ፍኖተ ሕይወት

@nshachannel


ይህ ቻነል ለነፍሳችን ያለንን ግንዛቤ ለማሳደግ ብቻ የተከፈተ ቻናል ነው።በዚህ ቻናል ማንኛውንም አይነት መጽሐፍት መዝሙር እና ትምህርት ከፈለጉ በቻልነው ፍጥነት እናደርስዎታለን። ጥያቄ ካለዎት በኮሜንት መስጫ ላይ ያድርሱን።

ወልደ ገብርኤል 🙏

ፍኖተ ሕይወት

04 Oct, 15:39


ክርስቶስን አንዘንጋ ፤🙏 የሚገባውን ስጦታ ከሱ አናስቀርበት።

ፍኖተ ሕይወት

30 Apr, 20:39


"የምትወዱት ሰዎች ፈጽሞ አልቅሱለት፡፡"

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

አባቱ ሞቶ የማያለቅስ ማን ነው?? አባቱ በሞተበትስ ሰሞን ዘፈንና ተደላ ደስታን የማይተዋት ማን ነው?? ክርሰቶስ ስለ እኛ ሲል ሁሉንም ተወ፦ መንግሥቱን መላእክቱን ክብሩን ሁሉንም ትቶ ስለ እኛ ስለሰው ልጆች ሰው ሆነ። በምላሹ አኛ አንድስ በደል እንኳን ስለስሙ መተው አቃተን። ዘፈን ዝሙትን ስንፍናን ስለስሙ እንተው። እርሱ ከተወልን እኛ የተውንለት አይበልጥምና ስለ ፍጹም ፍቅሩ ከኃጢአት እንራቅ።

"የምትወዱት ሰዎች ፈጽሞ አልቅሱለት፡፡"[ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ]

ፍኖተ ሕይወት

30 Apr, 07:18


ስለ ሰሙነ ሕማማት የእለት ስያሜዎች ያውቁ ኖሯል?

ሰኞ፡-
አንጽሖተ ቤተ መቅደስና መርገመ በለስ የተፈጸመበት ዕለት ነው፡፡ የሆሣዕና ዕለት ቢታንያ ያድራል፡፡ በማግስቱም ከቢታንያ ሲመጣ ተራበ ወበሳኒታ ወፂኦ እምቢታንያ ርኅበ ወርእየ በለሰ እምርኁቅ ወባቲ ቈጽለ ወሖረ ይርአይ እመቦ ዘይረክብ ፍሬ በውስቴታ ወበጺሖ ኀቤሃ አልቦ ዘረከበ ዘእንበለ ቈጽል ባሕቲቱ እስመ ኢኮነ ጊዜሁ ለበለስ፣ ቅጠል ያላት በለስ ከሩቅ ዓይቶ ወደ በለሲቱ ቀረበ፤ ነገር ግን ከቅጠል በቀር አንዳችም ፍሬ አላገኘባትም፤ ወአውሥአ ወይቤላ ለዓለም አልቦ ዘይበልዕ ፍሬ እምኔኪ እንከ፣ ከአሁን ጀምሮ ማንም ከአንቺ ፍሬ አይብላ ብሎ ረገማት፡፡ /ማር. 11፤11-12/
በለስ የተባለች ቤተ እስራኤል ናት፡፡ ፍሬ የተባለች ሃይማት ምግባር ናት፡፡ ከእስራኤል ፍቅርን ሃይማኖትን ምግባርን ፈለገ አላገኘም፡፡ እስራኤል ሕዝበ እስራኤል መባል እንጂ ደግ ሰው አይገኝብሽ ብሎ ረገማት፡፡ በመርገም ምክንያት እርሱ ከላያቸው በስተቀር ደግ ሰው ጠፋባት፡፡
አንድም በለስ ኦሪት ናት፡፡ በዚህ ዓለም ሰፍና ቢያገኛት ኦሪትና ነቢያትን ልሽር አልመጣሁም ልፈጽም እንጂ በማለት ፈጸማት፡፡ እጸ በለስን ፍሬ በአንቺ አይሁን አላት፡፡
አንድም በለስ ኃጢአት ናት፡፡ የበለስ ቅጠል ሠፊ እንደሆነች ኃጢአትም በዚህ ዓለም ሥፍራ ሰፍና አገኛት፡፡ በለስ ሲበሉት ይጣፍጣል፤ ቆይቶ ግን ይመራል፡፡ ኃጢአትም ሲሠሩት ደስ ያሰኛል፡፡ ኋላ ግን ያሳዝናል፡፡ ወደ እርሷ ሄደ ማለትም ከኃጥአን ጋር ዋለ፣ ኃጥእ ከመባል በቀር በመዋዕሉ ኃጢአት አለመሥራቱን ለመመልከት ፍሬ አላገኘባትም አለ፡፡ በአንቺ ፍሬ አይገኝ የሚውሉም በኃጢአት በፍዳ ተይዞ የሚቀር አይኑር ለማለት ነው፡፡ ስትረገም ፈጥና መድረቋም በአዳም በደል ያገኛትን እዳ በደል በእርሱ እንደጠፋችልን ለመግለጽ ነው፡፡
በመቀጠልም ወደ ቤተ መቅደሰ ሄደ፡፡ ቤተ መቅደስ ቤተ ጸሎት፣ ቤተ መሥዋዕት መሆኑ ቀርቶ ቤተ ምስያጥ /የንግድ ቤት/ ሁኖ ቢያገኘው ቤትየሰ ቤተ ጸሎት ትሰመይ፣ ቤቴ የጸሎት ቤት ትባላለች፡፡ እናንተ ግን የወንበዴዎች ዋሻ አደረጋችኋት ብሎ የሚሸጡበትን ሁሉ ገለበጠባቸው፤ ገርፎም አስወጣቸው፡፡ /ማር. 11፤17-19/ ይህም የሚያሳየው ማደሪያ ቤቱ የነበርን የአዳም ልጆች ኃጢአት ሰፍኖብን ስንኖር ቢያገኘን ኃጢአታችንን ሁሉ እንዳራቀልን የሚገልጽ ነው፡፡
በሰሙነ ሕማማት ካህናትና ምእመናን በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ተገኝተው ወዛቸው ጠብ እስኪል ድረስ በነግህ፣ በሠለስት፣ በስድስት ሰዓትና በተሰዓቱ ሰዓት መላልሰው ሲሰግዱና ሲጸልዩ ይሰነብታሉ፡፡ በተለይም ካህናት በማንኛውም አገልግሎት ጥቁር ልብስ ይለብሳሉ፡፡ ምክንያቱም የደረሰበትን መከራ ኀዘኑንና 5500 ዘመን የሰው ልጅ በጨለማ ሕይወት ይኖር እንደነበር ለማዘከር ነው፡፡

