Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

@hulaadiss


ትክክለኛዉ የሁሌ አዲስ ሚዲያ ገፆች

Facebook : bit.ly/42rUuKj
WhatsApp : bit.ly/Huleadis_whatsapp
YouTube : bit.ly/3p7kj3N
Twitter : bit.ly/3NVMRrB
Telegram: bit.ly/Huleadis_tele

ለጥቆማ ና አስተያየት እንዲሁም ለማስታወቂያ ስራ ተከታዮን አድራሻ ይጠቀሙ
bit.ly/3VMy7x7

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

23 Oct, 12:14


Capital News: አዲስ ነገር በሰራተኞች ደመወዝ ጉዳይ | የገንዘብ ሚኒስትር አነጋጋሪ ምላሽ | ጠ/ሚሩ አዲስ...
https://youtube.com/watch?v=_MWUf1zIK9M&si=C4LiaMg2cv1CmSSC

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

23 Oct, 08:05


የሞሪንጋ (ሽፈራው) ተክል በሕጻነት ላይ የሚከሰተውን የመቀንጨር ችግር እንደሚከላከል በጥናት መረጋገጡ ተገለጸ!

በኢትዮጵያ 'ሽፈራው' እየተባለ የሚጠራው የሞሪንጋ ተክል በሕጻነት ላይ የሚከሰተውን የመቀንጨር ችግር እንደሚከላከል በጥናት መረጋገጡ ተገልጿል፡፡ጥናት እና ምርምሩ ተግባራዊ እንዲሆን የጣሊያን መንግሥት፣ የተባበሩት መንግሥታት የኢንዲስትሪ ልማት ድርጅት እንዲሁም የአርባ ምንጭ ዩንቨርስቲ በጋራ የሰሩትን ፕሮጀክት ይፋ አድርገዋል፡፡

በአርባ ምንጭ ዩንቨርስቲ በምግብ ቴክኖሎጂና ባዮቴክኖሎጂ ተባባሪ ፕሮፌሰር አዲሱ ፍቃዱ፤ የሞሪንጋ ወይም የሽፈራው ተክል በሕጻነት ላይ የሚከሰተውን የመቀንጨር ችግር ጨምሮ ብዙ የጤና ጠቀሜታ እንዳለው በጥናት እና ምርምር መረጋገጡን ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡

በተክሉ ውስጥ የተለያዩ ንጥረ ነገሮች የሚገኝበት በመሆኑ ከሌሎች ምግቦች ጋር በመቀላቀል በመጠቀም እንደሚቻል አንስተው፤ የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፍ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡ ምርቶችንም ማስቀረት እንደሚችል ጠቁመዋል፡፡

ፕሮጀክቱ በዋናነት ተግባራዊ የተደረገው ተክሉ በስፋት የሚበቅልበት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አርባ ምንጭ ከተማ ዘይሴ ቀበሌ ሲሆን፤ የክልሉ ርዕሰ መስተዳደር አቶ ገብረመስቀል ጫላ ከተክሉ የተለያዩ ምርቶች እንደሚገኝበት እና ዘርፍ ብዙ ጠቀሜዎች እንዳሉት ተናግረዋል፡፡

በተገኘው ጥናት እና ምርምር መሰረት፤ ተክሉ በብዙ መልኩ የሚቀነባበርበት የፋብሪካ ግንባታ ተጠቀናቆ የተለያዩ ማሽኖችም መግባታቻውን አሐዱ ማረጋገጥ ችሏል፡፡የተጀመረው ፕሮጀክት ተግባራዊ እንዲሆን ያሉትን የመሰረተ ልማት ችግር ለመቅረፍ ምን እየተሰራ ነው? ሲል አሐዱ ለክልሉ ርዕሰ መስተዳደር ላነሳው ጥያቄም፤ የመንገድ እና የኤሌትሪክ አገልግሎት ችግሮች እንደሚፈቱም ተናግረዋል፡፡

