Arba Minch University Students`Union @amusuinfo Channel on Telegram

Arba Minch University Students`Union

@amusuinfo


☞This is the official AMU Students' Union Telegram channel★አርባ ምንጭ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ህብረት💡®


https://t.me/amuSUinfo


መረጃና አስተያየት ለማድረስ
👇👇👇
@AMUSU_bot

Arba Minch University Students`Union (Amharic)

በዚህ ወቅታዊ ጽሁፍ በአማርኛ ሰንበት እንዲሁም በዚህ መረጃ ውስጥ የተገኘባቸው መረጃዎችን ይመልከቱ። ይህ ላይ የሚቀጥል አዘጋጅቷ አራግቡ፣ እና ይልማ ጥያቄዎችን ለማስጠብብ በተጨማሪ ቦታ ካልሆነ መዳረፍ ማድረግ አለብን። በፓስት አለው የዩኒቨርስቲዎች ተማሪዎች ህብረት ኮምፒዎችን ለመተንተን የሚረዳ ከታላቁ ማስታወሻዎ እና መጠሪያዎ እንመለከታለን። የምርያም ማስታወሻ በመጠናቀቅ ይበቃል፣ ምሁር ችሎታን ተጠቅመው ለምሳሌ መሳሪያ ያደርሳል።

Arba Minch University Students`Union

14 Feb, 10:32


ማስታወቂያ

ለአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ አንደኛ አመት ተማሪዎች በሙሉ

የመጀመሪያ ሴሚስተር ፋይናል ፈተና እንኳን በሠላም ጨረሳችሁ እያልን
ከዲፓርትመንት መረጣ ጋር በተያያዘ በዚህ አመት አዲስ አሰራር ስለተዘረጋ
ማለትም ሁሉም ዲፓርትመንቶች መረጣ የሚካሄደው በመጀመሪያ ሴሚስተር ሆኖ ሁለተኛ ሴሚስቴር ላይ ይሰጡ የነበሩ የአንደኛ አመት ኮርሶች በየዲፓርትመንታችሁ የሚሰጡ ሲሆን
አጠቃላይ ስለዲፓርትመንቶች መጪው ሳምንት ትልቁ አዳራሽ ሰኞ ከሰዓት በቀን 10/06/2017 ዓ/ም አጠቃላይ ኦሬንቴሽን ስለሚሰጥ በሰዓቱ ተገኝታችሁ ግልፅ ያልሆነላችሁን ነገሮች በመጠየቅ ተገቢውን ምላሽ የምታገኙ ይሆናል።


ማሳሰቢያ
1. ማንኛውም ተማሪ ለእረፍት በሚል ወደ ቤት የሚሄድ ተማሪ ለሚፈጠሩት ችግሮች ሃላፊነቱን እራሱ ይወስዳል ግቢውም ሆነ የተማሪዎች ህብረት ሃላፊነቱን አይወስድም
2. ከአዲሱ የዲፓርትመንት ምደባ ጋር በተያያዘ ስህተት ቢፈጠር ቅሬታ በውክልና አይሰተናገድም ።
3.ለእረፍት ተብሎ በግልፅ የጊዜ ሰሌዳ ስላላካተተው ከግቢ ባትርቁ ይመረጣል።
4. በተለያዩ ችግሮች የፋይናል ፈተና መፈተን ያልቻላችሁ ተማሪዎች ማስረጃችሁን በማቅረብ ተሎ መፈተን ይኖርባችሁል ።ዲፓርትመንት ምደባ ላይ ችግር እንዳይፈጥርባችሁ ።
5. ዖረንቴሽን ሲጠጥ መገኜት ትልቅ ጥቅም አለው በዚህ ዖረንቴሽን እያንዳንዳቸው ዲፓርትመንቶች የሚፈልጉትን የተማሪ ብዛት ስለሚያሳውቁ መገኜት ይኖርባችኋል ።

የተ/ህ/ጽ/ቤት


Urgent notice

For all freshman students of Arba Minch University

We wish you to finish the first semester final exam with peace
Because a new system has been developed this year in relation to the selection of the department
That is, the selection of all departments is done in the first semester, besides that the first year courses that were offered in the second semester are given in your department. Additionally
General Orientation will be given on Monday afternoon on 17/02/2025 in the big hall next week, so you can attend on time and ask questions that are not clear to you.