ማክሰኞ፡-

የጥያቄ ቀን በመባል ይታወቃል፡፡ምክንያቱም ሹመትን ወይም ሥልጣንን ለሰው ልጅ የሰጠ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ሰኞ ባደረገው አንጽሖተ ቤተ መቅደስ ምክንያት በዚህ ዕለት ስለ ሥልጣኑ በጸሐፍት ፈሪሳውያን ተጠይቋልና፡፡
ጥያቄውም ከምድራውያን ነገሥታት፣ ከሌዋውያን ካህናት ያይደለህ ትምህርት ማስተማር፣ ተአምራት ማድረግ፣ ገበያ መፍታት በማን ሥልጣን ታደርጋለህ? የሚል ነበር ይህንስ ሥልጣን እነዚህን እንዳደርግ እነግራችኋለሁ፡፡ የዮሐንስ ጥምቀት ከወዴት ነበረች? ከሰማይ ወይስ ከሰው? አላቸው፡፡ እነርሱም ከሰማይ ነው ብንል ለምን አልተቀበላችሁትም? ይለናል፡፡ ከሰው ነው ብንል ሕዝቡ ሁሉ ዮሐንስን እንደ አባት ያከብሩታል፤ እንደ መምህርነቱም ይፈሩታልና ሕዝቡን እንፈራለን ተባብለው ወዴት እንደሆነ አናውቅም ብለው መለሱለት፡፡ እርሱም በማን ሥልጣን እነዚህን እንደማደርግ እኔም አልነግራችሁም አላቸው፡፡ ይህንንም መጠየቃቸው እርሱ የሚያደርጋቸውን ሁሉ በራሱ ሥልጣን እንዲያደርግ አጥተውት አልነበረም፡፡ ልቡናቸው በክፋትና በጥርጥር ስለተሞላ ነው እንጂ፡፡ ከዚህ የምንማረው የእነሱን ክፉ ጠባይና ግብር መከተል እንደማይገባን ነው፡፡
በዚህ ዕለት በቤተ መቅደስም ረጅም ትምህርት ስላስተማረ የትምህርት ቀንም ይባላል፡፡ ይኸውም ከሃይማኖት የራቁትን፣ ከፍቅረ እግዚአብሔር የተለዩትን አስተምሮ ማቅረብ፣ መክሮ መመለስ እንደሚገባ ሲያስተምር ነው፡፡