በተባበሩት መንግሥታት የኢንደስትሪ ልማት ድርጅት ተወካይ እና የፕሮጀክቱ ቴክኒካል አማካሪ ዶክተር ለምለም ሲሳይ በበኩላቸው፤ በገጠር ላሉ ሴቶች የኑሮ ማሻሻያ ያስፈልጋል በሚል ከመንግሥት በቀረበው ጥያቄ መሰረት ፕሮጀክቱ ተግባራዊ መደረጉን አንስተው ከክልሉ መንግሥት ጋር በጋራ እንደተሰራም አስረድተዋል፡፡የሞሪንጋ ወይም የሽፈራው ተክልን አብዛኛው የኢትዮጵያ የማህበረሰብ ክፍሎች የተለያዩ የካንሰር አይነቶችን እና ደምግፊትን ጨምሮ ሌሎች በሽታዎችን ለመከላከል እንደሚጠቀሙበት የሚታወቅ ነው፡፡

Via Ahadu

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

22 Oct, 16:17


ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በ11 የፖለቲካ ፓርቲዎች ላይ የዕግድ ውሳኔ ማሳለፉን አስታወቀ

#የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በጠቅላላ ጉባዔ፣ በኦዲት እና በሴት አባላት አማካኝነት ከሚገኝ የገንዘብ ድጋፍ ጋር በተያያዘ 11 የፖለቲካ ፓርቲዎችን ማገዱን ዛሬ ጥቅምት 12 ቀን 2017 ዓ.ም ባወጣው የዕግድ ደብዳቤ አስታውቋል።

የዕግድ ውሳኔ ከተሰጣባቸው ፓርቲዎች መካከልም የዎላይታ ብሔራዊ ንቅናቄ፣ የኦሮሞ ነጻነት ንቅናቄ፣ አንድ ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፖርቲ፣ ጌዲኦ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት፣ የሐረሪ ዲሞክራሲያዊ ድርጅት፣ የገዳ ሥራዓት ለኦሮሞ ነጻነት ፓርቲ፣ አዲስ ትውልድ ፓርቲ ይገኙበታል፡፡

በፓርቲዎቹ ላይ የተሰጠው የዕግድ ውሳኔ ቦርዱ የተለየ ውሳኔ እስከሚሰጥ ድረስ ለጊዜው ፓርቲዎችን ከማናቸውም ሕጋዊ እንቅስቃሴ ታቅበው እንዲቆዩ የሚያደርግ ነው ተብሏል፡፡

ቦርዱ በደብዳቤው ለኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት እንዳስታወቀው የሰጠውን የዕግድ ውሳኔ እስከሚያነሳ ድረስ በማናቸውም የጋራ ምክር ቤቱ በሚያዘጋጃቸው ጉባኤዎች ላይ ሊገኙ እንዲሁም ሊመርጡም ሊመረጡም ወይም በተለያዩ የኮሚቴ አባልነት ሊያገለግሉ አይችሉም ብሏል። የጋራ ምክር ቤቱ የእግድ ውሳኔ የተላለፈባቸውን ፓርቲዎች ከማናቸውም የምክር ቤቱ ሥራዎችም ሆነ እንቅስቃሴዎች እንዳይካፈሉ ተገቢውን ሁሉ እንዲያደረግ ቦርዱ በደብዳቤው አሳስቧል፡፡

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

22 Oct, 09:20


ዘለቀ ተመስገን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ሆነዉ ተሾሙ!

