Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ) @hulaadiss Channel on Telegram

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

@hulaadiss


ትክክለኛዉ የሁሌ አዲስ ሚዲያ ገፆች

Facebook : bit.ly/42rUuKj
WhatsApp : bit.ly/Huleadis_whatsapp
YouTube : bit.ly/3p7kj3N
Twitter : bit.ly/3NVMRrB
Telegram: bit.ly/Huleadis_tele

ለጥቆማ ና አስተያየት እንዲሁም ለማስታወቂያ ስራ ተከታዮን አድራሻ ይጠቀሙ
bit.ly/3VMy7x7

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ) (Amharic)

ሁሌ አዲስ ሚዲያ ከዚህ በታች በፊት ፊትህን ሊረዳ ይችላሉ። የትክክለኛዉ ሁሌ አዲስ ሚዲያ ማለት የትክክለኛ ቦታዎችን በክርስቲን ገበታ በሚጠቀም ትንሽ እና ሎሌ ለውጥ ስለተጠቀሙ ነው። ሁሌ አዲስ ሚዲያ ታለሉን የኢንተርኔት በሽታዎችን ይመልከቱ። በኢትዮጵያ የሚሞተበት የሁሌ አዲስ ሚዲያ ነው። ሁሌ አዲስ ሚዲያ የዚህን በሽታ መሰረት ያግኙ፣ የበረከትዉን ተጋላጭ አርሶ ያነቡ፣ ለወደቁዉ አዳዲስ መረጃዉን ያግኙ። ሁሌ አዲስ ሚዲያዉ በአማርኛ እና አፍሪካውም ስለ ትክክለኛ ያልሆነ እና ከዚህ በታች ሁሌ ሚዲያዉን ለመረጃዉና ለየትኛዉ እሴት የሚሳይ ተጎዋቂ ላይ በእነዚህ ቦታም ውስጥ በክርስቲን ገበታ በሚጠቀም ትንሽ እና ሎሌ ለውጥ ለሚጠቀም ልባቸዉን ይምረጡ። ይህ ነገር ለምሳሌ ሁሌ አዲስ ሚዲያዉ በጣም በአማርኛ እና አፍሪካውም ስለ ትክክለኛዉ ያልሆነ እና ስለ መመርመር የተጠቀመ ንብረት በከፈለዉ ስብስብ ማለት ይችላሉ።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

17 Feb, 19:00


ወንጂ ሸዋ ስኳር ፋብሪካ በተያዘው የበጀት ዓመት አንድ ሚሊዮን ኩንታል ስኳር አምርቶ ለገበያ ለማቅረብ ማቀዱ ተነገረ

ፋብሪካዉ ታሪክ አንድ ሚሊዮን ኩንታል የተመረተው አንዴ ብቻ ሲሆን በወቅቱም የአገዳ መትከያ መሬት ስፋት 12 ሺህ ሄክታር ነበር፤ አሁን አንድ ሚሊዮን ኩንታል ለማምረት ያለው የመሬት ስፋት ዘጠኝ ሺህ ሄክታር መሆኑ ተጠቁሟል ።

ኢፕድ የፋብሪካው ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ጀማል አማን ነገሩኝ ብሎ እንደዘገበው በ2016 ዓም 300 ሺ ኩንታል ስኳር አምርቷል፤ በተያዘው የበጀት ዓመት አንድ ሚሊዮን ኩንታል ስኳር ለማምረት ዝግጅት ተደርጓል።

አሁን ላይ አመራሩ ሰባቱንም ቀን ተከፋፍሎ፣ አገዳ አስገብቶ ስኳር አውጥቶ ነው የሚውለው፤ በእኔ ቀን ፋብሪካው የተሻለ ማምረት አለበት ብሎ እየሰራ ይገኛል ያሉ ሲሆን እስካሁን በቀን ሰባት ሺ ኩንታል ስኳር ይመረታልም መባሉን ከዘገባው ለመረዳት ተችሏል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

17 Feb, 18:19


የኤርትራው ፕረዚዳንት ኢሳያስ አፈወረቂ በሰሜኑ የኢትዮጵያ ክፍል አዲስ ግጭት ለመቀስቀስ እየሰራ ነው ሲል አልጀዚራ በአስተያየት መስጫው ላይ አስነብቧል

የኢሳያስ የ32 አመት የአገዛዝ ዘመን ኤርትራ ነፃነቷን ካወጀች በኋላ የህገመንግስት መዋቅር የላትም ብሏል። ሕገ መንግሥት የለም፣ ፓርላማ የለም፣ሲቪል ሰርቪስ የለም። ኤርትራ ውስጥ ህግ አስፈፃሚ፣ ህግ አውጭ እና ህጋዊ ተርጓሚ አንድ ብቻ ነው፣እሱም ፕሬዝዳንት ኢሳያስ ብቻ ነው ያላል አስተያየቱ።

በኤርትራ ወታደራዊ አገልግሎትም በግዴታ እና የአገልግሎት ዘመኑ በጊዜ ያልተገደበ ነው።

ወጣት ኤርትራዊያን ከፕሬዚዳንቱ ጦር ለማምጣት እድሜ ልካቸውን በሽሽት ይኖራሉ።
በዚህም ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የኤርትራ ወጣቶቾ በተለይ ወንዶች በህገ ወጥ መንገድ ወደ ጎረቤት ሀገራት እና አውሮፓ የሚሰደዱ እና ህይወታቸውን የሚያጠፉ ብዙ ናቸው።

ጦርነት የኤርትራ መንግስት ዋና የገቢ ምንጩ መሆኑን ዘገባው ያትታል። እዚህም እዚያም የሚቀሰቅስ ግጭት፣ አማፂያንን፣ወይም መንግስታትን በመደገፍ ጦርነትን ያባብሳል።

ዛሬ ኢሳያስ እንደገና ሊገመት በሚችል መልኩ አጥፊ በሆኑ እንቅስቃሴዎች ላይ ተጠምዷል።
በኢትዮጵያ ፌደራል መንግሥት እና በህወሓት መካከል የተፈጠረው ጦርነት በፕርቶሪያ ስምምነት ቢቋጭም ኢሳያስ አፈወርቂ በዚህ ስምምነት ደስተኛ አይደለም።

በዚህም በሰሜኑ የኢትዮጵያ ክፍል ድጋሚ ግጭት እንዲቀሰቀስ እየሰራ ነው፣አሁኑኑ እርምጃ መውሰድ  ይገባል" ይላል አስተያየት ገፁ።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

17 Feb, 14:55


ያለደረሰኝ ሲገበያዩ የተገኙ ከ2,900 በላይ ግለሰቦችና ተቋማት በገንዘብ ተቀጡ!

የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ያለደረሰኝ የሚደረግ ግብይትን መልክ ለማስያዝ በሚል በጀመረው የቁጥጥር ስራ #ያለደረሰኝ ሲገበያይ ያገኘሁትን 100 ሺህ ብር እቀጣለሁ ባልኩት መሰረት ቅጣቱን ተግባራዊ እያደረግኩ ነው ብሏል፡፡

በዚህ መሰረት በመንፈቅ ጊዜ ውስጥ 3,000 በላይ የንግድ ድርጅቶችና ግለሰቦችን አብዛኞቹን ማለትም 2,970ዎቹን እያንዳንዳቸውን 100,000 ብር በመቅጣት  ከ297 ሚሊዮን ብር በላይ መሰብሰቡንና የተቀሩትን 887ቱን ደግሞ የቃል ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷቸዋል።

ከአስተዳደራዊ እርምጃው ባሻገር ሌሎች 839 ግለሰቦች ደግሞ ጉዳያቸው በህግ እየታየ መሆኑን የገቢ አሰባሳቢ ቢሮው የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ሰውነት አየለ ተናግረዋል፡፡

በ3 ወራት ጊዜ ውስጥ ሳይከፈል ለረጅም ጊዜ ተከማችቶ ከነበረ 11 ቢሊዮን ብር የግብር እዳ ከ6 ቢሊዮን ብር በላዩን ከፋናንስ ኢንቴሌጀንት አስተዳደር ጋር በመሆን አስከፍለናል ብለዋል፡፡
በመንፈቅ ጊዜ ውስጥ 111 ቢሊዮን ብር ከገቢ ግብር መሰብሰቡን የሚናገረው ቢሮው በጥር ወር ብቻ ከ12 ቢሊዮን ብር በላይ ሰብስቢያለሁ ብሏል፡፡
#ሸገርኤፍኤም

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

17 Feb, 14:53


የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከኤር ባስ ኩባንያ ጋር የጥገና አገልግሎት ስምምነት ተፈራረመ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከኤር ባስ ኩባንያ ጋር የሰባት አመት የጥገና እና ተያያዥ አገልግሎቶች ስምምነት ተፈራረመ።


ኩባንያው 24 ለሚሆኑ A350 እንዲሁም A350-900 እና A350-1000 ሞዴል ኤር ባስ አውሮፕላኖች የጥገና አገልግሎቶችን እንደሚሰጥ ተነግሯል፡፡

ስምምነቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዓለምን ለማገናኘት ለሚያደርገው ጥረት ከፍተኛ እገዛ እንደሚያደርግለት ተጠቁሟል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ የኦፕሬሽን ዘርፍ ዋና ሃላፊ አቶ ረታ መላኩ፤ ስምምነቱ አየር መንገዱ የሚሰጠውን አገልግሎት እንዲያሳድግ እና የጥገና አገልግሎት መዘግየትን በማስቀረት በኩል ጉልህ ሚና ይኖረዋል ብለዋል፡፡

የኤር ባስ የአፍሪካ እና መካከለኛው ምስራቅ የደንበኞች አገልግሎት ምክትል ፕሬዚዳንት ላውረን ኔግሬ ተቋማቸው የኢትዮጵያ አየር መንገድ የጥገና አገልግሎትን ለመደገፍ ሃላፊነት በመውሰዱ ከፍተኛ ኩራት እንደሚሰማው ገልጸዋል፡፡

ስምምነቱ በኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ኤር ባስ መካከል ያለውን መልካም ግንኙነት ይበልጥ እንደሚያጠናክርም ተነግሯል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

17 Feb, 14:44


Capital: ፕሬዝዳንቱ ለፕሮጀክቱ ምላሽ ሰጡ| ከ 260 ሺህ በላይ የሳይበር ጥቃት ደረሰ |  ዳንጎቴ ለኢትዮጵያ...
https://youtube.com/watch?v=0zrEGRaWAdk&si=xhzzFGzES1ik0xyw

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

17 Feb, 14:05


የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት 54 ዓይነት የካንሰር መድኃኒቶች በ600 ሚሊየን ብር ወጪ በማድረግ ማስገባቱ ተገለፀ

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት የጤና ተቋማትን ፍላጎት መነሻ በማድረግ 54 ዓይነት የካንሰር መድኃኒት በማቅረብ የማህበረሰቡን ፍላጎት ለማሟላት እየሰራ ይገኛል ሲሉ የአገልግሎቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ሰሎሞን ንጉሴ ለብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቭዥን ገልፀዋል።

የካንሰር ህክምና አገልግሎት አሁን ላይ በ31 ጤና ተቋማት ላይ እንደሚሰጥ ገልፀው የፍላጎት መጠን መጨመር ምክንያት በማድረግ አጠቃላይ ፍላጎታቸውን መነሻ በማድረግ 600ሚሊዮን ብር ወጪ በማድረግ ትልልቅ ግዢ መፈፀሙን አቶ ሰለሞን ገልፀዋል። እነዚህ መዳኒቶች በአብዛኛው ወደ ሀገር ውስጥ ገብተው ወደ ጤና ተቋማት መሰራጨታቸውን አክለዋል እንዲሁም ከፊሉ መድሀኒት በመግባት ላይ ይገኛሉ ብለዋል። ስለሆነም በክምችት የመገኘት ምጣኔ ከ 80 በመቶ ገዳማ ላይ እንደሚገኝም አክለዋል።

የአቅርቦት መቆራረጥ እንዳይከሰት እንዲሁም የህዝቡ የፍላጎት መጠን መጨመር ጋር ተያይዞ የጤና ሚኒስትር በአንድ ፕሮግራም መልክ በመያዝ የካንሰር መድኃኒት የሚደጎሙበትን አግባብ የሶስትዮሽ ስምምነት በመፍጠር ጤና ተቋማት ከጤና ሚኒስትር እና የመድሀኒት አገልግሎት በመሆን ስምምነት መፈራረማቸውን ግልፀዋል። ስለሆነም በስምምነቱ መድሀኒት በተመጣጣኝ ዋጋ ለማቅረብ የዋጋውን 50 በመቶ ጤና ሚኒስትር ይሸፍናል እንዲሁም መድኃኒቱን ለማጓጓዝ እና የባንክ አገልግሎት እንዲሁም የጉምሩክ እና ሌሎች ክፍያዎችን ወደ 13 በመቶ ገደማ ጤና ሚኒስትር በመሸፈን ለተገልጋዮች ድጎማ ለማድረግ አቅደን እየሰራን ነው ያሉት የአገልግሎቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ሰሎሞን ንጉሴ ለብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቭዥን ጨምረው ገልፀዋል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

17 Feb, 11:04


በጋምቤላ ክልል በአራት ወረዳዎች በተከሰተ የአጣዳፊ ተቅማጥና ትውከት የዘጠኝ ሰዎች ህይወት ማለፉ ተነገረ።

የጋምቤላ ክልል የጤና ቢሮ የህብረተሰብ ጤና ዳይሬክተር አቶ ኝኪዎ ጊሎ ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንደተናገሩት፤ለክልሉ አጎራባች በሆነው ደቡብ ሱዳን በሽታው ተከስቶ እንደነበር ተናግረዋል።

በክልሉ ኑዌር ብሔረሰብ ዞን በአኮቦ፣ ዋንቱዋ፣ ማኩዌይ እና ላሬ ወረዳዎች የአጣዳፊ ተቅማጥና ትውከት መከሰቱን እና ኮሌራ መሆኑን ለማረጋገጥ ዉጤቱ እየተጠበቀ መሆኑን ነግረዉናል፡፡

በበሽታው ከተያዙት 1መቶ36 ሰዎች መካከል የዘጠኝ ሰዎች ህይወት ሲያልፍ፤31 ሰዎች በህክምና ላይ እንደሚገኙም ነዉ አቶ ኝኪዎ የገለጹት፡፡

96 ሰዎች ደግሞ ከበሽታው ማገገማቸውንም ዳይሬክተሩ ለጣቢያችን ተናግረዋል፡፡

በሽታው በተከሰተባቸው አራቱ ወረዳዎች መድኃኒቶችና የህክምና መገልገያ ቁሳቁሶችን ማድረስ መቻሉንም ነዉ የገለጹት፡፡

አቶ ኝኪዎ በሽታው ወደሌሎች አካባቢዎች እንዳይስፋፋ ሕብረተሰቡ አካባቢውን እንዲያጸዳ እና ንጽህናውን እንዲጠብቅም ተናግረዋል።

ሊዲያ ደሳለኝ

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

17 Feb, 11:04


የኬንያ መንግስት ከትናንት ጀምሮ በጫት ዋጋ ላይ ጭማሪ ማድረጉ ሱማሌያዊያንን አስቆጣ፡፡ የኬንያ የግብርና ሚኒስቴር ዛሬ ባወጣው መግለጫ የጫት ዋጋን ለመወሰን የተቋቋመ ኮሚቴ እንዳለ ጠቅሶ ኮሚቴው ወደውጭ አገር በሚላክ ምርት ላይ ጭማሪ ለማድረግ መወሰኑን አስረድቷል፡፡

ጭማሪው የተደረገውም ምርቱን በተመለከተ መረጃዎችን በማገናዘብ፣ አምራቾች የሚያደርጉትን ወጪ ከግምት ውስጥ በማስገባት እንዲሁም በአቅርቦትና ፍላጎት መካከል ያለውን ልዩነት በማየት እንደሆነ አስታውቋል፡፡

በዚህ መሰረት በአሁኑ ወቅት በኪሎግራም ሰባት መቶ ሽልንግ የነበረው ደረጃ አንድ የሚባለው ጫት አንድ ሺ ሶስት መቶ ብር መግባቱን የገለፀ ሲሆን ሁለተኛ ደረጃ ደግሞ ከሶስት መቶ ሀምሳ ሽልንግ ወደሰባት መቶ መጨመሩን አስታውቋል፡፡

እንዲሁም አለሌ የሚባለው ደግሞ ከአምስት መቶ ወደአንድ ሺህ መግባቱን ጠቅሶ ከዛሬ ጀምር ይህ ጭማሪ ተግባራዊ እንዲሆን ውሳኔ ማሳለፉን አስረድቷል፡፡ ይህ ይፋ መሆኑን ተከትሎ ሱማሊያዊያን በማህበራዊ ሚዲያዎች በኬንያ መንግስት ላይ ተቃውሞ ሲያሰሙ ውለዋል፡፡ ኬንያ ጫትን ለውጭ ገበያ የምታቀርበው ለሱማሊያ ብቻ መሆኑ የሚታወቅ ነው፡፡

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

16 Feb, 18:24


የፕሪቶሪያውን ስምምነት በሚመለከት በአፍሪካ ሕብረት ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተካሄደ

በትግራይ ክልል የነበረውን ግጭት ያስቆመው የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ሂደትን በተመለከተና ከስምምነቱ "ሌሎች ምን እንማር?" በሚል ርዕስ ዛሬ የካቲት 9ቀን 2017ዓ.ም
በአፍሪካ ህብረት ሪፓርት ቀርቦ ውይይት ተካሂዷል።

በዚህ ውይይት ላይም የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ እና የህወሓት ሊቀመንበር ደብረ ጽዮን ገብረሚካኤል(ዶ/ር) የተገኙ ሲሆን ከኢትዮጵያ መንግሥት በኩል ደግሞ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጌድዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ፣ የሰላም ሚኒስትሩ አቶ መሐመድ እድሪስ እና ሌሎች ተገኝተዋል።

የፕሪቶሪያውን ስምምነትና አፈፃፀም የተመለከተውን ሪፓርት ደግሞ ተሰናባቹ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር ሙሳ ፉኪ ማህማት፣ የቀድሞ የናይጀሪያ ፕሬዚዳንትና የአፍሪካ ህብረት አደራዳሪ ቡድን ሰብሳቢ ኡሊሲንጎን ኦባሳንጆ እና ከፍተኛ ኮሚሽነሮች አቅርበዋል።

ከአንድ ሰአት በላይ የዘለቀ ውይይት ከተካሄደ በኋላ አቶ ጌታቸው ከጋዜጠኞች ለቀረበላቸው ጥያቄዎች ምላሽ ሰጥተዋል።

የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዚዳንት <<የዛሬው መድረክ እስካሁን የሄድንበት ርቀት መገምገም ነው። ከጀመርነው ፍጥነት አንፃር ገና ያላለቁ ነገሮች አሉ። ግን በተሻለ ፍጥነት መጨረስ የምንችልበት እድል ለማግኘት ነው የመጣነው" ብለዋል። አክለውም ሰላምን ከመስበክ ፣ ሰላምን ከመተግበርም ሆነ ከምንም ነገር በላይ ግን ተፈናቃዮች ወደወትሮ ህይወታቸው የሚመለሱበትና ህገመንግስቱ በሚያስቀምጠው መሰረት የፕሪቶሪያ ውል ሙሉ ለሙሉ ተፈፃሚ የሚሆንበት ጉዳይ ላይ ነው ሀሳብ የተለዋወጥነው። በቀጣይም በዚህ መሰረት የምንቀጥል ይመስለኛል" ብለዋል።

Reporter

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

16 Feb, 13:39


#CapitalNews የኢትዮጵያ የአበባ የወጪ ንግድ በቫለንታይን ቀን በ7% መቀነሱ ተነገረ

በተለምዶ ንቁ የሆነው የኢትዮጵያ የአበባ በወጪ ንግድ ዘርፍ፣ ወሳኝ በሆነው የቫለንታይን ( የፍቅረኞች) ቀን ወቅት ማለትም ከጥር 24 እስከ የካቲት 6 ቀን 2017 ዓ.ም. ድረስ የተላከዉ ምርት ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ7% ቅናሽ አሳይቷል።

ካፒታል ከኢትዮጵያ የሆርቲካልቸር አምራች ላኪዎች ማኅበር ያገኘችዉ መረጃ እንደሚያመለክተው፣ የወጪ ንግድ መጠኑ በ2016 ከነበረው 2,913,178.50 ኪሎ ግራም በ207 ወደ 2,696,069 ኪሎ ግራም ቀንሷል።

ይህንን ዝቅተኛ አፈፃፀም ሊመጣ የቻለዉ በዋነኝነት በቁልፍ የአበባ ማምረቻ ክልሎች ውስጥ እየቀጠለ ባለዉ አለመረጋጋት ምክንያት መሆኑን ለመረዳት ተችሏል።

በአካባቢው ያለው አለመረጋጋት የምርትና የሎጂስቲክስ ሂደቶችን በማስተጓጎል ኢትዮጵያ የፍቅረኞች ቀን አበባዎች ከፍተኛ ፍላጎት መጠቀም እንዳትችል አድርጓታል ተብሏል።

የቫለንታይን ቀን ወቅት በተለምዶ ለአበባ እርሻዎች ወሳኝ ወቅት ሲሆን ከፍተኛ ገቢ እና የውጭ ምንዛሬ ያስገኛል። የ7% ቅናሽ መሰረታዊ ችግሮች ካልተፈቱ ለኢንዱስትሪው ሰፋ ያለ አንድምታ ሊኖረው እንደሚችል የሚያሳስብ አዝማሚያ እንደሚያሳይ ተጠቁሟል።

መረጃዎች እንደሚጠቁሙት ከጥር 13 እስከ የካቲት 6 ቀን 2016 ዓ.ም. ድረስ ባለው ጊዜ ውስጥ ኢትዮጵያ ከ4,500 ቶን በላይ አበባዎችን ለዓለም አቀፋዊ ገበያዎች የላከች ሲሆን የእነዚህ ጭነት ዋና መዳረሻዎች አውሮፓ፣ እንግሊዝ፣ አሜሪካ፣ መካከለኛው ምሥራቅ እና ሩቅ ምሥራቅን እንደሚያካትቱ ይታወቃል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

16 Feb, 13:14


ዳንጎቴ ግሩፕ በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንቱን ከሲሚንቶ አልፎ ወደ ስኳር ምርት ላይ አመራ!

በቅርቡ በአፍሪካ ውስጥ ካሉት ትላልቅ የኢንዱስትሪ ፕሮጀክቶች አንዱ የሆነውን ግዙፉን የዳንጎቴ ማጣሪያ ፋብሪካን ካስጀመረ በኋላ፣ ዳንጎቴ ግሩፕ በኢትዮጵያ ያለውን የኢንቨስትመንት አይነቱን በከፍተኛ ደረጃ እያሰፋ መሆኑን አስታውቋል።

የግሪፑ ለቀመንበርና ስራ አስፈፃሚ አሊኮ ዳንጎቴ የአገሪቱ እየተሻሻለ የመጣውን የኢንቨስትመንት ምቹ ሁኔታ እና በቅርቡ ከጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ጋር ያደረጓቸውን ውጤታማ ውይይቶች ተከትሎ በአዳዲስ ፕሮጀክቶች ላይ ለመሳተፍ ማቀዱን ገልጿል።

በናይጄሪያ የ 60,000 ሄክታር ስኳር እርሻ በማልማት ያገኘውን ልምድ በመጠቀም ኩባንያው በኦሞ ኩራዝ ስኳር ኩባንያ ውስጥ ኢንቨስት እንደሚያደርግ ጠቁሟል።

ወደፊትም ዳንጎቴ ግሩፕ የአገሪቱ የተፈጥሮ ጋዝ ክምችት ልማት ላይ በመመስረት የእርሻ ምርታማነትን ለማሳደግ ያለመ የማዳበሪያ ማምረቻ ፋብሪካ በኢትዮጵያ ለመመስረት እንቅድ እንዳለው ካፒታል ሰምታለች።

Via Capital

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

15 Feb, 16:47


የጅቡቲ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር መሃሙድ የሱፍ አዲሱ የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር ሆነው ተመረጡ

የ59 ዓመቱ ዲፕሎማት ለሚቀጥሉት አራት ዓመታት ኮሚሽኑን እንዲመሩ የተመረጡት ዛሬ በአዲስ አበባ መካሔድ በጀመረው የአፍሪካ ኅብረት ዓመታዊ የመሪዎች  ጉባኤ ላይ ነው።

የሱፍ የተመረጡት የኬንያውን የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ራይላ ኦዲንጋ እንዲሁም የማዳጋስካሩን ሪቻርድ ራንድሪያማንድራቶን በማሸነፍ ነዉ።

55 አባል አገራት ያሉትን ህብረቱን እኤአ ከ 2017 ጀምሮ በሊቀመንበርነት ሲመሩ የነበሩትን ሙሳ ፋኪን በመተካት ያገለግላሉ።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

15 Feb, 13:17


የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር # ''ጥቅማ ጥቅሞች'' !!

👉 የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን መቀመጫው የኅብረቱ ጽህፈት ቤት ሲሆን፣ የኅብረቱን የዕለት ተዕለት ሥራዎችን ይመራል ይቆጣጠራል።
👉 የአህጉራዊው ድርጅት ሊቀመንበር ኃላፈነቱን ከተረከበበት ጊዜ አንስቶ የአፍሪካ ኅብረት ዋነኛው ዲፕሎማት በመሆን በአባል አገራት፣ በዓለም አገራት እንዲሁም በዓለም አቀፍ እና አህጉራዊ ተቋማት የተለያ ተሰሚነት እና ቦታን ያገኛል።

👉 ኅብረቱ ኮሚሽን ሊቀመንበር መቀመጫው አዲስ አበባ ሲሆን፣ በኃላፊነቱ ከሚያገኘው ስም እና ዝና ባሻገር ለሚያከናውነው ተግባር ለእራሱ እና ለቤተሰቦቹ የተለያዩ ጥቅማጥቅሞችን ከኅብረቱ ያገኛል።

👉 የኅብረቱ ሊቀመንበር በወር ከ15 ሺህ 500 የአሜሪካ ዶላር በላይ ደሞዝ የሚያገኝ ሲሆን፣ ልጅ ካለ በእያንዳንዱ ልጅ ስም የ250 ዶላር ድጎማ፣ በተጨማሪ ለቤት ኪራይ፣ ለመብራት እና ለውሃ የሚውል በየወሩ 6000 ዶላር ተመድቦለታል።

👉 እንዲሁም የኅብረቱ ሊቀመንበር ልጆች በአፍሪካ ውስጥ ትምህርታቸውን የሚከታተሉ ከሆነ የትምህርት ወጪያቸው ሙሉ ለሙሉ ይሸፈንላቸዋል። ከአውሮፓ እና ከሰሜን አሜሪካ ውጪ ትምህርታቸውን የሚከታተሉ ከሆነ ሙሉ በሙሉ ወጪያቸው እንደሚሸፈን የኅብረቱ መተዳደሪያ ደንብ ያሳያል።

👉 የሊቀመንበሩ ልጆች በአውሮፓው ወይም በሰሜን አሜሪካ የሚማሩ ከሆነ ለእያንዳንዳቸው የትምህርት ወጪያቸውን የሚሸፍን 15 ሺህ ዶላር ክፍያ በዓመት ያገኛሉ። በተጨማሪም ከአህጉሪቱ ውጪ ለሚኖሩት ልጆች ለቤት ኪራይ ስድስት ሺህ ብር ድጎማ እንዳላቸው የቢቢሲ መረጃ ያሳያል ።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

15 Feb, 10:06


የአንጎላ ፕሬዚዳንት ዣዎ ማኑኤል ጎንሳልቬስ ሎሬንሶ የ2025 የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበርነትን ተረክበዋል።

38ኛው የአፍሪካ ህብረት ጉባኤ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

15 Feb, 07:35


በአቃቂ ቃሊቲ ቤቶችን በማኅበር የተቀበሉ ነዋሪዎች ከሕግ አግባብ ውጭ ታግደናል ሲሉ ቅሬታቸውን አቀረቡ!

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ በሕጋዊ መንገድ በማኅበር ተደራጅተው የመሬት ባለንብረት መሆን የቻሉ ማኅበራት ከ4 ዓመታት ወዲህ በክፍለ ከተማውና በከተማ አስተዳደሩ 'የኦዲት ግኝት ችግር ያሉባቸው ማኅበራት አሉ' በማለት፤ ማንኛውንም አይነት እንቅስቃሴ ማድረግ እንዳይችሉ ያለአግባብ መታገዳቸውን ለአሐዱ ባቀረቡት ቅሬታ ገልጸዋል።

ቅሬታ አቅራቢዎቹ 1997 ዓ.ም ሕጋዊ አሠራሩን በጠበቀ መልኩ በመደራጀት የቤት ባለንብረት መሆን መቻላቸውን ጠቁመው፤ አንድ ማኅበር ውስጥ 12 አባወራ አባላት መኖራቸውን ተናግረዋል።ሁሉም አባላት 94 ካሬ መሬት ይዞታ እንዳላቸውና ሕጋዊ ሰነድ ያሟሉ መሆናቸውን የገለጹም ሲሆን፤ "ነገር ግን በወቅቱ የተለያዩ ግርግሮች በመፈጠራቸው ምክንያት ይህንን አጋጣሚ ተገን በማድረግ 'በሕገወጥ መንገድ ባለንብረት የሆኑ ግለሰቦች አሉ' ተብሎ እግዱ ተጥሎብናል" ብለዋል።

አክለውም ለጉዳያቸው መፍትሔ ፍለጋ ወደሚመለከታቸው ተቋማት ቢሄዱም፤ መፍትሔ ማግኘት እንዳልቻሉ ጠቁመዋል።በዚህም "ቤቶችን መሸጥ መለወጥ እንዳችል እንዲሁም ግብር እንዳንከፍል አሳማኝ ባልሆነ ምክንያት ታግደናል" ብለዋል።ለተጠቀሱት ችግሮች ባለፉት 4 ዓመታት እልባት እንዳልተሰጣቸው የገለጹት ቅሬታ አቅራቢዎቹ፤ በዚህም ምክንያት ለአላስፈላጊ ወጪ እና ለእንግልት መዳረጋቸውን አብራርተዋል።

አሐዱ የቅሬታ አቅራቢዎችን አቤቱታ በማድመጥ ምላሽ ለማግኘት በጉዳዩ ዙሪያ የከተማ አስተዳዳሩን አነጋግሯል።የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኮምኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ እናትአለም መለሰ በሰሰጡት ምላሽ ከተማ አስተዳደሩ ከክፍለ ከተማ የሚመጡ ችግሮችን እልባት በመስጠት መልሶ ወደ ክፍለ ከተማ እንደሚልክ አንስተው፤ ጉዳዩን በዋናነት ክፍለ ከተማውን እንደሚመለከት ገልጸዋል፡፡

አሐዱም የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ዓለማየሁ ሚጀናን አነጋግሯል። ሥራ አስኪያጁም በምላሻቸው ማህበራቱ እንደታገዱ አምነው፤ የኦዲት ችግር ያለባቸው በመኖራቸው የማጣራት ሥራው ብዙ ጊዜ እንደሚፈጅ ተናግረዋል።

አያይዘውም በሕገ-ወጥ መንገድ ሕጋዊነት ያላቸው የሚመስሉ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫዎች የሚሰጡ ግለሰቦች በመኖራቸው ምክንያት የማጣራት ሥራው  አጽንኦት ተሰጥቶት እየተሰራበት መሆኑን አብራርተዋል፡፡አክለውም ከ900 በላይ ማህበራት በመኖራቸው ምክንያት የማጣራት ጊዜው መጓተቱን አስረድተው፤ "ምላሹን በቅርቡ ለመስጠት እየተሠራ ይገኛል" ሲሉ ገልጸዋል።

ቅሬታ አቅራቢዎች እንደገለጹት በተለያዩ ጊዜያት ወደ ከተማ አስተዳደሩ እና ክፍለ ከተማ በሚሄዱበት ወቅት የሚሰጣቸው ምላሽ በቅርብ ጊዜያት ውስጥ ለችግሩ እልባት እንደሚሰጥ ነው።ነገር ግን ላለፉት 4 ዓመታት ምላሻ እንዳላገኙ አሳስበዋል።የአዲስ አበባ ነዋሪዎች በተለያዩ ጊዜያት ከመሬት ይዞታ ጋር በተያያዘ በተደጋጋሚ አቤቱታዎችን ሲያሰሙ ይደመጣል።

Via Ahadu

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

15 Feb, 07:34


በሰሜን ጎጃም ጎንጂ ቆለላ ወረዳ 13 መምህራን በታጣቂዎች ታግተው መወሰዳቸውን ቤተሰቦች ተናገሩ!