የዘገየበትን ምክንያት የፖስት መደራረብ እንዳይኖር ነው። ከዘገየን ይቅርታ🙏🙏😊😊

ፍኖተ ሕይወት

¶¶@nshachannel
¶¶@nshachannel

ፍኖተ ሕይወት

29 Apr, 19:28


ሕማማትን በተመለከተ ብዙ ሰዎች በስልክም በጽሑፍም ጠይቃችሁኛል። ሥርዓተ ሕማማት።

፩) ከዕለተ ኃሙስ በስተቀር ሰላምታ አልተከለከለም።

፪) በሰሙነ ሕማማት ማንኛውም በዓል ቢውል ይሰገድበታል። ዓርብ ስቅለትኮ ከዐበይት በዓላት አንዱ ነው። በዚያ ቀን የሚሰገድ ከሆነ በሌላው የማይሰገድበት ምክንያት የለም።

፫) ሰው ቢሞት ፍትሐት አይኖርም። በሰሙነ ሕማማት ለሚሞቱ ሰዎች ጸሎተ ፍትሐት የተከናወነው እሑድ በዕለተ ሆሣዕና ነው።

፬) ቀሳውስት መስቀል ማሳለም የለም።

፭) በባዶ እግር መሄድ ግዴታ አይደለም።

እንበለ ደዌ ወሕማም
እንበለ ጻማ ወድካም
ያብጽሐኒ ያብጽሕክሙ እግዚአብሔር
በፍሥሓ ወበሰላም።

© በትረማርያም አበባው

(የመጻሕፍተ ሊቃውንት የመጻሕፍተ ብሉያትና የመጻሕፍተ መነኮሳት ትርጓሜ መምህር)

ስለ ሀይማኖት መምህራን ሊቃውንትን እንጠይቅ በተለይ የመጽሐፍ መምህር የሆኑ መጽሐፍትን ጠንቅቀው የሚያውቁ ቢሆን ይመረጣል

ፍኖተ ሕይወት

29 Apr, 19:24


በሰሙነ ሕማማት የተከለከሉ ወይም ማድረግ የማይቻሉ ነገሮች እና የሚፈቀዱ ወይም ማድረግ የሚቻሉ ነገሮች፦

አራት ዓይና መምህር ስምዓኮነ መልአክ

መምህር ብርሃን አድማስ፦ ንስሐ ስግደት እና ጸሎት

ፍኖተ ሕይወት

28 Apr, 00:23


ፍኖተ ሕይወት

¶¶@nshachannel
¶¶@nshachannel

ፍኖተ ሕይወት

27 Apr, 19:32


ሆሣዕና የዐብይ ጾም ስምንተኛ ሳምንት

ሆሣዕና ከስምንቱ የዐቢይ ጾም እሑዶች አንዱና የመጨረሻው ሳምንት ተብሎ የሚጠራው ከትንሣኤ ቀድሞ የሚገኝ የሕማማት መገቢያ ዋዜማ ነው።

ሆሣዕና አስቀድሞ ካለው ረቡዕ ጀምሮ የሚታሰብ ታላቅ የቤተክርስቲያን የበዓል ቀን እንደሆነ ይታወቃል። ይህን ስም በዚሁ ሰንበትና በዋዜማዎቹ ዕለታት የሚዘመረው ጾመ ድጓ ‘ሆሣዕና በአርያም’’ ‘ሆሣዕና ለወልደ ዳዊት’’ ‘ዕለተ ሆሣዕናሁ አርዓየ… ‘ ወዘተ. በማለት ሆሣዕና የሚለውን ቃል ቅዱስ ያሬድና ሌሎችም አባቶች በየቦታው እየጠቀሱና እየተዘመረለት በአህያ ውርንጭላ ላይ ተቀምጦ ኢየሩሳሌም የገባበትን ሁኔታ እየተረከ ስለሚዘምር ይህ ሰንበት በጌትነትና በክብር በውዳሴና ቅዳሴ ሆሣዕና በአርአያም እየተባለ በሽማግሌዎችና በሕፃናት አንደበት በድንጋዮችም ልሳን ሳይቀር እየተመሰገነ ወደ ቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌም በከብር ሲገባ ለሰጣቸው ለተቀደሰ ሰላሙና ፍቅሩ መታሰቢያ ሆኖ የተሰጠ ነው።
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ “ሌላ ቀን እንደ ተራ ሰው ሆኖ ወደ ኢየሩሳሌም ይገባ ነበር፡፡ በዚህ ቀን ግን የአይሁድ ንጉሥ ሆኖ በክብር ገባ፡፡ ከቢታንያ ተነሥቶ ደብረ ዘይት ሲደርስ ከሐዋርያቱ ሁለቱን በቤተፋጌ ሰው ተቀምጦባት የማያውቅ ውርንጭላ እንዲያመጡለት ላካቸው፡፡ “በፊታችሁ ወዳለችው መንደር ሒዱ በዚያን ጊዜም የታሰረችን አህያ ውርንጫም ከእርሷ ጋር ታገኛላችሁ፤ ፈትታችሁም አምጡልኝ፡፡ ማንም አንዳች ቢላችሁ ለጌታ ያስፈልጉታል በሉ" አላቸው፡፡ ማቴ.21፡1-17
ወደ ቤተፋጌም ሄደው አህያዪቱን አገኙአት፡፡ ሲፈቱአትም ሳለ ባለቤቶቹ መጡባቸውና አስቆሟቸው፡፡ እነርሱም ኢየሱስ እንደፈለጋት ነገሩአቸው፡፡ ባለቤቶቹ ይህንን ሲያውቁ ተውአቸው፡፡ ሐዋርያትም የአህያዪቱን ውርንጭላ ፈትተው ወደ ኢየሱስ ወሰዱ፡፡ አጠገቡም ሲደርሱ ልብሳቸውን በአህያዪቱ ውርንጭላ ላይ አንጥፈው ኢየሱስን አስቀመጡት፡፡
ለምን ዘንባባ ያዙ ቢባል፤ ዘንባባ እሾሃም ነው ፤አንተም የኃይል የድል ምልክት አለህ ሲሉ፤በሌላም በኩል ዘንባባ እሳት ለብልቦ ይተወዋል እንጂ አይበላውም አንተም ባህርይህ አይመረመርም ሲሉ፤አንድም ዘንባባ ረጅም /ልዑል/ ነው አንተም ባሕርይህ ልዑል ነው ሲሉ ዘንባባ ይዘው ተቀብለውታል፡፡