የተቋሙ ኮሚሽነር የሆኑት ሃና አርዓያስላሴ የፍትህ ሚኒስትር ሆነዉ በጠቅላይ ሚኒስትሩ መሾማቸውን ተከትሎ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽንን በምክትል ኮሚሽነርነት ሲመሩ የነበሩት ዘለቀ ተመስገን ( ዶ/ር) የኮሚሽነርነት ቦታን ተረክበዋል።

ዘለቀ ከጣልያን ቱሪን ዩኒቨርሲቲ በህዝብ አለምአቀፍ ሕግ የዶክትሬት ዲግሪ ማጠናቀቃቸው የተገለፀ ሲሆን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽንን ከመቀላቀላቸዉ በፊት የኢፌዲሪ የፌዴሬሽን ምክር ቤት የቢሮ ሃላፊ ሆነው አገልግለዋል።

በኢትዮጵያ የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ሆነው የሰሩት ዘለቀ ተመስገን ( ዶ/ር) የሀገሪቷን የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንትን ለመሳብና ለማበረታታት የተቋቋመውን ተቋም በኃላፊነት እንዲመሩ ተሹመዋል።

Via Capital

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

22 Oct, 09:11


ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በ#BRICS2024 የመሪዎች ጉባኤ ለመሳተፍ ካዛን ገቡ

ጠ/ሚኒስትር አብይ አህመድ በብሪክስ የመሪዎች ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ሩሲያ ካዛን መግባታቸው ተገለጸ!

ጠ/ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ #በብሪክስ (BRICS) የመሪዎች ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ሩሲያ መግባታቸውን የአዘጋጇ የሩሲያዋ ታታርስታን ግዛት ፐሬዝዳንት ጽ/ቤት ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።

"የኢትዮጵያ ጠ/ሚኒስትር አብይ አህመድ በ BRICS የመሪዎች ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ #ካዛን ገብተዋል፤ በካዛን አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የግዛቷ ፕሬዝዳንት ሩስታም ሚኒካኖቭ አቀባበል አድርገውላቸዋል" ሲል መግለጫው አትቷል።

በካዛን በሚካሄደው የመሪዎች ስብሰባ ከ30 ሀገራት በላይ ተወካዮች ይታደማሉ መባሉን ከሩሲያ የዜና አገልግሎት ታስ ያገኘነው መረጃ ያሳያል፤ የዩናይትድ አረብ #ኤሚሬቱ ፕሬዝዳንት ቢን ዛይድ፣ #የኢራኑ ፕሬዝዳንት ማሱድ ፔዜሽክያን፣ #የህንዱ ፕሬዝዳንት ናሬንድራ ሞዲ በካዛን ከተገኙ መሪዎች ይገኙበታል። ኢትዮጵያ በተያዘው የፈረንጆቹ 2024 መጀመሪያ ላይ ቡድኑን በይፋ መቀላቀሏ ይታወቃል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

22 Oct, 09:10


የፖለቲካ ፓርቲዎች በምርጫ ቦርድ የጊዜያዊ ዕውቅና ለማግኘት ሲከፍሉ የነበረው 100 ብር ከዚህ በኋላ 15ሺ መሆኑ ተገለጸ

የፖለቲካ ፓርቲዎች የጊዜያዊና ሙሉ ዕውቅና ለማግኘት የሚጠበቅባቸው ክፍያ መሻሻሉን ምርጫ ቦርድ አስታወቀ፤ ለጊዜያዊ ዕውቅና 15ሺ፣ ለሙሉ ዕውቅና 30ሺ ነው ብሏል።የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ጥቅምት 12 ቀን ባወጣው መግለጫ ለሀገር አቀፍ እና ለክልላዊ ፖለቲካ ፓርቲ ጊዜያዊ ሰርተፍኬት ለማግኘት 100 ብር ብቻ ያስከፍል እንደነበር አውስቶ ከጥቅምት 11 ቀን 2017 ዓ.ም በኋላ ግን ክፍያው 15ሺ ብር መሆኑን እወቁልኝ ብሏል።