በሰሜን ጎጃም ዞን ጎንጂ ቆለላ ወረዳ የኮሬ አንደኛ ደረጃ ትምሕርት ቤት 13 መምህራን ፋኖ ታጣቂዎች ናቸው ባሏቸው ታጣቂዎች ታግተው መወሰዳቸውን ቤተሰቦቻቸው ገለጹ።

ለደኅንነታቸው በመስጋት ስማቸውን በይፋ እንዳንጠቅስ የጠየቁን የታጋች ቤተሰቦች ለአሜሪካ ድምፅ እንደተናገሩት፣ በአካባቢው ትምህርት ከተከፈተ አንድ ወር እንዳለፈው ገልጸው ባለፈው ዕረቡ የካቲት 5 ቀን 2017 ዓ.ም ወደ ትምህርት ቤቱ የሄዱ መምሕራንን ታጣቂዎቹ አግተው ወደ በርሃ ይዘዋቸው እንደሄዱ መስማታቸውን ተናግረዋል።

ታጣቂዎቹ ከዚህ በፊትም ወደ ትምህርት ቤት የሚሄዱ መምህራንን ሥራ እንዳይጀምሩ ማስጠንቀቃቸውን እና ሥራ ለመጀመር ተንቀሳቅሰዋል የተባሉ መምሕራንን በማገት እስከ 50 ሺሕ ብር አስከፍለው እንደሚለቁ ተናግረዋል።በአሁኑ ሰዓት ወረዳው በመንግሥት ቁጥጥር ስር መሆኑን የሚናገሩት የአካባቢው ነዋሪዎች፣ የአካባቢው ባለሥልጣናት “መምህራኑን ሥራ ጀምሩ ጥበቃ ይደረግላችኋል” ብለዋቸው እንደነበርም አክለዋል።

የኮሬ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር አቶ ተረፈ አበጀ በስልክ አግኝተናቸው መምህራኑ መታገታቸውን አምነው ዝርዝር መረጃ ከመስጠት ግን ተቆጥበዋል።ለጎንጂ ቆለላ ወረዳ አስተዳዳሪ ለአቶ ጌታቸው ደገፋው ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ያደረግነው ጥረት ለጊዜው አልተሳካም። በአካባቢው ይንቀሳቀሳሉ ከተባሉ የፋኖ ታጣቂዎች ምላሽ ለማግኘትም ያደረግነው ጥረት አልተሳካም።

Via VoA

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

13 Feb, 15:18


ሰበር ዜና‼️

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ህወሓትን ለሶስት ወራት ከፖለቲካዊ እንቅስቃሴ አገደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፤ ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ለሶስት ወራት “በምንም አይነት” ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ እንዳይሳተፍ አገደ።

በዚህ ጊዜ ውስጥ ህወሓት ጠቅላላ ጉባኤ ለማካሄድ የሚያስችል “የእርምት እርምጃ” ካልወሰደ የፓርቲው ምዘገባ በቀጥታ እንደሚሰረዝ ቦርዱ አስታውቋል።

ብሔራዊው ምርጫ ቦርድ ይህን ያስታወቀው፤ ህወሓትን በተመለከተ ዛሬ ሐሙስ የካቲት 6፤ 2017 ባወጣው መግለጫ ነው። ቦርዱ ለህወሓት ህጋዊ ሰውነት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት “በልዩ ሁኔታ” መስጠቱን የገለጸው፤ በነሐሴ 2016 ዓ.ም. መጀመሪያ ላይ ነበር።

ይህ እርምጃ በጥር 2013 ዓ.ም. በምርጫ ቦርድ አማካኝነት ከፓርቲነት የተሰረዘው ህወሓትን፤ ወደ “ህጋዊ ሰውነት” የመለሰ እንደሆነ በወቅቱ ተገልጾ ነበር። ቦርዱ ህወሓትን ከፓርቲነት ሰርዞ የነበረው፤ “ኃይልን መሠረት ባደረገ የአመጻ ተግባር ላይ መሳተፉን” እንዳረጋገጠ በመጥቀስ ነበር።

ለህወሓት ህጋዊ ሰውነት ማጣት በምክንያትነት ተጠቅሶ የነበረው የሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት፤ በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ በተካሄደ የግጭት ማቆም ስምምነት በጥቅምት 2015 ዓ.ም. መቋጨቱ ይታወሳል። ስምምነቱን ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር የተፈራረመው ህወሓት፤ ህጋዊ ሰውነቱ እንዲመለስ ለቦርዱ ያቀረበው ጥያቄ “በህግ የተደገፈ አይደለም” በሚል ውድቅ ተደርጎ ነበር።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

12 Feb, 05:44


በአየር መንገድ ግቢ ውስጥ ከአመራሮች እውቅና ውጪ ተነሳ የተባለው ፎቶ በእውቅና መደረጉን የሚያሳይ ደብዳቤ ወጣ

ከቀናት በፊት ሲያነጋግር የነበረው የአየር መንገድ ግቢ ውስጥ የተነሳው ፎቶ እንደተባለው "ከተቋሙ አመራሮች እውቅና ውጪ" ሳይሆን በእውቅና መደረጉን የሚያሳይ ደብዳቤ ለመሠረት ሚድያ ደርሷል።

የአየር መንገዱ የአዲስ አበባ ሽያጭ ክፍል ዳይሬክተር አቶ ግሩም አበበ ለሲቪል አቪዬሽን ደህንነት ዋና መምሪያ ዳይሬክተር ታህሳስ 25/2017 ዓ/ም በፃፉት ደብዳቤ አርቲስት ምህረት ታደሰ በአየር መንገድ የአየር ክልል ውስጥ የፎቶ ፕሮግራም እንድታደርግ መጠየቋን ያሳያል።

ደብዳቤው አክሎም የፎቶ ፕሮግራሙ ለአየር መንገዱ ማስታወቂያነት ስለሚጠቅም ታህሳስ 27/2017 ዓ/ም ቅጥር ግቢ ውስጥ ገብተው ፎቶ እንዲነሱ ይጠይቃል።

የፎቶ ፕሮግራሙ በዚህ ሁኔታ በተቋሙ እውቅና ቢካሄድም ተቋሙ ከትናንት በስቲያ በፌስቡክ ገፁ "የግለሰቧ የአየር መንገድ ግቢ ውስጥ የልደት ምስል ቀረጻ ከተቋሙ አመራሮች እውቅና ውጭ የተደረገ ነው" ማለቱ ግርታን ፈጥሯል።

በተጨማሪም የፎቶ ፕሮርግራሙ የግል የልደት ፕሮግራም መሆኑን አርቲስቷ በሶሻል ሚድያ ገጿ ላይ የገለፀች ቢሆንም ይህ በምን መልኩ ለአየር መንገዱ በማስታወቂያነት እንደሚጠቅም ግልፅ አልሆነም።

ተቋሙ ለፎቶ ፕሮግራሙ ከአርቲስቷ ገንዘብ አለመቀበሉን እና ምንም አይነት ውል እንደሌለው በመግለጫው ላይ ገልፆ ነበር።

በርካታ የማህበራዊ ሚድያ ተጠቃሚዎች ድርጊቱን ከአየር የበረራ ክልል ደህንነት ጋር በማንሳት ጥያቄ ሲያቀርቡ ሌሎች ደግሞ በምን መስፈርት አንድ ግለሰብ የግል ልደት ከፍ ያለ ደህንነት በሚያስፈልገው አውሮፕላን ላይ ዲኮር በመስራት ተከበረ የሚል ጥያቄ አንስተዋል፣ በሌላ በኩል ደግሞ ክስተቱ ለአየር መንገዱ ጥሩ ማስታወቂያነት ውሏል ብለው ሀሳብ የሰጡም አልጠፉም።

መሰረት ሚዲያ

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

11 Feb, 20:04


አሜሪካ ውስጥ በመወለድ ዜግነት ከሚያሰጠው ሕግ ጋራ በተያያዘ ትረምፕ የፈረሙት ፕሬዝደንታዊ ትዕዛዝ በሦስተኛ ዳኛ ታገደ

አሜሪካ ውስጥ በመወለድ ዜግነት የሚያሰጠው ሕግ፣ ያለ ሕጋዊ ፈቃድ ወደ ዩናይትድ ስቴትስ በገቡ ሰዎች ለተወለዱ ልጆች ተፈጻሚ እንዳይሆን የሚያደርገውን ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ የፈረሙትን ፕሬዝዳንታዊ ትዕዛዝ በማገድ የኒው ሃምፕሸር ክፍለ ግዛቱ የፌዴራል ዳኛ ጆሴፍ ኤን ላፕላንት በትላንትናው ዕለት በሰጡት ብይን ሦስተኛው ዳኛ ሆኑ።

በዩናይትድ ስቴትስ የሲቪል መብት ማሕበራት ባቀረቧቸው ክሶች፤ ትረምፕ የፈረሙትን ፕሬዝዳንታዊ ትዕዛዝ ሕገ መንግስቱን የሚጥስ እና "ከዋነኞቹ የአሜሪካ ሕገ-መንግሥታዊ እሴቶች ውስጥ አንዱን ለመለወጥ የተደረገ ሙከራ ነው” ሲሉ ተከራክረዋል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

11 Feb, 19:21


የአፍሪካ ህብረት ስብሰባ መቃረቡን ተከትሎ አገልግሎት ላይ እንዳይውል በታገደ መርዝ በርካታ ሺህ ውሻዎች አዲስ አበባ ውስጥ እየተገደሉ መሆኑ ታወቀ

- መርዙ ወንዝ ዳር የሚበቅል ምግብ ሊበክል እንደሚችል ተሰግቷል

በአለም ጤና ድርጅት አገልግሎት ላይ እንዳይውል በታገደ መርዝ በርካታ ሺህ ውሻዎች አዲስ አበባ ውስጥ እየተገደሉ መሆኑን ከተለያዩ ቦታዎች የሚደርሱን ጥቆማዎች ያሳያሉ።

በኮሪደር ልማት ምክንያት እንደ ፒያሳ እና ካዛንችስ ያሉ ቦታዎች መፍረሳቸውን ተከትሎ መንገድ ላይ የቀሩ በርካታ ውሻዎች መኖራቸው ይታወቃል።

ይሁንና ቀጣዩን የአፍሪካ ህብረት ስብሰባ ለመሳተፍ የሚመጡ እንግዶች "ጎዳና ላይ እንዳያዩዋቸው" በሚል ከዚህ በፊት ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ በርካታ ሺህ ውሻዎች በመርዝ እየተገደሉ እንደሆነ ታውቋል።

ባለፈው ወር የፈረንሳዩ ፕሬዝደንት ኢማኑኤል ማክሮን ሊመጡ ሲልም ሲባልም በተመሳሳይ ብዙ ውሻዎችን በመርዝ መገደላቸው ታውቋል።

"መርዙ በአለም ጤና ድርጅት አገልግሎት ላይ እንዳይውል የታገደ ነው፣ እንዴትስ ወደ ሀገራችን ገባ የሚለው ጉዳይ አጠያያቂ ነው" ያሉት አንድ ጉዳዩን የሚከታተሉ ግለሰብ መርዙ ሰዎች እጅ ቢገባ በአንድ የሻይ ማንኪያ እሩብ በታች ሆነ መጠን ሺህ ህዝብ ሊጨርስ ይችላል ብለዋል።

"መርዙ ሽታ የሌለው በመሆኑ በምግብም ሆነ መጠጥ ውስጥ ሊገባና ሰዎችን ለመጉዳት ሊውል ይችላል። በዚህ መርዝ ያለ ሃጢያታቸው እየተገደሉ ያሉ ውሾች የሚጣሉበት ቦታ ሌላው አውሬ ምግብ ያገኘ መስሎት የሞተውን በድን ሲበላ እንደሚሞት፣ ተያይዞም አሞራዎች በልተውት የተረፋቸውን ወንዝ ላይ ቢጥሉት ውሃው የሚመረዝ መሆኑ ሊታወቅ ይሀገባል" በማለት ስጋታቸውን ገልፀዋል።

አክለውም ውሃው የከተማም ሆነ የገጠር የወንዝ ዳር አትክልት ልማት ላይ ሊውል ስለሚችል ተያያዥነቱ ረጅም በመሆኑ ህዝብ ሁሉ ይህንን ድርጊት እንዲኮንን ተማፅነዋል።

መሠረት ሚዲያ

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

11 Feb, 18:42


አስገዳጅ የባንኮች ውህደት እንደሚኖር ብሄራዊ ባንክ ገለፀ‼️
አስገዳጅ የባንኮች ውህደት እንደሚኖር የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ገዥ ማሞ እስመለአለም ምህረቱ ገለፁ።

እንደ ገዥው ገለፃ የውህደቱ ዋነኛ አላማ ችግር ያለባቸውን ባንኮች ለማዳን ነው ብለዋል።

በቅርቡ የፀደቀው የባንክ ስራ አዋጅ የባንኮችን ውህደት በተመለከተ የገለፀ ሲሆን ዝርዝር የአፈፃፀም መመሪያ እየተጠበቀ ነው።

ብሄርን መሰረት አድርገው ስለተመሰረቱ ባንኮች በውህደት ወቅት ስለ ሚያጋጥም ተግዳሮት የተጠየቁት አቶ ማሞ ውህደትን ጨምሮ አጠቃላይ የባንክ ስራ በህግ እንደሚመራ አስታውሰው፣ "ከዚህ አኳያ ከብሄር ጋር ተያይዞ የሚነሳው ጉዳይ በተለይ በአስገዳጅነት የሚፈፀም ውህደት ላይ የሚኖረው ተፅእኖ አናሳ ነው፣" ብለዋል።
Via:- #ቅዳሜገበያ

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

11 Feb, 18:12


የሱማሊላንድ ፕሬዝደንት ከኢትዮጵያ ጋር የተደረገውን የመግባቢያ ስምምነት ዘንድሮ እንደሚያጠናቅቁ ገለፁ፡፡ ፕሬዝደንቱ አብዲራሂም መሀመድ አብዱላሂ በዱባይ እየተከናወነ ባለው የአለም የአስተዳደር ጉባኤ ላይ ባደረጉት ንግግር አለም አቀፍ እውቅና የማግኘት ህልም እንዳላቸው ጠቅሰው ይህንን ህልማቸውን የአለም መንግስታት እውን እንዲያደርጉላቸው ጥሪ አቅርበዋል፡፡

ሲናገሩም ‹‹እንደአንድ ዲሞክራሲያዊ መንግስት አለም አቀፉ ማህበረሰብ እውቅና ይሰጠናል የሚል እምነት አለን፡፡ በተለይ እንግሊዝና አሜሪካ እውቅናውን እንደሚሰጡን ተስፋ አለን፡፡ ነገር ግን የመጀመሪያውን እውቅና ከአሜሪካ እንደምናገኝ እምነት ጥለናል›› ብለዋል፡፡

የሱማሊላንዱ መሪ በገለፃቸው ስለቀጣናዊ ግንኙነትና ኢኮኖሚያዊ ትብብርም ያነሱ ሲሆን በርበራ ወደብን የማዘመን እቅድ እንዳላቸውም አስረድተዋል፡፡ ኢትዮጵያ በበርበራ ወደብ ትልቅ ገበያ ሆና እንደምትቀጥል ያስታወቁት ፕሬዝደንቱ ባለፈው አመት ከኢትዮጵያ ጋር የተደረገውን የወደብ ኪራይ የመግባቢያ ስምምነት ዘንድሮ የማጠናቀቅ እቅድ መያዛቸውንም አስታውቀዋል፡፡

ባለፈው አመት የተፈፀመው ይህ ስምምነት በኢትዮጵያና በሱማሊያ መካከል ውዝግብ ፈጥሮ የቆየ ሲሆን በቱርክ አሸማጋይነት እርቅ መፈጠሩ መገለፁ ይታወሳል፡፡

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

11 Feb, 18:07


በኦሮሚያ ክልል በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ43 ሰዎች ሕይወት አለፈ።

በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን ውስጥ ከምትገኘው ሻምቡ ወደ አዲስ አበባ 87 ሰዎችን አሳፍሮ ይጓዝ በነበረ የህዝብ ማመላለሻ ላይ ነው አደጋው የደረሰው ።

42 ሰዎች ከባድ ጉዳት የደረሰባቸው ሲሆን 3 ሰዎች ላይ ቀላል ጉዳት አጋጥሟል። የአደጋው ምክንያት መሪ አለመታዘዝና ከመጠን በላይ መጫን መሆኑ ተገልጿል።

የዞኑ የትራፊክ ደህንነት ሃላፊ ኢንስፔክተር አስናቀ መስፍን በአደጋው ሕይወታቸው ያለፉ ሰዎች ቁጥር ሊጨምር እንደሚችልም ተናግረዋል፡፡

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

11 Feb, 14:39


ቢሊየነሩ ኤለን መስክ የአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ እንዲዘጋ ሀሳብ አቀረቡ።

በአዲሱ የመንግሥት ተቋመትን አፈጻጸም የሚገመግመውና በርካታ ውሳኔዎችን እያስተላለፈ የሚገኘው Department of Government Efficiency እያሥተዳደሩ የሚገኙት ኤሎን መስክ የአሜሪካ ድምፅ ሬዲዮ እንዲዘጋ በኤክስ ገጻቸው ሀሳብ አቅርበዋል።

"ማንም ሰው አያዳምጣቸውም ይዘጉ" ይላል ያሰፈሩት ጽሑፍ።

የአሜሪካ ድምፅ የሬዲዮና እና የቴሌቪዥን ሥርጭት መሠረቱን በአገረ አሜሪካ ዋሽንግተን ዲሲ ያደረገና በ47 ዓለም አቀፍ ቋንቋዎች ሥርጭቱን የሚያከናውን ተቋም ነው።

ይኸው ተቋም በአሜሪካ ፌደራል መንግሥት በጀት የሚመደብለት ተቋም ሲሆን ከ278 ሚሊዮን በላይ ሳምንታዊ ተተመልካች እና አድማጮች እንዳሉት ይነገራል። arts tv

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

11 Feb, 14:34


https://www.youtube.com/watch?v=YmHFx2yjVow

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

11 Feb, 06:06


የታክሲ አገልግሎት የሚሰጡ ተሽከርካሪዎች መተላለፊያ በሆኑ መንገዶች ዳር ተሽከርካሪ ማቆም ክልክል ነው፡- የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ

የታክሲ አገልግሎት የሚሰጡ ተሽከርካሪዎች በኮሪደር ልማት በለሙና የእንግዶች መተላለፊያ በሆኑ መንገዶች ላይ ለአጭር ደቂቃም ሆነ ለሰዓት በመንገድ ዳር ማቆም የተከለከለ መሆኑን የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ አስታውቋል፡፡

ከዛሬ ከንጋቱ 12:00 ጀምሮ እስከ የካቲት 09/2017 ዓ.ም ማታ 12:00 ድረስ የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ በኤሌክትሮኒክ ታክሲ ስርዓት(ኤታስ) አገልግሎት የሚሰጡ፣ የሜትር ታክሲ፣ የላዳ፣ የታክሲ እና መሰል ተሽከርካሪዎች ክልከላው የሚመለከታቸው መሆኑን ከቢሮው የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡

ለትራንስፖርት ጉዳዮች መረጃና ጥቆማ 9417 ነፃ የጥሪ መስመር መጠቀም እንደሚቻልም ቢሮው አመልክቷል፡፡

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

11 Feb, 05:46


የፓርላማ አባሉ ደሳለኝ ጫኔ (ፒ ኤች ዲ) ስለልደቱ አያሌው የጉዞ ክልከላ ካሰፈሩት!...

#Ethiopia | አቶ ልደቱን ጨምሮ ሌሎች በውጪ የሚገኙ የመንግስት ተቃዋሚዎችን በቅርቡ በጸደቁ አዋጆች ለመቅጣት በሰፊው ዝግጅት እየተደረገ ይመስለኛል። የመንግስት ተቃዋሚዎችን እና ደጋፊ ያልሆኑ ግለሰቦችን ለማጥቃት ጥቅም ላይ ሊውሉ ይችላሉ ብለን አጥብቀን የተቃወምናቸው ግን በሁለት እና ሦስት ተቃውሞ የፀደቁ አዋጆች ነበሩ፦

1ኛ) የኢሚግሬሽን እና ዜግነት ጉዳዮች አዋጅ፦ በአዋጁ ላይ እንደተመላከተው ወደ ኢትዮጵያ የሚበሩ ማናቸውም አየር መንገዶች የተጓዦችን ስም ዝርዝር ከ3 ቀን በፊት ለኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት የማሳወቅ ግዴታ ጥሎባቸዋል። መንግስት ከዚህ በፊት እንደተለመደው ወደ አገር እንዳይገቡ የተከለከሉ ሰዎችን በአገር ውስጥ ኤርፖርቶች አቆይቶ ወደ መጡበት እንዲመለሱ ከማድረግ ባለፈ ከመነሻቸው ወደ ኢትዮጵያ እንዳይበሩ መከልከልን እንደቀዳሚ ርምጃ እንዲወስድ ስልጣን የሰጠው ነው።

2ኛ) የንብረት ማስመለስ አዋጅ፦ መንግስት ምንጫቸው ያልታወቁ ናቸው ብሎ ያመናቸውን ንብረቶች የመውረስ ስልጣን የሰጠው ሲሆን፣ በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊን እና ትውልደ ኢትዮጵያን በዚህ አዋጅ ከተከሰሱ ደግሞ በጠበቃ ሳይሆን መከራከር የሚችሉት በአካል ቀርበው መሆን እንዳለበት የሚደነግግ ነው።

ስለዚህ አቶ ልደቱ ወደ አገር እንዳይገባ በመጀመሪያው አዋጅ መሠረት ተከልክሏል። ኢትዮጵያዊ ውስጥ ሀብት ንብረት ካለው ደግሞ በሀብት ማስመለስ አዋጁ መሠረት ሀብቱ ይወረሳል ማለት ነው።

በአናቱም በወንጀል የተገኘን ንብረት ህጋዊ አስመስሎ ማቅረብ እና ሽብረተኝነትን በገንዘብ መደገፍ አዋጁ ጋር የተያያዙ በርካታ ተቃዋሚዎችን የመምቻና የማሸማቀቂያ ድንጋጌዎች አሉ።

መንግስት ልደቱን ጨምሮ ሌሎች ተቃዋሚዎችን ለማስፈራሪያ እና ለመቅጫ ምን ያህል አነዚህን አዋጆች ይጠቀማቸዋል ለሚለው ጥያቄ ምላሹን ጊዜ የሚነግረን ይሆናል።

ዜጎች ወደ አገራቸው እንደልብ እንዳይገቡ እና ከአገር እንዳይወጡ በመንግስት የሚደረገው ክልከላ በማንኛውም መመዘኛ ተቀባይነት የሌለው እና ሊወገዝ የሚገባው ተግባር ነው።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

10 Feb, 16:28


ኢትዮዽያ መጓዝ እንደማልችል በአትላንታ የኢትዮዽያ አየር መንገድ ሀላፊ በሆኑት በአቶ ተሾመ ገ/ስላሴ ተነግሮኝ ተመልሻለሁ።

አቶ ልደቱ አያሌው


ወደ ኢትዮዽያ ለመሄድ በኢትዮዽያ አየር መንገድ ትኬት የቆረጥኩት ለዛሬ ስለሆነ ከጧቱ 12 ሰዓት በአትላንታ
ዓለም-አቀፍ አየር ማረፊያ ተገኝቸ ነበር። የአገልግሎት ጊዜው ያላለፈ የኢትዮዽያ ፓስፖርትና የተረጋገጠ የጉዞ ትኬት ይዥ የተገኘሁ ቢሆንም የኢትዮዽያ አየር መንገድ ግን በአሜሪካ የኢትዮዽያ ኤምባሲን አነጋግሬ የተለየ ፈቃድ ካልተሰጠኝ በስተቀር ወደ ኢትዮዽያ መጓዝ እንደማልችል በአትላንታ የኢትዮዽያ አየር መንገድ ሀላፊ በሆኑት በአቶ ተሾመ ገ/ስላሴ ተነግሮኝ ተመልሻለሁ።

በአሸባሪነት ወንጀል ሊከሰኝ እንደሚፈልግና በቁጥጥር ስር እንድውል ከኢንተር-ፖል ጋር ጭምር እየተነጋገረ እንደሆነ ሲገልፅ የነበረው የኢትዮዽያ መንግስት ዛሬ በራሴ ፈቃድ ወደ አገሬ ለመመለስ ስሞክር በእኔ ላይ ህገ-ወጥ ክልከላ ማድረጉ አስገርሞኛል። ምን አልባት እንዲህ አይነቱ ድርጊት በአለም ለመጀመሪያ ጊዜ የተፈፀመ ሊሆን ይችላል። መንግስት እኔን በወንጀለኛነት ከጠረጠረኝ ሊከሰኝና ሊያስረኝ ይችላል እንጅ ወደ አገሬ እንዳልገባ ሊከለክለኝ አይችልም።

አንድን ኢትዮዽያዊ የሆነና የኢትዮዽያ ፓስፖርት የያዘን ዜጋ ወደ አገሩ እንዳይገባ ለመከልከል የሚያስችል ምንም ዓይነት የህግ ማዕቀፍ የለም። ስለሆነም በሌላ አገር አየር መንገድ ትኬት ቆርጨ ሰሞኑን ወደ አገሬ ተመልሸ እንደምሄድ በዚህ አጋጣሚ አሳውቃለሁ።

ከአክብሮት ጋር
ልደቱ አያሌው

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

10 Feb, 15:08


38ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ እና 46ኛው የስራ አስፈፃሚ ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ በሰላም እንዲጠናቀቅ የፀጥታና ደኅንነት ጥምር ኃይል በቂ ዝግጅት አድርጎ ወደ ሥራ መግባቱን አስታውቋል።

የፀጥታና ደኅንነት ጥምር ኃይል እስከ አሁን ድረስ በአዲስ አበባና በሀገር ዓቀፍ ደረጃ የተከናወኑ የፀጥታ ስራዎች ስኬታማ መሆናቸውን ገምግሞ 38ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ እና 46ኛው የስራ አስፈፃሚ ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ በሰላም እንዲጠናቀቅ አዳዲስ ሎጅስቲክ አቅሞችን በመጠቀም ፤ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የፀጥታ ኃይል በማሰማራት በቴክኖሎጂ የታገዘ የፀጥታና የደኅንነት ሥራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ገልጿል።

በተከታታይ እየተካሄደ ያለው የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ፤ ብሔራዊ መረጃ እና ደህንነት አገልግሎት፣ የሪፐብሊካን ጋርድ፣ የአዲስ አበባ ፖሊስ እና ሌሎች አጋር የፀጥታ አካላት የተቀናጀ ኦፕሬሽን አዲስ አበባ ከተማ ፍፁም ሰላማዊ ሆና እንድትቀጥል ያስቻለና አሁን ላይ የከተማዋ ሰላም በአስተማማኝ ሁኔታ መቀጠሉን በግምገማው ያረጋገጠ መሆኑን ያመላከተው የፀጥታና ደኅንነት ጥምር ኃይል ባካሄደው ግምገማ ለተገኘው ሰላም እና በተካሄደው ኦፕሬሽን ለተገኘው ውጤት የህዝቡ ተሳትፎ ከፍተኛ ነበረ ብሏል።

አዲስ አበባ ከተማ የአፍሪካ ሕብረት እና የተለያዩ የዓለም አቀፍ ተቋማት መቀመጫ በመሆኗ ፀጥታዋ ፍጹም ሰላማዊ ሆኖ እንዲቀጥልም ከመቼውም ጊዜ በላይ ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት እየሰራ እንደሚገኝ በግምግማው ተነስቷል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ እንደ ሀገር ሁሉም የፀጥታ መዋቅር የሚመለከተውን የሥራ ድርሻ ወስዶ አካባቢውን ፍፁም ሰላማዊ ለማድረግ በኃላፊነትና በተጠያቂነት የድርሻውን እየተወጣ እንደሚገኝ የፀጥታና ደኅንነት ጥምር ኃይሉ ጨምሮ ገልጿል።

በጉባኤው ላይ የሚታደሙ እንግዶችን በኢትዮጵያዊ ወግና ባህል በመቀበል እና በማስተናገድ በቆይታቸዉ ጊዜ በተለያዩ አካባቢዎች ሲንቀሳቀሱ፤ ካረፉባቸው ሆቴሎች ወደ መሰብሰቢያ አዳራሽ በሚሄዱበት ወቅት ሰላም ወዳዱ ሕዝባችን በባለቤትነት የሚጠበቅበትን የዜግነት ድርሻውን በኃላፊነት እንዲወጣና ለፀጥታ አካላት እያደረገ ያለውን ቀና ትብብርም አጠናክሮ እንዲቀጥል የፀጥታና ደኅንነት ጥምር ኃይል ጥሪ አቅርቧል።
(ኤፍ ኤም ሲ)

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

10 Feb, 15:08


የግለሰቧ የአየር መንገድ ግቢ ውስጥ የልደት ምስል ቀረጻ ከተቋሙ እውቅና ውጭ የተደረገ ነው - አየር መንገዱ

ከሰሞኑ በማህበራዊ ትስስር ገጾች ሲዘዋወር የነበረው የአንዲት ግለሰብ የአየር መንገድ ግቢ ውስጥ የልደት ምስል ቀረጻ ከተቋሙ እውቅና ውጭ የተደረገ መሆኑን የኢትዮጵያ አየር መንገድ አስታወቀ፡፡

አየር መንገዱ ባወጣው መግለጫ አንዲት ግለሰብ በአውሮፕላኑ መወጣጫ ደረጃ  ላይ የተለያዩ ዲኮሮችን በማድረግ የተነሳችው ፎቶ ሲዘዋወር መታየቱን ገልጿል፡፡

ግለሰቧ የተነሳችው ለጥገና በቆመ አውሮፕላን ላይ መሆኑን የጠቆመው አየር መንገዱ÷ድርጊቱ ከተቋሙ እውቅና ውጭ የተደረገ መሆኑን አስታውቋል፡፡

አየር መንገዱ የሙያ አገልግሎት ሥነ-ምግባርን በመጠበቅ ደረጃውን የሚመጥን አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝ  አጽንኦት ሰጥቷል፡፡

ይሁን እንጂ ከጉዳዩ ጋር ተያይዞ ተቋሙ ከሙያዊ ሥነ ምግባር ውጪ ገንዘብ በመቀበል ለግለሰቧ ፈቃድ እንደሰጠ በማስመሰል በተሰራጨው መረጃ ማዘኑን አንስቷል፡፡

ጉዳዩን በተመለከተ ምርመራ እያደረገ መሆኑን የገለጸው አየር መንገዱ÷ ድርጊቱን በፈፀሙ አካላት ላይ አስተዳደራዊ ርምጃ እንደሚወስድ አረጋግጧል፡፡

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

10 Feb, 14:22


የትግራይ ምሁራን ‹‹ከአርባ ፐርሰንት በላይ የትግራይ መሬት በውጭ ሀይሎች በህገ ወጥ መንገድ ተወሯል›› ሲሉ ለትራምፕ ደብዳቤ አስገቡ

የትግራይ አለም አቀፍ የምሁራንና ፕሮፌሽናሎች ሶሳይቲ (ጂ ኤስቲ ኤስ) ለአሜሪካ ፕሬዝደንትና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደብዳቤ ፃፈ፡፡

ሶሳይቲው በፃፈው በዚህ ደብዳቤ ዶናልድ ትራምፕ አርባ ሰባተኛው የአሜሪካ ፕሬዝደንት በመሆናቸው የተሰማውን ደስታ በመግለፅ ጀምሮ በአመራርነት ዘመናቸው የአለም ማህበረሰብን መረጋጋትና ፍትህ ለማረጋገጥ እንደሚሰሩ ተስፋ እንዳለው ጠቅሷል፡፡

ሲቀጥልም በናይሮቢና በፕሪቶሪያ በኢትዮጵያ መንግስትና በትግራይ ክልል በሚገኙ ባለስልጣናት መካከል የግጭት ማቆም ስምምነት መደረጉን አንስቶ ለዚህ ስምምነት ትኩረት እንዲሰጡት አሳስቧል፡፡ የፕሪቶሪያው ስምምት መፈረሙ አውዳሚ የሆነውን ጦርነት ማስቆሙን የጠቀሰው ደብዳቤው ስምምነቱ ሙሉ በሙሉ ተፈፃሚ ቢሆን በትግራይ ያለውን ቀውስ ከመፍታት ባለፈ በኢትዮጵያ ሰላምና መረጋጋትን እንዲሁም በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ ፀጥታን ለማረጋገጥ እንደሚረዳም አስረድቷል፡፡

ስምምነቱ ጦርነቱን ማስቆም ቢችልም በስምምነቱ ላይ የሰፈሩት የህገ መንግስታዊ ግዴታዎች መከበር፣ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋትን ማስፈንና በዘር ማጥፋት ጦርነቱ የተጎዱ ህዝቦችን ማዳን እንዳልተቻለ የጠቀሰው ደብዳቤው በሚሊዮን የሚቆጠሩ ተፈናቃዮች በስቃይ ላይ እንደሚገኙም ገልጿል፡፡

ደብዳቤው ሲቀጥልም ‹‹ከትግራይ መሬት ውስጥ ከአርባ ፐርሰንት በላዩ የኤርትራ ወታደሮችንና የአማራ ሀይሎችን ጨምሮ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት አባል ባልሆኑ አካላት በህገ ወጥ መንገድ ተወሮ ይገኛል›› ያለ ሲሆን ይህም ከፕሪቶሪያው ስምምነትና ከኢትዮጵያ ህገ መንግስት ጋር የሚቃረን መሆኑን አስረድቷል፡፡ ፕሬዝደንት ትራምፕ ለትግራይ፣ ለኢትዮጵያና ለአፍሪካ ቀንድ ትኩረት እንዲሰጡ ጥሪ ያቀረበው ይህ ደብዳቤ በዚህ ረገድ ዲፕሎማሲያዊ ጫና ሊደረግባቸው የሚገቡ በሚል አራት ነጥቦችን አስቀምጧል፡፡