Reminder
1. Any student who goes home for vacation will be responsible for the problems , neither the managment bodies nor the student union will be responsible.
2. If any mistake happen regarding the new department selection , complaint will not be handled by representative
3. It is better not to stay away from campus as it is not a clear schedule for vacation

4. Students who are unable to take the final exam due to various problems, you should submit your evidence and take the exam separately.
5. It is very useful to attend the orientation. In this orientation, each department will inform you of the number of students they need.


Office of students Union

Arba Minch University Students`Union

13 Feb, 18:35


ማስታወቂያ

የመውጫ ፈተና የተፈተናችሁ ተማሪዎች በሙሉ
የመውጫ ፈተና ውጤት በሪጅስተራል በኩል የተላከ ሲሆን ተማሪዎች በ መታወቂያ ቁጥራቸው ገብተው ማዬት እንዲችሉ እያስተካከሉ ስለሆነ ትንሽ ታገሱን

ጉጉታችሁን እንረዳለን ።
ውጤቱ ያማረ ይሆንላችሁ ዘንድ እንመኛለን
የተ/ህ/ጽ/ቤት


All students who have taken the exit exam
The results of the exit exam have been sent through the registrar and they are editing it so that students can log in with their ID numbers, so please be patient.

We understand your enthusiasm.
We hope that the result will be good for you

office of students Union

Arba Minch University Students`Union

13 Feb, 10:07


Exit exam result ዛሬ ይለቀቃል
መልካም ያሰማን።

Arba Minch University Students`Union

11 Feb, 05:50


urgent

Arba Minch University Students`Union

02 Feb, 13:34


⭐️እንኳን ደስ ያላችሁ⭐️

ተቋማችን በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የስፖርት ፌስቲቫል ላይ በተካሄደው ውድድር አስደናቂ ውጤት አስመዝግቧል፡፡ ውጤታችን እንደሚከተለው ነው፡-

🏅ቼዝ (ሴቶች)፡- ሳምራዊት ግርማ የወርቅ ሜዳልያና ዋንጫ አሸንፋለች፡፡
🏅 አትሌቲክስ፡-
    * 100 ሜትር፡- ማቢል ቱት ኬ የብር ሜዳልያ አሸንፏል፡፡
    * 200 ሜትር፡- ማቢል ቱት ኬ የነሐስ ሜዳልያ አሸንፏል፡፡
🏅ዱላ ቅብብል፡- ማቢል ቱት ኬ፣ ቴዎድሮስ ጌትነት፣ ዳንኤል ተፈራ እና ያሬድ ታደሰ እያንዳንዳቸው የነሐስ ሜዳልያ አሸንፈዋል፡፡
🏅ዓለም አቀፍ ቴኳንዶ፡- ልዩወርቅ አሰበ የነሐስ ሜዳልያ አሸንፏል፡፡

በአጠቃላይ ተቋማችን አንድ የወርቅ ሜዳልያና ዋንጫ፣ አንድ የብር ሜዳልያና ስድስት የነሐስ ሜዳልያዎችን አሸንፏል፡፡

ነገ የሚደረገው የእግር ኳስ ጨዋታ በጣም ይጠበቃል፡፡

የተ/ህ/ጽ/ቤት

Arba Minch University Students`Union

01 Feb, 12:32


አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በቼዝ የወርቅ ሜዳልያና የዋንጫ አሸናፊ ሆነ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የስፖርት ልዑካን ቡድን በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ አዘጋጅነት በመካሄድ ላይ ባለው የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ስፖርት ፌስቲቫል ላይ ዛሬ ጥር 24/2017 ዓ/ም በተካሄደው በሴቶች የቼዝ የፍፃሜ ውድድር በሳምራዊት ግርማ አማካኝነት የመጀመሪያውን የወርቅ ሜዳልያ እና ዋንጫ አግኝቷል።

