ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች @sinksar Channel on Telegram

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

@sinksar


ይኼ ገጽ የአመቱ ስንክሳር በየቀኑ የሚቀርብበት ማብራሪያው ላልቀረበበትም የበለጠ እንድናነብ የሚረዳን መማማሪያ ነው።

" ዓለምን ወይም በዓለም ያሉትን አትውደዱ:: በዓለም ያለው ሁሉ: እርሱም የሥጋ ምኞትና የዓይን አምሮት: ስለ ገንዘብም መመካት ከዓለም ስለ ሆነ እንጂ ከአባት ስላልሆነ: ማንም ዓለምን ቢወድ የአባት ፍቅር በእርሱ ውስጥ የለም:: ዓለሙም: ምኞቱም ያልፋሉ::" 1ዮሐ. 2:15

# ያጋሩ

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች (Amharic)

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች የበለጠ እንድናነብ የሚረዳን መማማሪያ ገጽ ነው። ላልቀረበበትም ዓለምን ወይም በዓለም ያሉትን አትውደዱ፣ ዓለሙ ሥጋን ምኞትና ዓይን አምሮትን መግንአት። በዓለም ስለ ሆነ እንጂ ከአባት ስላልሆነ ግን እንደ ሰማይ የበላይ ቀንድ እየሰራቹን በአንድ በርም ላሉት ሰላምም ተናጋሁ። በዓለሙ መመካት ለሆኑ ባለሙያን ለሶስት ዓመታት ለሌሎችም መሬቷን ለበኣልት እንሠራለን። ምክንያቱም የዓለምን አባት ፍቅር በዓለሙ ውስጥ አላረከነኝም። ከዓለሙ ገንዘብ ስለ መመካት ሁሉ ባንዳኘችብን፣ ምኞቹ የለም። ይኼ ገጽ እንዴት እንደሚጠቀሙ መማማሪያውን በታማኝነት መኖር እና ለደገፉ ተቀባይተዋል። ስንክሳሩ እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች ጌሩ።

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

19 Feb, 15:24


🌹✞ ስንክሳር የካቲት 13 ✞🌹

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡

❖ የካቲት 13 ቀን የሚከበሩ
     ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

🌿+*" ማር ፊቅጦር "*+🌿

ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን በደማቸውና በገድላቸው ያስጌጡ ብዙ ሰማዕታት አሉ:: ነገር ግን ከኮከብም ኮከብ ይበልጣልና ማን እንደ ጊዮርጊስና እስጢፋኖስ! ከእነርሱ ቀጥለው ከሚጠሩ ሰማዕታት ደግሞ አንዱና ዋነኛው ቤተ ክርስቲያን "ማር" የምትለው ቅዱስ ፊቅጦር ነው::

እስኪ ከበዛው መዓዛ-ገድሉ ጥቂት እንካፈል:-
+ቅዱስ ፊቅጦር አባቱ ኅርማኖስ ይባላል:: አረማዊና ጨካኝ ነው:: እናቱ ግን የተመሰገች ቅድስት ማርታ ትባላለች:: ልጇን እንደሚገባ አሳድጋው 20 ዓመት ሲሞላው የአንጾኪያ ንጉሥ የሠራዊት አለቃና በመንግሥቱ 3ኛ አድርጐ ሾመው::

የድሮዋ አንጾኪያ (ሮም) እንደ ዛሬዋ አሜሪካ ዓለምን የተቆጣጠረች ሃገር ነበረች:: ቅዱስ ፊቅጦር ደም ግባቱ ያማረ: በጦርነትም ኃይለኛ ስለ ነበር ሁሉ ያከብሩት: ይወዱትም ነበር::

+እርሱ ግን ቀን ቀን ሲጾም: ነዳያንን ሲያበላ ይውል ነበር:: ሌሊት ደግሞ እኩሉን ሲጸልይና ሲሰግድ እኩሉን የእስረኞችን እግር ሲያጥብ ያድር ነበር:: ይህ ሁሉ ሲሆንኮ እርሱ የንጉሡ 3ኛ: የሠራዊትም አለቃ ነው:: በዘመኑ የሚያገድፍ ምግብና የወይን ጠጅ በአፉ ዙሮ አያውቅም::

+ከነገር ሁሉ በሁዋላ ንጉሡ ዲዮቅልጢያኖስ ካደ:: ዘመነ ሰማዕታትም ጀመረ:: አብያተ ክርስቲያናት ተቃጠሉ:: ከ47 ሚሊየን በላይ ክርስቲያኖች በመንኮራኩር ተፈጩ:: በመጋዝ ተተረተሩ:: ለአራዊት ተሰጡ:: በግፍም ተጨፈጨፉ:: ቀባሪ አጥተውም ወደቁ::

በዚሕ ጊዜ ማር ፊቅጦር እናቱን ቅድስት ማርታን በዕንባ ተሰናብቶ ወደ ንጉሡ ቀርቦ በክርስቶስ ስም ታመነ:: ክፉ አባትም በልጁ ላይ ሞትን መከረ::

ከዚያም ቅዱሱን አፉን በብረት ለጉመው ወደ ምድረ ግብፅ አወረዱት:: መሪያቸው እንዳልነበረ ወታደሮቹ መኩዋንንቱ ሁሉ ተዘባበቱበት:: እርሱ ከምድራዊ ንግሥና ሰማያዊ መንግስትን: በሰዎች ፊት ከመክበር ስለ ክርስቶስ ሲል መናቅን መርጧልና::

ለቀናት: ለወራትና ለዓመታት መኩዋንንቱ እየተፈራረቁ አሰቃዩት:: በርሱ ላይ ያልሞከሩት የስቃይ ዓይነት አልነበረም:: አካሉን ቆራርጠዋል: ዓይኖቹን አውጥተዋል: ምላሱንም ቆርጠዋል:: ሚያዝያ 27 ቀን ግን በሰይፍ አንገቱን ቆርጠውታል:: ስለዚህም እናት ቤተ ክርስቲያን በታላቅ ማክበር ታከብረዋለች::

❖እግዚአብሔርም ለቅዱስ ፊቅጦር እንዲህ አለው:- "እንደ አቅሙ ስምህን የጠራ: መታሠቢያህን ያደረገ: ስምህን ያከበረ: የብርሃን ልብስ አጐናጽፌ ወደ መንግስተ
ሰማያት አስገባዋለሁ::"

❖ይህች ቀን ማር ፊቅጦር የተወለደባት ናት፡፡ እናቱን ቅድስት ማርታ (ሶፍያንም) እናስባለን፡፡

❖ቸሩ አምላከ ፊቅጦር ሁላችንም ይማረን:: ከቃል ኪዳኑ አሳትፎ ለርስቱ ያብቃን::

✞ ቅዱስ አውሳብዮስ ካልዕ (ጥዑመ ዜና)✞

ቅዱስ አውሳብዮስ በወጣትነቱ ከተባረከች ሚስቱ ጋ በድንግልና የኖረ; በዘመኑ ባሕር ውስጥ ሰጥሞ ይጸልይ; 4,000 አቡነ ዘበሰማያት በአንድ ቀን ያደርስ የነበረ; ስለ ሃይማኖትም በቀስት የተወጋ; በእሳት የቃጠለ; አካሉን ቆራርጠው የጣሉትና እግዚአብሔር ከሞት ያስነሳው ጻድቅና ሰማዕት
ነው:: ከዚህ ሁሉ ነገር በኋላ ከነሥጋው ወደ ሰማይ
ተነጥቆ ለ14 ዓመታት ቆይቷል:: ወደ ምድርም ተመልሶ ለ40 ዓመታት በሐዋርያነት ከ85,000 በላይ አሕዛብን ወደ ሃይማኖት መልሷል::
ጌታም በስምህ የተማጸነውን እስከ 7 ትውልድ እምርልሃለሁ ብሎታል::"

❖አባቶቻችን ደግሞ 'ስም አጠራሩ የከበረ ዜና ሕይወቱ ያማረ' ሲሉ ይጠሩታል::

❖ ከበረከቱ ያድለን::

✞ የካቲት 13 ቀን የሚከበሩ
        ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱስ አውሳብዮስ ጻድቅ (ጥዑመ ዜና)
2.ቅዱስ ፊቅጦር ሰማዕት (ልደቱ)
3.ቅዱስ ሰርግዮስ ሰማዕት
4.ቅዱስ መፁን ቀሲስ
5.ቅዱስ ቴዎድሮስ ሰማዕት (የቅ/ፋሲለደስ ልጅ)
6.አባ ጢሞቴዎስ ሊቀ ዻዻሳት
7.አባ ክፍላ
8.አባ ኅብስ

     =>ወርኀዊ በዓላት
1.እግዚአብሔር አብ
2.ቅዱስ ሩፋኤል ሊቀ መላዕክት
3."99ኙ" ነገደ መላዕክት
4.ቅዱስ አስከናፍር
5."13ቱ" ግኁሳን አባቶች
6.ቅዱስ አርሳንዮስ ጠቢብ ገዳማዊ
7.አቡነ ዘርዐ ቡሩክ

=>+"+ እግዚአብሔር ቅዱሳንን ስላገለገላችሁ : እስከ አሁንም ስለምታገለግሏቸው ያደረጋችሁትን ሥራ : ለስሙም ያሳያችሁትን ፍቅር ይረሳ ዘንድ ዓመጸኛ አይደለምና:: በእምነትና በትእግስትም የተስፋውን ቃል የሚወርሱትን እንድትመስሉ እንጂ ዳተኞች እንዳትሆኑ ተስፋ እስኪሞላ ድረስ እያንዳንዳችሁ ያን ትጋት እስከ መጨረሻ እንድታሳዩ እንመኛለን::+"+ (ዕብ. 6:10-13)

🌹†††  ወስብሐት ለእግዚአብሔር  ††† 🌹
                    👇👇👇
በቴሌግራም ቻናላችን ይቀላቀሉና ቤተሰብ ይሁኑ
             https://t.me/Sinksar
             https://t.me/Sinksar
             https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

18 Feb, 20:13


† ስንክሳር የካቲት 12

እንኳን ለኢትዮዽያውያን ሰማዕታት ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን።

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

🌹† ኢትዮጲያውያን ሰማዕታት †🌹
በ1929 ዓ/ም: የካቲት 12 ቀን ከ30,000 በላይ ኢትዮዽያውያን አባቶች: እናቶች: ወጣቶችና ሕፃናት በሮማዊው የፋሽስት ጦር ደማቸው ፈሷል:: እነዚሕ ወገኖቻችን ደማቸው እንደ ጐርፍ አዲስ አበባ ላይ የፈሰሰው ስለ ሃገር ፍቅር ብቻ አልነበረም:: ስለ ቀናች ሃይማኖት ተዋሕዶ ጭምር ነው እንጂ::

ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ግፃዌ ላይ ስማቸውን ጽፋ በቅዱስ ዳዊት መዝሙር እንዲህ ታስባቸዋለች::

"አቤቱ አሕዛብ ወደ ርስትህ ገቡ::
የቅድስናህንም መቅደስ አረከሱ::
ኢየሩሳሌምንም እንደ መደብ አደረጉአት::
የባሪያዎችህንም በድኖች ለሰማይ ወፎች አደረጉ:: የጻድቃንህንም ሥጋ ለምድር አራዊት::
ደማቸውንም በኢየሩሳሌም ዙሪያ እንደ ውሃ አፈሰሱ:: የሚቀብራቸውም አጡ::"
(መዝ. 78:1)

††† ሰማዕታቱን እናስባቸው!

🌿† ሶምሶን ረዓይታዊ †🌿

እግዚአብሔር ሰማይንና ምድርን: 22ቱን ሥነ ፍጥረትን ፈጥሮ አዳምን ገዢ አደረገው:: አክሎም በነፍስ ሕያው አድርጐ: በመንፈስ ቅዱስ አክብሮ: ነቢይና ካህን አድርጐ: ካንዲት ዕፀ በለስ በቀር በፍጥረት ሁሉ ላይ አሰለጠነው::

አባታችን አዳም ግን ስሕተት አግኝቶት ከገነት ወጣ:: መከራና ፍዳም አገኘው:: በሁዋላም ለ100 ዓመት አልቅሶ ንስሃ ገባ:: ጌታም ንስሃውን ተቀብሎ "ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለሁ" የሚል ተስፋ ድህነትን ሰጠው::

ስለዚህም ምክንያት ለ5,500 ዓመታት ትንቢት ሲነገር: ሱባኤ ወደ ታች ሲቆጠር: ምሳሌም ሲመሰል ኖረ:: ከደግ ፍጥረት አዳም እስከ ኖኅ ድረስ: የሴት ልጆች እግዚአብሔርን በንጽሕና ሁነው በደብር ቅዱስ አመለኩ::

ትንሽ ቆይተው ግን ስለተቀላቀሉ ከቃየን ልጆች ጋር በማየ ድምሳሴ ጠፉ:: በጻድቅ ሰው ኖኅ የተጀመረው ትውልድም እግዚአብሔርን ለመዘንጋት ጊዜ አልፈጀበትም:: ነገር ግን ከሴም ዘር ቅንና ጻድቅ ሰው አብርሃም ተገኘ::

ከእርሱም ይስሐቅ: ከዚያም ያዕቆብ (ደጋጉ) ተገኙ:: ያዕቆብም "እሥራኤል" ተብሎ: በልጆቹ "ሕዝበ እግዚአብሔር" የተባለ ነገድ ተመሠረተ:: በተስፋይቱ ምድር በከነዓን እንዳይኖሩም ርሃብ ምድረ ግብጽ አወረዳቸው::

በዚያም ለ215 ዓመታት በጭንቅ የባርነትን ሕይወትን አሳለፉ:: እግዚአብሔርም ስለ ወዳጁ አብርሃም ሲል እሥራኤልን አሰባቸው:: የዋሕና ጻድቅ ሰው ሙሴን አስነስቶ እሥራኤልን ከግብጽ ባርነት አዳናቸው::

ይኸውም በጸናች እጅ: በበረታችም ክንድ: በ9 መቅሰፍት: በ10ኛ ሞተ በኩር: በ11ኛ ስጥመት ግብጻውያንን አጥፍቶ ነው:: በየመንገዱም ጠላቶቻቸውን እየተበቀለላቸው ነው:: ከዚህ ዘመን ጀምሮም እሥራኤል በመሳፍንትና በካህናት የሚተዳደሩ ሆኑ::

አስቀድሞ ሙሴ በምስፍና: አሮን በክህነት መሯቸው:: ቀጥሎም በቅዱስ ሙሴ ኢያሱ: በአሮን አልዓዛር ተተኩ:: እንዲህ እንዲህ እያለም ከኃያል ሰው ሶምሶን ረዓይታዊ ደረሱ:: ይኸውም ከዓለም ፍጥረት 4,200 ዓመታት በሁዋላ መሆኑ ነው::

በጊዜው እሥራኤል ጣዖትን እያመለኩ እግዚአብሔርን ስላሳዘኑት ለጠላቶቻቸው አሳልፎ ይሰጣቸው ነበር:: የአካባቢው መንግስታት እነ አሞን: አማሌቅ: ኢሎፍሊ ስንኩዋ ያኔ ዛሬም ቢሆን እንደምትመለከቱት ዶሮና ጥሬ ናቸው::

በጊዜውም የእሥራኤል ኃጢአት ስለ በዛ ኢሎፍላውያን (ፍልስጤማውያን) 40 ዓመት በባርነት ገዟቸው:: ንስሃ ሲገቡ ደግሞ ልጅ በማጣት ያዘኑ ማኑሄ እና ሚስቱ (እንትኩይ) : በቅዱስ ሚካኤል ተበሥረው ኃያሉን ሶምሶንን ወለዱላቸው::

እርሱም ናዝራዊ (ከእናቱ ማኅጸን ለጌታ የተለየ) ነበርና ፍልስጤማውያንን ቀጥቶ ወገኖቹን እስራኤልን ከባርነት : በአምላኩ ኃይል ታደገ:: ከኃይሉ ብዛት የተነሳም:-
¤አንበሳን እንደ ጠቦት ይገድል (መሣ. 14:5)
¤300 ቀበሮዎችን አባሮ ይይዝ (መሣ. 15:3)
¤በብርቱ ገመዶች ሲያስሩት እንደ ፈትል ይበጣጥሰው (መሣ. 15:14)
¤በአህያ መንጋጋ ሽህ ሰው ይገድል (መሣ. 15:15)
¤ጠባቂዎችን ከነ መቃናቸው ተሸክሞ ይወረውር ነበር:: (መሣ. 16:3)

ውሃ ሲጠማውም ከአህያ መንጋጋ ላይ ፈልቆለት ጠጥቷል:: (መሣ. 15:18) በፍጻሜው ግን ደሊላ በምትባል ሴት ተታልሎ ምሥጢሩን በመግለጡና ጸጉሩ በመላጨቱ ኃይሉን አጥቷል:: ጠላቶቹም ዐይኑን አውጥተው መዘባበቻ አድርገውታል::

በፍጻሜው ግን ኃይሉ እንዲመለስለት ፈጣሪውን ለምኖ : አሕዛብ ለጣኦት በዓል እንደተሰበሰቡ የአዳራሹን ምሰሶ አፍርሶ አጥፍቷቸው ዐርፏል:: (መሣ. 13--16)
ቅዱስ ሶምሶን የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጥላ (ምሳሌ) ነው::

††† በዘመኑ ሁሉ ቅዱስ ሚካኤል ረድቶታልና በዚህች ቀን መታሠቢያው ይደረግለታል::

††† የካቲት 12 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1."30,000" ሰማዕታተ ኢትዮዽያ (ሮማዊው ፋሽስት የገደላቸው)
2.ቅዱስ ሶምሶን ረዓይታዊ (የእስራኤል መስፍን)
3.ቅዱስ አባ ገላስዮስ ገዳማዊ
4.ቅድስት ዶርቃስ

††† ወርሐዊ በዓላት
1.ቅዱስ ሚካኤል ሊቀ መላዕክት
2.ቅዱስ ማቴዎስ ሐዋርያ
3.ቅዱስ ድሜጥሮስ
4.ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ
5.ቅዱስ ቴዎድሮስ ምሥራቃዊ (ሰማዕት)
6.ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ
7.አቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ
8.ቅዱስ ላሊበላ ጻድቅ

††† አምላከ አበው ቅዱሳን መዓዛ ቅድስናቸውን ያሳድርብን:: ከበረከታቸውም ይክፈለን::

††† "ሶምሶንም:- 'ስለ ሁለቱ ዓይኖቼ ፍልስጥኤማውያንን አሁን እንድበቀል : እግዚአብሔር አምላክ ሆይ! እባክህ አስበኝ? አምላክ ሆይ! . . . እባክህ አበርታኝ?' ብሎ እግዚአብሔርን ጠራ:: . . . ሶምሶንም:- 'ከፍልስጤማውያን ጋር ልሙት' አለ:: ተጐንብሶም ምሰሶዎችን በሙሉ ኃይሉ ገፋ:: . . . በሞቱም የገደላቸው ሙታን በሕይወት ሳለ ከገደላቸው በዙ::"
(መሣ. 16:28)

††† "እንግዲህ ምን እላለሁ? ስለ ጌዴዎንና ስለ ባርቅ: ስለ ሶምሶንም: ስለ ዮፍታሔም: ስለ ዳዊትና ስለ ሳሙኤልም: ስለ ነቢያትም እንዳልተርክ ጊዜ ያጥርብኛልና:: እነርሱ በእምነት መንግሥታትን ድል ነሡ:: ጽድቅንም አደረጉ . . ." †††
(ዕብ. 11:32)

🌹†††  ወስብሐት ለእግዚአብሔር  ††† 🌹
                    👇👇👇
በቴሌግራም ቻናላችን ይቀላቀሉና ቤተሰብ ይሁኑ
             https://t.me/Sinksar
             https://t.me/Sinksar
             https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

18 Feb, 20:12


በቅዱሳት ገድላትና ድርሳናት ዙሪያ እንዲሁም በጥንተ አብሶ ዙሪያ

፩፦ እስካሁን በተመለከትኩት ገድላት አያስፈልጉም መወገድ አለባቸው የሚል ንግግርም ጽሑፍም ከኦርቶዶክሳውያን አልሰማሁም። ምክንያቱም ገድላትና ድርሳናት የወንጌል ትርጉሞች ናቸው። የቅዱሳን ሕይወት የሚታይ የሚዳሰስ የወንጌልን ቃል በተግባር የሚያሳይ ነውና።

፪፦ ነገር ግን በአንዳንድ ገድላትና ድርሳናት ውስጥ በተለያዩ ምክንያቶች ብዙ ስሕተቶች ሊገኝባቸው ይችላል። ይህ እንዳይፈጠር የሊቃውንት ጉባኤያችን ጠንክሮ ማዕከላዊ የቅዱሳት መጻሕፍት ኅትመት ቢኖረውና በዚያ ቢታተሙ መልካም ነው። ብሔርን ከብሔር የሚያጣሉ፣ ጥላቻን የሚያስተላልፉ ሐሳቦች በግል በሚታተሙት ገድላት ይስተዋላል።

፫፦ ለምሳሌ ቡና ይጠጣል ወይስ አይጠጣም የሚለው ክርክር ምንጩ ገድልና ድርሳን ነው። ለምሳሌ እኔ ከአምስት የገድላትና የድርሳናት መጻሕፍት ቡና እንደማይጠጣ የሚገልጽ አግኝቻለሁ። በተማርኩባቸው ጉባኤ ቤቶችና በየትኛውም የመጻሕፍት ትርጓሜ ጉባኤ ቤት ቡና አይጠጣም የሚለው ሐሳብ ተቀባይነት የለውም። ታዲያ ጉባኤ ቤቶች ይህንን ሐሳብ ቀጥታ የመቀበል ግዴታ አለባቸውን?

፬፦ ባለፈው መጋቤ ሐዲስ ኃይለ እግዚእ አሰፋ (የጠቅላይ ቤተክህነት የትምህርትና ሥልጠና ክፍል ኃላፊ) ማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት በነበረው ሥልጠና እንደማሳያ ብለው ብዙ የተአምረ ማርያም ቅጅዎችን እንዳዩ ገልጸውልን ነበር። እና በአንዱ የብራና ተአምረ ማርያም ቅጂ አጼ ቴዎድሮስን እጅግ በጣም አክፋፍቶ የሚገልጽ እንዳገኙ ገልጸውልን ነበር። አስተውሉ በአንዱ ቅጂ ነው የተገኘ እንጂ በሁሉ አይደለም። ትክክልነቱ ምን ያህል ነው? የሚለው ጥናት ይጠይቃል።

፭፦ ገድለ ዮሐንስ መጥምቅ ላይ ዮሐንስ አሥር ጊዜ ከተለያዩ እናቶችና አባቶች እንደተወለደ የሚገልጽ አግኝቻለሁ። ዮሐንስ መጀመሪያ የተወለደ ከአዳምና ከሔዋን ሲሆን ስሙም ያን ጊዜ "ሔና" ነበረ ይላል። ከዚያ በየዘመናቱ እየተወለደና መጨረሻ ላይ ከዘካርያስና ከኤልሳቤጥ ተወለደ ይላል። ይህ በአንድ ወቅት ደብረ ሊባኖስ ገዳም ግጭት ፈጥሮ ነበር። በወቅቱ በገዳሙ የነበሩት የንታ ብሩክ ይህ መስተካከል አለበት ሲሉ አንዳንድ ከመጻሕፍት ሩቅ የነበሩ ሰዎች ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር ስለሌለ እንዳለ እንቀበላለን አሉ። ነገሩ ግን ከቤተክርስቲያን አስተምህሮ አንጻር መመርመር አለበት። ይህ በአንዳንድ የገድለ ዮሐንስ መጥምቅ ቅጂዎች አይገኝም።

፮፦ ገድለ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ላይ እስከ ዕለተ ምጽአት የጎጃም ሕዝብ ይቅር እንደማይባል ይገልጻል። በሌሎች ገድሎችና ድርሳኖች ለምሳሌ በገድለ አቡነ ሰላማ፣ በድርሳነ ኡራኤል፣ በገድለ ተከሥተ ብርሃን፣ በገድለ አቡነ ዜና ማርቆስ ደግሞ እስከ ዕለተ ምጽአት ወልድ ዋሕድ በተዋሕዶ ከበረ ብለው እግዚአብሔርን የሚያመልኩና እግዚአብሔርም የሚወዳቸው በሃይማኖታቸውና በምግባራቸው የተመሰከረላቸው የጎጃም ሰዎች ናቸው ይላል። እና የትኛውን እንቀበለው? መመርመር አለበት። ራእየ ማርያም ላይ ሻን*ቅላ ለዘለዓለም እንደማይጸድቅ የሚናገር አለ። በእውነት ይህን እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት የተናገረችው? ከክርስቶስ የማዳን ሥራ ጋር አይጋጭም?

፯፦ እንደዚህ እርስ በእርሱ የሚጋጩ ጉዳዮች ገድላት ላይና ድርሳናት ላይ ይስተዋላሉ። ይህ በተለያየ ምክንያት ነው። አንዳንድ መምህራን ሚሲዮናውያን ኢትዮጵያውያንን ለማለያየት ያስገቧቸው ናቸው ይላሉ። ይህ ሁሉ ቢሆንም ገድላትና ድርሳናት የሚታረሙት እየታረሙ በማዕከላዊነት በጠቅላይ ቤተክህነት ቢታተሙ እነዚህን ችግሮች መቅረፍ ይቻላል።

፰፦ በጥንተ አብሶ ዙሪያ ለምሳሌ ማኅበረ ቅዱሳን ባሳተመው ሊቀ ጉባኤ አባ አበራ በጻፉት መጽሐፍ የሰው ልጅ ከጥንተ አብሶ የሚላቀቅ ሲጠመቅ ነው ይላሉ። ሌሎች ደግሞ ጥንተ አብሶ በክርስቶስ መሰቀል ተወግዷል። ከዚህ በኋላ ሰው ቢኮነን እንኳ ራሱ በሠራው ኃጢአት እንጂ በጥንተ አብሶ አይደለም ይላሉ። (በጉባኤ ቤቶች ያለው አስተምህሮ ይህኛው ነው። በክርስቶስ መስቀል የውርስ ኃጢአት ጠፍቷል የሚል ነው። የእኔም አቋም ይህ ነው)። ጥንተ አብሶ የሚለው የግእዝ ቃል ሲሆን የበደል መጀመሪያ ማለት ነው። ይኸውም አዳምና ሔዋን የሠሩት በደል ነው። ይህ በደል ለአዳምና ለሔዋን ብቻ ይነገራል። የእነርሱ የበደል ውጤት (መርገም) ከእነርሱ ወደሚወለዱት ልጆች ተላልፏል። ይህን ውጤቱን የውርስ ኃጢአት እንለዋለን። ቅድስት ድንግል ማርያም የውርስ ኃጢአት የለባትም። ቀደሰ ማኅደሮ ልዑል እንዲል ከማኅፀን ጀምሮ ራሱ እግዚአብሔር ጠብቋታልና።

፱፦ በሚዲያ ዞር ዞር ስል ሕዝቤ ለሁለት ተቧድኖ ይቧቀሳል። በሁለቱም ወገን ያለው በእመቤታችን ንጽሕናና ቅድስና ይስማማል። ጠቡ በቃላት ያለመግባባት ሆኖ አግኝቼዋለሁ። ሁሉም ጽንፍ ይዞ የአንዱ ደጋፊና የአንዱ ነቃፊ ሆኖ በየራሱ ትርጉም ክፉ ስም ይሰጣጣል እንጂ ቆም ብሎ አንዱ አንዱን ለማዳመጥ ጊዜ ቢሰጣጡ ተመሳሳይ አረዳድ ላይ ይደርሱ ነበር። አንዳንዱ ደግሞ ስለጉዳዩ የሚያውቀው ነገር የለም። ነገር ግን በደጋፊነትና በነቃፊነት ጎራ ይተራመሳል። የዚህ መፍትሔው ከፍ ያሉ ጉዳዮች ላይ ዝም ብሎ ማዳመጥ የተሻለ ነው።

፲፦ ወቅት እየጠበቁ የሚያከራክሩ ጉዳዮች አሁንም ብዙ አሉ። ለምሳሌ የልደት ጾም በዘመነ ዮሐንስ ህዳር 15 ይጀመራል ወይስ 14? ጥምቀት ሰኞ ሲውል ቅዳሜና እሑድ ይጾማል ወይስ እሑድ ብቻ የመሳሰሉ ጉዳዮች ይነሳሉ። (እነዚህን የጠቀስኳቸው ታዋቂ ስለሆኑ እንጂ ሌላም ቀኖናዊ ያልሆኑ ከፍ ያሉ ብዙ ጉዳዮች አሉ። ለጊዜው ከዚህ አልጠቅሳቸውም)። አሁን ዘመኑ የሚዲያ ስለሆነ ሁሉም የየራሱን አብነት እየያዘ ከሚወጋገዝ በማዕከላዊነት ሊቃውንት ተሰብስበው ወጥ የሆነ እይታ እንዲኖር ማድረግ ግድ ይላል። የሊቃውንት ጉባኤ ከዘመኑ መቅደም አለበት። EOTC Tv ከአሉባልታና ከጳጳሳት ውዳሴ ወጥቶ ዘመኑን የሚመጥንና ጥያቄዎችን ቀድሞ የመመለስ ሥራ ሊሠራ ይገባል።

ኦርቶዶክሳዊው መንገድ ጉዳይ ተኮር ነው። ክርስቶስ ኃጢአትን እንጂ ኃጢአተኛን አልጠላም ብሏል። ይህ ጉዳይን በጉዳይነቱ መሞገት እንደሚገባ ያስረዳናል። ሁሉም ሰው የቤተክርስቲያንን አስተምህሮ ከውስጥም ከውጭም ጠላቶች መጠበቅ አለበት። ሲጠብቅ ግን እውነትን መሠረት አድርጎ እንጂ በተሳሳተ ፍረጃ፣ ስምን በማጥፋት፣ በስድብ ሊሆን አይገባም።

©በትረ ማርያም አበባው

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

18 Feb, 06:51


🔔  ስንክሳር የካቲት 11🔔

††† እንኳን ለጻድቁ አባ አውሎግ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን።

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †††

🌿† አባ አውሎግ አንበሳዊ †🌿

👉 አባ አውሎግ ማለት:-
*ከቀደመው ዘመን ጻድቃን አንዱ::
*እንደ ገዳማውያን ፍፁም ባሕታዊ::
*እንደ ሐዋርያት ብዙ ሃገራትን በስብከተ ወንጌል ያሳመኑ::
*በግብፅና በሶርያ በርሃዎች ለ90 ዓመታት የተጋደሉ ጻድቅና ሐዋርያ ሲሆኑ የሚጉዋዙበትና የሚታዘዛቸው ግሩም አንበሳ ነበር::
*በዚህም አባ አውሎግ "አንበሳዊ" ስትል ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ትጠራቸዋለች::

አባ አውሎግ ከሚታወቁበት አገልግሎት አንዱ ስብከተ ወንጌል ነው:: ምንም እንኩዋ ገዳማዊ ቅዱስ ቢሆኑም ያላመኑትን ለማሳመን : ያመኑትንም ለማጽናት ተጋድለዋል::

እግዚአብሔር በሰጣቸው አናብስት በአንዱ ላይ ተጭነው (መዝ. 90) : በሌላኛው ላይ እቃቸውን አስቀምጠው በየአኅጉራቱ ከመምህራቸው ቅዱስ አውሎጊን ጋር ይዘዋወሩም ነበር:: የጌታ ቸርነት ሆኖም አናብስቱ የቅዱሳኑን ፈቃድ ሳይነገራቸው ያውቁ ነበር::

ሲርባቸውም ተግተው ይመግቧቸው ነበር:: እንዲያውም አንዴ ቅዱሳኑ እንደራባቸው አንዱ አንበሳ ሲያውቅ ከበርሐ ወደ ገበያ መንገድ ወጥቶ ተመለከተ:: በአህያ ላይ ልጁንና ስንቁን (ዳቦ) ጭኖ የሚሔድ ሽማግሌ ነበርና ዳቦውን አንስቶ ወስዶ ለእነ አባ አውሎግ ሰጣቸው::

ከድንጋጤ የተነሳም ሕጻኑ ሙቶ ነበርና ሽማግሌ አባቱ አዘነ:: አንበሳው ግን ሕጻኑንም ወደ ቅዱሳኑ ወስዶ አስረከበ:: ቅዱሳኑም ከሕብስቱ በመጠናቸው በልተው ቢባርኩት እንዳልተበላ ሆነ:: ሕጻኑንም ከሞት በጸሎታቸው አስነስተው ለአንበሳው ሰጥተውታል::

አንበሳውም ስንቁንና ልጁን ለአረጋዊው ሰጥቶት በደስታ ወደ ሃገሩ ተመልሷል:: ቅዱስ አባ አውሎግና መምህሩ አውሎጊን ከ90 ዓመታት በላይ በዘለቀ ተጋድሏቸው አጋንንትን ያሳፍሩ ዘንድ : ለጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ንጹሕ መስዋዕት ይሆኑለት ዘንድ በትጋት ኑረዋል::

¤ብዙ ተአምራትን ሠርተው ፈጣሪያቸውን አክብረዋል::
¤እንደ ሊቀ ነቢያት ቅዱስ ሙሴ ባሕር ከፍለዋል::
¤እንደ ቅዱሳን ሐዋርያት ሙት አንስተዋል:: ድውያንን ፈውሰዋል::
¤እንደ ቅዱስ ዳንኤል አናብስትን ገዝተዋል::
¤ይህች ቀን ዕለተ ዕረፍታቸው ናት::

🌹†††  ቅዱስ በላትያኖስ †††🌹

ይህ ቅዱስ ሐዋርያዊ ዻዻስ የቀድሞዋ ሮም ሊቀ ዻዻሳት ሲሆን ቸር : ትጉህና በጐ እረኛ ነበር:: መናፍቃንን ሲያርም : ምዕመናንን ሲመክር : ስለ መንጋው እንቅልፍ አጥቶ ኑሯል:: በፍጻሜውም በዚህች ቀን የሮም ንጉሥ ለ1 ዓመት አሰቃይቶ ገድሎታል:: ዕሴተ ኖሎትን (የእረኝነት ዋጋንም) ከጌታችን ተቀብሏል::

††† አምላከ አበው ቅዱሳን በመጽናታቸው ያጽናን:: ከበረከታቸውም ያድለን::

††† የካቲት 11 ቀን የሚከበሩ
      ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.አባ አውሎግ አንበሳዊ
2.አባ አውሎጊን ጻድቅ (የአባ አውሎግ መምሕር)
3.አባ በትራ (የጻድቁ አባ ስልዋኖስ ደቀ መዝሙር)
4.አባ በላትያኖስ ሰማዕት (የሮም ሊቀ ዻዻሳት የነበረ)
5.አባ አብርሃም ኤዺስ ቆዾስ
6.አባ መቃቢስ
7.አባ ኮንቲ

††† ወርሐዊ በዓላት
1.ቅዱስ ያሬድ ካህን
2.ቅዱስ ገላውዴዎስ ሰማዕት
3.ቅዱስ ፋሲለደስ ሰማዕት
4.ብፁዐን ኢያቄም እና ሐና
5.አቡነ ሐራ ድንግል ጻድቅ

††† "በቅዱሳንም ዘንድ ያለው የርስት ክብር ባለ ጠግነት ምን እንዲሆን ለምናምንም ከኁሉ የሚበልጥ የኃይሉ ታላቅነት ምን እንደሆነ ታውቁ ዘንድ ነው::" †††    (ኤፌ. 1:19)

🌹†††  ወስብሐት ለእግዚአብሔር  ††† 🌹
                    👇👇👇
በቴሌግራም ቻናላችን ይቀላቀሉና ቤተሰብ ይሁኑ
             https://t.me/Sinksar
             https://t.me/Sinksar
             https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

17 Feb, 07:58


ፖለቲካውን ሳይሆን ፍትሕን ሳስባት አዝናለሁ።
የአለም ፍትሕ እንዲህ ናትና ተወልደህ፣ አድገህባት አግብተህ ወልደህ ዘር ብትተካም ከቤትህ ውጣ ተሰደድ! በቃህ ከተባልክ በቃህ ነው።
ምክንያቱም ያለነው በመንፈሳዊው አለም ሳይሆን በዚህች በስግብግብ አለም ነውና።

መጨረሻችንን ያሳምርልን።

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

17 Feb, 07:04


በቅዱሳን ስያሜ ከፍተን የምንሰራው ግራ ሲገባን እዩትማ።

በእውነት የኛ ስምና ግብር ወዴት አለ?

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

17 Feb, 06:43


#በቃል_ለሚመጣ_በቃል፤ #በመጽሐፍ_ለሚመጣም በመጽሐፍ #ምላሽ_መስጠት ተገቢ ነው።

ይህን ለማድረግ የተቋቋሙ የሊቃውንት ጉባኤን የመሰሉ ስብስቦች ነበሩ ነገር ግን በቂ ምላሽ ሲሰጡ ዐናይም። ከ1950ዎቹ ጀምረን ስንመለከት ብዙዎቹ ሊቃውንት ምላሽ ሲሰጡ የነበረ በግላቸው ነው። እነመልአከ ብርሃን አድማሱ ጀምበሬ (መድሎተ አሚን፣ ኰኲሐ ሃይማኖት) እነ አለቃ አያሌው ታምሩ (መች ተለመደ እና ከተኩላ ዝምድና) ወዘተ መጥቀስ ይቻላል።

በዚህ ዘመንም ቢሆን ሊቃውንቱ በግላቸው ምላሽ መስጠት ይኖርባቸዋል። ዝምታ ሲበዛ የክሕደቱ ትምህርት እውነት እየመሰለ ምእመናንን ያውካልና አደራ አለባችሁ።

መጽሐፍ መጻፍና ማሳተም ውጣ ውረዱ ብዙ ነው። ቢሆንም እያንዳንዳችን የራሳችንን ድርሻ እንወጣ። መጽሐፉን ጻፉትና ይቀመጥ። አንድ ቀን የሚያሳትመው አይጠፋም። የችሎታችሁን ከሠራችሁ ከደሙ ንጹሕ ናችሁ።

በሚዲያው ላይ ያለውንም እዚያው ሚዲያው ላይ መልስ ስጡ። 24 ሰዓት የሚሠራው የቴሌቪዥን ጣቢያ ምን ይሠራል ከዚህ ውጭ? የዜና ቋንጣ ሊቀርብበት አይደለም የተከፈተ። አንድ ዝግጅት ወር ሙሉ እያሳዩ ሰውን ለማሰልቸት አይደለም የሳተላይት ክፍያ የሚከፈለው? ያስ ባይሆን ወጭ የማይጠይቁ በስልክ ብቻ የሚሠሩ ሚዲያዎች ላይስ ማስተማር አይቻልምን? እንደተቋም ሊታሰብበት የሚገባ ነው።

ማንም እየተነሣ ድንበር የሚያፈርስበት መሠረት የሚንድበት መሆን የለበትም።

ከዲ/ን መልካሙ በየነ ።

#ወደ_ምሥራቅ_እንመልከት

✝️ ⛪️◈◈⛪️ ✝️

#ንነጽር_አዳም_ወሔዋን_ወንለቡ

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

16 Feb, 22:36


ስንክሳር የካቲት 10

✞✞✞ በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ አምላክ አሜን። ✞✞✞

=>+"+ እንኩዋን ለቅዱሳን አባቶቻችን ቅዱስ ያዕቆብ ሐዋርያ: ቅዱስ ዮስጦስ ሰማዕትና አባ ኤስድሮስ ገዳማዊ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ +"+

"† ቅዱስ ያእቆብ †"

=>ቅዱስ ያዕቆብ (የእልፍዮስ ልጅ)
ከ12ቱ ሐዋርያት አንዱ (ማቴ.10:1) ብዙ አሕጉር አስተምሮ በዚህ ቀን በሰማዕትነት ወደ ፈጣሪው ሔዷል::

=>ቅዱስ ዮስጦስ በ3ኛው ክ/ዘመን መጨረሻ ምድራዊ የንግሥና ዙፋንን ንቆ በክርስቶስ ስም በሰማዕትነት ከሚስቱ ቅድስት ታውክልያና ከአንድ ልጁ ቅዱስ አቦሊ ጋር ሰማያዊ ክብርን ተቀዳጅቷል::

=>አባ ኤስድሮስ ግብፃዊ ሲሆኑ ሹመትን ጠልተው ፈርማ በሚባል ገዳም ለ60 ዓመታት በበርሃ ውስጥ ከ18,000 በላይ ድርሳናትን ፅፈዋል:: ይሕም በዓለም ታሪክ ብዙ መጻሕፍትን በመጻፍ ቀዳሚው ያደርጋቸዋል:: ከድርሳናቱ መካከል 2,000 ያህሉ ዛሬም ድረስ በግብፅ በርሃ ውስጥ ይገኛሉ::

=>ከስንክሳር

    †አባ ፌሎ †

በዚች ቀን የፋርስ ሀገር ኤጲስቆጶስ አባ ፌሎ በሰማእትነት አረፈ ። ይህንንም ቅዱስ ለእሳት እንዲሰዋ ለፀሀይም እንዲሰግድ የፋርስ ንጉስ አዘዘው እምቢ በአለውም ጊዜ ታላቅ ስቃይን አሰቃይቶ እራሱን በሰይፍ ቆረጠው በመንግስተ ሰማያት የሰማእትነትን አክሊል ተቀበለ ።
በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር።

† አባ ኤስድሮስ †

በዚችም እለት በገድል የተጠመደ ምሁር የሆነ የአለሙ ሁሉ መምህር አባ ኤስድርስ ፈርማ ከሚባል አገር አረፈ። የዚህም ቅዱስ ወላጆቹ በምስር አገር የከበሩ ባለፀጉች ናቸው።

ለእስክንድርያ ሊቃነ ጳጳሳትም አባ ቴዎድሮስና አባ ቄርሎስ ዘመዶች ናቸውከእርሱም በቀር ልጅ የላቸውም መንፈሳዊ ትምህርትን ሁሉ አስተማሩት ።

ግልፅ አድርጎ አጠናቸው ጠበቃቸውም ዳግመኛም የዮናናውያንን የፍልስፍና ትምህርት የከዋክብትን አካሄድና አለምን መዞራቸውን ተማረ በእውቀቱና በጥበቡም ከብዙዎች ከፍ ከፍ አለ በገድልም የተጠመደ ትሁትና የሚተጋ ሆነ።

በሀገሮችም ያለ ሰዎች ሰለርሱ በሰሙ ጊዜ በእስክንድርያ  አገር ላይ ሊቀ ጵጵስና ይሾመት ዘንድ ተማክረው ከኤጲስቆጶሳቱ ጋር ተስማሙ ። በሌሊትም ወጥቶ ሽሽ ወደ ፈረማ ገዳም ደርሶ በዚያ መነኮሰ።

ከዚያም ወጥቶ ወደ አንዲት አነስተኛ ዋሻ ገብቶ ብቻውን በወስጧ ብዙ ዘመናት ኖረ ብዙ ድርሳናትንና ተግሳፃትንም ደረሰ ከዕርሳቸውም ስለ ነገስታትና ስለ መኳንንት የደረሳቸው አሉ   የቤተ ክርስቲያንን መፃህፍቶችን ብሉያትና ሀዲሳትን ተረጉመ።

የመፅሀፍታቹም ቁጥራቸው አስራ ስምንት ሺህ ነው።  እነዚህም ድርሳናት ተግሳፃት ጥያቄዎችና መልሶች ወደ ሊቃነ ጳጳሳትና ኤጲስቆጶሳት የተላኩ መልእክቶች ናቸው። ወደ ምእመናንም ወንዞች ውኃዎችን እንደሚያፈልቁ እርሱ በመንፈስ ቅዱስ የሚያስፈልቃቸው ሆኗልና።

ይህንንም በጎ ስራውን ሲፈፅሙ መልካም ጉዞውንም አከናውኖ ወደ በጎ ሽምግልና ደርሶ እግዚአብሄርንም አግልግሎ በሰላም አረፈ።

=>የካቲት 10 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱስ ያዕቆብ ሐዋርያ (ወልደ እልፍዮስ)
2.ቅዱስ ዮስጦስ ሰማዕት
3.አባ ኤስድሮስ ጻድቅ (ዘሃገረ ፈርማ)
4.አባ ፌሎ ሰማዕት
5.ቅዱስ ስምዖን
6.ቅዱስ ኒቆላዎስ

=>ወርሐዊ በዓላት
1.ቅዱስ ዕፀ-መስቀል
2.ቅዱስ ናትናኤል ሐዋርያ
3.ቅዱስ ኒቆላዎስ ዘሃገረ ሜራ
4.ቅዱስ ቆስጠንጢኖስ ጻድቅ ንጉሥ
5.ቅድስት ዕሌኒ ንግስት
6.አቡነ መልክዐ ክርስቶስ

=>+"+ . . . ራሳቸውም ስለ እናንተ ሲያማልዱ በእናንተ ላይ ከሚሆነው: ከሚበልጠው ከእግዚአብሔር ጸጋ የተነሳ ይናፍቁዋቹሀል::
ስለማይነገር ስጦታው እግዚአብሔር ይመስገን:: +"+ (2ኛ ቆሮ. 9:14)

=>+"+ ለቅዱሳን እንደሚገባ ግን ዝሙትና ርኩሰት ሁሉ: ወይም መመኘት በእናንተ ዘንድ ከቶ አይሰማ:: +"+ (ኤፌ. 5:3)

🌹†††  ወስብሐት ለእግዚአብሔር  ††† 🌹
                    👇👇👇
በቴሌግራም ቻናላችን ይቀላቀሉና ቤተሰብ ይሁኑ
             https://t.me/Sinksar
             https://t.me/Sinksar
             https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

16 Feb, 18:23


ከላይኛው👆 ሀሳብ የቀጠለ
👇
ኹለተኛው ነጥቤ - የወንድሜን አኬን አካሄድ ማዕከል ያደረገ ይኾናል። ይኸውም በአንድ በኩል አንድን ነገር ለማስረዳት የሚገልጽበት መንገድ ጸነን ማለት ሲኾን በሌላ በኩል ተደጋጋሚ ጊዜ ያቀረባቸውን የስሕተት ትምህርቶችን የሚመለከት ነው። እኔ ከእርሱ ጋር በአካል በተደጋጋሚ ጊዜ ባወራን ጊዜ ያገኘኹትና እንደ ወንድም ደጋግሜ መክሬው ግን እስካሁን አቋም አድርጎ የያዛቸው የስሕተት ትምህርቶችን በቅደም ተከተል ላስቀምጥ፦

1) ነገረ ክርስቶስን በተመለከተ ያቀረበው ስሕተት ነው። ይኸውም ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋው ወራት አብን አምልኳል የሚለው አንደኛው ሲኾን ሌላኛው ካረገም በኋላ አኹን አብን ያመልካል ብዬ አምናለሁ ብሎኛል።

ይህን በተመለከተ እጅግ ስላስደነገጠኝ በጣም ለምኜዋለሁኝ። እባክህን ይህ ክሕደት ነው ተስተካከል ብዬዋለሁኝ በጓደኞቹ ፊት በጉዳዩ የምችለውን ኹሉ ለማለት ሞክሬያለሁኝ። እርሱ ግን ሚዲያ ላይ ከእንግዲህ ወዲህ አላነሣውም ቢኾንም ግን አቋሜ ነው ብሎኝ ነበር። ለዚህ ስሕተት መነሻ ያደረገውም ዮሐ 4፥21-22 ላይ ቅዱስ ቄርሎስ ያብራራውን እና አምብሮስ ዘሚላን ያለውን ነበር።

በአቅሜ ለማስረዳት ሞክሬ ነበር። ያልኩትን አሁን አሻሽሎት ከኾነ ተመስገን ነው የምለው። ካልሆነ ግን በፍቅርና ክርስቲያናዊ በኾነ መንገድ እንዲያስተካክል ተማኅጽኖዬን በትሕትና በአደባባይ አቀርባለሁኝ።

2) ለኢየሱስ ክርስቶስ ከተዋሕዶ በኋላ አብ አምላኩ ነው የሚል አንዲት አጠር ያለች ቪዲዮ ሠርቶ ያ ቪዲዮ በብዙዎች ዘንድ ውዝግብን ፈጥሮ እንደ ነበር አስተውሳለኹኝ።

ሙስሊሞችም አኬ ማለት ባልፈለገው መንገድ አጣመው ሲያራግቡት ነበር። ወንድማዊ በኾነ መንገድ በተደጋጋሚ ይህንም ጉዳይ በተመለከተ አውርተናል።
ቪዲዮውንም እንዲያጠፋ ጽኑ ልመናዬን ከተግሣጽ ጋር በአካል አቅርቤለታለሁኝ። ኋላ ሌሎች መምህራንም ኾነን ተሰብስበን መክረነው ያን ቪዲዮ እንዳጠፋ ነግሮኝ ነበር። አቋሙ ግን እንደ ጸና ቀጥሏል። አብ ለኢየሱስ ከተዋሕዶ በኋላም አምላኩ ነው ማለት ምን ማለት ነው? ሥግው ቃል አንድ ከኾነና ሥጋን በመዋሐዱ ምክንያት ሥግው ቃል ፍጡር ነው የማይባል ከኾነ እንዴት ለሥግው ቃል አብ አምላኩ ሊባል ይችላል? በመጻሕፍት አምላኩ የተባለውን በጥንቃቄ ኾነን ቃል የተዋሐደው ሥጋ ፍጡር መኾኑንና ከተዋሕዶም በኋላ ያ ሥጋ አለመለወጡን ለማስረዳት መኾኑን እንገልጻለን እንጂ ከተዋሕዶ በኋላ ቃል የተለየው ዕሩቀ መለኮት የኾነ ሥጋ እንዳለ አድርገን አናምንም።

    ወንድሜ አክሊል ግን "ቃል የተዋሐደው ሥጋ ስላልተለወጠ አሁንም ያንሳል" ብሎ እንደሚያምን ነግሮኝ ነበር። አምላኬም ያለው በሥጋው ነው፤ ሥጋው ያንሣልና ብሎኝ ነበር። ይህ ደግሞ ምንታዌ ነው።

ሥጋ ምንም እንኳን ፍጡርነቱን ባይለቅም ከተዋሕዶ በኋላ ከቃል ስለማይለይ ያንሣል አይባልም። ያንሣል የሚለውን ስሑት ትምህርት አባቶቻችን አውግዘዋል። አባ ጊዮርጊስ በመጽሐፈ ምሥጢር፤ ሊቃውንት በመዝገበ ሃይማኖት ይህ ትምህርት የልዮናውያን እንደ ኾነና በኛ ዘንድ ተቀባይነት እንደ ሌለው አንሥተዋል።

ሥጋው ያንሣል ማለት በአንድ በኩል ከመለኮቱ ተለይቷል የሚያሰኝ ሲኾን በሌላ በኩል ያመልካል እንጂ አይመለክም የሚያሰኝ ነው። ይህ ደግሞ ተቀባይነት የለውም። በቀጥታ ምንታዌን የሚያስረዳ ነውና ይልቅስ በአበው ትምህርት ያለው ሥጋ ያለመለያየት በተዋሕዶ ከቃል ጋር አንድ ስለ ኾነ ይመለካል የሚል ነው።

3) ከመ*ና*ፍ*ቃን ጋር ሲወያይ "ለሥግው ቃል አንድ ፈቃድ እንዳለው ነገር ግን የሥጋ ፈቃድ ለመለኮት ፈቃድ ለዘላለም ሲገዛ እንደሚኖር" በተደጋጋሚ ጊዜ አንሥቶ ስምቼዋለሁኝ።
ይህም የምሥራቅ ኦርቶዶክሶች ትምህርት ነው። እነርሱ ኹለት ፈቃድ አለ፤
አንዱ ገዥ (የመለኮት ፈቃድ)
ሌላኛው ተገዥ (የትስብእት ፈቃድ) ብለው ያምናሉ።
መነሻቸው የባሕርይ ተዋሕዶ ስለሌለ ከኹለት ባሕርይ ኹለት ፈቃድና ኹለት ግብር ይመነጫል የሚል አቋም ስላላቸው እንዲያ ብለው ያምናሉ።
እኛ ግን ከኹለት ፈቃድ የተገኘ አንድ ፈቃድ ብለን ስለምናምን በሥግው ቃል ውስጥ የምንከፋፍለው ፈቃድ የለም። ፈቃዱ ከኹለት የተገኘ አንድ ነው። ይሄ የመለኮት ይህ ደግሞ የትስብእት ተብሎ ተለያይቶ ፈጽሞ አይነገርም። ይህን አድማሱ ጀንበሬና በመድሎተ አሚን፤ አለቃ አያሌው መች ተለመደና ከተኩላ ዝምድና በሚል መጽሐፋቸው አንሥተውታል።

አንዳንድ ቅዱሳን ሊቃውንት በጥንቃቄ የሥጋ ፈቃድ እንዳልጠፋ ለማስረዳት ያነሡት እንጂ እንደ ኬልቄዶናውያን ከፋፍሎ አንዱ ገዥ ሌላው ተገዥ በሚያሰኝ መንገድ እንድንረዳ ለማድረግ ፈጽሞ አይደለም። 

4) "ቃል የተዋሐደው የጎሠቆለ ሰውነትን ነው" ብሎ አውርተንበት ነበር። ይህን የሚመስል አገላለጽ ያቀረቡ ሊቃውንትን ሐሳብ እንዴት መረዳት እንዳለብን አስረድቼው በጊዜው ከዲያቆን ብርሃኑ አድማስም ጋር እንዲያወሩ አድርጌ መ/ር ብርሃኑ በዚህ እና በእመቤታችን ጉዳይ (የጎሠቆለ ሰውነትን ለብሳለች አልለበሰችም በሚለው) ጽሑፍ ጽፎ በቴሌግራም ልኮለት ነበር።

እኔም ከመ/ር ብርሃኑ አስቀድሜ ተው አክሊል አካሄድህ ጥሩ አይደለም ብዬ ረዘም ያለ የማብራሪያ ጽሑፍ  ከዓመት ከስድስት ወር በፊት ልኬለት ነበር፤ በተጨማሪ መምህር ግርማ ባቱን ጉዳዩን ነግሬያቸው ተገናኝተው እንዲነጋገሩ አሳስቤ የላኩለትንም ጽሑፍ ለመምህር ግርማ አያይዤ ልኬ አሳይቼው ነበር።
ወንድሜ አክሊል ግን እስካሁን ከአቋሙ አልተንቀሳቀሰም።

ሌላውን ለጊዜው እንተውና እንዲህ ዓይነት መሠረታዊ ትምህርቶች ላይ ስሕተት ተፈጥሯል። እነዚህን ስሕተቶች ቢያርም መልካም ነው። እግዚአብሔር ወንድማችንን ከክፉ ነገር ኹሉ ይጠብቅልን። እንዲህ ዓይነት ስሕተቶችንም እንዲያርም እግዚአብሔር ኃይሉን ያድልልን።

ምናልባትም አሁን ላይ እነዚህን ስሕተቶቹን አርሟቸውም ሊኾን ይችላል። ከኾነም እጅግ ደስ የሚያሰኝ ነው። እንዲህ አላልኩም ቢል እንኳን ደስታዬ ወደር የለውም። ዋናው ጉዳይ መስተካከሉ ነውና። አኹንም አቋም ኾኖ የተያዘ ከኾነ ግን ትልቅ ችግር ነው።

ወንድም እኅቶቻችን ሆይ በአገልግሎት ተሠማርተን ላለነው ለኹላችንም ከወደዳችሁን ከልብ ጸልዩልን፤ ክፉ ሰይጣን ቀስ አድርጎ እንዳይጥለንና እንዳያጠፋን የእውነት የኾነ ልባዊ ጸሎት ያስፈልገናልና።

ፍቅራችሁን እኛን ሊያድንና ሊጠቅመን በሚችል መንገድ ግለጹ እንጂ ሊጎዳን በሚችል መንገድ አታድርጉት።

       ቸር ተመኘሁ
🙏 ቸር ሰንብቱ !

#ወደ_ምሥራቅ_እንመልከት

✝️       ⛪️◈◈⛪️         ✝️

Via #ንነጽር_አዳም_ወሔዋን_ወንለቡ።
🌹<  ወስብሐት ለእግዚአብሔር >🌹                             👇👇👇
በቴሌግራም ቻናላችን ይቀላቀሉና ቤተሰብ ይሁኑ
          https://t.me/Sinksar
          https://t.me/Sinksar
          https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

16 Feb, 18:16


#ስለ_ወንድማችን_አክሊል_አንዳንድ_ነገሮች!
#በመምህር_ዮሐንስ_ጌታቸው

ክፍል-፩-

በመጀመሪያ አክሊልን ያወኩት በቲክቶክ ሲያስተምርና ለመ*ና*ፍ*ቃን መልስ ሲሰጥ ነው። በዚህ ረገድ በጣም የሚበረታታ ሥራን ሠርቷል፤ እየሠራም ይገኛል። በሚያቀርባቸው የሃይማኖት ትምህርቶች በቲክቶክ የሚከታተሉትን በውጭም በሀገር ውስጥም ያሉ ብዙ ምእመናንን አጽንቷል፤ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት እንዲረዱ ረድቷቸዋል። ይህም ብቻ ሳይኾን በኑ*ፋ*ቄ እሳት የነደዱትን መ*ና*ፍ*ቃንንም ወደ ቤተ ክርስቲያን እንዲመለሱ የበኩሉን አስተዋጽዖ አበርክቷል፤ አሁንም እያበረከተ ይገኛል። ይህን አገልግሎቱን የተረዳ ሰው ይጸልይለታል፤ እግዚአብሔር ከክፉ እንዲጠብቀው ያስበዋል።

እንደሚታወቀው አንድ ሰው አንድ መልካም ሥራ ሊሠራ ሲነሣ ብዙ ፈተናዎች ሊገጥሙት እንደሚችል ግልጽ ነው። ይህ ፈተና በመጀመሪያ ከራስ የሚመነጭ ነው። ይኸውም ስለ ራስ ያለ ቦታና ደረጃ ለወጥ እያለ የመሄድ ፈተና ቀዳሚው ነው። ይህ በእንዲህ ዓይነት ትጉህ አገልግሎት ላይ ባሉ ኹሉም ላይ ማለት እስኪቻል ድረስ የሚመጣ ፈተና ነው። ይህን ፈተና ተፈታኞቹ አንዳንዴ ላይረዱት ኹሉ ይችላሉ፤ አደገኛ የሚያደርገው ደግሞ ይህ ነው። በሌላ በኩል ደግሞ በምናቀርበው ነገር የተደሰቱ አካላት የሚያቀርቡልን ገነን ያለ ምስጋናና አክብሮት ሌላው የሕይወት ፈተና ይኾናል። ከእነዚህ ጋር ተያይዞ ደግሞ የበጎ ነገር ኹሉ ጠላት የኾነ ሰይጣን የሚያመጣብን ሰወር ያለ ወይም ግልጽ የኾነ ፈተና ይኖራል። ይህን መረዳት ተገቢ ነው። እንግዲህ ይህን በአጭሩም ቢኾንም ከግምት ውስጥ በማስገባት በአገልግሎት ላይ ላሉ ወንድሞቻችን ልንጸልይና ከእኛ እንደ ክርስቲያን የሚጠበቅብንን ልናደርግ ይገባል።

ኹለተኛው ነጥብ
ይቀጥላል....

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

16 Feb, 15:56


ዜና አበው

አባቶቻችንን እንወቅ
በእርጅና ቤት ከዋሉ አበው አንዱ
ዛሬም በሕይወት መሐላችን ያሉ
ያላስተዋልናቸው መንፈሳዊ ጌጣችን።

የጻድቁ አቡነ አንበስ ወዳጅ
መምሕረ ትሕትና መፍቀሬ ሰብእ
መፍቀሬ ገዳማት ወመነኮሳት
የአፋር በረሐ የፍቅር አብነት

በሙስሊም ክርስቲያኑ እጅግ የተወደዱ
የሚደንቃችሁ እየደከሙ ሲመጡ አበው
ተሰብስበው አባታችን ምን አለዎት ቢሏቸው አልጋው የቤተክህነቱ ነው ከነብርድ ልብሱ እረ ቤት አለዎት ገንዘብስ ባንክ ቢባሉ ምናምኒት አልተገኘባቸውም የለም የኘላስቲክ ነጠላ ጫማ ነው የሚያወትሩት አዋሽ ሄዳችሁ የሰሩትን የአረጋውያንን መጦሪያ ብታዮ ትደመማላችሁ።!!!!!

ብጹእ አቡነ ዮናስ
የአፋር ሐገረ ስብከት ሊቀጳጳስ
የቅዱስ ሲኖዶስ አባል። ለደብረ ወገግ ገዳም መብራት ናቸው። ይኸን ታላቅ ቅዱስ መካን ለመርገጥ ከባድ ቢሆንም
ከአፋር ሕዝብ ጋር ባላቸው ፍቅር በመነጋገር ልጆቻቸውን ከቅዱሱ መካን በኪደተ እግር በረከት እንድንሳተፍ አድርገዋል።

በየደረሱበት የቅዱሳንን ተጋድሎ ይመሰክራሉ ። የደብረ አዘሎ የደብረ ወገግና የደብረ ኪሩብን ክብር ተናግረው አይጠግቡም።

በእድሜ በጤና እግዚአብሔር ይጠብቅልን።

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

16 Feb, 05:28


🕊 ስንክሳር የካቲት 09 🕊

እንኳን ለአባታችን ታላቁ ቅዱስ በርሱማ ሶርያዊ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን።

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

🌿† ታላቁ አባ በርሱማ †🌿

ታላቁ አባ በርሱማ በሶርያ ቤተ ክርስቲያን ምንኩስናና ገዳማዊ ሕይወትን ያስፋፋ አባት ነው::

በ5ኛው መቶ ክ/ዘመን ምድረ ሶርያን ጨምሮ በብዙ ቦታዎች የቅድስና ሕይወትን ያስፋፋው ቅዱስ በርሱማ ለቤተ ክርስቲያን ምሰሶ ከሆኑላት አበው አንዱ ነው:: እርሱ ከተጋድሎው ብዛት ለ54 ዓመታት ያለ እንቅልፍ ቆይቷል::

በእነዚህ ዘመናትም ግድግዳ ላይ ጠጋ ብሎ ከማረፉ በቀር መቀመጥን እንኩዋ አልመረጠም:: በመዓልትም በሌሊትም በፍቅር አብዝቶ ስለ ራሱና ስለ ሕዝቡ በመጸለዩ የብዙዎቹን ነፍስ ወደ ሕይወት ማርኩዋል::

ገዳማትን ከማስፋፋትና ደቀ መዛሙርትን ከማብዛቱ ባለፈ በስብከተ ወንጌልም የተመሰከረለት አባት ነበር::
በ431 ዓ/ም በኤፌሶን በተደረገው የቅዱሳን ጉባኤ ላይ ከተገኙ ሊቃውንትም አንዱ ነው:: በቅድስና ሕይወቱ የተገረመው የቁስጥንጥንያው ንጉሥ (ትንሹ ቴዎዶስዮስ) የንግሥና ቀለበቱን እና ማኅተሙን ሸልሞታል::

ቅዱሱም የዋዛ አልነበረምና በንጉሡ ማኅተም እያተመ "ተፋቀሩ" የሚሉ ብዙ አዋጆችን ወደ መላው ዓለም ልኩዋል:: በ451 ዓ/ም በኬልቄዶን 636 ሰነፍ ዻዻሳት ጉባኤ አድርገው አባ ዲዮርስቆሮስን እንደ ገደሉት ሲሰማም ወደ ቤተ መንግስት ሒዶ ከሃዲዎቹን (መርቅያንና ሚስቱ ብርክልያን) በአደባባይ ዘልፏቸዋል::

ስለ አዘነባቸውም ተቀስፈዋል:: ታላቁ ቅዱስ አባ በርሱማ ፀሐይን ማቆሙን ጨምሮ በርካታ ተአምራትን ሠርቶ በዚህች ቀን ዐርፏል::

🌹🌹 ቸር አምላኩ ከበረከቱ ይክፈለን::

የካቲት 9 ቀን የሚከበሩ
       ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.አባ በርሱማ ሶርያዊ (ለሶርያ መነኮሳት ኁሉ አባት)
2.አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ (ኢትዮዽያዊ) የመነኮሱበት በዓል
3.ቅዱስ ዻውሎስ ሶርያዊ (ሰማዕት)
4.ቅዱስ ዼጥሮስ ሰማዕት

==> ወርሐዊ በዓላት
1."318ቱ" ቅዱሳን ሊቃውንት (ርቱዐነ ሃይማኖት ዘኒቅያ)
2.የብሔረ ብፁዐን ጻድቃን
3.አባ መልከ ጼዴቅ ዘሚዳ (ኢትዮዽያዊ)
4.ቅዱስ ዞሲማስ ጻድቅ (ዓለመ ብፁዐንን ያየ አባት)

"ምን ይዤ ወደ እግዚአብሔር ፊት ልምጣና በልዑል አምላክ ፊት ልስገድ? የሚቃጠለውን መስዋዕትና የአንዱን ዓመት ጥጃ ይዤ በፊቱ ልምጣን? እግዚአብሔርስ በሺህ አውራ በጐች: ወይስ በእልፍ የዘይት ፈሳሾች ደስ ይለዋልን? . . . ሰው ሆይ! መልካሙን ነግሮሃል:: እግዚአብሔርም ከአንተ ዘንድ የሚሻው ምንድር ነው? ፍርድን ታደርግ ዘንድ: ምሕረትንም ትወድ ዘንድ: ከአምላክህም ጋር በትሕትና ትሔድ ዘንድ አይደለምን?"† (ሚክ. 6:6)

🌹<  ወስብሐት ለእግዚአብሔር >🌹                             👇👇👇
በቴሌግራም ቻናላችን ይቀላቀሉና ቤተሰብ ይሁኑ
          https://t.me/Sinksar
         https://t.me/Sinksar
          https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

15 Feb, 15:54


በቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን የጸሎት መጻሕፍት።

ከዓመት በፊት "ለጸሎት የሚያተጋው ሳጥን" በማለት በደ/ኃ/ቅ/ራጉኤል ቤተክርስቲያን መጠለያ በሳጥን የጸሎት መጻሕፍት እንደሚገኝ በፌስቡክ ገጹ Zekaryas Kiros ጽፎ ተደንቀን ነበር።

ዘኪ እንዳስረዳን "በቤተክርስቲያኑ በመጠለያ ምሰሶ ላይ ከእንጨት የተሰራ ሳጥን ላይ የጸሎት መጻሕፍት ተደርድረዋል።

ማንኛውም ለጸሎት የመጣ ሰው ከዚህ ሳጥን ላይ የጸሎት መጽሐፍ እያነሳ ይጸልያል።

ጸሎቱንም ከጨረሰ በኃላ የጸሎት መጽሐፉን ያገኘበት ቦታ ላይ ያስቀምጣል። ሌላ ከእግዚአብሔር ጋር በጸሎት ለመገናኘት የሚያስብ ሰው በተራው ያነሣና ይጸልያል።"

በቅዱስ ራጉኤል የሚገኘውን በመጠለያ የጸሎት መጻሕፍት የማስቀመጥ መልካም ሥራ አርአያ በማድረግ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ውሉደ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት የጸሎት መጻሕፍት በሚሰቀል ሳጥን አዘጋጅተው ምእመናን እንዲጠቀሙ እያደረጉ ነው።

ስለዚህ በቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን የጸሎት መጻሕፍት በመጠለያ ማግኘት ትችላላችሁ። ይህን መልካም ሥራ በሌሎች አጥቢያ ቤተክርስቲያን እንዲኖር ቢደረግ መልካም ነው።

ዮሴፍ ፍስሀ እንደፃፈው

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

15 Feb, 05:44


ዛሬም ስደት!

በጅማ ዞን በርካታ ክርስቲያኖች መሰደዳቸውና መኖርያ ቤታቸው መቃጠሉ ተገለጸ !

#Ethiopia | በጅማ ዞን ጌራ ወረዳ ዋላ ቀበሌ ቦሬ ከተማ በሚገኙ ከአንድ ሺህ በላይ በሆኑ በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ክርስቲያን አማኞች ላይ ባነጣጠር ጥቃት መኖርያ ቤቶቻቸው እንዲሁም የንግድ ሱቆቻቸውን ጨምሮ ንብረቶቻቸው ሙሉ በሙሉ መውደሙን ምንጮች በስልክ ተናግረዋል፡፡

የጥቃቱ መነሻ ምን እንደሆነ እስከ አሁን በውል ባይታወቅም ፤ ጥቃቱ ከትናንትና ወዲያ የካቲት 6 ቀን 2017 ዓ.ም ከማለዳው 12:00 ሰዓት ጀምሮ በተተኮሰ ጥይት የተጀመረ ሲሆን በቀበሌው የሚገኙ ስምንት አብያተ ክርስቲያናት ከፍተኛ ስጋት ላይ ናቸው ተብሏል።

ጉዳዩን ለማረጋጋት የሀገር መከላከያ ሠራዊትን እና የመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች በሥፍራው ቢገኙም ጥቃቱ እስከ አሁን እንዳልቆመና ወደ ሌላ ቀበሌ እየተዛወረ ነው ተብሏል። የአካባቢው ነዋሪዎችም ጥቃቱን ሸሽተው ወደ አጎራባች የደቡብ ክልሎች እየሄዱ እንደሚገኙም ተጠቁሟል፡፡

በጅማ ሀገረ ስብከት በአብያተ ክርስቲያናት እና በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ምዕመናን ላይ መሰል የእሳት ቃጠሎ አደጋ ሲደርስ ይህ የመጀመሪያ አለመሆኑ የሚታወስ ነው፡፡

ማኅበረ ቅዱሳን ብሮድካስት አገልግሎት

🌹<  ወስብሐት ለእግዚአብሔር >🌹                             👇👇👇
ይቀላቀሉና ቤተሰብ ይሁኑ
         https://t.me/Sinksar
          https://t.me/Sinksar
          https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

15 Feb, 05:34


🔔✞ ስንክሳር የካቲት 8 ✞🔔

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡

❖ እንኳን አደረሳችሁ ❖

❖ የካቲት 8 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

+" በዓለ ስምዖን "+

ቅዱስ መጽሐፍ እንደሚነግረን ጌታ በተወለደ በ40 ቀኑ ራሱ የሠራውን ሕግ ይፈፅም ዘንድ ወደ ቤተ መቅደስ ገብቷል:: እንደ ሥርዓቱም እናቱ ቅድስት ድንግል ማርያምና አገልጋዩዋ ቅዱስ ዮሴፍ አረጋዊ የርግብ ግልገሎችና ዋኖስ አቅርበዋል::

ለ284 ዓመታት የአዳኙን (የመሢሁን) መምጣት
ይጠብቅ የነበረው አረጋዊው ስምዖን በዚህች ዕለት ስላየውና ስለታቀፈው ዕለቱ በዓለ ስምዖን ይባላል:: (ሉቃ. 2:22) ከዘጠኙ
የጌታ ንዑሳን በዓላት አንዱ ነው::

ይሕስ እንደ ምን ነው ቢሉ:-

ከዓለም ፍጥረት በ5,200 ዓመታት (ማለትም
ከክርስቶስ ልደት 300 ዓመታት በፊት) በጥሊሞስ
የሚሉት ንጉሥ በግሪክ
ነገሠ::

በጊዜውም በኃይለኝነቱ ሁሉን አስገብሮት ነበርና
"ዓለሙን እንደ ሰም አቅልጬ: እንደ ገል ቀጥቅጬ ገዛሁት:: ምን የቀረኝ ነገር አለ?" ሲል ተናገረ:: ባሮቹም "አንድ ነገር ቀርቶሃል:: በምድረ እሥራኤል ጥበብን የተሞሉ 46 መጻሕፍት
አሉ:: እነርሱን አስተርጉም" አሉት::

ያን ጊዜ እሥራኤላውያንን አስገብሯቸው ነበርና 46ቱን የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ከ72 ምሑራን (ተርጉዋሚዎች) ጋር እንዲያመጡለት አዛዦቹን ላከ:: እነርሱም 46ቱን መጻሕፍተ ብሉይ ኪዳን ከ72 ምሑራን ጋር አመጡለት::

አይሁድ ክፋተኞች መሆናቸውን ሰምቷልና 36 ድንኩዋን አዘጋጅቶ: ጥንድ ጥንድ ሆነው እንዲሠሩ: ሲተረጉሙ እንዳይመካከሩ 36 ጠባቂዎችን ሾመባቸው:: ይህ ነገር ለጊዜው ከንጉሡ ቢመስልም ጥበቡ ግን ከእግዚአብሔር ነው::

ምንያቱም በጊዜ ሒደት መጻሕፍተ ብሉያት በአደጋ
እንደሚጠፉ ያውቃልና ሳይበረዙ ለሐዲስ ኪዳን
ክርስቲያኖች ለእኛ እንዲደርሱ ነው:: ስለዚህም ከክርስቶስ ልደት 284 ዓመት በፊት 46ቱም ሁሉም መጻሕፍት (ብሉያት) ከእብራይስጥ
ወደ ጽርዕ ልሳን በ70ው ሊቃናት አማካኝነት ተተረጐሙ:: (በእርግጥ ከዚያ አስቀድሞ መጻሕፍት (ብሉያት) ወደ ሃገራችን መምጣቸውና ወደ ግዕዝ ልሳን መተርጐማቸውን ሳንዘነጋ ማለት ነው)

ወደ ዋናው ጉዳያችን ስንመለስ ከ70ው ሊቃናት
መካከል በእድሜው አረጋዊ የሆነ (እንደ ትውፊቱ ከሆነ 216 ዓመት የሆነው) ስምዖን የሚሉት ምሑረ ኦሪት ነበር:: በፈቃደ እግዚአብሔር ለእርሱ መጽሐፈ ትንቢተ ኢሳይያስ ደርሶት
እየተረጐመ ምዕራፍ 7 ላይ ደረሰ::

ቁጥር 7 ላይ ሲደርስ ግን "ናሁ ድንግል ትጸንስ:
ወትወልድ ወልደ" የሚል አይቶ "አሁን እንኳን የአሕዛብ ንጉሥ የእሥራኤልስ ቢሆን ድንግል በድንግልና ጸንሳ ትወልዳለች ብለው እንዴት ያምነኛል!" ሲል አሰበ:: "በዚያውስ ላይ
ኢሳይያስ በምናሴ የተገደለው ስለዚህ አይደል!" ብሎ ቃሉን ሊለውጠው ወሰነ::

አመሻሽ ላይም 'ድንግል' የሚለውን 'ወለት-ሴት ልጅ' ብሎ ቀየረው:: እርሱ ሲያንቀላፋ ቅዱስ መልአክ ወርዶ 'ድንግል' ብሎ አስተካከለው:: ከእንቅልፉ ሲነቃ ግራ ተጋብቶ እንደ ገና ፍቆ ቀየረው::

አሁንም መልአኩ 'ድንግል' ሲል ቀየረበት:: 3 ጊዜ
እንዲህ ከሆነ በኋላ ግን መልአኩ ተገልጦ ገሰጸው:: በዚያውም ላይ "ይህችን ድንግልና መሲሑን ልጇን ሳታየውና ሳትታቀፈው
ሞትን አታይም" ብሎት ተሰወረው:: አረጋዊ ስምዖን ከዚያች ዕለት በኋላ የመድኅን ክርስቶስን መምጣት ሲጠብቅ ለ284 ዓመታት የአልጋ ቁራኛ ሁኖ ኖረ:: አካሉም አለቀ::

+ለስም አጠራሩ ስግደት የሚገባው አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሰው በሆነበት በዚያ ሰሞን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምና ቅዱስ ዮሴፍ አረጋዊ ወደ ቤተ መቅደስ ወጡ::

ሕግን የሠራ ጌታ እርሱ 'ፈጻሜ ሕግ' ይባል ዘንድ
የርግብ ግልገሎችን (ዋኖሶችን) ይዘው በተወለደ በ40 ቀኑ ወደ ቤተ መቅደስ አስገቡት:: በዚህች ቀንም ቅዱስ መልአክ መጥቶ ቅዱስ ስምዖንን ከአልጋው ቀሰቀሰው:: ተስፋ የሚያደርገው አዳኙ (መሲሑ) እንደ መጣም ነገረው::

+ይህን ጊዜ አረጋዊው አካሉ ታድሶ እንደ 30 ዓመት ወጣት እመር ብሎ ከአልጋው ተነሳ:: እንደ በቅሎ እየሠገረም ወደ መቅደስ ወጣ:: በዚያ መሲሑን (ፈጣሪውን) ሲመለከት እንደ እንቦሳ ዘለለ:: ቀረብ ብሎም ሕጻን ጌታን ከድንግል
እናቱ እጅ ተቀበለው::

ከደስታው ብዛት የተነሳም "ይእዜ ትስዕሮ ለገብርከ: በሰላም እግዚኦ በከመ አዘዝከ-አቤቱ ባሪያህን እንደ ቃልህ በሰላም አሰናብተው" ሲል ጸለየ:: ትንቢትንም ተናገረ:: በዚያችው
ዕለትም ዐርፎ ተቀበረ::

"+ ሐና ነቢይት +"+

ዳግመኛ በዚህች ቀን አረጋዊቷን ነቢይት ቅድስት ሐናን እናስባለን:: ይህች ቅድስት ትውልዷ ከነገደ አሴር ሲሆን አባቷ ፋኑኤል ይባላል:: በትውፊት ትምሕርት ሐና የተዳረችው በልጅነቷ (በ12 /15/ ዓመቷ) ነው:: ለ7 ዓመታት ከልጅነት ባሏ
ጋር ኖራ ዕድሜዋ 19 (22) ሲደርስ ሞተባት::

እንደ እሥራኤል ልማድ ሌላ እንድታገባ ብትጠየቅም 'እንቢ' ብላ መበለት ሆነች:: ራሷንም ለእግዚአብሔር አሳልፋ ሰጠች:: በቤተ መቅደስም ለ84 ዓመታት ለፈጣሪዋ ተገዛች:: ፈጽማ ትጸልይና ትጾም ነበርና በእነዚህ ሁሉ
ዓመታት ውጪውን አልተመለከተችም::

ለእርሷ 103 (106) ዓመት ሲሆን መድኃኒታችን ተወለደ:: በዚህች ቀን ወደ ቤተ መቅደስ ሲገባ ተመልክታም ጌታን ባረከች:: ደስ እያላትም ትንቢትን ተናገረች:: ወደ ቤቷ ገብታም ነፍሷን ሰጠች:: (ሉቃ. 2:36-38)

ቸሩ መድኃኒታችን ተርፎ ከሚቀረው ዘመን ዕድሜ
ለንስሃ: ዘመን ለፍሥሐ አይንሳን:: ከቅዱሳኑ በረከትም አይለየን::

✞የካቲት 8 ቀን የሚከበሩ
      ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ ስምዖን አረጋዊ
2.ቅድስት ሐና ነቢይት (የፋኑኤል ልጅ)
3.ቅድስት ዓመተ ክርስቶስ እግዝእት
4.አባ ኤልያስ ገዳማዊ (በትህትና ያጌጠ ቅዱስ ሰው)

❖አረጋዊ ስምዖንን ከድካም አልጋ ያነሳ አምላከ ቅዱሳን እኛንም ድካመ ነፍስን ከሚያመጣ የበደል ምኝታ በቸርነቱ ያንሳን::

🌹<  ወስብሐት ለእግዚአብሔር >🌹              👇👇👇
በቴሌግራም ቻናላችን ይቀላቀሉና ቤተሰብ ይሁኑ
             https://t.me/Sinksar
             https://t.me/Sinksar
             https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

13 Feb, 18:40


🌿 ስንክሳር የካቲት 7 🌿

† እንኳን ለጻድቁ አባታችን አባ አብዱልማዎስ ገዳማዊ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †

††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †††

† አባ አብዱልማዎስ ገዳማዊ †

† ጻድቁ ግብጻዊ ሲሆኑ በበርሃ ሰው ሳያዩ ለ70 ዓመታት በቅድስና ኑረዋል:: በጊዜውም እግዚአብሔር አባ አብዱልማዎስን ወደ አባ ዕብሎይ ልኳቸው ነበር:: ሁለቱ ተገናኝተው አብረው ለ3 ቀናት ሲቆዩ ቅዱስ መልአክ እየተገለጸ አጽናንቷቸዋል:: ከሥውራን ማኅበርም ተቀላቅለው ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ተቀብለዋል::

† አባ ዕብሎይ ሲያርፍ አንበሶች እያገዟቸው ቀብረዋቸዋል:: እርሳቸውም "እኔን የሚቀብረኝ ስጠኝ" ብለው ጸልየው ነበርና 3 ገዳማውያን መጥተውላቸዋል:: የካቲት 5 ቀን አባ ዕብሎይን ገንዘው ቀብረው በ3ኛው ቀን አርፈዋል::

† የጻድቁ ክብር ይደርብን።

† የካቲት 7 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.አባ አብዱልማዎስ ገዳማዊ
2.አባ ቴዎድሮስ ሊቀ ጳጳሳት
3.አባ እለ እስክንድሮስ ሊቀ ጳጳሳት
4.ቅዱስ አባዲር

† ወርኀዊ በዓላት
1.ሥሉስ ቅዱስ (አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ)
2.አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
3.አባ ሲኖዳ (የባሕታውያን አለቃ)
4.አባ ዳንኤል ዘገዳመ ሲሐት
5.አባ ባውላ ገዳማዊ
6.ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ
7.ቅዱስ አግናጥዮስ

† የአብ በረከት: የወልድ ፍቅር: የመንፈስ ቅዱስ አንድነት: የድንግል ማርያም ምልጃ: የቅዱሳኑ ፀጋ በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን::

† "ስለ ጽድቅ የሚሰደዱ ብጹዓን ናቸው:: መንግስተ ሰማያት የእነርሱ ናትና:: ሲነቅፉአችሁና ሲያሳድዷችሁ በእኔም ምክንያት ክፉውን ሁሉ በውሸት ሲናገሩባችሁ ብጹዓን ናችሁ:: ዋጋችሁ በሰማያት ታላቅ ነውና ደስ ይበላችሁ:: ሐሴትም አድርጉ::" (ማቴ. ፭፥፲)

🌹🌹†††  ወስብሐት ለእግዚአብሔር  ††† 🌹
                    👇👇👇
በቴሌግራም ቻናላችን ይቀላቀሉና ቤተሰብ ይሁኑ
             https://t.me/Sinksar
             https://t.me/Sinksar
             https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

13 Feb, 09:41


"ወንጌል ስለ ኢየሱስ ብቻ ነው" ያለ ማን ነው?
ተሳስቷል።

የፍቅሩና ቤዛነቱ ምስክር የኾኑ ቅዱሳትና ቅዱሳን መታሰቢያቸው በወንጌል እንዲጻፍ ያዘዘ እርሱ ራሱ ኢየሱስ ነውና።

በዝሙት የኖረች አንዲት ሴት ነበረች። ማርያም ዘናይን/ኀጥእት ትባላለች።
የጌታችን ክርስቶስን የእጁን ተአምራት አላየችም። የቃሉን ትምህርት አልሰማችም። እንደወትሮዋ በመስታወት ፊት ቆማ ስትኳኳል፥ ውበቷን የሚያጠፋ ሞት ትዝ አላት።
ይቅርታና ምሕረት ለማግኘት ወደ መሐሪው ጌታ ፈጥና ኼደች። በስምዖን ፈሪሳዊ ቤት አገኘችው።

"የረከሰ ነገርን የነካችኹ እጆቼ ሆይ፥
የጌታ ክርስቶስን እግር ትዳስሱ ዘንድ ታደላችኹ።" እያለች የጌታዋን እግር በዕንባ አጠበች።
ጌታችን ክርስቶስም "እምነትሽ አድኖሻል በሰላም ሂጂ አላት"

ደቀ መዛሙርቱንም እንዲህ ሲል አዘዛቸው።
“እውነት እላችኋለሁ፥ ይህ ወንጌል በዓለም ሁሉ በማናቸውም ስፍራ በሚሰበክበት እርስዋ ያደረገችው ደግሞ ለእርስዋ መታሰቢያ እንዲሆን ይነገራል።”
ማቴዎስ 26፥13
በሰላም ሂጂ ያላት ጌታ፥ ዛሬ የካቲት ስድስት ወደ ጻድቃን ከተማ ወሰዳት።

ይኽች ማርያም፥ የአልዐዛር እኅት ማርያም ወይም ማርያም መግደላዊት አይደለችም።
የኔታ ስሙር
🌹†  ወስብሐት ለእግዚአብሔር † 🌹
                    👇👇👇
        https://t.me/Sinksar
        https://t.me/Sinksar
        https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

12 Feb, 20:40


🌿† የካቲት 6 †🌿

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።

† እንኩዋን ለእናታችን "ቅድስት ማርያም እንተ ዕፍረት" እና "ቅዱስ አቡሊዲስ" ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ።

🙏+*" ቅድስት ማርያም "*+🙏

ቅድስት ማርያም እንተ ዕፍረት ቅዱስ መጽሐፍ እንደሚለን በስምዖን ቤት የመድኃኔ ዓለምን እግር በእንባዋ አጥባለች:: በፀጉሯም አብሳ የ300 ብር ሽቱ ቀብታዋለች:: ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም የቀደመ ኀጢአቷን ይቅር ብሎ ከ36ቱ ቅዱሳት አንስት ደምሯታል:: (ሉቃ. 7:36-50)

ስለዚህች ቅድስት ሙሉ ታሪክ:-

1.ትርጉዋሜ ወንጌልን
2.ተአምረ ኢየሱስን
3.ስንክሳርን እና
4.መጽሐፈ ግንዘትን በማንበብ ማግኘት ይቻላል::

እንት ዕፍረት (ባለ ሽቱዋ ማለት ነው) ማርያም መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሚያስተምርበት ዘመን (በዘመነ ስብከቱ) የነበረችና ይህ ቀረሽ የማይሏት ቆንጆ ሴት ነበረች:: ግን መልክ የመልካም ነገሮች ምንጭ ሲሆን አይታይም::

በመልካቸው ማማር የጠፉና ያጠፉ ብዙ ሴቶችን ዓለማችን አስተናግዳለች:: ከክሊዎፓትራ እስከ ዘመናችን "ሞዴል" ነን ባዮች : እግዚአብሔር የሰጣቸውን ጸጋ የሰይጣን መደሰቻ : የገሃነም መንገድ አድርገውት ማየት (መስማት) እጅግ ያሳዝናል::

በአንጻሩ ደግሞ ብዙዎችን ያስደመመ መልካቸውን ንቀው : ሰማያዊ ሙሽርነትን የመረጡትን ቅዱሳቱን:- አርሴማን : ቴክላን : ጤቅላን : መሪናን : ጣጡስን : ሔራኒን : ኢራኒን : አትናስያን : ሶፍያን : ኢላርያን . . . ስናስብ ደስ ይለናል:: ዛሬም ጌታ በሚያውቀው ብዙ እናቶቻችን (እህቶቻችንም) ተመሳሳዩን በጐ ጐዳና መርጠው እየተጉዋዙ መሆኑን እናውቃለን::

ቅድስት ማርያምም ከፈጣሪዋ በተሰጣት ቁንጅና ክፋትን ትሠራ ዘንድ ሰይጣን ሲያገብራት "እሺ" ብላ የእሱ ወጥመድ ልትሆን ተራመደች:: ለዘመናትም ዓይነ-ዘማ : ልበ-ስስ የሆኑ ወንዶችን ወደ ኃጢአት ጐዳና ማረከች::

ለመልኩዋ ከነበራች ስስት የተነሳም ቶሎ ቶሎ ራሷን በመጽሔት (መስታውት ማለት ነው) ትመለከት ነበር:: መቼም አምላካችን ለሁሉም የመዳን ቀን ጥሪ አለውና (የሚያስተውለው ቢገኝ) ለማርያም ጥሪውን ላከላት:: ጥሪው ግን በስብከት : በመዝሙር : በመጽሐፍ . . . አልነበረም::

እንዳስለመደች ውበቷን ለመመልከት መስታውት ፊት ቆማ የራሷን ጸጉር : ግንባር : ዐይን : አፍንጫ : ጥርስ . . . እየተመለከተች ተደመመች:: ወዲያው ግን ይህ አካል አፈር እንደሚበላው የሚያስብ ልቡና መንፈስ ቅዱስ አምጥቶባት በጣም አዘነች:: የመኖር ተስፋዋ እንዳይቆረጥ ደግሞ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ዜና ሰማች::

መወሰን ነበረባትና ከሞት ወደ ሕይወት : ከጨለማ ወደ ብርሃን ልትሔድ ቆረጠች:: በአምላኩዋ ፊት የሚቀርቡም 3 ስጦታዎችን አዘጋጀች:: ሰይጣን ሊያጣት አልፈለገምና ወደ ክርስቶስ እንዳትደርስስ ብዙ መሰናክልን ፈጠረባት:: ግን ውሳኔዋ የእውነት ነበርና እያሳፈረችው ወደ አምላኩዋ ገሰገሰች::

የስምዖን ዘለምጽ በረኞችም ሊያስቀሰሯት አልተቻላቸውም::
ወደ ውስጥ ዘልቃ የያዘችውን ሁሉ ለመድኃኒታችን ሰዋች::
1.ከውስጧ እንባዋን:
2.ከአካሏ ጸጉሯን:
3.ከንብረቷ ውድ የሆነውን ሽቱ አቀረበች::

ብዙ ወዳለችና ብዙ ኃጢአቷ ተሠርዮ ቅድስት እናታችን ሆነች:: ብዙ አዝማናትን ከሐዋርያት ጋር አገልግላም በዚህች ቀን ዐርፋለች::

🙏" ቅዱስ አቡሊዲስ መምህረ ኩሉ ዓለም "🙏

=>የዓለም ሁሉ መምህር:
¤ባለ ብዙ ድርሳንና ተግሣጽ:
¤የቤተ ክርስቲያን ምሰሶ:
¤38 ሕግጋትን የደነገገ:
¤ስለ ቀናች እምነት የተጋደለ:
¤መራራ ሞትን በደስታ የተቀበለ:
¤የቀደመችዋ ሮም ሊቀ ዻዻሳት የነበረና:
¤ሐዋርያትን የመሰለ አባት ነው::

በ2ኛው መቶ ክ/ዘመን መጨረሻ አካባቢ ያበራው ይሀን ኮከብ ካቶሊካውያን ክደውታል:: እነርሱ "አቡሊዲስ የሚባል ዻዻስ አልነበረም" ቢሉም ምክንያታቸው ግን ከሰይጣን ነው:: ሃይማኖታቸውን ከመለወጣቸው 250 ዓመታት በፊት ስለተናገረባቸውና አንድ ባሕርይን ስላስተማረ መሆኑን ዓለም ያውቃል::

አባታችን ቅዱስ አቡሊዲስ የተገደለ የካቲት 5 ሲሆን የካቲት 6 ሥጋው የተገኘበት ነው::

=>አምላከ ቅዱሳን ከቅድስት ማርያም ንስሃዋን : ከአባ አቡሊዲስ ምሥጢረ ቅድስናውን ያድለን::

=>የካቲት 6 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅድስት ማርያም እንተ ዕፍረት
2.የዓለም ኁሉ መምሕር ቅዱስ አቡሊዲስ (ብዙ መንፈሳዊ ድርሳናትን የደረሰ ሊቀ ዻዻስና ሰማዕት)
3.ቅዱሳን አቡቂርና ዮሐንስ (ሰማዕታት)
4.ቅድስት አትናስያና 3ቱ ሰማዕታት ልጆቿ (ቴዎድራ : ቴዎፍናና ቴዎዶክስያ)

=>ወርኀዊ በዓላት
1.ቅድስት ደብረ ቁስቁዋም
2.አባታችን አዳምና እናታችን ሔዋን
3.አባታችን ኖኅና እናታችን ሐይከል
4.ቅዱስ ኤልያስ ነቢይ
5.ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሣርያ
6.ቅዱስ ዮሴፍ አረጋዊ
7.ቅድስት ሰሎሜ
8.አባ አርከ ሥሉስ
9.አባ ጽጌ ድንግል
10.ቅድስት አርሴማ ድንግል

=>ከበረከተ ቅዱሳን ይክፈለን::

" . . . አንተ ራሴን ዘይት አልቀባኸኝም:: እርሷ ግን እግሬን ሽቱ ቀባች:: ስለዚህ እልሃለሁ : እጅግ ወዳለችና ብዙ ያለው ኃጢአቷ ተሰርዮላታል:: ጥቂት ግን የሚሰረይለት ጥቂት ይወዳል:: እርስዋንም:- 'ኃጢአትሽ ተሰርዮልሻል' አላት:: ከእርሱም ጋር በማዕድ ተቀምጠው የነበሩት በልባቸው:- 'ኃጢአትን እንኩዋ የሚያስተሰርይ ይህ ማነው' ይሉ ጀመር:: ሴቲቱንም:- 'እምነትሽ አድኖሻል: በሰላም ሒጂ' አላት:: " (ሉቃ. 7:46)

🌹†††  ወስብሐት ለእግዚአብሔር  ††† 🌹
                    👇👇👇
በቴሌግራም ቻናላችን ይቀላቀሉና ቤተሰብ ይሁኑ
             https://t.me/Sinksar
             https://t.me/Sinksar
             https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

12 Feb, 04:36


🌿 ስንክሳር የካቲት 5 🌿

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።

† እንኳን ለአባታችን "አባ ብሶይ ዼጥሮስ" እና "ቅዱስ ዕብሎይ" ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ †

🌿† አክርጵዮስ †🌿
በዚች ቀን የእስክንድሪያ አገር ሊቀ ጳጳሳት የከበረ አባት አክርጵዮስ አረፈ። እርሱም ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት አስረኛ ነው። ይህም አባት እግዚአብሄርን የሚፈራ ንፁህ ቅዱስ ነው ።

በእስክንድርያ አገርም ቄስ ሆኖ የሚያገለግል ነበር ከእርሱ በፊት የነበረ ሊቀ ጳጳሳት አባ ከላድያኖስ በአረፈ ጊዜ የእስክንድር አገር ህዝብና ኤጲስቆጶሳቱ መረጡት በወንጌላዊው ማርቆስ ወንበር ላይ ሊቀ ጵጵስና ሾሙት።

ከዚህም በኃላ እንደ ሀዋሪያት መልካም ጉዞን ተጓዘ የእግዚአብሄርን ሀይማኖት ህይወት የሆነ ህጉንም እያስተማረ ቅዱሳት መፅህፍትንም እያነበበላቸውና እያስተማራቸው መንጋዎቹን ይጠብቃቸው ነበር ሁል ጊዜም ይመለከታቸዋል አንድ የብር አላድን ወይም አንድ የወርቅ ዲናርን ጥሪት አላኖረም ከእለት ምግቡ ከቁርና ከሀሩር ስጋውን ከሚሸፈንበት ልብስ በቀር ምንም አላከማቸም። በዚህም ተጋድሎ አስራ ሁለት አመት ኑሮ ጌታችንንም አገልግሎ በሰላም አረፈ።

 🌿" ቅዱስ ዕብሎይ "🌿
አባ ዕብሎይ በቀደመ ሕይወቱ ለ40 ዓመታት በኀጢአት የኖረ: እግዚአብሔር ለንስሃ ሲጠራው "እሺ" ብሎ : ለ40 ዓመታት በንስሃ ሕይወት ተመላልሶ በበርሃ የተጋደለ: እንባው እንደጐርፍ ይፈስ የነበረ: አጋንንትንም ድል የነሳና ለፍሬ: ለትሩፋት የበቃ ቅዱስ አባት ነው:: እግዚአብሔርም ብዙ ቃል ኪዳን ገብቶለታል::

<< ባርያ ሆኖ ያለ ኀጢአት: ጌታ ሆኖ ያለ ምሕረት የለምና ይቅር በለን !! >> (የአባ ዕብሎይ የንስሃ ጸሎት)

🌿" አባ ብሶይ (ዼጥሮስ) "🌿
=>ብሶይ (ቢሾይ) በቤተ ክርስቲያን ታሪክ የተለመደ የቅዱሳን ስም ነው:: በተለይ በምድረ ግብ በዚህ ስም ሰማዕታትም : ጻድቃንም ተጠርተውበታል:: ከእነዚህ ቅዱሳን (ከገዳማውያኑ) አንዱ የሆነው አባ ብሶይም
(አንዳንዴ አባ ዼጥሮስም ይባላል) የዘመነ ጻድቃን ፍሬ ነው::

ቤተ ክርስቲያን የቅዱሳን ቤት ናት:: ያ ማለት ራሳቸውን ለክርስቶስ የለዩ ሰዎች ይኖሩባታል:: እነዚህ ሰዎች ከተለያየ ጐዳና እና ማንነት ሊመጡ ይችላሉ:: ቢያንስ ግን በንስሃ የታጠቡ መሆናቸው ወደ ተቀደሰው አንድነት እንዲገቡ ትልቅ መሠረት ይሆናቸዋል::

ቅዱሳንም አንዳንዶቹ ከእናታቸው ማኅጸን ሲመረጡ : ሌሎቹ ደግሞ ከኃጢአት ሕይወት የተመለሱ ሆነው ይታያሉ:: ደስ የሚለው ደግሞ በንስሃ ከታጠቡ በሁዋላ በፍጹም ልባቸው በመጋደላቸው እነሆ በሰማያዊ አክሊል ተከልለዋል::

አባ ብሶይ ዼጥሮስም ከኃጢአት ተመልሰው ለቅድስና ከበቁ ቀደምት አበው አንዱ ነው:: ቅዱሱ ተወልዶ ባደገባት ምድረ ግብጽ የታወቀ ሽፍታ : ዝሙተኛና ክፋቱ የተገለጠ ሰው ነበር:: ለብዙ ዘመናት በእንዲህ ካለ ግብሩ መላቀቅ ባይችል እግዚአብሔር ጥሪውን ላከለት::

የአምላካችን የጥሪ መንገዱ ብዙ ነውና ለእርሱ ደዌን ላከለት:: መቼም ወደድንም ጠላንም በሽታ ወደ እግዚአብሔር የሚያቀርብ ጥሩ ፈሊጥ (አጋጣሚ) ነው:: ዛሬም ቢሆን ዘለን : ዘለን ስንሰበርና የሐኪም መፍትሔ ሲጠፋ የግዳችን ወደ እግዚአብሔር ቤት (ወደ ጸበሉ)
እንቀርባለንና:: አምላካችን ስለዚህ ጥበቡ ይክበር ይመስገን::

ቅዱስ አባት ብሶይም በሽፍትነትና በኃጢአት ኑሮ ሳለ ለሞት የሚያበቃ ደዌ ደርሶበት የአልጋ ቁራኛ ሆነ:: ኃይሉም ደከመ:: በእንዲህ እያለም በራዕዩ ያየው ነገር ፍጹም አስደነገጠው:: መላእክት ነፍሱን ወስደው መካነ ኩነኔን ካሳዩት በኋላ አለቀሰ::

ይልቁን ሌቦችና ዝሙተኞችን ከ4 ሲቆራርጣቸው ስላየ ፈጽሞ አዘነ : ተጸጸተ:: ፈጣሪውንም ዕድሜ ለንስሃ እንዲሰጠው ተማጸነ:: ጌታንም "አምላኬ ሆይ! ከበሽታየ
ብታድነኝ : ዳግመኛ አልበድልህም:: ዓለምን ሁሉም ንቄ አገለግልሃለሁ" ሲል ተማጸነው::

እግዚአብሔርም ሰምቶት ፈጥኖ ፈወሰው:: አባ ብሶይም እንደ ቃሉ በፍጹም ልቡ ንስሃ ገብቶ መነነ:: በገዳመ አስቄጥስ (ግብጽ) ለ38 ዓመታት ሲኖር የላመ የጣመ በልቶ : ከሞቀ መኝታ ተኝቶ አያውቅም::

ሰውነቱን ይቀጣት ዘንድም እስከ 30 ቀን ያለ እህል ውሃ ይጾም ነበር:: በዘመኑ ሁሉም የሴት መልክን አላየም:: ንስሃን የሚወድ ጌታም ጸጋውን አብዝቶለት ብዙ ድርሳናትን ጽፏል:: የሚገርመው ደግሞ ከትህትናውና ቅድስናው የተነሳ የእያንዳንዱ ሰው ኃጢአት ተገልጦ ይታየው ነበር:: ቅዱሱ አባታችን ብሶይ ዼጥሮስ በንስሃና በቅድስና ሕይወት እንዲህ ተመላልሶ በዚህች ቀን ዐርፎ በገዳሙ ተቀብሯል:: የድካሙን ዋጋም አድልዎ ከሌለበት : ከእውነተኛው ፈራጅ ከመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተቀብሏል::

=>አምላከ ቅዱሳን ዕድሜ ለንስሃ : ዘመን ለፍስሐ አይንሳን:: ከክብረ ቅዱሳንም ያካፍለን . . . አሜን !!

=>የካቲት 5 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ አባ ዕብሎይ ገዳማዊ
2.ቅዱስ አባ ብሶይ ጻድቅ
3.አባ አክርዽዮስ
4."49" አረጋውያን ሰማዕታት (ፍልሠታቸው)
5.ቅዱስ አሞኒና ሚስቱ ቅድስት ሙስያ (የታላቁ ዕብሎይ ወላጆች)
6.አባ ኖብ ጻድቅ : መነሳንሱ ዘወርቅ

=>ወርሐዊ በዓላት
1.ቅዱስ ዼጥሮስ ሊቀ ሐዋርያት
2.ቅዱስ ዻውሎስ ሐዋርያ
3.አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ
4.ቅዱስ ዮሐኒ ኢትዮዽያዊ
5.ቅዱስ አሞኒ ዘናሒሶ

=>አምላክ በበረከታቸው ይባርከን::
"መቶ በግ ያለው : ከእነርሱም አንዱ ቢጠፋ ዘጠና ዘጠኙን በበርሃ ትቶ የጠፋውን እስኪያገኘው ድረስ ሊፈልገው የማይሔድ ከእናንተ ማን ነው? ባገኘውም ጊዜ ደስ ብሎት በጫንቃው ይሸከመዋል:: ወደ ቤትም በመጣ ጊዜ ወዳጆቹንና ጐረቤቶቹን በአንድነት ጠርቶ 'የጠፋውን በጌን አግኝቼዋለሁና ከእኔ ጋር ደስ ይበላችሁ' ይላቸዋል:: እላችሁአለሁ: እንዲሁ ንስሃ ከማያስፈልጋቸው ከዘጠና ዘጠኝ ጻድቃን ይልቅ ንስሃ በሚገባ በአንድ ኃጢአተኛ በሰማይ ደስታ ይሆናል:: +"+ (ሉቃ. 15:3-7)

🌹†  ወስብሐት ለእግዚአብሔር † 🌹
                    👇👇👇
በቴሌግራም ቻናላችን ይቀላቀሉና ቤተሰብ ይሁኑ
             https://t.me/Sinksar
             https://t.me/Sinksar
             https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

07 Feb, 14:25


🌹 ስንክሳር የካቲት 1 🌹

እንኳን ለተፍጻሜተ ሰማዕት ቅዱስ ዼጥሮስ እና ለ150ው ቅዱሳን ሊቃውንት ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን።

††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †††

††† ቅዱስ ዼጥሮስ ሰማዕት †††
            🌿🌿🌿
††† የቅዱሳን ሰማዕታት መነሻቸው ቅዱስ እስጢፋኖስ ሲሆን ፍጻሜአቸው ደግሞ ቅዱስ ዼጥሮስ ሊቀ ዻዻሳት ነው::

ይህ ቅዱስ የሚታወቀው "ተፍጻሜተ ሰማዕት (የሰማዕታት መጨረሻ)" በሚለው ስሙ ነው:: ይሕስ እንደ ምን ነው ቢሉ:-
የቅዱሱ ሃገረ ሙላዱ ግብጽ ናት:: ዘመኑም 3ኛው መቶ ክ/ዘመን ነው:: ወላጆቹ ካህን ቴዎድሮስና ቡርክት ሶፍያ ልጅ አጥተው ሐምሌ 5 ቀን ወደ ፈጣሪ ቢማጸኑ በራዕይ ዼጥሮስ ወዻውሎስ ተገልጠው ብሥራትን ለሶፍያ ነገሯት:: በወለደችው ጊዜም በራዕዩ መሠረት "ዼጥሮስ" አለችው::

ሰባት ዓመት በሆነው ጊዜም ለቤተ እግዚአብሔር ሰጥተው በሊቀ ዻዻሳቱ ቅዱስ ቴዎናስ እጅ አደገና በወጣትነቱ ሊቅ: ጥዑመ ቃልና በጐ ሰው ሆነ:: ዲቁናና ቅስናን ተሹሞ ሲያገለግል ቅዱስ ቴዎናስ በማረፉ ቅዱስ ዼጥሮስን የግብጽ 17ኛ ፓትርያርክ አድርገው ሾሙት::

ዘመኑ ደግሞ እጅግ ጭንቅ ነበር:: ክርስቲያኖች በተገኙበት ስለሚገደሉ: አብያተ ክርስቲያናትም ስለ ተቃጠሉ የቅዱሱ መከራ የበዛ ነበር:: ለ14 ዓመታት በፍጹም ትጋት ከመንጋው ጋር ተጨነቀ::

አርዮስን (ተማሪው ነበር) አውግዞ ለየው:: ከጌታ ጋርም ብዙ ጊዜ ተነጋገረ:: ብዙ ተአምራትንም ሠራ:: በዚህ ሁሉ ጊዜ አንድም ቀን በመንበረ ዽዽስናው ላይ አልተቀመጠም:: በሁዋላ ግን ጨካኙ ንጉሥ እንዲገደል አዘዘ::

ሕዝቡ "ከእሱ በፊት እኛን ግደሉን" በማለታቸው ሁከት እንዳይነሳ ቅዱስ ዼጥሮስ ተደብቆ ሔደና በፈቃዱ ለወታደሮች ተሰጠ:: በዚያች ሌሊትም የእርሱ ደም የግፍ ማብቂያ እንዲሆን እያለቀሰ ጮኸ:: ከሰማይም "አሜን! ይሁን!" የሚል ቃል መጣ:: ያን ጊዜ የእርሱ አንገት ተሰየፈ:: ዘመነ ሰማዕታትም አለፈ::

††† የቅዱሳንን ዝክር ከማንበብ ባለፈ በስማቸው መጸለይ (ዘፀ. 32:13): በምጽዋትም ማሰብ (ማቴ. 10:41) ይገባል::

††† የካቲት 1 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

1."150"ቅዱሳን ሊቃውንት ዻዻሳት (በቁስጥንጥንያ ተሠብሥበው መናፍቃንን ያወገዙበት: ትምሕርተ ቤተ ክርስቲያንን ያፀኑበት /ጉባዔ ቁስጥንጥንያ/ በ381 ዓ/ም::
ከወቅቱ ቅዱሳን ሊቃውንት እነዚህ ይጠቀሳሉ:-
*ቅዱስ ጐርጐርዮስ ዘኑሲስ
*ቅዱስ ጐርጐርዮስ ዘእንዚናዙ
*ቅዱስ ጢሞቴዎስ ዘአልቦ ጥሪት
*ቅዱስ ቄርሎስ ዘኢየሩሳሌም)
2.ቅዱስ ዼጥሮስ ተፍጻሜተ ሰማዕት (ቅዳሴ ቤቱ)
3.ታላቁ ቴዎዶስዮስ ጻድቅ (ንጉሠ ቁስጥንጥንያ)

††† ወርሐዊ በዓላት
1.ልደታ ለቅድስት ድንግል ማርያም እግዝእትነ
2.ቅዱስ በርተሎሜዎስ ሐዋርያ
3.ቅዱስ ሚልኪ ቁልዝማዊ
4.ቅዱስ ራጉኤል ሊቀ መላዕክት
5.ቅዱሳን ኢያቄም ወሐና

††† "ስለዚህ በገዛ ደሙ የዋጃትን የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያንን ትጠብቁአት ዘንድ መንፈስ ቅዱስ እናንተን ዻዻሳት አድርጎ ለሾመባት: ለመንጋው ሁሉና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ:: ከሄድሁ በሁዋላ ለመንጋው የማይራሩ ጨካኞች ተኩላዎች እንዲገቡባችሁ እኔ አውቃለሁ:: ስለዚህ 3 ዓመት ሌሊትና ቀን በእንባ እያንዳንዳችሁን ከመገሰጽ እንዳላቁዋረጥሁ እያሰባችሁ ትጉ::" †††
(ሐዋ. 20:28)

🌹 ††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር ††† 🌹
             https://t.me/Sinksar
             https://t.me/Sinksar
             https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

07 Feb, 14:25


🌿 ስንክሳር ጥር 30 🌿

††† እንኳን ለቅዱሳት አንስት ሶፍያ ወአዋልዲሃ: ኦርኒ ወማኅበራኒሃ እና ለሊቁ ቅዱስ ጐርጐርዮስ ነባቤ መለኮት ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †††

††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †††

††† ቅድስት ሶፍያና ልጆቿ †††

††† በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ታዋቂ ከሆኑ የእናቶቻችን ስሞች "ሶፍያ" ቀዳሚው ነው:: ቃሉ በጥሬው ሲተረጐም "ጥበብ (ጥበበ ክርስቶስ) Wisdom of God" ማለት ነው:: ከጻድቃንና ከሰማዕታት ወገን በዚህ ስም የተጠሩ እናቶች አሉ::

ከእነዚህ መካከል አንዷ የሆነችው በዕለቱ የምናስባት እናት ቁጥሯ ከሰማዕታት ነው:: ዋናው ዘመነ ሰማዕታት ከመጀመሩ በፊት የነበረችው ቅድስት ሶፍያ ከሕግ ትዳር 3 ሴቶች ልጆችን አፍርታለች::

ስማቸውንም:- ጲስጢስ (ሃይማኖት) : አላጲስ (ተስፋ) : አጋጲስ (ፍቅር) ስትል ሰይማቸዋለች:: እንደሚገባም በሥርዓቱ አሳድጋ እድሜአቸው 9 : 10 እና 12 ሲደርስ ለሰማያዊ ሙሽርነት አጭታቸዋለች::

በዘመኑ "ክርስቶስን ካዱ" የሚል መሪ ተነስቶ ነበርና ቅዱሳቱ በመድኃኒታችን አምነው : ጣዖትን ዘልፈው አንገታቸውን ሰጥተዋል:: ክብረ ሰማዕትን : ሃገረ ክርስቶስንም ወርሰዋል::

††† ቅድስት ኦርኒ ሰማዕት †††

††† "ኦርኒ" ማለት በምሥራቃውያን ልሳን "ሰላም" ማለት ነው:: ቅድስቲቱ አርበኛ የዘመነ ሐዋርያት የቤተ ክርስቲያን ፍሬ ስትሆን ተወልዳ ያደገችውም በቀድሞው የሮም ግዛት ውስጥ ነው::

ምንም ዛሬ ያለ ትውልድ ቢዘነጋት ቅድስት ኦርኒ ተወዳዳሪ የሌላት ሰማዕት : ሐዋርያዊት : ድንግል ናት:: እርሷ ውበቷን : ንግሥናዋን : ክብሯን : ሃብቷን : ወጣትነቷንና ያላትን ሁሉ ስለ ፍቅረ ክርስቶስ ሰውታለችና ክብርት ናት::

በ1ኛው መቶ ክ/ዘመን መጨረሻ አካባቢ ከሮም ቤተ መንግስት የተወለደችው ቅድስት ኦርኒ እስከ ወጣትነቷ ድረስ ክርስቶስን ልታውቀው አልተቻላትም ነበር:: ምክንያቱ ደግሞ ንጉሡ አባቷ ጣዖትን ማምለኩ ነበር::

ንግሥት እናቷ ምንም ክርስቲያን ብትሆንም ስለ ክርስትና ልትነግራት አልደፈረችም:: ይህን ብታደርግ የሚደርስባትን መከራ ታውቃለችና:: ግን ደግሞ ውስጥ ውስጡን ትጸልይላት ነበርና ፈጣሪ መንገዱን ሊከፍት ጀመረ::

መምለኬ ጣዖት አባቷ ሰው እንዳያያት ቤተ መንግስት ሠርቶ : 12 ሞግዚቶችን መድቦ ጣዖት ከፊቷ አቁሞ ለዘመናት ዘጋት:: የሚገርመው ግን መልኳን እንዳያይ በበር ሆኖ የሚያስተምራት ፈላስፋ ተቀጥሮ ነበርና የዚህ ሰው ማንነቱ ነው::

መምለኬ ክርስቶስ ደግ ሰው ነበርና ፈሊጥን ይሻላት ገባ:: በዚህ መካከል ቅድስት ኦርኒ ራዕይን ታያለች:: የቤቷ መስኮቶች ተከፍተው ሳሉ በስተምሥራቅ ነጭ ርግብ : የዘይት (የወይራ) ዝንጣፊ ይዛ ገብታ : ከማዕዷ ላይ ጥላው ወጣች::

እርሷን ተከትሎ ቁራ በምዕራብ ገባ:: እባቡን ማዕዷ ላይ ጣለው:: በ3ኛው ደግሞ ንስር ገብቶ አክሊል ትቶላት ወጣ:: ቅድስቲቱም እየገረማት አረጋዊ መምህሯን "ተርጉምልኝ" አለችው::

††† እርሱም:-
"•ርግብ=ጥበብ (መንፈስ ቅዱስ)
•ዘይት=ጥምቀት
•ቁራ=ክፉ ንጉሥ
•እባብ=መከራ
•ንስር=ድል ነሺነት (ልዑላዊነት)
•አክሊልም=ክብረ ሰማዕታት ነው" ብሎ ተርጉሞ : ክርስቲያን ሆና ይህ ሁሉ እንደሚደረግ ነግሮ ተሰናበታት::

እርሷም ስትጸልይ ቅዱስ መልአክ ተገልጦ አጽናናት:: ያጠምቃትና ያስተምራት ዘንድም ሐዋርያው ቅዱስ ጢሞቴዎስን ልኮላታል:: ሐዋርያውም የቤተ መንግስቱን ግድግዳ ሰንጥቆ ገብቶ : ለሰማያዊ ሙሽርነት የሚያበቃ ትምህርትና ጥምቀትን ሰጥቷት ሔዷል::

ቅድስት ኦርኒም የአባቷን ጣዖታት ቀጥቅጣ ሰብራ ከአባቷ ጋር ተጣላች:: እርሱም "እገድላታለሁ" ብሎ በእንስሳት ጅራት ላይ ጸጉሯን ሲያስር እንስሶቹ ደንብረው : እጁን ገንጥለው መሬት ላይ ጥለው ገደሉት:: ቅድስት ኦርኒ ግን ጸሎት አድርሳ አባቷን ከሞት አስነሳችው:: እጁንም ቀጠለችለት::

በዚህ ምክንያት በዚያች ዕለት ብቻ አባቷና 30,000 የከተማው አሕዛብ አምነው ተጠምቀዋል:: ቅድስት ኦርኒ ግን ኃይለ መንፈስ ቅዱስ ታጥቃ ክርስትናን ሰበከች:: ብዙም ተሰቃየች:: ንጉሡ ዳኬዎስ : ልጁና ሌሎች 2 ያህል ነገሥታት በእሳት : በአራዊት : በግርፋትና በጦር ፈትነዋታል::

እርሷ ግን ሁሉን በኃይለ ክርስቶስ ድል ነስታለች:: ሙታም የተነሳችበት ጊዜ አለ:: በመጨረሻም በዚህች ቀን ወደ ሰማያዊ ርስት (ገነት) ተመስጣለች:: በዘመነ ስብከቷ ካሳመነቻቸው ባሻገር 130,000 የሚያህሉ ሰዎች ለሰማዕትነት እንዲበቁም ምክንያት ሆናለች::

††† ቅዱስ ጐርጐርዮስ ታኦሎጐስ †††

††† ቅዱሱ:-
•የዘመነ ሊቃውንት ፍሬ:
•የእንዚናዙ ኤጲስ ቆጶስ:
•የቁስጥንጥንያ ፓትርያርክ:
•የጉባዔ ቁስጥንጥንያ (በ381 ዓ/ም) 3ኛ ሊቀ መንበር:
•ባለ ብዙ ድርሳን:
•የቂሣርያ (ቀጰዶቅያ) ኮከብ:
•ብሩህ ገዳማዊ:
•መልካም እረኛ የነበረ አባት ነው::
መጽሐፈ ቅዳሴውን ጨምሮ በጻፋቸው ብዙ መጻሕፍትና በስብከቱ ከሊቃውንት ወገን "ታኦ(ዎ)ሎጐስ" ተብሎ የተጠራ እርሱ ብቻ ነው:: ትርጉሙም በግዕዙ "ነባቤ መለኮት" ማለት ነው:: በአማርኛም "አንድነትን : ሦስትነትን የተናገረ (ያመሠጠረ) እንደ ማለት ነው:: ቅዱሱ ዛሬ ዕረፍቱ ነው::

††† አምላከ ቅዱሳን ከበረከታቸው ይክፈለን፡፡
በመጽናታቸውም ያጽናን፡፡

††† እንዲህ ኃጢአታችን ጽዋዑን ሞልቶ በተረፈበት በዚህ ዘመን አንዲት ሰዓትም ውድ የሆነች የንስሃ ዕድሜ ናት:: እግዚአብሔር ግን ደግ ነውና ይሔው ጥርን አስፈጸመን:: ባይገባን ነው እንጂ በዚሕች ወር ውስጥ ሚሊየኖች በደዌ የአልጋ ቁራኛ ሁነዋል::

ሚሊየኖችም ለንስሃ ሳይበቁ እንዲሁ አንቀላፍተዋል (ሙተዋል):: እስኪ እርሱ አምላካችን ቀሪውን ዘመን ደግሞ ለንስሃና ለመልካም ሥራ ባርኮ ይስጠን::

††† ወርኀ ጥርን በቸር ያስፈፀመ አምላከ ቅዱሳን ወርኀ የካቲትን እንዲባርክልን እንለምነው::

††† ጥር 30 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅድስት ሶፍያና ሦስቱ ሰማዕታት ልጆቿ (ጲስጢስ አላጲስና አጋጲስ)
2.ቅድስት ኦርኒ ሰማዕት ( (በ5 ነገሥታት እጅ የተሰቃየች : የሐዋርያው ጢሞቴዎስ ተከታይና ወደ ብሔረ ሕያዋን የተነጠቀች እናት)
3.ቅዱስ ጐርጐርዮስ ነባቤ መለኮት
4.አባ አክርስጥሮስ
5.አምስቱ ደናግል ሰማዕታት (ጤቅላ: ማርያ: ማርታ: አበያ: ዓመታ)
6.ጻድቃነ ዴጌ (የተሠወሩበት)
7.አባ ሚናስ ሊቀ ጳጳሳት
8."130,000" ሰማዕታት (የቅድስት ኦርኒ ማኅበር)

††† ወርኀዊ በዓላት
1.ቅዱስ ማርቆስ ዘአንበሳ
2.ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቀ መለኮት
3.አባ ሣሉሲ ክቡር

††† "ለእናንተም ጠጉርን በመሸረብና ወርቅን በማንጠልጠል ወይም ልብስን በመጐናጸፍ በውጭ የሆነ ሽልማት አይሁንላችሁ:: ነገር ግን በእግዚአብሔር ፊት ዋጋው እጅግ የከበረ የዋህና ዝግተኛ መንፈስ ያለውን የማይጠፋውን ልብስ ለብሶ የተሰወረ የልብ ሰው ይሁንላችሁ::" †††
(፩ጴጥ. ፫፥፫)


🌹 ††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር ††† 🌹
             https://t.me/Sinksar
             https://t.me/Sinksar
             https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

05 Feb, 19:29


🌿†  ስንክሳር  ጥር 29  † 🌿

እንኳን ለቅዱሳን ጻድቃነ ዴጌ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን።

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!.

        🌿††† ጻድቃነ ዴጌ †††🌿

እነዚህ ጻድቃን ኢትዮዽያውያን ባይሆኑም ያበሩት በሃገራችን ነው:: ቅዱሳኑ በቁጥር 3,000 : በዜግነት ሮማውያን ናቸው:: ከሺህ አዝማናት በፊት ከሮም ግዛት ተሰባስበው እንደ ተስዓቱ ቅዱሳን ወደ ኢትዮዽያ (አክሱም) መጥተዋል::

ቀጥለውም እዛው አካባቢ ወደሚገኝ ገዳም ገብተዋል:: ይህ ቦታ ለአክሱም ቅርብ ሲሆን በዘመነ ሐዋርያት የቅዱስ ማቴዎስ ወንጌላዊ በዓት ነበር:: የሐዋርያው በትረ መስቀልም እስካሁን አለች::

ጻድቃነ ዴጌ ሕጋቸው አንዲት : እርሷም ፍቅር ናት:: ለዘመናት በፍቅረ ክርስቶስ ታሥረው : ፍቅርን ለብሰው : በፍቅር ኑረዋል:: ሁሌም በ29 የጌታችንን ስም እየጠሩ ጽዋ ጠጥተዋል:: ስለ ፍቅራቸውም ጌታችን 3,001ኛ ሆኖ : ነዳይ መስሎ አብሯቸው ጠጥቷል::

በመጨረሻም 3ሺው በአንድነት ተሠውረዋል::

††† ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን:: እኛንም በወዳጆቹ ጸሎት ይማረን:: . . .አሜን!

ጥር 29 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

1.ጻድቃን ቅዱሳን ማሕበረ ዶጌ (ዴጌ ጻድቃን)
(አክሱም አካባቢ በቁጥር ወደ 3,000 ሲሆኑ ከመድኃኔ ዓለም ጋር ማሕበር ይጠጡ የነበሩና በአንድ ላይ የተሠወሩ ቅዱሳን ናቸው)
2.አባ ገብረ ናዝራዊ ዘቃውንት (ኢትዮዽያዊ)
3.ቅድስት አክሳኒ ፈላሲት
4.ቅዱስ ሰርያኮስ ሰማዕት
5.አባ እስጢፋኖስ ገዳማዊ
6.ከድሮዋ ሮም የተነሱ ቅዱሳት አንስት

††† ወርሐዊ በዓላት
1.ቅድስት አርሴማ ሰማዕት
2.ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ እናታችን
3.ቅዱስ ዼጥሮስ ተፍፃሜተ ሰማዕት
4.ቅዱስ ማርቆስ ዘቶርማቅ
5.ቅዱስ ዘርዐ ክርስቶስ

††† "ጻድቃን ምድርን ይወርሳሉ::
በእርስዋም ለዘለዓለም ይኖራሉ::
የጻድቅ አፍ ጥበብን ያስተምራል::
አንደበቱም ፍርድን ይናገራል::
የአምላኩ ሕግ በልቡ ውስጥ ነው::
በእርምጃውም አይሰናከልም::" †††
(መዝ. 36:29)

🌹 ††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር ††† 🌹
             https://t.me/Sinksar
             https://t.me/Sinksar
             https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

05 Feb, 16:37


የቤተ ክርስቲያን አገልጋይና የማኅበረ ቅዱሳን ባሕር ዳር ማእከል አባል የሆኑት የዶ/ር አንዱዓለም ዳኘ (ገብረ ጻድቅ) የመንፈሳዊ አገልግሎት አጭር ታሪክ
+     +     +

“ሕይወታችሁ የሆነ ክርስቶስ በሚገለጥበት በዚያን ጊዜ እናንተ ደግሞ ከእርሱ ጋር በክብር ትገለጣላችሁ።"
ቆላ. 3፥4

ከአባታቸው ከአቶ ዳኜ ጠብቀው እና ከእናታቸው ከወ/ሮ ደጌ ጥጉ ግንቦት 5 ቀን 1980 ዓ/ም በምዕራብ ጎጃም ዞን በጓጉሳ ወንበርማ ወረዳ ቡራፈር ቀበሌ የተወለዱት ዶ/ር አንዱዓለም ዳኜ በልጅነታቸው በቡሬ ከተማ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን በሰ/ት/ቤት በመማርና በማገልገል ተኮትኩተው ያደጉ እና በአባቶች የተቀርጹ በምግባራቸውና በትምህርት ትጋታቸው በምሳሌነት የሚጠቀሱ ዕንቁ ሰው ነበሩ።

ቀጥሎም በመደበኛው የአስኳላ ትምህርት አመርቂ ውጤት በማምጣት ወደ ጅማ ዩኒቨርስቲ አቅንተው ከዩኒቨርስቲው መደበኛ የሕክምና ትምህርታቸው ጎን ለጎን በጅማ ዩኒቨርሲቲ ግቢ ጉባኤ በመማርና በማገልገል ተግተዋል።

በ2005 ዓ/ም የመጀመሪያ የሕክምና ዶክትሬት ዲግሪያቸውን በእጅግ ከፍተኛ ማዕረግ የወርቅ ሜዳሊያና በዩኒቨርሲቲ ደረጃ የዋንጫ ተሸላሚ በመሆን የተመረቁት ዶ/ር አንዱዓለም ዳኘ የመማር ማስተማር እና የሚወዱትን የሕክምና አገልግሎት በባሕር ዳር ዩኒቨርስቲ አሐዱ ብለው ጀምረዋል።

በዚህ በባሕር ዳር ከተማ ቆይታቸው በማኅበረ ቅዱሳን ባሕር ዳር ማእከል አባል በመሆን በሙያቸው የጤና ቡድን አባል በመሆን ለበርካታ ገዳማት እና አብነት ት/ቤቶች ከሌሎች ወንድሞቻቸው ጋር በእግራቸው ተጉዘው ለበርካቶች ብርሃን እና ፈውሰ ሥጋን የሰጡ ዕንቁ የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን አገልጋይ ነበሩ።

ከፍተኛ የመማር ፍላጎትና በላቀ የሙያ ደረጃ ሕዝባቸውን ዘወትር ማገልገል የሚወዱት ዶ/ር አንዱዓለም ዳኘ የጀመሩትን የሕክምና ትምህርትና አገልግሎት የበለጠ በማጠናከር በ2011 ዓ/ም ከባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የቀዶ ሕክምና ስፔሻሊቲ እንዲሁም በ2016 ዓ/ም ደግሞ የጉበት፣ የሀሞት ከረጢት እና የቆሽት ሰብ ስፔሻሊቲ ትምህርታቸውን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ተከታትለው በአመርቂ ውጤት አጠናቀዋል።

ዶ/ር አንዷለም ዳኘ በተለያዩ የትምህርት እርከኖች ሲያልፉ በልዩ ልዪ የውጭ ሀገራት ማለትም በጀርመን፣ በእንግሊዝ፣ በህንድ፣ በደቡብ አፍሪካ እና በቱርክ ሥልጠናዎችን በመውሰድ ከፍተኛ ልምድ ያካበቱ ምሁር ነበሩ።

በሙያቸው ሀገር ካፈራቻቸው ዕንቁዎች መሀከል አንዱ የሆኑት ገብረ ጻድቅ በመንፈሳዊ ሕይወታቸው እና በቅድስት ቤተ ክርስቲያን አገልግሎት የተፈጠሩበትን ሰማያዊ ዓላማ የተረዱ ለአምላካቸው ለእግዚአብሔር የታመኑ ቅን፣ ታዛዥ እና አስተዋይ አገልጋይም ነበሩ።

ዶ/ር አንዱዓለም ሕይወታቸው እስከአለፈበት ዕለት ድረስ በማኀበረ ቅዱሳን ባሕር ዳር ማእከል የሰባታሚት ወረዳ ማእከል አባል ከመሆንና ልዩ ልዩ ተልእኮዎችን በመከወን ከማገልገል ባሻገር በባሕር ዳር ሀገረ ስብከት የአንቀጸ ምሕረት ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ምክትል ሊቀ መንበር በመሆን እያገለገሉ ነበር፡፡

ቅን፣ ትጉህ፣ ደግ እና ለሰው ሁሉ መልካም አሳቢ የሆኑት ገብረ ጻድቅ በታላቁ ደብረ ሮሐ ቅዱስ ላሊበላ ገዳም በ2006 ዓ/ም ከውድ ባለቤታቸው ከወ/ሮ ቤዛዊት ግርማ ጋር ጋብቻቸውን በሥርዓተ ተክሊል የፈፀሙ ሲሆን የስምንት ዓመትና የአምስት ወር ዕድሜ ያላቸው ሁለት ሴቶችና የአምስት ዓመት እድሜ ያለው አንድ ወንድ ልጅ አባት ናቸው።

ቤተሰባቸውን በፍቅር የሚንከባከቡ እጅግ የሚናፈቁ ተወዳጅ አባት እንደሆኑ የሚመሰከርላቸው ሩህሩህ የቤት ራስ ነበሩ::

ዶ/ር አንዱዓለም ዳኘ ትውልዱን በጥሩ ሥነ ምግባር ለመቅረጽ ሲተጉ፣ ወገናቸውን በቅንነት እና በታማኝነት በሙያቸው ሲያገለግሉ፣ በክርስትና ሕይወት የሚጠበቅባቸውን ሕይወት ጠብቀው መንፈሳዊ አገልግሎታቸውን እየፈፀሙ በ37 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል።

ሥርዓተ ቀብራቸውም ቤተሰቦቻቸው፣ የማኅበረ ቅዱሳን ባሕር ዳር ማእከል አባላት፣ የሥራ ባል ደረቦቻቸው፣ ተማሪዎቻቸው፣ ታካሚዎቻቸው እና ወዳጆቻችው በተገኙበት ጥር 25 ቀን 2017 ዓ/ም ከቀኑ 8፡00 ሰዓት በባሕር ዳር ከተማ በደብረ ሰላም ድባንቄ መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ተፈጽሟል።

ቃለ መሐላቸውን እንደጠበቁ በወጣትነት ዕድሜያቸው ዘርፈ ብዙ ሥራዎችንና መንፈሳዊ አገልግሎታቸውን በመፈጸም በጥዋቱ ወደ አምላካቸው የተጠሩትን የእኒህን ቅን ሰው ነፍስ ልዑል እግዚአብሔር በአባቶቻችን በአብርሃም፣ በይስሐቅ እና በያዕቆብ ቦታ በአጸደ ገነት ያሳርፍልን ዘንድ ጸሎታችን ነው።

ለጋ ልጆቻቸውንና ባለቤታቸውን በማገዝ ሁላችንም የእኅትነትና የወንድምነት ድርሻችንን አበክረን እንድንወጣ ስንል አደራ እንላለን።

ማኅበረ ቅዱሳን ባሕር ዳር ማእከል ለቤተሰቦቻቸውና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው ሁሉ መጽናናትን ይመኛል፡፡

🌷 ወስብሐት ለእግዚአብሔር 🌷
             https://t.me/Sinksar
             https://t.me/Sinksar
             https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

05 Feb, 15:58


ማንኛውም የሰው ልጅ ህይወት ያለምክንያት ስታልፍ ማየት በጣም ያማል የባስ ደሞ እንዲህ ቀን ከሌት በቅንነት በሥጋው ጥበብ ብቻ ሳይሆን በመንፈሳዊ ህይወቱ አገልጋይ ልብን ይዞ ከጊዜው በተለየ ከጓደኞቹ ከፍ ብሎ የሚያበራን ሻማ በወጣትነት ዘመኑ ከዚህ ዓለም መለየት ለቀሪዎቻችን እጅግ ያማል።

በእውነት ያማል! ያ ሆነ ይህ ወንድማችን በዚህ ዓለም ሳለ ኑሮውን እንደምንም ለመኖር ሲጀምር ተጠርቷል። እኛስ?
ለመሆኑ በዚህ ዓለም ለመኖር ምን ያህል ተዘጋጅተናል? ለወዲያኛውስ ቢሆን?
ንስሓ እንግባ!

