከተሞች በፈራረሱ ሰዎች ሲሞሉ ፣ ሰው ለሰው ተኩላው ሲሆን ፣ ሺህ መልካምነት አወዳሽ አጥቶ አንድ ስህተት እንደ ሰማይ ስባሪ ሲታይ ፣ ከፍቅር ለቂም ዋጋ ሲሰጥ ፣ ዓመት ሙሉ የለፉበትን በሰከንድ ለማፍረስ ጎበዝ ሁሉ ሲጣደፍ ፣ አባት ሰሚ ፣ መምህር ተማሪ ፣ ንጉሡ መሪ ፣ ወላጅ ውላጅ ሲያጡ እኔ እልሃለሁ በእንተ ማርያም መሐረነ ክርስቶስ ።

አንድነት እንደ ኮሶ ሲመርር ፣ ባንዲራ ሲወድቅ ፣ መማጸኛዋ ቤት መማጸኛ ስትፈልግ ፣ ካህን ከመንበሩ ፣ ዳኛ ከችሎቱ ፣ ሊቅ ከደቂቅ ሲርቅ ፤ መካከለኛ ጠፍቶ ሁሉ ጽንፍ ይዞ ሲተኩስ፣ ለሚነደው እሳት ውኃ ጠፍቶ ሁሉ እንጨት ሲያቀብል ፣ ድልድዮች ፈራርሰው ግንቦች ሲበዙ፤ እኔ ግን እልሃለሁ በእንተ ማርያም መሐረነ ክርስቶስ!

ምእመን ለመካድ ሲከጅል ፣ ወርዶ የሚያወርድ ሲበዛ ፣ ተሳዳቢ ሐቀኛ ሲባል ፣ በደሀ ደረት የሚያለቅስ ሲበዛ ፣ የሰው ሞት ለሰው ሰርጉ ሲሆን ፣ ጅረቱ ሲታገድ ፣ ምንጩ ሲነጥፍ ፣ ደጉ ሲከፋ ፣ ምስኪን ሲደፋ ፣ አስታራቂ ሲጠፋ ፣ እውነት ከዐውደ ምሕረት ሲገፋ ፣ ተመልካች ዓይን ፣ ሰሚ ዶሮ ሲታጣ ፣ የጋራ ልቅሶ አክትሞ ሁሉም በየሰፈሩ ሲያነባ ፣ የሚገዛ የሚገዛም ሲታጣ ፣ ሁሉም ልምራ ብሎ መድረሻው ገደል ሲሆን፤ እኔ ግን እልሃለሁ በእንተ ማርያም መሐረነ ክርስቶስ !

ሀገር የማታስቀምጥ የጋለ ነሐስ ስትሆን ፣ የእናት ቤት ሲዘጋ ፣ የወንድም አለኝታ ሲጠፋ ፣ ጓደኛ ትዳርን ሲቀማ ፣ ሰውን በቁሙ ለመውረስ ፣ በሬን እየሄደ ለመጉረስ ፣ ሠረገላን እየበረረ ለመሳፈር ፣ ይሉኝታ የለሽነት ሲነግሥ ፤ ያጎረሰ እጅ ሲነከስ ፣ አውራው ሲገረሰስ ፣ ምልክት ሲጠፋ ፣ የአባት ድንበር ሲደመሰስ ፤ በረሃው ምድረ በዳ፣ ለምለሙ የተቃጠለ ሲሆን ፣ ከሚጠበቅበት የልኩ ሲታጣ ፣ ዝናብ የሌለው ደመና ሲበዛ ፣ ትልቅ ሥራ ተጠልቶ ትልቅ ወንበር ሲወደድ ፣ ሰው ስሙን ወድዶ ሰም ሆኖ ሲቀልጥ ፤ እኔ ግን እልሃለሁ በእንተ ማርያም መሐረነ ክርስቶስ !

በእንተ አብርሃም የ430 ዘመን ባርነት ተሰብሯል፣ በእንተ ዳዊት ኢየሩሳሌም ከመጣው ጦር ተጋርዳለች ፣ በእንተ ማርያም ስንልህ ከራሳችን ምርጫ አድነን!

ዲ.አ.መ
ነሐሴ 1 ቀን 2016 ዓ.ም.

ኦርቶዶክሳዊ ሕይወት

02 Jul, 08:19


የመጣል ስሜት (2)

የመጣል ስሜት ሕፃን ፣ አዋቂ ፤ ምሁር ያልተማረ ፤ ሀብታም ድሀ ፤ ዝነኛ የተረሳን ብንሆን ሊገጥመን ይችላል ። ይህ ስሜት ሲሰማን ቀድሞ የሚያስደስተን ነገር አሁን የማያስደስተን ይሆናል ። ቤታችንን እንደ መቃብር ፉካ ፣ ንብረታችንን እንደ ወዳደቀና የዛገ ብረት ፣ ዝናችንን ራሳችንን እንዳታለልንበት አረቄ ፣ መወደዳችንን እንደ ተሳሳትንበት መንገድ አድርገን መመልከት እንጀምራለን ። የመጣል ስሜት ማሩን ማምረር ፣ ወተቱን ማጥቆር ይጀምራል ። በጊዜ ካልተገታ ዳርቻውን እያሰፋ ፣ ያለንን ነገር እንዳናይ ጥቁር መጋረጃ ማልበስ ይጀምራል ። ለነገሮች ትርጉም ማጣት ፣ ሁሉንም ነገር ምን ዋጋ አለው ? በሚል በዜሮ ድምር ውስጥ መክተት እንጀምራለን ። ተሻገርሁ ስንል መልሶ ይህ ስሜት ይይዘናል ። አንድ ሰዓት ስድሳ ሰከንዶች ሳይሆን ስድሳ ዓመቶች ያሉት ሁኖ ይረዝምብናል ። እጅግ ቆየሁ ብለን ሰዓታችንን ስናየው የተገፋው ገና አምስት ደቂቃ ብቻ ነው ። ሌሊቱን መፍራት ፣ ቀኑ እንዴት ይጋመሳል ? ብሎ መጨነቅ እንጀምራለን ። የሚፈልጉንን ሰዎች መሸሽ ፣ የማይፈልጉንን ማሳደድ የመጣል ስሜት የሚፈጥርብን አዙሪት ነው ።

የመተው ስሜት በውስጣችን እያደገ ሲመጣ ትላንት የምናልፋቸውን ነገሮች ዛሬ ማለፍ ያስቸግረናል ። ደስታችንም ሩቅ አገር ይቀመጣል ። ማልቀስም መሳቅም ፣ መውደድም መጥላትም እያስፈራን ይመጣል ። የማናውቀው የፍርሃት ስሜት ይከበናል ። የብቸኝነት ብርድ ያንጠረጥረናል ። ምዕራብና ምሥራቅ ተቀራርበው ቢያቅፉን እንመኛለን ። አዎ የመጣል ስሜት ሲቆጣጠረን ልባችን የከዳን ፣ የሕይወት ፍሬን የላላ ይመስለናል ። ድንገት ከፊት ለፊታችን ከሚገጥመን ጋር እንጋጫለን ። ሰዎች ብቻ ሳይሆን ግዑዛን ነገሮችም እያናደዱን ይመጣሉ ። ደስ የማይል ፣ ልብ ላይ የሚንቀዋለል ፣ የሕይወት ማጥወልወል ይገጥመናል ። ፈልገን ማጣታችን ፣ ያዝኩት ስንል ከእጃችን የሚያመልጠን ነገር ይህን ስሜት ይፈጥርብናል ። ስሜት ዕለታዊ ሲሆን ምንም አይደለም ። ኑሮ ሲሆን ግን እንደገና መታየት አለበት ።