አንደኛው ነጥብ ከመከላከያ ሰራዊት ውጭ የሆኑ ሀይሎች በሙሉ ያለምንም ቅድመ ሁኔታና በፍጥነት ከትግራይ ክልል ለቀው እንዲወጡና የትግራይ ወሰን ከጦርነቱ በፊት ወደነበረው እንዲመለስ የሚል ነው፡፡

በሁለተኝነት በሚሊዮን የሚቆጠሩ ተፈናቃዮችና ስደተኞች ወደነበሩበት እንዲመለሱና እንዲቋቋሙ እንዲሁም ንብረታቸው እንዲመለለስ መደረግ እንዳለበትና በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ስር የሚገኙ የትግራይ የፀጥታ ሀይሎች የደህንነት ጥበቃ እንዲያደርጉላቸው የሚጠይቅ ሲሆን ይህ እንዲሆን አስፈላጊው ዲፕሎማሲያው ጫና እንዲከናወን ጥሪ አቅርቧል፡፡

በሶስተኝነት የአፍሪካ ቀንድን በማተራመስ ላይ በሚገኙ ሀይሎች ላይ ጠበቅ ላይ እርምጃ እንዲወሰድ የጠየቀው ደብዳቤው በዚህ በኩል የኤርትራ መንግስትንና አሸባሪው አልሸባብን ጠቅሷል፡፡

በአራተኝነት ደግሞ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ተልእኮውን እንዲወጣ የትራምፕ መንግስት አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርግም አሳስቧል፡፡

ዘሃበሻ

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

10 Feb, 07:04


የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ከሠራተኞቻቸው ደመወዝ ላይ የፓርቲ መዋጮ እንዳይሰበሰቡ የሚከለክል ረቂቅ አዋጅ በምርጫ ቦርድ ተዘጋጀ፡፡

ይኸው አዲስ ረቂቅ አዋጅ የመንግሥት ተቋማት ከሠራተኞቻቸው ደመወዝ ላይ "በቀጥታ" የፓርቲ መዋጮ እየሰበሰቡ እንዳያስገቡ ይከለክላል ነው የተባለው፡፡

"የኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና የምርጫ ሥነ ምግባር አዋጅ ማሻሻያ ረቂቅ" የተባለው እና ካለፈው ጥር ወር ጀምሮ ውይይት ሲደረግበት የቆየው ይኸው ረቂቅ አዋጅ በተጨማሪም በሁሉም አካባቢዎች በተመሳሳይ ጊዜ ጠቅላላ ምርጫ ማካሄድ በማይቻልበት ጊዜ ምርጫው "በተለያየ ጊዜ" ሊካሄድ እንደሚችልም ይደነግጋል ተብሏል፡፡

Arts tv

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

09 Feb, 20:00


ቤንዝል አንድ ሊትር 500 ብር እየሸጡ የነበሩ ግለሰቦች በአርባምንጭ ከተማ በቁጥጥር ስር ዋሉ።

በአርባምንጭ ከተማ ቤንዚል በመደበቅና በህገወጥ ንግድ ስራ የተሰማሩ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የአርባምንጭ ፖሊስ አስታወቀ።

እነዚህ ደላሎች ከጥቂት የዞኑን እና የከተማ አመራር ጋር በመመሳጠር በህዝብ ዕንባ ላይ ሀብት ሲያካብቱ የነበሩ እንደሆኑ የተረጋገጠ ሲሆን ደላሎቹ በቁጥጥር ስር የዋሉ ቢሆንም ከእነዚህ ቡድኖች ጋር ሲተባበሩ የነበሩ ባለስልጣናትን በተመለከተ ምርመራ እየተካሄ እንደሆነ እና ባለስልጣናቱ ላይ ከህግ ተጠያቂነት በተጨማሪ ፖለቲካዊ እርምጃም ሊወሰድ መሆኑን ተገልፆል።

እነዚህ ደላሎች እና ባለስልጣናት በአርባምንጭ ከተማ ህዝቡ በቤንዚል እጥረት እየተሰቃየ 1 ሊትር ቤንዚል በኮንትሮባንድ ከ450-500 ብር እንዲሸጥ እያደረጉ እና በቀን እስከ 40,000 ሊትር በኮንትሮባንድ ሲሸጡ የተያዙ ናቸው ብሏል የአርባምንጭ ፖሊስ።

ከዚህም በተጨማሪ ከፍተኛ መጠን ባለው የኮንትሮባንድ ስራ ተሰማርተው እየሰሩ እንደነበርና በሰነድ ማጭበርበር ስር ይሰሩ እንደነበር ተገልፆል

የደቡብ ክልል መንግስት እና የብሔራዊ ደህንነት ተቋሙ በቅንጅት ይህን ኦፕሬሽን በመስራት ተጠርጣሪዎቹን እጅ ከፍንጅ በቁጥጥር ስር እንዳዋሉት ለማወቅ ተችሏል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

08 Feb, 18:26


አትሌት ፅጌ ድጉማ በ800 ሜትር የአለም የቤት ውስጥ ውድድር አሸነፈች

በፈረንሳይ ሜዝ በተካሄደ የ800 ሜትር የዓለም የቤት ውስጥ ሩጫ ውድድር አትሌት ፅጌ ድጉማ አሸንፋለች፡፡

አትሌቷ ርቀቱን 1 ደቂቃ ከ58 ሰከንድ ከ97 ማይክሮ ሰከንድ በመጨረስ በቀዳሚነት ማጠናቀቋን የዓለም አትሌቲክስ መረጃ ያመላክታል፡፡

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

08 Feb, 18:25


የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር፣ በክልሉ የሚካሄዱ ወርቅና መዳብን ጨምሮ ማናቸውም የማዕድን ቁፋሮ ሥራዎች ከየካቲት 1 ጀምሮ ሙሉ በሙሉ እንዲቆሙ ውሳኔ ማሳለፉን የክልሉ ቴሌቪዥን ዘግቧል።


ጊዜያዊ አስተዳደሩ ይህን መመሪያ ያስተላለፈው፣ የክልሉ የማዕድን ሃብት በሕገወጥ መረቦች አማካኝነት እየተመዘበረ መኾኑን በተደጋጋሚ ሲገልጽ ቆይቷል። ጊዜያዊ አስተዳደሩ፣ በክልሉ የሚካሄደዱ መጠነ ሰፊ ሕገወጥ የማዕድን ቁፋሮዎችን የሚመረምር ግብረ ኃይል ማቋቋሙንም ቀደም ሲል ገልጦ ነበር።

በሕገወጥ የማዕድን ቁፋሮው የታጠቁ ቡድኖች በዋናነት እንደሚሳተፉና በተለይ የወርቅ የኮንትሮባንድ ንግድ መረብ እስከ አዲስ አበባ፣ አሥመራ፣ ካምፓላና ዱባይ ድረስ የተዘረጋ ስለመኾኑ በተደጋጋሚ እንደተዘገበ አይዘነጋም።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

08 Feb, 18:25


#CapitalNews እስከ 30,000 ብር የሚጠይቁት ህገወጥ የፍተሻ ጣቢያዎች ሊዘጉ ነዉ ተባለ

የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር የትራንስፖርት እንቅስቃሴን ለማቀላጠፍና የኢኮኖሚ እድገትን ለማሳደግ በሚደረገው እንቅስቃሴ በመላ አገሪቱ በርካታ ሕገ-ወጥ የፍተሻ ጣቢያዎች እንደሚዘጉ አስታውቋል።

ሚኒስትሩ ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) አንዳንድ ሲሉ የጠሯቸው ቀበሌዎችና ከተሞች ያልተፈቀዱ የፍተሻ ጣቢያዎችን በመክፈት ከ10 እስከ 30,000 ብር የሚደርስ ክፍያ ሲጠይቁ እንደነበር ገልጸዋል።

እነዚህ የፍተሻ ጣቢያዎች ብዙውን ጊዜ በአካባቢዎች መካከል በሚደረግ ፉክክር መንፈስ የሚቆሙ፣ አላስፈላጊና ለኢኮኖሚው ጎጂ እንደሆኑ ተመላክቷል።

ሚኒስትሩ እነዚህ የመንገድ መዝጊያዎች አላስፈላጊ ወጪዎችንና መዘግየቶችን ከማስከተላቸውም በላይ የሀገሪቱን ኢኮኖሚያዊ እድገት እንደሚያደናቅፉ አስረድተዋል።

በሁሉም መንገድ ላይ እውቅና የሌላቸው የፍተሻ ጣቢያዎች መኖራቸውን አምነው የተቀበሉት ሚኒስቴሩ የጉምሩክ ፣ የፀጥታ ፍተሻ ፣ የድንበር (ለገቢ/ወጪ) እና ዋና ዋና የጭነት ተርሚናል የፍተሻ ጣቢያዎች ( ኬላ) ብቻ የተፈቀዱ መሆናቸውን ግልጽ አድርገዋል ።
Capital newspaper

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

08 Feb, 16:51


'ብርጌድ ንሐመዱ' የተሰኘዉ የፕሬዝዳንት ኢሳያስ አገዛዝ ተቃዋሚ ቡድን አዲስአበባ ላይ ቢሮ ሊከፍት ነዉ ተባለ

በውጭ አገራት የተመሠረተው 'ብርጌድ ንሐመዱ' የተሠኘው የኤርትራ ተቃዋሚዎች ስብስብ ኢትዮጵያ ውስጥ በቀጣዮቹ ጥቂት ቀናት ቢሮ ሊከፍት መኾኑን መስማቱን አፍሪካ ኢንተለጀንስ ዘግቧል።

'ብርጌድ ንሐመዱ' ወይም 'የሰማያዊ አብዮት ንቅናቄ' የተሰኘው የለውጥ ፈላጊ ወጣቶች ስብስብ፣ ከአንድ ሳምንት በፊት አዲስ አበባ ውስጥ ስብሰባ ማካሄዱ ይታወሳል።

በዚኹ ስብሰባ ላይ ከተለያዩ የዓለም ክፍሎች የተወከሉ የንቅናቄው አባላት እንደተሳተፉ በወቅቱ ተዘግቦ ነበር።

ንቅናቄው በውጭ አገር የተመሠረተው ከኹለት ዓመት በፊት ሲኾን፣ በተለያዩ የምዕራቡ ዓለም አገራት የኤርትራ ኢምባሲዎችና የመንግሥት ደጋፊዎች ያካሄዷቸውን የባሕል ፌስቲቫሎች በማወክና በማስተጓጎል ይታወቃል።

Via ዋዜማ

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

08 Feb, 16:03


ትራምፕ ያወጡትን የዩኤስኤ.አይ.ዲ ሰራተኞች እረፍት እንዲወጡ የሚያስገድደውን ትዕዛዝ ዳኛ አገደው

ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና ቢሊየነሩ ኤሎን መስክ የአሜሪካ የልማት ተራድኦ ድርጅት (ዩ ኤስ ኤ አይ ዲ)ን ለማፍረስ የመጀመሪያ በሆነው እርምጃ የ30 ቀናት የጊዜ ገደብ የሚሰጠውን እና እረፍት እንዲወጡ በማስገደድ በሺዎች የሚቆጠሩ ሠራተኞችን ከሥራ ውጭ የሚያደርገውን ትዕዛዝ የፌደራል ዳኛ አግደውታል፡፡

በአሜሪካ የግዛት ዳኛ የሆኑት ካርል ኒኮልስ፣ በሺህ የሚቆጠሩ በውጭ ሀገራት የዩ ኤስ ኤ አይ ዲ ሠራተኞችን እና ቤተሰቦችን በመንግሥት ወጪ ወደ አሜሪካ ለመመለስ በ30 ቀናት ውስጥ ድንገተኛ አስተዳደራዊ ፈቃድ የሚሰጠውን ትእዛዝ አግደዋል።

ሁለቱም እርምጃዎች የአሜሪካ ሠራተኞች ፣ የትዳር ጓደኞቻቸው እና ልጆቻቸው ላልተገባ ወጪ እና አደጋ እንዲጋለጡ የሚያደርጉ እንደሆኑ ዳኛው ተናግረዋል።

ዳኛው አክለውም፣ የትራምፕ አስተዳደር ድርጅቱን እና ፕሮግራሞቹን ለመዝጋት ሲጣደፍ፣ አንዳንድ ሠራተኞችን የጤና ወይም የደህንነት ድንገተኛ አደጋ ቢከሰት የአሜሪካ መንግሥትን ለማሳወቅ የሚያስፈልጋቸውን ኢሜይል እና ሌሎች የመገናኛ ዘዴዎች እንደቆረጠ ከሠራተኞቹ የተገኘው መረጃ እንዳመላከተ መግለፃቸውን አሶሺዬትድ ፕሬስ ዘግቧል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

08 Feb, 16:00


የገንዘብ ሚኒስቴር  ህገወጥ እቃዎችን ለመያዝ መረጃ ለሚሰጡ ግለሰቦች ወረታ እንዲከፈላቸው የሚዘዉን መመሪያ ተግባራዊ አደረገ

የኮንትሮባንድ፣ የከበሩ ማዕድናትን እና የገንዘብ ሕገ-ወጥ ዝውውርን በመከላከል ረገድ ተሳትፎ ለሚያደርጉ አካላት ወረታ የሚከፍለው አዲሱ መመሪያ ተግባራዊ መደረግ ጀምሯል።

ከጥር 2017 ዓ.ም. ጀምሮ ወደ ስራ በገባዉ መመሪያ ላይ እንደተገለፀዉ በጠቋሚ መረጃ ሰጪነት ወደ አገር ሲገባ ወይም ከአገር ሲወጣ የተያዘ ሕገ ወጥ እቃ በሚያዝበት ጊዜ ለጠቋሚ እና ለያዥ ወረታ እንደሚከፈል ይደነግጋል።

አዲሱ መመሪያ "ሕገ-ወጥ ዕቃን የሚመለከት መረጃ አሰጣጥ፣ አመዘጋገብ፣ አያያዝ እና የወሮታ ክፍያ ለመወሰን የተዘጋጀ" መሆኑን አስቀምጧል።

በዚህ በተሻሻለው ደንብ መሰረት፣ መረጃ ሰጪዎች በጥቆማ መሰረት ከተያዙት ዕቃዎች ዋጋ ላይ 25% የሚያገኙ ሲሆይ የህግ አስከባሪ አካላት ደግሞ 20% እንዲሁም ህገ-ወጥ እቃዉ የተያዘዉ በሚሊሻ እና ብሔራዊ መረጃ አገልግሎት ከሆነ 10 በመቶ እንደሚያገኙ ተጠቁሟል።

ይህ እርምጃ ሪፖርት ማድረጉን ለማበረታታትና በኮንትሮባንድና በህገ-ወጥ ንግድ ላይ የሚደረገውን ትግል ለማጠናከር ያለመ መሆኑን ካፒታል ለመረዳት ችላለች።

መመሪያው ከዚህ ቀደም በ2002 የወጣውን በመረጃ አቀራረብ፣ በውርስ እና በሽልማት አወሳሰን ላይ የወጣውን መመሪያ ቁጥር 78/2002ን የሚተካ ሲሆን፣  እንዲሁም ግልጽ የሆነ ሪፖርት የማድረግ፣ የምርመራ እና ከተያዙ ዕቃዎች የሚገኘውን ገቢ ለህግ አስከባሪዎች አቅም ግንባታ እንዴት እንደሚውል የሚገልጽ አሰራር ያስቀምጣል።

Capital newspaper

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

07 Feb, 22:29


ትራምፕ ዩኤስኤአይዲን ለማፍረስ የሚወስዱትን እርምጃ በጊዜያዊነት ይገታል የተባለው ትዕዛዝ በፍርድቤት ተሰጠ

የአሜሪካ ቅርንጫፍ ዳኛ ካርል ኒኮልስ፣ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር የአሜሪካን ዓለም አቀፋዊ የልማት ድርጅት (USAID) ለመበተን የተወሰኑ እርምጃዎችን እንዳይወስድ "በጣም ውስን የሆነ" ጊዜያዊ ትዕዛዝ ለመስጠት እንዳሰቡ ገልጸዋል።

ይህ ውሳኔ፣ ሐሙስ ዕለት በአሜሪካ መንግሥት ሠራተኞች ትልቁ ዩኒየን እና የውጭ ጉዳይ ሠራተኞች ማኅበር ባቀረቡት ክስ ተከትሎ የመጣ ሲሆን፣ ይህም አስተዳደሩ ኤጀንሲውን ለመበተን የሚያደርገውን ጥረት ለማስቆም ያለመ መሆኑ ተጠቁሟል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

07 Feb, 20:32


⚡️ USAID signs are taken down at the agency's headquarters in DC.

#SputnikInt

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

07 Feb, 16:53


የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ከ9 ሺህ በላይ የአሜሪካ አለማቀፍ የልማት ተራድኦ ድርጅት (ዩኤስኤአይዲ) ሰራተኞችን ለማሰናበት ማቀዱ ተሰማ

ለእቅዱ ቅርበት ያላቸው አራት ምንጮች ነገሩኝ ብሎ ሬውተርስ እንዳስነበበው ድርጅቱ በመላው አለም ካሉት ከ10 ሺህ በላይ ሰራተኞች በስራ ገበታቸው የሚቀጥሉት 294ቱ ብቻ ናቸው።

ከድርጅቱ የአፍሪካ ቢሮዎች ውስጥ በስራቸው የሚቀጥሉት ስምንት ብቻ ናቸው፤ በእስያ ደግሞ ስምንት ይቀራሉ ብለዋል ምንጮቹ።
ዩኤስኤአይዲን ለስድስት አመታት የመሩት ብሪያን አትወድ እቅዱን "አስደንጋጭ" ያሉት ሲሆን፥ ከ9 ሺህ 700 በላይ ሰራተኞችን ማባረር የድርጅቱን ህልውና እንደሚገድል ተናግረዋል።

እቅዱ በመላው አለም በ10 ሚሊየን የሚቆጠሩ ድጋፍ ጠባቂዎችን ህይወት አደጋ ላይ እንደሚጥልም ነው ያነሱት።
ዩኤስኤአይዲን እንደገና እንዲያደራጅ ሀላፊነት የተሰጠው የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በሰራተኞች ቅነሳ እቅዱ ዙሪያ ማረጋገጫ አልሰጠም።

ትራምፕ እና የአለማችን ቁጥር አንድ ቢሊየነሩ ኤለን መስክ ድርጅቱን የአሜሪካውያን ታክስ ከፋዮችን ገንዘብ እያባከነ ነው፤ ሰራተኞቹም "ወንጀለኞች" ናቸው በማለት ይከሳሉ።
ድርጅቱ እንደአዲስ እስኪደራጅ ድረስም ቋሚ ቅጥረኞች ስራ እንዳይገቡ አዘዋል። የተወሰኑ ሰራተኞችም ከስራ መሰናበታቸውን የሚጠቁም ደብዳቤ እየደረሳቸው መሆኑን የሬውተርስ ምንጮች ተናግረዋል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

07 Feb, 16:52


በመርካቶ ሸማ ተራና አካባቢው ያጋጠመው የእሳት አደጋ መንስኤ ከኤሌክትሪክ ጋር በተያያዘ ችግር እንደሆነ የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል፡፡

ጥቅምት 11 ቀን 2017 ዓ.ም ምሽት ላይ በአዲስ አበባ ከተማ አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ በተለምዶ ሸማ ተራ ተብሎ በሚጠራው ነባር የገበያ ማዕከልና በአካባቢው የደረሰው የእሳት አደጋ በኤሌክትሪክ የቴክኒክ ችግር ምክንያት አማካኝነት ያጋጠመ መሆኑን በፎረንሲክ ምርመራ ማጣራቱንና ነው ኮሚሽኑ የገለጸው፡፡

ኮሚሽኑ ባለፉት 6 ወራት በአዲስ አበባና በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የደረሱ 103 የእሳት አደጋ መንስኤዎችን በፎረንሲክ ምርመራ አጣርቶ ውጤቱን ይፋ አድርጓል፡፡በዚህ የማጣራት ሂደትም በኤሌክትሪክ የቴክኒክ ችግር ምክንያት የደረሰ ቃጠሎ ብዛት 50፣ በመካኒካል ችግር ምክንያት የደረሰ 11 ቃጠሎ፣ ሆን ተብሎ በሰው አማካኝነት የደረሰ 10 ቃጠሎ፣ በቸልተኝነት የደረሰ 17 እና በሌሎች ምክንያቶች የደረሰ 15 ቃጠሎ መሆናቸውን አረጋግጫለሁ ብሏል፡፡

ባለፉት ስድስት ወራት በአዲስ አበባ ከተማ ብቻ 96 እና በክልሎች ደግሞ ሰባት በአጠቃላይ እንደ ሀገር 103 የእሳት ቃጠሎ አደጋዎች ደርሰው የአደጋ መንስኤዎችን ማጣራቱን ጨምሮ ገልጿል፡፡በግማሽ ዓመቱ በ582 መኖሪያ ቤቶች፣ በ12 ተሽከርካሪዎች፣ በ1ሺ 965 ንግድ ቤቶች፣ በስድስት ፋብሪካዎችና የተለያዩ ድርጅቶች በቃጠሎ ምክንያት ጉዳት ስለመድረሱ በፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን የስድስት ወራት ሪፖርት ተብራርቷል፡፡

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

07 Feb, 16:41


በጋምቤላ ክልል ከነገ ጀምሮ ለሦስት ወራት የሚቆይ የስራ ሰዓት ለውጥ ይደረጋል!

በጋምቤላ ክልል የሙቀት መጠን እየጨመረ በመምጣቱ የመንግስት የስራ ሰዓት ከነገ ጀምሮ ለውጥ እንደሚደረግ የክልሉ መስተዳድር ምክር ቤት አስታወቀ።የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኡቶው ኡኮት፣ በክልሉ የሙቀት መጠን እየጨመረ በመምጣቱ ከነገ የካቲት 1 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ለሶስት ወራት የሚቆይ የስራ ሰዓት ለውጥ ይደረጋል።

በለውጡ መሰረትም ቀደም ሲል የመደበኛው የስራ ሰዓት ከጠዋቱ አንድ ሰዓት እስከ ስድስት ሰዓት ተኩል የነበረው ከአንድ ሰዓት እስከ አምስት ሰዓት ተኩል እንደሚሆን አስታውቀዋል።እንዲሁም ከሰዓት በኋላ ከዘጠኝ ሰዓት እስከ 11 ተኩል የነበረው ከአስር ሰዓት እስከ 12 ሰዓት ተኩል እንዲሆን መወሰኑን አቶ ኡቶው አመልክተዋል።

የስራ ሰዓት ለውጡ በማጃንግ ዞን የመንገሺና የጎደሬ ወረዳዎችን እንደማይጨምር አስረድተዋል።በለውጡ መሰረትም የክልሉ የመንግስት ሰራተኞች በተጠቀሰው የስራ ስዓት መስሪያ ቤታቸው በመገኘት የተለመደ ተግባራቸውን እንዲያከናውኑ ማሳሰባቸውን ከጋምቤላ ክልል የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ገልጿል።

Via EPA

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

07 Feb, 16:40


#ነዳጅ

የነዳጅ ምርቶች ዋጋ በነበረበት ይቀጥላል ተብሏል።

የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል።


አንድ ሊትር ቤንዚን 101.47 ብር

አንድ ሊትር ናፍጣ 98.98 ብር

አንድ ሊትር ኬሮሲን 98.98 ብር

የአውሮፕላን ነዳጅ 109.56 ብር

አንድ ሊትር ከባድ ጥቁር ናፍጣ 105.97 ብር

አንድ ሊትር ቀላል ጥቁር ናፍጣ 108.30 ብር

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

07 Feb, 16:39


አንድ ኤርትራዊ ስደተኛ በፈረንሳይ ጠረፋማው ካላይ ከተማ አካባቢ ህይወቱ አልፎ መገኘቱ ተዘገበ

ይህ ወደእንግሊዝ ለመግባት ተስፋ ሰንቆ የነበረው ኤርትራዊ ማክሰኞ እለት ጠዋት ላይ በዚህ ከተማ መንገድ ላይ አስከሬኑ መገኘቱን የፈረንሳይ አቃቤ ህግ መስሪያ ቤት አስታውቋል፡፡

አቃቤ ህግ እንዳለው አንድ የፖርቹጋል ዜግነት ያለው የከባድ መኪና አሽከርካሪ በፍጥነት መንገድ ላይ በሚያልፍበት ወቅት አስከሬኑን ከርቀት በማየቱ ለሚመለከታቸው አካላት ሊያሳውቅ ችሏል፡፡ አስከሬኑ ከተነሳ በኋላም ስደተኛው በምን ምክንያት ህይወቱ እንዳለፈ ለማወቅ ምርመራ እየተከናወነ እንደሚገኝ አቃቤ ህግ ገልጿል፡፡

ይሁን እንጂ ትላንት ለንባብ የበቁ የፈረንሳይ አምስት ሚዲያዎች ባወጡት ዘገባ ለኤርትራዊው አሟሟት አምስት የተለያዩ ምክንያቶችን አቅርበዋል፡፡ ለምሳሌ ፍራንስ ኢንፎ ጋዜጣ በዘገባው ኤርትራዊው በአንድ የጭነት መኪና ላይ ተንጠልጥሎ በሚጓዝበት ወቅት ወድቆ ለሞት መዳረጉን ገልጿል፡፡ እንዲሁም ፍራንስ ቤኑ ኤርትራዊው በመኪና ተገጭቶ መገደሉን ሲዘግብ ለ ፊርጎ ጋዜጣ ደግሞ ኤርትራዊው በኮንቴይነር ውስጥ ተደብቆ ሲጓዝ ህይወቱ ማለፉንና ኮንቴይነሩን የሚያሽከረክረው ሹፌር ጥሎት መሄዱን ገልጿል፡፡

ይሁንና በፈረንሳይዋ ካላይ ከተማ የያዝነው የፈረንጆች አመት 2025 ስደተኞች ሞተው ሲገኙ ይህ ኤርትራዊ አራተኛው መሆኑ ተዘግቧል፡፡ ባለፈው አመት ከዚህች ከተማ ተነስተው በጀልባ ወደእንግሊዝ ለመግባት ከሞከሩ ስደተኞች መካከል ቢያንስ ሰባ ሰባት ያህሉ ህይወታቸው ማለፉ ይታወሳል፡፡ ከእነዚህ ውስጥ አብዛኛዎቹ ኤርትራዊያንና ኢትዮጵያዊያን መሆናቸውን በወቅቱ አደጋዎቹ በደረሱበት ወቅት ባቀረብናቸው ዘገባዎች መግለችፃን አይዘነጋም፡፡

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

06 Feb, 20:44


በ76 ዓመታቸው ልጅ የወለዱት የመቐለ ከተማ ነዋሪ
*****

ወ/ሮ መድህን ሓጎስ የተባሉ የመቐለ ከተማ ነዋሪ በ 76 ዓመታቸው ወንድ ልጅ ወልደዋል።

ወ/ሮ መድህን ከዚህ በፊት ልጅ የወለዱ አለመሆናቸውን እና ይህ የመጀመሪያቸው መሆኑን ኢቢሲ ከቤተሰቦቻቸው አረጋግጧል።

የልጃቸው ክርስትና ባለፋት ቀናቶች መከናወኑም ተገልጿል፡፡

ኢቢሲ ባለ ታሪኳን ለማነጋገር ያደረገው ጥረት ባይሳካም ወ/ሮ መድህን የወንድ ልጅ እናት ስለመሆናቸው ከቤተሰባቸው ማረጋገጥ ችሏል።

ወ/ሮ መድህን ሓጎስ በ76 ዓመታቸው ልጅ የመውለዳቸው ጉዳይ በማሕበራዊ ሚዲያው ብዙዎች እየተነጋገሩበት ይገኛል።

በሙሉጌታ ተስፋይ (ከመቐለ)

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

06 Feb, 18:16


ሰሞኑን በጠቅላይ ሚኒስቴር አቢይ አህመድ በትግሪኛ ቋንቋ የተላለፈውን መልእክት የህወሓት ከፍተኛ አመራር ወይዘሮ ፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሔር «ማስፈራሪያ» ነው አሉ።

ወይዘሮ ፈትለወርቅ ጦርነት አንፈልግም፥ ያለንን ጥያቄ ግን እናቀርባለን ነው ያሉት።

የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስቴር ለትግራይ ክልል ሕዝብ በተለይም ለትግራይ ልሂቅ በማለት በትግርኛ ላሰራጩት መልእክት ምላሽ የሰጡት የህወሓት ከፍተኛ አመራር ወይዘሮ ፈትለወርቅ ገብረ እግዚአብሔር፥ የጠቅላይ ሚኒስቴሩ መልአክም በጥሩ ቃላት የቀረበ እንኳን ቢሆንም የትግራይን ሕዝብ ለማስፈራራት ያለመ ሲሉ ኮንነውታል።

ጠቅላይ ሚኒስቴር አብይ አሕመድ በጽሑፍ መልእክታቸው ባለፉት 100 አመታት ከማዕከላዊ መንግሥት ጋር በተለያዩ ምክንያቶች ባጋጠሙ ቅሬታዎች፥ የትግራይ መሬት የጦርነት ምድር ሆኖ ቆይቷል ያሉ ሲሆን የህወሓት ጽሕፈት ቤት ሐላፊ የሆኑት ወይዘሮ ፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሔር ግን በምላሻቸው፥ የትግራይ ሕዝብ ባለፉት መቶ ዓመታት ወራሪዎችን መክቷል፣ ጨቋኞችን ታግሏል እንጂ የሆነ አካል ላይ ጦርነት የከፈተበት አጋጣሚ የለም ሲሉ ተናግረዋል።

"ያሉንን ጥያቄዎች እናቀርባለን ይህ ደግሞ ጦርነት መሻት አይደለም" ብለዋል።

ወይዘሮ ፈትለወርቅ «ልዝብ የሚመስል ግን ደግሞ በውስጡ ተጠንቀቁ የሚል ማስፈራርያ ያለው ስለሆነ ወደጦርነት ያስገባል የሚል ስጋት በሕዝብ ዘንድ ፈጥሯል።

ይህ ሆን ተብሎ የተደረገ ነው። ሕዝብ እንዲሸበር እየተደረገ ነው። ይህ በትግራይ ሕዝብ ላይ እየደረሰ ያለው በደል አካል አድርገን ነው የምንወስደው። የትግራይ ሕዝብ ይህ አይገባውም፣ ማስፈራራት አይገባውም።

በመላው ትግራይ ያለው ሁኔታ ለጦርነት የሚጋብዝ ነገር የለም። መብታችን ይከበር፣ ማንነታችን ይከበር፣ በፕሪቶሪያ ውል መሠረት ሁሉ ነገር ይፈፀም ማለት ግን ጥያቄያችን ነው። ይህ ግን ወደ ጦርነት የሚያስገባ አይደለም» ብለዋል።

ከዚህ በተጨማሪ 50 ዓመት የምስረታ በዓሉን ሊያከብር ቀናት የቀሩት ሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ፥ በታሪክ የከፋ የተባለ ክፍፍል ላይ ይገኛል።

Via ዶቼ ቬለ

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

06 Feb, 06:05


(ዜና) ዋዜማ ራዲዮ በጠዋቱ ባሰራጨው መረጃ "'በኦሮሚያ ክልል ጅማ ዞን በጅማ ከተማ ቤታቸው ለኮሪደር ልማት የፈረሠባቸው ነዋሪዎች መንግሥት በተከራየላቸው የሆቴል አልጋዎች፣ በግለሰብ መኖሪያዎችና በቀበሌ ቤቶች ውስጥ እየተንገላቱ መኾኑን ነገሩኝ" ሲል ዘግቧል።

"በከተማዋ አውራ ጎዳናዎች ግራና ቀኝ ያሉ የንግድና የመኖሪያ ቤቶች ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ ለኮሪደር ልማቱ መፍረሳቸውን ከምንጮቼ ሰምቻለው ያለው የራድዮው ዘገባ "ከፈረሱት ቤቶች መካከል፣ አብዛኞቹ ሕጋዊ ካርታ ያላቸውና ግብር ከፋይ እንደነበሩም" ጠቅሰዋል ብሏል።

"ለፈረሱት ቤቶች ባለቤቶች መንግሥት የገንዘብ ካሳም ይኹን ተለዋጭ ቦታ አልሠጣቸውም ብለዋል።" ሲል የዘገበው ዋዜማ "በኮሪደር ልማቱ የፈረሱት ቤቶች 15 ሺሕ ገደማ እንደኾኑ ተረድቻለሁ"ም ሲል ዘገባ አሰራጭቷል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ከሰሞኑ በጅማ ከተማ የኮሪደር ልማት ሥራዎችን ሲመርቁ ባደረጉት ንግግር "የጅማ ከተማ ነዋሪዎች ቤቶቻቸውን ሲያፈርሱም ሆነ ቦታዎችን ለፕሮጀክቶቹ ሲያስረክቡ ካሳ አለመጠየቃቸውን” በአድናቆት መግለጻቸው ይታወሳል። "የጅማ ከተማ ህዝብ፤ ካሳ ከመጠየቅ ይልቅ እስቲ ሃሳባችሁን አፍሱት፤ ልየው ነው ያለው። የጅማ አካባቢ ማህበረሰብ ለእነዚህ ህልሞች፣ ለእነዚህ ሃሳቦች መወለድ የነበረው ሚና፤ ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ትምህርት መሆን ያለበት ነው” ማለታቸው አይዘነጋም።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

06 Feb, 06:04


አስመጪዎች ያለባንክ ዋስትና መላክ የሚችሉት ቅድመ ክፍያ መጠን ላይ ማሻሻያ ሊደረግ ነዉ ተባለ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አስመጪዎች ያለባንክ  ዋስትና መላክ በሚቻለው ቅድመ ክፍያ መጠን ላይ ጭማሪ ለማድረግ መመሪያውን እየከለሰ እንደሚገኝ ተሰምቷል።

ላለፉት 27 አመታት ሲተገበር በቆየው አሰራር መሰረት አስመጪዎች ያለባንክ ዋስትና ለሚያስገቡት እቃ በቅድሚያ መላክ/መክፈል የሚችሉት የውጭ ምንዛሬ መጠን ከ5 ሺ ዶላር መብለጥ እንደማይችል የማእከላዊ ባንኩ መመሪያ ደንግጓል።

ይህን ተከትሎ ከ5ሺ ዶላር በላይ ቅድመ ክፍያ መፈፀም ከፈለጉ ከአገር ውስጥ ባንክ ዋስትና ማቅረብ ይጠበቅባቸው እንደነበር ይታወቃል ።

ይህ የጭማሪ መጠኑ ምን ያህል እንደሆነ የተገለፀ ነገር ባይኖርም አዲሱ መመሪያው ግን በቀጣይ መጋቢት ወር ወደ ስራ ይገባል ተብሎ ይጠበቃል።

Capital newspaper

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

06 Feb, 06:04


በኤሌክትሮኒክ የነዳጅ ግዥ ስርአት ውስጥ ሁሉም ባንኮች ሊካተቱ መሆኑ ተገለፀ

በነዳጅ ሽያጭ እየተሳተፉ የሚገኙት ቴሌ ብር፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና አንድ የግል ባንክ ብቻ የነበሩ ሲሆን አሁን ግን መንግስት ሌሎች የፋይናንስ ተቋማት መሳተፍ እንዲችሉ የወሰነ መሆኑ ታውቋል።

የነዳጅ ገበያውን ለማዘመን እና ህገወጥ አሰራርን ለማስቀረት በማሰብ መንግስት የነዳጅ ሽያጭ በሞባይል የክፍያ ስርአት ብቻ እንዲከናወን ወስኖ እየተተገበረ እንደሚገኝ ይታወሳል።

በዚህም ዘመናዊውን የግዥ መተግበሪያ/አፕ ያበለፀገው ኩባንያ ሌሎች ባንኮችን ለማካተት እየሰራ ሲሆን ባንኮቹ ግን ከመቼ ጀምሮ ወደ ስርአቱ ይገባሉ የሚለው አለመታወቁን ነው የተገለጸው ።

capital newspaper

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

05 Feb, 16:10


የአሜሪካ ዓለም አቀፍ ተራድኦ ድርጅት በመላው ዓለም የሚገኙ ሠራተኞቹን አሰናበተ

የትረምፕ አስተዳደር በመላው ዓለም የሚገኙ የአሜሪካ ዓለም አቀፍ ልማት ድርጅት (ዩ ኤስ ኤ አይ ዲ) ሠራተኞች ሥራ እንዲያቆሙ አዟል።

ላለፉት ስድሳ ዓመታት በመላው ዓለም ረሃብን በማስወገድ እና ለትምህርት ከፍተኛ የገንዘብ ድጋፍ በመስጠት የአሜሪካንን ደኅንነት ሲያስጠብቅ የከረመው ድርጅት የመዘጋት ዕጣ ገጥሞታል።

የትረምፕ አስተዳደር ለአሜሪካ ዓለም አቀፍ ልማት ድርጅት ሠራተኞች በኢሜይል በላከውና እና በድርጅቱ ድህረ ገጽ ላይ ባሠፈረው መልዕክት ነው ውሳኔውን ያስታወቀው።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

05 Feb, 09:59


በትረምፕ ትዕዛዝ በርከት ያሉ የዩናይትድ ስቴትስ የትምህርት ሚንስቴር ሠራተኞች እረፍት እንዲወስዱ ታዘዙ!