የታመመች ሀገር የተጎሳቆለች
በሽታዋን ይዛ መድኃኒት ቀበረች 😥

ወንድማችን አንተ ብቻ አይደለህም የሞትከዉ እኛና ሃገር ናት የሞተችው 💔

ወንድማችን እዚህ ለመድረስ ብዙ አመታትን በትምህርት አሳልፏል ቀን ሌሊት ሳይል እንቅልፍ እረፍት መዝናናት ሳያምረዉ አጥንቷል.
በዚህች ምድር ለ37 አመት በተከፈለ መስዋዕትነት ገና መኖር መጀመሩ እኮ ነበር።
ስንት ህዝብ ነዉ በእሱ ለመታከም ወረፋ እየጠበቀ ያለዉ?
በአሁን ሰዓት ባለው የሀገሪቱ የጤና ባለሙያ/ስፔሻሊስት/ እና በሽተኛ ምጣኔ መሠረት አንድ ሰብ-ስፔሻሊስትን መግደል 20 ሚሊየን ህዝብ መግደል መሆኑን ገዳዯች አልገባቸዉም!
ምነው እንዲህ የተጨካከን? ሟቹ አንድ ግለሰብ ብቻኮ አይደለም ነገር ግን የህዝብ ሀብት እኮ ነዉ የሀገር ሀብት እኮ ነዉ 😥
በጣም ነዉ የሚያሳዝነው ነፍስህ በሰላም ትረፍ ዶክተር ወንድማችን!
😢😢😢💐

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

05 Feb, 03:20


🌿 ስንክሳር ጥር 28 🌿

† እንኳን ለጌታችን አማኑኤል ክርስቶስ ዓመታዊ የተአምር በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †

† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †

አምረ እግዚእ

† "ተአምር" የሚለውን ቃል በቁሙ "ምልክት" ብሎ መተርጐም ይቻላል:: መሠረታዊ መልዕክቱ ግን ነጮቹ በልሳናቸው Miracle የሚሉት ዓይነት ነው:: ከተፈጥሮ ሕግ ውጪ (በላይ): ከፍጡራንም ችሎታ የላቀ ነገር ሲሠራ (ሲፈጸም) ተአምር ይባላል::

ተአምር የእግዚአብሔር የባሕርይ ገንዘቡ ነው:: እርሱ ዓለምን ከመፍጠሩ ጀምሮ እያንዳንዷ ተግባሩ ለእኛ ተአምራት ናቸው:: ስለዚህም ነው "ኤልሻዳይ - ከሐሌ ኩሉ - ሁሉን ቻይ" እያልን የምንጠራው::

እግዚአብሔር ፍጡራኑን ይወዳልና እርሱ ለወደዳቸውና ደስ ላሰኙት ተአምራት ማድረግን ሰጥቷል:: በብሉይ ኪዳን እነ ሙሴ ባሕር ሲከፍሉ: መና ሲያዘንሙ: ውሃ ሲያፈልቁ (ኦሪትን ተመልከት) እነ ኤልያስ ሰማይን ሲለጉሙ: እሳትን ሲያዘንሙ: ሙታንን ሲያስነሱ (1 ነገሥት) እንደ ነበር ይታወቃል::

እንዲያውም በሙሉ መጽሐፍ ቅዱስ የተአምር መጽሐፍ ነው ብሎ ለመናገርም ያስደፍራል:: በሐዲስ ኪዳንም መድኃኒታችን ብዙ ተአምራትን ሠርቶ ለሐዋርያቱ የተአምራት ጸጋውን ሰጥቷቸዋል:: (ማቴ. 10:8, 17:20, ማር. 16:17, ሉቃ. 10:17, ዮሐ. 14:12)

እነርሱም በተሰጣቸው ሥልጣን ብዙ ተአምራትን ሠርተዋል:: (ሐዋ. 3:6, 5:1, 5:12, 8:6, 9:33-43, 14:8, 19:11)

❤️††† ተአምራተ እግዚእ †††❤️

† ጌታችን በመዋዕለ ስብከቱ ብዙ ተአምራትን ሰርቷል:: እያንዳንዱ ግን ቢጻፍ ዓለም ለራሷ ባልበቃች ነበር:: ከእነዚህ መካከልም አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመዋዕለ ሥጋዌው በዚህ ዕለት በ7 እንጀራ እና በጥቂት ዓሣ ሴቶችና ሕፃናትን ሳይጨምር 4,000 ሰዎችን በቸርነቱ አበርክቶ አጥግቡዋል:: ደቀ መዛሙርቱም 7 ቅርጫት ማዕድ አንስተዋል::

ጌታችን በከሃሊነቱ የተራቡትን ሲያጠግብ እንዲሁ አይደለም:: በጊዜው የነበሩ አይሁድ ጠማሞች ነበሩና እነሱን ምላሽ በሚያሳጣ መንገድ ነበር እንጂ:: አይሁድ ላለማመን ብዙ ጥረት ነበራቸውና::

በዚህ ዕለትም እንጀራውን አበርክቶ ሲያበላቸው:-
1.ጊዜው አመሻሽ ላይ ነበር:: ምክንያት:- ጧት ላይ ቢሆን ከቤታችን የበላነው ሳይጐድል ብለው ከማመን ይርቁ ነበርና::

2.ከውሃ ዳር አድርጐታል:: መታጠቢያ ብናጣ በደንብ ሳንበላ ቀረን እንዳይሉ::

3.ሳር የበዛበት ቦታ ላይ አድርጐታል:: ምክንያቱም መቀመጫ ብናጣ በደንብ ሳንበላ ቀረን እንዳይሉ::

4.ከከተማ አርቆ ምድረ በዳ ላይ አድርጐታል:: ያማ ባይሆን "ፈጣን: ፈጣን ደቀ መዛሙርቱ ተሯሩጠው እየገዙ አቀረቡለት" ባሉ ነበርና::

† ለመድኃኒታችን ክርስቶስ አምልኮና ምስጋና ይሁን!
አማኑኤል አምላካችን ጣዕመ ፍቅሩን ያሳድርብን::

† ጥር 28 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ ቀሌምንጦስ ሰማዕት (ስለ ሃይማኖት 7 ጊዜ ሙቶ የተነሳ, 7 አክሊል የወረደለት)
2.ቅዱስ አካውህ መነኮስ
3."800" ሰማዕታት
4.ቅዱስ ዮሴፍ አይሁዳዊ (የእመቤታችን ወዳጅ)
5.ቅድስት ሳቤላ

† ወርሐዊ በዓላት
1.አባቶቻችን አብርሃም: ይስሐቅና ያዕቆብ
2.ቅዱስ ቴዎድሮስ ሮማዊ
3.ቅዱስ እንድራኒቆስና አትናስያ
4.ቅድስት ዓመተ ክርስቶስ

† "ጌታ ኢየሱስም ደቀ መዛሙርቱን ጠርቶ:- ሕዝቡ ከእኔ ጋር እስከ አሁን ሦስት ቀን ውለዋልና የሚበሉት ስለ ሌላቸው አዝንላቸዋለሁ:: በመንገድም እንዳይዝሉ ጦማቸውን ላሰናብታቸው አልወድም' አላቸው:: ደቀ መዛሙርቱም:- 'ይህን ያህል ሕዝብ የሚያጠግብ ይህን ያህል እንጀራ በምድረ በዳ ከወዴት እናገኛለን?' አሉት:: ጌታ ኢየሱስም:- 'ስንት እንጀራ አላችሁ?' አላቸው:: እነርሱም:- 'ሰባት: ጥቂትም ትንሽ ዓሣ' አሉት::
ሕዝቡም በምድር ላይ እንዲቀመጡ አዘዘ:: ሰባቱንም እንጀራ: ዓሣውንም ይዞ አመሰገነ:: ቆርሶም ለደቀ መዛሙርቱ ሰጠ:: ደቀ መዛሙርቱም ለሕዝቡ:: ሁሉም በሉና ጠገቡ:: የተረፈውንም ቁርስራሽ ሰባት ቅርጫት ሙሉ አነሱ:: የበሉትም ከሴቶችና ከልጆች በቀር አራት ሺህ ወንዶች ነበሩ::" † (ማቴ. 15:32)

🌹 ††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር ††† 🌹
             https://t.me/Sinksar
             https://t.me/Sinksar
             https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

04 Feb, 17:29


👆ከላይኛው የቀጠለ
.
.
.
፭ አጥቢያ ላይ የሚገኙ ማኅበራት ቅዱስ ሲኖዶስ በአጸደው ደንብ መሰረት ባልተዋቀሩበት እና የማኅበራት ማስተባበሪው በሀገረ ስብከት ደረጃ ተዋቅሮ አፈጻጸማቸውን የሚከታተል በሌለበት ሰንበት ትምህርት ቤቶችን ለመፍረስ የሚያጋልጥ በመሆኑ እና ለግጭት የሚዳርግ ይኾናል።በመኾኑም ቤተክርስቲያን ላይ ሰላማዊ አገልግሎት እንዳይኖር ስለሚያደርግ

ከላይ በጠቀስናቸው ምክንያቶች እና ደንቡን በግልጽ ቀርቦ ውይይት ባልተደረገበት ሁኔታ ማኅበረ በኩራት ዘወንቅሸት ገብርኤል የሚባለውን አጥቢያ ቤ/ክያን ላይ እንዲንቀሳቀስ መፈቀዱ ትክክል ነው ብለን አናምንም ይህንን አስመልክቶ ጉዳዩን ከሀገረ ስብከቱ ኃላፊዎች እስከ ብፁዕነታቸው ጋር ተነጋግረን መፍትሄ ለማሰጠት አንድነቱ እየሰራ መሆኑን እንገልጻለን።

በባሕረዳር ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

04 Feb, 17:29


ሰሞኑን በባህርዳርና አከባቢዋ ሀገረስብከት ሰንበት ት/ት ቤቶችና ማኅበራት በተፈጠረ አለመግባባት ከባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የተሰጠ መግለጫ።

ሰሞኑን ማኅበረ በኩራት ዘወንቅሸት ቅዱስ ገብርኤል ማኅበር የሚባል ከጠቅላይ ቤተክህነት እውቅና ፈቃድ በማግኘት ጠቅላላ ማኅበር በሚል ስያሜ ተሰጦት ትብብር እንዲደርግላቸው በተገለጸው መሰረት ለመንበረ ስብሐት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ቤተክርስቲያን ሰበካ ጉባኤ ድጋፍ እንዲደረግላቸው በሚል የድጋፍ ደብዳቤ ባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ለአጥቢያ ቤተክርስትያኑ እንደጻፈ እና አጥቢያ ቤተክርስቲያኑ ደግሞ ከ8:00 እስከ 10:00 አዳራሹን እንዲጠቀሙበት የፈቀደ መሆኑን ተረድተናል።

ስለሆነም
፩ ባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ማኅበራት ማስተባበሪያ ባልተቋቋመበት እና ምንም አይነት የጋራ መግባባት ባልተደረገበት ሁኔታ

፪ ጠ.ቤተክህነት እውቅና ፈቃድ በማግኘት ጠቅላላ ማኅበር በሚል ስያሜ ለሚመጡም ሆነ ሌሎች እውቅና የሚሰጣቸው ማኅበራት መቀመጫቸው እና ሂደታቸው ምን ይምሰል በሚል ውይይት ባልተደረገበት

፫ ቀጥታ አጥቢያ ቤ/ክን እየሄዱ ከአንድ ማኅበር በላይ እንዲገቡ ማድረግ ሰ/ት/ቤቶች ላይ ያልተገባ ጫና የሚፈጥር በመሆኑ

፬ ሰንበት ትምህርት ቤቶች በቅዱስ ሲኖዶስ ጸድቆ እየተተገበረ የሚገኘውን የሥርዓተ ትምህርት አተገባበር ላይ የሰዓት ገደብ የሚያመጣ እና ሰንበት ትምህርት ቤቶች አደራሾችን በሰዓት ከፋፍለው የሚያስተምሩበትን ጊዜ የሚሻማ በመሆኑ

ይቀጥላል...
.
.
.
👇

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

04 Feb, 12:20


የተሰበረ ጽዋዕ
እዚኽ ፎቶ ውስጥ በአካል የማውቀው ዘማርያምን ብቻ ነው፡፡ ሌሎች ግን በማኅበራዊው ሚዲያ መልስ ሲሰጡና ሲጠይቁ አያቸዋለሁ እንጂ ፊት ለፊት ተገናኝተን አናውቅም፡፡በወንድሞቻችን ፊት ፕሮቴስታንት ሰባክያን ምላሳቸውን ሲተሳሰር ብዙ ጊዜ አይቻለኹ፡፡ ሌላ ጊዜ ደግሞ "ከኦርቶዶክስ ወንድሞች ጋር እንዳትከራከሩ" የሚል አዋጅ ሲያውጁ ሰምቻለኹ ጰንጤዎቹ፡፡
በአጭሩ፥ እኒኽ ወንድሞቻችን የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱሳን መላእክትና ሰዎችን ታመልካለች የሚለውን ፕሮቴስታንታዊ የድር ምሽግ ሲበጣጥሱ ተመልክቻለኹ፡፡ ከዐይን ያውጣችኹ አልላችኹም፡፡ ዐይንም ጆሮም ውስጥ ናችኹና፡፡
ጽንዑ ወኀይሉ፡፡ ለማለት ነው አመጣጤ፡፡
ከእኒኽ ወንድሞች መኻል አንዱ ወይም ኹሉም ሊሳሳቱ የሚችሉ ናቸው፡፡ የቀለም ሠረገላ የማያሰናክለው የለምና፡፡
ደግሞም እኔ እንኳ የሰማኋቸው የሚታረሙ ስሕተቶች አሉ፡፡የሚታረም ነገር ተገኘ ማለት ግን፥ ሙሉ እርሻው አረም ነውና አያስፈልግም የሚል ቧልት መናገር ግን ቅንነትና ወንድማዊ ፍቅር ይጎድለዋል፡፡
በአንድ ወቅት፦
አንድ እጅግ የተከበሩ ሊቅ ከአንዲት ሴት ጋር ድቀት አገኛቸው፡፡ እኒኽን ሊቅ ብዙ ሰው ያውቃቸዋል፡፡ በዚኽኛው ታሪክ ግን ሰፊው ሕዝብ ስለማያውቃቸው ስማቸውን ልለፈው፡፡
ይኽን ድቀታቸውን የሰማ ደብተራ አንድ ቀን ማሕሌት ውስጥ አገኛቸው ሊቁን፡፡"ደግሞ አንተ እዚኽ ምን ልታደርግ ገባኽ?"
ሲል በፍና ተሣልቆ አፌዘባቸው፡፡ እርሳቸውም "እኔኮ የተሰበርኩ ጽዋዕ ነኝ" ብለው አንጀት የሚበላ መልስ ሰጡት፡፡
የተሰበረ ጽዋዕ ሰባራ ስለኾነ አይጣልም፡፡ንዋይ ቅዱስ ነውና በክብር ከዕቃ ቤት ይቀመጣል እንጂ፡፡

እንደዚያ ደብተራ ለቤተክርስቲያን የቀናን እየመሰለን ጥቂት ሸራፋ ያገኘንባቸው ጽዋወችን ኹሉ አውጥተን እንጣል ማለት እጅግ የከፋ በደል ነው፡፡ክርስቶሳዊውን መንገድ የረሳ ነውና፡፡ "ድኅረ ተሰብረ አጽንዖ ለሰብእናነ ልሕኵት፥ ለብሓዊ ክርስቶስ በማየ ሐዲስ ጥምቀት" የምትል ድንቅ የንጉሥ ጉባኤ ቃና አለች፡፡ ግርድፍ ትርጉሟ፦ ገላ'ችን ከተሰበረ በኋላ ሸክላ ሠሪው ክርስቶስ በአዲስ የውኀ ጥምቀት እንደገና ሠራው፡፡ ማለት ነው፡፡ ቤተክርስቲያን ከጌታዋ የተማረችው የተሰበረን መጠገን ነው፡፡
ችግሩ፥ መጠገን እንደመስበር ቀላል አይደለም፡፡ ለመጠገን ዕውቀትና ቅንነት ያስፈልጋል፡፡ ለመስበር ግን ኦርቶዶክሳዊ የዘብነት ቀለም የተቀባች ምላስ በቂ ናት፡፡
ወንድሞች በጎ ሲሠሩ እናበርታ፡፡ሲስቱ እንክርዳድ ከስንዴ እየለየን በፍቅር እናርም፡፡አልታረምም የሚል ካለ ደግሞ የቤክርስቲያን ቱንቢ ያርመዋል፡፡እንደ ግለሰብእ እኔ ነኝ ቱንቢው ማለት ግን የስሕተት ስሕተት ነው፡፡

በየሚዲያው ሌሎች ጥሩ ወንድሞችም አሉ፡፡ ነገር ግን በልዩ ልዩ የቤተክርስቲያን አገልግሎት የተገለጡ ናቸውና ተውኳቸው፡፡

የኔታ ስሙር አላምረው
🌹† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †🌹
        https://t.me/Sinksar
        https://t.me/Sinksar
        https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

04 Feb, 04:33


🌿 ስንክሳር ጥር 27. 🌿

† እንኳን ለቅዱሳን ቅዱስ ኄኖክ: ቅዱስ ጢሞቴዎስ ሐዋርያ: ቅዱስ ሱርያል ሊቀ መላዕክት ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †

††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †††

††† ቅዱስ ኄኖክ †††

††† ቅዱስ መጽሐፍ እንደሚነግረን ቅዱስ ኄኖክ ከአዳም ሰባተኛ ትውልድ ነው:: አዳም: ሴት: ሔኖስ: ቃይናን: መላልኤል: ያሬድ ብለን ሰባተኛው ኄኖክ ነውና::

ቅዱሱ የማቱሳላ አባትም ነው:: አካሔዱን ከእግዚአብሔር ጋር በማድረጉም ሞትን ያላየ: ብሔረ ሕያዋን የገባ የመጀመሪያው ሰው ሁኗል:: ለአዳም ልጆችም ተስፋ ድኅነት እንዳለ ማሳያ ሁኗል:: "በአቤል አፍርሆሙ: ወበኄኖክ አንቅሆሙ" እንዳለ ሊቁ::

ቅዱስ ኄኖክ በ1486 ዓ/ዓ የመጀመሪያውን የቅዱስ መጽሐፍ ክፍል (መጽሐፈ ኄኖክን) ከመጻፉ ባሻገር በብዙ ሥፍራ በክብር ተጠቅሶ ይገኛል::

††† ቅዱስ ጢሞቴዎስ ሐዋርያ †††

††† ይህ ቅዱስ ሐዋርያ አንድ የቤተ ክርስቲያናችን መብራት ነው:: ወደ ክርስትና የመጣው በ40ዎቹ ዓ/ም አካባቢ ሲሆን አሳምኖ ለቅድስና ያበቃው ብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ ነው::

በጊዜውም በነበረው ትጋትና ተጋድሎ ፍሬ አፍርቷል:: ሆዱንም እጅግ ያመው ነበር:: ቅዱስ ጳውሎስ ሲጠራው "የምወድህ ልጄ" እያለ ነበር:: በኤፌሶንም ጵጵስናን ሹሞ 2 መልዕክታትን ልኮለታል:: ቅዱስ ጢሞቴዎስ ቤተ ክርስቲያንን ለብዙ ዘመናት አገልግሎ በሰማዕትነት ዐርፏል::
ዛሬ ሥጋው ከኤፌሶን ወደ ቁስጥንጥንያ የፈለሰበት ነው፡፡ ጊዜውም 330ዎቹ መጀመሪያ ላይ እንደሆነ ይታመናል፡፡

"መድኃኒታችን እግዚአብሔር: ተስፋችንም ኢየሱስ ክርስቶስ እንዳዘዘው ትእዛዝ የኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያ የሆነ ጳውሎስ: በእምነት እውነተኛ ልጄ ለሆነ ለጢሞቴዎስ::
ከእግዚአብሔር ከአባታችን: ከክርስቶስ ኢየሱስም ከጌታችን: ጸጋና ምሕረት: ሰላምም ይሁን . . ."
(፩ጢሞ. ፩፥፩)

††† ቅዱስ ሱርያል ሊቀ መላዕክት †††

††† ከታላላቅ ሊቃናት አንዱ የሆነው ቅዱስ ሱርያል ክብሩ ብዙ ቢሆንም ብዙ ምዕመናን አያውቁትም:: የመላእክት መዓርግ ሲነገር ሚካኤል: ገብርኤል: ሩፋኤል ብሎ ቀጥሎ የሚመጣው ሱርያል ነው::

በሦስቱ ሰማያት ካሉት ዘጠኙ ዓለመ መላእክት የአንዱ (የሥልጣናት) መሪ (አለቃ) ነው:: መልአኩ እጅግ ርሕሩሕ እና ተራዳኢ ነውና አንዘንጋው:: ለኖኅ መርከብን ያሳራው: ከጥፋት ውኃም ያዳነው ይህ ቅዱስ መልአክ ነው::

በገድለ ሰማዕታትም ላይ እንደተጠቀሰው የሰማዕታት ረዳትና አዳኝም ነው:: ቅዱስ ሱርያል በሌላ ስሙ "እሥራልዩ" ይባላል:: "የእሥራኤል ረዳት" እንደ ማለት:: ዛሬ ደግሞ የሊቀ መልአኩ ቅዳሴ ቤቱ ነው::

††† የይቅርታ ጌታ መድኃኔ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ አይተወን . . . አይጣለን!

††† ጥር 27 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ ኄኖክ ነቢይ (ወደ ብሔረ ሕያዋን ያረገበት)
2.ቅዱስ ጢሞቴዎስ ሐዋርያ (ፍልሠቱ)
3.ቅዱስ አባ ቢፋሞን ሰማዕት
4.ቅዱስ ሰራብዮን ሰማዕት
5.ቅዱስ ሱርያል ሊቀ መላዕክት (ከሰባቱ ሊቃናት አንዱ)

††† ወርኀዊ በዓላት
1.መድኃኔ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ
2.አቡነ መባዐ ጽዮን
3.አባ መቃርስ ርዕሰ መነኮሳት
4.ቅዱስ ገላውዴዎስ ሰማዕት (ንጉሠ ኢትዮጵያ)
5.ቅዱስ ፊቅጦር ሰማዕት
6.ቅዱስ ያዕቆብ ዘግሙድ

††† "የተጠራችሁለት ለዚህ ነው:: ክርስቶስ ደግሞ ፍለጋውን እንድትከተሉ ምሳሌ ትቶላችሁ ስለ እናንተ መከራን ተቀብሏልና:: እርሱም ኃጢአት አላደረገም:: ተንኮልም በአፉ አልተገኘበትም:: ሲሰድቡት መልሶ አልተሳደበም:: መከራንም ሲቀበል አልዛተም . . . እርሱ ራሱ በሥጋው ኃጢአታችንን በእንጨት ላይ ተሸከመ::" †††
(፩ጴጥ. ፪፥፳፩-፳፭)

🌹 ††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር ††† 🌹
        https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

03 Feb, 16:52


4 ወር ተፈረደባቸው‼️
በጥምቀት ሰሞን በቅዱስ ሚካኤል ታቦት
እያሾፉ እና እየቀለዱ በቲክ ቶክ ቪዲዮ ለቀው የነበሩት እነዚህ ሶስት የአምቦ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች:
1ኛ. ተማሪ ገመቹ ምትኩ
2ኛ. ተማሪ ካሳን አድቬንቸር
3ኛ. ተማሪ ጋዲሳ ኢቲና
ዛሬ በአምቦ ዳዳቻ ወረዳ ፍርድ ቤት ቀርበው የነበረ ሲሆን እያንዳንዳቸው በ4 ወር እስር እንዲቀጡ ተወስኗል።
[አዩዘሀበሻ]

ምንም እንኳን በዚህ የወጣትነት ዘመን ብዙ መስራት ሲኖርባቸው ያለ እድሜያቸው ከተራነት በታች ወርደው ለዚህ ቢዳረጉና መቀጣት ድረስ ቢደርሱም ለሌሎች ማስተማሪያነት የሆነውን ከማድነቅ ወደ ኋላ አንልም።

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

02 Feb, 17:26


🌿 ስንክሳር ጥር 26 🌿

† እንኳን ለቅዱሳን አርባ ዘጠኝ አረጋውያን ሰማዕታት ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †

† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †

† አረጋውያን ሰማዕታት †

† ሰማዕትነት በክርስትና ለሃይማኖት የሚከፈል የመጨረሻው ዋጋ (መስዋዕትነት) ነው:: ሰው ለፈጣሪው ሰውነቱን ሊያስገዛ: ሃብት ንብረቱን ሊሰጥ ይችላል:: ከስጦታ በላይ ታላቅ ስጦታ ግን ራስን አሳልፎ መስጠት ነው::

ራስን መስጠት በትዳርም ሆነ በምናኔ ውስጥ ይቻላል:: የመጨረሻ ደረጃው ግን ሰማዕትነት ነው:: "አማን መነኑ ሰማዕት ጣዕማ ለዝ ዓለም: ወተዓገሡ ሞተ መሪረ በእንተ መንግስተ ሰማያት" እንዳለው ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ ሰማዕትነት ማለት መራራውን ሞት ስለ ፍቅረ እግዚአብሔር ሲሉ መታገስ ነው::

እርሱ ቅሉ መድኃኒታችን ክርስቶስ የሰማይና የምድር ጌታ ሲሆን ኃፍረተ መስቀልን ታግሦ ሙቶልን የለ! በዓለም ያሉ ብዙ እምነቶች ስለ መግደል በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ያስተምራሉ:: ክርስትና ግን መሞትን እንጂ መግደልን የሚመለከት ሕግ የለውም::

እርሱ ባለቤቱ "ጠላቶቻችሁን ውደዱ: የሚረግሟችሁን መርቁ: ስለሚያሳድዷችሁ ጸልዩ" ብሎናልና:: (ማቴ. 5:44) ነገር ግን
ዕለት ዕለት ራሳችንን በሃይማኖትና በምግባር ካልኮተኮትነው ክርስትና በአንድ ጀምበር ፍጹም የሚኮንበት እምነት አይደለምና በፈተና መውደቅ ይመጣል::

በተለይ የዘመኑ ክርስቲያን ወጣቶች ልናስተውል ይገባናል:: የቀደሙ ሰማዕታት ዜና የሚነገረን እንድንጸና ነውና::

የእነዚህ ሰማዕታት ቁጥራቸው 49 ሲሆን አባ ቢስዱራ የሚባል ጻድቅ ሰው 50ኛ ሁኖ ይመራቸው ነበር:: መኖሪያቸው ገዳመ አስቄጥስ (ግብጽ) ሆኖ ዘመኑ 5ኛው መቶ ክ/ዘ ነበር::

ሃምሳውም ሙሉ ዘመናቸውን በምናኔና በቅድስና ፈጽመው በስተእርጅና ደግሞ ሰማዕትነት መጣላቸው:: በ430ዎቹ አካባቢ
የዚያን ጊዜ በርበር ይባሉ የነበሩት አረማውያኑ (የዛሬዎቹ አሕዛብ አባቶች) "ሃይማኖት ካዱ" እያሉ ሰይፍን መዘዙባቸው::

በጊዜው አባ ቢስዱራ በማረፉ ሃላፊነቱን የወሰዱት አባ ዮሐንስ ከአርባ ስምንቱ ባልንጀሮቻቸው ጋር ተስማምተው በበርበር እጅ ሰማዕትነትን ተቀብለዋል:: ከንጉስ ቴዎዶስዮስ (ትንሹ) ተልኮ የነበረ አንድ ክርስቲያንም በፍቅረ ክርስቶስ ተስቦ ከወጣት ልጁ ጋር ተሰይፏል:: የብርሃን አክሊልም ለሃምሳ አንዱም ወርዷል::

† አምላከ ቅዱሳን ከተከፈተ ገነት : ከተነጠፈ ዕረፍት በቸርነቱ ያድርሰን::

† ጥር 26 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

1.አርባ ዘጠኝ አረጋውያን ሰማዕታት (ግብጽ ገዳመ አስቄጥስ ውስጥ)
2.ቅድስት አንስጣስያ (በ5ኛው መቶ ክ/ዘ ከቁስጥንጥንያ ወደ ግብጽ ወርዳ ፡ ንግሥናን ንቃ በበርሃ ስትጋደል የኖረች ቅድስት
እናት ናት::)
3.ቅዱስ ዮሴፍ (መፍቀሬ ነዳያን)
4.አባ ጽሕማ (ከተስዓቱ ቅዱሳን)

† ወርኀዊ በዓላት
1.ቅዱስ ቶማስ ሐዋርያ
2.አቡነ ሐብተ ማርያም ኢትዮጵያዊ
3.አቡነ ኢየሱስ ሞዐ ዘሐይቅ
4.አቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን

† "ከክርስቶስ ፍቅር ማን ይለየናል? መከራ: ወይስ
ጭንቀት: ወይስ ስደት: ወይስ ራብ: ወይስ ራቁትነት: ወይስ ፍርሃት: ወይስ ሰይፍ ነውን? 'ስለ አንተ ቀኑን ሁሉ እንገደላለን:: እንደሚታረዱ በጐች ተቈጠርን' ተብሎ እንደ ተጻፈ ነው:: በዚህ ሁሉ ግን በወደደን በእርሱ ከአሸናፊዎች እንበልጣለን::"
† (ሮሜ. ፰፥፴፭-፴፰)

🌹<  ወስብሐት ለእግዚአብሔር  >🌹
               🌹🌹🌹
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

02 Feb, 17:26


ስንክሳር ጥር 25

† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †

† እንኳን ለታላቁ ሰማዕት ቅዱስ መርቆሬዎስ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †

🌿††† ቅዱስ መርቆሬዎስ ኃያል †††🌿
ለክርስትና ሃይማኖት የሚከፈል ትልቁ ዋጋ ሰማዕትነት ነውና ቤተ ክርስቲያን ለምስክሮቿ ሰማዕታት ልዩ ክብር አላት::

ከኮከብ ኮከብ እንዲበልጥ ሁሉ ከሰማዕታትም ቅዱስ ጊዮርጊስን እና ቅዱስ መርቆሬዎስን የመሰሉት ደግሞ ክብራቸው በእጅጉ የላቀ ነው::
ቅዱስ መርቆሬዎስን ብዙ ጊዜ ሊቃውንት "ካልዕ (ሁለተኛው) ሊቀ ሰማዕታት" ሲሉ ይገልጹታል::
በ2ኛው መቶ ክ/ዘመን መጨረሻ አካባቢ ከሮም ግዛቶች በአንዱ (አስሌጥ) ከአባቱና ከሚስቱ ጋር የሚኖር "አሮስ" የሚሉት ሰው ይኖር ነበር:: ሚስቱ ደም ግባት የሠመረላት: እርሱም ደግነት ያለው ሰው ቢሆኑም የሚያመልኩት ግን ጣዖትን ነበር::

አንድ ቀን አሮስ ሚስቱን ከቤት ትቶ ለአደን ከአባቱ ጋር ወጣ:: እንደ ልማዳቸው ወጥመዱን አስተካክለው ተደበቁ:: የወጥመዱ ደወል ሲያቃጭል: "እንስሳ ተያዘልን" ብለው ሲሯሯጡ ዐይናቸው ያየው ነገር በድንጋጤ እንዲፈዙ አደረጋቸው:: 2 ገጻተ ከለባት በወጥመዱ ውስጥ ተይዘው ነበር::

እነዚህ ፍጡራን ሰዎች ናቸው:: ግን ባልታወቀ የተፈጥሮ አጋጣሚ እንደዚህ እንደ ሆኑ ይታመናል:: ግን እጅግ ግዙፍ: ከአንገታቸው በላይ እንደ ውሻ: ወገባቸው እንደ ሰው: ጉልበታቸው እንደ አንበሳ ሲሆን ታችኛው እግራቸው የጋለ የናስ ብረት ነው የሚመስል::

እነዚህን ፍጡራን ሰማያዊ ካልሆነ ምድራዊ ፍጡር አይችላቸውም:: አንበሳና ነብርን እንኩዋ እንደ ጨርቅ በጣጥሰው ይጥሏቸው እንደ ነበር ይነገራል:: ዐይናቸው እንደ እሳት ይነድ ስለ ነበር ማንም ትክ ብሎ ሊያያቸው አይችልም:: ምሥጢራቸውን ግን የሚያውቀው የፈጠራቸው አምላክ ነው::

ወደ ቀደመ ነገራችን እንመለስና:- አሮስና አባቱ ባዩአቸው ጊዜ ደንግጠው ወደቁ:: ገጻተ ከለባቱ የብረት ወጥመዱን እንደ ክር በጣጥሰው የአሮስን አባት በቅጽበት በሉት:: አሮስን ሊበሉት ሲሉ ግን ድንገት ቅዱስ መልአክ ወርዶ በእሳት ሰይፍ አጠራቸው:: "ከእርሱ የሚወጣ ቅዱስ ፍሬ አለና እንዳትነኩት" አላቸው:: ወዲያውም መልአኩ ያንን ኃይለኝነታቸውን አጠፋው:: በዚህ ጊዜ 2ቱም ወደ አሮስ ሒደው ሰገዱለት:: አሮስም ወደ ቤቱ ወስዶም ደበቃቸውና የሆነውን ሁሉ ለሚስቱ ነገራት:: ጥቂት ቆይታም ጸንሳ ወለደች:: ልጃቸውን ፒሉፓዴር ሲሉ ስም አወጡለት:: ትርጉሙም "መፍቀሬ አብ - የአብ ወዳጅ" ማለት ነው:: ከዚያም አሮስ ሚስቱን : ልጁንና 2ቱን ገጻተ ከለባት ይዞ ወደ ቤተ ክርስቲያን ሒዶ ተጠመቀ::

አበው ካህናት እሱን "ኖኅ" : ሚስቱን "ታቦት" : ልጁን ደግሞ "መርቆሬዎስ" ሲሉ ሰየሟቸው:: መርቆሬዎስ ማለትም "ገብረ ኢየሱስ ክርስቶስ - የኢየሱስ ክርስቶስ አገልጋይ" እንደ ማለት ነው::

ከዚያም ደስ እያላቸው: ክርስቶስን እያመለኩ: ነዳያንን እያሰቡ: ልጃቸውን መርቆሬዎስን አሳደጉ:: ነገር ግን የገጻተ ከለባት ወሬ በመሰማቱ ንጉሡ "ካላመጣሃቸው" አለው:: ኖኅ ጸልዮ ወደ ኃይለኝነታቸው መልሷቸው ስለነበር ፊታቸው ገና ሲገለጥ ብዙ አሕዛብ በድንጋጤ ሞቱ::

ንጉሡም ስለ ፈራ ኖኅን የጦር መኮንን አደረገው:: በጦርነት ጊዜም ገጻተ ከለባቱ ኃይላቸው ስለሚመለስ ተሸንፎ አያውቅም ነበር:: አንድ ጊዜ ግን 2ቱን ገጻተ ከለባት ንጉሡ አታሎ ወሰዳቸው:: ሃይማኖታቸውን ሊያስክዳቸው ሲል "እንቢ" በማለታቸው አንዱ ሲገደል ሌላኛው አምልጦ ጠፋ:: በዚያ ወራትም ኖኅ ለጦርነት ወጥቶ ተማረከ:: ንጉሡ ደግሞ ታቦትን "ላግባሽ" ስላላት የ5 ዓመት ልጇን ቅዱስ መርቆሬዎስን ይዛ ተሰደደች:: በስደት ጥቂት እንደ ቆየች ግን ባሏን ኖኅን አየችው::

እርሷ ብታውቀውም እርሱ ዘንግቷት ነበር:: በሁዋላ ግን በሕጻኑ መርቆሬዎስ አማካኝነት ማስታወስ በመቻሉ ደስ አላቸው:: በዚያው በሮም ዙሪያ ሳሉም አንዱ ገጸ ከልብ መጥቶ አገኛቸው:: በዚህም ምክንያት በስደት ሃገርም መኮንን ሆኖ ተሾመ:: በዚያም ቤተ ክርስቲያንን አንጾ: ቤቱን ቤተ ነዳያን አድርጐ ኖኅ ለዓመታት ኖረ:: ቅዱስ መርቆሬዎስ ወጣት ሲሆንም ወላጆቹ ታቦትና ኖኅ ዐረፉ:: እርሱ ከባልንጀራው ገጸ ከልብ ጋር ሆኖ በጾምና በጸሎት ሲኖር ስለ አባቱ ፈንታ የጦር መሪ አደረጉት::

በጦርነትም እጅግ ኃያል: በሰው ዘንድም ፍጹም ተወዳጅ: የጾምና የጸሎት ሰው ሆነ:: ያን ጊዜ ግን ዳክዮስ ንጉሡ ክርስቶስን በመካዱ ምዕመናን ላይ ሞት ታወጀ:: በጊዜው ደግሞ የበርበር ሰዎች በሮም መንግስት ላይ ጦርነትን በማንሳታቸው ዳኬዎስና ቅዱስ መርቆሬዎስ ለጦርነት ወጡ::

ነገር ግን በርበሮች እንደ አሸዋ ፈሰው ብዛታቸውን ሲያይ ንጉሡ ደነገጠ:: ለማግስቱ ቀጠሮ ተይዞ ቅዱስ መርቆሬዎስ ሲጸልይ ቅዱስ ገብርኤል ወርዶ ሰይፍ ሰጠው:: በማግስቱም "ምን ይሻላል?" ሲባል ቅዱስ መርቆሬዎስ "እኔ የክርስቶስ ባሪያ ነኝና ብቻየን እቋቋማቸዋለሁ" ቢል ሳቁበት::

እርሱ ግን በጥቁር ፈረሱ (አብሮት ያደገ ነው) ተጭኖ በርበሮችን "ጠብ ይቅርባችሁ: በሰላም ሒዱ" ቢላቸው ተሳለቁበት:: ያን ጊዜም ጸሎት አድርሶ የመልአኩን ሰይፍ ሲመዘው ብዙዎቹ ወደቁ:: ከበርበሮችም ለወሬ ነጋሪነት እንኩዋ የተረፈ አልነበረም::

ነገሩ በሮም ሲሰማ ታላቅ ሐሴት ሆነ:: ዳሩ ግን ከሃዲው ዳኬዎስ "ድሉ የጣዖቶቼ የነ አዽሎን ነው" በማለቱ ቅዱስ መርቆሬዎስ ሲያዝን አደረ::
በ3ኛው ቀንም "ለጣዖት ሠዋ" የሚል ትዕዛዝ ከንጉሡ ዘንድ መጣ:: ቅዱሱ ግን ወደ አደባባይ ሔደ:: የክብር ልብሱንና መታጠቂያውን አውልቆ በንጉሡ ፊት ወረወረው:: "ለእኔስ ክብሬ ክርስቶስ ነውና ንብረትህ ለጥፋት ይሁንህ" ሲልም ንጉሡን በአደባባይ ዘለፈው:: ዳኬዎስም በቁጣ እሳት አስነድዶ: የብረት አልጋውንም አግሎ ቅዱስ መርቆሬዎስን በዚያ ላይ አስተኛው:: ያም አልበቃው ብሎ ወታደሮች እየተፈራረቁ ሲደበድቡት ደሙ ፈሶ እሳቱን አጠፋው::

ከዚያም ወስደው ወኅኒ ቤት ውስጥ ጣሉት:: ክርስቶስን ያስክደው ዘንድ በረሃብ: በግርፋት: በእሳት: በስለትም አሰቃየው:: በመጨረሻ ግን አሰቃይተው እንዲገድሉት ወደ እስያ ሰደደው:: በስፍራውም ብዙ አሰቃይተው ኅዳር 25 ቀን አንገቱን ሰይፈውታል::

እርሱ ካረፈ በኋላም የተባረከ ፈረሱ ለዓመታት ወንጌልን ሰብኩዋል:: አረማውያንንም ከአፉ በወጣ እሳት አጥፍቷል::
ሰማዕቱ በዚህች ዕለት : በ4ኛው መቶ ክ/ዘመን ክርስቲያኖችን ያሰቃይና ይገድል የነበረውን ዑልያኖስን ያጠፋበት መታሠቢያ ይከበራል::

👉† ጥር 25 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ መርቆሬዎስ ሰማዕተ ሮሜ
2.ቅዱሳን ባስልዮስና ጎርጎርዮስ
3.ብፁዕ አባ ዼጥሮስ ጽሙድ (ለምጽዋት ራሱን የሸጠ አባት)
4.ቅዱስ ሰብስትያኖስ ሰማዕት
5.ቅዱ ስ አስኪላ ሰማዕት

👉† ወርሐዊ በዓላት
1.ቅዱስ አበከረዙን ሰማዕት
2.ቅዱስ ዱማድዮስ ሶርያዊ
3.ቅድስት ቴክላ ሐዋርያዊት
4.አቡነ አቢብ
5.አባ አቡፋና

🌹<  ወስብሐት ለእግዚአብሔር  >🌹
               🌹🌹🌹
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

31 Jan, 13:56


🙏 ስንክሳር ጥር 24 🙏

††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።

† እንኳን ለቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †

††† ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ሐዋርያዊ †††
👉† ልደት †
መልካም ዛፍ መልካም ፍሬን ያፈራልና ተክለ ሃይማኖትን የወለዱት ደጋጉ: ጸጋ ዘአብ ካህኑና እግዚእ ኃረያ ናቸው:: እርሱ በክህነቱ: እርሷ በደግነቷ: በምጽዋቷ ጸንተው ቢኖሩ እግዚአብሔር ጣፋጭ ፍሬን ሰጥቷቸዋል:: በዳሞቱ ገዢ በሞተለሚ አደጋ ቢደርስባቸው ቅዱስ
ሚካኤል: ጸጋ ዘአብን ከሞት: እግዚእ ኃረያን ከትድምርተ አረሚ (ከአረማዊ ጋብቻ) አድኗቸዋል:: በኋላም የቅዱሱን መወለድ አብስሯቸዋል::

ጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት የተጸነሱት መጋቢት 24 ቀን በ1206 ዓ/ም ሲሆን የተወለዱት ደግሞ ታኅሣሥ 24 ቀን በ1207 ዓ/ም ነው::

👉† ዕድገት
የጻድቁ የመጀመሪያ ስማቸው "ፍሥሃ ጽዮን" ይሰኛል:: ይሕንን ስም ይዘው: አባታቸው ጸጋ ዘአብን ተከትለው አድገዋል:: በተለይ ቅዱሳት መጻሕፍትን (ብሉያት: ሐዲሳትን) ተምረዋል:: በሥጋዊው ጐዳናም ብርቱ አዳኝ እንደ ነበሩ ይነገራል:: ዲቁናም ከወቅቱ ጳጳስ አባ ጌርሎስ ተቀብለዋል::

👉† መጠራት †††
አንድ ቀን ፍሥሃ ጽዮን ለአደን ወጥቶ ሲያነጣጥር ድንገት ከሰማይ አስደንጋጭ ድምጽ ተሰማ:: የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አእላፍ መላእክት እያመሰገኑት በሚካኤል ክንፍ ተቀምጦ ወረደ:: የወጣቱን አዳኝ ፍርሃቱን አርቆ ጌታችን ተናገረ:: "ከዛሬ ጀምሮ ስምህ ተክለ ሃይማኖት (ተክለ ሥላሴ) ይሁን:: ከዚህ በኋላ አራዊትን ሳይሆን ነፍሳትን ታድናለህ:: ዘወትር ካንተ ጋር ነኝ" ብሎ በግርማ ዐረገ:: ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከዚህ ጊዜ በኋላ ሰዓትን አላጠፉም:: ንብረታቸውን ለነዳያን በትነው በትር ብቻ ይዘው ቤታቸው
እንደ ተከፈተ ወደ ምናኔ ወጡ::

👉† አገልግሎት ††
ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከጳጳሱ ቅስና ተቀብለው የወንጌል አገልግሎትን ጀመሩ:: በመጀመሪያ ስብከታቸው እዚያው ሽዋ (ጽላልሽ) አካባቢ ብቻ በ10ሺ የሚቆጠሩ ሰዎችን አሳምነው አጠመቁ:: ያን ጊዜ ኢትዮጵያ 2 መልክ ነበራት::
1ኛ. ዮዲት (ጉዲት) በፈጠረችው ጣጣና በእስላሞች ተጽዕኖ ወደ ደቡብ አካባቢ ያለው ነዋሪ አንድም ሃይማኖቱን ክዷል: ወይም በባዕድ አምልኮ ተጠምዷል::
2ኛው ደግሞ በዛግዌ ነገሥታት ጥረት ክርስትናና ምናኔ ተነቃቅቶ ነበር:: ግማሹ ሃገር በጨለመበት ወቅት የደረሱት ሐዲስ ሐዋርያ አባ ተክለ ሃይማኖት በወጣት ጉልበታቸውና በኃይለ መንፈስ ቅዱስ ብዙ ቦታዎችን አደረሱ:: ሕዝቡን: መሣፍንቱን ወደ ሃይማኖት መልሰው: ማርያኖችን (ጠንቋዮችን) አጥፍተዋል::

👉† ገዳማዊ ሕይወት †
††† ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት በወንጌል ብርሃን ኢትዮጵያን ከማብራታቸው ባለፈ ገዳማዊ ሕይወትንም አስፋፍተዋል:: እርሳቸው ከሁሉ የተሻሉ ሳሉም በ3 ገዳማት በረድዕነት አገልግለዋል::

እነዚህም በአቡነ በጸሎተ ሚካኤል ገዳም ለ12 ዓመታት፣ በአቡነ ኢየሱስ ሞዐ ዘሐይቅ ገዳም ለ7 ዓመታት፣ በደብረ ዳሞ ከአቡነ ዮሐኒ ጋር ለ7 ዓመታት፣ በአጠቃላይ ለ26 ዓመታት አገልግለዋል::

በአቡነ ኢየሱስ ሞዐ ከመነኮሱ በኋላም ወደ ምድረ ሽዋ (ዞረሬ) ተመልሰው በአንዲት በዓት ውስጥ ለ22 ዓመታት ቆመው ጸልየዋል:: በተሰበረ እግራቸውም 6 ጦሮችን በግራና በቀኝ ተክለው ለ7 ዓመታት ጸልየዋል::

👉† ስድስት ክንፍ †
ኢትዮጵያዊው ጻድቅና ሐዋርያ ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከኢትዮጵያ ወደ ኢየሩሳሌም ተጉዘው ከቅዱሳት መካናት ተባርከዋል:: ጻድቁ ምድረ እሥራኤል የገቡት በየመንገዱ መንፈሳዊ ዘርን እየዘሩ: እያስተማሩና እያሳመኑ ነበር::

ከወቅቱ ሊቀ ጳጳሳት አባ ሚካኤል ጋርም ተገናኝተው ቡራኬን ተሰጣጥተዋል:: ዋናው ጉዳይ ግን ከዚህ በኋላ ነው:: ጻድቁ እመቤታችንና ጌታችን ከጽንሰታቸው እስከ ዕርገታቸው የረገጧቸውን ቦታዎች ሲመለከቱ በፍጹም ተደሞ እንባቸው ይፈስ ነበር:: ምክንያቱም እግዚአብሔር ስላበቃቸው ተክለ ሃይማኖት የሚያዩት ቦታውን አልነበረም:: በገሃድ:-
*በቤተ መቅደስ ብስራቱን
*በቤተ ልሔም ልደቱን
*በቤተ ዮሴፍ ግዝረቱን
*በፈለገ ዮርዳኖስ ጥምቀቱን
*በቤተ አልዓዛር ተአምራቱን ይመለከቱ ነበር::

የጉብኝታቸው የመጨረሻ ክፍል ወደ ሆነው ቀራንዮ
ደርሰው ጌታቸውን እንደ ተሰቀለ ሆኖ ቢመለከቱት
ከዓይናቸው ይፈስ የነበረው ቁጡ እንባ መልኩን ቀየረና ዓይናቸው ጠፋ::

በዚያች ቅጽበት ስም አጠራሯ የከበረ እመቤታችን ድንግል ማርያም ፈጥና ደርሳ አቡነ ተክለ ሃይማኖትን ወደ ሰማይ አሳረገቻቸው::

††† በዚያም:-
*የብርሃን ዐይን ተቀብለው
*6 ክንፍ አብቅለው
*የወርቅ ካባ ላንቃ ለብሰው
*ማዕጠንተ ወርቁን ይዘው
*ከ24ቱ ካህናተ ሰማይም ተደምረው
*ሥላሴን በአንድነቱና ሦስትነቱ ተመልክተው
*"ስብሐት ወክብር ለሥሉስ ቅዱስ ይደሉ" ብለው መንበረ ጸባኦትን አጥነው ወደ መሬት ተመልሰዋል::

👉† ተአምራት †††
የቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ተአምራት እንደ ሰማይ ከዋክብት የበዛ ነው::
*ሙት አንስተዋል
*ድውያንን ፈውሰዋል
*አጋንንትን አሳደዋል
*እሳትን ጨብጠዋል
*በክንፍ በረዋል
*ደመናን ዙፋን አድርገዋል::

ብዙ ደቀ መዛሙርትን አፍርተው ደብረ ሊባኖስን
መሥርተዋል:: በዚያም ሴትና ወንድ መነኮሳት እንደ
ሕጻናት አብረው ኑረዋል:: በዘመናቸው ሰይጣን
ታሥሯልና::

👉† ዕረፍት †††
††† ጻድቅ: ሰማዕትና ሐዋርያ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ብርሃን ሆነው: መከራን በብዙ ተቀብለው: እልፍ አእላፍ ፍሬን አፍርተው: በተወለዱ በ99 ዓመት: ከ8 ወር: ከ1 ቀናቸው
ነሐሴ 24 ቀን በ1306 ዓ/ም ዐርፈዋል:: ጌታ: ድንግል ማርያምና ቅዱሳን ከሰማይ ወርደው ተቀብለዋቸዋል:: 10 ትውልድ የሚያስምር ቃል ኪዳንም ተቀብለዋል::

††† በዚህ ዕለት አባታችን ተክለ ሃይማኖት ለ22 ዓመታት የቆሙበት ቀኝ እግራቸው መሠበሩንና በአንድ እግራቸው ለ7 ዓመታት ቆመው መጸለያቸውን ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ታስባለች::

††† ጥር 24 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1አቡነ ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት
2.ቅድስት ማርያ ግብጻዊት
3.ታላቁ አባ ቢፋ
4.አባ አብሳዲ ቀሲስ
5.ቅዱሳን ጻድቃነ ሐውዚን

††† ወርኀዊ በዓላት
1.አቡነ ዘዮሐንስ (ዘክብራን ገብርኤል-ጣና)
2.ቅድስት እናታችን ክርስቶስ ሠምራ
3.ቅዱስ ቶማስ ዘመርዓስ
4.ቅዱስ ሙሴ ጸሊም
5.ቅዱስ አጋቢጦስ
6.ሃያ አራቱ ካህናተ ሠማይ

††† "በድካም : አብዝቼ በመገረፍ : አብዝቼ በመታሠር : አትርፌ በመሞት ብዙ ጊዜ ሆንሁ:: በድካምና በጥረት : ብዙ ጊዜም እንቅልፍ በማጣት : በራብና በጥም : ብዙ ጊዜም በመጦም : በብርድና በራቁትነት ነበርሁ . . .
የቀረውን ነገር ሳልቆጥር ዕለት ዕለት የሚከብድብኝ
የአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ አሳብ ነው::" †
(፪ቆሮ ፲፩፥፳፫)

🌹<  ወስብሐት ለእግዚአብሔር  >🌹
                👇👇👇
        https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

31 Jan, 04:35


🙏 ስንክሳር ጥር 23🙏

† እንኳን ለቅዱስ ጢሞቴዎስ ሐዋርያ: እና ጻድቅ ንጉሥ ቴዎዶስዮስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †

††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †††

††† ቅዱስ ጢሞቴዎስ ሐዋርያ †††

††† ይህ ቅዱስ ሐዋርያ አንድ የቤተ ክርስቲያናችን መብራት ነው:: ወደ ክርስትና የመጣው በ40ዎቹ ዓ/ም አካባቢ ሲሆን አሳምኖ ለቅድስና ያበቃው ብርሃነ ዓለም ቅዱስ ዻውሎስ ነው::

በጊዜውም በነበረው ትጋትና ተጋድሎ ፍሬ አፍርቷል:: ሆዱንም እጅግ ያመው ነበር:: ቅዱስ ዻውሎስ ሲጠራው "የምወድህ ልጄ" እያለ ነበር:: በኤፌሶንም ዽዽስናን ሹሞ 2 መልዕክታትን ልኮለታል:: ቅዱስ ጢሞቴዎስ ቤተ ክርስቲያንን ለብዙ ዘመናት አገልግሎ በሰማዕትነት ዐርፏል::

ከሐዋርያው ቅዱስ ጢሞቴዎስ በረከትን እንሳተፍ ዘንድ ጊዜ ካለን ቅዱስ ዻውሎስ ለልጁ ጢሞቴዎስ ከላካቸው መልዕክቶች ጥቂት እናንብብ::

††† ቴዎዶስዮስ †††

††† በዚህ ስም የሚጠሩ ብዙ አበው አሉ:: ሰማዕታትም: ጻድቃንም: ሊቃውንትም: ነገሥታትም ተጠርተውበታልና:: ዛሬ የምናከብረውም ቴዎዶስዮስ ዘየዓቢ (ታላቁ) የሚባል ሲሆን ይህን የምንለው ከትንሹ ቴዎዶስዮስ (የልጅ ልጁ ነው) ለመለየት ነው::

ታላቁ ቴዎዶስዮስ በሮም የነገሠው በ370 ዓ/ም አካባቢ ሲሆን ከነ ቤተሰቡ ክርስቲያን ነበር:: እነዚህ ነገሮቹ ደግሞ በቤተ ክርስቲያን እንዲታሰብ አድርጐታል:-
1.በዓለም ታሪክ ክርስትና በሮም ግዛት ሁሉ ብሔራዊ ሃይማኖት እንዲሆን አውጇል::
2.የቤተክርስቲያንን ትልቁን 2ኛ ጉባኤ ቁስጥንጥንያን በ381 (373) ዓ/ም አሰናድቷል::
3.ከበጐነቱ የተነሳ የተቀደሱ ልጆችን አፍርቷል:: ሙሽራው ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ: ቅዱስ አኖሬዎስ: ቅዱስ አርቃዴዎስ እና ቅድሰት ታኦድራ ልጆቹ ሲሆኑ አቡነ ኪሮስ ትንሽ ወንድሙ ናቸው::

ጻድቁ ንጉሥ ቴዎዶስዮስ በ390 ዓ/ም አካባቢ ዐርፏል::

††† አምላከ ቅዱሳን ስለ አባቶቻችን ሲል ይማረን:: ከበረከታቸውም ይክፈለን::

††† ጥር 23 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ ጢሞቴዎስ (ሐዋርያና ሰማዕት-የቅዱስ ዻውሎስ ደቀ መዝሙር)
2.ቅዱስ ጌርሎስ ሰማዕት
3.ቅዱስ አትናቴዎስ ሰማዕት
4.ጻድቅ ንጉሥ ቴዎዶስዮስ (ዘቁስጥንጥንያ)

††† ወርሐዊ በዓላት
1.ቅዱስ ዳዊት ልበ አምላክ
2.ቅዱስ ጊዮርጊስ ሊቀ ሰማዕታት
3.ቅዱስ ሰሎሞን ንጉሠ እሥራኤል
4.አባ ጢሞቴዎስ ገዳማዊ
5.አባ ሳሙኤል
6.አባ ስምዖን
7.አባ ገብርኤል

🌹<  ወስብሐት ለእግዚአብሔር  >🌹
               🌹🌹🌹
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

30 Jan, 17:50


እንደ ክርስቲያን እንዲህ አይነት ዜናዎች ልብ ያሞቃሉ

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

30 Jan, 11:49


​​እንኳን ለቅዱስ ዑራኤል አመታዊ የመታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሳቹ አደረሰን!

መልዐኩ ቅዱስ ዑራኤልና አገልግሎቱ በጥቂቱ

ዑራኤል የሚለው ስም ዑር እና ኤል ከሚለው ሁለት ቃላት የተመሠረተ ነው ። ትርጉሙም ጌታ ብርሃን ወይም  አምላክ  ብርሃን ነው ማለት ነው።

ቅዱስ ዑራኤል ከ7ቱ ሊቃነ መላእክት አንዱ ሲሆን ከፍጥረተ ዓለም ጀምሮ መብረቅና ነጎድጓድ ላይ የተሾመ መልአክ ነው።በመሆኑም መባርቅት ለጥጋብና ለበረከት እንዲበቁ ነጓድጓድ ለሰላም እንዲሆን ያሰማራል። (መጽሐፈ ሄኖክ ፮፥፪)

እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከልጇ ከወዳጇ ከጌታችን ከመድኃኒታችን ከእየሱስ ክርስቶስ ጋር ወደ ግብጽ ስትሰደድ መንገድ እየመራ፤ ከእስራኤል ወደ ግብጽ ከዚያም ከእመቤታችን ጋር በሀገራችን ኢትዮጵያ እየመራ ያመጣት መልአክ ነው።

ጌታችን መድኃኒታችን እየሱስ ክርስቶስ ለዓለም ቤዛ ሆኖ በተሰቀለበት ጊዜ፥ክቡር ደሙ በብርሃን ጽዋ ተቀብሎ በብርሃን ነሳንስ የረጨው እሱ ነው።

ለነብዩ ዕዝራ ሱቱኤል ጽዋ ልቦና ያጠጣው፥ጥበብን ማስተዋልን የሰጠው የጠፉ መጽሓፍት በቃሉ አስታውሶ እንደገና ያጻፈው የረዳው መልአክ ነው።(ዕዝ፲፫፥፴፱)

አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነትና ትዕዛዝ ብዙ ድርሰት የደረሱት መልአኩ ቅዱስ ዑራኤል  ጽዋ ህይወት ስላጠጣቸው ነው።

በዓላቱም በዓመት 3ናቸው።
፩...ጥር። 22 በዓለ ሲመቱ፤
፪....መጋቢት 27 የጌታችንን ደም በአዓም የረጨበት፤
፫...ሐምሌ 21 እና 22 ቅዳሴ ቤቱ የተከበረበት ።

በጸሎቱ የተማጸነ ከእግዚአብሔር አምላክ በረከትን ፣ምህረትን የሚያሰጥ አዛኝ ጠባቂ ና የዋህ መልአክ ነው።በተለይም ህጻናትን የሚጠብቅ የሚለምኑትን ሁሉ የሚሰማ ፥ኃጢአተኞች ካሉበት ቦታ እኔን ላከኝ እያለ አምላኩን የሚማጸን አዛኝ የዋህ መልአክ ነው።

ይህ አለም በአማላጅነቱ አምኖ በእምነት ጸበሉን ቢጠጣ ፥ዝክሩንም ቢዘክር ከክፉ በሽታው እንደሚድን፤ እንደሚፈውሰው ቃል ኪዳን ተሰጥቶታል ።

ቅዱሳን መላዕክት እግዚአብሔርን በሚፈሩ ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራሉ ከመከራም ያድኑዋቸዋል።(መዝ ፴፫÷፯) የአባታችን የጠባቂያችን የአማላጃችን የመልአኩ የቅዱስ ዑራኤል ቃል ኪዳን አይለየን።

ለሁሉም ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች
#####  Share አድርጉ #####
🌹<  ወስብሐት ለእግዚአብሔር  >🌹
               🌹🌹🌹
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

29 Jan, 18:13


🌿 ስንክሳር ጥር 22 🌿
† እንኳን ለታላቁ ኮከበ ገዳም አባ እንጦንስ እና ቅዱስ ዑራኤል ሊቀ መላእክት ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †

† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †

† አባ እንጦንስ †

† በቤተ ክርስቲያን አስተምሕሮ "ታላቁ / ዓቢይ / THE GREAT" የሚል ስም የሚሰጣቸው አባቶች የተለዩ ናቸው:: አንድም እጅግ ብዙ ትሩፋቶችን የሠሩ ናቸው:: በሌላ በኩል ደግሞ በተመሳሳይ ስም ከሚጠሩ ሌሎች ቅዱሳን እንለይበታለን::

ገዳማዊ ሕይወት ጥንቱ ብሉይ ኪዳን ነው:: በቀዳሚነትም በደብር ቅዱስ አካባቢ ይኖሩ የነበሩ ደቂቀ ሴት እንደ ጀመሩት ይታመናል:: ሕይወቱ በጐላ: በተረዳ መንገድ የታየው ግን በታላቁ ጻድቅ ሄኖክ: ከዚያም በቅዱሱ ካህን መልከ ጼዴቅ አማካኝነት ነው::

ቀጥሎም እነ ቅዱስ ኤልያስ ነቢይ: እነ ኤልሳዕ ደቀ መዝሙሩ ኑረውበታል:: በሐዲስ ኪዳን ደግሞ ሙሉ ሕይወቱን በገዳም (በበርሃ) ያሳለፈው መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ቅድሚያውን ይይዛል::

ለስም አጠራሩ ስግደት ይሁንና መድኃኒታችን ክርስቶስ በገዳመ ቆረንቶስ ለ40 ቀናት በትሕርምት ኑሮ ገዳማዊ ሕይወትን ቀድሷል: አስተምሯል:: በዘመነ ስብከቱም ያድርባት የነበረችው የደብረ ዘይቷ በዓቱ (ኤሌዎን ዋሻ) በራሷ ለዚህ ሕይወት ትልቅ ማሳያ ናት::

ከጌታ ዕርገት በሁዋላም ክርስቲያኖቹ የዓለም ሁካታ ሲሰለቻቸው: አንድም በንጹሕና በተሸከፈ ልቡና ለፈጣሪያቸው መገዛትን ሲሹ ከከተማ ወጣ እያሉ ይኖሩ እንደ ነበር የታሪክ መዛግብት ያሳያሉ:: አኗኗራቸውም በቡድንም: በነጠላም ሊሆን ይችላል::

ዋናው ነገር ግን በጾምና በጸሎት መትጋታቸው ነው:: ይሕም ሲያያዝ እስከ 3ኛው መቶ ክ/ዘመን ደረሰ:: በዚህ ዘመን ግን አባ ዻውሊ የሚባል አንድ ንጹሕ ክርስቲያን ይሕንን ሕይወት ወደ ሌላ ደረጃ ከፍ አደረገው:: ለ80 ዓመታት ሰው ሳያይ ተጋድሎ "የባሕታውያን አባት" ተባለ:: ደንብ ያለው ተባሕትዎም ጀመረ::

ይህ ከሆነ ከ20 ዓመታት በሁዋላ ደግሞ አባ እንጦንስ የሚባሉ ደግ ክርስቲያን ይህንን ገዳማዊ ሕይወት በሌላ መንገድ አጣፈጡት:: በቅዱስ ሚካኤል አመንኩዋሽነት ገዳማዊ ሕይወት በምንኩስና ተቃኘ:: ስለዚህም አባ እንጦንስ የመነኮሳት አባት ተባሉ::

እርሳቸውም ሕይወቱን ለማስፋፋት ከተለያዩ አሕጉር ደቀ መዛሙርትን እየተቀበሉ አመንኩሰዋል:: ቅዱሳን የአባ እንጦንስ ልጆችም ወደየ ሃገራቸው ተመልሰው: ሕይወቱን በተግባር አሳይተው ገዳማዊነትን አስፋፍተዋል::

አባ እንጦንስ የመነኮሳት ሁሉ አባታቸው: ለገዳማውያን ሁሉም ሞገሳቸው ናቸው:: እንዲያውም ብዙ ጊዜ "ኮከበ ገዳም: ማኅቶተ ገድል (የበርሃው ኮከብ: የተጋድሎ መብራት)" ተብለውም ይጠራሉ::

ቤተ ክርስቲያን ለጀማሪዎች ትልቅ ትኩረት ትሰጣለች:: ለምሳሌ:- አባ ዻውሊን (የካቲት 2 የሚከበሩ) ለብሕትውና መሠረትን ስለ ጣሉ "አበ ባሕታውያን" ብላ ታከብራለች:: አባ እንጦንስን ደግሞ "አበ መነኮሳት (የመነኮሳት አባት): ቀዳሚሆሙ ለመነኮሳት (ለመነኮሳት ቀዳሚና ጀማሪ) ስትል ትጠራቸዋለች::

አባ እንጦንስ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ለሚነሱ ቅዱሳን መነኮሳት ሁሉ መንገድን ይጠርጉ ዘንድ ብዙ መከራን በትዕግስትና በአኮቴት ተቀብለዋል:: ላለፉት 1,700 ዓመታት እንደ ሻማ እየቀለጡ ያበሩ አበው ቅዱሳን ሁሉ የአባ እንጦንስ ልጆች ናቸው::

ከምጥ የከፋ የዲያብሎስ ፈተናን ተቀብለው ከመንፈሳዊ አብራካቸው ቅዱሳኑን ወልደዋል:: የመነኮሳት አለቃ የሆኑትን ታላቁን መቃርዮስን ጨምሮ በርካቶችን አመንኩሰው ለቅድስና አብቅተዋል::

አባ እንጦንስ ግብጻዊ ሲሆኑ የተወለዱት አቅማን በምትባል ቦታ አካባቢ ነው:: ጊዜውም በ252 ዓ/ም ነው:: የተባረኩ ወላጆች ለቅዱሱ እንጦንስና አስከትለው ለወለዷት ሴት ልጃቸው : አስቀድመው ፍቅረ ክርስቶስን: አስከትለውም ሃብት ንብረታቸውን አውርሰው ዐርፈዋል::

በዚህ ጊዜ የአባ እንጦንስ እድሜ አፍላ ወጣትነት ላይ ነበር:: በልጅነት ጊዜአቸውም አባ እንጦንስን ሲስቁ: ሲጫወቱ: አልያም ሲቀልዱ አየሁ የሚል ሰው አልነበረም:: ፍጹም ቁም ነገረኛና ታዛዥ: በዚያ ላይም አስተዋይ ነበሩና ሙሉ ጊዜአቸውንም ከቅዱስ ቃሉ በመመገብ: በትምሕርትና በማስቀደስ ያሳልፉ ነበር::

ዘወትርም ዜና ሐዋርያትን እያነበቡ በመንፈሳዊ ቅናት ይቃጠሉ ነበር:: በጊዜው የምናኔ ሕይወት ጐልቶ ባለ መገለጡ አባ እንጦንስ የሚያደርጉት ይጨንቃቸው ነበር:: ሲጸልዩም "አበው ሐዋርያት ይሕንን ክፉ ዓለም ንቃችሁ ጌታችሁን የተከተላችሁበት ጥበብ እንደ ምን ያለ ነው!" እያሉ ይደነቁ ነበር:: መሻታቸውን ያወቀ ጌታም ምሥጢርን ገለጠላቸው::

አንድ ቀን በቅዳሴ ላይ ወንጌል ሲነበብ ካህኑ ስለ ምናኔ የሚጠቅሰውን ክፍል አነበበ:: ለአንድ ባለ ጠጋ ሕግጋትን ከነገረው በሁዋላ "ፍጹም ልትሆን ከወደድክስ ያለህን ሁሉ ሸጠህ ተከተለኝ" (ማር. 10:17) የሚለውን ጥቅስ ሲሰሙ ተገርመው "ጌታ ሆይ! ይህንን የተናገርኸው ለእኔ ነው" ሲሉ አሰቡ:: በቀጥታም ሃብታቸውን ለአካባቢው ሰው አካፍለው: እህታቸውን ከደናግል ማሕበር ደምረው እርሳቸው ወደ ዱር ሔዱ::

ከዚህች ቀን ጀምረው አባ እንጦንስ ከ80 እስከ መቶ ለሚገመቱ ዓመታት ከአጋንንት ጋር በጦርነት ነበር የኖሩት:: በንጹሕ አምልኮታቸውና በቅድስናቸው የቀና ጠላት ሰይጣን በብዙ ጐዳና ፈተናቸው:: አቅም ቢያጥረው አራዊትን መስሎ ታገላቸው::

በዚህ አልሳካ ቢለው የእሳት ሰንሰለትን አምጥቶ ገረፋቸው:: በሞትና በሕይወት መካከል ጥሏቸው ሔደ:: ወድቀው ያገኟቸው ሰዎች ለዘመዶቻቸው ሰጥተዋቸው አገገሙ:: ልክ ሲነቁ ግን ፈጥነው ወደ በርሃ ተመለሱ::

ሰይጣን በርሃው የቅዱሳን ማደሪያ እንዳይሆን ሰግቷልና ጨክኖ ታገላቸው:: ግን አልቻላቸውምና ተረታ:: አምላከ ኃያላን ክርስቶስ ከቅዱሱ ጋር ነበርና:: ከዚህ በሁዋላ ግን ጸጋው በዝቶላቸው ድውያንን የሚፈውሱና ሰይጣን የማይቀርባቸው ሰው ሆኑ::

በረዥም ዘመነ ቅድስናቸውም:-
1.ብዙ አርድእትን ከመላው ዓለም ሰብስበው: አስተምረው: ምናኔን ከግብጽ ማዶ በመላው ዓለም አስፋፉ::
2.በደመና እየተጫኑ ብዙ አሕጉራትንም እየዞሩ ሰበኩ:: በዚህም አሕዛብን ወደ እምነት: ኃጥአንን ወደ ንስሃ መለሱ::
3.ጊዜው ዘመነ ሰማዕታት ነበርና ወደ አደባባይ ሒደው ከሃዲዎችን ገሠጹ:: ማንም ደፍሮ ግን አልገደላቸውም::

እነዚህንና ሌሎች ተግባራትን እየሠሩ በቅዱስ ሚካኤል እጅ መነኮሱ:: እርሳቸውም ብዙዎችን አመነኮሱ:: አርጅተው እንኩዋ ከተጋድሎ ያላረፉት አባታችን የጣመ ነገር ቀምሰው: ገላቸውን ታጥበው አያውቁም:: በ372 ዓ/ም በዚህች ቀን ሲያርፉም ዕድሜአቸው 120 ደርሶ ነበር::

የአባ እንጦንስን በዓል ለማክበር የምትሹ ቤተ ክርስቲያናቸው ጎንደር ከተማ ከቀሃ ኢየሱስ በላይ ይገኛል::

††† ለአባታችን እንጦንዮስ /እንጦንስ/ እንጦኒ ክብር ይገባል!

††† ጥር 22 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ አባ እንጦንስ (የመነኮሳት አባት - የበርሐው ኮከብ /ልደቱና ዕረፍቱ)
2.ቅዱስ ዑራኤል ሊቀ መላዕክት (ለተጠሙ ጽዋዓ ልቡናን የሚያጠጣ: ምሥጢር ገላጭ መልዐክ)
3.ቅዱስ ሚናስ ኤዺስ ቆዾስ

††† ወርሐዊ በዓላት
1.ቅዱስ ሉቃስ ወንጌላዊ
2.ቅዱስ ደቅስዮስ ኤዺስ ቆዾስ

🌹<  ወስብሐት ለእግዚአብሔር  >🌹
               🌹🌹🌹
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

29 Jan, 14:13


ቡግና

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

28 Jan, 19:25


🌿🌹🔔 ሥርዓተ ማኅሌት 🔔🌹🌿

ስንክሳር በየቀኑ
https://t.me/Sinksar

ዘአስተርእዮ ማርያም ጥር ፳፩

መልክአ ሥላሴ
ሰላም ለኲልያቲክሙ እለ ዕሩያን በአካል፤ ዓለመክሙ ሥላሴ አመ ሐወጸ በሣህል፤ እምኔክሙ አሐዱ እግዚአብሔር ቃል፣ ተፈጸመ ተስፋ አበው በማርያም ድንግል፤ ወበቀራንዮ ተተክለ መድኃኒት መስቀል።

ዚቅ
ሃሌ ሉያ ለአብ፤ ሃሌ ሉያ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ሥላሴ ዋህድ፤ ዕፎኑመ እመ አምላክ በከየት ደንጊፃ፤ ከመ ኲሉ ሰብእ ሞት ሶበ ሐወጻ፤ ዮሐንስ በልብሱ ከደነ ገፃ።

ወረብ
እፎኑመ እመ አምላክ በከየት ደንጊፃ በከየት እመ አምላክ/፪/
ከመ ኲሉ ሰብእ ሞት ሶበ ሐወጻ በከየት/፪/

ነግሥ
ሰላም ለዝክረ ስምኪ ዘመንክር ጣዕሙ፤ ለወልድኪ አምሳለ ደሙ፤ መሠረተ ሕይወት ማርያም ወጥንተ መድኃኒት ዘእምቀዲሙ፤ ኪያኪ ሠናይተ ዘፈጠረ ለቤዛ ዓለሙ፤ እግዚአብሔር ይትባረክ ወይትአኮት ስሙ።

ዚቅ
ሃሌ ሃሌ ሉያ፤ መጽአ ውስተ ዓለም፤ ወዓለሙኒ ኢክህለ ፀዊሮቶ፤ ፆረቶ ወአግመረቶ ማርያም።

ነግሥ
ለምንት ይዜኃር ኃያል በኃይሉ፤ ወባዕል በብዝኃ ብዕሉ፤ ኢያድለወ ሞተ ክርስቶስ ለሥጋ አባሉ፤ ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ፤ ሞታ ለማርያም የአፅብ ለኲሉ።

ዚቅ
እንበይነዝ አእምሩ በውስተ ፍትሕ ከመ ኢያደሉ፤ ትጥዓም ሞተ እሙ ወእመ ኲሉ፤ አዘዘ ወልድ በርቱዕ ቃሉ።

መልክአ ማርያም
ሰላም ሰላም ለዝክረ ስምኪ ሐዋዝ፤ እምነ ከልበኔ ወቊስጥ ወእምነ ሰንበልት ምዑዝ፤ ማርያም ድንግል ለባሲተ ዓቢይ ትእዛዝ፤ ይስቅየኒ ለለጽባሑ ወይነ ፍቅርኪ አዚዝ፤ ከመ ይሰቅዮ ውኂዝ ለሠናይ አርዝ።

ዚቅ
ለዛቲ ድንግል ሠረቀ ላዕሌሃ ብዕለ ጸጋሁ ለአብ፤ ወአግአዛ እምእኩይ ውስተ ሠናይ፤ እሞት ውስተ ሕይወት፤ ወረሰየ ይዝክሩ ስማ ውስተ ኲሉ ዓለም።

ወረብ
ለዛቲ ድንግል ሠረቀ ላዕሌሃ ብዕለ ጸጋሁ ለአብ/፪/
ወአግአዛ እምእኩይ ውስት ሠናይ እሞት ውስተ ሕይወት/፪/

መልክአ ማርያም
ሰላም ለእስትንፋስኪ ዘመዓዛሁ ሕይወት፤ ከመ መዓዛ ዕፅ ኅሩይ ዘውስተ ገነት፤ ማርያም ድንግል ቤተ ቅድሳት፤ ጽንሕኒ ውስተ ሠናይ ወሰውርኒ እሞት፤ በአክናፍኪ ርግብየ ኅሪት።

ዚቅ
አንጺሆ ሥጋሃ ቀዲሶ ኪያሃ፤ ኃደረ ቃል ላዕሌሃ፤ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፤ ወይቤላ ለድንግል፤ ሃሌ ሃሌ ሉያ፤ ሰሎሞን ይቤላ እኅትየ መርዓት ርግብየ ሠናይት፤ ፍናወ ዚአኪ ገነት፤ እስመ ኪያኪ ኀረየ ለታዕካሁ፤ ከመ ትኩኒዮ ማኅደረ ለልዑል።

ወረብ
'አንጺሆ ሥጋሃ'/፪/ ላዕሌሃ ኃደረ/፪/
ቀዲሶ ኪያሃ 'ሃሌ ሉያ'/፪/ ይቤላ ለድንግል/፪/

መልክአ ማርያም
ሰላም ለገቦኪ ዘሐመልማለ ወርቅ ክዳኑ፤ በከመ ዳዊት ይዜኑ፤ ማርያም ድንግል ለያዕቆብ ሞገሰ ስኑ፤ በልኒ እግዝእትየ አፈቅረከ አኮኑ፤ እንዘ ረዳኢትከ አነ ዘይክለከ መኑ።

ዚቅ
እምሰማያት ወረደ ወገብረ መድኃኒተ በማዕከለ ምድር፤ ኖላዊ ኄር ኖላዊሆሙ ለ፳ኤል፤ ወረደ ስኖ ለያዕቆብ ዘአፍቀረ፤ ወስኑሰ ለያዕቆብ ዘይቤ ይእቲ ሥጋ እንተ ነሥአ፤ መድኅን እማርያም።

ወረብ
ወስኑሰ ለያዕቆብ 'ዘይቤ'/፪/ ያዕቆብ/፪/
'ይእቲ ሥጋ'/፪/ እማርያም እንተ ነሥአ መድኅን/፪/

መልክአ ማርያም
ሰላም ለፀአተ ነፍስኪ እንበለ
ፃዕር ወፃማ፤ ለነቢር ዘልፈ በየማነ ወልድኪ ፌማ፤ ማርያም ድንግል ለባሲተ ሞገስ ወግርማ፤ አጽንዒ በረድኤትኪ ለሕይወትየ ድካማ፤ እምሕይወተ ኄራን አበው ኢታሕጽጺ ዐቅማ።

ዚቅ
ጊዜ ዕረፍታ ለሶልያና ወረደ ወልድ እምዲበ ልዕልና፤ ጠሊላነ ንግሥ ሶቤሃ ከደና።

ወረብ
ጊዜ ዕረፍታ ለማርያም 'ጊዜ'/፫/ ዕረፍታ ለማርያም/፪/
ወረደ ወልድ ዲበ እምዲበ ልዕልና ወረደ/፪/

መልክአ ማርያም
ሰላም እብል በድነ ሥጋኪ ጽሩየ፤ ዘተመሰለ ባሕርየ፤ ማርያም ድንግል ዐጸደ ወይንየ፤ ንስቲተ ለዕበየኪ እንተ አቅረብኩ ግናየ፤ ኢይትኃደግ ዲበ ምድር ምሥጢ ሰማየ።

ዚቅ
ኦ ትቤ ማርያም እወጽእ እምዝንቱ ሥጋየ፤ ወአሐውር ውስተ ሕይወት ዘለዓለም፤ ኦ ተዘከርኬ ዮሐንስ ዘይቤለከ ሊቅ አመ ትረፍቅ ዲበ ዕንግድዓሁ።

መልክአ ማርያም
ሰላም ለግንዘተ ሥጋኪ በእደ ሐዋርያት አርጋብ፤ በአፈወ ዕፍረት ቅድው ዘሐሳበ ሤጡ ዕፁብ፤ ማርያም ድንግል ወለተ ኅሩያን ሕዝብ፤ ረሰይኩኪ እግዝእትየ ህየንተ እም ወአብ፤ ይሕፅነኒ ከመ ጥብ ፍቅርኪ ሐሊብ።

ዚቅ
ተጋብኡ በቅጽበት ለግንዘተ እሙ ቅድስት፤ ብፁዓን ሐዋርያት ቦኡ ኀቤሃ፤ በሰላም አምኁ ኪያሃ፤ በስብሐት ገነዙ ሥጋሃ።

መልክአ ማርያም
ሰላም ለመቃብርኪ ለጌቴሴማኒ በመርኅባ፤ እንተ ይእቲ ለኢየሩሳሌም ቅሩባ፤ ማርያም ድንግል ለሀገረ መንግሥት ርግባ፤ ትትሜጦ ወረቀ እምአፌር ወጸበለ አፈው እምሳባ፤ ጌቴሴማኒ ለሥጋኪ ምስካባ።

ዚቅ
ሃሌ ሃሌ ሉያ፤ ዓውዳኒ ዘጽድቅ ወመርኅባኒ ዘዕንቊ፤ አንቀጸ አድኅኖ ሐዳስ ንጽቅ።

መልክአ ማርያም
ሰላም ለመቃብርኪ ለኢየሩሳሌም በአድያማ፤ እንተ ይእቲ ጌቴሴማኒ ስማ፤ ማርያም ሰንበት ዕረፍተ ጽዑራን እምፃማ፤ አመ ኀደረ ላዕሌኪ ፀሐየ ቅዱሳን ዘራማ፤ ኃይለ ልዑል ጸለለኪ በመንክር ግርማ።

ዚቅ
ኢይሜንንዋ ኪያሃኒ ወአድያሚሃኒ ነያ ጽዮን ቅድስት ሀገረ እግዚአብሔር።

ማኅሌተ ጽጌ
እግዚአብሔር ጽጌ ትንቢት ለቢሶ ሥጋኪ ሥጋ ዚአነ፤ አመ አስተርአየ በምድር ወተአምረ ለነ፤ ንዌድሰኪ እንዘ ንብል ምክሃ ዘመድነ፤ ዮም በፍሥሃ ለማርያም እምነ፤ አስተርእዮ በሰማይ ኮነ።

ዚቅ
አስተርአየ ዘኢያስተርኢ፤ ኮነ እሙነ አስተርእዮቱ ለመድኃኒነ ክርስቶስ፤ እሙነ ኮነ አስተርእዮቱ፤ እምድንግል ተወልደ፤ እሙነ ኮነ አስተርእዮቱ፤ በሥጋ ረቂቅ፤ እሙነ ኮነ አስተርእዮቱ፤ በ፴ ክረምት በዮርዳኖስ ተጠምቀ፤ በበህቅ ልህቀ።

አንገርጋሪ
ኢኮነ ነግደ ወፈላሴ ሀገሪቶሙ ለቅዱሳን፤ ንሕነ ሰብአ ቤቱ ለእግዚአብሔር ኲልነ፤ አምላክ ኀደረ ውስተ ሥጋ ተአቊረ፤ እንዘ ኢይትጋባዕ በሙላድ፤ ዘድንግል መናሥግተ ኢያርኂዎ፤ ዘኪሩቤል ኢርእዮ።

አመላለስ
ዘድንግል መናሥግተ ኢያርኂሆ/፪/
ኢያርኂሆ ዘኪሩቤል ኢርእዮ ኢያርኂዎ ኢርእዮ ዘኪሩቤል/፪/

ወረብ
'አምላክ ኀደረ'/፪/ ውስተ ሥጋ ተዓቊረ እንዘ ኢይትጋባዕ አምላክ ኀደረ/፪/
ዘድንግል መናሥግተ 'ኢያርኂዎ'/፪/ ኢርእዮ ዘኪሩቤል/፪/

እስመ ለዓለም
እግዝእትየ እብለኪ ወእሙ ለእግዚእየ እብለኪ፤ ቃል ቅዱስ፤ መንበሩ ዘኪሩቤል ኀደረ ላዕሌኪ፤ ዘመንበሩ ዓቢይ ውእቱ፤ ያቀድም አእምሮ ኅሊና ሰብእ፤ መንበሩ ዘኪሩቤል ኀደረ ላዕሌኪ፤ ግሩም እምግሩማን፤ ዘመጽአ ውስተ ዓለም፤ መንበሩ ዘኪሩቤል ኀደረ ላዕሌኪ፤ ስብሐት ዘኢየኃልቅ፤ ወሰን ዘኢያንጸበርቅ፤ መንበሩ ዘኪሩቤል ኀደረ ላዕሌኪ፤ ዘይሥዕሎሙ ለሕፃናት፤ ወይነግሥ ለመላእክት መንበሩ ዘኪሩቤል ኀደረ ላዕሌኪ፤ እስመ ንጉሥ ውእቱ ሰከበ በጎል፤ ሰገዱ ሎቱ ሰብአ ሰገል፤ መንበሩ ዘኪሩቤል ኀደረ ላዕሌኪ፤ እምግርማሁ ትርዕድ ምድር ዜናዊ ስቡሕ ዘለዓለም፤ ወእስከ ለዓለም ንጉሥ ውእቱ።

ወረብ
ዘመንበሩ ዓቢይ መንበሩ ውእቱ መንበሩ ዘኪሩቤል/፪/ያቀድም 'አእምሮ'/፪/ ኅሊና ሰብእ/፪/

🌹<  ወስብሐት ለእግዚአብሔር  >🌹
               🌹🌹🌹
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

28 Jan, 19:25


     ስንክሳር ጥር 21.   

እንኳን ለእመቤታችን ንጽሕት ድንግል ወላዲተ አምላክ ማርያም ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን።

† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †

† ዕረፍተ ድንግል †

† እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ቅድመ ዓለም በአምላክ ልቡና ታስባ ትኖር ነበር:: ከነገር ሁሉ በፊት እግዚአብሔር እናቱን ያውቃት ነበር:: ዓለም ተፈጥሮ: አዳምና ሔዋን ስተው: መርገመ ሥጋና መርገመ ነፍስ አግኝቷቸው: በኃዘን ንስሃ ቢገቡ " ከ5 ቀን ተኩል (5500 ዘመናት) በሁዋላ ካንተ ባሕርይ ከምትገኝ ንጽሕት ዘር ተወልጄ አድንሃለሁ" ብሎ ተስፋ ድኅነት ሰጠው::

*ከአዳም አንስቶ ለ5500 ዓመታት አበው: ነቢያትና ካህናት ስለ ድንግል ማርያም ብዙ ሐረገ ትንቢቶችን ተናገሩ:: መዳኛቸውን ሱባኤ ቆጠሩላት:: ምሳሌም መሰሉላት:: ከሩቅ ዘመን ሁነውም ሊያገኟት እየተመኙ እጅ ነሷት::

††† የድንግል ማርያም ሐረገ ትውልድ
*ከአዳም በሴት፣ ከያሬድ በሔኖክ፣ ከኖኅ በሴም፣ ከአብርሃም በይስሐቅ፣ ከያዕቆብ በይሁዳና በሌዊ፣ ከይሁዳ በእሴይ: በዳዊት: በሰሎሞንና በሕዝቅያስ ወርዳ ከኢያቄም ትደርሳለች::

*ከሌዊ ደግሞ በአሮን: አልዓዛር: ፊንሐስ: ቴክታና በጥሪቃ አድርጋ ከሐና ትደርሳለች::

*አባታችን አዳም ከገነት በወጣ በ5,485 ዓመት ወላዲተ አምላክ ንጽሕና ሳይጐድልባት: ኃጢአት ሳያገኛት: ጥንተ አብሶ ሳይደርስባት ከደጋጉ ኢያቄም ወሐና ትወለዳለች:: (ኢሳ. 1:9, መኃ. 4:7)

ከዚያም ከእናት ከአባቷ ቤት ለ3 ዓመታት ቆይታ ወደ ቤተ መቅደስ ትገባለች:: በቤተ መቅደስም ለ12 ዓመታት ፈጣሪዋን እግዚአብሔርን እያመሰገነችና እያገለገለች: እርሷን ደግሞ መላእክተ ብርሃን እያገለገሏት: ሕብስት ሰማያዊ ጽዋዕ ሰማያዊ እየመገቧት ኑራለች:: 15 ዓመት በሞላት ጊዜ አረጋዊ ዮሴፍ ያገለግላት ዘንድ ወደ ቤቱ ወሰዳት::

*በዚያም መልአከ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ዜና ድኅነትን ነግሯት አካላዊ ቃልን በማሕጸንዋ ጸነሰችው:: ነደ እሳትን ተሸከመችው: ቻለችው::
ወልደ እግዚአብሔርን ለ9 ወራት ከ5 ቀናት ጸንሳ: እንበለ ተፈትሆ (በድንግልና) ወለደችው:: (ኢሳ. 7:14) "ኢየሱስ" ብላ ስም አውጥታለት በገሊላ ለ2 ዓመታት ቆዩ::

*ሔሮድስ እገድላለሁ ብሎ በተነሳበት ወቅትም ልጇን አዝላ በረሃብ እና በጥም: በላበትና በድካም: በዕንባና በኃዘን ለ3 ዓመታት ከ6 ወራት ከገሊላ እስከ ኢትዮዽያ ተሰዳለች:: ልጇ ጌታችን 5 ዓመት ከ6 ወር ሲሆነው: ለድንግል ደግሞ 21 ዓመት ከ3 ወር ሲሆናት ወደ ናዝሬት ተመለሱ::

*በናዝሬትም ለ24 ዓመታት ከ6 ወራት ልጇን ክርስቶስን እያሳደገች: ነዳያንን እያሰበች ኑራለች:: እርሷ 45 ዓመት ልጇ 30 ዓመት ሲሆናቸው ጌታችን ተጠምቆ በጉባኤ ትምሕርት: ተአምራት ጀመረ:: ለ3 ዓመታት ከ3 ወራትም ከዋለበት እየዋለች: ካደረበትም እያደረች ትምሕርቱን ሰማች::

*የማዳን ቀኑ ደርሶ ልጇ ክርስቶስ ሲሰቀልም የመጨረሻውን ፍጹም ሐዘን አስተናገደች:: አንጀቷ በኃዘን ተቃጠለ:: በነፍሷም ሰይፍ አለፈ:: (ሉቃ. 2:35) ጌታ በተነሳ ጊዜም ከፍጥረት ሁሉ ቀድማ ትንሳኤውን አየች:: ለ40 ቀናትም ሳትለይ ከልጇ ጋር ቆየች:: ከልጇ ዕርገት በሁዋላ በጽርሐ ጽዮን ሐዋርያትን ሰብስባ ለጸጋ መንፈስ ቅዱስ አበቃች:: በጽርሐ ጽዮንም ከአደራ ልጇ ከቅዱስ ዮሐንስ ጋር ለ15 ዓመታት ኖረች:: በእነዚህ ዓመታት ሥራ ሳትፈታ ስለ ኃጥአን ስትማልድ: ቃል ኪዳንን ከልጇ ስትቀበል: ሐዋርያትን ስታጽናና: ምሥጢርም ስትገልጽላቸው ኑራለች::

ዕድሜዋ 64 በደረሰ ጊዜ ጥር 21 ቀን መድኃኒታችን አእላፍ ቅዱሳንን አስከትሎ መጣ:: ኢየሩሳሌምን ጨነቃት:: አካባቢውም በፈውስ ተሞላ:: በዓለም ላይም በጐ መዓዛ ወረደ:: እመ ብርሃን ለፍጡር ከዚያ በፊት ባልተደረገ: ለዘለዓለምም ለማንም በማይደረግ ሞገስ: ክብርና ተአምራት ዐረፈች:: ሞቷ ብዙዎችን አስደንቁአል:: "ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ::
ሞታ ለማርያም የአጽብ ለኩሉ::"/ሞትማ ለሁሉ ይገባል የድንግል ማርያም ሞት ግን ከሁሉ ይለያል/ እንዲል::

*ከዚህ በሁዋላ መላእክት እየዘመሩ: ሐዋርያቱም እያለቀሱ ወደ ጌቴሴማኒ: በአጐበር ሥጋዋን ጋርደው ወሰዱ::
ይሕንን ሊቃውንት:-
"ሐራ ሰማይ ብዙኃን እለ አልቦሙ ሐሳበ::
እንዘ ይዜምሩ ቅድሜኪ ወመንገለ ድኅሬኪ ካዕበ::
ማርያም ሞትኪ ይመስል ከብካበ" ሲሉ ይገልጡታል::

*በወቅቱ ግን አይሁድ በክፋት ሥጋዋን እናቃጥል ስላሉ ቅዱስ ገብርኤል (ጠባቂ መልአክ ነው) እነርሱን ቀጥቶ: እርሷን ከቅዱስ ዮሐንስ ጋር ወስዶ በዕጸ ሕይወት ሥር አኑሯታል:: በዚያም መላእክት እያመሰገኗት ለ205 ቀናት ቆይታለች::

ቅዱስ ዮሐንስ መጥቶ ለሐዋርያቱ ክብረ ድንግልን ቢነግራቸው በጐ ቅንአት ቀንተው በነሐሴ 1 ሱባኤ ጀመሩ:: 2ኛው ሱባኤ ሲጠናቀቅም ጌታ የድንግል ማርያምን ንጹሕ ሥጋ ሰጣቸው:: እየዘመሩም በጌቴሴማኒ ቀብረዋታል::

በ3ኛው ቀን (ነሐሴ 16) እንደ ልጇ ባለ ትንሳኤ ተነስታ ዐርጋለች:: ትንሳኤዋንና ዕርገቷንም ደጉ ሐዋርያ ቅዱስ ቶማስ አይቶ: መግነዟን ተቀብሏል:: ሐዋርያቱም መግነዟን ለበረከት ተካፍለው: እንደ ገና በዓመቱ ነሐሴ 1 ቀን ሱባኤ ገቡ::

*ለ2 ሳምንታት ቆይተው: ሁሉንም ወደ ሰማይ አወጣቸው:: በፍጡር አንደበት ተከናውኖ የማይነገር ተድላ: ደስታና ምሥጢርንም አዩ:: ጌታ ራሱ ቀድሶ ሁሉንም አቆረባቸው:: የበዓሉን ቃል ኪዳን ሰምተው: ከድንግል ተባርከው ወደ ደብረ ዘይት ተመልሰዋል::

††† ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን: ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሳን ለምኚልን:: አእምሮውን: ለብዎውን: ጥበቡን በልቡናችን ሳይብን አሳድሪብን:: †††

††† ጥር 21 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ በዓላት
1.በዓለ አስተርዕዮ ማርያም (እመቤታችን ከእረፍቱዋ በሁዋላ ለደቀ መዛሙርት በዚሁ ቀን ተገልጣ ነበር)
2.ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ (ታላቅ ሊቅና ጻድቅ)
3.ቅድስት ኢ

ላርያ እናታችን (የዘይኑን ንጉሥ ልጅ)
4.ቅዱስ ኤርምያስ ነቢይ
5.ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ
6.ቅዱስ ኒቆላዎስ ሰማዕት
7.አባ ፊቅጦር

††† ወርሐዊ በዓላት
1.አባ ምዕመነ ድንግል
2.አባ አምደ ሥላሴ
3.አባ አሮን ሶርያዊ
4.አባ መርትያኖስ
5.አበው ጎርጎርዮሳት

††† "ወዳጄ ሆይ! ተነሺ:: ውበቴ ሆይ! ነዪ:: በዓለት: በንቃቃትና በገደል መሸሸጊያ ያለሽ ርግብ ሆይ! ቃልሽ መልካም: ውበትሽም ያማረ ነውና: መልክሽን አሳዪኝ::
ድምጽሽንም አሰሚኝ::"
(መኃ. 2:13)

🌹<  ወስብሐት ለእግዚአብሔር  >🌹
               🌹🌹🌹
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

28 Jan, 05:05


🔔 ስንክሳር ጥር 20 🔔

† እንኳን ለቅዱሳን አክሎግ ቀሲስ: መርምሕናም: ወዮሐንስ ወንጌሉ ዘወርቅ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †

† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †

🌿† ቅዱስ አክሎግ ሰማዕት †🌿

† ቤተ ክርስቲያን ካፈራቻቸው ዓበይት ሰማዕታት አንዱ ይህ ቅዱስ ነው:: "አክሎግ" ማለት "በእግዚአብሔር ዘንድ ጣፋጭ (ተወዳጅ)" ማለት ነው:: እውነትም ጥዑም ዜና: ጣፋጭ ሕይወት ያለው አባት ነው:: "መልአክ ስምን ያወጣል" የሚባለው እንዲህ ላለው ነውና::

እርሱ የወላጆቹ ፍሬ ነው:: በ3ኛው መቶ ክ/ዘ የነበሩ ወላጆቹ ለልጃቸው ያወረሱት ሞልቶ የተረፈ ሃብታቸውን አልነበረም:: ይልቁኑ ፍቅረ ክርስቶስን: ምሥጢረ መጻሕፍትን: ክርስቲያናዊ ስምን ነው እንጂ::

ቅዱስ አክሎግ ገና ከልጅነቱ ወደ ት/ቤት ገብቶ: ቅዱሳት መጻሕፍትን ተምሮ: ሐዲስ ኪዳንን በሙሉ: መኀልየ ነቢያትን: መዝሙረ ዳዊትን አክሎ በቃሉ አጠና:: ቅዱስ ቃሉ ለእርሱ እውቀት አልነበረም: ሕይወት እንጂ:: ሳይሰለች ያነበው: በሕይወቱም ይተረጉመው ነበርና::

በዚህ ንጹሕ ሕይወቱም ፈጣሪውን አስደስቶ ብዙ ተአምራትን ሠርቷል:: ከዚያም ተጋድሎውን ቀጥሎ በትሕርምት ኑሯል:: ቀሲስ ሆኖ ሲሾምም ቅዱሳን መላእክት "ይገባዋል!" ሲሉ 3 ጊዜ ጮሁ:: በጽድቅ ጸንቶም ዘመናት አለፉ::

በዘመነ ሰማዕታትም ነጭ በነጭ ለብሶ ብዙ መከራን ተቀበለ:: በዚህች ቀንም ከብዙ ተከታዮቹ ጋር ደሙ ፈሷል:: ስለዚህም ቤተ ክርስቲያን "ጻድቅ: ንጹሕ: ድንግል: ባሕታዊ: ቀሲስ ወሰማዕት" ብላ ታከብረዋለች:: ጌታም "ስምህን ያከበረውን: የተሰየመውን እምርልሃለሁ" ብሎታል::

🌿† ቅዱስ መርምሕናም ሰማዕት †🌿

††† ሰማዕቱ በቤተ ክርስቲያን ትልቅ ቦታ ከሚሰጣቸው ዐበይት ቅዱሳን አንዱ ነው:: በየአብያተ ክርስቲያናቱ ከሚሳሉ ቅዱሳንም አንዱ ነው:: ሃገሩ አቶር (በፋርስ አካባቢ) ሲሆን አባቱ ሰናክሬም የሚባል ንጉሠ ነገሥት ነው::

እናቱ ምንም ክርስቲያን ብትሆንም ስለ ፈራች ሁለቱን ልጆቿን (መርምሕናምና ሣራን) ክርስትናን አላስተማረቻቸውም:: ሁለቱም ወጣት በሆኑ ጊዜም ከንጉሥ አባታቸው ጋር ይወጡ ይገቡ ነበርና እናታቸው በሐዘን ጸለየች:: ወዲያውም ወጣቷ ሣራ በለምጽ ተመታች::

የሚፈውሳት ጠፋ:: መርምሕናም ግን ጐበዝ ወጣት ነውና 40 የጦር አለቆችን ይመራ ነበር:: በዚያው በ4ኛው መቶ ክ/ዘመን ቅዱስ መርምሕናም 40 ተከታዮቹን ይዞ ለአደን ወደ ዱር ሲወጣ ከአባ ማቴዎስ ገዳማዊ ጋር ተገናኘ::

ጻድቁ ለብዙ ዓመታት በበርሃ የኖሩ አባት ናቸው:: አካላቸው በጸጉር ስለ ተሸፈነ ደንግጦ ሲሸሽ "ልጄ አትፍራ! እኔም እንዳንተ የክርስቶስ ፍጡር የሆንኩ ሰው ነኝ" አሉት::

እርሱ ግን "ደግሞ ክርስቶስ ማነው?" ሲል ጠየቃቸው:: አባ ማቴዎስም ምሥጢረ ክርስትናን ከመሠረቱ አስተምረው የክርስቶስን የባሕርይ አምላክነት ነገሩት::

ቅዱስ መርምሕናም ግን "ክርስቶስ አምላክ እንደ ሆነ አምን ዘንድ እህቴን አድንልኝ" አላቸው:: "አምጣት" ብለውት አመጣት:: ጻድቁ ጸሎት አድርሰው መሬትን ቢረግጧት ውኃን አፈለቀች:: "በእምነት: በስመ ሥላሴ ተጠመቁ" አሏቸው::

ቅዱሱ: እህቱ ሣራና 40 የጦር አለቆች ተጠምቀው ሲወጡ ሣራ ከለምጿ ነጻች:: ፈጽሞም ደስ አላቸው:: ወደ ቤተ መንግስት ተመልሰውም ቅዱስ መርምሕናም ከእናቱ: ከእህቱና ከ40 ተከታዮቹ ጋር ክርስቶስን ሊያመልኩ ጀመሩ::

ንጉሡ ሰናክሬም ግን ነገሩን ሲሰማ ተቆጣ:: እነርሱም ወደ ተራራ ሸሹ:: ንጉሡ "ልጆቼ! መንግስቴን ውረሱ" ብሎ ቢልክባቸውም እንቢ አሉ:: ስለ ተበሳጨም ቅዱስ መርምሕናምን: ቅድስት ሣራንና 40ውን ቅዱሳን በሰይፍ አስመታቸው::

ሥጋቸውን በእሳት ሊያቃጥሉ ሲሉ ግን መነዋወጥ ሆኖ ብዙ አረማውያን ሞቱ:: ንጉሡም አብዶ አውሬ (እሪያ) ሆነ:: ያን ጊዜ አባ ማቴዎስ ከበርሃ ወጥተው ንጉሡን ሰናክሬምን ፈወሱት::

እርሱም አምኖ የልጆቹና የ40ውን ሥጋ በክብር አኖረ:: በሃገሩ አቶርም የእመ ብርሃን ማርያምን ቤተ መቅደስ አነጸ:: በክርስትና ኑሮም ዐረፈ:: እርሱ ከተቀበረ በኋላ ግን የከለዳውያን ንጉሥ መጥቶ አቶርን ወረራት::

ንግሥቲቱን (የቅዱሳኑን እናት) ከሕፃኑ ልጇ ጋርም ገደለ:: በኋላም "ለጣዖት ስገዱ" ማለቱን የሰሙት የቅዱስ መርምሕናም ወታደሮች ደርሰው በምስክርነት ተሰየፉ:: ቁጥራቸውም 170,000 ሆነ::

††† ቸሩ እግዚአብሔር ከወዳጆቹ በረከት ያሳትፈን፡፡
††† ጥር 20 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ አክሎግ ቀሲስ (ሰማዕትና ጻድቅ)
2.ቅዱስ መርምሕናም ሰማዕት (ቅዳሴ ቤቱ)
3.ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌሉ ዘወርቅ (ቅዳሴ ቤቱ)
4.አባ አብድዩ ጻድቅ
5.ቅዱስ ብሕኑ ሰማዕት
6.ቅዱስ አብሮኮሮስ ሐዋርያ (የወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ ደቀ መዝሙር)
7.አባ ኖሕ

††† ወርኀዊ በዓላት
1.ቅዱስ ዮሐንስ ሐፂር
2.ቅዱስ ቴዎድሮስ ሊቀ ሠራዊት
3.ቅዱስ አሞንዮስ
4.ቅዱስ ካሌብ ንጉሠ ኢትዮጵያ
5.ቅድስት ሳድዥ የዋሂት

🌹<  ወስብሐት ለእግዚአብሔር  >🌹
               🌹🌹🌹
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

28 Jan, 01:08


ቤተ ክርስቲያንን ማዕከል አድርጎ መሥራት!
.
ስለቤተ ክርስቲያን ስንናገር፤ ስንመሰክር፤ ስንመካከርና ስንጽፍ በእውነትና በትክክል ማዕከል የምናደርገው ቤተ ክርስቲያንን ነው?
.
ስለቤተ ክርስቲያን ስንቆጭ፤ ስናዝንና ስንከፋ በእውነትና በትክክል ማዕከል የምናደርገው ቤተ ክርስቲያንን ነው?
.
ስለቤተ ክርስቲያን ጥብቅና ስንቆም፤ ስንሞግትና ስንከራከር በእውነትና በትክክል ማዕከል የምናደርገው ቤተ ክርስቲያንን ነው?
.
ስለቤተ ክርስቲያን ስንሰጋ፤ የቢሆን ሐሳባችንን ስናስቀምጥና መጻኢ ተግዳሮቶችን ስንተነብይ በእውነትና በትክክል ማዕከል የምናደርገው ቤተ ክርስቲያንን ነው?
.
ስለቤተ ክርስቲያን ስንቀና፤ ስህተት ነው ያልነውን ስንነቅፍ፤ ዳተኝነትን ስንተች፤ ተሳስተዋል ያልናቸውን ስናርም በእውነትና በትክክል ማዕከል የምናደርገው ቤተ ክርስቲያንን ነው?
.
በእውነትና በትክክል ቤተ ክርስቲያንን ማዕከል ማድረግ ብንችልማ በዚህ ልክ ቋንቋችን እንዴት ሊደበላለቅ ቻለ! በዚህ መጠንስ እንዴት ልንለያይ ቻልን፤ በዚህ ሁኔታስ ልዩነታችን እንዴት ሊሰፋ ቻለ! ባቢሎንስ በመካከላችን እንዴት ሆና በቅላ ታየች፤ ቋንቋችንስ እንዴት ተደባለቀ!!!
.
ቤተ ክርስቲያንን ማዕከል አድርገን መሥራት ከቻልን፤ የእያንዳንዱ ሙከራችን፤ የየግል ዕይታና ምልከታችን፤ የእያንዳዱ ተግባራችንና እንቅስቃሴያችን ማዕከሉ ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን እንድትሆን ማድረግ ከቻልን ልዩነታችን ይጠባል፤ ቋንቋችን የሚሰማና የሚደመጥ ይሆናል፤ ዜናችን እስከ ምድር ዳርቻ ድረስ የገነነና የተሰማ ይሆናል፤ የታፈረችና የተከበረች፤ የተደመጠችና የተፈራች፤ የሰፋችና የተዘረጋች፤ ቅርንጫፏን ያስረዘመችና ስሯን የሰደደች ክርስቶሳዊትና ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ትኖረናለች!
.
ቤተ ክርስቲያንን ማዕከል አድርገን አንሥራ!!!

በዔዶም ኃይሉ

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

27 Jan, 12:55


[[ኦርቶዶክሳዊ የትዳር ጉዞ]]

ጊዜው የትዳርም አይደል
እዚህም እዛም "መጣ መርአዊ.../ወመራት'' እየተባባልንም አይደል አዲስ አበቤዎች 50% የፍቺ መጠን ጨመረ ሲሉ ትዝ ሲለኝ ገዝቼ ያላነበብኩትን መጽሐፍ እንዲህ አንስቼ ጠገብኩበት ለናንተም ጋበዝኳችሁ።

በሚጠቅም ነገር ላይ ጊዜያችሁን አባክኑ Social Mediaንም ቢሆን አይናችሁን ካላዘናችሁለት የሚጠቅመውን ሰው Like and following ላይ ተጭነው ጊዜዎን ያትርፉ!

*"በትዳር ጉዞ...ማናቸውም የምናደርጋቸው ነገሮች ለአንድነታችን ቅድሚያ የሰጡ መሆናቸውን ልብ እንበል!....አረንጓዴ መብራት ሲበራ የማለፍ መብቱ የአንተ ቢሆንም የትዳር አጋርህ አምቡላንስ እየነዳች እንዳለ ቆጥረህ ቅድሚያ ስጥ!"

"አለም አቀፍ ጥናቶች እንደሚያሳዩት በትንሿ ቤተክርስቲያን ውስጥ የሚያጋጥሙንና አያያዛቸውን ካላወቅናቸው ወደ ፍቺ ሊዳርጉን የሚችሉ ዘጠኝ ዋና ዋና ምክንያቶች ተግባቦት፣ ቅራኔ፣ ገንዘብ፣ ልጅ አስተዳደግ፣ ቤተሰቦቻችን፣ ሩካቤ፣ ዘረኝነት፣ ጓደኞች እና ለራስና ለቤተሰብ የሚሰጡ ጊዜዎች ናቸው።"

የመጽሐፉ ስም:- ኦርቶዶክሳዊ የትዳር ጉዞ
ጸኃፊው:- ገብረ እግዚአብሔር ኪዴ ነው።
የሕትመት ዘመኗ:- ጥቅምት 2016(የመጀመሪያ ኅትመት)
የሽፋን ዋጋዋ:- 270 ብር
የገጽ ብዛት :- 140
በውስጥ ይዘቷ ከማውጫ፣ ከመቅድምና መግቢያ እንዲሁም በስተመጨረሻ ላይ ካላት ዋቢ መጻሕፍት ውጪ በ፮(6) ዋና ዋና ክፍል እጥር ምጥን ያለች ዝግጅትን የያዘች ቅመም መጽሐፍ ናት።

በክፍል አንድ ይዘቷ ስለ ኦርቶዶክሳዊ የትዳር ጉዞ መነሻነት ምንነትና መሠረት ምሳሌዎችን እያካተተች ወደ ሁለተኛው ክፍል ትዘልቃለች በሁለተኛው ክፍል "የትዳር ጉዞ መንገድ ዳር ምልክቶች" በሚል አርዕስት ስለ አራቱ የትዳር ሕይወት ጉዞ ፈረሶች በሰፊው ከነምሳሌው አብራርታ ትዘጋለች።
ክፍል ሦስት ላይ ስትደርሱ "የት እንደ ነበርን" በሚል አርዕስቷ ከትዳርና ከእጮኝነት ጊዜ በፊት ስለነበረን የቤተሰብ አስተዳደግ ጠባሳዎች በእጮኝነት እና በትዳር ሕይወት እንዴት ጣልቃ እንደሚገቡና ሊገቡ እንደሚችሉ እና ችግሩን ልናባብስም ልንፈታበት የምንችልባቸውን መንገዶች በምሳሌ(Case Scenarios) በማስደገፍ በአጭሩ ግልጽ በሆነ ቋንቋ ሥልጠናዊ አካሔድ ፍሰት ታስዳስሰናለች። በዚህ ክፍል መጨረሻ የተቀመጠ በአንድ እጮኝነት ሂደት ሂደታችን ጤናማ ስለመሆኑና አለመሆኑ እንዲሁም ለውሳኔያችን መጠየቅ ያሉብን የግንኙነት ሂደት መጠይቆች አስቀምጦልን ወደ አምስተኛው ክፍል ይሻገራል።

የአምስተኛው ክፍል ርዕሰ ጉዳይ "ለኦርቶዶክሳዊ ጉዞ የሚያስፈልጉ..." በሚል ጀምሮ ስለ መንፈሳዊነትና ከእግዚአብሔር ጋር መጣበቅን፣ ስለ ትዳር ወንጌል፣ ስለ ይቅርታና ንስሀ እና ምክረ ካህን አስፈላጊነት በጥቂቶ ዳስሶልን በኦርቶዶክሳዊ የእጮኝነት ደረጃ አምስት እንከኖችን በማብራራት ወደ መጨረሻው ክፍል ይዘልቃል።
ስድስተኛው ክፍል "ኦርቶዶክሳዊ የትዳር ጉዞ ስለሚጀመርበት(ሰርግ)" መሠረታዊ የሆኑ ዝግጅትና ውሎ በአጭሩ ጠቅሶ ያበቃል።

መጽሐፏ ልክ ስልጠና ላይ ተቀምጣችሁ ስልጠና እንደምትወስዱ ዓይነት የሥልጠና ፍሰት የተዘጋጀች ስለሆነች እንደምንም ብላችሁ ጀምሩ እንጂ ሳትጨርሷት ውላችሁ አታድሩም።

መጽሐፏ ላላገባም፣ ላገባም የምትሆን የመኖር ሚዛን መሠረት ማስጠበቂያ ናትና ባገኛችሁት አጋጣሚ አቅሙ ካላችሁ ገዝታችሁ አሊያም በሽያጭ ሱቅ በመሔድ እዛው ተቀምጣችሁ ማንበብ ብትችሉ ስል እንዲህ በዳሰሳ በማቅረብ ጋብዣችኋለሁ።

መልካም ቆይታ!
🌹<  ወስብሐት ለእግዚአብሔር  >🌹
               🌹🌹🌹
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

27 Jan, 09:46


ነገ ነገን ሲወልድ

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

27 Jan, 05:25


🔔ስንክሳር ጥር 19 🔔
እንኳን ለጻድቅ አቡነ ያፍቅረነ እግዚእ ዘጉጉቤን ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን።

† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †

† አቡነ ያፍቅረነ እግዚእ ዘጉጉቤን †

† በኢትዮዽያ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ መካከለኛው ዘመን (በተለይ ከ13ኛው እስከ 15ኛው መቶ ክ/ዘመን ድረስ ያለው) የብርሃን ዘመን ይባላል:: ምክንያቱም ዘመኑ
*ክርስትና ያበበበት::
*መጻሕፍት የተደረሱበት::
*ስብከተ ወንጌል የተስፋፋበት::
*ገዳማዊ ሕይወት የሠመረበት ወቅት በመሆኑ ነው::

ለዚህ ትልቁ አስተዋጽኦ ደግሞ:-
¤አቡነ ተክለ ሃይማኖት::
¤አቡነ ኤዎስጣቴዎስ::
¤አባ ሰላማ ካልዕ::
¤አቡነ ያዕቆብ::
¤ቅዱሱ ንጉሥ ዘርዓ ያዕቆብ::
¤አቡነ ኢየሱስ ሞዐ ዘሐይቅ::
¤አቡነ መድኃኒነ እግዚእን የመሰሉ አበው መነሳታቸው ነው::

በተጨማሪም:-
¤12ቱ ንቡራነ ዕድ::
¤7ቱ ከዋክብት::
¤47ቱ ከዋክብት::
¤5ቱ ከዋክብት የሚባሉ አበው አስተዋጽኦም ልዩ ነበር:: ከእነዚህ መካከልም የ7ቱ እና የ47ቱ ከዋክብት አስተማሪ: የአበው 3ቱ ሳሙኤሎች (ዘዋልድባ: ዘጣሬጣና ዘቆየጻ): የሌሎችም እልፍ አእላፍ ቅዱሳን አባት የሆኑት አባ መድኃኒነ እግዚእ የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳሉ::

ጻድቁ ቅዱሳኑን ሰብስበው: አስተምረው: አመንኩሰው: መርቀው ሰደው: ሃገራችንን እንዲያበሩ በማድረጋቸው እንደ አባ ኢየሱስ ሞዐ እርሳቸውም "ወላዴ አእላፍ ቅዱሳን" ይባላሉ::

ከእነዚህ ቅዱሳን የጻድቁ ፍሬዎች አንዱ አቡነ ያፍቅረነ እግዚእ ናቸው:: ጻድቁ አንዳንዴ "አፍቀረነ እግዚእ" እየተባሉም ይጠራሉ:: ትርጉሙም "ጌታ ወደደን" እንደ ማለት ነው::

ያፍቅረነ እግዚእ የነበሩት በ14ኛው መቶ ክ/ዘ ሲሆን ቁጥራቸው ከ7ቱ ከዋክብት ነው:: ጻድቁ ከልጅነት ጀምሮ በሥርዓቱ ከማደጋቸው ባሻገር እጅግ የተማሩ እንደነበሩም ይነገርላቸዋል::

ለምናኔ ከወጡ በሁዋላ ከኖሩባቸው ቦታዎችም 3ቱ ተጠቃሽ ናቸው:: የመጀመሪያውና ትልቁን ሥፍራ የሚይዘው ደግሞ ደብረ በንኮል ነው:: ጻድቁ በዚህ ገዳም ከታላቁ ቅዱስ አባ መድኃኒነ እግዚእ ሥርዓተ ገዳምን : ትኅርምተ አበውን : ተጋድሎተ ቅዱሳንን አጥንተው ለመዓርገ ምንኩስና በቅተዋል::

በገዳሙም ለተወሰነ ጊዜ አገልግለው ወደ ጣና አካባቢ ከአቡነ ያሳይና ከአባ ሳሙኤል ዘዋሊ ጋር መጥተዋል:: የመምጣታቸው ምክንያትም ስብከተ ወንጌልን ለማዳረስና ገዳማትን ለመመሥረት ነው::

ሶስቱ ቅዱሳን ለተወሰነ ጊዜ ከቆዩ በሁዋላ አቡነ ሳሙኤል ወደ ዋልድባ ሲሔዱ አቡነ ያሳይ ደግሞ ማንዳባን አቀኑ:: ያፍቅረነ እግዚእም ጌታ ባዘዛቸው መሠረት ጣና ውስጥ ገዳም አቅንተው ኑረዋል:: ይህ ገዳማቸው ዛሬም ድረስ በስማቸው ይጠራል::

ጻድቁ አፍቀረነ እግዚእ 3ኛው የሚታወቁበት ገዳም ማኅበረ ዴጌ (ጻድቃነ ዴጌ) ሲሆን ገዳሙ በአክሱም ዙሪያ ይገኛል:: እርሳቸው 3ሺ ቅዱሳን የተሠወሩበትን ገዳም በማገልገላቸውም ዛሬም ድረስ በአካባቢው የታወቁ ሆነዋል::

በተረፈም አክሱም አካባቢ ሌሎች ገዳማትን እንዳቀኑም ይነገርላቸዋል:: ጻድቁ አቡነ ያፍቅረነ እግዚእ ለብዙ ዘመናት በተጋድሎ : በስብከተ ወንጌልና ገዳማትን በማስፋፋት ከኖሩ በሁዋላ በዚህች ቀን ዐርፈው ለክብሩ : ለርስቱ በቅተዋል::

††† አምላከ ቅዱሳን በጻድቁ አማላጅነት ይቅር ብሎ በረከታቸውን ያሳድርብን::

††† ጥር 19 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ጻድቁ አቡነ ያፍቅረነ እግዚእ (አፍቀረነ እግዚእ ዘጉጉቤ - ጣና ውስጥ - ከሰባቱ ከዋክብት አንዱ)
2.አባ ባሱራ
3.ቅድስት ኔራ
4.ቅድስት በርስጢና
5.አባ ዝሑራ

††† ወርሐዊ በዓላት
1.ቅዱስ ገብርኤል ሊቀ መላዕክት
2.ቅዱስ ኤስድሮስ ሰማዕት
3.አባ ዓቢየ እግዚእ ጻድቅ (ታቦታቸው ጎንደር ከተማ ቀበሌ 09 አካባቢ ይገኛል)
4.አቡነ ስነ ኢየሱስ
5.አቡነ ዮሴፍ ብርሃነ ዓለም

🌹<  ወስብሐት ለእግዚአብሔር  >🌹
               🌹🌹🌹
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

25 Jan, 15:39


🙏 ስንክሳር ጥር 18 🙏

✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡

✞ ጥር 18 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ✞

" ቅዱስ ጊዮርጊስ ልዳዊ "

=> መጽሐፈ ገድሉ እንደሚለው የሰማዕታት አለቃቸው: አንድም ሞገሳቸው ታላቅና ክቡር ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ ከ7 ዓመታት
ስቃይ በኋላ ተሰይፏል:: ይህስ ጥንተ ነገሩ እንደምን ነው ቢሉ:-

ቅዱሱ የተወለደው ከአባቱ ዘረንቶስ (አንስጣስዮስ) እና ከእናቱ ቴዎብስታ የድሮው ፋርስ ግዛት ፍልስጥኤም (ልዳ) ውስጥ
ነው:: የተባረኩ ወላጆቹ ክርስትናን ጠንቅቀው
አስተምረውት አባቱ ይሞታል::

ቅዱስ ጊዮርጊስ 20 ዓመት ሲሞላው የአባቱን ስልጣን እጅ ለማድረግ ሲሔድ የቢሩት (የአሁኗ ቤይሩት-ሊባኖስ) ሰዎች ዘንዶ/ደራጎን ሲያመልኩ አገኛቸው:: እርሱ ግን የከተማውን ሕዝብ አስተምሮ: አሳምኖ: ደራጎኑንም በፈጣሪው ኃይል ገድሎ መንገዱን ቀጥሏል::

ቅዱስ ጊዮርጊስ ወደ ዱድያኖስና 70 ነገሥታት ዘንድ ሲደርስ ክርስቶስ ተክዶ ለጣዖት ይሠገድ ነበር:: በዚያች ሰዓት ድንግል እመቤታችን ወደ ሰማዕቱ መጥታ መከራውንና ክብሩን ነገረችው:: እርሱም በክርስቶስ ስም መሞት ምርጫው ነበርና ከእመቤታችን ተባርኮ ወደ ምስክርነት አደባባይ (ዐውደ ስምዕ) ደረሰ::

ከዚያም ለተከታታይ 7 ዓመታት ብዙ ጸዋትወ
መከራዎችን ተቀበለ:: 3 ጊዜ ሙቶ ተነሳ:: ከሰው ልጅ የተፈጥሮ ትዕግስት
በላይ የሆነ ስቃይን ስለ ቀናች ሃይማኖት ሲል በመቀበሉ
የሰማዕታት አለቃቸው: ፀሐይና የንጋት ኮከብ በሚል ይጠራል:: "ተውላጠ ጻማሁ ወሕማሙ:
ዘተለዐለ ሞገሰ ስሙ" እንዲል መጽሐፍ::

ከ7 ዓመታት መከራ በኋላም ከብዙ ተዓምራት ጋር
ተሰይፎ ደም: ውሃና ወተት ከአንገቱ ፈሷል:: 7
አክሊላትም ወርደውለታል::

+" ዝርወተ ዓጽሙ "+

ይህቺ ዕለት ለሰማዕቱ 'ዝርወተ አጽሙ' ትባላለች::
በቁሙ 'አጥንቱ የተበተነበት' እንደ ማለት ነው:: ቅዱስ ጊዮርጊስን ለዘመናት በብዙ ስቃያት ሲያስጨንቁት ኖረው በጽናቱ አሸነፋቸው:: 70 ነገሥታትን ከነ ሠራዊታቸው ከማሳፈሩ ባሻገርም በርካታ (በመቶ ሺ የሚቆጠሩ) አሕዛብን ማርኮ ለሰማዕትነት አበቃ::

በዚህ የተበሳጨ ዱድያኖስም ኮከበ ፋርስ ቅዱስ
ጊዮርጊስን እንዲቆራርጡት አዘዘ:: ወታደሮቹም ቅዱሱን ቆራርጠው: በብረት ምጣድ ላይ ጠበሱት:: ያለ ርሕራሔም አካሉን አሳረሩት::
ቀጥለውም ፈጭተው አመድ አደረጉት::

በአካባቢው ወደ ነበረው ትልቅ ተራራ ጫፍ (ደብረ
ይድራስ) ወጥተውም በነፋስ በተኑት::
"ሐረድዎ ወገመድዎ: ወዘረዉ ሥጋሁ ከመ ዓመድ" እንዲል:: (ምቅናይ)

እነርሱ ይህንን ፈጽመው ዘወር ሲሉ ግን የቅዱሱ ዓጽም ባረፈባቸው ዛፎች: ቅጠሎችና ድንጋዮች ሁሉ "ቅዱስ ጊዮርጊስ ሊቀ ሰማዕታት" የሚል ጽሑፍ ተገኘ:: ስለዚህም ይህቺ ዕለት ቅዱሱ አለቅነትን የተሾመባት ናት ማለት ነው::

ወዲያው ግን ኃያል ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ
ከተበተነበት ተነስቶ ወታደሮችን አገኛቸውና "በክርስቶስ እመኑ" ብሎ: አስደንቆ ወደ ሕይወት መራቸው:: 70ው ነገሥታት ግን አፈሩ::

+" ቅዱስ ባኮስ ጃንደረባው "+

'ጃንደረባ' የሚለው ቃል በግዕዙ 'ሕጽው' ተብሏል:: ይህ ስም በቤተ ክርስቲያን የተለመደ እንጂ እንግዳ አይደለም:: መድኃኒታችን እንዳለው በተፈጥሮ የሆኑ: ሰዎች እንዲያ ያደረጉዋቸውና ራሳቸውን ስለ ጽድቅ ጃንደረባ ያደረጉ ብዙዎች ናቸውና::

ኢትዮዽያዊው ጃንደረባ ቅዱስ ባኮስም (አንዳንዴ
አቤላክ / አቤሜሌክም ይባላል):- *በ1ኛው መቶ ክ/ዘመን በሃገራችን ኢትዮዽያ ተወልዶ
ያደገ *ነገሥታቱንና ሃገሩን በሙያው ያገለገለ
*በተለይ ከ34 እስከ 46 ዓ/ም ለነገሠችው ንግሥት ሕንደኬ ገርስሞት በገንዘብ ሚንስትርነት ያገለገለ
*በገንዘቧ ላይ ሁሉ አዛዥ (ታማኝ) የነበረ
*ጃንደረባ በመሆኑ ለንግሥቲቱና ቤተሰቧ ቅርብ የነበረ
*መጻሕፍትን የሚያነብና የሚመረምር
*ዘወትር ወደ ኢየሩሳሌም እየሔደ ከቅዱሳት መካናት የሚሳለም በጐ ሰው ነበር::

በግብረ ሐዋርያት ምዕ. 8:26 ላይ እንደ ተጠቀሰው ቅዱሱ ከኢየሩሳሌም ለፋሲካና ለእሸት በዓል ነበር የሔደው:: ሲመለስ መንፈስ ቅዱስ ከፊልዾስ ጋር በጋዛ አገናኝቶታል:: በዚያም ምሥጢረ ክርስትናን ተምሮ: በክርስቶስ
አምላክነትና አዳኝነት አምኖ ተጠምቁዋል::

ክርስትናን ለኢትዮዽያ በ34 ዓ/ም አምጥቷል::
"ጃንደረባው ለወገኖቹ ሐዋርያ ሆነ" ሲል ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ እንደ ተናገረው ወደ ሃገራችን ተመልሶ: ስለ ክርስቶስ ሰብኮ በርካቶችን አሳምኗል::

ቀጥሎም ሃብቱን ንቆ (መንኖ): ከኢትዮዽያ እስከ ሕንድ ወንጌልን ሰብኮ በዚህች ዕለት በሰማዕትነት ዐርፏል:: (ተሰውሯል የሚሉም አሉ)

<< በእውነት ለቅዱስ ባኮስ ክብር ይገባል:: >>

+" ቅዱስ ያዕቆብ ዘንጽቢን "+

ይህ ቅዱስ ሰው:--
*እጅግ የተመሠከረለት ሊቅ
*በፍጹም ትሕርምት የኖረ ገዳማዊ
*በርካቶችን ወደ ክርስትና ያመጣ ሐዋርያዊ
*ለአእላፍ ምዕመናን እረኛ የሆነ የንጽቢን (ሶርያ) ዻዻስ
*ለጀሮ ድንቅ የሆኑ ተአምራትን የሠራ ገባሬ መንክራት
*ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊን ጨምሮ በርካታ ሊቃውንትን ያፈራ ታላቅ መምሕር
*ለክርስቶስና ለእመቤታችን ታጥቆ የተገዛ የፍቅር ሰው
*እጣቶቹ እንደ ፋና የሚያበሩለት ማኅቶት
*ራሱን ዝቅ አድርጐ በቆሸሸ ልብስ የሚኖር የትህትና ሰው ነው::

በ325 (318) ዓ/ም: በኒቅያ 318ቱ ሊቃውንት
ሲሰበሰቡና አርዮስን ሲያወግዙ እርሱ አንዱ ነበር::
በሥፍራውም ሙት አስነስቶ ሕዝቡን አስደምሟል:: በዚያም የቤተ ክርስቲያንን ሥርዓት ሠርቶ ወደ ሃገሩ ተመልሶ በቅድስና ኑሮ በዚህች ቀን
ዐርፎ በክብር ተቀብሯል::

✞ጥር 18 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ ጊዮርጊስ መክብበ ሰማዕታት (ዝርወተ ዓጽሙ)
2.ቅዱሳት ደናግል ማርያ እና ማርታ (ከ36ቱ ቅዱሳት
አንስት)
3.ቅዱስ ያዕቆብ ዘንፅቢን (ከ318ቱ)
4.ቅዱስ ባኮስ ኢትዮዽያዊ (አቤላክ / አቤሜሌክ)

=> ወርኀዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ ፊልዾስ ሐዋርያ
2.አቡነ ኤዎስጣቴዎስ ሰባኬ ሃይማኖት (ረባን)
3.አቡነ አኖሬዎስ ዘደብረ ጽጋጋ
4.ማር ያዕቆብ ግብፃዊ
5.ቅዱስ ያዕቆብ ሐዋርያ (ከ72ቱ አርድእት

🌹<  ወስብሐት ለእግዚአብሔር  >🌹
               🌹🌹🌹
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

24 Jan, 19:26


🌹 ስንክሳር ጥር 17 🌹

✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞

" አበዊነ ቅዱሳን መክሲሞስ ወዱማቴዎስ "
እኒህ ቅዱሳን የሥጋ ወንድማማቾች ሲሆኑ በቤተ ክርስቲያን ታሪክ እጅግ ተወዳጅ አባቶች ናቸው: ይኸውም "እንደ ንጋት ኮከብ የምታበሩ: ተጋዳይ: ቅዱሳንና ክቡራን የሆናችሁ ሮማውያን አባቶቻችን" ማለት ነው:: ሃገረ ሙላዳቸው ሮም ሁና አባታቸው ንጉሥ ለውንድዮስ ይባላል:: ይህ ንጉሥ ሮምን በምታክል ታላቅ ሃገር በ4ኛው መቶ ክ/ዘመን ነግሦ ሳለ መልካም ሰው ሆኖ ተገኝቷል::

ከመልካም ሚስቱ ከወለዳቸው መካከልም 2ቱ ከዋክብት ይጠቀሳሉ:: 2ቱ ቅዱሳን በአጭር የጊዜ ልዩነት የተወለዱ በመሆናቸው እንደ መንትያ ይቆጠራሉ::

ንጉሡ ለውንድዮስም ከእግዚአብሔር ዘንድ ላገኛቸው ልጆቹ ስም ሲያወጣ ታላቁን መክሲሞስ: ታናሹን ደግሞ ዱማቴዎስ ብሎታል:: ቅዱሳኑ በንጉሥ አባታቸው መልካም ፈቃድ ክርስትናን ተምረዋል::

ምንም እንኳ የንጉሥ ልጆች እና ልዑላን ቢሆኑም ተቀማጥለው አላደጉም:: ምቾት ብዙዎችን አጥፍቷልና:: ይህንን የተረዳ አባታቸው ሞገስን በፈጣሪያቸው ዘንድ እንዲያገኙ እንዲህ በበጐ ጐዳና አሳደጋቸው:: ቅዱሳን መክሲሞስና ዱማቴዎስ ካደጉና ለአካለ መጠን ከደረሱ በኋላ ቅዱሳት መጻሕፍትን ለማንበብ ይተጉ ነበር:: በተለይ ዜና ቅዱሳንን ከማንበብ አይጠግቡም ነበር:: እግዚአብሔርንም በፍቅር እያመለኩ በጾምና በጸሎት ይገዙለት ነበር::

ቅዱሳኑንም ለየት የሚያደርጋቸው አንዱ ይሔው ነው:: ወርቅና ብር በፊታቸው ፈሶ: በእግራቸው እየረገጡት: አገሩና ምድሩ እየሰገደላቸው: የላመ የጣመ ምግብ እየቀረበላቸው: የሞቀ የደመቀ መኝታ እየተነጠፈላቸው . . . ሁሉንም ስለ ፍቅረ
ክርስቶስ መናቃቸው ይደነቃል::

እነርሱ በክርስቶስ ፍቅር ሆነው የዚህን ዓለም ጣዕም ንቀዋልና የአባታቸውን ቤተ መንግስት ሊተዉ አሰቡ:: ወደ በርሃ ሔደው ለፈጣሪ ለመገዛት ሲያስቡ መውጫ መንገዳቸውን ይሹ ነበርና አንድ ጐዳና ተገለጠላቸው:: ከዚያም ለንጉሥ አባታቸው ሔደው "አባ! እኛ ወደ ኒቅያ (ታናሽ እስያ) ሔደን መባረክ እንፈልጋለን" ሲሉ ጠየቁት:: ወቅቱ ቦታዋ ስለ 318ቱ ቅዱሳን ሊቃውንት ሞገስን ያገኘችበት ጊዜ ነበር:: አባታቸውም መንፈሳዊ ሰው ነበርና ደስ እያለው ፈቀደላቸው:: ብዙ ወርቅን ሰጥቶ: ሸልሞ ከብዙ ሠራዊት ጋር ሸኛቸው::

ቅዱሳኑ ግን ለጥቂት ጊዜ በኒቅያ ሲጸልዩና ሲባረኩ ሰንብተው የአባታቸውን ሰራዊት ሰብስበው "እኛ ሱባኤ ልንይዝ ስለ ሆነ እንመጣለን" የሚል ደብዳቤን ሰጥተው ወደ ሮም ሸኟቸው::

ወታደሮችን ከሸኙ በኋላ ቅዱሳኑ በአካባቢው ወደ ሚገኝ አንድ ገዳም ሒደው ለአንድ ደግ መናኝ ምሥጢራቸውን ገለጹለት:: ልክ የንጉሡ ለውንድዮስ ልጆች መሆናቸውን ሲያውቅ
'አመንኩሰን' ያሉትን እንቢ አላቸው:: "ለምን?" ሲሉት "ደጉን አባታችሁን ማሳዘን አልፈልግም:: ግን ፈቃዳችሁ እንዲፈጸምላችሁ ወደ ሶርያ
ዝለቁ:: በዚያ አባ አጋብዮስ የሚባል ጻድቅ ገዳማዊ ሰው ታገኛላችሁ" ብሎ ወደ ሶርያ አሰናበታቸው:: ንጉሡ አባታቸው በወታደሮቹ ዓለምን ቢያካልልም ሊያገኛቸው አልቻለም::

እርሱ ፈጽሞ ሲያዝን እናታቸው ፈጽማ መጽናናትን እንቢ አለች:: መክሲሞስና ዱማቴዎስ ግን ምድረ ሶርያ ገብትው የጻድቁ አባ አጋብዮስ ደቀ መዛሙርት ሆኑ:: በእርሱም ዘንድ ለምናኔ የሚያስፈልጉ በጐ ምግባራትንና ትሩፋትን ከተማሩ በኋላ 2ቱንም አመነኮሳቸው::

በዚያ ቦታም እየታዘዙ: ፈጣሪን እያመለኩ: በጾም: በጸሎትና በትህትና ኖሩ:: አንድ ቀን ግን አባ አጋብዮስ ጠርቶ "ልጆቼ! ተባረኩ! በእናንተ ምክንያት ደስ ብሎኛልና::

በዚህች ሌሊት የመነኮሳት ሁሉ አለቃ ታላቁ ቅዱስ መቃርዮስ በራዕ ተገልጦ: ልጆች እንዲሆኑኝ ስጠኝ ብሎኛልና እኔ ሳርፍ ወደ ግብጽ ገዳመ አስቄጥስ እንድትሔዱ" አላቸው:: አባ አጋብዮስ ካረፈ በኋላ ግን እንደ ትዕዛዙ አልሔዱም:: ውዳሴ ከንቱን ይፈሩ ነበርና:: በዚያው በምድረ ሶርያ ግን በጥቂት ጊዜ: ገና በወጣትነት ከብቃት መዓርግ ስለ ደረሱ በርካታ ተአምራትን ሠሩ:: በሰው ዘንድም ፍጹም ተወዳጅ ሆኑ::

ስም አጠራራቸውም ሶርያን መላት:: በዘመኑ
በአካባቢው አንድ ግዙፍ ዘንዶ ተነስቶ ሰውንም
እንስሶችንም ፈጃቸው:: ሕዝቡም ሒደው በቅዱሳኑ ፊት አለቀሱ:: ያን ጊዜ ቅዱስ
መክሲሞስ (ትልቁ) ክርታስ አውጥቶ "አንተ ዘንዶ ይህ ክርታስ ወደ አንተ ሲደርስ ከማደሪያህ ውጣ: ሙት: ወፎችም ይብሉህ" ሲል ጻፈበት::

"ሒዳችሁ በበሩ ጣሉት" አላቸው:: አንድ ደፋር ሰው ተነስቶ ሰዎች ሁሉ እያዩት ወስዶ በዘንዶው መውጫ ላይ ጣለው:: በቅጽበትም ዘንዶው ወጥቶ ሞተ:: አሞሮችም ተሰብስበው
በሉት:: ከዚህ ድንቅ ተአምር የተነሳ ሕዝቡ የቅዱሳኑን አምላክ አከበረ::

ከዚህ በተረፈም በቅዱሳኑ ስም ታላላቅ ተአምራት ተደረጉ:: ርኩሳት መናፍስት ሁሉ ስማቸውን እየሰሙ ይሸሹ ነበርና:: ድውያን እነሱ በሌሉበት ስማቸው ሲጠራላቸው ይፈወሱ ነበር:: የአካባቢው ሰው ስማቸውን እየጠራ: በእነርሱም እየተማጸነ
ከመከራው ሁሉ ይድን ነበርና ለሕዝበ ክርስቲያኑ ሞገስ ሆኑ::

መርከበኞች ደግሞ ከማዕበል ለመዳን የቅዱሳኑን ስም በጀልባዎቻቸው ላይ ይጽፉ ነበር:: አንድ ቀን ግን የንጉሡ ለውንድዮስ ባለሟል ይህንን ጽሑፍ ተመልክቶ ስለ ጠረጠረ መርከበኛውን በንጉሡ ፊት አቀረበው::

ንጉሡም መርከበኛውን "የጻፍከው የማንን ስም ነው?" ቢለው "በሶርያ የሚገኙ 2 ወንድማማች ቅዱሳን ስም ነው" አለው:: ልጆቹ እንደ ሆኑ ገምቶ በመርከበኛው መሪነት ንግሥቲቱንና ሴት ልጁን ላካቸው:: እነርሱ በሐዘን ተሰብረው ነበርና::

ወደ ሶርያ ወርደው ባገኟቸው ጊዜም ከናፍቆትና ደስታ የተነሳ ታላቅ ጩኸትን እየጮሁ አለቀሱ:: "እንሒድ ወደ ሮም" ሲሏቸው ግን ቅዱሳኑ "የለም! እኛ የክርስቶስ ነን" ብለው እንቢ ስላሏቸው እያዘኑ ተመለሱ:: ንጉሡ ግን ይህንን ሲሰማ ደስ አለው:: "እነርሱ የዚህን ዓለም ኃላፊነት ተረድተዋል"
ሲልም አወደሳቸው::

በኋላ ግን "የሮሜ ሊቀ ዻዻሳት መሆን አለባችሁ" የሚል ነገር ሲሰማ ቅዱሳን መክሲሞስና ዱማቴዎስ ከሶርያ ወጥተው ወደ ግብጽ ወረዱ:: የከታላቁ ቅዱስ መቃርስ ዘንድ ደርሰውም ልጆቹ እንዲሆኑ ለመኑት::

"ልጆቼ! በርሃ አይከብዳችሁም?" ቢላቸው "ግዴለም!" አሉት:: በዚያም ከተራራው ሥር በዓት ሠርቶላቸው ለ3 ዓመታት በአርምሞ ቆዩ:: አንድ ቀንም ቅዱሳኑ እየጸለዩ ከአፋቸው የወጣ የብርሃን ምሰሶ ከመንበረ ጸባኦት ሲደርስ አይቶ ታላቁ መቃርስ አደነቀ:: በ5ኛው መቶ ክ/ዘመን መጀመሪያ አካባቢም ጥር 14 ቀን ታላቁ ቅዱስ መክሲሞስ ዐረፈ:: በዕለቱም የሰማይ ቅዱሳን ሁሉ ወርደው እየዘመሩ ወሰዱት:: ከ3 ቀን በኋላ ደግሞ ቅዱስ ዱማቴዎስ ዐረፈ::
በተመሳሳይ ቅዱሳኑ ሲወስዱት 2ቱንም ቅዱሳን ታላቁ መቃርስ በበዓታቸው ቀብሯቸዋል:: ቦታውም ደብረ ብርስም ተብሏል:: ትርጉሙም የሮማውያኑ ቅዱሳን ደብር እንደ ማለት ነው::

✞አምላከ ቅዱሳን በእነርሱ ላይ የበዛች ፍቅሩን ለእኛም ያድለን:: ፍሬ ትሩፋት: ፍሬ ክብር እንድናፈራም ይርዳን:: ክብራቸውንም አያጉድልብን::

✞ጥር 17 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን
በዓላት
1.ቅዱሳን እና ክቡራን የሚሆኑ አባቶቻችን "መክሲሞስ እና ዱማቴዎስ"

🌹<  ወስብሐት ለእግዚአብሔር  >🌹
               🌹🌹🌹
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

24 Jan, 14:22


በብፁዕ አቡነ ኤርምያስ አስተባባሪነት በወይብላ ምሥራቀ ፀሐይ ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን እየተገነባ የሚገኘውን አዳሪ የአብነት ት/ቤት በመደገፍ ክርስቲያናዊ ኃላፊነትዎን ይወጡ።

ፕሮጀክቱን ለመደገፍ፦
ለሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት አዳሪ የአብነት ት/ቤት ግንባታ ፕሮጀክት

#የኢትዮጵያ_ንግድ_ባንክ➛ 1000268895993
#አባይ_ባንክ ➛ 2071111086582027
#ህብረት_ባንክ ➛ 2100116574227024
#ዳሽን_ባንክ ➛ 5222981650011
#አቢሲኒያ_ባንክ ➛ 15332956
#ቡና_ባንክ ➛ 1559501004676
#አዋሽ_ባንክ ➛ 01320281141100
#ብርሃን_ባንክ ➛ 1001038222028
#ኦሮሚያ_ኢንተርናሽናል_ባንክ ➛ 3662379
#አማራ_ባንክ ➛ 9900018948811

ለበለጠ መረጃ፦
➛ +251 913708168
➛ +251 924397121
➛ +251 911549205

#ለወዳጅዎ_ያጋሩ

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

24 Jan, 12:46


ስፍራህን አትለቅም!
.
የኤርትራ ባሕር ሲከፈል ያየሁ እኔ ዮርዳኖስን መሻገር ያስፈራኛል!
.
ፈርዖንና ሠራዊቱ ሲሰጥሙ የተመለከትሁ እኔ ጎልያድን እፈራዋለሁ!
.
ከእሑድ እስከ አርብ መና የወረደልኝ እኔ አንድ ቅዳሜን ማመን አቅቶኝ መና ለቀማ ማልጄ እወጣለሁ፤ ትእዛዝ አፍርሼ ብዙ ብለቅምም አልተረፈልኝም፤ ትዕዛዝ አክብሮ ጥቂት የለቀመውም ከእኔ አላነሰበትም!
.
የተውኋትን ካራንን፤ የናቅኋትን ተሰሎንቄን ተመልሼ እናፍቃለሁ! የአባቴ ባሮች እንጀራ ጠግበው ተርፏቸው እየደፉ እኔ ግን ከዕርያ አሠር ልጠግብ እመኛለሁ፤ ቦኤዝ የሚቤዠኝ ሆኜ እያለሁ ቃርሚያ ልለቅም እወጣለሁ!
.
አንተ አልጋህን ተሸክመህ ሒድ ብለኸኝ፤ እኔ ግን የፈወሰኝን ማንነት የማላውቅ ነኝ!
.
የሕይወትን ውኃ አግኝቼው ጉድጓዱ ጥልቅ ነው፤ መቅጃም የለህም እያልሁ እከራከራለሁ!
.
በዘመን መካከል መለወጥ የሌለብህ፤ ትናንት እንደሠራኸው ዛሬም የምትሠራ አንተ ግን ያው አንተ ነህ! ስፍራህን አትለቅም!