የመጣል ስሜት በታላቅ ተቃውሞ ውስጥ በማለፍ የሚፈጥርብን መደፍረስ ነው ። ሕይወታችንን የሰጠናቸው ሕይወታችንን ሲጋፉ ፣ የኖርንላቸው ከማመስገን ወቀሳ ሲያበዙብን ፣ ልጆቻችን እንከናችንን ሲፈልጉ የመጣል ስሜት ይገጥመናል ። በምንሸለምበት ነገር ልብሳችን ሲገፈፍ ፣ በምንኖርበት ዕድሜ ሞት ሲታወጅብን የመጣል ስሜት ይጫጫነናል ። ያሳደግነው ሲነክሰን ፣ የተንከባከብነው እሾህ ሁኖ ካባችንን ሲይዝብን የመጣል ስሜት ውስጥ እንገባለን ። ለአንድ ነገር ሁለት ዋጋ አይከፈልም ። ምድር ከሸለመን ሰማይ በባዶ ይሸኘናል ። ሲያሳድዱአችሁ ደስ ይበላችሁ ያለው ክርስቶስ ፣ ሲያሞግሱአችሁ ወዮላችሁ ብሎናል ። ክርስቶስን የምንመስለው በመገፋት እንጂ በመሸለም አይደለም ።

የመጣል ስሜት ከማይለምዱ ሰዎች ጋር በመኖር የሚከሰት ነው ። ገቡ ሲባሉ ከሚወጡ ፣ ተገኙ ሲባሉ ከሚጠፉ ፣ ቀረቡ ሲባሉ ከሚርቁ ሰዎች ጋር መኖር የሕይወት ዝለት ያመጣል ። አቋም የሌለውን ሰው ተሸክሞ መኖር አቋምም መቆሚያም ያሳጣል ። በውድ የገዛናቸው ፣ በርካሽ የሚሸጡን ጊዜ ጥቂት አይደለም ። ያ የመጣል ስሜት ያመጣል ። ክዳት ለእውነተኛ አፍቃሪ የማይለመድ የሕይወት ቅንቅን ነው ። ዛሬ ነገሥታት ከሚገዙት ሕዝብ ወረት የሚገዛው ይበዛል ። ዘመናዊነት ወረት ነው ። ሰው ማለዋወጥ ሥልጣኔ ተደርጎ የሚታይ ነው ። በቃል ኪዳን አለመጽናት ፣ እንዴት እንኑር ሳይሆን እንዴት እንለያይ ብሎ የመውጫውን በር ሲቆፍሩ ማደር ፣ ሰውን ተጠቅሞ መጣል የጊዜአችን በሽታ ሆኗል ። ስለከዱን ሰዎች ሳይሆን ከእኛ ጋር ስላለው እግዚአብሔር ማሰብ ይገባናል ። ከአባት ከእናታችን በፊት የሚያውቀን ጌታ ዛሬም አለ ። ለቅጽበት ዓይኑን ከእኛ ላይ አንሥቶ የማያውቀው ጌታ ደስታችን ነው ። ሁሉ የራሱን ሥዕል ይሰጠናል ። በጥሩ ዓይኖቹ የሚያየን ክርስቶስ ግን አሟልቶ ያነበናል ። የዓለም አስቀያሚ ብንሆን እንኳ የክርስቶስ ውቦች ነን ። ውብ ልቦች ሁሉን ውብ አድርገው ይመለከታሉ ። በተቀደሰው በኢየሱስ ልብ መኖሪያ አግኝተናል ።

“ሰይጣን ተስፋ የለውም ፣ ግን ተስፋ አይቆርጥም ፤ ሰው ተስፋ አለው ፣ ነገር ግን ተስፋ ይቆርጣል ።” እግዚአብሔርን በሰው ሚዛን ይለካዋል ። ሰዎች አጠገባችን የሉም ማለት እግዚአብሔር ከሰው ጋር አደመ ማለት አይደለም ። እርሱ የራሱ ሚዛን አለው ። በእኛ ላይ ያለውን የራሱን ዓላማ ያያል ። እርሱ አይተወንም ። ሰዎችን ስንለካ ፣ ስንመዝን ፣ ስንመትር መኖር ዋጋ የለውም ። የማይታበል ፍቅር ከእኛ ጋር ነው ። ሊወድቅ ያለውን የሕይወት ምሰሶ እንደገና እናጽናው ። መተው የማያውቀው አምላክ ከእኛ ጋር ነው ። ታሪክ እገሌን ጣለ ብሎ አልጻፈለትም ፣ ክርስቶስ ሰውን መጣል በእኛ አይጀምርም ።

ምስጋና ለማይተው ፍቅርህ ! አሜን !

ዲ.አ.መ
የካቲት 23 ቀን 2016 ዓ.ም.

ኦርቶዶክሳዊ ሕይወት

26 Jun, 18:52


የኤጲፋንዮስ ቅዳሴ

(ክፍል አንድ)

እግዚአብሔር በገናንነቱ ገናና ነው፤ በቅድስናው የተቀደሰ ነው፤ በምስጋናው የተመሰገነ ነው፤ በክብሩም የከበረ ነው፡፡

ከመቼ ወዲህ የማይሉት ቀዳማዊ ነው፤ እስከዛሬ የማይሉት ማእከላዊ ነው፣ እስከዚህ የማይሉትም ደኃራዊ ነው፡፡

ለአነዋወሩ ጥንት የለውም፤ ለአኳኋኑም ፍጻሜ የለውም፤ ለዘመኑ ቁጥር የለውም፤ ለውርዝውናውም ማርጀት የለበትም፤ ለኃይሉም ጽናት ድካም የለበትም፤ ለመልኩ ጥፋት የለበትም፡፡ ለፊቱ ብርሃንም ጨለማ የለበትም፡፡
ለጥበቡ ባሕር ድንበር የለውም፤ ለትእዛዙም ይቅርታ መስፈርት የለውም፤ ለመንግሥቱ ስፋት ዐቅም ልክ የለውም፣ ለአገዛዙም ስፋት ወሰን የለውም፡፡