በተመሳሳይ የሀገር አቀፍ እና ክልላዊ የፖለቲካ ፓርቲዎች ሙሉ ዕውቅና ለማግኘት እስከ ትላንት ጥቅምት 11 ቀን 2017 ዓ.ም ይከፍሉ የነበረው 200 ብር ብቻ መሆኑን አስታውሶ ከዚህ በኋላ ግን ክፍያው 30ሺ ብር ነው ሲል አስታውቋል።የተመዘገቡ ፖለቲካ ፓርቲዎች መሰረታዊ ሰነዶቻቸውን በጉባኤ አሻሽለው ሲያቀርቡ 30 ብር የአገልግሎት ክፍያ ሲያስከፍል እንደነበር ጠቁሞ ከዚህ በኋላ ግን ሰነዶቹን ያሻሻለ ፓርቲ 5ሺ እንዲከፍል ወስኛለሁ ሲል ገልጿል።

ምርጫ ቦርድ ክፍያውን ያሻሻልኩት የፖለቲካ ፓርቲዎች የምዝገባ እና የሰነድ ማሻሻያ አገልግሎት ክፍያ መጠኑ በቦርዱ እንዲወስን በአዋጅ ስልጣን ስለተሰጠኝ ነው ብሏል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

22 Oct, 05:09


ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ ( ዶ/ር ) ኢትዮጵያ በ2029 የአፍሪካ ዋንጫን ለማዘጋጀት ይፋዊ ጥያቄ አቀረቡ

ኢትዮጵያ በ2029 የሚካሄደውን የአፍሪካ ዋንጫ የማዘጋጀት አቅም እንዳላት የገለፁት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለካፍ ፣ለፊፋ ፕሬዚዳንቶች እና ለካፍ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ከፍተኛ አመራሮች በታላቁ ቤተ-መንግስት የእራት ግብዣ አከናውነዋል።

በፕሮግራሙ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ የ2029 አፍሪካ ዋንጫን እንድታዘጋጅ በይፋ ጠይቀዋል።

የካፍ ፕሬዚዳንት ፓትሪስ ሙትሴፔ በበኩላቸው ÷ በኢትዮጵያ ለተደረገላቸው ደማቅ አቀባበል ምስጋና አቅርበው፣ የኢትዮጵያውያን ባህል፣እሴትና እንግዳ ተቀባይነት ኢትዮጵያ ቤታችን እንደሆነች እንዲሰማን አድርጎናል ብለዋል፡፡

ኢትዮጵያ የ2029ኙን የአፍሪካ ዋንጫ ለማዘጋጀት ያቀረበችውን ጥያቄ ካፍ ከኮሚቴው ጋር እንደሚመክርበት ገልዋጸል።

የፊፋ ፕሬዚዳንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ ÷ የሰው ዘር መገኛ የሆነችው ኢትዮጵያ፤ የኛም ሀገር ነች ሲሉ ተናግረዋል።

በመርሐ ግብሩ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ለሁለቱም ፕሬዚዳንቶች የኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን መለያን በስጦታ አበርክተዋል፡፡

በተመሳሳይ የፊፋው ፕሬዚዳንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ 2029 የሚል ፊርማቸውን ያሳረፉበትን ኳስ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) አበርክተዋል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

22 Oct, 05:06


የመርካቶው የእሳት አደጋ አሁናዊ ሁኔታ ከቦታው

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

21 Oct, 19:34


አዲሱን የደሞዝ ጭማሪን ከታች ይመልከቱ

የተሻሻለው የመንግስት ደሞዝ ጭማሪ ስኬል ይፋ ሆኗል።

የጥቅምት ወር የመግስት ሰራተኞች ደመወዝ በተጠቀሰው ስኬል መሰረት ይተገበራል ተብሏል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

21 Oct, 19:21


ለ 56 ዓመት በሳምንት አንዴ እየተገናኙ ቢራ የጠጡት እንግሊዝያውያን ጓደኛሞች አነጋጋሪ ሆነዋል

ይህ የእንግሊዝ በ 80 ዎቹ እድሜ ላይ የጡረተኞች ቡድን በፈረንጆቹ ከ 1968 ጀምሮ ጠንካራ ትስስርን አስጠብቆ ቆይቷል፣።

በየሳምንቱ ሐሙስ በየመጠጥ ቤቱ ለ56 ዓመታት እየተሰበሰቡ ተገናኝተዋል።
በኮሮና ጊዜ እና በአንዳንድ በአሎች ላይ ባይገናኙም ረጅሙን አመት ግን ተገናኝተው ተጫውተዋል።
BBC