በመ/ር ዔዶም ኃይሉ

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

24 Jan, 11:21


ገና በቁም ይፈርሳሉ!
ይሞታሉ!
ይጠፋሉ!
ይረሳሉም ቤተክርስቲያን ግን ትቀጥላለቾ! መሠረቷ ክርስቶስ ነውና ክርስትና በደሙ ለዘላለም ትኖራለች።

የሰራዊት አምላክ ጌታችን ሥጋውን ቆርሶ ደሙን አፍሶባት ከአንድ አካል በምሳሌነቱ አንድ ኅብረት/አንዲት ቤተ-ክርስቲያን መስርቶ ያጸናትን ቅድስት ቤታችንን ለመክፈል ከደርግ ዘመን ጀምሮ ከ40-50 ዓመታት በላይ ቀንናሌት በሴራ ሊበትኖት ያሰቡ እኩይ ልጆች የዛሬ አዛውንቶች ይኼው ሳንሞት በሕይወት በቁማቸው እየፈረሱ ነው።

ጌታ የቅድስት ቤተክርስቲያንን አንድነት ለዘለዓለሙ ይጠብቅልን!

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

24 Jan, 04:29


የዕቅበተ እምነት አካሔዳችን ላይ!!!
(ደብተራ በአማን እንደከተበው!)

1. ያለፉት ዓመታት የዕቅበተ እምነት አካሔዶቻችንን መመርመር፣ መፈተሸ፣ የሚታረመውን ማረም ያስፈልጋል፡፡ አካሄዳችን በስሕተት ትምህርት የታመመውን ለማከም ጥረት ከማድረግ ይልቅ በዋናነት ሕመሙ ወደሌላው አካል እንዳይሰራጭ በመስጋት ላይ ያተኮረ እንደ ነበረ ይሰማኛል፡፡ ሕመሙን እንደሚገባው ባለመመርመር መዳን የሚችል አካልም የሚቆረጥበት አጋጣሚ መኖሩን አልፎ አልፎ ከሚመለሱት ወንድሞቻችን እንረዳለን፡፡
ዕቅበተ እምነት ማለት ያለውንም እንዳይወጣ እያረሙ ከሕማሙ እየፈወሱ በቤቱ ማቆየት ነውኮ!

2. የተዋሥኦ ባሕላችን በጉባኤ ቤት ጥሩ የሚባል ነው፡፡ የጉባኤ ቤቱን ወደ አደባባይ ማውጣት ላይ ግን ጥንቃቄ ያስፈልጋል፡፡
ከውስጥ ያለውን ለጥርጥር፣ የውጩን ለነቀፋ፣ ባለሐሳቡንም ለፍረጃ እንዳናጋልጥ፡፡ አነጋጋሪ አርእስት ላይ ጥንቃቄ ማድረግ መልካም ነው፡፡ ምናልባት ግራ ቀኙን አመሳክሮ በመጽሐፍ መልክ ማውጣቱ ይሻላል፡፡
የዲጂታሉ ዓለም ተደራሲ ብዙ መልክ ስላለው በዚያ የሚካሔድ ተዋሥኦ ጥንቃቄ ይሻል፡፡

3. ለተዋሥኦ የሚሰጡት ተግሣጻዊ ምላሾች ወዲያው፣ በቅን ልቡናና የሚያስኬደውን አስተምህሮ በማቅረብ ቢሆን ያንጻሉ፡፡ ዝም ብሎ ስም ለመስጠት ሲሆን ተናጋሪውንም ላልተገባ የተዐብዮ ፆር ያጋልጣሉ፡፡

4. የተመለሱ ወንድሞችን የምንይዝበት መንገድ ያሳቅቃል፡፡ ያማቅቃልም እንጂ! አንድ ወቅት እንዲህ ሆነ፡- አንድ መነኮስ ቆቡን ጥሎ ወደዚያኛው ቤት ኮበለለ፡፡ ቆይቶ በነባር ጓደኞቹም በራሱም ሕሊና ተወቅሶ ተመለሰ፡፡ ሲመለስ መኖሪያ ሥራም ቤትም አልነበረውም፡፡ የተጣለ ቆብ አይነሣም! ነገር ግን የቢሮ ሥራ መስጠት ይቻል ነበር፡፡ አልሆነም፡፡ ወደ ቀደመች እምነቱ እንዲመለስ የተደረገውን ጥረት ያህል ለኑሮው አልታሰበም፡፡ ሰውዬው ተመልሶ ወደዚያኛው ቤት አልሄደም፡፡

ነገር ግን ቤተ ክርስቲያንም አልገባም፡፡ ዓለማዊ ሆነ፡፡ ስዱድ ሆነ፡፡ ለሱስ ተጋለጠ፡፡ ሱሱ ጨረሰው፡፡ ሞተ፡፡ በዝግ ቤት ሞተ። ሞቱ የታወቀው ከቀናት በኋላ ነበር፡፡ ጠያቂ አልነበረውም፡፡ አያያዛችን ርኅራኄ ይጎድለዋል! ከቤተ ክርስቲያን ወጥተው የሚመለሱ ወንድሞች በአብዛኛው ሌላ ሙያ የላቸውም፤ በአግልግሎት ነው የኖሩ፡፡ ‹‹ዘእንበለ ሥጋ ኢትቀውም ነፍስ›› ለእነርሱም ይሠራል፡፡ በኢኮኖሚ መደገፍ ያስፈልጋል፡፡
እዚህ አካባቢ የማየው መመጻደቅ ደስ አይለኝም፡፡ ወጥተው የተመለሱ ወንድሞች ፍቅርና እንክብካቤ ሊደረግላቸው፣ ለንስሐቸው ዋጋ ሊሰጥ ሲገባ ያለፈ ታሪክን እንደ ወንጀል ‹‹ሪከርድ›› ይዞ ከሳሽነትን የሙጥኝ ብሎ ማሳደድ ልብ ይሰብራል፡፡

5. ወንድምን ለማዳን አለመሞከር፣ የተመለሰውን መልሶ መግፋት በቀኖና ቤተ ክርስቲያን ያስወግዛል፡፡ አቀራረባችን ተደጋግሞ እንደ ተነገረው እንደ ዳኛ ሳይሆን እንደ ጥንቁቅ ሐኪም ይሁን፡፡ የደከሙ፣ የሳቱ የመሰለንን ወንድሞች በጸሎት እናስብ!
‹‹የአንድ ሰው መጉደል ከጎጆ ቤት አንዲት ሳር ተመዝዛ የመውደቅ ያህል ነው›› የሚል አካሔድ በተደጋጋመ ቁጥር ስስ ያደርጋል፡፡
ይልቁንስ በአንድ ሰው መዳን በሰማያት ደስታ ይሆናል እንበል!

ደብተራ በአማን

🌹<  ወስብሐት ለእግዚአብሔር  >🌹
               🌹🌹🌹
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

24 Jan, 04:23


🌿 ስንክሳር ጥር 16 🌿

እንኩዋን ለአበው ቅዱሳን "አባ ዳንኤል" : "አባ ዸላድዮስ" : ወቅዱስ "ፊላታዎስ ሰማዕት" ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ

+*" ማር ዳንኤል "*+

=>"ዘዓምድ" በሚል ስም ከሚታወቁ የቤተ ክርስቲያን አበው መካከል 4ቱ ቅድሚያውን ይይዛሉ:: እነዚህም:-
1.ቅዱስ ስምዖን ዘዓምድ:
2.ቅዱስ አጋቶን ዘዓምድ:
3.ቅዱስ ዳንኤል ዘዓምድ እና
4.ቅዱስ ሉቃስ ዘዓምድ ናቸው::

+"ዘዓምድ" የሚለውን ቃል ምሥራቃውያን በልሳናቸው 'THE STYLITE' ይሉታል:: የእኛው ቃል ደግሞ ከግዕዝ የተወረሰ ነውና በቁሙ ቢተረጐም "የምሰሶው" የሚል ትርጉምን ይይዛል:: ይህም በ2 ምክንያቶች ነው::

+አንደኛው ቅዱሳኑ ተጋድሏቸውን የፈጸሙት ከረዥም ምሰሶ ላይ ወጥተው በመጸለይ ስለሆነ ነው:: ሌላኛው ምክንያት ደግሞ እነዚህ አባቶች በዘመኑ ለነበሩ ምዕመናንና መነኮሳት አጽናኝ: አስተማሪ: መሪና ፈዋሽ በመሆናቸውና እንደ ምሰሶ ተተክለው ሳይነቃነቁ በመጸለያቸው ነው::

+ልክ ከዓለም ሃገራት ብዙ ስውራንን እና ቅዱሳን ነገሥታትን በመያዝ ሃገራችን ቀዳሚ እንደ ሆነችው ሁሉ ምሰሶ ላይ ወጥተው የሚጋደሉ ቅዱሳንም ሶርያውያንና ምሥራቃውያን ናቸው:: በዚህ ዕለትም ቅድስት ቤተ ክርስቲያን የታላቁን ቅዱስ ማር ዳንኤልን በዓል ታከብራለችና ከዜና ሕይወቱ ለበረከት ጥቂት እንካፈል::

=>ይህ ቅዱስ ሰው (በስዕሉ የሚታየው) ሶርያዊ ሲሆን ተወልዶ ያደገባት አካባቢ በቀድሞው አጠራር "ሃገረ ዓምድ" ይሏታል:: "ማር" የሚለው ቃል በቤተ ክርስቲያን ቅድስናንና አለቅነትን የሚገልጽ ስም ነው:: በዚህ ስም ጥቂቶች ብቻ ሲጠሩበት ለሊቃውንትም: ለሰማዕታትም: ለጻድቃንም አገልግሏል::

+ቅዱሱ "ማር" ብቻ ሳይሆን "ዘዓምድ" ተብሎም ተጠርቷል:: ለዚህ ምክንያቱ ደግሞ እርሱም በፊት እንደ ጠቀስናቸው አበው ምሰሶ ላይ ተጠግቶ (ቆሞ): ትኩል ከመ ዓምድ ሆኖ በመጸለዩ ነው::

+ማር ዳንኤል በምድረ ሶርያ ስመ ጥር ጻድቅ ነው:: በዘመነ ጻድቃን መጨረሻ አካባቢ ከክርስቲያን ወገኖቹ ተወልዶ: በሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን አድጐ: ገና በልጅነቱ ለቤተ እግዚአብሔር ተሰጥቷል::

+የወቅቱ የሃገረ ዓምድ ዻዻስ (አባ ዼጥሮስ) ለማር ዳንኤል ፍኖተ ጽድቅን (የሕይወት - የእውነትን ጐዳና) በማሳየት ከፍ ያለውን አስተዋጽኦ አበርክቷል:: አስተምሮም ለመዓርገ ክህነት አብቅቶታል::

+ቅዱሱ በእድሜው እየበሰለ ሲሔድ ግን ምርጫው ምናኔ ሆኖ በመገኘቱ በፈቃዱ ወደ በርሃ ሔደ:: በዚያም መዓርገ ምንኩስናን ተቀብሎ በጾም: በጸሎትና በትሕርምት ይጋደል ገባ::

+ማር ዳንኤል በበዓቱ ተወስኖ ሲጾም: ሲጸልይና እግዚአብሔርን ሲያመልክ ከጸጋ (ከብቅዓት) ደረሰ:: ብዙ ተአምራትንም በመሥራቱ ስም አጠራሩ በአካባቢው ተሰማ:: እርሱ ግን ከሰው: ይልቁንም ከሴቶች ይርቅ: ላለማየትም ራሱን ይከለክል ነበር::

+ለአንድ መናኝ በሰዎች መካከል: ይልቁንም በተቃራኒ ጾታ ጐን መኖር ያልተፈቀደ: ፈታኝም ድርጊት ነውና ከፈጣሪው ጋር እንዲህ የሚል ቃልን ገባ:: "ከዚህ በሁዋላ ሴት ልጅን አላይምም" አለ:: በእንዲህ ያለ የቅድስና ሕይወት ሳለ ወላጅ እናቱ ልታየው ተመኘች::

+ወደ ገዳሙ መጥታም "ልጄ! ላይህ ሽቻለውና ልግባ : ወይ ብቅ በል" ስትል ላከከችበት:: ቅዱሱ ግን "እናቴ! ሴትን አላይም ብየ ቃል ስለ ገባሁ አልችልም" ሲል መለሰላት:: በጣም አዝና "እኔ ወልጄ: አዝዬ: አጥብቼ: አሳድጌ እንደ ሌሎች ሴቶች አስመሰልከኝ? በል ፈጣሪ 2 ሴቶች በአንድ ልብስ ሆነው ይዩህ!" ብላ ረግማው ወደ ቤቷ ተመለሰች::

+የሚገርመው ማር ዳንኤል በበርሃ የበቃውን ያህል እናቱ በዓለም ሳለች በጐ ሰርታለችና እርሷም ጸጋውን አብዝቶላታል:: በምን ይታወቃል ቢሉ:- ያቺ የተናገረቻት ነገር ሁሉ ደርሶበታልና::

+አንድ ቀን ለገንዘብ ሲል አንድ ሰው የገደለውን አምጥቶ በቅዱሱ በር ላይ ጣለው:: ቅዱሱም ያለ አበሳው ታሥሮ ወደ ከተማ ሲወሰድ መታጠቢያ (shower) ቤት ውስጥ የነበሩ ሴቶች ሊያዩት ቸኩለው: አንድ ልብስ ለብሰው ወጥተዋል:: ማር ዳንኤል ይህንን ሲያይ የእናቱ ነገር ትዝ ብሎት ሳቅ ብሏል::

+በታሠረበት ቦታ ግን የሞተውን ሰው በጸሎቱ በማስነሳቱ በክብር ወደ በዓቱ ተመልሷል:: የከተማዋ ንጉሥም ገዳምን አንጾለታል:: በተረፈ ዘመኑም ለብዙ ቅዱሳን አባት ሆኖ እስከ እርጅናው አገልግሏል:: በዚህች ቀንም በክብር ዐርፏል::

+*" አባ ዸላድዮስ "*+

=>አባ ዸላድዮስም በተመሳሳይ የዘመነ ጻድቃን ፍሬ ነው:: በርሃ ከገባባት ቀን ጀምሮ ጾምን: ጸሎትን አዘውትሮ ክርስትናውን አጽንቷል:: ሙሉ እድሜውን በጐ በመሥራት በማሳለፉ ፈጣሪውን ሲያስደስት ለብዙዎች አንባ: መጠጊያ መሆን ችሏል::

+በጸሎቱ አካባቢውን በደህንነት ይጠብቅ ነበር:: ምዕመናን እንኩዋን ወደ እርሱ መጥተው ተባርከው ባሉበት ቦታ ሁነው ተማጽነው እንኩዋ መሻታቸውን አያጡም ነበር:: ምንም ያህል ኃጢአተኞች ይሁኑ እግዚአብሔር ስለ አባ ዸላድዮስ ሲል ይለመናቸው ነበር::

+አንድ ቀን አንድ ነጋዴ ሰው በባሕር ላይ ሲሔድ ድንገት ማዕበል ይነሳበታል:: ብቻውን ነበርና ጨነቀው:: እሱ ያለባት ጀልባም ትንሽ በመሆኗ ልትሠበር ደረሰች:: መዳን እንደ ማይችል ሲያውቅ ተስፋ ቆረጠ::

+ድንገት ግን አባ ዸላድዮስ ትዝ ብሎት ቀና ብሎ "ጌታየ! ስለ ቅዱሱ አባት ብለህ ብትምረኝ ለወዳጅህ መቶ ዲናር ወርቅ እሰጣለሁ" ሲል ተሳለ:: ቃሉን ተናግሮ ሳይጨርስ አባ ዸላድዮስ በጀልባው ላይ ቁጭ ብሎ ታየው:: ማዕበሉም ጸጥ እንዲል አድርጐ ከወደብ አድርሶ ተለየው::

+ነጋዴውም ፈጣሪውን ስለ ድኅነቱ እያመሰገነ 100 ዲናር ወርቁን ይዞ አባ ዸላድዮስን ፍለጋ ወጣ:: የሚያውቀው በዝና ብቻ ነበርና:: መንገድ ላይም ሞሪት የሚባል መሪ አግኝቶ ከአባ ዸላድዮስ በዓት ደረሰ::

+ከቅዱሱ ተባርኮ ወርቁን ቢያቀርብለት "ልጄ! እኔ ይህን አልፈልገውም:: ለነዳያን በትነው" አለው:: ነጋዴው ሲወጣ ግን ሞሪት (መሪው) ገንዘቡን ፈልጐ ገደለውና ከጻድቁ በር ላይ ጣለው:: ሃገረ ገዢውም ሲሰማ አባ ዸላድዮስን አሠረው::

+ጻድቁ ግን የሞተውን ባርኮ አስነሳውና "ማን ገደለህ" ቢለው "ሞሪት" ሲል መልሷል:: መኮንኑ ሞሪትን ሊገድለው ቢልም "የለም" ብሎ ነጋዴውን በደስታ: ሞሪትን ደግሞ በንስሃ ሸኝቷቸዋል:: አባ ዸላድዮስ ግን ተረፈ ዘመኑን በቅድስና ሲጋደል ኑሮ በክብር ዐርፏል::

=>ጥር 16 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱስ ፊላታዎስ ሰማዕት
2.አባ ዸላድዮስ ገዳማዊ
3.ማር ዳንኤል ሶርያዊ
4.አባ ዮሐንስ መሐሪ (ሊቀ ዻዻሳት)
5.11,004 ሰማዕታት (የቅ/ቂርቆስ ማሕበር)
6.11,503 (የቅ/ፊላታዎስ ማሕበር)
7.አባ ጽሕማ (ከተስዓቱ ቅዱሳን አንዱ)

=>ወርሐዊ በዓላት
1.በዓለ ኪዳና ለድንግል
2.ቅዱስ አኖሬዎስ ንጉሥ
3.ቅዱስ ገብረ ማርያም (ንጉሠ ኢትዮዽያ)
4.ቅድስት ኤልሳቤጥ
5.አባ ዳንኤል
6.አባ አቡናፍር ገዳማዊ
7.አባ ዮሐንስ ወንጌሉ ዘወርቅ

🌹<  ወስብሐት ለእግዚአብሔር  >🌹
               🌹🌹🌹
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

22 Jan, 16:06


🕊 ስንክሳር ጥር 15 🕊

እንኳን ለሰማዕታት ቅዱሳን ቂርቆስ ወኢየሉጣ: ወነቢይ አብድዩ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን።

† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †

ቂርቆስ ወኢየሉጣ

††† ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ካሏት ዐበይት ሰማዕታት አንዱ ቅዱስ ቂርቆስ ነው:: በተለይ በዘመነ ሰማዕታት ተነስተው እንደ ከዋክብት ካበሩትም አንዱ ነው:: ቅዱስ ወንጌል እንዲህ ይላል:- "መልካም ዛፍ መልካም ፍሬን ያፈራል::" (ማቴ. 7:17)

መልካም ዛፍ ቅድስት ኢየሉጣ መልካም ፍሬ ብጹዕ ቂርቆስን አፍርታ ተገኝታለችና ክብር ይገባታል:: ቡርክተ ማሕጸንም እንላታለን:: የተባረከ ማሕጸኗ የተባረከ ልጅን ለ9 ወር ተሸክሟልና::

በዚያ ክርስቲያን መሆን መከራ በነበረበት ዘመን ይህንን ደግ ሕጻን እርሷን መስሎ: እርሷንም አህሎ እንዲገኝ አስችላለችና:: አበው በትውፊት እንዳቆዩልን ከሆነ በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን እናታችን ቅድስት ኢየሉጣ ብጹዕ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስን ወልዳለች::

በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን በሮም ግዛት ክርስትና ቢስፋፋም በዚያው ልክ መምለክያነ ጣዖቱ የገነኑ ነበሩ:: በተለይ ከነገሥታቱ ጀምሮ ዋና ዋና የሥልጣን ቦታዎች በአሕዛብ እጅ በመሆናቸው ለዘመኑ ክርስቲያኖች ፈታኝ ነበር::

ማንኛውም ክርስቲያን መሠረታዊ ፍላጐቶቹ እንዲሟሉለት አሕዛብ ላቆሟቸው ጣዖቶች መንበርከክ ነበረበት:: መብቱን ከመገፈፉ ባሻገር "ተበድያለሁ" ብሎ ወደ ፍርድ ቤት ሔዶ እንኩዋ የመጮህ እድል አልነበረውም:: ምክንያቱም የሚሰማው አልነበረም::

በዚያ ላይ በየጊዜው ለክርስቲያኖች ፈታኝ የሆኑ አዋጆች ይወጣሉ:: የክርስትናን ጐዳና ይበልጥ የሚያጠቡ ሕጐችም ዕለት ዕለት ይፈበረኩ ነበር:: ስለዚህም በወቅቱ የነበረ አንድ ክርስቲያን ሃይማኖቱን ከወደደ ወይ እስከ ሞት መታገስ: ካልሆነ ደግሞ ሃገርን ጥሎ በዱር: በገደል መሰደድ ነበረበት::

እውነት ለመናገር ዜና ሰማዕታትን የማያውቅ ክርስቲያን ክርስቶሳዊ ነው ሊባል አይችልም:: ምክንያቱም ዛሬ እንዲህ እንደ ዋዛ የያዝናት ሃይማኖታችን እንዴት እንደ መጣችና ምን እንደ ተከፈለባት አብዛኛው ትውልድ አያውቅምና::

ሕጻኑ ቅዱስ ቂርቆስና እናቱ ብጽዕት ኢየሉጣም የዚህ ዘመን (የዘመነ ሰማዕታት) ፍሬ ናቸው:: በጊዜው በሮም ግዛት ሥር እስክንድሮስ የሚሉት ክፉ ንጉሥ ነግሦ ነበርና ብዙ ክርስቲያኖች ተሰደዱ:: ጣዖትን ላለማምለክም ተሰው::

በዚህ ጊዜ አንጌቤናይት (ኢጣልያዊት) ብጽዕት ኢየሉጣም በመበለትነት (ባሏ በሕይወት ባለ መኖሩ) ትኖር ነበር:: ልጇ ቅዱስ ቂርቆስ ምንም ገና 3 ዓመቱ ቢሆንም ነገረ ሃይማኖትን ታስተምረው: ፍቅረ ክርስቶስን ትስልበት ነበር::

እስክንድሮስ የክህደት አዋጅን ሲያውጅም ቅድስቲቱ ለሕጻን ልጇ ራርታ ሽሽትን መረጠች:: ሃብት ንብረቷን: ወገንና ርስቷንም ትታ: ሕጻን ልጇን ተሸክማ ተሰደደች:: መከራው ግን በሔደችበት አለቀቃትም::

እስክንድሮስ ተከትሎ ባለችበት ቦታም አገኛት:: ወታደሮች ልጇን ሳያገኙ እርሷን ብቻ ይዘው ወደ መኮንኑ አቀረቧት:: መኮንኑም "ስምሽን ንገሪኝ" ቢላት "ስሜ ክርስቲያን ነው" አለችው:: ተቆጥቶ "ትክክለኛውን ስምሽን ተናገሪ" ቢላት "እውነተኛው ስሜ ክርስቲያን ነው:: ሞክሼ (ሞክሲ) ስም ከፈለግህ ኢየሉጣ እባላለሁ" አለችው::

"ለጣዖት ልትሰግጂ ይገባል" ሲላትም "እውነትን ይነግረን ዘንድ የ3 ዓመት ሕጻን ፈልገህ አምጣና ተረዳ" ስላለችው ወታደሮቹን እንዲፈልጉ ላካቸው:: የሃገሩ ሰዎች ልጆቻቸውን ስለደበቁ የተገኘ ቅዱስ ቂርቆስ ነበር::

ቅዱሱ ሕጻን በወታደሮች ተይዞ ሲቀርብ መልኩ ያበራ ነበርና መኮንኑ "በሐከ ፍሡሕ ሕጻን - ደስ የተሰኘህ ሕጻን እንዴት ነህ" ቢለው "ትክክል ነህ! እኔ በጌታየ ክርስቶስ ዘንድ ደስታ ይጠብቀኛል:: አንተ ግን በክህደትህ ወደ ገሃነም ትወርዳለህ" አለው::

በሕጻኑ ድፍረት የደነገጠው መኮንኑ በብስጭት "እሺ! ስምህን ንገረኝ" አለው:: ያን ጊዜ "ከንጹሕ ምንጭ የተቀዳ: ስሜ ክርስቲያን ነው:: እናቴ የሰየመችኝን ከፈለክ ግን ቂርቆስ ነው" ሲል መለሰለት::

ከዚያም እየደጋገመ "እኔ ክርስቲያን ነኝ" ብሎ በመጮሁ መኮንኑ ስቃይን በቅዱሱ ሕጻን እና በቡርክት እናቱ ላይ አዘዘ:: ከዚህ በሁዋላ በእነርሱ ላይ የተፈጸመውን ግፍና የወረደባቸውን የመከራ ዶፍ እናገር (እጽፍ) ዘንድ ግን የሚቻለኝ አይመስለኝም::

በግርፋት የጀመረ ስቃይ ሊሰሙት ወደ ሚጨንቅ መከራ ቀጠለ::
*7 ብረት አግለው በዐይናቸው: በጆሯቸው: በአፋቸውና በልባቸው ከተቱ::
*በ4 ችንካሮች ላይ አስቀመጧቸው::
*በእሳት አቃጠሏቸው::
*ጸጉራቸውን ከቆዳቸው ጋር ገፈፉ::
*ከዚህ በላይ ብዙ ስቃይንም አመጡባቸው::

እናትና ልጅ ግን ለክርስቶስ ታምነዋልና ጸኑ:: ቅድስት ኢየሉጣ ብትደነግጥ ልጇ አጸናት:: ከብዙ ስቃይና መከራ በሁዋላም በዚህች ዕለት በሰማዕትነት ሲያርፉ ጌታ እንደ ቃሉ የሕጻኑን ሥጋ በሠረገላ ኤልያስ አኑሮታል:: ለእኛ የሚጠቅም ብዙ ቃል ኪዳንንም ሰጥቶታል::

††† ቅዱስ አብድዩ ነቢይ †††

††† "አብድዩ" ማለት "የእግዚአብሔር አገልጋይ" ማለት ነው:: ቁጥሩ ከ12ቱ ደቂቀ ነቢያት ሲሆን የቅዱስ ኤልያስ ታላቁም ደቀ መዝሙር ነው:: ቅዱሳን ነቢያት ዮናስና ኤልሳዕም ባልንጀሮቹ ነበሩ::

ቅዱስ አብድዩ ቅድመ ልደተ ክርስቶስ በ800 ዓመት አካባቢ የከሃዲው ንጉሥ የጦር መሪ ሆኖ በሃምሳ አለቃነት አገልግሏል:: ግፈኛዋ ኤልዛቤል ነቢያተ እሥራኤልን ስታስፈጅ 50ውን በአንድ ዋሻ : 50ውን ደግሞ በሌላ ዋሻ አድርጐ አትርፏቸዋል:: 900ው ግን ተጨፍጭፈዋል::

ያተረፋቸውንም ክፉ ዘመን እስኪያልፍ ድረስ መግቧቸዋል:: አክአብና ኤልዛቤል ከሞቱ በሁዋላም ቅዱስ ኤልያስን ተከትሎ ሹመቱን ትቷል:: እግዚአብሔር ገልጾለትም ትንቢት ሲናገር: ሕዝቡንም ሲገሥጽ ኑሯል::

በብሉይ ኪዳን ካሉ የትንቢት መጻሕፍትም በጣም አጭሩን የጻፈው ይሕ ነቢይ ነው:: ትንቢተ አብድዩ ባለ አንድ ምዕራፍ ብቻ ናትና:: ቅዱሱ በዚህች ቀን ዐርፎ ወገኖቹ ቀብረውታል::

††† አምላከ ሰማዕታት በምሕረቱ ይማረን:: በይቅርታው ኃጢአታችንን ይተውልን:: ከበረከተ ሰማዕታትም ይክፈለን::

††† ጥር 15 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ ቂርቆስና እናቱ ቅድስት ኢየሉጣ
2.ቅዱስ አብድዩ ነቢይ
3.ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ
4.ቅድስት ሶፍያ
5.ቅድስት አድምራ
6."11,004" ሰማዕታት (ከቅዱስ ቂርቆስ ጋር በሰማዕትነት ያለፉ)

††† ወርሐዊ በዓላት
1.ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ
2.ቅዱስ ሚናስ ሰማዕት
3.ቅድስት ክርስጢና
4.ቅድስት እንባ መሪና

††† "በተሰነጠቀ ዓለት ውስጥ የምትኖር: ማደሪያህንም ከፍ ከፍ ያደረግህ: በልብህም:- 'ወደ ምድር የሚያወርደኝ ማን ነው?' የምትል አንተ ሆይ! የልብህ ትዕቢት አታልሎሃል:: እንደ ንስር መጥቀህ ብትወጣ: ቤትህም በከዋክብት መካከል ቢሆን: 'ከዚያ አወርድሃለሁ' ይላል እግዚአብሔር::"
(አብድዩ 1:3)

† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
(መዝ. 36:28)

🌹<  ወስብሐት ለእግዚአብሔር  >🌹
               🌹🌹🌹
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

21 Jan, 19:29


ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት የተሰጠ መግለጫ!

#Ethiopia | የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የከተራ፣የጥምቀትና የቃና ዘገሊላ በዓላት በመላ ሀገራችን ከፍተኛ ቁጥር ባስመዘገበ ምልዓተ ሕዝብ በሰላም ተከብሮ በመዋሉ ለልዑል እግዚአብሔር ምስጋናዋን ታቀርባለች።

የ2017 ዓ.ም የጥምቀት በዓል በመላ ሀገራችን በድምቀት ተከብሮ መዋል ይችል ዘንድ በማዕከልም ሆነ በአህጉረ ስብከት ደረጃ በሊቃነ ጳጳሳት ተቋቁመው ሥራቸውን በሚገባ የተወጡ የሥራ ኃላፊዎችና የጥምቀት በዓል ዝግጅት አስተባባሪዎች፣
ካህናት፣የሰንበት ትምህርት ቤት ተማሪዎች፣በዓሉ በድምቀት እንዲከበር አደባባዮችን በማስዋብና ሥነሥርዓትን በማስከበር ትልቁን ሚና የተጫወቱ ኦርቶዶክሳዊያን ወጣት ልጆቻችን ምዕመናንና ምዕመናት በሙሉ በዓላቶቻችን ያለአንዳች ችግር በሰላም ተከብረው እንዲውሉ ስላደረጋችሁ ቅድስት ቤተክርስቲያን ልባዊ ምስጋናዋን ታቀርብላችኋለች።

በተለይም በመዲናችን አዲስ አበባ ጃን ሜዳ የተከበሩት ሦስቱ በዓላት በታላቅ ድምቀትና ውበት ተከብረው መዋል እንዲችሉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ክብርት ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ልዩ ትኩረት በመስጠት የክብር እንግዶች የሚቀመጡበት መድረክ ከነ ሙሉ ግብዓቱ፣የድምጽ ማጉያና መሰል ለበዓል አከባባሩ የሚያስፈልጉትን ሁሉ በከተማ አስተዳደሩ ወጪ በመሸፈን ስላቀረቡልን እንዲሁም ከኮሪደር ልማቱ ጋር በተያያዘ የታቦታት እንቅስቃሴ እንዳይስተጓጎል አስፈላጊውን መመሪያ በመስጠትና አፈጻጸሙን በቅርበት በመከታተል ከልማቱ ጋር የተያያዘ ምንም አይነት መጉላላት እንዳይፈጠር በማድረግ በዓሉ የጋራችን መሆኑን የሚያረጋግጥ ሥራ በመሥራት ላበረከቱት የላቀ አስተዋጽኦ ቤተክርስቲያናችን ምስጋናዋን ታቀርባለች።

በዓላችን ያለምንም የጸጥታ ችግር በሰላም ተከብሮ እንዲውል ለማድረግ የመንግስት የጸጥታ ተቋማት በተለይም የጸጥታና የደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል፣ የአዲስ አበባ ፓሊስ ኮሚሽንና ሌሎች የጸጥታ ተቋማት ያለመታከት ላደረጉት አስተዋጽኦ ቅድስት ቤተክርስቲያን የተሰማትን ደስታ በመግለጽ ምስጋናዋን ታቀርባለች።

በተያያዘ የአራዳ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የበዓል አከባበር ሂደቱን በቅርበት በመከታተልና እንቅፋቶች እንዳይፈጠሩ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ በመስራትና የታቦታት ማለፊያ ቦታዎችን በማጽዳት ያበረከተው አስተዋጽኦን ቅድስት ቤተክርስቲያን የምታደንቀውና ምስጋናም የምትቸረው ነው።

በዓላችን በመላ ሀገራችን በልዩ ድምቀትና ውበት ተከብሮ መዋል ይችል ዘንድ በየ ክልሉ የሚገኙ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች መዋቅራቸውን በመጠቀም ታቦታት የሚጓዙበትን ቦታዎች በሚገባ ዝግጁ በማድረግ ለታቦታት ማክበሪያ የሆኑ ይዞታዎችን በመፍቀድና በሰነድ የተረጋገጠ የባለቤትነት መብትን በማጎናጸፍ እንዲሁም በዓሉ በምልዓተ ሕዝብ በሰላም ተከብሮ እንዲውል ላደረጉት ድጋፍና ትብብር ቅድስት ቤተክረስቲያን ምስጋናዋን ታቀርባለች።

በዓለም አቀፍ ደረጃ በማይዳሰስ ቅርስነት የተመዘገበው የጥምቀት በዓል የሀገራችን ኢትዮጵያና የመላው ሕዝባችን በዓል መሆኑን በተግባር በማረጋገጥ ደረጃ በተለይም ሙስሊም ወንድሞቻችን ያሳያችሁት ፍቅርና አንድነትን የሚገልጽ ተግባር በእጅጉ የሚያስመሰግን አንድነትና አብሮነትን የሚያጠናክር በመሆኑ ቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያናችን ላሳያችሁት ፍቅርና ክብር በልዑል እግዚአብሔር ስም ልባዊ ምስጋናዋን ታቀርባለች።

በአጠቃላይ የዘንድሮ የከተራ፣የጥምቀትና የቃና ዘገሊላ በዓላት በመላ አገራችን እጅግ ከፍተኛ ቁጥር የተመዘገበበት ሕዝበ ክርስቲያን በአደባባይ ተገኝቶ በልዩ ውበት በሰላም ያከበራቸው መሆኑን ከመላ አገራችን የደረሰን ሪፖርት የሚያመለክት ሲሆን በዚህ ልክ በዓላቶቻችን በሰላም ተከብረው መዋላቸው ደግሞ በእጅጉ የሚያስደስትና ለአገራችን የቱሪዝም እድገትና የገጽታ ግንባታም ላቅ ያለ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ቤተክርስቲያን ታምናለች።

ስለሆነም በዓላቶቻችን በዚህ መልኩ ተከብረው መዋል እንዲችሉ ለማድረግ አቅማችሁን በማስተባበር ዋጋ ለከፈላችሁ ልጆቻችን በሙሉ እግዚአብሔር አምላክ ዋጋችሁን እንዲከፍላችሁ ቤተክርስቲያን የዘወትር ጸሎቷ መሆኑን ስትገልጽ በልጆቿ መንፈሳዊ ተጋድሎ ከፍተኛ ደስታ የተሰማት መሆኑን በመግለጽ ጭምር ነው።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን
መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
ጥር 12 ቀን 2017 ዓ.ም
አዲስአበባ -ኢትዮጵያ

🌹<  ወስብሐት ለእግዚአብሔር  >🌹
               🌹🌹🌹
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

21 Jan, 19:21


" ሂጃቧን ትለብሳለች ትምህርቷንም ትማራለች ! " - ሰልፈኞች

#ለ17 ሴት ተማሪ የተደረገ አስገራሚ ሀገራዊ ሰላማዊ ሰልፍ እና ጩኸት!

በአክሱም ከተማ በሚገኙ ትምህርት ቤቶች ከሂጃብ ክልከላ ጋር ተያይዞ የፍርድ ቤት እና የትምህርት ቢሮ ወሳኔና ትእዛዝ እንዲተገበር የሚጠይቅ ሰላማዊ ሰልፍ በመቐለ ተካሂደዋል።

ሰልፉ የተዘጋጀው በትግራይ እስልምና ጉዳዮች ም/ቤት አማካኝነት ነው።

ምክር ቤቱ ዛሬ " ሂጃቧን ትለብሳለች ትምህርቷንም ትማራለች " በሚል መሪ ቃል በመቐለ ከተማ ሮማናት አደባባይ በጠራው ሰላማዊ ሰልፍ በሺዎች የሚቆጠሩ ምዕመናን ተገኝተው ነበር።

ሰልፈኞቹ ፦

- ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታ ይመለሱ !
- ህገ-መንግስት ይከበር !
- ፍትህ ለእህቶቻችን ነፃነት ለሁሉ !
- ሂጃብ መልበስ ሃይማኖታዊ መብትና ግዴታ ነው !
- ሂጃቤ መልኬ ነው !
- የፍርድ ቤት ትእዛዝ ይከበር !
- ሰላም እና ፍትህ ለትግራይ !
- መብታችን ይጠበቅልን !
- ከተበዳዮች ጎን እንቁም !
- ፍትህን እንጠይቃለን !
- ከሂጃባችን ጋር ታግለናል፤ ሂጃባችን ለብሰን እንማራለን !
- ሂጃባችን ምርጫችን እና መብታችን ነው !
... የሚሉና እና ሌሎች መፈክሮች አሰምተዋል።

በመቐለ ሮማናት አደባባይ ለተሰባሰቡት ሰልፈኞች መልእክት ያስተላለፉት የትግራይ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት ፕሬዜዳንት ሸኽ አደም ዓብደልቃድር  ፥ " ትግራይ የሃይማኖቶች የመቻቻል የነፃነት ተምሳሌት ነች፤ ይሁን እንጂ ይህንኑ ስልጡንነት ወደ ኋላ በሚመልስ መልኩ ልጆቻችን ሂጃባቸው ለብሰው እንዳይማሩ ከዘንድሮ የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና እንዲቀሩ ተደርገዋል "  ብለዋል።

***
እውነታውስ?

በሌላ በኩል ፥ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ሂጃብ ለብሰው እንዳይማሩ ክልከላ አድርገዋል የተባሉት በአክሱም ከተማ የቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ የጋራ የፅሁፍ ምላሽ ሰጥተዋል።

ት/ቤቶቹ ምን አሉ ?
" 1. የሴት ሙስሊም ተማሪዎች የሂጃብ አጠቃቀም አስመልክቶ በትግራይ ያለው ህግ እና አተገባበሩ ምን ይመስላል ?

ትምህር ቤቶቻችን የትግራይ ትምህርት ቢሮ በ1995 ዓ.ም ያወጣው የትምህርት አደረጃጀት መመሪያ ነው እየተጠቀሙ ያሉት ። አዲስ ፖሊሲ ወይም መመሪያ እና ደንብ በትምህርት ሚንስቴር ከወጣ ደግሞ ከትምህርት ቢሮ ጋር ተነጋግሮ ይህንን መመሪያ እና ደንብ ተጠቀሙ ብሎ ይልክልናል ። እኛም ተግባራዊ እናደርጋለን። ይህን ባለልሆነበት ' እህያውን ፈርቶ ዳውላውን ' የሆነ ጥያቄ እና ጫና ግን ግራ የሚያጋባ ነው።  በ1995 ዓ.ም የወጣው የትምህርት አደረጃጀት መመሪያ ደግሞ ተማሪዎች መምህራን ወላጆች ተወያይተው ያፀዱቁት ላለፉት 22 ዓመታት እየተጠቀሙት ያለ መመሪያ ደንብ ነው።  በ1995 ዓ.ም የወጣው የትምህርት አደረጃጀት መመሪያ ደንብ ደግሞ እንዲታይ በያዝነው ዓመት መጀመሪያ ከወላጅ ተማሪዎች ጥያቄ ተነስቶ ነበር ። የተነሳው ጥያቄ መሰረት በማድረግ በመመሪያ እና ደንቡ ውይይት ተካሂዶ ታህሳስ 6/2017 ዓ.ም በአንድ ተቃውሞ በሙሉ ድምፅ ፀድቀዋል።

በውይይት እና ድምፅ አሰጣጡ የሙስሊም እምነት ተከታይ ወንድሞቻችን ተሳትፈውበት በሙሉ መግባባት መተማመን የተደረሰበት ነው። ታድያ ከአሁን በፊት ታይቶ የማይታወቅ የሂጃብ ክልከላ ጥያቄ ከየት ? እንዴት መጣ ? ትምህርት ቤቶታቻችን ግራ ገብቶዋቸዋል።

2. የትምህርት ቤት ዩኒፎርም አለባበስ ደንብ እና ስነ-ሰርዓት ምን ይመስላል ?
በ1995 ዓ.ም በፀደቀው የትምህርት ቤቶች አደረጃጀት መምሪያ እና ደንብ መሰረት ትምህርት ቤቶቻችን የሚከተለውን የአለባበስ ስርዓት እንዲተገብሩ ያስገድዳል። የቤተክርስትያን ካህናት እና ዲያቆናት ተማሪዎች ሻሽ መጠምጠምያ ፣ ነጠላ ማድረግ አይፈቀድም። ወንድ ተማሪዎች ባንከር ፣ ፍሪዝ የፀጉር አቆራረጥ አይፈቀድም።

ሴት ተማሪዎችም ነጠላ ፣ መሃረብ ፣ ሻሽ መጠምጠምያ ፣ ጥቁር የሃዘን ሻርፕ ፣ ሂል ጫማ ፣ ሱሪ ፣ የማንኛውም ሃይማኖት አለባበስ የሚያንፀባርቅ ልብስ እንዲለብሱ አይፈቀድም። ይህ የሆነበት ደግሞ በመካከላቸው የሃብት የሃይማኖት ልዩነት ፈጥሮ የመማር የማስተማር ሂደቱ እንዳይታወክ ለማድረግ ያለመ ነው።  ይህ ህግ ደግሞ ክርስትያን ፣ ሙስሊም መምህር የተማሪ ወላጅ ተወያይተው ያፀደቁት እና የሚተዳሩበት ነው። አሁን ታድያ ምን አዲስ ነገር ተፈጥሮ ነው በትምህርት ቤቶቻችን ላይ የሚዘመተው ? 

 3. ስለ ዘንድሮ 12ኛ ክፍል ተፈታኝ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች መሬት ላይ ያለው መረጃ ምንድነው ?
በአክሱም አራት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አሉ።  በአራቱ ትምህርት ቤቶች ዘንድሮ ለ12ኛ ክፍል አገር  አቀፍ ፈተና የሚቀርቡት  ተማሪዎች 1044 ናቸው። ከነዚህ 1044 ተማሪዎች 17 ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ናቸው። ከነዚህ 17 ሴት ተማሪዎች ለ22 ዓመታት በቆየው የትምህርት ቤቶች አደረጃጀት መመሪያ እና ደንብ በመቀበል 7 ሴት ተማሪዎች ፈተናው ለመውሰድ ፎርም ሞልተዋል።  10 ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ደግሞ ከአክሱም ከተማ እስከ ሳውዲ ዓረብያ በተዘረጋ የውጭ ተፅእኖ ፈተና ለመውሰድ የሚያስችላቸው ፎርም አልሞሉም። ሃቁ ይህ ሆኖ እያለ ' 159 ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ከ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ምዝገባ እንዲስተጓጎሉ ተደረገ ' እየተባለ ነው የሚወራው። 142 ሴት ሙስሊም ተማሪዎች በትምህርት ቤቶቻችን የሌሉ የፈጠራ ድርሰቶች ናቸው።

የተቀሩት 10 ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ቢሆኑ ፎርም መልተው ለመፈተን ፍላጎት አላቸው ፤ ከትግራይ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፣ ከመቐለ ፣ ከአዲስ አበባ እስከ ሳውዲ ዓረብያ በየቀኑ እየተደወለ ማስፈራርያ ይደርሳቸዋል። ይህ አካሄድ ደግሞ የቆየውን አብሮነት እና መቻቻል የሚጎዳ ለህዝብ እና አገር የማይጠቅም መወገዝ ያለበት ተግባር ነው። " ... ሲሉ ትምህርት ቤቶቹ በጥምር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ በላኩት የፅሁፍ ምላሽ ገልጸዋል።

#UPDATE ትምህርት ቤቶቹ ዛግይተው በላኩት መልዕክት ሁሉም ተፈታኞች ፎርም ሞልተዋል ለፈተናም ብቁ ናቸው ብለዋል።

#TikvahEthiopiaMekelle
#ቲክቫህኢትዮጵያመቐለ

@tikvahethiopia

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

21 Jan, 15:55


🔔   ስንክሳር ጥር 14   🔔
† እንኳን ለጻድቃን ቅዱሳን አቡነ አረጋዊ እና አባ አርከሌድስ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †

† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †††

††† አቡነ አረጋዊ ዘደብረ ዳሞ †††

††† ጻድቁ ገድላቸውን የፈጸሙት በኢትዮዽያ ቢሆንም ሃገረ ሙላዳቸው የጥንቱ የሮም ግዛት የሆነችው ታናሽ እስያ ናት:: አቡነ አረጋዊ ከዘጠኙ (ተስዓቱ) ቅዱሳን አንዱ ናቸው:: ዘጠኙ ቅዱሳን ተወልደው ያደጉት ምንም በአንድ የሮም ግዛት ሥር ቢሆንም መነሻ ቦታቸው ግን የተለያየ ነው::

ሁሉንም አንድ ያደረጋቸው መንፈስ ቅዱስ በኪነ ጥበቡ ነው:: በምክንያት ደረጃ እንግለጸው ከተባለ ደግሞ የአንድነታቸው ምሥጢር:-
1.የቀናች ሃይማኖታቸው ተዋሕዶ:
2.ዓላማ (የእግዚአብሔር መንግስት) እና
3.ገዳማዊ ሕይወት ነው::

አቡነ አረጋዊን ጨምሮ ሁሉም ቅዱሳን ዘራቸው ከቤተ መንግስት ነው:: እነርሱ ግን ምድራዊውን ክብር ንቀው ሰማያዊውን ክብር ገንዘብ ማድረግን መርጠዋል:: አስቀድመው ቅዱሳት መጻሕፍትን ያጠኑት አበው በተለያየ ጊዜ እየመነኑ ከሮም ግዛት ወደ ግብጽ በርሃዎች ወርደዋል::

በምናኔ ቅድሚያውን አባ ዸንጠሌዎንና አቡነ አረጋዊ ይይዛሉ:: ዘመኑ የተዋሕዶ አማኞች የሚሰደዱበት 5ኛው መቶ ክ/ዘመን ነበርና እምነትን ላለመለወጥ ዘጠኙ ቅዱሳን ስደትን መረጡ::

በወቅቱ ደግሞ ለስደት መጠለያ የምትሆንና ከኢትዮዽያ የተሻለች ሃገር አልነበረችም:: ስለዚህም በ470ዎቹ ዓ/ም አልዓሜዳ በኢትዮዽያ ነግሦ ሳለ ቅዱሳኑ በአረጋዊ መሪነት መጡ::

ንጉሡም ሲጀመር የእግዚአብሔር እንግዳ ስለሆኑ: ሲቀጥል ደግሞ ቅድስናቸውን ተመልክቶ መልካም አቀባበልን አደረገላቸው:: ማረፊያ ትሆናቸውም ዘንድ አክሱም ውስጥ አንዲት ቦታን ወስኖ ሰጣቸው:: ይህች ቦታ ቤተ ቀጢን ትባላለች:: አቡነ አረጋዊና 8ቱ ቅዱሳን ወደ ሃገራችን እንደገቡ የመጀመሪያ ሥራቸው ቋንቋን መማር ነበር::

ልሳነ ግዕዝን በወጉ ተምረው እዛው አክሱም አካባቢ ሥራቸውን አንድ አሉ:: በወቅቱ በአቡነ ሰላማ: በአብርሃ ወአጽብሐና በአቡነ ሙሴ ቀዳማዊ የተቀጣጠለው ክርስትና በተወሰነ መንገድ ተቀዛቅዞ ነበርና እነ አቡነ አረጋዊ እንደገና አቀጣጠሉት::

ሕዝቡን በራሱ ልሳን ለክርስትና ይነቃቃ ዘንድ ሰበኩት:: የካደውን እየመለሱ: የቀዘቀዘውን እያሟሟቁ ለዓመታት ወንጌልን ሰበኩ:: ቀጣዩ ሥራቸው ደግሞ መጻሕፍትን መተርጐም ሆነ::

ከሃገራቸው ያመጧቸውን ቅዱሳት መጻሕፍት ተከፋፍለው ወደ ግዕዝ ልሳን ተረጐሟቸው:: በዚህም ለሃገራችን ትልቁን ውለታ ዋሉ:: ይህ ሁሉ ሲሆን እነ አቡነ አረጋዊ የሚመገቡትም ሆነ የሚጸልዩት በማሕበር ነበር:: በመካከላቸውም ፍጹም ፍቅር ነበር:: ጸጋ እግዚአብሔር አልተለያቸውም::

የነ አቡነ አረጋዊ ቀጣዩ ተግባራቸው ደግሞ ገዳማዊ ሕይወትን ማስፋፋት ሆነ:: ይህንን ለማድረግ ግን የግድ መለያየት አስፈለጋቸው:: እያንዳንዱም መንፈስ ቅዱስ ወደ መራው ቦታ ሔደ::

*ዸንጠሌዎን በጾማዕት:
*ገሪማ በመደራ:
*ሊቃኖስ በቆናጽል:
*አባ ይምዓታ በገርዓልታ:
*ጽሕማ በጸድያ:
*ሌሎችም በሌላ ቦታ ገዳማትን መሠረቱ::
*አባ አረጋዊ ደግሞ በመንፈስ ቅዱስ መሪነት ምርጫቸው ዳሞ (እዛው ትግራይ) ሆነ::

በሃገራችን ስም አጠራራቸው ከከበረ አባቶች አንዱ እኒህ ጻድቅ ናቸው:: ጻድቁ የተወለዱት በ5ኛው መቶ ክ/ዘ አጋማሽ አካባቢ ሲሆን ወላጆቻቸው ንጉሥ ይስሐቅና ቅድስት እድና ይባላሉ:: የተለወለዱበት አካባቢም ሮም ነው::

ስማቸው ብዙ ዓይነት ነው:: ወላጆቻቸው "ዘሚካኤል" ሲሏቸው በበርሃ "ገብረ አምላክ" ተብለዋል:: በኢትዮዽያ ደግሞ "አረጋዊ" ይባላሉ:: አቡነ አረጋዊ ምንም የንጉሥ ልጅ ቢሆኑም በልጅነታቸው መጻሕፍትን ተምረው ነበርና ጠፍተው ገዳም ገቡ::

በዚያም በገዳመ ዳውናስ (ግብጽ) የታላቁ ቅዱስ ዻኩሚስ ደቀ መዝሙር ሆነው ከነ አባ ቴዎድሮስ ጋር ሥርዓተ መነኮሳትን ተምረዋል:: ከመነኮሱ ከዓመታት በሁዋላም ወደ ሃገራቸው ሮም ተመልሰው በማስተማር 7 ያህል የቤተ መንግስት ሰዎችን ወደ ምናኔ ማርከዋል::

"የት ልሒድ" ብለው ሲያስቡም ቅዱስ መልአክ በክንፉ ጭኖ ወስዶ ኢትዮዽያን አሳያቸው:: ተመልሰውም ለ8 ባልንጀሮቻቸው "ሃገርስ ባሳየሁዋችሁ! ሐዋርያ ሳያስተምራት በሕጉ በሥርዓቱ ጸንታ የምትኖር" ብለው ከ8ቱ ጋር ወደ ኢትዮዽያ መጡ::

በዚህ ጊዜም እናታቸው ቅድስት እድናና ደቀ መዝሙራቸው አባ ማትያስ አብረው ነበሩ:: ወደ ሃገራችን የመጡ በ470ዎቹ አካባቢ ሲሆን አልዓሜዳ በክብር ተቀብሏቸዋል:: በቤተ ቀጢን (አክሱም) ተቀምጠውም መጻሕፍትን እየተረጐሙ: ወንጌልን እየሰበኩ ቆይተዋል::

ለሥራ በተለያዩ ጊዜም አቡነ አረጋዊ በዓት ፍለጋ ብዙ ደክመዋል:: በመጨረሻ ግን ደብረ ዳሞን (ደብረ ሃሌ ሉያን) አይተው ወደዷት:: የሚወጡበት ቢያጡም ጅራቱ 60 ክንድ የሚያህል ዘንዶ ተሸክሞ ከላይ አድርሷቸዋል::

እንደ ወጡም "ሃሌ ሉያ ለአብ: ሃሌ ሉያ ለወልድ: ሃሌ ሉያ ለመንፈስ ቅዱስ" ብለው ቢያመሰግኑ ከሰማይ ሕብስት ወርዶላቸው ተመግበዋል:: በዚህም ቦታዋ "ደብረ ሃሌ ሉያ" ተብላለች:: ጻድቁ ቦታውን ከገደሙ በሁዋላ ከተለያየ ቦታ መጥተው 6ሺ ያህል ሰዎች በእጃቸው መንኩሰዋል::

ምናኔን በማስፋፋታቸውና ሥርዓቱን በማስተማራቸውም "አቡሆሙ ለመነኮሳት ዘኢትዮዽያ - የኢትዮዽያ መነኮሳት አባት" ይባላሉ:: አቡነ አረጋዊ በሕይወታቸው ከተጋድሎ ባሻገር በወንጌል አገልግሎትና መጻሕፍትን በማዘጋጀትም ደክመዋል::

ቅዱስ ያሬድና አፄ ገብረ መስቀልም ወዳጆቻቸው ነበሩ:: በተራራው ግርጌ ያለችውን ኪዳነ ምሕረትን ለሴቶች ሲገድሟት ቀዳሚዋ መነኮስ እናታቸው ንግስት እድና ሁናለች::

ጻድቁ ንጹሕ ሕይወታቸውን ፈጽመው በተወለዱ በ99 ዓመታቸው በገዳሙ በስተ ምሥራቅ አካባቢ ተሰውረው ብሔረ ሕያዋን ገብተዋል:: ጌታም 15 ትውልድን የሚያስምር የምሕረት ቃል ኪዳን ሰጥቷቸዋል:: ዛሬ ጻድቁ የተወለዱበት ቀን ነው::
††† አምላከ ቅዱሳን ለእነርሱ ካደለው ፍቅራቸው ለእኛም አይንሳን:: በረከታቸውንም ያብዛልን::

††† ጥር 14 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.አቡነ አረጋዊ (ዘሚካኤል)
2.ቅዱስ አባ መክሲሞስ
3.ቅዱስ አባ አርከሌድስ
4.ቅድስት እምራይስ
5.ቅድስት ምሕራኤል
6."4034"ሰማዕታት (ማሕበራነ ቅዱስ ቂርቆስ)

††† ወርሐዊ በዓላት
1.አባ ስምዖን
2.አባ ዮሐንስ
3.ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ (ሙሽራው)
4.ቅዱስ ሙሴ
5.ቅዱስ ፊልዾስ (ከ72 አርድዕት)
6.ቅድስት ነሣሒት

††† "እግዚአብሔር ፍርድን ይወድዳልና::
ቅዱሳኑንም አይጥላቸውምና::
ለዘለዓለምም ይጠብቃቸዋል . . .
ጻድቃን ምድርን ይወርሳሉ::
በእርስዋም ለዘላለም ይኖራሉ::
የጻድቅ አፍ ጥበብን ያስተምራል::
አንደበቱም ፍርድን ይናገራል::
የአምላኩ ሕግ በልቡ ውስጥ ነው::
በእርምጃውም አይሰናከልም::" †††
(መዝ. 36:28)

🌹<  ወስብሐት ለእግዚአብሔር  >🌹
               🌹🌹🌹
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

21 Jan, 12:36


ጊጎ(GIGO)

በትንሿ የIT/Information Techenology/
መግቢያ መሠረታዊ ትምህርት GIGO
(Garbage In Garbage Out) የሚለውን ተርም የመግቢያ ትምህርቱ መነሻ ነው።
ያ ማለት በኮምፒውተር መረጃ ሥርዓት የመጨረሻ ውጤትህ ያስገባኸቸው ገቢ መረጃ/ input/ ድምር ውጤት ነው ማለት ነው። የሰው ልጅም እንዲህ ነው ገና ከማህፀን ሰው ሆኖ በአርባ ቀኑ ከውሀነት መሰብሰብ ሲጀምር ስሜትን መሰብሰብ ይጀምራል ይላሉ አባቶች። ይኼ በጤናው research/ጥናት አሁን አሁን unique finding/አዲስ ግኝት/ እየተባለ መለጠፍ ጀምሯል ነገር ግን እውነቱ እውነት ነውና ብራናዎች ከጥንቱ ከትበውት በጉባዔ ሊቃውንቱ ስነቃል ከሆነ ዘመን የለውም ያም ሆነ ይህ ወደነገራችን ስንመለስ።

በዚህ ሳምንት ያየናቸው እነዚህ ልጆች ሃይማኖታቸው ምን ይሁን ምን በሰው ሃይማኖት ሥርዓት እንዲህ ባላዋቂነት ለመሳለቅ ያደፋፈራቸው አስተምህሮና ስነልቦና ከየት አዳበሩት? ስለውጤቱ ሳይሆን ስለመንስዔው አውርተን በመሠረቱ ላይ ካልሠራን ጮኸታችን ከንቱ ሆኖ እንዲያው ስሙልኛ አይነት ነገር ሆኖ ብቻ ሊቀር ይችላል!

አንድ በወጣት እድሜ ያለ ወዳጅህን ስለሱ ህይወት ጥሩ ሞዴል የምትለው መንፈሳዊ መምህር ማነው ብትሉት እርግጠኛ ነኝ የሚልህ ነገር ቢኖር
መ/ር፣ ቀሲስ፣ ፓስተር አገልጋይ እና የመሳሰሉትን አንዱን ሰው ይጠራልሀል።

ከዛ "እንትና በጣም ጥሩ ሰባኪ(መ/ር) ነው።" ብሎህ ሲያበቃ
እንዴት?
ካልከው
"አቤት እነ እንትናን ሲሰድብኮ ልክልካቸውን እስከ ጥግ ነው የሚነግራቸው።" ብሎህ ያርፋል። በቃ የዘመኑ ወጣት ምርጡ ሰባኪ መምህር፣ ዘማሪ ወይም መካሪ እነ እንትና ቤት ገብቶ መፈትፈት የቻለ ነው። ይኼ አስተሳሰብና ይኼ መንገድ ነው ክፉ እሾህ። ይኼ መንገድ ነው እዚህም ቤት እዛም ቤት እሳት የሚያሞቀው።

ወዳጄ አትጠራጠር በዚህ መንገድ ያለ ቄስ፣ ባህታዊ፣ ፓስተር፣ ጳጳስ በለው ማን ገና ወንጌል አልገባውም ማለት ነው!

ወንጌል እውነት ናት። ላንተ እስኪገባህ ተማራት ከገባችህ ኑራት!፣ ከኖርካት አንድም ህይወትህ ሌሎችን ትሰብካለች ሌላም በአንደበትህ ለሌሎች ትመሰክራለህ!

የኤክትሪክ ገመድ እሳት አስተላላፊ ከሆነ መጀመሪያ ለራሱ ሙቀት ሲኖረው ብቻ ነው። ለራሱ ሙቀት የማይኖረው የኤሌክትሪክ ገመድ "የተቃጠለ ገመድ!" ተብሎ ይጣላል። አምፖልም ቢሆን "የተቃጠለ አንፑል" ተብሎ በቆሻሻ መጣያ ይወገዳል።

አየህ የተሰበከው ወንጌል ለራስህ ካልገባህ እንደነዚህ ምስኪን ልጆች ትሆናለህ። ወደ ሰው ቤት ገብተህ ቀልደህና አሹፈህ በወንጌል ወዳመንክበት ቤትህ ለማስገባትና ለዘላለም ሕይወት መስራትህን ረስተህ እንዲህ ወዳጅ ዘመድ ከማጣት በላይ ለቅስፈት ራስህን ታዘጋጃለህ።

በግሌ ብዙ የጵሮቴስታንት እምነት ተከታይ ዘመዶችም ሆኑ አብሮ አደግ ጓደኞች አሉኝ። እንደውም ዝም ብሎ ምዕመን ብቻ ሳይሆኑ አገልጋዮችም ጭምር ናቸው አብሮ አደጎቼ ግን የገባቸው ናቸውና እንኳን እንዲህ አድርገው ሊያሳዩ በንግግራችን መሀል ንግግራቸው እንዳያስቀይመን የሚጠነቀቁ መሆናቸውን ዘወትር አስተውላለሁ። ይኼ እውነት የአብነት እሴት የትክክለኛ አስተምህሮ ፍሬ ነው።

ሃይማኖት ማመን ነውና በወጣትነትም ሆነ በጎልማሳነትህ የምታምነው ከልጅነት ጀምሮ የተማርከውን ነው። ከልጅነት ጀምሮ የተማርከው ቤተሰብህንም መምህርህንም ሆነ አከባቢህን መምሰሉ ግድ ነው። በዚህ ሂደት ትክክል ሆነም አልሆነም የተጋትከውን ትርክትም ይዘህ ትቀጥላለህ። ሲገልጽልህ እና ሲፈቅድልህ ከብዙ ተራ ሰዎች ወጣ ብለህ ታነብ፣ ትመራመርና ተፈላስፈህ ወደ አንድ እውነት ትደርሳለህ!

ባንተ ዝግጅት ማጣት፣ መስነፍና ቸልተኝነት ግን ብዙ ዘመናትን በሆነ ካባ ስር ሃይማኖተኛ መስለህ በሃይማኖት ጥላ እንዲህ ትወርዳለህ።
ስለዚህ አባቶችና ከላይ ከመንበሩ ያላችሁ የሃይማኖት መሪዎች አስተምህሮ ግምገማ ላይ፣ ክቡር በሆነው የሰው ልጅ ስነ ቢህሪ እና ጠባያት ግንባታ ላይ ጊዜያችንን እንስጥ!

ሕንፃ ሥላሴ ሲኖር ነውና ሕንፃ ቤተክርስቲያን የምትኖረው ኢትዮጲያዊነት ላይ አብረን ሰርተን የአብሮነት ገመድ፣ የጋራነት እሴት በወሬ ሳይሆን በተግባር እንገንባ!

እስኪ አሰብ ሰከን ብላችሁ ይኼን በመጥፋት ያለን ሕዝብ እንታደግ!።
"አስተዋይም መልካም ምክርን ገንዘቡ ያደርጋል።" ምሳ 1-:-5

🌹<  ወስብሐት ለእግዚአብሔር  >🌹
               🌹🌹🌹
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

21 Jan, 10:52


ተይዘዋል!
በቃ ፍትሕ እንዲህ ነው ሳይንሸዋረር ሲታይ
በእውነት ደስ ይላል
አሁንም የተቀሩትን ሰዎች ሼር እና report እያደረግን ወደ ፍትህ እናቅርባቸው።

መቼ ጥል ክርክሩና ዘረኝነቱ በረደልንና ነው
በሃይማኖት ስም ነገር እንዲነሳ እሳት የሚያሞቁት?

አሁንም ፍትሕ ለስርዓታችን!

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

21 Jan, 10:19


ወደ ግብር አባታችሁ ወደ ዲያብሎስ እስክትሄዱ ፈንጩ

በትምህርት አልቻሉም ፣ በዕውቀት አልቻሉም ፣ በአመክንዮም አልሆነላቸውም ፣ የመጽሐፍትን ጥቅስ እየጠቀሱ መሟገትም አልሳካ አላቸው ፣ የመጽሐፍ ቅዱስን ትምህርት እንደሥጋ ፍቃድ በመተርጎምም ውጤት አላመጡም በመጨረሻም እንዲህ እንደምትመለከቷቸው በቤተ ክርስቲያን ንዋያት እና በዓላት ለማሾፍ ሞክሩ ።

ያው እሱም አይሳካም ምክንያቱም በእግዚአብሔር ንዋያት ሲያሾፍ የነበረውን ብልጣሶርን የቀጣ እግዚአብሔር ዛሬም አለና ። ለሁሉም እንደየሥራው ዋጋ የሚከፍል ኢየሱስ ክርስቶስ ዛሬም ያው ነው ። እግዚአብሔርን ተገን ያደረጉ ሰዎችን ዘመንን እና ምቹ ጊዜን ተገን ያደረጉ ሰዎች ድል ሲነሷቸው አይተንም ሰምተንም አናውቅም ።

የኢየሱስ ክርስቶስን ቤተ ክርስቲያን በማንጓጠጥ ኢየሱስ ክርስቶስን ማምለክ አይቻልም ። ቤተ ክርስቲያናችን እንኳን እናንተን ይቅርና ለአባታችሁ ለዲያብሎስም ክንዷ ዝሎ አያውቅም።
ዘመኗን ሙሉ ስታመልከው የምትኖረው ጌታዋ አምላኳ መድኃኒቷ ኢየሱስ ክርስቶስ "እስከ መከር ድረስ ተዋቸው" ብሎ ቃል ስለገባላት እስከዚያው ድረስ ፈንጩ ፣ ተሳደቡ ፣ አንጓጡ ፣ ጨፍሩ ፣ ጥቅስ እያጣመማችሁ ተሳለቁ በመከሩ ጊዜ ግን ወደላካችሁ አባታችሁ ዲያብሎስ ትኳትናላችሁ ።

የማይጠረቃ ሆዳችችሁን የማይሰግድ ጉልበታችሁን የማያመሰግን አንደበታችሁን በመዝሙር አሳባችሁ የምትደንሱበትን ሰውነታችሁን ይዛችሁ ወደላካችሁ የግብር አባታችሁ ሳጥናኤል ትሄዳላችሁ ። ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንን እና ምዕመናንን ለማጥላላት የምትሄዱበት እረቀት ከትዝብት ቢጥላችሁ እንጂ ኦርቶዶክሳዊ ማንነትን ቅንጣት ታክል የምትጎዱበት ነገር የለም ።

Via Zekaryas Kiros fb page

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

21 Jan, 07:25


ካህን በወንጀል ከተገኘ ክህነቱ ምን ይሆናል?
======
(ቀሲስ ኤፍሬም እሸቴ)
አንድ ካህን በተከሰሰበት ወንጀል "ወንጀለኛ" (በዚህ ሀገር አነጋገር Convicted felon) ሆኖ ከተገኘ ሥልጣነ ክህነቱ ምን ይኾናል?
======
ማስታወሻ፦ ቀሲስ በላይ በተከሰሱበት የባንክ የማጭበርበር ክስ ወንጀለኛ መሆናቸውን ፍርድ ቤት የወሰነ ሲሆን ፍርዱ ግን ለሌላ ጊዜ ተቀጥሯል።

"የፌደራሉ ፍርድ ቤት፣ ከአፍሪካ ኅብረት የባንክ ሂሳብ 6 ሚሊየን 50 ሺሕ ዶላር በሐሰተኛ ሰነድ ለማውጣት ሞክረዋል ተብለው በተከሰሱት ቀሲስ በላይ መኮንንና ግብረ አበሮቻቸው በእያሱ እንዳለ፣ በረከት ሙላቱ፣ ዓለምገና ሳሙኤል እና የኒሞና ንግድ ስራ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ሥራ አስኪያጅ በኾኑት አበራ መርጋ ላይ የጥፋተኛነት ውሳኔ መስጠቱን ፋና ሜዲያ ዘግቧል። ሦስቱ የችሎቱ ዳኞች በሙሉ ድምጽ ቀሲስ በላይ ጥፋተኛ ናቸው በማለት የወሰኑ ሲኾን፣ በእያሱና በረከት ጥፋተኛነት ላይ ግን አንድ ዳኛ በውሳኔ እንደተለዩ ዘገባው ጠቅሷል። ዓለምገና እና አበራ ፖሊስ ፍርድ ቤት ሊያቀርባቸው ባለመቻሉ፣ ክሳቸው ቀደም ሲል ተቋርጧል። ችሎቱ በሦስቱ ጥፋተኞች ላይ የቅጣት ውሳኔ ለመስጠት ለጥር 22 ቀጥሯል ተብሏል።"
[ዋዜማ ሬዲዮ]
======
ጊዜ ያልፋል። በእግዚአብሔር እና በቤተ ክርስቲያን ላይ የድፍረት ቃል መናገር። ጊዜ ሰጠኝ ብሎ አምላክን የሚያሳዝን ተግባር መፈጸም፤ ካህን ከሆኑ በኋላ ኢሬቻን በመሰለ የሌላ እምነት (ዋቄፈና) ሥርዓተ አምልኮ ላይ መገኘት፣ ለሌሎች የዋኅ ምእመናን መሰናከል መሆን ምንም ጥቅም የለውም።
======
"አትሳቱ፤ እግዚአብሔር አይዘበትበትም። ሰው የሚዘራውን ሁሉ ያንኑ ደግሞ ያጭዳልና" (ወደ ገላትያ ሰዎች 6፥7)

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

21 Jan, 07:20


😭መንግስት ካለ

በርግጥ ፍርዱ ከላይ ነው ቢሆንም ቀን ሲጥል ማታ ከሚሆነው በፊት የሕዝብን ሀደራ በሚወስድ መንግስት ፊት በስሩ ጥላ ሊያውም ዩኒቨርሳል በሆነው ዩኑቨርሲቲ ተብሎ በተሰየመ ተቋም እንዲህ ያለ ወራዳ ተግባር ባለቤቶን የተማመነች በግ ላቷን ከደጅ እንደምታሳድረው አይነት ተረት ይሆናል ነገሩ።

ሼር አድርጉት ለአምቦ ዩኒቨርስቲና ለመንግስት የጸጥታ አካላት ይድረስ! ይፍረዱም ይተው እሳቱን ከመለኮስ አለን በሚሉት እውነት ይዳኙን!

የሀማኖት መቻቻል እና እኩልነት ባለባት ኢትዮጵያ ምድር ላይ.....

እነዚህ 3 ልጆች

* ነገ ሀገር ይገነባሉ
* ነገ ተምረው ለህብረተቡም ሆነ ለሀገር ይጠቅማሉ ሲባሉ

እነሱ ግን ከኢትዮጵያዊነት ባፈነገጠ መልኩ ብዙ ሚሊዮን ተከታዬች ያለውን የኦሮቶዶክ እምነት የሆነው የቅዱስ ሚካኤልን ታቦት በማሾፍ ቬዝ በሚመስል መልኩ ቪዲዮ ሰርተው ቢቲክ ቶክ በሚባለው አፕ ለቀዋል::

መረጃዎች እንደሚያመለክቱት እነዚህ ልጆች በአምቦ ዩኒቨርስቲ የሚማሩ እንደሆኑ ሲሆን

* የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት
* የአምቦ ዩኒቨርስቲ አላፊዎች

አጣርተው እነዚህ ልጆችን ለህግ እንዲያቀርብ ብዙ ኢትዮጵያውያን እየተማፀኑ ይገኛል::

እናንተም ይሄ ነገር ሼር በማድረግ እንድትተባበሩ
ጥሪ ቀርቧል::

😭

🌴🌴🌴

🌹<  ወስብሐት ለእግዚአብሔር  >🌹
               🌹🌹🌹
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

20 Jan, 18:02


👉 "#ሚዛን!"👈
ውድ ኦርቶዶክሳዊያን እያወቅንም ሳናውቅም በምናደርጋቸው ጉዳዩች ተውና እረፉን ወደተመቸን ለማስጠጋት ፈልገን ከተዘነጋን "መሠረታችን ክርስትና እስከሆነ ድረስ ወይ የመጽሐፍ ቅዱስ እውነት ወይ ክርስቶስ ሊያግባባን ግድ ነው!"
ያለ ክርስቶስ እውነት ያለ ቅዱስ መጽሐፍ የሚነገሩ ንግርቶች፣ ስብከቶች፣ ዜማና መወድሶች ከእውነት ካስወጡን ውስጣቸው ሲበስል ነገ ክህደት ናቸውና ከልብ ሚዛናችን ጠንቀቅ እንበል!"

🌹<  ወስብሐት ለእግዚአብሔር  >🌹
               🌹🌹🌹
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

20 Jan, 15:32


🌿 ስንክሳር ጥር 13 🌿

እንኩዋን ለጻድቃን ቅዱሳን አቡነ ዘርዓ ቡሩክ እና 7ቱ ደቂቅ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ።

🙏 አቡነ ዘርዓ ቡሩክ 🙏

=>ሃገራችን ኢትዮዽያ:-
*ብሉይ ከሐዲስ ያልጐደለባት
*በክርስቶስና በድንግል እናቱ ኪደተ እግር የተቀደሰች
*የቅዱሳን መጠጊያ እና
*ብዙ ቅዱሳንን ከእቅፏ ያፈራች ስለ ሆነች የተባረከች ሃገር ትባላለች::

+ሁሉም የሃገራችን ክፍሎች ቅዱሳንን አፍርተዋል:: በምሥራቅም: በምዕራብም: በሰሜንም: በደቡብም ያሉ አካባቢዎች ሁሉ የቅዱሳን ቤቶች ናቸው:: ቅዱሳንን በብዛት ካፈሩ አካባቢዎች አንዱ ደግሞ ምድረ ጐጃም ነው::

በጐጃም አካባቢ ከተነሱ ቅዱሳን ደግሞ አንዱና ስመ ጥሩ ጻድቅ አቡነ ዘርዓ ቡሩክ ናቸው:: አቡነ ዘርዓ ቡሩክ በብዙ ጐዳና የተለዩ አባት ናቸው:: ለመጥቀስ ያህል እንኩዋ:-

1.በታሪክ ዓለምን ከበው የያዙ 2ቱ ግሩማን አራዊት (ብሔሞትና ሌዋታንን) ጥርስ ቆጥረው: ብዙ ምሥጢራትንም ተመልክተው ተመልሰዋል:: (በነገራችሁ ላይ ይህ ጉዳይ ዛሬም ድረስ ሳይንሱ በብዙ ድካም ያልደረሰበት ነው)

2.ጻድቁ በልደታቸው ጊዜ ዓይነ ስውራንን አብርተዋል:: ለራሳቸው ግን ይህን የግፍ ዓለም ላለማየት ጸልየው ዓይናቸው እንዲጠፋ አድርገዋል::

3.መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚል ቅዱስ ኢያሱ በገባኦን ፀሐይን አቁሟል:: ዘርዓ ቡሩክ ግን በጥበበ እግዚአብሔር ፀሐይን ለ5 ዓመት አቁመዋል::

4.ጻድቁ ከንጽሕናቸው ብዛት 12 ክንፍ (መንፈሳዊ ክንፍ) ተሰጥቷቸው ነበር:: ከዚህ በተረፈም በጾም: በጸሎት: በትርምትና በስብከተ ወንጌል ፍጹም ጽሙድ ነበሩ::

ጻድቁ የተወለዱት በ16ኛው መቶ ክ/ዘመን እዚያው ጐጃም ውስጥ ሲሆን አባታቸው ደመ ክርስቶስ: እናታቸው ደግሞ ማርያም ሞገሳ ይባላሉ:: ወላጆች በልጅ እጦት ተማለው ይህን የተቀደሰ ፍሬ አገኙ:: "ጸጋ ኢየሱስ" ብለውታል:: ከኢየሱስ ክርስቶስ ተሰጥቷቸዋልና::

ቀጥሎ የወለዱትንም "ተስፋ ኢየሱስ" ብለውታል:: ይህም የጻድቁ ታናሽ ወንድም ነው:: በሒደት ግን የጸጋ ኢየሱስ ስም በፈቃደ እግዚአብሔር ወደ ዘርዓ ቡሩክነት ተቀይሯል:: ጻድቁን ስመ ጥር ካደረጉዋቸው ሥራዎቻቸው መካከል በአፄ ሱስንዮስ ዘመን የሠሩት ቅድሚያውን ይወስዳል::

ነገሩ እንዲህ ነው:: በ1598 ዓ/ም በኢትዮዽያ ላይ የነገሡት አፄ ሱስንዮስ ዼጥሮስ ፓኤዝ (ፔድሮ ፓኤዝ) ከሚባል ፈረንጅ መናፍቅ ጋር በፈጠሩት ወዳጅነት ሃይማኖታቸውን ለወጡ:: ካቶሊክ (ሮማዊ)ም ሆኑ::

በሁዋላም አልፎንሱ ሜንዴዝ የሚሉት እሾህ መጥቶ ሁሉም የኢትዮዽያ ሕዝብ መናፍቅ እንዲሆን ከንጉሡ ጋር መከረ:: ለጊዜው በቤተ መንግስቱ አካባቢ የነበሩ መሣፍንት ተቀላቀሉ:: እየቆየ ግን ዜናው በመላ ሃገሪቱ ተሰማ::

በተለይ በ1611 በተዋሕዶ አማኞችና በመናፍቁ ንጉሥ መካከል ነገሩ ተካሮ ዻዻሱ አቡነ ስምዖን ጠዳ ላይ መገደላቸው ተሰማ:: በዚህ ጊዜ ገበሬው ከእርሻው: ሴቷ ከማዕድ ቤት: ካህኑ ከመቅደሱ: ነጋዴው ከገበያው እየወጡ ስለ ቀናችው ሃይማኖት ደማቸውን አፈሰሱ::

በበዓት የተወሰኑ በሺህ የሚቆጠሩ ቅዱሳንም ወጥተው ተሰየፉ:: በዚህ ጊዜም የግሺው አቡነ ዘርዓ ቡሩክ ዳዊታቸውን አንግበው ለሰማዕትነት ሔዱ:: ዓባይ ወንዝ ላይ ሲደርሱ ዳዊታቸውን ወደ ወንዙ ውስጥ ጣሉት::

ተሻግረውም ከንጉሡ አደባባይ ደንቀዝ ደረሱ:: በጊዜውም ልክ እንደነ ፍቅርተ ክርስቶስና ወለተ ዼጥሮስ እርሳቸውም መከራ ደረሰባቸው:: ንጉሡም ሳይገደሉ እንዲታሠሩ አደረገ:: በጨለማ እስር ቤትም 5 ዓመታትን ሲያሳልፉ ትኩስ ምግብን ያመጡላቸው ነበር::

እርሳቸው ግን ምግባቸው ሰማያዊ ነበርና አልነኩትም:: ከ5 ዓመት በሁዋላም ያ ሁሉ ምግብ በተአምራት በትኩስነቱ እየጨሰ ተገኝቷል:: ዘርዓ ቡሩክም ከእሥር ተፈትተዋል::

እግዚአብሔርም በከሐዲው ንጉሥ ላይ ፈርዶ ፋሲል ነግሷል: ሃይማኖት ተመልሷል:: ጻድቁም በዓባይ ወንዝ ላይ የጣሉት ዳዊታቸውን ሳይርስ አግኝተውታል::

ጐጃም ሲደርሱም ሰይጣን እርሳቸውን መስሎ ሲያስት ስላገኙት ወደ ጥልቁ አስጥመውታል:: በተረፈ ዘመናቸው አቡነ ዘርዓ ቡሩክ ብዙ ተጋድለው ጥር 13 ቀን ዐርፈዋል:: ታኅሳስ 13 ቀን ልደታቸው ነው::

<< ድንቅ ሠሪ አባት ናቸውና ዛሬም በግሺ ብዙ ተአምራት ይደረጋሉ >>

=>አምላከ አበው ቅዱሳን በመጽናታቸው ያጽናን:: ከበረከታቸውም ያድለን::
ጥር 13 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.አቡነ ዘርዓ ቡሩክ ኢትዮዽያዊ (እረፍታቸው)
2.ሰባቱ ደቂቅ ቅዱሳን (ከኤፌሶን)
3.ቅዱስ አባ ነካሮ
4.ቅዱስ ቃሮስ

=>ወርሐዊ በዓላት
1.እግዚአብሔር አብ
2.ቅዱስ ሩፋኤል ሊቀ መላእክት
3.ቅዱስ አስከናፍር
4."13 ግኁሳን ጻድቃን"
5.ቅዱስ አርሳንዮስ ጠቢብ
6.ዘጠና ዘጠኙ ነገደ መላእክት

" በተቀደሰ አሳሳም እርስ በርሳችሁ ሰላምታ ተሰጣጡ:: ቅዱሳን ሁሉ ሰላምታ ያቀርቡላቹሃል:: የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ: የእግዚአብሔርም ፍቅር: የመንፈስ ቅዱስም ኅብረት ከሁላችሁ ጋር ይሁን:: አሜን:: " (2ቆሮ. 13:12)


🌹<  ወስብሐት ለእግዚአብሔር  >🌹
               🌹🌹🌹
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

20 Jan, 15:32


🔔 ስንክሳር ጥር 12 🔔

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡

✞ እንኳን አደረሰን ✞

ጥር 12 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

🌿ቃና ዘገሊላ🌿

ቃና' የሚለው ቃል በሃገራችን ልሳን (በአማርኛ)
የምግብን: የመጠጥን ጥፍጥና ወይም በጐ መዓዛን የሚያመለክት ነው:: ምንአልባትም ከዚህ በዓል ምሥጢር የተወሰደ ሳይሆን አይቀርም::

በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ግን ቃና ከገሊላ አውራጃዎች አንዷ ናት:: ለስም አጠራሩ ስግደት ይሁንና የክብር ባለቤት መድኃኒታችን ክርስቶስ በዚህች ሥፍራ ተገኝቶ በድንግል እናቱ ምልጃ ታላቅ ተአምርን በዚህች ዕለት ሠርቷል::

ተአምር የሚለውን ቃል በቁሙ 'ምልክት' ብሎ
መተርጐም ይቻላል:: መሠረታዊ መልዕክቱ ግን ነጮቹ በልሳናቸው Miracle የሚሉት ዓይነት ነው:: ከተፈጥሮ ሕግ ውጪ (በላይ):
ከፍጡራንም ችሎታ የላቀ ነገር ሲሠራ (ሲፈጸም) ተአምር ይባላል:: ተአምር የእግዚአብሔር የባሕርይ ገንዘቡ ነው:: እርሱ ዓለምን ከመፍጠሩ ጀምሮ እያንዳንዷ ተግባሩ ለእኛ ተአምራት ናቸው::

ስለዚህም ነው 'ኤልሻዳይ / ከሐሌ ኩሉ / ሁሉን
ቻይ' እያልን የምንጠራው:: እግዚአብሔር ፍጡራኑን ይወዳልና እርሱ ለወደዳቸውና
ደስ ላሰኙት ተአምራት ማድረግን ሰጥቷል:: በብሉይ ኪዳን እነ ሙሴ ባሕር ሲከፍሉ: መና ሲያዘንሙ: ውሃ ሲያፈልቁ (ኦሪትን ተመልከት) እነ ኤልያስ ሰማይን ሲለጉሙ: እሳትን ሲያዘንሙ: ሙታንን ሲያስነሱ (1ነገሥትን ተመልከት) እንደ ነበር ይታወቃል::

እንዲያውም በሙሉ መጽሐፍ ቅዱስ የተአምር መጽሐፍ ነው ብሎ ለመናገርም ያስደፍራል:: በሐዲስ ኪዳንም መድኃኒታችን ብዙ ተአምራትን ሠርቶ ለሐዋርያቱ የተአምራት ጸጋውን ሰጥቷቸዋል:: (ማቴ. 10:8, 17:20, ማር. 16:17, ሉቃ. 10:17, ዮሐ. 14:12) እነርሱም በተሰጣቸው ሥልጣን ብዙ ተአምራትን ሠርተዋል:: (ሐዋ. 3:6, 5:1, 5:12, 8:6, 9:33-43, 14:8, 19:11)

ቅዱስ ዮሐንስ ሐዋርያ በወንጌሉ ምዕራፍ 2 ላይ
እንዳስቀመጠው የቃና ዘገሊላው ተአምር የመጀመሪያው ነው:: "ወዝንቱ ቀዳሜ ተአምር ዘገብረ . . ." እንዲል:: (ዮሐ. 2:11) ያ ማለት ግን ጌታ ከዚያ በፊት ተአምራትን አልሠራም ማለት አይደለም::

ይልቁኑ ራሱን ከገለጠና ከተጠመቀ በኋላ የሠራው
የመጀመሪያው ተአምር ነው ሲል ነው እንጂ:: ምክንያቱም መድኃኒታችን እንደ ተጠመቀ ዕለቱኑ ገዳመ ቆረንቶስ ገብቷልና:: (ማቴ. 4:1) አንድም በቃና ሌሎች ተአምራትን የሚሠራ ነውና ይህ
ተአምር በቃና የመጀመሪያው ሆነ::

+ትክክለኛው የቃና ዘገሊላ ቀን የካቲት 23 ነው:: ጥር 11 ተጠምቆ: የካቲት 21 ቀን ከጾም ተመልሷል:: ከዚያም የካቲት 23 ቀን ደቀ መዛሙርቱን ሰብስቦ ሒዷል:: ነገር ግን አበው መንፈስ ቅዱስ እንደ መራቸው የውሃ በዓል
ከውሃ በዓል ጋር ይስማማል ብለው ጥር 12 ቀን አድርገውታል::

በቃና ዘገሊላ ሙሽራው ዶኪማስ ሲሆን ባለ ሠርጉ
ደግሞ አባቱ ዮአኪን ነው:: ይህም ለሐዋርያው ቅዱስ ናትናኤል አጐቱ ነው:: የልጁ ጋብቻ የተቀደሰ ይሆን ዘንድም ጌታ ክርስቶስን: ድንግል እናቱንና ባለሟሎቹ ሐዋርያትን ወደ ሠርጉ ጠራ::

ምንም እንኳ መድኃኒታችንና እመቤታችን ከድግሱ
የማይበሉ ቢሆኑም (በትሕርምት ኗሪዎች ነበሩና)
ጠሪውን ደስ ለማሰኘት ሠርጉን (ብቻውን) ለመቀደስና የጋብቻን ክቡርነት ለማሳየት አብረው ታደሙ::

የሠርጉ ሥነ ሥርዓት ሲጀመር በድንኳኑ ውስጥ ጌታ ከመካከል ተቀመጠ:: ድንግል በቀኙ: ዮሐንስ በግራው
ሲቀመጡ: ሌሎች
ሐዋርያት ግራና ቀኝ ከበው ተቀመጡ:: ሲበላና ሲጠጣ
ድንገት የተደገሰው ምግብና መጠጥ አለቀ::
ደጋሾቹ በጭንቅ ላይ ሳሉም አይጠና ሆዷ ድንግል እመ ብርሃን የሆነውን አወቀች:: እንዴት አወቀች ቢሉ:- በጸጋ: አንድም 'ከልጅሽ አማልጂን' ብለው ቢለምኗት ነው ይሏል:: እመቤታችን በዚያ ጊዜ ወደ ልጇ ቀርባ ቸር ልጇን "ወይንኬ አልቦሙ-ወይኑኮ አልቆባቸዋል" አለችው::

+ለጊዜው ወይኑም: ምግቡም ስላለቀባቸው እንዲህ አለች:: በምሥጢሩ ግን ወይን ያለችው ፍቅርን: ቅዱስ ቃሉንና ክቡር ደሙን ነው:: ጌታም ይመልሳል:- "ምንት ብየ ምስሌኪ ኦ ብእሲቶ: ዓዲ ኢበጽሐ ጊዜየ-አንቺ ሆይ! (እናቴ ሆይ!)
ያልሺኚን አላደርግ ዘንድ ካንቺ ጋር ምን ጠብ አለኝ? ነገር
ግን ጊዜው ገና አልደረሰም ብየ ነው እንጂ" አላት::
ምክንያቱም ጌታ:-

*የወይን ጋኖቹ እስኪያልቁ ይጠብቅ ነበር:: (አበረከተ ይሉታልና) *አንድም ይሁዳ ወጥቶ ነበርና እርሱ እስኪመለስ ነው:: (እኔ ስወጣ ጠብቆ ተአምር ሠራ ብሎ ለክፋቱ ምክንያት እንዳያቀርብ) አንድም "ወይን (ቅዱስ ደሜን) የምሰጠው በቀራንዮ አንባ ነው" ሲል "ጊዜየ ገና ነው" ብሏታል:: አንዳንድ ልቡናቸው የጠፋ ወገኖቻችን ጌታ እመቤታችንን እንዳቃለላት (ሎቱ ስብሐት! ወላቲ ስብሐት!) አስመስለው ይናገራሉ:: ይህንን ስእንኅን ጌታ ባለጌዎቹ እነሱም አያደርጉት:: "አባትህንና እናትህን አክብር" (ዘጸ. 20) ያለ ጌታ እንዴት ለእናቱ ክብርን ይነፍጋል?ልቡና ይስጠን!

ወደ ጉዳያችን ስንመለስ መድኃኒታችን እንዲህ ሲል መለስላት:: ተግባብተዋልና እመ ብርሃን አሳላፊዎቹን "ኩሎ ዘይቤለክሙ ግበሩ-የሚላችሁን ሁሉ አድርጉ" አለቻቸው:: (ዮሐ. 2:5) ጌታም በ6ቱ ጋኖች ውሃ አስሞልቶ በተአምራት ወይን አደረጋቸው::

+እንጀራውን ወጡን በየሥፍራው ሞላው:: ታላቅ ደስታም ሆነ:: የአሳላፊዎቹ አለቃም (ለአባታችን አብርሃም ምሳሌ ነው) ከወይኑ ጥፍጥና የተነሳ አደነቀ:: በዚህም የድንግል ማርያም አማላጅነት: የመድኃኒታችን ከሃሊነት ታወቀ: ተገለጠ::

✞አምላከ ቅዱሳን ወይነ ቃና ፍቅሩን ያሳድርብን::
ከድንግል እናቱ ምልጃና ከቅዱሳኑ በረከትም አይለየን::

✞ጥር 12 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቃና ዘገሊላ
2.ቅዱስ ያዕቆብ እሥራኤል
3.ቅዱስ ቴዎድሮስ በናድሌዎስ
4.ቅዱሳን ለውንድዮስ እና ኒቆሮስ
5."2.5 ሚሊየን" ሰማዕታት (የቅዱስ ቴዎድሮስ ማሕበር)

🌹<  ወስብሐት ለእግዚአብሔር  >🌹
               🌹🌹🌹
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

19 Jan, 15:30


የኢትዮጲያ ጌጥ!

ለኢትዮጵያ ውበትም ድምቀትም የሆነችው የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን

ይህቺ ጥንታዊት ዘላለማዊት ቅድስት ቤተክርስቲያን በስጋም በነፍስም ለደከሙ ህይወት ትዘራለች ሰላምንም ትሰብካለች
ከዚያም አልፎ የኢትዮጵያን ታሪክን በመፅኃፍት የሰነደች በጥንታዊ የስነ ህንፃ ውበትም ለኢትዮጵያ ውበት ያጎናፀፈች ናት

ከዚህ በተጨማሪም ለኢትዮጵያ የዶላር የገቢ ምንጭም የፈጠረች ናት

አንድ የውጭ ዜጋ ሊጎበኝ ወደ ኢትዮጵያ ለመምጣት ሲያስብ በቀዳሚነት ታሳቢ የሚያደርገው በዩኔስኮ የተመዘገቡትን የዚህችን ቤተክርስትያን ንብረቶች የሆኑትን እንደ
1.የላሊበላ አቢያተ ክርስቲያናትን;
2.የጎንደርን የጥምቀተ ባህር አከባበር 3.ጥንታዊ የጣና ገዳማትን
4.የመስቀል በዓልን
5.ጥንታዊዉን የደብረብርሃን ስላሴን እና ሌሎች የቤተክርስቲያኗን ንብረቶችታሳቢ አድርጎ ነው ::

ይህችን ለነፍስም ለስጋም በረከት የሆነችን ቤተክርስቲያን ለዋለችው ከፍተኛ ውለታ የሚገባትን ክብር እንስጣት

እስኪ በኮሜንት ላይ እናመስግናለን ቅድስት ቤተክርስቲያን በሏት ፍቅራችሁን ግለፁላት

እንኳን አደረሳችሁ
🙏🙏🙏

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

18 Jan, 23:10


ከተራ እና ጥምቀትን ጥቁር ለብሰው ማቅ ነስንሰው በሐዘን ያከበሩ ዘንድ የተፈረደባቸው በሀዲያ ዞን የሚገኙት የጊንብቾ ከተማ ኦርቶዶክሳውያን
***

በተለያዩ ከተሞች ከተገለጡ ደማቅ የከተራ ትዕይንቶች በላይ እስከ አጥንት ዘልቆ የሚሰማ ሐዘን ቅድስት ቤተክርስትያን በሀዲያ ዞን ጊንብቾ ከተማ እያሳለፈች ትገኛለች።

የጥምቀት ማክበርያ ስፍራ ተነፍገው መከራን እየተጋፈጡ የሚገኙት የጊንብቾ ኦርቶዶክሳውያን ከተራን እንዲህ ጥቁር ለብሰው ማቅ ነስንሰው አሳልፈዋል።

ተለመነንን 🙏🙏?

Vua Kune Demelash kassaye -Arba Minchnch

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

18 Jan, 22:53


ስለወላይታ ኦርቶዶክሳውያን ደምቀው ያልተሰሙ መገለጫዎች
***

ወላይታ ሲባል ኦርቶዶክሳዊነት ብዙም የለመለመ ለማይመስላቸው ሰዎች ይህን አድርሱ።

ወላይታ... የጻድቁ አባታችን አቡነ ተክለሃይማኖት ሰፊ እና ረጅም አመታትን ታላቅ ተጋድሎ የተፈጸመባት የጻድቁ አባታችን የአደራ ምድር ናት

የኢ/ኦ/ተ/ቤተክርስቲያን 3ኛው ቅዱስ ፓትርያሪክ የሆኑት ብጽዑ ወቅዱስ አቡነ ተክለሃይማኖት እና በጣልያን ጥይት ተደብድበው የሞቱት ብጽዑ አቡነ ጴጥሮስ የተገኙባት ከእዚህች ምድር ከተገደሙ ገዳማት ውስጥ ነው ።

ከደቡብ ኢትዮጵያ የዞን ዋና ከተሞች መሃል እንደ ወላይታ ሶዶ ከተማ በቁጥር የበዙ አብያተክርስቲያናትን የያዘ ከተማ የለም

ወላይታ ሶዶ ወደ 23 ደብራት ያሏት ሲሆን ይህም አርባምንጭ ከተማ ላይ ካሉ አብያተክርስቲያናት ብዛት በ2 ዕጥፍ ይበልጣል።

አበው መኖኮሳትን በማፍራት ረገድ ዛሬም ድረስ ያልነጠፉ 2 ገዳማትን በመሃል ከተማ የተተከለባት ከተማ ስም ወላይታ ሶዶ ይባላል።

ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ የአብያተክርስቲያናትን የመቅደስ አገልግሎት የሚፈጽሙ ካህናትን (ሊቀጳጳሱን ጨምሮ) በአከባቢ ቋንቋ ተናጋሪ ካህናት የሸፈነች ምድር ናት።

የኦርቶዶክሳዊ ምዕመናንን ፍሰት ሙሉ በሙሉ ቆሞባት ጠንካራ ሐዋርያዊ አገልግሎት በመፈጸን ሙሉ የሌላ ቤተ እምነት ሙሉ በሙሉ እስከ መቀየር የሚደርስ አዳዲስ ምዕመናንን የማስጠመቅ ልምድ የተገለጠባት ምድር ናት።

እነሆ ዛሬም ወላይታ ሶዶ ከተራን እንዲህ አሳልፋለች

Via Kune Demelash kassaye -Arba Minch

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

08 Jan, 06:05


ገና እንዘምራለን

እግዚአብሔር ለምን ሰው ሆነ?
የተዘጋ አንደበትን ለምስጋና ሊከፍት አይደለምን?
ከተፈወሱ ድውያን መካከል ዲዳዎች ይገኙበታል። ዲዳነት ምንድነው?
ደንቆሮነትስ?
እግዚአብሔርን ካለማመስገን በላይ ዲዳነት አለ?
ቃለ እግዚአብሔር ካለመስማት የበለጠ ደንቆሮነጽ የት ይገኛል?

ሊቃውንቱ “በሀማነ ሥጋ በተአምራት፣ በሀማነ ነፍስ በትምህርት ተፈውሰዋል” ያሉት ስለዚህ ነው።
ደዌ ሥጋንም ደዌ ነፍስንም ሊያድን መጥቷልና አንደበቱ ተፈቶለት ከሚናገር ዲዳ በላይ ነፍሱ የዝማሬን ቃል የተናገረችለት ክርስቲያን በክርስቶስ ፊት ታላቅ ተአምራት ተደርጎለታል።
“ኤፍታህ” የተባለች ነፍስ ማለት ይህች ናት ማር. 7፥34።

የአእላፋት ዝማሬን ስመለከት እግዚአብሔር የምስጋና ስጦታን ለዘመናችን ትውልድ እየሰጠ መሆኑን ተረድቻለሁ። እልፍ ኃጢአት ተሠርቶ በሚያድርበት ዘመን እልፍ ሆነን ለዝማሬ እንድንነሣ ያደረገንን አምላክ በልቤ አመሰገንሁት።
ክርስቶስን ማዕከል አድርገን ምስጋና በጀመርንበት ቀን ዛሬም ለምስጋና መሰብሰባችን ከሰይጣን በቀር ማንንም ያስደነግጣል ብየ አላስብም።
ብዙ የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮችና አገልግሎታቸው የተወደደ መምህራን እና ዘማርያን ሁሉ ሲሳተፉበት ስላየሁ እኔን የተሰማኝ የደስታ ስሜት ሌሎችም ዘንድ መኖሩን አውቄአለሁ። ለነገሩ እንዳለመታደል ሆኖ መቃወም የሚወዱ ወይም ጥንቃቄና ጥርጣሬ ለተቀላቀለባቸው ካልሆነ በቀር የቤተ ክርስቲያናችን ፓትርያርክ እና ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የተገኙበትን መርሐግብር መቃወም በራሱ በቀኖና ቤተ ክርስቲያን ለሚያምን አንድ ክርስቲያን የሚቻል አይደለም።
ምናልባት ሌላ የተለየ ጉዳይ ካልገጠመ በስተቀር እንደ አእላፋት ዝማሬ ያለ ያልተሸፋፈነ፣ ከጀርባው ድብቅ አጀንዳ የሌለው፣ ለመተቸትም ሆነ ለማመስገን ለሚፈልግ ሰው ቅኔ ሆኖ ፍቱልኝ ተብሎ የማያስቸግር መርሐግብር ላይ ቅዱስ ፓትርያርኩ መገኘታቸው ብቻ የቤተ ክርስቲያን መሆኑ በቂ ማስረጃ ነው። ሌላ አንቀጽ ሳንጠቅስ የቅዱስነታቸውን መልዕክት ብቻ በመስማት ልንቀበለው የሚገባ ጉዳይ ነው።

የአእላፋት ዝማሬ ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚአብሔር እንድትዘረጋ የሚያደርግ መርሐግብር ነው። አንድም ሰው የጭንቀት ፊት አይታይበትም ነበር ሁሉም ደስ ብሏቸው የሚዘምሩ ምዕመናንን ብቻ ነው የተመለከትሁት። ማንም ምንም ነገር ከማሰብ ወጥቶ በዚያ ሰዓት እግዚአብሔርን ብቻ በማሰብ ውስጥ እንደሆነ ይሰማኛል።

ባለፈው ዓመት የነበረው መርሐግብር ላይ የመጀመሪያው መሥመር ላይ ተሰልፌ መዘመሬን እንድታውቁልኝ እፈልጋለሁ። ዘንድሮ በቦታው ባልገኝም ተጀምሮ እስከሚያልቅ ደስ ብሎኝ እያለቀስሁ ነው የተመለከትሁት። ይሄንን ያህል ቁጥሩን እንኳን የማናውቀውን ሕዝብ በዚያ ሁሉ ሰዓት ደስታን የሚፈጥር መዝሙር ማቅረቡ የደስታ መንፈስን ለቤተ ክርስቲያን የሰጠ መንፈስ ቅዱስ ዛሬም በመቅደሳችን ውስጥ ያልተለየ መሆኑን ይመሰክርልናል።

የአእላፋት ዝማሬ በእውነት ለአእላፋት መዳን የተዘጋጀ መርሐ ግብር ነው። በሌሎች ጉባኤያት እና በዚህ ጊዜ የነበረውን የሥነ ምግባር መጠበቅ እስኪ ተመልከቱት? ነጭ ለብሰን መምጣታችን አንድ ነገር ሆኖ ወንዶቹ አስበውበት ነጠላ ለብሰው ለአገልግሎት ተዘጋጅተው መምጣታቸው በራሱ የሚያዘጋጀን ካገኘን ለማገልገል ዝግጁ ነን የሚል መልዕክት አስተላልፎልኛል።

አንዳንዴ እኮ የሴቶችን ነጠላ ቀምተው ከበሮ ለመምታት ወደ መድረክ የሚወጡ አገልጋዮችን አይተን እናውቃለን። የአእላፋት ዝማሬ ሰውን ወደ ልብሱ የመለሰ መርሐ ግብር ነው።

በጣም የገረመኝ የአእላፋት ዝማሬ ሁሉም መሣሪያውን ጥሎ ለዝማሬ ብቻ እንዲሰለፍ ያደረገ መሆኑ ነው። እረኛ ዋሽንቱን፣ ንጉሥ ዙፋኑን ጥሎ በዘመረበት ቀን ማን ለዝማሬ የማይጠቅም መሣሪያ ይዞ ይመጣል? ብለው መሰለኝ ሌላ ጊዜ ፕሮግራም ሊሠሩ የሚመጡ ሁሉ ከምስጋና በቀር ምንም የማይሠሩበት ቀን አድርገውት አይተናል።

መርሐ ግብሩን በመላው ዓለም ለማስተላለፍ ከተዘጋጁ ካሜራዎች በቀር ሌላ ማንም ካሜራውን አንጠልጥሎ የመጣ ሰው እኔ አላየሁም። በካሜራ ቀርጸው በልዩ ልዩ መገናኛ ዘዴዎች ለዓለም የሚያዳርሱ የነበሩ ወንድሞችና እኅቶች ሁሉ ከካሜራ ጋር መታገሉን ትተው በተመስጦ ሲዘምሩ አይተናቸዋል።

እግዚአብሔር ከዚህ ሌላ ከእኛ ምን ይፈልጋል?
አንድ ሆነን በፍቅር እንድንዘምር አይደለምን?
በኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ስም የተሰየመው የጃንደረባው ትውልድ ሊመሰገን ይገባዋል።
በዓለም ፊት የሚያስደንቅ ውበታችንን የገለጠ ጩኸት ሳያበዛ፣ እዩልኝ ስሙልኝ ሳይል የሚያገለግሉ ወንዶችና ሴቶችን ካህናትንና ዲያቆናትንም ያካተተ ኅብረት ነው። በዘመኔ ምድር በምስጋና ስትሞላ በማየቴ ደስ ብሎኛል። ለዚያውም የዕርጋታ መንፈስ በተሞላበት መንፈስ የሚዘምሩ መዘምራንን ማየት እጅግ በዘመኔ ትውልድ እንድመካበት አድርጎኛል።

በስም ብጠራ ብዙ ናችሁ በዚያውም ላይ እኔ ያየሁት ካሜራው ያመጣልኝን ነው እንጅ ከካሜራ ዐይን ያልገባችሁ አገር የሚያውቃችሁ መምህራንና ዘማርያን በእውነት ታኮራላችሁ።

ከመድረክ በታች ሆኖ ማገልገል ምን ያክል ፈታኝ እንደሆነ ነጭ መጋረጃ ከጀርባችን፣ ወርቀ ዘቦ ግምጃ ከወንበራችን የማይለየን ሰዎች እናውቀዋለን።
ታላላቆቼ! ክርስትና እንዲህ አንድ ሆነን የእግዚአብሔርን መንግሥት የምንወርስበት ሕይወት ነውና ከሰበካችሁበት ቀን ይልቅ ዛሬ ብዙ አስተምራችሁኛል። በተለይ ዲያቆን ብርሃኑ አድማስ ብርሄ ያንተስ ይለያል ባለፈውም ዓመትም ዘንድሮም ሳይህ የምስጋና ተመስጦህ ተለይቶብኛል። ካወቅሁህ ጊዜ ጀምሮ እንዲሁ ሳልወድህ የቀረሁበት ቀን አልነበረም ዛሬ ደግሞ ለመውደዴ ምክንያት የሚሆን ነገር ጨመርህልኝ።

የቤተ ልሔምን እረኞች ለምስጋና የጠራቸውን መልአክ አስታውሱት ሉቃ. 2፥9 ዲያቆን ሄኖክ ማለት ያ መልአክ ነው። ሄኖኬ አንተን ለመንቀፍ ነው የምንቸገር እንጅ ለማመስገን ብዙ ምክንያት አለን። እኔ በበኩሌ ዝም የምለው ባመሰገንሁህ ቁጥር ፈታኝ እየጋበዝሁብህ ወይም ለሰይጣን ጥቆማ እየሰጠሁብህ እንደሆነ ስለሚሰማኝ ነው። “ቤተ ክርስቲያንን አንተውም ከቶ፤ የሰጠንን አምላክ በደሙ መሥርቶ” ብለህ ግጥምና ዜማ ሠርተህ የለ? በል ይሄንን ቃልህን እንዳትረሳ የሚቀጥለው ዓመት ናፍቆኛል።

ከአእላፋት ወደ ትእልፊት እየተሸጋገርን ገና እንዘምራለን።
በአንድ ከተማ ብቻ ሳይሆን በመላው ዓለም ይሄ መርሐ ግብር ተጀምሮልን ገና እንዘምራለን!።

መ/ር ስምዐኮነ መልአከ
29/04/2017
🌹<  ወስብሐት ለእግዚአብሔር  >🌹
               🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

07 Jan, 16:43


ስንክሳር ታሕሳስ  30

እንኩዋን ለቅዱሳን ጻድቃን ወገዳማውያን "አባ ዮሐንስ" : "አባ ዘካርያስ ወአባ ዮሐንስ" ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ

🙏" አባ ዮሐንስ ዘአስቄጥስ "🙏

ገዳማዊ ሕይወት ጥንቱ ብሉይ ኪዳን ነው:: በቀዳሚነትም በደብር ቅዱስ አካባቢ ይኖሩ የነበሩ ደቂቀ ሴት እንደ ጀመሩት ይታመናል:: ሕይወቱ በጐላ: በተረዳ መንገድ የታየው ግን በታላቁ ጻድቅ ሄኖክ: ከዚያም በቅዱሱ ካህን መልከ ጼዴቅ አማካኝነት ነው::

ቀጥሎም እነ ቅዱስ ኤልያስ ነቢይ: እነ ኤልሳዕ ደቀ መዝሙሩ ኑረውበታል:: በሐዲስ ኪዳን ደግሞ ሙሉ ሕይወቱን በገዳም (በበርሃ) ያሳለፈው መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ቅድሚያውን ይይዛል::

ለስም አጠራሩ ስግደት ይሁንና መድኃኒታችን ክርስቶስ በገዳመ ቆረንቶስ ለ40 ቀናት በትሕርምት ኑሮ ገዳማዊ ሕይወትን ቀድሷል: አስተምሯል:: በዘመነ ስብከቱም ያድርባት የነበረችው የደብረ ዘይቷ በዓቱ (ኤሌዎን ዋሻ) በራሷ ለዚህ ሕይወት ትልቅ ማሳያ ናት::

ከጌታ ዕርገት በሁዋላም ክርስቲያኖቹ የዓለም ሁካታ ሲሰለቻቸው: አንድም በንጹሕና በተሸከፈ ልቡና ለፈጣሪያቸው መገዛትን ሲሹ ከከተማ ወጣ እያሉ ይኖሩ እንደ ነበር የታሪክ መዛግብት ያሳያሉ:: አኗኗራቸውም በቡድንም: በነጠላም ሊሆን ይችላል::

ዋናው ነገር ግን በጾምና በጸሎት መትጋታቸው ነው:: ይሕም ሲያያዝ እስከ 3ኛው መቶ ክ/ዘመን ደረሰ:: በዚህ ዘመን ግን አባ ዻውሊ የሚባል አንድ ንጹሕ ክርስቲያን ይሕንን ሕይወት ወደ ሌላ ደረጃ ከፍ አደረገው:: ለ80 ዓመታት ሰው ሳያይ ተጋድሎ "የባሕታውያን አባት" ተባለ:: ደንብ ያለው ተባሕትዎም ጀመረ::

ይህ ከሆነ ከ20 ዓመታት በሁዋላ ደግሞ አባ እንጦንስ የሚባሉ ደግ ክርስቲያን ይህንን ገዳማዊ ሕይወት በሌላ መንገድ አጣፈጡት:: በቅዱስ ሚካኤል አመንኩዋሽነት ገዳማዊ ሕይወት በምንኩስና ተቃኘ:: ስለዚህም አባ እንጦንስ የመነኮሳት አባት ተባሉ::

እርሳቸውም ሕይወቱን ለማስፋፋት ከተለያዩ አሕጉር ደቀ መዛሙርትን እየተቀበሉ አመንኩሰዋል:: ቅዱሳን የአባ እንጦንስ ልጆችም ወደየ ሃገራቸው ተመልሰው: ሕይወቱን በተግባር አሳይተው ገዳማዊነትን አስፋፍተዋል::

አባ እንጦንስ አባ መቃርስን: አባ መቃርስ አባ ዮሐንስን ወልደዋል:: አባ ዮሐንስም የታላቁ ገዳመ አስቄጥስ አበ ምኔት ሆነው በጸጋ አገልግለዋል:: አስቄጥስ በምድረ ግብጽ የሚገኝ: በስፋቱና ብዙ ቅዱሳንን በማፍራቱ ተወዳዳሪ የሌለው የዓለማችን ቁጥር አንድ ገዳም ነው::

ሕይወተ ምንኩሰናም ወደ መላው ዓለም የተስፋፋ በዚህ ገዳም መናንያን አማካኝነት ነው:: በዚህ ገዳም ላይ የሚሾሙ አበው ደግሞ በብዛት መንፈስ ቅዱስ ያደረባቸውና አባታቸውን ቅዱስ መቃርስ ታላቁን የመሰሉ ናቸውና ኃላፊነቱ እጅግ ከባድ ነው::

በ5ኛው መቶ ክ/ዘመን በምድረ ግብጽ ተወልደው ያደጉት አባ ዮሐንስ ከመነኑባት ዕለት ጀምረው በፍጹም ተጸምዶና ተጋድሎ ለፈጣሪያቸው ስለ ተገዙ የታላቁ ገዳም አበ ምኔት ሊሆኑ ተገባቸው::

+በአበ ምኔትነት ዘመናቸውም መንጋውን ይጠብቁ ዘንድ ብዙ ደከሙ:: በተለይ ቅዱስ ቃሉን ያስተምሩ ዘንድ ተጉ:: ሕይወተ መላእክትንም ያሳዩ ዘንድ በቃል ብቻ ያይደለ በተግባር ሆነው ከመንፈሳዊ አብራካቸው ብዙ ቅዱሳንን ወለዱ::

ከዋክብቱ አባ ገዐርጊ: አባ አብርሃም: አባ ሚናስ: አባ ዘካርያስ . . . የአባ ዮሐንስ ፍሬዎች ናቸውና:: ጻድቁ በዘመናቸው ብዙ ተአምራትን ሠርተዋል:: ከዕረፍታቸው በሁዋላ እንኩዋ መግነዛቸውና የልብሳቸው እራፊ ብዙ ድውያንን ፈውሷል::

አንድ ጊዜም ለልጆቻቸው መነኮሳት ቤዛ ሆነው በበርበር (አረማውያን) ተማርከዋል:: በዚያም ክፉዎች ባሪያ ቢያደርጉዋቸው እግዚአብሔር ድንቅን ሠርቶ ወደ ገዳማቸው መልሷቸዋል:: ከብዙ ተጋድሎ በሁዋላም በ90 ዓመታቸው በዚህች ቀን ዐርፈው በበዓታቸው ተቀብረዋል::

=>ታሕሳስ 30 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.አባ ዮሐንስ አበ ምኔት
2.አባ ዘካርያስ ገዳማዊ
3.አባ ዮሐንስ ብጹዕ
4."144 ሺ" ሕጻናት (ሔሮድስ የገደላቸው)

=>ወርኀዊ በዓላት
1.ቅዱስ ማርቆስ ሐዋርያ
2.ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቀ መለኮት
3.ቅዱስ ጐርጐርዮስ ነባቤ መለኮት
4.ቅድስት ሶፍያ ሰማዕት
5.አባ ሣሉሲ ክቡር ጻድቅ

🌹<  ወስብሐት ለእግዚአብሔር  >🌹
               🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

07 Jan, 04:29


ስንክሳር ታኅሳስ 29

እኛን ስለ ወደደ ሰው የሆነ ጌታ ፍቅሩን ይሳልብን:: ከድንግል እናቱና ከልደቱ በረከትም ያሣትፈን::

ታሕሳስ 29 ቀን የሚከበሩ
         ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ልደተ ክርስቶስ ስቡሕ
2.ታኦዶኮስ (ድንግል ማርያም)
3.ቅዱስ ኢያሱ ነቢይ (ልደቱ)
4.ቅዱስ ላሊበላ (ልደቱ)
5.አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ (ልደታቸው)
6.ጻድቅ አቃርዮስ (ንጉሠ ሮሃ)
7.ቅዱስ ቆሪል ገመላዊ
8.ሰብአ ሰገል
9.ዮሴፍና ሰሎሜ
10.ቅዱሳን ሰማዕታተ አክሚም

=>ወርኀዊ በዓላት
1.ቅዱስ ዼጥሮስ ተፍጻሜተ ሰማዕት
2.ቅዱስ ማርቆስ ዘቶርማቅ
3.ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ ኢትዮዽያዊት
4.ቅዱስ ዘርዐ ክርስቶስ
5.ቅድስት አርሴማ ድንግል

" እነሆ ለሕዝቡ ሁሉ የሚሆን ታላቅ ደስታ የምሥራች እነግራቹሃለሁና አትፍሩ:: ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት: እርሱም ክርስቶስ: ጌታ የሆነ ተወልዶላቹሃልና:: " (ሉቃ. 2:10)

🌹<  ወስብሐት ለእግዚአብሔር  >🌹
               🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

06 Jan, 17:39


"ሕዝብ ዘይነብር ውተ ጽልመት ወጽላሎተ ሞት ብርሃን ዓቢይ ሠረቀ ላዕሌሆሙ።"
ይህንን ሊቃውንት ሲተረጉሙት

"በድንቁርና/በቀቢፀ ተስፋ/ ለነበሩ ሰዎች ዕውቀት ተሰጣቸው፣
አንድ ገጽ በማለት ለነበሩ ሰዎች ክርስቶስ ተወለደላቸው ወንጌልም ተጻፈላቸው ፣
በሞተ ሥጋ በሞተ ነፍስ ለነበሩ ሰዎች ልጅነት ተሰጣቸው ፣
በኃጢአት በክህደት ለነበሩ ሰዎች ሃይማኖት ተሰጣቸው።"

ቅዱስ ሳዊሮስም በሃይማኖተ አበው 85:35-37
እንኳን በሰላም ለዚህች ቀን አደረሰን!
🙏🙏🙏
🌹<  ወስብሐት ለእግዚአብሔር  >🌹
               🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

06 Jan, 10:39


“ወደ ቀደመው ዘመን አገልግሎታችን እንመለስ!!” በሚል መሪ ቃል በማኅበረ ቅዱሳን የሰቆጣ ማእከል የአባላት የማትጊያ መርሐ ግብር ተካሄደ፡፡

“ወደ ቀደመው ዘመን አገልግሎታችን እንመለስ!!” በሚል መሪ ቃል በማኅበረ ቅዱሳን የሰቆጣ ማእከል አዘጋጅነት በትላትናው ዕለት ታኀሣሥ 27 ቀን 2017 ዓ.ም የአባላት የማትጊያ መርሐ ግብር ተካሂዷል፡፡

በተካሄደው መርሐ ግብሩ ላይ በማእከሉ የሥልጠና እና አቅም ማጎልበቻ ክፍል ኃላፊ ዲያቆን ደባሽ ደሳለኝ ባቀረቡት የመወያያ ጹሁፍ እንደገለጹት ስለአገልግሎት ስናስብ ወደ ኋላ ተመልሰን የቀደሙ የማኅበረ ቅዱሳን አባላት የነበራቸውን ትጋትና ጥንካሬ በማየት እነርሱ ያለፋበትን የአገልግሎት መንገድና ትጋት መከተል ከእያንዳንዱ አባል ይጠበቃል ብለዋል። መንፈሳዊ ዝለትና የኢኮኖሚ አቅም ማነስ ለማኅበረ ቅዱሳን አገልግሎት መዳከም ተግዳሮት እየሆኑ ነው ያሉት ዲ/ን ደባሹ በጊዜ የለኝም መንፈስ በቁርጠኝነት ማገልገልና የኢኮኖሚ አቅም የምንፈጥርባቸው ፕሮጀክቶችንና የልማት ሥራዎችን በትበብር መፍጠር ያስፈልጋል ሲሉ መፍትሄውን አመላክተዋል።

ዲ/ን ናትናኤል ሙሊሽዋ የማእከሉ ምክትል ሰብሳቢ በበኩላቸው ሁሉም አባል ለአገልግሎት መትጋትና ቤተ ክርስቲያኗ ከአባሉ የምትፈልገውን አገልግሎት በቅንነት፣በታማኝነትና በተጠያቂነት በመወጣት ማኅበሩ ሊደርስብት ላቀደው ግብ መሳካት መሥራት ይኖርበታል ሲሉ አሳስበዋል።

በአባላት ማንቂያ መርሐ ግብሩ ላይ የገተገኙት የወለህ ነቅዓ ሕይወት የአራቱ ጉባኤ ቤት መምህር መዝገበቃል ገ/ሕይወት መንፈሳዊ አገልግሎትን የተመለከተ ትምህርት ያስተማሩ ሲሆን ከቅዱሳን ህብረት ለመቀላቀል ነቅቶና ተግቶ ማገልገል ያስፈልጋል በማለት ገልጸው እያንዳንዱ አባል በኢኮኖሚያዊ፣ በፖለቲካዊና በማህበራዊ ዘርፍ ንቁ ተሳትፎ ማድረግ እንደሚኖርበት ተናግረዋል፡፡

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

05 Jan, 15:23


  ስንክሳር ታሕሳስ 28
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡

እንኳን አደረሳችሁ

=>ታሕሳስ 28 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

" ቅዱስ አማኑኤል "+

የክርስትና ሃይማኖት እጅግ ብዙ ምሥጢራትን
ያካትታል:: ታላቅ መዝገብ ነውና:: ሰዎች እናልፋለን:: ዓለምም ታረጃለች እንጂ ምሥጢረ ክርስትና አያረጅም:: እዚህ ቦታ ላይ ይጠናቀቃልም አይባልም::