ተማሪ ሳምራዊት በውድድሩ አንድም ሽንፈት ያላስተናገደች ሲሆን ከተካሄዱ 7 ዙሮች 6ቱን በመርታት በአንዱ አቻ በመለያየት በአጠቃላይ 6.5/7 ነጥብ በማምጣት የወርቅ ሜዳልያ ለዩኒቨርሲቲው አስገኝታለች።

የቼዝ አሰልጣኝ መ/ር ጌታሁን ሞኝነት በውጤቱ ደስተኛ እንደሆነና የተመዘገበው ስኬት በሌሎችም የስፖርት ዓይነቶች መሰል ውጤት እንዲመዘገብ የራሱ አስተዋጽኦ እንዳለው በመጠቆም ለመላው የዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት አስተላልፏል ።

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ
የብሩህ ተስፋ ማዕከል!

ለተጨማሪ መረጃ በድረ-ገጽና በማኅበራዊ ትስስር ገጾቻችን ይከተሉን፡-

ድረ-ገጽ - https://www.amu.edu.et/
ቴሌግራም - https://t.me/arbaminch_university
ፌስቡክ - https://www.facebook.com/ArbaMinchUniversityccd/
ዩቲዩብ - https://www.youtube.com/channel/UCOO_nclhMo8M3r74OyPBlVA

የሕዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት

Arba Minch University Students`Union

31 Jan, 11:01


የዩኒቨርሲቲው የስፖርት ልዑክ በኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ስፖርት ፌስቲቫል ላይ አመርቂ ውጤት እያስመዘገበ ይገኛል

ዛሬ በቀን 23/05/2017 ዓ/ም አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከሰላሌ ዩኒቨርሲቲ ባደረጉት የእግር ኳስ ውድድር ዩኒቨርሲቲያችን 6 ለ 1 በሚገርም የጎል ልዩነት በማሸነፍ ወደ ግማሽ ፍፃሜ ያለፈ መሆኑን እናሳውቃለን ።

የተ/ህ/ጽ/ቤት

Arba Minch University Students`Union

22 Jan, 06:48


Another announcement.

Arba Minch University Students`Union

22 Jan, 06:48


ለአንደኛ አመት (2017 አዲስ ገቢ እና 2016 ሬሜዲያል)ተማሪዎች በሙሉ

🔺የኤሌክትሮኒክ ትምህርትን (e-Learning) በተመለከተ የግንዛቤ ማስጨበጫ ፕሮግራም መካሄዱ ይታወቃል። በዚሁም መሠረት ከታች በተጠቀሰው ሰዓት እና ቦታ በመገኘት ኢሜል አክቲቬት እንድታደርጉ እና ወደ ሲስተሙ እንድትገቡ እናሳውቃለን። በተጠቀሰው ቀን እና ሰዓት ምንም አይነት የትምህርት መርሃ ግብር የማይኖር መሆኑን አውቃችሁ በቦታው እንድትገኙ እናሳውቃለን።

ተ/ህ/ጽ/ቤት

For all first-year students (2017 new entrants and 2016 remedial students)

🔺 An awareness creation program regarding e-Learning is scheduled. Accordingly, we inform you to activate your email and log in to the system by attending the program at the specified time and place below. Please be aware that there will be no regular classes scheduled on the specified date and time, and we expect your presence at the designated location.