የተምር ዛፍ ዝንጣፊ ነው ቢሉ፤ ተምር ፍሬው አንድ ነው አንተም ባህርይህ አንድ ነው ሲሉ፡፡አንድም፤ተምር ልዑል/ረጅም/ ነው አነተም ልዑለ ባህርይ ነህ ሲሉ፡፡ አንድም፤የተምር ፍሬው በእሾህ የተከበበ ነው በቀላሉ መለቀም አይቻልም ፤የአንተም ምስጢር አነተ ካልገለጠከው አይመረመርም ሲሉ ነው፡፡
የወይራ ዛፍ ዝንጣፊ ነው ቢሉ፤ ወይራ ጽኑዕ/ ጠንካራ/ ነው አንተም ጽኑዓ ባህርይ ነህ ሲሉ፤አንድም ወይራ ለመስዋዕት ይሆናል፤ አንተም መስዋዕት ትሆናለህ ሲሉ፤አንድም ወይራ ዘይቱ ለመብራት ይሆናል አንተም የዓለም ብርሃን ነህ ሲሉ ይህንን ይዘው አያመሰገኑ ተቀበሉት፡፡
ልብሳቸውንም ማንጠፋቸው፤ እንኳን አንተ የተቀመጥክባት አህያ እንኳን መሬት መርገጥ አይገባትም ሲሉ ልብሳቸውን አነጠፉለት፡፡ እነዚያ ያላመኑ አይሁድ ለተቀመጠባት አህያ ይህንን ያህል ክብር ከሰጡ፤ በድንግልና ጸንሳ ለወለደችው እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ምን ያህል ክብር ልናድረግለት ይገባን ይሆን?፡፡         
“የጽዮን ልጅ ሆይ አትፍሪ እነሆ ንጉሥሽ በአህያ ውርንጭላ ላይ ተቀምጦ ይመጣል” ዘካ.9፡9 የሚለው የዘካርያስ ትንቢት ተፈጸመ፡፡ ሕዝቡም ኢየሱስ በመምጣት ላይ እንዳለ ሲያውቅ ሊቀበለው ወጣ፡፡ አንዳንዶች ያልፍበት በነበረ መንገድ ልብሳቸውን እንዳንዶቹ ደግሞ የዘንባበ ዝንጣፊ ያነጥፉ ነበር፡፡ ከፊትና በኋላ ያሉት ደግሞ “ሆሳዕና በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው፤ ሆሳዕና ለዳዊት ልጅ” እያሉ በታላቅ ድምፅ ይጮሁ ነበር፡፡ ኢየሱስ በሕዝቡ እልልታና ደስታ ታጅቦ ሲገባ ተጠንቅቀው ይታዘቡትና ይመለከቱት የነበሩ ፈሪሳውያን ደቀ መዛሙርቱን ዝም እንዲያሰኛቸው ተናገሩት፡፡ እርሱም ሕዝቡ ዝም ቢል ድንጋዮች እንደሚጮኹ አስታወቃቸው፡፡ ኢየሱስ ኢየሩሳሌምን ሲያያት አለቀሰላት፡፡ “አንቺ ኢየሩሳሌም ለሰላምሽ የሚያስፈልገውን ነገር ምነው አውቀሽ ቢሆን ኖሮ አሁን ግን ይህ ነገር ከዓይንሽ ተሰውሮብሻል ጠላቶችሽ በዙሪያሽ እንደ አጥር ከብበው በዚህም በዚያም አንቺን የሚያስጨንቁበት ጊዜ ይመጣል… ምክንያቱም እግዚአብሔር ሊያድንሽና ሊጐበኝሽ የመጣበትን ጊዜ ባለማወቅሽ ነው” እያለ ረገማት፡፡

መድሐኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ  ወደ ኢየሩሳሌም የገባው ሰለ ደኅንተቷ ሊያሳስባት ፈልጐ ነው፡፡ በማያወላዳ መንገድ ንጉሷና መድኃኒቷ እንደሆነ ገለጸላት፡፡ ወደ ራሷ ተመልሳ ጸጋዋን እንድትቀበል የልቧን ድንዳኔ ትታ እርሱን እንድትሰማ አስጠነጠቃት፡፡ ግን አልተጠነቀቀችም፡፡ ለጊዜው በክብር ተቀበለችው፡፡ ከጥቂት ቀን በኋላ ግን ተወችው፤ በመስቀል ላይ ሰቀለችው፡፡ የደኅንነቷን ቀን ማወቅ ተሳናት፡፡ በዚህም ደግሞ ከብዙ ዓመታት በኋላ መዓት ወረደባት፡፡ ይህ የሚያሳዝን የኢየሩሳሌም ሥራ የእኛም ሥራ ነው፡፡ ኢየሱስን መድኃኒታችንን መቀበል አንፈልግም ወይም ተቀብለን በኃጢአታችን ከእኛ እንዲርቅ እናደርገዋለን፡፡ በቅዱስ ቁርባን ወደ እኛ ሲመጣ በደስታ እንቀበለዋለን፡፡ ትንሽ ቆየት ብለን ደግሞ እናዋርደዋለን፡፡ ከእርሱ ጋር እንጣላለን፡፡ ከኃጢአት ጋር ጓደኝነት እንይዛለን፡፡ በኃጢአት ስንወድቅ እርሱን እንደገና እንሰቅለዋለን፡፡ ኢየሱስ እኛን “አቤት በዚህ ቀን ለደኅንነትህ የሚደረገውን ብታውቅ ኖሮ …፣ ይህ ሁሉ ከዓይንህ ተሰውሮብሃል ማወቅን አልፈለግህም፡፡ ይህን እወቅ ግን አንድ ቀን …” እያለ አዝኖ ይፈርድብናል፡፡ ይህንን በማሰብ ሲመጣና ሲናገረን እምቢ አንበለው አናባርረው፡፡ በኋላ እርሱ ቂም ይዞ እምቢ እንዳይለና እንዳያባርረን ደኅንነታችንን ራሳችን አናጥፋት፡፡

ምስባክ

መዝ.80÷3 "ንፍሑ ቀርነ በዕለት ሠርቅ፡፡ በእምርት ዕለት በዓልነ፡፡ እስመ ሥርዓቱ ለእስራኤል ውእቱ"
ትርጉም፦ በመባቻ ቀን በታወቀችው በዓላችን ቀን መለከትን ንፉ፤ ለእስራኤል ሥርዐቱ ነውና÷ የያዕቆብም አምላክ ፍርድ ነውና፡፡
መዝ.80÷2 "እምአፈ ደቂቅ ወሕፃናት አስተዳሎከ ስብሓተ፡፡ በእንተ ጸላዒ፡፡ ከመ ትንሥቶ ለጸላዒ ወለገፋዒ፡፡"
ወይም
ትርጉም፦ ከሕፃናትና ከሚጠቡ ልጆች አፍ ምስጋናን አዘጋጀህ፡፡ ስለ ጠላት÷ ጠላትንና ግፈኛን ታጠፋው ዘንድ፡፡