'አማኑኤል' የሚለውን ስም መረዳት የሚቻለው በአንድ መንገድ: እርሱም ምሥጢረ ሥላሴንና ምሥጢረ ሥጋዌን ጠንቅቆ በመማር ነው:: ምሥጢራት ደግሞ በእምነት ለማይኖር:
በትሕትናም ለማይቀርብ የሚገለጡ አይደሉም::

እግዚአብሔር አንድም ነው: ሦስትም ነው:: ጊዜ
ሣይሠፈር ዘመንም ሳይቆጠር እግዚአብሔር በስም: በአካል: በግብር ሦስትነቱ: በባሕርይ: በሕልውና: በመለኮትና በሥልጣን አንድነቱ የጸና አምላክ ነው::

ከዓለም መፈጠር በፊት ስለ ነበረው ነገር የሚያውቅ ራሱ ሥላሴ ብቻ ነው:: ዓለምን ከፈጠረ በኋላም ምሥጢረ ሥላሴ (መለኮት) ብለን የምንማረው ትምሕርት እንድንና እንጠቀም ዘንድ እርሱ የገለጠልንን ያህል ብቻ ነው::

ይኼውም በየጊዜው እርሱ ለወደዳቸውና ደስ ላሰኙት ቅዱሳኑ የገለጠው ምሥጢር ነው:: ከዚህ አልፈን በሥጋዊ አዕምሯችን ጌታን 'እንመርምርሕ' ብንለው ግን ፍጻሜአችን ሞት: ማደሪያችንም ገሃነመ እሳት መሆኑ አይቀርም::

ወደ ቀደመ ነገራችን እንመለስና እግዚአብሔር
በአንድነቱና ሦስትነቱ ሳለ ይህንን ዓለም ፈጠረ::
እግዚአብሔር ዓለምን ለምን ፈጠረ ቢሉ:- ስሙን ቀድሰን ክብሩን እንድንወርስ ነው:: ከዚህ የተረፈውን ምክንያት ግን ራሱ ባለቤቱ ያውቃል::

እግዚአብሔር በሁዋለኛው ዘመን ሰው የሆነበት
ምሥጢር እኛን ለማዳን ቢሆንም ይሔው ተግባሩ ዓለም ሳይፈጠር ያሰበው እንጂ በአዳም ውድቀት ምክንያት ድንገት የታሰበ አይደለም::

እግዚአብሔር አዳምን በ7 ሃብታት አክብሮ በገነት
ቢያኖረው 'አትብላ' የተባለውን ዕፀ በለስ በላ:: በዚህም ከፈጣሪው ተጣልቶ: በሞተ ሥጋ ሞተ ነፍስ: በርደተ መቃብር ርደተ ገሃነም ተፈረደበት:: በኋላ ግን ንስሃ ስለ ገባ "ከ5 ቀንተኩል (5,500 ዘመን) በኋላ ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለሁ" የሚል ቃል ኪዳንን ሰጠው::

ከዚህ በኋላ ለ5,500 ዘመናት ጊዜ ወደ ታች ይቆጠር ጀመር:: ስለ እግዚአብሔር ሰው መሆንና ዓለምን ማዳንም ትንቢት ይነገር: ሱባኤ ይቆጠር: ምሳሌም ይመሰል ገባ::

ከአዳም እስከ ሙሴ (ዘመነ አበው) ምሳሌያት ይበዛሉ:: ከሙሴ እስከ ዳዊት (ዘመነ መሣፍንት) ምሳሌያቱ እየጐሉ መጥተዋል:: ከልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት እስከ ቅዱስ ሚልክያስ ድረስ (በዘመነ ነቢያት / ነገሥት) ግን ትንቢቶች ስለ
ክርስቶስና ስለ ማደሪያ እናቱ እንደ ጐርፍ ፈሰዋል::

ነቢያትም የመሲህን መምጣት እየጠበቁ በጾም:
በጸሎትና በትሕርምት ኑረዋል:: እንባቸውንም አፍሰው ቅድመ እግዚአብሔር ደርሶላቸዋል:: መድኅን ክርስቶስም ተወልዶ አድኗቸዋል::

'አማኑኤል' የሚለው ቃል ከእብራይስጥ ልሳን (ከጽርዕ የሚሉም አሉ) በቀጥታ የተወረሰ ሲሆን ትርጉሙም "እግዚአብሔር ምስሌነ-እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ሆነ" እንደ ማለት ነው:: (ኢሳ. 7:14, ማቴ. 1:22) ምሥጢሩ ግን ከዚህ የሠፋ ነው::

'አማኑኤል' ማለት "እግዚአብሔር ከሥጋችን ሥጋን: ከነፍሳችን ነፍስን ነስቶ በፍጹም ተዋሕዶ እኛን መሰለን" ማለት ነው:: በሌላ አነጋገርም "አምላክ ሰው ሆነ: ሰውም አምላክ ሆነ" እንደ ማለት ነው::

ይሕንን ሲያደንቁ ቅዱሳን ሊቃውንት "ወዝንቱ ስም
ዓቢይ: ወኢይደሉ ፈሊጦቶ-ይህ ስም ታላቅ ነው:: ወደ ሁለት ሊከፍሉት (ሊለዩት) አይገባም" ብለው ምሥጢረ ተዋሕዶን አስረድተዋል:: (ሃይ.አበ. ዘሳዊሮስ)

ስለዚህም ከሦስቱ አካላት አንዱ ወልድ እኛን ያድን
ዘንድ በተለየ አካሉና በከዊነ ቃልነቱ ፍጹም የድንግል ማርያምን ሥጋ ተዋሕዶ የሰውነትንም: የአምላክነቱንም ሥራ ሠርቶ አድኖናል::

በማሕጸነ ድንግል ከተቀረጸባት ደቂቃ ጀምሮም ፍጹም ተዋሕዶን ፈጽሟልና መቼም መች አምላክም: ሰውም ነው እንጂ ወደ ሁለትነት: ማለትም አምላክን ለብቻ: ሰውን ለብቻ
አናደርግም::

ስለዚህም ዛሬም: ዘወትርም እግዚአብሔር ቃል
የተዋሐደው ሥጋችን በዘባነ ኪሩብ ሲሠለስና ሲቀደስ ይኖራል:: እርሱ ጌታችን እስከዚህ ድረስ ወዶናልና::

ፈጣሪያች በሦስትነቱ:- ሥላሴ (አብ: ወልድ: መንፈስ ቅዱስ): በአንድነቱ:- እግዚአብሔር: ኤልሻዳይ: አልፋ: ወዖ: ቤጣ: የውጣ: ኦሜጋ . . . እያልን እንደምንጠራው ሁሉ በሥጋዌው ምክንያት:- አማኑኤል: መድኃኔ ዓለም: ኢየሱስ:
ክርስቶስ እያልን እንጠራዋለን::

የድንግል ማርያም ልጅ አማኑኤል ክርስቶስ በርሕራሔው ይማረን:: ከበረከተ ልደቱም ያሳትፈን::

ታሕሳስ 28 ቀን የሚከበሩ
     ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.አማኑኤል አምላካችን
2.በዓለ ጌና ስቡሕ
3.ዕለተ ማርያም ድንግል
4."174" ሰማዕታት (የቅዱስ ዻውሎስ ማሕበር)

++"+ የዳዊት ልጅ ዮሴፍ ሆይ! ከእርስዋ የተጸነሰው ከመንፈስ ቅዱስ ነውና እጮኛህን ማርያምን ለመውሰድ አትፍራ:: ልጅም ትወልዳለች:: እርሱ ሕዝቡን ከኃጢአታቸው
ያድናቸዋልና ስሙን ኢየሱስ ትለዋለህ:: በነቢይ ከጌታ ዘንድ:- 'እነሆ ድንግል ትጸንሳለች:: ልጅም ትወልዳለች:: ስሙንም አማኑኤል ይሉታል::' የተባለው ይፈጸም ዘንድ ይህ ሁሉ ሆኗል:: ትርጉዋሜውም እግዚአብሔር ከእኛ ጋር የሚል ነው:: " (ማቴ. 1:20)

🌹<  ወስብሐት ለእግዚአብሔር  >🌹
               🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

04 Jan, 14:52


🌹 ስንክሳር ታህሳስ 27 🌹

✞ እንኩዋን ለቅዱሱ አባ አብሳዲ ለጻድቁ "አባ በግዑ" ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ::✞

+"+ ቅዱስ አባ አብሳዲ +"+

=>ቅዱሱን የመሰሉ አባቶች "መስተጋድላን" ይባላሉ በግዕዙ:: ለሃይማኖታቸው እስከ ደም ጠብታና እስከ መጨረሻዋ ህቅታ ድረስ መጋደላቸውን የሚያሳይ ነው:: መጋደል ጐዳናው ብዙ ዓይነት ነው::

+ከራሱ ጋር የሚጋደል አለ:: ከዓለም ጋር የሚጋደልም አለ:: የቅዱሳኑ ተጋድሎ ግን በዋነኝነት ከ2 አካላት ጋር ነው:: በመጀመሪያ ፍትወታት እኩያትን (ኃጣውዕን) ከሚያመጡ አጋንንት ጋር ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ "ሃይማኖቸታችሁን ካዱ: ለጣዖትም ስገዱ" ከሚሉ ከሃድያን ጋር የሚደረግ ትግል ነው::

+በተለይ 2ኛው እስከ ሞት የሚያደርስ ውሳኔን ይጠይቃል:: የዚህን ቅዱስ ሕይወት ለመረዳት ግን አንድ ነገርን ልብ እንድትሉልኝ እፈልጋለሁ::

+ያለንበት ዘመን ክርስትና በራድ (ቀዝቃዛ) በመሆኑ የቀደሙ አባቶች የጸና ተጋድሎ አንዳንዴ ግራ ሲያጋባን ተመልክቻለሁ:: ቅዱሳኑ ሁሌም አንድ ነገርን እያሰቡ ይኖራሉ:: ይኼውም በዘመኑ በርካቶቻችን የረሳነው: ወይም ማስታወስ የማንፈልገው ነገር ይመስላል::

+ሰማያዊው አምላክ ከዙፋኑ ወርዶ በተዋሐደው ሥጋ በቃል ሊገለጽ የማይችል መከራን ስለ እኛ ተቀብሏል:: ክርስትና ማለት ቀራንዮን በልብ ውስጥ መሳል ነው:: ፍቅረ መስቀሉን: የጌታንም ውለታ የሚያስብ ማንኛውም ሰው: የትኛውም ዓይነት መከራ ቢመጣበት አይታወክም::

+ቅዱሳኑም የፍቅራቸውና የትእግስታቸው ምሥጢር ይኼው ነው:: ጌታችን "የሚወደኝ ቢኖር የሞቱን መስቀል ተሸክሞ ይከተለኝ" (ማቴ. 16:18) እንዳለው ቅዱሳኑ ይህንን ቃል በቃል ሲፈጽሙት እነሆ እንመለከታለን::

🌿" አባ በግዑ ጻድቅ "🌿

እኒህ አባት በመካከለኛው ዘመን የሃገራችን ታሪክ ሰፊ ቦታን ይዘው ይገኛሉ:: ተጋድሏቸውን የፈጸሙት በደብረ ሐይቅ ነው:: ጻድቁ ብዙ ጊዜ የሁዋለኛው ዘመን ሙሴ ጸሊም ይባላሉ:: ብዙ የሕወታቸው ጐዳና ተመሳሳይ ነው::

ልክ ቅዱስ ሙሴ ጸሊም ከኃጢአት ከሽፍትነት ሕይወት እንደ መጣው ሁሉ አባ በግዑም አስቸጋሪ ሰው እንደ ነበሩ ይነገርላቸዋል:: ከዚያ የከፋ የኃጢአት ኑሮ እግዚአብሔር ሲጠራቸው ግን ክሳደ ልቡናቸውን አላደነደኑም:: "እሺ" ብለው ንስሃ ገቡ እንጂ::

ከዚያም በደብረ ሐይቅ (ወሎ) በፍጹም ተጋድሎ ኑረዋል:: ያዩ ሁሉም ፍጹም ያደንቁ ነበር:: ስትበላ: ስትጠጣ የኖረችውን ሰውነት ራሳቸውን ውሃ ለዘመናት በመከልከል ቀጥተዋታል:: ስለዚህም "ውሃ የማይጠጣው አባት" ይባሉም ነበር:: ጻድቁ ሲያርፉ ፈጣሪያቸው አክብሯቸዋል::

አምላከ አበው ቅዱሳን አሠረ ፍኖታቸውን ይግለጽልን:: ከበረከታቸውም ያድለን::

ታሕሳስ 27 ቀን የሚከበሩ
       ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ አብሳዲ ሰማዕት
2.አባ አላኒቆስ ሰማዕት
3.አባ በግዑ ጻድቅ
4.አባ ፊልዾስ

         ወርኀዊ በዓላት
1.ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ
2.አቡነ መብዓ ጽዮን ጻድቅ
3.ቅዱስ መቃርስ (የመነኮሳት ሁሉ አለቃ)
4.ቅዱስ ያዕቆብ ዘግሙድ
5.ቅዱስ ገላውዴዎስ ሰማዕት (ንጉሠ ኢትዮዽያ)
6.ቅዱስ ቢፋሞን ጻድቅና ሰማዕት
7.ማር ቅዱስ ፊቅጦር ሰማዕት

🌹<  ወስብሐት ለእግዚአብሔር  >🌹
               🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

03 Jan, 15:23


  ስንክሳር ታህሣስ 26 
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞

🌿" ቅድስት አንስጣስያ "🌿

እስኪ ዛሬ በጥቂቱ የተባረኩ (ቡሩካት) እናቶቻችን
እንዘክር:: "ቅድስት" የሚለው ቃል ለሁሉም ቅዱሳት እናቶች ቢሰጥም ቅሉ ለድንግል ማርያም ሲሰጥ ግን ትርጉሙ ይለያል:: እርሷ 'ቅድስተ ቅዱሳን: ንጽሕተ ንጹሐን: ቡርክት እምቡሩካን: ኅሪት እምኅሩያን ናትና::

ከሰው ልጆችም ሁሉ ትበልጣለች:: ይቅርና የሰው ልጅን ንጹሐን መላእክትንም በንጽሕናና በቅድስና
ትበልጣቸዋለች:: እርሷ እመ ብርሃን: የአምላክ እናቱ: የሰውነታችን መመኪያ ናትና::

እመቤታችንን "ቅድስት" ስንል "ጽንዕት: ንጽሕት: ክብርት: ልዩ" ማለታችን ነው::
1."ንጽሕት" ትባላለች:: ሌሎች ሰዎች (ቅዱሳን) ቢነጹ ከገቢር: ከነቢብ ኃጢአት ነው እንጂ ከኃልዮ ኃጢአት አይደለም:: እርሷ ግን ከነቢብ: ከገቢር: ከኃልዮ ንጽሕት ናት::

"ለመኑ ተውኅቦ ተደንግሎ ኅሊና: ለመላእክትሂ
ኢተክህሎሙ-ኃጢአትን ከማሰብ መጠበቅ ከሰው ልጆች ለማን ተሰጠው: ይህስ ለመላእክትም አልተቻላቸውም" እንዲል:: (ተአምረ ማርያም)

2."ጽንዕት" እንላታለን:: ሴቶች ቢጸኑ ለጊዜው ነው እንጂ በኋላ በጊዜው ተፈትሆ አለባቸው:: እመቤታችን ግን ቅድመ ጸኒስ: ጊዜ ጸኒስ: ድኅረ ጸኒስ: ቅድመ ወሊድ: ጊዜ ወሊድ: ድኅረ ወሊድ ድንግል ናትና:: "ጽንዕት በድንግልና አልባቲ ሙስና" እንዳላት:: (ቅዱስ ያሬድ) ታላቁ ቅዱስ ባስልዮስም "ወትረ ድንግል ማርያም- ማርያም ዘለዓለማዊት ድንግል ናት" እንዳለ:: (መጽሐፈ ቅዳሴ)

3.ድንግልን "ክብርት" እንላታለን:: ሌሎች ሴቶች ቢከብሩ ጻድቃን ሰማዕታትን: ነቢያት ሐዋርያትን ወልደው ነው:: እመቤታችንን ግን የምናከብራት "ወላዲተ አምላክ- የአምላክ እናቱ" ብለን ነውና::

4.እመቤታችንን "ልዩ" እንላታለን:: ከእርሷ በቀር እናት ሁና ድንግል: እመቤት ሁና አገልጋይ የሆነች: በድንግልና ወልዳ ወተትን (ሐሊበ ድንግልናዌን) ያስገኘች ሌላ ሴት የለችምና::

የእመ ብርሃን ይቆየንና ደግሞ ሌሎች ቅዱሳት
እናቶቻችንን እንመልከት:: እናቶቻችን ስናከብር
የምንጀምረው በቅድስት ሔዋን ነው:: ብዙ ጊዜ የእናታችን ሔዋን ጥፋቷ እንጂ በጐ ነገሯ: ደግነቷ: ንስሃዋ አይነገርላትም:: ሆኖም እናታችን ቅድስት ሔዋን ክብር የሚገባት ሴት ናት::

*ክርስቶስ ሰው የሆነ እርሷንና ልጆቿን ለመቀደስ ነውና:: "ከመ ይስዓር መርገማ ለሔዋን ዲበ ዕፅ ተሰቅለ" እንዲል:: (ድጉዋ)

ቀጥሎ በብሉይ ኪዳን እነ ሐይከል: እድና: ሣራ: ርብቃ: አስኔት: ሲፓራ: ሐና: ቤርሳቤህን የመሰሉ እናቶቻችን በበጐው መንገድ ፈጣሪን ደስ አሰኝተዋል:: በዘመነ ሥጋዌም
ቅዱሳቱ ሐና: ኤልሳቤጥ: ማርያም: ሶፍያ: ሰሎሜ: ዮሐና እና 36ቱ ቅዱሳት አንስት በጐነታቸው ያበራል::

ከዚያ ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ ለ2,000 ዓመታት የተነሱ አእላፍ ቅዱሳት እናቶቻችንን ግን ዘርዝረን አንዘልቃቸውም:: በቅድስናቸው አራዊትን ያሰገዱ: ነገሥታትን ያንቀጠቀጡ: አጋንንቸትን የረገጡ: በዘንዶ ላይ የተጫሙ ብዙ እናቶችን ቤተ ክርስቲያን አፍርታለች::

ዛሬም ቢሆን በበርሃና በከተማ በጐውን ጐዳና የተከተሉ ብዙ እናቶች እንዳሉን እናውቃለን:: አንድም እናምናለን:: ግን ግን በከተሞች የምንመለከተው ሥርዓቱን የለቀቀው
የበርካታ እህቶቻችን አካሔድ ለሃገርም ለቤተ
ክርስቲያንም ትልቅ ስጋት ነው:: ክብርና ነውር የማይለይበት ዘመን ይመስላል::

ይህንን እያነበባችሁ ያላችሁ እህቶቼ! አንድ ነገር
ልንገራችሁ:: በመልካቸው ብዙዎችን ያጋጩ: አጊጠው በመታየታቸው ብዙዎችን ያሰናከሉ: ለብዙ ምዕመናንም የጥፋት ምክንያት የሆኑ ብዙ ሴቶች በታሪክ ነበሩ::

የሚያሳዝነው ግን ዛሬ ያሉት ከመሬት በታች ነው:: አፈር በልቷቸዋል:: ስም አጠራራቸውም ጠፍቷል:: በጣም የሚያሳዝነው ደግሞ ዛሬ በዘለዓለማዊው እሳት እየተቃጠሉ በሲኦል: በጥልቁ ውስጥ አሉ::

እናም ወገኖቼ! ይህን አውቀን እንንቃ:: ይህ ዓለም
ጠፊም: አጥፊም ነውና:: እድሜአችን ቢረዝምና ከዚህ በኋላ ለ100 ዓመታት ብንኖርም እርሱም ማለቁ አይቀርምና:: ምርጫችን ዘለዓለማዊው ሕይወት ይሁን ትላለች ቅድስት ቤተ ክርስቲያን::

" ቅድስት አንስጣስያ "

ይህች ቅድስት እንደ በርካቶቹ ቅዱሳት እናቶቻችን ሁሉ የዘመነ ሰማዕታት ፍሬ ናት:: በቀደመችው ታናሽ እስያ አካባቢ ተወልዳ: የነገሥታት ዘር በመሆኗ ያደገችው በቤተ መንግሥት ነው:: አባቷ ከክቡራኑ አንዱ ቢሆንም ሙያው
ጣዖትን ማምለክ ነበር::

ጊዜው የመከራ በመሆኑ ብዙ ሴቶች የሚኖሩት
ክርስትናቸውን ደብቀው ነው:: ከእነዚህ መካከል አንዷ. ደግሞ የቅድስት አንስጣስያ እናት ናት:: ማንን እንደምታመልክ አረሚ ባሏ አያውቅም ነበር::

አንስጣስያን በወለደች ጊዜም በድብቅ አስጠመቀቻት:: ከሕጻንነቷ ጀምሮም ፍቅረ ክርስትና እንዲያድርባት ነገረ ሃይማኖትን
አስተማረቻት:: ቅድስት አንስጣስያ ወጣት በሆነች ጊዜ ግን ከውበቷ የተነሳ ተመልካቿ በዛ:: እርሷ ግን ይህ ሁሉ የዓለም ኮተት አይገባትም ነበር::

በፈጣሪዋ ፍቅር ከመጠመዷ የተነሳ ለመሰል ነገሮች ትኩረት አልነበራትም:: ትጾማለች: ትጸልያለች: ነዳያንና እሥረኞችን
ትጐበኛለች:: በዚህም ዘወትር ደስ ይላት ነበር:: ነገር ግን አባቷ ባላሰበችው ጊዜ ለአንድ አረማዊ አጋባት:: በጣም አዘነች: ግን ተስፋ አልቆረጠችምና መፍትሔ ፈለገች::

ድንግልናዋን እንዳያረክስ በጫጉላዋ ቀን ታመምኩ ብላ ተኛች:: ከዚያ በኋላም አንዴ በልማደ አንስት: አንዴ በሕመም እያመካኘች አላስቀርብ አለችው:: እርሱ የጦር አለቃ በመሆኑ ወደ ጦርነት ሲሔድ እርሷ ታጥቃ ስለ ቀናች እምነት የታሠሩ
ክርስቲያኖችን ታገለግል ነበር::

ቁስላቸውን እያጠበች: አንጀታቸውን በምግብ እየደገፈች ደስ ታሰኛቸውም ነበር:: ባሏ ሲመለስ ግን ይህንን በመስማቱ ድጋሚ እንዳትወጣ ቆልፎባት ወደ ጦርነት ተመለሰ:: ፈጽማ ስላዘነችበትም እግዚአብሔር በጠላቶቹ እጅ
አሳልፎ ሰጠውና ሞተ::

እርሷም ከነ ድንግልናዋ ቀሪ ሕይወቷን ስትመራ
መከራው ወደ እርሷ ደረሰ:: ተይዛ ቀርባ በአረማውያን እጅ ብዙ ተሰቃየች:: በዚህች ቀንም ስለ ክርስቶስ ተገድላ ክብረ ሰማዕታትን ተቀዳጀች::

" ቅዱስ አቦሊ ጻድቅ "

ቅዱሱ በቤተ ክርስቲያን ታሪክ የክርስቶስን ሕማማት ለመሳተፍ ሲተጉ ከኖሩ ጻድቃን አንዱ ነው:: መሉ ጊዜውን በበርሃ ሲያሳልፍ ብዙ ተጋድሎን ፈጽሟል:: በተለይ ሲጸልይ
እግሩን ከዛፍ ላይ አስሮ: ቁልቁል ከባሕር ውስጥ ሰጥሞ ነው:: ዛሬ ቤተ ክርስቲያን ዕረፍቱን ታስባለች::

አምላከ ቅዱሳን ጸጋውን: ክብሩን ያድለን:: ከወዳጆቹ በረከትም አይለየን::
ታሕሳስ 26 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅድስት አንስጣስያ ሰማዕት
2.ቅዱስ አቦሊ ጻድቅ
3.ቅድሰት ዮልያና ሰማዕት

🌹<  ወስብሐት ለእግዚአብሔር  >🌹
               🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

03 Jan, 04:16


ስንክሳር ታህሳስ 25
✞እንኩዋን ለ5ቱ "ቅዱሳን መቃብያን" እና "ቅዱስ ዮሐንስ ከማ" ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ::✞

🙏" 5ቱ መቃብያን "🙏

=>እግዚአብሔር ሰማይንና ምድርን: 22ቱን ሥነ ፍጥረትን ፈጥሮ አዳምን ገዢ አደረገው:: አክሎም በነፍስ ሕያው አድርጐ: በመንፈስ ቅዱስ አክብሮ: ነቢይና ካህን አድርጐ: ካንዲት ዕፀ በለስ በቀር በፍጥረት ሁሉ ላይ አሰለጠነው::

አባታችን አዳም ግን ስሕተት አግኝቶት ከገነት ወጣ:: መከራና ፍዳም አገኘው:: በሁዋላም ለ100 ዓመት አልቅሶ ንስሃ ገባ:: ጌታም ንስሃውን ተቀብሎ "ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለሁ" የሚል ተስፋ ድህነትን ሰጠው::

ስለዚህም ምክንያት ለ5,500 ዓመታት ትንቢት ሲነገር: ሱባኤ ወደ ታች ሲቆጠር: ምሳሌም ሲመሰል ኖረ:: ከደግ ፍጥረት አዳም እስከ ኖኅ ድረስ: የሴት ልጆች እግዚአብሔርን በንጽሕና ሁነው በደብር ቅዱስ አመለኩ::

ትንሽ ቆይተው ግን ስለተቀላቀሉ ከቃየን ልጆች ጋር በማየ ድምሳሴ ጠፉ:: በጻድቅ ሰው ኖኅ የተጀመረው ትውልድም እግዚአብሔርን ለመዘንጋት ጊዜ አልፈጀበትም:: ነገር ግን ከሴም ዘር ቅንና ጻድቅ ሰው አብርሃም ተገኘ::

ከእርሱም ይስሐቅ: ከዚያም ያዕቆብ ደጋጉ ተገኙ:: ያዕቆብም "እሥራኤል" ተብሎ በልጆቹ "ሕዝበ እግዚአብሔር" የተባለ ነገድ ተመሠረተ:: በተስፋይቱ ምድር በከነዓን እንዳይኖሩም ረሃብ ምድረ ግብጽ አወረዳቸው::

በዚያም ለ215 ዓመታት በጭንቅ የባርነትን ሕይወትን አሳለፉ:: እግዚአብሔርም ስለ ወዳጁ አብርሃም ሲል እሥራኤልን አሰባቸው:: የዋሕና ጻድቅ ሰው ሙሴን አስነስቶ እሥራኤልን ከግብጽ ባርነት አዳናቸው::

ይኸውም በጸናች እጅ: በበረታችም ክንድ: በ9 መቅሰፍት: በ10ኛ ሞተ በኩር: በ11ኛ ስጥመት ግብጻውያንን አጥፍቶ ነው:: በየመንገዱም ጠላቶቻቸውን እየተበቀለላቸው ነው:: ከዚህ ዘመን ጀምሮም እሥራኤል በመሳፍንትና በካህናት የሚተዳደሩ ሆኑ::

አስቀድሞ ሙሴ በምስፍና: አሮን በክህነት መሯቸው:: ቀጥሎም በቅዱስ ሙሴ ኢያሱ: በአሮን አልዓዛር ተተኩ::

ከዚህ በሁዋላ ለ300 ዓመታት ያህል መሣፍንት እየተቀያየሩ አስተዳደሩዋቸው:: ሲበድሉ ጠላት እየገዛቸው: ሲጸጸቱ በጐ መሥፍን እየመጣላቸው ከነቢዩ ሳሙኤል ደረሱ::

በዚህ ጊዜም ሕዝቡ እንደ አሕዛብ ሥርዓት ንጉሥ በመፈለጋቸው ክፉው ሳዖል ለ40 ዓመት ገዛቸው:: ቀጥሎ ግን እንደ አምላክ ልብ የሆነ ቅዱስ ሰው ዳዊት ነግሦላቸው እሥራኤል ከፍ ከፍ አሉ:: ከቅዱስ ዳዊት እስከ ሮብዓም ቆይተው ግን እሥራኤል ከ2 ተከፈሉ::

10ሩ ነገድ በሰማርያ ሲኖሩ ግፍን ስላበዙ ስልምናሶር ማርኮ አሦር አወረዳቸው:: ባሮችም አደረጋቸው:: 2ቱ ነገድ ደግሞ ከብረው: ገነው በኢየሩሳሌም ቢኖሩም እነርሱም አመጸኞች ነበሩና ናቡከደነጾር ወስዶ የባቢሎን ባሪያ አደረጋቸው::

እግዚአብሔር ግን እንደ ነቢያቱ ቃል 70ው ዘመን ሲፈጸም በኃይል ወደ ርስታቸው መለሳቸው:: በዚያም ዘሩባቤል የሚባል ደግ ንጉሥ ነግሦላቸው: ቤተ መቅደስ ታንጾላቸው ኖሩ:: ክፋታቸው ግን ማብቂያ አልነበረውምና ከዘሩባቤል በሁዋላ ቅን ንጉሥን ማግኘት አልቻሉም::

እግዚአብሔር ግን ምሕረቱንና መግቦቱን አይተውምና አልዓዛርን የመሰሉ ደጋግ ካህናትን እያስነሳ ሰው እስከሚሆንባት ቀን ድረስ አቆይቷቸዋል:: በዚህም ምክንያት ይህ ዘመን "ዘመነ ካህናት" ተብሏል::

በዚህ በዘመነ ካህናት ውስጥ ደግሞ በጐነታቸው የታወቀላቸው: ግን ደግሞ መከራው የበዛባቸው እሥራኤላውያን ነበሩ:: ብዙ ጊዜ የሚጠሩት "መቃብያን" በሚል ስም ነው::

በያዕቆብ እሥራኤል: በዔቦር ዕብራውያን: በይሁዳ አይሁድ: በፋሬስ ፈሪሳውያን: በሳዶቅ ሰዱቃውያን እንደተባሉት ሁሉ እነዚህም በአባታቸው በመቃቢስ ምክንያት መቃብያን ተብለዋል:: ታሪካቸው ሰፊና በመጽሐፈ መቃብያን የተጻፈ ሲሆን እኛ ግን በአጭሩ አንዷን የታሪክ ዘለላ ብቻ እንመለከታለን::

በዘመኑ መቃቢስ የሚባል ደግ ሰው 5 (3) ወንዶች ልጆችን (መቃብያንን) ወልዶ ነበር:: እነዚህም በመልክ ይህ ቀራችሁ የማይባሉ: በጠባይ እጅግ የተመሰገኑ: በኃይላቸው ጽናትም የተፈሩ ነበሩ::

በተለይ 3ቱ ከግሩማን አራዊት አንበሳና ድብ ታግለው ያሸነፉ: በጦርነትም ጠላትን ያንበረከኩ ነበሩ:: ታዲያ ይህ ሁሉ የተሰጣቸው ከእግዚአብሔር እንደ ሆነ ያውቁ ነበርና ፈጣሪያቸውን በንጹሕ ልብ ያመልኩት ነበር::

በዘመኑ ደግሞ ሞዐባውያንና ሜዶናውያን አካባቢውን ያስገብሩ ነበር:: በተለይ የሞዐቡ ንጉሥ ጺሩጻይዳን ከክፋቱ ብዛት 70 ጣዖታት በወንድና በሴት ምሳሌ አስቀርጾ ያመልክ ነበር:: ከዚያም አልፎ ሕዝቡን "አምልኩ" እያለ ያውክ: ይቀጣ: ይገድልም ነበር::

ቅዱሳን መቃብያን ይህንን ሲሰሙ ወደ እርሱ ገሰገሱ:: ምንም እንኩዋ ሊያጠፉት ኃይል ቢኖራቸውም አላደረጉትም:: ይልቁኑ ቀርበው ዘለፉት እንጂ::

እርሱም "ጣዖትን አናመልክም" ስላሉ ለአንበሳ ጣላቸው:: አንበሶቹም ለቅዱሳኑ ሰግደው የንጉሡን ወታደሮች ፈጇቸው:: እርሱም 3ቱን ወደ እሥር ቤት ጣላቸው:: በዚህ ጊዜ 2ቱ ወንድሞቻቸው መጥተው ተቀላቀሉ::

ቀጥሎም 5ቱንም አስወጥቶ በሰይፍ አስመታቸው:: ከተገደሉ በሁዋላም ወደ ውሃ ጥሏቸው: በእሳት አቃጥሏቸው ነበር:: ባይሳካለት ስለ ተቆጣ ሳይቀበሩ እንዲጣሉ አዘዘ:: ከ14 ቀናት በሁዋላም የቅዱሳኑ አካል እንደ መብረቅ እያብለጨለጨ ተገኝቶ በክብር እንዲቀበር ሆኗል::

<< ቀሪው ታሪካቸው በመጽሐፈ መቃብያን የተጻፈ አይደለምን !! >>
አምላከ ቅዱሳን ይራዳን: ይባርከን: ይቀድሰን:: ከወዳጆቹ በረከትም ያሳትፈን::

ታሕሳስ 25 ቀን የሚከበሩ
       ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱሳን 5ቱ መቃብያን
2.ቅዱስ ዮሐንስ ከማ (እና የተቀደሰች ሚስቱ)
3.ቅዱስ ዳንኤል መነኮስ
4.ቅዱስ ኒቆላዎስ መኮንን

=>ወርሐዊ በዓላት
1.ቅዱስ መርቆሬዎስ ሰማዕት
2.ቅድስት ቴክላ ሐዋርያዊት
3.ቅዱስ አበከረዙን ሰማዕት
4.ቅዱስ ዱማድዮስ ሶርያዊ
5.አቡነ አቢብ (አባ ቡላ)
6.ቅዱስ አባ አቡፋና ጻድቅ
7.ታላቁ አባ ቢጻርዮን ገዳማዊ

=>+"+ ቃሌን የሚጠብቅ: በትዕዛዜም ጸንቶ የሚኖር: በረከቴን የሚያገኝ: በእኔ ዘንድ የሚከብር እርሱ ነው::
ቃሌን የሚጠብቅ: በትዕዛዜም ጸንቶ የሚኖር ሰው ሁሉ ከምድር የተገኘውን ድልብ ይበላል:: ቅን ልቡና ያላቸው ደጋጎች ነገሥታት ወደ ገቡበት ወደ ገነትም ገብቶ ይኖራል:: +"+ (መቃ. 12:43)

🌹<  ወስብሐት ለእግዚአብሔር  >🌹
               🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

02 Jan, 19:14


https://www.youtube.com/watch?v=GOs-dn90mI4&t=10s

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

02 Jan, 17:20


አሐዱ፡ ባንክ 3ኛ ዓመት የምሥረታ ጉባዔ በዓሉን ምክንያት በማድረግ የባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድ ሰብሳቢ እና የቦርድ  አባላት÷ የማኔጅመንት አባላት እና ሠራተኞች በመቄዶንያ የአረጋውያን እና የአእምሮ ሕሙማን የበጎ አድራጎት ማኅበር በቦታው በመገኘት ነዳያንን የመጎብኘት እና የምሳ ምገባ መርሐ ግብር  ተከናውኗል።በዕለቱም የባንካችን ተጠባባቂ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሲሳይ ገብሩ አሐዱ:ባንክ ካለው ላይ ቀንሶ በመስጠት ማኅበራዊ ኃላፊነቱን እየተወጣ ይገኛል÷አጠናክሮም ይቀጥላል በማለት በአጽንኦት ተናግረዋል::
የማኅበሩ መሥራች ክቡር ዶ/ር ብንያም በለጠም በበኩላቸው   መቄዶንያ ክቡሩን የሰው ልጅ አገልግለን ከፈጣሪ ክብር የምናገኝበት የበረከት ስፍራ ነው ሲሉ ተደምጠዋል::

በዕለቱም በሰብአዊነት ዕሴቱ  የሰው ሕይወትን  ለመታደግ በዋናው መሥሪያ ቤት የደም ልገሳ መርሐ ግብር በማከናወን  በበጎ ተግባር በደመቀ ሁኔታ ተከብሯል፡፡

በተያያዘም ከ 100 በላይ በደረሱ የባንካችን ቅርንጫፎች በተለያዩ የበጎ አድራጎት ተግባራት ተከብሮ  ውሏል::
አሐዱ፡ ባንክ
ከብዙዎች ለብዙዎች!

#_ምዕራፍ ፪ _“ከአሐዱ ጋር ነኝ"
የአሐዱ፡ባንክ ማኅበራዊ ትስስር ገጾችን ይቀላቀሉ

👉https://linktr.ee/Ahadu_Bank

🌹<  ወስብሐት ለእግዚአብሔር  >🌹
               🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

02 Jan, 08:49


https://youtu.be/JpzprQk_q-g?si=e7IlVRtmeI20yHUQ

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

01 Jan, 19:36


https://www.youtube.com/watch?v=1iLN824i92o&t=21s

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

01 Jan, 15:18


ማኅበረ ቅዱሳን በ400 ሚሊዮን ብር ወጪ ባለ 12 ወለል ሕንጻ ሊያስገነባ ነው

#Maleda : ማኅበረ ቅዱሳን በ400 ሚሊዮን ብር ወጪ ዘመኑን ያገናዘበ ሥራ ለመስራት ሁለንተናዊ የሕፃናት እና የወጣቶች የስብዕና ግንባታ ፕሮጀክት የሚያከናውንበት ባለ 12 ወለል ሕንጻ ማዕከል ሊያስገነባ እንደሆነ አስታወቋል ፡፡

"ኑ ዛሬ ትውልድ ላይ እንሥራ ሀገር እና ቤተ ክርስቲያንን እናድን " የሚለው ፕሮጀክቱ የነገን የሀገር እና የቤተ ክርስቲያንን ተስፋ እንደሚያለመልም ይጠበቃል ።

ማህበሩ "ሁሉም ምዕመን የፕሮጀክቱን ዓላማ በመረዳት ባለ 12 ወለል ሕንጻውን የማዕከል ግንባታ እንዲፋጠን የበኩሉን አስተዋፅኦ እንዲያደርግ" ሲል ጥሪውን አቅርቧል ።

የማዕከሉን የፕሮጀክት ሕንፃ በአጭር ጊዜ ገንብቶ ማጠናቀቅ እና ለአገልግሎት ዝግጁ በማድረግ ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን የሚጠብቅ ፤በዕውቀት የበለጸገ በሥነ ምግባር የታነፀ ብቁ ዜጋ በማፍራት፣ ለቤተ ክርስቲያን እና ሀገር ተተኪ ትውልድ የሚያፈራ ተቋም ማዘጋጀት ዋነኛ ዓላማው እንደሆነ ተጠቁሟል ።

በመንፈሳዊ እና በዓለማዊ ጥበብ የታነፀ ፤ የነገ ሀገር እና ቤተ ክርስቲያን ተረካቢ ትውልድ ማፍራት የፕሮጀክቱ አላማ ነው እንደሆነም ተገልጿል ። በዚህ ማዕከል የሕፃናት እና የወጣቶች የሰብዕና፣ የክህሎትና ሙያዊ ሥልጠና የሚሰጥበት ጭምር ነው ብለዋል።

በተጨማሪም የኦርቶዶክሳዊ ቤተሰብ ሥልጠና የሚሰጥበት ከመሆኑም በተጨማሪ ሁለንተናዊ የስነ ልቦና አገልግሎት የሚሰጥበት እንደሆነም ተነግሯል ። ለዚህ ዓላማ ማህበሩ የሚያስገነባው ሕንጻ ባለ 12 ወለል ህንጻ ሲሆን የአብነት ትምህርት ቤት፣ የሥነ ምግባር ትምህርት ቤት፤ የአቅም ግንባታ አገልግሎት ሥልጠና የሚሰጡ ይሆናል ነው የተባለው ።
የፕሮጀክቱን ማስተዋዎቅ ያስተባበረው ሎዛ ኦርቶዶክሳዊ ኹነቶች አዘጋጅ እንደገለጸው ፤ ለማዕከሉ ግንባታ የተለያዩ የገቢ ማሰባስቢያዎች በመካሄድ ላይ እንደሆነ የተገለጸ ሲሆን ፤ ከነዚህም ውስጥ እንዱ በመቶ ብር የሚሽጥ የበረከት እጣ ነው። ወደ ቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌም ደርሶ መልስ ጉብኝት የግብጽ ገዳማት ጉብኝት የወርቅ መስትልን ጨምሮ በርካታ ሽልማቶች በእጣው ተካቷል፡፡

ምዕመኑም አጣውን በመግዛት ፕሮጀክቱን እንዲደግፍ ጥሪ ቀርቧል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ በአሐዱ በረከት እና በተዘጋጁ የባንክ አካውንቶች ድጋፍ ማድረግ ይቻላል ተብሏል ፡፡
በማኅበረ ቅዱሳን የአዲስ አበባ ማእከል ሁለንተናዊ የሕፃናት እና ወጣቶች የስብእና መገንቢያ ፕሮጀክት ድጋፍ ማድረጊያ የባንክ አካውንት ቁጥሮች

1. አሐዱ ባንክ 470002505310101
2 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ1000303949112
३. ሕብረት ባንክ 4131111274007010
4. አቢሲኒያ ባንክ 68960665
5. ዳሽን ባንክ 0088211311011
6. አዋሽ ባንክ 01304868950900
7. ንብ ባንክ 7000020208177
8. ቡና ባንክ 1099528000065
9. ዓባይ ባንክ 1891119601313011
FCY ha
1. 0003488710601 Mahibere Kidusan Addis Ababa Center Children and Youth Training Project FCY/ Dollar Account Ahadu Bank Swift Code: AHUUETAA
2. 1171161364012 Dashen Bank sost kutir Mazoria Branch Swift code DASHETAA

@ማለዳ ሚዲያ እንደዘገበው

🌹<  ወስብሐት ለእግዚአብሔር  >🌹
               🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

01 Jan, 14:54


፠  + + + ሥርዓተ ማኅሌት ዘታኅሣሥ ተክለሃይማኖት + + +  ፠

እንኳን ለጻድቁ አባታችን ለአቡነ ተክለሃይማኖት ዓመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! የሌሊቱን ሥርዓተ ማኅሌት ከሊቃውንቱ ጋራ ለማመስገን ይረዳን ዘንድ እንደሚከተለው ተዘጋጅቷል።

፩. ነግሥ / መልክአ ሥላሴ /

ሰላም ለንዋየ ውስጥ ምሕረትክሙ፤
ትሩፋተ ገድል ኩኑኒ ሥላሴ አምጣነ ትሩፋት አንትሙ፤
ሶበ ሖርኩሰ ከመ እሳተፍ ገድሎሙ፤
ጊዮርጊስ ኢወሀበኒ መጠነ ነጥበ ጠል እምደሙ፤
ወተክለ ሃይማኖት ከልአኒ ስባረ እምዐፅሙ።

ዚቅ፦

ሃሌ ሉያ ለአብ ሃሌ ሉያ ለወልድ ሃሌ ሃሌ ሉያ ወለመንፈስ ቅዱስ ፨ አክሊለ ሰማዕት ሠያሜ ካህናት፤ ወረደ እምሰማይ ዲበ ምድር፨ በመሥፈርተ ጥበቡ ለአቡሁ።

፪. ለሕጽንከ / መልክአ ሚካኤል /

ሰላም ለሕጽንከ እንተ በዲቤሁ ሕቁፍ ፤
ጸሎተ ቅዱሳን ዉኩፍ፤
ሚካኤል ክቡር መስፍነ ትጉሃን አእላፍ፤
ለረዲኦትየ ከመ ዘሠሰርር ዖፍ ፤
እንዘ ትሰሠርር ነዓ በክልኤ አክናፍ፡፡

ዚቅ፦

እስመ አሐዱ ውእቱ ሚካኤል ዘይረድኦሙ ፨ ለኵሎሙ ቅዱሳን፡፡

፫. ነግሥ / ዘመንክር ጣዕሙ /

ሰላም ለዝክረ ስምኪ ዘመንክር ጣዕሙ፤
ለወልድኪ አምሳለ ደሙ፤
መሠረተ ሕይወት ማርያም ወጥንተ መድኃኒት ዘእምቀዲሙ፤
ኪያኪ ሠናይተ ዘፈጠረ ለቤዛ ዓለሙ፤
እግዚአብሔር ይትባረክ ወይትአኮት ስሙ።

ዚቅ፦

ቅንዑ ለእንተ ተዓቢ ጸጋ ፨ መድኃኒት ለነፍስ ወሥጋ ፨
እስመ ርቱዓት ፍናዊሃ ጸድቃን የሐውርዎን ፨ ወኃጥአን ይስእንዎን ፨ ዘእንበለ ትብጻሕ ግብተ ፨ አሠንዩ ፍኖተ
ይፈኑ ለክሙ እመቅደሱ፨ረድኤተ መድኃኒተ መቤዛዊተ እሞ ቅድስተ፡፡

፬. ነግሥ / ለልደትከ /

ሰላም ለልደትከ ተክለ ሃይማኖት ሐዋርያ፤
ለሰብአ ግብጽ ወኢትዮጵያ፤
ሞገሰ ልደትከ አባ አዕይንቲሃ ርእያ፤
ነፍስየ ትባርኮሙ ወታስተበጽኦሙ ነያ፤
ለጸጋ ዘአብ ወለእግዚእ ኃረያ ፡፡

ዚቅ፦

ኮከብ ብሩህ ዘሠረቀ እምአቅሌስያ ቤተ ክርስቲያን ዘንሰምያ ፨ ኮኖሙ አበ ለሰብአ ግብፅ ወኢትዮጵያ ፨
አማን ተክለ ሃይማኖት ሐዋርያ፡፡

፭. ለፅንሰትከ / መልክአ ተክለ ሃይማኖት /

ሰላም ለፅንሰትከ ወለልደትከ እምከርሥ፤
አመ ዕሥራ ወረቡዑ ለወርኃ ታኅሣሥ፤
ተክለ ሃይማኖት በኵሉ ወበውስተ ኵሉ ውዱስ፤
ናሁ ወጠንኩ ወእቤ ለስብሐቲከ ሐዲስ፤
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ፡፡

ዚቅ፦

በእንተ ልደቱ ለተክለ ሃይማኖት አድባር ኮኑ ሕብስተ ሕይወት ፨ ወዕፀወ ገዳምኒ ፈረዩ አስካለ በረከት
ማየ ባሕርኒ ኮነት ሀሊበ ወመዓረ ፨ ወመላእክት ተጋቢዖሙ ሰፍሑ ክነፊሆሙ ፨ ወጸለሉ ላዕለ ተክለ ሃይማኖት፤ ወበህየ ገብሩ በዓለ፡፡

፮. ለልሳንከ / መልክአ ተክለ ሃይማኖት /

ሰላም ለልሳንከ በሠሉስ ዕለት ዘተውህባ፤
አኰቴተ ታቅርብ ለወልደ ማርያም ንጉሠ ሕዝባ፤
ተክለ ሃይማኖት ጸዋሚ ዮሐንስ ዘቤተ ራባ፤
ታሠምረከ ልሳንየ በአምጣነ ኵሉ ንባባ፤
ከመ አሥመሮሙ ያዕቆብ ለላባ፡፡

ዚቅ፦

ከሠተ አፉሁ ወልሳኑ ነበበ፤ አእኰቶ ወባረኮ ለእግዚአብሔር፨መልአ መንፈስ ቅዱስ ላዕለ ተክለ ሃይማኖት፨ ተነበየ ወይቤ አንሥአ ለነ ቀርነ መድኃኒትነ፡፡

፯. ለኅንብርትከ / መልክአ ተክለ ሃይማኖት /

ሰላም ለኅንብርትከ ማእከለ ከርሥ ሀላዊ፤
ዘተቶስሐ በደሙ ለወልደ ማርያም ናዝራዊ፤
ተክለ ሃይማኖት ጽጌ ዘሠረጽከ እምአረጋዊ፤
ተበሀሉ በእንቲአከ ካህናተ ይሁዳ ወሌዊ፤
መልአክኑ ሰማያዊ ወብእሲ ምድራዊ፡፡

ዚቅ፦

በከመ ዜነዎ መንፈሳዊ ፨ ለጸጋ ዘአብ አረጋዊ ፨
ተክለ ሃይማኖት ተወልደ ዓርኩ ለመርዓዊ ሰማያዊ፡፡

፰. ለቆምከ / መልክአ ተክለ ሃይማኖት /

ሰላም ለቆምከ ዘጶደሬ ሰማይ ልብሱ፤
ልሳናት ቦቱ እለ ይቄድሱ፤
ተክለ ሃይማኖት በለዝ ለእግዚአብሔር ዓምደ መቅደሱ፤
ጸውዐኒ እትሉ እግዚኦ ኀበ እግርከ አንሶሱ፤
ከመ ተለዎ ለሙሴ ኢያሱ፡፡

ዚቅ፦

ሃሌ ሉያ ሃሌ ሃሌ ሉያ ፨ ዘለዓለም ፍሡሕ ገጹ ብሩህ እምነቢያት ልሳኑ በሊሕ ፨ (ዘ)ቆሙ ነዊሕ ዲበ ዕንግድዓሁ ጽሕሙ ስፉሕ ፨ ( ዘ)ተክለ ሃይማኖትኒ ይቤ ድምፆ ሰማዕኩ ግብሮ አንከርኩ ፍኖቶ ዘእምዓለም ርኢኩ፡፡

፱. እንዘ አኃሥሥ / መልክአ ተክለ ሃይማኖት /

እንዘ አኃሥሥ በረከተከ አእዳወ ልብየ በአንሥኦ፤
እለ መርሐ ክርስቶስ ወጴጥሮስ ከመ ኀሠሡከ በተማልዖ፤
ተክለ ሃይማኖት ውኁደ ሰአልኩከ በአስተበቊዖ፤
ለጻድቅሰ ኅዳጥ ቃል ይበቊዖ፤
ተሰጥወኒ እግዚኦ እግዚኦ፡፡

ዚቅ፦

አባ ተክለ ሃይማኖት ጸሊ በእንቲአነ ፨ እንዘ ብዙኅ ውዳሴከ ውሑደ ነገርኩ ይኩነኒ ምዝጋና፡፡


°༺༒༻°   አንገርጋሪ °༺༒༻°  

አባ አቡነ መምህርነ እምአዕላፍ ኅሩይ ሐውጽ እምሰማይ፨
ብርሃነከ ከመ ንርአይ አማን ተክለ ሃይማኖት ፀሐይ፡፡

°༺༒༻° እስመ ለዓለም ዘዘወት °༺༒༻°  

ኖላዊነ ዘወረደ እምሰማያት ኖላዊሆሙ ለእሥራኤል አንሥእ ኃይለከ ወነዓ አድኅነነ፨ አንሥእ ኃይለከ ወነዓ አድኅነነ ተዘከር ኪዳነከ፨ አንሥእ ኃይለከ ወነዓ አድኅነነ ዘምስለ አብርሃም ፍቁርከ፨ ይስሐቅ ቊልዔከ ወእስራኤል ቅዱስከ፨ አንሥእ ኃይለከ ወነዓ አድኅነነ፨ ሐውጽ እምሰማይ ወርኢ ወእምድልው ጽርሐ መቅደስከ፨አንሥእ ኃይለከ ወነዓ አድኅነነ እስመ ወረድከ እምሰማይ ከመ ታድኅን ሕዝበከ፨ አንሥእ ኃይለከ ወነዓ አድኅነነ ተዘከር ኪዳነከ ዘመሐልከ ለዳዊት ገብርከ ፨ አንሥእ ኃይለከ ወነዓ አድኅነነ፨ ወኢንርኃቅ እምኔከ አሕይወነ ንጸውዕ ስመከ፨ አንሥእ ኃይለከ ወነዓ አድኅነነ ፨ አብርህ ገጸከ ላዕለ ገብርከ ፨እግዚኡ ለተክለ ሃይማኖት ስማዕ ቃለ ሕዝብከ፡፡

°༺༒༻°  አቡን  °༺༒༻°  

መጽአ ወልድ ውስተ ዓለም ወለብሰ ሥጋነ ሰብአ ኮነ በአርአያ ዚአነ ተመስሉ ኪያነ ምስለ ሕዝባዊ ሕዝባዌ ኮነ ሊቀ ካህናት ፍጹመ ተሰይመ በከመ ይቤ ዳዊት በመዝሙር አንተ ካህኑ ለዓለም።

°༺༒༻°   ዓራ   °༺༒༻°  

ዝንቱሰ ብእሲ ዘእምንእሱ ሕይወቱ ውስተ ቤተ እግዚአብሔር ከመ አብ ዘኮነ ለዕጓለማውታ ፈጻሜ ተጽናሶን ለዕቤራት እስመ ውስተ ልብሱ ክህነት (፫) ኲሉ ዓለም።

°༺༒༻°  ቅንዋት °༺༒༻°  

ሐራሲ በዕርፈ መስቀል ሰባኬ ወንጌል አባ ተክለሃይማኖት ክቡር ብእሲ ኄር ብእሴ እግዚአብሔር ለአሕዛብ መምሕር ትከብር ነፍስየ በቅድሜከ ዮም ባርከኒ አባ እንሣእ በረከተከ።

  °༺༒༻°   ሰላም °༺༒༻°  

ባርከኒ አባ እንሣእ በረከተከ በእንተ ሰላማ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን አባ ባርከኒ እንሣእ በረከተከ፡፡

+++++++++++++ ተፈጸመ ++++++++++++

🌹<  ወስብሐት ለእግዚአብሔር  >🌹
               🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

01 Jan, 14:53


ስንክሳር ታህሣስ 24

✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞

+*" ቅዱስ  #‎ተክለ_ሃይማኖት  ሐዋርያዊ "*+

*ልደት*

=>መልካም ዛፍ መልካም ፍሬን ያፈራልና ተክለ ሃይማኖትን የወለዱት ደጋጉ:  #‎ጸጋ_ዘአብ  ካህኑና  #‎እግዚእ_ኃረያ  ናቸው:: እርሱ በክህነቱ: እርሷ በደግነቷ: በምጽዋቷ ጸንተው ቢኖሩ እግዚአብሔር ጣፋጭ ፍሬን ሰጥቷቸዋል::

+በዳሞቱ ገዢ በሞተለሚ አደጋ ቢደርስባቸው  #‎ቅዱስ_ሚካኤል : ጸጋ ዘአብን ከሞት: እግዚእ ኃረያን ከትድምርተ አረሚ (ከአረማዊ ጋብቻ) አድኗቸዋል:: በኋላም የቅዱሱን መወለድ አብስሯቸዋል::

+አቡነ ተክለ ሃይማኖት የጸነሱት መጋቢት 24, በ1206 (1196) ሲሆን የተወለዱት ታሕሳስ 24, በ1207 (1197) ዓ/ም ነው:: በተወለዱበት ቀንም ብዙ ተአምራት ተገልጸዋል:: ቤታቸውም በበረከት ሞልቷል::

*ዕድገት*

=>የጻድቁ የመጀመሪያ ስማቸው " #‎ፍሥሃ_ጽዮን " ይሰኛል:: ይሕንን ስም ይዘው: አባታቸው ጸጋ ዘአብን ተከትለው አድገዋል:: በተለይ ቅዱሳት መጻሕፍትን (ብሉያት: ሐዲሳትን) ተምረዋል:: በሥጋዊው ጐዳናም ብርቱ አዳኝ እንደ ነበሩ ይነገራል:: ዲቁና ከወቅቱ ዻዻስ  #‎አባ_ጌርሎስ  ተቀብለዋል::

*መጠራት*

=>አንድ ቀን ፍሥሃ ጽዮን ለአደን ወጥቶ ሲያነጣጥር ድንገት ከሰማይ አስደንጋጭ ድምጽ ተሰማ:: የክብር ባለቤት  #‎ጌታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ  አእላፍ መላእክት እያመሰገኑ በሚካኤል ክንፍ ተቀምጦ ወረደ::

+የወጣቱን አዳኝ ፍርሃቱን አርቆ ጌታችን ተናገረ:

"ከዛሬ ጀምሮ ስምህ ተክለ ሃይማኖት (ተክለ ሥላሴ) ይሁን:: አራዊትን ሳይሆን ነፍሳትን ታድናለህ:: ዘወትር ካንተ ጋር ነኝ" ብሎ በግርማ ዐረገ:: ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከዚህ ጊዜ በኋላሰዓትን አላጠፉም:: ንብረታቸውን ለነዳያን በትነው በትር ብቻ ይዘው ቤታቸው እንደ ተከፈተ ወደ ምናኔ ወጡ::

*አገልግሎት*

=>ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከዻዻሱ ቅስና ተቀብለው የወንጌል አገልግሎትን ጀመሩ:: በመጀመሪያ ስብከታቸው እዚያው ሽዋ ( #‎ጽላልሽ ) አካባቢ ብቻ በ10ሺ የሚቆጠሩ ሰዎችን አሳምነው አጠመቁ:: ያንጊዜ  #‎ኢትዮዽያ  2 መልክ ነበራት::

1.ዮዲት (ጉዲት) በፈጠረችው ጣጣና በእስላሞች ተጽዕኖ ወደ ደቡብ አካባቢ ያለው ነዋሪ አንድም ሃይማኖቱን ክዷል: ወይም በባዕድ አምልኮ ተጠምዷል::

2.ደግሞ በዛግዌ ነገሥታት ጥረት ክርስትናና ምናኔ ተነቃቅቶ ነበር::

+ግማሹ ሃገር በጨለመበት ወቅት የደረሱት  #‎ሐዲስ_ሐዋርያ  አባ ተክለ ሃይማኖት በወጣት ጉልበታቸውና በኃይለ መንፈስ ቅዱስ ብዙ ቦታዎችን አደረሱ:: ሕዝቡን: መሣፍንቱን ወደ ሃይማኖት መልሰው: ማርያኖችን (ጠንቁዋዮችን) አጥፍተዋል::

*ገዳማዊ ሕይወት*

=>ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት በወንጌል ብርሃን ኢትዮዽያን ከማብራታቸው ባለፈ ገዳማዊ ሕይወትንም አስፋፍተዋል:: እርሳቸው ከሁሉ የተሻሉ ሳሉም በ3 ገዳማት በረድዕነት አገልግለዋል::

+እነዚህም በአቡነ  #‎በጸሎተ_ሚካኤል  ገዳም ለ12 ዓመታት: በአቡነ  #‎ኢየሱስ_ሞዐ_ዘሐይቅ  ገዳም ለ7 ዓመታት: በደብረ ዳሞ ከአቡነ  #‎ዮሐኒ  ጋር ለ7 ዓመታት: በአጠቃላይ ለ26 ዓመታት አገልግለዋል::

+በአቡነ ኢየሱስ ሞዐ ከመነኮሱ በኋላም ወደ ምድረ ሽዋ  #‎ዞረሬ  ተመልሰው በአንዲት በዓት ውስጥ ለ22 ዓመታት ቆመው ጸልየዋል:: በተሰበረ እግራቸውም 6 ጦሮችን በግራና በቀኝ ተክለው ለ7 ዓመታት ጸልየዋል::

*ስድስት ክንፍ*

=>ኢትዮዽያዊው ጻድቅና ሐዋርያ ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከኢትዮዽያ ወደ ኢየሩሳሌም ተጉዘው ከቅዱሳት መካናት ተባርከዋል:: ጻድቁ ምድረ  #‎እሥራኤል  የገቡት በየመንገዱ መንፈሳዊ ዘርን እየዘሩ: እያስተማሩና እያሳመኑ ነበር::

+የወቅቱ ሊቀ ዻዻሳት  #‎አባ_ሚካኤል  ጋርም ተገናኝተው ቡራኬን ተሰጣጥተዋል:: ዋናው ጉዳይ ግን ከዚህ በኋላ ነው:: ጻድቁ እመቤታችንና ጌታችን ከጽንሰታቸው እስከ ዕርገታቸው የረገጧቸውን ቦታዎች ሲመለከቱ በፍጹም ተደሞ እንባቸው ይፈስ ነበር::

+ምክንያቱም እግዚአብሔር ስላበቃቸው ተክለ ሃይማኖት የሚያዩት ቦታውን አልነበረም:: በገሃድ:-
¤በቤተ መቅደስ ብስራቱን
¤በቤተ ልሔም ልደቱን
¤በቤተ ዮሴፍ ግዝረቱን
¤በፈለገ ዮርዳኖስ ጥምቀቱን
¤በቤተ አልዓዛር ተአምራቱን ይመለከቱ ነበር::

+የጉብኝታቸው የመጨረሻ ክፍል ወደሆነው  #‎ቀራንዮ  ደርሰው ጌታቸውን እንደ ተሰቀለ ሆኖ ቢመለከቱት ከዓይናቸው ይፈስ የነበረው ቁጡ እንባ መልኩን ቀየረና ዓይናቸው ጠፋ::
በዚያች ቅጽበት ስም አጠራሯ የከበረ  #‎እመቤታችን_ድንግል_ማርያም  ፈጥና ደርሳ ተክልየን ወደሰማይ አሳረገቻቸው::

+በዚያም:-
¤የብርሃን ዐይን ተቀብለው
¤6 ክንፍ አብቅለው
¤የወርቅ ካባ ላንቃ ለብሰው
¤ማዕጠንተ ወርቁን ይዘው
¤ከ24ቱ ካህናተ ሰማይም ተደምረው
¤ሥላሴን በአንድነቱና ሦስትነቱ ተመልክተው
¤"ስብሐት ወክብር ለሥሉስ ቅዱስ ይደሉ" ብለው መንበረ ጸባኦትን አጥነው ወደ መሬት ተመልሰዋል::

*ተአምራት*

=>የተክልየ ተአምራት እንደ ሰማይ ከዋክብት የበዛ ነው::
*ሙት አንስተዋል
*ድውያንን ፈውሰዋል
*አጋንንትን አሳደዋል
*እሳትን ጨብጠዋል
*በክንፍ በረዋል
*ደመናን ዙፋን አድርገዋል::

+ብዙ ደቀ መዛሙርትን አፍርተው ደብረ ሊባኖስን መሥርተዋል:: በዚያም ሴትና ወንድ መነኮሳት እንደ ሕጻናት አብረው ኑረዋል:: በዘመናቸው ሰይጣን ታሥሯልና::

*ዕረፍት*

=>ጻድቅ: ሰማዕትና ሐዋርያ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ብርሃን ሆነው መከራን በብዙ ተቀብለው: አእላፍ ፍሬን አፍርተው: በተወለዱ በ99 ዓመት: ከ8 ወር: ከ1 ቀናቸው ነሐሴ 24, በ1306 (1296) ዓ/ም ዐርፈዋል:: ጌታ: ድንግል ማርያምና ቅዱሳን ከሰማይ ወርደው ተቀብለዋቸዋል:: 10 ትውልድ የሚያስምር ቃል ኪዳንም ተቀብለዋል::

=>የጻድቁ አባታችን ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት የቅድስናና የክብር ስሞች :-

1.ተክለ አብ: ተክለ ወልድ: ተክለ መንፈስ ቅዱስ
2.ፍስሐ ፅዮን
3.ሐዲስ ሐዋርያ
4.መምሕረ ትሩፋት
5.ካህነ ሠማይ
6.ምድራዊ መልዐክ
7.እለ ስድስቱ ክነፊሁ (ባለስድስት ክንፍ)
8.ጻድቅ ገዳማዊ
9.ትሩፈ ምግባር
10.ሰማዕት
11.የኢትዮዽያ መነኮሳት አለቃ
12.ፀሐይ ዘበፀጋ
13.የኢትዮዽያ ብርሃኑዋ
14.ብእሴ እግዚአብሔር (የእግዚአብሔር ሰው)
15.መናኒ
16.ኤዺስ ቆዾስ (እጨጌ)

=>እነዚህ የአባታችን ስሞች እንደዘመኑ ሰው ለመሞጋገስ የወጡ ሳይሆኑ ሁሉም በትክክል ሥራዎቹንና ለቤተ ክርስቲያን የሆነላትን የሚያዘክሩ ናቸው:

=>ታሕሳስ 24 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት
2.ቅዱሳን ጸጋ ዘአብና እግዚእ ኃረያ
3.ቅዱስ አግናጥዮስ ሐዋርያ
4.ቅድስት አስቴር
5.አባ ፊሎንጐስ ሊቀ ዻዻሳት
6.አባ ዻውሊ ጻድቅ
7.ጻድቃን ቅዱሳን ዘከዲህ

=>ወርኀዊ በዓላት
1.ቅዱስ ቶማስ ዘመርዐስ
2.አቡነ ዘዮሐንስ ጻድቅ ዘክብራን
3.ቅዱስ አጋቢጦስ (ጻድቅ ኤዺስቆዾስ)
4.ቅዱስ አብላርዮስ ታላቁ
5."24ቱ" ካኅናተ ሰማይ (ሱራፌል)
6.ቅዱስ አባ ሙሴ ጸሊም (ኢትዮዽያዊ)
7.ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ

🌹<  ወስብሐት ለእግዚአብሔር  >🌹
               🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

01 Jan, 14:53


"+ዕረፍት +"+

=>ነቢየ ጽድቅ: ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት እሥራኤልን ለ40 ዓመታት መርቶ አረጀ:: 'ምነው ያ ኃያል የእግዚአብሔር ሰው ቶሎ አረጀ?' ቢሉ ከገድሉ ጽናት ሰውነቱ ተቀጥቅጦ ነበርና::

*በዚያውም ላይ አንድ ቀን ስለ ሕዝበ አሥራኤል ቤዛ ይሆናቸው ዘንድ በቀሳፊ መልአክ ፊት ቆሞ ነበርና (ዜና. 21:16) ሰውነቱ ደከመ:: በዚህ ጊዜም ልጁን ሰሎሞንን አንግሦ በ70 ዓመቱ ከክርስቶስ ልደት ሺህ ዓመት በፊት በዚህች ቀን ዐርፏል::

+"+ ዳዊት በሰማይ +"+

=>በራዕየ ጐርጐርዮስ እንደ ተጻፈው ቅዱስ ዳዊትን በሰማይ 99ኙ ነገደ መላእክት ከበውት ያመሰግናል:: ከርሱ ዝማሬ ግርማ የተነሳ የሰማያት ግዘፋቸው ይናወጻል:: በገድለ አቡነ ኪሮስ እንደ ተጻፈው ደግሞ ቅዱሳን ነፍሳቸው ከሥጋቸው የምትለየው በዳዊት በገና ጣዕመ ዝማሬ ነው::

*በነገረ ማርያም ትምሕርት ደግሞ የቅዱስ ዳዊት ቤቱ ከልዑል አምላክ መንበር ሥር ነው::
*እንግዲህ ምን እላለሁ! ስለ ቅዱስ ዳዊት ከዚህም በላይ መጻሕፍት ብዙ ይላሉ:: ክብሩ ታላቅ ነውና::

<< በእውነት . . . በእውነት . . . በእውነት . . . ያለ ሐሰት ለቅዱስ ዳዊት ክብርና ምስጋና ይገባል >>

=>አምላከ ዳዊት ስለ ከበረው ቃል ኪዳኑ ይማረን:: ከንጹሕ አምልኮው ይክፈለን:: በዝቶ ከተረፈ በረከቱም አይለየን::

✞✞✞ ታሕሳስ 23 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱስ ዳዊት ልበ አምላክ
2.አባ ጢሞቴዎስ ገዳማዊ
3.አባ ሳሙኤል ጻድቅ
4.አባ ስምዖን ጻድቅ
5.አባ ገብርኤል ጻድቅ
6.አባ ይስሐቅ ጻድቅ

=>ወርኀዊ በዓላት
1.ቅዱስ ጊዮርጊስ ሊቀ ሰማዕታት
2.ነቢየ ጽድቅ ቅዱስ ሰሎሞን (ንጉሠ እሥራኤል)
3.ቅዱስ ዳንኤል ነቢይ

=>+"+ ከሕዝቤም የተመረጠውን ከፍ ከፍ አደረግሁ::
ባሪያየን ዳዊትን አገኘሁት::
ቅዱስ ዘይትም ቀባሁት::
እጄም ትረዳዋለች::
ክንዴም ታጸናዋለች::
ጠላት በእርሱ ላይ አይጠቀምም::
የዓመጻ ልጅም መከራ አይጨምርበትም::
ጠላቶቹን ከፊቱ አጠፋለሁ::
የሚጠሉትንም አዋርዳቸዋለሁ:: +"+ (መዝ. 88:20)

🌹<  ወስብሐት ለእግዚአብሔር  >🌹
               🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

30 Dec, 13:15


“የገና ስጦታ ለየኔታ” በሚል መሪ ቃል የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር መካሄዱ ተገለጸ

“የገና ስጦታ ለየኔታ” በሚል መሪ ቃል ለገዳማትና ለአብነት ትምህርት ቤቶች ማጠናከሪያና ማስፋፊያ የሚሆን የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር ታኅሣሥ 20 ቀን 2017 ዓ.ም በዮድ አብሲኒያ የባህል አዳራሽ ተካሄዷል።

በመርሐ ግብሩ የማኅበረ ቅዱሳን ዋና ሥራ አስፈጻሚ መምህር ዋሲሁን በላይ ና የማኅበረ ቅዱሳን ስራ አመራር አባል ቀሲስ ሙሉጌታ ስዩም (ዶ/ር) እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው ምእመናን ተገኝተዋል።

ቀሲስ ዶ/ር ሙሉጌታ ሥዩም የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉ ሲሆን “ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲወለድ የሩቅ ምስራቅ ሰዎች የእጅ መንሻ፣ እንሰሳት እስትንፋሳቸውን እንደሰጡ እኛም የእርሱን አስተምህሮ ላስቀጠሉልን ለገዳማትና ለአብነት ትምህርት ቤቶች ካለን ላይ ማካፈል ይጠበቅብናል” በማለት ገልጸዋል።

ህዳር 15 የተጀመረው የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት እስከ ታኅሣሥ 30 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚቆይ የተገለጸ ሲሆን ምእመናን የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ለገዳማትና ለአብነት ትምህርት ቤቶች ስጦታቸውን መለገስ እንደሚችሉ ተጠቁማል።

©ማኅበረ ቅዱሳን ሚዲያ

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

30 Dec, 05:59


መሬት ምን ሆናለች ምን አንቀጠቀጣት
ጥፋቷ ምንድነው ማን ይሆን የቀጣት

ምነው አልተው አላት ምነው ደጋገማት
ምን አጥፍታ ይሆን እንዲህ የረገማት

የምድሪቱ ወገብ መቀነቷ ላልቶ
መተንፈሻ ሲያጣ በረመጥ ተሞልቶ
ሰው በሰው ጨክኖ ሰው በሰው ተበልቶ
አንዱ አንዱን ሊያጠፋ ሴራውን ዶልቶ

ይሄ ነው እንግዲ....

የአቅመቢሱ ድሃ የህፃናቶች እምባ
ልጅ አባቱን ሲያጣ በፈንታሌ አምባ
ሹፌር ወጥቶ ሲቀር ግራ እየተጋባ
ደም እየፈሰሰ መሬት እየገባ

ይሄ ይሆን እንዴ....

ውስጧ ተጠራቅሞ ሐጢያት ሆኖባት
ከውስጧ ሊወጣ የሚያርገበግባት

ወይስ እንደ በጓ በላይዋ ላይ ሆኖ የሚበላላትን
አርግፋ ለመጣል እምትደጋግመው እርግፍግፍ ማለትን

የገሀነም እሳት ለመውጣት ሲያጓራ
ምን ደብቆ ይሆን የፈንታሌው ጋራ
ብቻ አደራሺን አንቺ መተሀራ ።

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

30 Dec, 04:18


🌹 ስንክሳር ታህሳስ 21 🌹

እንኩዋን "ለኖላዊ ሔር ክርስቶስ" : ለቅዱሳን "በርናባስ ሐዋርያ" እና "አባ ይስሐቅ" ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ::

🌿" ኖላዊ ሔር "🌿

እግዚአብሔር አዳምን በ7 ሃብታት አክብሮ በገነት ቢያኖረው "አትብላ" የተባለውን ዕፀ በለስ በላ:: በዚህም ከፈጣሪው ተጣልቶ: በሞተ ሥጋ ሞተ ነፍስ: በርደተ መቃብር ርደተ ገሃነም ተፈረደበት:: በሁዋላ ግን ንስሃ ስለ ገባ "ከ5 ቀን ተኩል (5,500 ዘመን) በሁዋላ ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለሁ" የሚል ቃል ኪዳንን ሰጠው::

ከዚህ በሁዋላ ለ5,500 ዘመናት ጊዜ ወደ ታች ይቆጠር ጀመር:: ስለ እግዚአብሔር ሰው መሆንና ዓለምን ማዳንም ትንቢት ይነገር: ሱባኤ ይቆጠር: ምሳሌም ይመሰል ገባ::

ከአዳም እስከ ሙሴ (ዘመነ አበው) ምሳሌያት ይበዛሉ:: ከሙሴ እስከ ዳዊት (ዘመነ መሣፍንት) ምሳሌያቱ እየጐሉ መጥተዋል:: ከልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት እስከ ቅዱስ ሚልክያስ ድረስ (በዘመነ ነቢያት / ነገሥት) ግን ትንቢቶች ስለ ክርስቶስና ስለ ማደሪያ እናቱ እንደ ጐርፍ ፈሰዋል::

ነቢያትም የመሲህን መምጣት እየጠበቁ በጾም: በጸሎትና በትሕርምት ኑረዋል:: እንባቸውንም አፍሰው ቅድመ እግዚአብሔር ደርሶላቸዋል::

ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ይህችን ዕለት "ኖላዊ ሔር" ብላ ታከብራለች:: ይሕንንም ለሳምንት ያህል ታዘክራለች:: መሠረታዊ መነሻዋም (ዮሐ. 10:1) ነው:: "ኖላዊ" ማለት በቁሙ "እረኛ" ማለት ሲሆን "ሔር" ደግሞ "ቸር-ርሕሩሕ-አዛኝ" እንደ ማለት ነው::

ገጥመን ብንተረጉመው ደግሞ "ቸር እረኛ" የሚል ትርጉምን ይሰጠናል:: ከአባታችን አዳም ስህተት በሁዋላ ተፈጥረው ከነበሩ ችግሮች አንዱ ቸር እረኛ ማጣት ነው:: እግዚአብሔር አዳምን ፈጥሮ: ቸር እረኛ ሆኖ በገነት አሰማርቶት ነበር::

ኤዶም ገነት የለመለመች: ፈሳሾች የሞሉባት መልካም መስክ ናትና:: አባታችን ቅዱስ አዳም ደግሞ እንደ አቅሙ የጸጋ እረኝነት ተሰጥቶት ነበር:: ድቀት ካገኘው በሁዋላ ግን ከነፍስ እረኛው ጋር ተጣልቶ ከመልካሟ መስክ ገነት ወጣ::

እርሷንና የነፍሱን እረኛ ሲሻም አለቀሰ:: ተስፋ ድኅነት ሲሰጠውም ለልጆቹ ነገራቸው:: ከዚያም በመንጋው ላይ በአዳም ሴት ተተካ:: ከሴት ኄኖስ: ከኄኖስ: ቃይናን . . . እያለ ከኖኅ ደረሰ::

ከኖኅም በሴም ከአብርሃም: ከአብርሃምም በይስሐቅና በያዕቆብ ወርዶ ከሙሴ ደረሰ:: ከሙሴም በኢያሱ አልፎ ከነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ዳዊት ደረሰ:: እነዚህ ሁሉ እረኞች ምንም እንኩዋ ለእግዚአብሔር ሕዝብ በትጋት ቢሠሩም ሕዝቡን ከሲዖል ማዳን አልቻሉም::

ከሲዖል የሚያድን የነፍስ እረኛ ነውና ያን ጊዜ ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት የራሱን: የአባቶቹንና የልጆቹን ጩኸት ባንድ አድርጐ ጮኸላቸው:: "ኖላዊሆሙ ለእሥራኤል አጽምዕ - የእሥራኤል እረኛ ሆይ ስማን!" አለ:: (መዝ. 79:1)

ጩኸቱም ቅድመ እግዚአብሔር ደረሰ:: ይህንን የሰማ ጌታም በጊዜው ከድንግል ማርያም ተወለደ:: በየጥቂቱ አድጐ ቸር እረኝነቱን ገለጠ:: መድኃኒታችን እንዳስተማረን እርሱ ቸር እረኛ ነው::

ከእርሱ በፊት የተነሱት ቴዎዳስ ዘግብጽና ይሁዳ ዘገሊላ (ሐዋ. 5:36, ዮሐ. 10:8) ሐሰተኛ እረኞች ነበሩ:: እርሱ ግን እውነተኛው የበጐች በር ነውና (ዮሐ. 10:7) በእርሱ የሚገቡ ሁሉ የዘለዓለም ሕይወትን ያገኛሉ::

እርሱ እውነተኛ እረኛ ነውና (ዮሐ. 10:11) ለመንጋው ራሱን አሳልፎ ይሰጣል:: በእሥራኤል ባሕል እረኞች ከፊት: መንጋው (በጐቹ) ከሁዋላ ሆነው ይሔዳሉና ገዳይ ቢመጣ መጀመሪያ የሚገድለው እረኛውን ነው::

መድኃኒታችን ክርስቶስ በሞቱ ሕይወትን: በመራቆቱ የጸጋ ልብስን: በውርደቱ ክብርን: በድካሙ ኃይልን ይሰጠን ዘንድ ስለ እኛ ራሱን አሳልፎ ሰጠ:: የማይሞት ንጉሥ ስለ መንጋው ሞተ:: ሰማይን ከነግሡ ምድርንም ከነልብሱ የፈጠረ ጌታ (ዘፍ. 1:1, ዮሐ. 1:2) ስለ በጐቹ ይህንን ሁሉ ታግሦ ከሲዖል አዳነን::

በሚያርግ ጊዜም በእርሱ ፈንታ ባለ ሙሉ ስልጣን እረኞችን: ሐዋርያትን (ዮሐ. 21:15) ሊቃነ ዻዻሳትን (ሐዋ. 20:28) ካህናትን (ማቴ. 18:18) ሾመልን:: እነርሱን እረኞች አሰኝቶ እርሱ "ሊቀ ኖሎት-የእረኞች አለቃ" ተባለ:: እነርሱም እስከ ዓለም ፍጻም የክርስቶስን መንጋ ሊጠብቁ ስልጣኑም: ኃላፊነቱም አለባቸው:: (ማቴ. 28:19)

" አባ ይስሐቅ ጻድቅ "

ይህ ቅዱስ በመካከለኛው ዘመን በምድረ ግብጽ የነበረ ገዳማዊ ነው:: መንኖ ለብዙ ዘመናት በገዳም ሲኖር ምኞቱ አንዲት ብቻ ነበረች:: እመቤታችንን በአካል መመልከትን ይፈልግ ነበር::

የገዳሙ ጠባቂ በመሆኑ መነኮሳት ሲተኙ መቅደሱን ከፍቶ በድንግል ማርያም ስዕል ፊት ይጸልይ: ይሰግድ: ያነባ ነበር:: እንዲህ ለ7 ዓመታት ስለ ተጋ ድንግል እመ ብርሃን ልመናውን ሰማች::

በዚህ ዕለትም ከፀሐይ 7 እጅ ደምቃ ወደ እርሱ መጣች:: ደንግጦ ሲወድቅ አነሳችው:: "ከ3 ቀናት በሁዋላ እመለሳለሁ" ብላም ተሠወረችው:: በ23ም ዐረፈ::
"በዛቲ ዕለት ሶበ ጸለየ ጥቡዐ::
ለይስሐቅ አስተርዓየቶ እም አይቆናሃ ወጺአ::
እምጸዳለ መብረቅ ጥቀ እንዘ ትጸድል ስብአ::" እንዳለ ደራሲ:: (አርኬ)

የእሥራኤል እረኛ ሥጋችንን ከመቅሰፍት: ነፍሳችንን ከገሃነመ እሳት ይጠብቅልን:: ከበረከተ ቅዱሳንም ይክፈለን::

ታሕሳስ 21 ቀን የሚከበሩ
      ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ኖላዊ ሔር
2.ቅዱስ በርናባስ ሐዋርያ
3.አባ ይስሐቅ

🌹✞ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ✞🌹
               🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

29 Dec, 05:45


የናቁሽ ሁሉ ከእግርሽ ሥር ይወድቃሉ!
ወንጌላዊ ሄኖክ ወደ እናት ቤተክርስቲያኑ መመለሱን ዛሬ አሳውቋል ሳያውቅ ለሰደባት ላንቋሸሻት ይቅርታ ጠይቋል።

እኛንም በቤቱ እያለን ከጠፋንበት እንዲመልሰን ፈጣሪ ይርዳን!

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

29 Dec, 04:51


🌹 ስንክሳር ታህሳስ 20 🌹

እንኩዋን ለነቢየ እግዚአብሔር "ቅዱስ ሐጌ" ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ::

🌿" ቅዱስ ሐጌ ነቢይ "🌿

ነቢይ ማለት በቁሙ ኃላፍያትን (አልፎ የተሠወረውን ምሥጢር) : መጻዕያትን (ገና ለወደ ፊት የሚሆነውን) የሚያውቅ ሰው ማለት ነው:: ሃብተ ትንቢት የእግዚአብሔር የባሕርይ ገንዘቡ ሲሆን እርሱ ለወደደው ደግሞ በጸጋ ይሰጠዋል:: እነዚህም ከጌታ ሃብተ ትንቢት የተሰጣቸው አባቶችና እናቶች "ቅዱሳን ነቢያት" በመባል ይታወቃሉ::

"ዘመነ ነቢያት" ተብሎ የሚታወቀው ብሉይ ኪዳን ቢሆንም እስከ ምጽዓት ድረስ ጸጋውን እግዚአብሔር ለፈቀደላቸው አይነሳቸውም:: በሐዋርያት መካከልም ቅዱስ አጋቦስን የመሰሉ ነቢያት ነበሩ:: (ሐዋ. 11:27) ቅዱሳን ነቢያት ከእግዚአብሔር እየተላኩ ሰውን ከፈጣሪው እንዲታረቅ ይመክራሉ: ይገስጻሉ::

ከበጐ ሃይማኖታቸውና ንጽሕናቸው የተነሳም እግዚአብሔርን በተለያየ አርአያና አምሳል አይተውታል::
"እስመ በአንጽሖ መንፈስ ርዕይዎ ነቢያት ለእግዚአብሔር: ወተናጸሩ ገጸ በገጽ" እንዳለ አባ ሕርያቆስ:: (ቅዳሴ ማርያም)

+ቅዱሳን ነቢያት በዋነኝነት "15ቱ አበው ነቢያት" : "4ቱ ዐበይት ነቢያት" : "12ቱ ደቂቀ ነቢያት" ና "ካልአን ነቢያት" ተብለው በ4 ይከፈላሉ::

ቅዱስ ሐጌ ቁጥሩ ከ12ቱ ደቂቀ ነቢያት ሲሆን ዘመነ ትንቢቱም ቅ.ል. ክርስቶስ በ450 ዓ/ዓ አካባቢ ነው:: "ደቂቀ ነቢያት" ማለት በጥሬው "የነቢያት ልጆች" ማለት ነው:: አንድም የጻፏቸው ትንቢቶች ሲበዙ 14 ምዕራፍ: ሲያንስ አንድ ምዕራፍ ያላቸው ናቸው::

=>"ሐጌ" ማለት መልአከ እግዚአብሔር (የእግዚአብሔር መልእክተኛ) ማለት ነው:: አንዳንዴም "በዓል" ተብሎ ይተረጐማል:: ትውልዱ ከነገደ ጋድ ሲሆን አባቱ አግታ: እናቱ ሲን ይባላሉ::

በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ከደኃርት (ከሁዋለኛው ዘመን ነቢያት) አንዱ ነው ይባላል:: ቁጥሩም ከ12ቱ ደቂቀ ነቢያት ነው:: ጥንተ ነገሩስ እንደ ምን ነው ቢሉ:-

እሥራኤል ከተከፈለችበት ከመንግስተ ሮብዓም (ከክርስቶስ ልደት 931 ዓመታት በፊት) በሁዋላ 10ሩ ነገድ "እሥራኤል": 2ቱ ነገድ "ይሁዳ" ተብለው በሰሜንና በደቡብ አቅጣጫ ተለያዩ:: መናገሻቸውም ኢየሩሳሌምና ሰማርያ ሆኑ::

ከዕለት ዕለት ግን የሁሉም ኃጢአት እየበዛ በመሔዱ እግዚአብሔር አዘነባቸው:: ለአሕዛብም አሳልፎ ሰጣቸው:: አስቀድሞ ቅድመ ልደተ ክርስቶስ በ722 ዓመት የአሦሩ ንጉሥ ስልምናሶር መጥቶ ሰማርያን አጠፋት:: 10ሩን ነገድም በባርነት አሦር አወረዳቸው::

ከዚህ ትምሕርት መውሰድ የተሳናቸው 2ቱ ነገድም ሊገሰጹ አልቻሉምና ተመሳሳይ ዕጣ ደረሰባቸው:: የእግዚአብሔርንና የነቢያቱን ድምጽ: ይልቁኑ የኤርምያስን ምክር አልሰሙምና ከክርስቶስ ልደት 586 ዓመታት በፊት ኃይለኛው የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነጾር መጣ::

የሚገድለውን ገድሎ: ሕዝቡንም ማርኮ ወደ ፋርስ ባቢሎን ሲያወርዳቸው ኢየሩሳሌምን ምድረ በዳ አደረጋት:: (2ነገ. )

እግዚአብሔርን የማይሰማ ሕዝብ ምን ጊዜም እጣ ፈንታው ይሔው ነው:: በተለይ ብዙ ጊዜ የእግዚአብሔር ቸርነት የበዛለት ሕዝብ እንዲህ አንገተ ደንዳና ሲሆን ይገርማል:: በእርግጥ ዛሬ እስራኤል ያይደለ ሃገረ እግዚአብሔር ኢትዮዽያ ናትና ከመሰል መከራ ለመራቅ ድምጹን መስማት ያስፈልጋል::

ሕዝቡ ግን ፋርስ : ባቢሎን ወርደው መከራን ሲቀበሉ : ነቢያት ያሉት ሁሉ ሲፈጸምባቸው ተጸጸቱ:: ፈጣሪም ተስፋ እንዳይቆርጡ በዚያው ዳንኤልን የመሰሉ ነቢያትን አስነሳላቸው:: እነ ኤርምያስንም ከግብጽ ላከላቸው::

ሕዝቡም (በተለይ "ትሩፋን" የተባሉት) "እግዚአብሔር ሆይ! 'ወሰብዓ ዓም ኃሊቆ' ባልከው ቃልህ : 70ው ዘመን ሲፈጸም ወደ አባቶቻችን ርስት ብትመልሰን መቅደስህን እናንጻለን:: በጐ ምግባርን እንይዛለን" ሲሉ ተሳሉ::

ልመናን የሚሰማ ቸሩ ፈጣሪም እንደ ቃሉ 70ው ዘመን ሲፈጸም እሥራኤል በነ ኤርምያስ ባሮክና እና ሌሎችም አማካኝነት በኃይል: በድንቅና በተአምራት ከፋርስ ባቢሎን ወጡ:: በድል ተጉዘውም ወደ ርስታቸው ገቡ::

የሰው ነገር አስቸጋሪ ነውና ከርስታቸው ከገቡ በሁዋላ ግን ስዕለታቸውን ሳይፈጽሙ ቀሩ:: በዚህ ጊዜም እንደ ዘወትሩ ይገሥጻቸው ዘንድ እግዚአብሔር ነቢያቱን ሐጌን : ዘካርያስንና ሚልክያስን አስነሳቸው::

ሕዝቡ "እስመ ኢኮነ ጊዜሁ ለሐኒጽ - ለማነጽ ወቅቱ አልረዳንም" እያሉ ቤተ መቅደሱ ሳይታነጽ ዘመናት አለፉ:: የሚገርመው ግን ቤተ መቅደሱ ምድረ በዳ ሆኖ የራሳቸውን ቤት አሳምረው ያንጹ ነበር::

በዚህ ጊዜ በመካከላቸው የነበረው ቅዱስ ሐጌ ዘለፋቸው::
"እምጊዜሁ ለክሙ ከመ አንትሙ ትንበሩ ውስተ ቤት ጥፉር: ወቤትየሰ ምዝቡር? - ቤቴ ፈርሶ ሳለ እናንተ ባማሩ ቤቶቻችሁ ልትኖሩ ጊዜው ነውን?" (ሐጌ. 1:4) አላቸው::

አክሎም "ቃላችሁን አልፈጸማችሁምና በረከቴን ከእናንተ አርቃለሁ" አላቸው:: ተግሣጹን ከልብ የሰሙት ሕዝቡም በዘሩባቤል መሪነት 46 ዓመታት የፈጀውን ቤተ መቅደስን አንጸዋል::

ቅዱስ ሐጌም በሕጉ እየኖረ: ትንቢትን እየተናገረ ዘመኑን ፈጽሟል:: በትውፊት ትምሕርትም ቅዱሱ የተወለደው በ500 ዓ/ዓ ሲሆን ያረፈው በ70 ዓመቱ በ5,070 ዓ/ዓ ነው:: ከክርስቶስ ልደት 430 ዓመታት በፊት ማለት ነው::

=>አምላከ ሐጌ ለቤቱ የምናስብበትን ዘመን ያምጣልን:: ከቅዱሱ ነቢይ በረከትም ይክፈለን::

ታሕሳስ 20 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱስ ሐጌ ነቢይ
2.አባ አውጋንዮስ
3.ታውፊና ንግሥት

=>ወርኀዊ በዓላት
1..ቅዱስ ዮሐንስ ሐፂር
2.ቅዱስ አክሎግ ቀሲስ
3.ቅዱስ አፄ ካሌብ ጻድቅ (ንጉሠ ኢትዮዽያ)
4.አባ አሞንዮስ ዘሃገረ ቶና
5.ቅድስት ሳድዥ የዋሒት
6.ማር ቴዎድሮስ ኃያል ሰማዕት

=>+"+ 'ብሩ የእኔ ነው:: ወርቁም የእኔ ነው' ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር:: 'ከፊተኛው ይልቅ የዚህ የሁለተኛው ቤት ክብር ይበልጣል' ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር:: በዚህም ሥፍራ ሰላምን እሰጣለሁ:: +"+ (ሐጌ. 2:9)

🌹✞ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ✞🌹
(ይህ የቴሌግራም ቻናላችን ነው ይቀላቀሉን)
               🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

28 Dec, 03:57


https://youtu.be/rByJOIQJt-g?si=jS7xtS_km7rs1Q8f

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

28 Dec, 03:55


#የሚጠብቀኝ_አይተኛም

የሚጠብቀኝ አይተኛም/2/
አያንቀላፋም

ቤት ባይኖረኝም እደጅ ባድርም
ቀን እና ለሊት ከኔ አይርቅም
ድምጸ አራዊት የለሊት ግርማ
ወደኔ አይቀርብም ድምጽህ ሲሰማ

አዝ________________

መሰናክልን ለእግሮቼ አይሰጥም
ይሰውረኛል በቀኙ ሰላም
ፀሐይም በቀን አይተኩሰኝም
የአጋንንትም ሀይል አያስፈራኝም

አዝ________________

ነፍሴን ጠበቃት ከጠላት ወጥመድ
ጌታዬ መራኝ በጽድቅ መንገድ
መውጣት መግባቴን እየጠበቀ
ለዚህ አበቃኝ እርሱ ባወቀ

አዝ________________

የሰማዩን ጠል እታገሳለው
ሰው ከጨከነ ምን እሆናለው
ለሊት በድብቅ ለሚጎበኙኝ
ለጻድቃኑ ክብር አምላክ ይስጥልኝ

አዝ________________

እንቅልፌን ባርኮ ለሰጠኝ የጌታ
በአለም ሀሳብ ሳልንገላታ
የእለት ምግቤንም ላልነሳኝ ፍጹም
ምስጋና ላቅርብ እስከ ዘለዓለም

መዝሙር
ሊቀ-መዘምራን ይልማ ኃይሉ

"እነሆ፥ እስራኤልን የሚጠብቅ
አይተኛም አያንቀላፋምም።"
👉 መዝሙረ ዳዊት 121:4

"ክርስቲያን ወገኖቼ እኛን የሚጠብቅ
አይተኛም እና አትፍሩ"

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

28 Dec, 03:53


🌹  ስንክሳር ታህሣስ 19 🌹
† እንኳን ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል: ቅዱስ ዮሐንስ ዘቡርልስ እና አቡነ ስነ ኢየሱስ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †

† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †

🔔† ቅዱስ ገብርኤል ሊቀ መላእክት †🔔

† በቤተ ክርስቲያን ክቡር ከሆኑ ሊቃነ መላእክት አንዱ የሆነው ቅዱስ ገብርኤል ብዙ የክብር ስሞች አሉት:: በተለይ ግን:-
*ሊቀ አርባብ:
*መጋቤ ሐዲስ:
*መልአከ ሰላም:
*ብሥራታዊ:
*ዖፍ አርያማዊ:
*ፍሡሐ ገጽ:
*ቤዛዊ መልአክ:
*ዘአልቦ ሙስና . . . እየተባለ ይጠራል::

በብሉይ ኪዳንም ሆነ በሐዲስ ኪዳን ስሙ በብዛት ተጠቅሷል:: ስለ ረዳትነቱና አማላጅነቱም ቤተ ክርስቲያን በስሙ ታቦት ቀርጻ: መቅደስ አንጻ በሥርዓት ክብሩን ትገልጻለች::

ከእነዚህም አንዱ ሠለስቱ ደቂቅን እንዳዳነ የሚታሰብበት አንዱ በዓሉ ዛሬ ነው::
"ለዝንቱ ዜናዊ መልአከ ኃይል:: በዛቲ ዕለት ከመ ይትገበር በዓል:: መምሕራን አዘዙ ወሠርዑ በቃል::" እንዲል:: (አርኬ)

ንጉሡ ከምርኮ ወጣቶች ለቤተ መንግስት ሲመርጥ ሦስቱ ቅዱሳንና ዳንኤል ተመርጠው የምቾት ሕይወት ተዘጋጅቶላቸው ነበር:: ነገር ግን በምግብና በአምልኮ ከአሕዛብ ጋር መተባበርን አልፈለጉምና ምርጫቸው ጾምና ጸሎት ከቆሎ ጋር ሆነ::

ምንም እንኳ በቤተ መንግስት ውስጥ ቢኖሩ: ምንም የነገሥታት ልጆች ቢሆኑ ለእነርሱ ከእግዚአብሔር ፍቅር የተሻለ አልነበረምና በጥሬ ቆሎ ተወስነው ኖሩ::

አምላካቸው ከሃሊ ነውና በውበትም ሆነ በጥበብ በባቢሎን ምድር ከነርሱ የሚደርስ አልተገኘም:: ንጉሡም በባቢሎንና በአውራጃዋ ላይ ሾማቸው:: ስማቸውንም በአማልክቱ ስም ሲድራቅ: ሚሳቅና አብደናጐ አላቸው::

ከነገር ሁሉ በኋላ አሕዛብ ቀንተውባቸዋልና የክፋት አዋጅን አሳወጁ:: ናቡከደነጾር 60 ክንድ ቁመት ያለውን የወርቅ ምስል አቁሞ ስገዱ ቢላቸው አይሆንም በማለታቸው ተቃጥለው እንዲሞቱ እሳት ተፈረደባቸው:: ነበልባሉ ከጉድጓዱ ወደ ላይ 49 ክንድ ቢነድም ቅንጣት ያህል ፍርሃት አልጎበኛቸውም::

ወደ እሳቱም ሲጥሏቸው መልዐከ አድኅኖ ቅዱስ ገብርኤል ደርሶ አዳናቸው:: ከሆነው ነገር የተነሳ አሕዛብ አፈሩ:: ናቡከደነጾር ግን ከዙፋኑ ተነስቶ የቅዱሳኑን አምላክ እግዚአብሔርን ባረከ::

ቅዱሳኑን ያዳነ ቅዱስ መልአክ እኛንም ያድነን ዘንድ እንደ አባቶቻችን
"አድኅነኒ ዘአድኃንኮሙ በአክናፊከ ምንትው::
አመ ውስተ እሳት ተወድዩ ሠለስቱ እደው::" እያልን እንለምነው:: (መልክዐ ገብርኤል)

† ቅዱስ ዮሐንስ ዘቡርልስ †

† ይህ ቅዱስ አባት ስም አጠራሩ የከበረ ነው:: ሊቅም: ጻድቅም: ጳጳስም: ገዳማዊም ነው:: ከሁሉም በላይ ግን ዛሬም ድረስ ቤተ ክርስቲያን በተድላ ለምትጠቀምባቸው መጻሕፍት (ስንክሳር: ግጻዌ እና ሃይማኖተ አበው) መሠረትን የጣለ ቅዱስ ሰው ነው::

ቅዱስ ዮሐንስ በትውልዱ ግብጻዊ ሲሆን ጊዜውም 5ኛው መቶ ክ/ዘ ነው:: ወላጆቹ ክርስቲያኖች: በዚያውም ላይ ሞልቶ የተረፋቸው ባለ ጠጐች ነበሩ:: እንደ ሕጉ ወጣት እስኪሆንና ራሱን እስኪችል ድረስ አሳደጉት::

ከዚያ ግን ድንገት አባቱና እናቱ ተከታትለው ዐረፉ:: ከቁጥር የበዛ ሃብትን የግሉ ያደረገው ቅዱስ ዮሐንስ ምን እንደሚያደርግበት ጨነቀው:: አንድ ትልቅ ነገር ግን ከማይሆን ጐዳና ጠበቀው::

ወላጆቹ ሁሌም መዝገብን በሰማያት ያገኙ ዘንድ ለነዳያን ይራሩ ነበርና ይህንኑ ለመቀጠል ወሰነ:: መልካም ፍሬ ከመልካም ዛፍ ነውና (ማቴ. 7:16) ወላጅ ለልጁ ማውረስ ያለበት ምድራዊ ሃብትን ሳይሆን በጐ ሕሊናን ነው:: ሳይሠሩ ያገኙት ሃብት ብዙዎችን አጥፍቷቸዋል::

ለዛም ይመስላል ዛሬ አንዳንዶቻችን በቤተሰቦቻችን ሃብት ከእኛ አልፈን ትውልዱን እየገደልንበት ያለው:: ለዚህ ደግሞ እግዚአብሔር ንስሃ ካልገባን ይመጣብናል:: መቅረዛችን (ሕይወታችንም) ከእኛ ላይ ይወስዳል::

ፍርድ የሚሆነው በክፉው ትውልድ ላይ ብቻ አይደለም:: ይህንን ትውልድ በፈጠርነውና መልካሙን መንገድ ባልመራነው በሁላችንም ላይ እንጂ:: (ራዕ. 2:5)

ወደ ቀደመ ነገራችን እንመለስና ቅዱስ ዮሐንስ በወላጆቹ ሃብት የእንግዶች ማረፊያ የሚሆኑ ቤቶችን አንጾ ነዳያንን ይንከባከብ ገባ:: ሙሉውን ቀን ለነዳያን ሲራራ ይውላል:: አመሻሽ ላይ እንግዶችን ተቀብሎ: አብልቶ ያሳርፋል::

ከዚያም ፈጣሪውን ያመሰግናል:: በእንዲህ ያለ ሕይወት ዘመናትን ካሳለፈ በኋላ አንድ እንግዳ መነኮስ ወደ ቤቱ መጣ:: አስተናግዶት ሲጨዋወቱ አደሩ:: ሌሊት ላይ ግን ስለ ምንኩስና ሕይወትና ስለ ክብሩ ነግሮት ነበርና ልቡ ተመሰጠ::

መነኮሱን ከሸኘው በኋላም ይመንን ዘንድ ቆረጠ:: ነዳያንን ሰብስቦ ሃብቱን አካፈላቸው:: ከዚያም ወደ ገዳመ አስቄጥስ ሒዶ የታላቁ አባ ዳንኤል ደቀ መዝሙር ሆነ:: በትሕትና ለአባቶች እየታዘዘ ከቆየ በኋላ በጭንቅ ደዌ ተያዘ:: ሰይጣን በቅንዓት ገርፎት ነበርና::

እርሱ ግን በደዌው ምክንያት ለዓመታት መሬት ላይ ወድቆ ቢቆይም ፈጣሪውን ፈጽሞ ያመሰግን ነበር:: እግዚአብሔር ደግሞ በፈውስና በኃይል አስነሳው::

በጊዜው የቡርልስ ጳጳስ ዐርፎ ነበርና አባት ፍለጋ ወደ አስቄጥስ ገዳም መጥተው ነበር:: መንፈስ ቅዱስ መርጦታልና አበው ቅዱስ ዮሐንስ ጳጳስ ይሆን ዘንድ አስገደዱት:: እርሱም የፈጣሪ ፈቃድ መሆኑን ስላወቀ ሔደ::

በዚያም (በሃገረ ቡርልስ) ታላቁን ገድል ተጋደለ:: ወደ ከተማዋ ሲገባ ብዙ ነገሮች ከሚገባው ሥርዓት የወጡ ነበሩ:: ብዙ ሰው የእግዚአብሔርን ድምጽ ከመስማት ይልቅ ባላስፈላጊ ነገሮች ላይ ተጠምዶ ነበርና መንጋውን ያድን ዘንድ ተጋ::

ሳይሆኑ "ባሕታዊ": "አጥማቂ" ነን እያሉ ሕዝቡን የሚያሳስቱ ተኩላዎችንም አስወገደ:: ለሕዝቡ አጉል ሕልም: ሟርትን የሚያስተምሩትን ገሠጸ:: አንመለስም ያሉ መናፍቃንን እሳት ከሰማይ ወርዳ በላቻቸው::

ቅዱስ ዮሐንስ ከቅድስናው ብዛት ዘወትር ሲቀድስ መድኃኒታችንንና አእላፍ መላእክትን ያይ ነበር:: ከከዊነ እሳት ማዕረግ በመድረሱም አካሉ በመፈተት ሰዓት እንደ እሳት ይነድ ነበር:: እንባውም እንደ ውኃ ይፈስ ነበር::

ቅዱስ ዮሐንስ ከዚህ ጐን ዛሬም ድረስ የሚታወቅበትን ታላቅ ሥራም ሠርቷል:: መንፈስ ቅዱስ አነሳስቷቸው ቅዱሱና የሃገረ አትሪብ ጳጳስ የነበረው ሊቁ አባ ሚካኤል መጽሐፈ ስንክሳርን : መጽሐፈ ግጻዌንና ሃይማኖተ አበውን ለመጀመሪያ ጊዜ አዘጋጅተዋል::

"ስንክሳር" የቅዱሳንና የፈጣሪን ነገር በየዕለቱ የሚዘግብ መጽሐፍ ሲሆን "ግጻዌ" የየዕለቱን በዓላት ከምስባክና ምንባባት ጋር አስማምቶ የያዘ መጽሐፍ ነው:: "ሃይማኖተ አበው" ደግሞ የዶግማ መጽሐፍ ሆኖ ከሐዋርያት እስከ ሊቃውንት ድረስ የጻፉትን የያዘ ነው:: ሦስቱን የሚያመሳስላቸው "ስብስብ / እስትጉቡዕ / Collection" መሆናቸው ነው::

ቅዱሱ ዮሐንስ በሃገረ ቡርልስ በከፍተኛ ድካም ይህንን ፈጽሞ በዚህች ቀን ዐርፏል::
† አምላከ ቅዱሳን በመልአኩ ረድኤት ጠብቆ ለጻድቃኑ በረከት ያብቃን::

❤️ ታኅሣሥ 19 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ ገብርኤል ሊቀ መላእክት
2.ቅዱስ ዮሐንስ ዘቡርልስ
3.አቡነ ስነ ኢየሱስ ጻድቅ

† ወርኀዊ በዓላት
1.ቅዱስ ኤስድሮስ ሰማዕት
2.አቡነ ዓቢየ እግዚእ ጻድቅ
3.አቡነ ዮሴፍ ብርሃነ ዓለም
4.ቅዱስ ይምርሐነ ክርስቶስ

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

04 Dec, 11:47


🌹✞ ስንክሳር ኅዳር 25 ✞🌹

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡

እንኩዋን ለታላቁ ሰማዕት "ቅዱስ መርቆሬዎስ" ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ::

🌿" ቅዱስ መርቆሬዎስ ኃያል "🌿

ለክርስትና ሃይማኖት የሚከፈል ትልቁ ዋጋ ሰማዕትነት ነውና ቤተ ክርስቲያን ለምስክሮቿ ሰማዕታት ልዩ ክብር አላት:: ከኮከብ ኮከብ እንዲበልጥ ሁሉ ከሰማዕታትም ቅዱስ ጊዮርጊስን እና ቅዱስ መርቆሬዎስን የመሰሉት ደግሞ ክብራቸው በእጅጉ የላቀ ነው::

ቅዱስ መርቆሬዎስን ብዙ ጊዜ ሊቃውንት "ካልዕ (ሁለተኛው) ሊቀ ሰማዕታት" ሲሉ ይገልጹታል::

በ2ኛው መቶ ክ/ዘመን መጨረሻ አካባቢ ከሮም ግዛቶች በአንዱ (አስሌጥ) ከአባቱና ከሚስቱ ጋር የሚኖር "አሮስ" የሚሉት ሰው ይኖር ነበር:: ሚስቱ ደም ግባት የሠመረላት: እርሱም ደግነት ያለው ሰው ቢሆኑም የሚያመልኩት ግን ጣዖትን ነበር::

አንድ ቀን አሮስ ሚስቱን ከቤት ትቶ ለአደን ከአባቱ ጋር ወጣ:: እንደ ልማዳቸው ወጥመዱን አስተካክለው ተደበቁ:: የወጥመዱ ደወል ሲያቃጭል: "እንስሳ ተያዘልን" ብለው ሲሯሯጡ ዐይናቸው ያየው ነገር በድንጋጤ እንዲፈዙ አደረጋቸው:: 2 ገጻተ ከለባት በወጥመዱ ውስጥ ተይዘው ነበር::

እነዚህ ፍጡራን ሰዎች ናቸው:: ግን ባልታወቀ የተፈጥሮ አጋጣሚ እንደዚህ እንደ ሆኑ ይታመናል:: ግን እጅግ ግዙፍ: ከአንገታቸው በላይ እንደ ውሻ: ወገባቸው እንደ ሰው: ጉልበታቸው እንደ አንበሳ ሲሆን ታችኛው እግራቸው የጋለ የናስ ብረት ነው የሚመስል::

እነዚህን ፍጡራን ሰማያዊ ካልሆነ ምድራዊ ፍጡር አይችላቸውም:: አንበሳና ነብርን እንኩዋ እንደ ጨርቅ በጣጥሰው ይጥሏቸው እንደ ነበር ይነገራል:: ዐይናቸው እንደ እሳት ይነድ ስለ ነበር ማንም ትክ ብሎ ሊያያቸው አይችልም:: ምሥጢራቸውን ግን የሚያውቀው የፈጠራቸው አምላክ ነው::

ወደ ቀደመ ነገራችን እንመለስና:- አሮስና አባቱ ባዩአቸው ጊዜ ደንግጠው ወደቁ:: ገጻተ ከለባቱ የብረት ወጥመዱን እንደ ክር በጣጥሰው የአሮስን አባት በቅጽበት በሉት:: አሮስን ሊበሉት ሲሉ ግን ድንገት ቅዱስ መልአክ ወርዶ በእሳት ሰይፍ አጠራቸው::

"ከእርሱ የሚወጣ ቅዱስ ፍሬ አለና እንዳትነኩት" አላቸው:: ወዲያውም መልአኩ ያንን ኃይለኝነታቸውን አጠፋው:: በዚህ ጊዜ 2ቱም ወደ አሮስ ሒደው ሰገዱለት:: አሮስም ወደ ቤቱ ወስዶም ደበቃቸውና የሆነውን ሁሉ ለሚስቱ ነገራት::

ጥቂት ቆይታም ጸንሳ ወለደች:: ልጃቸውን ፒሉፓዴር (ፒሉፓተር) ሲሉ ስም አወጡለት:: ትርጉሙም "መፍቀሬ አብ - የአብ ወዳጅ" ማለት ነው:: ከዚያም አሮስ ሚስቱን : ልጁንና 2ቱን ገጻተ ከለባት ይዞ ወደ ቤተ ክርስቲያን ሒዶ ተጠመቀ::

አበው ካህናት እሱን "ኖኅ" : ሚስቱን "ታቦት" : ልጁን ደግሞ "መርቆሬዎስ" ሲሉ ሰየሟቸው:: መርቆሬዎስ ማለትም "ገብረ ኢየሱስ ክርስቶስ - የኢየሱስ ክርስቶስ አገልጋይ" እንደ ማለት ነው::

ከዚያም ደስ እያላቸው: ክርስቶስን እያመለኩ: ነዳያንን እያሰቡ: ልጃቸውን መርቆሬዎስን አሳደጉ:: ነገር ግን የገጻተ ከለባት ወሬ በመሰማቱ ንጉሡ "ካላመጣሃቸው" አለው:: ኖኅ ጸልዮ ወደ ኃይለኝነታቸው መልሷቸው ስለነበር ፊታቸው ገና ሲገለጥ ብዙ አሕዛብ በድንጋጤ ሞቱ::

ንጉሡም ስለ ፈራ ኖኅን የጦር መኮንን አደረገው:: በጦርነት ጊዜም ገጻተ ከለባቱ ኃይላቸው ስለሚመለስ ተሸንፎ አያውቅም ነበር:: አንድ ጊዜ ግን 2ቱን ገጻተ ከለባት ንጉሡ አታሎ ወሰዳቸው:: ሃይማኖታቸውን ሊያስክዳቸው ሲል "እንቢ" በማለታቸው አንዱ ሲገደል ሌላኛው አምልጦ ጠፋ::

በዚያ ወራትም ኖኅ ለጦርነት ወጥቶ ተማረከ:: ንጉሡ ደግሞ ታቦትን "ላግባሽ" ስላላት የ5 ዓመት ልጇን ቅዱስ መርቆሬዎስን ይዛ ተሰደደች:: በስደት ጥቂት እንደ ቆየች ግን ባሏን ኖኅን አየችው::

እርሷ ብታውቀውም እርሱ ዘንግቷት ነበር:: በሁዋላ ግን በሕጻኑ መርቆሬዎስ አማካኝነት ማስታወስ በመቻሉ ደስ አላቸው:: በዚያው በሮም ዙሪያ ሳሉም አንዱ ገጸ ከልብ መጥቶ አገኛቸው:: በዚህም ምክንያት በስደት ሃገርም መኮንን ሆኖ ተሾመ::

በዚያም ቤተ ክርስቲያንን አንጾ: ቤቱን ቤተ ነዳያን አድርጐ ኖኅ ለዓመታት ኖረ:: ቅዱስ መርቆሬዎስ ወጣት ሲሆንም ወላጆቹ ታቦትና ኖኅ ዐረፉ:: እርሱ ከባልንጀራው ገጸ ከልብ ጋር ሆኖ በጾምና ጸሎት ሲኖር ስለ አባቱ ፈንታ የጦር መሪ አደረጉት::

በጦርነትም እጅግ ኃያል: በሰው ዘንድም ፍጹም ተወዳጅ: የጾምና የጸሎት ሰው ሆነ:: ያን ጊዜ ግን ዳክዮስ ንጉሡ ክርስቶስን በመካዱ ምዕመናን ላይ ሞት ታወጀ:: በጊዜው ደግሞ የበርበር ሰዎች በሮም መንግስት ላይ ጦርነትን በማንሳታቸው ዳኬዎስና ቅዱስ መርቆሬዎስ ለጦርነት ወጡ::

ነገር ግን በርበሮች እንደ አሸዋ ፈሰው ብዛታቸውን ሲያይ ንጉሡ ደነገጠ:: ለማግስቱ ቀጠሮ ተይዞ ቅዱስ መርቆሬዎስ ሲጸልይ ቅዱስ ገብርኤል ወርዶ ሰይፍ ሰጠው::

በማግስቱም "ምን ይሻላል?" ሲባል ቅዱስ መርቆሬዎስ "እኔ የክርስቶስ ባሪያ ነኝና ብቻየን እቁዋቁዋማቸዋለሁ" ቢል ሳቁበት::
እርሱ ግን በጥቁር ፈረሱ (አብሮት ያደገ ነው) ተጭኖ በርበሮችን "ጠብ ይቅርባችሁ: በሰላም ሒዱ" ቢላቸው ተሳለቁበት:: ያን ጊዜም ጸሎት አድርሶ የመልአኩን ሰይፍ ሲመዘው ብዙዎቹ ወደቁ:: ከበርበሮችም ለወሬ ነጋሪነት እንኩዋ የተረፈ አልነበረም::

ነገሩ በሮም ሲሰማ ታላቅ ሐሴት ሆነ:: ዳሩ ግን ከሃዲው ዳኬዎስ "ድሉ የጣዖቶቼ የነ አዽሎን ነው" በማለቱ ቅዱስ መርቆሬዎስ ሲያዝን አደረ::

በ3ኛው ቀንም "ለጣዖት ሠዋ" የሚል ትዕዛዝ ከንጉሡ ዘንድ መጣ:: ቅዱሱ ግን ወደ አደባባይ ሔደ:: የክብር ልብሱንና መታጠቂያውን አውልቆ በንጉሡ ፊት ወረወረው::

"ለእኔስ ክብሬ ክርስቶስ ነውና ንብረትህ ለጥፋት ይሁንህ" ሲልም ንጉሡን በአደባባይ ዘለፈው:: ዳኬዎስም በቁጣ እሳት አስነድዶ: የብረት አልጋውንም አግሎ ቅዱስ መርቆሬዎስን በዚያ ላይ አስተኛው::

ያም አልበቃ ብሎት ወታደሮች እየተፈራረቁ ሲደበድቡት ደሙ ፈሶ እሳቱን አጠፋው:: ከዚያም ወስደው ወኅኒ ቤት ውስጥ ጣሉት:: ክርስቶስን ያስክደው ዘንድ በረሃብ: በግርፋት: በእሳት: በስለትም አሰቃየው:: በመጨረሻ ግን አሰቃይተው እንዲገድሉት ወደ እስያ ሰደደው:: በስፍራውም ብዙ አሰቃይተው ኅዳር 25 ቀን አንገቱን ሰይፈውታል::

እርሱ ካረፈ በሁዋላም የተባረከ ፈረሱ ለዓመታት ወንጌልን ሰብኩዋል:: አረማውያንንም ከአፉ በወጣ እሳት አጥፍቷል:: ተአምረኛውና ኃያሉ ሰማዕት ቅዱስ መርቆሬዎስ በ200 ዓ/ም እንደ ተወለደ: በ220 ዓ/ም መከራ መቀበል እንደ ጀመረና በ225 ዓ/ም ሰማዕት እንደሆነ ይታመናል::
<<የቅዱሱ ክብር ታላቅ ነው>>

አምላከ ቅዱስ መርቆሬዎስ በከበረ ቃል ኪዳኑ ይጠብቀን:: ከርስቱም አያናውጠን:: ከበረከቱም ይክፈለን::

🙏 ኅዳር 25 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ መርቆሬዎስ ሰማዕት
2.ቅዱሳን ታቦትና ኖኅ (ወላጆቹ)
3.ቅዱስ ሮማኖስ

🙏 ወርሐዊ በዓላት
1.አቡነ አቢብ (አባ ቡላ)
2.ቅድስት ቴክላ ሐዋርያዊት
3.ቅዱስ አበከረዙን ሰማዕት
4.ቅዱስ ዱማድዮስ ሶርያዊ
5.ቅዱስ አቡፋና ጻድቅ
6.ታላቁ አባ ቢጻርዮን

🌹✞ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ✞🌹
(ይህ የቴሌግራም ቻናላችን ነው ይቀላቀሉን)
               🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

03 Dec, 05:16


🌿† ስንክሳር ኅዳር 24 †🌿

እንኳን ለ24ቱ ቅዱሳን ካህናተ ሰማይ እና ቅዱስ አዝቂር ሰማዕት ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን።

† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †

† ሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ †

† እግዚአብሔር ቅዱሳን መላእክትን ሲፈጥራቸው በነገድ መቶ (100): በክፍለ ነገድ አሥር (10) አድርጓቸዋል:: አቀማመጣቸውንም በሦስት ሰማያትና በ10 ከተሞች (ዓለማት) አድርጓል::

† መላእክት ያሉባቸው ከተሞች ከታች ወደ ላይ "ኤረር: ራማና ኢዮር" ይባላሉ:: አሥሩ ክፍለ ነገድ ደግሞ ከነ አለቆቻቸው ይህንን ይመስላሉ:-
1."አጋእዝት" (የቀድሞ አለቃቸው ሳጥናኤል: አሁን የተረፉት በቅዱስ ሚካኤል ሥር ናቸው)
2."ኪሩቤል" (አለቃቸው ኪሩብ)
3."ሱራፌል" (አለቃቸው ሱራፊ)
4."ኃይላት" (አለቃቸው ሚካኤል)
5."አርባብ" (አለቃቸው ገብርኤል)
6."መናብርት" (አለቃቸው ሩፋኤል)
7."ስልጣናት" (አለቃቸው ሱርያል)
8."መኳንንት" (አለቃቸው ሰዳካኤል)
9."ሊቃናት" (አለቃቸው ሰላታኤል)
10."መላእክት" (አለቃቸው አናንኤል) ናቸው::

† ከእነዚህም:-
*አጋእዝት: *ኪሩቤል *ሱራፌልና *ኃይላት መኖሪያቸው በኢዮር (በ3ኛው ሰማይ) ነው::
*አርባብ: *መናብርትና *ስልጣናት ቤታቸው ራማ (2ኛው ሰማይ) ነው::
*መኳንንት: *ሊቃናትና *መላእክት ደግሞ የሚኖሩት በኤረር (በ1ኛው) ሰማይ ነው::

መላእክት ተፈጥሯቸው እምኀበ አልቦ ኀበ ቦ ነው:: አይራቡም: አይጠሙም: አይዋለዱም: አይሞቱም:: ተፈጥሯቸውም ረቂቅ ነው:: ተግባራቸውም ዘወትር "ቅዱስ: ቅዱስ: ቅዱስ" እያሉ ፈጣሪያቸውን ማመስገን ነው:: ምግባቸውም ይሔው ነው::

ዕረፍት ብሎ ነገርን አያውቁም:: "አኮቴቶሙ ዕረፍቶሙ: ወዕረፍቶሙ አኮቴቶሙ" እንዲል:: በተጨማሪም መልአክ ማለት ተላላኪ (አገልጋይ) ነውና ከፈጣሪ ወደ ሰው ልጆች ለምሕረትም: ለመዓትም ይላካሉ::

ምሕረትን ያወርዳሉ:: ልመናን ያሳርጋሉ:: ቅጡ ሲባሉም ይቀጣሉ:: ስነ ፍጥረት (አራቱ ወቅቶች) እንዳይዛቡ ይጠብቃሉ::
*ዘወትርም ስለ ሰው ልጆች ያማልዳሉ:: (ዘካ. 1:12)
*ምሥጢርን ይገልጣሉ:: (ዳን. 9:21)
*ይረዳሉ:: (ኢያ. 5:13)
*እንዳንሰናከል ይጠብቃሉ:: (መዝ. 90:11)
*ያድናሉ:: (መዝ. 33:7)
*ስግደት ይገባቸዋል:: (መሳ. 13:20, ኢያ. 5:13, ራዕ. 22:8)
*በፍርድ ቀንም ኃጥአንን ከጻድቃን ይለያሉ:: (ማቴ. 25:31)
*በአጠቃላይ ለሰው ልጆች ሕይወትና ድኅነት ሲባል ከፈጣሪያቸው የተሰጣቸውን ትዕዛዝ ሲጠብቁና ፈቃዱን ሲፈጽሙ ይኖራሉ::

ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በዚህች ዕለት የሃያ አራቱን ቅዱሳን ካህናተ ሰማይን መታሰቢያ ታደርጋለች:: እኒህ ቅዱሳን መላእክት በነገድ 10 ሲሆኑ መጠሪያቸው "ሱራፌል" : መኖሪያቸውም በኢዮር ነው:: ነገር ግን ሃያ አራቱ አለቆቻቸው ተመርጠው በመሪያቸው በቅዱስ ሱራፊ አለቅነት በጽርሐ አርያም ያገለግላሉ::

በቀናች ሃይማኖት ትምሕርት ሁሉም ቅዱሳን መላእክት ለእግዚአብሔር ቅርብ ቢሆኑም: በነጠላ የቅዱስ ሚካኤልን ያህል: በነገድ ደግሞ የኪሩቤል (አራቱ እንስሳ) እና የሱራፌልን (ሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ) ያህል ቅርብ የለም::

† ሃያ አራቱ ቅዱሳን ካህናት ሥራቸው:-
1.እንደ ሞገድ ከአንደበታቸው ምስጋና እየወጣ: ጧት ማታ ፈጣሪያቸውን ይቀድሱታል:: (ኢሳ. 6:1, ራዕይ 4:11, 5:11)

2.የሥላሴን መንበር ያለ ማቋረጥ ያጥናሉ:: (ራዕይ 5:8)

3.የሰው ልጆችን: በተለይም የቅዱሳንን ጸሎት በማዕጠንታቸው ያሳርጋሉ:: (ራዕይ 8:3)

4.የረከሱትን ይቀድሳሉ:: (ኢሳ. 6:6)

5.ዘወትርም ለሰው ልጆች ምሕረትን ሲለምኑ ይኖራሉ:: (ዘካ. 1:12)

ስለ እነዚህ ቅዱሳን ካህናት (ሱራፌል) ታላቁ ቅዱስ መጽሐፍ ብዙ ይላል:: ለምሳሌ:- ዐቢይ ነቢይ ወልዑለ ቃል ኢሳይያስ ፈጣሪው ተቀይሞት በነበረበትና ዖዝያን በሞተበት ወራት: ግሩማን ሆነው ሥላሴን "ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ" እያሉ ዙሪያውን ከበው ሲያመሰግኑ ሰምቷል::

ከእነርሱም አንዱ (ሱራፊ) መጥቶ በጉጠት እሳት ከንፈሩን ዳስሶ ከለምጹ አንጽቶታል:: (ኢሳ. 6:1) አቡቀለምሲስ የተባለ ቅዱስ ዮሐንስም በራዕዩ በግርማ: በአምሳለ አረጋዊ ተመልክቷቸዋል:: (ራዕይ 4:4)

አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫን የመሰሉ ቅዱሳን ሊቃውንት ደግሞ በጣዕመ ምስጋናቸው ሲገልጿቸው:-
"ካህናተ ሰማይ ቅውማን በዐውዱ::
አክሊላቲሆሙ ያወርዱ::
ቅድመ መንበሩ እንዘ ይሰግዱ::
ይርዕዱ::
ከመ ኢይዝብጦሙ ሶበ ይበርቅ ነዱ::" ብለዋል:: (መጽሐፈ ሰዓታት)
ትርጉሙም "በፈጣሪ መንበር ዙሪያ የሚቆሙ የሰማይ ካህናት አክሊለ ክብራቸውን አውርደው በመንበሩ ፊት ይሰግዳሉ:: መብረቀ መለኮቱ በተገለጠ ጊዜም በፍርሃት ይንቀጠቀጣሉ::" ነው:: ግሩም ባሕርየ ሥላሴን ሊቋቋመው የሚችል ፍጡር የለምና::

ቅዱሳን ካህናተ ሰማይ በምስጋናቸው: በማዕጠንታቸውና በምልጃቸው ክቡራን ናቸውና ዘወትር ልናከብራቸው ይገባናል:: የረከሰ ማንነታችንን ይቀድሱ ዘንድ: በምልጃቸውም ዘንድ እንድንታሰብ: ጸሎታችንንም ያሳርጉልን ዘንድ እንለምናቸው::

† ኅዳር 24 ቀን ዓመታዊ በዓላቸው ነው ማለት በየወሩ በ24 ወርኀዊ በዓላቸው መሆኑን ያሳያልና ዘወትር ልናስባቸው ይገባል::

በተለይ ያዘነን ልብ ደስ ያሰኛሉና እንደ ሊቃውንት እንዲህ ብለን እንጠራቸዋለን::
"ሰላም ለክሙ ካህናተ ሕጉ ወትዕዛዙ::
ለእግዚአብሔር ቃል ዘጶዴሬ ሥጋ አራዙ::
እምነቅዐ አፉክሙ ሐሴት ዘኢይነጽፍ ዉሒዙ::
ኪያየ ኅዙነ ወትኩዘ ልብ ናዝዙ::
ወበክንፍክሙ ብርሃናዊ ዐውድየ ሐውዙ::" (አርኬ ዘኅዳር 24)
† አምላከ ቅዱሳን ካህናተ ሰማይ ከምስጋናቸው ሐሴትን: ከማዕጠንታቸው በጐ መዓዛን ያውርድልን:: በረከታቸውንም ያብዛልን::

† ኅዳር 24 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1."24ቱ" ቅዱሳን ካህናተ ሰማይ (ሱራፌል)
2.ቅዱስ አዝቂር ሰማዕት
3."48" ሰማዕታት (ማሕበሩ)
4.አባ ዮሴፍ ዘሃገረ ጻን
5.ቅዱስ ዲዮስቆሮስ ጥዑመ ዜና
6.ቅዱስ ኪርያቅ ሰማዕት

† ወርኀዊ በዓላት
1.ቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት (መምሕረ ትሩፋት)
2.ቅዱስ ቶማስ ዘመርዐስ
3.አቡነ ዘዮሐንስ ጻድቅ ዘክብራን
4.ቅዱስ አጋቢጦስ (ጻድቅ ኤጲስቆጶስ)
5.ቅዱስ አብላርዮስ ታላቁ
6.ቅዱስ አባ ሙሴ ጸሊም (ኢትዮጵያዊ)
7.ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ

† "በዙፋኑ ዙሪያም ሃያ አራት ዙፋኖች ነበሩ:: በዙፋኖቹም ላይ ነጭ ልብስ ለብሰው: በራሳቸውም የወርቅ አክሊል ደፍተው ሃያ አራት ሽማግሌዎች ተቀምጠው ነበር:: ከዙፋኑም መብረቅና ድምጽ: ነጐድጓድም ይወጣል:: በዙፋኑም ፊት ሰባት የእሳት መብራቶች ይበሩ ነበር:: እነርሱም ሰባቱ የእግዚአብሔር መናፍስት ናቸው::" †
(ራዕይ ፬፥፬)

🌹✞ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ✞🌹
(ይህ የቴሌግራም ቻናላችን ነው ይቀላቀሉን)
🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
https://t.me/Sinksar
https://t.me/Sinksar
https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

02 Dec, 03:20


ከላይኛው የቀጠለ
#በስልት_ማሰለት
ክፍል-፪-
እግዚአብሔር  በነጻነታችን ውስጥ ሁነን የምንሠራውን መልካም ተግባር ይባርክልናል እንጂ አይጠላውም።
ነገር ግን ገና ለገና አልበቃሁም እያለ ዝም ብሎ እንዲቀመጥ ማድረግ ግን የቀደመችው የኢየሱሳውያን የሚሽኖች ተንኮል ናት።
እነዚህ አስተማሪዎች ከእግዚአብሔር ጋራ ማገልገል የሚሉት ከሚያጠፋን ሥርዓቱ ጋራ ማገልገል ለማለት መሆኑንም አንዘነጋም።
ዓይናችሁን ጨፍኑ ይታያችኋል አይነት ስብከት የተጀመረው ለዚህ ነው።
የእግዚአብሔር ማደሪያ ለመሆንም እንሠራለን።
የእግዚአብሔር ማደሪያ ሁነንም እንሠራለን።
ጸጋ እግዚአብሔር ነገረ ድኅነት በሂደት እስከ ዕለተ ሞት ትፈጸማለች እንጃ አንድ ጊዜ አትጨረስምና።
ለመሆኑ መልከም አስቦ መሥራት እግዚአብሔር አልባ ነውን?
ወደን ፈቅደን በነጻ ፈቃድ የምንሠራው እግዚአብሔርም የሚባርክልን ሥራ የለምን?
አንድ ሰው ከእግዚአብሔር ጋራ የሚሆነው መቸ ነው?
ከእግዚአብሔር ጋራ መሆኑን እስኪያውቅ ድረስ እጁን እግሩ አጣጥፎ ይቀመጣል ማለት ነውን?
አንድ ክርስቲያን ካመነ ከጠተመቀ ሥጋውን ደሙን ከተቀበለ ጀምሮ ጸጋው ቢለያይም የወይኑ ግንድ ቅርንጫፍ የክርስቶስ ኅዋስ አይደለም ወይ?
"እኔ የወይን ግንድ ነኝ እናንተም ቅርንጫፎች ናችሁ። ያለ እኔ ምንም ልታደርጉ አትችሉ።"ዮሐ.፲፭.፭ እንዲል።
ተው የቤተ ክርስቲያንን መከራ ነጠላ ለብሰን በመድረክ ተገትረን አናራዝምባት።
ትውልዱን በመንፈስም፣በጊዜም፣በሥራም..ወዲያ ወዲህ መጎተት ምንድን ነው ጥቅሙ?

ይቆየን
መ/ር ገብረ መድኅን እንየው
ኅዳር 2017ዓ.ም

🌹✞ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ✞🌹
(ይህ የቴሌግራም ቻናላችን ነው ይቀላቀሉን)
               🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

02 Dec, 03:18


#በስልት_ማሰለት
"እግዚአብሔርን ማገልገል።"
"ከእግዚአብሔር ጋራ ማገልገል።"
አሁን አሁን የተነቃባቸው አፋዛዥ አስተማሪዎች ከሚያነሧቸው አሳቦች እነሆ፦
"ከእግዚአብሔር ጋራ ስለማናገለግል ነው መፍትሄ ያጣነው።ስለሆነም የትኛውንም ሥራ ከመሥራታችን ቅድሚያ ሕይወታችን ከእግዚአብሔር ጋራ ይሁን ከዚያ በኋላ እናገለግላለን" ይላሉ።
ይሄንን ሀሳብ ስናስበው ጥሩ ይመስላል ዋና ዓላማው ግን ችግሩ ሁሉ የገጠመን ከእግዚአብሔር ጋራ ስለማናገለግል ነው ከእርሱ ጋር አንድ እስክንሆን ድረስ አርፈን እንቀመጥ ለማለት ነው።
"እንዲያውም ስለ ቤተ ክርስቲያን መጨነቅ አያስፈልግም እግዚአብሔር ለቤቱ ያስባል አንዳንዶች እግዚአብሔር እያገለገሉ ነው መከራውን ያመጡት"ይላሉ።ይሄ ማለት አስበው አቅደው ነገን ተመልክተው የሚሠሩ ሰዎች አያስፈልጉም ማለት ነው። ምክንያቱም ከእግዚአብሔር ጋራ ሳይሆን ለእግዚአብሔር እያገለግሉ ስለሆነ።
ይሄንን የሚሉት የሥርዓቱ አስጠባቂ አስተማሪዎች ናቸው። ለእነሱ ትልቁ ቁም ነገር ማንም ሰው ያገባኛል በቤተ ክርስቲያኔ ብሎ የአቅሙን አቅዶ እንዳይሠራ "ከእግዚአብሔር ጋር አይደለህም አብርሆት አልደረስህም" እያሉ ማጀዘብ ማስተኛት ነው።
ይህች ሀሳብ የማናት? የጤና ናት?ለምን ተፈለገች?