የፌደራሉ የሠራተኞች ማኅበር እንዳመለከተው በዩናይትድ ስቴትስ ትምህርት ሚንስቴር ውስጥ የሚሠሩ ቁጥራቸው የበዛ ሠራተኞች ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በአወጡት እና በፌዴራል መንግሥት ውስጥ ‘ብዝሃነት፣ ፍትሃዊነት እና አካታችነት’ የተባሉ ፕሮግራሞችን ለመሰረዝ በሰጡት ትእዛዝ መሰረት መፈጸሙን አመልክቷል።

የዩናይትድ ስቴትስ የመንግሥት ሠራተኞች ፌዴሬሽን የትምህርት ሚንስቴር ሠራተኞችን የሚወክለው 252 የተባለው ጽ/ቤት ፕሬዝዳንት ሸሪያ ስሚዝ በትላንትናው ዕለት ሲናገሩት ደሞዝ እየተከፈላቸው ለጊዜው እረፍት እንዲወስዱ የታዘዙት ሠራተኞች ቁጥራቸው ምን ያህል እንደሆነ፤ ወይም በምን ምክንያት ይህ ውሳኔ ሊሰጣቸው እንደቻለ ግልፅ አይደለም’ ብለዋል።

ቢያንስ ቁጥራቸው 55 የሚደርሱ ሠራተኞች ቀደም ሲል ትራምፕ በፈረሙት የፕሬዝዳንታዊ ትዕዛዝ መሰረት ወዲያውኑ እንደሚፈጸም የሚገልጽ የኢሜል መልዕክት ባለፈው አርብ ደርሷቸዋል።ትራምፕ ‘የትምህርት ሚኒስቴርን እዘጋለሁ’ የሚል ቃል በመግባት የምርጫ ቅስቀሳ ማድረጋቸው ይታወሳል።

Via VoA

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

05 Feb, 08:36


የ9 ዓመት ሴት ህፃን ልጅ አታልሎ የደፈረዉ አዛዉንት በጽኑ እስራት መቀጣቱን የቦረዳ ወረዳ ፖሊስ ገለፀ።

ተከሳሽ አቶ እሳቱ ዳንጎረ የተባለው የ60 ዓመት አዛውንት ጥር 5/2017 ዓ.ም ከቀኑ 9:00 ሰዓት ገደማ የግል ተበዳይ የ9 ዓመት ህጻን የሆነች በጎቹን ለመጠበቅ በቦረዳ ወረዳ ዘፍነ ቀጠና 3 ሀንዝያ መሄጃ ልዩ ስፍራ ሾንከ ዛፍ ተብሎ በሚጠራበት አከባቢ ባህር ዛፍ ውስጥ ሸንኮራ እንቺ በማለት አታሏዋት ወደራሱ አቅርቦ አስገድዶ የግብረ ሥጋ ግንኙነት ወንጀል በመፈፀሙ የቦረዳ ወረዳ ፖሊስ በሰውና ሀኪም ማስረጃ ምርመራዉን አጣርቶ ለዐቃቤ ህግ ያቀረበዉ ክስ ተከፍቶ የቀረበለት የወረዳዉ ፍርድ ቤት አከራክሮ ጥር 27/2017 ዓ.ም በዋለው 1ኛ ወንጀል ችሎት ተከሳሽን በ16 ዓመት ጽኑ እስራት እንድቀጣ ወስነዋል።

መረጃዉ፦ የቦረዳ ወረዳ ፖሊስ ህዝብ ግንኙነት ነዉ።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

04 Feb, 21:50


በማረሚያ ቤት ውስጥ ፎቶ ተነስተዋል በተባሉት ታራሚዎች ዘንድ ተንቀሳቃሽ ስልክ በፍተሻ መገኘቱን የፌደራል ማረሚያ ቤት አስታወቀ

ከሰሞኑ በማረሚያ ቤት የአየር መንገድ ደህንነትን አደጋ ላይ ለመጣል ተንቀሳቅሰዋል ተብለው በወንጀል ተከሰው ጉዳያቸውን በማረሚያ ቤት ሆነው የሚከታተሉ እነ ጆን ዳንኤል ከማረሚያ ቤት ሆነው ለቀውታል በተባለ ፎቶ ዙሪያ ብስራት ሬድዮ እና ቴሌቪዥን የማረሚያ ቤቱን አስተዳደር ጠይቆ ምላሽ አግኝቷል።

የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነት ዋና ዳሬክተር አቶ ገረመው አያሌው ለብስራት ሬድዮና ቴሌቪዥን እንደተናገሩት ስልኩ በፍተሻ ተገኝቷል።

ይህን ባደረጉ አካላት ላይ የማጥራት ስራ ተሰርቶ ጥፋተኛው ላይ በአሰራሩ መሠረት በህግ አግባብ ተመጣጣኝ እርምጃ የሚወሰድ መሆኑንም አቶ ገረመው ለብስራት ተናግረዋል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

04 Feb, 17:32


ከ5 ሺህ በላይ ሰራተኞች ውላቸው እንዲቋረጥ መመሪያ ተሰጠ።

ጤና ሚኒስቴር በሲዲሲ እና ዩኤስኤይድ (USAID) ድጋፍ የተቀጠሩ ከ5 ሺህ በላይ ስራተኞችን ውል እንዲቋረጥ መመሪያ ሰጠ።

ጤና ሚኒስቴር ከአሜሪካ መንግሥት በሲዲሲ (CDC) ወይም ዩኤስኤይድ (USAID) አማካኝነት በተገኘ የበጀት ድጋፍ የሚከናወን ማንኛውም ስራም ሆነ ክፍያ እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር ከጃንዋሪ 24 ,2025 ጀምሮ እንዲቋረጥ ማሳሰቢያ እንደደረሰው ገልጿል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተመለከተው እና በጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ ተፈርሞ ለሁሉም የክልል ጤና ቢሮዎች የተሰራጨው ደብዳቤ " በጤና ሚኒስቴር ድጋፍ የተቀጠሩ እና ተቋማችሁ ከCDC ወይም USAID ጋር በሚያደርገው ውል መሰረት የተቀጠሩ ሰራተኞችን በተመለከተ ስራ ላይ እንዲውል አሳስባለሁ " ይላል።

ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ የደብዳቤውን #ትክክለኛነት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጠዋል።

ሚኒስትር ዴኤታው በሰጡን ተጨማሪ ማብራሪያ በመላው ሃገሪቱ በሲዲሲ እና ዩኤስኤይድ አማካኝነት በኮንትራት እያገለገሉ ያሉ ሰራተኞች ቁጥር 5 ሺህ እንደሚሻገር ገልጸዋል።

ሚንስትሩ " ሰው እንዲዘጋጅ ነው እንጂ የአሜሪካ መንግሥትም ሃሳቡን ሊቀይር ይችላል የተቀየረ ነገር ካለ የሚቀጥል ይሆናል አሁን ባለው ሁኔታ ግን ድጋፉን ካቋረጠ ሌላ መፍትሄ ማፈላለግ ያስፈልጋል " ብለዋል።

" ለዚህ ደግሞ ሰራተኞቻችን እንዲዘጋጁ ከመንግስት ጋርም ንግግር እየተደረገ ነው ያለው የመንግስት ሰራተኞች ስራውን እንዲያስቀጥሉ የCDC እና USAID ሰራተኞች ስራውን እንዲያቆሙ ተወስኗል " ብለዋል።

ሚኒስትር ዴኤታው በዝርዝር ምን አሉ ?

" እኛን በዋናነት የሚመለከተን በጀቱ በቀጥታ በእኛ በኩል ስለሚመጣ የሲዲሲ ሰራተኞችን ነው ዩኤስኤይድ ግን ቅጥር የሚያከናውነው በራሱ በኩል ነው ውሉንም የሚያቋርጡት ራሳቸው ናቸው።

የአሜሪካ መንግሥት ሃሳቡን ቀይሮ ሌላ መረጃ የሚያስተላልፍ ከሆነ እኛም ሌላ መረጃ የምናስተላልፍ ይሆናል አሁን ባለው የአሜሪካ መንግስት ውሳኔ ግን ኮንትራታቸውን ማቋረጥ አስፈላጊ በመሆኑ ይህንን ደብዳቤ አስተላልፈናል።

ከ5 ሺ በላይ ይሆናል ትክክለኛ ቁጥራቸውን ለማወቅ መረጃ የመሰብሰብ ስራ እየሰራን ነው ሁሉም በኮንትራት ናቸው ኮንትራታቸው በየአመቱ ይታደሳል ስራቸውም ከኤች አይ ቪ ጋር የተገናኙ ስለሆነ አብዛኞቹ የቆዩ ሰራተኞች ናቸው።

በጣም አስፈላጊ በመሆናቸው ነበር በዚህ ያህል በጀት ተቀጥረው ሲሰሩ የነበረው 15 እና 20 ዓመት የሞላቸውም አሉ ስራው ላይ ችግር ሊያመጣ ይችላል።

በአንድ ጊዜ ይሄን ያህል ሰው ከሴክተሩ ከተቀነሰ ችግር ሊፈጠር ይችላል ዋናው ነገር ግን ስራው እንዳይስተጓጎል ሃላፊነቱን ላለው የመንግስት ሰራተኛ እያስተላለፉ መሄድ ያስፈልጋል።

ቀላል ስራ አይደለም የሚጠብቀን የሚቻለውን ሁሉ እናደርጋለን።

የመጨረሻ ውሳኔዎችን አልሰማንም ከአሜሪካ መንግሥት በየጊዜው የተለያዩ ውሳኔዎች እየተላለፈ ስለሆነ ዛሬ ሌላ ነገ ሌላ ነው የሚባለው ሁሉም የአፍሪካ ሃገራት ተመሳሳይ ነገር ነው እያደረጉ ያሉት ከሁሉም ጋር ውይይት እየተደረገ ነው።

የዓለም ጤና ድርጅትም በቦርድ ደረጃ ከሁሉም የአፍሪካ ሃገራት ጋር ውይይቶችን እያደረገ ይገኛል።

ሰራተኞችም እንዲያውቁ እኛም ጫናውን ለማሳወቅ እና መፍትሄው አብሮ ለመፈለግ እንዲቻል ለመንግሥትም አሳውቀናል ስራ እንዳይጎዳ ከፍተኛ ጥንቃቄ ይደረጋል።

በዚሁ ከቀጠለ ሌላም ከባባድ ውሳኔዎች ሊወሰን ይችላል የመድኃኒት ግዢ እና ሌሎችም ድጋፎች ሊቋረጡ ይችላሉ አይታወቅም እንዳይቋረጥ እና እንዲቀጥል እኛም እንደሃገር የምንችለውን ጫና እናደርጋለን።

በውስጥ አቅም በውስን የሰው ሃብት ባለን በጀት ስራዎች እንዳይስተጓጎሉ በሽታዎች ተመልሰው ከፍ እንዳይሉ አስፈላጊውን እርምጃ መውሰድ ያስፈልጋል ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይቶችን እያደረግን እንገኛለን በሚቀጥሉት ጊዜያት የሚመጡ ውጤቶችን እና ቀጣይ ውሳኔዎችን እናሳውቃለን " ብለዋል።

#TikvahEthiopia

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

04 Feb, 17:07


በሰው ልጆች አፈጣጠር ሣይንሳዊ ምልከታ 3.18 ሚሊዮን ዓመት እድሜ እንዳለው የሚገመተው የሉሲ ወይንም ድንቅነሽ ቅሪተ-አጽም አውሮጳ ውስጥ ለዕይታ ሊቀርብ ነዉ ተብሏል።

በሰሜን ምሥራቅ የኢትዮጵያ ክፍል አፋር ውስጥ ከግማሽ ምእተ ዓመት በፊት የተገኘው ይህ ቅሪተ-አካል ከዚህ ቀደም ወደ ዩናይትድ ስቴትስ ለዕይታ ተወስዶ ነበር ።

አሁን በአውሮጳ፤ ቼክ ዋና ከተማ ፕራኅ ብሔራዊ ቤተ-መዘክር ለመጀመሪያ ጊዜ ለዕይታ ይቀርባል ይቀርባል ተብሎ ይጠበቃል ።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

04 Feb, 15:03


#CapitalNews ከዩ.ኤስ.ኤይድ የገንዘብ ድጋፍ የሚያገኙ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ሃብትና ገንዘብን ለሶስተኛ ወገን እንዳያስተላልፉ ማስጠንቀቂያ ተሰጠ

በአሁኑ ወቅት ከዩ.ኤስ.ኤይድ የገንዘብ ድጋፍ የሚያገኙ ድርጅቶች በማናቸውም መልኩ ሃብትና ገንዘብን ለሶስተኛ ወገን ማስተላለፍ የተከለከለ መሆኑንና ይህነ  በሚተላለፉ ተቋማት ላይ እርምጃ እወዳለሁ ብሏል።

ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ለሁሉም የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በጻፈው እና ለካፒታል በደሰረዉ ደብዳቤ ላይ እንደተገለፀዉ ያለ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ግልፅ ፍቃድ ንብረት የማስተላለፍ፣ የማስወገድ ወይም የመሸጥ ወይም ከመደበኛ/ፕሮጀክት ስራዎች ጋር ተያያዥ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ብቻ እንዲንቀሳቀሱ ጠይቋል።

ይሁን እንጂ በማናቸውም መልኩ ሃብትና ገንዘብን ለሶስተኛ ወገን ማስተላለፍ የተከለከለ መሆኑን የገለፀው ባለስልጣኑ ይህንን ማሳሰቢያ በመተላለፍ በሚንቀሳቀሱ ድርጅቶች ላይ ተገቢውን እርምጃ እንደሚወስድ ጠቁሟል።

ከሰሞኑ በአሜሪካ ተራድኦ ድርጅት (ዩ.ኤስ.ኤይድ) በኩል የእርዳታ ማቆም ውሳኔ ጉዳዩን በቅርበት እየተከታተለ መሆኑንና ዝርዝር ሁኔታዎችን መሰረት በማድረግ በቀጣይ አስፈላጊው ድጋፍና ክትትል የሚያከናዎን መሆኑን ተቆጣጣሪ አካሉ አስታውቋል ።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

04 Feb, 13:47


ኬንያ በኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ላይ ያነጣጠረ ወታደራዊ ዘመቻ መጀመሯን አስታወቀች!

ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር በምትዋሰንበት የድንበር ግዛቶቿ ላይ ባሉ የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ላይ ያነጣጠረ ወታደራዊ ዘመቻ መጀመሯን አስታወቀች።የኬንያ መንግሥት የጦሩ አባላት ተደብቀውባቸዋል ባላቸው የማርሳቤት እና ኢሲዮሎ ግዛቶች ላይ "ወንጀለኞችን የማስወገድ" የተሰኘ ከፍተኛ የጸጥታ ዘመቻ ባለፈው ወር ጥር፣ 25/ 2017 ዓ.ም መጀመሩን ገልጿል።

እነዚህ ግዛቶችን "ድንበር ዘለል የወንጀል ድርጊቶችን ለማሳለጥ የሚጠቀምባቸው ናቸው" ሲል የኬንያ መንግሥት ብሔራዊ የፖሊስ አገልግሎት ሰኞ ጥር፣ 26/ 2017 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ ቡድኑን ወንጅሎታል።የኢትዮጵያ መንግሥት በተለያዩ ጥሰቶች የሚወነጅለው "ሸኔ" እያለ የሚጠራው የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት በኬንያ ግዛቶች ውስጥም ህገወጥ የማዕድን ማውጣትን ጨምሮ ሌሎች ጥሰቶች እየፈጸመ ነው ኬንያ ወንጅላለች።

የኬንያ ብሔራዊ ፖሊስ ቡድኑ "በተለያዩ ህገወጥ የጦር መሳሪያ፣ አደንዛዥ ዕጾች ዝውውር፣ ህገወጥ የማዕድን ማውጣት ህገወጥ የሰዎች ዝውውር ንግድ ተሰማርቶ ይገኛል" ብሎታል በመግለጫው።የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት "ለገንዘብ ሲል እገታዎችን በመፈጸም እንዲሁም ድንበር ዘለል ወረራዎችን በማካሄድ እና በጎሳዎች መካከል ግጭቶች እንዲቀሰቀሱ በማድረግ ለኬንያ የብሔራዊ ደህንነት ከፍተኛ ስጋት" ሆኗል ሲል መግለጫው አስፍሯል።

የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት በበኩሉ ቡድኑን መወንጀል አዲስ ነገር እንዳልሆነ ጠቅሶ በዘረፋዎችም ሆነ በህገወጥ ተግባራት እንዳልተሳተፈ እና "ለፍትህ" የሚታገል ድርጅት መሆኑን ለቢቢሲ ገልጿል።"እንዲህ አይነት ጥሰቶችን የሚፈጽሙ አካላትን ከኬንያ መንግሥት ጋር በመተባባር እንደሚዋጉ" የጦሩ ዋና አዛዥ አማካሪ ጂሬኛ ጉዴታ ለቢቢሲ ተናግረዋል።

ኬንያ በታጣቂዎቹ ላይ የጀመረችው ዘመቻ ባለፈው ወር የኢትዮጵያ ብሔራዊ መረጃ እና ደኅንነት አገልግሎት ዳይሬክተር ጄኔራል አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ወደ ኬንያ ተጉዘው ከአገሪቱ ፕሬዚዳንት ዊልያም ሩቶ ጋር ከተነጋገሩ በኋላ ነው።በውይይቱ ላይ የኬንያው የብሔራዊ መረጃ አገልግሎት ዳይሬክተር ጄኔራል ኑረዲን ሐጂ ተገኝተው ነበር።

ታጣቂው ቡድን "በኬንያ ቦረና እና በኢትዮጵያ ኦሮሞ መካከል ያለውን የባህል ትስስር እንዲሁም ቅርብ ዝምድና በመጠቀም በማርሳቤት እና ኢሶዮሎ ግዛቶች ውስጥ ባሉ ህዝቦች መካከል ሰርጎ በመግባት በድንበር አካባቢ በሚኖሩ ማህበረሰቦች ላይ ጥሰቶችን" እየፈጸመ ይገኛል ብሎታል የኬንያ ፖሊስ መግለጫ።

መግለጫው አክሎም "ቡድኑ በሴቶች እና በታዳጊዎች ላይ ወሲባዊ ጥቃቶችን ጨምሮ ማስፈራራት፣ በኃይል ንብረትን መውሰድ በአካባቢው በመፈጸሙ ማህበረሰቡን ለሰቆቃ ዳርጎታል" ብሏል።

ህይወትን፣ ንብረትን እንዲሁም ሰላምን ለማስጠበቅ በግዛቲቱ ተደብቀው የሚገኙ "የኦሮሞ ነጻነት ወንጀለኞችን ለማስወገድ" የኬንያ ብሔራዊ የፖሊስ አገልግሎት የወታደራዊ የመጀመሪያ ምዕራፍ ዘመቻ በይፋ መጀመሩን የአገሪቱ ፖሊስ ምክትል ዋና አዛዥ ጊልበርት ማንጊሲ እንዲሁም የወንጀል ምርመራ አገልግሎት ዳይሬክተር መሀመድ አሚን በትናንትናው ዕለት ገልጸዋል።

Via BBC

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

04 Feb, 07:55


በተለመዶ የጣራና ግድግዳ እየተባለ የሚጠራው የቤትና ቦታ ግብር ያለቅጣትና ወለድ የሚከፈልበት ጊዜ እየተጠናቀቀ በመሆኑ ግብር ከፋዮች ከወዲሁ እንዲከፍሉ ተጠየቀ፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በተለመዶ የጣራና ግድግዳ እየተባለ የሚጠራ የቤትና ቦታ ግብር የሚከፍሉ ግብር ከፋዮች ግብሩ ያለቅጣትና ወለድ የሚከፈልበት ጊዜ እየተጠናቀቀ መሆኑን በመገንዘብ ከወዲሁ ግብራቸውን እንዲከፍሉ ተጠየቀ፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ የገቢ አወሳሰንና አሰባሰብ ዳይሬክተር አቶ ወንድማገኝ ካሳዬ እንደገለፁት በመዲናዋ 429 ሺህ 829 ግብር ከፋዮች የቤትና ቦታ ግብር ክፍያ እንዲፈፅሙ ይጠበቃል፡፡

ይሁንና እስካሁን ባለው ሂደት 228 ሺህ 222 ግብር ከፋዮች የቤትና ቦታ ግብር መፈፀማቸውን በመግለፅ ይህም የዕቅዱ 51 በመቶ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

አክለውም የቤትና ቦታ ግብራቸውን ከከፈሉ ግብር ከፋዮችም 2 ነጥብ 24 ሚሊዮን ብር መሰብሰቡን ተናግረዋል፡፡

የቤትና ቦታ ግብር በተለምዶ የአፈር፣ የቤትና ጣሪያ በሚሉና መሰል ስያሜዎች እስከ የካቲት 30 ድረስ የሚሰበሰብ የግብር አይነት መሆኑ ተገልጿል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

22 Jan, 18:56


ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ፣ የመግቢያ ፍቃድ ያገኙ ስደተኞች ወደ አሜሪካ እንዳይገቡ እገዳ ጥለዋል

አሜሪካ ፍልሰተኞችንና ስደተኞችን ለማስተናገድ አቅም እንደሚያንሳት በመግለጽ ፕሬዝዳንት ባስተላለፉት ትዕዛዝ መሠረት፣ አዳዲስ ስደተኞችን ለመቀበል የተጀመሩ ሂደቶችን ማቆሙን የአገሪቱ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት አስታውቋል። ስደተኞችን መቀበል ከአሜሪካ ጥቅሞች ጋር መጣጣም አለመጣጣሙ እስኪረጋገጥ ድረስ፣ የስደተኞች መቀበያ ፕሮግራም ታግዶ እንደሚቆይም ተገልጧል

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

22 Jan, 13:28


“በኢትዮጵያ አሁን ላይ ሁሉንም ጉዳዮች  በውይይት እንፍታ የሚል መሪ እና መንግሰት ነው ያለው”  የመንግሰት ዋና ተጠሪ ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር )

በብሔራዊ መግባባት ላይ ያተኮረው ሁለተኛው የፓርላማ የዜጎች መድረክ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እየተካሄደ ይገኛል፡፡

በዚህ ውይይትም በተለየ በሃገራዊ መግባባት እና በሃገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ ዙሪያ ብዙ ሃሳቦች እና ጥያቄዎች ከተሳታፊዎች እየተነሱ ይገኛል፡፡

የመንግስትን መሪ አቋምን  በተመለከተ በውይይቱ  ተሳታፊዎች ጥያቄ ተነስቷል፡፡

አሁን ላይ የመንግስት አቋምን በተመለከተ ማብራሪያ የሰጡት የመንግሰት ተጠሪ  ተስፋዬ በልጅጌ( ዶ/ር) ፤ አሁን ኢትዮጵያ ላይ ከመቼውም ጊዜ በላይ ''ሁሉንም አጀንዳዎች በውይይት እንፍታ የሚል  መንግስት ነው'' ያለው ሲሉ ተደምጠዋል፡፡

ዶ/ር  ተስፋዬ በተለይም ሁሉንም የፖለቲካ አጀንዳዎች በውይይት እና በጠረጴዛ  ዙሪያ እንፍታ የሚል የመነግስት ተቋም ተፈጥሯል ብለዋል፡፡

ለአብነት ያነሱት  ሃገራዊ ምክክር  ምክር ቤት መቋቋሙ የመንግስት ቁርጠኝነትን በደንብ ያሳየ መሆኑን አመላካች ነው ሲሉ ገለጸዋል፡፡

የመንግሰት ተጠሪው ለዚህ ማሳይ ብለው የቤንሻነጉል ጉምዝ  ታጣቂዎች ሰላም አማራጭን መከተልን እንዲሁም የቅርቡን የእነ ጃል ሰኚ እና የመንግሰት የሰላም ስምምነትን ጠቅሰዋል፡፡

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

21 Jan, 20:35


"የ20 ኢትዮጵያውያን ህይወት አልፏል" - IOM

መነሻውን ከጅቡቲ በማድረግ 35 ኢትዮጵያውያንን አሳፍሮ ወደ የመን ሲያቀና የነበረ የስደተኞች መርከብ በኃልኛ ንፋስ ተመቶ በደረሰው አደጋ የ20 ኢትዮጵያውያን ህይወት ማለፉን ዓለማቀፉ የስደተኞች ድርጅት (IOM) አስታውቋል።

አደጋው ቅዳሜ ዕለት (ጥር 10) መድረሱን፤ የ9 ሴቶች እና የ11 ወንዶች ህይወት ማለፉን የጠቀሰው ድርጅቱ በመርከቡ የነበሩ 15 ኢትዮጵያውያን እና ሁለት የየመን ዜግነት ያላቸው መርከበኞች ደግሞ በህይወት መትረፋቸውን ገልጿል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

21 Jan, 17:54


ሁሉንም በአንድ የያዘ ስማርት ካርድ ወደ ሥራ ለማስገባት እየተሰራ ነው ተብሏል።

የአዲስ አበባ ከተማ የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ የፋይዳ መታወቂያ ቁጥር የያዘ፣ የመንጃ ፍቃድ ቁጥር ያለው እንዲሁም እንደ ኤቲ ኤም ካርድ የሚያገለግል ሁሉንም በአንድ የያዘ የነዋሪነት መታወቂያ ስማርት ካርድ ወደ ሥራ ለማስገባት በፕሮጀክት ደረጃ እየሰራ መሆኑን ጠቅሷል።

የአዲስ አበባ ከተማ የነዋሪነት መታወቂያን ስማርት አርጎ አሁን ከምንጠቀምበት የተሻለ ተደርጎ ሰዎች የተለያዩ ካርድ ይዘው ከሚንቀሳቀሱ ሁሉንም አገልግሎቶችን በአንድ የያዘ ካርድ በቀጣዮቹ 6 ወራት ውስጥ ወደ አገልግሎት ለማስገባት በእቅድ ይዞ እየሰራ መሆኑን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከኤጀንሲው ሰምቷል።

ካርዱ የሚሰራበት ዋነኛ አላማም አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ያሉ ችግሮችን በመቅረፍ፣ ነዋሪዎች 3 ወይም 4 ካርድ ይዘው ከሚንቀሳቀሱ በ1 ካርድ ሁሉንም አገልግሎቶች አግኝተው አገልግሎት አሰጣጥና ተጠቃሚነትን ቀላል ለማረግ መሆኑን አሳውቋል።

ኤጀንሲው ለቲክቫህ እንደገለፀው ይህ ጉዳይ ከሚመለከታቸው ተቋማት ጋር ትስስር ሊኖር እንደሚገባና በአሁኑ ሰዓትም ፋይዳ ጋር በጋራ እየሰራ መሆኑን አስታውቋል።

ለወደፊት ደሞ ስራው ተጠናቆ ካርዱ ወደስራ ሲገባ ባንኮች እና ሌሎች የሚመለከታቸው ተቋማት የጋራ ትብብር እንደሚፈጠርም ተገልጿል።

ይህ አገልገሎት በሚቀጥሉት 6 ወራት ውስጥ ወደ ስራ ለማስገባት እቅድ የተያዘለት ፕሮጀክቱ አሁን ላይ ማሳያዎች (Samples) እየተሰራ ይገኛል።

አዲስ የሚሻሻለው የመታወቂያ አገልግሎት ፕሮጀክት ተግባር ላይ መዋል ሲጀምር ወይም የሚሻሻሉ፣ የሚጨመሩ ጉዳዮች ሲኖሩ ኤጀንሲው ለህዝብ በይፍ እንደሚያሳውቅም ነው ያስታወቀው።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

21 Jan, 17:53


የአዲስ አበባ የግማሽ ዓመት የፍቺ መጠን፤ ከአምናው ተመሳሳይ ጊዜ በ34 በመቶ መጨመሩ ተገለጸ

አዲስ አበባ ከተማ ባለፈው መንፈቅ ዓመት በይፋ የተመዘገበው የፍቺ መጠን፤ አምና በተመሳሳይ ጊዜ ከነበረው ጋር ሲነጻጸር በ34 በመቶ መጨመሩን የከተማይቱ የሲቪል እና የነዋሪነት ምዝገባ አገልግሎት ኤጀንሲ አስታወቀ።

በዚሁ ጊዜ የተመዘገበው የጋብቻ መጠን፤ ባለፈው በጀት ዓመት ስድስት ወራት ጊዜ ውስጥ ከተመዘገበው በሰባት በመቶ መቀነሱንም ኤጀንሲው ገልጿል።

ተቋሙ ይህን የገለጸው የ2017 በጀት ዓመት የስድስት ወራት የስራ አፈጻጸሙን አስመልክቶ፤ ዛሬ ማክሰኞ ጥር 13 በዋና መስሪያ ቤቱ በሰጠው መግለጫ ነው።

የመታወቂያ ስርጭት፣ የልደት እና የሞት ምዝገባ፣ ያላገባ የምስክር ወረቀት፣ የማስረጃ የማረጋገጥ ስራን ለመዲናይቱ ነዋሪዎች የሚሰጠው ኤጀንሲው፤ በከተማይቱ የተከናወኑ ጋብቻ እና ፍቺዎችንም ያከናውናል።

የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮናስ አለማየሁ፤ መስሪያ ቤታቸው ባለፉት ስድስት ወራት የመዘገበው ፍቺ 3,769 መሆኑን በዛሬው መግለጫ ላይ አመልክተዋል።

ኤጀንሲው ባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት የመዘገበው ፍቺ 2,832 እንደነበር የጠቀሱት ዋና ዳይሬክተሩ፤ የዘንድሮው የፍቺ መጠን በ34 በመቶ ጭማሪ ያሳየ እንደሆነ አስገንዘበዋል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