ፍኖተ ሕይወት

¶¶@nshachannel
¶¶@nshachannel

ፍኖተ ሕይወት

26 Apr, 19:37


ፍኖተ ሕይወት

¶¶@nshachannel
¶¶@nshachannel

ፍኖተ ሕይወት

25 Apr, 13:56


 ሰው ወደ ኃጢአት በተራመደ መጠን ሃሳቡ ደካማ ይሆናል። ወደ ኃጢአትም ያዘነብላል። በውስጡም ለኃጢአት ሥፍራ ያዘጋጃል። ተጨማሪ እርምጃ በተራመደ ቁጥር በልቡ ውስጥ የነበረው ፍቅረ እግዚአብሔር ይቀንሳል። መውደቁም ግልጽ እየሆነ ይሄዳል። ስለዚህም በመጽሐፍ _"አንች ወራዳ የባቢሎን ልጅ ሆይ ሕፃናቶችሽን ይዞ በዓለት ላይ የሚፈጠፍጣቸው የተመሰገነ ነው "ተብሎአል። [መዝ 136*8_9] የባቢሎን ልጅ [የምርኮ ሀገር)  የተባለ ኃጢአት ነው። ልጆች የተባሉት ፈቃዳተ ኃጢአት ናቸው። እነዚህን ልጆች የተባሉ ፈቃዳተ ኃጢአት የሚፈጠፍጣቸው ዓለት የተባለ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። [1ቆሮ 10*4]  ስለዚህ ኃጢአትንና ፈቃዳቱን ሁሉ በክርስቶስ አጋዥነት የሚቋቋምና በአእምሮው ሲታሰብ ጀምሮ ኃጢአትን የሚጠላ ሰው ብፁዕ ነው። 


[አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ]
¶¶@nshachannel
¶¶@nshachannel

ፍኖተ ሕይወት

24 Apr, 06:22


ሰይጣን ክፉ ሰው ሊያደርግህ ሞክሮ ካልሆነለት መልካም ተግባራትን ያስተውሀል የማትፀልይ፣መፅሐፍ ቅዱስ የማታነብ፣ቅዳሴ ላይ የማትሳተፍ ወዘተ በማድረግ ለሌሎች ስጋዊ ተግባራት ለመዝናናት ምናምን ግን ግዜ ያለህ እንድትሆን ያደርግሀል ስለዚህ ስንፍናን ተዋጋ "ስንፍና" ከሰይጣን ነው!!

ፍኖተ ሕይወት

22 Apr, 16:28


"ልጄ ሆይ በክርስትናህ መጎልመስ ከፈለክ ከቅዱሳት መጻህፍት ጋር ራስህን አዛምድ" ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

ሰማዕትነት አያምልጣችሁ፣ ኦሪት ዘፍጥረት፣ ወደ ኦሎምፒያስ የተላኩ መልዕክቶች፣ ወደ ቴዎድሮስ የተላኩ መልዕክቶች፣ ትምህርት በእንተ ምክንያተ ሐውልታት፣ በእንተ ክህነት፣ ኦርቶዶክሳዊ ቤተሰብን እና ውዳሴ ጳውሎስ የተሰኙ መጻሕፍትን በሚማርክ በሚስብና በሚመስጥ ለዛ ባለው አማርኛ የታላቁን አባት ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅን ድርሳናት በመተርጎም ያበረከተልን ወንድማችን #ገብረ_እግዚአብሔር_ኪደ ቅዱሱ አባት በክርስትና ሕይወት እንጎለምስ ዘንድ ከቅዱሳት መጻሕፍት ጋር ራሳችንን እናዛምድ እንዳለው "አምስቱ የንስሐ መንገዶች እና ሌሎች" በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ የተሰኘ መጻሕፍት  በቅርብ ቀን ይዞልን ይቀርባል።

"ቅዱሳት መጻህፍትን የማያውቅ ክርስቶስን አያውቅም"[ቅዱስ ጄሮም]

ፍኖተ ሕይወት

22 Apr, 16:22


ምክረ አበው

አንድ ወንድም ዓለምን በመናቅ ያለውን ሁሉ ሽጦ ለድሆች ካካፈለ በኋላ ለግል ፍጆታው እንድትሆን ጥቂት ነገር ያስቀራል፡፡ ከዚህ በኋላ አባ እንጦንስን ለማየት ወደ እርሱ ይሄድና ያደረገውን ያለውን ሁሉ ለድሆች እንደሰጠ ይነግረዋል፡፡ አባ እንጦንስም ‹‹መነኩሴ ለመሆን ከፈለገህ ወደ መንደር ተመልሰህ ሂድ ከዚያም ሥጋ ከገዛህ በኋላ ዕርቃንህን ወደዚህ ተመልሰህ ና›› ይለዋል፡፡ ሰውየውም የተነገረውን አድርጎ ወደ አባ እንጦንስ ሲመለስ ውሾችና አሞራዎች ሰውነቱን ይዘነጣጥሉታል፡፡ አባ እንጦንስም የታዘዘውን በትክክል መፈጸሙንና አለመፈጸሙን ይጠይቀዋል፡፡ በዚህ ጊዜ ሰውየው የተነካከሰ ገላውን ገልጦ አባ እንጦንስን ሲያሳየው አባ እንጦንስም ‹‹ዓለምን ንቀናል ካሉ በኋላ ለራሳቸው ፍጆታ የሚሆን ነገር የሚያስቀሩ ሰዎችም ልክ እንደዚሁ በእነርሱ ላይ በሚከፍቱ ርኩሳን መናፍስት አማካይነት ይዘነጣጥሉታል›› በማለት አስተምሮታል፡፡