ይቀጥላል. . . .
በመ/ር ገብረ መድኅን እንየው።

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

01 Dec, 16:29


🌿† ስንክሳር ኅዳር 23 † 🌿

እንኳን ለቅዱሳን ቆርኔሌዎስ ሐዋርያዊ እና አብድዩ ነቢይ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †††

††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †††

††† ቅዱስ ቆርኔሌዎስ †††

††† ዛሬ የምንመለከተው የዚህ ቅዱስ ዜና ሕይወት በአብዛኛው የተወሰደው ከሐዋርያት ሥራ ምዕራፍ 10 ላይ ነው:: በቤተ ክርስቲያን የሐዲስ ኪዳን ታሪክ ወሳኝ ከሚባሉ ክዋኔዎች የዚህ ቅዱስ አምኖ መጠመቅ ነውና በታላቁ ቅዱስ መጽሐፍ ላይ በስፋት ተመዝግቧል::

ምንም እንኩዋ ከእርሱ አስቀድሞ ኢትዮዽያዊው ባኮስ እንዳመነና እንደ ተጠመቀ ቢታወቅም (ሐዋ. 8:26) ቅዱስ ቆርኔሌዎስ ከአሕዛብ ወገን አምኖ ሐዋርያትን የተቀላቀለ የመጀመሪያው ሰው ነው:: ጥንተ ነገሩስ እንደ ምን ነው ቢሉ:-
የሮም መንግሥት በቄሣሮች ሥር በ1ኛው መቶ ክ/ዘመን ዓለምን እንደ ሰም አቅልጦ: እንደ ገል ቀጥቅጦ ይገዛ ነበር:: በየ አሕጉሩም እስከ መንደርተኛ ሹሞች ድረስ ተሹመው ግብርን ለቄሣር ይሰበስቡ: ሕዝቡን ለቄሣር ያስገዙ ነበር::

ከእነዚህ መካከልም አንዱ የሆነው ቆርኔሌዎስ በቂሣርያ ዘፍልስጥኤም (ሌላ ቂሣርያ ስላለች ነው) የመቶ አለቃ (ሃቤ ምዕት): የሠራዊት መሪ (ሊቀ ሐራ) ሆኖ ተሹሞ ነበር:: የሠራዊቱን ስምም "ኢጣሊቄ" ይሉታል::

ቆርኔሌዎስ እግዚአብሔርን አያውቅም:: እንደ አረሚ (ግሪካውያን) የከዋክብት አምላኪ ነበር እንጂ:: ያም ሆኖ ክፋትን የሚጠላ: ደግነትን የሚያበዛ: ምጽዋትን የሚያዘወትርና በሐቲት (በምርምር) የሚኖር ሰው ነበር::

ታዲያ በዚያ ሰሞን ክርስቶስ ኢየሱስ መድኃኒታችን የማዳን ሥራውን ፈጽሞ: አበው ሐዋርያት ለትምሕርተ ወንጌል እንደ ሠጋር በቅሎ ይፋጠኑ ነበር:: ሹም (አለቃ) ነውና ቆርኔሌዎስ የሐዋርያት ዜና ፈጥኖ ነበር የደረሰው::

ቅዱሳኑ በስመ ክርስቶስ ድውያንን እንደሚፈውሱ: ሙታንን እንደሚያነሱ: በኃይለ መንፈስ ቅዱስም ብዙ ምልክቶችን (ተአምራትን) እንደሚያደርጉ ሰምቶ ተገረመ:: እርሱ የሚያመልከው ዙሐል (የኮከብ ስም ነው) አቅመ ቢስ ፍጡር መሆኑን ተረዳና እርግፍ አድርጐ ተወው::

ምንም የሠራዊት አለቃ ሹም ቢሆንም ዘወትር በመዓልትና በሌሊት ይጾምና ይጸልይ ገባ:: ጸሎቱም "የእውነት አምላክ ተገለጥ" ነበር:: ጾምና ጸሎት ያለ ምጽዋት ቁም ነገር አይሠሩምና ቤቱን ቤተ-ርሑባን: ቤተ-ነዳያን አደረገው::

ይሕ ተወዳጅ ጾም: ጸሎትና ምጽዋት ደግሞ ያለ ከልካይ ወደ ሰማያት: ቅድመ እግዚአብሔር ደረሰ:: ምንም አሕዛባዊ (ኢ-ጥሙቅ) ቢሆንም ጌታ ግን ቅዱስ መልአኩን ላከለት::

አንድ ቀን እንዳስለመደ ሲጸልይ ዘጠኝ ሰዓት (በሠርክ) አካባቢ መልአኩ ብሩህ ልብስ ተጐናጽፎ ተገለጠለት:: "ቆርኔሌዎስ ሆይ! ጸሎትህና ምጽዋትህ ወደ እግዚአብሔር ደረሰልህ:: እግዚአብሔርም አሰበህ" አለው::

"አሁንም ትድን ዘንድ በሰፋዪ ስምዖን ቤት: በሃገረ ኢዮዼ: ዼጥሮስ የሚሉት ስምዖን አለና እርሱን ጥራው:: እርሱ የምትድንበትን ይነግርሃል" ብሎት: የምሥራቹንም ነግሮት ተሰወረው:: ወዲያውም ከራዕዩ የተነሳ እያደነቀ ብላቴኖቹን ጠርቶ ወደ ኢዮዼ ላካቸው::

በዚያች ዕለትም የሐዋርያት አለቃ ቅዱስ ዼጥሮስ በቤተ ስምዖን ሰፋዪ ሳለ ይጸልይ ዘንድ ወደ ደርቡ (ፎቅ) ወጣ:: በዚያም በጸሎት ላይ ሳለ ተደሞ መጣበት:: ግሩም ራዕይንም ተመለከተ:: "ሞጣሕት ስፍሕት" ይላታል:: ከሰማይ በ4 ማዐዝን የተያዘች መጋረጃ: በውስጧ የእንስሳት: የአራዊት: የአዕዋፍ ስዕል ተስሎባት ስትወርድ ተመለከተ::

አንዲት እጅም ወደ እሪያው (አሳማ) እያመለከተች "ተንስእ ኦ ዼጥሮስ ኅርድ ዘንተ ወብላእ . . . - ዼጥሮስ ሆይ! ተነስ: ይህንንም አርደህ ብላ" ስትለው:: እርሱ ግን "ግሙራ ኢቦአ ርኩስ ውስተ አፉየ-የረከሰ ነገር ከአፌ ገብቶ አያውቅም" ብሎ መለሰ::

መልሶም "ዘእግዚአብሔር አንጽሐ አንተ ኢታስተራኩስ- እግዚአብሔር ያነጻውን አንተ አታርክሰው" ሲለው:: ይሕም ራዕይ 3 ጊዜ ሲደጋገም ተመለከተ:: ወዲያውም ያቺ መጋረጃም ወደ ላይ ተመለሰች::

የራዕዩ ምሥጢር ለጊዜው እግዚአብሔር ከፈጠረው "ርኩስ" የሚባል እንደ ሌለ ያጠይቃል:: ለፍጻሜው ግን ያቺ ሞጣሕት የወንጌል (የክርስትና) አንድም የእመ ብርሃን ድንግል ማርያም ምሳሌ ናት::

እሪያው ደግሞ የቅዱስ ቆርኔሌዎስ ምሳሌ ነውና "አትጸየፈው: አጥምቀው" ሲለው ነበር:: ቅዱስ ዼጥሮስ ስለዚህ ነገር ሲያሰላስል የቅዱስ ቆርኔሌዎስ ብላቴኖች ደርሰው ጠሩት:: መንፈስ ቅዱስ "አብረሃቸው ሒድ" ብሎታልና አብሯቸው ሔደ::

ወደ ቆርኔሌዎስ ዘንድ ደርሶም 2ቱ ራዕያቸውን ተጨዋወቱ:: ቆርኔሌዎስም በግንባሩ ተደፍቶ ለሊቀ ሐዋርያት ሰገደለት:: ቅዱስ ዼጥሮስ ግን ስለ ትሕትና "አትስገድልኝ" አለው:: ከዚያም አፉን ከፍቶ ለእርሱና ለቤተሰቡ ከቅዱስ ቃሉ መገባቸው:: አጥምቆም እጁን ሲጭንባቸው ከቅዱስ መንፈሱ ተካፈሉ::

ከዚህች ዕለት በሁዋላም ቅዱስ ቆርኔሌዎስ ሃብቱን: ንብረቱን: ሹመቱንና ክብሩን ንቆ ሐዋርያትን ተከተላቸው:: ለስብከተ ወንጌል አገልግሎትም አንዲት በትር ብቻ ይዞ ወደ ምድረ ግብጽ ወረደ:: በዚያም ብዙዎችን ወደ ክርስትና ስቦ: ለዓመታት ተጋድሎ በዚህች ቀን ዐርፏል::

††† ቅዱስ አብድዩ ነቢይ †††

††† "አብድዩ" ማለት "የእግዚአብሔር አገልጋይ" ማለት ነው:: ቁጥሩ ከ12ቱ ደቂቀ ነቢያት ሲሆን የቅዱስ ኤልያስ ታላቁም ደቀ መዝሙር ነው:: ቅዱሳን ነቢያት ዮናስና ኤልሳዕም ባልንጀሮቹ ነበሩ::

ቅዱስ አብድዩ ቅድመ ልደተ ክርስቶስ በ800 ዓመት አካባቢ የከሃዲው ንጉሥ የጦር መሪ ሆኖ በሃምሳ አለቃነት አገልግሏል:: ግፈኛዋ ኤልዛቤል ነቢያተ እሥራኤልን ስታስፈጅ 50ውን በአንድ ዋሻ 50ውን ደግሞ በሌላ ዋሻ አድርጐ አትርፏቸዋል:: 900ው ግን ተጨፍጭፈዋል::

ያተረፋቸውንም ክፉ ዘመን እስኪያልፍ ድረስ መግቧቸዋል:: አክአብና ኤልዛቤል ከሞቱ በሁዋላም ቅዱስ ኤልያስን ተከትሎ ሹመቱን ትቷል:: እግዚአብሔር ገልጾለትም ትንቢት ሲናገር: ሕዝቡንም ሲገሥጽ ኑሯል::

በብሉይ ኪዳን ካሉ የትንቢት መጻሕፍትም በጣም አጭሩን የጻፈው ይሕ ነቢይ ነው:: ትንቢተ አብድዩ ባለ አንድ ምዕራፍ ብቻ ናትና:: ቅዱሱ በዚህች ቀን ዐርፎ ወገኖቹ ቀብረውታል::

††† አምላከ ነቢያት ወሐዋርያት የበረከትና የሰላም ዘመንን ያምጣልን:: ከበረከታቸውም ይክፈለን::

††† ኅዳር 23 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ ቆርኔሌዎስ (ሐዋርያዊ ጻድቅ)
2.ቅዱስ አብድዩ ነቢይ

††† ወርኀዊ በዓላት
1.ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት
2.ቅዱስ ጊዮርጊስ ሊቀ ሰማዕታት
3.ነቢየ ጽድቅ ቅዱስ ሰሎሞን (ንጉሠ እሥራኤል)
4.አባ ጢሞቴዎስ ገዳማዊ
5.ቅዱስ ዳንኤል ነቢይ
6.አባ ሳሙኤል
7.አባ ስምዖን
8.አባ ገብርኤል

††† "በተሰነጠቀ ዓለት ውስጥ የምትኖር: ማደሪያህንም ከፍ ከፍ ያደረግህ: በልብህም:- 'ወደ ምድር የሚያወርደኝ ማን ነው?' የምትል አንተ ሆይ! የልብህ ትዕቢት አታልሎሃል:: እንደ ንስር መጥቀህ ብትወጣ: ቤትህም በከዋክብት መካከል ቢሆን: 'ከዚያ አወርድሃለሁ' ይላል እግዚአብሔር::" †††
(አብድዩ 1:3)

🌹✞ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ✞🌹
(ይህ የቴሌግራም ቻናላችን ነው ይቀላቀሉን)
               🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

30 Nov, 17:13


† ስንክሳር ኅዳር 22 †

ኅዳር 22 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱሳን ቆዝሞስ ወድምያኖስ (ሰማዕታት)
2.ቅድስት ቴዎዳዳ (እናታቸው)
3.ቅዱሳን አንቲቆስ: ዮንዲኖስና አብራንዮስ (ወንድሞቻቸው)
4."311" ሰማዕታት (የነ ቆዝሞስ ማኅበር)

††† ወርኀዊ በዓላት
1.ቅዱስ ዑራኤል ሊቀ መላእክት
2.ቅዱስ ደቅስዮስ (የእመቤታችን ወዳጅ)
3.አባ እንጦንስ አበ መነኮሳት
4.አባ ጳውሊ የዋህ
5.ቅዱስ ዮልዮስ ሰማዕት
6.ቅዱስ ሉቃስ ወንጌላዊ ሐዋርያ

††† "ልጆች ሆይ እናንተ ከእግዚአብሔር ናችሁ:: አሸንፋችሁአቸውማል:: በዓለም ካለው ይልቅ በእናንተ ያለው ታላቅ ነውና:: እነርሱ ከዓለም ናቸው:: ስለዚህ ከዓለም የሆነውን ይናገራሉ:: ዓለሙም ይሰማቸዋል:: እኛ ከእግዚአብሔር ነን:: እግዚአብሔርን የሚያውቅ ይሰማናል:: ከእግዚአብሔር ያልሆነ አይሰማንም::" †††
(፩ዮሐ. ፬፥፬)

✍️† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †✍️
               🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

29 Nov, 18:11


🌿"ጽዮን ማርያም"🌿

​​እንኳን ለጽዮን "ማርያም ማሕደረ አምላክ"  ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ

"ጽዮን ማርያም"

"ጽዮን" ማለት "ጸወን - አምባ - መጠጊያ" ማለት ነው:: አንድም በምሥጢሩ "ማሕደረ አምላክ" ማለት ነው:: ጽዮን የሚለው ስም በቁሙ ለቅዱስ ዳዊት ተራራና ለኪዳኑ ጽላት ሲያገለግል በትንቢታዊ ምሥጢሩ ግን ለድንግል ማርያም: ለቤተ ክርስቲያንና ለዘለዓለማዊት ርስት ያገለግላል

እግዚአብሔር ከዘመነ አበው በኋላ በጊዜው ለእሥራኤላውያን ክብር: ሞገስ: አምባ የምትሆናቸውን ታቦተ ጽዮንን በቅዱስ ሙሴ አማካኝነት ሰጥቷቸዋል:: (ዘጸ. 31:18) ከዚያም ለ500 ዓመታት ከእነሱ ጋር በመሆኗ በፈጣሪና በእነሱ መካከል ድልድይ ሆና ኖራለች

ከዚያም ባለቤቱ ሲፈቅድ በዘመነ ሳባ: በቀዳማዊ ምኒልክ (እብነ መለክ-እብነ ሐኪም) አማካኝነት ወደ ኢትዮዽያ መጥታለች:: እነሆ በሃገራችን የ3ሺ ዓመት ቆይታዋን ልትደፍን የቀራት ጥቂት ዓመታት ብቻ ናቸው:: ጌታ እንደ ፈቀደ ቅዱስ መስቀሉንና ታቦተ ጽዮንን ይዘን ይሔው በቸርነቱ እንኖራለን

ያም ሆኖ ታቦተ ጽዮንን መስረቅ የሚፈልጉ ብዙ ቀሳጢዎች እንዳሉ እናውቃለን:: ግን አንጨነቅም:: ምክንያቱም የመጣችውም: የምትጠበቀውም በፈቃደ እግዚአብሔር ነውና እንጸልያለን እንጂ አንጨነቅም:: በተለያየ ወሬም ራሳችንን አናማጥንም:: ባለቤቱ እንድትሔድ ከፈቀደ ደግሞ ማንም ጉልበተኛ አያስቀራትም።

ታቦተ ጽዮን ብዙ ጊዜ "ጽላተ ኪዳን: ታቦተ ሕጉ" እየተባለች ትጠራለች::
"ጽሌ" ማለት "ሰሌዳ" እንደ ማለት ሲሆን "ጽላት" ደግሞ በብዙ ቁጥር ነው:: "ኪዳን" ደግሞ በፈጣሪና በሰው ልጆች መካከል ያለ "ውል - ስምምነት" ነው::

"ታቦት" ማለት "ማሕደር-ማደሪያ" እንደ ማለት ነው:: ሕጉ የተጻፈባቸውን ሰላድው "ጽላት" ስንላቸው የጽላቱ ማደሪያ ደግሞ "ታቦት" ይባላል:: ጽላት (ታቦትን) ያመጣ ፈጣሪ ነው:: በሐዲስ ኪዳንም ምሥጢርና ሐተታ ቢኖረውም 2 ቦታ ላይ ስለ ታቦት ተጠቅሶ እናገኛለን:: (2ቆሮ. 6:16, ራዕይ. 11:19)

በመጨረሻም_ኅዳር_21 ቀን ጽዮን ማርያምን የምናከብርባቸውን ምክንያቶች ስንመለከት:: በዚህች ቀን:-

1. ታቦተ ጽዮን (ጽላተ ኪዳን) ለሊቀ ነቢያት ቅዱስ ሙሴ መሰጠቷን እናስባለን:: ይሕ ሲሆንም ቅዱስ ሙሴ 40 መዓልት: 40 ሌሊት ጾሞ እንደ ተቀበለ ሳንዘነጋ ማለት ነው:: (ዘጸ. 31:18, ዘዳ. 9:19)

2. በዘመነ ኤሊ ሊቀ ካህናት ታቦተ ጽዮን በታሪኩዋ ለመጀመሪያ ጊዜ በአሕዛብ (ኢሎፍላውያን) እጅ ተማርካለች:: ግን ደግሞ ዳጐንን ቀጥቅጣዋለች:: (1ሳሙ. 5:1)

3. በዘመነ ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት በአሚናዳብ ሠረገላ ሁና: ከአቢዳራ ቤት ስትመጣ ቅዱሱ ንጉሥ በታላቅ ሐሴት በፊቷ ዘመረ: አገለገለ:: ምድራዊ ክብሩን እስኪረሳ ድረስ ለታቦተ አምላክ ተቀኘላት:: በዚህም ሜልኮል ንቃው ማሕጸኗ ተዘግቷል:: (1ዜና. 15:25) ሊቃውንትም "ድንግል እመቤታችን ማርያም በትንቢት መነጽር ተመልክቷል" ብለውናል

"ሰላም ለኪ ማርያም እምነ::
ዘሰመይናኪ ጸወነ::
ሶበ እምርሑቅ ርእየ ዘጽላሎትኪ ስነ::
ለቢሶ ዳዊት ልብሰ ክብር ዘየኀይድ ዓይነ::
ቅድመ ታቦተ ሕግ ኀለየ ወዓዲ ዘፈነ::" እንዲል:: (አርኬ ዘኅዳር 21)

4. በዘመነ ንጉሥ ሰሎሞን (መፍቀሬ ጥበብ) ግሩም የሆነ ቤተ መቅደስ ተሰርቶላት ስትገባ ታላቅ ሐሴት ተደርጉዋል:: እግዚአብሔርም በደመና ወርዶ ንጉሡን አነጋግሯል:: (2ዜና. 5:1, 1ነገ. 8:1)

5. በዚያው ዘመንም በፈጣሪ ፈቃድ ንጉሥ ምኒልክ ቀዳማዊ (ዕብነ ሐኪም) ታቦተ ጽዮንን ይዞ ወደ ኢትዮዽያ ገብቷል።

6. በዘመነ አፄ ባዜን (በ4 ዓ/ም አካባቢ) አማናዊት ጽዮን ድንግል ማርያም ወደ አክሱም ጽዮን በስደት መጥታ ገብታለች:: በዚህ ጊዜም 2ቱ ጽዮኖች ሲገናኙ ታላቅ ብርሃን አክሱምን ውጧታል።

7. በ4ኛው መቶ ክ/ዘመንም ነገሥት ጻድቃን አብርሐ ወአጽብሐ 12 መቅደሶች ያሏትን ግሩም ቤተ ክርስቲያን ለእመ ብርሃን ሠርተው በዚሁ ቀን በጌታችን ተቀድሷል።

8. በተጨማሪም በየጊዜው: ማለትም በዮዲት ጉዲትና በግራኝ አማካኝነት ስትፈርስ ወደ ዝዋይ ትሰደድ ነበር:: ተመልሳ ስትታነጽም ቅዳሴ ቤቷ የሚከበረው ኅዳር 21 ቀን ነው:: በእነዚህና በሌሎች ምክንያቶች ይህ በዓል ልዩ ነው::

" አማናዊት ጽዮን እመ ብርሃን ድንግል ማርያምን እንዲህ እንላታለን "

"ቅድስት" የሚለው ቃል ለሁሉም ቅዱሳት እናቶች ቢሰጥም ቅሉ ለድንግል ማርያም ሲሰጥ ግን ትርጉሙ ይለያል:: እርሷ "ቅድስተ ቅዱሳን: ንጽሕተ ንጹሐን: ቡርክት እምቡሩካን: ኅሪት እምኅሩያን" ናትና። ከሰው ልጆችም ሁሉ ትበልጣለች:: የሰው ልጅን ይቅርና ንጹሐን መላእክትንም በንጽሕናና በቅድስና ትበልጣቸዋለች:: እርሷ እመ ብርሃን: የአምላክ እናቱ: የሰውነታችን መመኪያ ናትና

#እመቤታችንን "#ቅድስት" ስንል "ጽንዕት: ንጽሕት: ክብርት: ልዩ" ማለታችን ነው

1. "ንጽሕት" ትባላለች:: ሌሎች ቅዱሳን ቢነጹ ከገቢር: ከነቢብ ኃጢአት ነው እንጂ ከኃልዮ ኃጢአት አይደለም:: እርሷ ግን ከነቢብ: ከገቢር: ከኃልዮ ንጽሕት ናት

"ኃጢአትን ከማሰብ መጠበቅ ከሰው ልጆች ለማን ተሰጠው: ይህስ ለመላእክትም አልተቻላቸውም" እንዲል:: (ተአምረ ማርያም)

2. "ጽንዕት" እንላታለን:: ሴቶች ቢጸኑ ለጊዜው ነው እንጂ በሁዋላ በጊዜው ተፈትሆ አለባቸው:: እመቤታችን ግን ቅድመ ጸኒስ: ጊዜ ጸኒስ: ድኅረ ጸኒስ: ቅድመ ወሊድ: ጊዜ ወሊድ: ድኅረ ወሊድ ድንግል ናትና።

¤ "ጽንዕት በድንግልና አልባቲ ሙስና" እንዳላት:: (ቅዱስ ያሬድ)
¤ ታላቁ ቅዱስ ባስልዮስም "ወትረ ድንግል ማርያም-ማርያም ዘለዓለማዊት ድንግል ናት" እንዳለ:: (መጽሐፈ ቅዳሴ)

3. ድንግልን "ክብርት" እንላታለን:: ሌሎች ሴቶች ቢከብሩ ጻድቃን ሰማዕታትን: ነቢያት ሐዋርያትን ወልደው ነው:: እመቤታችንን ግን የምናከብራት "ወላዲተ አምላክ-የአምላክ እናቱ" ብለን ነውና

4. እመቤታችንን "ልዩ" እንላታለን:: ከእርሷ በቀር እናት ሁና ድንግል: እመቤት ሁና አገልጋይ የሆነች: በድንግልና ወልዳ ወተትን (ሐሊበ ድንግልናዌን) ያስገኘች ሌላ ሴት የለችምና።

#ምንጭ ፦ ዝማሬ ዳዊት
✍️† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †✍️
               🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

29 Nov, 12:35


✞ ስንክሳር ኅዳር 21 ✞
እንኩዋን ለጽዮን "ማርያም ማሕደረ አምላክ" እና ለቅዱሳኑ "ጐርጐርዮስ ወዮሐንስ" ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ::

🙏  " ጽዮን ማርያም " 🙏

"ጽዮን" ማለት "ጸወን - አምባ - መጠጊያ" ማለት ነው:: አንድም በምሥጢሩ "ማሕደረ አምላክ" ማለት ነው:: ጽዮን የሚለው ስም በቁሙ ለቅዱስ ዳዊት ተራራና ለኪዳኑ ጽላት ሲያገለግል በትንቢታዊ ምሥጢሩ ግን ለድንግል ማርያም: ለቤተ ክርስቲያንና ለዘለዓለማዊት ርስት ያገለግላል::

እግዚአብሔር ከዘመነ አበው በሁዋላ በጊዜው ለእሥራኤላውያን ክብር: ሞገስ: አምባ የምትሆናቸውን ታቦተ ጽዮንን በቅዱስ ሙሴ አማካኝነት ሰጥቷቸዋል:: (ዘጸ. 31:18) ከዚያም ለ500 ዓመታት ከእነሱ ጋር በመሆኗ በፈጣሪና በእነሱ መካከል ድልድይ ሆና ኖራለች::

ከዚያም ባለቤቱ ሲፈቅድ በዘመነ ሳባ: በቀዳማዊ ምኒልክ (እብነ መለክ-እብነ ሐኪም) አማካኝነት ወደ ኢትዮዽያ መጥታለች:: እነሆ በሃገራችን የ3ሺ ዓመት ቆይታዋን ልትደፍን የቀራት ጥቂት ዓመታት ብቻ ናቸው:: ጌታ እንደ ፈቀደ ቅዱስ መስቀሉንና ታቦተ ጽዮንን ይዘን ይሔው በቸርነቱ እንኖራለን::

ያም ሆኖ ታቦተ ጽዮንን መስረቅ የሚፈልጉ ብዙ ቀሳጢዎች እንዳሉ እናውቃለን:: ግን አንጨነቅም:: ምክንያቱም የመጣችውም: የምትጠበቀውም በፈቃደ እግዚአብሔር ነውና እንጸልያለን እንጂ አንጨነቅም:: በተለያየ ወሬም ራሳችንን አናማጥንም:: ባለቤቱ እንድትሔድ ከፈቀደ ደግሞ ማንም ጉልበተኛ አያስቀራትም::

ታቦተ ጽዮን ብዙ ጊዜ "ጽላተ ኪዳን: ታቦተ ሕጉ" እየተባለች ትጠራለች:: "ጽሌ" ማለት "ሰሌዳ" እንደ ማለት ሲሆን "ጽላት" ደግሞ በብዙ ቁጥር ነው:: "ኪዳን" ደግሞ በፈጣሪና በሰው ልጆች መካከል ያለ "ውል - ስምምነት" ነው::

"ታቦት" ማለት "ማሕደር-ማደሪያ" እንደ ማለት ነው:: ሕጉ የተጻፈባቸውን ሰላድው "ጽላት" ስንላቸው የጽላቱ ማደሪያ ደግሞ "ታቦት" ይባላል:: ጽላት (ታቦትን) ያመጣ ፈጣሪ ነው:: በሐዲስ ኪዳንም ምሥጢርና ሐተታ ቢኖረውም 2 ቦታ ላይ ስለ ታቦት ተጠቅሶ እናገኛለን:: (2ቆሮ. 6:16, ራዕይ. 11:19)

በመጨረሻም ኅዳር 21 ቀን ጽዮን ማርያምን የምናከብርባቸውን ምክንያቶች እንመለከታለን:: በዚህች ቀን:-

👉 1.ታቦተ ጽዮን (ጽላተ ኪዳን) ለሊቀ ነቢያት ቅዱስ ሙሴ መሰጠቷን እናስባለን:: ይሕ ሲሆንም ቅዱስ ሙሴ 40 መዓልት: 40 ሌሊት ጾሞ እንደ ተቀበለ ሳንዘነጋ ማለት ነው:: (ዘጸ. 31:18, ዘዳ. 9:19)

👉 2.በዘመነ ኤሊ ሊቀ ካህናት ታቦተ ጽዮን በታሪኩዋ ለመጀመሪያ ጊዜ በአሕዛብ (ኢሎፍላውያን) እጅ ተማርካለች:: ግን ደግሞ ዳጐንን ቀጥቅጣዋለች:: (1ሳሙ. 5:1)

👉 3.በዘመነ ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት በአሚናዳብ ሠረገላ ሁና: ከአቢዳራ ቤት ስትመጣ ቅዱሱ ንጉሥ በታላቅ ሐሴት በፊቷ ዘመረ: አገለገለ:: ምድራዊ ክብሩን እስኪረሳ ድረስ ለታቦተ አምላክ ተቀኘላት:: በዚህም ሜልኮል ንቃው ማሕጸኗ ተዘግቷል:: (1ዜና. 15:25) ሊቃውንትም "ድንግል እመቤታችን ማርያም በትንቢት መነጽር ተመልክቷል" ብለውናል::

"ሰላም ለኪ ማርያም እምነ::
ዘሰመይናኪ ጸወነ::
ሶበ እምርሑቅ ርእየ ዘጽላሎትኪ ስነ::
ለቢሶ ዳዊት ልብሰ ክብር ዘየኀይድ ዓይነ::
ቅድመ ታቦተ ሕግ ኀለየ ወዓዲ ዘፈነ::" እንዲል:: (አርኬ ዘኅዳር 21)

👉 4.በዘመነ ንጉሥ ሰሎሞን (መፍቀሬ ጥበብ) ግሩም የሆነ ቤተ መቅደስ ተሰርቶላት ስትገባ ታላቅ ሐሴት ተደርጉዋል:: እግዚአብሔርም በደመና ወርዶ ንጉሡን አነጋግሯል:: (2ዜና. 5:1, 1ነገ. 8:1)

👉 5.በዚያው ዘመንም በፈጣሪ ፈቃድ ንጉሥ ምኒልክ ቀዳማዊ (ዕብነ ሐኪም) ታቦተ ጽዮንን ይዞ ወደ ኢትዮዽያ ገብቷል::

👉 6.በዘመነ አፄ ባዜን (በ4 ዓ/ም አካባቢ) አማናዊት ጽዮን ድንግል ማርያም ወደ አክሱም ጽዮን በስደት መጥታ ገብታለች:: በዚህ ጊዜም 2ቱ ጽዮኖች ሲገናኙ ታላቅ ብርሃን አክሱምን ውጧታል::

👉 7.በ4ኛው መቶ ክ/ዘመንም ነገሥት ጻድቃን አብርሐ ወአጽብሐ 12 መቅደሶች ያሏትን ግሩም ቤተ ክርስቲያን ለእመ ብርሃን ሠርተው በዚሁ ቀን በጌታችን ተቀድሷል::

👉 8.በተጨማሪም በየጊዜው: ማለትም በዮዲት ጉዲትና በግራኝ አማካኝነት ስትፈርስ ወደ ዝዋይ ትሰደድ ነበር:: ተመልሳ ስትታነጽም ቅዳሴ ቤቷ የሚከበረው ኅዳር 21 ቀን ነው:: በእነዚህና በሌሎች ምክንያቶች ይህ በዓል ልዩ ነው::

" አማናዊት ጽዮን እመ ብርሃን ድንግል ማርያምን እንዲህ እንላታለን "

"ቅድስት" የሚለው ቃል ለሁሉም ቅዱሳት እናቶች ቢሰጥም ቅሉ ለድንግል ማርያም ሲሰጥ ግን ትርጉሙ ይለያል:: እርሷ "ቅድስተ ቅዱሳን: ንጽሕተ ንጹሐን: ቡርክት እምቡሩካን: ኅሪት እምኅሩያን" ናትና::

ከሰው ልጆችም ሁሉ ትበልጣለች:: ይቅርና የሰው ልጅን ንጹሐን መላእክትንም በንጽሕናና በቅድስና ትበልጣቸዋለች:: እርሷ እመ ብርሃን: የአምላክ እናቱ: የሰውነታችን መመኪያ ናትና::

እመቤታችንን "ቅድስት" ስንል "ጽንዕት: ንጽሕት: ክብርት: ልዩ" ማለታችን ነው::

🌿 1."ንጽሕት" ትባላለች:: ሌሎች ቅዱሳን ቢነጹ ከገቢር: ከነቢብ ኃጢአት ነው እንጂ ከኃልዮ ኃጢአት አይደለም:: እርሷ ግን ከነቢብ: ከገቢር: ከኃልዮ ንጽሕት ናት::

"ለመኑ ተውኅቦ ተደንግሎ ኅሊና: ለመላእክትሂ ኢተክህሎሙ-ኃጢአትን ከማሰብ መጠበቅ ከሰው ልጆች ለማን ተሰጠው: ይህስ ለመላእክትም አልተቻላቸውም" እንዲል:: (ተአምረ ማርያም)

🌿 2."ጽንዕት" እንላታለን:: ሴቶች ቢጸኑ ለጊዜው ነው እንጂ በሁዋላ በጊዜው ተፈትሆ አለባቸው:: እመቤታችን ግን ቅድመ ጸኒስ: ጊዜ ጸኒስ: ድኅረ ጸኒስ: ቅድመ ወሊድ: ጊዜ ወሊድ: ድኅረ ወሊድ ድንግል ናትና::

¤"ጽንዕት በድንግልና አልባቲ ሙስና" እንዳላት:: (ቅዱስ ያሬድ)
¤ታላቁ ቅዱስ ባስልዮስም "ወትረ ድንግል ማርያም-ማርያም ዘለዓለማዊት ድንግል ናት" እንዳለ:: (መጽሐፈ ቅዳሴ)

🌿 3.ድንግልን "ክብርት" እንላታለን:: ሌሎች ሴቶች ቢከብሩ ጻድቃን ሰማዕታትን: ነቢያት ሐዋርያትን ወልደው ነው:: እመቤታችንን ግን የምናከብራት "ወላዲተ አምላክ-የአምላክ እናቱ" ብለን ነውና::

🌿 4.እመቤታችንን "ልዩ" እንላታለን:: ከእርሷ በቀር እናት ሁና ድንግል: እመቤት ሁና አገልጋይ የሆነች: በድንግልና ወልዳ ወተትን (ሐሊበ ድንግልናዌን) ያስገኘች ሌላ ሴት የለችምና::

አምላከ ቅዱሳን የአማናዊት ጽዮን ድንግል ማርያምን ጣዕሟን ፍቅሯን: ጸጋ በረከቷን ያሳድርብን:: ከአበው በረከትም አይለየን::

ኅዳር 21 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅድስት ጽዮን ድንግል ማርያም
2.ቅዱስ ጐርጐርዮስ ዘሮሜ
3.ቅዱስ ዮሐንስ ዘአስዩጥ
4.ቅዱስ ቆዝሞስ ሊቀ ዻዻሳት
5.ቅድስት ዲቦራ ዘድልበት
6.ቅዱስ ዘኬዎስ ሐጺር

ወርኀዊ በዓላት
1.አበው ጎርጎርዮሳት
2.አቡነ ምዕመነ ድንግል
3.አቡነ አምደ ሥላሴ
4.አባ አሮን ሶርያዊ
5.አባ መርትያኖስ ጻድቅ

✍️† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †✍️
               🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

29 Nov, 05:02


🙏 ስንክሳር ኅዳር 20 🙏

✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞

✞ እንኩዋን ለኃያል ሰማዕት "ማር ቴዎድሮስ" እና "ቅዱስ አንያኖስ" ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞

🌿" ቅዱስ ቴዎድሮስ ማር ሰማዕት +"🌿

በቤተ ክርስቲያን የሰማዕታት አለቅነት ከተሰጣቸው ሰማዕታት አንዱ የሆነው ማር ቴዎድሮስ የተወለደው በምድረ አንጾኪያ (ሶርያ) በ3ኛው መቶ ክ/ዘ ነው:: አባቱ ዮሐንስ በትውልድ ግብጻዊ የሆነ ክርስቲያን ነው:: እናቱ ግን አስቸጋሪና ጣዖት አምላኪ ሶርያዊት ነበረች::

ባልና ሚስት አብረው ሲኖሩ ሚስት ባሏ ክርስቲያን መሆኑን አታውቅም ነበር:: ቴዎድሮስ (የእግዚአብሔር ስጦታ ማለት ነው) በተወለደ ጊዜ ግን ጠብ ተነሳ:: እሱ ክርስትና ለማስነሳት: ሚስት ደግሞ ወደ ጣዖት ቤት ለመውሰድ ተጋጩ:: ሚስት ወገኖቿ ባለስልጣኖች ናቸውና ልጁን ቀምታ ባሏን ዮሐንስን ወደ ግብፅ አሳደደችው::

ዮሐንስ በስደት ባለበት ሃገር ስለ ልጁ ፈጽሞ ይጸልይ: ያለቅስም ገባ:: እግዚአብሔር ደግሞ ልመናውን ሰማ:: ማር ቴዎድሮስ ወጣት በሆነ ጊዜ ማንም ሳይጠራው ወደ ቤተ ክርስቲያን ሔዶ ተማረ: ተጠመቀ:: ዕለት ዕለትም ጾምና ጸሎትን ከምጽዋት ጋር ያበዛ: ድንግልናውን ለመጠበቅ ይተጋ ነበር::

በዛው ልክ ደግሞ ገና በ20 ዓመቱ በጉልበቱ ኃያል: በውበቱም ደመ ግቡ: በጠባዩም ገራገር ነበርና ተወዳጅ ነበር:: ነገሥታቱም የአንጾኪያ የጦር ሠራዊት አለቃ አድርገው ሾሙት:: እነሆ እስከ ዛሬ "የሠራዊት አለቃ" ተብሎ ይጠራል::

ማር ቴዎድሮስ በተሳተፈባቸው ጦርነቶች ሁሉ ተሸንፎ አያውቅም:: ይልቁኑ የነገሥታቱን (የጠላት) ልጆች በመማረክ ነው የሚታወቀው:: እንዲያውም አንድ ጊዜ ከአሕዛብ ጋር በተደረገ ጦርነት ብቻውን አሸንፏቸዋል::

የፋርስ ሰዎች ሊዋጉ ሲመጡ መልአክ ከሰማይ ወርዶ ሰይፍ ሰጠው:: ፋርሶችን "በከንቱ ከምትጠፉ ወደ ሃገራችሁ ተመለሱ" አላቸው:: እነርሱ ግን ተሳለቁበት:: ከፈረሱ ወርዶ ወደ ምስራቅ ዙሮ ጸልዮ በመስቀል አማተበ:: በመካከላቸው ገብቶም በመልአኩ ሰይፍ ለወሬ ነጋሪ ሳያስቀር አጠፋቸው::

አንድ ቀን ወደ አንድ ከተማ ቢገባ ዘንዶ ሲመለክ አገኘ:: ይባስ ብሎ የአንዲት ክርስቲያን ልጆችን ለመስዋዕትነት ሲያቀርበቧቸው ተመለከተ:: በስመ ሥላሴ አማትቦ: በፈረሱ ላይም ተቀምጦ ዘንዶውን በጦር ገደለው:: የዘንዶውም ርዝመት 24 ክንድ ነበር::

ከነገር ሁሉ በሁዋላ ቅዱስ ቴዎድሮስ ስለ አባቱ ወሬ ሰምቶ: ካለበት ሥፍራ አፈላልጎ አግኝቶ ደስ አሰኘው:: እስኪያርፍ አብሮት ቆይቶ: ቀብሮት ወደ አንጾኪያ ሲመለስ ግን የሚያሳዝን ነገር ጠበቀው::

ክርስቶስ ተክዶ: ጣዖት ቁሞ: አብያተ ክርስቲያናት ተቃጥለው: የክርስቲያኖች ደም ፈሶ: ከተማዋ በግፍ ተሞልታ ተመለከተ:: እርሱም በዚያች ሰዓት መወሰን ነበረበትና አደረገው:: የሁሉ ሠራዊት አለቃ ቢሆንም የክብር ልብሱን አውልቆ: ባጭር ታጥቆ በንጉሡ ዲዮቅልጢያኖስ ፊት ቆመ::

ማር ቴዎድሮስ በአደባባይ እንዲህ ተናገረ:- "አንሰ አመልኮ ለክርስቶስ ንጉሠ ስብሐት በኩሉ ልብየ: ወእሠውዕ ሎቱ - እኔስ የክብር ባለቤት ክርስቶስን በፍጹም ልቤ አመልከዋለሁ: ለእርሱም ብቻ እሠዋለሁ::" ንጉሡ በቁጣ መሬት ላይ ጥለው እንዲደበድቡት አዘዘ:: ወታደሮቹ ደሙ እስኪንጠፈጠፍ ገረፉት::

በብዙ መክፈልተ ኩነኔ አሰቃይተው በእሳት አቃጠሉት:: እርሱ ግን በጸሎቱ እሳቱን ውሃ አደረገው:: ወታደሮቹ እርሱን በብዙ አሰቃዩ:: እርሱ ግን በእግዚአብሔር ኃይል ጸና: ታገሠ::

በመጨረሻም ጌታችን በግርማ ወርዶ "ወዳጄ ቴዎድሮስ ስምህን የጠራ: መታሠቢያህን ያደረገ: ገድልህን (ዜናህን) የጻፈ: ያጻፈ: ያነበበ: ገዝቶ በቤቱ ውስጥ ያኖረውን ሁሉ
እምርልሃለሁ" አለው::

በስሙም ረድኤት እንደሚደረግ ነግሮት ዐረገ:: ወታደሮቹም በዚህ ቀን አንገቱን ሰይፈው የክብር አክሊልን ተቀብሏል:: እጅግ ብዙ ሺህ ሰዎችም አብረውት ተሰይፈዋል::

🌿" ቅዱስ አንያኖስ ዘግብጽ "🌿

ይህ ቅዱስ አባት ውለታው ከፍ ያለ ነውና በምድረ ግብጽ እጅግ ይከበራል:: በተለይ ክርስትናን ከሐዋርያት ተቀብሎ ለምዕመናን ያስረከበ አባት በመሆኑ ልዩ ቦታ ይሰጠዋል:: ይህስ እንደ ምን ነው ቢሉ:-

ወንጌላዊው ሐዋርያ ቅዱስ ማርቆስ በሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ ዼጥሮስ ተመድቦ: በፈቃደ እግዚአብሔር ወንጌልን ይሰብክ ዘንድ በ50ዎቹ ዓ/ም አካባቢ ወደ ምድረ ግብጽ ወረደ::

እስክንድርያ ከተማ በሜዲትራኒያን ባሕር ዳርቻ እንደ መኖሯም መጀመሪያ ወደ እርሷ ደረሰ:: ልክ ወደ ከተማ ሲገባ ገና አንደበቱ ለወንጌል ሳይከፈት እንቅፋት መትቶት ጫማው ተበጠሰ:: ያን ሁሉ በርሃ የቻለች ጫማ በእንቅፋት በመበጠሷ እያዘነ ወደ ጫማ ሰፊ ዘንድ ደርሶ "ሥራልኝ?" ይለዋል::

ይህ ጫማ ሰፊ አንያኖስ (አንያኑ) ይባላል:: ጣዖት አምላኪ: ግን ደግሞ ቅንና ገር የሆነ ሰው ነበር:: "እሺ" ብሎ ሲሰፋለት መሳፈቻው (መስፊያው) ስቶ መሐል እጣቱን ስለ ወጋው "ኢታስታኦስ (አታኦስ)" ብሎ ጮኸ:: ትርጉሙም "አንድ አምላክ" ማለት ነበር::

ይህንን የሰማው ቅዱስ ማርቆስ ቀና ብሎ "ጌታየ ሆይ! ጐዳናየን ስላቀናህልኝ አመሰግንሃለሁ!" ብሎ: ምራቁን እትፍ ብሎ በጭቃ የአንያኖስን እጅ ቀባው::

ወዲያውም ደሙ ቁሞ: ቁስሉም ድኖ እንደ ነበረው ሆነ:: በዚህ ተአምር ድንጋጤም: ደስታም ቢሰማው "ማነህ አንተ?" ሲል ቅዱሱን ጠየቀው:: ወንጌላዊውም መልሶ "እኔ የክርስቶስ ሐዋርያ ነኝ" አለው::

አንያኖስም "እባክህ ወደ ቤቴ እንሒድ" ብሎ ሐዋርያውን ጋበዘው:: እቤት ሲደርሱም ከሚስቱና ከልጆቹ ጋር አስተናግደውት የሕይወትን ቃል ለመኑት:: ቅዱስ ማርቆስም ከስነ ፍጥረት እስከ ጌታችን የማዳን ሥራ አስተምሯቸው አመኑ:: አጥምቆ ሥጋውን ደሙን አቀበላቸው::

ይህቺው የቅዱስ አንያኖስ ቤትም በምድረ ግብጽ የመጀመሪያዋ ጉባኤ ቤትና ቤተ ክርስቲያን ሆነች:: ቅዱሱ ሐዋርያ በ60 ዓ/ም አካባቢ በቅዱስ አንያኑ ቤት ሆኖ በርካቶችን አሳመነ:: በሰማዕትነት ከማረፉ በፊትም ቅዱስ አንያኖስን የምድረ ግብጽ ሁሉ ሊቀ ዻዻሳት (ፓትርያርክ) አድርጐ ሾመው::

ቅዱስ አንያኖስም ለ12 ዓመታት የክርስቶስን መንጋ እያበዛ ተጋደለ:: ከሐዋርያው የተቀበለውን ንጹሕ ዘር ዘራ:: የድኅነት የምሥራቹንም አዳረሰ:: ይሔው ይህ መልካም ተክል ዛሬም ድረስ ሳይጠወልግ አለ::

የአሁኑ ፓትርያርክ አቡነ ታውድሮስም ከቅዱስ ማርቆስ 118ኛ ሲሆኑ ከቅዱስ አንያኖስ 117ኛ ናቸው:: ቅዱሱ ለእኛ ኢትዮዽያውያንም የክህነት አባታችን ነው:: ይህች ቀንም ዕለተ ዕረፍቱ ናት::

አምላከ ቅዱሳን ክፉውን አርቆ ከበጐው ዘመን ያድርሰን:: ከበረከታቸውም ይክፈለን::

ኅዳር 20 ቀን የሚከበሩ
👉  ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ማር ቴዎድሮስ ኃያል ሰማዕት
2.ቅዱስ አንያኖስ (አንያኑ)

👉 ወርኀዊ በዓላት
1..ቅዱስ ዮሐንስ ሐፂር
2.ቅዱስ አክሎግ ቀሲስ
3.ቅዱስ አፄ ካሌብ ጻድቅ (ንጉሠ ኢትዮዽያ)
4.አባ አሞንዮስ ዘሃገረ ቶና
5.ቅድስት ሳድዥ የዋሒት ያድርጉ

🌹✞ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ✞🌹
               🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

28 Nov, 03:08


🙏† ስንክሳር ኅዳር 19 †🙏

እንኳን ለቅዱሳን ሰማዕታት ሰርጊስ ወቴዎፍሎስ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን።

† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †

🌿††† ቅዱሳን ባኮስ ወሰርጊስ †††🌿

† ሰማዕትነት በክርስትና ለሃይማኖት የሚከፈል የመጨረሻው ዋጋ (መስዋዕትነት) ነው:: ሰው ለፈጣሪው ሰውነቱን ሊያስገዛ: ሃብት ንብረቱን ሊሰጥ ይችላል:: ከስጦታ በላይ ታላቅ ስጦታ ግን ራስን አሳልፎ መስጠት ነው::

ራስን መስጠት በትዳርም ሆነ በምናኔ ውስጥ ይቻላል:: የመጨረሻ ደረጃው ግን ሰማዕትነት ነው:: "አማን መነኑ ሰማዕት ጣዕማ ለዝ ዓለም: ወተዓገሡ ሞተ መሪረ በእንተ መንግስተ ሰማያት" እንዳለው ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ ሰማዕትነት ማለት መራራውን ሞት ስለ ፍቅረ እግዚአብሔር ሲሉ መታገስ ነው::

እርሱ ቅሉ መድኃኒታችን ክርስቶስ የሰማይና የምድር ጌታ ሲሆን ኃፍረተ መስቀልን ታግሦ ሙቶልን የለ! በዓለም ያሉ ብዙ እምነቶች ስለ መግደል በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ያስተምራሉ:: ክርስትና ግን መሞትን እንጂ መግደልን የሚመለከት ሕግ የለውም::

እርሱ ባለቤቱ "ጠላቶቻችሁን ውደዱ:: የሚረግሟችሁን መርቁ:: ስለሚያሳድዷችሁ ጸልዩ::" ብሎናልና:: (ማቴ. 5:44) ነገር ግን ዕለት ዕለት ራሳችንን በሃይማኖትና በምግባር ካልኮተኮትነው ክርስትና በአንድ ጀምበር ፍጹም የሚኮንበት እምነት አይደለምና በፈተና መውደቅ ይመጣል::

በተለይ የዘመኑ ክርስቲያን ወጣቶች ልናስተውል ይገባናል:: የቀደሙ ወጣት ሰማዕታት ዜና የሚነገረን እንድንጸና ነውና:: እስኪ ለዛሬ ደግሞ በአጭሩ የቅዱሳን ባኮስና ሰርጊስን ዜና እንካፈል::

እነዚህ ቅዱሳን የዘመነ ሰማዕታት ፍሬዎች ናቸው:: ባኮስ እና ሰርጊስ (ሰርግዮስ) ከልጅነት ጀምሮ ባልንጀሮች ናቸው:: በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን በሮም ግዛት ሥር መክስምያኖስና ዲዮቅልጢያኖስ እስከ ነገሡበት ዘመን ድረስ በአንጻሩም ቢሆን ሰላም ነበር::

ታዲያ በዚህ የሰላም ጊዜ ሁለቱ ቅዱሳን ሥራ አልፈቱም:: ጾምን: ጸሎትንና በጐ ምግባራትን ሁሉ ይከተሉ ነበር:: ለመከራ ዘመን ስንቅ የሚሆነን በሰላሙ ዘመን የተያዘ ስንቅ ነውና::

በዚያው አንጻር ደግሞ ሠርቶ መብላት ይገባልና ሥራ ሲፈልጉ መክስምያኖስ ሠራዊት መሰብሰብ ጀመረ:: እነርሱም ከሠራዊቱ ዘንድ ተቆጥረው የምድራዊ ንጉሥ ጭፍሮች ሆኑ:: በእርግጥ በዘመናችን ለክርስትና አይመቹም ከሚባልላቸው ሥራዎች አንዱ ውትድርና ነው::

ነገር ግን ብዙ ቅዱሳንን ስትመለከቷቸው ሙያቸው ይሔው ነበር:: ቅዱሳን ባኮስና ሰርጊስ ጊዜው የሰላምም ይሁን የጦርነት ይጾማሉ:: ይጸልያሉ:: ይመጸውታሉ:: እንዲህ እንዲህ እያሉም ዘመናት አለፉ::

ከቆይታ በኋላ ግን ሰይጣን ያደረበት ንጉሡ መክስምያኖስ ጣዖት አመለከ:: አዋጅም አውጥቶ ክርስቲያኖችን ያሰቃይ: ይገድልም ያዘ:: ቅዱሳኑ ይህንን ሲሰሙ አዘኑ::

ቁጭ ብለውም ተወያዩ:: በልባቸው ፍቅረ ክርስቶስ ይነድ ነበርና ወጣትነታቸው: መልካቸው: ተወዳጅነታቸው ሁሉ ሊያታልላቸው አልቻለም:: እንደ አንድ ልብ መካሪ: እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ ስለ ሃይማኖት ሊሰው ወሰኑ::

በማግስቱም ንጉሡ ወደ ሾመው የቅርብ አለቃቸው ቀረቡና "የምንነግርህ ነገር አለን" አሉት:: "እሺ" ሲላቸው በወገባቸው ያለውን የክብር መታጠቂያና የክብር ልብሳቸውን በፊቱ ወረወሩለትና "እኛ የክርስቶስ ጭፍሮች ነንና ከዚህ በኋላ ላንተ: ለጣዖት አምላኪው አንታዘዝም" አሉት::

መኮንኑ ነዶታልና አስገረፋቸው: አሳሰራቸው:: በረሃብና በጥም: በብዙ መክፈልተ ኩነኔም አሰቃያቸው:: እነርሱ ግን ጽኑዓን ነበሩና አልቻሏቸውም:: ጥቅምት 4 ቀን በሆነ ጊዜ ግን ሁለቱን ለያዩዋቸው:: ቅዱስ ባኮስን ለብቻው ወስደው ትልቅ ድንጋይ በአንገቱ ላይ አሠሩበትና ባሕር ውስጥ አሰጠሙት::

ነፍሱም ከስጋው ስትለይ ባሕር ወደ ዳር አስወጣችው:: በአካባቢውም "ባባ" እና "ማማ" የሚባሉ ባሕታውያን ነበሩና እግዚአብሔር እንዲገንዙት አዘዛቸው:: ሲሔዱም ቅዱስ ሥጋውን አንበሳና ተኩላ ሲጠብቁት አግኝተው: በታላቅ ዝማሬ ገንዘው: በራሳቸው ተሸክመው ወስደው: በበዓታቸው ውስጥ ቀበሩት::

ቅዱስ ሰርጊስን ደግሞ ለ6 ቀናት ካሠሩት በኋላ እጁንና እግሩን በእንጨት ላይ ቸንክረው: በእንስሳት ጭራ ላይ አስረው ሲጐትቱት ውለዋል:: አንገቱን በሰየፉት ጊዜም አንዲት ወጣት ደሙን ተቀብላ በረከትን አግኝታለች:: የመከራ ዘመን ካለፈ በኋላም ለቅዱሳኑ ቤተ ክርስቲያን ታንጾ በዚህች ቀን ተቀድሷል: ተአምራትም ታይተዋል::

††† ቅዱስ ቴዎፍሎስና ቤተሰቡ †††

††† ቅዱስ ቴዎፍሎስ በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን በሮም ግዛት ሥር ይኖር የነበረ ጽኑዕ ክርስቲያን ነው:: እግዚአብሔር ሲያድለው ደግሞ ጸንታ የምታጸና: በርትታ የምታበረታ ሚስትን ሰጠው:: ስሟም ጰጥሪቃ ይባላል::

በክርስትናዋና በፈጣሪዋ ፍቅር ላይ ይሉኝታና ድርድርን የማታውቅ ብርቱ ሴት ናት:: ሁለቱ ተጋብተው በሕጉና በሥርዓቱ ሲኖሩ እግዚአብሔር በረድኤት ጐበኛቸውና ቅድስት ጰጥሪቃ ጸነሰች:: በወለደችውም ጊዜ "ደማሊስ" ስትል በሃገራቸው ልሳን ስም አወጣችለት::

ልክ ግን ከአራስነት አልጋዋ በተነሳችበት ወራት ያ የመከራ ዘመን (ዘመነ ሰማዕታት) ድንገት ደረሰ:: እሷም አካሏ አልጸናም: ልጇም ገና 5 ወሩ ነው:: ባሏ ቅዱስ ቴዎፍሎስ ደግሞ በጨካኙ ንጉሥ እጅ መውደቁን (መታሠሩን) ሰማች::

ይኼ እጅግ ከባድ ፈተና ቢመስልም እርሷ ግን ልጇን አዝላ ወደ እሥር ቤት ሔደች:: ባሏንም "ወንድሜ! እኔና ልጅህን በክርስቶስ ዘንድ ስለምታገኘን ጽና:: ክብርህን እንዳትተው" አለችው:: እርሱም ደስ ብሎት ብዙ መከራን ተቀበለ::

ግርፋቱ: እሳቱ ስለቱ ሁሉ ሲያልፍበት በተአምራቱ አሕዛብን ማረከ:: ቅዱስ መልአክም ከሰማይ ወርዶ ማርና ወተትን መገበው:: ከዚያም በዚህ ቀን ለአንበሳ ተሰጠ:: አንበሳውም ለቅዱሱ ሰግዶ: እግሩንም ስሞ: አንገቱን ተጭኖ ገደለው::

ወዲያው ሚስቱ ቅድስት ጰጥሪቃ ተይዛ እርሷም ከነ ልጇ ለአንበሳ ተሰጠች:: በዚህ ጊዜ የ5 ወር ሕጻን ቅዱስ ደማሊስ አፉን ከፍቶ "እኔስ በሥላሴ አምናለሁና አንበሳን አልፈራም" ሲል እየሳቀ ጮኸ:: ወዲያውም እናትና ልጅን አንበሳው ገደላቸው:: ቅዱሱ ቤተሰብም ለክብር በቃ::

††† አምላከ ሰማዕታት ጽንዐታቸውን: ትእግስታቸውንም ያድለን:: ከበረከታቸውም ይክፈለን::

††† ኅዳር 19 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ ሰርጊስ ሰማዕት
2.ቅዱስ ቴዎፍሎስ ሰማዕት
3.ቅዱሳን ጰጥሪቃና ደማሊስ (የቅዱሱ ሚስትና ልጅ)
4.ቅዱስ በርተሎሜዎስ ሐዋርያ (ልደቱ)

††† ወርሐዊ በዓላት
1.ቅዱስ ገብርኤል ሊቀ መላእክት
2.ቅዱስ ኤስድሮስ ሰማዕት
3.አቡነ ዓቢየ እግዚእ ጻድቅ
4.አቡነ ስነ ኢየሱስ
5.አቡነ ዮሴፍ ብርሃነ ዓለም
6.ቅዱስ ይምርሐነ ክርስቶስ

† "እግዚአብሔር ለኛ የሰማዕትነትን ሥራ ይሰጠን ዘንድ ቅዱሳን ስለሚሆኑ ሰማዕታት እንማልዳለን::" †
(ሥርዓተ ቅዳሴ ቁ. ፸፫)

✍️† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †✍️
🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
https://t.me/Sinksar
https://t.me/Sinksar
https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

27 Nov, 15:28


#ጤና!

የአለም ጤና ድርጅት አንድ ሰው ጤናማ ነው ከሚያስብሉት ነገሮች ዋነኞቹ ብሎ ከጠቀሳቸው አካታች ሰብዓዊ መሻቶች በዋናነት ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊ፣ አካላዊ፣ ሰዎች ለሰዎች ያላቸው ጤናማ መስተጋብራዊ መዋቅሮች (ማኅበረሰባዊ) ጤንነቶች ከፊት ይሰለፋሉ።

አብሮነት፣ ማኅበራዊ እሴት እና ግብረ ገብነት የሚባሉ እውነቶች በተግባር ከማየት ከሚያርቁብን ዋነኞቹ ምክንያቶች ውስጥ አንዱ እንዲህ በሕይወት ዘመን በገንዘብ የማይለኩትን የአብሮነት ገመድ የሚበጥሱት አሰራሮችና መዋቅሮች ዋነኞቹ ናቸው።

ስንት ዘመን የመኖር አብሮነት ዋጋው በተመን አይለካም!

እነ እገሌ እና እንትና፣ ወይኔ ያ ደብር፣ ያ አገልጋይ፣ ያ ካህን፣ ያ ኅብረት ብሎ ለመናገር የተረጋጋ መንደር እና መግቢያ መውጫው የሚታወቅ ትውልድ ያስፈልገናል። ልቡ ከፈቀደ ዝም ብሎ የሚኖርን አንድ መንደርተኛ እንደ ሽማግሌ ገስጾ ከመጥፎ ጠባዩ(በተለምዶ ከባህሪው ) ለመለወጥ ልብ ለልብ መተዋወቅ ያሸዋል። ያለ መተዋወቅ የሚደረግ የኅብረት ጉዞ ከልብ በታች የታይታ ነው።
ስለዚህ በማኅበረሰቡ ዘንድ የአብሮነት ታሪክ እና ቅርስ በዋጋ በማይተመንበት ሁናቴ ሕዝብን በአግባቡ ማከም ብልህነት ነው።

ብዙ ሺህ የማኅበረሰብ ሳይንስ ሙህራን ባሉባት በዚህች ምስኪን ሀገር የሚደረግ ለውጥ አይሉት ነውጥ ጤናማ እንዲሆን ጸሎታችን እና ትግላችን ይሁን!

ይቆየን!

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

27 Nov, 14:29


ይህን የመጅሊሱን መግለጫ የሚያብራራልኝ አለ? ሁለት አንኳር ርዕሰ ጉዳዮች ግን በትኩረት መታየት ይገባቸዋል።

1 የአረብ ሊግ አባልነት ጉዳይ ሰፊ ትንታኔ የሚፈልግ ጥቅምና ጉዳቱ ተመዝኖ በባለሙያዎች ሃገራዊ ጥናት ተደርጎበት ወይስ በመጅሊሱ ደላላነት?

የአረብ ሊግ አባልነትን "ከሃይማኖት ጋር አታያይዙት" ቢባል እንኳን የሊጉ ጸሐፊ ወደ ኢትዮጵያ ለጉብኝት በመጡበት ወቅት ከመጅሊሱ አመራሮች ጋር የተወያዩት ምንድነው? ለምንስ ጥያቄው በሃይማኖት መሪዎቹ በኩል መጣ?

2 የዲፕሎማቶች ምደባን በተመለከተም የተነሳው የአካታችነትና የቁጥር ጥያቄ በመብትነት የተነሳ ወይስ ቀጣዩን እቅድ የሚያመላክት?

የሆነው ሆኖ የእኛው ሲኖዶስ በየሴክተሩ እንዲህ ያሉ ውይይቶች የሚያደርገው መቼ ነው?

ብርሃኑ ተክለያሬድ(ቀሲስ)

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

27 Nov, 05:15


በዕቅበተ እምነት ጥንቃቄ የሚሹ ተግባራት (ከብርሃኑ አድማስ ጽሑፍ በምኅጻር የተወሰደ)
በአማን ነጸረ
1.የዕቅበተ አምነትን ሁለት ዋና ዋና ጠባያት መረዳት፡-
(1) ሃይማኖት/እምነት ከአምላክ የተገለጠ እውነት መሆኑን ተረድቶ ማጽናትና (2) በእምነት የደከሙትን/የሳቱትን ሰዎች ራሳን እንደ ደጉ ሳምራዊ አድርጎ በርኅራኄ ቁስላቸውን አክሞ ለማዳን መፋጠን ሁለቱ የቅበተ እምነት መሠረታውያን ጠባዕያት ናቸው፡፡
--
2. በዕቅበተ እምነት ውስጥ የማይታለፉ ጉዳዮች፡-

(1)ዐቂበ እምነት፡- የሃይማኖትን ምንነት በቤተ ክርስቲያናዊ አስተምህሮ ላይ ተመሥርቶ መግለጥና ያንን የሚቃወም ስሑት ትምህርት በየዘመናቱ ሲመጣ ትምህርቱ የአባቶች አለመሆኑን ማሳየት፡፡

(2)እውነት ላይ ማተኮር፡- ዐቃቤ እምነት ትኩረቱ እውነት እንጂ አሸናፊነት አይደለም፣ ትኩረቱ ወደተሳሳተው አስተምህሮ እንጂ ወደተሳሳተው ግለሰብ አይደለም- ልክ መድኃኒት በሽታን እንጂ በሽተኛን ለማጥቃት እንደማይሰጠው፡፡

(3)አሳማኝነት፡- ጭብጥ አቀራረጹና አቀራረቡ ሐሳብን ሊያስተላልፍና የተለያየ ዕውቀትና ግንዛቤ ላላላቸው ሰዎች ተደራሽና ሰዎች ሐሳቡን ሊጋሩት በሚችል መልኩ ሆኖ መቅረብ አለበት፡፡

(4)ክርክርን በተገቢው መንገድ ማቅረብ፡- የዕቅበተ እምነት ሥራ ዐላማው አማኞችን ከመጠራጠር መጠበቅና የሔዱትን መመለስ እንደመሆኑ መጠን አቀራረቡ የሚያቀርቡትን ጭብጥ መረዳት (understanding)ንና ተደራስያን ሊረዱ በሚችሉበት ቋንቋ የማቅረብ አቅምን፣ ያልተድበሰበሰ ውሳኔን (judgment)ና የሚሟገታቸውን ሐሳቦች ስሑትነት የሚያሳይና የሚያቀርበውን ሐሳብ ከትችት ያራቀ አጠይቆት(reasoning)ን ማማከል ይገባዋል፡፡
--
3.የዕቅበተ እምነት ጸያፎች፡-

(1)ሐሰተኛ ትርጉም መስጠት (Proselytism)፡- ማለትም የምንሞግተውን ሐሳብ ተሞጋቹ በሚለው ሳይሆን እኛ በሰጠነው ትርጉም ሰይሞ ምላሽ ለማዘጋጀት መሞከር፡፡ ለምሳሌ፡- ኦርቶዶክሳውያን እመቤታችንን እናከብራታለን እንጂ አናመልካትም፡፡ ተቃዋሚዎች ግን ማክበራችንን ማምለክ ብለው ተርጉመው የዕቅበተ እምነት ሥራ ሠራን ይላሉ፡፡ በእኛም ቤት ካቶሊካውያን እመቤታችንን ኃይል አርያማዊት ይላሉ የሚል ልማድ ያገነነው ስሑት አበባል አለ፡፡ ይኼ ሐሰተኛ ትርጉም መስጠት ይባላል፡፡

(2)ሥነ ልቡናዊ ርግጠኝነት (Psychological Certainity)፡- የሰማዕያን/አንባብያንን ድክመት ተጠቅሞ የማያውቁትን ሐሳብ ወይም ቋንቋ ከዐውድ ውጪ በመውሰድ ለማሳመን መሞከር ነው፡፡ ምሳሌ፡- ኦርቶዶክሳውያን ለሥዕል የምንሰጠውን ክብር ዘፀ.20፡4 ላይ ያለውን ‹‹የተቀረጸውን ምስል ለአንተ አታድርግ›› የሚል ጥቅስ ተጠቅሞ ቅዱሳት ሥዕላትን ጣዖት አድርጎና የጥቅሱ መተርጎሚያ አድርጎ መጠቀም፡፡ ያላነበቡትን እንዳነበቡ፣ የማያውቁትን ግእዝ ወይም እንግሊዝኛ ወይም ደግሞ ሌላ ቋቋ የሚያውቁ መስሎ ለማሳመን መሞከርም በሰማዒው/አንባቢው ላይ የሥነ ልቡና ርግጠኝነትን ፈጥሮ ለመቀሰጥ ሙከራ የሚደረግበት የዕቅበተ እምነት ጸያፍ ነው፡፡

(3)መንሸራተት (Deviation)፡- ከጭብጥ መሸሽ ወይም ጭብጥን ለራስ በሚመች መልኩ ቀርጾ መዳከር፡፡

(4)ከአመክንዮ በተቃርኖ መቆም (Logical fallacy)፡- ምንም እንኳ ነገረ ሃይማኖት ከአመክንዮ ባሻገር ቢሆንም አንድን የፍሬ ነገር መለኪያ ለተለያየ መደምደሚያ መጠቀም፡፡ ምሳሌ፡- ተሐድሶዎች የደቂቀ እስጢፋስ ገድላት ላይ መፍቀርያነ ገድል መስለው ሲያበቁ በሌሎች ቅዱሳን ላይ ሲሆን የምናውቀውንና እዚህ የማንናገረውን ጸያፍ አንደበት እንደሚጠቀሙት፡፡

(5)ሁሉን ጠልነት (Negativism)፡- የሚቃወሙት ሰው/ቡድን የተናገረውን ሁሉ በጅምላ ማነወር፡፡ አውንታዊ ምሳሌ ብንጠቅስ፡- መልአከ ብርሃን አድማሱ ምላሽ የጻፉላቸው ሰዎች ትክክለኛ ነገር ሲጽፉ እንዳላዩ አያልፉም፤ እዚህ ላይ ትክክል ነህ ይላሉ፣ ሁሉን ጠል ስላልሆኑ፡፡

(6)አድሏዊነት (Inclination/Bias)፡- በአንድ ስሕተት የሚያውቁትን ሰው እንደሚሳሳት አስቦ ሥራዎቹን ማየት ወይም በስሕተት የወደቁ ሰዎችን በአካባቢ ወይም በተማሩበት ት/ቤት ፈርጆ ‹‹ወትሮስ ከዚያ የወጡ!›› እያሉ መፈረጅ ጸያፍ ነው፡፡
--
ምንጭ፡- አድማሱ ጀንበሬ፡ ሕይወቱ ወሐተታ መጻሕፍቱ፣ 2011፣ ገጽ 12-39 (በምኅፃር ተጨምቆ የቀረበ፡፡)

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

27 Nov, 03:04


https://www.youtube.com/watch?v=3SK5ly9CG5w

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

26 Nov, 18:24


✞ ስንክሳር ኅዳር 18 ✞
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡
እንኩዋን ለቅዱስ #ፊልዾስ_ሐዋርያ: ለቅዱስ #ኤላውትሮስ እና #ለደናግል_አጥራስስ_ወዮና ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ::

🙏 " ቅዱስ #ፊልዾስ_ሐዋርያ " 🙏

እንደ አባቶቻችን ትርጉም 'ፊልዾስ' ማለት '#መፍቀሬ_አኃው-#ወንድሞችን_የሚወድ' ማለት ሲሆን ከ12ቱ ቅዱሳን ሐዋርያት አንዱ ነው:: (ማቴ. 10:3) በዚህ ስም የሚጠራ ሐዋርያ ከ72ቱ አርድእት ውስጥ ነበር:: እርሱም ጃንደረባውን #ባኮስን ያጠመቀው ነው::

አንዳንዴ የ2ቱ ታሪክ ሲቀላቀል እንሰማለን:: ለሁሉም ይህኛው ቅዱስ ፊልዾስ ቁጥሩ ከ12ቱ ሐዋርያት ሆኖ ምሑራነ ኦሪት ከሚባሉትም አንዱ ነበር:: በወቅቱ ገማልያል የሚሉት ክቡርና ምሑረ ኦሪት በርካታ ምሑራነ ኦሪትን አፍርቶ ነበር::

እንደ ምሳሌም ቅዱሳኑን "ዻውሎስን: ኒቆዲሞስን: ናትናኤልን: እስጢፋኖስንና የዛሬውን ሐዋርያ ቅዱስ ፊልዾስን" መጥቀስ እንችላለን:: ቅዱስ ፊልዾስ ነገዱ ከእሥራኤል ሲሆን ተወልዶ ያደገው በቤተ ሳይዳ ነው:: ኦሪትን ተምሮ በመንገድ ዳር ቁጭ ብሎ 'መሲሕ ቀረ' እያለ ሲተክዝ ለስም አጠራሩ ጌትነት ይሁንና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ እርሱ ደረሰ::

ትክ ብሎ አይቶት "ተከተለኝ" አለው:: (ዮሐ. 1:44) ቅዱስ ፊልዾስም ያለ ማመንታት: ሁሉን ትቶ በመንኖ ጥሪት ተከተለው:: በዚህ ዓይነት ጥሪ መድኃኒታችን ቅዱስ ማቴዎስንም ጠርቶታል:: (ማቴ. 9:9) ቅዱስ ፊልዾስ ጌታን ከተከተለ በሁዋላ ሥራ አልፈታም:: ወዲያውኑ ሒዶ ለናትናኤል (ቀናተኛው ስምዖን) ሰበከለት እንጂ::

"ሙሴ በኦሪት: ነቢያትም የተነበዩለትን መሲሕን አግኝቸዋለሁ" አለው:: ይሕ አነጋገሩም ምሑረ ኦሪት እንደ ነበር በእርግጥ ያሳያል:: (ዮሐ. 1:46) ቅዱስ ናትናኤልም ምሑር ነውና "ከናዝሬት ደግ እንዴት ይወጣል?" ቢለው ቅዱስ ፊልዾስም መልሶ "ነዐ ትርአይ-ታይ ዘንድ ና" አለው::

ናትናኤልም ሒዶ በጌታ አመነ:: ቅዱስ ፊልዾስ አገልጋይ እንደ መሆኑ መጠን በዮሐንስ ወንጌል ተደጋግሞ ስሙ ተጠቅሷል:: በተለይ ደግሞ ጌታ የ5 ገበያ ሕዝብን አበርክቶ ሲመግብ አስቀድሞ ጥያቄ ቀርቦለት ነበር:: እርሱ ግን "ጌታ ሆይ! የ200 ዲናር እንጀራ ብንገዛም አንዘልቀውም" ብሎ ነበር::

በሁዋላ ግን የጌታን ድንቅ ተአምር ተመለከተ:: (ዮሐ. 6:5) በተለይ ደግሞ በሐዋርያት አበው መካከል ለጌታ እንደ እንደራሴ ሆኖ ያገለግል እንደ ነበርም ተጠቅሷል:: ሰዎች ጌታን ማግኘት ሲፈልጉ እሱና እንድርያስን ያናግሩ ነበር:: (ዮሐ. 12:20) አንድ ጊዜ ግን እስካሁን ሊቃውንትን የምታስደምም ጥያቄ ጠይቆ ነበር::

አጠያየቁ ደግሞ ፍጹም የዋሕ እንደ ሆነ ያሳያል:: ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ ባሕርይ አባቱ አብ እየነገራቸው ሳለ ቅዱስ ፊልዾስ ከመካከል ተነስቶ "እግዚኦ አርእነሁ ለአብ ወየአክለነ": ልክ ወልድን በዐይኑ እንዳየ ሁሉ አብን ሊያይ ቸኩሎ "አቤቱ ስለ አብ የሰማነው ይበቃልና አሳየን" ብሎታል:: (ዮሐ. 14:8)

ጌታችን ግን "ዘርእየ ኪያየ ርዕዮ ለአብ-እኔን ያየ አብን አይቷል" (ዮሐ.14:9) ብሎ ምሥጢረ ባሕርዩን: አንድነቱን ሦስትነቱን አስረድቶታል:: ቅዱስ ፊልዾስም ጌታን እስከ ሕማሙ አገልግሎ: ቅድስት ትንሳኤውን አይቶ: ለ40 ቀናት መጽሐፈ ኪዳንን: ትምሕርተ ኅቡዓትን ተምሮ: ቅዱስ መንፈሱን ከ72 ልሳን ጋር ነስቶ ለስብከተ ወንጌል ወጥቷል::

ቅዱሳን ሐዋርያት ዓለምን በእጣ ሲካፈሉ ለእርሱ አፍራቅያ (አፍሪካ) ደርሳዋለች:: ስለዚህም በምድረ አፍሪካ ወንጌልን ከሰበኩ ሐዋርያት አንዱ ነው:: በአፍራቅያና በቀድሞው የኃምስቱ አሕጉር ግዛት ድንቅ ድንቅ ተአምራትን አድርጐ ብዙዎችን ወደ መንጋው (ወደ ክርስትና በረት) ቀላቀለ::

ለበርካታ ዓመታትም በተለያዩ የዓለም ክፍሎች እየተዘዋወረ ወንጌልን ሲሰብክ: ብርሃነ ክርስቶስን ሲያበራ: ነፍሳትንም ሲማርክ ቆየ:: ገድለ ሐዋርያት እንደሚለው የቅዱስ ፊልዾስ ፍጻሜው በሰማዕትነት እንደ ሆነ ቢታወቅም የትኛው ሃገር ውስጥ እንደ ሆነ መለየት አልተቻለም::

ዜናው ግን እንዲህ ነው:- በአንዲት ሃገር ውስጥ ገብቶ ሰበከ:: ብዙዎችንም አሳመነ:: ያላመኑት ግን ይዘው አሰቃዩት: ገረፉት:: "በክርስቶስ እመኑ እባካችሁ!" እያለ እየለመናቸው ዘቅዝቀው ሰቅለው ገደሉት::

ከዚያም በእሳት እናቃጥላለን ሲሉ ቅዱስ መልአክ ከእጃቸው ነጥቆ ወደ ኢየሩሳሌም ወሰደው:: በዚህ የደነገጡት ገዳዮቹ ለ3 ቀናት ጾሙ: ተማለሉ:: በዚህ ምክንያት የቅዱሱ ሥጋ ተመልሶላቸው: ገንዘው ቀብረውት በክርስቶስ አምነዋል::

🙏+" ቅዱስ ኤላውትሮስ ሰማዕት "+🙏

ቅዱሱ ሰማዕትና ቅድስት እናቱ (እንትያ ትባላለች) የዘመነ ሰማዕታት ፍሬዎች ናቸው:: ቅድስት እንትያ መልካም እናት ናትና ቅዱስ ኤላውትሮስን በሃይማኖት በሥርዓት አሳደገችው:: በ17 ዓመቱ ዲቁናን ተሾመ:: በ18 ዓመቱ ቅስና: በ20 ዓመቱ ደግሞ ዽዽስናን ተሾመ::

ያን ጊዜ ሃገራቸው ሮም የግፍ ቦታ ነበረችና የቅዱሱ ዜና ሕይወት: ብርሃንነቱ: ስብከቱ: ንጹሕ ሕይወቱ በሃገረ ገዢው ዘንድ ተሰማ:: አንዱን መኮንን ጠርቶ "ሒድ አምጣው" አለው:: መኮንኑ ሲደርስ ቅዱስ ኤላውትሮስ እየሰበከ ነበርና በጣዕመ ስብከቱ ተማርኮ ከነ ተከታዮቹ አምኖ በዚያው ቀረ:: አገረ ገዢውም ሌላ መኮንን ልኮ አስመጣውና ቅዱሱን "ለምን የተሰቀለውን ታመልካለህ?" አለው::

ቅዱሱም መልሶ "ማስተዋል የተሳነህ! ቢገባህ ኑሮ የተቀለው እኮ ለእኔና ለአንተ ነው" አለው:: ሞት ተፈርዶበት ቅዱሱን ብዙ አሰቃይተው እሥር ቤት ሲጥሉት ርግብ መጥታ መገበችው::

እግሩን ቸንክረው በመንገድ ላይ ሲጐትቱት መልአክ ወርዶ ፈታው:: ወደ በርሃም ወሰደው:: ከጊዜያት በሁዋላ እንደ ገና ይዘው አምጥተው: ብዙ አሰቃይተው በዚህች ዕለት: ከእናቱ ቅድስት እንትያ ጋር በጦር እየወጉ ገድለዋቸዋል::

ሊቃውንትም የሰማዕታቱንና የሐዋርያውን ተጋድሎ እያደነቁ እንዲህ ጸልየዋል:- "ሰላም ለፊልዾስ ጽዑረ አባል በመቅሰፍት: ወለኤላውትሮስ ርጉዝ በብልኃ ኩናት: ምስለ እንትያ እባእ ኀበ ተርኅወ ገነት: ያሩጸኒ መዓዛሆሙ ወጼናሆሙ ዕፍረት:
ለዝ ሐዋርያ ወለዝ ሰማዕት::" (አርኬ)

አምላከ ቅዱሳን ስለ ወዳጆቹ ሲል ቸርነቱን: ምሕረቱን ይላክልን:: ከበረከታቸውም ይክፈለን::

🌿 ኅዳር 18 ቀን የሚከበሩ

ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ ፊልዾስ ሐዋርያ (ከ12ቱ)
2.ቅዱስ ኤላውትሮስና እናቱ እንትያ (ሰማዕታት)
3.ቅዱሳት ደናግል አጥራስስ ወዮና (ሰማዕታት)
4.ቅዱስ አትናቴዎስ የዋሕ

🌿ወርሐዊ በዓላት

1.አቡነ ኤዎስጣቴዎስ ረባን
2.አቡነ አኖሬዎስ ዓቢይ
3.ማር ያዕቆብ ግብጻዊ
4.ቅዱስ ያዕቆብ ሐዋርያ (ከ72ቱ አርድእት)

🌹✞ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ✞🌹
               🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

26 Nov, 18:03


https://www.youtube.com/watch?v=1t8-3PUBQqY

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

26 Nov, 05:52


  ስንክሳር ኅዳር 17 
እንኳን ለዓለም ሁሉ መምሕር ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ እና ቅድስት ወለተ ጴጥሮስ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን።

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

††† ለቤተ ክርስቲያን የብርሃን ምሰሶ ስለሆነላት ስለ ታላቁ ሐዋርያዊ ሊቅ ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ምን እላለሁ? ምንስ እናገራለሁ? እንደ እኔ ያለ ኃጥእ: ለባሴ ሥጋና ገባሬ ንስሃ ስለሱ ሊናገር አይቻለውምና:: አባቶቻችን እንደ ነገሩን ስለ አፈ ወርቅ ለመናገር አፈ ወርቅ መሆን ያስፈልጋል:: እስኪ በቅዱሱ አባት ምልጃ ጥቂት ልሞክር::

††† ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ማን ነው?

††† ነገዱ ከሶርያ: የተወለደው በ347 ዓ/ም በእስክንድርያ ሲሆን አባቱ አስፋኒዶስ እናቱ ደግሞ አትናስያ ይባላሉ:: እነርሱ ደግ ቢሆኑ ይህንን እንቁ ልጅ እግዚአብሔር ሰጣቸው:: ዮሐንስ ለክርስቲያን እንደሚገባ በትምሕርትና በጥበብ አደገ:: ገና በሕጻንነቱ ወደ ግሪክ ሔዶ የዘመኑን ሳይንስ (ፍልስፍና) ከአፉ እስከ ገደፉ ተምሮ ተመልሷል::

ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅን ለየት ከሚያደርጉት ነገሮችም አንዱ ይሔው ነው:: በዘመናዊም ሆነ በመንፈሳዊ ትምሕርት ይህ ቀረህ የማይሉት ሊቅ የሆነው ገና በ15 ዓመቱ ነበር:: በ2 ወገን የተሳለ ሰይፍ በመሆኑ ስንኩዋን በሕይወተ ሥጋ እያለ ዛሬም ለንፉቃን ትልቅ የራስ ምታት ነው::

ቅዱሱ ገና በ16 ዓመቱ ሃብት: ንብረት: ውበት: ክብርና እውቀት የሞላለት ቢሆንም ያለውን ሁሉ ለነዳያን ሰጥቶ መጻሕፍትን ብቻ ሰብስቦ ከባልንጀራው ቅዱስ ባስልዮስ ጋር በርሃ ገባ:: ሰውነቱን በጾምና በጸሎት እየቀጣ በበርሃ ሲኖር ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስና ሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ ዼጥሮስ ወደ እርሱ መጡ:: ሊቀ ሐዋርያት የመንግስተ ሰማያትን መክፈቻ ስልጣን ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌሉን ሰጥተው ተሰወሩት::

ከዚህች እለት በሁዋላ ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ባሕረ ምስጢራት ሆነ:: ብሉይ ከሐዲስ: ከኦሪት ዘፍጥረት እስከ ራዕየ ዮሐንስ ድረስ በአንድምታ ትርጉዋሜ ተነተናቸው:: በተለይ ሐዲስ ኪዳንን እየመላለሰ አመሰጠረው:: ቅዱስ ሕሊናው ሳይታክት: ንጹሕ እጆቹ ሳይዝሉ የጻፋቸው ድርሳናት: መልዕክታትና ትርጉዋሜያት ቢቆጠሩ አሥር ሺህ ሞሉ:: በእውነት ለዚህ አንክሮ ይገባል! የሚገርመው ይህን ሁሉ ሲሰራ እድሜው ገና ለጋ: ማዕርጉም ዲቁና ነበር::

ከዚህ በሁዋላ በእግዚአብሔር ትእዛዝ ቅስና ተሹሞ በስብከተ ወንጌል ብዙ ቦታዎችን አዳረሰ:: በቅድስናው ወደውታልና የቁስጥንጥንያ ፓትርያርክ አድርገው ሾሙት:: አፈ ወርቅ ሲናገርም ሆነ ሲያስተምር እንኩዋን የሚያወራ ኮሽ የሚል የለም:: ከጣዕመ ትምሕርቱ የተነሳ ሕዝቡ በተደሞ ይሰሙት ነበር:: ሲያስተምር ምድራዊው ሰው ይቅርና ልዑላኑ መላእክት ተሰብስበው ያደንቁት ነበር:: አንዴም እመቤታችን በሕዝብ መካከል አፈ ወርቅ ብላ ጠርታዋለች:: ለዛም ነው አፈ ወርቅ የሚባለው:: ቅዱሱ በሥልጣነ ቃሉ መልዐከ ሞትን ገስፆ 10 ዓመት አቁሞታል::

ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ለሰው ፊት አያደላም:: በርሱ ዘንድ ንጉሥና ደሃ ነዳይ እኩል ነው:: ለሞት ያበቃውም ይሔው ነበር:: ምክንያቱም የወቅቱ ንግስት አውዶክስያ ያንዲት ድሃ መበለትን መሬት ቀምታ አልመልስም በማለቷ መክሮ አወገዛት:: እርሷ ግን ከኃጥአንና መናፍቃን ጋር መክራ 2 ጊዜ አጋዘችው:: በተሰደደበት ሃገር ፍሬ አፍርቶ: አስተምሮና አሳምኖ በ407 ዓ/ም አርፏል:: ቤተ ክርስቲያንና ምእመናን ሳይጠግቡት እንደናፈቁት በ60 ዓመቱ አጡት:: በወቅቱ ታላቅ ሐዘንና ለቅሶ ተደረገ::

አንድ ቀን የዘመኑ ደግ ንጉሥ አርቃድዮስ ግብር አገባ:: (ግብዣ አዘጋጀ) በዚያች ሌሊት ደግሞ ቅዱሱ ሊቅ ታጥቆ ሲጸልይ ሳለ: አባ ማርዳሪ የሚባል ጻድቅ ደግሞ 12ቱ ሊቃነ መላእክት (እነ ቅዱስ ሚካኤል) ከሰማይ በግርማ ሲወርዱ ተመለከተ::

ደንግጦ "ወዴት ናችሁ ጌቶቼ" ቢላቸው "ቁስጥንጥንያ: ወደ ዮሐንስ አፈ ወርቅ እንሔዳለን:: እርሱ እመቤታችንን እንደሚያመሰግናት ጌታ ነግሮናልና" አሉት:: "እባካችሁ እኔም የአፈ ወርቅ ምስጋናው እንዲገለጥልኝ መርቁኝ" አላቸው:: ሊቃነ መላእክቱም መርቀውት ጐዳናቸውን ቀጠሉ::

በማግስቱ በቤተ መንግስት ውስጥ ሊቃውንቱ: መሳፍንቱ: ዻዻሳቱ: ሕዝቡ ሁሉ ተሰብስበው ከድግሱ በሉ:: ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ግን በመንበሩ ተቀምጦ ነበር እንጂ አልበላም:: ድግሱ ሲጠናቀቅ ንጉሡ አርቃድዮስ ሊቁን "ጥያቄ አለኝ" ብሎ በጉባኤ መካከል ጠየቀው::

"ምነው ወንጌላዊ ማቴዎስ 'ኢያዕመራ ዮሴፍ እስከ አመ ወለደት ወለደ ዘበኩራ - የበኩር ልጇን እስክትወልድ ድረስ አላወቃትም' ማለቱ (ማቴ. 1:25) ስለ ምን ነው?" ቢለው ቅዱሱ ተነስቶ: በመንፈስ ቅዱስ ተቃኝቶ ይተረጉምለት ጀመር::

"ድንግል ማርያም ንጹሕ ብርሌን ትመስላለች:: ብርሌ የተለያየ ቀለም ያለው ፈሳሽ ቢያስገቡበት ቀለሙ አብሮ ይቀያየራል:: እመቤታችንም ጌታን ጸንሳለችና ሕብረ መለኮቱ ሲለዋወጥ መልኩዋ አብሮ ሲለዋወጥ እያየ ዮሴፍ ይደነግጥ ነበር::

'እርሷ ማን ናት? በማሕጸኗ ያለውስ ማን ነው?' እያለ ይጨነቅ ነበር:: ጌታን ከወለደች በሁዋላ ግን አንድ ሕብረ መልክ ሆናለችና:: አስቀድሞ ማን እንደ ነበረች አላወቀም::

አሁን ግን እርሷም ወላዲተ አምላክ: ልጇም አምላክ ዘበአማን መሆኗን አወቀ ማለት ነው" እያለ ሲተረጉም ሰምተው ሁሉም ሲያደንቁ: በዚያ የነበረች ስዕለ አድኅኖ "አፈ ወርቅ! ልሳነ ወርቅ! አፈ በረከት!" ስትል ተናገረች::

ያን ጊዜ አርቃድዮስ የወርቅ ልሳን በሊቁና በስዕሏ ላይ አደረገ:: አፈ ወርቅ ግን ባጭር ታጥቆ "እሰግድ ለኪ! እሰግድ ለኪ! ወእዌድሰኪ . . ." ብሎ ዛሬ በተአምረ ማርያም የምናውቀውን ምስጋና ሰተት አድርጐ አደረሰላት:: ይህንን ምስጋናም ሊቃነ መላእክቱ ሰምተው እያደነቁ ወደ ሰማይ ወጥተዋል::

ሊቁ ባረፈ በ35 ዓመቱ በትንሹ ቴዎዶስዮስ ዘመን: በዚህ ቀን ሥጋው ፈልሷል:: ወደ ቁስጥንጥንያ ሲደርስም ከናፍቆት የተነሳ ታላቅ ዝማሬና እንባ ተደርጉዋል:: አፈ ወርቅም ቀና ብሎ ሕዝቡን ባርኩዋል::

††† ቅዱሱ ሲጠራ እንዲሕ ነው:-
*ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ
*አፈ በረከት
*አፈ መዐር (ማር)
*አፈ ሶከር (ስኩዋር)
*አፈ አፈው (ሽቱ)
*ልሳነ ወርቅ
*የዓለም ሁሉ መምሕር
*ርዕሰ ሊቃውንት
*ዓምደ ብርሃን (የብርሃን ምሰሶ)
*ሐዲስ ዳንኤል
*ሊቀ ዻዻሳት ዘበርትዕ (እውነተኛው)
*መምሕር ወመገስጽ ዘኢያደሉ ለገጽ
*ጥዑመ ቃል - - -

††† የጥቡዓን አምላክ የሊቁን ምሥጢር: የቅድስናቸውን  በረከት ይክፈለን::

††† ኅዳር 17 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ (ፍልሠቱ)
2.ቅድስት ወለተ ዼጥሮስ ኢትዮዽያዊት
3.አባ ሲኖዳ (ዘደብረ ጽሙና - ጐጃም)
4.ጻድቃን እለ ወጺፍ
5.ቅዱሳን አብርሃምና ሐሪክ
6.ቅድስት ወለተ ዻውሎስና ወለተ ክርስቶስ

††† ወርኀዊ በዓላት
1.እስጢፋኖስ ሊቀ ዲያቆናት
2.ያዕቆብ ሐዋርያ
3.መክሲሞስና ዱማቴዎስ
4.አባ ገሪማ
5.አባ ዸላሞን
6.አባ ለትጹን
7.ቅዱስ ኤዺፋንዮስ

🌹✞ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ✞🌹
               🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

24 Nov, 19:31


🌿ስንክሳር ኅዳር 16 🌿

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡
እንኩዋን ለቅዱሳን "አኖሬዎስ ንጉሥ" : "አባ ዳንኤል" : "ቅድስት ጣጡስ" : "ወአባ አቡናፍር" ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ።

" ቅዱስ አኖሬዎስ ወአባ ዳንኤል "

አኖሬዎስ የሚለው ስም በቤተ ክርስቲያን እጅግ ተወዳጅ ነው:: በሃገራችንና በሌሎች አብያተ ክርስቲያናትም ብዙ ቅዱሳን በዚህ ስም ተጠርተዋል:: ቅድሚያውን ግን ቅዱሱ ንጉሥ አኖሬዎስ ይወስዳል::

ቅዱስ አኖሬዎስ ተወልዶ ያደገው በሮም ከተማ ሲሆን የደጉ ንጉሥ ዐቢይ ቴዎዶስዮስና የመርኬዛ ልጅ ነው:: ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ ሙሽራው እና ደጉ አርቃዴዎስ ወንድሞቹ: ጻድቁ አቡነ ኪሮስ ደግሞ አጐቱ ናቸው:: በልጅነቱ ክርስትናን የተማረው ከታላቁ ቅዱስ አርሳኒ ነው::

ምንም በቤተ መንግስት ውስጥ ቢያድግም ቅዱስ አርሳኒ እንደ ተራ ሰው እየገረፈና እየቀጣ አሳድጐታል:: ቴዎዶስዮስ ቄሣር (አባቱ) ባረፈ ጊዜ የሮም ግዛትን በስምምነት ከወንድሙ አርቃዴዎስ ጋር ተካፈሉ:: በ390ዎቹ አካባቢም አኖሬዎስ በሮም: አርቃዴዎስ በቁስጥንጥንያ ነገሡ::

ቅዱስ አኖሬዎስ ይሕንን ዓለም አልፈለገውምና ወደ ገዳም ልኮ አንድ ባሕታዊ (አባ አውሎጊስ ይባላል) አስመጥቶ ሥርዓተ ምንኩስናን ፈጸመ:: አክሊለ ሦኩንም በወርቅ ዘውዱ ውስጥ አደረገው::

ልብሰ ምንኩስናውን በሰንሰለት በውስጥ አሥሮ በላዩ ላይ የመንግስቱን ካባ ደረበ:: ቀን ቀን እንደ ንጉሠ ነገሥት ሲፈርድ: ሲተች: የተበደለ ሲያስክስ: የተቀማ ሲያስመልስ ይውል ነበር::

ሌሊት ደግሞ ባጭር ታጥቆ ሲወድቅ ሲነሳ: ሲጸልይ ሲሰግድ: ያለ ዕረፍት ያድራል:: መቼም ቢሆን ከደረቅ ቂጣ: ከጨውና ከጥሬ ጐመን በቀር ሌላ ምግብን አይቀምስም:: ይኸውንም ጾሞ ውሎ ማታ ብቻ ይመገብ ነበር::

ይሕንንም ሲያደርግ ሰሌን ሰፍቶ: ያንን አሽጦ እንጂ በሌሎች ገንዘብ አልነበረም:: ሰዎች እንዳይጠረጥሩትም "በእልፍኙ ውስጥ ሚስት አለችው" እያለ ያስወራ ነበር:: በዚያ ላይ መልኩ ያማረ ስለ ነበር በዚህ የጠረጠረው የለም:: በዚህ መንገድ ከአባ አውሎጊስና ከደቀ መዝሙሩ ጋር ሆኖ ለ40 ዓመታት ተጋደለ::

🌿" አባ ዳንኤል ገዳማዊ "🌿

በ4ኛው ክ/ዘመን መጨረሻና በ5ኛው መጀመሪያ በግብጽ ውስጥ ከነበሩ ከዋክብት አንዱ ሲሆን መንኖ ገዳም ከገባባት ቀን ጀምሮ በፍጹም ተጸምዶ: ከእህል ተከልክሎ: ቅጠል እየበላ ለ40 ዓመታት ተጋደለ:: አንድ ቀን ግን ተፈተነ:: በትዕቢት "ከእኔ የሚበልጥ ማን አለ?" ሲል በማሰቡ ፈጣሪ መልአኩን ልኮ ገሰጸው::

ቀጥሎም "ሒድና ንጉሡን አኖሬዎስን እየው:: እሱ ንጉሥ ቢሆንም በቅድስና ይተካከልሃል" አለው:: አባ ዳንኤልም በደመና ወደ ሮም ሒዶ ቅዱሱን ንጉሥ ተገናኘው:: ቅድስናውን ዐይቶም ለቅዱስ አኖሬዎስ ሰገደለት:: እያለቀሰም ወደ በዓቱ ተመለሰ::

ቅዱስ አኖሬዎስ ግን ከመምሕሩ ቅዱስ አውሎጊስና ከደቀ መዝሙሩ ጋር መንግስቱን ትቶ: ጠፍቶ: በርሃ ገብቶ ከአባ ዳንኤል ጋር ተቀመጠ:: ከተጋድሎ በሁዋላም 4ቱም ቅዱሳን በዚህች ቀን ዐርፈዋል::

🌿" ቅድስት ጣጡስ ሰማዕት "🌿

በቤተ ክርስቲያን ታሪክ እንደዚህች ቅድስት ወጣት መልከ መልካም አልነበረም ይባላል:: ቅድስት ጣጡስ በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን (በዘመነ ሰማዕታት) የነበረች ሮማዊት ክርስቲያን ስትሆን መልኩዋን ያየ ሁሉ ይደነቅ: ይደነግጥም ነበር::

እርሷ ግን ለወንድሞቿ እንቅፋት እንዳትሆን በፊቷ ላይ ዐይነ ርግብ ጣል አድርጋና እንደ ነገሩ ለብሳ ትኖር ነበር:: (እንዲህ ነበሩ እናቶቻችን!!!) ታዲያ በዘመኑ እስክንድሮስ የሚባል አረማዊ "ለጣዖት ስገዱ" እያለ ክርስቲያኖችን ሲገድል የእርሷ ተራ ደረሰ::

በዐውደ ስምዕ (በምስክርነት አደባባይ) ላይ አቁሟት "ፊቷን ግለጡልኝ" አለ:: ቢገልጧት ከመልኩዋ ማማር የተነሳ ፈዘዘ:: እጅግ በመፍጠንም "ላግባሽ?" አላት:: "ሙሽርነቴ ሰማያዊ ነውና አይሆንም!" አለችው:: ለመናት: አልሰማችውም:: አስፈራራት: አልደነገጠችም::

ከዚያ ግን ገላዋን አስገረፈ:: ከአካሏም ስለ ደም ፈንታ ወተት ፈሰሰ:: ተበሳጭቶ ለአራዊት ጣላት:: እነሱ ግን ሰገዱላት:: በእሳትም ፈተናት:: እርሷ ሁሉንም ታግሣ ጸናች:: በመጨረሻው ግን በዚህች ቀን አስገደላት:: ፈጣሪዋ ክርስቶስም በሰማያዊ አክሊል ከለላት::
🔔 ኅዳር 16 ቀን የሚከበሩ

ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
👉1.ቅዱስ አኖሬዎስ ጻድቅ (ንጉሠ ሮም)
👉2.አባ ዳንኤል ገዳማዊ
👉3.ቅዱስ አውሎጊስ መነኮስ
👉4.ቅድስት ጣጡስ ሰማዕት
👉5.አባ አቡናፍር ገዳማዊ
👉6.ቅዱስ ኪስጦስ ሰማዕት
👉7.ቅዱስ ፊቅጦር ምዑዝ
👉8.አባ ዮሐንስ መሐሪ

ወርኀዊ በዓላት

1.ኪዳነ ምሕረት (የሰባቱ ኪዳናት ማሕተም)
2.ቅድስት ኤልሳቤጥ (የመጥምቁ ዮሐንስ እናት)
3.ቅዱስ ገብረ ማርያም ጻድቅ ንጉሠ ኢትዮዽያ
4.ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌሉ ዘወርቅ

" ዓለምን ወይም በዓለም ያሉትን አትውደዱ:: በዓለም ያለው ሁሉ: እርሱም የሥጋ ምኞትና የዓይን አምሮት: ስለ ገንዘብም መመካት ከዓለም ስለ ሆነ እንጂ ከአባት ስላልሆነ: ማንም ዓለምን ቢወድ የአባት ፍቅር በእርሱ ውስጥ የለም:: ዓለሙም: ምኞቱም ያልፋሉ:: የእግዚአብሔርን ፈቃድ የሚያደርግ ግን ለዘለዓለም ይኖራል:: " (1ዮሐ. 2:15)
የለም አንልም

መልካም የነቢያት(የገና) ጾም ይሁንልን።🙏

🌹✞ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ✞🌹
               🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

24 Nov, 16:45


ይልመድብን
የንስሃ አባቶች ፍሬ!

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

22 Nov, 04:15


🙏 ስንክሳር ኅዳር 13 🙏

† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ አምላክ አሜን! †

† እንኩዋን "ለ99ኙ ነገደ መላእክት": "ቅዱስ አስከናፍር" እና "ቅዱስ ጢሞቴዎስ" ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ †

† አእላፍ መላእክት †

እግዚአብሔር ቅዱሳን መላእክትን ሲፈጥራቸው በነገድ መቶ (100): በክፍለ ነገድ አሥር (10) አድርጉዋቸዋል:: አቀማመጣቸውንም በ3 ሰማያትና በ10 ከተሞች (ዓለማት) አድርጉዋል::

መላእክት ያሉባቸው ከተሞች ከታች ወደ ላይ "ኤረር: ራማና ኢዮር" ይባላሉ:: አሥሩ ክፍለ ነገድ ደግሞ ከነ አለቆቻቸው ይህንን ይመስላሉ:-

1.አጋእዝት (የቀድሞ አለቃቸው ሳጥናኤል: አህን የተረፉት በቅዱስ ሚካኤል ሥር ናቸው)
2.ኪሩቤል (አለቃቸው ኪሩብ)
3.ሱራፌል (አለቃቸው ሱራፊ)
4.ኃይላት (አለቃቸው ሚካኤል)
5.አርባብ (አለቃቸው ገብርኤል)
6.መናብርት (አለቃቸው ሩፋኤል)
7.ስልጣናት (አለቃቸው ሱርያል)
8.መኩዋንንት (አለቃቸው ሰዳካኤል)
9.ሊቃናት (አለቃቸው ሰላታኤል)
10.መላእክት (አለቃቸው አናንኤል) ናቸው::

ከእነዚህም *አጋእዝት: *ኪሩቤል *ሱራፌልና *ኃይላት መኖሪያቸው በኢዮር (በ3ኛው ሰማይ) ነው:: *አርባብ: *መናብርትና *ስልጣናት ቤታቸው ራማ (2ኛው ሰማይ) ነው:: *መኩዋንንት: *ሊቃናትና *መላእክት ደግሞ የሚኖሩት በኤረር (በ1ኛው) ሰማይ ነው::

መላእክት ተፈጥሯቸው እምኀበ አልቦ ኀበ ቦ ነው:: አይራቡም: አይጠሙም: አይዋለዱም: አይሞቱም:: ተፈጥሯቸውም ረቂቅ ነው:: ተግባራቸውም ዘወትር "ቅዱስ: ቅዱስ: ቅዱስ" እያሉ ፈጣሪያቸውን ማመስገን ነው:: ምግባቸውም ይሔው ነው::

ዕረፍት ብሎ ነገርን አያውቁም:: "አኮቴቶሙ ዕረፍቶሙ: ወዕረፍቶሙ አኮቴቶሙ" እንዲል:: በተጨማሪም መልአክ ማለት ተላላኪ (አገልጋይ) ነውና ከፈጣሪ ወደ ሰው ልጆች ለምሕረትም: ለመዓትም ይላካሉ::

ምሕረትን ያወርዳሉ:: ልመናን ያሳርጋሉ:: ቅጡ ሲባሉም ይቀጣሉ:: ስነ ፍጥረት (አራቱ ወቅቶች) እንዳይዛቡ ይጠብቃሉ::

*ዘወትርም ስለ ሰው ልጆች ያማልዳሉ (ዘካ. 1:12)
*ምሥጢርን ይገልጣሉ (ዳን. 9:21)
*ይረዳሉ (ኢያ. 5:13)
*እንዳንሰናከል ይጠብቃሉ (መዝ. 90:11)
*ያድናሉ (መዝ. 33:7)
*ስግደት ይገባቸዋል (መሳ. 13:20, ኢያ. 5:13, ራዕ. 22:8)
*በፍርድ ቀንም ኃጥአንን ከጻድቃን ይለያሉ (ማቴ. 25:31)
*በአጠቃላይ ለሰው ልጆች ሕይወትና ድኅነት ሲባል ከፈጣሪያቸው የተሰጣቸውን ትዕዛዝ ሲጠብቁና ፈቃዱን ሲፈጽሙ ይኖራሉ::

+"+ አእላፍ +"+

=>ይህ ዕለት በሊቃውንት አንደበት "አእላፍ" እየተባለ ይጠራል:: በሃይማኖት: በተልእኮትና በምስጋና የሚኖሩ 99ኙ ነገደ መላእክት በአንድ ላይ የሚከበሩበት ቀን ነው:: ምንም እንኩዋን የጐንደሩን ፊት ሚካኤልን ጨምሮ በአንዳንድ አድባራት ታቦቱ ቢኖርም ሲያነግሡ ተመልክቼ አላውቅም::

+ሊቃውንቱ በማሕሌት: ካህናቱም በቅዳሴ እንደሚያከብሯቸው ግን ይታወቃል:: ሕዳር 13 ቀን ዓመታዊ በዓላቸው ነው ማለት በየወሩ በ13 ወርሃዊ በዓላቸው መሆኑን ያሳያልና ዘወትር ልናስባቸው ይገባል::

+ቅዱስ መጽሐፍ ቅዱሳን መላእክትን በስምና በማዕረግ እንደሚነግረን ሁሉ በማሕበር (በትዕይንት) አገልግሎታቸውም ይነግረናል:: ለምሳሌ:-

*ያዕቆብ= በረዥም መሰላል ሲወጡና ሲወርዱ ተመልክቷል:: (ዘፍ. 28:12)
*ኤልሳዕ ለግያዝ አሳይቶታል:: (2ነገ. 6:17)
*ዳንኤል ተመልክቷል:: (ዳን. 7:10)
*በልደት ጊዜ በዝማሬ መገለጣቸውን ቅዱስ ሉቃስ ጽፏል:: (ሉቃ. 2:13)
*ዮሐንስ በራዕዩ አይቷቸዋል:: (ራዕይ. 5:11)

+ከዚህም በላይ በብዙ የመጻሕፍት ክፍል ተጠቅሰዋል:: ቅዱሳን መላእክተ ብርሃን: መንፈሳውያን: ሰባሕያን: መዘምራን: መተንብላን (አማላጆች) ተብለውም ይጠራሉና ያስቡን ዘንድ ልናስባቸው ይገባል::

=>ኅዳር 13 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.አእላፍ (99ኙ) ነገደ መላእክት
2.ቅዱስ አስከናፍር ሮማዊ
3."13ቱ" ግኁሳን አበው (ሽፍቶች የነበሩ)
4.ቅዱስ ጢሞቴዎስ ዘእንጽና
5.አባ ዘካርያስ ሊቀ ዻዻሳት

=>ወርኀዊ በዓላት
1.እግዚአብሔር አብ
2.ቅዱስ ሩፋኤል ሊቀ መላዕክት
3.ቅዱስ አርሳንዮስ ጠቢብ ገዳማዊ
4.አቡነ ዘርዐ ቡሩክ

=>+"+ ስለ መላእክትም:-
"መላእክቱን መናፍስት: አገልጋዮቹንም የእሳት ነበልባል የሚያደርግ" ይላል . . .
ነገር ግን ከመላእክት:-
"ጠላቶችህን የእግርህ መረገጫ እስካደርግልህ ድረስ በቀኜ ተቀመጥ" ከቶ ለማን ተብሏል?
ሁሉ መዳንን ይወርሱ ዘንድ ስላላቸው ለማገዝ የሚላኩ: የሚያገለግሉም መናፍስት አይደሉምን? +"+ (ዕብ. 1:7-14)

✍️† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †✍️
🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
https://t.me/Sinksar
https://t.me/Sinksar
https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

20 Nov, 18:21


የሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል በዓለ ሢመት

ሚካኤል ማለት መኑ ከመ እግዚአብሔር ሚ ዕፁብ ነገር ማለት ነው፤ በዕብራይስጥ ‹‹እንደ እግዚአብሔር ያለ ማን ነው!›› ማለት እንደሆነ ቅዱሳት መጻሕፍት ይጠቅሳሉ፡፡

አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ በመዝገበ ቃላት መጽሐፋቸው ላይ እንዳሰፈሩት ደግሞ የስሙን ፊደላት በመተንተን እንዲህ ተርጉመውታል፤ ሚ-መኑ፣ ካ-ከመ፣ ኤል-አምላክ፤ ‹‹መኑ ከመ አምላክ፤ እንደ አምላክ ማን ነው!›› (መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገበ ቃላት ሐዲስ)

በዚች ዕለት እስራኤልን በሙሴና በአሮን መሪነት ባሕር ከፍሎ ጠላት ገድሎ፣ መና አውርዶ፣ ደመና ጋርዶ በብዙ ሣህል ታድጎ ከምድረ ግብጽ ማውጣቱ ይነገራል፡፡

እግዚአብሔር አምላክ ሕዝበ እስራኤልን ከግብጽ ባርነት ነፃ ሲያወጣቸው ይመራቸው የነበረ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ነበር፡፡ ሹመቱ በእግዚአብሔር ሕዝብ ላይም በመሆኑ ስለ እነርሱ ዲያብሎስን ይዋጋው፣ በጸሎትም ረድቷቸዋል፡፡

አምላካችን እግዚአብሔር ሳጥናኤልን በትዕቢቱ ምክንያት ከሥልጣኑ አውርዶ ወደ ምድር ሲጥለው ቅዱስ ሚካኤል በእርሱ ቦታ በዐሥሩ ከተማ በመቶውም ነገደ መላእክት ላይ ተሹሟል፡፡ የቅዱስ ሚካኤል ሹመት በነገደ መላእክት ላይ ብቻ አይደለም ፤ ነገር ግን የእግዚአብሔር ሕዝብ በሆኑት ላይም ጭምር ነው፡፡

በኅዳር ወር በዐሥራ ሁለተኛው ቀን ቤተ ክርስቲያናችን የታላቁ መልአክ የቅዱስ ሚካኤልን በዓል በታላቅ ድምቀት ታከብረዋለች፡፡

መላእክት ሰዎች በዓለም ፈተና ውስጥ ሆነው ሰይጣን ሊያደክማቸው ሲፈልግ ኃይልን ብርታትን የሚሰጡ፣ ይህን ዓለም ንቀው በበርሃ ወድቀው ከሥጋ ምኞት ጋር የሚጋደሉትን፣ በከተማም እየኖሩ መንፈሳዊ ትሩፋት የሚያደርጉትን ደግሞ የሚያበረቱ ናቸው፡፡

የቅዱስ ሚካኤል አማላጅነት በሐዲስ ኪዳንም እንደነበር ይህ ነቢይ በትንቢቱ ‹‹በዚያም ዘመን ስለ ሕዝብህ ልጆች የሚቆመው ታላቁ ሚካኤል ይነሣል›› በማለት ተናግሮለታል፡፡ ስለዚህም ቅዱስ ሚካኤል እኛን ከሰይጣን አሽክላና ወጥመድ ይጠብቀንና በጸሎቱ በእግዚአብሔር ፊት ይቆምልን ዘንድ በእኛም ላይ ሹም ነው፡፡ ምክንያቱም እኛ የእግዚአብሔር ሕዝቦችና የርስቱ ወራሾች ነንና፡፡ (ዳን.፲፪፥፩)

በመጽሐፈ ስንክሳርም ተመዝግቦ እንደምናኘው ቅዱስ ሚካኤል በየወሩ በዐሥራ ሁለት ቀን ለመታሰቢያው በዓል ተሠርቶለታል፤ እርሱ ስለ እኛ የምድሩን ፍሬ ይባርክልን ዘንድ ዝናሙም በጊዜው እንዲወርድልን የወንዙንም ውኃ እንዲመላልን ነፋሱንም የምሕረት ነፋስ እንዲያደርግልን ሁሉንም የተስተካከለ እንዲያደርግልን ወደ እግዚአብሔር በጸሎት ይማልዳልና፡፡ (ስንክሳር ኅዳር ፲፪)

ቅዱስ ኤጲፋንዮስ ‹ሚካኤል ሥዩም በዲበ ኃይላት፤ በኃይላት ላይ የተሾምክ ሚካኤል› ሲል ያመሰገነው ቅዱስ ሚካኤል በኃይላት መላእክት ላይ የተሾመ ሊቀ መላእክት እንደመሆኑ በዓለ ሢመቱ ኅዳር ፲፪ ቀን በመላው የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በድምቀት ይከበራል፡፡ (መጽሐፈ አክሲማሮስ)

የሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል አማላጅነትና ተራዳኢነት አይለየን፤ አሜን፡፡

ምንጭ፤ መጽሐፈ አክሲማሮስ
ስንክሳር ዘወርኃ ኅዳር
መድብለ ታሪክ ቁጥር አንድ (በመ/ር ዐይነ ኩሉ ያየህ 2011 ዓ.ም)

Via MK Fb page

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

20 Nov, 13:25


እናማ እንዲህ እየሆነ የተስፋፋው በሽታ በአዲስ አበባ ብቻ ሳይወሰን ወደ ባላገሩ ተላልፎ ብዙ ሰው ፈጅቷል ቢባልም የአዲስ አበባን ያክል የጠነከረበት የሀገሪቱ ክፍል አልነበረም።

በአጠቃላይ ግን በመላዋ ኢትዮጵያ እስከ 40ሺ የሚገመት ሰው በበሽታው ማለቁ ተሰማ። በስተመጨረሻም ይህ ወረርሽኝ የአካባቢን ንጽሕና በመጠበቅ ቆሻሻንም ሰብስቦ በማቃጠል ዘመቻ እየቀነሰ መጥቶ ጠፋ።

ከዛን በኋላ የሆነብንን ለማሰብ ወቅቱንም ለመዘከር በየዓመቱ በኅዳር ሚካኤል ሰሞን ቆሻሻ እየተሰበሰበ ማቃጠል ልማድ ሆነ ይኼው እኛም እስካሁንም ድረስ የደረሰብን ቸነፈር ብንረሳውም ልማዱን ግን አየፈጸምን አለን።
   
#ምንጭ፦መርስኄ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ "የሐያኛው መቶ  ክፍለ ዘመን መባቻ"

#ወደ_ምሥራቅ_እንመልከት

      ✝️⛪️⛪️✝️
#ንነጽር_አዳም_ወሔዋን_ለቡ!

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

20 Nov, 13:23


#ተኅዳር_ሲታተን!

#ኅዳር_ሲታጠን_የተባለው_ታሪኩ_ምንድን_ነው ?

አባቶች እንደሚያስተምሩን ከሆነ የታሪኩ መነሻ የ1911 ዓ.ም የበሽታ መቅሰፍት ነው። በዚህ በሽታ ብዙ ሰው በአለምም በሀገራችንም አልቋል ።

በሽታው አንደኛው የዓለም ጦርነት ፍጻሜ ተከትሎ በኹሉም ዘንድ የተዳረሰና በታሪክ «#እስፓኒሽ_ፍሉ» በመባል የታወቀው #የእንፍሎዌንዛ ወረርሽኝ ነው።

አንዳንድ ፈረንጆች "#ግሪፐ " ይሉታል በአዲስ አበባ ግን በኅዳር ወር ደርሶ ስለታወቀ "የኅዳር በሽታ" ተብሎ ይጠራ ነበር። የሕመሙ ምልክት ከባድ ነው። እንደ ጉንፋን በማሳል ይጀምርና በሰውነት ላይ ንዳድ (ትኩሳት) ይለቃል ።

ተቅማጥና ውጋት ነስርም ያስከትላል አንዳንዱን ደግሞ አእምሮውን ያሳጣዋል። እንዲህ እያደረገ ሰውን በሦስት በዐራት ቀን ይገለዋል። ከዐራት ቀን በላ የሰነበተ በሽትኛ ካለ ግን እድለኛ ሆኖ ከሞት አምልጧል ማለት ነው ።

አንዳንድ ቦታ ቤተሰቡ በሙሉ ይታመም ስለነበር አስታማሚ በማጣት በረሀብና በውኃ ጥም ብዙ ሰው ይጎዳበት እንደነበር የታሪክ ድርሳናት በማይጠፋ በራና ዘግበውታል።

ስለዚህ በአዲስ አበባ በየቀኑ ኹለት ሦስት መቶ ሰው ከዚያም በላይ ይሞት ጀመር። በአንድ የመቃብር ጉድጓድም ከአንድ በላይ አስከሬን  እስከ መቅበርም ተደረሰና ደሃ የለ ባለጸጋ አሽከር አይቀረው መኳንንት ሁሉን ፈጀ።

በዚያ  ሰሞን መቃብር የሚቆፍር ሬሳን ተሸክሞ የሚወስድ ሰው ማግኘት ከባድ ነገር ሆነ። ከቤተሰብ ውስጥ ከበሽታው ያመለጠ ሰው ካለ ኹለት ይሆኑና አስከሬን እያመላለሱ ይቀብራሉ በዚህ መንገድ ባል ሚስቱን አባት ልጁን ለብቻቸው እስከ መቅበር ደረሰው ነበር። ቤተሰቡ በሙሉ የታመመ ካለ ደግሞ በአሳዛኝ ሁኔታ በአውሬ ተበልተው ያልቁ ነበር።     

ይቀጥላል. . .                               

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

20 Nov, 11:28


የእግዚአብሔርን ቃል ወደ ራስ ፈቃድና ሐሳብ መጎተት መጨረሻው እንደዚህ ነው!
.
"የጨው ገደል ሲናድ ሞኝ ይስቃል፤ ብልህ ያለቅሳል" የሚለውን ብሒል ማስታወሱ ግን አይከፋም!!!

የመናፍቅ መንገድ ወደ የት እያመራ ነው?

ክፍል-፩-
የቸርች ኦፍ ስዊዲን ሌሎች ሁለት አሳፋሪ ቅሌቶች!

1. ቸርች ኦፍ ስዊዲን ሥር የሚገኙ አባል "ቤተክርስቲያናት?" ከክርስትና እምነት አንፃር ለመስማት እንኳን የሚቀፉ LGBTQ-ተኮር ትርጉሞችን ከመፅሐፍ ቅዱስ አጣምመው እየተረጎሙ ለሕፃናት እያስተማሩ ይገኛሉ፤ በዚህም አስተምሮአቸው ለኢየሱስ ከ"LGBTQ" በ"Q" የተገለፀውን "QUEER" የሚለውን የፆታ ምድብ ሰጥተዋል።


2. ሁለተኛው የቸርች ኦፍ ስዊዲን ቅሌት የሚመዘዘው ከምሥራቅ ሃይማኖቶች በተለይም ከሂንዱይዝም እና ከቡዲሂዝም ጋር በተገናኘ ነው። ቸርች ኦፍ ስዊዲን በቤተ-LGBTQ ሕንፃዋ ሥር ለአባሎቿ እንደ ዮጋና ማይንድፈልነስ ያሉ የቡዲሂዝምንና የሕንዱይዝም ልምምዶችን እንዲተገብሩ ታበረታታለች፤ የሚገርመው ሥልጠናውን የሚሰጡት ከክርስትና እምነት ውጭ ያሉ የምሥራቅ ሃይማኖቶች ልምምድ አሰልጣኞች መሆናቸው ነው። ስለ ልምምዶቹ ወደፊት በስፋት እመለሳለሁ። እስከዚያው መረጃውን ከጎግል ላይ "Meditation and Other New Spiritual Practices in the Church of Sweden Katarina Plank, Linnea Lundgren, and Helene Egnell" በሚል ርዕስ ፒ ዲ ኤፍ ፋይል አውርዶ መቃኘት ይቻላል።

ወደገደለው ስንገባ በቅርቡ የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን ከየአቅጣጫው የቀረበባትን ጫና ተከትሎ ከቸርች ኦፍ ስዊዲን ጋር ያላትን ግንኙነት እንደምታቋርጥ መግለጫ መስጠቷ ይታወሳል። ባለቤትነቱ የቃለሕይወት፣ የመካነ ኢየሱስና የሌሎች ወንጌላውያን ቤተክርስቲያናት የሆነውና ሳር ቤት አካባቢ የሚገኘው የኢትዮጵያ ሥነ መለኮት ድህረ ምረቃ ት/ቤት(EGST) ግን እስካሁን ድረስ ከቸርች ኦፍ ስዊዲን ጋር ያለውን ግንኙነት ለማቋረጥ ፈቃደኛ አልሆነም፤ ይልቁን ግንኙነቱ ኢ-መፅሐፍ ቅዱሳዊ ስለመሆኑ ቲዖሎጂውን ሰርታችሁ አምጡ የሚል ቀሽም መከራከሪያ ከአንዳንድ የተቋሙ ሠራተኞች እየተነሳ ይገኛል። ኢየሱስን "Queer" ዮሴፍን "transvestite" ብፅይትና ቅድስት ድንግል ማሪያምን ዘልማዳዊውን የፆታ ትስስር የሰበረች አብዮተኛ አድርገዋት ከሚያስተምሩ ጋር ግንኙነት ለመፍጠር የሚፈቅድ ሥነመለኮታዊ ሰበብ መነሻ የሚገኘው ከወዴት ይሆን? በእዚህ ግልፅ በሆነ የግብረሰዶማውያን ቅሌት ዙሪያ ቲዖሎጂ የሚሰራው እንዴት ይሆን? ለማሳሰብ ያህል በEGST እና በቸርች ኦፍ ስዊዲን መካከል ከ15 ዓመታት በላይ ስለዘለቀው ግንኙነት ማስረጃው የተገኘው ከራሱ ከEGST ድህረ ገፅና ከሶሻል ሚዲያ የፌስቡክ ገፁ ነው።

ግንኙነቱ ከልማት ዘርፍ ባለፈ የቲዖሎጂ ፕሮግራም(Gender, Health, Theology) እስከመቅረፅ የዘለቀ ስለመሆኑ ወደፊት በስፋት አነሳለሁ።

በዚህ ረገድ የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን ፕሬዝዳንት የሆኑት ዶ/ር ጣሰው ገብሬ፣ የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ፕሬዚዳንት የሆኑት ዶ/ር ዮናስ ይገዙና የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ሕብረት ፕሬዚዳንት የሆኑት መጋቢ ፃዲቁ አብዶ የእምነት ተቋማቸውን በጋራም(በባለድርሻ አካላት የካውንስል ቦርድ አማካይነት) ይሁን በተነጠል በመወከል በቸርች ኦፍ ስዊዲንና በEGST መካከል ስላለው ግንኙነት እስካሁን የሰጡት መግለጫ የለም።

በነገራችን ላይ የ"EGST" ተቋም ባለቤትነት፣ 40% የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን፣ 40% የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ እና ቀሪው
20% የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ሕብረት መሆኑ ይታወቃል።

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

20 Nov, 03:56


ስንክሳር ኅዳር 12
እንኩዋን ለሊቀ መላእክት "ቅዱስ ሚካኤል" እና "ለቅዱሳኑ" ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ::

✞ ቅዱስ ሚካኤል ሊቀ መላእክት ✞

ቅዱስ ሚካኤል በጥንተ ተፈጥሮ በኢዮር: ኃይላት በተባሉት ነገደ መላእክት ተሹሞ ነበር:: ሳጥናኤል በካደ ጊዜ እግዚአብሔር ባወቀ: አንድም በትሕትናውና ደግነቱ በ99ኙ ነገደ መላእክት ላይ ሁሉ ተሹሟል::

ከፍጥረት ወገን ከእመቤታችን ቀጥሎ የቅዱስ ሚካኤልን ያሕል ክብርና ርሕሩሕ የለም:: በምልጃውም: በረዳትነቱም የታወቀ መልአክ ነው:: መጽሐፍ "መልአከ ምክሩ ለእግዚአብሔር" ይለዋል:: "ወስሙ መስተሣሕልም" ይለዋል:: ቂም የሌለው: ለምሕረት የሚፋጠን: ደግ መልአክ ነውና::

በብሉይ ኪዳን በመከራ ለነበሩ ቅዱሳን ሁሉ ሞገስ: ረዳትና አዳኝ ቢሆናቸው "መጋቤ ብሉይ" ተሰኝቷል:: እሥራኤልን 40 ዘመን በበርሃ መርቷል:: መግቧልም:: ቅዱስ መጽሐፍ ስለ እርሱ ብዙ ይላል:: (ዘፍ. 48:16, ኢያ. 5:13, መሳ. 13:17, ዳን. 10:21, 12:1, መዝ. 33:7, ራዕይ. 12:7)

ደስ የሚለው ደግሞ ርሕሩሑ መልአክ ከእመቤታችን ጋር ልዩ ፍቅር አለው:: ከእናቷ ማሕጸን ጀምሮ እስከ ዛሬ እነሆ አብሯት አለ:: ደስ ብሎት ይታዘዛታል:: ማማለድ ሲፈልግም "እመቤቴ ሆይ! ቅደሚ" ይላታል:: ወደ እሳት መጋረጃ አብረው ገብተው ለዓለም ምሕረትን: በረከትን ያወርዳሉ::

🌿+" ቅዱስ ኢያሱ ነቢይ "+🌿

ዳግመኛ በዚህች ዕለት ቅዱስ ሚካኤል ኢያሱን እንደ ረዳው ታስተምራለች:: ይህስ እንደ ምን ነው ቢሉ:-

በመጽሐፈ ኢያሱ ምዕራፍ 5 ላይ እንደ ተጻፈው ቅዱሱ መልአክ ለኢያሱ ተገልጦለታል:: እሥራኤልን በምድረ በዳ የመራ ሊቀ ነቢያት ቅዱስ ሙሴ ሲያርፍ ታላቅ ሐዘንና ድንጋጤ ተፈጥሮ ነበር::

እግዚአብሔር ግን ኢያሱን አስነስቶ አረጋግቷቸዋል:: ቅዱስ ሚካኤል 40ውን ዘመን እሥራኤልን ደመና ጋርዶ: መና አውርዶ: ክንፉን ዘርግቶ: ጠላትን መክቶ ከሙሴ ጋ እንደ መራቸው ከኢያሱ ጋርም ይሆን ዘንድ ከሰማይ ወረደ::

በኢያሪኮ አካባቢም የተመዘዘ ሰይፉን ይዞ በግርማ ለኢያሱ ታየው:: ኢያሱም ወደ እርሱ ቀርቦ "አንተ ከእኛ ወገን ነህን? ወይስ ከጠላቶቻችን?" ሲል ጠየቀው:: ቅዱስ ሚካኤልም መልሶ "እረዳህ ዘንድ እነሆ የሠራዊት አለቃ ሆኜ ተሹሜ መጥተቻለሁ" አለው::

ያን ጊዜ ታላቁ ነቢይ ቅዱስ ኢያሱ በግንባሩ ተደፍቶ ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ሰገደለት:: ቅዱሱ መልአክም አክሎ "ፍታሕ ቶታነ አሳዕኒከ እም እገሪከ: እስመ ምድር እንተ ትከይዳ ቅድስት ይዕቲ - የረገጥካት ምድር የተቀደሰች ናትና ጫማህን ከእግርህ አውጣ" አለው::

ኢያሱም የተባለውን አደረገ:: ለዚህ ነው ቤተ ክርስቲያናችን "ለመላእክት የጸጋ (የአክብሮ) ስግደት ይገባል: በቅዱሳኑ ፊትም ጫማ ተለብሶ አይቆምም" የምትለው:: ያ መሬት ሊቀ መላእክት ቢቆምበት ተቀድሷል:: ዛሬም ቤቱ በታነጸበት: ታቦቱ በተቀረጸበት ቦታ ሁሉ ቅዱሱ መልአክ አለና ጫማን አውልቆ: ባጭሩ ታጥቆ መግባት ይገባል::

ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ከኢያሱ ጋር ሆኖ አማሌቅን ጨምሮ የእሥራኤልን ጠላት አጥፍቷል:: ጥቅመ ኢያሪኮን (ቅጥሩን) አፍርሷል:: ምድረ ርስትን አውርሷል:: በገባኦን ፀሐይን: በቆላተ ኤሎምም ጨረቃን ሲያቆም ከእርሱ ጋር ሆኖ ረድቶታል::

🌿" ዱራታኦስና ቴዎብስታ "🌿

ቅዱሳኑ ዱራታኦስ (ዶርታኦስ) እና ቴዎብስታ (ቴዎብስትያ) የቅዱስ ሚካኤል ወዳጆች ናቸውና በዚህች ዕለት ይታሰባሉ:: በድርሳነ ሚካኤልና በመጽሐፈ ስንክሳር ተጽፎ እንደምናገኘው 2ቱ ቅዱሳን በተቀደሰ ትዳር ተወስነው: ሕጉን ትዕዛዙን ፈጽመው: ለነዳያን ራርተው: ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ተቀብለው የሚኖሩ ነበሩ::

ይልቁኑ ግን የጌታችን: የእመቤታችንን እና የቅዱስ ሚካኤልን መታሰቢያ ያለማስታጐል ያደርጉ ነበር:: ከጊዜ በሁዋላ ግን ሐብት ንብረታቸው አልቆ ተቸገሩ:: ግን የጨነቃቸው መቸገራቸው ሳይሆን የቅዱስ ሚካኤልን መታሰቢያ ሊያቆሙ መሆናቸው ነው::

አማራጭ ሲያጡ ተቀምጠው ተመካከሩ:: የቅዱሱ መልአክ ዝክር ከሚቀር ልብሳቸውን (ያውም የክብር ልብሳቸውን) ሊሸጡ ተስማሙ:: በዚህ መሰረት ቅዱስ ዱራታኦስ ወደ ገበያ ሲሔድ ወዳጁ ቅዱስ ሚካኤል ከሰማይ ወረደለት::

መንገድ ላይም የጦር መኮንን ሃገረ ገዢ መስሎ ተገናኝቶ አጫወተው:: ችግሩን ጠይቆም መፍትሔውን ነገረው:: "እኔ እዋስሃለሁና ለበዓል የሚያስፈልጉህን ነገሮች ሁሉ ገዝተህ አሰናዳ" አለው::

"እኔ ወደ ቤትህ መጥቼ ስለምስተናገድ አንድ አሣ አምጥተህ አቆየኝ:: እኔ ሳልመጣ ግን አትረደው" አለው:: ቅዱስ ዱራታኦስ የተባለውን ሁሉ ፈጽሞ ወደ ቤቱ ሲሔድ ድንቅ ነገርን ተመለከተ:: ሚስቱ ቅድስት ቴዎብስታ በቤቱ መካከል ሁና ቤቱ በበረከት ሞልቷል::

ማሩ: ቅቤው: እሕሉ ሁሉ በየሥፍራው ሞልቷል:: ባልና ሚስቱ ደስ ብሏቸው:: ነዳያንን ሲያበሉ: እንግዳ ሲቀበሉ ዋሉ:: በሁዋላ ያ መኮንን (ቅዱስ ሚካኤል) በቤታቸው መጥቶ ተስተናገደ::

በእርሱ ትዕዛዝ የአሣው ራስ (ሆድ) ሲከፈት በውስጡ 300 ዲናር ወርቅ (እንቁ) ተገኘ:: ቅዱሳኑ ይህን ተመልክተው ሲደነግጡ ቅዱስ ሚካኤል ክንፉን ዘርግቶ ራሱን ገለጸላቸው:: ደንግጠው በግንባራቸው ተደፉ::

እርሱ ግን "በተገኘው ሃብት እዳችሁን ክፈሉ:: ከዚህ በሁዋላ ግን በምድር አትቸገሩም:: በሰማይም ክፍላችሁ ከእኔ ጋር ነው" ብሎ ባርኩዋቸው ወደ ሰማይ ዐረገ:: እነርሱም በሐሴትና በበጐ ምግባር ኖረው ዐርፈዋል:: ለርስቱም በቅተዋል::

🌿+" ቅዱስ ባሕራን ቀሲስ "+🌿

የደጋግ ክርስቲያኖች ግን የድሆች ልጅ::
*በሕጻንነቱ በግፍ ወደ ባሕር የተጣለ::
*በእግዚአብሔር ጥበብ አድጎ የግፈኛውን ንብረት የወረሰ::
*በመልካም ትዳር በቅስና ያገለገለ::
*ምጽዋትን ያዘወተረ::
*አብያተ ክርስቲያናትን ያሳነጸ ደግ ክርስቲያን ነው::
¤አርፎ ቅዱስ ሚካኤል ወዳጁ በዕረፍተ ገነት አኑሮታል::

🌿+" አፄ በእደ ማርያም "+🌿

"በዕደ ማርያም" ማለት "በማርያም እጅ" እንደ ማለት ነው:: እኒህ ሰው የኢትዮዽያ ንጉሥ ሲሆኑ የነገሡትም በ1460 ዓ/ም ነው:: ደጉ አባታቸው አፄ ዘርዓ ያዕቆብ ሲያርፉ በመንግስቱ ተተክተው ሃገራችንን አስተዳድረዋል:: ድርሰት ደርሰዋል:: አብያተ መቃድስ አንጸዋል::

በተለይ ለቅኔ ትምሕርት ማበብ ልዩ የሆነ አስተዋጽኦ እንዳደረጉ ይነገራል:: ልክ በነገሡ በ10 ዓመታቸው ግን መንግስተ ምድር በቃኝ ብለው በምናኔ በርሃ ገብተዋል:: በዙፋናቸውም አፄ እስክንድር ተተክተዋል:: ጻድቁ ንጉሥ ግን ቅዱስ ሚካኤልን ይወዱት ነበርና በዚህች ቀን ዐርፈዋል::

አምላከ ቅዱሳን በክንፈ ሚካኤል ከክፉው ሁሉ ይሰውረን:: ከበረከታቸውም አይለየን::

ኅዳር 12 ቀን የሚከበሩ
ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ ሚካኤል ሊቀ መላእክት
2.ቅዱስ ኢያሱ ነቢይ
3.ቅዱሳን ዱራታኦስና ቴዎብስታ
4.አፄ በዕደ ማርያም ጻድቅ
5.ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ
6.ቅዱስ ባሕራን ቀሲስ
7.አባ ፊላታዎስ ሊቀ ዻዻሳት

ወርሐዊ በዓላት
1.ቅዱስ ላሊበላ ጻድቅ (ንጉሠ ኢትዮዽያ)
2.ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ
3.ቅዱስ ቴዎድሮስ ምሥራቃዊ (ሰማዕት)
4.ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ
5.አቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ
6.ቅዱስ ማቴዎስ ሐዋርያ
7.ቅዱስ ድሜጥሮስ ሊቅ

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

19 Nov, 17:37


ዘመን!