21 Jan, 16:48


ከጅብ መንጋጋ ልጇን ያስጣለችው እናት

በሀዲያ  ዞን በሆሳዕና ከተማ በጀሎ ናራሞ ቀበሌ መንደር 16 ነዋሪ  ወይዘሮ  ደንባሌ አሥራት ጥር 11/2017  ዓ/ም  ከጠት 3 ስዓት  አከባቢ ላይ  ሽላንሻ  ወንዝ ልብስ ለማጠብ  የ12ዓመት ሕፃን አሥከትላ በመሄድ ሥራዋን  መከወን ላይ እያለች  ጅብ ወደ እነርሱ  ይመጣል። በአጠገብ ከነበረች  ከሌላ ሴት  ጋር  በመሆን  ይህንኑ  ህፃን በመሀል አሥገብተዉ ቆመው  ያያሉ ።

ይህ ጅብ  ማለፍ  ይቅርና በ2ቱም  ሴቶች  መከከል  ያለውን  ህፃን ዘሎ ቀኝ እግሩን ነክሶ  በመያዝ ለመውሰድ ሲሞክር   ወላጅ እናት ቀኝ እጇን  በጅብ  አፍ  ውሥጥ  በመክተት  የጅቡን ጉሮሮ በግራ እጅ  አንቃ በመያዝ በላዩላይ ትወድቃለች  አብረው   የነበረችው  ሴት ከጅብ አፍ ህፃኑን   ነጥቃ  በማውጣት   ትታደጋለች ።  በጩኸት   የወጡ ሰዎች ህፃኑን ሊባላ  የቋመጠውን ጅብ  ብዙም  ሳይሄድም  ሰዎች  ተባብሮ   ተገሏል ተብሏል።

የሀዲያ  ዞን  ፖሊስ   ህዝብ ግንኘነት ነው የዘገበው::

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

21 Jan, 09:54


ትላንት በታቦት ላይ ሲቀልዱ የነበሩት የአምቦ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች በኦሮሚያ ፓሊስ በቁጥጥር ስር መዋላቸው ሁሌ አዲስ ሚዲያ ሰምቷል

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

21 Jan, 09:51


ትራምፕ የቲክቶክን እገዳ በአሜሪካ ለ75 ቀናት አራዝመዋል

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

21 Jan, 09:03


“ አቡበከር ናስር የት እንዳለ አላውቅም “ አሰልጣኝ ጋቪን ሀንት

“ ለተፈጠረው የመረጃ ክፍተት ይቅርታ ጠይቄያለሁ “ አቡበከር ናስር

የሱፐር ስፖርት ዩናይትዱ አሰልጣኝ ጋቪን ሀንት ኢትዮጵያዊው አቡበከር ናስር ባለፉት ሁለት ሳምንታት " ወደ ልምምድ አልመጣም " ሲሉ ለጋዜጠኞች ተናግረው ነበር።

አሰልጣኝ ጋቪን ሀንት በአስተያየታቸው “ አቡበከር የት እንዳለ አላውቅም “ ያሉ ሲሆን ቀጥለውም “ ለሁለት ሳምንታት ልምምድም አልሰራም “ ነበር ያሉት።

አሰልጣኙ አክለውም “ አቡበከርን ለማግኘት ጥረት አድርገናል ነገርግን ምላሽ አልሰጠንም ይሄ ከተጨዋቾቼ የምጠብቀው ባህሪ አይደለም ”ሲሉ ተደምጠው ነበር።

የክለቡ ቃል አቀባይ በበኩላቸው “ አቡበከር ናስርን ለማግኘት ሞክረናል ነገርግን ምላሽ አላገኘንም ስለ ደህንነቱ አስበናል ደህና መሆኑን ማረጋገጥ እንፈልጋለን “ ሲሉ ተናግረዋል።

አቡበከር ናስር በበኩሉ በይፋዊ የፌስቡክ ማህበራዊ ትስስር ገፁ ባሰፈረው ፅሁፍ “ ከክለቡ ጋር የመረጃ ክፍተት ተፈጥሮ ነው “ ብሏል።

“ ባለብኝ ጉዳት ምክንያት ከክለቡ ህክምና ቡድን እረፍት ተሰጥቶኝ ነበር “ ያለው አቡበከር “ በኋላም የተፈጠረውን ክፍተት ለክለቡ አስረድቼ ይቅርታ ጠይቄያለሁ “ በማለት አሳውቋል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

21 Jan, 06:30


ሰበር - ፕሬዝዳንት ትራምፕ ቢሮ በገቡ የመጀመሪያው ቀን ዩናይትድ ስቴትስን ከዓለም ጤና ድርጅት (WHO) የመውጣት ሂደት የሚያስጀምረውን የሥራ አስፈፃሚ ትዕዛዝ (Executive Order) ፈረሙ።

አሜሪካ ለዓለም ጤና ድርጅት ከፍተኛ የገንዘብ ድጋፍ ከሚያደርጉ አገሮች ግንባር ቀደሟ እንደሆነች ይታወቃል።

ከዚህ ቀደም ፕሬዝዳንቱ "ድርጅቱ ቻይናን ለኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ተጠያቂ ማድረግ ሳይችል ቀርቷል" ካሉ በሗላ አክለውም ቻይን ለመቅጣት የሚወስዷቸውን እርምጃዎች ይፋ ሲያደርጉ “ቻይና የዓለም ጤና ድርጅትን ሙሉ በመሉ ትቆጣጠረዋለች” ማለታቸው ይታወሳል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

21 Jan, 06:29


በመቐለ ከተማ በአክሱም ሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለውን በደል አስመልክቶ ሰላማዊ ሰልፍ እየተካሄደ ይገኛል!

ፍርድቤት የትምህርተ ቤቱ በሂጃብ የተሸፈኑ ሴት ተማሪዎችን አላስተናግድም ማለቱነ በማገድ ለፈተና እንዲመዘገቡ ቢያዝም ትዕዛዙን በመተላለፍ እስካሁነ ተማሪዎቹ አልተመዘገቡም።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

19 Jan, 05:36


ቲክቶክ በአሜሪካ አገልግሎቱ ተቋረጠ

ቲክቶክ ከደቂቃዎች በፊት በአሜሪካ መስራት አቁሟል።

ከቻይና መንግስት ጋር ግንኙነት እንዳለው በአሜሪካ መንግስት ክስ የቀረበበት የቲክቶክ ዋና ድርጅት ባይት ዳንስ ማስተካከያ እንዲያደርግ ወይም የድርጅቱን የአሜሪካ ቅርንጫፍ ለአሜሪካ ኩባንያዎች እንዲሸጥ ተጠይቆ ነበር።

ቲክቶክ አገልግሎቱ ለ175 ሚልዮን አሜሪካውያን ዛሬ ቢቋረጥም ሰኞ እለት ወደ ስልጣን የሚመጡት ዶናልድ ትራምፕ እገዳውን እንደሚያስቆሙት ይጠበቃል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

18 Jan, 05:36


 
የአዲስ አበባ ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት፤ ከምክር ቤቱ አሰራርና መመሪያ ውጪ ከ250 ሚሊዮን ብር በላይ መመዝበሩ በኦዲት ግኝት ተረጋገጠ

የንግድ ምክር ቤቱ በ78 ዓመታት ታሪኩ አንድም ጊዜ #የፋይናንስ_ሪፖርት አቅርቦ እንደማያውቅ የንግድ ምክር ቤቱ ምክትል ዋና ፀሃፊና የኢኖቬሽንና የሪሶርስ ዘርፍ ሃላፊው አቶ ለሜሳ ጉደታ ነግረውናል፡፡

በተቋሙ በተደጋጋሚ የሚስተዋለውን የህግና መመሪያ ጥሰትና የሃብት ምዝበራ በተጨባጭ ማረጋገጥ በማስፈለጉ ከ2015 ዓ.ም አጋማሽ እስከ 2016 ዓ.ም መጨረሻ ድረስ ያለውን በመውሰድ፤ በተሰራው ልዩ የኦዲት ምርመራ በተለያዩ ጊዜያት ከአሰራር ውጪ የወጣና የት እንደገባ የማይታወቅ ገንዘብ መኖሩ ተረጋግጧል ብለዋል፡፡

ለአብነትም በተሰራው የኦዲት ምርመራ ምዝበራዎቹ በ321 ማስረጃዎች እንደተደገፉ የሚያስረዱት ምክትል ዋና ፀሃፊው አቶ ለሜሳ፣ ከ31 ሚሊዮን ብር በላይ ያለ መመሪያ መከፈሉ ተረጋግጧል፤ ላልተሰጠ ስልጠና ከ223 ሚሊዮን ብር በላይ ለአባላቱ ተከፍሏል፡፡

ከ5 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጣ ባለቤትነቱ የማህበር አባላቱ የሆነ #መኪና ያለ አግባብ ለግለሰብ በሽልማትነት መሰጠቱ ከኦዲት ግኝቱ መካከል ናቸው እነዚህ እንኳን ሲደመሩ የተመዘበረውን ገንዘብ ከ250 ሚሊዮን ብር በላይ ያደርሰዋል ሲሉም ነግረውናል፡፡

ከዚህም  በተጨማሪ ከካዝናው በሚሊዮኖች የሚቆጠር #ገንዘብ እየወጣ አንድ ሰው በዓመት ውስጥ 57 ጊዜ ያለ አግባብ የውጭ ጉዞ ማድረጉን የኦዲት ግኝቱ አሳይቷል፡፡

ምንም አይነት አሰራር ሳይኖር ለግለሰቦች ሽልማት እየተባለ ቅጣ ያጣ የሃብት ማድፋፋት መፈፀሙንም አቶ ለሜሳ ያነሳሉ፡፡

በዚህ ምዝበራ ውስጥ እጃቸው አለበት በሚል የቻምበሩ 4 የስራ ሃላፊዎች ከስራ እስከ ማሰናበት የደረሰ የዲሲፕሊን እርምጃ እንደተወሰደባቸው ሃላፊው ተናግረዋል፡፡

እነዚህን ችግሮች ተመልክተን ቻምበሩ #ሪፎርም እንደሚያስፈልገው በመግባባት በተደረገው ሪፎርም የአሰራር ማሻሻያ ተደርጓልም ብለዋል፡፡

የቦርድ አባላት ለውጥ በማድረግ ትናንት ሃሙስ ጥር 8 ቀን 2017 ዓ.ም  አዳዲሶቹን የቦርድ አባላት በመረጠበት 18ኛው ጠቅላላ ጉባኤ ወ/ሮ ዛህራ መሃመድን በወ/ሮ መሰንበት ሸንቁጤ ምትክ ፕሬዝዳንት አድርጎ መርጧል፡፡

11 የቦርድ አባላት ባሉት ስብስብ ኢንጂነር አበበ ጉርሜሳ ምክትል ፕሬዝዳንት ሆነው ተመርጠዋል፡፡

አዳዲሶቹ ተመራጮች በገንዘብ ምዝበራ ተጠርጥረው የዲሲፕሊን እርምጃ የተወሰደባቸው 4ቱ የቻምበሩ የስራ ሃላፊዎች በህግ እንዲጠየቁ የማድረግ ሃላፊነት ተጥሎባቸዋል፡፡

ShegerFMRadio102_1

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

17 Jan, 18:42


ትራምፕ ለጋዛ የተኩስ አቁም ስምምነት ባይደን ምስጋና መዉሰዳቸዉን ተገቢ ያልሆነ ሲሉ ተናገሩ

ተመራጩ የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በጋዛ የተኩስ አቁም ስምምነት በእርሳቸውና በመጪው አስተዳደራቸው ግፊት ባይደረግ ኖሮ ፈጽሞ ሊደረስ እንደማይችል በመግለጽ ሙሉ እውቅና ሰጥተዋል።"በዚህ ስምምነት ውስጥ ባንሳተፍ ኖሮ የተኩስ አቁም ስምምነቱ በጭራሽ አይደረስም ነበር" ሲሉ ትራምፕ ተናግረዋል ሲል የአጃንስ ፍራንስ ፕሬስ የዜና አገልግሎት ዘግቧል።

"መንገዱን ቀይረነዋል፣ እናም በፍጥነት ቀይረነዋል፣ እውነቱን ለመናገር፣ እኔ ስልጣን ላይ ከመሆኔ በፊት ቢደረግ ይሻላል" ብለዋል።ትራምፕ በቴሌቭዥን ቀርበው አስተያየት የሰጡ ሲሆን ባይደን "ምንም አላደረጉም!" ሲሉ  ተናግረዋል።"ይህን ባላደርግ ኖሮ ታጋቾቹ በጭራሽ አይወጡም ነበር" ሲሉም አክለዋል። በሌላ በኩል የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የታጋቾችን የመልቀቅ ስምምነት ላይ መደረሱን አረጋግጧል፡፡

የቤንጃሚን ኔታንያሁ ጽህፈት ቤት የእስራኤል ተደራዳሪ ቡድን ስምምነቱ መጠናቀቁን አረጋግጧል።የሀገሪቱ የደህንነት ካቢኔ እና ከዚያም መንግስት ስምምነቱን ለማፅደቅ ስብሰባ ይቀመጣል፡፡ስምምነቱን የሚቃወሙት ሁለት የቀኝ ክንፍ ሚኒስትሮች ኢታማር ቤን ጊቪር እና ቤዛሌል ስሞትሪች በተቃውሞ ስልጣናቸውን እንደሚለቁ ተናግረዋል።

የተኩስ አቁም እና የታጋቾች የመልቀቅ ድርድር ምዕራፍ አንድ ሲያበቃ፣ መንግስትን ለማውረድ ተቃዉሞ ኃይሉን እንደማይቀላቀሉ ጠቁመዋል።የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ዋና ጸሀፊ አንቶኒ ብሊንከን የመጀመሪያዎቹን ሶስት እስራኤላውያን ታጋቾች በመልቀቅ የተኩስ አቁም ስምምነቱ በታቀደው መሰረት እሁድ ይጀመራል ብለው እንደሚጠብቁ ተናግረዋል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

17 Jan, 18:42


በኢትዮጵያ ታዳጊ ሴቶች የመጀመሪያ የግብረ ስጋ ግንኙነት በ17 ዓመት የእድሜ ክልል ውስጥ እንደሚፈፅሙ ተነገረ


በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የግብረ ስጋ ግንኙነት አማካይ እድሜ ላይ መሻሻሎች ቢኖሩም በአሁኑ ሰአት በ17  አመት እድሜ ውስጥ ያሉ ኢትዮጵያውያን ሴቶች የመጀመሪያ የግብረ ስጋ ግንኙነትን እንደሚፈፅሙ ተነግሯል።

በአዲስ አበባ ዮኒቨርሲቲ የስኩል ኦፍ ፐብሊክ ሄልዝ መምህር አቶ አሰፋ ስሜ ለብስራት ሬዲዮና ቴሌቪዥን እንደተናገሩት ጉዳዮን አስመልክቶ በፈረንጆቹ አቅጣጠር 2021 ላይ በፒ.ኤም.ኤ ኢትዮጵያ አማካኝነት የዳሰሳ ጥናት ተደርጓል።

ጥናቱ በገጠርና በከተማ መካሄዱን የገለፁት አቶ አሰፋ ከ25 እስከ 29 ፣ ከ30 እስከ 34 እንዲሁም ከ35 እስከ 39 የእድሜ ክልል ውስጥ ያሉ ሴቶች ላይ ትኩረት በማድረግ ተጠንቷል ብለዋል።

በጥናቱ መሰረት ከከተማ ይልቅ የገጠር ሴቶች የመጀመሪያ ወሲብ የመፈፀሚያ እድሜ እንደሚቀንስ የተገለፀ ሲሆን እድሜያቸው ከ35 እስከ 39 ያሉ እናቶች ቀደም ብለው የመጀመሪያ የወሲብ ግንኙነትን ስለመፈፀማቸው ተገልጻል።የግዳጅ ጋብቻ መኖር በገጠር የሚኖሩ ሴቶች ቀድመው የመጀመሪያ ወሲብን እንዲፈፅሙ ያደረገ ዋነኛው ምክንያት እንደሆነ ተነግሯል።

ቀደም ባሉት ጊዜያት የነበሩ እናቶች በ16 አመት እድሜ ላይ እያሉ ይህንን ተግባራዊ  ያደርጉ እንደነበር አቶ አሰፋ የገለፁ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ግን በ17 አመት እድሜ ክልል ውስጥ የመጀመሪያ ጊዜ የወሲብ ግንኙነትን ይፈፅማሉ ብለዋል።

ይህም የመጀመሪያ ጊዜ ወሲብ  መዘግየትን ያሳያል በማለት ተናግረው፤ ሴቶች በበሰለ እድሜ ላይ ሆነው ከጋብቻና ከልጆች ፍላጎት ጋር በተገናኘ መወሰን እንዲችሉ ጠቀሜታው የጎላ ነው ሲሉ አስረድተዋል።

የቤተሰብ እቅድ ምጣኔን አስመልክቶ እድሜዋ ከ35 እስከ 39 ያለች አንዲት የገጠር  ሴት በ 26 አመት እድሜ እያለች ትጠቀም እንደነበር በማስታወስ አሁን ላይ በ20ዎቹ  እድሜ ውስጥ ተግባራዊ እያደረገች እንደምትገኝ ተጠቅሷል።ይህም ለውጥ የመጣው  በሴቶች ዘንድ ያለው ግንዛቤ በማደጉ እና የእርግዝና መከላከያ አቅርቦት በመሻሻሉ ነው ተብሏል።

በቅድስት ደጀኔ

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

17 Jan, 18:42


ራሱን አግቶ ከቤተሰቦቹ ገንዘብ የጠየቀው በቁጥጥር ስር ዋለ

በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ምስራቅ ደንቢያ ወረዳ ጋና ዮሀንስ ቀበሌ ለቤተሰቦቹ ታግቻለሁ በማለት ብር እንዲከፈል ተጠይቆ ቤተሰቦቹ ብሩን ለመስጠት አይከል ከተማ ድረስ ተጉዘው ብሩን በተጠየቁበት አግባብ ሊሰጡ ሲል በፖሊስ በተደረገ ክትትል ሊቀበል ሲወጣ እጅ ከፍንጅ ሲያዝ ታግቻለሁ ያለው እራሱ ሆኖ ተገኝቷል።

#ዳጉ_ጆርናል

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

17 Jan, 18:41


የጣርያና ግድግዳ ግብር  ሕገ ወጥ ነው ተባለ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የጣሪያ ግድግዳ/የንብረት ግብር ብሎ ከከተማዋ ነዋሪ እየሰበበሰበ ያለው ግብር ሕገ ወጥ ነው በሚል የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ውሳኔ ሰጠ።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የጣሪያ ግድግዳ/የንብረት ግብር ብሎ ከከተማዋ ነዋሪ እየሰበበሰበ ያለው ግብር "ሕገ ወጥ መኾኑን" በመግለጽ እናት ፓርቲ ክስ መመሥረቱን አስታዉሶ ክሱን የተመለከተው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎት ዛሬ ጥር 9 ቀን  2017 ዓ.ም. ባስቻለው ችሎት የንብረት ግብር ማሻሻያ ጥናት ተብሎ ሚያዝያ 3 ቀን 2015 ዓ.ም. የወጣውና "ለግብሩ መሰብሰብ መሠረት የሆነው መመሪያ ተፈጻሚነት ሊኖረው አይገባም" ተብሎ መመሪያው እንዲሻር በሙሉ ድምጽ ወስኖልኛል ሲል እናት ፓርቲ በማህበራዊ ገፁ አስታውቋል::

#ዳጉ_ጆርናል

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

17 Jan, 18:41


በጥምቀት በዓል መዳረሻ በርካታ ወጣቶች በአዲስ አበባ ከተማ እየታፈሱ መሆኑ ታወቀ

በአዲስ አበባ ከተማ በርካታ ስፍራዎች በተለይ በደማቁ የጥምቀት በአል ወቅት ንቁ ተሳትፎ በማድረግ የሚታወቁ ወጣቶች እየታፈሱ መሆኑ ታውቋል።

እንደ ሽሮ ሜዳ፣ ፈረንሳይ፣ ካዛንችስ፣ ሳሪስ፣ አዋሬ ወዘተ ባሉ ስፍራዎች የሚገኙ ወጣቶች በብዛት በቁጥጥር ስር እየዋሉ ነው።

ሽሮ ሜዳ አካባቢ ትናንት ማታ ከ30 በላይ ወጣቶችን የሽሮ ሜዳ ፖሊስ አፍሶ እንደወሰዳቸው የአይን እማኞች ተናግረዋል። ወጣቶቹ የቤተክርስቲያን ጥምቀት አስተባባሪዎች እና ምንጣፍ የሚሸከሙ ልጆች መሆናቸው ታውቋል።

በሌላ በኩል በዛሬው እለት ሳሪስ አዲስ ሰፈር እና ብሄረ ፅጌ አካባቢ ለጥምቀት በአል የተሰቀሉ ማስዋቢያዎችን ፖሊስ በሀይል ያነሳ ሲሆን ሰቅላችኋል የተባሉ አንዳንድ ወጣቶችም እንደታሰሩ ታውቋል።

ከዚህ በፊት በየመንገዱ የሚሰቀሉ እና የኦርቶዶክስ አርማ ያለበት ባንዲራ ጭምር በፖሊስ በበርካታ ስፍራዎች እንዲወርድ እየተደረገ መሆኑን ሰምተናል።

ማምሻውን ከፖሊስ ምላሽ ለማግኘት ያረግነው ሙከራ አልተሳካም።

ፎቶ: ፋይል

መሠረት ሚዲያ

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

17 Jan, 18:40


' ቲክቶክ ' አሜሪካ ውስጥ ከእሁድ ጀምሮ እስከ ወዲያኛው እንዲዘጋ ወይም እንዲሸጥ የሚለውን ውሳኔ የአሜሪካ ጠቅላይ ፍ/ቤት ደገፈ።

ዛሬ የአሜሪካ ጠቅላይ ፍ/ቤት ' ቲክቶክ ' በአሜሪካ እንዲዘጋ ካልሆነም እዲሸጥ ለሚጠይቀው የፌደራል ህግ ድጋፍ ሰጥቷል።

' ቲክቶክ ' ይግባኝ ቢጠይቅም ውድቅ ሆናል።

ከዚህ ቀደም መተግበሪያው " የአሜሪካውያንን የግል መረጃ ለቻይና መንግሥት አሳልፎ ይሰጣል በዚህ የብሔራዊ ጸጥታ አደጋ ደቅኗል "  በሚል እንዲታገድ ካልሆነም ለአሜሪካ ሰዎች እንዲሸጥ የሚል ውሳኔ መተላለፉ ይታወሳል።

ዛሬ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከዚህ ቀደም የተላለፈውን ውሳኔ ደግፏል።

ይህን ውሳኔ ተከትሎ ' ቲክቶክ ' ከእሁድ ጀምሮ ይታገዳል።

የእግዱ ተግባራዊነት ' ቲክቶክ 'ን ከአፕስቶር እና ፕሌይስቶር ላይ እንዲወገድ ያደርጋል።

አዲስ ተጠቃሚዎች ' ቲክቶክ ' ማውረድ አይችሉም ፤ ነባር ተጠቃሚዎች አፕዴት ማድረግ አይችሉም።

ተመራጩ ፕሬዜዳንት ዶናልድ ትራምፕ ' ቲክቶክ ' ን ለመታደግ እና የመታገዱ ውሳኔ እንዲዘገይ ለጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ጠይቀው የነበረ ቢሆንም ፍርድ ቤቱ ግን የመጨረሻ ያለውን ውሳኔ አሳልፏል።

እንሆ ስልጣኑ ያበቃው የባይደን አስተዳደር " ህጉን ማስተግበር የቀጣዩ አስተዳደር ኃላፊነት ነው " ብሏል።

የ' ቲክቶክ ' ን እገዳ ለማዘግየት የሞከሩት ትራምፕ ሰኞ ስልጣናቸውን ይረከባሉ። ህጉን ማስተግበርም በሳቸው ላይ ተጥሏል።

ትራምፕ ከፍርድ ቤቱ ውሳኔ በኃላ በሰጡት ቃል " ውሳኔውን እኔው ወስናለሁ ፤ ውሳኔው እኔ ጋር ነው ምን እንደማደርግ ታያላችሁ " ብለዋል።

170 ሚሊዮን ተጠቃሚ አሜሪካ ውስጥ ያለው ' ቲክቶክ ' እስከወዲያኛው ይታገድ ይሆን ? ወይስ ከዚህ በኃላ ትራምፕ ማድረግ የሚችሉት ነገር ይኖር ይሆን ? በቀጣይ ይታያል።

[መረጃውን ከተለያዩ ምንጮች ሰብስቦ የዘገበው ቲክቫህ ኢትዮጵያ ነው]

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

17 Jan, 18:40


#TPLF

" የኢትዮጵያ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ የተናጠል ውሳኔን ዛሬ ይሁን ነገ አልቀበልም " - በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር ) የሚመራው ህወሓት ማእከላይ ኮሚቴ

በደብረጽዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው የህወሓት ማእከላይ ኮሚቴ ከጥር 5 እስከ ጥር 7 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ በወቅታዊ የክልሉ ሁኔታ ላይ አተኩሮ ስብሰባ ተቀምጦ ነበር።

ይህንን ተከትሎ ዛሬ ምሽት መግለጫ አውጥቷል።

በዚህም ቡድኑ ፦
- እስከ አሁን ያልተረጋገጠው የትግራይ ግዛታዊ አንድነት፤
- ተፈናቃዮች እና ስደተኞች ወደ ቄያቸው አለመመለስ፤
- የኢትዮጵያ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ ያወጣውን መግለጫ፤
- የፕሪቶሪያ የሰላም ውል አፈፃፀም በሚሉ አጀንዳዎች ላይ መወያየቱን ገልጾ " ቀጣይ የመፍትሄ እና የትግል አቅጣጫ አስቀምጫለሁ " ብሏል።

የህወሓት ማእከላዊ ኮሚቴ ባወጣው መግለጫ ፤ በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት መሰረት የኢፌዴሪ ህገ-መንግስት እውቅና የሰጠው የትግራይ ግዛታዊ አንድነት አለመረጋገጡ ጠቅሶ " ተፈናቃይ እና ስደተኞች ወደ ቄያቸው ባለመመለሳቸው ሃዘን እና ቁጣ ተስምተኞናል ይህንን አስመልክቶ ' ይበቃል ' በሚል የተካሄደው ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ እደግፋለሁ " ብሏል።

ቡድኑ በመግለጫው " የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በአግባቡ እንዳይፈፀም የኢትዮጵያ መንግስት እንቅፋት እየሆነ ነው ፡ በትግራይ ውስጥ የበቀለ
#ከሃዲ_ሃይልም በተጨማሪ ስምምነቱ እያደናቀፈ ነው " የሚል ክስ አሰምቷል።

እንዴት እንደሆነ ባያብራራም " ችግሩ ከስር መሰረቱ ለመለወጥ ቆርጬ ተነስቻለሁ " ብሏል።

በመሰረተ ሃሳብ ደረጃ DDR ተቀባይነት ያለው እንደሆነ የገለፀም ሲሆን " ይሁን እንጂ DDR እንደምክንያት በመጠቀም የትግራይ ሰራዊት ለማፍረስ እየተደረገ ያለው ሴራ ተቀባይነተ የለውም " ሲል ገልጿል።

የኢትዮጵያ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ ህወሓት ህጋዊ ጉባኤ እንዲያካሂድ በማስመልከት በቅርቡ ያወጣው ቀን ገደብ ያካተተ መግለጫ አስመልክቶ በሰጠው ምላሽ ፥ " ቦርዱ ' ጉባኤ አካሂዱ ' የሚል ጨምሮ በተንኮል የተተበተቡ የተለያዩ  ትእዛዞች ከመስጠት ተቆጥቦ የተፈጠሩ ልዩነቶች  በፓለቲካዊ ውይይት ለመፍታት የተጀመረው ጥረት በማስቀጠሉ ላይ ያተኩር "  ብሏል።

" ህወሓት ሁሌም ለሁለትዮሽ ውይይት ዝግጁ ነው ፤ የትግራይ ህዝብ ትግል እና መስዋእትነት የሚያራክስ የኢትዮጵያ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ የተናጠል ውሳኔ ግን ዛሬ ይሁን ነገ አልቀበልም " ሲል አቋሙን አንጸባርቋል።

ህወሓት ጊዚያዊ አስተዳደሩ በማቋቋም የአንበሳ ድርሻ እንደነበረው እና እንዳለው የጠቀሰው መግለጫው " አሁንም እንዲጠናከር ይሰራል ይሁን እንጂ ጊዚያዊ አስተዳደሩ ለማጠናከር እና ለመቆጣጠር በሚል ይቋቋማል የሚባለው ካውንስል አካል መሆን አልፈግም " ሲል ግልፅ አድርጓል።

በሊቀመንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር ) የሚመራው ህወሓት ማእከላይ ኮሚቴ በመግለጫው ማጠቃለያ ፤ " የኢትዮጵያ መንግስት ከጣልቃ ገብነት ተቆጥቦ የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በቅን ልቦና በመፈፀም ለዘላቂ ሰላም እንዲሰራ " የሚል ጥሪ አቅርበዋል። 

የህወሓት ቡድን ለሁለት ተከፍሎ የለየለት አለመግባባት ውስጥ ከገባ ወራት የተቆጠሩ ሲሆን ከወራት በፊት ለሁለት የተከፈሉት አመራሮች እና የጊዜያዊ አስተዳደሩ አመራሮች አዲስ አበባ ሄደው ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ውይይት አድርገው ነበር።

ወደ መቐለ ከተመለሱ በኃላ ግን እስከ ዛሬ መግባባት ሳይፈጥሩ በመግላጫ ምልልስ ላይ ናቸው።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ደግሞ ህወሓት በልዩ ሁኔታ የተመዘገበው ነሀሴ 3 ቀን 2016 ዓ.ም መሆኑን በመግለጽ ጠቅላላ ጉባኤውን እስከ የካቲት 3 ቀን 2017 ዓ.ም እንዲያደርግ አሳስቧል።

ይህ በሕግ ፓርቲው ላይ የተጣለ ግዴታ በወቅቱ ሳይፈፀም ቢቀር ቦርዱ ሕጉን መሠረት በማድረግ ተገቢ ነው የሚለውን ውሳኔ የሚሰጥ መሆኑንም ገልጾ ነበር።

ከዚህ ቀደም የህወሓት አመራሮችን ለሁለት የከፈለ ጉባኤ መደረጉ አይዘነጋም። በወቅቱም ምርጫ ቦርድ ያልተገኘበትን እና ስርዓቱን ያልተከተለ ጠቅላላ ጉባኤ እውቅና እንደማይሰጥ ማስገንዘቡ ይታወሳል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

17 Jan, 18:39


የአዲስ አበባ ፖሊስ ለከተራ እና ለጥምቀት በዓል የሚዘጉ መንገዶችን ይፋ አደረገ

የአዲስ አበባ ፖሊስ ለከተራ እና ለጥምቀት በዓል የሚዘጉ መንገዶችን ይፋ አድርጓል።

ፖሊስ ከጥር 10 እስከ ጥር 12 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ ጃን ሜዳ እና አቃቂ ቃሊቲ ታቦት ማደሪያ በሚከበረው የከተራና የጥምቀት በዓል ምክንያት የትራፊክ መጨናነቅ እንዳይፈጠር የተወሰኑ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ ስለሚሆኑ አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ አሳስቧል።

ከጥር 10 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በ11ዱም ክፍለ ከተሞች ጥምቀተ ባህር ባሉባቸው ቦታዎች ሁሉ በ500 ሜትር ክልል ውስጥ ታቦታት ሲወጡና ሲገቡ እንዲሁም በሚሄዱባቸው መንገዶች ለአጭር ጊዜም ይሁን ለረዥም ጊዜ ተሽከርካሪ አቁሞ መሄድ የተከለከለ መሆኑን ፖሊስ አስታውቋል።

እንዲሁም ከጥር 10 እስከ ጥር 12 ቀን 2017 ዓ/ም ድረስ በጃን ሜዳ እና አቃቂ ቃሊቲ ታቦት ማደሪያ በሚከበረው የከተራና የጥምቀት በዓል ምክንያት በአካባቢው የትራፊክ መጨናነቅ እንዳይፈጠር፦

ከ6 ኪሎ አደባባይ - ምኒልክ ሆስፒታል

ከምኒልክ ሆስፒታል - መከላከያ 3ኛ ሻለቃ አደባባይ

ከ3ኛ ሻለቃ አደባባይ - 6 ኪሎ አደባባይ እንዲሁም አቃቂ ቃሊቲ አካባቢ

ከዋልያ ቢራ - ጥሩነሽ ቤይጂንግ ሆስፒታል

ከአቃቂ ዋናው መንገድ - ጥሩነሽ ቤይጂንግ ሆስፒታል

ከ08 - አቃቂ ድልድይ ድረስ ከጥር 10 ቀን 2017 ዓ/ም ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት ጀምሮ መንገዱ ለተሽከርካሪዎች ዝግ ስለሚሆን አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገዶችን መጠቀም እንደሚገባቸው የአዲስ አበባ ፖሊስ መልዕክቱን አስተላልፏል።

በዓሉ የሠላምና የፍቅር እንዲሆን መልካም ምኞቱንም ገልጿል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

16 Jan, 13:22


ሕብረተሰቡ "በካናዳ የሥራ እና ትምህርት ዕድል ለማመቻቸት ሕጋዊ ውክልና ተሰጥቶናል" ከሚሉ አጭበርባሪዎች ራሱን እንዲጠብቅ ማሳሰቢያ ተሰጠ