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

21 Oct, 19:21


በመርካቶ ሸማ ተራ አከባቢ የተከሰተውን የእሳት አደጋ እስከ አሁን መቆጣጠር ባለመቻሉ በሄሊኮፕተር እየተሞከረ መሆኑ ተገለጸ

👉 "በመርካቶ ሸማ ተራ አከባቢ በተከሰተው የእሳት አደጋ በንብረት ላይ ለደረሰው ጉዳት እጅግ አዝነናል" ከንቲባ አዳነች አቤቤ

የተከሰተውን የእሳት አደጋ ለመቆጣጠር ከእሳት አደጋ  እና ስጋት መከላከል እንዲሁም  ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር በመሆን ርብርብ እየተደረገ  ስለመሆኑ የገለጹት ከንቲባዋ አደጋውን ቶሎ ለመቆጣጠር እየተደረገ ያለዉን ጥረት  አዳጋች ያደረገዉ የአካባቢው መንገድ የእሳት አደጋ መኪና በተሟላ ሁኔታ ለመንቀሳቀስ አስቸጋሪ በመሆኑ ምክንያት ነው ብለዋል።

በመሆኑም የእሳት አደጋውን ለመቆጣጠር በሄሊኮፕተር ለመጠቀም እየጣርን  ነው ሲሉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገልጸዋል። 

ከንቲባዋ አክለውም ይህንን አደጋ ለመቀነስ ርብርብ እያደረጉ የሚገኙትን አካላት ሁሉ ጥረታቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ አሳስበዋል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

21 Oct, 08:38


የኦጋዴን ብሄራዊ ነፃ አውጭ ግንባር (ኦብነግ) በብሔራዊ ምክክር ኮሚሽን ውስጥ የነበረውን ተሳትፎ ማቆሙን አስታወቀ!

የኦጋዴን ነጻ አውጪ ግንባር (ኦብነግ) አሳታፊነትና ግልጸኝነት ስላላየሁበት ከአገራዊ ምክክር ኮሚሽን ተሳታፊነት እራሴን አግልያለሁ ሲል ባወጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡በሶማሌ ክልል ገዢው ፓርቲ በቅርቡ የወሰዳቸው እርምጃዎች ተሳታፊዎችን አንድ ወገንን በመምረጥ፣ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ያለውን ስምምነት በመጣስ እና የተለያዩ ድምፆችን ወደ ጎን በመተው ሂደቱን አግላይ በማድረጉ ምክንያት ራሱን ከምክክር ሂደቱ ማግለሉን ነው የገለጸው፡፡

ሁሉንም ባለድርሻ አካላት በማሰባሰብ የግጭት መንስኤዎችን ለመፍታት የታቀደውን የብሔራዊ ውይይት ዓላማን የሚቃረን፣ ከአማራ፣ ከኦሮሚያ እና ከትግራይ የተውጣጡ ቁልፍ የፖለቲካ ተዋናዮች በሌሉበት እና እየተከሰቱ ያሉ ግጭቶችን ለመፍታት ጥረት እየተደረገ ባልሆነበት ሁኔታ፣ አሁን ያለው ውይይት የአንድ ወገንን ያማከለ በመሆኑ እውነተኛ ሰላም የማምጣት አቅም የሌለው መሆኑን ፓርቲው በመግለጫው አንስቷል።