ክፍል-፪-(የመጨረሻ ክፍል!)

ዘመኑ መካሪ የበዛበት ነው። አንድም ሰው ሳይመሩ ስለአመራር የሚመክሩ፣
ኳስ መምታት ሳይችሉ ስለኳስ ትንታኔ የሚሰጡ፣
ትዳር ሳይዙ ስለትዳር  የሚመክሩ፣
እንዲሁም ልጅ ሳይወልዱ 3 ልጅ ወልደው ላሳደጉት ምክር የሚሰጡ የበረከቱበት ዘመን ነው።

እንዲህ ዓይነት ሰዎችን ሳይ ሱሪ የሚሸጡ ሴቶችን ይመስሉኛል። ሱሪ የሚሸጡ ሴቶች ለዓመታት ሱሪ እየገዛን ለለበስን ወንዶች ስለሱሪው ማማር አስተያየት ሰጥተው ሊሸጡልን ሲሞክሩ አልታዘባችሁም? ነገሩ እንደዚያ ያለ "ከጳጳሱ በላይ ካቶሊክ" ነን የሚሉ የበዙበት ሆኗል።

ለውጦችን ካልተረዳናቸው በብዙ መንገድ ተጎጂ ልንሆን እንችላለን። ዘመን ባመጣው ለውጥ እንዳንጎዳ ለውጦቹን መረዳት የመጀመሪያው ነገር ነው። ቀጣዩ ጉዳይ ከለውጥ ጋር ለመስማማት ራስን ማስተካከል ነው።

ከለውጥ ጋር ሳይስማሙ እንደ ዳይኖሰር ብን ብለው የጠፉ፣ ከራሳቸው ጋር የተጠፋፉ ሰዎች፣ ተቋሞች፣ ትዳሮች እና ሀገራት አሉ። ይህ እንዳይሆንብሽ ንቂ፣ ንቃ እንንቃ!

በኢኮኖሚው ለውጥ የኑሮ ጫና ሲከብድ የራስን አኗኗር ማስተካከል ነው። ለዚህም አንድ ገቢን መጨመር ካልሆነም ወጪን መቀነስ ነው።

ኑሮ ሲወደድ በፊት ይበቃ የነበረው ገቢ አሁን አይበቃም። በዚህም የቤት አኗኗር ይቃወሳል። ለዚህ መፍትሔው መጨቃጨቅ ሳይሆን ገቢን ለመጨመር መንቀሳቀስ ነው። ዳይ ወደ ስራ!

ሚስት ወይም ባል አንዳቸው ብቻ የሚሠሩ ከሆነ ሁለቱም ወደ ሥራ መሠማራት ነው። መሥራት መቀጠር ብቻ አይደለም ሚስት ያላትን ሙያ ገበያ ታውጣው! ወጧ ከጣፈጠላት በወጧ፣ ሽያጭ ላይ ከበረቴች በሽያጭ፣ በአስተዳደርና በልጆች አስተዳደግ ከተመሰገነች ልጆችን በአደራ እሷ ጋር በማዋል የራሷን ሥራ ፈጠረች ማለት ትችላለች።

ለሥራ የደረሱ ልጆች ካሉ ገቢ በሚያመጣ ሥራ ላይ ማሠማራት ነው። በትናንቱ ዓይነት አኗኗር እየኖሩ የባሰ ችግር ውስጥ ይገባ ይሆናል እንጂ ከችግር ማምለጥ አይቻለም። ንቁ! ዘመኑን ዋጁ! መስቀል ከማይወዱት እንዲሁም መስቀልን አጥብቀው ከሚጠሉት ሰዎች መስቀል ያለውን ጥለት ለመግዛት እንደ ምን ያለ አእምሮ ይሆን የተመቸን? እ?
ገቃችሁ? ይበቃናል! ለጠቢብኮ አንድ ቃል በቂ ነበር። ጌታችን ደቀመዛሙርቶችን ሲጠራ "#ተከተለኝ! የሚለው ቃል ብቻ በቂያቸው ነበር። እንዲህ ነገር እያንዛዛን ግን እንዴት መግባባት አቃተን? በዚያ በሰማኑ አንድ የተከበሩ የመጽሐፍ መምህር የግብጽ ገዳማትን እና የአባቶችን አሁናዊ ሕይወት ካዩ ከተረዱ ልምድም ከወሰዱ ቦኋላ ለልጆቻቸው #እኛ_ግን_አለን? ነበር ጥያቄያቸው። እውነት ግን እኛ ግን አለን!

ሥራ ከጠፋ የምትሠራበትን ዘርፍ ወይም ቦታ መቀየር አንድ አማራጭ ነው። ከሁሉ በላይ ግን የራስን ዓቅም መገንባት ወይም ያልተጠቀምክበት ዓቅምህን መጠቀም ብልህነት ነው። የተመረቅህበት ዘርፍ ሥራ ካላስያዘህ አሁን ነቃ ብለህ ሥራ በሚገኝበት ዘርፍ ተማር ወይም ራስህን አስተምር ወይም ወደ ሥራ ተሠማራ። ተሸከም፣ ፍለጥ፣ ጭቃ አቡካ፣ አንጽ፣ እርዳ!

አሁን በዘመናዊው አስኮላ አንድ ተመራቂ እንደተመረቀ በጣም ብዙ የተጠራ ክፍያ ካገኘ ከ8000 እስከ 9000 ብር አያልፍም!። አንተ በቀን ሸቅል በአሁን ዋጋ ከ400-1500 እንደሙያው በሚከፈልበት ሀገር ለዛውም ሰራተኛ ጠፍቷል እየተባለ በመንግስት ጉያ ምን አርመሰመሰህ?

ሲቪል ኢንጂነሪንግ ካላዋጣህ ኮምፕዩተር ግራፊክስ ወይም ማርኬቲንግ ተማር። ብቻ ለሥራ አብዝቶ በሚፈለግ ዘርፍ ተሰማራ። ሽጥ፣ አሻሽጥ፣ ነግድ፣ አስተባብር! ትምህርት የሥራ ምንጭ መሆኑ አብቅቷል ወዳጄ ንቃ!

ፖለቲካው በግጭት የተሞላ ከሆነ አካባቢህን ቀይር። ዝሆኖቹ ሲራገጡ የሚጎዳው ሳሩ ነው የሚለውን የአፍሪካውያን ብሂል አስታውስ። ሳሩስ እሺ መሄድ አቅቶት ይረገጥ አንተን ግን ምን ያዘህ? ሰሜኑ አላሰራህ ካለ ምስራቅ፣ ደቡብ፣ ምእራቡ ምን አለህ? ለዚህ ደሞ ከዘር አሸንክታብ፣ ከሴራ ራስህንና ልብህን አጽዳ! አንገትህን ብቻ ሳይሆን ራስህን አዋርደህ ድፍን ኢትዮጲያን ዙራት! ወዳጄ፣ ዘመዴ፣ እናቴን አባቴን ካልክ አብረህ እከክ! ወዳጄ ከዚህ በኋላ መንግስት ቢቀየርኮ እንዲህና ይሔ ቢሆን በሚል የሞኝ ተስፋ የኑሮ ውድነት ይረክሳል ብለህ አትጠብቅ።

የኤሌክትሪክ፣ የነዳጅ፣ የውሃ ዋጋ ይወርዳል ብለህ ከጠበክ አንተ በእውነት የአለማችን ትልቁ ሞኝ ነህ ከወጣ ወጣ ነው ወዳጄ። የአቅራቢው ስግብግብነት አብዝቶ ስላየለ የአቅራቢው ብዛት ወይም ዓይነት ካልተቀየረ እንዲሁም ፈሪሀ ፈጣሪ ፈሪሀ እግዚአብሔር ካልታከለበት በቀር ፈጽሞ አይወርድም ለዚህ ደሞ ከጎረቤቶችህ ጀምሮ አይደለም ከነሱ ከቤተሰብህ ጀምሮ ብዙ የቤት ሥራዎች ይጠበቁብሀል።

ይልቅ የጤፍ ስንዴ እና በቆሎ ዋጋ ሊወርድ ይችላል። ይህ የሚሆነው ግን እንደሚወራው ምርት ከጨመረ ነው። ምርት ጨምሮ ዋጋ ካልወረደ ችግር አለ። ችግሩም ገንዘብ ታትሞ ከተረጨ ነው። አዲስ የሚረጭ ገንዘብ የሰዎችን ጥሪት በማመንመን ትርፉ ችግር መፍጠር ነው። አሁን መንግስት እያደረገ ያለው ከገበያ ጥሬ ብር የማጥፋት ዘዴ ወደድክም ጠላህም ለሕዝቡ ጠቃሚ ነው!

እንግዲህ የዘመኑ ለውጥ ለትምህርት፣ ለሥራ፣ ለጉዞ፣ ለቀለብ፣ ለትዳር፣ ለልጅ አስተዳደግ፣ ለዜና እና መረጃ፣ ለግንኙነት፣ ለንግድ፣ ለሀገር፣ ... ያለውን አስተሳሰብ ከሥሩ እየናደ እና በአዲስ አስተሳበብ እየተካ ነው። መደበኛ ትምህርት አለመማር፣ ከቤት ሆኖ መሥራት፣ አለማግባት ወይም ተመሳሳይ ጾ'ታ መጋባት ወይም መፋታት፣ ልጅ ለብቻ ማሳደግ፣ የሃይማኖት መሠረቶች መለወጥ፣ የልጅ ነጻነት መስፋት፣ የመረጃ መብዛት፣ የጊዜ ማጠር፣ የአዲስ ፈጠራ መብዛትና መስፋፋት የአዲሱ ዘመን ፈተናዎች ናቸው።

ይህንን ለመቋቋም አዲስ እና በፍጥነት ራሱን የሚቃኝ የአስተሳሰብ መንገድ ወይም የልቦና ውቅር #mindset ከቅዱሱ መጽሐፍ ጋር አዋዶ የሚሔድ ትውልድ ያስፈልገናል።

አሁን በለውጥ ጎርፍ መሃል ቆሞ መፍራት አያዋጣም፣ ልብስን አውልቆ ለመዋኘት መፍራትም አያዋጣም፣ ዳር ቆሞ ማየትም አያዋጣም። የሚሻለው ሳያፍሩ ልብስን አውልቆ እየዋኙ መሻገር ነው። ለዚህ የዋና ዓቅምን መገንባት ግድ ነው። ኢኮኖሚው ቤተክርስቲያንን እየፈተነ ነው። ስለዚህ ወለተ እንትና ወልደ ትንሤኤ ና፣ ነይ አውጪ፣ አውጣ ሳይሆን ራሷን በማይናወጥ መሠረት ላይ ገንብታ የሰውን ኪስ ሳይሆን ሕይወት የምትሳሳ ቤተክርስቲያን እና አስተዳደር አቅም እንዲኖረን መትጋት ግድ ይላል!

ስለዚህ ወዳጄ የሚያዋጣው ሁሉን መመርመር፣ መልካሙን መያዝ ነው።

"ኩሉ አመክሩ ወዘሰናይ አጽንዑ"

ተብሎ የለ?

ይቆየን!
አስተያየት ካላችሁ ለመቀበል ዝግጁ ነን!

ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን!

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

19 Nov, 14:18


ዘመን!

ክፍል-፩-

አንድ ወዳጄ "ዘመኑ ተቀይሯል!" በሚል አርዕስተ ጉዳይ በማኅበራዊ ሚዲያ ባስነበበን የሀሳብ መነሻ እኔም የራሴን አክዬ ለናንተ ለወዳጆቼ እንዲህ አሰናስየዋለሁ።

ዘመን!
ዘመኑ ብዙ ለውጦችን እያስተናገደ ነው። ለውጦች በቴክኖሎጂ፣ በህግ፣ በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በማህበራዊ አኗኗር፣ በሥራ ሁኔታ፣ በአስተሳሰብ፣ በትዳር፣ በልጆች አያያዝ፣... በመሳሰሉት እየታዩ ነው። የአንድ ሀገር መሠረት ከጤናማ ቤተሰብ ይጀምራል ያም ሆኖ ያለምክንያት የሚፈርስ ትዳርን በአሐዝ ለመግለጽ ከባድ ሆኗል። ይህ ለውጥ በዓለም ዙሪያ ቢታይም የለውጡ ጫና በአንዳንድ ሀገራት የበረታ ነው። በሀገራችንም የለውጡ ጫና የበረታ ለመሆኑ ማስረጃ አያሻም።

ሰዉ ሁሉ ዋና ነገሩ አንድም ብሩ አንድም የእጅ ስልኩ ሆኗል። የዛሬ 20 እና 25 ዓመት የእጅ ስልክ መያዝ ብርቅ ነበር። ዛሬ ከቴሌቪዥን ስክሪን በላይ የሚጎበኘው የእጅ ስልክ ሆኗል። የሰው ሁሉ ዋና ንብረቱ የእጅ ስልክ ሆኗል። የእጅ ስልክ አለመያዝ ከዘመኑ ውጭ መሆን ነው። የእጅ ስልክ መጥፋት በእጅጉ ይረብሻል እሱ ብቻ አይደለም ሥራንም ያበላሻል፣ ላልተዘጋጁት መረጃን ያጠፋል።

በዚህ ዘመን የተለወጠው የስልኩ ዓይነት ብቻ አይደለም። ስልኩ ይዞ የሚያመጣውና የሚያገናኘው የሰው ዓይነትና ሃሳብም እንደ ድሮው ሳይሆን ዛሬ እጅግ ተለውጧል። የዘመኑ ቴክኖሎጂ ላንተ የሚያስብልህን ብቻ አይምሰልህ ወዳጄ የሚያቀርበው ወዳጅ መስሎህ ገደል የሚከትህን ሰው በብርሃን ፍጥነት ያመጣልሃል እንጂ።

በዚያው ልክ ደግሞ በጥሩ መልኩ መልካሙን አስቦ ለሚውል ምስኪን ሰው 'ሰው! የሆነ ሰው ያገናኝሃል። ይህ የሚወሰነው በራስህ ሀሳብ ልክ ነውና ሀሳብህን አጥራ።
ስለዚህ ወዳጄ ሆይ ከተኛህ ንቃ!

ስማርት ስልክ ስላለህ ስማርት አትሆንም
የዘመኑ ስማርት ሰው ከዚህ ሁሉ መባዘን ሊያድነው የሚችለውን እሱነቱን በማግኘትና ባለማግኘት የሚመዘን የተረጋጋ እና የተመጠነ ሕይወት ለመምራት የተዘጋጀ ሰው ብቻ ነው።

ሁሉ ነገር በመረጃ ብለው መተማመናችንን ያጠፉት ሰዎች ሁሉ አሁን ያለ መረጃና ማስረጃ የሚያምኑት አንድ መንፈሳዊ ኃይል ከሕይወት ሚዛን ከተጓደለ ሰዎች ሕይወትን አልኖሯትም ብለው ደምድመዋል። ይሔ ጥቅል ሀሳብ ሚዛናዊ ሕይወት(Balanced life ) ይባላል።

እንደ ኢትዮጲያዊነት ከመዘንን ኢትዮጲያዊነት እራሷ ሚዛናዊነት ነው። ኢትዮጲያ እንዳሁኑ በመጤ ወጎች፣ በመጤ እሳቤዎችና በመጤ አስተምሮዋ ሳትበረዝ እስልምናውም ሆነ ክርስትናው ወግ ነበረው ያ ዘመን ብናምንም ባናምንበትም የኢትዮጲያዊነት ልክ የኢትዮጲያ ሚዛን ነው። እስኪ አንዳንድ የኢትዮጲያ ገጠራማ አከባቢዎች ለመጎብኘት ሞክሩ!
ኢትዮጲያ ማለት ከ15-20% ከተማ ከ80-85% ገጠራማ ናት።
እና?
እናማ ከተማ ተወልደን ከተማ ካደግን አሊያም ገጠር ተወልደን በልጅነት ከተማን ለተቀላቀልን አሊያም ከተማ ተወልደን ላረጀን ኢትዮጲያ የምናውቃት ብቻ እንዳልሆነች የሚያስረዳን የገጠሩ ያልተበረዘ ማንነታችን ነውና ስለ ሚዛናዊ ሕይወትና ኑሮ ሁለቱን እንጎብኝ።

ክፍል-፪-
ይቀጥላል!. . . .

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

19 Nov, 14:18


ስንክሳር ኅዳር 11

"እንኩዋን "ለቅድስት ወብጽዕት ሐና" (እመ ማርያም) ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ "

" ብጽዕት ሐና "

"ሐና" ማለት በእብራይስጥኛው "የእግዚአብሔር ስጦታ" እንደ ማለት ነው:: "ሐና: ዮሐና: ሐናንያ" የሚሉ የዕብራይስጥ ስሞች ትርጉማቸው ተወራራሽ ነው:: የዚህችን ቅድስት እናት ክብሯን መናገር የሚችል የለም:: እርሷ ሰማይና ምድርን ለፈጠረ ለእግዚአብሔር ወልድ በሥጋ አያቱ ተብላለችና::

👉 አንድም ለሰማይና ለምድር ንግስት ለድንግል ማርያም ወላጅ እናቷ ናትና:: ከዓለም ሴቶች ሁሉ የቅድስት ሐና ማሕጸን እንደ ምን ይከብር! በፍጥረት ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ጥንተ አብሶ (የአዳም በደል) መተላለፍ የቀረው በማሕጸነ ሐና ውስጥ ነውና:: (ለዚህ አንክሮ ይገባል!!!)

ይስሐቅን የተሸከመ የሣራ ማሕጸን ቡሩክ ከተባለ የቅድስት ሐናማ እንደምን አይባል! ከፍጥረታት ሁሉ እግዚአብሔር ድንግል ማርያምን እንደ መረጠ ሁሉ ቅድስት ሐናንም ለአያትነት መርጧታል::

🙏 ለመሆኑ ቅድስት ሐና ማን ናት? ለዚህ ክብርስ ያበቃት ምሥጢረ ቅድስናዋ ምንድን ነው?

ቅድስት ሐና ትውልዷ: ነገዷ ከላይ ከቅዱስ አብርሃም: ከታች ደግሞ ከነገደ ካህናት ነው:: ይሕስ እንደ ምን ነው ቢሉ:-

👉 አብርሃም ይስሐቅን: ይስሐቅ ያዕቆብን: ያያዕቆብ ደግሞ ሌዊንና 11 ወንድሞቹን ይወልዳል::
👉 ሌዊ ቀዓትን: ቀዓት እንበረምን: እንበረም አሮን ካህኑን ይወልዳሉ::
👉 ቅዱስ አሮን አልዓዛርን: አልዓዛር ፊንሐስን እያለ ትውልዱ እስከ ቴክታና በጥሪቃ ይወርዳል:: ቴክታና በጥሪቃም ልጅ በማጣት ኖረው: የእንቦሳዎች: የፀሐይና: የጨረቃን ምሥጢር ተመልክተው ሄኤሜንን ይወልዳሉ::
👉 ሄኤሜን ዴርዴን: ዴርዴ ቶናሕን: ቶናሕ ሲካርን: ሲካርም ሔርሜላን ይወልዳሉ::
👉ሔርሜላም ከክርስቶስ ልደት 90 ዓመታት በፊት ማጣት ("ጣ" ጠብቆ ይነበብ) የሚባል ደግ ሰው ከካህናት ወገን አግብታ በስርዓተ ኦሪት ትኖር ነበር:: እግዚአብሔር ለዚህች ደግ ሴት የተባረኩ 3 ሴቶች ልጆችን ሰጣት::

የመጀመሪያዋን "ማርያም" አለቻት:: ይህቺውም የአረጋዊው ዮሴፍ ሚስትና የቅድስት ሰሎሜ ቡርክት እናት ናት:: ሁለተኛዋን "ሶፍያ" አለቻት:: እርሷም ቅድስት ኤልሳቤጥን (የመጥምቁን እናት) ወልዳለች:: በመጨረሻ የወለዷትን ግን "ሐና" አሏት:: ይህቺውም የፈጣሪ የሥጋ አያቱ: የድንግል ማርያምም እናቷ ትሆን ዘንድ የተመረጠችውና ስም አጠራሯ የከበረው: ዛሬ የምናከብራት እናት ናት::

መጽሐፈ ስንክሳርን ስመለከት እንዲህ የሚል ዓረፍተ ነገር አየሁ:: "ለዛቲ ቅድስት ኢያዕመርነ ገድላቲሃ ዘትገብሮን በኅቡዕ ከመ ንዝክሮን" ይላል:: ትርጉሙም "የዚህቺን ቅድስት ገድሏንና ትሩፋቷን እንዳንዘረዝር አላወቅነውም" እንደ ማለት ነው::

የሚገርመው አበው እንዲህ ያሉት ክብሯን መግለጹን አልጠግብ ብለው ነው:: እኛም በመጠናችን የብጽዕት ሐናን ሕይወት በአጭሩ ቀጥለን እንመልከት::

ብጽዕት ሐና ወላጆቿ (ማጣትና ሔርሜላ) ከካህናት ወገን በመሆናቸው ልጆቻቸውን በጥንቃቄ: በሥርዓተ ኦሪት እንዳሳደጉ ይታመናል:: ቅድስት ሐናንም ለአቅመ ሔዋን እስክትደርስ ድረስ በሕጉ: በሥርዓቱ አሳድገዋታል::

በወቅቱ በፈቃደ እግዚአብሔር ትውልዱ ከነገደ ይሁዳ የሚሆን አንድ ደግ ሰው አጩላት:: ይህ ሰው "ኢያቄም" ይባላል:: አንዳንዴም "ሳዶቅ" ወይም "ዮናኪር" እየተባለ ይጠራል:: ቅዱስ ኢያቄም ማለት ክፉ ከአንደበቱ የማይወጣው: ምጽዋትን የሚወድ: አምላከ እሥራኤልን በንጹሕ ልቡ የሚያመልክ ሰው ነበረ::

እንደ ኦሪቱ ሥርዓት 2ቱ (ኢያቄም ወሐና) ከተጋቡ በሁዋላ ቶሎ መውለድ አልቻሉም:: ይሕ ደግሞ የወቅቱ ከባድ ፈተና ነው:: በዘመድ የከበሩ: በጠባያቸው የተመሰገኑ: መልካምንም የሚሠሩ ሰዎች ልጅ ስለሌላቸው ብቻ "ኅጡአነ በረከት" እየተባሉ ከቤተ እግዚአብሔር ይገፉ: በአደባባይም ይነቀፉ ነበር::
ምክንያቱም በብሉይ ኪዳን ልጅ አለመውለድ እንደ ኃጢአተኛ ያስቆጥር ነበር:: ደግነቱ የወቅቱ ሊቀ ካህናት ቅዱስ ዘካርያስ (የመጥምቁ አባት) እንደ እነሱ ልጅ ያጣ በመሆኑ አብረው ይጽናኑ ነበር::
የሆነው ሆኖ እኒህ ቡሩካን ሰዎች አምላከ እሥራኤልን ከመለመንና ከማመስገን በቀር ሌላ ትርፍ አልተገኘባቸውም:: ምንም የሞላቸውና የደላቸው ባይሆኑም ደሃን ሳያጐርሱ አይበሉም ነበር::
ቅድስት ሐናን ግን "ቢወልዷት እንጂ አትወልድ: ድንጋይ: በቅሎ" እያሉ ጐረቤቶቿ ይሳለቁባት ነበር:: ከማልቀስ በቀር ደግሞ መልስ አልነበራትም::
አንድ ቀን ግን ርግቦች ከልጆቻቸው ጋር ሲጫወቱ ተመልክታ "ፈጣሪ ሆይ! የእንስሳትን ማሕጸን የምትከፍት: ዕፀዋትንም ከባሕርያቸው እንዲያፈሩ የምታደርግ:: እውነትም ሐናን ድንጋይ አድርገህ ፈጥረሃታልን?" ስትል አለቀሰች::
ቅዱስ ኢያቄምም ወደ ተራራ ወጥቶ ለ40 ቀናት አለቀሰ: ተማለለ:: ይህ ሲሆን 2ቱም አርጅተው ነበር:: ሐምሌ 30 ቀን ግን ነጭ ርግብ 7ቱን ሰማያት ሰንጥቃ በማሕጸነ ሐና ስታድር አዩ:: ደስ ብሏቸው ለ7 ቀናት ሱባኤ ይዘው ቅድስት ሐና እመቤታችንን ነሐሴ 7 ቀን ጸነሰቻት::
ይሕም ለእነርሱም: ለወገኖቻቸውም ታላቅ ተድላ ሆነ:: ብጽዕት ሐና ግን ፈጣሪዋን ታከብረው ዘንድ በጐነትንና ንጽሕናን አበዛች:: ጸንሳ ሳለም ዕውራንን አበራች: ድውያንን ፈወሰች::
የጦሊቅ ልጅ በሞተ ጊዜም እያለቀሰች ስትዞረው ጥላዋ ቢያርፍበት አፈፍ ብሎ ተነስቶ:- "ሰላም ለኪ እሙ ለፀሐየ ጽድቅ" ብሎ ድንግል ማርያምን::
"ወሰላም ለኪ እምሔውቱ ለዘገብረ ሰማየ ወምድረ" ብሎ ቅድስት ሐናን አመስግኗል:: ትርጉሙም ድንግልን "የፀሐየ ጽድቅ እናቱ": ሐናን "ሰማይና ምድርን ለፈጠረ አያቱ" ማለት ነው::
ይህንን ያዩ አይሁድ ቅድስት ሐናን ሊገድሉ ብዙ ጊዜ ሞክረዋል:: ግን መልአከ ሰላም ቅዱስ ገብርኤል አልፈቀደላቸውም:: ግንቦት 1 ቀንም የሰማይና የምድር ንግስትን ሊባኖስ ተራራ ላይ ወልዳ ሽሙጥን ከሁላችንም አራቀች::

ስሟን "ማርያም-የአምላክ ስጦታ" ብለው ሰይመው ለ3 ዓመታት አሳድገዋታል:: የሚገርመው በ3ቱ ዓመታት ውስጥ ቅድስት ሐና ድንግል ማርያምን ከክንዷ አውርዳት አታውቅም ነበር:: አንድ ጊዜም መላእክት ወስደውባት ፍጹም አልቅሳለች:: ሁዋላ ግን መልሰውላታል::

ሌላኛው የሚደንቀው እግዚአብሔር የዓለም ውዱን ስጦታ እመ ብርሃንን ሰጣቸው:: እነርሱም ይሕችን ውድ ስጦታ ሳይሰስቱ ለፈጣሪ መለሱለት::

ቅድስት ሐና ድንግል ወደ ቤተ መቅደስ ከገባች በሁዋላ የእናትነት ፍቅሯ እያገበራት ለ5 ዓመታት እየተመላለሰች ትጐበኛት: ትስማት ነበር:: እመቤታችን 8 ዓመት በሞላት ጊዜ ግን የእግዚአብሔር ጥሪ ወደ ቅድስት ሐና ደረሰ::

ከክርስቶስ ልደት 8 ዓመታት አስቀድማ ብጽዕት እናት ሐና በዚህች ቀን ዐረፈች:: ትንሽ ቆይቶም ባለቤቷ ቅዱስ ኢያቄም ተከተላት እኛም ልጆቿ "ብጽዕት ሐና ብጽዓን ይገባሻል!" እያልን እናመስግናት::

ኅዳር 11 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅድስት ሐና ቡርክት2.ቅዱስ አርኬላዎስ ሰማዕት
3.አባ ኤልሳዕ አበ ምኔት
4.አባ ዻኩሚስ መነኮስ
5.ቅዱስ ሚናስ ሰማዕት
6.ቅድስት አውራንያ (የሰማዕቱ እናት)

ወርሐዊ በዓላት
1.ቅዱስ ያሬድ ካህን
2.ማር ገላውዴዎስ ሰማዕት
3.ቅዱስ ፋሲለደስ ሰማዕት
4.አቡነ ሐራ ድንግል ጻድቅ

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

19 Nov, 07:36


🙏 ስንክሳር ኅዳር 10 🙏

✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞

✞ ኅዳር 10 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ✞

✞ ቅድስት ሶፍያ ወቅዱሳት አንስት ✞

✞ እስኪ ዛሬ በጥቂቱ የተባረኩ (ቡሩካት) እናቶቻችን እንዘክር:: "ቅድስት" የሚለው ቃል ለሁሉም ቅዱሳት እናቶች ቢሰጥም ቅሉ ለድንግል ማርያም ሲሰጥ ግን ትርጉሙ ይለያል:: እርሷ 'ቅድስተ ቅዱሳን: ንጽሕተ ንጹሐን: ቡርክት እምቡሩካን: ኅሪት እምኅሩያን ናትና::

ከሰው ልጆችም ሁሉ ትበልጣለች:: ይቅርና የሰው ልጅን ንጹሐን መላእክትንም በንጽሕናና በቅድስና ትበልጣቸዋለች:: እርሷ እመ ብርሃን: የአምላክ እናቱ: የሰውነታችን መመኪያ ናትና::

እመቤታችንን "ቅድስት" ስንል "ጽንዕት: ንጽሕት: ክብርት: ልዩ" ማለታችን ነው::
1."ንጽሕት" ትባላለች:: ሌሎች ሰዎች (ቅዱሳን) ቢነጹ ከገቢር: ከነቢብ ኃጢአት ነው እንጂ ከኃልዮ ኃጢአት አይደለም:: እርሷ ግን ከነቢብ: ከገቢር: ከኃልዮ ንጽሕት ናት::

"ለመኑ ተውኅቦ ተደንግሎ ኅሊና: ለመላእክትሂ ኢተክህሎሙ-ኃጢአትን ከማሰብ መጠበቅ ከሰው ልጆች ለማን ተሰጠው: ይህስ ለመላእክትም አልተቻላቸውም" እንዲል:: (ተአምረ ማርያም)

2."ጽንዕት" እንላታለን:: ሴቶች ቢጸኑ ለጊዜው ነው እንጂ በኋላ በጊዜው ተፈትሆ አለባቸው:: እመቤታችን ግን ቅድመ ጸኒስ: ጊዜ ጸኒስ: ድኅረ ጸኒስ: ቅድመ ወሊድ: ጊዜ ወሊድ: ድኅረ ወሊድ ድንግል ናትና::

"ጽንዕት በድንግልና አልባቲ ሙስና" እንዳላት:: (ቅዱስ ያሬድ) ታላቁ ቅዱስ ባስልዮስም "ወትረ ድንግል ማርያም-ማርያም ዘለዓለማዊት ድንግል ናት" እንዳለ:: (መጽሐፈ ቅዳሴ)

3.ድንግልን "ክብርት" እንላታለን:: ሌሎች ሴቶች ቢከብሩ ጻድቃን ሰማዕታትን: ነቢያት ሐዋርያትን ወልደው ነው:: እመቤታችንን ግን የምናከብራት "ወላዲተ አምላክ-የአምላክ እናቱ" ብለን ነውና::

4.እመቤታችንን "ልዩ" እንላታለን:: ከእርሷ በቀር እናት ሁና ድንግል: እመቤት ሁና አገልጋይ የሆነች: በድንግልና ወልዳ ወተትን (ሐሊበ ድንግልናዌን) ያስገኘች ሌላ ሴት የለችምና::

የእመ ብርሃን ይቆየንና ደግሞ ሌሎች ቅዱሳት እናቶቻችንን እንመልከት:: እናቶቻችን ስናከብር የምንጀምረው በቅድስት ሔዋን ነው:: ብዙ ጊዜ የእናታችን ሔዋን ጥፋቷ እንጂ በጐ ነገሯ: ደግነቷ: ንስሃዋ አይነገርላትም:: ሆኖም እናታችን ቅድስት ሔዋን ክብር የሚገባት ሴት ናት::

ክርስቶስ ሰው የሆነ እርሷንና ልጆቿን ለመቀደስ ነውና:: "ከመ ይስዓር መርገማ ለሔዋን ዲበ ዕፅ ተሰቅለ" እንዲል:: (ድጓ)

ቀጥሎ በብሉይ ኪዳን እነ ሐይከል: እድና: ሣራ: ርብቃ: አስኔት: ሲፓራ: ሐና: ቤርሳቤህን የመሰሉ እናቶቻችን በበጐው መንገድ ፈጣሪን ደስ አሰኝተዋል:: በዘመነ ሥጋዌም ቅዱሳቱ ሐና: ኤልሳቤጥ: ማርያም: ሶፍያ: ሰሎሜ: ዮሐና እና 36ቱ ቅዱሳት አንስት በጐነታቸው ያበራል::

ከዚያ ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ ለ2,000 ዓመታት የተነሱ አእላፍ ቅዱሳት እናቶቻችንን ግን ዘርዝረን አንዘልቃቸውም:: በቅድስናቸው አራዊትን ያሰገዱ: ነገሥታትን ያንቀጠቀጡ: አጋንንቸትን የረገጡ: በዘንዶ ላይ የተጫሙ ብዙ እናቶችን ቤተ ክርስቲያን አፍርታለች::

ዛሬም ቢሆን በበርሃና በከተማ በጐውን ጐዳና የተከተሉ ብዙ እናቶች እንዳሉን እናውቃለን:: አንድም እናምናለን:: ግን ግን በከተሞች የምንመለከተው ሥርዓቱን የለቀቀው የበርካታ እህቶቻችን አካሔድ ለሃገርም ለቤተ ክርስቲያንም ትልቅ ስጋት ነው:: ክብርና ነውር የማይለይበት ዘመን ይመስላል::

ይህንን እያነበባችሁ ያላችሁ እህቶቼ! አንድ ነገር ልንገራችሁ:: በመልካቸው ብዙዎችን ያጋጩ: አጊጠው በመታየታቸው ብዙዎችን ያሰናከሉ: ለብዙ ምዕመናንም የጥፋት ምክንያት የሆኑ ብዙ ሴቶች በታሪክ ነበሩ::

የሚያሳዝነው ግን ዛሬ ያሉት ከመሬት በታች ነው:: አፈር በልቷቸዋል:: ስም አጠራራቸውም ጠፍቷል:: በጣም የሚያሳዝነው ደግሞ ዛሬ በዘለዓለማዊው እሳት እየተቃጠሉ በሲኦል: በጥልቁ ውስጥ አሉ::

እናም ወገኖቼ! ይህን አውቀን እንንቃ:: ይህ ዓለም ጠፊም: አጥፊም ነውና:: እድሜአችን ቢረዝምና ከዚህ በኋላ ለ100 ዓመታት ብንኖርም እርሱም ማለቁ አይቀርምና:: ምርጫችን ዘለዓለማዊው ሕይወት ይሁን ትላለች ቅድስት ቤተ ክርስቲያን::

🌿+" እለ ቅድስት ሶፍያ "+🌿

ቅድስት ሶፍያና አብረዋት በዚህ ዕለት የሚከበሩ ቅዱሳት አንስት በ4ኛው መቶ ክ/ዘመን በሮም የነበሩ ክረስቲያኖች ናቸው:: አብዛኞቹ መልክ (ደም ግባት) ከጠባይ ጋር የተስማማላቸው ነበሩ:: ነገር ግን ከምድራዊው ክብር ሰማያዊውን መርጠው ለመንፈሳዊው ሙሽርነት ወደ ገዳም ገቡ::

ከእነዚህ ቅዱሳን መካከል በጸጋና በሞገስ: በትምሕርትም የምትበልጥ ቅድስት ሶፍያ ናትና እመ ምኔት አድርገው ሾሟት:: እርሷም ለገዳሙ በጐውን ሥርዓት ሠራች:: ሁሉም (ደናግሉም መነኮሳይያቱም) በአንድነት ይጾማሉ: ይጸልያሉ: ይሰግዳሉ: የቅዱሳንን ተጋድሎ ያነባሉ:: ሥጋውን ደሙን ይቀበላሉ::

እርስ በርስ ደግሞ ፈጽመው ይፋቀራሉ:: በዚህ ሕይወት አንዳንዶቹ እስከ 70 ዓመት ቆዩ:: የቅድስናቸው ዜና ሲሰማ በሮም ግዛት ያሉ ወጣት ሴቶች እየመጡ ይቀላቀሏቸው ነበር:: ቅድስት ሶፍያም የሕይወትን መንገድ ታሳያቸው ነበር::

ከዚህ ሁሉ በኋላ ከሐዲው ንጉሥ ዑልያኖስ ለጦርነት ወደ ፋርስ ሲሔድ ስላያቸው ባንድነት ሰብስቦ ሁሉንም በሰይፍ አስመታቸው:: ቅድስት ሶፍያም አብራ ሰማዕት ሆነች:: ስለ ቅዱሳኑ የሚበቀል ጌታም ቅዱስ መርቆሬዎስን ልኮ በጦርነቱ መካከል በጦር ወጋው:: ዑልያኖስ ወደ ዘለዓለም ኩነኔ ሲሔድ: ቅዱሳት አንስት ወደ ገነት ሔደዋል::

+" ባሕረ ሐሳብ "+

+ዳግመኛ በዚህ ቀን: በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን ባሕረ ሐሳብ በዓለማቀፍ ደረጃ ተቀባይነትን አግኝቷል:: ሊቁ ቅዱስ ድሜጥሮስ (የግብጽ 12ኛ ፓትርያርክ) መንፈስ ቅዱስ ቀመረ ባሕረ ሐሳብን ገልጾለት በዓለም ላሉ ሊቃነ ዻዻሳት ልኮላቸው በዚህች ዕለት በሮም ከተማ ተሰበሰቡ::

ሊቃውንትም ሐዋርያት ካስተማሩት ጋር ተመሳሳይ ሆኖ ቢያገኙት በደስታ ተቀብለውታል:: እነሆ እስከ ዛሬ ድረስ ለ1,700 ዓመታት ቤተ ክርስቲያን እየተገለገለችበት ይገኛል::

የቅዱሳት እናቶቻችን አምላክ ዛሬም እንደ እነርሱ ያሉትን አያሳጣን:: በጸሎታቸው ምሮ ከበረከታቸው ይክፈለን::

ኅዳር 10 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅድስት ሶፍያ ሰማዕት
2.ደናግለ ሮሜ (ሰማዕታት)
3.ቅዱስ ዻውሎስ ሰማዕት
4.ቅዱስ ድሜጥሮስ ሊቅ
5.ጉቡዓን ኤዺስ ቆዾሳት

=> ወርኀዊ  የቅዱሳን  በዓላት
1.ቅዱስ ናትናኤል ሐዋርያ
2.ቅዱስ ኒቆላዎስ ዘሃገረ ሜራ
3.አቡነ መልክዐ ክርስቶስ
4.ቅዱስ ያዕቆብ ሐዋርያ (ወልደ እልፍዮስ)
5.ቅድስት ዕሌኒ ንግስት
6.ቅዱስ ዕፀ መስቀል
7.ታላቁ ቅዱስ ቆስጠንጢኖስ

" ለእናንተም ጠጉርን በመሸረብና ወርቅን በማንጠልጠል ወይም ልብስን በመጐናጸፍ በውጭ የሆነ ሽልማት አይሁንላችሁ:: ነገር ግን በእግዚአብሔር ፊት ዋጋው እጅግ የከበረ የዋህና ዝግተኛ መንፈስ ያለውን የማይጠፋውን ልብስ ለብሶ የተሰወረ የልብ ሰው ይሁንላችሁ:: " (1ዼጥ. 3:3)

ቤተሰብ ይሁኑ
👇👇
✍️† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †✍️
               🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

18 Nov, 09:18


ቦታ እና ማዕድን ብቻ አይደለም ሙሉ ከተማ ለባለሀብት መሸጥን በመለማመድ ላይ ነን?

ነገ ደሞ ሀገር ትሸጥ ይሆን?

#ከዜናዎቻችን| የቢሾፍቱ ከተማ ለዱባይ ባለሀብቶች በሊዝ ሊሰጥ መሆኑን መረጃ ማቅረባችንን ተከትሎ ነዋሪዎች አዲስ መረጃ ከመንግስት ተነገረን አሉ

(መሠረት ሚድያ)- መሠረት ሚድያ ባሳለፍነው ሳምንት ባጋራው መረጃው ቢሾፍቱ ከተማ ለዱባይ ባለሀብቶች በሊዝ እንደተሸጠ ለነዋሪዎች እንደተነገራቸው ጠቁሞ ነበር።

በዚህም ምክንያት ነዋሪዎች በአንድ ሳምንት ከመኖርያ እና የስራ ቦታቸው እንዲነሱ መታዘዛቸው መታወቁን ዘግበን ነበር።

ይህን ተከትሎ በደረሰን መረጃ መሰረት ደግሞ የቢሾፍቱ ከተማ አመራሮች ባሳለፍነው ሳምንት መባቻ ነዋሪዎችን ሰብስበው የአየር ካርታ ላላቸው ነዋሪዎች በምትኩ 105 ካሬ ቦታ እንሰጣለን ማለታቸው ታውቋል።

"በተመሳሳይ ለገበሬዎች 105 ካሬ እና የሊዝ ዋጋ ካሳ እንከፍላለን ብለውን ሄደዋል" በማለት ተናግረዋል።

ቢሾፍቱን 'በምስራቅ አፍሪካ የቱሪዝም ማዕከል' ለማድረግ እየተሰራ ካለው ስራ ጋር በተያያዘ በርካታ የከተማው ቦታ ለተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ሊሰጥ እንደሆነ በመጀመርያ የተሰማው የዛሬ ሁለት ወር ገደማ ነበር።

(#ከዜናዎቻችን በሳምንቱ በቪድዮ ዩትዩብ ላይ ያቀረብናቸውን የተመረጡ መረጃዎች ቆየት ብለን በድጋሜ በፅሁፍ የምናቀርብበት አምድ ነው)

መረጃን ከመሠረት!

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

18 Nov, 06:06


ቅበላ እና የቅበላ ነገር
እንኳን ደስ አለን እንኳንም አደረሰን!

💠💠💠   የገና ጾመ 💠💠💠
እንኳን በድጋሜ ለገና ጾም በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን!🙏

🌹የገና ጾም የሚጀምረው- እሁድ ኅዳር 15 ሲሆን የጌታችን ልደትና የጾሙ ፍፃሜ ደግሞ :-ታህሣስ 29 ይውላል።

በዚህ መሠረት የዚህ ዓመት ጾም መግቢያ የፊታችን እሁድ በእለተ ሰንበቱ ኅዳር 15 ይጀምራል። እናም ሰንበት ሰንበት ነውና ከመብል ባንታቀብም ከእንስሳት ውጤቶች ግን በመራቅ ጾሙን አሐዱ ብለን እንጀምራለን።

🫀የፊታችን ቅዳሜ 14/03/2017ዓ.ም የቅበላ ቀን ነው። ቅበላ ስንል ንስሀ ገብተን ነጽተን በሙሉ ልብ ለጌታችን መወለድ ከሥጋ ኃጢያት የምንለይበት የጾም መግቢያ ማለታችን ነው። ልብ አድርጉ ቅበላ እንጂ ብቀላን አልተባለምና ከመጠን በላይ በመብላትና በመጠጣት ብቀላን አትውደዱ!።

በርግጥ ወቅቱ እና የኑሮ ውድነቱ ትንሽ ልጓም ይሆነናል ብዬ አስባለሁ ሆኖም ትንሽ ያለንም ከቻልን ምን ቀምሼ ላስብ ለሚል ለንደኔ አይነት ምስኪን(የኔቢጤ) ማዕድ በማጋራት ደስታቸውን ሙሉ ማድረግ እንዳለብን አስባለሁ።

ይሔ የኔ ኃጢያተኛው ድምጽ አይደለም የአምላክህ እንጂ ቃሉም እንዲህ ይላል
.
.
.
" የአምላክህን የእግዚአብሔርን ቃል ብትሰማ ዛሬም ያዘዝሁህን ትእዛዙን ሁሉ ብታደርግ ብትጠብቅም አምላክህ እግዚአብሔር ከምድር አሕዛብ ሁሉ ላይ ከፍ ከፍ ያደርግሃል ።...አንተ በከተማ ቡሩክ ትሆናለህ በእርሻም ቡሩክ ትሆናለህ ።  የሆድህ ፍሬ የምድርም ፍሬ የከብትህም ፍሬ የላምህም ርቢ የበግህም ርቢ ቡሩክ ይሆናል ። አንተም በመግባትህ ቡሩክ ትሆናለህ በመውጣትህም ቡሩክ ትሆናለህ ። እግዚአብሔርም  በላይህ የሚቆሙትን ጠላቶችህን በፊትህ የተመቱ ያደርጋቸዋል ። እግዚአብሔር በረከቱ በአንተ ላይ በጎተራህ በእጅህም ሥራ ሁሉ እንዲወርድ ያዝዛል።"
    ዘዳ 28*1_8

ሰይጣን ራሳችንን ስንገዛና ከራሳችን ጋር ስንሆን ኃጢአታችንንም ስናስተውል ስለንሰሐም ስናስብ ይፈራል።

ጾም ስጋችንን የምንገዛበት ልጓም ነው። ፈረስ ጋሪም ሆነ መኪናም ራሱን የሚገዛው በልጓሙ ወይም በፍሬን ነው። ሰውም ያለገደብ የሚፈስ የሥጋውን ጥያቄና ፍላጎት የሚገታው በጾም ነው።
የተለቀቀ ስጋ የነፃነቱን ጥግ በኃጢአት ሊመሸግ ያምረዋልና በጾም ጊዜ ከዚህ አሸንክታብ ማምለጥ ይቻለናል። ጾም መንፈሳዊ ትጥቅ ሲሆን የጨለማው ጦር መመከቻም ነው። ጾም በአይን ከምናየው፣ በጆሮ ከምንሰማው፣ ከምንቀምሰው ከምንነካው ከምንናገረው ሁሉ የምንጠበቅበት ልጓም ነው።

ለምን እንፆማለን?
፩:- መርፌ ባለፈበት ክር እንደሚያልፍ ሁሉ። ክርስቶስ ባለፈበት ሰው ሊያልፍ ግድ የሚጠበቅ ትምሕርት ነውና ተጠምቆ ተጠመቁ፣ ጹሞ ፁሙ ብሎናልና ስንፆም የኃጢያት ስርየትን እናገኛለንና ካደፍንበት እንድንነፃ እንጾማለን።

፪:- ፆም ጠላታችንን ማሸነፊያ ጋሻ ነውና።
ጦረኛ ካልተዘጋጀ ጠላቱን ማሸነፍ አይችልም እኛም ክርስትያኖች ካልፆምን ካልፀለይን ሰይጣንን ማሸነፍ አንችልም። በመብል ምክንያት አዳም እንደወደቀ፣ በዳግማዊው አዳም በክርስቶስ መፆም ጠላት ድል ተመቷልና። አዎ አኛም ሰላም ያሳጣንን፣ ወንድም ከወንድሙ፣ ቤተሰብ ከቤተሰቡ ፍቅርን የነሳንን ጠላት አሸንፈን በአብሮነት የምንሻገረው በፆም ስለሆነ እንጾማለን።

፫:- ፈቃደ ስጋን ለፈቃደ ነብስ ለማስገዛት።
መኪናም ፍሬን አለው ፈረስም ልጓም አለውና የስጋችን ልጓሙ ፆምና ፀሎት ነው።

፬:- እንደ ሥርዓቱ ከሔድን ለተራቡ ሰወች እንድናዝን ክርስትያን መፆም ያለበት አፍ እስኪመረው ድረስ ነውና በዛ ችግር ውስጥ ካለፍን የሰወችን ችግር መረዳት እንችላለን
አምላከ ቅዱሳን በጊዜያዊ ችግር ሳንረታ ዘለዓለማዊ የሕይወት ጽናት እንዲኖረን ይርዳን።

በጾም ለተወሰነ ሰዓት ከምግበ ሥጋ የመከልከላችን ዓላማ ራሳችንን መግዛት እንድንችል ነው፡፡ ስለዚህ እየጾምኩ ነው የሚል ሰው ካለ ከምንም በፊት ትዕግሥተኛ፣ ልበ_ትሑትና የዋህ፣ እግዚአብሔርን የሚፈራ ልቡና ያለው፣ የፍትወታትን ጅረት ከኹለንተናው የሚያስወግድ፣ ዘወትር በልቡናው ዕለተ ምጽአትን የሚያስብ፣ በእግዚአብሔር የፍርድ ዙፋን ፊት እንደሚቆም የማይረሳ፣ በፍቅረ ንዋይ ወጥመድ ተይዞ ምጽዋትን የማይጠላ፣
ወንድሙን ከልቡ የሚወድ ይኹን እውነተኛ ጾም ማለት ይኼ ነውና፡፡

“ታዲያ እግዚአብሔር የመረጠው ጾም እንዴት ያለ ነው?” ትሉኝ እንደ ኾነም የእግዚአብሔር አፈ ንጉሥ የሆነው ነቢዩ ኢሳይያስ እንዲህ ሲል ይመልስልናል፡- “የበደልን እስራት ፍታ(ይቅር በል ሲል)፤ ለተራበው እንጀራህን አጥግበው፤ ድሆችን ወደ ቤትህ አስገብተህ አሳድራቸው፡፡” እንዲህ ስታደርግ፡- “ያን ጊዜ ብርሃንህ እንደ ንጋት ይበራል፡፡ ፈውስህም ፈጥኖ ይወጣል” (ኢሳ.58፥5-8)፡፡

ስለዚህ ወዳጄ ክርስትና የሚጀምረዉ ከተግባር እንጂ ከወሬ አይደለምና እኒህን የተገበርክ እለት ወደ ፈጣሪ ትቀርባለህ።

ስለዚህ ወዳጄ ለጾሙ ጊዜ ነፍስህን ከፈጣሪ ለማስታረቅ ምን ምን ነገሮች ያስፈልጉሀል?
ነጠላ?
የጸሎት መጽሐፍ?
ምጽዋት መስጠት?
ይቅርታ ማድረግ?
ይቅርታ መስጠት?
ጽሙና(ከራስ ጋር መነጋገር)
ጾሙን ለመጨረስ ጽናት?
የቱ ላይ ለውጥ ለማምጣት ለራስህ ቃል ትገባለህ?

መልካም ጾም!
መልካም ቀን!

✍️† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †✍️
               🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

17 Nov, 12:47


ስንክሳር ኅዳር 9

††† እንኳን ለአበው ቅዱሳን "318ቱ ሊቃውንት" ዓመታዊ የጉባኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †††

††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †††

††† ጉባኤ ኒቅያ †††

††† በዚህች ዕለት (ኅዳር 9 ቀን) በሃገረ ኒቅያ በእመቤታችን እና በአምላክ ልጇ የሚያምኑ 318ቱ ቅዱሳን ሊቃውንት ተሰብስበዋል::

የሊብያው ሰው አርዮስ ጌትነት ገንዘቡ የሆነ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ክዶ ሊያስክድ ሲሯሯጥ በፈቃደ እግዚአብሔር: በጻድቁ ንጉሥ ቆስጠንጢኖስ ጥሪ: 2348 ምሑራን ከመላው ዓለም ተሰበሰቡ::

ጥሪው የተላለፈው በወርኀ ሚያዝያ ሲሆን በመንገድ ችግር ሁሉም ተጠቃለው ኒቅያ የገቡት መስከረም 21 ቀን ነበር:: ከተሰበሰበው ብዙ ሰው መካከል የአበውን ደቀ መዛሙርት ሳንቆጥር ሃይማኖታቸው የቀና: ምግባራቸው የጸና 318ቱ አበው ሊቃውንት ተገኙ::

እነዚህ አባቶች "ሊቃውንት" ሲባሉ እንዲሁ በእውቀት ብቻ የበሰሉ እንዳይመስሉን:: 318ቱ አበው እኩሎቹ በዘመነ ሰማዕታት እጅና እግራቸውን የተቆረጡና ለሃይማኖታቸው ብዙ ዋጋ የከፈሉ ናቸው::

እኩሎቹ ደግሞ በገዳማዊ ሕይወት ያጌጡ: ፍቅረ ክርስቶስ በውስጣቸው የሚነድ: የመንፈስ ቅዱስ ቤት ናቸው:: እስኪ እናውቃቸው ዘንድ የጥቂቶችን ማንነት በስምና በመገለጫ እንመልከት:-
1.ቅዱስ ቶማስ ዘመርዓስ (በዘመነ ሰማዕታት ለ22 ዓመት ሲቆራርጡት ኖረው በጉባኤው ላይ የተገኘው ያለ እጅ: እግር: ጀሮ: ከንፈር: ቅንድብ ነው)
2.ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ (ስለ ቀናች እምነት ለ50 ዓመታት የተጋደለና ለ15 ዓመታት በስደት የኖረ ነው)
3.ቅዱስ እለእስክንድሮስ ሊቅ (ከሰማይ ብርሃን ይወርድለት የነበረ አባት ነው)
4.ታላቁ ቅዱስ ባስልዮስ (በጸሎቱ አጋንንትን ያንቀጠቀጠ: ነፍሳትን ከሲዖል የቀማና ከከዊነ እሳት የደረሰ አባት ነው)
5.ቅዱስ ጐርጐርዮስ ዘአርማንያ (ስለ ቀናች እምነት መጸዳጃ ጉድጓድ ውስጥ ለ15 ዓመታት ተጥሎ የኖረ ሰማዕት ነው)
6.ቅዱስ ኒቆላዎስ ዘሜራ (ከሕጻንነቱ የተቀደሰ: በበርሃ የተጋደለ: በዘመነ ሰማዕታት ብዙ መከራን የተቀበለ አባት ነው)
7.ቅዱስ ያዕቆብ ዘንጽቢን (በደግነቱ ሙታንን ያስነሳ: ወንዝን በጸሎቱ ያቆመ: በንጽሕና የተጋደለ አባት ነው)
8.ቅዱስ ሶል ጴጥሮስ (ቅዱሱን ንጉሥ ያጠመቀ:
ቁስጥንጥንያን በወንጌል ያበራ ሊቅ ነው)
9.ቅዱስ ኤዎስጣቴዎስ (ስለ ቀናች እምነቱ ብዙ ግፍ የደረሰበትና በስደት ያረፈ አባት ነው)

ለአብነት እንዲሆኑን እነዚህን አነሳን እንጂ 318ቱም ሊቃውንት ስለ ቤተ ክርስቲያን ተግተው የተጋደሉ: ብዙ ዋጋም የከፈሉ አባቶች ናቸው::

በወቅቱ ታዲያ ቤተ ክርስቲያንን የበጠበጡ ብዙ መናፍቃን ቢኖሩም የአርዮስ ግን ከመጠኑ አለፈ:: የእርሱ ኑፋቄ (ፈጣሪያችንን ፍጡር ነው ማለቱ) መነሻው ከእርሱ በፊት ነው:: መናፍቃን ከዘመነ ሐዋርያት ጀምሮ ቤተ ክርስቲያንን ሲያውኩ መኖራቸው ግልጽ ነው::

በተለይ ደግሞ ቢጽ ሐሳውያንና ግኖስቲኮች የወለዷቸው እሾሆች አባቶቻችንን እንቅልፍ ነስተው ነበር:: የሚገርመኝ በዘመኑ እንደ ነበሩ መናፍቃን ኃይለኝነት የእኞቹ ከዋክብት ሊቃውንት ባይኖሩ ምን ሊፈጠር እንደሚችል ያሳስብ ነበር::

ግን እግዚአብሔር ለሁሉ እንደሚገባ ያዘጋጃልና አበው ብርቱ መናፍቃንን በብርቱ መንፈሳዊ ክንድ እያደቀቁ ከጐዳና አስወገዷቸው:: የዛሬውን ደካማ ትውልድ ደግሞ የአርዮስ ልጆች 2 (3) ጥቅስ ይዘው ሲያደናብሩት ይውላሉ::

ሐረገ መናፍቃን በርጉም ሳምሳጢ ጳውሎስ: በመርቅያንና በማኒ ይጀምራል:: በእርግጥ አርጌንስ እና የግብጹ ቀሌምንጦስም ተቀላቅለዋቸዋል:: ርጉም ሳምሳጢ ድያድርስን በኑፋቄ ወልዶታል:: ድያድርስ ሉቅያኖስን: ሉቅያኖስ ደግሞ አርዮስን ወልደዋል::

ይህ አርዮስ እጅግ ተንኮለኛ በመሆኑ ልክ እንደ ዘመኑ መሰሎቹ ግጥምና ዜማ እየጻፈ በየመንገዱ እያደለ: በየቤቱ እየሰበከ ብዙዎችን በኑፋቄው በከለ:: በመጀመሪያ ተፍጻሜተ ሰማዕት
ቅዱስ ጴጥሮስ (አስተማሪው) መከረው:: ባይሰማው ከአንዴም ሁለት ጊዜ አወገዘው::

ቆይቶ ሰነፉ ጳጳስ አኪላስ ቢፈታውም ሊቁ ቅዱስ
እለእስክንድሮስ እንደ ገና አወገዘው:: እንደ አርዮስ ሐሳብ መድኃኒታችን ክርስቶስ የባሕርይ አምላክ አይደለም (ሎቱ ስብሐት!) ማለት ክርስትናን ከሥሩ ፈንቅሎ መጣል ነው::

ስለ ክርስቶስ እግዚአብሔርነት ብሉይም ሐዲስም እየመሰከሩ (ኢሳ. 9:6, መዝ. 46:5, 77:65, ዘካ. 14:4, ዮሐ. 1:1, 10:30, ራዕይ. 1:8, ሮሜ. 9:5) አርዮስና የዛሬ መሰሎቹ አንዲት ጥቅስ ይዘው ክርስትናን ከመሠረቱ ለመናድ መሞከራቸው በእርግጥም ከሰይጣን መላካቸውን ያሳያል::

በወቅቱም በመወገዙ "ተበደልኩ" ብሎ የጮኸው አርዮስ ከ2ቱ አውሳብዮሶች ባልንጀሮቹ (ዘቂሣርያና ዘኒቆምድያ) ጋር ሆኖ ወደ ቅዱስ ቆስጠንጢኖስ ሔዶ ከሰሰ:: ቅዱሱ ንጉሥም የጉዳዩን ክብደት ተመልክቶ የዓለም ሊቃውነት ይሰበሰቡ ዘንድ አዘዘ::

ከሚያዝያ 21 እስከ መስከረም 21 ተጠቃለው ገቡ:: በ325 ዓ/ም (በእኛው በ318 ዓ/ም) ለ40 ቀናት የሚቆይ ሱባኤን ያዙ:: ሱባኤውን ሲጨርሱም በ4ቱ ፓትርያርኮች (እለእስክንድሮስ: ሶል ጴጥሮስ: ዮናክንዲኖስና ኤዎስጣቴዎስ) መሪነት: በእለእስክንድሮስ ሊቀ መንበርነት: በአትናቴዎስ ጸሐፊነት ጉባኤው ተጀመረ::

በጉባኤው ሙሉ ስልጣን በሰማይ ከፈጣሪ: በምድር ከንጉሡ የተሰጣቸው አበው አርዮስን ተከራክረው ከነ ጀሌዎቹ ምላሽ አሳጡት:: ክርስቶስ አምላክ ወልደ አምላክ: ሥግው ቃል: ራሱም እግዚአብሔር መሆኑን አስረዱት:: በጉባኤው መጨረሻም:-
1.አልመለስም በማለቱ አርዮስን አወገዙ::
2.ጸሎተ ሃይማኖትን "ለመንግስቱም ፍጻሜ የለውም" እስከሚለው ድረስ ተናገሩ::
3.ፍትሐ ነገሥትን ሥጋዊና መንፈሳዊ ብለው አዘጋጁ::
4.ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን እንደሚገባ አደራጁ::
5.በስማቸው የሚጠራ አንድ ቅዳሴን ደረሱ::

ይህ ሁሉ ሲሆን መድኃኒታችን ክርስቶስ 319ኛ ሆኖና ገሊላዊ ጳጳስን መስሎ ሁሉን አከናውኖላቸዋል:: አባቶችም ሥራቸውን
ከጨረሱ በኋላ ቅዱስ ቆስጠንጢኖስን ባርከው ወደየ ሃገረ ስብከታቸው ተመልሰዋል::

††† በየዘመኑም ዐርፈው ለክብረ መንግስተ ሰማያት በቅተዋል:: እኛም እነሆ "አባቶቻችን:
መምሕሮቻችን:
መሠረቶቻችን:
ብርሃኖቻችን:
ምሰሶዎቻችን" እያልን እናከብራቸዋለን::

††† አምላከ ቅዱሳን ሊቃውንት በጸሎታቸው እኛንም: ቤተ ክርስቲያናችንንም ከክፉ ጠላት ይጠብቅልን:: ከበረከታቸውም ይክፈለን::

††† ኅዳር 9 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱሳን 318ቱ ሊቃውንት
2.ቅዱስ እለእስክንድሮስ ሊቅ
3.ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ
4.አባ ይስሐቅ ሊቀ ጳጳሳት
5.ሊቁ አካለ ወልድ

††† ወርሐዊ በዓላት
1.አባ በርሱማ ሶርያዊ (ለሶርያ መነኮሳት ሁሉ አባት)
2.አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ
3.የብሔረ ብፁዐን ጻድቃን
4.አባ መልከ ጼዴቅ ዘሚዳ
5.ቅዱስ ዞሲማስ ጻድቅ

✍️† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †✍️
               🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

17 Nov, 03:48


አመስግኑ!
"ዲያብሎስ በእናንተ ላይ እጅግ ክፉ ነገርን በማምጣት አሳዝኖአችኋልን? እናንተም ኢዮብን አብነት አድርጋችሁ እግዚአብሔር ይመስገን በማለት አሳዝኑት፡፡ ዲያብሎስን ድል ማድረግ ስትሹ ይህን መሣርያ ዘወትር ያዙ እሱም ምስጋና ነው::"

#ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈ_ወርቅ

መልካም ቀን!
✍️† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †✍️
               🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

16 Nov, 15:38


ስንክሳር ኅዳር 8

እንኩዋን ለቅዱሳን ኪሩቤል (ዐርባዕቱ እንስሳ): ቅዱስ ቆስጠንጢኖስ ወአባ ቅፍሮንያ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ

+"+ ዐርባዕቱ እንስሳ +"+

=>እግዚአብሔር ቅዱሳን መላእክትን ሲፈጥራቸው በነገድ መቶ (100): በክፍለ ነገድ አሥር (10) አድርጉዋቸዋል:: አቀማመጣቸውንም በ3 ሰማያትና በ10 ከተሞች (ዓለማት) አድርጉዋል::

+መላእክት ያሉባቸው ከተሞች ከታች ወደ ላይ 'ኤረር: ራማና ኢዮር' ይባላሉ:: አሥሩ ክፍለ ነገድ ደግሞ ከነ አለቆቻቸው ይህንን ይመስላሉ:-

1.አጋእዝት (የቀድሞ አለቃቸው ሳጥናኤል: አህን የተረፉት በቅዱስ ሚካኤል ሥር ናቸው)
2.ኪሩቤል (አለቃቸው ኪሩብ)
3.ሱራፌል (አለቃቸው ሱራፊ)
4.ኃይላት (አለቃቸው ሚካኤል)
5.አርባብ (አለቃቸው ገብርኤል)

6.መናብርት (አለቃቸው ሩፋኤል)
7.ስልጣናት (አለቃቸው ሱርያል)
8.መኩዋንንት (አለቃቸው ሰዳካኤል)
9.ሊቃናት (አለቃቸው ሰላታኤል)
10.መላእክት (አለቃቸው አናንኤል) ናቸው::

+ከእነዚህም *አጋእዝት: *ኪሩቤል *ሱራፌልና *ኃይላት መኖሪያቸው በኢዮር (በ3ኛው ሰማይ) ነው:: *አርባብ: *መናብርትና *ስልጣናት ቤታቸው ራማ (2ኛው ሰማይ) ነው:: *መኩዋንንት: *ሊቃናትና *መላእክት ደግሞ የሚኖሩት በኤረር (በ1ኛው) ሰማይ ነው::

+መላእክት ተፈጥሯቸው እምኀበ አልቦ ኀበ ቦ ነው:: አይራቡም: አይጠሙም: አይዋለዱም: አይሞቱም:: ተፈጥሯቸውም ረቂቅ ነው:: ተግባራቸው ዘወትር "ቅዱስ: ቅዱስ: ቅዱስ" እያሉ ፈጣሪያቸውን ማመስገን ነው:: ምግባቸውም ይሔው ነው::

+ዕረፍት ብሎ ነገርን አያውቁም:: "አኮቴቶሙ ዕረፍቶሙ: ወዕረፍቶሙ አኮቴቶሙ" እንዲል:: በተጨማሪም መልአክ ማለት ተላላኪ (አገልጋይ) ነውና ከፈጣሪ ወደ ሰው ልጆች ለምሕረትም: ለመዓትም ይላካሉ::

+ምሕረትን ያወርዳሉ:: ልመናን ያሳርጋሉ:: ቅጡ ሲባሉም ይቀጣሉ:: ስነ ፍጥረት (አራቱ ወቅቶች) እንዳይዛቡ ይጠብቃሉ::

*ዘወትርም ስለ ሰው ልጆች ያማልዳሉ (ዘካ. 1:12)
*ምሥጢርን ይገልጣሉ (ዳን. 9:21)
*ይረዳሉ (ኢያ. 5:13)
*እንዳንሰናከል ይጠብቃሉ (መዝ. 90:11)
*ያድናሉ (መዝ. 33:7)
*ስግደት ይገባቸዋል (መሳ. 13:20, ኢያ. 5:13, ራዕ. 22:8)
*በፍርድ ቀንም ኃጥአንን ከጻድቃን ይለያሉ (ማቴ. 25:31)
*በአጠቃላይ ለሰው ልጆች ሕይወትና ድኅነት ሲባል ከፈጣሪያቸው የተሰጣቸውን ትዕዛዝ ሲጠብቁና ፈቃዱን ሲፈጽሙ ይኖራሉ::

+ከእነዚህ ቅዱሳን መላእክት መካከል ደግሞ ትልቁን ሥፍራ ዛሬ የምናከብራቸው ነገደ ኪሩቤል (ዐርባዕቱ እንስሳ) ይይዛሉ:: መንፈሳውያን ከመሆናቸው በላይ መንበረ ጸባኦትን እንዲሸከሙ ስላደላቸው ክብራቸው ታላቅ ነው:: ከመላእክት ወገንም ቅሩባን እነርሱ ናቸው::

+ዘወትርም ስለ ፍጥረታት (ሰዎች: እንስሳት: አራዊትና አዕዋፍ) ምሕረትን ይለምናሉ:: ለዚህም ነው በ4 እንስሳት (በሰው: በንስር: በላምና በአንበሳ) መልክ የተሳሉት:: ቅዱስ መጽሐፍም ስለ እነርሱ ብዙ ይላል:: (ሕዝ. 1:5, ራዕ. 4:6, ኢሳ. 6:1)

+በተለይ ግርማቸው እንደሚያስፈራ ተጽፏል:: "ምሉዓነ ዐዕይንት - ዐይንን የተሞሉ" ይላቸዋል:: ይህንንም መተርጉማን "ምሥጢር አዋቂነታቸውንና ግርማቸውን ያጠይቃል" ሲሉ ተርጉመውታል::

+ዐርባዕቱ እንስሳን 4 ሆነው በስዕል ብናያቸውም "ከመ ርዕየተ እለ ቄጥሩ" እንዲል እያንዳንዱ ከወገብ በላይ አራት በመሆናቸው ተሸካሚዎቹ 16 መልክ አላቸው:: በ2 ክንፋቸው ፊታቸውን: በ2ቱ እግራቸውን ሸፍነው በ2 ክንፋቸው ይበራሉ:: ይህም ብዙ ምሥጢር ሲኖረው ዋናው ግን አርአያ ትእምርተ መስቀል ነው::

+"4ቱ" እንስሳ (ኪሩቤል) በሐዲስ ኪዳንም ልዩ ክብር አላቸው:: 4ቱ ወንጌል ሲጻፍ እየተራዱ ስላጻፉ በስማቸው ተሰይሟል:: ቅዱስ ማቴዎስን ገጸ ሰብእ: ቅዱስ ማርቆስን ገጸ አንበሳ: ቅዱስ ሉቃስን ገጸ ላህም: ቅዱስ ዮሐንስን ገጸ ንስር እየተራዱ ስላጻፏቸው እነሆ እስከ ዛሬ ድረስ "ዘብእሲ ማቴዎስ": "ዘአንበሳ ማርቆስ": "ዘላሕም ሉቃስ" እና "ዘንስር ዮሐንስ" እየተባሉ ይጠራሉ::

+እነዚህ ቅዱሳን መላእክት የሰው ልጆችን ስለ መራዳታቸውም በብዙ ገድላትና ድርሳናት ላይ ተጽፏል:: የራሳቸውን "ድርሳነ ዐርባዕቱ እንስሳን" ጨምሮ በገድለ አባ መቃርስና በገድለ አባ ብስንድዮስ ላይ በስፋት ግብራቸው ተጽፏል::

+እኛም ኦርቶዶክሳውያን ክርስቲያኖች ክብራቸውን: ረድኤታቸውንና ምልጃቸውን አምነን ዘወትር እናከብራቸዋለን:: አባቶቻችን እንዲህ እያሉ እንደ ጸለዩ:-

"ሰላም ለክሙ ኪሩባውያን አፍራሱ:
ለመሐይምን ወጻድቅ እንተ ወርቅ አክሊለ ርዕሱ:
ኀበ ዝ አምላክ ለእለ ትጸውርዎ በአትሮንሱ:
ለእለ ጌገዩ ወለእለሂ አበሱ:
ሰአሉ መድኃኒተ ወምሕረተ ኅሡ::" (አርኬ)

+" ታላቁ ቅዱስ ቆስጠንጢኖስ "+

=>ቅዱስ ቆስጠንጢኖስ ለቤተ ክርስቲያን የፈፀመውን መልካም ተግባር ያሕል መሥራት የቻለ ንጉሥ በሐዲስ ኪዳን የለም:: ጻድቁ ንጉሥ ከቅድስት እናቱ እሌኒና ከአረማዊ አባቱ ቁንስጣ በበራንጥያ ተወለደ::

+ዘመኑ ዘመነ ዐጸባ /የመከራ ጊዜ/ ወይም የሰማዕታት ዘመን በመሆኑ ክርስቲያኖች በግፍ የሚጨፈጨፉበት ወቅት ነበር:: ክርስቲያኖችን ከምድረ ገፅ ለማጥፋት በተደረገው የ40 ዓመታት ዘመቻ አብያተ-መቃድስና መጻሕፍት ተቃጠሉ::
ብዙዎቹ በየበርሃው ተሰደዱ:: ሚሊየኖች በግፍ አለቁ::

+የዚሕን ዘመን መከራ በውል ያልተረዳ ሰው ቅዱስ ቆንጠንጢኖስን ሊያከብር አይችልም:: ምክንያቱም ይህን የመከራ ዘመን በፈቃደ እግዚአብሔር አስቁሞ: ቀርነ-ሃይማኖት የቆመው: ብዙ ሥርዓት የተሠራው: ቤተ ክርስቲያንም ያበራችው በዘመኑ ነውና::

+ቅዱሱ ንጉሥ ለሁሉም ነቢያት: ሐዋርያትና ሰማዕታት አብያተ ክርስቲያናትን ራሱ በመሠረታት በቁስጥንጥንያ አንጿል:: በዘመኑ ቤተ ክርስቲያን በሰላም ኖራለት: በኃይለ መስቀሉ ጠላት ጠፍቶለት ኑሮ በዚህች ቀን አርፏል::

+ይህቺ ቀን ታላቁ ንጉሥ በፈለገ ኮቦር ቅዱስ መስቀልን የተመለከተባት ናት:: መክስምያኖስን ሊወጋ ወደ ሮም በተጉዋዘ ጊዜ በሰማይ ላይ መድኅን መስቀል ተዘርግቶ በላዩ ላይ "ኒኮስጣጣን" የሚል በዮናኒ ልሳን ተጽፎበት ተመልክቷል::

+ይህንንም "በዚህ ጠላትህን ድል ታደርጋለህ" ማለት ነው ብለው ተርጉመውለታል:: እርሱም በጋሻው: በጦሩ: በሰይፉ: በፈረሱ ላይ የመስቀል ምልክትን አድርጐ ማሕደረ ሰይጣን መክስምያኖስን ድል ነስቶታል:: እኛንም በሞገሰ መስቀሉ ይጠብቀን::

=>አምላከ ቅዱሳን መላእክት እነርሱን ለረድኤት ይላክልን:: ከበረከታቸውም ይክፈለን::

=>ኅዳር 8 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱሳን 4ቱ እንስሳ (ኪሩቤል)
2.ቅዱስ አፍኒን ሊቀ መላእክት
3.አባ ቅፍሮንያ ጻድቅ
4.ቅዱስ ቆስጠንጢኖስ ንጉሥ (ዘምስለ ቅዱስ መስቀል)
5.ቅድስት እግዚእ ክብራ

=>ወርሐዊ በዓላት
1.ቅዱስ ሙሴ ሊቀ ነቢያት
2.አባ ብሶይ (ቢሾይ)
3.አቡነ ኪሮስ
4.አባ ሳሙኤል ዘደብረ ቀልሞን
5.ቅዱስ ማትያስ ሐዋርያ (ከ12ቱ ሐዋርያት)
✍️† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †✍️
🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
https://t.me/Sinksar
https://t.me/Sinksar
https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

16 Nov, 09:54


https://www.youtube.com/watch?v=DF1YW4keOYw

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

16 Nov, 09:24


https://www.youtube.com/watch?v=capFRtyV7xc

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

16 Nov, 09:17


https://www.youtube.com/watch?v=rMrj2zOnT4E

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

16 Nov, 07:28


ዘወትር ጠዋት ከእንቅልፍ ሲነቁ
ፈጣሪን በጸሎት ተገናኝተው የቀን ዉሎዎን ይንደፉ!
እንዴት?
ዛሬ ምን ሰርተው ይውላሉ?
ለመንፈሳዊነት ወይም ራስዎን ለማዳመጥ ምን ያህል የጥሞና ጊዜ ለመስጠት አቅደዋል?
እስካሁንስ ምን ሰሩ?

ረዥሙ ህልሞ ምን ነበረ
ወደ ረዥሙ ጉዞ መዳረሻ ምን እቅድ አቅደው ምን ያህል ሰሩ?

የቀን ተቀን ውሎና ተግባርዎ ለረዥሙ ህልሞ ምን ያህል ድርሻ አለው?

ይኼ የሁል ጊዜ ጥያቄዎ ይሁን!

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

15 Nov, 17:35


ከአጓጉል ኢኮኖሚያዊ ተሽኮርማሚነት እንውጣ!
--

እንደ ግለሰብ ጥሩ ነን፣ በማኅበር መደራጀተን ለኢኮኖሚያዊ ዐላማ በመጠቀም ረገድ ግን ሲበዛ ተሽኮርማሚዎች ሳንሆን አንቀርም። የተቋቋሙትንም ከመደገፍ ይልቅ በተጋነነ ትችትና ጠባቂነት እናባክናችዋለን።

በኅብረት በአንድነት ተቋም ማቆም፣ ያቆሙትን ማጽናት፣ በጸናው ተለውጦ ሀገርንም መለወጥ የተገባ ሥራ ነው። ከዓመታት በፊት ስለባንክ ሥራ ስናወጋ ወለድና አራጣ እየተምታቱ ያነጋግሩ ነበር። ዛሬ እንደ ተቀረፈ ተስፋ አለን።

#አሐዱ ዐይን ገላጭ ነው።
@የኔታ በአማን ነጸረ

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

02 Nov, 02:17


🙏ስንክሳር ጥቅምት 23 🙏

† እንኳን ለጻድቅ ሊቀ ዻዻሳት አባ ዮሴፍ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን።

† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †

🌿† ጻድቅ ሊቀ ዻዻሳት አባ ዮሴፍ †🌿

† በእስክንድርያ (ግብጽ) ሊቀ ዽዽስናን ከተሾሙና በጐ ሥራን ከሠሩ አበው አንዱ አባ ዮሴፍ ነው:: እርሱ ለግብጽ 52ኛ ፓትርያርክ ነውና በ9ኛው መቶ ክ/ዘመን አካባቢ እንደ ነበር ይታመናል::
ጥንተ ነገሩስ እንደ ምን ነው ቢሉ:-
በግብጽ የሚኖሩ የዘመኑ ክርስቲያን ባልና ሚስት ወደ ፈጣሪ ለምነው ልጅ ሲወልዱ 'ዮሴፍ' አሉት:: እጅግ ሃብታሞች ቢሆኑም እርሱ ገና ልጅ እያለ ሁለቱም ዐረፉ:: ሕጻኑ ዮሴፍም ዕጓለ ሙታን (ወላጅ አልባ) ሆነ:: ሕጻኑ ሲያለቅስ የተመለከተ አንድ ደግ ጐረቤቱ ግን ወደ ቤቱ ወሰደው::

እንደ ልጁ ተንከባክቦ: ክርስትናንም አስተምሮ አሳደገው:: እድሜው 20 ሲደርስም "የወላጆችህን ንብረት ንሳ" ብሎ አወረሰው:: ወጣቱ ዮሴፍ ግን "አኮኑ ዝንቱ ኩሉ ኃላፊ-ይህ ሁሉ ሃብት ጠፊ አይደለምን" ብሎ ናቀው::

ለነዳያንም በትኖት እያመሰገነ ወደ ገዳመ አስቄጥስ ገሰገሰ:: በዚያም የአሞክሮ ጊዜውን ፈጽሞ መዓርገ ምንኩስናን ተቀበለ:: ለዓመታትም በዲቁና ገዳሙን እያገለገለ: እየተጋደለ ኖረ::

የአባ ዮሴፍን ደግነት የሰማው የወቅቱ ፓትርያርክ አባ ማርቆስም ከገዳም አውጥቶ በመንበረ ዽዽስናው እንዲራዳውና ሕዝቡን እንዲያስተምርለት ወደ ከተማ አመጣው::

ከጥቂት ቆይታ በኋላ ግን አባ ዮሴፍ ወደ ፓትርያርኩ አባ ማርቆስ ቀርቦ "አባቴ! ወደ ገዳሜ አሰናብተኝ:: ለመነኮስ በከተማ መኖር ፍትሕ አይደለምና" ሲል ተማጸነው:: ፓትርያርኩም "እሺ" ብሎ ቅስናን ሹሞ አሰናበተው::

ወደ ገዳመ አስቄጥስ ከተመለሰ ጀምሮ አባ ዮሴፍ በዓት ለየ:: እስከ 59 ዓመቱም ድረስ በጾምና በጸሎት በበዓቱ ጸንቶ ኖረ:: በአጠቃላይ በገዳም የኖረባቸው ዓመታትም 39 ደረሱ::

በዚህ ጊዜ ግን የወቅቱ ፓትርያርክ አባ ስምዖን (ከአባ ማርቆስ በኋላ 3 ፓትርያርኮች ዐርፈዋል) በማረፉ ግብጽ እረኛን ስትፈልግ ነበር:: 'ማንን እንሹም' እያሉ ሲጨነቁ አንድ ሰው ጉቦ ሰጥቶ ሊሾም መሆኑን አበው ሰሙ:: ይህ ሰው ደግሞ ጭራሹኑ ልጅ ያለው ነው::

አባቶች ተሯሩጠው ያ ጉቦኛ ባለ ሚስት እንዳይሾም አደረጉ:: ቀጥለው ማንን እንደ ሚሾሙ ሲጨነቁ የሁሉም ሕሊና ስለ አንድ ሰው (አባ ዮሴፍ) ያስብ ነበር:: ሁሉም ተሰብሳቢዎች ስለ ነገሩ ተጨዋውተው አባ ዮሴፍን ይሾሙ ዘንድ ቆረጡ::

ተሰብስበው በመንገድ ላይ ሳሉም እንዲህ ተባባሉ:: "ወደ በዓቱ ስንደርስ ቤቱ ክፍት ከቆየን ፈቃደ እግዚአብሔር ነው:: ዝግ ከሆነ ግን ፈጣሪ አልፈቀደም ማለት ነው" ሲሉ ተስማሙ:: ምክንያቱም የአበው በዓት ቶሎ ቶሎ አይከፈትምና::

ነገሩ ጥበበ እግዚአብሔር ነበረበትና ልክ ሲደርሱ እንግዳ ሊሸኝ በዓቱን ከፍቶ አገኙት:: እንዳያመልጣቸው ተረባርበው ያዙት:: ግጥም አድርገው አሥረው "አክዮስ-ይደልዎ-ይገባዋል" እያሉ ሥርዓተ ሲመት አደረሱለት:: እርሱ (አባ ዮሴፍ) ግን "እኔ ኃጢአተኛ ነኝ: አይገባኝም: ልቀቁኝ" እያለ ይጮህ ነበረ::

አበው ግን ሥርዓተ ሢመቱን ፈጽመው ወስደው በመንበረ ዽዽስና: በቅዱስ ማርቆስ ወንጌላዊ ዙፋን ላይ አስቀመጡት:: በቁጥርም 52ኛ ሁኖ ተቆጠረ:: አምላክ ደጉን ሰው ጠቁሟቸዋልና ለቤተ ክርስቲያን ይተጋ ጀመር::

ሕዝቡን እያስተማረ: አብያተ ክርስቲያናትን እያነጸ: መጻሕፍትን እየተረጐመ: ተአምራትን እየሠራ: በመንኖ ጥሪት ለ19 ዓመታት አገልግሏል:: ወቅቱም ተንባላት (አማሌቃውያን) በምድረ ግብጽ የሰለጠኑበት ነበርና ብዙ ችግሮችን አሳልፏል::

የግብጹ ሱልጣንም ሊገድለው 2 ጊዜ ሞክሮ አልተሳካለትም:: 2 ጊዜም ለአባ ዮሴፍ የሰነዘረው ሰይፍ በመልአክ እየተመለሰ ተመልክቶ ትቶታል:: አባ ዮሴፍ በዘመኑ ተሰዶ የነበረውን የኢትዮዽያ ዻዻስ አባ ዮሐንስንም ከተሰደደበት ወደ ሃገራችን
እንደ መለሰው በዜና ሕይወቱ ተጽፏል:: አባ ዮሴፍ እንዲህ ተመላልሶ በ78 ዓመቱ በዚህች ቀን ዐርፏል::

† ቸር አምላክ በጻድቁ ሊቀ ዻዻሳት ጸሎት ይማረን::
ከበረከቱም ይክፈለን::

† ጥቅምት 23 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.አባ ዮሴፍ ጻድቅ ሊቀ ዻዻሳት
2.ቅዱስ ዲዮናስዮስ ሰማዕት
3.ቅዱስ ኢላርዮስ
4.ቅድስት እለእስክንድርያ ሰማዕት

† "ኤዺስ ቆዾስ እንደ እግዚአብሔር መጋቢ የማይነቀፍ ሊሆን ይገባዋልና:: የማይኮራ: የማይቆጣ: የማይሰክር: የማይጨቃጨቅ: ነውረኛ ረብ የማይወድ: ነገር ግን እንግዳ ተቀባይ: በጐ የሆነውን ነገር የሚወድ: ጠንቃቃ: ጻድቅ: ቅዱስ: ራሱን የሚገዛ ይሁን::" † (ቲቶ. ፩፥፯)

✍️† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †✍️
🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇

https://t.me/Sinksar
https://t.me/Sinksar
https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

01 Nov, 02:53


🙏ስንክሳር ጥቅምት 22 🙏

✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ✞

✞ ጥቅምት 22 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ✞

" ቅዱስ ሉቃስ ወንጌላዊ "

✞ ቅዱስ ሉቃስ:-
👉 ሐዋርያ ነው
👉 ወንጌላዊ ነው
👉 ሰማዕት ነው
👉 ዓቃቤ ሥራይ (ዶክተር) ነው
👉 የጥበብ ሰው (ሰዓሊ) ነው
👉 ዘጋቢ (የሐዋርያትን ዜና ሕይወት የጻፈ) ነው::

ይሕስ እንደምን ነው ቢሉ:-

በመጀመሪያው መቶ ክ/ዘመን መነሻ አካባቢ: በተወደደች የጌታ ዓመት ከእሥራኤላውያን ወገኖቹ ቅዱስ ሉቃስ ተወልዷል:: ያደገውም መቄዶንያ አካባቢ ነው:: ጌታችን ተጠምቆ ማስተማር ሲጀምር ከተከተሉት የ5 ገበያ ሕዝብ መካከል 120ውን ለቤተሰብነት መምረጡ ይታወቃል::

ታዲያ እንዲጠቅም አውቆ ቅዱስ ሉቃስን ከ72ቱ አርድእት ደምሮታል:: ቅዱስ ሉቃስ ጌታን ከተከተለ በኋላ ለ3 ዓመት ከ3 ወር: ከዋለበት እየዋለ: ካደረበትም እያደረ የቃሉን ትምሕርት: የእጆቹን ተአምራት በጥሞና ይከታተል ነበር::

ጌታችን ለዓለም ድኅነት ተሰቅሎ: ሙቶ: ከተነሳ በኋላ ስለዚህ ቅዱስ የሚናገር አንድ የወንጌል ክፍል እናገኛለን:: በሉቃስ ወንጌል ምዕራፍ 24 ላይ ከምናያቸው የኤማሁስ መንገደኞች አንዱ ይህ ቅዱስ እንደ ሆነ አባቶች አስተምረውናል::

በእርግጥ 'ቀለዮዻ' የሚለው ስም በዘመኑ የብዙዎች መጠሪያ ቢሆንም እርሱም ጌታን ከመከተሉ በፊት በዚህ ስም ይጠራ እንደ ነበር ይታመናል:: በወቅቱ ታዲያ 2ቱ ደቀ መዛሙርት (ሉቃስና ኒቆዲሞስ) ወደ ኤማሁስ ሲሔዱ ጌታ መንገድ ላይ ተገልጦ እያጫወታቸው አብሮ ተጉዟል::

እነርሱም ማንነቱን አላወቁምና ስለ ራሱ ለራሱ እየሰበኩለት ተጉዘዋል:: ከሐዘናቸው ብዛት ማስተዋል ተስኗቸው: ቀቢጸ ተስፋም ወሯቸው ነበርና መድኃኒታችን ክርስቶስ የነቢያትን ትንቢት ተረጐመላቸው::

በዚህ ጊዜም ከነገሩ ማማር: ከምሥጢሩ መሥመር ጋር እየገረማቸው ልቦናቸው ይቃጠል (ይቀልጥባቸው) ነበር:: "አኮኑ ይነድደነ ልበነ" እንዲል:: ወደ ኤማሁስ ሲደርሱ ግን ደጐች ናቸውና "በቤት ካላደርክ: ራት ካልበላህ" ብለው ግድ አሉት::

በማዕድ ሰዓት ግን ቡራኬውን ሰጥቷቸው: ቸር አምላክነቱን ገልጦላቸው ተሰወራቸው:: እነርሱም በሐሴት ከኤማሁት ተመልሰው እየሮጡ ኢየሩሳሌም ደርሰው ትንሳኤውን ሰበኩ::

የመንገዱ ርዝመትም አልታወቃቸውም ነበር:: ከዚህ በኋላ ቅዱስ ሉቃስ እንደ ሐዋርያቱ መጽሐፈ ኪዳንን: ትምሕርተ ኅቡዓትን ተምሮ: መንፈስ ቅዱስን ተቀብሎ ለስብከተ ወንጌል ወጥቷል::

🙏 " ቅዱሱ ዶክተር " 🙏

በትውፊት ትምሕርት እንደ ተማርነው ቅዱስ ሉቃስ ጌታን ከመከተሉ በፊት ሥራው ሐኪምነት (ዶክተር) ነበር:: በዚህም አበው "አቃቤ ሥራይ / ባለ መድኃኒት" ይሉታል:: በተሰጠው ሙያም ብዙዎችን አገልግሏል::

የጌታ ደቀ መዝሙር ከሆነ በኋላ ደግሞ "አቃቤ ሥራይ ዘነፍስ-የነፍስ ሐኪም" ተብሏል:: እንዲያውም አባቶቻችን ሐዋርያትን ያክማቸው ነበር ይባላል:: ምክንያቱም ቅዱሳን ሐዋርያት አብዛኞቹ በሽተኞች ነበርና ነው:: ከደግነታቸው የተነሳም እልፍ አእላፍ ድውያንን በተአምራት ሲፈውሱ እነርሱ ግን በስቃይ ይኖሩ ነበር::

ሕመማቸው ሲጠናባቸው ግን ቅዱሱ ዶክተር ሉቃስ ይራዳቸው ነበር:: ይሕንንም ቅዱስ ዻውሎስ በቆላስይስ መልእክቱ ላይ "የተወደደው ባለ መድኃኒቱ ሉቃስ: ዴማስም ሰላምታ ያቀርቡላቹሃል" ሲል ገልጾታል:: (ቆላ. 4:14)

" ዘጋቢው ሐዋርያ "

ቅዱስ ሉቃስ እንደ ዛሬው ነገሮች ምቹ ባልነበሩበት ዘመን እጅግ አድካሚ የሆነ ጉዞ አድርጐ የሐዋርያትን ዜና ሕይወት ዘግቦልናል:: ልክ ወንጌሉን ለታኦፊላ (ቴዎፍሎስ) ደቀ መዝሙሩ እንደ ጻፈለት ግብረ ሐዋርያትንም ለእርሱ በትረካ መልክ አቅርቦለታል::

ሲጽፍለትም "ሰማሁ" እያለ ሳይሆን: አብሮ እያለ ያየውንና የተሳተፈበትን ነው:: አተራረኩም በአንደኛና በ3ኛ መደብ አድርጐ እያቀያየረ ነው:: ማለትም አንዳንዴ "እኛ" እያለ ሌላ ጊዜ ደግሞ "እነርሱ" እያለ ነበር የሚተርክለት::

መጽሐፉም 28 ምዕራፎች ሲኖሩት በጌታ ዕርገት ጀምሮ በኢየሩሳሌምና በአሕዛብ የነበረውን ስብከተ ወንጌል ገልጦ: የቅዱስ ዻውሎስን ጉዞዎች በሰፊው ዳስሶ ይጠናቀቃል::

🌿 " ወንጌላዊው ሐዋርያ " 🌿

ቅዱስ ሉቃስ ወንጌልን እንዲጽፉ ከተመረጡ (ከተፈቀደላቸው) ሐዋርያት አንዱ ነው:: በቤተ ክርስቲያንም "ዘላሕም" እየተባለ ይጠራል:: ለዚህም ምክንያቱ:-

1.ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በበረት: በላምና በአህያ መካከል መወለዱን በመጻፉ
2.ጌታችንን "መግዝአ ላሕም-የሚታረድ ሜልገች (ላም)" ብሎ በመግለጹ እና
3.ከ4ቱ እንስሳ (ኪሩቤል) አንዱ (ገጸ ላሕም) ይራዳው: ይጠብቀውም ስለ ነበር ነው::

ቅዱስ ሉቃስ ወንጌሉን የጻፈው ጌታ ባረገ በ22ኛው ዓመት ሲሆን ይኼውም በ56 ዓ/ም አካባቢ ማለት ነው:: ሲጽፍም ብቻውን አልነበረም:: ልክ ቅዱስ ማርቆስ ወንጌሉን የጻፈው ከሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ ዼጥሮስ ጋር እንደ ሆነው ሁሉ: ቅዱስ ሉቃስም የጻፈው ከብርሃነ ዓለም ቅዱስ ዻውሎስ ጋር ነው:: ምክንያቱም ለረዥም ዓመታት አብረው ለስብከተ ወንጌል ተጉዘዋልና::

ቅዱስ ሉቃስ ወንጌሉን ሲጽፍ በነ ዘካርያስ ቤተሰብ ጀምሮ: ብሥራተ ገብርኤልን: ክብረ ድንግል ማርያምን: የጌታን ልደት: እድገት: መጠመቅ: ማስተማር: መሰቀል: መሞት: መነሳትና ማረግ በቅደም ተከተል ይተርክልናል::

" ጥበበኛው (ሰዓሊው) ሐዋርያ "

ቅዱስ ሉቃስን ለየት ከሚያደርጉት ነገሮች ሌላኛው ደግሞ ጐበዝ ሰዓሊ የነበረ መሆኑ ነው:: በሐዲስ ኪዳንም የመጀመሪያውን የእመቤታችንን ስዕል (ምስለ ፍቁር ወልዳን) የሳለው እሱ ነው::

አንድ ቀን የአምላክ እናት ባለችበት ከጌታ አስፈቅዶ የሳላት ስዕለ አድኅኖ ሥጋን የለበሰች: ከፊቷ ወዝ የሚወጣ: የምታለቅስ: ስትወጋ የምትደማና ድውያንን የምትፈውስ ሆና ተገኝታለች:: ይህች ስዕል ዛሬ ሃገራችን ኢትዮዽያ ውስጥ አለች ይባላል::


✞ አምላከ ቅዱስ ሉቃስ ምሥጢሩን: ፍቅሩን: ጥበቡን ይግለጽልን:: ከሐዋርያው በረከትም ያሳትፈን::

🙏 ጥቅምት 22 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ ሉቃስ ወንጌላዊ ሐዋርያ
2.ቅዱስ ሲላስ አረጋዊ (የቅዱስ ሉቃስ ረድእ)
3.ቅዱስ ታኦፊላ
4."477" ሰማዕታት (የቅዱስ ሉቃስ ማሕበር)

" የከበርህ ቴዎፍሎስ ሆይ! ከመጀመሪያው በዓይን ያዩትና የቃሉ አገልጋዮች የሆኑት እንዳስተላለፉልን: በእኛ ዘንድ ስለ ተፈጸመው ነገር ብዙዎች ታሪክን በየተራው ለማዘጋጀት ስለ ሞከሩ: እኔ ደግሞ ስለ ተማርከው ቃል እርግጡን እንድታውቅ: በጥንቃቄ ሁሉን ከመጀመሪያው ተከትዬ በየተራው ልጽፍልህ መልካም ሆኖ ታየኝ:: " (ሉቃ. 1:1)

✍️† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †✍️
               🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇

       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

31 Oct, 13:54


ማኅበረ ቅዱሳን ይፍረስ!👹

ይኼ ጩኸት የጀመረው ከማኅበሩ መመሥረት ጊዜ ጀምሮ ነው። እድሜው የአንድ ወጣት እድሜን የሚተካከል ሠላሳን ያለፈ ነው።

ለነገሩ ከውጪ ያለ ጊዜው በክፉ ሀሳብ መጣ እንጂ የማኅበሩም ሀሳብ ሔዶ ሔዶ ኅብረቱን ማፍረስ ነው። ጤፍ የሚዘራበት ጊዜ አለው ተዘርቶም የሚታጨድበት እና የሚወቃበት ጊዜ አለው። ። ማኅበሩም በእግዚአብሔር ፈቃድ ጊዜው ሆኖ ተወልዷል ተወልዶ ፍሬ እያፈራ ፍሬው ሲሰምር በራሱ ጊዜ ይበተናል። አንድ ኮሚቴ የሚቋቋመው ለአንድ ዓላማ ወይም ተግባር አሊያም ችግር ነው። ልክ እንደዛው ማኅበሩም ባያቸው የቤተክርስቲያን ፈተናዎች መፍትሔ ብሎ ባሰባቸው አቅጣጫዎች በበጎ ፈቃድ ለመስራት መንፈስ ቅዱስ መርቶት ተወልዷል። የቅድስት ቤተክርስቲያን ችግሮች ሲቀረፉ የማኅበሩ አስፈላጊነት ኢመንት ሲሆን እንደ ልጅነቱ በቤተክርስቲያን ኅብረት ይቀጥላል እስከዛው ያለጊዜው ለማጨድ የሚሯሯጡትን በዝምታ እያየ ሥራውን ወደ ፊት ገፍቶ ያሳያል።

ክርስቶስ ከሚወለድበት ቀን አንዲት ሰኮንድ እንዳልዘገየው በሥጋ ሞቶ ሙታንን ድል ይነሱ ዘንድ ዐርአያነቱን ለማሳየት እንዲሁ እንዳላፈጠኑበት አሁንም በየጊዜው የሚወለዱ አላዊያን ከክህደትም ሆነ ከምንፍቅና ከትእቢትም ሆነ ከምቀኝነት ጎን ቆመው ፈተና ቢሆኑበትም በየጊዜው የራሱ ጠባሳ ጥለው ከማለፍ በስተቀር የማኅበሩን የአገልግሎት በር ጨርሰው አልዘጉትም።

ግን ዛሬ ስለ ምቹ ሁኔታዎችና ጊዜና ቦታዎች አንድ ወንድማችን ያጋራንን ወደናንተ ወደ አንባቢያን እናድርስ።

የማኅበረ ቅዱሳንን ያህል ለመሥራት ጳጳስ መሆን ያስፈልግ ይሆንን?

ምቹ ጊዜና ምቹ ሁኔታ እየጠበቅን እስከመቼ?

ማኅበረ ቅዱሳን እየሠራ ያለው ከጳጳሳትና ከቤተ ክህነት ጋር አይደለምን?

ምንደነቅባቸውን ዘመኑን የዋጁ አገልግሎቶች እየፈጸመስ ያለው እኛ አባል በሆንባት ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሆኖ እየሠራ አይደለምን?

ለእኛ ምቹ ያልሆነልን የአገልግሎት ዐውድ ለማኅበረ ቅዱሳን ሲሆን እንዴት ምቹ ሊሆን ቻለ?

እኛን አያሳትፍም እያልን የምናማውና የምንወቅሰው ቤተ ክህነት ለማኅበረ ቅዱሳን ብቻ እንዴት አሳታፊ ሊሆን ቻለ?

የማኅበረ ቅዱሳን ብልጫው በተግባር መገለጡ ብቻ ነው!
እኛን የሚያደክሙን፣ የሚያሰለቹንና የሚያበሳጩን የቤተ ክርስቲያናችን አስተዳደራዊ ሁኔታዎች ለማኅበረ ቅዱሳንም ተመሳሳይና አንድ አይነት ናቸው!!

እኛ በምናውቀው የቤተ ክርስቲያናችን ነባራዊ ሁኔታ ውስጥ እኮ ነው ማኅበረ ቅዱሳን ብዙዎቻችን የምንደነቅበትን አገልግሎት እየፈጸመ ያለው!!!

የእግዚአብሔር መንግሥት ሥራ “አቦ አቦ” ተብለን የምናገለግልበት ሳይሆን ከመናፍስት ጋር እየተዋጋንና እየታገልን፤ እየተሰደብንና እየተንጓጠጥን . . . ገንዘባችንን፣ ጉልበታችንን፣ እውቀታችንን፣ ጊዜያችንንና ስሜታችንን . . . እየከሠርን የምንፈጽመው አገልግሎት ነው!!!

ሁሉንም ችግርና ክፍተት ጠቅልሎ ለቤተ ክህነቱ ማሸከም ተገቢ አይደለም!!! ለሁሉም ውድቀትና ክፍተት ሰበብ የምናደርገው ቤተ ክህነት ባለበት ነው ማኅበረ ቅዱሳን በዚህ ልክ አርዐያ ሆኖ በተግባር ሊታይ በሚችል ለውጥ መገለጥ የቻለው፡፡

እውነቱ ይህ ከሆነ ደግሞ ክፍተቱ ከቤተ ክህነቱ ሳይሆን በተግባር መገለጥ ካቃተን ከእኛ ከምእመናን ነው ማለት ነው!!!

በቤተ ክህነታችን የተዝረከረከና ዘመኑን ያልዋጀ አገልግሎት አሠጣጥ ማሳበባችንን ትተን በዚህ ውስጥም ሆኖ ስለማገልገል እናስብ!🤔

“ቤተ ክህነቱ አያሠራም፣ አያቀርብም፣ ገፊና ኋላ ቀር ነው . . .” እያልን ማሳበባችንን እንተውና እኛ በተጨባጭ ልንወስደው ስለምንችለው ድርሻና ልንወጣው ስለሚገባን ኃላፊነት ብቻ እናስብ!!!

ማኅበረ ቅዱሳን ያንን ሁሉ ሥራ የሠራውና እየሠራም ያለው እኛ ከምንወቅሳቸው ጳጳሳት . . . እኛ ከምናማርራቸው ሥራ አስኪያጆች . . . እኛ ከምንከፋባቸው አስተዳዳሪዎች . . . እኛ ከምናዝንባቸው ካህናት . . . እኛ ከምንበሳጭበት ቤተ ክህነት ጋር ሆኖ ነው!!! . . . ማኅበረ ቅዱሳን ይህን ማድረግ የቻለው እንዴት ነው? . . . እንደ እኛ ማማረር አይችልም ነበርን? . . . እንደ እኛ ጳጳሳቱንና ቤተ ክህነቱን መውቀስ አይችልም ነበርን? . . . እንደ እኛ ቤተ ክህነቱ ስለማያሠራኝ ምን አጨቃጨቀኝ ብሎ ከዳር ተቀምጦ መመልከት አይችልም ነበርን?

የምናነሳቸውና የምንጠቅሳቸው ችግሮች እውነተኞች ቢሆኑም በምንለው ልክ ግን ቤተ ክህነታችን የማያሠራና የማያፈናፍን አይደለም!!!

ማኅበረ ቅዱሳን የምእመናን ስብስብ አይደለምን? . . . እኛስ ምእመናን አይደለንምን? . . . ማኅበረ ቅዱሳን የበጎ ፈቃደኞች ስብስብ አይደለምን? . . . እኛስ በበጎ ፈቃድ የምንችለውን ልናበረክት የምንችልበት ምንም ዐይነት አውድ የለምን? . . . ማኅበረ ቅዱሳን እየሠራ ያለው እኛ ከምናውቀው ቤተ ክህነት ጋር አይደለምን? . . . እኛስ ከቤተ ክነቱ ጋር መሥራት የለብንምን? . . . የለውጡ ጀማሪዎች መሆን ያለበትስ ማን ነው?

ሁላችንም እያማረርንና ለውጡን ከሌላ ወገን እየጠበቅን ለውጡን እውን ማድረግ የምንችለው እንዴት ነው? . . . እኛ ተስፋ በቆረጥንበትና በተውነው ነገርስ ተስፋ የመፍጠር ዕዳ የወደቀበት ማን ነው?
.
“የሁሉም ችግር ምንጭና መንስኤ ጳጳሳቱ፣ ቤተ ክህነቱና ካህናቱ ናቸው” ብሎ መበየን ጭፍንና ጨለምተኛ ድምዳሜ ነው!!! ቤተ ክህነታችን ዘመኑን ያልዋጀ መሆኑ እውነት ቢሆንም ፈጽሞ “የማያሠራና እንጥፍጣፊ ዕድል የሌለበት ነው” ብሎ ከዳር ተቀምጦ መተቸት ግን ከሥራ የመለገምና የስንፍና መገለጫ ነው!!!

🤔ወደራሳችን የምናየው መቼ ነው? . . . የእኛን ክፍተትስ ደፍረን የምንናገረው መቼ ነው? . . . ስላልወሰድነው ድርሻና ስላልተወጣነው ኃለፊነት ራሳችንን ጥፋተኛ የምናደርገው መቼ ነው?
ስላጎደልነው ነገር እራሳችንን የምንወቅሰውስ መቼ ነው? . . . ለሁሉም ችግር መንስኤና መፍትሔ ጳጳሰቱና ቤተ ክህነቱ ብቻ ሊሆኑ የሚችሉት በምን አመክንዮ ነው? . . . እሺ የምእመናኑስ ክፍተትና ቸልተኝነት መቼ ነው የሚነገረው!!!

የምእመናን ድርሻ ገንዘብ መስጠት ብቻ ነው ያለውስ ማን ነው? “ገንዘቤን ከሰጠሁና በሥርዐተ አምልኮው ከተሳተፍሁ” በቂ ነው ማለትስ ምን ያህል ተገቢና አዋጭ ነው?

ከቤተ ክህነት ጋር አብሮ መሥራትና ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል ምስክራችንም ሆነ ማሳያችን ማኅበረ ቅዱሳን ነው!!!

ብዙዎች ይሔን ማኅበር ከሥሩ ለመገንጠል ብዙ ለፍተዋል፣ ብዙ ስም ሰጥተው ብዙ ከሰውታል። ግን የማኅበረ ቅዱሳንን ያህል ለመሥራት የግድ ጳጳስ መሆን ወይም ደግሞ የሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ መሆን አይጠበቅም! “ከአንጀት ካለቀሱ እንባ አይገድም” እንዲሉ በምናወራው ልክ ለውጥና መሻሻልን አፍቃሪዎች ከሆንን ከቤተ ክህነታችን ጋር ሆነን የምንሠራቸው ሥራዎች እጅጉን ብዙ ናቸው!!!

ወዳጄ ለአገልግሎትህ መዳከም ሰበብ አትደርድር፣ ለስንፍናህ ምቹ ጊዜ አትዘጋጅ!

Via @EdomHailu
ይቆየን!

✍️† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †✍️
               🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

31 Oct, 04:36


ዝም ብላችሁ ሥራችሁን ስሩ!

ክፍል-፪-(የመጨረሻው ክፍል)

መናገራችን ከሚጠቅመው ይልቅ የሚጎዳው፤ ከሚያንጸው ይልቅ የሚያፈርሰው የሚበልጥ ከሆነ አለመናገራችን የተሻለና ተመራጭም እንደሚሆን መቀበል አለብን!!! ስንት ዘመን ያለ ተግባር ተናግረን ምን ለወጥን? ብዙዎቻችን ዝም የምንለውና የማንናገረው ስለምንፈራ፣ እውነቱ እንዲደበቅ ስለምንሻ፣ የክፉዎችን ተግባር ስለምንደግፍና ስለምንተባበር፣ ለውጥና መሻሻልን ስለምንጠላ፣ ለቤተ ክርስቲያናችን ስለማንቆረቆርና ስለማንወግን  . . . ሳይሆን መናገራችን የበለጠ ጉዳት ሊያስከትል ስለሚችል ወይም ደግሞ መናገራችን የሚለውጠው ነገር ሳይኖር ሲቀር ነው!!!

አሁን ባለው የአብዛኛው ኦርቶዶክሳዊ ሁኔታ ቤተ ክህነቱን በመስደብና በመርገም የሚጽናናው በጣም ብዙ ነው፤ መስደቡንና መራገሙን ልክ እንደስኬት ተቀብሎ ወደ ተግባር መግባት እንዳለበት እንኳን ዘንግቶታል!!

ቤተ ክህነትን መስደብና ችግሩን መላልሶ ማውራት ለቤተ ክርስቲያን የመቆርቆር መገለጫ ከሆነ ውሎ አድሯል! “ተግባር ላይ ይተኮር፤ መፍትሔ ተኮር እንሁን” የሚሉ አካላትም ከቤተ ክህነቱ ጋር አብረው የሚፈረጁና የሚረገሙ ሆነዋል!!!

🛖ስለቤተ ክህነቱ ማውራትና ስንፍናውን ማጋለጥ በጣም ቀላሉ ነገር ነው፤ ግን ደግሞ የቤተ ክህነቱን የተዝረከረከና ዘመኑን ያልዋጀ አሠራር ማጋለጥ ብቻውን የሚፈይደው ነገር ምንድን ነው?

እኛስ ብንሆን ከቤተ ክህነቱ ምን ብልጫ እናደርጋለን? ምንስ ድርሻ እንወስዳለን? ከመውቀስና ከማውራት ባለፈስ በተግባርና በድርጊት ተገልጠን እናውቃለን ወይ?

መውቀስና የሌላውን ስህተት መንገር ቀላሉ ነገር ነው፤ ግን ደግሞ መፍትሔ ተኮር ካልሆንንና ለመፍትሔውም ቢያንስ አንድ ጠጠር መጣል የምንችል ካልሆንን የእኛስ ብልጫ ምኑ ላይ ነው?🤔

መናገራችን ብቻውንስ ምን ሊፈይድ፤ ምንስ ሊለውጥ ይችላል?🤔

አሁን ላይ የተሻለው አማራጭ ቤተ ክህነቱን መስደብና ማነወር ሳይሆን እኛ ልንወስደው ስለምንችለው ድርሻ መመካከርና በእኛ ተጨባጭ ሁኔታ ልንሳተፍ የምንችልበትን ዐውድ መፍጠር ነው!!

ቤተ ክህነቱ የእኛ እስከሆነ ድረስ ከድሮ እስከ ዘንድሮ አብጠርጥረን እናውቀዋለን! በተለያዩ አጋጣሚዎች ተገናኝተን እናውቃለን፣ ብዙ ሥራዎችንም አብረነው ሠርተናል፣ የእጅ መዳፋችንን ያህል እናውቀዋለን ስላወቅነው ብቻ ግን ያወቅነውን ሁሉ አንናገርም!!!

የመናገራችንን ፋይዳ ቀድመን ማሳብ አለብን!!!

🛖ስለቤተ ክህነት የምናውቀውን ሁሉ ብንናገር ምናልባትም ቤተ ክርስቲያኒቱን ሊያፈርሳትም እኮ ይችላል!!! የምናውቀው ሁሉ ቢነገር ተቋማዊ ሕልውናችን ጥያቄ ውስጥ ሊወድቅ እንደሚችልም መረዳት አለብን!!!

ብንሰማ ልንሸከመውና ልንቋቋመው የማንችለውን ጉዳይ ካልወጣና ካልተነገረ የሚል እልህ ውስጥ መግባት ተገቢ አይደለም!!!

ሁሉም አይነገርም፤ ሁሉንም ለመስማት መጓጓትም ጤናማ ልማድ አይደለም! ስንናገርም ሆነ ስንሰማ ጥቅምና ጉዳቱን አመዛዝነን እንናገር፣
ረብ ያለውን ብቻም እንስማ!!!

መልካም ቀን መልካም ቆይታ!

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

31 Oct, 04:29


ዝም ብላችሁ ሥራችሁን ስሩ!

ክፍል-፩-

ቤተ ክህነቱን ከእግር እስከ ራሱ እናውቀዋለን፤ ያወቅነውን ሁሉ ግን አንናገርም!

መናገር በጣም ቀላሉ ነገር ነው፤ ከተናገርን በኋላ ውጤቱ ምን ሊሆን ይችላል ብሎ ማሳብ ግን ዋናውና ወሳኙ ነገር ነው!!!

ከተናገርን በኋላ የሚመጣውን ውጤት ለመቀበልና ያፈረስነውን ደግመን ለመገንባት የምንገደድበት ሁኔታ መኖር አለመኖሩን ሳንናገር በፊት እርግጠኞች መሆን አለብን!!

ስለማውቅ ተብሎ ብቻ ያወቁት ሁሉ አይነገርም፤ መረጃ ስለለን ብቻም ሁሉንም ወደ ዐደባባይ ይዘን አንወጣም!!!

🛖ቤተ ክርስቲያንን ሊጠቅምና ምእመናንን ሊያንጽ፤ ተቋማዊ አሠራራችንንም ሊያስቀጥል የሚችል እስካልሆነ ድረስ መነገሩና መወራቱ ብቻውን ምን ይፈይዳል! ገና ለገና እውነት ነው በሚልና መረጃው አለኝ በሚል አመክንዮ ጭርስ አድርጎ መናገር ጉዳቱ ብዙ ነው!!!

ስንናገርም ሆነ ዝም ስንል ለቤተ ክርስቲያን ብለን ነው መሆን ያለበት!!!

ይቀጥላል!

✍️† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †✍️
               🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

31 Oct, 04:20


"ቤተክርስቲያንን የሚያስቀጥሉ ሦስት ሰንሰለቶች አሉ እነርሱም:---
    ትዳር ፣ ምንኩስና እና ክህነት ናቸው።

እነዚህ እክል ስለገጠማቸው ነው ቤተክርስቲያን እየተቸገረች ያለቸው እንጂ ሌሎች ሰዎች ወይም አህዛብ ክፉ ስለሆኑ አይደለም። እነሱ ደግ የሚሆኑበት ዘመን ነገም እኔ አልጠብቅም ሰይጣን ባለበት መልካም ነገር አይመጣም።

እኛ ግን የጎደለን ይህ ነው፣ በተከበረ ትዳር ፣በተከበረ ምንኩስና እና በተከበረ ክህነት ቤተክርስቲያን ትቀጥላለች።

ምሳሌ እንዴት ካልን፦
👉የተከበረ ትዳር:- የተከበረ መነኩሴ ይወልዳል።
👉የተከበረ መነኩሴ:- የተከበረን ጵጵስናን ያመጣል።
👉የተከበረ ጳጳስ:-  የተከበረን ክህነትን ይሾምና
🙏የተከበረው ክህነት:- የተከበረ ትዳርን ባርኮ ያጋባል።
👉የተከበረው ትዳር መልሶ እንደገና የተከበረ ካህንን ይወልዳል።

በዚህ ዑደት ነው ቤተክርስቲያን ተጠብቃ የምትኖረው። አሁን ግን ምንጩ ደፍርሷል። ለዚህም ሁላችንም መስተካከል አለብን።

አሁን እኔ ሁሉም ሥርዓት እየፈረሰ እንደሆነ ነው የሚሰማኝ! ተምረን ማግባትና፣ ተምረን መመንኮስም ሆነ  ክህነት መያዝን ማስቀጠል አለብን።"

ርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
✍️† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †✍️
               🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

31 Oct, 04:19


✞ ስንክሳር ጥቅምት 21 ✞

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን

✞ ጥቅምት 21 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ✞

👉✞ እግዝእትነ ማርያም ✞👈

እመቤታችን ድንግል ማርያም የወልደ እግዚአብሔር እናቱ ናትና ሁሉን ትችላለች:: እርሱን ከሃሊ (ሁሉን ቻይ) ካልን እርሷን "ከሃሊት" ልንላት ይገባል:: ልክ ልጇ ሁሉን ማድረግ ሲችል በትእግስት ዝም እንደሚለው እመብርሃንም ስንት ነገር እየተደረገ: በእርሷ ላይም አንዳንዶቹ
ስንት ነገርን ሲናገሩ እንደማትሰማ ዝም ትላለች::

እኛ ኃጥአን ንስሃ እስክንገባ ድረስም "ልጄ! የዛሬን
ታገሣቸው?" እያለች ትለምንልናለች:: ቸሩ ልጇም ሊምረን እንጂ ሊያጠፋን አይሻምና "እሺ እናቴ!" እያለ ይኼው በዚህ ሁሉ ክፋታችን እስከ ዛሬ ድረስ አላጠፋንም::
*ቸር ነው
*መሐሪ ነው
*ይቅር ባይ ነው
*ታጋሽ ነው
*ርሕሩሕ ነው
*ቂምም የለውም:: በንስሃ ካልተመለስን ግን አንድ ቀን መፍረዱ አይቀርምና ወገኖቼ ንስሃ እንግባ: ወደ እርሱም እንቅረብ::

ይህቺ ዕለት ለእመቤታችን እሥረኞችን የምትፈታባት ናት:: የሰው ልጅ በ3 ወገን እሥረኛ ሊሆን ይችላል:: በሥጋዊው:- አጥፍቶም ሆነ ሳያጠፋ ሊታሠር ይችላል:: በመንፈሳዊው ግን ሰው በኃጢአት ማሠሪያ የሚታሠረው በጥፋቱ ብቻ ነው::

ሌላኛው ማሠሪያ ደግሞ ማዕሠረ ደዌ (በደዌ ዳኝነት) መታሠር ነው:: መታመም የኃጢአተኛነት መገለጫ አይደለም:: ምክንያቱም ከቅዱሳን ወገን ከ80 % (ፐርሰንቱ) በላይ ድውያን ነበሩና::

ታዲያ በዚህች ዕለት እመ በርሃን 3ቱንም ማሠሪያዎች እንደምትፈታ እናምናለን:: በእሥር ቤትም: በኃጢአትም ሆነ በደዌ ማሠሪያ የታሠርን ሁላችን በዚሁ ዕለት እንድትፈታን የአምላክ እናትን እንለምናት::

በ3ቱም ማሠሪያዎች የታሠሩ ወገኖቻችንንም እያሰብን "ይባእ ቅድሜከ ገዐሮሙ ለሙቁሐን-የእሥረኞች ጩኸት ወደ አንተ ይድረስ" እያልን (መዝ. 78:11) ልንጸልይ ይገባል::

እመ ብርሃንንም እንደ ሊቃውንቱ:- "እማእሠረ ጌጋይ ፍትሕኒ ወላዲተ ክርስቶስ አምላክ: እምነ ሙቃሔ ጽኑዕ ወእማዕሠር ድሩክ:
ከመ ፈታሕኪዮ ዮም ለማትያስ ላዕክ::" እንበላት::

🙏+" ቅዱስ አልዓዛር ሐዋርያ "+🙏

ቅዱስ አልዓዛር በሃገረ ቢታንያ ከእህቶቹ ማርያና ማርታ ጋር ይኖር ነበር:: ሦስቱም ድንግልናቸውን ጠብቅው ጌታችንን ያገለግሉት ነበርና አልዓዛርን ከ72ቱ አርድእት ማርያና ማርታን ደግሞ ከ36ቱ ቅዱሳት አንስት ቆጥሯቸዋል::

በወንጌል ጌታችን ይወዳቸው እንደነበር ተገልጧል:: ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲወድ የሚያበላልጥ ሆኖ አይደለም:: ይልቁኑ በምሥጢር እነርሱ ተወዳጅ የሚያደርጋቸውን ሥራ ይሠሩ እንደነበር ሲነግረን ነው እንጂ::

ቅዱስ መጽሐፍ እንደነገረን ጌታችን በነአልዓዛር ቤት በእንግድነት ይስተናገድ ነበር:: በመጨረሻዋ ምሴተ ሐሙስም ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ለሐዋርያቱ ያቀበላቸው በእነዚህ ቅዱሳን ቤት ውስጥ ነው::

ቅዱስ አልዓዛር በጽኑዕ ታሞ አርፏል:: ቅዱሳት እህቶቹ ማርያና ማርታ ከታላቅ ለቅሶ ጋር ዕለቱኑ ቀብረውታል:: (ዮሐ.11)

ቸር ጌታችን ክርስቶስ ከ4 ቀናት በኋላ ሊያስነሳው
ይመጣል::

ለስም አጠራሩ ስግደት: ክብር: ጌትነት ይድረሰውና
አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ አልዓዛር ባረፈ በአራተኛው ቀን ወደ ቢታንያ ደረሰ:: ማርታ ቀድማ ወጥታ ከእንባ ጋር ተቀበለችው::

'አዳም ወዴት ነህ' ያለ (ዘፍ. 3) የአዳም ፈጣሪ
'አልዓዛርን ወዴት ቀበራችሁት' አለ:: ቸርነቱ: ባሕርዩ
ያራራዋልና ማርያም ስታለቅስ ባያት ጊዜ አብሮ አለቀሰ::

ከዚያም በባሕርይ ስልጣኑ "አልዓዛር አልዓዛር" ብሎ አልዓዛርን አስነሳው:: ይሕች ተአምርም በአይሁድ ዘንድ ግርምት ሆነች:: ለጌታም የሞት ምክንያት አደረጉዋት:: ቅድስት ቤተ ክርስቲያን መጽሐፍ ቅዱስን መሠረት አድርጋ እንዲህ ታስተምራለች:: (ዮሐ. 11:1-ፍጻሜው)

ቅዱስ አልዓዛር ጌታችን ካስነሳው በኋላ በበዓለ ሃምሳ መንፈስ ቅዱስን ተቀብሎ (ቁጥሩ ከ72ቱ አርድእት ነውና): ለ40 ዓመታት ወንጌልን አስተምሮ: በ74 ዓ/ም አካባቢ ቆዽሮስ ውስጥ አርፏል::

+" ፍልሠት "+

ይህቺ ዕለት ለቅዱሱ ሐዋርያ በዓለ ፍልሠቱ ስትሆን ይህ የተደረገውም በ4ኛው መቶ ክ/ዘመን ነው:: ቅዱሱ ያረፈው ቆዽሮስ ውስጥ ነው:: ግን ባልታወቀ ጊዜና ምክንያት ወደ ኢየሩሳሌም ሒዷል::

አንድ ቀንም በመንፈስ ቅዱስ መሪነት ኢየሩሳሌም
ውስጥ ሲቆፍሩ አንድ አንድ ሳጥን አገኙ:: በላዩ ላይ ደግሞ "ይህ የጌታ ወዳጅ የአልዓዛር ሥጋ ነው" የሚል ጽሑፍ አግኝተው ደስ ተሰኝተዋል:: በታላቅ ዝማሬና ፍስሐም ከኢየሩሳሌም ወደ ቁስጥንጥንያ አፍልሠውታል:: የጌታችን ቸርነቱ: የአልዓዛር በረከቱ ይድረሰን::

🌿+" አባ ዮሐንስ ዘኢየሩሳሌም "+🌿

እኒህ ጻድቅ ሰው ግብጻዊ ሲሆኑ በሰፊው የሚታወቁት በኢትዮዽያና በኢየሩሳሌም ነበር:: ገና በወጣትነት የጀመሩትን የተጋድሎ ሕይወት ገፍተው በበርሃ ሲኖሩ የወቅቱ የግብጽ ሲኖዶስ ከበርሃ ጠርቶ የኢየሩሳሌም ዻዻስ እንዳደረጋቸው ይነገራል::

በቅድስት ሃገርም በንጽሕናና በመንኖ ጥሪት ወንጌልን እየሰበኩ ኑረዋል:: አባ ዮሐንስ የነበሩበት ዘመን 14ኛው መቶ ክ/ዘመን ሲሆን የወቅቱ የኢትዮዽያ ንጉሥ ደጉ አፄ ዳዊት ነበሩ::

ንጉሡ የግብጽ ክርስቲያኖችን ደም ለመበቀል (በወቅቱ ከሊፋዎች ያሰቃዩዋቸው ነበር) እስከ ላይኛው ግብጽ ወርደዋል:: በሃገር ውስጥ ያሉ ተንባላት አባሪዎቻቸውንም ቀጥተዋል:: በዚህ የተደናገጠው የግብጹ ሡልጣን 'አስታርቁኝ' ብሎ
ስለ ለመነ ለእርቅ የተመረጡ አባ ዮሐንስና አባ ሳዊሮስ ዘምሥር ናቸው::

እነዚህ አባቶች በ1390ዎቹ አካባቢ ወደ ኢትዮዽያ
ከመጡ በኋላ አልተመለሱም:: ምክንያቱም ደጉ አፄ ዳዊት እጅግ ስለ ወደዷቸው 'አትሔዱም' ብለው ስላስቀሯቸው ነው:: እንዲያውም ለግማደ መስቀሉ መምጣት ትልቁን አስተዋጽኦ ያደረጉት አባ ዮሐንስ ሳይሆኑ አይቀሩም:: ዛሬ የጻድቁ ዕረፍታቸው ነው::

አምላከ ቅዱሳን ስለ ድንግል እናቱ ብሎ ከኃጢአት ሁሉ ማሠሪያ ይፍታን:: የወዳጆቹን በረከትም አያርቅብን::

ጥቅምት 21 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.እግዝእትነ ማርያም
2.ቅዱስ አልዓዛር ሐዋርያ
3.አባ ዮሐንስ ዘኢየሩሳሌም
4.ቅዱስ ኢዩኤል ነቢይ
5.ቅዱስ ማትያስ ረድእ

" ጌታ ኢየሱስም 'ብታምኚስ የእግዚአብሔርን ክብር እንድታዪ አልነገርሁሽምን?' አላት... ይሕንም ብሎ በታላቅ ድምጽ 'አልዓዛር ሆይ ወደ ውጭ ና' ብሎ ጮኸ:: የሞተውም እጆቹና እግሮቹ በመግነዝ እንደ ተገነዙ ወጣ:: ፊቱም በጨርቅ እንደ ተጠመጠመ ነበረ:: ጌታ ኢየሱስም
'ፍቱትና ይሂድ ተውት' አላቸው::" (ዮሐ.11:40-44)

✍️† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †✍️
🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇

https://t.me/Sinksar
https://t.me/Sinksar
https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

30 Oct, 13:40


እኛ ስንሸሻቸው ሌላው ያጠምዳቸዋል!

አባቶቻችንን እንዴት እንቅረባቸው?

የቤተ ክርስቲያናችንን አባቶች ስለምንቀርብበትና ስለምንይዝበት አካሔድ፤ እነርሱን አስመልክተን ስለምናወጣቸው ቃላትና ስለምንጠቀማቸው ንግግሮች እጅጉን መጠንቀቅና ነገሩን ሁሉ በብልሐት ማድረግ ነው ያለብን!

ችግሮች ስላሉ ብለን ብቻ ያለአግባብ ሁሉንምና ዝርዝር ጉዳዩንም ጭምር ለገበያ የምናቀርበው፣ ለሚዲያ ፍጆታም የምናውለው ከሆነ በአባቶች ዘንድ የመናቅና የመገፋት ስሜት እንዲፈጠርባቸው ስለሚያደርግ ጉዳቱ ከፍተኛ ይሆናል፡፡

ለአንድ መንፈሳዊ አባት ደግሞ በመንፈሳዊ ልጆቹ እንደመከበር ያለ ቅድሚያ የሚሰጠውና አጥብቆ የሚፈልገው ጉዳይ የለም!!!

ለለውጥና መሻሻል ብለን የምንከተላቸው መንገዶችም ሆኑ የምናቀርባቸው አማራጮች የት እንደሚያደርሱንና እንዴት ያለ የጎንዮሽ ጉዳት ሊያስከትሉ እንደሚችሉ አስቀድመን ማሰብና መመርመር ይጠበቅብናል!

ሳናስብና ሳናጠና የምንከተላቸው መንገዶች ችግሩን የበለጠ የሚያወሳስቡበትና ከመፍትሔ የሚያርቁበት አጋጣሚ ሰፊ ነው፡፡ ንግግራችንም ሆነ ተግባራዊ አካሔዳችን በእጅጉ የተጠናና ውጤታማነቱ የተረጋገጥ መሆን አለበት፡፡ በግብታዊነት የሚሰነዘሩ ሐሳቦች፣ የሚሰጡ አስተያየቶችና የሚወሰዱ ተግባራዊ እርምጃዎች አፍራሽ ውጤት እንዳይኖራቸው አስቀድሞ ማሰብና በጥንቃቄ መመርመር ተገቢ ነው!!!

መፍትሔ ይሆናሉ ብለን የምናነሳቸው ሐሳቦችና የምንሰነዝራቸው አስተያየቶች በአባቶች ዘንድ ሊፈጥሩ የሚችሉትን ስሜትና የሚያሳድሩትን ሁለንተናዊ ጫና ገምግመን ነው መነሳት ያለብን! ይህን ማድረግ ካልቻልን ግን አባቶቻችን የመገፋትና የመናቅ ስሜት ስለሚያድርባቸው ተገፍተናል ብለው ባሰቡበት ቅጽበት ከእኛ የተሻለ የቃላት አጠቃቀምና የታረመ አካሔድን የሚከተል አፍራሽ ኃይል ሊያጠምዳቸውና በተሳሳተ መንገድ ሊጠቀምባቸው እንደሚችል ማሰብ ተገቢ ነው!!!

በቅርቡ የቤተ ክህነታችን ታሪክ ውስጥ ያየናቸውና ያስተዋልናቸው ልዩነቶችና እልህ የተቀላቀላቸው አካሔዶች ለምን ሆኑ ብለን ብንጠይቅ አላግባብ ተገፍቻለሁ፣ ተንቄያለሁና ተዋርጃለሁ የሚል የራስን ክብር የመከላከልና የማስጠበቅ ዝንባሌ ነው፡፡

የሰው ልጅ በተፈጥሮው ለክብሩ ልዩ ትኩረትና ፍላጎት ያለው መሆኑ እሙን ነው፤ ለአባቶች ሲሆን ደግሞ ደረጃው ከፍ ማለቱ የማይቀር ነው!!!

ለአንድ ኦርቶዶክሳዊ አባት ከክብሩ የሚበልጥበትና ከክብሩም ይልቅ የሚያሳስበውና የሚያስቀድመው ምን ነገር ይኖራል? የክብርና የመንበር ከፍታ ጉዳይ አይደለም እንዴ በታሪክ ውስጥ ቤተ ክርስቲያንን ሲከፋፍላትና ዋጋ ሲያስከፍላት የኖረው!!!

እንደ ተዋረደና እንደተናቀ የተሰማው ሰውስ እንዴት አድርጎ ነው ንቀውኛልና አዋርደውኛል ብሎ ከሚያስባቸው ሰዎች ጋር አብሮ ሊሠራና ሊተባባር የሚችለው! ከዚህ ይልቅ ግን ተንቄበታለሁ፣ ክብሬም ተነክቶበታል ብሎ ካሰበው ዐውድ የመነጠልና ሌላ አዲስ አጋር የመፈለግ ዕድሉ ብዙ ነው!!!

ቤተ ክርስቲያንን እንጠቅምበታለን ብለን የምንከተለው አካሔድና ችግሮችን ለመፍታት በሚል የምንጠቀመው ቃል ሊያመጣ የሚችለውን ቀጣይ ውጤትና የምንከሳቸው ሰዎች ላይ የሚፈጥረውን ስሜታዊም ሆነ ስነ ልቡናዊ ጫና ታሳቢ ያደረገ መሆን አለበት፡፡

ቃላት አጠቃቀማችንም ሆነ መፍትሔ የምንፈልግበት መንገድ እጅጉን ጥንቃቄ የታከለበት፣ የተጠናና የተመረጠ፣ የመገፋትና የመተው ስሜት የማይፈጥር፣ አዎንታዊ ውጤት ሊኖረው የሚችል . . . መሆን አለበት!