SUO

Arba Minch University Students`Union

18 Jan, 20:19


⚠️አስቸኳይ ማስታወቂያ ለተመራቂ ተማሪዎች በሙሉ

➡️ለአርባምንጭ ዩንቨርስቲ መደበኛ እና ኢ-መደበኛ  ተመራቂ ተማሪዎች በሙሉ እስካሁን ድረስ አብዛኛው ተማሪ Basic profile እንዳላስተካከለ ከቢሮ ማሳሰቢያ ተነግሮናል።በመሆኑም በአስቸኳይ በSmis ላይ Login በማለት በመቀጠልም ''Basic profile'' ላይ ''Email እና ስልክ ቁጥር እንድታስገቡ እንደዚሁም Passport size ፎቶ upload እንድታደርጉ እናሳስባለን።
🔗STEP
Dashboard➡️Basic profile

🔔እስከ 12/05/2017 ማለትም እስከ ማክሰኞ እንድትጨርሱ እናሳስባለን ።ለሚፈጠሩ መዘግየት እና መሰል ችግሮች ተማሪ ሕብረቱ ሐላፊነት እንደማይወስድ ከወዲሁ ለማሳወቅ እንወዳለን ።

ተ/ህ/ጽ/ቤት

⚠️ Urgent notice to all graduating students

➡️For all Regular and non-regular students of Arbaminch University, we have been informed by the office that most of the students have not adjusted their basic profile on SMiS yet. Therefore, we urge you to immediately log in on SMiS and then enter your email and phone number on "Basic profile" and also upload a passport size photo. .
🔗STEP
Dashboard➡️Basic profile

🔔We urge you to finish by 12/05/2017, that is, by Tuesday.(E.C)

                     AMU Student Union Office

Arba Minch University Students`Union

17 Jan, 13:50


https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSdVXtRqKCgO781KvI-TWcR3oXrww_szesNcbd7s8q8wKnvUDg/viewform?usp=sharing

The link ☝️ france scholarship

Arba Minch University Students`Union

17 Jan, 08:16


⚠️የሰዓት ለውጥ

✔️7:00 ሊካሄድ የነበረው የፈረንሳይ ስኮላርሽፕ ገለጻ በዛሬው የFinal ፈተና ምክንያት ወደ 10:00 መቀየሩን እናሳውቃለን።

✔️9:30 ላይ በሁሉም ካምፓስ ሰርቪስ ስለሚጠብቃችሁ በጊዜ እንድትገኙ እናሳስባለን

Arba Minch University Students`Union

16 Jan, 15:58


💥የፈረንሳይ ስኮላርሺፕ💥

ለአርባምንጭ ዩንቨርስቲ ተማሪዎች በሙሉ የፈረንሳይ ኤንባሲ ለተማሪዎች ልዩ የሆነ የስኮላርሺፕ እድልን ይዞ ከተፍ ብሏል።በመሆኑም ስለስኮላርሺፑ አጠቃላይ መረጃ እና ገለፃ አርብ ከሰዓት ስለሚደረግ ይህን እድል መጠቀም የምትፈልጉ ተማሪዎች Main Campus ዋናው መግቢያ በር ላይ በሚገኘው አዳርሽ እንድትገኙ እናሳስባለን።

💥ከቀኑ 7:00 ላይ በሁሉም ካምፓስ ሰርቪስ ስለተዘጋጀ በቦታው በጊዜ እንድትገኙ።👍

                        የተ/ህ/ጽ/ቤት

Arba Minch University Students`Union

16 Jan, 15:58


French scholarship 💥

For all the students of Arba minch University
, the French Embassy has opened a special scholarship opportunity for students. Therefore, the general information and explanation about the scholarship will be given on Friday afternoon in AMIT HALL MAIN CAMPUS

💥 At 7:00Am local time . all campus services are arranged so that you can be there on time.