በኅሊና የማያገኙት ሥውር ነው፤ በልቡናም የማይረዱት ምጡቅ ነው፤ አንሥርት የማይደርሱበት ረጅም ነው፤ ዓሣዎች የማይዋኙበት ጥልቅ ነው፡፡
ከተራሮች ራስ ይልቅ ከፍ ያለ ነው፤ ከባሕር ጥልቅነት ይልቅ ጥልቅ ነው፤ ነገሥታት የማይነሳሱበት ጽኑ ነው፤ መኳንንት የማይቃወሙት አሸናፊ ነው፡፡

የጥበበኞችን ምክር የሚያጠፋ ጥበበበኛ ነው፤ የሚመክሩትን ሰዎች አሳባቸውን የሚያስረሳ ዐዋቂ ነው፤ የጸኑ ልጓሞችን የሚፈታ ኃያል ነው፤ የኃጥአንን ጥርሶች የሚያደቅ፣ የትእቢተኞችንም ክንድ የሚቀጠቅጥ ብርቱ ነው፡፡

የግብዞችን ፊት የሚያዋርድ ክቡር ነው፤ የዝንጉዎችን ብርሃን የሚያርቅ ከሃሊ ነው፡፡
ባልንጀራ የሌለው አንድ ነው፤ ዘመድ የሌለው ሥሉጥ ነው፤ ሰማያት ይጠፋሉ፤ የብስም ትጠፋለች፤ ሁሉም እንደ ልብስ ያረጃል፡፡ እርሱ ግን እስከ ዘለዓለሙ እርሱ ነው፡፡

የባሕር መመላለሷ ድንቅ ነው፤ ድንቅስ በልዕልናው እግዚአብሔር ነው፤ የሚመስለው የለም፤ ከፍጥረትም ሁሉ ከአማልክትም ልጆች ሁሉ የሚተካከለው የለም፡፡ እርሱ ብቻ አምላክ ነው፤ እርሱም ብቻ ጌታ ነው፤ ፈጣሪም እርሱ ብቻ ነው፤ ሠሪም እርሱ ብቻ ነው፡፡

ስላሰበው ጥበብ እረዳት አይሻም፤ ስለ ወደደውም ሥራ መካር አይሻም፡፡ ሳይሆን ቀድሞ እንደ ሆነ አድርጎ፤ ያልተደረገውንም እንደ ተደረገ አድርጎ ሁሉን ያውቃል፡፡

ሳይጠይቅ ኅሊናን ይመረምራል፤ ሳይመረምር ልቡናን ይፈትናል፤ ያለመብራት በጨለማ ያለውን ያያል፡፡

ጻድቁን ጽድቅን ሳይሠራ ያውቀዋል፤ ኃጥኡንም ኃጢአት ሳይሠራ ያውቀዋል፤ ልበኞችን ከአባታቸው ወገብ (አብራክ) ሳይወጡ ያውቃቸዋል፤ ኃጥአንንም ከእናታቸው ማኅጸን ያውቃቸዋል፡፡
የሚሸሸገው የለም የሚሰወረውም የለም፤ ከእርሱም የሚሰወር የለም፤ ሁሉ በእርሱ ዘንድ የተገለጸ ነው፤ በዓይኖቹም ፊት ሁሉ የተዘረጋ ነው፡፡ ሁሉ በመጽሐፉ የተጻፈ ነው፤ በኅሊናውም ሁሉ የተጠራ ነው፡፡

ቁጥር የሌላቸው ታላላቆችን፣ መመርመር የሌለባቸውን የተደነቁ፣ የከበሩ ሥራዎችን ይሠራል:: ሥራው ካየነው ይልቅ እጹብ ነው፤ ኃይሉም ከሰማነው ይልቅ ድንቅ ነው፤ ጌትነቱም ከነገሩን ይልቅ ድንቅ ነው፡፡

ከጨለማ ለይቶ ብርሃንን ፈጠረ፣ ደመናውን መለየት ያውቃል፡፡ ውኃውን እንደወደደ ይከፍለዋል፤ የተመረጡትን በደመና ይሠውራል፡፡
ምድርን ፈጠራት መጠኗንም አዘጋጀ፤ ፍጻሜዋንም እንደምንም ተከለ፤ ማዕዘኗንም አጸና፡፡

ባሕርን ከእናቷ ሆድ በወጣች ጊዜ በበሮች አጠራት፡፡ ልብሷንም ደመና አደረገላት፤ በጉም ጠቀለላት፤ ወሰን አደረገላት፤ በውስጧም መዝጊያዎችንና ቁልፎችን አደረገላት፡፡ ‘‘እስከዚህ ድረሺ፤ ከወሰንሽም አትተላለፊ፤ ማዕበልሽ በውስጥሽ ይመላለስ (ይነቃነቅ) እንጂ’’ አላት፡፡
በበላይዋ ላይ የንጋት ብርሃን ተዘጋጀ፤ የአጥቢያ ኮከብም ትእዛዙን ዐወቀ፡፡ እርሱ ከምድር ጭቃን ነሥቶ ሕያው የሆነውን ፈጠረ፡፡ በምድርም ላይ እንዲነጋገር አደረገው፡፡ እርሱ እስከ ዓለም ዳርቻ ደረሰ፡፡ በጥልቅ ፍለጋም ተመላለሰ፡፡

ከግርማው የተነሳ የሞት ደጆች ይከፈታሉ፤ የሲኦል በሮችም ባዩት ጊዜ ይደነግጣሉ፡፡ ከሰማይ በታች ያለውን ስፋቱን፣ ከሰማይ በላይ የሚሆነውንም እርሱ ያውቀዋል፡፡

በእርሱ ትእዛዝ ዋግ ከመዝገቡ ይወጣል፡፡ ከሰማይ በታች ያለ አዜብ (ነፋስ ) ይመላለሳል፡፡ ዝናምን በምድረበዳ ያጸናዋል፣ ሰው በሌለበትና የሰው ልጅ በማይኖርበት ይዘንም ዘንድ፡፡

እርሱ የውኃውን መፍሰሻ ወሰነ፤ ክረምትንም በያመቱ ይከፍታል፤ በጋውንም ኋላ በጊዜው ጊዜ ያመጣዋል፡፡ደመናውንም በቃሉ ይጠራዋል ውኃም እየተንቀጠቀጠ ይመልስለታል፡፡

ብልጭልጭታውንም እርሱ ይልከዋል፤ እርሱም ይሄዳል፤ ‘‘ምንድር ነው?’’ እያለ ይመልስለታል፡፡ እርሱ ደመናን በጥበቡ ይቆጥረዋል፡፡ ሰማይን (ጠፈርን ) ወደ ምድር ያዘነብለዋል፡፡
እርሱ ብቻ የአርያምን ኃይል ለበሰ፤ በምስጋናና በክብር ተጌጠ፡፡

እሳታውያን ኪሩቤል፣ ብርሃን የለበሱ ሱራፌልም እርሱን ያመሰግናሉ፡፡ በማያርፍ ቃል፣ ዝም በማይል፣ በማይደክምም አንደበት ሁሉም ተባብረው ተሰጥዎ ባለበት ባንድ ቃል ‘‘የጌትነትህ ምስጋና በሰማይ በምድር የመላ ፍጹም አሸናፊ ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እግዚአብሔር’’ ይላሉ፡፡