ኦብነግ ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም ማምጣት የሚችል እውነተኛ፣ ሁሉን አቀፍ እና ግልጽ ውይይት ለማድረግ ቁርጠኛ ቢሆንም፤ እንዲህ ያለው ምክክር ሁሉን አቀፍ እና ታእማኒ እስኪሆን ድረስ አሁን ባለው ማዕቀፍ ውስጥ አልሳተፍም ሲል ገልጿል።የኦጋዴን ብሄራዊ ነፃ አውጭ ግንባር (ኦብነግ) በ2010 ዓ.ም ሰላማዊ የፖለቲካ እንቅስቃሴን ለማድረግ ከመንግሥት ጋር ስምምነት አድርጎ ወደሀገር ውስጥ መግባቱ የሚታወስ ነው፡፡

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

20 Oct, 14:02


" ትናንትና 2 ዛሬ ደግሞ 10 አስክሬን ተገኝቷል " - የጋሞ ዞን ፖሊስ

ከአቡሎ አርፋጮ ወደ አርባምንጭ ከተማ 16 ሰዎችን እና ሙዝ ጭና ስትጓዝ የነበረች ጀልባ ባሳለፍነው ሐሙስ 10 ሠዓት ከ20 ገደማ ጫሞ ሐይቅ ላይ ሰጥማ ነበር።

ይህ ተከትሎ እየተከናወነ ባለ የነፍስ አድን ሥራ ትናንት 2 ዛሬ ደግሞ 10 አስከሬን መገኘቱን የጋሞ ዞን ፖሊስ መምሪያ አሳውቋል።

እስከ ዓርብ ድረስ ባለው 3 ሰዎች በሕይወት መገኘታቸውን ገልጿል።

በአጠቃላይ በጀልባዋ ከተሳፈሩት መካከል እስከ አሁን የአንዱ ሰው ሁኔታ ስላልታወቀ ፍለጋው መቀጠሉ ተመላክቷል።

የጋሞ ዞን ፖሊስ የአደጋው መንስኤን በተመለከተ ፥ " የጀልባዋ የመጫን አቅም 35 ኩንታል ሆኖ ሳለ በዕለቱ 70 ኩንታል ሙዝ እና 16 ሰዎችን ጭና ነበር፤ ይህም ከልክ በላይ መጫን በመሆኑ ለአደጋው መከሰት መንስዔ ሆኗል " ብሏል።

መረጃው የኤፍ ቢ ሲ ነው።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

20 Oct, 04:53


Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ) pinned «ሰበር ዜና ..😭 የግድያዉ ምክንያት ታወቀ ..አንቆ ገደላት | በአደባባይ ባለቤቱን አዋረዳት ! Ethiopia Ne... https://youtu.be/Na7qIYARZe8?si=82HiSqwDmXogtb9s»

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

20 Oct, 04:53


ሰበር ዜና ..😭 የግድያዉ ምክንያት ታወቀ ..አንቆ ገደላት | በአደባባይ ባለቤቱን አዋረዳት ! Ethiopia Ne...

https://youtu.be/Na7qIYARZe8?si=82HiSqwDmXogtb9s

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

19 Oct, 15:37


አዲሱ የመንግስት ስራተኞች ደመወዝ ከጥቅምት ወር ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚደረግ የገለፀው የገንዘብ ሚኒስትር ለዚህም የአፈፃፀም መመሪያ መዘጋጀቱን አስታወቀ!

የገንዘብ ሚኒስትር እንደገለፀው የጥቅምት ወር የደመወዝ ክፍያ በአዲሱ በተሻሻለው የደመወዝ ስኬል መሰረት መሆን ይጀምራል ብሏል። ለዚህም በቂ ዝግጅት ከመደረጉ በላይ የአፈፃፀም መመሪያ መዘጋጀቱን አስታዉቋል።

ካፒታል ከዚህ ቀደም በተደረገዉ ማሻሻያ ላይ የመንግስት ሰራተኞች ያቀረብትን ቅሬታ አስመልክቶ እንደዘገበው አዲሱ የደመወዝ ማሻሻያ ጥናት: የሚኒስትሮች ምክር-ቤት ከማፅደቁ አስቀድሞ ሰራተኞችን ማወያየት እንዳለበት እና በድጋሚ መታየት እንደሚኖርበት ተጠይቆ ነበር።እነዚሁ ሠራተኞች እንደገለፁት የደመወዝ ማሻሻያው አሁን ያሉበትን የኑሮ ሁኔታ እንደተባለውም ከግምት ያላስገባና እንደጠበቁት እንዳልሆነ ማስረዳታቸው ይታወቃል።