                        The office of Students Union

Arba Minch University Students`Union

07 Jan, 12:54


የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ አመራሮች የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በዓልን ከዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች ጋር አከበሩ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ አመራሮች ከዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች ጋር ዛሬ ታኅሣሥ 29/2017 ዓ/ም የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በዓልን አክብረዋል፡፡

ከፍተኛ አመራሮቹ ተማሪዎች ከወላጆቻቸው ርቀው በትምህርት ላይ ስለሚገኙ ብቸኝነት እንዳይሰማቸው እና ከተማሪው ጋር ተቀራርቦ በመሥራት ስኬታማ የመማር ማስተማር ሒደትን ለማስፈን በዓሉን በጋራ ማሳለፋቸውን ገልጸው ለተማሪዎች፣ ለወላጆቻቸው፣ ለዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብና ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ የመልካም ምኞት መልእክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ኅብረት ፕሬዝደንት ተማሪ ሶፎኒያስ ፈንቴ የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች በዓሉን ከተማሪው ጋር ማሳለፋቸው ቤተሰባዊ መንፈስ እንዲዳብር የሚያስችልና በተማሪዎች በኩል መነቃቃትና የተሻለ ስሜትን የሚፈጥር መሆኑን ገልጿል፡፡ ተማሪ ሶፎኒያስ በቀጣይም በመማር ማስተማርና በሁለንተናዊ እንቅስቃሴዎች ተማሪዎችን በመጎብኘትና የሚገጥሙ ተግዳሮቶችን በመፍታት ለተማሪዎቹ ስኬታማነት የተቻላቸውን ሁሉ እንዲያደርጉ አጽንኦት የሰጠ ሲሆን ተማሪዎችም የዩኒቨርሲቲውን ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሒደት ከማስጠበቅ ባሻገር ዩኒቨርሲቲው በሚያደርገው ራስ ገዝ የመሆን ጉዞ የበኩላቸውን ኃላፊነት ሊወጡ እንደሚገባም አሳስቧል፡፡

ተማሪዎቹ በዓሉን በድምቀት እንዲያከብሩ ከዝግጅት ጀምሮ ሥራዎች መሠራታቸውን የገለጹት በዋናው ግቢ ተማሪዎች አገልግሎት ምግብ ዝግጅትና መስተንግዶ አስተባባሪ አቶ ሸዋንግዛው ታደሰ ለተማሪዎችና ለወላጆች መልካም የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በዓል እንዲሆንላቸው መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል፡፡

በተማሪዎች አገልግሎት ምግብ ዝግጅትና መስተንግዶ ክፍል ሼፍ ወ/ሮ ውድነሽ ተረፈ በበኩላቸው ከዋዜማው ጀምሮ በቂ ዝግጅት በማድረግ ከተማሪዎች ጋር በዓሉን ማሳለፍ መቻሌ ደስታን ፈጥሮልኛል ብለዋል፡፡ ‹‹እኛም በሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች የሚማሩ ልጆች አሉን›› ያሉት ወ/ሮ ውድነሽ ተማሪዎች በመልካም ስሜት በዓሉን እንዲያሳልፉ ተመኝተው የእንኳን አደረሳችሁ ልባዊ ምኞታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

የ5ኛ ዓመት የኤሌክትሪካል ምኅንድስና ፋከልቲ ተማሪ ማሺን ዊዩዓል የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች ከእኛ ጋር በመሆን የቀመስነውን ቀምሰው ማየት መቻሌ በእኔና በዩኒቨርሲቲው መካከል የተሻለ ግንኙትን መኖሩን ማሳያ ምልክት ሆኖ አግንቼዋለሁ ብሏል፡፡

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ
የብሩህ ተስፋ ማዕከል!