የአባቶቻችን የአበው በረከታቸው ረድኤታቸው ከሁላችን ጋር
ይሁን፡፡

ፍኖተ ሕይወት

22 Apr, 04:40


"አንድ ሰዉ በእግዚአብሔር ዕቅፍ ውስጥ እንዳለ ካወቀና እግዚአብሔር ሁሉን ያከናዉንልኛል ካለ ልቡ ፍጹም ይሆናል።"

[ማር ይስሐቅ]

ፍኖተ ሕይወት

21 Apr, 11:48


ኒቆዲሞስ የዐብይ ሰባተኛ ሰንበት

ኒቆዲሞስ ማን ነዉ?

ኒቆዲሞስ ቃሉ የግሪክ ሲሆን ድል ማድረግን ወይም አሸናፊነትን ያመለክታል፡: ኒቆዲሞስ ፈሪሳዊ፥ ከአይሁድ አለቆችና መምህራና አንዱ ነው። በወንጌለ ዮሐንስ ምዕራፍ ሦስት ከፈሪሳውያን ወገን የአይሁድ አለቃ የሆነ ኒቆዲሞስ የተባለ አንድ ሰው እንደነበረና እርሱም በሌሊት ወደ ጌታችን መጥቶ እንደተማረ ተጠቅሷል። (ዮሐ ፩-፪)
በአይሁድ አለቆች ፊትም ”ሕጋችን አስቀድሞ ሳይሰማ የሠራውንም ሳያውቅ በሰው ይፈርዳልን?” በማለት ስለ መድኃኔዓለም ክርስቶስ የተናገረ እሱ ነው። እነርሱ ግን በክርስቶስ እግዚአብሔርነት ያመኑበት ኦሪትን የማያዉቁ ስሑታን እንደሆኑ ያስቡ ስለ ነበር ”አንተም ደግሞ ከገሊላ ነህን? ከገሊላ ነቢይ እንደማይነሳ መርምርና እይ“ አሉት እንጂ አልተቀበሉትም። ዮሐ ፯፥፵፰-፶፪። ኒቆዲሞስ የአርማትያስ ሰው ከሚሆን ከዮሴፍ ጋር በመሆን የጌታችንን ቅዱስ ሥጋ በንጹሕ በፍታ ገንዞ በአዲስ መቃብር ቀብሯል። ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ ”ቀድሞ በሌሊት ወደ ጌታችን ኢየሱስ ሄዶ የነበረዉ ኒቆዲሞስም መጣ፤ ቀብተውም የሚቀበርበትን መቶ ወቄት የከርቤና የሬት ቅልቅል ሽቶ አመጣ።” እንዳለ። ዮሐ ፲፱፥፴፱። በዚህም ኒቆዲሞስ ከምክረ አይሁድ ያልተቀላቀለ መሆኑ ይታወቃል።
የሌሊት ተማሪው ኒቆዲሞስ የሌሊቱን ጊዜ ለትምህርት ለምን መረጠ
             የሌሊት ተማሪው ኒቆዲሞስ ዮሃ ፫፤፪
                 ከፈሪሳዊያን ወገን የሆነ የአይሁድ አለቃ የሆነ ኒቆዲሞስ የሚባል አንድ ሰው በሌሊት ወደ ጌታ እየሄደ ይማር ነበር ኒቆዲሞስ ከቀኑ ክፍለ ጊዜ ይልቅ የሌሊቱን ጊዜ ለትምህርት ለምን መረጠ ?
   ፩. ኒቆዲሞስ መምህር ስለነበር ስማር ሰዎች ቢያዩኝ ውዳሴ ከንቱ መምህር መባል ይቀርብኛል ብሎ ነው እኛስ ዛሬ የዘላለም ህይወት የሚሰጠንን ቅዱስ ቃል ብትህትና መማር ሲገባን ለምድራዊ ክብር ብለን በቀን ጊዜያችን መማር ያልቻልን ስንቶቻችን ነን ስለዚህ ቀን ጊዜአችንን በአግባቡ ልንጠቀምበት ይገባል‹ ማንም ሊሰራ የማይችልባት ሌሊት ትመጣለችና › ዮሃ ፱፤፬
 