በካናዳ የሥራ እና ትምህርት ዕድል ለማመቻቸት ሕጋዊ ውክልና በውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞትዮስ (ዶ/ር) የተሰጣቸው በማስመሰል ሕገ ወጥ ደብዳቤ አዘጋጅተው እያሰራጩ ያሉ አካላት መኖራቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡

የሚኒስትሩ ሥም ተጠቅሶ በተለያዩ የማህበራዊ ሚድያ አውታሮች እየተዘዋወረ የሚገኘው ደብዳቤ ሀሰተኛ መሆኑንም ገልጿል።

እንዲህ አይነቱን የወንጀል ተግባር እየፈፀሙ የሚገኙ አካላትን በሕግ ተጠያቂ ለማድረግ ከሚመለከታቸው ጋር እየተሰራ መሆኑን ሚኒስቴሩ አመላክቷል።

ሕብረተሰቡም ይህንን ተገንዝቦ ራሱን ከአጭበርባሪዎች እንዲጠብቅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አሳስቧል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

16 Jan, 08:54


ማይክሮሶፍት የዊንዶውስ 10 ተጠቃሚዎች ወደ ዊንዶውስ 11 እንዲያሻሽሉ በጥብቅ አሳሰበ
💻💻💻💻💻💻💻💻🖥🖥🖥🖥🖥🖥🖥🖥🖥🖥🖥🖥
ዊንዶውስ 10 እና ዊንዶውስ 11 በንድፍ፣ በአፈጻጸም እና በባህሪያት ከፍተኛ ልዩነት አላቸው። የትኛውን ፍላጎትዎን በተሻለ ሊያሟላ እንደሚችል ለመወሰን እንዲረዳዎ በንፅፅር እንይ:

1. 💻💻የተጠቃሚ እይታ (UI) እና ዲዛይን
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
ዊንዶውስ 10፡ በስተግራ በኩል የተስተካከለ ባህላዊ ዝርዝር ወይም ንድፍ ያለው። የማስጀመርያ ሜኑ የቀጥታ ዝርዝሮች ያለው ሲሆን፣ ይህም ለረጅም ጊዜ የዊንዶውስ ተጠቃሚዎች የበለጠ የተለመደ ያደርገዋል።
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
ዊንዶውስ 11፡ ዘመናዊ እና አነስተኛ ዝርዝር ሜኑ ወይም ንድፍ የያዘ ለማስጀመር ብቻ በተግባር እንዲያገለግል የተሰራ ሜኑ ወይም ንድፍ አለው።

2. 💻💻አፈጻጸም
👇👇👇👇👇👇
👉👉ዊንዶውስ 10: በአሮጌ ሃርድዌር ላይ በደንብ ይሰራል እና በዝቅተኛ መሳሪያዎች ወይም ሃርድዌር ላይ የተረጋጋ አፈፃፀም ያሳያል በዘመናዊ ሃርድዌር ላይ ይህ የተረጋጋ አፈፃፀም አይታይም። ቡዙ ስራዎች ባአንድ ላይ ማከናወን አይችልም።

👉👉 ዊንዶውስ 11፡ ለዘመናዊ ሃርድዌር የተሻሻለ እንደ ማጫወቻ ወይም ጌም ወይም ምስል ቪድዮ ኢድቲንግ፣ መተግበሪያ ማስጀመሪያዎች ወይም ሜኑ እና ብዙ ስራዎች ባአንድ ላይ ያከናውናል። እንደ DirectStorage ያሉ ባህሪያት የጨዋታ ጭነት ጊዜን ይቀንሳሉ፣ ነገር ግን በአሮጌ መሳሪያዎች ወይም ሃርድዌር ላይ በብቃት ኣይሰራም።

3.💻💻 የሃርድዌር መስፈርቶች

👉👉ዊንዶውስ 10፡ ከብዙ ሃርድዌር ጋር ተኳሃኝ፣ ይህም ለአሮጌ መሳሪያዎች ጥሩ ምርጫ ያደርገዋል።

👉👉 ዊንዶውስ 11፡ TPM 2.0፣ Secure Boot እና አዲስ ሲፒዩዎችን ጨምሮ አዲስ ሃርድዌር ይፈልጋል፣ ይህም ከአሮጌ መሳሪያዎች ጋር ያለውን ተኳሃኝነት ሊገድብ ይችላል።

4. 💻💻ማጫዋቻ ወይም ጌሚግ ሲስተም

👉👉ዊንዶውስ 10፡ አብዛኞቹን የጨዋታ ባህሪያትን ይደግፋል ነገር ግን እንደ ራስ ኤች ዲ አር ያሉ የላቁ ቴክኖሎጂዎች የሉትም።

👉👉ዊንዶውስ 11፡ ለተሻሻሉ እይታዎች እና ፈጣን የመጫኛ ጊዜዎች እንደ Auto HDR እና Direct Storage ያሉ ባህሪያት ያካተተ ሲሆን ለምን ፈልገው ምስል ማጫዋቻ የተሻለ ነው። እንዲሁም Xbox Game Passን በተሻለ ሁኔታ ያዋህዳል።
5. 💻💻ባህሪያት

👉👉 ዊንዶውስ 10፡- ምንም አይነት የአንድሮይድ መተግበሪያ ድጋፍ የለውም።

👉👉ዊንዶውስ 11፡- በAmazon Appstore በኩል የአንድሮይድ መተግበሪያዎችን ይደግፋል።

👉👉 ለተሻሻለ ባለብዙ ተግባር የSnap Layouts ይሰጣል።

👉👉 ከማይክሮሶፍት ቡድኖች ጋር የተሻለ ውህደት ይፈጥራል።

👉👉የተሻሻለ ምናባዊ የዴስክቶፕ ድጋፍ ያስገኛል።

6. 💻💻ተከታታይ ያለው የመዘመኛ ድጋፍ update system support

👉👉 ዊንዶውስ 10፡ ዋናው ድጋፍ ኦክቶበር 14፣ 2025 ያበቃል፣ ይህ ማለት በደህንነት ላይ ያተኮሩ ድጋፍ ያቆማል ማለት ነው ። no update system

👉👉 ዊንዶውስ 11፡ አዳዲስ ባህሪያት እና ማሻሻያዎች በዋናነት በዚህ ስሪት ወደፊት መሄዱ ላይ ያተኩራል
💻💻💻💻💻💻💻💻💻💻💻💻💻💻💻💻
በዚህም ምክንያት ማይክሮሶፍት 2025ን "የዊንዶውስ 11 ፒሲ ማደስ አመት" ብሎ አውጇል ይህም ተጠቃሚዎችን ከዊንዶውስ 10 ለማሸጋገር ትልቅ ግስጋሴ መሆኑን ያሳያል። በጥቅምት ወር የሚያበቃው የዊንዶውስ 10 ድጋፍ ተጠቃሚዎቹ አዲሱን ኦፕሬቲንግ ሲስተም እንዲቀበሉ ለማድረግ ኩባንያው ጥረቱን እያጠናከረ ነው። እ.ኤ.አ. በ 2024 ማይክሮሶፍት የሙሉ ስክሪን ማሻሻያ ጥያቄዎችን አሰማርቷል ፣ እና አሁን የቆዩ ፒሲዎችን ከዊንዶውስ 11 ሙሉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ የማደስ አስፈላጊነት ላይ አፅንዖት ሰጥቷል።

👉👉ባለፈው ዓመት፣ ማይክሮሶፍት 2024ን “የ AI ፒሲ ዓመት” ብሎ ሰይሞት ነበር፣ በኮፒሎት ፕላስ የተጎለበተ ፒሲዎች አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ከዕለታዊ ኮምፒውተር ጋር መቀላቀላቸውን አሳይተዋል። በዚህ ሳምንት በተካሄደው የሸማቾች ኤሌክትሮኒክስ ሾው (ሲኢኤስ) ማይክሮሶፍት ትኩረቱን አጠናክሮ የዊንዶው 10 ፒሲ ማሻሻል በ2025 አዲስ ቲቪ ወይም ስማርት ስልክ ከመግዛት የበለጠ ጠቃሚ መሆኑን አስረግጦ ተናግሯል።

👉👉ማይክሮሶፍት እ.ኤ.አ. ከጥር 10/2023 ጀምሮ ለዊንዶውስ 8.1 ሁሉንም የደህንነት ዝመናዎች እና ቴክኒካዊ ድጋፎች ማቆሙን አስታውቆ ነበር። በተመሳሳይ የዊንዶውስ 7 ድጋፍ በጥር 14/2020 ማብቃቱ ይታወሳል። አሁን ደግሞ የዊንዶውስ 10 ድጋፍ እ.ኤ.አ. ከጥቅምት 14/2025 ጀምሮ እንደሚያቆም ማይክሮሶፍት ገልጿል። ይህም እነዚህ ኦፕሬቲንግ ሲስተሞች ከተጠቀሰው ጊዜ በኋላ ሁሉንም አይነት ዝመናዎችን ስለማያገኙ ለደህንነት ስጋቶች ተጋላጭ ይሆናሉ።

በአሁኑ ጊዜ ዊንዶውስ 7ን፣ ዊንዶውስ 8.1ን ወይም ዊንዶውስ 10ን ለሚጠቀሙ ስርዓቶች፡-
👉👉• ኮምፒውተርዎ ዊንዶውስ 11ን ለመጫን አነስተኛ መስፈርቶችን የሚያሟላ መሆኑን እንዲያረጋግጡ፤
👉👉• በዊንዶውስ ዝመና ውስጥ ያለውን የማሻሻያ አማራጭ እንዲከተሉ፤
👉👉• ኮምፒውተርዎ መስፈርቶቹን የማያሟላ ከሆነ ወይም ምትክ የሚያስፈልገው ከሆነ ዊንዶውስ 11ን ወደሚደግፍ አዲስ ኮምፒውተር ለመሸጋገር የሚያስችልዎትን አማራጭ እንዲወስዱ ማይክሮሶፍት በሰጠው ማሳሰቢያ ገልጿል፡፡

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

15 Jan, 19:51


በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ ነዳጅ ማደያዎችን ወደ ኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች የኃይል መሙያ ጣቢያ ለመቀየር ጥናት እየተደረገ ነው ተባለ።

ይህንን ያሉት የአዲስ አበባ ከተማ ትራንስፖርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ ወርቁ ደስታ ናቸው፡፡

ከዚህ በተጨማሪ " በሁለተኛው ምዕራፍ እየተከናወነ ባለው የኮሪደር ልማት በመኪና ማቆሚያዎች የኃይል መሙያ እየተሠራ ነው " ሲሉ ተደምጠዋል።

የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ዴዔታ በርኦ ሀሰን፥ ደግሞ " ከዚህ በኃላ የተሽከርካሪ አስመጪና የሚገጣጥሙ ድርጅቶች የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ የኃይል መሙያ ሳይተክሉ በሥራ ላይ መሰማራት አይችሉም " ብለዋል።

" አሁን ላይ ከ400 በላይ ተቋማት የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ እያስመጡና እየገጣጠሙ ናቸው " ያሉ ሲሆን ሁሉም የኃይል መሙያ አላቸው " ሲሉ ገልጸዋል።

ኤፍኤምሲ

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

15 Jan, 19:50


ቪድዮ  ፦ #ሀማስ እና #እስራኤል የተኩስ አቁም ለማድረግ መስማማታቸው መነገሩን ተከትሎ ፍልስጤማውያን ደስታቸውን ለመግለፅ በጋዛ አደባባይ ወጥተዋል።

" አላሁ አክበር ! አላሁ አክበር ! " ይህ በስምምነቱ መረጃ የተደሰቱ ፍልስጤማውያን ድምፅ ነው።

በርካቶች የሰላም ወሬ በመንፈሱ በደስታ አልቅሰዋል ፤ አንብተዋል ፤ ፈጣሪ ቀጣዩን ጊዜ ደግሞ የሰላም ያደርግላቸው ዘንድ ተማፅነዋል።

ፍልስጤማውያን ስምምነቱን ተከትሎ እስራኤል የያዘቻቸውን ያሰረቻቸውን ወገኖቻቸውን ትፈታለች ብለው ተስፋ አድርገዋል።

በአስከፊው ጦርነት እጅግ በርካታ ፍልጤማውያን ህጻናት፣ ሴቶች፣ እናቶች ፣ አዛውንቶች አልቀዋል። ላለፉት 15 ወራት የሰቀቀን ህይወት ሲገፉም ነበር።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

15 Jan, 17:03


ፍርድ ቤቱ "ተማሪዎች ሒጃባቸውን ለብሰው ወደ ትምህርት ገበታቸው ይመለሱ" በሚል ውሳኔ አሳለፈ

#Ethiopia | የአክሱም ወረዳ ፍርድ ቤት ሂጃብ መልበስ የሚከለክለው መመሪያ ላይ ዕገዳ ጣለ፤ በሂጃብ ምክንያት ተማሪዎችን ያገዱ ትምህርት ቤቶች ፍርድ ቤት እንዲቀርቡም አዟል!

የትግራይ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት በአክሱም ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ሒጃብ ለብሰው እንዳይማሩ አስተዳደራዊ እግድ ባደረጉ 5 ትምህርት ቤቶች ላይ ክስ መመስረቱ ይታወቃል።

ጉዳዩ በዛሬው ዕለት የአክሱም ከተማ ወረዳ ፍርድ ቤት ቀርቦ ውሳኔ ተስጥቶበታል። ፍርድ ቤቱ አስተዳደራዊ እግድ ባደረጉ ትምህርት ቤቶች ላይ እግድ ጥሏል።

ጉዳዩ በተማሪዎቹ ላይ የማይቀለበስ የሰብአዊ መብት ጉዳት ሊያደርስ ስለሚችል ተማሪዎቹ ሒጃባቸውን ለብሰው ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዲመለሱ የሚል ውሳኔ አስተላልፏል።

በሂጃብ ምክንያት ተማሪዎችን ያገዱ ትምህርት ቤቶች ለጥር 16/2017 ፍርድቤት ቀርበው ቃላቸውን እንዲሰጡ ትእዛዝ ተሰጥቷል።

በተያያዘ ዜና የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት በሰጠው ማሳሰቢያ ፥ የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ምዝገባ ዛሬ ጥር 6/2017 ዓ.ል ከቀኑ 11፡00 ሰዓት ላይ ተጠናቋል።

የአክሱም ሁለተኛ ደረጃ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ለመሳተፍ የሚያስችላቸው ፎርም ሳይሞሉ የተሰጠው የምዝገበ ቀነ ገደብ ዛሬ መጠናቀቁን አስታውሶ የዘገበው ሃሩን ሚዲያ ነው።

የአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ይህንንና መሰል ጉዳዮችን በንቃት ይከታተላል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

14 Jan, 09:15


የአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ መምህሩ ሳምሶን መኮንን (ዶ/ር) የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሆነው ተሾሙ

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሳምሶን መኮንን (ዶ/ር) በአቶ መሐመድ እድሪስ ምትክ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር እንዲሆኑ የቀረበለትን ሹመት አፀደቀ።

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ መምህር፣ የኮሚኒኬሽን እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ምክትል ፕሬዚዳንት እንዲሁም በዩንቨርስቲው የማርኬቲንግና ኮሚኒኬሽን ረዳት ፕሮፌሰር የሆኑትን ሳምሶን መኮንን (ዶ/ር) የባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር እንዲሆኑ በእጩነት አቅርበዋል።

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 15ኛ መደበኛ ጉባዔ ሳምሶን መኮንን (ዶ/ር) የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሆነው እንዲሾሙ የቀረበለትን ጥያቄ አፅድቋል።

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር የነበሩት አቶ መሐመድ እድሪስ የሰላም ሚኒስትር ሆነው መሾማቸው ይታወቃል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

10 Jan, 19:37


ወጋገን ባንክ የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ ላይ በቀዳሚነት የተመዘገበ ኩባንያ ሆነ

ወጋገን ባንክ አክሲዮኑን በማስመዝገብ ወደ ገበያ ለማውጣት የሚያስችለውን ታሪካዊ እርምጃ መዉሰድ ችሏል።

ይህ የተገለጸው የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ አዲስ አበባ በሚገኘው የሳይንስ ሙዚየም ጥር 2 ቀን 2017 ዓ.ም ባዘጋጀው የተደራጀ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ ይፋዊ የማስጀመሪያ ስነ-ስርዓት ላይ ሲሆን በዚህም በገበያው ላይ በቀዳሚነት የተመዘገበ ኩባንያ መሆን መቻሉን አረጋግጧል።

ባንኩ በኢትዮጵያ በገበያው ላይ በመመዝገቡ ከተለምዷዊ የአክሲዮን መሸጫ ዘይቤዎች ወደ ዘመናዊ እና ቴክኖሎጂ ተኮር አማራጮች በመሸጋገር ተጨማሪ ካፒታል ለመሰብሰብ እንደሚያስችለዉ አስታውቋል።

Capital Newspaper

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

10 Jan, 17:18


ያልተለመዱ እና በከፍተኛ ፍጥነት ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የቁስ አካላት ስብስቦች ሺ ጂያን-19 የተባለ ሳተላይት ቀሪ አካል ሊሆን እንደሚችል ተነገረ

የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ ሶሳይቲ በትናንትናው ዕለት ምሽት 1:30 ሰዓት ገደማ አካባቢ በከፍተኛ ፍጥነት ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ባለቤትነቱ የቻይና የሆነ ሺ ጂያን-19 የተባለ ሳተላይት ቀሪ አካል ሊሆን እንደሚችል አገኘሁት ባለዉ መረጃ በመመርኮዝ አስታውቋል ።

እንደ ተቋሙ ከሆነ ሳተላይቱ በ መስከረም 17 2017 ዓ.ም ወደ ምህዋር የተወነጨፈ ሲሆን ተልዕኮውን ጨርሶ በ ጥቅምት 1 2017 ዓ.ም  ወደ መሬት ተመልሷል።

ነገር ግን ሳተላይቱ በተልዕኮው ላይ ሲገለገልባቸው የነበሩ የተለያዩ ክፍሎቹ ከዋናው ሳተላይት ተነጥለው በምህዋር ላይ ሲዞሩ መቆየታቸውን ጠቅሷል።

ከተለያዩ የሕዋ አካላት መከታተያ እና የመረጃ ቋቶች ያገኛቸዉን መረጃዎችን ዋቢ ያደረገው ተቋሙ የተረጋገጠ መረጃውን የሳተላይቱ ባለቤት ሃገር ቻይና እስክታረጋግጥ መጠበቅ ይኖርብናል ብሏል።

በትላንትናዉ ዕለት አመሻሽ ላይ በደቡብ እና ደቡብ ምዕራብ የሀገሪቱ ክፍሎች በሰማይ ላይ እየተቀጣጠሉ በከፍተኛ ፍጥነት ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የቁስ አካላት ስብስብ መታየታቸው ይታወቃል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

10 Jan, 16:40


በኢትዮጵያ በይፋ የአክሲዮን ግብይት ተጀምሯል

የኢትዮጵያ የሰነድ ሙዓለ ንዋይ ገበያ ዛሬ ዓርብ የአክሲዮን ሽያጭና ግዢ ግብይቱን በይፋ መጀመሩን አስታውቋል ።

የአክሲዮን ገበያ ሥራውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ በይፋ ያስጀመሩት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ "በጉጉት ሲጠበቅ የቆየው የሰነድ ሙዓለ ንዋይ ግብይት በዛሬው ዕለት ጥር 2 ቀን 2017 ዓ.ም የመጀመሪያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ ደወል ደውለናል" ብለዋል።

የሰነድ ሙዓለ ንዋይ ገበያው ዋና ዳይሬክተር ጥላሁን ካሳሁን በቀጣዮቹ ዓመታት ውስጥ 50 ያህል ኩባንያዎች በዚህ ገበያ ላይ የአክሲዮን ድርሻዎችን ለግብይት እንደሚያቀርቡ ጠይቀዋል ።

በተለምዶ ክፍት ገበያ በመባል የሚታወቀው የሰነደ መዋዕለ ንዋይ ገበያ የተማከለ የፋይናንሺያል ገበያን የሚያመለክት ሲሆን የተዘረዘሩ ኩባንያዎችን የዋስትና ሰነዶች፣ኮሞዲቲዎች ጨምሮ በአክሲዮን ሻጮች እና ገዥዎች መካከል የሚገዙበት እና የሚሸጡበት ማዕከል መሆኑ ይታወቃል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

08 Jan, 13:54


መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ያደረጉ ዲፕሎማቶች ለመንግሥት ሳያሳውቁ ከከተማ እንዳይወጡ ደብዳቤ ተላከላቸው

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መቀመጫውቸን በአዲስ አበባ ላደረጉ ዲፕሎማቶች ለመንግሥት ሳያሳውቁ ከከተማ እንዳይወጡ ማሳሰቢያ ሰጠ፡፡

ሪፖርተር የተመለከተውና ከአንድ ሳምንት በፊት በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በኩል ለዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ የተላከው ደብዳቤ እንደሚያስረዳው፣ ዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ ድርጅቶች በአገሪቱ ድንበር ውስጥ ለሚያደርጓቸው ማናቸው እንቅስቃሴዎች ቅድመ ፈቃድ እንዲጠይቁ አሳስቧል፡፡

በአዲስ አበባ ለሚገኙ ዓለም አቀፍና ቀጣናዊ ተቋማት፣ ዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ ድርጅቶችና መንግሥታዊ ያልሆኑ ዓለም አቀፍ ተቋማት፣ ከአዲስ አበባ ውጭ የሚያደርጓቸውን ጉዞዎች በተመለከተ በሚኒስቴር መሥሪያ ቤት በተቀመጠ የቅድሚያ ማሳወቂያ ፎርም ከሞሉ በኋላ መሆን እንዳለበት አመላክቷል፡፡

ይሁን እንጂ ለዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ የተጻፈው ደብዳቤ ማስጠንቀቂያው ለሥራ ወይም ለግል ጉዳይ የሚጓዙትን እንደሆነ በግልጽ አያስረዳም፡፡

ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ እንደሚያስረዳው ከዚህ ተመሳሳይ ድበዳቤ ተጽፎ የነበረ ቢሆንም፣ አንዳንድ ዲፕሎማቶች አሁንም ከፌዴራል መንግሥቱ ዕውቅና ውጭ ሲንቀሳቀሱ በመገኘቱ እንደሆነ ተገልጿል፡፡

ከዓመት በፊት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሪፖርቱን ባቀረበበት ወቅት፣ ክልሎች በአገሪቱ ሕገ መንግሥት ለፌዴራል መንግሥቱ ብቻ በተሰጠው የውጭ ግንኙነት ሥራ ላይ እየተሳተፉ በመሆኑ ፓርላማው ማሳሰቢያ እንዲሰጥ ተጠይቆ ነበር፡፡

ምንጭ: ሪፖርተር

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

08 Jan, 08:45


ዩናይትድ ስቴትስ ሩሲያ ሁለቱንም የሱዳን ተፋላሚዎች በገንዘብ እየደገፈች ነው ስትል ከሰሰች!

"ሩሲያ ሱዳን ውስጥ የሚዋጉትን ሁለቱን ወገኖች በገንዘብ ትደግፋለች" ስትል ዩናይትድ ስቴትስ ትላንት ሰኞ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ከሳታለች፡፡ ይህም ሞስኮ የራሷን የፖለቲካ ዓላማ ለማሳካት ሁለቱንም ወገኖች ደጋፊያቸው እየመሰለች መጫወት ይዛለች የሚለውን የቀደመውን ዋሽንግተን ድምዳሜ ከፍ ያደረገ ሆኖ ታይቷል፡፡

በሱዳን ጦር ኃይሎች እና በፈጥኖ ደራሽ ቡድኑ መካከል በጎርጎርሳውያኑ ሚያዚያ 2023 የተጀመረው የእርስ በእርስ ጦርነት በዓለም ትልቁን የመፈናቀል እና የረሃብ ቀውስ አስከትሏል።

ባለፈው ኅዳር በመንግሥታቱ ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት ሁለቱም ተፋላሚ ወገኖች ጦርነቱን በአስቸኳይ እንዲያቆሙ እና የሰብአዊ ርዳታ መግባቱን እንዲያረጋግጡ የሚጠይቀውን ረቂቅ ውሳኔ ቀሪዎቹ 14 የምክር ቤት አባላት ሲደግፉት ሩሲያ ድምጽ በመሻር ሥልጣኗ ተጠቅማ ጥላዋለች፡፡

በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የዩናይትድ ስቴትስ አምባሳደር ሊንዳ ቶማስ-ግሪንፊልድ ትላንት ሰኞ ዝርዝር ውስጥ ሳይገቡ ለምክር ቤቱ ባደረጉት ንግግር "ሩሲያ ማደናቀፍን መርጣለች፡፡ ብቻዋን ቆማ ሲቪሎች እንዲጎዱ ድምጽ ሰጥታለች፡፡ ሁለቱንም ተፋላሚ ወገኖች በገንዘብ ትደግፋለች፡፡ አዎ! ሁለቱንም ወገኖች እያልኩ ነው" ብለዋል።

በመንግሥታቱ ድርጅት የአሜሪካ ልዑክ ቃል አቀባይ ማብራሪያ እንዲሰጡበት ተጠይቀው፤ ሩሲያ "በሱዳን የወርቅ ንግድ ውስጥ ጥቅም እንዳላት ዋሽንግተንእንደምታውቅ ገልጸው ለተፋላሚዎቹ ወገኖች "በህገወጥ የወርቅ ንግድም ሆነ በጦር መሳሪያ አቅርቦት መልክ የሚደረግ ቁሳዊ ድጋፍ ዩናይትድ ስቴትስ ታወግዛለች" ብለዋል፡፡

በመንግሥታቱ ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት የሩሲያ ምክትል አምባሳደር ዲሚትሪ ፖሊያንስኪ በሰጡት ምላሽ “ዩናይትድ ስቴትስ ሌሎች የዓለም ኃያላን መንግሥታት ላይ በራሷ መለኪያ ለመፍረድ በመሞከሯ እናዝናለን” ብለዋል።ሮይተርስ ስለጉዳዩ ከሱዳን ተፋላሚ ወገኞች ወዲያውኑ ለዘገባው ምላሽ ሊያገኝ አለመቻሉን አስታውቋል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

08 Jan, 08:45


በሶማሊያ ስለሚሰፍረው የግብጽ ጦር ዙሪያ ሁለቱ ሀገራት በቀጣይ ሳምንት እንደሚመክሩ ተገለጸ!

ግብጽ በአፍሪካ ህብረት ልዩ ተልዕኮ ተሰጥቶት በሶማሊያ በሚሰማራው የጦር ሰራዊቷ ዙሪያ በቀጣይ ሳምንት ከሶማሊያ መንግስት ባለስልጣናት ጋር እንደምትመክር ተገለጸ።በሁለቱ ሀገራት መካከል ውይይቱ የሚካሄደው ከጥር 7 እስከ 9 ቀን 2017 ዓ.ም መሆኑን የሶማሊያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አሊ ባርካድ እንደነገሩት ብሉንበርግ አስነብቧል።

ግብጽ አትሚስን በሚተካው በአዲሱ በሶማሊያ የአፍሪካ ህብረት የድጋፍ ተልዕኮ (AUSSOM) ውስጥ እንደምትሳተፍ የሀገሪቱ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ባድር አብዳላቲ ማረጋገጣቸውን መዘገባችን ይታወሳል።በሶማሊያ አዲስ ተልዕኮ ተሰጥቶት በሚሰፍረው የአፍሪካ ህብረት የሰላም አስከባሪ ጦር AUSSOM ግብጽ ወታደሮቿን የምታዋጣው ከሶማሊያ በኩል በቀረበላት ጥሪ መሰረት ነው ሲል ብሉንበርግ በዘገባው አመላክቷል።

የሶማሊያ መንግሥት የኢትዮጵያ ወታደሮች በአፍሪካ ኅብረት ልዑክ ውስጥ መካተታቸውን በተመለከተ “መልሶ ለማጤን” ዝግጁ መኾኑን ማስታወቁን መዘገባችን ይታወሳል።ብሉንበርግ ባስነበበው ዘገባው የሶማሊያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ኢትዮጵያ የአውሶም ጦር ውስጥ ምን ያክል ቁጥር ያለው ሰራዊት እንድታሰማራ እንደተፈቀደላት የታወቀ ነገር አለመኖሩን እንደነገሩት ጠቁሟል።

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት ከቀናት በፊት ታህሳስ 18 ቀን 2017 ዓ.ም ባካሄደው ስብሰባ በሶማሊያ በሰላም ማስከበር ተግባር ተሰማርቶ በቆየው አትሚስ አተካክ ረቂቅ ውሳኔ ላይ ውሳኔ ማሳለፉን መዘገባችን ይታወሳል።አትሚስን በመተካት ልዩ ተልዕኮ ተሰጥቶ ለሚሰፍረው የሰላም አስከባሪ ጦር ይሁንታ መስጠቱን፤ የቆይታ ግዜውም 12 ወራት እንዲሆን መፍቀዱን በዘገባው ተካቷል።

Via Addis Standard

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

08 Jan, 08:44


በቻይናዋ ቲቤት ግዛት ውስጥ በደረሰው የርዕደ መሬት አደጋ የሟቾች ቁጥር 126 ደረሰ
***************

በቻይና በሂማላያ ተራሮች ስር በምትገኘው ቲቤት ግዛት ውስጥ በተከሰተው በዚህ ከባድ የርዕደ መሬት አደጋ ምክንያት በርካቶች አሁንም የደረሱበት አልታወቀም ተብሏል።

በሬክተር ስኬል 6.8 የተለካው የርዕደ መሬት አደጋ በግዛቷ በቅርብ ዓመታት ውስጥ ከተከሰቱት መሰል አደጋዎች እጅግ የከፋው ስለመሆኑ ተገልጿል።

ርዕደ መሬቱ ከቲቤት አልፎም እስከ ጎረቤት ቡትሀን፣ ህንድ እና ናፓል ድረስ ዘልቆ ህንጻዎችን አንቀጥቅጧል ነው የተባለው።

ርዕደ መሬቱ ከተከሰተ በኋላ በፍርስራሽ ውስጥ የተቀበሩ ነዋሪዎችን ለማውጣት በቦታው የነበረው ከባድ ቅዝቃዜ ትልቅ ፈተና ደቅኖ ነበር።

በዚህም እስካሁን ቢያንስ 126 ሰዎች መሞታቸው እና 188 ደግሞ መጎዳታቸው ተዘግቧል።

800 ሺህ ሰዎች እንደሚኖሩባት በምትገመተው የቲቤቷ ሺጋሴ ግዛት ቢያንስ 3 ሺህ ቤቶች መውደማቸውን የመጀመሪያ ዙር ቆጠራ አመላክቷል።

ቀሪ የአደጋው ሰለባዎችን ለመታደግ ከ1 ሺህ 800 በላይ የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች እና 1 ሺህ 600 ገደማ ወታደሮች አደጋው ወደተከሰተበት ግዛት ተሰማርተዋል።

መንግሥት ለአደጋው ተጋላጭ የሆኑ 30 ሺህ ሰዎች አካባቢያቸውን ለቀው እንዲወጡ አድርጓል።

የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ሺ ጂንፒንግ ተጎጂዎችን የመታደጉ እንቅስቃሴ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ትዕዛዝ ማስተላለፋቸውን እና የነፍስ አድን ስራው በስፋት እየተከናወነ መሆኑን ቢቢሲ ዘግቧል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

07 Jan, 15:50


ሚኒስቴሩ ከዛሬ አመሻሽ ጀምሮ በሥራ ላይ የሚውል የነዳጅ ምርቶች ችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ይፋ አደረገ

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ከዛሬ አመሻሽ ጀምሮ በሥራ ላይ የሚውል የነዳጅ ምርቶች ችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ይፋ አድርጓል።

ሚኒስቴሩ በላከው መግለጫ እንደጠቀሰው የነዳጅ ምርቶችን ችርቻሮ ዋጋ መሸጫ በየወሩ እየከለሰ በስራ ላይ እንዲውል በሚኒስቴሮች ምክር ቤት ውሳኔ የተጣለበትን ሃላፊነት አውስቷል።

በዚህም ከዛሬ ታኅሣሥ 29 ቀን 2017 ዓ.ም ምሽት 12 ሰዓት ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ ተግባራዊ የሚደረግ የነዳጅ ምርቶች ችርቻሮ መሸጫ ዋጋን ይፋ አድርጓል።

በዚህም አንድ ሊተር የነዳጅ ምርት ችርቻሮ ዋጋ በብር ሲገበያይ እንደነዳጁ አይነት በሚከተለው መልኩ እንዲሆን መወሰኑን ገልጿል።

አንድ ሊትር ቤንዚን በብር 101.47፣ ናፍጣ በብር 98.98፣ ኬሮሲን በብር 98.98፣ የአውሮፕላን ነዳጅ በብር 109.56፣ የከባድ ጥቁር ናፍጣ በብር 105.97 እንዲሁም የቀላል ጥቁር ናፍጣ በብር108.30 መሆኑን አሳወቋል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

05 Jan, 10:05


በአፋር እና በኦሮሚያ ክልሎች እየተከሰተ ባለው የርዕደ-መሬት ክስተት ሁኔታና ምላሽን አስመልክቶ ከኢትዮጵያ አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን የተሰጠ መግለጫ
******