ለተጨማሪ መረጃ በድረ-ገጽና በማኅበራዊ ትስስር ገጾቻችን ይከተሉን፡-
ድረ-ገጽ - https://www.amu.edu.et/
ቴሌግራም - https://t.me/arbaminch_university
ፌስቡክ - https://www.facebook.com/ArbaMinchUniversityccd/
ዩቲዩብ - https://www.youtube.com/channel/UCOO_nclhMo8M3r74OyPBlVA

የሕዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት

Arba Minch University Students`Union

13 Dec, 15:43


ከአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ህብረት አዲስ ለተመደቡ የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች የተሰጠ የመልካም ምኞት መግለጫ

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከቀዳሚ ትውልድ ዩኒቨርሲቲዎች አንዱ ሲሆን ገናና ስም ካላቸው ዩኒቨርሲቲዎች ተርታም ይመደባል ፡፡ለዚህም በዩኒቨርሲቲው ውስጥ የነበረው አመራር ጥንካሬ በመሆኑ ከዚህ ቀደም የነበራችሁ የዩኒቨርሲቲው አመራሮች ዩኒቨርሲቲው በመማር ማስተማር ልቆ እንዲወጣ፣ ሰላሙ የተጠበቀና ለሃገሪቱ የሰላም አምባሳደር ምልክት መሆን እንዲችል ለተማሪዎችም እንደመፈክሩ የብሩህ ተስፋ ማዕከል መሆኑ እንዲመሰከርለት ስላደረጋችሁ፣ የዩኒቨርሲቲውን የተማሪዎች ህብረት በሙሉ አቅማችሁ በመደገፍ ላበረከታችሁት አስተዋፅዖ ከልብ የመነጨ ምስጋናችንን እናቀርባለን፡፡

አዲስ ለተመደባችሁ ለዩኒቨርሲቲያችን ከፍተኛ አመራሮች ይህን ግዙፍ ሃገራዊ ተቋም ለመምራት ዕድል ስላገኛችሁ እንኳን ደስ አላችሁ እንላለን፡፡

እንደተማሪዎች ህብረት እንደከዚህ ቀደሙ ሁሉ አብረናችሁ ለመስራት እና የሚጠበቅብንን ሁሉ ለማድረግ ተሰናድተናል። በተማሪዎች እና በአመራሩ መሀከል ድልድይ በመሆን ፤ የመማር ማስተማር ሂደቱን በማስጠበቅ ፣ የተቋሙን ሰላም በማስቀጠል በበለጠ ለመትጋት እንደተሰናዳን መግለጽ እንሻለን።

በተለይም በአሁኑ ሰዓት አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ወደ ራስገዝነት ለሚያደርገው ሽግግር የሁሉም ባለድርሻ አካላትን ተሳትፎ እንደሚሻ የምንገነዘበው ነው። የትምህርት ዘርፉ ሪፎርምም ይኼንን ተልዕኮ ከግንዛቤ ያስገባ መሆኑን እናምናለን። የተማሪዎች ህብረትም የዩኒቨርስቲው ማህረበሰብ አስኳል እንደመሆኑ መጠን ከትላንት በተሻለ ትጋት ፤ ከአምናው በበለጠ ጥረት መስራት እንደሚገባንና የሚጠበቅብንን ለመከወን ፣ የተሰጠንን ተልዕኮ ለመተግበር እና ከተማሪዎች የሚነሱ ሀሳቦችን ለማስፈፀም ተግተን እንሰራለን፡፡

መልካም የስራ ዘመን ይሁንልን !

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ህብረት

Arba Minch University Students`Union

01 Dec, 20:07


በ2017 የትምህርት ዘመን አዲስ አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ለተመደባችሁ የአቅም ማሻሻያ (Remedial) ፕሮግራም ተማሪዎች የመግቢያ ጥሪ ማስታወቂያ

በ2017 የትምህርት ዘመን አዲስ አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ለተመደባችሁ የአቅም ማሻሻያ (Remedial) ፕሮግራም ተማሪዎች ቅበላ ረቡዕ ታህሳስ 2 ቀን 2017 ዓ.ም፣ ምዝገባ ሐሙስና ዓርብ ታህሳስ 3 እና 4 ቀን 2017 ዓ.ም፣ ትምህርት የሚጀመረው ሰኞ ታህሳስ 7 ቀን 2017 ዓ.ም እንዲሆን ተወስኗል፡፡