ፍጹም አሸናፊ እግዚአብሔር የጌትነትህ ምስጋና በሰማይና በምድር የመላ ነው፡፡

ሁሉ ከእርሱ ነው፣ ሁሉም ስለእርሱ ነው፣ ሁሉም የእርሱ ነው፣ ሰማይ በእርሱ ነው፣ ከሰማያት በላይ ያለ ሰማይም የእርሱ ነው፣ የአርያም ስፋት የክብሩ ዙፋን ነው፣ የምድርም ስፋት የእግሩ መመላለሻ ናት፡፡

ፀሐይ የእርሱ ነው፣ ጨረቃም ከእርሱ ነው፣ ከዋክብትም የእጁ ሥራ ናቸው፣ ደመናት መልክተኞቹ፣ ነፋሳትም ሠረገላዎቹ ናቸው፣ እሳትም የቤቱ ግርግዳ ነው፡፡

የቤቱ ጠፈር ውኃ ነው፣ የዙርያውም ጸፍጸፍ የበረድ ሰሌዳ ነው፣ ድንኳኖቹ ብርሃናት ናቸው፡፡ የመሰወሪያ መጋረጃውም የብርሃን መብረቅ ነው፤ መመላለሻውም በአየር ነው ::

የመናገሩ ድምፅ በብልጭልጭታ ያለ ነው፡፡ የነጎድጓዱ ቃል በሠረገላዎች አለ፡፡ ባሕር ባሪያው ናት፣ የወንዝ ፈሳሾች ተገዥዎቹ ናቸው፡፡ ቁር አስሐትያም ፈቃዱን የሚሠሩ ናቸው፡፡

ከምድር ዳርቻ ደመናውን ያወጣል፣ መብረቅንም በዝናም ጊዜ አደረገ፣ ዝናምንም እንደ መሽረብ ነጠብጣብ ያፈሳል፣ ጉምን እንደ አመድ ይበትነዋል፣ በረድንም እያጠቃቀነ ያወርዳል፣ ለእንስሳም ሣሩን ያለመልማል፡፡

እንዳሰበ ያደርጋል፣ እንደ ጀመረም የጀመረውን ይፈጽማል፣ እንደወደደም ያከናውናል፡፡ ያሳዝናል፣ ደስ ያሰኛል፤ ያደኸያል፣ ባለጸጋም ያደርጋል፡፡

ያዋርዳል፣ ያከብራል፤ ይገድላል፣ ያድናልም፤ ድውይ ያደርጋል፣ ይፈውሳልም፤ ይኮንናል፣ ያጸድቃልም፡፡
የወደደውን ይምራል፣ ሊያስጨንቀው የወደደውን ያስጨንቃል፣ የሚምረውን ይምረዋል፡፡ ይቅር የሚለውን ይቅር ይለዋል፡፡

ኦርቶዶክሳዊ ሕይወት

11 May, 10:54


248)። ዘማሪው ንጉሥ ዳዊት እነዚህ የእግዚአብሔር ወዳጆች በቊጥር እጅግ ስለበዙበት በመደነቅ፦ “ወበኀቤየሰ ፈድፋደ ክቡራን አእርክቲከ እግዚኦ፥ ወፈድፋደ ጸንዑ እምቀደምቶሙ፥ እኄልቆሙ እምኆጻ ይበዝኁ - በእኔ ዘንድ ወዳጆችህ (ባለሟሎችህ) እጅግ የከበሩ ናቸው፥ አስቀድመው ከነበሩት ይልቅ ጸኑ፥ ብቈጥራቸው ከአሸዋ ይልቅ ይበዛሉ” ሲል ዘምሯል (መዝ. 138/139፥17፣ መዝሙረ ዳዊት ትርጓሜ፥ ገጽ 640)። ቅዱሳን የሌሏትና በሕይወታቸው አምላካቸውን ላከበሩ ለእግዚአብሔር ምርጦች እውቅና የማትሰጥ ቤተ ክርስቲያን ልትኖር አትችልም፤ የክርስቶስ አካል የሆነችው ቤተ ክርስቲያን የቅዱሳን ኅብረት ናትና።

ኦርቶዶክሳዊ ሕይወት

11 May, 10:54


+ የቅዱሳን ኅብረት (Communion of Saints)

የዛሬ 3 ዓመታት አካባቢ Wadi El Natroon በሚባለው ሸለቆ ውስጥ የሚገኙትን የግብጽ ገዳማት ለመጎብኘትና በበረሃው ያሉ አባቶችን እውነተኛና ኦርቶዶክሳዊ መንፈሳዊነት በመጠኑ ለመማር ወደ ቦታው አቅንቼ ነበር። ሺሀት (Shihat) ከሚለው የቅብጥ (Coptic) ቃል ተወስዶ “መዳልወ አልባብ = የልብ ሚዛን” የሚል ትርጉም በተሰጠው አስቄጥስ (Scetis) በረሃ ውስጥ በታላቁ አባ መቃርስ፥ በአባ ቢሾይ፥ እና በኢትዮጵያዊው ቅዱስ አባ ሙሴ ጸሊም ስም የተሰየሙ፥ በረሃውን የተለየ ግርማ ሞገስ ያላበሱ ገዳማት ይገኛሉ። ለሮማውያን ማስታወሻ “Baramous” በሚል ስም የሚታወቀውና ሶርያዊ መጠሪያ የያዘው “El-Suriani” የተሰኘውም ገዳም የአስቄጥስ በረሃ አባላት ናቸው። Baramous ገዳም አካባቢ ዘግተው ይኖሩ የነበሩና ግብጻውያኑ Abouna Abdil-Messih (አባታችን ገብረ ክርስቶስ) እያሉ የሚጠሯቸው ኢትዮጵያዊ ቅዱስ፥ በፖፕ ሺኖዳ ሣልሳይ የፕትርክና ዘመን ፓትርያርኩን ተሰናብተው ወደ ኢየሩሳሌም እንደሄዱ፥ መጨረሻቸውም እንዳልታወቀ ሰምቻለሁ። “አቡነ አብድል መሲህ አል ሀበሺ” በሚል ርእስ ገዳሙ በአረብኛ ያዘጋጀውን የኢትዮጵያዊውን ቅዱስ መንፈሳዊ ተጋድሎ የሚተርክ መጽሐፍንም አባ ኖፈር የተባለ መነኮስ በስጦታ አበርክቶልኛል።