ይሁን እንጂ የገንዘብ ሚኒስቴር ደመወዝ ማሻሻያ ረቂቅ ለሚኒስትሮች ምክርቤት በቀን 28 /12/ 2016 ዓ.ም. ያቀረበዉ ከሰሞኑ በካቢኔው መፅደቁን አስታዉቋል።ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ እንዳስታወቁት " በአጠቃላይ ሪፎርሙ በህብረተሰቡ ላይ የተለየ ጫና አለማምጣቱን እና የተፈራው የዋጋ ንረት አለመድረሱን " የተናገሩት የካቢኔው የ 100 ቀን አፈፃፀም ግምገማ አስመልክተው በሰጡት ማብራሪያ ነዉ።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ካፒታል ማሻሻያው ተከትሎ በወቅቱ በሰራዉ ዘገባ የደሞዝ ጭማሪ መኖሩን መንግስት መናገሩን ተከትሎ በማግስቱ  የሁሉም ነገር ዋጋ በሁለት እጥፍ ጨምሯል። በዚህም ሰራተኛዉም ሆነ በዝቅተኛ ኑሮ ላይ የነበሩት ሰዎች ምንም የተሰጣቸዉ ነገር ሳይኖርና ጭማሪ እጃቸዉ ሳይገባ የኑሮ ዉድነቱ ተባብሶ ቀጥሏል ሲሉም ሁኔታዉን በምሬት ገልፀዉለት እንደነበር ይታወሳል።
Via Capital

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

19 Oct, 11:50


ኢትዮጵያንና ሌሎች ወታደር አዋጭ የሆኑ ሃገራት በሶማሊያ በአዲሱ የሰላም ማስከበር ተልዕኮ ውስጥ ለመቀጠል ያላቸውን 'ፈቃደኝነት እና ዝግጁነት' ገለጹ

ኢትዮጵያን ጨምሮ ሌሎች በሶማሊያ የአፍሪካ ህብረት የሽግግር ተልዕኮ (አትሚስ) ወታደር አዋጭ የሆኑ ሀገራት የመከላከያ ሚንስትሮች በሶማሊያ የሰላም ማስከበር ጥረታቸውን በአዲሱ ተልዕኮ ለመቀጠል ያላቸውን “ፍላጎት እና ዝግጁነት” ገልጸዋል።

ሚንስትሮቹ ይህን የገለጹት ጥቅምት 6 ቀን 2017 ዓ.ም በኢትዮጵያ መከላከያ ሚኒስትር አይሻ መሀመድ ጋባዥነት ከተዘጋጀው የአፍሪካ መከላከያ ሚኒስትሮች ጉባኤ ጎን ለጎን የተካሄደው የሚኒስትሮች ስብሰባ መጠናቀቁን ተከትሎ ባወጡት የጋራ መግለጫ ነው።

ስብሰባው ከብሩንዲ፣ ጅቡቲ፣ ኢትዮጵያ፣ ኬንያ እና ዩጋንዳ የተውጣጡ የመከላከያ ሚንስትሮችን አካቷል ተብሏል።

አዲስ ስታንዳርድ የተመለከተው የጋራ መግለጫ እንዳስታወቀው ባለፉት አስራ ሰባት ዓመታት ወታደር አዋጭ የሆኑ ሃገራት በሶማሊያ ሽብርተኝነትን በመዋጋትና ሀገሪቱን በማረጋጋት የከፈሉትን መስዋዕትነት እውቅና ሰጥቶ፤ ለሶማሊያ ፌደራል መንግስት ተቋማትን በማጎልበት እንዲሁም በማሳደግ ረገድ አስተዋጽኦ አድረጓል ብሏል።