በዚህ መሠረት የተፈጥሮ ሳይንስ (Natural Science) የአቅም ማሻሻያ (Remedial) ፕሮግራም ተማሪዎች በአርባ ምንጭ ከተማ በሚገኘው አባያ ካምፓስ፣

የስማችሁ የመጀመሪያ ፊደል ከ A እስከ R የሆናችሁ የማህበራዊ ሳይንስ (Social Science) የአቅም ማሻሻያ (Remedial) ፕሮግራም ተማሪዎች በአርባ ምንጭ ከተማ በሚገኘው ጫሞ ካምፓስ፣

እንዲሁም የስማችሁ የመጀመሪያ ፊደል ከ S እስከ Z የሆናችሁ የማህበራዊ ሳይንስ (Social Science) የአቅም ማሻሻያ (Remedial) ፕሮግራም ተማሪዎች በጎፋ ዞን ሳውላ ከተማ በሚገኘው ሳውላ ካምፓስ ሬጅስትራር ማስተባበሪያ ጽ/ቤቶች በአካል እየቀረባችሁ በተጠቀሰው ቀን ሪፖርት እንድታደርጉ፣ ምዝገባ እንድትፈጽሙ እና ትምህርት እንድትጀምሩ እናሳውቃለን፡፡

ማሳሰቢያ፡-
1ኛ) ሁሉም ተማሪዎች ከ9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕትና የ12ኛ ክፍል ሰርተፍኬት ኦርጂናልና የማይመለስ ሁለት ኮፒ እንዲሁም አንሶላ፣ የትራስ ጨርቅ እና የስፖርት ትጥቅ በመያዝ መምጣት ይጠበቅባቸዋል፡፡

2ኛ) ከተጠቀሰው ቀን ቀድሞም ሆነ ዘግይቶ የሚመጣ ተማሪን ዩኒቨርሲቲው አያስተናግድም፡፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሬጂስትራርና አልሙናይ ዳይሬክቶሬት
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ
የብሩህ ተስፋ ማዕከል

Arba Minch University Students`Union

10 Nov, 11:59


በ2017 የትምህርት ዘመን አዲስ አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ለተመደባችሁ እና በ2016 ትምህርት ዘመን የአቅም ማሻሻያ (Remedial) ፕሮግራም በመከታተል የማለፊያ ውጤት ላስመዘገባችሁ ተማሪዎች የመግቢያ ጥሪ ማስታወቂያ

በ2017 የትምህርት ዘመን አዲስ አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ለተመደባችሁ እና በ2016 ትምህርት ዘመን የአቅም ማሻሻያ (Remedial) ፕሮግራም በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በመከታተል የማለፊያ ውጤት ላስመዘገባችሁ የቅድመ-ምረቃ መደበኛ ፕሮግራም ተማሪዎች ቅበላ ቅዳሜና እሁድ ህዳር 7 እና 8 ቀን 2017 ዓ.ም፣ ምዝገባ ሰኞ እና ማክሰኞ ኅዳር 9 እና 10 ቀን 2017 ዓ.ም፣ ትምህርት የሚጀምረው ረቡዕ ኀዳር 11 ቀን 2017 ዓ.ም እንዲሆን ተወስኗል፡፡