ከገዳማተ አስቄጥስ ጉብኝት (pilgrimage) እና በቦታው ካገኘሁት መንፈሳዊ በረከት በተጨማሪ በካይሮ ከተማ ዙሪያ የሚገኙ ታሪካዊ አብያተ ክርስቲያን (ለምሳሌ፦ ዝነኛዋ ዘይቱን ማርያም) እና አነስተኛ ገዳማትን የማየትም እድል ነበረኝ። በቅዱስ ጊዮርጊስ (ማር ጊርጊስ) ስም የተሰየመውን የሴቶች ገዳም (Convent) በመጎብኘት ላይ እያለን፥ ከላይ የምትመለከቱትን አስደናቂ ሥዕለ-ቅዱሳን ተመለከትሁ። ቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ውስጥ የ2ኛ ዓመት ዲግሪ ፕሮግራም ተማሪ እያለሁ፥ ዶ/ር አንቱን ያዕቆብ ሚካኤል የተባለ ግብጻዊ ፕሮፌሰር አረብኛ አስተምሮን ስለነበር፥ ያለችኝን መጠነኛ የአረብኛ ንባብ ችሎታ በመጠቀም ከሥዕሉ በላይ የተጻፉትን ሁለት ቃላት አነበብኳቸው። እንደ አረብኛ የአነባበብ ህግ ከቀኝ ወደ ግራ ሲነበቡ፦ “አል ከኒሳ፥ አል መንታምራህ” ይላሉ። “ከኒሳ” በአረብኛ “ቤተ ክርስቲያን” ማለት እንደሆነ አውቃለሁ። ሁለተኛውን ቃል ግን ባነበውም ትርጉሙን ስላላወቅሁት አንዲት ግብጻዊት ሴት ጠይቄ፥ ሁለቱ ቃላት በአንድ ላይ “ድል አድራጊዋ ቤተ ክርስቲያን” የሚል ትርጉም እንደሚሰጡ ተረዳሁ። ሥዕሉን ጎላ አድርጋችሁ ከተመለከታችሁት፥ ከቅዱሳኑ መካከል ኢትዮጵያዊው ሐዋርያና ገዳማዊ ቅዱስ አባ ተክለ ሃይማኖት ይገኙበታል።

የነገረ መለኮት ሊቃውንት ሰማያዊቷን ቤተ ክርስቲያን “Victorious Church” ወይም “The Church Triumphant” በሚል ስያሜ ይጠሯታል። የዚህች ቤተ ክርስቲያን አባላት፥ በቅዳሴ ማርያም እንደተጠቀሰው፦ ለምስጋና ትጉሃን የሆኑ ቅዱሳን መላእክት እና በዐጸደ ነፍስ ያሉ ቅዱሳን ነቢያት፥ ወንጌልን የሰበኩ ሐዋርያት፥ ድል የነሡ ሰማዕታት፥ ቡሩካን የሆኑ ጻድቃን፥ ሥዩማን ካህናትና ትዕግስተኞቹ ደናግል ወመነኮሳት ናቸው። የዕብራውያን መልእክት ጸሐፊ በዐጸደ ነፍስ ያሉ ቅዱሳንን፥ ዙሪያችንን በሚከብበን ደመና እየመሰለ “የእምነት ምስክሮች” በማለት ይጠራቸዋል (ዕብ. 12፡1-2)።

በመንፈሳዊ ትግል ላይ ያለችው የምደራዊቷ ቤተ ክርስቲያን “Earthly Church” ወይም “Church Militant” አባላት ደግሞ በኃጢአት ስንወድቅ በንስሐ የምንነሳው፥ በዚህ ዓለም በሕይወት ያለነው አምንያን ነን። የምድራዊቷ ቤተ ክርስቲያን አባላት የሆንን ክርስቲያኖች የመንፈሳዊ ጉዟችን ፍጻሜ፥ ሰማያዊውን የቅዱሳን ማኅበር መቀላቀል እንደሆነ በዚሁ በዕብራውያን መልእክት ተጠቅሷል፦ “ነገር ግን ወደ ጽዮን ተራራና ወደ ሕያው እግዚአብሔር ከተማ ደርሳችኋል፥ ወደ ሰማያዊቱም ኢየሩሳሌም፥ በደስታም ወደ ተሰበሰቡት ወደ አእላፋት መላእክት፥ በሰማያትም ወደ ተጻፉ ወደ በኵራት ማኅበር፥ የሁሉም ዳኛ ወደሚሆን ወደ እግዚአብሔር፥ ፍጹማንም ወደ ሆኑት ወደ ጻድቃን መንፈሶች” (12፥22-23)።

በተለያዩ ሁለት ዓለማት እንደምንኖር ለማጠየቅ ያህል “ምድራዊቷ እና ሰማያቷ ቤተ ክርስቲያን” የሚል አገላለጽ መጠቀም የተለመደ ቢሆንም፥ ቤተ ክርስቲያን በባሕርይዋ አንዲት ናት። ለእግዚአብሔር መንግሥት የተጠራችው ecclesia (ቤተ ክርስቲያን)፥ የቅዱሳን ማኅበር ስለሆነች ከእኛ አስቀድመው ያረፉ ቅዱሳን “በእምነታቸው ተመስክሮላቸው ሳሉ፥ የተሰጠውን የተስፋ ቃል አላገኙም፥ ያለእኛ ፍጹማን እንዳይሆኑ እግዚአብሔር ስለእኛ አንዳች የሚበልጥ ነገርን አስቀድሞ አይቶ ነበርና” (ዕብ. 11፥39-40)። በእምነታቸው ምክንያት መከራን በመቀበልና በሞት ቢቀድሙንም፥ የክብር አክሊልን በመሸለም ግን አልቀደሙንም። እነርሱም፥ እኛም የአንዱ የክርስቶስ አካል አባላት ስለሆንን፥ በምድር ያለን እኛ በሞት ወደ እነርሱ ተወስደን የእነርሱን ክብር እስክናገኝ ድረስ ይጠብቃሉ፤ እኛ የእነርሱን ክብር ስናገኝም እንደራሳቸው ክብር ቆጥረውት ደስ ይላቸዋል (ድርሳን ዘቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፥ 28፣ ቊ. 63-72)።