ለቤተ ክርስቲያን መቅናታችን ትክክልና ተገቢ ቢሆንም ግላዊ ስሜቶቻችንንና ብስጭታችንን ግን በአግባቡ ማስተዳደርና መቆጣጠር አለብን!

ችግር እንፈታለን ብለን ችግሩን ማወሳሰብና ተጨማሪ ችግር መፍጠር የለብንም፡፡ ምክንያቱም እኒያ አባቶች እንደኛው ሰዎች ናቸው። ስሜት አላቸው። ስሜት መግዛት የአንድ መንፈሳዊ አባት ግዴታ ቢሆንም ምናልባት አሁንም በሰውነታቸው ዝለት ይኖርባቸዋልና እንጠንቀቅ!።እስከዛሬ ከነበሩ አካሔዶቻችንና ከቀደመ ስህተታችን መማርና መታረም አለብን!!!
ያለአግባብ ያስተናገድናቸው፣ ያስቆጣናቸው፣ ያበሳጨናቸው፣ የገፋናቸውና እልህ ያጋባናቸው ጓዳ ጎድጓዳችንን ያውቁ የነበሩ ሰዎች ናቸው አሁን ላይ ቤተ ክርስቲያናችንን ዋጋ እያስከፈሏት ያሉት!!! ሌላ ጠላት ከሩቅ አልመጣብንም አይመጣብንም።

እንኳንስ ተግሳጽና ነቀፌታችን ፍቅርና መውደዳችንም፣ ድጋፍና ትብብራችንም ቢሆን የታሰበበት፣ የተመረጠና የተጠናና አዎንታዊ ውጤት ያለው ነው መሆን ያለበት! እኛ ለበጎ ብለን ያወጣነው ቃልና የተከተልነው አካሔድ ሌላኛው አካል ዘንድ ሲደርስ እንዴት እንደሚተረጎምና ምን አይነት ስዕል ሊፈጥር እንደሚችል እርግጠኞች መሆን ስለማንችል የቤተ ክርስቲያናችንን አካላት አስመልክቶ የምንሰጣቸው አስተያየቶችና የምንሰነዝራቸው ሐሳቦች ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚደረግባቸው መሆን አለባቸው!!!

የቃላትን ኃይል መዘንጋት የለብንም! የሚገነቡትንና የሚጠግኑትን ያህል ሊያፈራርሱና ሊሰባብሩ ስለሚችሉ ቃላት አጠቃቀማችን ላይ መጠንቀቅና መታረም ይኖርብናል፡፡ እንደሸሸናቸው፣ እንደናቅናቸውና እንደገፋናቸው የተሰማቸው የቤተ ክርስቲያን አካላት አሰላለፋቸውን ከተቃራኒ ወገን ጋር እንዲያደርጉ አሰፍስፎና ማባበያ አሰናድቶ የሚጠብቃቸው አካል አለ፤ እኛ ስንሸሻቸውና ስንገፋቸው ሌላው ደግሞ ያጠምዳቸዋልና አራት ዐይና ሆነን አካሔዳችንን ሁሉ በጥንቃቄ፣ ወደፊትና ወደኋላ መመልከትና ቅድመ ውጤት ግምገማ ማድረግ አለበን!!!

ችግርና ክፈተት ስላለ ብቻ ነገሩን ሁሉ የልጆች ጨዋታና የመንደር ብሽሽቅ ማድረግ፤ ሁሉንም ጉዳይ የአዳባባይ አጀንዳና የሚዲያ ግብአት ማድረግ ለወደረኞቻችን መመቸት፣ ራስን ማስገመትና ቤተ ክርስቲያናችንንም ዋጋ ማስከፈል ነው!!!

ይቆየን!
በመ/ር ዔዶም ሀይሉ

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

29 Oct, 23:48


🙏 ስንክሳር ጥቅምት 20 🙏

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡

✞✞✞ እንኩዋን ለታላቁ ቅዱስ አባ ዮሐንስ ሐጺር እና ለቅዱስ ኤልሳዕ ነቢይ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞✞✞

🔔🌿" ቅዱስ አባ ዮሐንስ ሐጺር "🌿🔔

በቤተ ክርስቲያን ያሉ አበው ሊቃውንት እንደሚሉት ከቅዱሳን በቁመቱ የአባ አርሳኒን ያክል ረዥም አልነበረም:: እርሱ እንደ ዝግባ ቀጥ ያለ ነበር:: በዚያው ልክ ደግሞ የቅዱስ ዮሐንስን (ዛሬ የምናከብረውን) ያህል አጭር አልነበረም:: በዚህ ምክንያት ይሔው ለዘለዓለም "ዮሐንስ ሐጺር - አጭሩ አባ ዮሐንስ" ሲባል ይኖራል::

ሊቃውንትም ቁመቱንና ቅድስናውን በንጽጽር ሲገልጡ:- "ሰላም ሰላም ዕብሎ በሕቁ:
ለዮሐንስ ሐጺር ዘነዊኅ ሒሩተ ጽድቁ" ይላሉ:: "ቁመቱ እጅግ ያጠረ: ጽድቁ ግን ከሰማይ የደረሰ ቅዱስ ዮሐንስን ሰላም ሰላም እንለዋለን" እንደ ማለት ነው::

ቅዱሱ የተወለደው በ4ኛው መቶ ክ/ዘመን በምድረ ግብጽ ነው:: ወላጆቹ ምንም ከሥጋዊ ሃብት ድሆች ቢሆኑም ባለ መልካም ክርስትና ነበሩና በጐውን ሕይወት አስተምረውታል:: ወደ ምናኔ የገባው ገና በ18 ዓመቱ ሲሆን የታላቁ አባ ባይሞይ ደቀ መዝሙር ሆኖ ተጋድሎንና ትሕርምትን ተምሯል::

ቅዱስ ዮሐንስ ሐጺር በወቅቱ ከነበሩ ቅዱሳን ከቁመቱ ባሻገር በትሕትናው: በትእግስቱና በመታዘዙ ይታወቅ ነበር:: አባ ባይሞይ ይጠራውና ያለ ምንም ምክንያት ደብድቦ ያባርረው ነበር:: እርሱ ግን "ምን አጠፋሁ?" ብሎ እንኩዋ ሳይጠይቅ "አባቴ ሆይ! ማረኝ?" እያለ ከእግሩ ሥር ይወድቅ ነበር::

ለብዙ ጊዜ በተመሳሳይ ሲደበድበው: እርሱም እርሱው ተደብድቦ: እርሱው ይቅርታን ሲጠይቅ ኖረ:: አንድ ቀን ግን እንደ ልማዱ ሊገርፈው ሲሔድ 7ቱ ሊቃነ መላእክት ከበውት አይቶ ደንግጦ ተመልሷል::

አባ ባይሞይ ይሕንን ሁሉ የሚያደርገው ጠልቶት ወይ ክፉ ሆኖ አይደለም:: አንድ ሰው የሌላኛውን ግፍ መቀበል ካልቻለ ሰይጣንን ድል አይነሳም የሚል ትምሕርት ስለ ነበረ ነው እንጂ::

አንድ ቀን ቅዱስ ዮሐንስ ወደ መምሕሩ ቀርቦ "አባቴ ጅብ ካገኘሁ ምን ላድርግ?" ሲል ጠየቀው:: (የአካባቢው ጅብ መናጢ ነበር) አባ ባይሞይ ግን "ይዘህልኝ አምጣው" አለው:: ትዕዛዝ ነውና ቅዱሱ ወደ በርሃ ወርዶ: ጅብ አልምዶ ይዞለት መጥቷል::

ሌላ ቀን ደግሞ አባ ባይሞይ ቅዱስ ዮሐንስን ጠራውና ተፈልጦ የወደቀ ደረቅ እንጨት ሠጠው:: "ምን ላድርገው አባ?" አለው:: "ትከለውና እንዲያፈራ አድርገው:: ከዚያ አምጥተህ አብላኝ" ሲል መለሰለት:: ይህ ነገር ከተፈጥሮ ሥርዓት ውጪ መሆኑን እያወቀ ቅዱስ ዮሐንስ "እሺ" ብሎ ወስዶ ተከለው::

ከዚያም ለ2 ዓመታት ሳይታክት ውሃ አጠጣው:: ውሃውን የሚያመጣበት ቦታ ደግሞ 10 ኪሎ ሜትር ያህል ከገዳሙ ይርቅ ነበር:: ቅዱሱ ላቡን እያፈሰሰ አሁንም ማጠጣቱን ቀጠለ::

በ3ኛው ዓመት ግን ለምልሞ አበበ: ደግሞም አፈራ:: ካፈራው በኩረ ሎሚም ወስዶ ለመምሕሩ "አባቴ! እንካ ብላ" ብሎ ሰጠው:: አባ ባይሞይ ግን ማመን አልቻለም:: እጅግ አደነቀ: አለቀሰም::

ወዲያው ያን ፍሬ ታቅፎ ወስዶ ለገዳሙ መነኮሳት አላቸው- "ንሱ ብሉ: በረከትንም አግኙ:: ይህ የዛፍ ሳይሆን የመታዘዝ ፍሬ ነው:: ቅዱስ ዮሐንስ አባ ባይሞይ ቢታመም ለ12 ዓመት አስታሞታል::

መምሕሩ ከማረፉ በፊትም መነኮሳቱን ሰብስቦ የቅዱስ ዮሐንስን እጅ አስጨበጣቸው:: "ይህ የያዛችሁት እጅ የሰው ሳይሆን የመልአክ እጅ ነው" ብሏቸው ዐርፏል:: ቅዱስ ዮሐንስም ከዓመታት ቆይታ በሁዋላ የገዳሙ አበ ምኔት ሆኖ አገልግሏል:: ብዙ ነፍሳትንም ለቅድስና ማርኩዋል::

መላእክት ንጽሕናው ደስ ስለሚያሰኛቸው አብረውት ይውሉ ነበር:: ሲተኛም በተራ በተራ ክንፋቸውን ያለብሱት ነበር:: ምጽዋትን በጣም ስለሚወድ ሰፌድ እየሰፋ ይሸጥና ገንዘቡን ለነዳያን ያን ያካፍል ነበር::

አንድ ቀን እንደ ልማዱ ወደ ገበያ ወጥቶ ሳለ ተደሞ (ተመስጦ) መጣበት:: ሰማያት ተከፍተው: ቅዱሳን ሊቃነ መላእክት ሚካኤልና ገብርኤል በግርማ በጌታ ፊት ቆመው ተመለከተ::

"እጹብ: እጹብ" እያለ ሲያደንቅ አንድ ገዢ መጥቶ "ባለ እንቅብ ዋጋው ስንት ነው?" ቢለው "እኁየ ሚካኤልኑ የዓቢ ወሚመ ገብርኤል - ከሚካኤልና ከገብርኤል ማን ይበልጣል?" ብሎታል:: ገዢውም ደንግጦ "እብድ መነኩሴ" ብሎት ሔዷል::

ቅዱስ ዮሐንስ ሐጺር ወደ ባቢሎን (የአሁኗ ኢራቅ) ሒዶ ከተመለሰ በሁዋላ በበርበሮች ምክንያት ከአስቄጥስ ወደ ቁልዝም ተሰዷል:: በዚያም በአባ እንጦንስ በዓት ውስጥ ዐርፏል:: ለ400 ዓመታት በዚያው ቆይቷል::

በ825 ዓ/ም ግን በአባ ዮሐንስ ፓትርያርክ ዘመን ክቡር ሥጋው ወደ ገዳመ አስቄጥስ ተመልሷል:: ቅዱሱ ያረፈው ጥቅምት 20 ቀን ሲሆን ዛሬ ሥጋው የፈለሠበት ነው:: በዚህ ዕለትም የቅዱስ ዮሐንስ ሐጺርና የታላቁ ቅዱስ መቃርስ ሥጋ በተገናኙ ጊዜ ግሩም ተአምር ተደርጉዋል:: ወደ ቤተ ክርስቲያኑ ሲገባም ታላቅ የብርሃን ጐርፍ ሲፈስ ታይቷል::

ሰማያዊ መዓዛም አካባቢውን ሞልቶታል:: ከዻዻሳቱ አንዱ እባረካለሁ ብሎ የቅዱስ ዮሐንስን ሥጋ ቢገልጠው አካባቢው ተናወጠ:: መባርቅትም (መብረቆች) ተብለጨለጩ:: ደንግጠው ቶሎ ቢያለብሱት ጸጥታ ሆኗል:: በዚህ ሁሉ ደስ ያላቸው አበው ቅዱሱን በዝማሬ ሲያወድሱት ውለዋል::

🌿+" ቅዱስ ኤልሳዕ ነቢይ "+🌿

+ከነቢያተ እሥራኤል አንዱ
+ከእርሻ ሥራ ቅዱስ ኤልያስን የተከተለ
+መናኔ ጥሪት የተባለ
+በድንግልና ሕይወት የኖረ
+የታላቁ ነቢይ ኤልያስ መንፈስ እጥፍ የሆነለት
+እጅግ ብዙ ተአምራትን ያደረገ
+አንዴ በሕይወቱ: አንዴ በአጽሙ ሙታንን ያስነሳ ታላቅ ነቢይና አባት ነው::

ቅዱስ ኤልሳዕ በጣም ረዥም: ራሱ ገባ ያለ (ራሰ በራ): ቀጠን ያለ: ፊቱ ቅጭም ያለ (የማይስቅ) ሽማግሌ ነበር::

=>አምላከ ቅዱሳን የሐጺር ቅዱስ ዮሐንስን መታዘዙን: ትሕትናውን: ትእግስቱንና ቅንነቱን ያድለን:: በበረከቱም ይባርከን::

=>ጥቅምት 20 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ አባ ዮሐንስ ሐጺር
2.ቅዱስ ኤልሳዕ ነቢይ
3.አባ ባይሞይ

=>ወርኀዊ በዓላት
1..ቅዱስ ዮሐንስ ሐፂር
2.ቅዱስ አክሎግ ቀሲስ
3.ቅዱስ አፄ ካሌብ ጻድቅ (ንጉሠ ኢትዮዽያ)
4.አባ አሞንዮስ ዘሃገረ ቶና
5.ቅድስት ሳድዥ የዋሒት
6.ቅዱስ ወክቡር ማር ቴዎድሮስ ሰማዕት

"እናንተ ደግሞ የታዘዛችሁትን ሁሉ ባደረጋችሁ ጊዜ 'የማንጠቅም ባሪያዎች ነን: ልናደርገው የሚገባንን አድርገናል' በሉ:: " (ሉቃ. 17:10)

✍️† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †✍️
               🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

29 Oct, 05:29


የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን እውቅና የሰጠችው የአዋልድ መጻሕፍት ኅትመት ያስፈልጋል፡፡

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤ/ን እውቅና ያለው ማለትም ይሄ ነው የሚወክለኝ የምትለው በአብዛኛው አዋልድ መጻሕፍት ቨርሽን የለም፡፡

በዚህ ዘመን ቤተ ክርስቲያኒቱን የማይወክሉና ከዕውቅናዋ ውጭ የወጡ ኅትመቶች (unauthorized versions) ያለቤ/ን እውቅና የሚታተሙ በየገበያው ማግኘት የተለመደ ነው፡፡

ስለዚህ በቤ/ን መጻሕፍት አግባብነት በሌለው መንገድ የሚነሱትን ነቀፋና ዘለፋ ሙሉ በሙሉ authorized versions በማዘጋጀት መቅረፍ ባይቻልም ነገር ግን ማዘጋጀቱ በብዙ መንገድ ጠቀሜታ አለው፡፡

የውስጥ ጠጋኝ አጥፊ አውዳሚ አይደለም፡፡ ለምሳሌ ተአምረ ማርያምን ለማንሳት ብንሞክር የፕ/ር ጌታቸው አስተያየት መሠረት በማድረግ እውቅና ያለው ኅትመት ማዘጋጀት ይቻላል፡፡

"በአሁኑ ሰዓት የግዕዝ ሥነ ጽሑፍ ስድስት መቶ የሚደርሱ የማርያም ታምሮች አሉት፡፡ እርግጥ አንዳንዶቹ በተለያየ አጻጻፍ ተደጋግመው የተደረሱ ናቸው፡፡” (ጌታቸው ኃይሌ፣ ከግዕዝ ሥነ ጽሑፍ ጋር ብዙ አፍታ ቆይታ ) ስለዚህ አንዳንዶቹ በተለያየ አጻጻፍ ተደጋግመው የተደረሱ የተባሉትን ቤ/ን በመዛግብት የሚገኙትን ተመሳሳይ ታሪክ ያላቸውን በተለያየ አጻጻፍ የተደረሱትን ተአምራት በባለሙያ ለይታ ማሳተም ይገባታል፡፡

እንዲሁም በቅዱስ ሲኖዶስ ደረጃ ውሳኔ የተሰጠበትን ከዕውቅናዋ ውጭ በታተመ ተአምረ ማርያም የተካተቱትን እንደ ፓትርያርክ አቡነ ጳውሎስን እና ኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለ ማርያምን አይነት ተገቢ ያልሆነ “ተአምራት” በማለት የገቡትን እንዲወጡ/እንዲወገዱ በማድረግ ቤ/ን እውቅና የሰጠችው ኅትመት (authorized versions) ማዘጋጀት ይገባል፡፡

በነገራችን ላይ ፕ/ር ጌታቸው "ከግዕዝ ሥነ ጽሑፍ ጋር ብዙ አፍታ ቆይታ" በተሰኘ መጽሐፋቸው በገጽ-364 “ዐፄ ዳዊት ከአስተረጎማቸው ተአምራት በላይ ያሉትን ሁሉ ያስጻፋቸው ዘርዐ ያዕቆብ ባይሆንም በአሁኑ ሰዓት የግዕዝ ሥነ ጽሑፍ ስድስት መቶ የሚደርሱ የማርያም ታምሮች አሉት፡፡ እርግጥ አንዳንዶቹ በተለያየ አጻጻፍ ተደጋግመው የተደረሱ ናቸው፡፡” ይላሉ፡፡

ማንም ተራ ፓስተርና ጽንፈኛ ብሔርተኞች በአዋልድ መጻሕፍት ላይ ያለ አግባብ አፉቸውን የሚከፍቱትን በሕግ፣ በቃል፣በጽሑፉ… መጠየቅና መልስ መስጠት አግባብ ቢሆንም ነገር ግን በቤታችን መሥራት የሚገባንን የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያንን የሚወክሉና ከዕውቅናዋ ውጭ ያልወጡ ኅትመቶች (authorized versions) የሚመለከተው አካል ማዘጋጀት ይገባዋል ስንል ለቀጣይ ትውልድ በማሰብ ነው፡፡

የቤታችን ክፍተት ላይ ትኩረት በማድረግ መሥራት ይገባናል፡፡ ቤ/ን መሥራት የሚችሉ ብቁ የሆኑ ሊቃውንት ነበሯት የሚያስተባብር የቤተ ክህነት አካል ጠፋ እንጅ …

በአጠቃላይ አዋልድ መጻሕፍት authorized versions ይዘጋጅላቸው፡፡ ጨከን ብለን መታረም ያለባቸውን ማረም ያስፈልጋል፡፡ የውስጥ ጠጋኝ አጥፊ አይደለም፡፡ በተጨማሪ የግንጊልቻ መጽሐፍ ደራሲ ከትርጓሜ መጻሕፍት ጀምሮ በአጠቃላይ በአዋልድ መጻሕፍት ላይ ያነሳቸውን ወሳኝ አስተያየት ልብ ማለት መልካም ነው፡፡

ቢያንስ ቢያንስ በግንጊልቻ መጽሐፍ የተጠቆሙትን ሐሳቦች ለመፍትሔነት እንጠቀም፡፡ ይህ ነገር በተቋም ደረጃ በምሁራን በተደራጀ መልኩ ሊሠራ የሚገባው ነው። በተለይ ከፍተኛ የPhilology ሙያ ያላቸው አማኝ የቤተክርስቲያን ልጆች ያስፈልጉናል። አማኝ የሚለውን አስምሩበት።

ቤተክህነቱ ሥራውን አምኖበት በጀት በጅቶ ሊያሠራ ይገባዋል። ከዚህ ውጭ ለቀጣይ ትውልድ በማሰብ መሠረታዊ መፍትሔ በግለሰብ ደረጃ ማምጣት የሚቻል አይመስለኝም።

በመ/ር ዮሴፍ ፍስሐ
✍️† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †✍️
               🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

28 Oct, 17:54


የኤፌሶን ወንዝ ቅዳሜ ለሁሉም መጽሐፍ መደብሮች ትሰራጫለች። የሽፋን ዋጋ 400ብር
ሙሉ ገቢው ለግሸን ደብረ ከርቤ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስትያን ሕንፃ ቤተ መቅደስ እድሳት የሚውል።

መጽሐፍ መደብሮች ቀድማችሁ እዘዙ!
እስካሁን ያዘዙን!
1ኛ.ጃፋር መጻሕፍት መደብር 500ኮፒ
2ኛ.የኔነህ መጻሕፍት መደብር ቃሊቲ 1000ኮፒ
3ኛ.ጎንደር ማዕከል 100ኮፒ
4ኛ.አርባምንጭ 100ኮፒ
5ኛ.ሀሁ መጻሕፍት መደብር 100ኮፒ
6ኛ.ብራና መጻሕፍት መደብር 500ኮፒ
7ኛ.ሓያት ሳሪስ መጻሕፍት መደብር 50ኮፒ
8ኛ. ሰርዲኖን መጽሐፍ መደብር/ Sardinon Book Store  100ኮፒ
9.በላይ መጻሕፍት መደብር 50ኮፒ
10.ጌታቸው መጻሕፍት መደብር 100ኮፒ
11.እንሆ መጻሕፍት መደብር 50ኮፒ
12. ኢትዮፋጎስ መጽሐፍ ማእከል- EthioFagos Book Center 100ኮፒ
13.ተዋሕዶ መጻሕፍት መደብር 500ኮፒ
14.ጋሽ ይልማ ፮ኪሎ 100ኮፒ
15.ሀዋሳ ማዕከል 100ኮፒ
16.ሱመያ መርካቶ 200ኮፒ
17.ማኅደር አርጋኖን መቐለ 50ኮፒ
18.ዮሴፍ መጻሕፍት መደብር መቐለ 100ኮፒ
19.ጃፋር 4ኪሎ ቅርንጫፍ 500ኮፒ
20.ባኮስ መጽሐፍ መደብር 200ኮፒ
21.ሽታው መጽ መደብር 50ኮፒ
22.ጅማ ሰንበት ትቤት 36ኮፒ
23.አሪፍ መጻሕፍት መደብር 200ኮፒ
24.ኤዞፕ መጻሕፍት መደብር ፕያሳ 100ኮፒ
25.ተኽሌ መጻሕፍት መደብር  ፕያሳ 100ኮፒ
26.ደብረ አሚን ሰ/ቤት 50ኮፒ



ዋና አከፋፋይ አርጋኖን መጻሕፍት መደብር Areganon Book Store

አድራሻ
#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_4ኪሎ

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

28 Oct, 13:52


✞ ስንክሳር ጥቅምት 19 ✞

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞✞✞

✞✞✞ ጥቅምት 19 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ✞✞✞

+" ቅዱስ ይምርሐነ ክርስቶስ ንጉሥ "+

✞✞✞ የሰው ልጅ 'ንጉሥ' ተብሎ 'ቅዱስ' መባል ግን ምን ይደንቅ?! ይህ ታላቅ ኢትዮዽያዊ መሪ ንጉሥ ሲሆን: እንደ ደናግል ድንግል: እንደ ባሕታውያን ገዳማዊ: እንደ ቀስውስት ካህን: እንደ ሐዋርያት ሰባኪ ሆኖ መገኘቱ ይደንቃል::

+የሚያሳዝነው ይህንን እንቁ ንጉሣችን ብዙ ኢትዮዽያውያን መዘንጋታችን ብቻ ነው:: የላስታ አካባቢ እጅግ የታደለችና የተቀደሰች ናት:: እንደ ሌሎቹ የሃገራችን ክፍሎች ሁሉ እሷም መካነ ቅዱሳን ናትና::

+ቅዱስ ይምርሐ የዘር ሐረጉ ከዛግዌ ነገሥታት ሥር ሲሆን አባቱ ግርማ ስዩም ይባላል:: ይኸውም በመጀመሪያው ሺህ ዓመት (Millenium) መጠናቀቂያ ላይ ነግሶ የነበረ ነው:: ዣን ስዩም
(የላሊበላ አባት): ጠጠውድም (ንጉሡ) እና ግርማ ስዩም ወንድማማቾች ናቸው::

+ቅዱሱ ሲወለድ አባቱ በሕይወት አልነበረም:: እናቱና የወቅቱ አባቶች "ይምርሐነ ክርስቶስ-ክርስቶስ ይምራን" አሉት:: ገና ከሕጻንነቱ መንፈስ ቅዱስ አድሮበታልና ረቡዕና ዓርብ ቀን እስከ 9 ሰዓት ድረስ የእናቱን ጡት አይቀምስም ነበር:: እናቱ ግን ባለመረዳት ትጨነቅ ነበር::

+የወቅቱ ንጉሥ ጠጠውድም "ከእኔ ቀጥሎ የሚነግሠውን ባወኩት" እያለ ሲመኝ በሕልሙ "ሕጻኑ ይምርሐ ነው" የሚል በማየቱ ሕጻኑን አስመጣው:: ከደም ግባቱ የተነሳም ቅንዓት አድሮበት አማካሪዎቹን "ምን ላድርገው?" አላቸው::

+እነርሱም "ብትገድለው እግዚአብሔር በደሙ ይጠይቅሃል:: ግን እንዳይወርስብህ ከፈለክ እረኛ አድርገው" አሉት:: (የዋሃን! ቅዱስ ዳዊት ከእረኝነት መጠራቱን ዘንግተውታል) ከ7 ቀናት በኋላ ግን መጥተው "ንጉሥ ሆይ! ፈጣሪ ካለ የሚቀር ነገር የለምና በቃ ዝም ብለህ ግደለው" አሉት::

+በዚያች ሰዓት ቅዱስ ሩፋኤል ከሰማይ ወርዶ እናቱን "ይምርሐን ስጭኝ" አላት:: እናት ናትና ጨነቃት:: መልአኩ ግን እንደሚጠብቀው ቃል ገብቶላት ከላስታ ነጥቆ ኢየሩሳሌም አደረሰው::

+ቅዱስ ይምርሐነ ክርስቶስም ለዓመታት ተምሮ ዲቁናን ተቀበለ:: በኢየሩሳሌም አካባቢም በጾምና በጸሎት ተወስኖ ፈጣሪውን እያገለገለና ወንጌልን እየሰበከ የወጣትነት እድሜውን ገፋ::

+አንድ ቀን ግን መድኃኒታችን ተገልጦ "ወዳጄ ይምርሐ! ሚስት አግብተሀ: ቅስና ተቀብለህ አገልግለኝ" አለው:: ቅዱሱ ይህንን ሲሰማ አዝኖ "ጌታየ! የእኔስ ፈቃዴ በድንግልና አገለግልህ ዘንድ ነው" አለው:: ጌታችንም "ግዴለህም! ሁሉም አይቀርብህም" ብሎ አንዲት ሕዝባ የምትባል ደግ እሥራኤላዊት ጠቆመው::

+ቅዱስ ይምርሐም ቅድስት ሕዝባን በተክሊል አግብቶ: ቅስናን ተቀበለ:: ግሩም የሚያሰኘው ግን 2ቱ ቅዱሳን ከ40 ዓመታት በላይ በትዳርም: በድንግልናም መኖራቸው ነው:: "ለሚያምን ሁሉ ይቻላል" ይል የለ ቅዱስ መጽሐፍ!

+ቅዱሳኑ ወዲያው ለአገልግሎት ወደ ግብጽ ወረዱ:: በዚያ ለጥቂት ዓመታት እንደቆዩ ቅዱስ ይምርሐነ ክርስቶስ ወደ ኢትይዽያ መመለስ ፈለገ:: አንድ ቀን ሕዝቡ ተሰብስበው ጸሎተ ኪዳንን ሲመራ "እግዚአብሔር አብ ወሐቤ ብርሃን-ብርሃንን የምትሰጥ እግዚአብሔር አብ" ከሚል ሲደርስ ወደ ሰማይጮኸ::

+ከሰማይም "አቤት ልጄ ሆይ!" የሚል መልስ መጣለት:: ይምርሐም "ምነው ጌታየ በሰው ሃገር ረሳኸኝ?" ቢለው "አልረሳውህም:: ይልቁኑ ሊገድልህ የሚፈልግህ ንጉሥ ሙቷልና ሒደህ ንገሥ" ሲል አዘዘው::

+ቅዱሱም ሚስቱን ሕዝባን ይዞ ላስታ ሲደርስ ሕዝቡ በዕልልታ ተቀብሎ ወዲያው አነገሠው:: በዚያም ለ15 ዓመታት ቅዱስ ሩፋኤል እየተራዳው: ሕብስትና ጽዋዕ ከሰማይ እየወረደለት ቀድሷል:: ሃገሪቱንም መርቷል::

+አንድ ቀን ግን ክፉ መካሪዎች "ተጨማሪ ሚስት አግባ" ቢሉት ተቆጣቸው:: በኋላ ደግሞ 'ለምን ተቆጣሁ' ብሎ አዘነ:: ስለዚህም ሃሳቡ ሰማያዊው ስጦታ ቀረበት::

+እያለቀሰ ጌታን ቢማጸን ጌታችን "ስላሰብከው ክፉ ሃሳብ (ለምን ተቆጣሁ ማለቱ ወደ ምክራቸው ማዘንበሉን ያሳይነበርና) ይቅር ብየሃለሁ:: ነገር ግን እኔ ወደ ማሳይህ ቦታ ካልሔድክ 2ኛ አይወርድልህም" አለው::

+ቅዱሱ ለጊዜው ትንሽ ቢከራከርም "እሺ" ብሎ በቅዱስ ሩፋኤል መሪነት ዛሬ ወደ ምናውቀው አካባቢው ሔደ:: በዚያም አራዊትን በጸሎቱ አድክሞ: መሠሪዎችን አስተምሮ: ሕዝቡንም አሳምኖ አጠመቃቸው::

+ጌታም "ከኢየሩሳሌም በደመና እየጫንክ በዚህ ባሕር ላይ ቤቴን ሥራልኝ" አለው:: ቅዱስ ይምርሐም መስከረም 13 ቀን (በበዓለ ባስልዮስ) ጀምሮ ሰኔ 20 (በበዓለ ሕንጸታ) ፈጸመና ታቦተ ገብርኤልን ሰኔ 21 ቀን ቀደሰው::

+ቅዱስ ይምርሐነ ክርስቶስ ግን በዚያ ቦታ እየቀደሰ ለ25 ዓመታት ሃገሪቱን አስተዳደረ:: አንድ ጊዜ ቅዱስ ሩፋኤል ለንጉሡ ከሰማይ ሕብስትና ጽዋዕ ሲያወርድለት 1 ባሕታዊ አይቶ "ለምን?" ብሎ ተቆጣ:: መልአኩ ግን የንጉሡን ክብር ነግሮ "እየዞርክ ስበክ" ብሎታል::

+በዚያ ባሕታዊ ስብከትም ከመላው ዓለም ብዙ ሺህ ሰወች መጥተው ቅዱስ ይምርሐን "ቀድሰህ አቁርበን?" ብለውለምነውታል:: ቅዱሱም ሲያቆርባቸው በመምሸቱ ጸሐይን አቁሟታል::

+ቅዱስ ይምርሐነ ክርስቶስ እንዲህ ባለ ጣዕመ ሕይወት ኑሮ: ለ40 ዓመታት ሃገራችንን አስተዳድሮ ጥቅምት 19 ቀን ዐርፎ በዚያው ሥፍራ ተቀብሯል:: ጌታችንም "መታሰቢያህን ያደረገውን: ደጅህን የረገጠውን እምርልሃለሁ" ብሎታል::

✞✞✞ አምላከ ይምርሐ ደጉን መሪ: አምላከ ዮሐንስ ቸሩን አስተማሪ ያምጣልን:: ከበረከታቸውም ይክፈለን::

ጥቅምት 19 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ ይምርሐነ ክርስቶስ (ጻድቅ ንጉሠ ኢትዮዽያ)
2.ቅዱስ ዮሐንስ ዘጸይለም
3.አባ ስምኦን ገዳማዊ
4.ቅዱሳን በርተሎሜዎስና ሚስቱ (ሰማዕታት)
5.አበው ኤዺስ ቆዾሳት (ሳምሳጢን ያወገዙ)
6.ጻድቃን እለ መጥራ

++"+ አቤቱ በኃይልህ ንጉሥ ደስ ይለዋል::በማዳንህ እጅግ ሐሴትን ያደርጋል:: የልቡን ፈቃድ ሰጠኸው::የከንፈሩንም ልመና አልከለከልኸውም:: በበጐ በረከት ደርሰህለታልና::ከከበረ ዕንቁ የሆነ ዘውድን በራሱላይ አኖርህ:: ሕይወትን ለመነህ ሰጠኸውም::ለረጅም ዘመን ለዘለዓለሙ:: በማዳንህ ክብሩ ታላቅ ነው:: +"+ (መዝ. 20:1-5)

✍️† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †✍️
               🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

27 Oct, 14:40


✞ ስንክሳር ጥቅምት 18 ✞

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡

✞ ጥቅምት 18 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ✞

🙏" ቅዱስ ቴዎፍሎስ ሊቅ "🙏

✞ በምድረ ግብጽ ከተነሱና ለቤተ ክርስቲያን አብዝተው ከደከሙ አባቶች አንዱ አባ ቴዎፍሎስ ነው:: የተወለደው በ4ኛው መቶ ክ/ዘመን መጀመሪያ አካባቢ ሲሆን ቴዎፍሎስ (ታኦፊላ) በመባል ይታወቃል:: ገና ልጅ እያለ ቴዎዶስዮስ ከሚባል ባልንጀራው ጋ በተመሳሳይ ሌሊት ተመሳሳይ ሕልምን ያያሉ::

2ቱ ሕጻናት ያዩት እንጨት ሲለቅሙ ነበር:: ሕልምን የሚተረጉመው ሰውም ቴዎዶስዮስን "ትነግሣለህ" ሲለው ቴዎፍሎስን "ፓትርያርክ ትሆናለህ" አለው:: ለጊዜው አልመሰላቸውም::

ከዚያም ወደ ት/ቤት ገብተው: መጻሕፍትን ተምረው ቴዎዶስዮስ ወደ ንጉሡ ከተማ ቁስጥንጥንያ ሲሕድ ቅዱስ ቴዎፍሎስ ግን የታላቁ ሊቅ አባ አትናቴዎስ ደቀ መዝሙር ሆነ:: በዚያም ከቅዱሱ እየተማረ: እያገለገለ ዘመናት አለፉ::

ቅዱስ አትናቴዎስ ካረፈ በኋላም ለ2 ፓትርያርኮች ረዳት ሆኖ ተመርጧል:: በመጨረሻ ግን ሕልም ተርጉዋሚው ያለው አልቀረምና ቴዎዶስዮስ 'ታላቁ' ተብሎ በቁስጥንጥንያ ላይ ሲነገሥ ቅዱስ ቴዎፍሎስም ፓትርያርክ (ሊቀ ዻዻሳት) ተብሎ በመንበረ ማርቆስ ላይ ተቀመጠ::

በ384 ዓ/ም የእስክንድርያ 23ኛው ሊቀ ዻዻሳት ከሆነ በኋላ የመጀመሪያ ሥራው በዘመኑ ገነው የነበሩ መናፍቃንን መዋጋት ነበር:: ለዚህም ይረዳው ዘንድ የእህቱ ልጅ የሆነውን ቅዱስ ቄርሎስን ወስዶ አስተማረው:: 2ቱ አባቶች እየተጋገዙም ቤተ ክርስቲያንን ከአራዊት (መናፍቃን) ጠበቁ:: ዛሬ በሃይማኖተ አበው የምናውቀውን ጨምሮ ቅዱሱ በርካታ ድርሰቶችንም ደረሰ::

ቅዱስ ቴዎፍሎስን ለየት ከሚያደርጉት ነገሮች መካከል ጥቂቶቹን እንመልከት:-

1.ቅዱሱ በዘመኑ ከመንበረ ዽዽስናው በር ቁጭ ብሎ ይተክዝ ነበርና አንዲት ባለ ጸጋ ሴት መጥታ "አባቴ! ምን ያስተክዝሃል?" ስትል ጠየቀችው::

ሊቁም "ልጄ! እዚህ የቆምንበት ቦታ ውስጥ ወርቅ ተቀብሮ ሳለ ነዳያን ጦማቸውን ያድራሉ:: አባቴ አትናቴዎስ እንዳዘነ አለፈ:: እኔም ያው ማለፌ ነው" አላት:: ባዕለ ጸጋዋም "አባ አንተ ጸሎት: እኔ ጉልበትና ሃብት ሁነን እናውጣው" አለችው::

"እሺ" ብሏት ሱባኤ ገባና ከመሬት በታች 3 ጋን ሙሉ ወርቅ ተገኝቶ ደስ አላቸው:: ግን በላያቸው ላይ ተመሣሣይ "ቴዳ: ቴዳ: ቴዳ" የሚል ጽሑፍ ነበረውና ማን ይፍታው:: በዚህ ጊዜ ቅዱስ ቴዎፍሎስ ወደ እመቤታችን አመልክቶ ምሥጢር ተገለጠለትና ሲተረጉመው ማሕተሞቹ ተፈቱ::

ሲተረጐምም ቴዳ 1 "ክርስቶስ" ማለት ሆነ:: ይሔም ለነዳያን ተበተነ:: ቴዳ 2 "ቴዎፍሎስ" ማለት ሆነ:: አብያተ ክርስቲያናት ታነጹበት:: ቴዳ 3 ደግሞ "ቴዎዶስዮስ" ሆነ:: 'የቄሣርን ለቄሣር' እንዲል 3ኛው ጋን የአቡነ ኪሮስ ወንድምና የገብረ ክርስቶስ መርዓዊ አባት ለሆነው ለደጉ ንጉሥ ቴዎዶስዮስ ተላከለት::

ንጉሡ ግን ከወርቁ ጥቂት ለበረከት ወስዶ ለአባ ቴዎፍሎስ መለሰለት:: አብያተ ጣዖቶችን እያፈረሰ አብያተ ክርስቲያናትን እንዲያንጽም ስልጣን ሰጠው:: ቅዱስ ቴዎፍሎስም በዚህ ገንዘብ በመቶ የሚቆጠሩ አብያተ ክርስቲያናትን እንዳነጸበት ይነገራል::

በተለይ ደግሞ የቅዱስ ሩፋኤልን ቤት በአሣ አንበሪ ጀርባ ላይ ያነጸው እርሱ ነው:: (ድርሳነ ሩፋኤል) የድንግል ማርያምን ሲያንጽም እመቤታችን ተገልጣለታለች::

የቅዱስ ዮሐንስ መጥምቁን አጽም አፍልሦ ከነቢዩ ኤልሳዕ ጋር ቤቱን ሲቀድስለትም ተአምራት ተደርገዋል:: የሠለስቱ ደቂቅን ቤተ ክርስቲያን አንጾ የቀደሰ ጊዜ ደግሞ ቅዱሳኑ ከሰማይ ወርደውለታል::

2.ቅዱስ ቴዎፍሎስ እመቤታችንን ይወዳት ነበርና ለ8 ጊዜ ያህል ተገልጣ አነጋግራዋለች:: "ደፋሩ አርበኛ" ስትል ጠርታ: ሙሉ ዜና ስደቷንና ሕይወቷን አጽፋዋለች:: (ተአምረ ማርይም)
3.ሕጻናትን ሲያጠምቅም ከብቃት የተነሳ የብርሃን መስቀል ይወርድለት ነበር:: ቅዱስ ቴዎፍሎስ በሊቀ ዽዽስና በቆየባቸው 28 ዓመታት እንዲህ ተመላልሶ በ412 ዓ/ም ዐርፎ ቅዱስ ቄርሎስ በመንበሩ ተተክቷል:: ነገር ግን አንዳንድ የዘመናችን 'ጸሐፊ ነን ባዮች' የመናፍቃንን መጻሕፍት እየገለበጡ ቅዱሱን ይሳደባሉና ብንጠነቀቅ እመክራለሁ::

🌿+" ቅዱስ ሮማኖስ ሰማዕት "+🌿

✞ ይህ ቅዱስ ሰማዕት ብዙ ጊዜ "ኃያሉ" እየተባለ ነው የሚጠራው:: በዘመነ ሰማዕታት ከራሱ አልፎ ብዙ ክርስቲያኖችን በድፍረት ያጸናቸው ነበር:: በወቅቱ በምድረ ግብጽ መከራው እጅግ ስለ በዛ ብዙዎቹ አልቀው: እኩሉም ተሰደው: አንዳንዶቹ ደግሞ መካዳቸውን ሲሰማ ቅዱሱ ለጸሎት ከተወሰነበት ቦታ ወጥቶ: ሕዝቡን ሰብስቦ መከራቸው::

"ወገኖቼ! ልቡናችንን በክርስቶስ ፍቅር ካጸናነው ሞት ቀላልና አስደሳች ነገር ነው" ብሎም አበረታታቸው:: ይህን የሰማ መኮንኑ ግን ተቆጥቶ አስጠራው:: በዓየር ላይ ዘቅዝቆም ኢ-ሰብአዊ በሆነ ጭካኔ ደሙ እስኪንጠፈጠፍ ድረስ አሰቃየው::

ይህ ሁሉ እየሆነበት ቅዱስ ሮማኖስ ልቡ በአምላኩ ፍቅር ተመስጦ ነበርና አንዳች አልመለሰም:: መኮንኑ ግን ገርሞት "እንዴት ይህ ሁሉ እየሆነብህ ዝም አልክ?" ቢለው የ3 ዓመት ሕጻን ጥራና ስለ እውነተኛው አምላክ ጠይቀው" አለው::

አንድ ሕጻን አስመጥቶ በአደባባይ ጠየቀው:: ሕጻኑም መለሰና "አዕምሮ የጐደለህ መኮንን ሆይ! አስተውል:: ከክርስቶስ በቀር ሌላ አምላክ የለም" ሲል ገሰጸው:: መኮንኑ በቁጣ ሕጻኑን በዓየር ላይ አሰቅሎ አስገረፈው:: ሕጻኑ ሕጻኑ ደሙ ሲፈስ እናቱን "ውሃ አጠጪኝ?" አላት:: እርሷ ግን "ልጄ! እኔ ውሃ የለኝም:: ወደ ሕይወት ውሃ ክርስቶስ ሒድ" አለችው::

በዚያን ጊዜ መኮንኑ የሕጻኑን ራስና የቅዱስ ሮማኖስን ምላስ አስቆረጠ:: ቅዱሱ ግን መንፈሳዊ ልሳን ተሰጥቶት ፈጣሪውን አመሰገነው:: የሚያደርገውን ያጣው መኮንኑም በዚህ ዕለት ቅዱሱን ገድሎታል::
✞ አምላከ ቅዱሳን ጸጋውን ክብሩን አይንሳን:: የአባቶቻችንንም በረከት ያብዛልን::

ጥቅምት 18 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ ቴዎፍሎስ ሊቅ
2.ቅዱስ ሮማኖስ ሰማዕት
3.ቅዱስ ዮሐንስ ሰማዕት
4.ቅድስት አስማኒትና 7ቱ ልጆቿ

" ሞቱን በሚመስል ሞት ከእርሱ ጋር ከተባበርን: ትንሳኤውን በሚመስል ትንሳኤ ደግሞ ከእርሱ ጋር እንተባበራለን:: ከእንግዲህስ ወዲያ ለኃጢአት እንዳንገዛ የኃጢአት ሥጋ ይሻር ዘንድ አሮጌው ሰዋችን ከእርሱ ጋር እንደ ተሰቀለ እናውቃለን:: " (ሮሜ. 6:5)

✍️† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †✍️
               🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

26 Oct, 14:41


🌿 ስንክሳር ጥቅምት 17 🌿

" እንኩዋን ለቅዱስ "እስጢፋኖስ ሊቀ ዲያቆናት": ለቅዱስ "ፊልያስ" እና ለቅድስት "ሐና ነቢይት" ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ "

🙏+*" ቅዱስ እስጢፋኖስ ሊቀ ዲያቆናት "*+🙏

በሕገ ወንጌል (ክርስትና) የመጀመሪያው ሊቀ ዲያቆናትና ቀዳሚው ሰማዕት ይህ ቅዱስ ነው:: ቅዱሱ በመጀመሪያው መቶ ክ/ዘመን አስገራሚ ማንነት ከነበራቸው እሥራኤላውያን አንዱ ነበር:: ይህስ እንደ ምን ነው ቢሉ:-

የቅዱስ እስጢፋኖስ ወላጆቹ ስምዖንና ማርያም ይባላሉ:: (ሌሎች ናቸው የሚሉም አሉ) ገና ከልጅነቱ ቁም ነገር ወዳድ የነበረው ቅዱስ በሥርዓተ ኦሪት አድጐ እድሜው ሲደርስ ወደ ት/ቤት ገባ:: የወቅቱ ታላቅ መምሕር ገማልያል ይባል ነበር:: ይህ ሰው በሐዋርያት ሥራ ምዕራፍ 5:33 ላይ ተጠቅሷል::

በትውፊት ትምሕርት ደግሞ ይህ ደግ (ትልቅ) ሰው በርካታ ቅዱሳንን (እስጢፋኖስን: ዻውሎስን: ናትናኤልን: ኒቆዲሞስን . . .) አስተምሯል:: በጌታችን መዋዕለ ስብከት ጊዜም ከፈጣሪያችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ እየቀረበ ይጨዋወት ነበር:: በፍጻሜውም አምኗል::

ወደ ቀደመ ነገራችን እንመለስና ቅዱስ እስጢፋኖስ ከዚህ ምሑር ዘንድ ተምሮ: ኦሪቱን ነቢያቱን ጠንቅቆ ወጣ:: ወቅቱ አስቸጋሪና ለኃጢአት ሕይወት የተመቸ ቢሆንም ቅዱሱ ግን የመሲህን መምጣት በጸሎትና በተስፋ ይጠባበቅ ነበር::

በወቅቱ ደግሞ መጥምቁ ቅዱስ ዮሐንስ የንስሃ ጥምቀትን እየሰበከ መምጣቱን የተመለከተ ቅዱስ እስጢፋኖስ ነገሩን መረመረ:: ከእግዚአብሔር ሆኖ ቢያገኘው የመጥምቁ ዮሐንስ ደቀ መዝሙር ሆነ:: ለ6 ወራትም በትጋት ቅዱስ ዮሐንስን አገለገለ::

ለ6 ወራት ከቅዱስ ዮሐንስ ዘንድ ከተማረ በሁዋላ ለስም አጠራሩ ስግደት ይድረሰውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተጠመቀ::
በወቅቱ የተደረገውን ታላቅ ተአምር ልብ ያለው ቅዱስ እስጢፋኖስ መምሕሩን ቅዱስ ዮሐንስን እንዲያስረዳው ጠየቀው::

"ከእኔ ይልቅ ከፈጣሪው አንደበት ይስማው" በሚል ላከው:: ቅዱሱም ከጌታ ዘንድ ሔዶ: እጅ ነስቶ ተማረ:: (ሉቃ. 7:18) በዚያውም የጌታ ደቀ መዝሙር ሆኖ ቀረ:: ጌታም ከ72ቱ አርድእት አንዱ አድርጐት ለአገልግሎት ላከው:: አጋንንትም ተገዙለት:: (ሉቃ. 10:17)

ቅዱስ እስጢፋኖስ ጌታችን መድኃኔ ዓለም ከዋለበት እየዋለ: ካደረበት እያደረ ወንጌልን ተማረ:: ምሥጢር አስተረጐመ:: ጌታ በፈቃዱ ስለ እኛ ሙቶ ከተነሳ በሁዋላ ሲያርግ ደቀ መዛሙርቱን በአንብሮ እድ ባርኩዋል::

በዚህ ጊዜም ቅዱሱ እንደ ወንድሞቹ ሐዋርያት ቅስናን (ዽዽስናን) ተሹሟል:: በበዓለ ሃምሳም መንፈስ ቅዱስ በወረደ ጊዜ ከ72ቱ አርድእት የእርሱን ያህል ልሳን የበዛለት: ምሥጢርም የተገለጠለት የለም:: በፍጹም ድፍረትም ወንጌልን ይሰብክ ገባ::

በመጀመሪያይቱ ዘመን ቤተ ክርስቲያን ከማዕድ ሥርዓት ጋር በተያያዘ ፈተና ሲመጣ በመንፈስ ቅዱስ ምርጫ 7 ዲያቆናት ሲመረጡ አንዱ እርሱ ነበር:: አልፎም የ6ቱ ዲያቆናት አለቃ እና የ8ሺው ማሕበር መሪ (አስተዳዳሪ) ሆኗል::

8ሺ ሰውን ከአጋንንት ፈተና መጠበቅ ምን ያህል ከባድ እንደ ሆነ ለማወቅ አባቶቻችንን መጠየቅ ነው:: አንድን ሰው ተቆጣጥሮ ለድኅነት ማብቃት እንኩዋ እጅግ ፈተና ነው:: መጽሐፍ እንደሚል ግን "መንፈስ ቅዱስ የሞላበት: ማሕደረ እግዚአብሔር" ነውና ለእርሱ ተቻለው:: (ሐዋ. 6:5)

አንዳንዶቻችን ቅዱስ እስጢፋኖስ "ሊቀ ዲያቆናት" ሲባል እንደ ዘመኑ ይመስለን ይሆናል:: እርሱ በመጀመሪያ ሐዋርያና ካህን ነው:: ዲቁናው ለእርሱ "በራት ላይ ዳረጐት" ነው እንጂ እንዲሁ ዲያቆን ብቻ አይደለም::

ቅዱስ እስጢፋኖስ ከጌታ ዕርገት በሁዋላ ለ 1 ዓመት ያህል 8ሺውን ማሕበር እየመራ: ወንጌልን እየሰበከ ቢጋደል ኦሪት "እጠፋ እጠፋ": ወንጌል ደግሞ "እሰፋ እሰፋ" አለች:: በዚህ ጊዜ "ክርስትናን ለማጥፋት መፍትሔው ቅዱስ እስጢፋኖስን መግደል ነው" ብለው አይሁድ በማመናቸው ሊገልድሉት አስበውም አልቀሩ ገደሉት::

እርሱ ግን ፊቱ እንደ እግዚአብሔር መልአክ እያበራ ፈጣሪውን በብዙ ነገር መሰለው:: በመጨረሻውም ስለ እነሱ ምሕረትን እየለመነ በድንጋይ ወገሩት:: ደቀ መዛሙርቱም ታላቅ ለቅሶን እያለቀሱ ቀበሩት::

ይህች ዕለት ለቅዱስ እስጢፋኖስ በዓለ ሲመቱ ናት:: ቅዱሱ መጽሐፍ እንደሚል "ምሉዓ ጸጋ ወሞገስ-ሞገስና ጸጋ የሞላለት" (ሐዋ. 6:5, ቅዳሴ ማርያም) ነውና የ6ቱ ዲያቆናት አለቃና የ8ሺው ማሕበር መሪ ሆኖ ተመርጦ እንደሚገባ አገልግሏል:: በሰማይ ባለችው መቅደስም የሚያገለግለው በዚሁ ማዕረጉ ነው::

👉+"+ ቅዱስ ፊልያስ ሰማዕት +"+👈

ሰማዕቱ የነበረበት ዘመን 3ኛው መቶ ክ/ዘ (ዘመነ ሰማዕታት) ሲሆን ቀምስ ለምትባል የግብጽ አውራጃም ዻዻስ ነበር:: ቅዱሱ እጅግ ጻድቅ በዚያውም ላይ ክቡርና ተወዳጅ ሰው ነበር:: የመከራው ዘመን ሲመጣ በቃሉ ያስተማራቸውን እንደ በጐ እረኝነቱ በተግባር ይገልጠው ዘንድ ወደ መኮንኑ ሔደ::

ሕዝቡ በአንድነት ተሰብስበው ሳለ መኮንኑ ቁልቁልያኖስ ቅዱስ ፊልያስን 4 ጥያቄዎችን ጠየቀው:: ምላሾቹ ለእኛ ሕይወትነት ያላቸው ናቸውና እንመልከታቸው::

1."የእናንተ እግዚአብሔር ምን ዓይነት መስዋዕትን ይሻል?" ቢለው "ልበ ትሑተ: ወመንፈሰ የዋሃ: ወነገረ ሕልወ: ወኩነኔ ጽድቅ: ዘከመዝ መስዋዕት ያሠምሮ ለእግዚአብሔር-እግዚአብሔርን ትሑት ልቦና: የዋህ ሰብእና: የቀና ፍርድና ቁም ነገር ደስ ያሰኘዋል" ሲል መለሰለት::

2."የምትወዳቸው ሚስትና ልጆች የሉህም?" ሲለው ደግሞ "እምኩሉ የአቢ ፍቅረ እግዚአብሔር - ከሁሉ የእግዚአብሔር ፍቅር ይበልጣል" አለው::

3."ለነፍስህ ትጋደላለህ ወይስ ለሥጋህ?" ቢለው "ለ2ቱም እጋደላለሁ:: አምላክ በአንድነት ፈጥሯቸዋልና:: በትንሳኤ ዘጉባኤም ይዋሐዳሉና" ብሎታል::

4."አምላካችሁ የሠራው ምን በጐ ነገር አለ?" ብሎትም ነበር:: ቅዱስ ፊልያስ መልሶ: "አስቀድሞ ፍጥረታትን በጥንተ ተፈጥሮ ፈጠረ:: በሁዋላም በሐዲስ ተፈጥሮ ያከብረን ዘንድ ወርዶ ሞተልን: ተነሣ: ዐረገ" ቢለው መኮንኑ "እንዴት አምላክ ሞተ ትላለህ!" ብሎ ተቆጣ:: ቅዱሱም "አዎ! በለበሰው ሥጋ ስለ እኛ ሙቷል" ብሎ እቅጩን ነገረው::

ወዲያውም "እስከ አሁን የታገስኩህ በዘመድ የከበርክ ስለሆንክ ነው" ቢለው ቅዱሱ መልሶ "ክብሬ ክርስቶስ ነው:: መልካምን ካሰብክልኝ ቶሎ ግደለኝ" አለው:: በዚያን ጊዜ የሃገሩ ሰዎች "አትሙትብን! እባክህን ለመኮንኑ ታዘዘው?" ሲሉ ለመኑት::
=>ጥቅምት 17 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ እስጢፋኖስ ሊቀ ዲያቆናት (ወቀዳሜ ሰማዕት)
2.ቅዱስ ፊልያስ ሰማዕት
3.ቅድስት ሐና ነቢይት
4.ታላቁ ሊቅ ቅዱስ ጐርጐርዮስ ዘኑሲስ
5.የደብረ ሊባኖስ ሰማዕታት (ካቶሊካውያን የገደሏቸው)
6.ቅዱሳን ሔራን ሰማዕታት
7.አባ ዲዮስቆሮስ ካልዕ

=>ወርኀዊ በዓላት
1.ቅዱስ ያዕቆብ ሐዋርያ (ወልደ ዘብዴዎስ)
2.ቅዱሳን አበው መክሲሞስና ዱማቴዎስ
3.አባ ገሪማ ዘመደራ
4.አባ ዸላሞን ፈላሢ
5.አባ ለትጹን የዋህ
6.ቅዱስ ኤዺፋንዮስ ሊቅ (ዘደሴተ ቆዽሮስ)

✍️† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †✍️
               🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

26 Oct, 06:04


#አባቶቻችንን_እንወቅ!

#መጋቤ_ምሥጢር_ዶ/ር_አባ_ኅሩይ_ኤርምያስ

"አዲስ አበባ ካፈራቻቸው የቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት አንዱ። ከዚህ ተነሥቶ ጎጃም ጉባኤ ቤት ገብቶ፣ ከዚያ አስመስክሮ እቲሳ ላይ ጉባኤ ተክሎ፣ እንደገና በቤተ ክህነት አገልግሎ፣ በተጓዳኝ ዘመናዊ ትምህርት እስከ ዶክትሬት ተምሮ፣ በዚህ ሁሉ መካከል በርካታ መጻሕፍትን በማዘጋጀትና በመተርጎም የትሩፋት ሥራ (በነጻ) መሥራት ደስ አይልም? አያኮራም? መነኮሳትን በጅምላ እንዳንፈርጅ ምክንያት አይሆንም? ተሸሽጎ በሥራው ብቻ የሚናገር ሰው ምስጉን ነው። አንድም ኅሩይ ነው!"(#ደብተራ_በአማን)

ትልቅ ሰው ላስተዋውቃችሁ።
ያልታደልከው የያኔው ትውልድ በጋሻው ደሳለኝን የቤተክርስቲያን ትምህርት አዋቂ አድርገህ የተከተልክ ሕዝብ ሆይ እባክህ አባቶችህን እወቅ!
የግዕዝ ተነሽ ወዳቂ የማያውቀው ሁሉ አይንዳህ። አይጎትትህ። ለማንኛውም ትልቅ ሰው ላስተዋውቃችሁ። አባ ኅሩይ ኤርምያስ (ዶ/ር) በተለይ በትርጉም ሥራቸው በመጽሐፈ ምስጢር መጽሐፍ ይታወቃሉ። ሙሉ ስማቸው መጋቤ ምሥጢር ዶ/ር አባ ኅሩይ ኤርምያስ የቅኔና የትርጓሜ መጻሕፍት መምህር ፣ ዜማና ቅዳሴ ዐዋቂ ፣ አገልግሎታቸውን የጀመሩት በሰሜን ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት ውስጥ በሚገኘው የአቡነ ተክል ሃይማኖት የትውልድ ቦታ በሆነው ጥንታዊው የእቲሳ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም ቡልጋ የቅኔ መምህር በመሆን ነው።

ከ1990 - 2003 ድረስ በአዲስ አበባ በወይብላ ቅድስት ማርያም፣ በላፍቶ ቅዱስ ሚካኤል እና በቅዱስ ቂርቆስ አብያተ ክርስቲያናት በዋና ጸሐፊነትና ልዩ ልዩ የአስተዳደር እርከን አገልግለዋል። ይሁን እንጂ ለመንፈሳዊ አገልግሎት ቅድሚያ የሚሰጡ በመሆናቸው በአጽዋማትና በበዓላት ቅኔ በመቀኘት፣ ማኅሌት በመቆም፣ ትምህርተ ወንጌል በመስጠት፣ በተለይ በጾመ ፍልሰታ ጊዜ ውዳሴ ማርያም፣ ቅዳሴ ማርያም፣ ጸሎተ ሃይማኖትና ወንጌል በመተርጎም ሰፊ አገልግሎት እንደሰጡ ባገለገሉባቸው ደብር የሚገኙ ካህናትና መምህራን ይመሰክሩላቸዋል።

በኤክስቴንሽን የቲኦሎጂ ትምህርታቸውን በመከታተል የባችለር ዲግሪያቸውን በ1997 ከቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ያገኙ (የማዕረግ ተመራቂ ናቸው) ሲሆን የሁለተኛ እና ሦስተኛ ዲግሪያቸውን በኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ከጀርመን የሐምቡርግ ዩኒቨርስቲ ይዘዋል።

ከ2005 እስከ 2010 ለ5 ዐመት የምዕራብ፣ ምሥራቅና ደቡብ አውሮፓ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ ሆነው አገልግለዋል። አሁንም እዚያው ጀርመን የካስል መድኃኔዓለምንና የሐምቡርግ ኪዳነ ምሕረትን አብያተ ክርስቲያናት በማስተዳደር ላይ ሲሆኑ የምርምር ሥራቸውን ጎን ለጎን በማካሄድ ላይ ይገኛሉ። በእቲሳ እያሉ እንደጻፏቸው ከሚነገሩላቸው ከ15 ጊዜ በላይ ተደጋግመው ከታተሙት ከመዝገበ ታሪክ ቁጥር 1 እና 2 ጀምሮ እስካሁን ከ18 በላይ መጻሕፍትንና በርካታ የምርምር ሥራዎችን አሳትመዋል።

በመጽሔት፣ በጋዜጣና በኢንተርኔት ገጾች የወጡ በርካታ ጽሑፎችም አሏቸው። የኢትዮጵያን ብርቅዬ የሥነ ጽሑፍ ውጤቶች በእንግሊዝኛ እና በጀርመንኛ በመተርጎም የኢትዮጵያን ታሪክና ባህል በማስተዋወቅ ጉልህ አስተዋጽኦ በማበርከትም ላይ ናቸው።

ያዘጋጁት መጻሕፍት እና የምርምር ሥራዎች መካከል
1)መዝገበ ታሪክ ቁጥር 1
2)መዝገበ ታሪክ ቁጥር 2
3)መልካም ዜጋ ማነው?
4)ገድለ ቂርቆስ - ትርጉም
5)ገድለ ፋሲለደስ - ትርጉም
6)ገድለ አቡነ ቀውስጦስ - ትርጉም
7)ገድለ አቡነ ታዴዎስ - ትርጉም
8)ገድለ አቡነ አፍጼ - ትርጉም
9)መጻሕፍትን መርምሩ
10)መርኆ ምሥጢር
11)መጽሐፈ ምሥጢር ዘአባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ- ትርጉም
12)ቅዳሴ ወቁርባን
13)ቅዱስ ላሊበላ - መንፈሳዊ ቲአትር
14)ቅድስት አርሴማ - መንፈሳዊ ቲአትር
15)ኢትዮጵያ የወርቅ ሙዳይ - የግጥም መድበል
16)መዐዛ ቅዳሴ - ንባቡና ትርጓሜው - አንድምታ
17)ድርሳን ዘሄርማን - ንባቡና ትርጓሜው - አንድምታ
18)Review of Comparative classification of Geʿez verbs in the three traditional schools of the Ethiopian Orthodox Church by Muluken Andualem Siferew, published in Aethiopica: International Journal of Ethiopian and Eritrean Studies), 2017
19)The Issues of ʾAggabāb (Classic Gəʽəz Grammar) According to the tradition of Qǝne Schools, Digital Publication. Digital Library of Hamburg University, 302 Pages, 2019
20)Nägasi Gǝdäy, Ṭomarä Mäwati, ‘Letter of the dead’ Journal Review, Aethiopica- Uni. Hamburg, 2020.
21)The Amharic proverbs and their use in Gəʽəz Qəne, in press, AJHC, 2020
22)ʾAggabab according to the Qane School Tradition, Classical Geez (updated version of ‘The Issues …’), Gorgias Publisher, 384 pages, New York, 2021
23)The vita of St. Qawǝsṭos a fourteenth century Ethiopian saint and martyr (a new-critical edition, translation, and commentary), Digital publication, Digital Library of Uni. Hamburg, 2014 updated 2021.
24)Accounts Regarding Historical Events Exposed in the Hagiography of St. Qawǝsṭos, in Jaalhc, 2021
25)Bitu of Ethiopia and his Heresy, in Jaalch volume 11, Issue 1 (08-2022)
26)Christologie - nach dem Glauben und der Erklärung der Äthiopisch-Orthodoxen Tewahədo- Kirche, (German) Hamburg, 2022
27)The place of St. Mary in the Orthodox Christianity of Ethiopia (Journal article)
28)Certain peculiarities of the liturgical tradition of the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church in comparison with the Coptic Orthodox Church (Journal article)
29)The Book of Mystery of Abba Giyorgis of Sägla, annotated translation, Nägarit Publisher, May- 2024, Hamburg

ምንጭ ዊኪፒዲያ እና በዮሴፍ ፍስሀ መጠነኛ ማሻሻያ ጋር።
✍️† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †✍️
               🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

26 Oct, 03:15


✞ ስንክሳር ጥቅምት 16 ✞

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞✞✞

✞✞✞ እንኩዋን አደረሳችሁ ✞✞✞

+"+ 7ቱ ኪዳናት ወአባ ያቃቱ ሊቀ ዻዻሳት +"+

+"+ 7ቱ ኪዳናት +"+

=>"ተካየደ" ማለት "ተስማማ: ተማማለ" እንደ ማለት
ሲሆን "ኪዳን" በቁሙ "ውል: ስምምነት" እንደ ማለት
ነው:: ይኸውም እግዚአብሔር ከሰዎች ጋር: ሰዎችም
ከሰዎች ጋር የሚያደርጉት ሊሆን ይችላል:: ልዩነቱ
የእግዚአብሔር ቃል ኪዳን ቅዱስና የማይለወጥ መሆኑ ነው::

+እግዚአብሔር አምላክ ከሥነ ፍጥረት ጀምሮ በየጊዜው
ከብዙ ወዳጆቹ ጋር ኪዳንን አድርጉዋል:: ቅድስት ቤተ
ክርስቲያንም እነዚህን ኪዳናት ጥቅልል አድርጋ 7 እንደ
ሆኑ ታስተምራለች:: ስለዚህም ዛሬ ፈጣሪ ቢረዳን
እነዚሁን 7 ኪዳናት በጥቂቱ እንመለከታለን::
"ኪዳነ ተካየድኩ ምስለ ኅሩያንየ"
"ከመረጥኩዋቸው ጋር ቃል ኪዳንን አደረግሁ" (መዝ. 88:3)

(1) +"+ ኪዳነ አዳም +"+

=>አዳም ማለት የእግዚአብሔር ድንቅ ፍጥረት:
የፍጡራን አስተዳዳሪ: ነቢይ: ካህንና ንጉሥ ነው::
እግዚአብሔር ከአዳም ጋር አስቀድሞ በእጸ በለስ
አማካኝነት ቃል ኪዳን ነበራቸው:: ነገር ግን አባታችን
በዲያብሎስ ሴራ በመረታቱ ኪዳኑ ፈረሰ:: (ዘፍ. 3:1)

+አዳምና ሔዋን ተጸጽተው ቢያለቅሱ ግን አዲስ የኪዳን
ተስፋ: "ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለሁ" የሚል ኪዳንን
ተቀበሉ:: (ቀሌምንጦስ: ገላ. 4:4)

(2) +"+ ኪዳነ ኖኅ +"+

=>ከአዳም እስከ ኖኅ ድረስ ባሉት 10 ትውልድ ዓለም
በዓመፃ ተሞላች:: ቅዱስ ኖኅ በደግነቱ መርከብ ሠርቶ
ቤተሰቡን ሲያተርፍ ዓለም በማየ ሥራዌ ጠፋች::
ከመርከቡ ከወጣ በሁዋላ ኖኅና እግዚአብሔር በቀስተ
ደመና ምልክትነት ቃል ኪዳን ተጋቡ:: "ኢያማስና
ለምድር ዳግመ በማየ አይኅ" እንዲል:: (ዘፍ. 9:12)

(3) +"+ ኪዳነ መልከ ጼዴቅ +"+

=>መልከ ጼዴቅ የእግዚአብሔር ካህኑ: የክርስቶስም
ምሳሌው የሆነ የሳሌም ንጉሥ ነው:: በ15 ዓመቱ
መንኖ: አጽመ አዳምን ይዞ: በቀራንዮ በሕብስትና በወይን
ያስታኩት ነበር::

+እግዚአብሔር ለመልከ ጼዴቅ: በሐዲስ ኪዳን
ለምትሠራው ክህነትና ምሥጢረ ቁርባን ምሳሌ አድርጐ
በቃል ኪዳን አትሞታል:: በዚህም ተሰውሮ ይኖራል እንጂ
ሞትን እስካሁን አልቀመሰም:: ይህም ካህኑ መልከ
ጼዴቅ ከአብርሃም ጋር በተገናኙበት ጊዜ ተገልጧል:: (ዘፍ. 14:17, ዕብ. 7:1)

(4) +"+ ኪዳነ አብርሃም +"+

=>ቅዱስ አብርሃም የሕዝብና የአሕዛብ አባት: ሥርወ
ሃይማኖት: የጽድቅም አበጋዝ ነው:: ስለ ፍቅረ
እግዚአብሔር ሲል ከርስቱና ከወገኖቹ ተለይቶ በቅድስና
ኑሯልና እግዚአብሔር "በዘርሕ አሕዛብ ይባረካሉ"
አለው:: (ዘፍ. 12:1) የቃል ኪዳን ምልክትም ይሆነው
ዘንድ ግዝረትን ሰጠው:: (ዘፍ. 17:1-14)

(5) +"+ ኪዳነ ሙሴ +"+

=>ቅዱስ ሙሴ የነቢያት አለቃ: የእሥራኤል እረኛ:
የእግዚአብሔር ሰው እና ፍጹም ትሑት (የዋህ) ሰው
ነው:: በፈጣሪው ትዕዛዝ እሥራኤልን ከግብጽ ባርነት
አውጥቶ ለ40 ዘመናት በበርሃ ሲመራቸው
ከእግዚአብሔር የኪዳንን ጽላትና አሠርቱን ትዕዛዛት
ተቀብሏል:: (ዘጸ. 20:1, 31:18)

(6) +"+ ኪዳነ ዳዊት +"+

=>ቅዱስ ዳዊት ሥርወ ነገሥት: ጻድቅ: የዋህና ቡሩክ
የሆነ አባት ነው:: እግዚአብሔር ከእረኝነት ጠርቶ ንጉሥ
አድርጐ ሹሞት "ከሆድህ ፍሬ በዙፋንህ ላይ
አኖራለሁ" (መዝ. 131:11) ሲል ምሎለታል:: አክሎም
ሰፊ ቃል ኪዳን ሰጥቶ "አልዋሰሽህም" ብሎ ሲምልለት
እንመለከታለን:: (መዝ. 88:35)

(7) +"+ ኪዳነ ምሕረት +"+

=>በብሉይ ኪዳን የነበሩ 6ቱ ኪዳናት በዘመናቸው ክቡርና
ሕዝቡን ከመቅሰፍት ይታደጉ የነበሩ ቢሆንም ከሲዖል
ማዳን ግን አልቻሉም:: ስለዚህም አንድ ፍጹም ኪዳን
ያስፈልግ ነበር:: ይህን ፍጹም ኪዳን ይፈጽም ዘንድም
ከቅድስት ሥላሴ አንዱ ወልድ ከሰማያት ወርዶ በድንግል
ማርያም ማሕጸን አደረ::

+በፍጹም ተዋሕዶም በሕቱም ድንግልና ተወልዶ: አድጎ:
ተጠምቆ: አስተምሮ: ሙቶ: ተነስቶና ዐርጐ ሥጋ
ማርያምን በዘባነ ኪሩብ አስቀመጠው:: ኪዳነ ምሕረት
(የምሕረት ኪዳን) የምንለው አንዱ ታዲያ ይሔው ነው::

+የጌታችን መጸነሱ: መወለዱ: መሰደዱ: መጠመቁ:
ማስተማሩ: ሥጋውንና ደሙን መስጠቱ: መሰቀሉ:
መሞቱና መነሳቱ: ማረጉና መንፈስ ቅዱስን መላኩ
በአንድ ላይ ኪዳነ ምሕረት ይባላል:: ታዲያ ይህ ሁሉ
የተደረገው በሥጋ ማርያም ነውና የኪዳኑ ባለቤት
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት::

+የእርሷ ኪዳን የ6ቱን አበው ኪዳናት ፍጹም በማድረጉ
"የኪዳናት ማሕተም" ይባላል:: የድንግል ማርያም ኪዳኗ
ከሲዖልና ከገሃነም ሊታደገን አቅሙ አለውና::
መድኃኒታችን ክርስቶስ ለድንግል እናቱ ቃል ኪዳኑን
ያጸናላት ደግሞ ካረገ ከዓመታት በሁዋላ ጐልጐታ ላይ ነው::

+እመ ብርሃን በዚያ ቁማ ስለ ኃጥአን ስታለቅስ "እናቴ
ሆይ! በስምሽ ያመነውን: በቃል ኪዳንሽ የተማጸነውን
እምርልሻለሁ" ብሎ ደስ አሰኝቷታልና:: ይሔው በእመ
ብርሃን ምልጃና ቃል ኪዳን ምዕመናን ከመቅሰፍትና
ከገሃነመ እሳት ማምለጥ ከጀመሩ 2ሺ ዓመታት ሆኑ::
ዛሬም እኛ ኃጥአን ልጆቿ ከእሳት እንደምታድነን አምነን
በጥላዋ ሥር እንኖራለን::

*" ኢትዝክሪ ብነ አበሳነ: ኃጢአተነ: ወጌጋየነ፡፡
ማርያም እሙ ለእግዚእነ፡፡
በኪዳንኪ: ወበስደትኪ ድንግል ተማሕጸነ:: "*

"ድንግል ሆይ! ኃጢአታችን: አበሳችንና በደላችንን
አታስቢብን ዘንድ በስደትሽና በኪዳንሽ ተማጽነናል::"

=>ቸሩ ልጇ ከበረከተ ኪዳኗ አይለየን::

+"+ አባ ያቃቱ ሊቀ ዻዻሳት +"+

=>በምድረ ግብጽ ከተነሱና ለመንጋው ከራሩ አበው
ዻዻሳት አንዱ አባ ያቃቱ ናቸው:: አባ ያቃቱ መጻሕፍትን
የተማሩ: በገዳምም የኖሩ በመሆናቸው እንደ
ቀደምቶቻቸው ቤተ ክርስቲያኗን በቅን መርተዋል::

+ፓትርያርክ ሆነው ከተሾሙ በሁዋላ ብዙ ጭንቅ ያሳለፉ
ሲሆን እግዚአብሔር አቅሎላቸዋል:: ከማረፋቸው
በፊትም ከእርሳቸው ቀጥለው የሚሾሙትን በጸጋ
ተናግረዋል:: አባ ያቃቱ ለግብጽ 49ኛ ሊቀ ዻዻሳት
ናቸው::

=>በረከታቸው ይደርብን::

=>ጥቅምት 16 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን
በዓላት=
1.አባ ያቃቱ ሊቀ ዻዻሳት
2.ጻድቃን እለ ድርቂ
3.አባ ዻውሊ ገዳማዊ
4.አባ ማርቆስ መስተጋድል
5.አባ አሮን መስተጋድል

=>ወርኀዊ በዓላት
1.ኪዳነ ምሕረት (የሰባቱ ኪዳናት ማሕተም)
2.ቅድስት ኤልሳቤጥ (የመጥምቁ ዮሐንስ እናት)
3.ቅዱስ ገብረ ማርያም ጻድቅ ንጉሠ ኢትዮዽያ (የቅ/ላሊበላ ወንድም)
4.ቅዱስ አኖሬዎስ ንጉሥ ጻድቅ
5.አባ አቡናፍር ገዳማዊ
6.አባ ዳንኤል ጻድቅ
7.ቅዱስ አባ ዮሐንስ ጻድቅ (ወንጌሉ ዘወርቅ)

=>+"+ የምድር ባለጠጐች አሕዛብ በፊትሽ ይማለላሉ::
ለሐሴቦን ንጉሥ ልጅ ሁሉ ክብሯ ነው::
ልብሷ የወርቅ መጐናጸፊያ ነው::
በሁዋላዋ ደናግሉን ለንጉሥ ይወስዳሉ . . .
በአባቶችሽ ፈንታ ልጆች ተወለዱልሽ::
በምድርም ሁሉ ላይ ገዥዎች አድርገሽ ትሾሚያቸዋለሽ::
ለልጅ ልጅ ሁሉ ስምሽን ያሳስባሉ:: +"+ (መዝ.
44:12-17)


✍️† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †✍️
🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇

https://t.me/Sinksar
https://t.me/Sinksar
https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

25 Oct, 12:54


ሕገ ወጥ ነው!
🔴
ሐምሌ 26 ቀን 2015 ዓ/ም በቅዱስ ሲኖዶስ አስቸኳይ ምልዓተ ጉኤ የተወገዙት በትግራይ ክልል የሚገኙ አባቶች የራሳቸውን “ሲኖዶስ’’ ማቋቋማቸውን ገለጹ፡፡

በትግራይ ክልል የሚገኘው “መንበረ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን ከፍተኛ ቤተ ክህነት” ብሎ ራሱን የሚጠራው አካል ትላንት ባወጣው መግለጫ፣ “የትግራይ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሲኖዶስ” በሚል ማቋቋሙን አስታውቋል።

ሐምሌ 16 እና 23 ቀን 2015 ዓ.ም በክልል ትግራይ በማእከላዊ ዞን አክሱም ሀገረ ስብከት በርእሰ አድባራት ወገዳማት አክሱም ጽዮን ማርያም ገዳም ውስጥ የተፈጸመውን ሕገ ወጥ የቀኖና ቤተ ክርስቲያን ጥሰት አስመልከቶ ቅዱስ ሲኖዶስ አስቸኳይ ምልዓተ ጉባኤ በማድረግ በእኩይ ተግባሩ የተሳተፉ አባቶችን ከቤተ ክርስቲያን የተሰጣቸውን ከዲቁና ጀምሮ ያለው ሙሉ ሥልጣነ ክህነት በመሻር አውግዞ መለየቱ የሚታወስ ነው፡፡

ቅዱስ ሲኖዶስም በምልዓተ ጉባኤው በሕገ ወጥ ሹመቱ የተሳተፉ አባቶች በይቅርታ ወደ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እንዲመለሱ ጥሪ ያቀረበ ሲሆን ምእመናን ከዚህ ሕገ ወጥ ድርጊት በመቆጠብ አንድነታቸውን ሊያጠናክሩ እንደሚገባም ማሳሰባቸው ይታወቃል፡፡

ነገር ግን ይህንን ሕገ ወጥ ተግባር በመቀጠል ጥቅምት 13 ቀን 2017 ዓ.ም በሰጡት መግለጫ “የትግራይ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስትያን ሲኖዶስ” በሚል መቋቋሙን አስታውቀዋል።

አሁን ላይ በክልሉ ያሉ ምእመናን በዘረፈ ብዙ ችግሮች ውስጥ የተወጠሩበት እና ይህንን አጋጣሚ በመጠቀምም የመናፍቃን እንቅስቃሴ በርዳታ ስም የተጠናከረበት ወቅት ነው:: ነገር ግን ምእመናንን በሃይማኖታቸው እንዲጸኑና ከደረሰባቸው ችግር እንዲጽናኑ ማድረግ ሲገባ ይህ አካል ሌላ ችግር ይዞ መጥቷል ተብሏል::

MK fb Publishing

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

25 Oct, 04:09


🌹ስንክሳር ጥቅምት 15🌹

✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡

✞✞✞ እንኩዋን ለአባቶቻችን ቅዱሳን "12ቱ ሐዋርያት" እና ለቅዱስ "ቢላሞን ሰማዕት" ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞✞✞

🌿+"+ ቅዱሳን 12ቱ ሐዋርያት +"+🌿

በቅድስት ቤተ ክርስቲያን አስተምሕሮ ከእመቤታችን በቀር ከቅዱሳን ሐዋርያት የሚበልጥ አልተነሳም:: "ሐዋርያ" ማለት "ፍንው: ልዑክ: የተላከ: የጽድቅ መንገደኛ" እንደ ማለት ነው:: በምሥጢሩ ግን "ባለሟል" ብለው ሊቃውንቱ ተርጉመውታል::

ይህስ እንደምን ነው ቢሉ:-

¤የፍጥረታት ሁሉ ጌታ: የክብር ባለቤት መድኃኔ ዓለም ከድንግል ማርያም ተወልዶ: አድጐ: ተጠምቆ: ጾሞ: ከገዳመ ቆረንቶስ ሲመለስ ቀዳሚ ሥራው ያደረገው ደቀ መዛሙርቱን መጥራት ነበር::

ከተከተሉት የ5 ገበያ ሕዝብ መካከል "ወሐረየ እምሰብአ ዚአሁ አሠርተ ወክልኤተ ሐዋርያተ" እንዲል በመጀመሪያ 12ቱን ሐዋርያት መረጠ::

እሊህም:-
1.ዼጥሮስ የተባለ ስምኦን
2.እንድርያስ (ወንድሙ)
3.ያዕቆብ ወልደ ዘብዴዎስ
4.ዮሐንስ (ወንድሙ)
5.ፊልዾስ
6.በርተሎሜዎስ
7.ቶማስ
8.ማቴዎስ
9.ያዕቆብ ወልደ እልፍዮስ
10.ታዴዎስ (ልብድዮስ)
11.ናትናኤል (ቀናተኛው ስምዖን) እና
12.ማትያስ (በይሁዳ የተተካ) ናቸው:: (ማቴ. 10:1)

እነዚህን 12 አርድእቱን ከጠራ በሁዋላ ለ3 ዓመታት ከ3 ወራት ከዋለበት ሲማሩ ይውሉ ነበር:: ሌሊት ደግሞ ምሥጢር ሲያስተረጉሙ ያድሩ ነበር::

ጌታ እንደሚገባ ካስተማራቸው በሁዋላ ከፍ ያለ ኃላፊነትን ሾማቸው:: ለዓለም እረኞች: የእርሱም ባለሟሎች ሆኑ:: እጅግ ብዙ መከራ እንደሚገጥማቸው ነገራቸው:: (ማቴ. 10:16, ዮሐ. 16:33) በዚያው ልክ ክብራቸውንም አከለላቸው:: (ማቴ. 19:28)
ሥልጣናቸው ደግሞ እስከዚህ ድረስ ሆነ:: "በምድር ያሠራችሁት በሰማይ የታሰረ ይሆናል: በምድር የፈታችሁት በሰማይ የተፈታ ይሆናል::" (ማቴ. 18:18) "ይቅር ያላችሁዋቸው ኃጢአታቸው ይቀርላቸዋል: ያላላቹሃቸው ግን አይቀርላቸውም::" (ዮሐ. 20:23)

የመንግስተ ሰማያትን መክፈቻ (ማቴ. 16:19): እረኝነትን (ዮሐ. 21:15) ተቀበሉ:: ጌታ በንጹሕ አንደበቱ ሐዋርያቱን እጅግ ሲያከብራቸው "ጨው: የዓለም ብርሃናት" (ማቴ. 5:13) አላቸው:: ወንድሞቹም ተባሉ:: (ዮሐ. 7:5) ከዚህም በሚበልጥ በሌላ ክብር አከበራቸው::

ከዚህ ሁሉ ነገር በሁዋላ በጌታ ሕማማት ጌዜ ገና ነበሩና አንዳንዶቹ ፈርተው ተበተኑ:: ተመልሰው ግን በጽርሐ ጽዮን ሲጸልዩ ሰንብተው የጌታን ትንሳኤ ተመለከቱ:: እጆቹን: እግሮቹንም ዳስሰው ሐሴትን አደረጉ::

ለ40 ቀናት መጽሐፈ ኪዳንን: ትምሕርተ ኅቡዓት: ሌላም በፍጡር አንደበት የማይነገር ብዙ ምሥጢራትን ተምረው: ጌታ ሊቀ ዽዽስናን ሹሟቸው ዐረገ::

ለ10 ቀናት በእመ ብርሃን ሥር ተጠልለው ሲጸልዩና በአንድ ልብ ሲተጉ ሰንብተው መንፈስ ቅዱስ ወረደላቸው:: በአንዴም ከፍርሃት ወደ ድፍረት ተመልሰው ፍጹማን: ብርሃናውያን ሆኑ:: 71 ልሳናትን ነስተው በአንዲት ስብከት ብቻ 3ሺ ነፍሳትን ማረኩ:: (ሐዋ. 2:41)

ቅዱሳን ሐዋርያት በኅብረት ለአንድ ዓመት ያህል በኢየሩሳሌምና በዙሪያዋ እየተመላለሱ አስተምረው ብዙ እሥራኤላውያንን ወደ ክርስትና ማርከዋል:: ከዚህ በሁዋላ ግን እንደ ትውፊቱ በዚህች ቀን ዓለምን በእጣ ለ12 ተካፈሏት::

ይህ ሲሆን መንፈስ ቅዱስ አብሯቸው ነበርና ለእያንዳንዳቸው እንደሚገባቸው አሕጉረ ስብከቶች ደረሷቸው:: እነርሱም ደቀ መዛሙርቶቻቸውን አስከትለው ለታላቁ መንፈሳዊ ዘመቻ ወረዱ::
+በሔዱበት ቦታም ከተኩላ: ከአንበሳና ከነምር ጋር ታገሉ:: በጸጋቸውም አራዊትን (ክፉ ሰዎችን) ወደ በግነት መልሰው ለክርስቶስ አስረከቡ:: በየሃገሩ እየሰበኩ ድውያንን ፈወሱ:: ለምጻሞችን አነጹ:: እውራንን አበሩ:: አንካሶችን አረቱ:: ጐባጦችን አቀኑ:: ሙታንንም አስነሱ:: እልፍ አእላፍ አሕዛብንም ወደ መንጋው ቀላቀሉ::

ስለዚህ ፈንታም ብዙዎቹ በእሳት ተቃጠሉ:: ቆዳቸው ተገፈፈ:: በምጣድ ተጠበሱ:: ደማቸው በምድር ላይ ፈሰሰ:: ከአንድ ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ በቀር ሁሉም ይህችን ዓለም በሰማዕትነት ተሰናበቱ:: ጨው ሆነው አጣፍጠዋልና: ብርሃንም ሆነው አብርተዋልና እናከብራቸዋለን:: "አባቶቻችን: መምሕሮቻችን: ጌቶቻችንና ሊቆቻችን" እንላቸዋለን::

🌹+"+ ቅዱስ ቢላሞን ሰማዕት +"+🌹

=>በዘመነ ሰማዕታት የነበረው ቅዱስ ቢላሞን በወቅቱ ይታወቅ የነበረው በክርስቲያንነቱ ሳይሆን በፈላስፋነቱ ነበር:: እጅግ የተማረ ጥበበኛ: ግን ደግሞ ወገኑ ከኢ-አማንያን በመሆኑ ክርስቶስን አያውቀውም ነበር::

እግዚአብሔር ግን እንዲጠፋ አልፈቀደምና አንድ ካህንን ላከለት:: ከመቀራረብ የተነሳ ብዙ ስለተነጋገሩ ቢላሞን ወደ ክርስትና እየተሳበ ሔደ:: በመጨረሻም ተምሮ በካህኑ እጅ ተጠምቁዋል:: ቀጥሎም ይጾም: ይጸልይ: ይጋደል ነበር::

በትንሽ ጊዜም ከጸጋ ደርሶ ድውያንን ይፈውስ ገባ:: ብዙ አሕዛብን እያስተማረ: ከደዌአቸውም እየፈወሰ ወደ ክርስትና መለሳቸው:: አንድ ቀን ግን "ዐይነ ሥውር አብርተሃል" በሚል ተከሶ ሞት ተፈረደበት::

ከመገደሉ በፍትም ጌታችን ከሰማይ ወርዶ "ወዳጄ!" ሲለው ወታደሮች ሰሙ:: በዚህ ምክንያት አምነው በዚህች ቀን 158 ወታደሮች አብረውት ተሰይፈዋል::
=>አምላከ ቅዱሳን ሐዋርያት ቸርነቱን: ምሕረቱን ያብዛልን:: በምልጃቸው ሃገራችንን ከክፉ ጠብቆ ከበረከታቸው ይክፈለን::

=>ጥቅምት 15 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1."12ቱ" ቅዱሳን ሐዋርያት
2.ቅዱስ ቢላሞን ሰማዕት
3."158" ሰማዕታት (የቅዱስ ቢላሞን ማሕበር)
4.ቅዱስ ሲላስ ሐዋርያ
5.ቅድስት ጾመታ

=>ወርሐዊ በዓላት
1.ቅዱስ ቂርቆስና እናቱ ኢየሉጣ
2.ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ (አፈ በረከት)
3.ቅዱስ ሚናስ ግብፃዊ
4.ቅድስት እንባ መሪና
5.ቅድስት ክርስጢና

" በዚያን ጊዜ ዼጥሮስ መልሶ:- 'እነሆ እኛ ሁሉን ትተን ተከተልንህ:: እንኪያስ ምን እናገኝ ይሆን?' አለው:: ጌታ ኢየሱስም እንዲህ አላቸው:- 'እውነት እላቹሃለሁ! እናንተስ የተከተላችሁኝ በዳግመኛ ልደት: የሰው ልጅ በክብሩ ዙፋን በሚቀመጥበት ጊዜ እናንተ ደግሞ በአሥራ ሁለቱ የእሥራኤል ነገድ ስትፈርዱ በአሥራ ሁለት ዙፋን ትቀመጣላችሁ:: ". (ማቴ. 19:27)

✍️† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †✍️
🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇

https://t.me/Sinksar
https://t.me/Sinksar
https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

22 Oct, 15:46


ሰኞ ማታ!
ቀን:- 11/02/2017ዓ.ም

በአ.አ ከተማ መርካቶ አካባቢ ከቆርቆሮ እና ከኮነቴነር ቤቶች አቅራቢያ ወዳለው ' ነባር የገበያ ማዕከል (ህንጻ) ' የተዛመተው እሳት የህንጻውን አንደኛውን ክፍል ክፉኛ አውድሞታል።

እስካሁን ሰው ላይ ስለደረሰ ጉዳት ሪፖርት አልተደረገም።

በትላንት ምሽቱ የእሳት አደጋ ምንም እንኳን ይፋዊ የጉዳት መጠን ባይገለጽም የደረሰው ጉዳት ከፍተኛ ነው።

በርካቶች ብዙ የደከሙበት ንብረታቸው በአንድ ምሽት ወደ አመድነት ተቀይሯል።

ምን ያህሎቻችን ነን ግን ለነገ አብዝቶ የሚያስጨንቀን?

ይኼው ነው!።

ክፉ አታምጣብን
ሰላም አውለህ ሰላም አሳድረን በሉ/እንበል/

ፎቶ ፦ ' መርካቶ ሸማ ተራ ' ከትላንት ምሽቱ አስከፊና ከባድ የእሳት አደጋ በኃላ ዛሬ ላይ ከላይ በፎቶው የምትመለከቱትን ይመስላል።

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

22 Oct, 15:29


#ኦርቶዶክስተዋሕዶ

" ...አለመግባባት በዝቷል፤ ማኵረፍና መቀያየም ሰፍቷል ፤ ነገሩ ሁሉ ግራ የሚያጋባና የተመሰቃቀለ ሆኖ ይታያል፡፡ ችግሩ ከሕዝብ አልፎ የአምልኮ ስፍራዎችንና የአምልኮው ፈጻሚዎችን ዒላማ ያደረገ እግዚአብሔርን መዳፈር እየተለመደ መጥቷል " - ቅዱስነታቸው

የጥቅምት 2017 ዓ/ም የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ ተጀመረ።

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተወሕዶ ቤተክርስቲያን ሁለንተናዊ አገልግሎትና የስራ አፈጻጸም ላይ ለመምከርና ለመወሰን ኃላፊነት ያለው ቅዱስ ሲኖዶስ ዛሬ መደበኛና ዓመታዊ ጉባኤውን ጀምሯል።

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የጉባኤውን መጀመረ አስመልክተው መልዕክት አስተላልፈዋል።

ከመልዕክታቸው ፦

" የሰው ልጆች በዚህ ዓለም ሲኖሩ የተሟላ ሰላምና ጣዕመ ሕይወት ሊኖራቸው የሚችለው በመንፈሳዊ ኑሮአቸው የተሻለ ነገር ስላገኙ ብቻ አይደለም፡፡

ሰዎች ከሥጋዊ ክዋኔም ጭምር የተፈጠሩ እንጂ እንደመላእክት ሥጋ የሌላቸው መንፈስ ስላይደሉ ለኑሮአቸውና ለሥጋዊ ክዋኔአቸው የሚሆን ነገር ያስፈልጋቸዋል፡፡

በዚህም ዓለማዊው አስተዳደር የተመቻቸ መደላድል ሊፈጥርላቸው ግድ ነው፤ ዓለማዊው አስተዳደርም የመለኮትን ተልእኮ ለመፈጸም የተሾመ ሹመኛ እንደመሆኑ የእግዚአብሔርን ሕዝብ በትክክል መምራት ይጠበቅበታል፡፡

ምንም ቢሆን የተቀበለው ኃላፊነት የእግዚአብሔር ነውና በሚሰራው ሁሉ በሿሚው አምላክ ከመጠየቅ አያመልጥም፡፡

እኛም በዚህ ዓለም የእግዚአብሔር ወኪሎች ስለሆንን ቢሰሙንም ባይሰሙንም ዓለማውያን ሹማምንትን የማስተማርና የመምከር ኃላፊነት አለብን፡፡

ይህ የሁለታችን ኃላፊነት እንደ እግዚብሔር ፈቃድ ስንፈጽም የሕዝብ ሰላምና በረከት፣ ፍቅርና አንድነት፣ ዕድገትና ልማት በአስተማማኝ ሁኔታ ይረጋገጣል፡፡

ነገር ግን በአሁኑ ጊዜ በሀገራችንም ሆነ በአካባቢያችን እየሆነ ያለው ይህ አይደለም፤ አለመግባባት በዝቶአል፣ ማኵረፍና መቀያየም ሰፍቶአል፤ ነገሩ ሁሉ ግራ የሚያጋባና የተመሰቃቀለ ሆኖ ይታያል፡፡

ችግሩ ከሕዝብ አልፎ የአምልኮ ስፍራዎችንና የአምልኮው ፈጻሚዎችን ዒላማ ያደረገ እግዚአብሔርን መዳፈር እየተለመደ መጥቶአል፤ ይህ ለአንድ ሀገር ወይም ሕዝብ የውድቀት ምክንያት ከሚሆን በቀር ከቶውኑም የዕድገት ምልክት ሊሆን አይችልም፡፡

ከሁሉም በላይ የሚያሳዝነው ደግሞ ይህ ክፉ ድርጊት እየተፈጸመ ያለው በእኛው ልጆች በኢትዮጵያውያን መሆኑ ነው፤ ስለሆነም በከተማም፣ በጫካም፣ በገጠርም በየትኛውም ስፍራ የምትገኙ ልጆቻችን ምንም ይሁን ምን ሀገርንና ሕዝብን ከመጉዳት ተቆጠቡ፡፡

በተለይም ከቤተ ክርስቲያንና ከሀገር እንደዚሁም ሕዝቡን ከሚያገለግሉ ካህናትና ሲቪል ሰራተኞች እባካችሁ እጃችሁን አንሡ፤ ቤተ ክርስቲያን እኮ የእናንተና የሕዝቡ ሁሉ እናት ናት፤ በእናታችሁ ላይ መጨከንን እንዴት ተለማመዳችሁት ? አሁንም ንስሐ ግቡ ያለፈው ይበቃል፡፡

ልብ በሉ ከእግዚአብሔር ጋር መጣላት አይበጅም፤ ሰውን መጉዳትና እግዚአብሔርን መዳፈር አቁሙ፤ የእግዚአብሔር ገንዘብ የሆነውን ሥርዓተ አምልኮም ያለቦታው አታውሉ፤ ጥያቄአችሁን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ዕድል ስጡ፡፡

በእግዚአብሔር ስም ለመላው ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችንና ልጆቻችን የምናስተላፈው ወቅታዊ መልእክታችን ይህ ነው፡፡ "

(የቅዱስነታቸው ሙሉ መልዕክት ከታች ተያይዟል)

የዘገባው ምንጭ
@tikvahethiopia

✍️† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †✍️
               🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

21 Oct, 12:09


🌹✞ ስንክሳር ጥቅምት ፲፪ (12)  ✞🌹

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞✞✞

✞✞✞ እንኩዋን ለልበ አምላክ "ቅዱስ ዳዊት":
ለቅዱስ "ማቴዎስ ሐዋርያ" እና ለቅዱስ "ድሜጥሮስ" ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ።

🙏+*" ቅዱስ ዳዊት ልበ አምላክ "*+🙏

ቅዱስ መጽሐፍ እንዲህ ይላል:-
"እግዚአብሔር ለዳዊት በእውነት ማለ:
አይጸጸትም::" (መዝ. 131:11) አሁን በእግዚአብሔር መጸጸት ኑሮበት አይደለም:: ቅዱስ ዳዊት የማያጸጽት ፍጹም ወዳጅ መሆኑን ሲገልጥ ነው እንጂ:: ጌታ ቅዱስ ዳዊትን "እንደ ልቤ የሆነ: ፈቃዴን የሚፈጽም: ባሪያየን ዳዊትን አገኘሁት" (መዝ. 88:19) ብሎ ሲናገር ሰምተን እጅግ አደነቅን::

እንደ አምላክ ልብ ሆኖ መገኘት ምን ይረቅ?! ምንስ ይደንቅ?! ለዚህ አንክሮ ይገባል !! ጌታ ይቀጥልና ደግሞ "ዳዊትን እንዳልዋሸው አንድ ጊዜ በቅዱስነቴ ማልሁ" (መዝ. 88:35) ይላል:: *" አቤት አባታችን ዳዊት!!! . . . ክብር: የክብር ክብር: ውዳሴና ስግደትም ላንተ በጸጋ ይገባል "* እንላለን::
ነቢየ ጽድቅ ቅዱስ ዳዊት 7 ሃብታት ሲኖሩት:-
1.ሃብተ ትንቢት
2.ሃብተ መንግስት
3.ሃብተ ክህነት
4.ሃብተ በገና (መዝሙር)
5.ሃብተ ፈውስ
6.ሃብተ መዊዕ (ድል መንሳት)
7.ሃብተ ኃይል ተብለው ይታወቃሉ::

በ7ቱ ስሞቹም:-
1.ጻድቅ
2.የዋህ
3.ንጹሕ
4.ብእሴ እግዚአብሔር
5.ነቢየ ጽድቅ
6.መዘምር እና
7.ልበ አምላክ ተብሎ ይጠራል::

ይህች ቀን ለእሥራኤል የነገሠባት ቀን ናት::
እግዚአብሔር ሳዖልን ከናቀው በሁዋላ ከእሴይ ልጆች መካከል "እንደ ልቤ የሆነውን ቀብተህ አንግስልኝ" ቢለው በዚህች ቀን ነቢዩ ሳሙኤል ቤተ ልሔም ገብቷል::

በዚያም ከኤልያብ እስከ አሚናዳብ: 7ቱን የእሴይን ልጆች ቢፈትን አልሆነም:: በቅዱስ ሚካኤል ጠቁዋሚነት ግን ከእረኝነቱ ዳዊት ተጠራ:: ገና ከርቀት ሲመጣ የዘይት ቀርኑ ቦግ ብሎ ተከፈተ::

በቅዱስ ዳዊት ራስ ላይም እንደ እሳት ፈላ:: በአምላክ ምርጫም በ12 ዓመቱ ንጉሥ ተባለ:: የቅዱሱ ዜና ብዙ ነውና ለታሕሳስ 23 ይቆየን:: በቸር ቢያደርሰን በዚያው ቀን ከክብሩ እንካፈላለንና::

🙏+"+ ቅዱስ ማቴዎስ ሐዋርያ +"+🙏

ቅዱሱ በቀዳሚ ስሙ "ሌዊ": በቀዳሚ ግብሩ ደግሞ "ቀራጩ" ይባል ነበር:: ወንጌል እንደሚል ጌታችን የጠራው ከሚቀርጥበት ቦታ ሲሆን (ማቴ. 9:9) ከ12ቱ ሐዋርያት ደምሮ (ማቴ. 10:1) ስሙን "ማቴዎስ" ብሎታል:: ትርጉሙም "ኅሩይ" (ምርጥ) እንደ ማለት ነው::

ጌታችንን በዘመነ ሥጋዌው በፍጹም ምናኔ ከማገልገሉ ባለፈ ከዋለበት እየዋለ: ካደረበት እያደረ: የእጁን ተአምራት ተመልክቷል:: የቃሉንም ትምሕርት ሰምቷል:: በጌታ ሕማማት ጊዜ ምንም በፍርሃት ከተበተኑት አንዱ እሱ ቢሆን አመሻሽ ላይ ወደ ማርቆስ እናት ቤት (ጽርሐ ጽዮን) ሒዶ ወንድሞቹን ሐዋርያትን ተቀላቅሏል::

የክብር ባለቤት መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ
ከሙታን ተነስቶ ትንሳኤውን ሲገልጥም ቅዱስ ማቴዎስ ነበረ:: ለ40 ቀናት መጽሐፈ ኪዳንን: ትምሕርተ ኅቡዓትን ተምሮ በጌታ ዕርገት ጊዜ ሊቀ ዽዽስናን ተሹሟል:: በ50ኛው ቀን መንፈስ ቅዱስ በወረደ ጊዜም ጸጋውንና 71 ልሳናትን ተቀብሎ በኢየሩሳሌምና በዙሪያዋ ወንጌልን ሰብኩዋል::

ሐዋርያት ወንጌልን ለዓለም ለማዳረስ እጣ በተጣጣሉ ጊዜ ለቅዱስ ማቴዎስ ምድረ ፍልስጥኤም ደረሰችው:: ሃገረ ስብከቱን ካዳረሰ በሁዋላም ወደ ሌሎች ሃገራት ተጉዞ ሰብኩዋል::

ለምሳሌ በገድለ ሐዋርያት ላይ በኢትዮዽያ: በፋርስና በባቢሎን አካባቢ ማስተማሩን ይገልጻል:: የሚገርመው ደሞ ለዚህ ማረጋገጫ የሚሆን ነገር ሃገራችን ውስጥ መኖሩ ነው::

ወደ አክሱምና አካባቢዋ ቅዱሳት መካናትን ለመሳለም በሔድንበት ወቅት በጻድቃነ ዴጌ/ዶጌ ገዳም ውስጥ (አክሱም አካባቢ የሚገኝ የ3ሺ ስውራን ቦታ ነው) የቅዱስ ማቴዎስን በትረ መስቀል መመልከት ችለናል:: አባቶችም ቅዱስ ማቴዎስ በዘመነ ስብከቱ አክሱም አካባቢ መጥቶ እንደ ነበር ነግረውናል::

+ቅዱሱ ሐዋርያ በአይሁድ: በአሕዛብና በአረሚ መካከል እየተመላለሰ አስተምሮ በርካታ ተአምራትን ሠርቷል:: የጣዖት ካህናትንና ነገሥታትን ጨምሮ እልፍ አእላፍ ነፍሳትን ወደ ክርስትና መልሷል::

ስለዚህ ፈንታም እጅግ ብዙ መከራዎች
ተፈራርቀውበታል:: ጌታችንም በየጊዜው እየተገለጸ ያጽናናው ነበር:: በቤተ ክርስቲያን ታሪክ የመጀመሪያውን ወንጌል በምድረ ፍልስጥኤም ሲጽፍ: ዘመኑም ጌታ ባረገ በ8ኛው ዓመት (ማለት በ43 ዓ/ም) አካባቢ ነው::

ወንጌሉ 28 ምዕራፎች ሲኖሩት በጌታ የዘር ሐረግ ጀምሮ የጌታችንን ትምሕርቱንና ተአምራቱን በሰፊው ያትታል:: በመጨረሻም ከምሴተ ሐሙስ እስከ ትንሳኤ ድረስ አትቶ ይጠናቀቃል::

ቅዱስ ማቴዎስ ከ12ቱ ሐዋርያት በአንድ ነገሩ
ይለያል:: ከ5ቱ ዓለማት አንዱን (ብሔረ ብጹዓንን)
ያስተምር ዘንድ ተመርጧል:: ዘወትር እሑድ በደመና እየተነጠቀ ኃጢአት ወደ ሌለበት ዓለም ገብቶ ብጹዓንን ያስተምር ነበር:: "ሰላም ለማቴዎስ በደመና ሰማይ ዘተነጥቀ: ኅሩያነ ይርዓይ ዘብሔረ ብጹዓን ደቂቀ::" እንዲል::

+በዚያም ዘወትር ጌታችንን ያየው ነበር:: ቅዱስ ማቴዎስ እንዲህ ከተመላለሰ በሁዋላ በፍጻሜው ለጊዜው ባልለየናት አንዲት ሃገር ውስጥ አረማውያን አስረው አሰቃይተውታል:: በዚህች ቀንም ገድለውታል::

ጥቅምት 12 ቀን የሚከበሩ
👉ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ ዳዊትልበ አምላክ (የነገሠበት)
2.ቅዱስ ማቴዎስ ሐዋርያ
3.ቅዱስ ድሜጥሮስ ሊቅ
4.ቅድስት ልዕልተ ወይን
5.ቅዱስ ሳሙኤል ነቢይ
6.ጻድቃን ዼጥሮስ ወዻውሎስ

👉 ወርሐዊ በዓላት
1.ቅዱስ ሚካኤል ሊቀ መላእክት
2.ቅዱስ ላሊበላ ጻድቅ (ንጉሠ ኢትዮዽያ)
3.ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ
4.ቅዱስ ቴዎድሮስ ምሥራቃዊ (ሰማዕት)
5.ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ
6.አቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ

✍️† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †✍️
               🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

20 Oct, 22:37


የትላንቱ ማሕሌተ ጽጌ ያሳደረብኝ ስጋት

በልጅነታችን ቤተክርስቲያ ያደግን የእድሜ እኩዮቼ ከየትኛውም የከተማችን ጥግ ተሰባስበን ባሳደገን ደብር ውስጥ ማሕሌተ ጽጌን ቆመናል። ነገር ግን በጣም ሀዘን ውስጥ የጣለኝ አንድ ልምድ ሲቀር ታዝቤ በስጋት ሌቱን አሳልፌያለሁ።

በግራ እና በቀኝ ከሊቃውንቱ ቀጥለው የሚቆሙ ታዳጊዎች የወረብ ዑደት አልቆ ዝማሬው ወድ ቸብቸቦ ሲቀየር ሊቃውንቱ ይጨርሱና ታዳጊዎች በድጋሚ በግራ እና በቀኝ እየዘመሩ ወደ ሰዓታቱ ለመገናኘት ያመራሉ። ይህ የዝማሬ አገልግሎት እስከዚህኛው ዓመት ድረስ ደምቆ የቆየ ነበር።

በትላንትናው ዕለት ግን በብዛት የታዳጊዎች ልምድ የነበረው ዝማሬ አልነበረም። ምክንያቱም ታዳጊዎች በቤተክርቲያኒቱ በብዛት አልነበሩም።

አራዳ በሚገኘው የመናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ዙሪያ የሚገኙ መንደሮች ኗሪ የነበሩ የአጥቢያው ምዕመናን በአብላጫው "ለልማት" ከመንደሩ ተነስተዋል።

በልጅነቱ ሲያገለግል ያደገ ሁላ በአዋቂነት እድሜው ቤተክርስቲያንን ርቆ ይቀር ዘንድ አይቻለውምና የእድሜ እኩዬቼ ወንዶችም ሴቶችም አሁንም ከቤተ ክርስቲያን አልቀረንም።

ይቺ ምስኪን ቤተክርስቲያናችን ቀጣይ ተተኪ ይኖራት ይሆን?
አስፈርቶኛል።

"ሕጻናት ወደ እኔ ይመጡ ዘንድ አትከልክሏቸው"
ሉቃስ፣ 18-16

ጥቅምት 10-2017 ዓ.ም
ጋዜጠኛ ያሬድ ሹመቴ

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

20 Oct, 22:28


✞ ስንክሳር ጥቅምት 11 ✞
🌿🌹🌿

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡

✞ እንኩዋን ለአባ "ያዕቆብ ስዱድ" እና ለእናታችን "ቅድስት ዺላግያ" ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ።

🌹" አባ ያዕቆብ ስዱድ "🌹
"ዻዻስ" ማለት "አባት - መሪ - እረኛ" ማለት ነው::
በቅድስት ቤተ ክርስቲያን አስተምሕሮ በሐዲስ ኪዳን የመንፈሳዊ ስልጣን ደረጃዎች በጥቅሉ 3 ናቸው:: እነሱም ዲቁና: ቅስና: ዽዽስና ሲሆኑ በሥራቸው ወደ 9 ያህል ክፍሎች አላቸው:: ከእነዚህም ከፍተኛው ስልጣን ዽዽስና ነው::

ዽዽስና ማለት የክርስቶስን መንጋ እንደ ባለቤቱ
አድርጐ መጠበቅ ማለት ነው:: ሥልጣኑ በምድር
"ሸክም: ዕዳ" ሲሆን በሰማይ ግን "ክብር" ነው::
ማንም በሥጋው ላይ ካልጨከነ በቀር ዽዽስናን
አይመኝም::

ቅዱስ ዻውሎስ "ሠናየ ግብረ ፈተወ - ማንም
ዽዽስናን ቢመኝ መልካም ሥራን ተመኘ" (1ጢሞ. 3:1) ማለቱን ይዞ "ሹሙኝ" ማለት ወደ ማይጠፋ እሳት የሚያስጥል ከባድ ውሳኔ ነው:: ምክንያቱም አንድ ክርስቲያን የሚጠየቅ በራሱ ኃጢአት ሲሆን አንድ ካህን ደግሞ ስለ ልጆቹ ይጠየቃል:: የከፋው ግን የዻዻሱ ነው::

አንድ ዻዻስ ቢጾም ቢጸልይም እንኩዋ ለድኅነቱ በቂ አይደለም:: ምክንያቱም በመንበሩ ላይ ያስቀመጠው መንጋውን እንጂ ራሱን እንዲያድን አይደለምና:: ጌታ እንዳለ መልካም እረኛ "ይሜጡ ነፍሶ ቤዛ አባግኢሁ - መልካሙ እረኛ ስለ በጐቹ ቤዛ ራሱን አሳልፎ የሚሰጥ ነው::" (ዮሐ. 10) ስለዚህም ክህነት ( ዽዽስና) ሐዋርያዊ አገልግሎት ከባድም ኃላፊነት ነው::

አባቶቻችን ሐዋርያትና ተከታዮቻቸው ሐዋርያውያን
ታላላቅ የዽዽስና መንበሮችን መሥርተው: ትምሕርቱን ከነ ወንበሩ አስተላልፈዋል:: ከእነዚህ መንበረ ዽዽስናዎች 4ቱ የበላይ ናቸው::

እነዚህም የቅዱስ ዼጥሮሱ የሮም: የቅዱስ ዮሐንሱ የአንጾኪያ: የቅዱስ ማርቆሱ የእስክንድርያና የቅዱስ ዻውሎሱ የኤፌሶን መናብርት ናቸው::

እነዚህ መንበሮችም ከክርስቶስ ዕርገት እስከ 443
(451) ዓ/ም: ጉባኤ ኬልቄዶን ድረስ በአንድነት ቆይተው ተለያይተዋል:: ከእነዚህ መናብርት መካከል የእስክንድርያው (የግብጹ) እና የአንጾኪያው (የሶርያው) ዛሬም ድረስ በተዋሕዶ እምነት የጸኑ ናቸው::

የእኛ ቤተ ክርስቲያንም ሐዋርያዊት እንደ መሆኗ
ሐዋርያትን መስለው: ሐዋርያትን አህለው የተነሱ አበው ዻዻሳትን በየጊዜው በበዓላት ታስባለች: ታከብራለች::

በተለይ ደግሞ የእስክንድርያና የአንጾኪያ በርካታ
አባቶችን እናከብራለን:: እነርሱ ለቀናች ሃይማኖትና
ለመንጋው ሲሉ ብዙ መከራን በአኮቴት ተቀብለዋልና:: ከእነዚህም መካከል አንዱ አባ ያዕቆብ ሲባሉ በ5ኛው መቶ ክ/ዘመን አካባቢ የአንጾኪያ መንበር ፓትርያርክ ነበሩ::

ቅዱሱ በገዳማዊ ሕይወት የተመሠከረላቸው:
በትምሕርት የበሰሉና ለመንጋው የሚራሩ በመሆናቸው በምዕመናን ይወደዱ ነበር:: ነገር ግን ተረፈ አርዮሳውያንና መለካውያን ከነገሥታቱ ጋር አብረው ብዙ አሰቃዩዋቸው:: በመጨረሻም ከመንበራቸው አፈናቅለው ወደ በርሃ አሳድደዋቸዋል:: ከስደት በሁዋላም አባ ያዕቆብ በዚህች ቀን ዐርፈዋል::

🌿"🌹 ቅድስት ዺላግያ ገዳማዊት 🌹"🌿

=>ቅዱስ መጽሐፍ እንደሚል እግዚአብሔር የኃጥኡን መመለስ እንጂ ሞቱን አይፈልግም:: በጠፋው በግ መገኘት ደስ ይለዋል:: በእግርህ ሒድ እንኩዋ አይለውም:: ይልቁኑ በትከሻው ተሸክሞ ከጐረቤቶቹ ጋር ደስ ይለዋል እንጂ::

ቤተ ክርስቲያን ካፈራቻቸው ቅዱሳን አንዳንዶቹ ጭንቅ ከሆነ የኃጢአት ሕይወት የተመለሱ ናቸው:: ግን ድንቅ በሆነ ንስሃቸው "ቅዱሳን" ከመባል ደርሰዋል:: ከእነዚህም አንዷ ቅድስት ዺላግያ ናት::

=>ይህቺ ቅድስት እናት በልጅነቷ በመልኩዋ ምክንያት ስሕተት ያገኛት ናት:: አምላክ የፈጠረውን መልክና ገላ እንዴት መጠቀም እንዳለብን እየተማርን አይደለምና በአርአያ ሥላሴ የተፈጠረውን ገላችን ለዲያብሎስ ሰጥተነዋል::

ይህቺ እናትም ችግሯ ይኼው ነበር:: ስለ ገጽታዋና
ገላዋ የነበራት የተሳሳተ አመለካከት መጀመሪያ ወደ ትውዝፍት (ምንዝር ጌጥ): ቀጥሎም ወደ ዝሙት ከተታት:: ለዘመናትም የሰይጣን ወጥመድ ሆና ኑራለች::

ፈጣሪ ግን ለሁላችንም የመዳን ቀን ጥሪ አለውና
እሷንም ጠራት:: ምናልባትም በዘመኗ የብዙ ሰባክያንን ትምሕርት ሰምታለች:: አንዱም ግን ወደ ልቧ አልገባም::

ምክንያቱም መንፈስ ቅዱስ ያላደረበት አስተማሪ በጥሩ አማርኛ ልባችን ደስ ያሰኝ ይሆናል እንጂ ሊለውጠን አይችልም::

በዘመኑም የሚታየው ትልቁ ችግር ይኼው
ይመስለኛል:: እግዚአብሔር የሾማቸው አባቶቻችን
ተቀምጠው ወጣቶች መድረኩን የሙጥኝ ብለነዋል::

ወደ ቀደመ ነገራችን እንመለስና ዺላግያ አንድ ቀን
የሰማችው የደጉ ዻዻስ ትምሕርት ግን ፈጽሞ ዘልቆ ተሰማት:: ተጸጸተች: አለቀሰች:: ወደ ዻዻሱ ሔዳ "ማረኝ" አለች: ንስሃ ሰጣት:: እርሷም ንብረቷን ሁሉ መጽውታ በርሃ ገባች::

አንገቷን ደፍታ በጾምና በጸሎት ሰይጣንን ድል ነሳችው:: ከሃገሯ ሶርያ ወደ ቀራንዮ ደርሳ ተመልሳ ለ30 ዓመታት ዘጋች:: ተባሕትዎዋን ስትፈጽም በጸጋ እግዚአብሔር ተአምራትን ሠርታ: ለኃጥአን መንገድ ጧፍ ሆና አብርታ
በዚህች ቀን ዐርፋለች::

=>አምላከ ቅዱሳን የሚያስተውለውን የንስሃ አእምሮን ያድለን:: ከወዳጆቹ በረከትም አያርቀን::

=> ጥቅምት 11 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን
በዓላት
1.ቅዱስ አባ ያዕቆብ (ስደተኛው ሊቀ ዻዻሳት)
2.ቅድስት ዺላግያ ገዳማዊት
3.ቅዱስ ፋሲለደስ ሰማዕት
4.ቅዱስ አርማሚ ሰማዕት

=> ወርሐዊ በዓላት
1.ቅዱስ ያሬድ ካህን
2.ማር ገላውዴዎስ ሰማዕት
3.ብፁዐን ኢያቄምና ሐና
4.አቡነ ሐራ ድንግል ጻድቅ

" መቶ በግ ያለው ከእነርሱም አንዱ ቢጠፋ ዘጠና
ዘጠኙን በበርሃ ትቶ የጠፋውን እስኪያገኘው ድረስ
ሊፈልገው የማይሔድ ከእናንተ ማን ነው? ባገኘውም ጊዜ ደስ ብሎት በጫንቃው ይሸከመዋል:: ወደ ቤትም በመጣ ጊዜ ወዳጆቹንና ጐረቤቶቹን በአንድነት ጠርቶ 'የጠፋውን በጌን አግኝቼዋለሁና ከእኔ ጋር ደስ ይበላችሁ' ይላቸዋል:: እላችሁአለሁ: እንዲሁ ንስሃ ከማያስፈልጋቸው ከዘጠና ዘጠኝ ጻድቃን ይልቅ ንስሃ በሚገባ በአንድ ኃጢአተኛ በሰማይ ደስታ ይሆናል:: "
(ሉቃ. 15:3-7)

✍️† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †✍️
🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇

https://t.me/Sinksar
https://t.me/Sinksar
https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

19 Oct, 18:02


🌿 ስንክሳር ጥቅምት 10 🌿
✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞

✞ እንኩዋን ለቅዱሳን ሰማዕታት "ባኮስ ወሰርጊስ" ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ።

🌹" ቅዱሳን ባኮስ ወሰርጊስ "🌹

ሰማዕትነት በክርስትና ለሃይማኖት የሚከፈል
የመጨረሻው ዋጋ (መስዋዕትነት) ነው:: ሰው ለፈጣሪው ሰውነቱን ሊያስገዛ: ሃብት ንብረቱን ሊሰጥ ይችላል:: ከስጦታ በላይ ታላቅ ስጦታ ግን ራስን አሳልፎ መስጠት ነው::

ራስን መስጠት በትዳርም ሆነ በምናኔ ውስጥ ይቻላል:: የመጨረሻ ደረጃው ግን ሰማዕትነት ነው:: "አማን መነኑ ሰማዕት ጣዕማ ለዝ ዓለም: ወተዓገሡ ሞተ መሪረ በእንተ መንግስተ ሰማያት" እንዳለው ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ ሰማዕትነት ማለት መራራውን ሞት ስለ ፍቅረ እግዚአብሔር ሲሉ መታገስ ነው::

እርሱ ቅሉ መድኃኒታችን ክርስቶስ የሰማይና የምድር ጌታ ሲሆን ኃፍረተ መስቀልን ታግሦ ሙቶልን የለ! በዓለም ያሉ ብዙ እምነቶች ስለ መግደል በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ያስተምራሉ:: ክርስትና ግን መሞትን እንጂ መግደልን የሚመለከት ሕግ የለውም::

እርሱ ባለቤቱ "ጠላቶቻችሁን ውደዱ: የሚረግሟችሁን መርቁ: ስለሚያሳድዷችሁ ጸልዩ" ብሎናልና:: (ማቴ. 5:44) ነገር ግን ዕለት ዕለት ራሳችንን በሃይማኖትና በምግባር ካልኮተኮትነው ክርስትና በአንድ ጀምበር ፍጹም የሚኮንበት እምነት አይደለምና በፈተና መውደቅ
ይመጣል::

በተለይ የዘመኑ ክርስቲያን ወጣቶች ልናስተውል
ይገባናል:: የቀደሙ ወጣት ሰማዕታት ዜና የሚነገረን እንድንጸና ነውና::

እስኪ ለዛሬ ደግሞ በአጭሩ የቅዱሳን ባኮስና ሰርጊስን ዜና እንካፈል::

እነዚህ ቅዱሳን የዘመነ ሰማዕታት ፍሬዎች ናቸው::
ባኮስ እና ሰርጊስ (ሰርግዮስ) ከልጅነት ጀምሮ ባልንጀሮች ናቸው:: በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን በሮም ግዛት ሥር መክስምያኖስና ዲዮቅልጢያኖስ እስከ ነገሡበት ዘመን ድረስ በአንጻሩም ቢሆን ሰላም
ነበር::

ታዲያ በዚህ የሰላም ጊዜ 2ቱ ቅዱሳን ሥራ
አልፈቱም:: ጾምን: ጸሎትንና በጐ ምግባራትን ሁሉ
ይከተሉ ነበር:: ለመከራ ዘመን ስንቅ የሚሆነን በሰላሙ ዘመን የተያዘ ስንቅ ነውና::

በዚያው አንጻር ደግሞ ሠርቶ መብላት ይገባልና ሥራ ሲፈልጉ መክስምያኖስ ሠራዊት መሰብሰብ ጀመረ:: እነርሱም ከሠራዊቱ ዘንድ ተቆጥረው የምድራዊ ንጉሥ ጭፍሮች ሆኑ:: በእርግጥ በዘመናችን ለክርስትና አይመቹም ከሚባልላቸው ሥራዎች አንዱ ውትድርና ነው::

ነገር ግን ብዙ ቅዱሳንን ስትመለከቷቸው ሙያቸው
ይሔው ነበር:: ቅዱሳን ባኮስና ሰርጊስ ጊዜው የሰላምም ይሁን የጦርነት ይጾማሉ: ይጸልያሉ: ይመጸውታሉ:: እንዲህ እንዲህ እያሉም ዘመናት አለፉ::

ከቆይታ በሁዋላ ግን ሰይጣን ያደረበት ንጉሡ
መክስምያኖስ ጣዖት አመለከ:: አዋጅም አውጥቶ
ክርስቲያኖችን ያሰቃይ: ይገድልም ያዘ:: ቅዱሳኑ ይህንን ሲሰሙ አዘኑ::

ቁጭ ብለውም ተወያዩ:: በልባቸው ፍቅረ ክርስቶስ
ይነድ ነበርና ወጣትነታቸው: መልካቸው: ተወዳጅነታቸው ሁሉ ሊያታልላቸው አልቻለም:: እንደ አንድ ልብ መካሪ: እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ ስለ ሃይማኖት ሊሰው ወሰኑ::

በማግስቱም ንጉሡ ወደ ሾመው የቅርብ አለቃቸው ቀረቡና "የምንነግርህ ነገር አለን" አሉት:: "እሺ" ሲላቸው በወገባቸው ያለውን የክብር መታጠቀያና የክብር ልብሳቸውን በፊቱ ወረወሩለትና "እኛ የክርስቶስ ጭፍሮች
ነንና ከዚህ በሁዋላ ላንተ: ለጣዖት አምላኪው
አንታዘዝም" አሉት::

መኮንኑ ነዶታልና አስገረፋቸው: አሳሰራቸው:: በረሃብና በጥም: በብዙ መክፈልተ ኩነኔም አሰቃያቸው:: እነርሱ ግን ጽኑዓን ነበሩና አልቻሏቸውም:: ጥቅምት 4 ቀን በሆነ
ጊዜ ግን 2ቱን ለያዩዋቸው::

ቅዱስ ባኮስን ለብቻው ወስደው ትልቅ ድንጋይ በአንገቱ ላይ አሠሩበትና ባሕር ውስጥ አሰጠሙት::

ነፍሱም ከስጋው ስትለይ ባሕር ወደ ዳር
አስወጣችው:: በአካባባቢውም "ባባ" እና "ማማ"
የሚባሉ ባሕታውያን ነበሩና እግዚአብሔር እንዲገንዙት አዘዛቸው:: ሲሔዱም ቅዱስ ሥጋውን አንበሳና ተኩላ ሲጠብቁት አግኝተው: በታላቅ ዝማሬ ገንዘው: በራሳቸው ተሸክመው ወስደው: በበዓታቸው ውስጥ ቀበሩት::

ቅዱስ ሰርጊስን ደግሞ ለ6 ቀናት ካሠሩት በሁዋላ
በዚህች ቀን እጁንና እግሩን በእንጨት ላይ ቸንክረው: በእንስሳት ጭራ ላይ አስረው ሲጐትቱት ውለዋል:: አንገቱን በሰየፉት ጊዜም አንዲት ወጣት ደሙን ተቀብላ በረከትን አግኝታለች:: የመከራ ዘመን ካለፈ በሁዋላም ለቅዱሳኑ ቤተ ክርስቲያን ታንጾ በዚህች ቀን ተቀድሷል:: ተአምራትም ታይተዋል::

=>አምላከ ሰማዕታት ጽንዓት: ትእግስታቸውን አሳድሮ ከበረከታቸው ይክፈለን::

ጥቅምት 10 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን
በዓላት
1.ቅዱሳን ባኮስና ሰርጊስ (ሰማዕታት)
2.ቅዱስ ዮሐንስ መስተጋድል
3.አባ አውማንዮስ ሊቀ ዻዻሳት

=>ወርሐዊ በዓላት
1.ቅዱስ ናትናኤል ሐዋርያ
2.ቅዱስ ኒቆላዎስ ዘሃገረ ሜራ
3.አቡነ መልክዐ ክርስቶስ
4.ቅዱስ ያዕቆብ ሐዋርያ (ወልደ እልፍዮስ)
5.ቅድስት ዕሌኒ ንግስት
6.ታላቁ ቅዱስ ቆስጠንጢኖስ
7.ቅዱስ እፀ መስቀል

<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>

👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇

       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

19 Oct, 16:01


ተፈጸመ !

የሊቀ ትጉኃን ባሕታዊ አባ መፍቀሬ ሰብእ ኪዳነወልድ የቀብር ስነ-ስርዓት በሐይቅ ዛሬ በቀን 09/02/2017ዓ.ም
በቅዱስ እስጢፋኖስ እና አቡነ ኢየሱስ ሞዓ አንድነት ገዳም ተፈጽሟል።

የሥራቸው ትጋት እና የንፁህ ልብ ትሁት በረከታቸው በሁላችን ላይ ትደር።

ቅዱስ እግዚአብሔር ነፍሳቸውን ከቅዱሳኑ ጎን ያሳርፍልን!