በዚህ መሠረት የተፈጥሮ ሳይንስ (Natural Science) ተማሪዎች በአርባ ምንጭ ከተማ በሚገኘው አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ዋና ግቢ፣ የስማችሁ የመጀመሪያ ፊደል ከ A እስከ Q የሆናችሁ የማኅበራዊ ሳይንስ (Social Science) ተማሪዎች በአርባ ምንጭ ከተማ በሚገኘው ጫሞ ካምፓስ፣ እንዲሁም የስማችሁ የመጀመሪያ ፊደል ከ R እስከ Z የሆናችሁ የማኅበራዊ ሳይንስ (Social Science) ተማሪዎች በጎፋ ዞን ሳውላ ከተማ በሚገኘው ሳውላ ካምፓስ ሬጂስትራር ማስተባበሪያ ጽ/ቤቶች እየቀረባችሁ በተጠቀሰው ቀን ሪፖርት እንድታደርጉና ምዝገባ እንድትፈጽሙ እናሳውቃለን፡፡

ማሳሰቢያ፡-
1ኛ) ሁሉም ተማሪዎች ከ9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕትና የ12ኛ ክፍል ሰርተፊኬት ኦርጂናልና የማይመለስ ሁለት ኮፒ እንዲሁም አንሶላ፣ የትራስ ጨርቅ እና የስፖርት ትጥቅ በመያዝ መምጣት ይጠበቅባቸዋል፡፡

2ኛ) ከተጠቀሰው ቀን ቀድሞም ሆነ ዘግይቶ የሚመጣ ተማሪን ዩኒቨርሲቲው አያስተናግድም፡፡፡
 
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሬጂስትራርና አልሙናይ ዳይሬክቶሬት

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ
የብሩህ ተስፋ ማዕከል!

ለተጨማሪ መረጃ በድረ-ገጽና በማኅበራዊ ትስስር ገጾቻችን ይከተሉን፡-
ድረ-ገጽ
https://www.amu.edu.et
ቴሌግራም - https://t.me/arbaminch_university
ፌስቡክ - https://www.facebook.com/ArbaMinchUniversityCAD/
ዩቲዩብ - https://www.youtube.com/channel/UCOO_nclhMo8M3r74OyPBlVA

የሕዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት

Arba Minch University Students`Union

23 Oct, 17:34


https://forms.office.com/r/gxWbxnyTPB

Arba Minch University Students`Union

20 Oct, 16:53


For For GC students:
any one interested to get certified for DAAP 2017 E.C. Get registered using this link.

https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSfx2p-iQDWsS_Uc8fBX4jLf2HJII7_7X8-96xzUQlirmixvuQ/viewform?usp=sf_link

Arba Minch University Students`Union

18 Oct, 03:50


📣ለዋና ገቢ ተመራቂ ተማሪዎች በሙሉ (ቅዳሜ  ጠዋት 2:30 AMIT New Hall)📣
ደረጃ.ኮም ከማስተርካርድ ፋውንዴሽን ጋር በመተባበር 🎓ለ2017 ተመራቂ ተማሪዎች 🎓የተለያዩ ነባር እና አዳዲስ አገልግሎቶቹን የማስጀመሪያ ዝግጅት ጥቅምት 9 /2017 ቅዳሜ  ጠዋት  በ AMIT የመመረቂያ አዳራሽ ስለሚካሄድ ተመራቂ ተማሪዎች በሙሉ ተገኝታቹ የእድሉ ተጠቃሚ ይሁኑ።

Arba Minch University Students`Union

17 Oct, 19:57


This Link is for Data collection Sofoniyas please distribute it so they can register on it

Arba Minch University Students`Union

17 Oct, 19:57


https://ee-eu.kobotoolbox.org/x/0nr7jAef

Arba Minch University Students`Union

14 Oct, 07:29


Dear Mohammed, this is the telegram channel I told you about over a phone. It is a place where students can join from all universities and support one another regarding registration and course enrollment. We will also be sharing resources for the students in this channel, so please share it with your students via your campus telegram channels so that the students can join.

Thank You!

https://t.me/ask_eSHE_for_students

Arba Minch University Students`Union

14 Oct, 07:29


Forward this to all campus representatives. Campus representatives are required to coordinate the students on the dates specified. Except main campus other campuses did very well coordination during the awareness creation. If you are free in the morning contact me in person.