፪.ኒቆዲሞስ የአይሁድ መምህር ስለነበር እንዳያዩት ፈርቶ ሌሊት እየመጣ ይማር ነበር እኛስ ዛሬ ልባችን የተረዳውን እውነት በግልጥ እንዳንፈጽም በፍራቻ በይሉኝታ የምንሰውር ስንቶቻችን ነን ‹ፍጹምፍቅር ፍርሃት የለውም ፍርሃት ቅጣት አለውና› ፩ዮሃ ፬፤፲፰ ፍርሃትን አስወግደን ለእውነት ልንቆም ይገባል
 
፫ ኒቆዲሞስ ከቀን ልብ ይልቅ የሌሊት ልብ የተካተተ ስለሆነ በሙሉ ልቡ በማስተዋል ለመማር ስለፈለገ ከቀኑ ክፍለ ጊዜ ይልቅ የማታውን መረጠ ዛሬስ ስንቶቻችን ነን ቅዱስ ቃሉን በማስተዋል ከልብ ሆነን የምንማር የሰማነው ቅዱስ ቃል በህይወታችን ፍሬ እንዲያፈራ ቅዱስ ቃሉን ከልብ ሆነን በማስተዋል ልንሰማ ይገባናል ቃሉን ሰምቶ የሚያስተውል ልብ መልካም መሬት ተብሏል ‹በመልካም መሬት የተዘራውም ይህ ቃሉን ሰምቶ የሚያስተውል ነው› ማቴ ፲፫፡፳፫ አንዳንዶቻችን ጸሎት እያደረግን እንኳን አንደበታችን የእግዚአብሄርን ቃል ይነዳል ልባችን ሌላ ቦታ ይንጎዳጎዳል በማህበር ጸሎትም አብረን እየጸልይን በመሃል ሳይን አውት አርገን ልክ ሲፈጸም አለቀ እንዴ ብለን ሳይን ኢን የምናደርግ አንጠፋም
            
፬ ሌሊት ጨለማ ነው ብርሃን የለም ይህም የኃጢአት ምሳሌ ነው ኒቆዲሞስ በሌሊት መምጣቱ በኃጢአት እንዳለ ንስሃ እንደሚፈግ ያስረዳናል ዛሬስ ስንቶቻችን ነን ቅዱስ ቃሉን ስንሰማ በተአምኖ ኃጢአት በንስሃ ውስጥ ሆነን የምንሰማ ያለንስሃ የምንሰማው ቃል በህይወታችን ፍሬ የማፍራት እድሉ ጠባብ ነው ምክንያቱም በንስሃ ከልባችን ያልጸዱት ክፉ ምኞቶች እንደ እሾህ ሆነው ያንቁታልና
‹ሌላውም በእሾህ መካከል ወደቀ እሾህም ወጣና አነቀው› ማቴ፲፫፤፰ ተብሎ የተጻፈው ለዚህ ነው
            
፭ ሌሊት የቆየው ኪዳን ወይም የብሉይ ኪዳን ምሳሌ ነው ኒቆዲሞስም እኔ ምሁረ ኦሪት እንጂ ምሁረ ወንጌል አይደለሁም ወንጌልን ካንተ እማር ዘንድ ያስፈልገኛል ሲል በሌሊት ይመጣ ነበር ብሉያት ከሓዲሳት ጋር ተዋህደው ሲተረጎሙ ሰሙና ወርቁ ተጣምሮ የሕይወት ትምህርት ያስገኛል አንዳንዶች ዛሬ ብሉያት ጭራሽ አያስፈልጉም ሲሉ ይደመጣሉ ነገር ግን እንደ ኒቆዲሞስ ሁለቱን ኪዳናት አዋህዶ መጓዝ ትክክለኛው መንገድ ነው ለዚህም ነው ጌታ ሲያስተምር‹እውነት እላችኋለው ሰማይና ምድረስኪያልፍ ድረስ ከህግ አንዲት የውጣ ወይም አንዲት ነጥብ አታልፍም› ማቴ፭፤፲፰ በማለት አበክሮ የተናገረው ኒቆዲሞስ ምንም እንኳን የቀኑ ክፍለ ጊዜ ባይመቸውም በሌሊቱ ሰአት ለመማር ችⶀል እኛም ከሱ ተምረን ከልብ ካለቀሱ እንባ አይጠፋምና ምንም ስራ ቢበዛብን ለቅዱስ ቃሉ ጊዜ አይጠፋምና ህይወት ለሚገኝበት ትምህርት ጊዜ ልንሰት ይገባል።

2,170

subscribers

126

photos

36

videos