ስለዚህ ቤተ ክርስቲያን (ecclesia)፡ በዓለመ መላእክት የተመሠረተች፥ በዚህ ምድር የመንግሥተ ሰማያት ምሳሌ ሆና የምትኖር፥ ክርስቶስ ዳግም ሲመጣ ወደ ሰማያዊ መንግሥቱ የሚጠቀልላት ማኅበረ ቅዱሳን ናት። ሠራዒው ካህን በቅዳሴ ሰዓት እያንዳንዱን ካህን እያጠነ፦ “ቄሱ አባቴ ሆይ፥ ክብርት በምትሆን በጸሎትህ ታስበኝ ዘንድ እለምንሃለሁ” ሲል፥ የብሉይ ኪዳን ካህናት “ማኅበረ በኵር” ተብላ የምትጠራው ጥንታዊ ማኅበር (ቤተ ክርስቲያን) አባላት መሆናቸውን በማመልከት፥ ካህናቱ የሚከተለውን መልስ ይሰጡታል፦
የመልከ ጼዴቅን መሥዋዕት፥ በበኵር ቤተ ክርስቲያን የሚኖሩ የአሮንና የዘካርያስንም ዕጣን እንደ ተቀበለ፥ እግዚአብሔር መሥዋዕትህን ይቀበል፥ የዕጣንህንም መዓዛ ይቀበል (ያሽትት)፥ ክህነትህንም በእውነት ይጠብቃት (ሥርዓተ ቅዳሴ፣ ቊ. 124)።
የብሉይ ኪዳን ካህናቱ አሮንና ዘካርያስ “የበኵር ቤተ ክርስቲያን” አባላት ተብለው እንደተጠቀሱ ልብ እንበል። በምድር ላይ ያለች ሰማይ (Heaven on earth) የሆነችው የቅዱሳን ማኅበር (ቤተ ክርስቲያን) በአባልነት፦ ቅዱሳን መላእክትን፥ የብሉይ ኪዳን ነቢያትንና ካህናትን፥ እና የአዲስ ኪዳን ቅዱሳንን ሁሉ ታቅፋለች። ለዚህም ነው ማሕሌታውያን የቅዱስ ያሬድ ልጆች፥ የሥላሴን አንድነትና ሦስትነት የምታስተምር ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያንን ሥሮቿ በምድር ተተክለው ቅጠሎቿ ሰማይ በደረሱ ትልቅ ዛፍ መስለው የዘመሩላት፦ “እንተ በምድር ሥረዊሃ፥ ወበሰማይ አዕፁቂሃ እንተ በሥሉስ ትትገመድ” (ዚቅ ዘዘመነ ጽጌ፥ አመ፫ ለጥቅምት፤ ገጽ. 39)።

ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያንን በምድር ላይ ያለች ሰማይ (Heaven on earth) የምንልበት ምክንያት ከሰማያዊው ቅዳሴ (Heavenly Liturgy) ጋር የአምልኮ ኅብረት ስላላት ነው። የቅዳሴው ሰዓት (liturgical time) ከተራው የዚህ ዓለም ሰዓት (chronos)፥ የተለየ ሰዓት (kairos) ነው። ለዚህም ነው ሠራዒው ካህን ቅዳሴውን ሲጀምር፥ “ሚመጠን ግርምት ዛቲ ዕለት ወዕፅብት ዛቲ ሰዓት - ይህች ቀን ምን ያህል የምታስፈራ ናት! ይህችስ ሰዓት ምን ያህል የምታስጨንቅ ናት!” የሚለው (ሥርዓተ ቅዳሴ ቊ.

ኦርቶዶክሳዊ ሕይወት

11 May, 10:54


1)። የቅዳሴ ሰዓት፥ ወደ ፊት የሚጠብቀንን ሰማያዊ አምልኮና የበጉን ሠርግ አስቀድመን የምንቀምስበት ጽዋ፥ የምንሳተፍበት ዕድል፥ የምንለማመድበት ጸጋ ነው። የሰማያዊው ዓለም አምልኮ የተገለጸላቸው ዓበይት ነቢያቱ ሕዝቅኤልና ኢሳይያስ፥ እንዲሁም ባለራእዩ ወንጌላዊ ዮሐንስ የተወሰነ ሥዕላዊ መግለጫ ሰጥተውናል (ሕዝ. 1፥4-28፤ ኢሳ. 6፥1-4፤ ራእይ 4፥1-11)። Sanctus (angelic hymn) በመባል የሚታወቀውን የመላእክትን ዝማሬ፦ “ቅዱስ፥ ቅዱስ፥ ቅዱስ፥ የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር፤ ምድር ሁሉ ከክብሩ ተሞልታለች” (ኢሳ. 6፥3) እያልን በዚህ ምድር ስንዘምረው ፥ የሰማያውያን ቅዱሳን መላእክት አምልኮ ተካፋዮች እንሆናለን።

ስለዚህ በቅዳሴ ጊዜ አምልኮው የሚካሄድበት ሥፍራ (liturgical space) ሰማይ ዘበምድር (በምድር ላይ ያለ ሰማይ) ወደ መሆን ይለወጣል፤ ሰማያዊቷና ምድራዊቷ ቤተ ክርስቲያንም ያለምንም ልዩነት አንዲት ቤተ ክርስቲያን ይሆናሉ። ኢትዮጵያዊው ሊቅ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ፥ በሰማያውያንና በምድራውያን ፍጥረታት በኅብረት ለሚመሰገነው ልዑል እግዚአብሔር የአምልኮ ምስጋና ሲያቀርብ እንዲህ ይላል፦
ንሴብሖ ለእግዚአብሔር ለዘበስብሐተ ቅዱሳን ይሴባሕ። ዘኪያሁ ይሴብሑ ማኅበረ መላእክት ፍሡሓን። ሎቱ ይትቀነያ ነፍሳተ ጻድቃን። ወሎቱ ትሰግድ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን፥ እንዘ ትብል፦ ‘ስብሐት በአርያም፥ ወሰላም በምድር ለዘሠምሮ ለሰብእ (መጽሐፈ ሰዓታት፣ ገጽ. 23)።
(በቅዱሳን ምስጋና የሚመሰገን እግዚአብሔርን እናመስግነው። ደስተኞች የሆኑ የመላእክት ማኅበር እርሱን ያመሰግናሉ፥ የጻድቃን ነፍሳት ለእርሱ ይገዛሉ። ቅድስት ቤተ ክርስቲያንም ‘ክብር በአርያም ይሁን ሰላምም በምድር ለሰውም በጎ ፈቃድ’ እያለች ለእርሱ ትሰግዳለች)።

ቤተ ክርስቲያን የክርስቶስ አካል ስለሆነች፥ በዐጸደ ነፍስ ያሉ ቅዱሳን ሞትን ድል አድረጎ በተነሳው፥ ትንሣኤና ሕይወት በሆነው ጌታ ምክንያት ሕያዋን ናቸው። ይህንን መረዳት የተሳናቸውና ራሳቸውን Protestants (ተቃዋሚዎች) በሚል ስያሜ የሚጠሩ ወገኖቻችን፥ “በዐጸደ ነፍስ ያሉ ቅዱሳን፥ ሕያዋን ናቸው” የሚለውን ኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮ ሲቃወሙ እንሰማለን። እዚህ ላይ ልብ ልንለው የሚገባ ትልቅ ቁም ነገር ቢኖር፥ ምድራዊ ሩጫቸውን ጨርሰው በአካለ ነፍስ ወደ እግዚአብሔር የሄዱ ቅዱሳን (መጽ. መክ. 3፥21፤ 12፥7) ሕያዋን ናቸው የምንለው “ፊተኛውና መጨረሻው ሕያውም እኔ ነኝ፥ ሞቼም ነበርሁ እነሆም፥ ከዘላለም እስከ ዘላለም ድረስ ሕያው ነኝ” (ራእይ 1፥17-18) ማለት የተቻለው የክርስቶስ ንጽሕትና ቅድስት አካል የሆነችው (የቤተ ክርስቲያን) አባላት ስለሆኑ ነው። “ቅዱሳን በዐጸደ ነፍስ ሕያዋን አይደሉም” ማለት፥ የክርስቶስን አካል ሕያውነት እንደመካድ ይቆጠራል።