ነፍስ ይማር!
😢

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

19 Oct, 04:48


🌹ስንክሳር ጥቅምት 9 🌹

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞✞✞

✞✞✞ ጥቅምት 9 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ✞✞✞

+" ቅዱስ ቶማስ ሐዋርያ "+

✞✞✞ ደጉ ሐዋርያ ቅዱስ ቶማስ ከኢትዮዽያ እስከ ሕንድና ባርቶስ በደረሰች ስብከቱ እጅግ ድንቅ የሆኑ ተአምራትን ሠርቷል:: 'አሐደ እምተአምራቲሁ' እንዲሉ አበው ከእነዚህ ዛሬ አንዱን እንመለከታለን::

+ቅዱስ ቶማስ ጐና ወደምትባል የሕንድ አውራጃ መግቢያ ፈሊጥ ቢያጣ ጌታ ወርዶ አበኒስ ለሚባል ነጋዴ ባሪያ አድርጐ ይሸጠዋል:: በመጀመሪያ በንጉሡ ሠርግ ቤት ውስጥ ተአምራትን አሳይቶ ሕዝቡን ከነ ሙሽሮቹና ንጉሣቸው አሳምኗል::

+ቀጥሎ ግን ጎንዶፎር ለሚባል ሌላ ንጉሥ 'ቤተ መንግስት ሥራ' ተብሎ ይላካል:: ሐዋርያውም ንጉሡን "የማንጽበትን ወርቅና ብር ስጠኝ" ብሎት ይሰጠዋል:: ንጉሡ ዘወር ሲል ግን "ወእሁብ ዘንጉሥ ለንጉሥ-የምድራዊው ንጉሥ ለሰማያዊው ንጉሥ እሰጣለሁ" እያለ ገንዘቡን ሁሉ ለነዳያን በተነው::

+ገንዘቡ ሲያልቅበት "ንጉሥ ሆይ! መሠረቱ ታንጿልና ለግድግዳው ላክልኝ" ይለዋል:: ሲልክለት ይመጸውተዋል:: አሁንም "ንጉሥ ሆይ! ለጣሪያው ላክልኝ" ይለውና ይመጸውተዋል:: መጽሐፍ እንደሚል ምጽዋት ለሐዋርያው ልማዱ ነውና::

+በመጨረሻ ግን ንጉሡ ሲመጣ ባዶ መሬት ላይ ነዳያን ገንዘቡን ሲበሉት አገኘ:: ተበሳጭቶም ቅዱስ ቶማስን ይገድለው ዘንድ አሠረው:: በዚያች ሌሊት ግን የንጉሡ ወንድም ጋዶን ሙቶ ሐዘን በሆነ ጊዜ ሐዋርያው አስነሳው::

+ጋዶንም ለቅዱሱ ሰግዶ በሰማይ ለንጉሥ ጐንዶፎር ትልቅ ቤት ታንጾ ማየቱን ተናገረ:: ንጉሡና ሠራዊቱም በፊቱ ሰግደው አመኑ:: አጥምቋቸውም ሔዷል::

+" ቅዱስ እስጢፋኖስ ካልዕ "+

+በዚህ ስም ከሚጠሩ ቅዱሳን ሊቀ ዲያቆናቱ ቅድሚያውን ሲይዝ ዛሬ የምናከብረው ቅዱስ ደግሞ 'ካልዕ እስጢፋኖስ' (ሁለተኛው) ይባላል:: 2ቱም 'ቀዳሜ ሰማዕት' ይባላሉ:: ዋናው በሐዋርያት ዘመን ቀድሞ እንደተሰዋ ሁሉ ሁለተኛው በዘመነ ዲዮቅልጢያኖስ ርጉም ቀድሞ ተሰይፏል::

+ቅዱሱ የተወለደው በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን አጋማሽ ሲሆን በአንጾኪያ ቤተ መንግስት ውስጥ ከነበሩ ልዑላንና የጦር መሪዋችም አንዱ ነበር:: በዝምድና ደረጃም የታላቁ ቅዱስ ፋሲለደስ የእህቱ ልጅ ነው:: በቤተ ፋሲለደስ ከማደጉ የተነሳም የእርሱ ልጅ እንደ ሆነ በገድሉ ተጠቅሷል::

+ቅዱስ እስጢፋኖስ ካልዕ ማለት መልክ ከደም ግባት የተባበረለት: ጾምና ጸሎትን የሚወድ: የነዳያን አጉራሽ: ኃያል የጦር ሰውና ተወዳጅ ክርስቲያን ነው:: ያ ክፉ አውሬ በዓለም በሚገኙ ምዕመናን ሁሉ ላይ ሞትና ስቃይን ሲያውጅ በአካባቢው የነበረ ይኼው ቅዱስ ነው::

+በቦታው ከነበሩ ብዙ ሺህ ሰዎች ንጉሡን ደፍሮ የተናገረው አንድም አልነበረም:: ቅዱስ እስጢፋኖስ ግን ለክርስቶስ ቀና:: ከሕዝቡ መካከልም እየሮጠ አልፎ በንጉሡ ፊት አዋጅ የሚያነበውን ወታደር ቀማውና በአደባባይ ያችን የክህደት ደብዳቤ ቦጫጭቆ ጣላት::

+ንጉሡንም "ሰነፍ" ሲል ገሠጸው:: እጅግ የተቆጣው ንጉሡ ግን ቅዱሱን በሰይፍ ሰንዝሮ ከ2 ከፈለው:: አካሉ መሬት ላይ ሲወድቅ ራሱ ግን በዓየር ላይ ሁና ለ3 ቀናት ትንቢትን ተናገረች:: ለዚያ አስጨናቂ የመከራ ዘመንም በር ከፋቹ ቅዱስ እስጢፋኖስ ካልዕ ሆነ::

ዐርፏል::

✞✞✞ ቸሩ አምላክ እንዲህ ለመንጋው የሚራሩ እረኞችን አይንሳን:: ከሐዋርያው: ከሰማዕቱና ከደጉ ፓትርያርክም ጸጋ በረከትን ይክፈለን::

🌹 ጥቅምት 9 ቀን የሚከበሩ
ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ ቶማስ ሐዋርያ
2.ቅዱስ እስጢፋኖስ ካልዕ (ሰማዕት)
3.ቅዱስ አትናስዮስ ብጹዕ
4.ቅዱስ ስምዖን ሰማዕት
5.ቅዱስ ሊዋርዮስ ሊቀ ዻዻሳት
6.ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሣርያ
7.ቅዱስ ቄርሎስ ሊቀ ዻዻሳት
8.አቡነ መዝገበ ሥላሴ ጻድቅ (ኢትዮዽያዊ)
9.አፄ ዳዊት ጻድቅ ንጉሠ ኢትዮዽያ (ግማደ መስቀሉን ያመጡ)

✞ ለመንጋው ምሳሌ ሁኑ እንጂ ማኅበሮቻችሁን በኃይል አትግዙ:: የእረኞችም አለቃ በሚገለጥበት ጊዜ የማያልፈውን የክብርን አክሊል ትቀበላላችሁ:: እንዲሁም ጐበዞች ሆይ! ለሽማግሌዎች ተገዙ:: ሁላችሁም እርስ በርሳችሁ እየተዋረዳችሁ ትሕትናን እንደ ልብስ ታጠቁ:: እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማልና:: ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣል:: ✞✞✞ (1ዼጥ. 5:3)

<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>

🌹✞ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ✞🌹

        https://t.me/Sinksar
        https://t.me/Sinksar
        https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

17 Oct, 19:36


✞ ስንክሳር ጥቅምት 8 ✞
🌿🌿🌿

እንኩዋን ለአበው ቅዱሳን "አባ አጋቶን ወአባ መጥራ" ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ።

" አባ አጋቶን ባሕታዊ "

ይህንን ቅዱስ የማያውቅ የቤተ ክርስቲያን ሰው ይኖራል ብየ አልገምትም:: እርሱ ታላቅ ጻድቅ: ገዳማዊና የእግዚአብሔር ሰው ሲሆን አንደበቱን ከክፋት ይከለክል ዘንድ ለ30 ዓመታት ድንጋይ ጐርሶ ኖሯል::

ይህንን ቅዱስ ሊቃውንት ሲገልጹት:
"ክምረ ክምር ጽድቁ እስከ አስተርአየ" ይሉታል:: ትእግስቱ: ደግነቱ: አርምሞው: ትሩፋቱ ከመነገር በላይ ነው:: በነበረበት በ4ኛው መቶ ክ/ዘመንም እንደ ኮከብ ያበራ ታላቅ አባት ነው::

ታላቁ ገዳማዊ ሰው አባ አጋቶን የታላቁ መቃርዮስ ቅዱስ ልጅ ነው:: ገዳመ አስቄጥስ እልፍ አእላፍ ቅዱሳንን ስታፈራ ይህ አባት ቅድሚያውን ይይዛል:: ምንም በብዛት የሚታወቀው በአርምሞው (በዝምታው) ቢሆንም ባለ ብዙ ትሩፋት አባት ነው::

የሚገርመው የቀደሙ አባቶቻችን የፈለገውን ያህል መናኝ ቢሆኑም የሰው ጥገኛ መሆንን አይፈልጉም:: "ሊሠራ የማይወድ አይብላ" የሚለውን መለኮታዊ ትዕዛዝ መሠረት አድርገው ከተጋድሎ በተረፈቻቸው ሰዓት ሥራ ይሠራሉ::

አንዳንዶቹ እንደሚመስላቸው ምናኔ ሥራ መፍታት አይደለምና ሰሌን: ዕንቅብ: ሠፌድ የመሳሰለውን ይሠፋሉ:: ታላቁ አባ አጋቶንም በአንደበቱ ድንጋይ ጐርሶ: በእግሮቹ ቀጥ ብሎ ቆሞ እንቅቦችን ይሠፋ ነበር::

ለነገሩስ ዛሬ ዛሬ እንኩዋን ወንዶቹ ሴቶችም ብንሆን ይህንን ሙያ እየረሳነው ነው:: ቅዱሱ ግን ይሰፋና ወደ ገበያ ይወጣል:: በጠየቁት ዋጋ ሽጦት አንዲት ቂጣ (ዻኩሲማ) ይገዛል:: የተረፈውን ገንዘብ ግን እዚያው ለነዳያን አካፍሎት ይመጣል እንጂ ወደ ገዳሙ አይመልሰውም::

ታዲያ አንድ ቀን እንደልማዱ የሠፋቸውን 5 እንቅቦች ተሸክሞ ወደ ገበያ ሲሔድ መንገድ ላይ አንድ ነዳይ (የኔ ቢጤ) ወድቆ ያገኛል:: እንደ ደረሰም ስመ እግዚአብሔር ጠርቶ ይለምነዋል:: አባ አጋቶን ከእንቅቦቹ ውጪ ምንም ነገር አልነበረውምና "እንቅቡን እንካ" አለው::

ነዳዩ ግን ወይ የሚበላ: ካልሆነም ገንዘብ እንደሚፈልግ ይነግረዋል:: ወዲያው ደግሞ "የምትሠጠኝ ነገር ከሌለህ ለምን ወደ ገበያ ተሸክመህ አትወስደኝም?" አለው:: የነዳዩ አካል እጅግ የቆሳሰለ በመሆኑ እንኩዋን ሊሸከሙት ሊያዩትም የሚከብድ ነበር::

ጻድቁ ግን ደስ እያለው: ያለማመንታት አንስቶ ተሸከመው:: ከረጅም መንገድ በሁዋላም ከገበያ በመድረሳቸው አውርዶ ከጐኑ አስቀመጠው:: ያ ነዳይ አላፊ አግዳሚውን ሁሉ ቢለምንም የሚዘከረው አጣ:: አባ አጋቶን አንዷን እንቅብ ሲሸጥ "ስጠኝ?" ይለዋል:: ጻድቁም ይሠጠዋል::

እንዲህ "ስጠኝ" እያለ የ5ቱንም እንቅቦች ዋጋ ያ ነዳይ ወሰደበት:: አባ አጋቶን ግን ምንም ቂጣ ባይገዛ: በሆነው ነገር አልተከፋምና ሊሔድ ሲነሳ ነዳዩ "ወደ ቦታየ ተሸክመህ መልሰኝ" አለው:: አባቶቻችን ትእግስታቸው ጥግ (ዳር) የለውምና ጐንበስ ብሎ በፍቅር አንስቶት አዘለውና ሔደ::

ካነሳበት ቦታ ላይ ሲደርሱ ይወርድለት ዘንድ ጻድቁ ቆመ:: ነዳዩ ግን አልወርድም አለ:: መቼም እኛ ብንሆን ብለን እናስበውና . . . ምን እንደምናደርግ ይታወቃል:: ጻድቁ ግን ዝም ብሎ ቆመለት::

ትንሽ ቆይቶ ግን ስለ ለቀቀው ሊያየው ዞር ቢል መሬት ላይ የለም:: ቀና ሲል ግን ያየውን ነገር ማመን አልቻለም:: ደንግጦ በግንባሩ ተደፋ:: ነዳይ መስሎ እንዲያ ሲፈትነው የነበረው ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ነበር::

ክንፎቹን ዘርግቶ: በብርሃን ተከቦ: በግርማ ታየው:: ከወደቀበትም አነሳው:: "ወዳጄ አጋቶን! ፍሬህ: ትእግስትህ: ደግነትህ ግሩም ነውና ዘወትር ካንተ ጋር ነኝ" ብሎት ተሰወረው:: ጻድቁም በደስታ ወደ በዓቱ ሔደ:: አባ አጋቶን ተረፈ ዘመኑን በአርምሞ ኑሮ ዐርፏል::

🌿" ቅዱስ መጥራ አረጋዊ "🌿

ቅዱሱ የ3ኛው መቶ ክ/ዘመን ክርስቲያን ሲሆን በትውልድ ግብጻዊ ነው:: ከልጅነት እስከ እውቀት: ከእውቀት እስከ ሽበት ክርስቶስን ሲያመልክ ኑሯል:: ዘመኑ ክርስቲያኖች ስለ ሃይማኖታቸው ከባዱን ዋጋ (ሕይወታቸውን) የሚከፍሉበት ነበር::

በወቅቱ ብርቱ የቤተ ክርስቲያን ጠላቶች ቢበዙም ብርቱ መንፈሳዊያን ተዋጊ ክርስቲያኖች ነበሩና ውጊያው ተመጣጣኝ ነበር:: ዛሬ ደግሞ ሁሉም በዛለበት ዘመን ላይ ተገኝተናል::

ቅዱስ መጥራ ካረጀ በሁዋላ ነገሥታቱ "ክርስቶስን ካዱ" እያሉ መጡ:: ቅዱሱ ወሬውን ሲሰማ እጅግ ተገረመ:: ምክንያቱም መድኃኔ ዓለምን መካድ ፈጽሞ የሚታሰብ ነገር አይደለምና:: ቅዱሱ አረጋዊ ስለ 2 ነገር ሰማዕትነትን ፈለገ::

አንደኛ በክርስቶስ ስም መሞት የክብር ክብርን ያስገኛልና ከዚሁ ለመሳተፍ ነው:: ሁለተኛው ግን ለወጣቶች አብነት (ምሳሌ) ለመሆን ነበር:: መልካም መሪ ባለበት ዘንድ ብዙ ፍሬዎች አይጠፉምና:: ቅዱስ መጥራ እንዳሰበው ወደ መኮንኑ ሒዶ በአሕዛብ ፊት ክርስቶስን ሰበከ:: ስለዚህ ፈንታም ብዙ አሰቃይተው በዚህች ቀን ከተከታዮቹ ጋር ገድለውታል::

አምላከ ቅዱሳን ትእግስታቸውን ያሳድርብን:: ከአባቶቻችንም በረከትን ይክፈለን::

ጥቅምት 8 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.አባ አጋቶን ባሕታዊ
2.ቅዱስ መጥራ አረጋዊ (ሰማዕት)
3.ቅድስት ሶስናና ልጆቿ (ሰማዕታት)
4.አባ ሖር
5.ቅድስት በላግያ ሰማዕት

=>ወርሐዊ በዓላት
1.ቅዱስ ሙሴ ሊቀ ነቢያት
2.ኪሩቤል (አርባዕቱ እንስሳ)
3.አባ ብሶይ (ቢሾይ)
4.አቡነ ኪሮስ
5.አባ ሳሙኤል ዘደብረ ቀልሞን
6.ቅዱስ ማትያስ ሐዋርያ (ከ12ቱ ሐዋርያት)

"ጸሎቴን በፊትህ እንደ እጣን ተቀበልልኝ::
እጅ መንሳቴም እንደ ሠርክ መስዋዕት ትሁን::
አቤቱ ለአፌ ጠባቂ አኑር:: የከንፈሮቼንም መዝጊያ ጠብቅ:: ልቤን ወደ ክፉ ነገር አትመልሰው::
ለኃጢአት ምክንያት እንዳልሠጥ::
ከምርጦቻቸውም ጋር አልተባበር::
ጻድቅ በምሕረት ይገሥጸኝ: ይዝለፈኝም::
" (መዝ. 140:2)

✍️† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †✍️
🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇

https://t.me/Sinksar
https://t.me/Sinksar
https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

17 Oct, 10:04


🌸ፍትሐ_ነገሥት ክፍል ፳፰

🌻አንቀጽ ፴፱ - በእንተ ተአምኖ -
ራሱን የቻለ አካለ መጠን ያደረሰ ሰው በእውነት በደሉን ቢናገር ኃጢአት ስለሠራ ንስሓ ይገባዋል፡፡
                        🌻አንቀጽ ፵
        በእንተ ዘይትረከብ እምዘተኀጥአ
አንድ ሰው የጠፋ ገንዘብን ቢያገኝ ካገኘበት ቦታ እስከ ሰባት ቀን ያስመርምር፡፡ በየገበያው በየአደባባዩ ያስመርምር፡፡ ባለገንዘብ ነኝ ያለ ሰው ከመጣ የጠፋውን ገንዘብ ተለይቶ የሚታወቅበት መልኩን ይናገር፡፡
                      🌻አንቀጽ ፵፩
                 በእንተ ዘይኤዝዝ በንዋዩ
ይህ አንቀጽ መዋቲ ለወራሲ ወይም ለሌላ ሰው ስለሚያዝዘው ንብረት ይናገራል፡፡ መዋቲ ከተወው ገንዘብ አስቀድሞ የመግነዝ ዋጋ፣ መቃብር ለሚቆፍሩ ሰዎች ዋጋ ማወጣጣት ይገባል፡፡ የአብድ የዝንጉዕ ትእዛዙ አይጸናም፡፡ አዛዚ የሚያዝበትን ገንዘብ እንጂ የማያዝበትን ገንዘብ ቢያዝ ትእዛዙ አይጸናም፡፡ ንብረቱን ሁለት እጅ ለልጆቹ ሲሶውን ለሰብአ ቤተ ክርስቲያን ርቦውን ለዘፈቀደ ብሎ ያዝዝ፡፡ ክርስቲያን ሰው ድኅነተ ነፍስ በሌለበት ገንዘቡን መበተን አይገባውም አለ ለዘዋሪ ለአዝማሪ ለመሸታ ለጋለሞታ መበተን አይገባውም፡፡
                     🌻አንቀጽ ፵፪
                        በእንተ ርስት
ለራሱ መታሰቢያ ሊሆነው ከሞተው ሰው ገንዘብ ለነዳያን ስጡ፡፡ ዕለተ ሞቱ ለደረሰበት ሰው በፍርድ ቀን ዋጋ ሊሆነው ከገንዘቡ ለነዳያን ማዘዝ ይገባዋል፡፡ አበዳሪ ወይም ሌላ ባለዕዳ ከሟቹ ዘጠኝ ቀን አስቀድሞ መጠየቅ አይገባውም፡፡ የመዋቲ ሚስት ከባሏ ወራሾች ጋራ እኩሌታውን ገንዘብ ትካፈል፡፡ ልጆቿ ቢሆኑ ግን ከልጆቿ እንደ አንዱ ሆና ትካፈል፡፡ ልጆችም ተካክለው ይካፈሉ፡፡ በእናት በኩል ካለ ዘመድ በአባት በኩል ያለ ዘመድ አስቀድሞ ይውረስ፡፡ ቅርብ ዘመዶች ይውረሱ፡፡ ከዚያ ሩቅ ዘመዶች ሊወርሱ ይገባል፡፡ ከዘመዶቹ ውጭ የሆነ የታዘዘለት ሰው ካለም ይውረስ፡፡ አባት እናት የልጃቸውን ገንዘብ ከወንድሙ ከእኅቱ በልጠው ቀድመው መውረስ ይገባቸዋል፡፡ ከአባት አስቀድሞ አያት ከልጅ አስቀድሞ የልጅ ልጅ ከወንድም አስቀድሞ አጎት መውረስ አይገባቸውም፡፡ ባል የሚስቱን ገንዘብ መውረስ ይገባዋል፡፡ አወራረስ ከላይ ወደታች ማለትም ከአባት ወደ ልጅ ከልጅ ወደ የልጅ ልጅ ይወርዳል፡፡ ወደታች ልጅ የልጅ ልጅ ቢታጣ ግን ወደላይ ይወጣል፡፡ መውረስ የሚገባው ከሕግ ሚስት የተወለደ ነው፡፡ መውረስ ለቅርብ ዘመድ ሊሆን ይገባል፡፡ ለመዋቲ እናት አባት ባይኖሩ ወንድ አያቱ ሴት አያቱ ከወንድሞቹ ከእኅቶቹ ጋራ ይውረሱ፡፡ ከወንድም ልጆች ወንድም ይቀርባል፡፡ በጎንና በጎን ካሉ ከአጎት ከአክስት ወደላይ ያሉ አያቶች ይቀድማሉ፡፡ ወራሽ የሌለው ሰው ገንዘቡ ለመንግሥት ይሁን፡፡ በገንዘቡ ያዝበት ዘንድ የወደደውንም ያደርግበት ዘንድ ለወደደውም ያወርስ ዘንድ የኤጲስ ቆጶሱና የቤተክርስቲያኑ ገንዘብ ተለይቶ የታወቀ ይሁን፡፡ ኤጲስ ቆጶስ ከተሾመ በኋላ ያገኘው ገንዘብ ከሞተ በኋላ ለቤተ ክርስቲያን ይሁን፡፡ ምንም ቢያዝለት ኢአማኒ አማኒውን አይውረሰው፡፡ አውራሹን የገደለ አይውረስ፡፡
                     🌻አንቀጽ ፵፫
                       በእንተ ፈታሒ
በሀገር ተሰብስቦ ሲኖሩ ጸብ አይቀርም፡፡ ተጣልቶም ዕርቅ አይቀርም፡፡ ይህም ያለዳኛ አይፈጸመም፡፡ ዳኛ ግብሩ ጠባዩ ያማረ ሊሆን ይገባዋል፡፡ ፈጣሪያችሁ እግዚአብሔር በሰጣችሁ ሀገር ሁሉ ሹም ሹሙ፡፡ ዳኛ በፍርድ ጊዜ የማያዳላ፣ መማለጃ የማይቀበል ሊሆን ይገባዋል፡፡ ዳኛ አካለ መጠን ያደረሰ ከሠላሳ በላይ ዓመት የሆነው ወንድ ይሁን፡፡ ዳኛ የተማረ ይሾም እንጂ ያልተማረ አይሾም፡፡ ዳኛ ኦርቶዶክሳዊ ምእመን ሊሆን ይገባል፡፡ ዳኛ ከነውር ከነቀፋ የራቀ፣ ብልህ አዋቂ፣ በቁጣ ጊዜ የሚታገሥ፣ እግዚአብሔርን የሚፈራ ሊሆን ይገባዋል፡፡ ዳኛ ጆሮው የማያከራክረው ዓይኑ የሚያስተውል፣ አንደበቱ የበረታ፣ የሕዝቡን ቋንቋ የሚያውቅ፣ መጽሐፍ አዋቂ ይሁን፡፡ ምስክሮችን መመርመር ይገባል፡፡ ከሐሰት ንጹሓን የሆኑ፣ የታመኑ፣ ደጋግ እንደሆኑ መመርመር ይገባል፡፡ በሐሰት ከፈረዳችሁት ፍርድ የተነሣ ለቅጣት የተዘጋጃችሁ እንዳትሆኑ ረበናትን ከመምሰል ተጠበቁ፡፡ ዳኞች ፍርዳችሁ እውነት ቢሆን በዚህ ዓለምም በወዲያኛው ዓለምም በእውነት ዋጋችሁን ከእግዚአብሔር ታገኛላችሁ፡፡ ዳኛ ተቆጥቶ ሳለ፣ ፈርቶ ሳለ፣ አዝኖ ሳለ፣ ደስ ብሎት ሳለ፣ ተርቦ ሳለ፣ ተጠምቶ ሳለ፣ ታሞ ሳለ፣ አንቀላፍቶት ሳለ፣ ሰንፎ ደክሞ ሳለ፣ ሰክሮ ሳለ፣ ሰልችቶት ሳለ አይፍረድ፡፡ ዳኛ ሳይፈርድባችሁ ባላጋራ ሳያወርድባችሁ አትማሉ፡፡ መሓላ በጸብ በክርክር ጊዜ በግድ ያለውድ ይሻል፡፡ በፈራሽ በተርታ ነገር ስመ እግዚአብሔርን ጠርተህ አትማል፡፡ ከካህናት ወገን በሐሰት ስመ እግዚአብሔርን ጠርቶ የማለ ሰው ሦስት ዓመት ይለይ፡፡ በምትፈርዱበት አደባባይ ክርስቶስ ከእናንተ ጋር እንዳለ ዕወቁ፡፡ ፍርድ ለመፍረድ ከቤተ እግዚአብሔር ገብቶ መቀመጥ አይገባም፡፡ በቤተ ክርስቲያን ፀብ ክርክር ጩኸት ሊደረግበት አይገባም፡፡ ዳኞች በዕለተ እሑድ መፍረድ መቅጣት አይገባቸውም፡፡ በዕለተ እሑድ የተጣሉትን ብታስታርቁ ብፁዓን ገባርያነ ሰላም ከተባሉት ትቆጠራላችሁ፡፡ የአንዱን ቃል ሰምታችሁ ባላጋራ ሳይመጣ አትፍረዱ፡፡ ከሁሉ ጋር ለመስማማት ቸኩል፡፡ እግዚአብሔር የይቅርታ የርኅራኄ ባለቤት ነው፡፡ ክርስቲያናዊ ወደአሕዛብ ዳኛ መሔድ አይገባውም፡፡ ይፈርዱለት ይፈርዱበት ዘንድ ወደ ሸሁ ወደ ቃልቻው መሔድ አይገባውም፡፡ በካህናቱ የሚፈረደውን ፍርድ ወደመኳንንት አይውሰዱት፡፡ የሚመሰክሩ ሰዎች እውቀት ያነሳቸው አይሁኑ፡፡ ኢአማኒ በአማኒ መመስከር አይገባውም፡፡ ኻያ ዓመት ያልሆነው ሕፃንም አይመስክር፡፡ በሐፃኒ በመጋቢ እጅ ያለ ሰውም አይመስክር፡፡ አውቆ አበድ አይመስክር፡፡ ዲ*ዳ አይመስክር፡፡ የዕለት ራት የጣት ቀለበት የሌለው ድኻ አይመስክር፡፡ ሎሌ ለጌታው ጭፍራ ለአለቃው አይመስክር፡፡ ሰካራም አይመስክር፡፡ ሰው ለራሱ ሊመሰክር አይገባም፡፡ በራሱ ላይ መመስከር ግን ይችላል፡፡ ዘመድ ለዘመዱ መመስከር አይገባውም፡፡ ሰው በጠላቶቹ መመስከር አይገባውም፡፡ አበዳሪ በተበዳሪ መመስከር አይገባውም፡፡ በኤጲስ ቆጶስ ላይ የመ*ና*ቃ*ንን ምስክርነት መቀበል አይገባም፡፡ የአንዱን ኤጲስ ቆጶስ ምስክርነት በአንዱ ኤጲስ ቆጶስ አይቀበሉት፡፡ በወንድሞቻቸው ቀንተው ክፉ ነገሩን ወደው በሐሰት የሚመሰክሩ ብዙ ናቸውና ሰውን ሁሉ በምስክርነት አይመኑት፡፡ ነገራቸው እውነት ቢሆን ነው እንጂ እውነት ካልሆነ ምስክሮችን ብዙ ናቸው ብለው ሊያምኗቸው አይገባም፡፡
 
© በመ/ር በትረ ማርያም አበባው
         ክፍል-፳፱- ይቀጥላል. . .
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
               🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

17 Oct, 09:57


የተመሳሳይ ጾታ አፍቃሪያን የጸደቀውን ሕግ በጽኑ አውግዘውታል። እርምጃው የጣሊያኗ ጠቅላይ ሚንስትር ጆርጂና ሜሎኒ ድጋፍም አለበት ተብሏል።
ራሳቸውን እንደ ክርስትያን እናት የሚቆጥሩት ጠቅላይ ሚንስትሯ፣ ልጆች መወለድ ያለባቸው ከወንድ አባት እና ሴት እናት ብቻ ነው ብለው ያምናሉ።
ሜሎኒ ቀደም ሲል ስለማሕጸን ኪራይ አላስፈላጊነት ሲናገሩ ተሰምተው ነበር።
በምርጫ ቅስቃሳቸው ወቅትም የተመሳሳይ ጾታ ጋብቻን የማይደግፍ እንቅስቃሴ ሲያደርጉ ነበር።
በ2023 የእርሳቸው መንግሥት ከተመሳሳይ ጾታ የተገኙ ልጆችን እንዳይመዘገብ ለሚላን ከተማ ትዕዛዝ ሰጥቶ ነበር።
ጠቅላይ ሚንስትር ሜሎኒ የማሕጸን ኪራይ የፈጣሪን ጸጋ እና ብቸኛ ስልጣን በገንዘብ መግዛት እንደሚቻል ለማሰየት የሚሞክር ማጭበርበር ነው ብለው ያምናሉ።
ጠቅላይ ሚንስትሯ ብቻ ሳይሆኑ ምክትላቸው ማቴዮ ሳልቪኒም የማሕጸን ኪራይን በጽኑ አውግዘውታል። “ሴቶችን እንደ ኤቲኤም ማሽን የሚቆጥር ድርጊት ነው” ብለውታል።
ቢቢሲ ያነጋገራቸው ባለሙያ እንደሚሉት የማህጸን ኪራይ ከሚፈጽሙት 90 በመቶ የሚሆኑት የተቃራኒ ጾታ ጥንዶች ናቸው።
የማሕጸን ኪራይን በተመለከተ የተለያዩ አገራት የተለያየ ሕግ አላቸው። ፈረንሳይ፣ ስፔን፣ ጣሊያን እና ጀርመን የማሕጸን ኪራይን በሕግ የከለከሉ የአውሮፓ አገራት ናቸው።
በዩናይትድ ኪንግደም የማሕጸን ኪራይ ቢፈቀድም ጽንሱን ለምትሸከመው ሴት የተጋነነ ክፍያ መፈጸም ክልክል ነው። በአየርላንድ፣ ሆላንድ፣ ቤልጂየም እና ቼክ ሪፐብሊክ ፍርድ ቤት ስለማሕጸን ኪራይ ውሳኔ አይሰጥም።
ግሪክ ደግሞ የውጭ አገር ሰዎች የማሕጸን ኪራይ ቢፈጽሙ በሕጋዊነት ትቀበላቸዋለች። ነገር ግን ማሕጸን የምታከራየዋ ሴት ትዳር የሌላት መሆኗ መረጋገጥ አለበት።
አሜሪካ እና ካናዳ ለተመሳሳይ ጾታ ጥንዶች የማሕጸን ኪራይን የሚፈቅዱ ሲሆን ጥንዶቹ ከውልደት ጀምሮ የወላጅነት መብትም ያገኛሉ።

BBC

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

17 Oct, 09:56


ጣሊያን ጥንዶች ለማሕጸን ኪራይ ወደ ውጭ አገራት እንዳይሄዱ ከለከለች

ክፍል-፩-
ጣሊያን፤ ጥንዶች ማሕጸን ለመከራየት ወደ ውጭ ሀገራት እንዳይሄዱ የሚከለክል ሕግ በማጽደቅ ድርጊቱ በወንጀል የሚያስቀጣ መሆኑን ገልጻለች።
ጣሊያን ያገደችው ጥንዶች ወይም የፍቅር አጋሮች ልጅ ለመውለድ ሲባል ወደ ውጭ አገር በመጓዝ በገንዘብ በመደራደር ከሌላ ሴት ማሕጸን እንዳይከራዩ የሚያስችል ነው።
ወደ ውጭ አገራት በመሄድ የማሕጸን ኪራይ ከሚፈጽሙት በተጨማሪ በአገር ውስጥም ተመሳሳይ ድርጊት እንዳይፈጸም እገዳ ጥላለች።
ይህንን ክልከላ ተላልፈው የተገኙ ግለሰቦች እስከ ሁለት ዓመት እስራት እና አንድ ሚሊዮን ዩሮ ቅጣት እንደሚጣልባቸው ተገልጿል።
በጣሊያን ወግ አጥባቂ ፓርቲ የረቀቀው ይህ ሕግ፣ ብዙ ትችቶችን እያስተናገደ ነው። ተችዎቹ የጸደቀው ሕግ በተለይ የተመሳሳይ ጾታ አፍቃሪያንን ዒላማ ያደረገ ነው ብለውታል።
የማሕጸን ኪራይ ማለት በመካንነት ወይም በሌላ ምክንያት መውለድ የማይችሉ ሰዎችን ጽንስ ሌላ ሴት በማሕጸኗ እንድታሳድግ ማድረግ ነው።
ይህንን ድርጊት መውለድ የተሳናቸው ተቃራኒ ጾታዎች ብቻ ሳይሆኑ ወንድ ጥንዶችም [የተመሳሳይ ጾታ አፍቃሪያን] ይፈጽሙታል።
በጣሊያን ሕጉ የጸደቀው በአብላጫ ድምጽ ረቡዕ [06/02/2017 ዓ.ም] ነው። ሕጉ ከመጽደቁ በፊት ረቂቁ ከፍተኛ ተቃውሞ ገጥሞት ነበር።
በተለይ ሰዎች በአገሪቱ ቤተሰብ አልባ መሆናቸው እና የወሊድ መጠን እያሽቆለቆለ መሆኑን በመጥቀስ ሕጉ እንዳይጸድቅ የሞገቱ በርካቶች ቢሆኑም በ84 ድጋፍ እና በ58 ተቃውሞ የአገሪቱ ሕግ ሆኖ እንዲጸድቅ ተደርጓል።

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

17 Oct, 05:51


🌹ስንክሳር ጥቅምት 7 🌹
✞ እንኩዋን ለታላቁ ገዳማዊ "ቅዱስ አባ ባውላ" ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ።

🌿"አባ ባውላ መስተጋድል "🌿

ቅዱሱን የመሰሉ አባቶች "መስተጋድላን" ይባላሉ በግዕዙ:: ለሃይማኖታቸው እስከ ደም ጠብታና እስከ መጨረሻዋ ህቅታ ድረስ መጋደላቸውን የሚያሳይ ነው:: መጋደል ጐዳናው ብዙ ዓይነት ነው::

ከራሱ ጋር የሚጋደል አለ:: ከዓለም ጋር የሚጋደልም አለ:: የቅዱሳኑ ተጋድሎ ግን በዋነኝነት ከ2 አካላት ጋር ነው:: በመጀመሪያ ፍትወታት እኩያትን (ኃጣውዕን) ከሚያመጡ አጋንንት ጋር ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ "ሃይማኖቸታችሁን ካዱ: ለጣዖትም ስገዱ" ከሚሉ ከሃድያን ጋር የሚደረግ ትግል ነው::

በተለይ 2ኛው እስከ ሞት የሚያደርስ ውሳኔን ይጠይቃል:: ታላቁ አባ ባውላ ገዳማዊ ጻድቅ እንደ መሆኑ ትግሉ የነበረው ከአጋንንት ጋር ነው:: የዚህን ቅዱስ ሕይወት ለመረዳት ግን አንድ ነገርን ልብ እንድትሉልኝ እፈልጋለሁ::

ያለንበት ዘመን ክርስትና በራድ (ቀዝቃዛ) በመሆኑ የቀደሙ አባቶች የጸና ተጋድሎ አንዳንዴ ግራ ሲያጋባን ተመልክቻለሁ:: ቅዱሳኑ ሁሌም አንድ ነገርን እያሰቡ ይኖራሉ:: ይኼውም በዘመኑ በርካቶቻችን የረሳነው: ወይም ማስታወስ የማንፈልገው ነገር ይመስላል::

ሰማያዊው አምላክ ከዙፋኑ ወርዶ በተዋሐደው ሥጋ በቃል ሊገለጽ የማይችል መከራን ስለ እኛ ተቀብሏል:: ክርስትና ማለት ቀራንዮን በልብ ውስጥ መሳል ነው:: ፍቅረ መስቀሉን: የጌታንም ውለታ የሚያስብ ማንኛውም ሰው: የትኛውም ዓይነት መከራ ቢመጣበት አይታወክም::

ቅዱሳኑም የፍቅራቸውና የትእግስታቸው ምሥጢር ይኼው ነው:: ጌታ "የሚወደኝ ቢኖር የሞቱን መስቀል ተሸክሞ ይከተለኝ" (ማቴ. 16:24) እንዳለው: ቅዱሳኑ ይህንን ቃል በቃል ሲፈጽሙት እነሆ እንመለከታለን::

ታላቁ አባ ባውላ የተወለደው በላይኛው ግብጽ አካባቢ ሲሆን ዘመኑም 4ኛው መቶ ክ/ዘመን ነው:: ከክርስቲያን ወላጆቹ መንፈሳዊ ነገሮችን ተምሮ በወጣትነቱ መንኗል:: ያ ዘመን እልፍ አእላፍ ቅዱሳን የነበሩበት ነውና ወደ ጠመው አካባቢ ሔዶ ምናኔን ተምሯል::

ሥርዓተ ገዳምን ማለትም:- አገልግሎትን: ፍቅርን: ተጋድሎንና የመሳሰሉትን ከተማረ በሁዋላም ደቀ መዝሙሩን አባ ሕዝቅኤልን አስከትሎ ለዋናው የተጋድሎ ሕይወት ወደ በርሃ ወጣ:: አባ ባውላ ዘወትር በፍቅረ ክርስቶስ ይመሰጥ ነበርና የተጋድሎ ምርጫው ልዩ ሆነ::

አንድ ቀንም እንዲህ ሲል አሰበ:- "ጌታ ሆይ! አንተ ለእኛ ለኃጥአን ኃፍረተ መስቀልን ታግሠህ: ሞትን ከሞትክልን እኛ ደግሞ ስለ ንጹሑ አምላክ ስንል እልፍ ሞትን መታገስ አለብን::"

ይህንን ብሎ ከወትሮው በተለየ መንገድ ሊጋደል ጀመረ:: በዚህ እጅግ የጸና ተጋድሎው ምክንያትም 7 ጊዜ ሙቶ 7 ጊዜ ተነሳ::

👉1.እግሩን ከረዥም ዛፍ ላይ አስሮ: ወደ ታች ተዘቅዝቆ ይጸልይ ጀመረ:: እህልም: እንቅልፍም: ዕረፍትም አልነበረውምና ደሙ በአፍ: በአፍንጫው ፈሶ አለቀ:: እንዲህ በሆነ በ40ኛው ቀንም ሞተ:: መልአከ እግዚአብሔር መጥቶ ከሞት አስነሳው::

👉2.ጥልቅ ባሕር ውስጥ ሰጥሞ እንዳስለመደ ይጸልይ ጀመረ:: ከባሕሩ ሳይወጣ: ከቆመ ሳያርፍ: ከዘረጋም ሳያጥፍ ለ40 ቀናት ጸለየ:: በዚያው ሳለም ለ2ኛ ጊዜ ሞተ:: ቅዱስ መልአክ መጥቶ ከሞት አስነሳው::

👉3.እርሱ በሚኖርበት ጠመው አካባቢ ረዥም ተራራ ነበርና ወደዚያ ወጣ:: ከተራራው ጫፍ ሆኖ ወደ ታች ተመለከተ:: የተጠራረቡ ድንጋዮች በየመንገዱ ተሰልፈው ነበር:: በዚያች ቅጽበት የጌታ ኅማማት ከፊቱ ቢደቀንበት ከላይ ወደ ታች ተወርውሮ ሔደ::
በየመንገዱ ያሉት ጥርብ ድንጋዮች ቢቀበሉት አካሉ እየተነተፈና እየተቆራረጠ በየመንገዱ ቀረ:: በዚህም ሞተ:: አሁንም ፈጣሪው ከሞት አስነሳው::

👉4.አንድ ቀን ደግሞ (ዕለቱ ዓርብ ነበር) የጌታን ኅማማት እያሰበ የሚያደርገው ጠፋው:: ከቆመበት አካባቢ ትልቅ ዛፍ ነበርና ወደዚያ ወጥቶ ሲመለከት ከመሬት ላይ የተነጠፈ ትልቅ ድንጋይ አየ:: ከላይ ወደ ታች ሲወድቅና ድንጋዩ ላይ ሲያርፍ ለሁለት ተከፍሎ ሞተ:: አሁንም በፈጣሪ ትዕዛዝ ተነሳ::

👉5.በሌላ ቀን ደግሞ በዕለተ ዓርብ ጭንቅላቱን ከእግሩ ጋር አሥሮ ይጸልይ ገባ:: ያለ ምንም እህል: ውሃና እንቅልፍ ለ40 ቀናት ቆይቶ ሞተ:: እንደገናም ተነሳ::

👉6.እጅግ ሊመለከቱት እንኩዋ በሚከብድ የጉድጉዋድ ውሃ ውስጥ ገብቶ ለ40 ቀናት እጆቹን ዘርግቶ ቢጸልይ ከጭንቁ ብዛት ነፍሱ ከሥጋው ተለየች::

👉7.አንድ ቀንም እንደዚሁ የጌታን ሕማማት እያሰበ ወደ ጽኑ ቆላ ወረደ:: በአካባቢው ከአሸዋ በቀር ምንም አልነበረምና ቆሞ ሲጸልይ አሸዋው ውጦ ደፈነውና ለ7ኛ ጊዜ ሞተ:: በዚህ ጊዜ ግን ሊያስነሳው የመጣው እንደ ወትሮው ቅዱስ መልአክ ሳይሆን ራሱ የክብር ባለቤት መድኃኒታችን ክርስቶስ ነበር::

ጌታችን አባ ባውላን ከሞተበት አስነስቶ:- "ወዳጄ ባውላ! ስለ እኔ ፍቅር እጅግ ተሰቃየህ" አለው:: ቅዱሱ ግን "ጌታየ ሆይ! የእኔ መከራ በአንተ መከራ ሲታሰብ ኢምንት ነውና እባክህ ስለ ስምህ ሌሎች መከራዎችን እንድቀበል ፍቀድልኝ? ገና ሕማምህን አስቤ አልረካሁምና" አለው::

ጌታ ግን "የለም! መከራው ይበቃሃል:: መጥቼ እስክወስድህ ድረስ ከአባ ብሶይ ጋር ቆይ" ብሎት: ባርኮት ዐረገ:: አባ ባውላም እንደ ታዘዘው በአባ ብሶይ ገዳም ከቅዱስ ብሶይ ጋር ቆይቶ በዚህች ቀን ዐርፏል::

ይህቺውም ዕረፍቱ ለ8ኛ ጊዜ ሆና ተቆጥራለች:: የቅዱሱን ዜና የጻፈው ደቀ መዝሙሩ አባ ሕዝቅኤል ሲሆን ያሰፈረው እንባው እንደ ዥረት እየወረደ ነው:: አባቶቻችን ሊቃውንትስ ታላቁን ጻድቅ ሲያመሰግኑት እንዲህ አይደለምን!
"ውስተ ገድል ጽኑዕ ዘአልቦ ምምዐ:
ወደቀ ስብአ: ወተንሳእከ ስብአ::"

አምላከ አባ ባውላ በጻድቁ ላይ ያሳደረውን ፍቅሩን ያሳድርብን:: ከበረከቱም ያድለን::

🌹ጥቅምት 7 ቀን የሚከበሩ
ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.አባ ባውላ መስተጋድል
2.አባ ሕዝቅኤል ጻድቅ
3.ቅዱስ ሚናስ ሰማዕት
4.ቅዱስ ሐናሲ ሰማዕት

ወርሐዊ በዓላት
1.ሥሉስ ቅዱስ (አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ)
2.አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
3.አባ ሲኖዳ (የባሕታውያን አለቃ)
4.አባ ዳንኤል ዘገዳመ ሲሐት
5.አባ ባውላ ገዳማዊ
6.ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ
7.ቅዱስ አግናጥዮስ (ለአንበሳ የተሰጠ)

<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>

👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇

       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

16 Oct, 15:39


#ከተሜው_ልብህን_አጽና!

ቀቢጸ ተስፋ የዲያብሎስ ኃጢአት ናት። በጊዜው፣ በሥርዓቱ፣ በወቅቱ፣ በኑሮው..ሰበብ እያደረጉ ተስፋ መቁረጥ ትልቅ በደል ነው።

ሁሉንም ነገር መቀደስ እየቻልነ ያረከስነው እኛው ነን።ሁሉም እኛ ስናከፋው ይከፋል እኛ ስንለውጠው ይለወጣል። ጨው እንድንሆን ተነግሮናል።"እናንተ የምድር ጨው ናችሁ ጨው አልጫ ቢሆን ግን በምን ይጣፍጣል?"ማቴ.፭፥፲፫ ተብሎ ታዲያ እኛው ጨው ሁነን ሟሙተን ያላጣፈጥነውን ለውጥ ከየት እናመጠዋለን? ተስፋ ለመቁረጥ የሚያበቃን ጨው ሁነን ምን ሠርተን ነው?

የዲያብሎስ ኃጢአቱ፦ሴሰኝነት፣ሱስ፣ሆድ አይደለም።ቀቢጸ ተስፋ እና ተዕቢት ነው።በትዕቢት ላይ ቀቢጸ ተስፋ ሲጨመር ጨለማውን አስቡት።

ቀቢጸ ተስፋ፦በምድር ዓላማን ታስታለች በሰማይ ተስፋ ድኂንን ታጠፋለች።

ለምን ተስፋ እንቆርጣለን?
የምንመገበው ስላጣነ ነውን?
ሥርዓቱ ስላስጨነቀን ነውን?
ኑሮ ስለከበደን ነውን?
የምንፈልገው ውጤት ስለቀረብን?
ወይስ ከራስ ወዳድነታችን የተነሣ?
ወይስ የሞት ድምጽ ከበራችን ሁል ጊዜ ስለሚጮህብን?

ገዢዎች ሰላም ስላሳጡን?...
የምንችለውን ስለማናውቀው ወይም ስለማናደርገው ነው እንጂ በየትኛውም የሕይወት ጥያቄ አይነት ውስጥ ሁሉ ቀዳሽነታችንን ሊያሳጣን የሚችል ነገር አልነበረም።

ይሄ ሁሉ ከምን መጣ? እንዴት ልለውጠው? እንዴት ድርሻየን ልወጣ? እንዴት ጨው ልሁን? እንዴት ልቀድሰው? እንድንል ያደርጋል እንጂ ተስፋ አያስቆርጥም።

ተስፋ መቁረጥ የሚባል ደዌ በልቡናው የዞረበት ሰው ሁሉ ይጨልምበታል።ዓይኑ ጨለማ ጉልበቱ ቄጤማ ይሆናል።የሚችለው ነገር ሁሉ ያለ አይመስለውም። ትዝ የሚለው፦ራሱን ማጥፋት፣መሰደድ፣ለተለያየ ሱስ መዳረግ፣ሰውን መጥላት፣ሥራ መፍታት፣ቁጭ ብሎ መቆዘም፣ወይም ራስን በኃጢአት መድፈቅ፣ መታወክ፣ መደበር፣ መቀባጠር፣..የመሳሰለው የቀቢጸ ተስፋ ሠራዊቶች ሁሉ ይዘምቱበታል።

ጠላት የሚመለሰው ባጭር ታጥቆ፣ጦር ሰብቆ፣ጋሻ ነጥቆ እንደሆነ ሁሉ ወገብ ልቡናችንን በተቀደሰ ተስፋ ታጥቀን፣ዓላማን እንደ ዝናር ጠምጥመን፣ተግባርን እንደ ጦር ጨብጠን፣ ትዕግሥትን እንደ ጋሻ መክተን፣እንደ ጨው ሟሙተን፣እንደ አጃ ተፈትገን፣ቀቢጸ ተስፋን ተዋግተን ራስን ነጻ ማድረግ እና ሁሉን እንደሚገባው መለወጥ ስንችል ነው።

የቱ ይሻላል? ተስፋ ቆርጦ ዝም ማለት? ወይስ የብዙዎች ተስፋን ለመቀጠል መሥራት?
አስመሳይነታችን ለተስፋ መቁረጥ ይዳርገናል።ተስፋ መቁረጣችንም የምንኖርለትን ዓለማ ያጠፋብናል።ዓላማ የሌለው ሰው ደግም ወና በሆነ አኗኗር ውስጥ ራሱን ፈልጎ ማግኘት እና ለሌላው መትረፍ አይችልም።

ዓላማ ያለው ሰው ግን ዓማውን ከሕይወቱ አስቀድሞ ይሠራል እንጂ አይወሰልትም።
በቀቢጸ ተስፋ የተያዘ ሰው እንኳን በምድር ሊያበረክት ስለሚገባው ይቅርና ትንሣኤ ሙታን መኖሩ ያዘነጋል።

ሊቁ ዮሐንስ አፈወርቅ፦“ከመ ኢይስሀት መኑሂ በስህተተ ኃጢአት ዘውእቱ ቀቢጸ
ተስፋ ዘበአማን እምስህተተ ሰይጣን ውእቱ ወይሬስዮ ለሰብእ ከመ ይበል አልቦ ትንሣኤ ለግሙራ ወኢ መንግሥተ ሰማያት ወኢ ኩነኔ ለግሙራ 'ኃጢአት ባመጣው ቀቢጸ ተስፋ ማንም እንዳይያዝ ይኸውም እውነተኛ ተስፋ የለም ማለት ነው።

ተስፋ መቁረጥ ከሰይጣን
የተገኘ ነውና። ሰውንም ትንሣኤ ሙታን ፈጽሞ የለም መንግሥተ ሰማያትም የለም
የዘለዓለም ኩነኔ ፈጽሞ የለም እንዲል ያደርገዋል” ሃይአበ ፷፭፥፳፫ ብሎ አስተምሮናል።

እግዚአብሔርን ዝም ብለህ መና አውርድ፣ሁሉን አስተካክል ማለት ስንፍና ነው።እየሠሩ ባርክልኝ ማለት ግን ጠቢብነት ነው። ራስ ወዳድነት ትልቅ ሰይጣናዊት ደዌ ናት።ለዓላማ መኖር ግን የህሊና ዕረፍት ናት።ቀቢጸ ተስፋ ደግሞ የመልካም ህሊና ሁሉ ማማ

የኔታ ገብረ መድኅን እንየው

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

16 Oct, 07:27


https://youtu.be/TKOPyJ3Aic0?si=HW5kAzMhhCsVlC1I

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

16 Oct, 05:37


-በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የቅዱስ ሲኖዶስ አባል የነበሩና የሆኑ አባቶች ጳጳሳት የጻፏቸው መጻሕፍት በከፊል፡፡ አባቶች አንዱ አገልግሎታቸው መጻሕፍት መጻፍ ነው፡፡ መሆንም አለበት፡፡

1. ፍኖተ እግዚአብሔር በብፁዕ አቡነ ቶማስ

2. ፍኖተ ሕይወት በብፁዕ አቡነ ማትያስ

3. ይግባኝ ለክርስቶስ እና ዓለም ጉድ ወለደች በብፁዕ አቡነ ቀውስጦስ

4. ኅብረ ብዙ በብፁዕ አቡነ ቄርሎስ

5. ርትዕት ሃይማኖት በብፁዕ አቡነ ገብርኤል

6. ኮሮና ኤልያስ በብፁዕ አቡነ ቄርሎስ

7. መሠረተ እምነት ለሕጻናት በብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ

8. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ በብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ

9. የቤተ ክርስቲያን ታሪክ በዓለም መድረክ በብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ

10. ብጹዓን ገባርያነ ሰላም በብፁዕ አቡነ ሳሙኤል

11. ነገረ መንፈስ ቅዱስ በብፁዕ አቡነ ሳሙኤል

12. ፈለገ አሚን ዘኦርቶዶክስ በብፁዕ አቡነ ሳሙኤል

13. ፍኖተ ሕይወት በብፁዕ አቡነ ቀውስጦስ

14. የኢትዮጺያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በየዘመናቱ በብፁዕ አቡነ ቀውስጦስ

15. የኢትዮጲያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ታሪክ በብፁዕ አቡነ ቀውስጦስ

16. ሥረወ ሃይማኖት ብፁእ አቡነ ማቴዎስ የኢየሩሳሌም የምስካየ ኅዙናን የበአታ ሊቀጳጳስ የነበሩ

17. ሀልወተ እግዚአብሔር በዘመናት በብፁዕ አቡነ ሳሙኤል

18. ድሕነት እና ኢትዮጵያ በብፁዕ አቡነ ሳሙኤል

19. የሃይማኖት መቻቻል በኢትዮጵያ አለን? በብፁዕ አቡነ ሳሙኤል

20. ግብረ ሰዶማዊነትና የኃጢአት ደመወዝ በብፁዕ አቡነ ሳሙኤል

21.መዝሙረ ዳዊት ትርጓሜ በፖትርያርክ ብፁእ አቡነ ቴዎፍሎስ

22. “Filsata: The Feast of the Assumption of the Virgin Mary and the Mariological Tradition of the Ethiopian Othodox Tewahedo Church” በፓትርያርክ ብፁእ አቡነ ጳውሎስ

23. ዜና ሕይወቱ ለቅዱስ ጳውሎስ በብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ

24. ስለ እግዚአብሔር መኖር በብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ

25. ትምህርተ አበ ነፍስ በብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ

26. ክብረ ድንግል በብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ

27. ድንግልናዊ ሕይወት በብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ

28. የእግዚአብሔር ሕገ መንግሥት በብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ

29. እንጸልይ በብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ

30. ማኅበራዊ ኑሮ በኢትዮጵያ በብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ

31. ጥንታዊ የኢትዮጵያ ትምህርት በብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ

32. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን እምነት እና ትምህርት በብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ

33.ትምህርተ ሃይማኖት በብፁዕ አቡነ ገሪማ

34.Monasticism and ascetic life in Ethiopia በብፁዕ አቡነ ሳሙኤል

35. ክብረ ቅዱሳን በብፁዕ አቡነ ገብርኤል

36.ትምህርተ ክርስትና በብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ

37.ግብረ ሕማማት በአቡነ ያዕቆብ

38.ፍኖተ ቅድስና በአባ ማትያስ

39.ፍሬ ጸሎት ወንስሐ በአቡነ ኤጲፋንዮስ

40.ፍኖተ ሃይማኖት ሰባቱ ምስጢራተ ቤተክርስቲያን በአማርኛ እና በኦሮምኛ አብነ ኤጲፋንዮስ

41.ክህነት አገልግሎት በአማርኛ እና በኦሮምኛ በአብነ ኤጲፋንዮስ

44.ከጥንት ሲወርድ ሲዋረድ የመጣው የሃይማኖተ አበው አስተዋጽዖ በአብነ ኤጲፋንዮስ

45.መጽሐፈ ጸሎተ ሱባዔ በአባ ሳሙኤል

46.ሲኖዶሳዊው ጉዞ በኦርቶዶክሳዊ ቀኖና ሲመዘን በብጹዕ አቡነ ጴጥሮስ

47.የምሥጢራቱ ቁልፍ በብጹዕ አቡነ ጴጥሮስ

48.መጽሐፈ በቁዔት ዘጾም ወዘበዓል (1946) በብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ካልዓይ

49. ርትዕት ፍኖት ዘባስልዮስ በባሕረ ጣና (1948) በብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ካልዓይ

50. የቅዱስ ጳውሎስ መልእክት ትርጓሜ (1948) በብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ካልዓይ

51. ቃለ ምዕዳን (1948) በብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ካልዓይ

52. የሐዋርያት ሥራ ትርጓሜ፣ የሰባቱ መልእክታትን ትርጓሜ እና የዮሐንስ ራእይን ትርጓሜ (1951) በብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ካልዓይ

53.ቃለ ምዕዳን (1948) በብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ካልዓይ

54.መዝገበ ሃይማኖት (1950) በብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ካልዓይ

55.ኦርቶዶክሳዊ የስብከት ዘዴ በብጹዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ

56.ፍኖተ ቤተ ክህነት ወቤተ መንግሥት በአቡነ ሕርያቆስ

57.The Ethiopian Orthodox Tewahedo Church. An Integrally African Church. በአቡነ ይስሐቅ

58.የአቤል ደም በብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ

59.የሃይማኖት መሠረት በአቡነ ሕዝቅኤል

60.RAAJII MAARIYAAM(ተአምረ ማርያም) በኦሮምኛ፣ በግዕዝ እና በአማርኛ የተዘጋጀ ፣በብፁዕ አቡነ ናትናኤል

-ያልተጠቀሰ ካለ ይጠቁሙን፡፡ አሻሽየ ያዘጋጀሁት ጽሑፍ ነው።

በመ/ር ዮሴፍ ፍስሀ ሰውነት

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

16 Oct, 05:36


🌹✞ ስንክሳር ጥቅምት 6 ✞🌹

🌿🌿🌿

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡

✞ እንኩዋን ለቅዱስ "ዲዮናስዮስ ሐዋርያዊ" ወአባ "ዸንጠሌዎን" ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ:: ✞

"ቅዱስ ዲዮናስዮስ ሐዋርያዊ ሊቅ"
በዘመነ ሐዋርያት ከነበሩና አስደናቂ ታሪክ ከነበራቸው ቅዱሳን አንዱ ይህ አባት ነው:: ቅዱስ ዲዮናስዮስ በትውልዱ አረሚ (ግሪካዊ) የሆነ ፈላስፋ: ከነ አሪስቶትል ሲያያዝ የመጣውን ፍልስፍና ጨርሶ በማጥናቱ ርዕሰ ሊቃውንት (የፈላስፎች አለቃ) የሚል ስም ተሰጥቶት
ነበር::

በግሪክ አቴና (ATHENS) ለነበሩ ፈላስፎችም ሁሉ የበላይ ሲሆን በአርዮስፋጐስ (ሐዋ. 17) ታላቁ ሰው እርሱ ነበር:: ይህ ሁሉ ሲሆን ግን እድሜው ገና ወጣት ነበር:: ቅዱስ ዲዮናስዮስ ፈላስፋ ስለ ሆነ ቅሉ ይመራመር ነበር::

ይልቁኑ ስለ እውነተኛው አምላክ ያስብ ነበር:: በግሪክ ምድር ከሚመለኩ 250 አማልክት መካከል ቁም ነገር አልተገኘምና:: ነገር ግን አንድ ቀን ዓለም በተፈጠረች በ5,534 ዓመት: መጋቢት 27 ቀን: በዕለተ ዓርብ: 6 ሰዓት ላይ ምድር ተናወጠች:: ፀሐይ ጨለመች: ጨረቃ
ደም ሆነች: ከዋክብትም ረገፉ::

በዚህ የተደናገጡ የአቴና (ATHENS) ነዋሪዎችና
ፈላስፎች ወደ ዲዮናስዮስ ተሰብስበው "መምሕራችን የተፈጠረውን ነገር መርምረህ አስረዳን" አሉት::

ዲዮናስዮስም ባለው ጥበብ ባሕሩን: የብሱን: ፀሐይ: ጨረቃን: ከዋክብትን መረመራቸው:: "ወረከቦሙ ኅዱዓነ" እንዲል በቀደመ ቦታቸው አገኛቸው:: ግራ ቢገባው እንቅልፍ ከዐይኑ ተከለከለ::

ከዚያም ወደ ቤተ መዛግብቱ ገብቶ መጻሕፍትን
ሲያገላብጥ "አርስጣላባ" የሚባል ግዙፍ መጽሐፍ
አግኝቶ ቢገልጠው "እልመክኑን" የሚል ጽሑፍ አገኘ:: ወደ ውጪ ወጥቶ በሕዝቡና ጠቢባኑ ፊት ልብሱን ቀድዶ አለቀሰ:: እነርሱም ደንግጠው "ምነው መምሕራችን? ምን ሆንህ?" ቢሉት "የማይታየው አምላክ ቢወርድ በምቀኝነት ገደሉት የሚል ጽሑፍ አገኘሁ" አላቸው:: "እልመክኑን" ማለት "የማይታይ አምላክ" ማለት ነውና::
"ዘኢያስተርኢ ኅቡዕ እስመ አስተርአየ ለነ:
እሳት በላኢ አምላክነ" እንዲል::

ከዚህ በሁዋላ ደቀ መዛሙርቱን (ተማሮቹን) ጠርቶ
(ኡሲፎስና ኡርያኖስ ይባላሉ) "እልመክኑን" የሚለውን ስም "ከቤተ ጣዖቱ በር ላይ ለጥፉት" ብሏቸው ለጠፉት:: በእንዲህ ያለ መንገድ 14 ዓመታት አልፈው ቅዱስ ዻውሎስ ወንጌልን እየሰበከ አቴና ደረሰ:: ዘመኑም በ48 ዓ/ም ነበር::

ወደ ከተማዋ ሲገባ በጣዖት ቤቱ በር ላይ
የተለጠፈውን ጽሑፍ ተመለከተና ያስተምራቸው ያዘ:: ትምሕርቱን የሰሙ ጠቢባኑና ሕዝቡ ሐዋርያውን ይዘው ወደ ዲዮናስዮስ ፊት አቀረቡት:: "ምንድን ነው በደሉ?" ቢላቸው "አዲስ አምላክን ሲያስተምር አግኝተነዋል" አሉት::

ቅዱስ ዻውሎስም "እኔ አዲስ አምላክን
የምሰብክላችሁ አይደለሁም:: ይልቁኑ ከቀድሞም
የፈጠራችሁ: ቀጥሎም የሞተላችሁ: እናንተም
"እልመክኑን" ብላችሁ ሳታውቁት ታመልኩት የነበረውን ጌታ እንጂ:: እርሱም ኢየሱስ ክርስቶስ ነው አላቸው::

ዲዮናስዮስም ቅዱስ ዻውሎስን "ለዚህ ምን ምልክት አለህ?" ቢለው "የዛሬ 14 ዓመት: መጋቢት 27 ቀን: በዕለተ ዓርብ 6 ሰዓት ላይ ታላላቅ ተአምራት የተደረጉ አይደለምን! እነዚህ ሁሉ የተደረጉት በስቅለቱ ጊዜ ነው" ሲል መለሰለት::

ዲዮናስዮስም ፈጥኖ በክርስቶስ አመነ:: የአካባቢው ጠቢባንና ሕዝቡም አምነው ከመሪያቸው ጋር ተጠመቁ:: ቅዱስ ዻውሎስም ቅዱስ ዲዮናስዮስን አስተምሮ የአቴና የመጀመሪያው ዻዻስ አደረገው:: ቅዱሱም ክርስቲያኖችን ያበዛ: መንጋውንም ያጸና ዘንድ ብዙ ተጋ::

በተለይ በመጀመሪያው መቶ ክ/ዘመን ከነበሩ ታዋቂ ደራስያን አንዱ ሆነ:: በርካታ ድርሰቶችንም በመንፈስ ቅዱስ ደረሰ:: ዛሬ ድረስ እንኩዋ ሃይማኖተ አበው ውስጥ የሚገኘው ድርሰቱ (ዘዲዮናስዮስ) ጣዕሙ ልዩ ነው:: ቅዱሱ ለብዙ ዘመናት ለወንጌል አገልግሎት ተግቶ: በዚህች ቀን የአካባቢው አገረ ገዥ አንገቱን አስቆርጦት ሰማዕት ሆኗል::

የሚገርመው ግን ሲገድሉት በቦታው ሰው ስላልነበረ ቅዱሱ ተነስቶ: ተቆርጣ የወደቀች ራሱን አነሳት:: በጐኑ አቅፎም ደቀ መዛሙርቱ እስካሉበት ሒዶ በፊታቸው ዘንበል አለ:: ምዕመናንም እያለቀሱና እየዘመሩ ከአርድእቱ ኡሲፎስና ኡርያኖስ ጋር ቀብረውታል:: እነርሱም አብረውት ተሰይፈዋልና::

" አባ ዸንጠሌዎን ዘጾማዕት "

ታላቁ ጻድቅ: ሰባኬ ወንጌልና ገዳማዊ አባ
ዸንጠሌዎን የተስዓቱ (ዘጠኙ) ቅዱሳን መሪ (አባት) ናቸው:: ጻድቁ ሃገረ ሙላዳቸው ሮም ቢሆንም ገድላቸውን የፈጸሙት በኢትዮዽያ ነው::

ወላጆቻቸው በሮም ቤተ መንግስት የቀኝ መንበር
ያላቸው ክቡራን ቢሆኑም ልጃቸውን ይማር ብለው ወደ ገዳም ከተቷቸው:: በገዳም ትምሕርቱን ከጠነቀቁ በሁዋላ በዚያው ጠፍተው ወደ ግብጽ ወረዱ:: በዚያም መነኮሱ::

እድሜአቸው እየገፋ ሲሔድ በመንፈስ ቅዱስ መሪነት 8ቱን ቅዱሳን ሰብስበው: በአቡነ አረጋዊ (ዘሚካኤል) መሪነት ወደ ሃገራችን መጡ:: በ470ዎቹ አካባቢ የነበረው ንጉሥ አልዓሜዳም በክብር ተቀብሎ አክሱም ውስጥ "ቤተ - ቀጢን" የሚባል ቦታን ሰጣቸው::

ዘጠኙ ቅዱሳን በአንድነት: ቀን ቀን ወንጌልን
ሲያስተምሩ ውለው ሌሊት ሲጸልዩና መጻሕፍትን
ሲተረጉሙ ያድሩ ነበር:: ነገር ግን ለየብቻቸው
መኖራቸውን መንፈስ ቅዱስ ስለ ወደደ ሁሉም
በየራሳቸው ገዳማትን መሠረቱ::

=>አምላከ አበው ወገኖቻችንን ሁሉ በሰላም ያቆይልን።
ከክብረ ቅዱሳንም አይለየን::

ጥቅምት 6 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ ዲዮናስዮስ ሐዋርያዊ
2.አባ ዸንጠሌዎን ዘጾማዕት
3.ቅዱስ ዕንባቆም ነቢይ (ዕን. ከ1 - 3 ያንብቡ)
4.ቅድስት ሐና ነቢይት (የሳሙኤል እናት - 1ሳሙ. ከ1 - 2ን ያንብቡ)
5.ቅዱሳን ኡሲፎርና ኡርያኖስ (ሰማዕታት)
6.አቡነ በጸሎተ ሚካኤል ኢትዮዽያዊ (ፍልሠቱ)
7.ቅዱስ ሄኖስ ነቢይ

✍️† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †✍️
               🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇

       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

14 Oct, 15:42


https://youtu.be/GpSc9QcWCqQ?si=wkQ-zAOFj8zlh_5A

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

14 Oct, 15:39


🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀
ሥርዓተ ማኅሌት ዘጥቅምት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ

ሰላም ለሕፅንክሙ ምርፋቀ ጻድቃን አግብርቲሁ፤ ማያተ ኢያሱ ሥላሴ እለ ትውኅዙ እምሕሊናሁ፤ እንዘ በአፍአሁ አንትሙ ወአንትሙ በውሣጤሁ፤ ኢነጸረ ኀበ ሐይመት ከመ አብርሃም አቡሁ፤ ወመስኮተ ነቢይ ዳንኤል ኢፈቀደ ያርኁ።

ዚቅ
በአፍአኒ አንትሙ፣ ወበውሣጤኒ አንትሙ፤ በገዳምኒ አንትሙ፤ ብርሃኑ ለዓለም (ለኢያሱ) አንትሙ።

መልክአ ሚካኤል
ሰላም ለሕፅንከ እንተ በዲቤሁ ሕቁፍ፤ ጸሎተ ቅዱሳን ውኩፍ፤ ሚካኤል ክቡር መስፍነ ትጉሃን አእላፍ፤ ለረዲኦትየ ከመ ዘይሠርር ዖፍ፤ እንዘ ትሠርር ነዓ በ፪ኤ አክናፍ።

ዚቅ
ከመ መዓዛ ቅዱሳን፤ ውስተ አብያተ ክርስቲያን፤ ይሰምዖሙ ጸሎቶሙ ለንጹሐን ከመ መዓዛ ቅዱሳን።

ዘምንክር ጣዕሙ

ሰላም ለዝክረ ስምኪ ዘመንክር ጣዕሙ፤ ለወልድኪ አምሳለ ደሙ፤ መሠረተ ህይወት ማርያም ወጥንተ መድኃኒት ዘእምቀዲሙ፤ ኪያኪ ሠናይተ ዘፈጠረ ለቤዛ ዓለሙ፤ እግዚአብሔር ይትባረክ ወይትአኮት ስሙ።

ዚቅ
እስመ ርእየ ሕማማ ለዓመቱ፤ ወገብረ ኃይለ በመዝራዕቱ፤ መዝገቡ ለቃል ጽጌ እንተ ኢትትነገፍ መድኃኒተ ሕዝብ፤ መዓዛሆሙ ለቅዱሳን።

መልክዓ ገብረ መንፈስ ቅዱስ

ሰላም ለዝክረ ስምከ ዘኆኅያቲሁ ቅሩጽ፤ ኀበ ዓምደ ብርሃን ጽዱል ወአኮ ዘዕፅ፤ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ኃያል ሠዋቄ ትንቱናን እምዳኅፅ፤ ለዝክረ ስምከ ሠናየ ዜና ወድምፅ፤ ትሴብሕ ኢትዮጵያ ወትዜምር ግብፅ።

ዚቅ
ኮከብ ብሩህ ዘሠረቀ እምአቅሌስያ፤ ቤተ ክርስቲያን ዘንሰምያ፤ ኮኖሙ አበ ለሰብአ ግብፅ ወኢትዮጵያ፤ አማን ገብረ መንፈስ ቅዱስ ሐዋርያ።

ወረብ
ኮከብ ብሩህ ዘሠረቀ እምአቅሌስያ ቤተ ክርስቲያን ዘንሰምያ/፪/
ኮኖሙ አበ ለሰብአ ግብፅ ወኢትዮጵያ አማን በአማን ሐዋርያ/፪

ዓዲ (ወይም)
ዚቅ
ፃማ ቅዱሳን ዲቤሁ አዕረፈ፤ አፈዋተ ወንጌል ጸገየ ዘልፈ፤ አባ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ሃይማኖተ ተአጽፈ፤ ኀበ ዓምደ ወርቅ ስሙ ተጽሕፈ።

መልክአ ገብረ መንፈስ ቅዱስ

ሰላም ለጒርኤከ ኅሩመ መብልዕ ዘኮነ፤ ወእስከ ስቴ ማይ መነነ፤ ሶበ ረድኤተከ ርእዩ ወኪዳነከ እሙነ፤ ይቤሉከ ኲሉ ገብረ መንፈስ ቅዱስ አቡነ፤ በኪዳንከ አሥራተ ንሥአነ።

ወረብ
አሥራተ ንሥአነ አሥራተ ንሥአነ/፪/
ገብረ መንፈስ ቅዱስ አሥራተ ንሥአነ/፪/

ዚቅ
በመንግሥተ ሰማያት ይነግሥ ምስሌከ፤ ኃጥእ ዘገብረ ተዝካረከ፤ ወጸውዓ ስመከ እንዘ ይብል አምላከ ተካየድከ፤ በእንተዝ ንሥአነ ለሕዝብከ፤ ገብረ መንፈስ ቅዱስ አሥራተ በኪዳንከ።


መልክአ ገብረ መንፈስ ቅዱስ


ሰላም ለአዕጋሪከ እለ ኢሖራ በፍናዊሃ፤ ለዛቲ ዓለም ዘዕበድ ጥበባቲሃ፤ ለኢትዮጵያ ምድርነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ሐዋርያሃ፤ ውስተ ገፀ ኲሉ ደወላ ዜና ነገርከ በዝኃ፤ ወእስከ ጽንፋ ለምድር ነቢብከ በጽሐ።

ዚቅ
ዝንቱሰ ብእሲ መምህርነ፤ ዘተፈነወ ውስተ ምድርነ፤ ይክሥት ብርሃነ ይፈውስ ዱያነ፤ ሐዋርያ ዘኮነ ወተሰምዓ ዜናሁ፤ ውስተ ኲሉ ምድር።

ወረብ
ዝንቱሰ ገብረ ሕይወት ተፈነወ ውስተ ምድርነ/፪/
ይክሥት ብርሃነ ይፈውስ ዱያነ ሐዋርያ ሐዋርያ ዘኮነ/፪/

ሰቆቃወ ድንግል


እስከ ማእዜኑ እግዝእትየ ማርያም ውስተ ምድረ ነኪር ትሔልዊ፤ሀገረኪ ናሁ ገሊላ እትዊ፤ለወልድኪ ሕፃን ዘስሙ ናዝራዊ፤ለክብረ ቅዱሳን በከመይቤ ኦዝያን ዜናዊ፤እምግብጽ ይጼውዖ አቡሁ ራማዊ።

ወረብ
በከመይቤ"ኦዝያን"(፪) ለክብረ ቅዱሳን/2/
እምግብጽ ይጼውዖ ለወልድኪ አቡሁ ራማዊ አቡ/2/

ዚቅ
ትንቢተ ኢሳይያስ ዘተብህለ እምግብፅ ጸዋዕክዎ ለወልድየ ለክብረ ቅዱሳን ጸዋዕክዎ


ማኅሌተ ጽጌ


እምደቂቀ ሕዝብኪ አነ እንዘ ነዳይ ወአባሲ፤ በብዕለ ዚአኪ ድንግል እትሜካሕ ከመ ነጋሢ፤ወበጽድቅኪ እትፌሣሕ አርአያ ጻድቅ ብእሲ፤እስመ ብየ ተአምርኪ ጌጋየ ኃጥአን ደምሳሲ፤ወመዝገበ ብዕል ጽጌኪ ለኲሉ ዘይሴሲ

ዚቅ
ማርያምሰ ረከብኪ ሞገሰ በኀበ እግዚአብሔር፤ወአነሂ እትፌሣሕ በእንቲአኪ፤እስመ ረከብኩ እምዉስተ ደቂቅኪ እለ የሐዉር በትእዛዝየ፤አምኂ አምኂ፤አምኂ ደቂቀ እኅትኪ ኅሪት።

 ምልጣን


ኮከብ ብሩህ ዘሠረቀ እምአቅሌስያ፤ ቤተ ክርስቲያን ዘንሰምያ፤ ኮኖሙ አበ ለሰብአ ግብፅ ወኢትዮጵያ፤ አማን ገብረ መንፈስ ቅዱስ ሐዋርያ።

አመላለስ


አማን በአማን/፬/
ገብረ መንፈስ ቅዱስ ሐዋርያ/፬/

እስመ ለዓለም


ንጉሥኪ ጽዮን አሠርገዋ ለምድር በጽጌያት፤ወለሰማይኒ በከዋክብት፤ውእቱ ክብሮሙ ለቅዱሳን፤ብርሃኖሙ ለመሐይምናን፤ዘየአምር እምቅድመ ሕሊና፤ዘይሔሊ ልብ አርአየ ኃይሎ፤በላዕሌነ ወጸገወነ ሠናይቶ


ወረቦቹን ለማድመጥ  👉🏿 https://youtu.be/s4wuMZ0Ws1g?si=eZkDIA3v3iQegCOE
መልክዓ ሥላሴ

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

14 Oct, 13:31


✞ ስንክሳር ጥቅምት 5 ✞

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞✞✞

✞✞✞ እንኩዋን ለጻድቁ "አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ" እና "ቅዱስ ኪራኮስ አረጋዊ" ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞✞✞

+"+ አቡነ ገብረ ሕይወት +"+

=>ጻድቁ የተወለዱት ግብፅ (ንሒሳ አካባቢ) ሲሆን
አባታቸው ስምዖን እናታቸው አቅሌስያ ይባላሉ:: አባታችን
ገብረ ሕይወት የጻድቃን አለቃ: የቅዱሳን የበላይ:
ተጋድሎአቸውና ድንቅ ተአምራቸው እንደ ሰማይ
ከዋክብት የበዛ ቅዱስ ሰው ናቸው::

+የጻድቁን ክብር መናገር የሚችል ምን አነደበት
ይኖራል?
እንደ ምንስ ባለ ብራና ይጻፋል?
ዜናቸውንስ ለመስማት የታደለ እንደ ምን ዓይነት ሰው
ይሆን?

+አባታችን ገብረ መንፈስ ቅዱስ ለ562 ዓመታት በዚህች
ዓለም ሲኖሩ እህል ያልቀመሱ (ምግባቸው ምስጋና
ነውና): ልብስ ያልለበሱ (ጠጉር አካላቸውን ይሸፍን
ነበርና): ሐዋርያዊ ሆነው ከግብፅ እስከ ኢትዮዽያ ብዙ
ነፍሳትን ያዳኑ አባት: ሃገራችንን አስምረው: አስራት
እንድትሆናቸውም ተቀብለው ምድረ ከብድ አካባቢ
አርፈዋል::

+ጻድቁ ገብረ መንፈስ ቅዱስም: ገብረ ሕይወትም
ይባላሉ:: በ562 ዓመታት ሕይወታቸው እንደ ሐዋርያት
ከምድረ ግብጸ እስከ ኢትዮዽያ ወንጌልን ሰብከዋል::
በዚህም በሚሊየን (አእላፍ) ለሚቆጠሩ ነፍሳት የድኅነት
ምክንያት ሆነዋል::

+ጻድቁ እንደ ሰማዕታትም ከከሃዲ ሰዎች ብዙ መከራን
ተቀብለዋል:: እንደ ባሕታውያን ለብዙ መቶ ዓመታት ሰው
ሳያዩ ቆይተዋል:: ለየት የሚለው ግን የጽድቅ
ሕይወታቸው ነው:: ከእልፍ አዕላፍ አጋንንት ጋር
ተዋግተው ድል ማድረግ ችለዋልና::

+የንሒሳው ኮከብ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ለኢትዮዽያ ልዩ
ፍቀር አላቸው:: ስለ ሃገሪቱና ሕዝቧ ፍቅር ሲሉ ለ100
ዓመታት በደብረ ዝቁዋላ መከራን ተቀብለዋል:: ምሕረትን ሲለምኑ ሥጋቸው አልቆ በአጥንታቸው ቁመው
ነበርና ሃገራችን አሥራት ሆና ተሰጠቻቸው::

+ስለዚህም ነው በሃገሪቱ ውስጥ ከ2,000 በላይ የጻድቁ
አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳማትና አድባራት ዛሬም
ድረስ ያሉት:: በ8ኛው ክ/ዘመን አካባቢ የተወለዱት
አባታችን ያረፉት በ14ኛው መቶ ክ/ዘመን አካባቢ ነው::
ፍጥረታትን ሁሉ አዘው መጋቢት 5 ቀን ሲያርፉ ግሩማን
መላእክት ገንዘው አካላቸውን ሠውረዋል::

+ሥላሴን የተሸከመ አካላቸው በጐልጐታ ተቀብሯል
የሚሉም አሉ::
"ሰላም ለመቃብሪከ ዘኢተከሥተ ለባዕድ:
ከመ መቃብሩ ለሙሴ ወልደ ዮካብድ:
ዜና መቃብሪከሰ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ጸማድ:
ቦ ዘይቤ በኢየሩሳሌም አጸድ:
ወቦ ዘይቤ ኀለወ በከብድ::" እንዲል::

+የጻድቁ በዓል ጥቅምት 5 ቀን የሚከበረው ብዙ ጊዜ
መጋቢት 5 ዐቢይ ጾም ውስጥ ስለሚውል ተውላጥ
(ቅያሪ) ሆኖ ነው::

+"+ ቅዱስ ኪራኮስ አረጋዊ +"+

=>ይህ ቅዱስ አባት ስም አጠራሩ የከበረ:
ሽምግልናውም ያማረ ነው:: ብዙዎቻችን የምናውቀው
በበዓለ መስቀል ስሙ ተደጋግሞ ሲጠራ ነው:: ግን ይህ
ታላቅ ሰው ለቅድስት እሌኒ መካነ መስቀሉን አሳያት
ከሚል አረፍተ ነገር የዘለለ ታሪኩ ሲነገርለት ብዙ ጊዜ
አንሰማምና እስኪ በዕለተ ዕረፍቱ ስለ ቅዱሱ ጥቂት
እንበል::

+ቅዱስ ኪራኮስ የተወለደው በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን
ሲሆን እናቱ ቅድስት ሐና ትባላለች:: በእጅጉ የተባረከች
ሴት ናት:: ምንም በነገዳቸው አይሁድ ቢሆኑም የዘመኑ
የአይሁድ ክፋት አልገዛቸውም:: የተባረከች እናቱ ታሪክ
እያስጠናች ከማሳደጉዋ ባለፈ አስቀድማ ኦሪቱን:
ነቢያቱን እንዲያውቅ አደረገች::

+አስከትላም ሕገ ክርስትናን እንዲረዳ አደረገችው::
የታሪክና የመጻሕፍት ምሑሩ ቅዱስ ኪራኮስ ከእናቱ ጋር
ሆኖ እግዚአብሔርን እያገለገለ: ክርስቶስን እያመለከ
ቆየ:: በዚህ ጊዜ ግን እድሜው እየገፋ ነበር::

+ሠለስቱ ምዕት (318ቱ ሊቃውንት) ጉባኤያቸውን
ከፈጸሙ በሁዋላ ቅድስት እሌኒም መስቀሉን ፍለጋ
ስትወጣ ትልቁ ፈተናዋ የተቀበረበትን ቦታ ማወቅ
አለመቻሏ ነበር:: እንዲያውም አማራጭ ስታጣ
በአካባቢው የነበሩ አይሁድን ምሥጢር እንዲያወጡ
ቀጥታቸው ነበር:: በሁዋላ ግን ኪራኮስ ስለሚባል ደግ
ታሪክ አዋቂ ሰው ሰምታ ተገናኙ::

+ቅዱስ ኪራኮስም አባቶቹ አይሁድ ናቸውና አካባቢውን
ያውቀው ነበር:: ችግሩ ቆሻሻው ተራራ በመሆኑ ከ3ቱ
የትኛው እንደ ሆነ አለመታወቁ ነበር:: ቅዱሱ ግን
ለዚህም መፍትሔ ነበረውና "ደመራ ደምረሽ: በእሳት
አቃጥለሽ: እጣን ጨምሪበትና ይገለጥልሻል" አላት::

+ቅድስት እሌኒም የተባለችውን በትክክል ፈጽማ
የመድኅን ክርስቶስን ቅዱስ ዕጸ መስቀል አገኘች::
ቅድስት እሌኒ ወደ ሃገሯ ከተመለሰች በሁዋላም ቅዱስ
ኪራኮስ በኢየሩሳሌም አካባቢ ዻዻስ ሆኖ ተሾመ::

+አረጋዊው ቅዱስ የሚገርም እረኛ ነውና የባዘኑትን
ሲፈልግ: በቤቱ ያሉትንም ሲያጸና ብዙ ደከመ:: በቅርቡ
ያሉትን በአፉ: የራቁትን ደግሞ በጦማር (በመልእክት)
አስተማረ:: በወቅቱ በአካባቢው ኤልያኖስ የሚሉት ከሃዲ
ንጉሥ ነበርና በቅዱስ ኪራኮስ ላይ ተቆጣ::

+ወደ እርሱ አስጠርቶ በአደባባይ: ቅዱስ ቃሉን ይጽፍበት
የነበረው ቀኝ እጁን አስቆረጠው:: ቅዱስ ኪራኮስ ግን
እጁ መሬት ላይ ወድቃ: ደሙ እየተንጠፈጠፈ ተናገረ:-
"አንተ ልብ የሌለህ ንጉሥ! እጄን ቆርጠህ ከክርስቶስ
ፍቅር ልትለየኝ አትችልም" አለው::

+በዚህ የተበሳጨ ንጉሡ እሳት አስነድዶ: አልጋውን
አግሎ ቅዱሱን ጠበሰው:: ኪራኮስ ግን በእሳቱ ላይ ሳለ
ወደ እሥራኤል ፈጣሪ በእብራይስጥኛ ጸለየ:: በማግስቱ
እናቱን ቅድስት ሐናን አምጥተው የነደደ እሳት ውስጥ
ጣሏት::

+ለ3 ሰዓት ያህል በእሳት ውስጥ ስትጸልይ ቆይታ በጦር
ወግተው ገደሏት:: ቅዱስ ኪራኮስንም ለአራዊት ሰጡት::
አራዊቱ ሰገዱለት:: በሌሎች ዓይነት ስቃዮችም ፈተኑት:
ግን እንቢ አላቸው:: በመጨረሻው በዚህ ቀን ገድለውት
የክብርን አክሊል ተቀዳጅቷል::

=>አምላከ ቅዱሳን በእነርሱ ላይ የበዛች ፍቅሩን ለእኛም
ያድለን:: ፍሬ ትሩፋት: ፍሬ ክብር እንድናፈራም ይርዳን::
ክብራቸውንም አያጉድልብን::

=>ጥቅምት 5 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ጻድቅ
2.ቅዱስ ኪራኮስ አረጋዊ (ዻዻስ ወሰማዕት)
3.ቅድስት ሐና ሰማዕት (እናቱ)
4.ቅዱስ ያዕቆብ ወልደ እልፍዮስ (ከ12ቱ ሐዋርያት)
5.አባ ዻውሎስ ሰማዕት (አርዮሳውያን አንቀው የገደሉት አባት)

=>ወርሐዊ በዓላት
1.ቅዱስ ዼጥሮስ ሊቀ ሐዋርያት
2.ቅዱስ ዻውሎስ ብርሃነ ዓለም
3.ቅዱስ ዮሐኒ ኢትዮዽያዊ
4.ቅዱስ አሞኒ ዘናሒሶ
5.ቅድስት አውጋንያ (ሰማዕትና ጻድቅ)

† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
               🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

14 Oct, 03:53


🙏† ስንክሳር ጥቅምት 4 †🙏
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿

እንኩዋን ለቅዱሳን ነገሥታት "አብርሃ ወአጽብሃ" እና ለቅዱስ "ሐናንያ ሐዋርያ" ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ።

+"+ ቅዱሳን አብርሃ ወአጽብሃ +"+

እነዚህ ነገሥታት ሞገሶቻችን: ብርሃኖቻችን ናቸውና ደስ እያለን እንወዳቸዋለን: እናከብራቸዋለን:: ሥላሴ ቢመርጧቸው ዛሬ ላለንበት ሕይወት መሠረቱን ጥለው አልፈዋልና::

2ቱ ቅዱሳን ነግሥታት መንትያዎች ሲሆኑ ወላጆቻቸው ንጉሥ ታዜር / አይዛና / ሠይፈ አርዕድ እና ንግሥት አሕየዋ / ሶፍያ ይባላል:: ንጉሡና ባለቤቱ ልጅ ቢያጡ ወደ እግዚአብሔር ለመኑ:: ፈጣሪም በቅዱስ ሚካኤል አብሳሪነት 2 ዕንቁዎችን አስረከባቸው::

ንግስት አሕየዋ (ሶፍያም) መጋቢት 29 ቀን በ311 ዓ/ም ጸንሳ: ታሕሳስ 29 ቀን በ312 ዓ/ም 2ቱን ቅዱሳን ወልዳቸዋለች:: "አምላክ ሽሙጥን አራቀልኝ" ስትልም "አዝጉዋጉ" ብላቸዋለች:: እነዚህ 2 ፍሬዎች በልጅነታቸው ከወቅቱ ሊቀ ካህናት እንበረም ኦሪቱን ጠንቅቀው ተምረዋል::

ከእግዚአብሔር የተሰጡ ናቸውና በ12 ዓመታቸው ወደ ቤተ መቅደስ ገብተዋል:: ትንሽ ቆይቶ ግን አባታቸው ታዜር በማረፉ ሕዝቡ 2ቱን ቅዱሳን "ንገሡልን" አሏቸው:: እነርሱም "እኛ የፈጣሪ አገልጋዮች ነንና አንችልም" በማለታቸው ለተወሰነ ጊዜ እናታቸው አስተዳደረች::

ቆይቶ ግን ቅዱስ ሚካኤል ለሊቀ ካህናቱ እንበረም "የፈጣሪ ፈቃዱ ስለ ሆነ አትዘኑ:: 2ታችሁም በአንድ ዙፋን ላይ ንገሡ: ታላቅ ጸጋ ለሃገሪቱ ይሆናል በላቸው" አለው::

ሊቀ ካህናቱም የታዘዘውን ተናግሮ: በ19 ዓመታቸው: 2ቱንም በአንድ ዙፋን ላይ "ነገሥተ ኢትዮዽያ" ሲል አስቀምጦ ቀባቸው:: ስማቸውን "ኢዛና" እና "ሳይዛና" አላቸው:: ቅዱሳኑ እንደ ነገሡ ቀዳሚ ሥራቸው የቀናችውን ሃይማኖት መፈለግ ሆነ::

በወቅቱ ፍሬምናጦስ (የሁዋላው አቡነ ሰላማ) በቤተ መንግስቱ ውስጥ የቅርብ አማካሪ ነበርና ጠርተው ተጨዋወቱት:: "አንተ ወንድማችን! ክርስቶስ ይወርዳል: ይወለዳል ተብሎ የተቆጠረው ሱባኤ እኮ አልፏል:: ምነው ቀረሳ? በርግጥ ምሥጢሩ ንገረን" አሉት::

እርሱም አትቶ: አመሥጥሮ: ከ300 ዓመታት በፊት አምላክ ሰው መሆኑንና ዓለምን ማዳኑን አስተማራቸው:: "አጥምቀን?" ቢሉት "አልችልም" አላቸው:: እነርሱም ከብዙ ስጦታ ጋር ወደ ግብጽ ላኩት::

ቅዱስ አትናቴዎስም ፍሬምናጦስን "አቡነ ሰላማ" ብሎ ከብዙ መጻሕፍት ጋር ላከው:: በመጀመሪያ ኢዛናና ሳይዛና ተጠመቁ:: ስማቸውም "አብርሃ ወአጽብሃ" ተባለ:: ቀጥሎም ሠራዊቱና ሕዝቡ ተጠመቀ::

ሃገራችንም በእነዚህ ቅዱሳን አማካኝነት ከጨለማ ወደ ብርሃን መጣች:: የክርስትና ደሴት ሆነች:: ሃገረ እግዚአብሔርነቷንም አጸናች:: ቅዱሳኑ ከዚህ በሁዋላ በሞገስ ክርስትናን ያስፋፉ ዘንድ ደከሙ:: ከ154 በላይ አብያተ ክርስቲያናትን ሲያንጹ አብዛኞቹ ፍልፍል ነበሩ::

በተለይ ግን በአክሱም ከተማ ላይ ያነጿትና 12 ቤተ መቅደሶች የነበሯት የጽዮን ቤተ ክርስቲያን ልናያት ትናፍቀናለች:: ጌጧ: ብርሃኗ ውል ውል ይልብናል:: ይህቺው ቤተ ክርስቲያን በ10 ኛው ክ/ዘመን ዮዲት ጉዲት በእሳት አውድማታለችና:: መሠረቱ ግን ዛሬም አለ::

ቅዱሳን አብርሃ ወአጽብሃ ግን ክርስትናን ለማስፋፋትና መንግስትን ለማጽናት ሲሉ ከአክሱም በተጨማሪ በሽዋም ዙፋንን ዘረጉ:: ለብዙ ዓመታትም አምላክ በፈቀደው መንገድ እስከ የመን ድረስ ገዙ:: ክርስትናንም አስፋፉ::

ቅዱስ አብርሃ በተወለደ በ52 ዓመቱ: በ364 ዓ/ም ጥቅምት 4 ቀን ሲያርፍ ወንድሙ ለ15 ዓመታት ብቻውን አስተዳድሯል:: በ379 ዓ/ም ደግሞ በዚሁ በጥቅምት 4 ቀን ቅዱስ አጽብሃም በተወለደ በ67 ዓመቱ በክብር ዐርፏል::

ከሁለቱም መቃብር ላይ ለ30 ቀናት የብርሃን ምሰሶ ተተክሎ ታይቷል:: ጌታችንም በማይታበል ቃሉ "ስማችሁን የጠራውን: መታሰቢያችሁን ያደረገውንም እምርላቹሃለሁ" ሲል ቃል ኪዳን ገብቶላቸዋል::

" ቅዱስ ሐናንያ ሐዋርያ "

ሐናንያ ቁጥሩ ከ72ቱ አርድእት ሲሆን መጽሐፍ ቅዱስ ላይ ስማቸው ተመዝግቦ ከተቀመጠልን ከጥቂቶቹ ዋነኛው ነው:: ከነገደ እሥራኤል ተወልዶ: በሕገ ኦሪት አድጐ: ከወጣትነት ዕድሜው ትንሽ እልፍ ሲል ጌታችን ወንጌልን ማስተማር ጀምሯልና ጠራው:: እርሱም በበጐ ፈቃድ ተከትሎታልና ከ72ቱ አርድእት ደመረው::

ለ3 ዓመታት ከጌታ እግር ተምሮ: ከዕለተ ስቅለት በፊት ሀብተ ፈውስም ተሰጥቶት ነበር:: ምክንያቱም ቅዱስ ሉቃስ እንደ ጻፈልን ሰብዐው አርድእት "ጌታ ሆይ! አጋንንት በስምህ ተገዙልን" ማለታቸውን አስቀምጦልናል:: (ሉቃ. 10:17) ቅዱስ ሐናንያ በበዓለ ዕርገት ተባርኮ በ50ኛው ቀንም መንፈስ ቅዱስን ተቀብሎ ለስብከተ ወንጌል ወጥቷል::

በሚያስተምር ጊዜ የሶርያዋን ደማስቆን ማዕከል አድርጐ ነበር:: በሁዋላም አበው ሐዋርያት የዚህች ከተማ የመጀመሪያው ዻዻስ አድርገው ሹመውታል:: ጌታ ባረገ በ8ኛው ዓመት ክርስቲያኖችን ያሰቃይ የነበረው ሳውል (የሁዋላው ቅዱስ ዻውሎስ) ወደ ደማስቆ የተጉዋዘው ክርስቲያኖችን በተለይም ቅዱስ ሐናንያን ለማሠር ነበር::

ለእግዚአብሔር ምርጥ ዕቃ ይሆን ዘንድ መብረቅ ዐይኑን አጠፋው:: ወዲያውም ጌታችን ሳውልን ወደ ሐናንያ እንዲሔድ ነው የነገረው:: ከ3 ቀናት በሁዋላ ጌታችን ለሐናንያ ተገልጦ አነጋግሮታል:: ሳውል (ዻውሎስ) ወደ ሐናንያ የደረሰው በመሪ ነበር::

2ቱ እንደተገናኙ ቅዱስ ሐናንያ ሳውልን አስተማረው: ፈወሰው: አጠመቀው: በጐ መንገድንም መራው:: በዚህ ምክንያት ቅዱሱ ሐዋርያ የቅዱስ ዻውሎስ የንስሃ አባቱ ይሰኛል:: (ሐዋ. 9:1-19)

ከዚህ በሁዋላ ቅዱስ ሐናንያ ለብዙ ዓመታት በተለያዩ የዓለም ክፍሎች ወንጌልን አስተማረ መከራንም ተቀበለ:: በመጨረሻም በዚህ ቀን ክፉዎች ከብዙ ስቃይ በሁዋላ በድንጋይ ወግረው ገድለውታል::

አምላከ አብርሃ ወአጽብሃ "ድሃ ተበደለ: ፍርድ ተጉዋደለ" የሚል ዳኛ: ሃይማኖቱ የቀና መሪንም ያምጣልን:: የቅዱሳኑን ክብር በእኛ ላይ ያድርግልን::

ጥቅምት 4 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱሳን ነገሥት አብርሃ ወአጽብሃ
2.ቅዱስ ሐናንያ ሐዋርያ (ከ72ቱ አርድእት)
3.ቅዱስ በርተሎሜዎስ ሐዋርያ
4.ቅዱስ ባኮስ ሰማዕት
5.ቅዱሳን ባባ እና ማማ
6.ቅዱስ ዮሐንስ ሕጽው

=>ወርኀዊ በዓላት
1.ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ
2.ቅዱስ እንድርያስ ሐዋርያ
3.ቅድስት ሶፍያ ሰማዕት
4.ቅዱስ ዮሐንስ ዘሐራቅሊ (ሰማዕት)

" እንግዲህ እግዚአብሔርን በመምሰልና በጭምትነት ሁሉ: ጸጥና ዝግ ብለን እንድንኖር: ልመናና ጸሎት: ምልጃም: ምስጋናም ስለ ሰዎች ሁሉ: ስለ ነገሥታትና መኩዋንንትም ሁሉ እንዲደረጉ ከሁሉ በፊት እመክራለሁ:: ሰዎች ሁሉ ሊድኑና እውነቱን ወደ ማወቅ ሊደርሱ በሚወድ በእግዚአብሔር በመድኃኒታችን ፊት መልካምና ደስ የሚያሰኝ ይህ ነው:: " (1ጢሞ. 2:1-4)

✍️† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †✍️
🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇

https://t.me/Sinksar
https://t.me/Sinksar
https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

13 Oct, 13:04


🌸ፍትሐ_ነገሥት ክፍል ፳፯

🏵️አንቀጽ ፴፩ -በእንተ ግዕዛን -
የፈረስ ጉልበት የጦር አንደበት አንዱ ለአንዱ ይገዛ ዘንድ መገዛት ታመጣበታለች እንጂ ሰው ሁሉ ከአንድ ከአዳም በመገኘት ባለመገዛት አንድ ነው፡፡

ጦርነት ድል የተነሡትን ድል ለነሡት እንዲገዙ ታደርጋለች፡፡ ባርያን ነጻ ማውጣት ከትሩፋት ሥራ ወገን ናት፡፡ ባርያን ሁሉ ነጻ ማውጣት ይገባል፡፡
    
🏵️አንቀጽ ፴፪ - በእንተ ምግብና -
አንቀጽ 29 ላይ የተገለጸው የቤተ መንግሥት ሹም ነው፡፡ ከዚህኛው አንቀጽ የተገለጸው ደግሞ የሐፃኒ የመጋቢ ነው፡፡ ለባሕርይው የሚስማማውን ለሰውነቱ የሚያሻውን ማወቅ ለማይቻለው ሰው ሊሾሙለት ሊሾሙበት ይገባል፡፡ 

💐አንቀጽ ፴፫ - በእንተ ተሣይጦ ወሠይጥ
ይህ አንቀጽ ስለመሸጥ ስለመግዛት ይናገራል፡፡ ሻጭና ገዥ በገንዘባቸው ቢያዙ ቢሰለጥኑ ነው እንጂ ካላዘዙ ካልሠለጠኑ መሸጥ መግዛት አይጸናም አይፈጸምም፡፡ አውቀው ወደው ቢዋዋሉ ነው እንጂ ካልተዋዋሉ አይጸናም አይፈጸምም፡፡ መሸጥ መግዛት በደብዳቤም ያለደብዳቤም ሊደረግ ይችላል፡፡ ሻጭ ከገዥ እጅ አረቦን (ቀብድ) መቀበል ፈጽሞ ለመሸጥ ለመግዛት እንደሆነ ያስረዳል፡፡
ገዥ ውሉን ቢያፈርስ አረቦኑ ለሻጭ ይሆናል፡፡
ሻጭ ቢያፈርስ ግን አረቦኑን እጥፍ አድርጎ ይክፈል፡፡ በወንዝ ያለውን ዓሣ፣ በዱር ያለውን ፌቆ ዋልያ ድኩላ ወንዙ የእኔ ነው ዱሩ የእኔ ነው ብሎ ዓሣው በባሕር እያለ ዋልያው በዱሩ እያለ ሳይያዝ መሸጥ አይገባም፡፡

በመርዛቸው የሚገድሉ እንስሳትን ሥጋ የአህያን የፈረስን የበቅሎን ሥጋ፣ የአውሬውን ትራፊ፣ ሙቶ ያደረውን ሥጋ መሸጥ አይገባም፡፡

ጽንሱን ከእናቱ ለይቶ መሸጥ አይገባም፡፡
ሳይታለብ ወተቱን፣ በማድጋ ውስጥ ያለውን ማር ሳያሳዩ መሸጥ ሳያዩ መግዛት አይገባም፡፡
የአንድነትን ቦታ አንድ ግለሰብ መሸጥ አይገባውም፡፡ ከእናቱ ጋር ቢሆን ነው እንጂ ጡት ሳይተው ጥጃን ከእናቱ ለይተው መሸጥ እናቱን ከልጇ ለይቶ መሸጥ አይገባም፡፡ ሰውን ለማሳዘን የሚሆን ዋጋ ሁሉ አይገባም፡፡ እሑድ እሑድ፣ በጌታችን በዓላትና በእመቤታችን በዓላት መሸጥ መግዛት አይገባም፡፡

 💐አንቀጽ ፴፬ - በእንተ ተሳትፎ -
ተሳትፎ የሚለው አንዱ በከብት አንዱ በጉልበት የሚነግዱት ንግድ ነው፡፡ ትርፉን የሚሹትን ገንዘብ አወጣጥቶ በመነገድ ትጸናለች፡፡ በገንዘብ በማይተካከሉ ሰዎች መካከል ትጸናለች፡፡
 
💐አንቀጽ ፴፭ - በእንተ አገብሮ ወተኀይሎ
አገብሮ የሚለው የግድም የውድም ነው፡፡ ተኀይሎ የግድ ነው፡፡ አንድ ሰው አንዱን ሰው ሃይማኖትህን ካድ ብሎ ቢያገብረው በፍጹም ልቡናው ቢያምን መከራውን እንጂ አገብሮውን መቀበል ፈጽሞ አይገባም፡፡ በሰማዕትነት ቢሞት እንደ ቅዱስ ጊዮርጊስ እንደ ቅዱስ ቂርቆስ ሰማዕት ይባላል፡፡ በተኀይሎ አንድ ባዕለ ጸጋ ቢቀማ በአንድ አራት በአንድ አምስት ይክፈል፡፡
 
💐አንቀጽ ፴፮ - በእንተ ተዐስቦታት
ተዐስቦ ረብሕ ጥቅም ለማግኘት በመጠመን በማስጠመን ጊዜ በቃል የሚዋዋሏት ውል ናት፡፡ የመጠመን የማስጠመን ሥርዓት በተጠማኝ በአስጠማኝ ፈቃድ ነው እንጂ ያለእነዚህ ፈቃድ አይጸናም፡፡ አስጠማኝ ለተጠማኝ ከብቱን መሬቱን አሳይቶ አሳውቆ መስጠት ይገባዋል፡፡
ልብስ ሰፊ፣ እንጀራ ጋጋሪ እኩሌታውንም ቢሆን መላውንም ቢሆን ሥራቸውን ሳይፈጽሙ ዋጋችንን ስጡን ማለት አይገባቸውም፡፡ ባለቦታ ባለቤት ከቤት ተከራዮች ጋር ከተዋዋለበት ቀን ጀምሮ ያደሩበትን ዋጋ ያስከፍል፡፡

ሠራተኛ ሁሉ ዋጋውን እስኪቀበል ድረስ የሚሠራውን መያዝ ይገባዋል፡፡ ተጠማኝ ደንጊያ ሊሸከም ወፍጮ ሊጠርብ ቢዋዋል አልችል አላውቅ ብሎ ቢሠበር መክፈል ይገባዋል፡፡
ለልብስ አጣቢ ልብስ ከሠጡት በኋላ አይጥ ቢበላበት መክፈል ይገባዋል፡፡
ማንኛውም ገንዘብ ለመጠበቅ የተጠመነ ሰው ቸል ብሎ ባይጠብቅ ዕዳ መሆን ይገባዋል፡፡ ዘር ለመዝራት መሬትን መጠመን ማስጠመን ይገባል፡፡
አናጺ ሥራውን ከፈጸመ በኋላ ዋጋውን መቀበል ይገባዋል፡፡ ማናቸውንም ገንዘብ የተጠመነ ሰው ከእግዚአብሔር ዘንድ መዓት ታዞ ቢያጠፋው በተገኘው ጥፋት ዕዳ የለበትም፡፡

💐አንቀጽ ፴፯ - በእንተ ፍናዋት ወመራሕብት
የአንድነት ቤት ካላቸው ሰዎች አንዱ ከባልንጀሮቹ ፈቃድ ወጥቶ ጠባቂ ሹም መሾም አይገባውም፡፡ የአንድነቱንም አጥር ቅጥር አንዱ ማፍረስ ወይም መሥራት አይገባውም፡፡ በባልንጀራው ፈቃድ ቢሆን ነው እንጂ፡፡ አንድ ሰውስ ስንኳ በአንድነቱ አጥር አጠገብ የማድ ቤት የውሽባ ቤት መሥራት አይገባውም፡፡
አንድ ሰው በደርብ ያሉትን ሰዎች የሚያፍናቸው ጢስ የሚወጣበት ማድ ቤት የውሽባ ቤት ቢሠራ ጢስ ከማጤስ ይከለከል ዘንድ መጽሐፍ ያዝዛል፡፡ በደርብ ያሉትም ወደታችኛው ቤት እጣቢውን ማፍሰስ ጥራጊውን መጣል አይገባቸውም፡፡ ሰው ሁሉ በቤቱ ጎረቤቱን የሚያሳዝንበትን ጎረቤቱ የሚጎዳበትን ሥራ መሥራት አይገባውም፡፡
አንድ ሰውስ እንኳ ከሰው አጥር ላይ ጥራጊውን እጣቢውን መጣል ማፍሰስ አይገባም፡፡ ማናቸውም ሰው የሁሉ መውጫ መጋጫ ሜዳውን ማፍረስ መቆፈር አይገባውም፡፡ ዳኞች ከመፍረዳቸው በፊት ወጉን ታሪኩን ማጥናት መመርመር ይገባቸዋል፡፡

💐አንቀጽ ፴፰ - በእንተ ልቃሕ -
አንቀጽ 27 ስለእጅ ብድር ሲናገር ይህኛው አንቀጽ ደግሞ ትርፍ የጋራ ነው፡፡ በብድር መዋዋል ገንዘባቸውን በማወጣጣት በሠለጠኑ ሰዎች መካከል ሊሆን ይገባል፡፡


© በመ/ር በትረ ማርያም አበባው
         ክፍል-፳፰- ይቀጥላል. . .
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
               🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

13 Oct, 03:19


✞ ስንክሳር ጥቅምት 3 ✞

እንኩዋን ለቅዱስ  #አባ_ጊዮርጊስ_ዘጋስጫ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞✞✞
አባ_ጊዮርጊስ_ዘጋስጫ

ታላቁ ኢትዮዽያዊ ሊቅና ጻድቅ የተወለደው ወሎ ጋስጫ ውስጥ በ1358 (1357) ዓ/ም ነው:: ከልጅነቱ ትምሕርት አልገባሕ ቢለውም በልቡናው ግን ቅን እና ታዛዥ ነበር:: መምሕሩ "ትምሕርት አይገባውምና ውሰዱት" ቢላቸው "የእግዚአብሔር ነውና ያገልግላችሁ" ብለው መለሱት:: መገፋቱን የተመለከተ #አባ_ጊዮርጊስ #እመቤታታችንን ከልቡ ይወዳት ነበረና ይማጸናት ገባ::

ቀን ቀን ገዳሙን ሲረዳ: እሕል ሲፈጭና ሲከካ: ላቡንም ሲያፈስ ውሎ ሌሊት ደግሞ ሲጸልይ ያነጋ ነበር:: ድንግል እመቤታችን ጸሎቱን ሰምታለችና ቅዱስ_ዑራኤልን አስከትላ መጣችለት:: በንጹሐት እጆቿ ባርካው ምሥጢርንም ነገረችው:: "ወነገረቶ ሐምስተ ቃላተ" እንዲል:: ጽዋዐ ልቡናን አጠጥታው ተሠወረችው::

ከዚህች ሰዓት ጀምሮ አባ ጊዮርጊስ ፍጹም ተለወጠ:: በጽድቁ ላይ የሊቅነትን ካባ ደረበ:: ቅዱሳት መጻሕፍትን ይተነትናቸው: መናፍቃንንም ምላሽ ያሳጣቸው ገባ:: የተረጐማቸውና ያተታቸውን ሳይጨምር 41 ድርሰቶችን ደረሰ:: (መጽሐፈ ሰዓታት: መጽሐፈ ምሥጢር: አርጋኖን: ኆኅተ ብርሃን: ውዳሴ መስቀል: ወዘተ . . . የእርሱ ድርሰቶች ነበሩ)

ስለ ሃይማኖትም ጠበቃ ነበር:: ስለ ቅድስናውና ውለታው የኢ/ኦ/ተ/ቤ እንዲህ ትጠራዋለች:-
1.#ሊቀ_ሊቃውንት
2.#በላዔ_መጻሕፍት
3.#ዓምደ_ሃይማኖት
4.#ዳግማዊ_ቄርሎስ
5.#ጠቢብ_ወማዕምር

ጻድቁ ሊቅ በተወለደ በ60 ዓመቱ በ1418 (1417) ዓ/ም ዐርፏል:: አባ ጊዮርጊስ የተወለደውም ያረፈውም ሐምሌ 7 ቀን ነው::

ይህች ዕለት (ጥቅምት 3 በ1357 / 1358) ቅዱስ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ የተጸነሰባት ናት::

"በረከት በጻድቅ ራስ ላይ ነው:: የኃጥአንን አፍ ግን ግፍ ይከድነዋል:: የጻድቅ መታሠቢያ ለበረከት ነው:: "(ምሳ. 10:7)

"እግዚአብሔር ፍርድን ይወድዳልና::
ቅዱሳኑንም አይጥላቸውምና::
ለዘለዓለምም ይጠብቃቸዋል. . .
ጻድቃን ምድርን ይወርሳሉ::
በእርስዋም ለዘላለም ይኖራሉ::
የጻድቅ አፍ ጥበብን ያስተምራል::
አንደበቱም ፍርድን ይናገራል::
የአምላኩ ሕግ በልቡ ውስጥ ነው::
በእርምጃውም አይሰናከልም:: "
(መዝ. 36:28-31)

✍️† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †✍️
               🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
✍️† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †✍️
               🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

12 Oct, 05:54


አሐዱ ባንክ "ማሕደር" የተሰኘ ለጥቃቅን ፡ አነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተረፕራይዞች የገንዘብ ፍሰት ላይ ትኩረቱን ባደረገ መተግበሪያ ያለመያዣ ብድር መስጠት ሊጀምር መሆኑን አበሰረ፡፡

አሐዱ ባንክ "ከብዙዎች ለብዙዎች" የሚለውን መርሕ ተግባራዊ በማድረግ በጥቃቅን እና አነስተኛ የሥራ ዘርፍ ለተሠማሩ የኢኮኖሚ አንቀሳቃሾች ያለመያዣ የብድር አገልግሎት መስጠት ሊጀመር መሆኑ ተገለፀ፡፡
ይህንን ርዕዩን ተግባራዊ ለማድረግ አሐዱ ባንክ ከኤስኤንቪ (SNV)፣ የኔዘርላንድ ልማት ድርጅት እና ከኬኤምዲ አፕሲስ (KMD Apsis) ጋር በመተባበር በጥቃቅንና አነስተኛ ንግድ ወይም በማምረት ሥራ ላይ ለተሰማሩ የዘርፉ አንቀሳቃሾች ያለመያዣ ብድር ለመስጠት የመጨረሻ ምዕራፍ ላይ መድረሱን አበሰረ ፡፡
የብድር አሰጣጡ ሂደት ተጠቃሚዎቹ የሚኖራቸውን የገንዘብ እንቅስቃሴ ወይም (Cash flow) መሠረት ያደረገ ሲሆን፣ ይህም "ማሕደር" የተባለ ቀላልና አመቺ የቴክኖሎጂ መተግበሪያን በመጠቀም ተበዳሪዎች የንብረት ዋስትና ማቅረብ ሳያስፈልጋቸው ብድር እንዲያገኙ ያስችላል፡፡ በብድር አመላለስ ሒደት ችግርን ለመቀነስ ብድሩ ከመድን ሰጪ ድርጅቶች ጋር በመተባበር የሚሠራ ይሆናል፡፡
ከዚህ ሌላ ደንበኞች ይህንን መተግበሪያ በመጠቀም ሒሳብ መክፈት እና ማንኛውንም የብድር ጥያቄ ማቅረብ የሚችሉበት እድል ተመቻችቷል፡፡
አሐዱ ባንክ በአሁኑ ወቅት፤ ለዘርፉ ትልቅ ትኩረት በመስጠት፤ አጠቃላይ ከሚሰጠው የብድር መጠን እስከ 25% የሚሆነውን ድርሻ ለዚህ ዘርፍ መድቧል፡፡

አሐዱ፡ባንክ
ከብዙዎች ለብዙዎች
የአሐዱ፡ባንክ ማኅበራዊ ትስስር ገጾችን ይቀላቀሉ
??https://linktr.ee/Ahadu_Bank

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

12 Oct, 05:29


🌸ፍትሐ_ነገሥት_ክፍል ፳፮

    አንቀጽ ፳፭ - በእንተ አኅርሞተ ዕቁባት -

በኦሪት ነው እንጂ ክብርት ልዩ በምትሆን በሕጋችን በወንጌልስ ዕቁባት ማኖር አይገባም፡፡ ዕቁባት ማኖር ይሰማ ይልማ ብለው የሚሠሩት ዝሙት ነው፡፡ በብሉይ ዘመን በዚህ ዓለም ሰዎች አንሰው ስለነበረ ዕቁባትና ብዙ ማግባት አልተከለከለም ነበረ፡፡ እንዲሁም ውኁዳነ አእምሮ ውኁዳነ ሥርዓት ስለነበሩ ነው፡፡

በሐዲስ ኪዳን ግን እግዚአብሔር ዕውቀት እንደጸና ሥርዓት እንደሰፋ ባየ ጊዜ ዕቁባት ማኖርን ከለከለ፡፡ አንድ ወንድ በአንዲት ሴት እንዲወሰን ተደረገ፡፡
   
🌸አንቀጽ ፳፮ - በእንተ ሀብት -
ገንዘብ ላለው ለባለጸጋ የሚሰጡት ስጦታ ሀብት ይባላል፡፡ ገንዘብ ለሌለው ለድኻ የሚሰጡት ስጦታ ምጽዋት ይባላል፡፡ ስጦታ ነውር ቢገኝበት ይመለሳል፡፡ ምጽዋት ግን አይመለስም፡፡ ተቀባይ ስጦታውን ከተቀበለ በኋላ በገንዘቡ ማዘዝ መሠልጠን ይገባዋል፡፡ ስጦታን የሚሰጥ ሰጪም አካለ መጠን ያደረሰ፣ አዋቂ፣ ራሱን የቻለ ሊሆን ይገባል፡፡ ሰጪ ቢሞትም ስጦታ አይመለስም፡፡ ሰጭ ልቡናው ድል የሚነሣበትን ገንዘብ መስጠት አይገባውም፡፡
  🏵️አንቀጽ ፳፯ - በእንተ ልቃሕ -
ይህ አንቀጽ በመያዣ በዋስ ማበደር መበደር እንደሚገባ ይናገራል፡፡ ብድር የምጽዋት ወገን ናት፡፡ በረኀብ ዘመን በዓይነታው ማበደር ከምጽዋት ቁጥር ነውና፡፡ ተበዳሪ ብድሩን ለመክፈል ማሰብ መትጋት ይገባዋል፡፡ የሚከፍለውን እስኪያገኝ ድረስም አበዳሪ ተበዳሪን መታገሥ ይገባዋል፡፡ ተበዳሪ የምከፍለውን ገንዘብ አጣሁ ቢል አበዳሪ ከተበዳሪ ገንዘብ በዳኛ ትእዛዝ ያገኘውን መውሰድ ይገባዋል፡፡ አራጣ ከመቀበል መራቅ ይገባናል፡፡ ከሰው ገንዘብ ያለው ሰው እስከ ሠላሳ ዘመን ስጠኝ ባይለው ከሠላሳ ዘመን በኋላ ተመልሶ ገንዘቤን ስጠኝ ማለት አይገባውም፡፡ አባት በልጁ ብድር ወንድም በወንድሙ ብድር መያዝ አይገባቸውም፡፡ አድኅኖሰ ዘነፍስ ውእቱ፡፡ አድኅኖ የእጅ ዋስ ነው፡፡ ወተሐብዮ ዘንዋይ፡፡ ተሐብዮ የገንዘብ ዋስ ነው፡፡ ገንዘብ ላለው ሰው ሊዋሱት ይገባል፡፡ ለአበዳሪ የሚገባው አስቀድሞ ተበዳሪን መያዝ ነው፡፡ ተበዳሪው ባይከፍለው ዋሱን መያዝ ይገባዋል፡፡ ዋሶች አራት ቢሆኑ ዕርቦ ዕርቦውን ይክፈሉ፡፡ የእጅ ዋስ የሆነ ሰው እጁን ማቅረብ ይገባዋል፡፡ ካህን አንዱንስ እንኳ በጭዋ ዳኛ ቁሞ መዋስ ማዋስ መያዣ መያዝ ማስያዝ አይገባውም፡፡ ሴት ዋስ መሆን አይገባትም፡፡
      🏵️አንቀጽ ፳፰ - በእንተ ሕስት
ይህ አንቀጽ የውሰትን ነገር ይናገራል፡፡ ሕስት ዋጋ ሳይሰጡና ዋጋን ሳይቀገበሉ መዋስ ማዋስ ነው፡፡ እስከዚህ ቦታ ብሎ ከብት የተዋሰ ሰው ቢኖር እና አልፎ የሔደ ቢሆን የተዋሳት ከብት ጥፋት ቢያገኛት ብትሞት መክፈል ይገባዋል፡፡ አልፎም ባይሔድ በስንፍናውና በቸልታ ምክንያት ችግር ቢደርስባት መክፈል ይገባዋል፡፡ ወይም በገደል አፋፍ ሆና ስትበላ አይቶ ዝም ቢልና ችግር ቢደርስባት መክፈል ይገባዋል፡፡ ብትጠፋ ጥፋቷ በዋጋዋ ይሆናል፡፡
 
🏵️አንቀጽ ፳፱ - በእንተ ማኅፀንት
ይህ አንቀጽ ስለአደራ ይናገራል፡፡ አደራ አስጠባቂ ለጠባቂ ይጠብቃት ዘንድ የሚሰጣት ገንዘብ ናት፡፡ አስጠባቂ ከጠባቂ ዘንድ አምኖ የሚያኖራት ገንዘብ ናት፡፡ የተቀበላትም ሰው በፍጹም ትጋት መጠበቅ ይገባዋል፡፡ ተግቶ እንደገንዘቡ አድርጎ ሲጠብቃት ብትጠፋ ዕዳ የለበትም፡፡ አደራን እንደገንዘብ አድርጎ መጠበቅ ይገባል፡፡ ለባለቤቱ እስኪመልስለት ድረስ አደራውን ይጠብቅ፡፡ አደራ ያስጠበቀው ሰው ቢሞት ለወራሾቹ ይመልስላቸው፡፡ አደራውን እንደገንዘቡ አድርጎ ባለመንከባከቡ አደራው ቢጠፋ ጠባቂው መክፈል ይገባዋል፡፡ አደራ ጠብቆ መመለስ ለለመደ ነው እንጂ ላልለመደ መስጠት አይገባም፡፡
     🏵️አንቀጽ ፴ - በእንተ ምግብና
ይህ አንቀጽ የሹመትን ነገር ይናገራል፡፡ ግብሩ ጠባዩ ያማረ፣ የሹመትን ሥርዓቷን ያወቀ የጠነቀቀ መሾም ይገባዋል፡፡ የጌታው ገንዘብ ያለተንኮል ያለስንፍና በሹሙ እጅ ቢጠፋ መክፈል አይገባውም፡፡ ሹም በቃሉ ነግሮ በመልእክት ልኮ ጌታው ካዘዘው ወጥቶ መግዛት አይገባውም፡፡

© በመ/ር በትረ ማርያም አበባው
         ክፍል-፳፯- ይቀጥላል. . .
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
               🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

12 Oct, 05:09


👆👆👆ከላይኛው የቀጠለ
ከሚጋቡት ሰዎች አንዱ ድንግል ከሆነ ለድንግሉ/ሊቱ ተክሊል ለሌላኛው ፍትሐት ዘወልድ ይደገምለታል/ላታል፡፡ ከአራተኛ ጋብቻ የተወለዱ ልጆች ለክህነት ለርስት አይገቡም፡፡ ሁለት ሴት አግብቶ በአንድ ላይ ማኖር አልተፈቀደም፡፡ ይህንን ያደረገ ሰው ካለ ሁለተኛይቱን እስኪፈታ ድረስ ቤተክርስቲያን ከመግባት ሥጋውን ደሙን ከመቀበል ይከልከል፡፡
የአመነች ሴት ያላመነውን ወንድ ብታገባ ከምእመናን ትለይ፡፡ ከእርሱ ተለይታ ንስሓ ብትገባ ግን ይቀበሏት፡፡ እህቱን ልጁን ለኢአማኒ ያጋባ ሰው ካጋባት ሰው እርሷን ለይቶ ንስሓ እስኪገባ ከምእመናን ይለይ፡፡
ባል ለሚስቱ የሚገባውን ፍቅር ያድርግላት፡፡ ሴትም ለባሏ የሚገባውን ፍቅር ታድርግለት፡፡ ባልና ሚስት ሊገናኙባቸው የማይገቡ ዕለታት በሴቷ የወር አበባ ጊዜ፣ ልጇ ክርስትና እስኪነሣ በአራስነቷ ጊዜ፣ ልጃቸው ክርስትና ከተነሣ በኋላ ስለ ክብረ መንፈስ ቅዱስ ሁለት ቀን፣ በፊት ሁለት ቀን ከሩካቤ መከልከል ይገባል፡፡

ጋብቻን ርኩስ ነው የሚል ቢኖር የተወገዘ ይሁን፡፡

ከደሟ ያልነጻች ሴት ወደቤተ ክርስቲያን አትግባ፡፡ የደሟ ወራት እስኪፈጸም ድረስ አትግባ፡፡ ይህን ተደፋፍሮ ወደቤተክርስቲያን ያስገባ ካህን ቢኖር ከሹመቱ ይሻር፡፡

አራስ ሴትም ወንድ ከወለደች አርባ ቀን ሴት ከወለደች ሰማንያ ቀን ቤተ ክርስቲያን ከመግባት ትከልከል፡፡ አዳም ልጅነት አግኝቶ ገነት የገባ በአርባ ቀን ነውና፡፡ ሔዋን ልጅነት አግኝታ ገነት የገባች በሰማንያ ቀን ነውና፡፡

አዋላጆችም ወንድን ካዋለዱ ለ፳ ቀን ሴትን ካዋለዱ ለ፹ ቀን ሥጋውን ደሙን አይቀበሉ፡፡ የቄስ ሚስት ባሏ ከሞተ በኋላ ሌላ ብታገባ ንስሓ ይገባታል አለ በታች መቆም በኋላ መቀበል ይገባታል ነው፡፡

ጋብቻ በሦስት ነገር ይፈርሳል፡፡ አንዱ ባልና ሚስት ተመካክረው በፈቃዳቸው ከመነኮሱ ነው፡፡ ሁለተኛው አንዱ የአንዱን ፈቃድ አልፈጽምም ሲል ጋብቻ ይፈርሳል፡፡ ሦስተኛው በዝሙት ምክንያት ይፈርሳል፡፡ ሚስት ባሏን ሌሎች ሊገድሉት እንደመከሩበት እያወቀች ባትነግረው ጋብቻ ይፈርሳል፡፡

© በመ/ር በትረ ማርያም አበባው
         ክፍል-፳፮- ይቀጥላል. . .
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
               🌹🌹🌹
👇👇👇ቤተሰብ ይሁኑ👇👇👇
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar
       https://t.me/Sinksar

🌹የዩቲዩብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

ስንክሳር እና ወቅታዊ የቤ/ክ ጉዳዮች

12 Oct, 05:04


🌸ፍትሐ_ነገሥት_ክፍል ፳፭
     🌹አንቀጽ ፳፬ - በእንተ ፍኅረት -
የጋብቻ ዓላማ አንደኛው ዘር ለመተካት ነው፡፡ ሁለተኛው ለአቅልሎ ፍትወት ነው፡፡ ሦስተኛው ለተራድኦ ነው፡፡ ወንድ ከሴት ሔዶ ማጨት ይገባዋል፡፡ ቃል የመርዓዊ፣ ትስብእት የመርዓት ምሳሌ፡፡ ቃል ሽቶ ተዋሕዷል እንጂ ሥጋ ሽቶ አልተዋሐደምና ሔዶ ይጭ አለ፡፡

በፈቲው ፆር ሲናደዱ ከመኖር ማግባት ይሻላል፡፡ አንተ ሰው ሚስት ብታገባ ልፍታት አትበል፡፡ ያገባ ሰው መልካም አደረገ፡፡ ይልቁንም ያላገባ ሰው መልካም አደረገ፡፡
አባለ ዘርን ቆርጦ መጣል ትልቅ በደል ነው፡፡ ማግባት በኦሪትም በወንጌልም የተፈቀደ ነው፡፡ ንጽሕ ጠብቄ እኖራለሁ ብሎ ከተሳለ በኋላ ማግባት ኀፍረት ነው፡፡ ይህ ሰው ቢያገባ ፍርዱ ሁለተኛ ሴት እንዳገባ ፍርድ ይሆናል፡፡
በሁለተኛ ግቢ ጸሎተ ተክሊል አይደገምም፡፡ ተጋቢዎች ፍትሐት ዘወልድ ተደግሞላቸው ይጋባሉ እንጂ፡፡
ሁለተኛ ማግባት ክህነትን ታፈርሳለች፡፡ ከሦስተኛ ጋብቻ በኋላ መጽሐፍ ያዘዘው ጋብቻ የለም፡፡
ቅዱሳን ጋብቻን ዘር ለመተካት እንጂ ዝሙትን ሽተው አላደረጉትም፡፡

ወንድ ጽንሷ ከገፋ ሆዷ ከገፋ በኋላ ከሚስቱ ጋር መገናኘት አይገባውም፡፡ ለማያገባ ሰው ማጨት አይገባም፡፡ የሚያጭ ልጅ በሐፃኒ በመጋቢ እጅ ካልሆነ ለራሱ ሔዶ ማጨት ይገባዋል፡፡
ጋብቻ ከሚከለከልባቸው ዝምድናዎች አንዱ 👉የሥጋ ዝምድና ነው፡፡ በዚህም በአንድ ወገን ሰባት በአንድ ወገን ሰባት ሆኖ በስምንተኛው መጋባት ነው፡፡ የአበልጅም እንደዚሁ ነው፡፡
👉ሁለተኛው የክርስትና ዝምድና ነው፡፡
👉ሦስተኛው ዝምድና የማደጎ ዝምድና ነው፡፡ የማደጎ ዝምድና አንድ ሰው አንድን ልጅ ከቤቱ ወስዶ ቢያሳድገው ነው፡፡
👉አራተኛው ጋብቻ የሚከለከልበት ዝምድና የጋብቻ ዝምድና ነው። የጌታ ሚስት ባሏ ነጻ ያወጣውን ባሪያ ማግባት አይገባትም፡፡ ልጇን እንደማግባት ይቆጠራልና፡፡
ወንድ በሃይማኖት ከእርሱ ልዩ የሆነችን ሴት ማግባት አይገባውም፡፡ ሴትም እንደዚሁ፡፡ ጋብቻን የሚከለክሉ ሁኔታዎች የሚከተሉት ናቸው፡፡ ከእናቱ ማኅፀን ጀምሮ ባልደረባ ሆኖ የተወለደ (ለመሽኛ ያህል የሽንብራ አፍንጫ የምታህል አባለ ዘር ያለው) አያግባ።

ፈናፍንታም አያግባ፡፡ ፈናፍንታም የሚባለው የሴትም የወንድም የጾታ ምልክት ያለበት ሰው ነው፡፡ ፈናፍንት ሲጠመቅ የሚሸናበት ጾታ ታይቶ በወንዱ አካል የሚሸና ከሆነ በ፵ኛው ቀን፣ በሴት የጾታ ምልክት የሚሸና ቢሆን በሰማንያ ቀን ይጠመቃል፡፡ ሴትም ሩካቤን የሚከለክል አፅም ካለባት ልታገባ አይገባም፡፡ አካልን የሚቆራርጥ ደዌ ሥጋ ያለበት ሰውም አያግባ፡፡ ስትሰስን ተገኝታ የተፈታችውን ሴት ንስሓ እስክትገባ ድረስ አያግቧት፡፡
መነኮሳትን ማግባት አይገባም፡፡
ከስልሳ ዓመት በላይ የሆናትን ሴት ማግባት አይገባም፡፡
የባሏን ሙት ዓመት ያልፈጸመችን ሴት ማግባት አይገባም፡፡ ከዐሥር ወር በኋላ ግን ማግባት ትችላለች፡፡ ወንድም እንዲሁ፡፡ ከዚህ አስቀድሞ ያገባ ወንድ ግን የሚስቱን ገንዘብ ከመውረስ ይከልከል፡፡ ሚስትም ከዚህ አስቀድማ ካገባች የባሏን ርስት ከመውረስ ትከልከል፡፡
እስከ ዐሥር ወር ባለው ግን ማግባት ነው እንጂ የማይገባ መተጫጨት ይቻላል፡፡
ከሐፃኒ ከመጋቢ በታች ያለ ሕፃን ሐፃኒ መጋቢ ሳይፈቅድለት ማጨት አይገባውም፡፡
በባልና ሚስት ፈቃድ ነው እንጂ ያለሁለቱ ፈቃድ አያጋቧቸው፡፡
ያጨ ሙሽራ ማጫ ከሰጠ የታጨች ሙሽሪት ማጫ ከተቀበለች በኋላ አንዱ ሊመነኩስ ቢወድ ያጨ ሰው አስቀድሞ የሰጣት ማጫውን መቀበል ይገባዋል፡፡
መተጫጨት መልክን፣ ጠባይን፣ ዝምድናን ለመመርመር ነው፡፡ መተጫጨት ከጋብቻ ቀድሞ የሚደረግ ቃል ኪዳን መግባባት ነው፡፡ በደብዳቤም ያለደብዳቤም ይሆናል፡፡
ካህናት የሚተጫጩትን እጅ ለእጅ አያይዘው መስቀል አስጨብጠው አንድ ቀለበት አድርገው ያተጫጯቸዋል፡፡
በባሏ ሞት ያዘነች ሴት ከመታጨት አትከልከል፡፡
አዳም ከሰባት ቀን አስቀድሞ ሔዋንን እንዳላገኘ ሰባት ዓመት ላልሆነው ሕፃን ማጨት አይገባም፡፡
አጭቶ ለማግባት ቀን ያልወሰነ ሰው በሀገር ያለ ቢሆን ሁለት ዓመት ይጠብቁት፡፡
ሩቅ ሀገር የሔደ ቢሆን ሦስት ዓመት መጠበቅ ይገባል፡፡
በታወቀ ምክንያት የቀረ ቢሆን አራት ዓመት መጠበቅ ይገባል፡፡
አባት ከሥልጣኑ በታች ያለች ሴት ልጁን ወደድኩ ብሎ መስጠት ጠላሁ ብሎ መንሣት ይገባዋል፡፡
ዓረቦን የተቀበለ ሰው ከተቀበለ በኋላ አይሆንም ቢል ውሉን ቢያፈርስ የወሰደውን ዓረቦን እጥፍ አድርጎ ይመልስ፡፡
ዓረቦን የሰጠ ሰው አይሆንም ቢል የሰጠው ዓረቦን ይቀራል፡፡
የታጨች ሴት ብትሞት ያጫት ሰው ስለእርሷ የሰጠውን ገንዘብ ከዘመዶቿ ይቀበል፡፡ ያጩለት ሰው ቢሞት ወራሽ ባይኖረው ለሴቷ ከእርሱ የተቀበለችውን ዓረቦን ይተዉላት፡፡
ወራሾች ቢኖሩ ግን እኩሌታውን ገንዘብ ይመልሱላቸው፡፡ እኩሌታው ይቅርላት፡፡

ወንዶች ፈጽመው አካለ መጠን የሚያደርሱበት ኻያ ዓመት ነው፡፡ ይህም ባይሆን ኻያ አምስት ዓመት ነው፡፡
ሴቶችም አካለ መጠን የሚያርሱት ዐሥራ ሁለት ዓመት ነው፡፡ ይህም ባይሆን ዐሥራ አምስት ዓመት ነው፡፡
ልጁ በንጽሕና እኖራለሁ ካለ አባት ግድ አግባ ማለት አይገባውም፡፡ ኻያ አምስት ዓመት የሆናት ሴት ራሷን ችላ የምትኖር ከሆነች በራሷ ፈቃድ ባል ማግባት ይገባታል፡፡
ጋብቻ በባልና በሚስት ፈቃድ ነው እንጂ ያለሁለቱ ፈቃድ ሊሆን አይገባም፡፡
የሚጋቡት ሴትና ወንድም አካለ መጠን ያደረሱ ሊሆኑ ይገባል፡፡ አንዲት ሴት አካለ መጠን ሳታደርስ ብታገባ የሕግ ሚስት አትባልም፡፡ ወማዕሠረ ተዋስቦሰ ኢይከውን ወኢይትፌጸም ዘእንበለ በሀልወተ ካህናት፡፡ የጋብቻ አንድነት ካህናት ቢኖሩ ነው እንጂ ካህናት ከሌሉ አይጸናም አይፈጸምም፡፡ ተክሊል ቢያደርሱላቸው፣ ሥጋውን ደሙን ቢያቀብሏቸው ነው እንጂ ያለዚህ ጋብቻ አይፈጸምም፡፡ ጋብቻውም አይቆጠርም፡፡ ወንድን ከሴት ሴትን ከወንድ አንድ የምታደርግ ጸሎት ናት፡፡ የተክሊል ሥርዓት እንዲህ ነው፡፡ የወንድ ወገኖች ወንዱን ይዘው በሰሜን የሴት ወገኖች ሴቲቱን ይዘው በደቡብ ይገባሉ፡፡ በደቡብ በኩል ዙፋን ይዘረጋል፡፡ ግራ ቀኝ መከዳ ይደረጋል፡፡ ከዚያ ላይ ያስቀምጧቸዋል፣ አንድ ልብስ ያለብሷቸዋል፣ ከጣታቸው አንድ ቀለበት ያገቡላቸዋል፣ ቀለበቱ ጠባብ ከሆነ ፊት ወንዱ አግብቶ ለሴቲቱ ይሰጣታል፣ አንድ መስቀል ያስጨብጧቸዋል፣ አንድ ዘውድ ይደፉላቸዋል ማለት እርሱ ደፍቶ ለእርሷ ይሰጣታል፣ አንድ ልብስ አልብሰው ያቆርቧቸዋል ቦታ ስለማያገናኛቸው እርሱ ቆርቦ ለእርሷ ይሰድላታል፡፡ እርሷ ቆርባ ልብሱ ከዕቃ ቤት ገብቶ ይቀመጣል፡፡ አርባው ቀን ሲፈጸም ሠርጉን ያደርጉላቸዋል፡፡ ልብስ የልጅነት፣ ቀለበት የሃይማኖት፣ ዘውድ የክብራቸው፣ መስቀል የመከራቸው ምሳሌ ነው፡፡

ካህን ሁለተኛ ካገባ ከክህነቱ ይሻራል፡፡ ምእመን ሚስቱ ብትሞትበት ወይም በሌላ ምክንያት ቢፋቱ ሁለተኛ እንዲያገባ ይፈቀድለታል፡፡ ሁለተኛው ብትሞትበት ሦስተኛ እንዲያገባ ይፈቀድለታል፡፡ ከሦስተኛ በላይ ጋብቻ ግን አይፈቀድም፡፡ ሴት ልጅ ስልሳ ዘመን ከሆናት በኋላ ብታገባ ከምእመናን ትለይ፡፡ መጽሐፈ ተክሊል የሚደረሰው ለድንግል ወንድና ለድንግል ሴት ነው፡፡
ይቀጥላል
👇👇👇

2,674

subscribers

1,847

photos

78

videos