በአፋር ክልል አዋሽ ፈንታሌ እና ዱለቻ ወረዳዎች እንዲሁም በኦሮሚያ ክልል ፈንታሌ ወረዳ የርዕደ መሬት ከስተት የተፈጥሮ የቅድመ ማስጠንቀቂያ ደወለን ተከተሎ መንግስት የተለያዩ ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል፡፡ በእስካሁኑ ሁኔታና ምላሽ እየታየ ያለው ስራ አመርቂ ነው፡፡

በአፋር ከልል ሁለት ወረዳዎች ማለትም አዋሽ ፈንታሌና ዱለቻ (ዱለሳ) ወረዳዎች ለችግሩ ተጋላጭ ናቸው:: በሁለቱም ወረዳዎች ማለትም በአዋሽ ፈንታሌ 6 ተጋላጭ ቀበሌዎች 15 ሺህ ነዋሪዎች ተጋላጭ ሲሆኑ እስከ አሁን 7 ሺህ ወገኖች ከስጋቱ ቀጠና ወደ ሌላ ስፈራ ተጓጉዘዋል፡፡

በዱለቻ ወረዳ ደግሞ 20 ሺህ የሚሆኑ የ2 ቀበሌዎች ወገኖች ተጋላጭ ሲሆኑ፤ ከነዚህ ቀበሌዎች እስከ አሁን 6 ሺህ 223 ህዝብ አካባቢውን ለቀዋል፡፡

በኦሮሚያ ክልል ፈንታሌ ወረዳ የ5 ቀበሌዎች ወገኖች ለአደጋው ተጋላጅ ናቸው:: በ5ቱም ቀበሌዎች 16 ሺህ 182 ሕዝብ ተጋላጭ ሲሆን እስከ አሁን ድረስ 7 ሺህ 350 ሕዝብ ከተጋላጨ ስፍራ ወጥተዋል፡፡ 8 ሺህ 832 የሚሆኑት ቀሪዎቹ ሰዎች ደግሞ በሚቀጥሉት ቀናት ውስጥ ከስፍራው እንዲንቀሳቀሱ እየተሠራ ይገኛል፡፡

ክስተቱን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲና ከሌሎች የሚመለከታቸው ተቋማት የተውጣጡ የሳይንቲፊክ ኮሚቴ፣ ያለውን ሁኔታ እየተከታተለ ሲሆን መገለጽ ያለበትን ቅድመ-ጥንቃቄዎች አስመልከቶ አስፈላጊው መረጃ ለሕዝብ በተከታታይ የሚቀርብ ይሆናል፡፡ ይህንንም ከኢትዮጵያ አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን ማህበራዊ ሚዲያዎችና ድህረ ገጽ መከታተል ይቻላል፡፡

የርዕደ መሬት ንዝረቱ ባለበት አካባቢ ያለ ማህበረሰብ ከንዝረቱ በፊት፣ በንዝረቱ ወቅትና ከንዝረቱ በኋላ ያለውን መወሰድ ያለባቸው ጥንቃቄ እንዲወስዱ አስፈላጊው መረጃ እየተሰጠ ይገኛል፡፡

ሰብዓዊ ድጋፍን በተመለከተ እስከ አሁን ለ70 ሺህ የህብረተሰብ ክፍሎች የሚሆን 11 ሺህ 550 ኩንታል ምግብ-ነክ እና ለ700 አባወራ የሚሆን ምግብ ነክ ያልሆኑ ቁሳቁሶች ወደ ስፍራው ተልኳል፡፡ ይህም በንዘብ ሲተመን ለምግብ 216 ሚሊየን 562 ሺህ ብር በላይ እና ምግብ ነክ ላልሆኑ ቁሳቁሶች 65 ሚሊየን 625 ሺህ ብር በድምሩ 281 ሚሊየን 562 ሺህ ብር በላይ የሚገመት ነው፡፡

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

04 Jan, 15:30


#አማራ ክልል ባለፉት አምስት ወራት ብቻ ከ1.3 ሚሊዮን በላይ ሰዎች በወባ በሽታ መያዛቸው ተገለጸ

በአማራ ክልል ባለፉት አምስት ወራት ብቻ ከ1.3 ሚሊዮን በላይ ሰዎች በወባ በሽታ መያዛቸውን በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማዕረግ የማኅበራዊ ክላስተር አሥተባባሪ እና የክልላዊ የወባ መከላከል ግብረ ኀይል ሠብሣቢ ሙሉነሽ ደሴ (ዶ.ር ) ገለጹ።

ይህም ካለፈው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፃር በ64 በመቶ ጭማሪ ማሳየቱን ገልጸው በተለይም ደግሞ በክልሉ የሚገኙ 40 ወረዳዎች የክልሉን 70 በመቶ የወባ ሥርጭት ይሸፍናሉ ብለዋል።

የአካባቢ ቁጥጥር ሥራ በትኩረት አለመሥራት፣ የአየር ንብረት ለውጥ፣ የመኝታ አጎበር በወቅቱ አለመተካቱ እና ማኅበረሰቡም የተሰጠውን የመኝታ አጎበር በአግባቡ አለመጠቀም ለበሽታው ሥርጭት መጨመር ዋነኛ ምክንያት መሆናቸውን ጠቅሰዋል ሲል አሚኮ ዘግቧል።

ሠብሣቢዋ ሥርጭቱን ለመከላከልም ባለፉት ወራት ከፍተኛ የወባ ጫና ባለባቸው 27 ወረዳዎች በሚገኙ 233 ቀበሌዎች የቤት ውስጥ የጸረ ወባ ትንኝ ኬሚካል ርጭት መካሄዱንም ጠቁመዋል።

በተጨማሪም ከጥቅምት 15/2017 ዓ.ም ጀምሮ ደግሞ ዘወትር አርብ "የአርብ ጠንካራ እጆች የወባ በሽታን ይገታሉ" በሚል መሪ መልዕክት ለተከታታይ 11 ሳምንታት ክልላዊ የአካባቢ ቁጥጥር ሥራ ዘመቻ እየተሠራ እንደሚገኝ አመላክተዋል።

ይሁን እንጂ በሽታው በክልሉ የተለያዩ ወረዳዎች አሁንም በከፍተኛ ሁኔታ መጨምሩን ነዋሪዎችና የጤና ባለሙያዎች እየገለጹ ይገኛሉ።
ለአብነትም የምግብ ዕጥረት በተከሰተበት ሰሜን ወሎ ዞን ቡግና ወረዳ ባለፉት 5 ወራት በአማካይ ከሚመረመሩ ህሙማን መካከል 72 በመቶ የሚሆኑት የወባ ታማሚዎች እንደሆኑ መገለጹን ዘገባዎች አመለክተዋል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

04 Jan, 15:30


መንግሥት የርዕደ መሬቱ ማዕከል ከሆኑ አካባቢዎች ከ80ሺህ በላይ ሰዎችን ወደ ሌላ ቦታ ለማሥፈር እየሰራሁ ነው አለ

መንግሥት የርዕደ መሬት ማዕከል ናቸው ተብለው በተለዩ በ12 ቀበሌዎች የሚገኙ ከ80ሺህ በላይ ሰዎችን ወደ ሌላ ቦታ ለማሥፈር እየሰራ መሆኑን አስታወቀ።

የርዕደ መሬቱ ማዕከል (epicenter) የሆኑ አካባቢዎችን በመለየት በ12 ቀበሌዎች ላይ ከተለያዩ የሙያ ዘርፎች የተውጣጡ የአደጋ ጊዜ ሠራተኞች በቦታው በማሰማራት የጉዳቱን መጠን አሠሣ እያደረገ መሆኑን ዛሬ ታህሳስ 26 ቀን 2017 ዓ.ም ባስተላለፈው ወቅታዊ መግለጫ ጠቁሟል።

ዛሬ ሌሊት 9:52 ሰዓት ላይ ንዝረቱ አዲስ አበባ ድረስ የተሰማ በሬክተር ስኬል 5 ነጥብ 8 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ በአቦምሳ መከሰቱን የአሜሪካ የጂኦሎጂ ሰርቬይ መረጃ አመልክቷል፡፡

በተጨማሪም በአፋር ክልል ዱለቻ ወረዳ ዶፋን ተራራ ላይ በትናንትናው ዕለት እሳተ ገሞራ የተከሰተ ሲሆን ሳጋንቶ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንቀጥቀጥ ሳቢያ በበርካታ ሥፍራዎች ላይ #ፍልውሃዎች እና ቅባት አዘል ጥቁር ውሃ ከመሬት እየፈለቁ ይገኛሉ።

በቀበሌው በተለይ በዶፈን ተራራ ላይ የመሬት መንቀጥቀጡ በመጠኑም በድግግሞሹም ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መሆኑን በዚህም ሳቢያ ተራራው እየተናደ እንደሆነ ኢቢሲ በዘገባው አመላክቷል።’

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

03 Jan, 17:02


አዲስ ዓመትን እንዲያከብሩ እስረኞችን ፈቶ የለቀቀው ፖሊስ በቁጥጥር ስር ዋለ፡፡
***
ድርጊቱ ፈገግታን ቢጭርም በስካር መንፈስ ውስጥ ሆኖ የአዲስ አመት ዋዜማን እንዲያከብሩ 13 ታሳሪዎችን ከፖሊስ ጣቢያ የለቀቀው የፖሊስ አባል በቁጥጥር ስር ውሎ የሀገሪቱ ፖሊስ የተለቀቁትን እስረኞች እያፈላለገ ነው ተብሏል፡፡

የዛምቢያ ፖሊስ አባል የሆነው መርማሪ ኢንስፔክተር ቲተስ ፊሪ የተባለው ፖሊስ በቁጥጥር ስር የሚገኙ ተጠርጣሪዎቹን በዋና ከተማዋ ሉሳካ ከሚገኘው ሊዮናርድ ቼሎ ፖሊስ ጣቢያ ነው ፈቶ የለቀቃቸው፡፡

ለረጅም ሰአታት በጠጣው መጠጥ በአልኮል ተጽዕኖ ውስጥ የነበረው ኢንስፔክተሩ ድርጊቱን ከፈጸመ በኋላ ከህግ ለማምለጥ ጥረት አድርጓል፡፡

ባልጠበቁት ሁኔታ ከእስር ቤት እንዲወጡ የተፈቀደላቸው ታሳሪዎች በዝርፊያ ፣ ስርቆት እና አካላዊ ጥቃት በማድረስ ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የሚገኙ ነበሩ፡፡

በአሁኑ ወቅት ሉሳካ የሚገኘው የሊዮናርድ ቼሎ ፖሊስ ጣቢያ ፖሊስ አባላት ያመለጡትን ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ለማዋል በአደን ላይ ይገኛሉ፡፡

የፖሊስ ቃል አቀባይ ሬ ሀሙንጋ ድርጊቱን የፈጸመው ኢንስፔክተር ቲተስ ፊሪ በአዲስ አመት ዋዜማ ተረኛ የእስረኞች ጠባቂ ከሆነችው የፖሊስ አባል የእስር ቤቶቹን ቁልፍ በሀይል እንደቀማት ተናግረዋል፡፡

በመቀጠልም ኢንስፔክተሩ የወንድ እና ሴት የእስር ቤት ክፍሎችን በመክፈት "ወደ አዲሱ አመት ለመሻገር ነፃ ሆናችኋል" በማለት ከእስር ቤቱ እንዲወጡ እንዳዘዛቸው ቃል አቀባዩ ገልጸዋል፡፡

በስካር መንፈስ ውስጥ ሆኖ ያልተጠበቀውን ድርጊት የፈጸመው መርማሪ ኢንስፔክተር ወዲያው ከአካባቢው ለመሸሽ ቢሞክርም በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውሏል፡፡

ኢንስፔክተሩ ድርጊቱን ለምን እንደፈጸመ እስካሁን ቃሉን እንዳልሰጠ የተገለጸ ሲሆን ፖሊስ በበኩሉ ከእስረኞቹ መለቀቅ ጀርባ የስካር ስህተት ወይስ ድብቅ ዓላማ ያለው የተቀነባባረ ድርጊት የሚለውን ለማጣራት በምርመራ ላይ እገኛለሁ ብሏል፡፡
@አልአይን

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

03 Jan, 16:50


ዓርብ፣ ታኅሳስ 25/2017 ዓ፣ም ዕለታዊ ዜናዎች

1፤ የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ደዔታ ምስጋኑ አረጋ፣ የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን ትናንት ሞቃዲሾ ውስጥ ከሱማሊያ ባለሥልጣናት ጋር የኹለትዮሽ ግንኙነቶችን በማጠናከር ዙሪያ "ገንቢ" ውይይት ማድረጉን በ"ኤክስ" ገጻቸው አስታውቀዋል። የሱማሊያ ባለሥልጣናት፣ የኢትዮጵያ ወታደሮች ይንቀሳቀሱባቸው የነበሩ አካባቢዎች በአዲሱ የአፍሪካ ኅብረት ተልዕኮ ለሚሳተፉ አገራት ወታደሮች እንደተሰጡ በመጥቀስ፣ የኢትዮጵያ ወታደሮች በተልዕኮው ከተሳተፉ በሌሎች አካባቢዎች እንዲሠማሩ ለልዑካን ቡድኑ ሃሳብ ማቅረባቸውን የሱማሊያ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። የሱማሊያ ባለሥልጣናት፣ የኢትዮጵያ ወታደሮች በተለይ በጁባላንድና ሳውዝዌስት ግዛቶች እንዳይሠማሩ ቅድመ ኹኔታ ማስቀመጣቸውን ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል። ኾኖም የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን ይህንኑ ሃሳብ እንዳልተቀበለውና የሱማሊያ ልዐካን ቡድን ቀጣይ ውይይት ለማድረግ ወደ አዲስ አበባ የመጓዝ ሃሳብ እንዳለው ተሰምቷል።

2፤ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ ከግብር ጋር በተያያዘ በአዲስ አበባ ባሉ በተሽከርካሪ አስመጪዎች ላይ ያወጣው አዲስ መመሪያ ስህተት እንዳለበት ገልጦ አነስተኛ ማስተካከያ ማደርጉን ዋዜማ ሰምታለች። አዲሱ መመሪያ የተጨማሪ እሴት ታክስን ማካተቱ ስህተት መኾኑን ቢሮው ማመኑ ታውቋል። ጉዳዩን የሚያውቁ ምንጮች ግን፣ ቢሮው ጉዳዩ በመገናኛ ብዙኃን መነጋገሪያ መኾኑን ተከትሎ አደረኩት ያለው ቅናሽ እዚህ ግባ የማይባል መኾኑን ለዋዜማ ተናግረዋል። በሕጉ መሠረት ተጨማሪ ዕሴት ታክስ የሚጣለው በነዳጅ በሚሠሩ ተሽከርካሪዎችና ነዳጅና ኤሌክትሪክ በሚጠቀሙ ተሽከርካሪዎች ላይ ነው። የከተማዋ ትራንስፖርት ቢሮም፣ ኹሉም የመንገድ ትራንስፖርት ቢሮዎች አዲሱን የስም ማዞሪያ የክፍያ ቀመር ተግባራዊ እንዲያደርጉ መመሪያ አስተላልፏል።

3፤ ትናንት በመቀሌ ለተቃውሞ ሰልፍ የወጡ የጦር ጉዳተኞች ከከተማዋ ወደ አውሮፕላን ማረፊያው የሚወስደውን መንገድ ለኹለት ሰዓታት ዘግተው እንደነበር ቢቢሲ ሬዲዮ ዘግቧል። በመንገዱ መዘጋት ሳቢያ በዕለቱ በረራ የነበራቸው መንገደኞች ተጉላልተው እንደነበር ዘገባው ጠቅሷል። የጦር ጉዳተኞቹ መንገዱን የዘጉት፣ የቀድሞ ተዋጊዎችን ትጥቅ የማስፈታት፣ የመበተንና መልሶ የመቀላቀል ፕሮግራሙ ትግበራ ዘግይቶብናል በሚል ቅሬታ እንደኾነ ዘገባው አመልክቷል። የክልሉ ጸጥታ ሃላፊዎች የቀድሞ ተዋጊዎችን ከኅብረተሰቡ ጋር የመቀላቀል ሂደቱ እንዳልተቋረጠና ከፌደራል መንግሥቱ ጋር በሚደረግ ንግግር እንደገና እንደሚቀጥል ለጦር ጉዳተኞቹ ገልጸውላቸዋል ተብሏል።

4፤ አይ ኤስ የተባለው ዓለማቀፍ ነውጠኛ ቡድን ሰሞኑን በኢትዮጵያ አጎራባች በኾነችው የሱማሊያዋ ፑንትላንድ ግዛት ኃይሎች ላይ ተጣቂዎች ለፈጸሙት ጥቃት ሃላፊነቱን ወስዷል። የፑንትላንድ መንግሥት ጸጥታ ኃይሎቹ ጥቃቱን በመመከት፣ በርካታ የውጭ ዜጎችን ጨምሮ ዘጠኝ የቡድኑን ተዋጊዎች እንደገደሉ አስታውቋል። በፑንትላንድ ተራራማ አካባቢዎች ላለፉት ጥቂት ዓመታት የመሸጉት የአይ ኤስ ታጣቂዎች፣ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተጠናከሩ እንደሄዱ አሜሪካ ቀደም ሲል መግለጧ አይዘነጋም። [ዋዜማ]

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

03 Jan, 16:49


የመሬት መንቀጥቀጥ እየተከሰተባቸው ካሉ ስፍራዎች ነዋሪዎችን ማዘዋወር ተጀመረ

በአፋር ክልል ገቢ ረሱ ዞን ተደጋጋሚ የመሬት መንቀጥቀጥ እየደረሰባቸው ባሉ ሁለት ቀበሌዎች የሚኖሩ አራት ሺህ ገደማ አባወራዎችን፤ “የአደጋ ስጋት ወዳልሆነ ስፍራ” የማዘዋወር ስራ መጀመሩን አንድ የአካባቢው ባለስልጣን ተናገሩ።

አደጋውን ሸሽተው ወደ አዋሽ አርባ ከተማ የገቡ ነዋሪዎችን በአንድ ማዕከል ለማሰባሰብ ምዝገባ እየተካሄደ መሆኑንም ገልጸዋል።

በክልሉ በድግግሞሽም ሆነ በመጠን ባለፈው አንድ ሳምንት ይበልጥ በበረታው የመሬት መንቀጥቀጥ ይበልጡኑ የተጠቁ ስፍራዎች፤ በገቢ ረሱ ዞን፣ ዱለሳ ወረዳ ስር የሚገኙት የዱሩፍሊ እና ሳገንቶ የተባሉት ቀበሌዎች ናቸው።

በቀበሌዎቹ እየደረሰ ያለውን የመሬት መንቀጥቀጥ ተከትሎ “የእሳተ ገሞራ ፍንዳታ” እና በመኖሪያ ቤቶች አካባቢ ድንገት ውሃ መፍለቅ መከሰቱን የዱለሳ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ አሊ ደስታ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል።

በአካባቢው ወደፊት ሊደርስ የሚችለውን አደጋ ታሳቢ በማድረግ፤ ከትላንት በስቲያ ረቡዕ ታህሳስ 23፤ 2017 ጀምሮ የሁለቱን ቀበሌ ነዋሪዎች በአቅራቢያው ወደሚገኘው አዋሽ አርባ ከተማ የማጓጓዝ ስራ እየተከናወነ መሆኑን አቶ አሊ ገልጸዋል።

“የእሳተ ገሞራ ፍንዳታ የቱ ጋር ሊከሰት እንደሚችል ትክክለኛ ቦታዎችን እያወቅን አይደለም። የመሬት መንቀጥቀጥ አናሳ ወደ ሆነበት አካባቢ ነው [ነዋሪዎችን] እያዘዋወርን ያለነው” ሲሉ የወረዳው አስተዳዳሪ አስረድተዋል።
ኢትዮጵያ ኢንሳይደር

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

03 Jan, 16:49


ቅርጫ በህገወጥ የስጋ ዝዉዉር ስር የማይካተት በመሆኑ ክልከላ አልተደረገም ተባለ።

በአል አስመልክቶ ህብረተሰቡ በቤቱ እና በየአካባቢዉ የቁም እንስሳትን ቅርጫ በማረድ መከፋፈል አለመከልከሉን ሰምተናል።

ይህ የተባለዉ የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት በሰጠዉ ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ነዉ።

ሆኖም በአልን ተከትሎ የሚከናወኑ እርዶች ንፅህና እና ጤናማቱን በማረጋገጥ መሆን እንዳለበት ተገልፆል።

የአዲስ አበባ ከተማ አርሶአደር እና ግብርና ኮምሽን ተወካይ ዶ/ር አስናቀዉ አወቀ እንደገለፁት በህገወጥ እርድ እና ስጋ ዝዉዉር ላይ የወጣዉ ደንብ ቅርጫን የማያካትት ነዉ ብለዋል።

በጋራም ሆነ በግል እርድ የሚደረግባቸዉ  የስጋ ፍጆታዎች ከአካባቢ ጥበቃ እና ብክለት ነፃ መሆን የሚገባቸዉ ግን እንደሆነ አንስተዋል።

የቅርጫ ስርአቱ ንፅህና በጠበቀ መልኩ መከወን የሚችልበት አግባብ በመፍጠር ህብረተሰቡ መከፋፈል የሚችል መሆኑን አስታወቀዋል።

ነገር ግን  በህገ ወጥ መንገድ እርድ በመፈፀም ለሆቴሎች እና ለስጋ ቤቶች በማከፋፈል ተግባር ላይ የሚገኙ አካላት ላይ እርምጃዎች እንደሚወሰዱ ተገልጿል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

02 Jan, 08:10


ከሕመም ጋር አራት ልጆችን ያለአባት የማሳደግ የእናትነት ብርቱ ፈተና…

ጸሃይ ተሻለ ትባላለች፤ የአዲስ አበባ ነዋሪ ስትሆን ሕመምተኛ እና የአራት ልጆች እናት ናት፡፡

የሕይወት መልኩ ብዙ ነው፣ አንዴ ጥሩ የሆነው ሌላ ጊዜ መጥፎ ገጽታውን ሊያሳይ ይችላል፡፡

ጸሃይ ተሻለም ከባለቤቷ ጋር ትዳር ስትመሰርት ደስተኛ ነበረች፤ ትዳራቸው የሰመረ ሆኖም ጥንዶቹ በልጅ ተባረኩ፡፡ ልጅ ሲመጣ ትዳር ይደምቃልና የጸሃይና ባለቤቷ ፍቅርም በልጆች ፍቅር ታጅቦ ዓመታትን አሳለፈ፡፡

ይሁን እንጂ ጸሃይና ባለቤቷ ሶስት ልጆችን ከወለዱ በኃላ በተለያዩ ምክንያቶች ትዳራቸው እክል አጋጠመው፤ ጥንዶቹ ልዩነትን በውይይት ከመፍታት ይልቅ ወደ ግጭት አካላዊ ጉዳት አመሩ፣ በዚህ ሁኔታ ላይም ጸሃይ አራተኛ ልጇን ነፍሰ ጡር እያለች ባለቤቷ ልጆቹን አደራ እንኳን ሳይል ጥሏት ጠፋ፡፡

ጸሃይ ከባለቤቷ ጋር በተፈጠረ አለመግባባት በመለያየታቸውም አሁን ላይ አራት ልጆችን ብቻዋን የማሳደግ ሃላፊነት ተሸክማለች፡፡

ከአንድ ዓመት በፊት ከባለቤቷ ጋር ልጆችን ለማሳደግ እና ሕይወትን ለማሸነፍና በርካታ ውጣ ውረድ እንዳሳለፈች ትናገራለች፡፡

ከድጡ ወደ ማጡ እንዲሉ.. በአሁኑ ወቅትም አባት የት እንዳለ ባለመታወቁ ከማይድን ሕመም ጋር አራት ልጆችን ለማሳደግ ብርቱ ችግር ውስጥ እንደምትገኝ አንስታለች፡፡

ልጆቹን ለማሳደግና ትምህርት ለማስተማር ልብስ ከማጠብ ጀምሮ የተለያዩ አድካሚ ሥራዎችን እንደምትሰራ ነው የገለጸችው፡፡

ይሁን እንጂ አሁን ላይ ባለው ሁኔታ መሰል ሥራዎችን በህመም እየተሰቃየች ሰርታ አራት ልጆችን ማሳደግ ከአቅሟ በላይ መሆኑን ለፋና ዲጂታል አስረድታለች።

ይህን ተከትሎም ልጆቿ ትምህርታቸውን እንዳያቋርጡ እና የእለት ጉርሳቸውን ለማግኘት ጎዳና በመውጣት ለልመና መዳረጓን አብራርታለች፡፡

''ያን ቀን እንደወትሮው ቤት ውስጥ የሚላስ የሚቀመስ የለም፤ልጆቼን እያለቀስኩ አየኋቸው፤ ፊታቸው ጠውልጓል፤ እርቧቸዋልም፤ ከዛም የልጆቼን ርሃብ ለማስታገስ እግሬ ወደ አመራኝ ጎዳና ወጣሁ'' ትላለች ልመና የወጣችበትን ቅጽበት ስታስታውስ።

በእርግጥ ጎዳና ወጥቶ እንደመለመን ከባድ ፈተና የለም የምትለው ጸሃይ÷ አማራጮቿን ሁሉ ሞክራ የልጆቿን ቀጣይ ሕይወት አደጋ ላይ ላለመጣል የቀራት ብቸኛ አማራጭ የሰዎችን ትብብር መጠየቅ እንደሆነ ተናግራለች፡፡

7ኛ ክፍል የሆነው የመጀመሪያ ልጇ እንደ እርሷ የማይድን ሕመም ተጠቂ መሆኑን ስትናገር እንባዋ ይተናነቃታል፡፡

ሁለተኛ ልጇ 2ኛ ክፍል፣ ሶስተኛ ልጇ የቅድመ መደበኛ ተማሪ እንዲሁም የመጨረሻ ልጇ ደግሞ የ1 ዓመት ከሶሶት ወር ዕድሜ እንዳላት ገልጻለች፡፡

እናትነት፣ አቅም ማጣት እና የልጅን ቀጣይ እጣ ፈንታ የመወሰን ከባድ ፈተና ከሕመሟ ጋር ተዳምረው በንግግሯ መሃል የምትለው ይጠፋታል፡፡

ከሁሉም በላይ ልጆቼን አስተምሬ ጥሩ ደረጃ እንዲደርሱ ፍላጎት አለኝ የምትለው ምስኪኗ እናት፤ ልጆችም በጥሩ ሁኔታ ትምህርታቸውን ተከታትለው የተቸገሩ ሰዎችን የመርዳት ሕልም እንዳላቸው እንደሚነግሯት አንስታለች፡፡

አሁን ላይ ከልጆቿ ጋር የምትኖርበት ቤት ለአደጋ የሚያጋልጥ ከመሆኑ በላይ ውሃ እና መብራት እንደሌለው እና ምቹ አለመሆኑን አብራርታለች፡፡

ልጆችን ተከታትሎ ማስተማርና የእለት ጉርስ መፈለግም የእናትነት የእለት ጭንቀቷ መሆኑን በተሰበረ ልብ ታስረዳለች፡፡

ስለሆነም በሀገር ውስጥም ሆነ በውጪ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ያለባትን ጽኑ ችግር ተረድተው እጃቸውን እንዲዘረጉላት እናት ጸሃይ ተማጽናለች፡፡

ባለታሪኳን ማግኘትና መርዳት ለሚፈልግ👉ጸሃይ ተሻለ ዘሪሁን፤ስልክ፣0923149392

በመላኩ ገድፍ ( Fbc)

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

01 Jan, 15:29


Capital News: በህገወጥ መንገድ ግብር ተቆረጠ | የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ፈተና | ኢሰማኮ ምን ገጠመዉ
https://youtube.com/watch?v=dR8r1suPNmk&si=suhNE1rwx9PZgZGL

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

01 Jan, 08:07


" በአምቡላንሶቹ ላይ የተፈጸመው ጥቃት ዘግናኝ ነው " - የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር

የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር በሠራተኞቹ እና በአምቡላንሶቹ ላይ " ዘግናኝ " ሲል የገለጸው ጥቃት መፈጸሙን አመለከተ።

የማኅበሩ አምቡላንሶች በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ወለጋ ዞን ሲቡ ሲሬ ወረዳ እና በአማራ ክልል ሰሜን ጎንደር ዞን ታች አርማጭሆ ወረዳ ለህይወት አድን ተግባር በሚንቀሳቀሱበት ወቅት ባልታወቁ ኃይሎች በተተኮሰባቸው ጥይት የሁለቱም አምቡላንስ አሽከርካሪዎች ለከፍተኛ ጉዳት የተዳረጉ ሲሆን አምቡላንስ ተሽከርካሪዎቹም ላይ ጉዳት መድረሱን ገልጿል።

ማኅበሩ ከጊዜ ወደ ጊዜ ሠራተኞቹን ጨምሮ በበጎፈቃደኞቹ እና ተሽከርካሪዎቹ ላይ በሚፈፀሙ ጥቃቶች አማካኝነት ሰብዓዊ አገልግሎቱን ለሚፈልጉ ወገኖች ለማድረስ ፈተና እየሆነበት እንደሆነ አሳውቋል።

ጥቃት የሚፈፅሙ የትኛውም ተፋላሚ ኃይሎች ድርጊቱ ኢትዮጵያ የፈረመችውን ዓለም አቀፍ የጄኔቫ ሥምምነቶችን የሚፃረርና ከማኅበሩ ዓላማ ውጪ መሆኑን ተረድተው የማኅበሩ ሠራተኞች፣ በጎፈቃደኞችም ሆኑ ተሽከርካሪዎች በነፃነት ተንቀሳቅሰው ሰብዓዊ ተግባራቸውን ማከናወን እንዲችሉ፣ ደህንነታቸው እንዲጠበቅ፣ ከመሰል ድርጊታቸው እንዲቆጠቡና ማኅበረሰቡም ድርጊቶቹን እንዲያወግ ተማፅኖ አቅርቧል። እናቀርባለን፡፡

ማኅበሩ " የወገኖቻቸውን ህይወት ለመታደግ ሲንቀሳቀሱ የጥቃት ሰለባ በመሆን መተኪያ የሌላት ውድ ህይወታቸውን ላጡ ሠራተኞች እና በጎፈቃደኞች ቤተሰቦች መፅናናትን እንዲሁም ለተጎዱት በቶሎ ማገገምን እንመኛለን " ብሏል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

01 Jan, 08:03


በ #ኦሮሚያ ክልል #አሙሩ ወረዳ “ልጆቻቸው ወደ ታጣቂዎች ተቀላቅለዋል” የተባሉ 17 ሰዎች ታሰሩ

በአሮሚያ ክልል አሙሩ ወረዳ “ልጆቻችሁ ወደ ታጣቂዎች ተቀላቅለዋል፤ አምጡ” በሚል የ75 ዓመት አዛውንትን ጨምሮ 17 ሰዎች መታሰራቸውን ነዋሪዎች ተናገሩ።

በወረዳው ከሰባት ወራት እስር በኋላ ተፈተው ከነበሩ አርሶ አደሮች መካከል “ልጆቻቹ ከጫካ አልተመለሱም” ተብለው ድጋሚ የታሰሩ ሰዎች መኖራቸውን ዶቸ ቬለ ዘግቧል። በዚህም የ75 ዓመት አዛውንት በተመሳሳይ ክስ ድጋሚ መታሰራቸውን ልጃቸው ገልጸዋል።

አክለውም የ75 ዓመት ሽማግሌን ዕድሜው ከ25 ዓመት በላይ ለሆነው ልጅ ኃላፊነት ውሰድ ተብሎ 8 እና 9 ወራት ፖሊስ ጣቢያ ያለ ምንም ፍርድ ማስቀመጥ የሰብአዊ መብት ጥሰት ነው” ብሏል።

የአሙሩ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ዲንሳ ዱጉማ በወረዳው “ቤተሰብ ከታጣቂዎች ጋር የተቀላቀሉ ልጆቹን እንዲያመጣ በተቀመጠ አቅጣጫ” የታሰሩ የቤተሰብ አባላትን መኖራቸውን አረጋግጠዋል፡፡

ኃላፊው አክለውም “በየጊዜው እየጠየቅን፣ እያጣራን ልጆቻቸውን እንዲያመጡ አንድ ወርና ሁለት ወር ይሰጣቸዋል፡፡ ታስሮም ብዙዎች እየተለቀቁ ነው” ማለታቸውን ዘገባው አመላክቷል።

ባሳለፍነው ወር በወረዳው ኦቦራ በተሰኘ ፖሊስ ጣቢያ ውስጥ ከ130 በላይ ሰላማዊ ሰዎች “ከኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት አባላት ጋር ቤተሰባዊ ግንኙነት አላችሁ” በሚል ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ ከሰባት ወራት በላይ ታስረው እንደሚገኙ የታሳሪ ቤተሰቦችን ዋቢ አድርጎ አዲስ ስታንዳርድ መዘገቡ ይታወሳል።

በምዕራብ ኦሮሚያ በተለይም በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን ላለፉት ስድስት አመታት በኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት፣ በፋኖ ታጣቂዎች እና በመንግስት ጸጥታ ኃይሎች መካከል በተደጋጋሚ በሚካሄዱ ግጭቶች የበርካታ ሰዎች ህይወት እያለፈ ይገኛል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

01 Jan, 07:40


በኢትዮጵያኢትዮጵያ የወንድ የዘር ፈሳሽ ልገሳ፣  የሰውነት አካል መለገስ እና በህክምና የታገዘ ሞት እንዲጀመር የሚፈቅደው ህግ ጸደቀ።

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጤና አገልግሎት እና አስተዳድር ረቂቅ አዋጅን አጽድቋል። አዋጁ ከዚህ በፊት በኢትዮጵያ ተጀምረው የማያውቁ እና አዳዲስ አገልግሎቶችን መስጠት የሚያስችሉ የጤና አገልግሎቶች እንዲጀመሩ የሚያደርግ ነው።

ለአብነትም መዳን በማይችል እና በስቃይ ውስጥ ያሉ ታማሚዎች በሀኪሞች እርዳታ እንዲሞቱ የሚፈቅደው፣ የሰውነት አካልን ያለ ክፍያ መለገስ፣ የወንድ የዘር ፍሬ እንዲለገስ እና ሌሎችም አዳዲስ የህክምና አገልግሎቶችን ይፈቅዳል። ምክር ቤቱ ላለፉት ወራት የተለያዩ ውይይቶችን ሲያደርግ ቆይቷል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

01 Jan, 07:39


ባለሀብቱ በራቸው ላይ በተተኮሰባቸው ጥይት ተገደሉ

ታዋቂው የአክሰስ ኮም ኩባንያ ባለቤት እና የሸበል በረንታ ሲሚንቶ ፋብሪካ ስራ አስኪያጅ አቶ ቢረሳው ምናለ ትናንት ምሽት 1:30 ላይ ቤታቸው በር ላይ በጥይት ተመትተው እንደተገደሉ ታውቋል።

መሠረት ሚድያ የደረሰው መረጃ እንደሚጠቁመው ባለሀብቱ በለሚ ኩራ፣ ወረዳ ዘጠኝ 'አትሌቶች መንደር' መውረጃ አስፓልት አጠገብ በሚገኝ መኖሪያ ቤታቸው በር ላይ መኪና ውስጥ ሆነው የግቢው በር እንዲከፈት ክላክስ እያደረጉ ባሉበት ወቅት በጥይት ጥቃት ተፈፅሞባቸዋል።

"በሰዓቱ የአስፓልቱና የአካባቢው መብራት ጠፍቶ ነበር" የሚሉት የአካባቢው ነዋሪዎች በአካባቢው ምንም የፀጥታ አካል አልነበረም፣ በስፍራው የደረሱትም ነግቶ ነው ብለዋል።

የምስራቅ ጎጃም ቢቸና ወረዳ ተወላጅ የሆኑት እና የ 'ምናሉ ሆቴል' ባለቤት አቶ ቢረሳው የቀብር ስነስርዐት በዛሬው እለት በሳሊተ ምህረት ቤተክርስቲያን ተፈፅሟል።

መሠረት ሚድያ የአዲስ አበባ ፖሊስን በግድያው ዙርያ መረጃ የጠየቀ ሲሆን "መረጃው አልደረሰንም" የሚል ምላሽ አግኝቷል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

01 Jan, 07:39


የባንክ ሒሳብ ለመክፈት የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ይዞ የመቅረብ ቅድመ ሁኔታ ተጀመረ‼️

አዲስ አበባ በሚገኙ ባንኮች የባንክ ሒሳብ ለመክፈት የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ (የፋይዳ ቁጥር) ይዞ መቅረብ ዛሬ እንደ መጀመሪያ ቅድመ ሁኔታ ተግባራዊ መደረግ ጀምሯል፡፡

ቅድመ ሁኔታው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባወጣው መመሪያ መሠረት ነው ከዛሬ ታሕሣሥ 23 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ በሚገኙ ሁሉም ባንኮች ተግባራዊ መሆን የጀመረው፡፡

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

01 Jan, 06:35


ባንኮች ላይ ተጥሎ የነበረው አመታዊ የብድር እድገት ገደብ በመጠኑ ተሻሻለ!!