በተጨማሪ፥ ቅዱሳን ሕያዋን ካልሆኑ ለኃጢአታችን በታረደው በግ ዙፋን ፊት ከቅዱሳን መላእክት ጋር የአምልኮ ኅብረት ሲያደርጉ በወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ የራእይ መጽሐፍ ለምን ተጻፈ? እንዲያውም በአካለ ነፍስ ያሉ ቅዱሳን ሰዎች፥ ስለ ምድራዊቷ ቤተ ክርስቲያን የሚያቀርቡት የአማላጅነት ጸሎትና ልመና ሁለት ጊዜ በዕጣን እንደተመሰለ ልብ እንበል፦ “መጽሐፉንም በወሰደ ጊዜ አራቱ እንስሶችና ሀያ አራቱ ሽማግሌዎች በበጉ ፊት ወደቁ፥ እያንዳንዳቸውም በገናንና የቅዱሳን ጸሎት የሆነ ዕጣን የሞላበትን የወርቅ ዕቃ ያዙ” (5፥8)፤ “ሌላም መልአክ መጣና የወርቅ ጥና ይዞ በመሰዊያው አጠገብ ቆመ፤ በዙፋኑም ፊት ባለው በወርቅ መሰዊያ ላይ ለቅዱሳን ሁሉ ጸሎት እንዲጨምረው ብዙ ዕጣን ተሰጠው። የዕጣኑም ጢስ ከቅዱሳን ጸሎት ጋር ከመልአኩ እጅ በእግዚአብሔር ፊት ወጣ” (8፥3-4)።

ከላይ የተጠቀሱት ሁለት የራእየ ዮሐንስ ጥቅሶች በግልጽ የሚያመለክቱት በዐጸደ ነፍስ ያሉ የቅዱሳን ሰዎች ነፍሳት ከመላእክት ጋር የአምልኮ ኅብረት እንዳላቸው ነው። እግዚአብሔር፦ “የአብርሃም አምላክ፥ የይስሐቅም አምላክ፥ የያዕቆብም አምላክ” ተብሎ መጠራትን እንደወደደ ሁሉ፥ በሕይወታቸው እርሱን ያከበሩ እልፍ አእላፍ ቅዱሳን አምላክም ነው። ስለዚህ፥ ለሰዱቃውያን በሰጠው መልስ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንደነገረን፥ “ሁሉ ለእርሱ ሕያዋን ስለሆኑ፥ የሕያዋን አምላክ ነው እንጂ የሙታን አይደለም” (ሉቃ. 20፥ 37-38)። “ሁሉ ለእርሱ ሕያዋን ስለሆኑ” የሚለውን ሐረግ በማስተዋል እንመልከት። ይህን ዓለም በሞት ተሰናብተው ቢሄዱም ሥጋዊው ሞት የሕልውናቸው መጨረሻ አይደለም፥ የዘላለማዊ ሕይወት (eternal life) መጀመሪያ እንጂ። ስለዚህ “ሕያዋን” የሆኑለትን አምላክ በሰማያት ያመልካሉ፤ “ከአለቆችና ከሥልጣናት ጋር ከዚህም ከጨለማ ዓለም ገዦች ጋር በሰማያዊም ስፍራ ካለ ከክፋት መንፈሳውያን ሠራዊት ጋር” (ኤፌ. 6፥12) መንፈሳዊ ተጋድሎ ላለባት ምድራዊት ቤተ ክርስቲያን ጸሎትንና ምልጃንም ያቀርባሉ።

ማጠቃለያ
ኦርቶዶክሳዊው ትምህርተ-ቤተ ክርሰቲያን (ecclesiology) ከክፉው ዓለም ለእግዚአብሔር መንግሥት የተለየች አንዲት የቅዱሳን ማኅበር እንዳለች ያስተምረናል። ይህች ቅድስት ማኅበር ወይም ecclesia የአማንያን (የምድራውያን ሰዎች)፥ ሕያዋን የሆኑ የቅዱሳን መላእክትና በዐጸደ ነፍስ ያሉ ቅዱሳን ኅብረት ናት። የድኅነት (መዳን) ጉዞአችን ተፈጻሚነት የሚያገኘው የዚህች ቅድስት ማኅበር አባላት በመሆን እስከጸናን ድረስ ነው፤ ከቤተ ክርስቲያን ውጪ ድኅነት የለምና። ለዚህም ነው በኦርቶዶክሳውያን ዘንድ የታወቀው ዝነኛ አባባል፦ “Outside the Church there is no salvation” የሚለው። የእያንዳንዱ ክርስቲያን ድኅነት (መዳን) የሚወሰነው የክርስቶስ አካል ከሆነችው ቤተ ክርስቲያን ጋር ካለው ኅብረት አንጻር ነው። አንድ ታላቅ ኦርቶዶክሳዊ ምሁር እንዳሉት፦ “ማንኛውም ሰው ሲወድቅ ብቻውን ይወድቃል፤ ነገር ግን፥ ማንም ብቻውን መዳን አይችልም። የቤተ ክርስቲያን አባል እንደመሆናችን፥ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ፥ ከሁሉም አባላት ጋር በኅብረት እንድናለን” (Ware, p. 232)። ሁላችንም እንድን ዘንድ የሚወድ ቸሩ አምላካችን የምንድንበትን መንገድ በዚህ ምድር የመንግሥቱ መገለጫ አድርጎ በመሠረታት ቅድስት ቤተ ክርስቲያኑ በኩል ሰጥቶናል፤ ቤተ ክርስቲያንም እግዚአብሔርን አሳውቃናለች። ይህን አንድነት ይበልጥ ግልጽ የሚያደርግልን የካርቴጅ ሊቀ ጳጳስ የነበረው የቅዱስ ቆጵርያኖስ (St. Cyprian of Carthage, + A.D. 258) ዝነኛ አባባል ነው፦ “ቤተ ክርስቲያንን እንደ እናቱ ያልተቀበለ ሰው፥ እግዚአብሔርን እንደ አባቱ ሊቀበል አይችልም” (“On the Unity of the Catholic Church, 6” quoted in Ware, p. 240)::

የቅድስቲቱ ማኅበር አባላት የሆኑና ከዘመነ ብሉይ ጀምሮ የተነሱ ቅዱሳን የቤተ ክርስቲያን ጌጦች ናቸው። በየዘመኑ የሚነሱ ትውልደ ቅዱሳን፥ ከእነርሱ በፊት ከነበሩ የጻድቃን ነፍሳት ጋር ሊበጠስ የማይችል ኅብረት ስላላቸው፥ እንደ St. Symeon the New Theologian አገላለጽ፦ “ብርሃንን የተመላ የወርቅ ሰንሰለትን ይመስላሉ” (“Centuries, III, 2-4” quoted in Ware, p.

ኦርቶዶክሳዊ ሕይወት

05 May, 11:07


እንኳን ለ2016 ዓ.ም. ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የትንሣኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ !

የጌታችን ትንሣኤ የአማኞች ድኅነት ፣ የቤተ ክርስቲያን ልደት ፣ የሥጋ ክብረት ፣ የተስፋ ምሰሶ ፣ የሞት መውጊያ ፣ የቅድስና ኃይል ፣ የምእመናን ፍቅር ፣ የሰማዕትነት ብርታት ፣ የእባቡን ራስ ለመቀጥቀጥ ጽናት ፣ የሐዋርያት ምስክርነት ፣ የዲያቆናት አዋጅ ፣ የካህናት ሞገስ ፣ የሰው ልጆች ይቅርታ ነው ።

ትንሣኤው ዓመታዊ በዓላችን ብቻ ሳይሆን ዕለታዊ ኑሮአችንም ነው ። በዚህ በዓል የትንሣኤውን ምሥጢር ጠብ የተገደለበትን ሁነት በማሰብ ይቅርታና ፍቅር በአገራችንና በምድራችን እንዲመጣ ልንተጋበት ይገባል ። የሞተብን ውድ ነገር ትንሣኤ ያገኛል ። ቡሩክ ፋሲካ ይሁንላችሁ !

ዲ.አ.መ
ሚያዝያ 27 ቀን 2016 ዓ.ም.

ኦርቶዶክሳዊ ሕይወት

02 Apr, 11:19


❝ሰማይንና ምድርን የፈጠርኽ ፥ ተስፋ የሚያደርጉኽን የማተው ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ዘንዶውን ድል እንዳደርግ ራሱንም እንድቀጠቅጥ ስለአደረከኝ አመሰግንሃለኹ ! ለባሪያዎችኽ ዕረፍት ስጣቸው፣ የጠላቶቻችን ግፍ የመጨረሻ ሰለባ ተጠቂ ነኝና ይኽን ዕረፍት ስጠኝ ! ለቤተክርስትያንኽ ሰላምን ስጣት ፥ ከዲያብሎስ ጨቋኝነት ንጠቃት። አሜን።
« ቅዱስ ቴዎዶጦስ ዘዕንቆራ»

ኦርቶዶክሳዊ ሕይወት

29 Feb, 08:10


የቅዱስ አንብሮስ የንስሐ ጸሎት

"ቁስሌን የሚፈውስልኝ ጌታ ኢየሱስ ሆይ አንተን ብቻ እከተላለሁ ፡፡ በአንተ ካለው የእግዚአብሔር ፍቅር ምን ይለየኛል? መከራ ፣ ጭንቀት ወይስ ረሃብ? በምስማር እንደ ተያዘ እኔ  በፍቅር ሰንሰለቶችህ ታስሬአለሁ። ጌታዬ ኢየሱስ ሆይ ኃጢአቶቼ በበረታው ጎራዴህ ከእኔ ቁረጥ ፡፡ በፍቅርህ እስራት ጠብቀኝ በእኔ ውስጥ ያለውን የተበላሸውን ነገሬ አስወግድ ፡፡ በፍጥነት ወደ እኔ ና የበዛውን ፣ የተሰወረውንና የደበቀውን መከራዬን ፍጻሜ አበጅለት ፡፡ አንተ የቆሸሸውን በውስጤ ያለውን አፅዳ፡፡

በኃጢአቶቻችሁ ውስጥ ሰካራም ሀሳቦችን የምታወጡ ፤ እናንተ ምድራዊ ሰዎች ሆይ ስሙኝ ፈዋሼን አጊንቻለሁ ፡፡ እርሱ በሰማያት ተቀምጧል በፈውሱ ምድርን ሞልቷል።  እርሱ ብቻ ህመሜን ሊፈውስ የሚችለው። እሱ ብቻ ነው። እርሱ ብቻ ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰወረውን የሚያውቅ ፣ የልቤን ሀዘን ፣ የነፍሴን ፍርሃት ሊያስወግድ የሚችል። ክርስቶስ ጸጋ ነው ፣ ክርስቶስ ሕይወት ነው ፣ ክርስቶስ ትንሣኤ ነው! አሜን"

ትርጉም፡ ብስራት ገብርኤል
[ምንጭ ፦ A Prayer of Repentance and Conviction by St. Ambrose of Milan]

ተቀላቀሉ መልዕክቱን ለሌሎች ያካፍሉ!
https://t.me/orthodoxy_life

ኦርቶዶክሳዊ ሕይወት

27 Feb, 14:27


የእግዚአብሔር ልጆች "የእውነት ፈርጦች" የአባቶችን ጥበብና ምክር አዘል ትረካ!

👉ሙሉውን በዩቲዩብ ይመልከቱ :
https://yt.psee.ly/5n4d52

ኦርቶዶክሳዊ ሕይወት

27 Feb, 14:15


https://youtu.be/kR_XkGhz0GY?si=ibfjkHXGBnGR4GsF

ኦርቶዶክሳዊ ሕይወት

25 Feb, 14:22


የሰማይ አዕዋፋትን የሚመግበው የሰማዩ አባታችን ለእኛ እጅግ ይራራል!

"ወደ ሰማይ ወፎች ተመልከቱ፤ አይዘሩም አያጭዱምም በጎተራም አይከቱም፥ የሰማዩ አባታችሁም ይመግባቸዋል፤ እናንተ ከእነርሱ እጅግ አትበልጡምን?" (ማቴ 6: 26)

ኦርቶዶክሳዊ ሕይወት

21 Feb, 09:17


የተወደዳችሁ ኦርቶዶክሳውያን የቻናላችን ቤተሰቦች የተለያዩ መንፈሳዊ ትረካዎችን ፣ ትምህርቶችንና ታሪኮችን በዪቲዮብ/ YouTube ይዘን መጥተናል እንድታደምጡ በክርስቶስ ፍቅር እንጋብዛችኋለን!

እንዲደርሶት ቻናሉን ሰብስክራይብ/subscribe ያድርጉ!

https://youtube.com/@orthodoxy_life?si=F9z9izEPP2GrrWXH

ኦርቶዶክሳዊ ሕይወት

19 Feb, 15:59


ቆነጃጅትም!
|
"ቆነጃጅትም የእግዚአብሔር ቃል እንዳይሰደብ፥ ባሎቻቸውን የሚወዱ፥ ልጆቻቸውን የሚወዱ፥ ራሳቸውን የሚገዙ፥ ንጹሖች፥ በቤት የሚሠሩ፥ በጎዎች፥ ለባሎቻቸው የሚታዘዙ እንዲሆኑ ይምከሩአቸው።" (ቲቶ 2: 4-5)

Join us:
https://t.me/orthodoxy_life

ኦርቶዶክሳዊ ሕይወት

19 Feb, 06:07


❝ ክርስቶስ በመስክ ውስጥ የተደበቀ ሀብት ነው ፤ መስኩ ደግሞ መለኮታዊው ቅዱሳት መጻሕፍት ነው።❞

☦️ቅዱስ ሄሬኔዎስ ( ኢራንየስ)

8,717

subscribers

236

photos

1

videos