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ቦርድ በቅርቡ ማእከላዊ ባንኩን ለማቋቋም በፀደቀው አዲስ አዋጅ መሰረት በተቋቋመው የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ የቀረበለትን የውሳኔ ሃሳብ አፅድቋል።

በዚህመሰረት ከፀደቁ የውሳኔ ሃሳቦች መካከል በ2015ዓም ነሃሴ ወር አንስቶ ተግባራዊ መደረግ የጀመረው የባንኮች አመታዊ ብድር እድገት ገደብ ላይ ማሻሻያ አድርጓል።

በዚህ መሰረት ቀደም ሲል ተጥሎ ከነበረው የ14 በመቶ አመታዊ እድገት ወደ 18 በመቶ እንዲሆን ተወስኗል።

ካፒታል

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

01 Jan, 06:34


(ዘ-ሐበሻ፟) በዛሬው ዕለት አብዛኛው የአለማችን ነዋሪ አዲስ አመትን ተቀብሏል:: ዛሬ ለአብዛኛው የአለማችን ህዝብ ጃንዋሪ አንድ ቀን 2025 ገብቶ አዲስ አመት የሚከበር ቢሆንም አራት የአለማችን አገራት ግን ይህ እንደማይመለከታቸው ጋርዲያን ጋዜጣ ዛሬ ዘግቧል፡፡

ጋዜጣው ከእነዚህ አራት አገራት መካከል በአንደኝነት ኢትዮጵያን ጠቅሷል፡፡ የኮፕቲክ ዘመን አቆጣጠርን የምትከተለው ኢትዮጵያ አዲስ አመትን የምታከብረው ሴፕቴምበር 11 ወይንም 12 እንደሆነም አስረድቷል፡፡

ጋዜጣው ጨምሮም ዛሬ የተቀረው አለም ወደ2025 የተሻገረ ቢሆንም በኢትዮጵያ ግን ገና 2017 አመተ ምህረት መሆኑን አስታውቋል፡፡ ጋዜጣው በሁለተኝነት የጠቀሰው ኔፓልን ነው፡፡ በኔፓል ሁለት አይነት ዘመን አቆጣጠር እንዳለ የጠቀሰ ሲሆን አንደኛው ካሌንደር ከጎርጎሪያዊያን አቆጣጠር በሀምሳ ሰባት አመት እንደሚቀድም አስረድቷል፡፡ በሌላኛው ካሌንደር ደግሞ አዲስ አመት ኤፕሪል ላይ እንደሚውል ጠቅሷል፡፡

ዛሬ አዲስ አመትን የማታከብረው ሌላኛዋ አገር ደግሞ ኢራን ናት፡፡ ኢራን የሂጅራ ካሌንደርን ስለምትከተል አዲስ አመትን የምታከብረው ማርች 21 ቀን መሆኑንም ገልጿል፡፡ አራተኛዋ አገር ደግሞ አፍጋኒስታን ናት፡፡ የአፍጋኒታን ዘመን አቆጣጠር ከኢራን ጋር እንደሚቀራረብ ዘገባው ጨምሮ አስታውቋል፡፡

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

30 Dec, 19:18


በጋምቤላ ክልል ወርቅ ለማወጣት የውሃ እጥረት መሰናክል ሆኗል።

በክልሉ የሚገኙ የወርቅ አዉጪዎች  ከፍተኛ የዉሃ እጥረት እንደገጠማቸው ተሰምቷል።


በተለይም የበጋ ወቅትን ተከትሎ በወርቅ ማዉጪ አካባቢዎች ዉሃ አለመኖር በስራቸው ላይ ችግር እንደፈጠረ ሰምተናል።

በክልሉ የወርቅ ማዉጣት ላይ ተሰማርተው ያሉ አምራቾች ችግሩ ለስራቸዉ እንቅፋት እንደሆነባቸዉም ተገልፆል።

የጋምቤላ ክልል የማእድን ልማት ቢሮ የፍቃድ አሰጣጥ ዘርፍ ባለሙያ አቶ ሙት ሎንግ ይህ የዉሃ እጥረት የምርት ብክለት እንዲኖር ስለማድረጉ ለጣቢያችን ገልፀዋል።

በወርቅ ማዉጣት ሂደቱ ላይ ከፍተኛ የዉሃ ፍላጎት እንደሚኖር  ተነስቷል።

ሆኖም  የዉሃ አለመኖር በስራ ወቅት ወርቅን  ከአፈር ለማላቀቅ እንዳይቻል እና አስቸጋሪ እንዳደረገዉ አቶ ሙት ሎንግ ገልፀዋል።

በተጨማሪም ለወርቅ ቁፋሮ ሥራ የሚያገለግሉ ማሽነሪዎች ለማስገባት አመቺ የመንገድ የመሰረተ ልማት አለመኖር በአምራቾች ዘንድ ሌላዉ እንደ ችግር እየተነሳ መሆኑን አያይዘዉ አንስተዋል።

በአሁኑ ወቅት በክልሉ የወርቅ አወጣጥ ስርአቱን እንዲሁም ጥራቱን ለመጠበቅ በቴክኖሎጂ በመደገፍ እየተሰራ መሆኑን አቶ ሙት ሎንግ አያይዘዉ ገልፀዋል።

የወርቅ ምርት በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ውስጥ ቁልፍ ሚና ከሚጫወቱ የኤክስፖርት ምርቶች መካከል አንዱ ሲሆን የወርቅ ጥራት ጉድለት የገቢ መቀነስ ከሚያስከትሉ ችግሮች ዉስጥ ይቀመጣል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

30 Dec, 19:18


የሱማሌያው ኘሬዝዳን ከጂቡቲ ወደ ሀገራቸው ሲመለሱ የኢትዮጵያን አየር ክልል ላለመጠቀም ወይም ለመሸሽ በሶማሌ ላንድ በኩል በማለፍቸው ሶማሌ ላንድ የአየር ክልሌ ተጥሷል በማለት ከሳለች።

የሶማሊያው ፕሬዝዳንት የሶማሌላንድን ሉዓላዊ የአየር ክልል ያለፈቃድ ጥሰው በመግባት ዓለም አቀፍ ደንቦችን እና የሶማሊላንድን የግዛት መብቶች በመጣስ እየተከሰሱ ነው።

ፎከር 70 5Y-KBX በሚል ስም የተመዘገበ እና በኬንያ አየር መንገድ ስካይዋርድ ኤክስፕረስ የሚተዳደረው አውሮፕላኑ ከሶስት ሰአት በፊት የሶማሌላንድን የአየር ክልል አልፎ ወደ ሞቃዲሾ ሲመለስ የኢትዮጵያን ግዛት በመሸሽ ነው።

ሶማሊያላንዳዊያን<< ይህ ያልተፈቀደ ወረራ አፋጣኝ እርምጃ ይጠይቃል። አየር መንገዱ ይህንን ጥሰት በማቀላጠፍ ቅጣት ሊጣልበት ይገባል፤ ወደፊትም የሶማሊያ ባለስልጣናት የሶማሌላንድን የአየር ክልል እንዳይጠቀሙ ሙሉ በሙሉ መታገድ አለባቸው።

"የሶማሌላንድ አየር ክልል ሉዓላዊ ነው፣ እና ማንኛውም ያልተፈቀደ አጠቃቀም የራስ ገዝ ግዛቷን እና አስተዳደርን የሚነካ ነው።" ብለዋል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

30 Dec, 19:18


ከኢትዮጵያ ወደ ፑንትላንድ የሚገቡ ተሽከርካሪዎች የመግቢያ ክፍያ ቀረ!

ከኢትዮጵያ ወደ ፑንትላንድ የቦሳሶና አዲሱ ጋራኣድ ወደቦች ጭነት ለማንሳት የሚገቡ ተሽከርካሪዎች የመግቢያ ክፍያ ሲከፈሉ ቆይተዋል።የፑንትላንድ መንግስት የገንዘብ ሚኒስቴር ይህንን ክፍያ ወይንም ቀረጥን ማንሳቱን አስታውቋል።

በኢትዮጵያ መንግስት እና በሶማሊያ የፑንትላንድ መንግስት መካከል የንግድ እና ትብብርን ለማበረታታት ሁሉም ሃላፊዎች ከኢትዮጵያ ድንበር በተለይም በዶሎ የሚደርሰውን የጭነት ተሽከርካሪ ፍሰት እንዲያጠናክሩ ደብዳቤው ያሳያል።

ሁሉም የፑንትላንድ ኬላዎች የእንስሳት እና የንግድ ጭነት ተሽከርካሪዎች ወደ ጋራካድ እና ቦሳሳው ወደቦች እንዲደርሱ ያዛል።ይህ ውሳኔውም ለሚመለከታቸው አካላት ባሰራጨው በደብዳቤ ላይ ተገልጿል።

[ቅዳሜ ገበያ]

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

30 Dec, 19:18


''ከንቲባውን አገናኙኝ ብዬ ወደ ቢሮ ስልክ ስደውል 'የትኛውን ከንቲባ' ተብዬ እየጠየቃለሁ'' ሲል የህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም ተናገረ፡፡

''በሕወሃት ፓርቲ መካከል በተፈጠረው ልዩነት ምክንያት ህዝቡ እየተንገላታ ነው'' ሲል የህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም የመቀሌ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ተናግሯል፡፡በሕወሃት መካከል የተፈጠረው መከፋፈል ከተሞች ሁለት ከንቲባ እና አስተዳደሪ እንዲኖራቸው አድርጓል፡፡ይህም ተገልጋዩ ለእንግልት ዳርጓል ብሏል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቱ፡፡

የክልሉ ዋና ከተማ መቀሌ እና አዲግራትን ጨምሮ በክልሉ ያሉ አንዳንድ ወረዳዎች በጊዜአዊ አስተዳደሩም እና በእነ ደብረጺዮን ገ/ሚካኤል(ዶ/ር) በሚመራው ህወሃትም ከንቲባ እና አስተዳዳሪ ይሾምላቸዋል ሲሉ የጽህፈት ቤቱ ሃላፊ አቶ ፀሃዬ አንባዬ አስታውሰዋል፡፡

ይህም አንዱ ለአንዱ ስለማይታዘዝ ተገልጋዩ ጉዳዩን የሚፈጽምለት አጥቶ ተቸግሮ ነው ያለው ሲሉ አቶ ጸሃዬ እንባዬ አስረድተዋል፡፡በተመሳሳይ ወረዳ እና ከፍለ ከተማ ላይ ያሉ የስራ ሃላፊዎች  አንዱ የመራውን ደብዳቤ ሌላኛው እኔ የእገሌን ትዕዛዝ አልፈጽምም ይላሉ ሲሉ አቶ ጸሃዬ ተናግረዋል፡፡

በሌላ በኩል የህዝብ እምባ ጠባቂ ተቋም ራሱ የህዝብን አቤቱታ ለማስፈፀም መቸገሩን ነገሮናል፡፡በሕወሃት መካከል የተፈጠረው ልዩነት ከንቲባውን ፈልገን ስልክ ስንደውል እንኳን 'የትኛውን ከንቲባ' እየተባልን እየተጠየቅን ጉዳይ ለማስፈፀም ተቸግረናል ብሏል፡፡

Via Sheger

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

29 Dec, 19:05


በአዲስ አበባ በሬክተር ስኬል 5 ሆኖ የተመዘገበ ተደጋጋሚ የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረት ተሰማ
**************

በአዲስ አበባ ከተማ ዛሬ ምሽት 2 ሰዓት አካባቢ በሬክተር ስኬል 5 ሆኖ የተመዘገበ ተደጋጋሚ የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረት ተሰምቷል፡፡

በአዋሽ ፈንታሌ አካባቢ በተደጋጋሚ እየተከሰተ ባለው የመሬት መንቀጥቀጥ ምክንያት በአዲስ አበባ ተደጋጋሚ የመሬት ንዝረት መከሰቱን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂኦፊዚክስና ስፔስ ሳይንስ ዳይሬክተር ዶ/ር ኤሊያስ ሌዊ ለ EBC DOTSTREAM አረጋግጠዋል።

በዚህ ሳምንት በአዋሽ ፈንታሌ አካባቢ ያለው የመሬት መንቀጥቀጥ በተደጋጋሚ እየተከሰተ መሆኑን የገለጹት ዶ/ር ኤሊያስ፤ ምሽቱን በሬክተር ስኬል 5 ሆኖ የተመዘገበው የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረቱ በአዲስ አበባ በተደጋጋሚ መሰማቱን ተናግረዋል።

በአካባቢው ያለው የቅልጥ ዓለት ድንጋይ (ማግማ) እንቅስቃሴ አሁንም በመቀጠሉ የመሬት መንቀጥቀጥ በተደጋጋሚ እንዲከሰት ማስቻሉን ዶ/ር ኤሊያስ ጨምረው ገልጸዋል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

29 Dec, 17:20


በሲዳማ ክልል በደረሰ ከባድ የትራፊክ አደጋ 74   ሰዎች መሞታቸው ተሰምቷል

ዛሬ ታኀሣሥ 20 ቀን 2017 ዓ.ም በሲዳማ ክልል በቦና ዙሪያ ወረዳ በጋላና ወንዝ ድልድይ ላይ በደረሰው  አደጋ ከ74  በላይ  ሰዎች ህይወት አልፏል።

አደጋው  የተከሰተው አንድ አይሱዙ መኪና ከ70  በላይ  የሠርግ አጃቢዎች አሳፍሮ ወደ ዳዬ በንሳ መሥመር እየተጓዘ ሳለ የጋላና ድልድይን ጥሱ  ወደ ወንዙ በመግባቱ መሆኑ ተነግሯል ።

የሲዳማ ኒውስ ኔትዎርክ ከቦና ሆስፒታል አገኘሁት ባለው መረጃ  የሟቹች ቁጥር አሁን 74 ደርሷል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

24 Dec, 19:41


“የገቢዎች ቢሮ ያሳለፈው ውሳኔ የኢንዱስትሪ ሰላምን እንዳያውክ እሰጋለሁ”_የኢትዮጵያ ሆቴልና ቱሪዝም ፌደሬሽን

የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የደሞዝ ግብር ማጭበርበርን ለመቅረፍ እንደ ሆቴሎች እና ካፌቴሪያዎች ባሉ የተመረጡ የንግድ ተቋማት ላይ “ዝቅተኛ የደመወዝ ተመን እና የሰራተኛ ብዛትን” በተመለከተ ያሳለፈው ውሳኔ የኢንዱስትሪ ሰላምን እንዳያውክ እሰጋለኹ ሲል የኢትዮጵያ ሆቴልና ቱሪዝም ፌደሬሽን አስታወቀ።

የፌደሬሽኑ ፕሬዝደንት ዶ/ር ፍትህ ወልደሰንበት የቢሮው ውሳኔ የአሠሪና ሠራተኛ አዋጁን መሠረት ያላደረገና ዝቅተኛ የደመወዝ ወለልም እንደሃገር ገና በሂደት ላይ ባለበት ወቅት የተወሰነ መሆኑን መግለጻቸውን ቪኦኤ ዘግቧል።

"ውሳኔውን በተመለከተ ከንግድ ማህበረሰቡ ጋር በቂ ውይይት አልተደረገም" ያሉት ፕሬዝዳንቱ ዝቅተኛ የሠራተኛ ብዛትን በተመለከተ ንግድን በነጻነት ከትንሽ ተነስቶ ለማሳደግ አዳጋች እንደሚያደርገው ጠቁመዋል።

የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ሰውነት አየለ በበኩላቸው ከዚህ በፊት እንደ ምግብ እና መጠጥ ቤቶች ያሉት የንግድ ተቋማት ለሠራተኞቻቸው ስለሚከፍሉት ደመወዝ በአግባቡ እንደማይገልጹ ጠቅሰው የግብር ማጭበርበርን ለማስቀረት አዲስ አሰራር መዘርጋቱን አመልክተዋል።

በዚህም ቢሮው ለሆቴሎች፣ ለካፊቴሪያዎች፣ ለምግብ እና መጠጥ ቤቶች እንዲሁም ለሥጋ ቤቶች ዝቅተኛ የሰራተኛ ብዛት ተመን እና ዝቅተኛ የሰራተኞች ደመወዝ ወለል ማስቀመጡን ተናግረዋል።

አክለውም ይህ አዲስ አሰራር አነስተኛ የንግድ ተቋማትን እንደማይመለከት ገልጸው የንግድ ሥርዓቱን የሚያውክ ነገር የለም ብለዋል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

23 Dec, 20:15


በፈንታሌ ተራራ ፍንዳታና ጭስ የታየበት በሬክተር ስኬል 4 ነጥብ 6 የሆነ  የመሬት መንቀጥቀጥ ተከሰተ

በአዋሽ ፈንታሌ ተራራ በሬክተር ስኬል 4 ነጥብ 6 የሆነ የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂኦፊዚክስ፣ ሕዋ ሳይንስና አስትሮኖሚ ኢንስቲትዩት አስታውቋል።

በዩኒቨርሲቲው የጂኦ ፊዚክስ ሕዋ ሣይንስና አስትሮኖሚ ተቋም የሴስሞሎጂ ትምህርት ክፍል ኃላፊ፣ የመሬት መንቀጥቀጥ ሣይንስ መምህርና ተመራማሪ አታላይ አየለ (ፕ/ር) እንዳሉት፥በአዋሽ ፋንታሌ ወረዳና አካባቢው ከታሕሣሥ 10 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ የተለያየ መጠን ያለው የመሬት መንቀጥቀጥ እየተከሰተ ነው፡፡

በዛሬው ዕለትም ከቀኑ 9 ሰዓት አካባቢ ሰሞኑን ከተከሰቱት ከፍተኛውና በሬክተር ስኬል 4 ነጥብ 6 የሆነ የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን ለፋና ዲጂታል ተናግረዋል።

የመሬት መንቀጥቀጡን ተከትሎም ተራራው የመሰንጠቅ እና የመደርመስ ምልክት ማሳየቱን ነው ያስረዱት፡፡

በአካባቢው የሚስተዋለው የመሬት መንቀጥቀጥ ከቀን ቀን እየጨመረ መምጣቱን ጠቁመው÷ነዋሪዎች ላይ ችግር እንዳያስከትል የቅርብ ክትትል ማድረግ እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል፡፡

በአፋር ክልል የዞን 3 ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብዶ አሊ አቡበከር በኩላቸው÷ዛሬ ከሰዓት በአዋሽ ፈንታሌ ተራራ የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ የፍንዳታ ድምጽ ያስከተለ እና ጭስ የታየበት ነው ብለዋል፡፡

በመሬት መንቀጥቀጡ የፍንዳታ ድምጽ መሰማቱ እና ጭስ መታየቱም በአካባቢው ነዋሪዎች ዘንድ ድንጋጤ መፈጠሩን ማብራራታቸው ተገልጿል፡፡

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

23 Dec, 08:50


የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌደሬሽን አዲስ የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት ታውቀዋል፡፡

በ28ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ጉባዔተኛው የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላትን መርጧል።
በእጩነት ከቀረቡት 14 ወንድ እና 12 ሴት ተመራጮች መሃል
1. አትሌት መሰረት ደፍር -18
2. ወ/ሮ ሳራ ሀሰን - 16
3. ወ/ሮ አበባ የሱፍ - 13
4. ዶ/ር ኤፍራህ መሀመድ -12
5.  አቶ ቢንያም ምሩፅ ይፍጠር- 10
6. አቶ አድማሱ ሳጅን - 10
7. ኢንጂነር ጌቱ ገረመው - 9
8. ዶ.ር ትዛዙ ሞሴ - 11
ድምጾችን በማግኘት የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት ሆነው ተመርጠዋል።

በብሩክ ገነነ

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

23 Dec, 08:49


ከኮሪደር ልማት የፍርስራሽ ግምት ለግል ጥቅማቸው ሊያውሉ የሞከሩ 3 አመራሮች በቁጥጥር ስር መዋላቸው ተገለጸ

በአዲስ አበባ መንግስትና ህዝብ የጣለባቸውን ሃላፊነት ወደ ጎን በመተው ከኮሪደር ልማት የፍርስራሽ ግምት ለግል ጥቅማቸው ሊያውሉ የሞከሩ 3 አመራሮች በከተማው የፀጥታ አካላት በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ።

በቁጥጥር ስር የዋሉት አመራሮቹ፤ የየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 06 ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ራሄል ኃ/ኢየሱስ ጨምሮ የወረዳው ስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ደበበ ጉልማ፣ የወረዳው የፋይናስ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ታደለ ግዛቸው መሆናቸውን የከተማ አስተዳደርሩ ትናንት ባወጣው መግለጫ ገልጿል።

ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ስር የዋሉት በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 06 በካዛንችስ የኮሪደር ልማት ላይ ባልተገባ አካሄድ የፍርስራሽ ግምት ለግል ጥቅም ለማዋል በመሞከር ላይ እያሉ የሰላምና ፀጥታ ቢሮ ከከተማ እስከ ክ/ከተማ የፀጥታ መዋቅሩን በመጠቀምና ክትትል በማድረግ መሆኑን ተገልጿል።

በዚህም መሠረት የወንጀል ማጣራት ሂደቱ በሚመለከተው አካል እየተካሄደ ይገኛል ያለው መግለጫው አስተዳደሩ ሌብነትና ብልሹ አሰራር የልማታችን ዕንቅፋት እንዳይሆን ተገቢውን እርምጃ ወስዷል ብሏል፡፡

አስተዳደሩ “አስተዳደሩ የከተማዋን ፈተናዎች ባሏት ፀጋዎቿ በማሻገር ሁለንተናዊ ብልፅግናዋን ለማረጋገጥ በሚጥርበት በዚህ ወቅት የኮሪደር ልማትን መነሻ በማድረግ የግል ፍላጎታቸውንና ጥቅማቸውን ለማስጠበቅ የሚሯሯጡ አልጠፉም” ሲሉም ገልጿል።

በቀጣይም የተጀመሩ ልማቶቻችንን በማሳለጥ ሌብነት ላይ የሚደረገው ትግል ተጠናክሮ ይቀጥላል ብሏል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

23 Dec, 08:48


የአለም ባንክ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን ጨምሮ ሶስት ባንኮችን አሰራር ለማሻሻል የሚውል 700 ሚሊየን ዶላር ብድር መስጠቱ ተጠቆመ

የአለም ባንክ ኢትዮጵያ ለምታካሂደው የፋይናንስ ስርአት ማሻሻያ የሚውል 700 ሚሊየን ዶላር ብድር መስጠቱ ተገለጸ፤ ብድሩ የሚውለው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን መልሶ ለማደራጀት፣ ብሔራዊ ባንክንና የልማት ባንክን አሰራር ለማሻሻል መሆኑም ተጠቁሟል።

ብድሩን ያጸደቀው አለም አቀፉ የልማት ማህበር (IDA) መሆኑን ባንኩ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።

ማህበሩ ብድሩን ያጸደቀው የሀገሪቱ የገንዘብ ስርአት ቀጣይነት ያለው እና የተረጋጋ እንዲሆን ለሚተገበሩ ፕሮጀክቶች በሚል መሆኑን ባንኩ ጠቁሟል።

የኢትዮጵያ የፋይናንስ ዘርፍ በርካታ አሳሳቢ ፈተናዎች የተጋረጠ ነው ሲል የገለጸው የአለም ባንክ መግለጫ በተለይም በቂ ያልሆነ የቁጥጥር ማዕቀፎች ያሉት እና የህዝብ የፋይናንስ ተቋማቱ እጅግ ደካማ መሆናቸው ነው ሲል አመላክቷል።

የማሻሻያ ፕሮጀክቱ በዋናነት እነዚህን ችግሮች የሚፈቱ አሰራሮችን ለመዘርጋት ይውላል ሲል ገልጿል፤ ከፕሮጀክቶቹ መካከልም የብሔራዊ ባንክ የክትትልና የቁጥጥር ማዕቀፍን ማዘመን አንዱ መሆኑን ጠቁሟል።

የአለም ባንክ ከፈቀደው ብድር ውስጥ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን የአስተዳደር ስርአት ማሻሻል፣ የባንኩን የሒሳብ መዛግብት መልሶ ማዋቀር እና ባንኩን መልሶ ማደራጀት የሚያስችል ፕሮጀክት መተግበሪያም የሚሆን እንደሚገኝበት አመላክቷል።

ሌላኛው ብድሩ የሚውለው ልማት ባንክ ወደ ዘላቂ ልማት ፋይናንስ ተቋምነት ለማሸጋገር ለሚተገበሩ ፕሮጀክቶች መሆኑንም አስታውቋል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

23 Dec, 08:48


በአዲስ አበባ በስድስት ክፍለ ከተሞች የሥምና ንብረት ዝውውር ታገደ!

በአዲስ አበባ ከተማ ለመሬት ይዞታ ማረጋገጥ ሥራ ሲባል ለቀጣይ 5 ወራት በስድስት ክፍለ ከተሞች እና በተመረጡ ወረዳዎች የሥምና ንብረት ዝውውር መታገዱን የከተማዋ መሬት ይዞታ ምዝገባና መረጃ ኤጄንሲ አስታውቋል።ኤጄንሲው ከመሬት ይዞታ ጋር ተያይዞ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የገለጸ ሲሆን፤ ለዚህም ዘመናዊ ሁለገብ ካዳስተር ግንባታ ስርዓት በመዲናዋ ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ለማድረግ ሥራ መጀመሩን አመልክቷል፡፡

አሁን ላይ ከአዲስ አበባ ጠቅላላ የቆዳ ስፋት ውስጥ 54 በመቶ ለሚሆነው የመሬት ይዞታ ማረጋገጥ ሥራ መሰራቱን ገልጿል።በተያዘው በጀት ዓመት ለመጨረሻ ጊዜ በ136 ቀጠናዎች የሚገኙ ይዞታዎችን አረጋግጦ ለመመዝገብ እየተሰራ መሆኑንም አመላክቷል።በዚህ መሠረትም የይዞታ ማረጋገጥ ሥራው በተመረጡ ስድስት ክፍለ ከተሞች በቀጣይ አምስት ወራት ውስጥ እንደሚከናወን ተጠቅሷል።

ክፍለ ከተሞችም የካ፣ ለሚ ኩራ፣ አቃቂ ቃሊቲ፣ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ፣ቦሌ እና ኮልፌ ቀራኒዮ መሆናቸው ተገልጿል።ለመሬት ይዞታ ማረጋገጥ ሥራው ሲባልም ምዝባ በሚካሄድባቸው የክ/ከተሞቹ ወረዳዎች እስከ ቀጣዩ ሚያዝያ ወር ድረስ የሥምና ንብረት ዝውውር መታገዱ ተገልጿል።ባለይዞታዎች ከታሕሣሥ 20 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 10 ቀናት የይዞታ ይረጋገጥልኝ ማመልከቻ እንዲያቀርቡም ጥሪ ቀርቧል።

Via Ahadu

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

22 Dec, 11:52


''ምርጫው ፍትሀዊ አይደለም'' የተከበሩ አቶ ዱቤ ጁሎ

ለኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ምርጫ እጩ ሆነው የተወዳደሩት ዱቤ ጁሎ(የተከበሩ) ምርጫው ፍትሀዊ አይደለም ሲሉ ለጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ(ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል) ተናግረዋል።

በሀገር ላይ ከፍተኛ ደባ እየተሠራ ነው፤እኔ ይሄንን ፍትሃዊ ምርጫ ነው ብዬ አልቀበልም ያሉት አቶ ዱቤ ምርጫው ያለቀለት ነው ወደ ጉባኤው አትሂድ ተብዬ ነበር፤ በጉባኤውም የገጠመኝ ይኸው ነው ሲሉ ተናግረዋል

ሌላው ቢቀር የወከለኝ ክልል እንዴት አንድ ድምፅ ይነፍገኛል፤ይሄ ራሱ የምርጫውን ፍትሃዊ አለመሆን ያሳያል ባለመመረጤ አልበሳጭም በአትሌቲክሱም ተስፋ አልቆርጥም ሲሉ ከውጤቱ በኋላ ምልከታቸውን አጋርተዋል።

ባላገሩ ስፖርት

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

22 Dec, 10:08


ሰበር ዜና!

አትሌት ስለሺ ስህን ፕሬዝዳንት ሆኖ ተመረጠ!

አትሌት ስለሺ ስህን የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌደሬሽን ፕሬዝዳንት ሆኖ ተመረጠ።

የኢትዮጵያ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን 28ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔውን አድርጎ ኮማንደር አትሌት ስለሽ ስህንን ለቀጣይ አራት አመታት በፕሬዝዳንትነት እንዲያገለግል ተመርጧል።

አዲሱ ተመራጭ ፕሬዝዳንት አትሌት ስለሽ ስህን 45 ድምፅ በማግኘት ተወዳዳሪዎቹን አሽንፏል።

በዚህ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ላይ አትሌት ገ/እግዜአብሄ ገ/ማሪያም፣ የተከበሩ አቶ ዱቤ ጅሎ ፣ ወ/ሮ ሪሳል ኦፒዮ ፣ ኮማንደር ግርማ ዳባ እና አቶ ያየ ሀዲስ መወዳደራቸው ይታወሳል። Hagere tv

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

20 Dec, 14:02


የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በኢነርጂ ፍጆታዎች ላይ ተጨማሪ እሴት ታክስ ተግባራዊ ማድረጉን አስታወቀ

የኢትዮጵያ ኤሌትሪክ አገልግሎት ከ200 ኪሎ ዋት ሰዓት በላይ በሚጠቀሙ ደንበኞች የፍጆታ ሂሳብ ላይ እና አዲስ ደንበኛ ማገናኘትን ጨምሮ ደንበኞች በሚፈፅሟቸው ልዩ ልዩ የአገልግሎት ክፍያዎች ላይ የተጨማሪ እሴት ታክስ ተግባራዊ ማድረጉን አስታውቋል ።

ይህን ተከትሎ ደንበኞች ወርሃዊ የፍጆታ ሂሳብ በሚከፍሉበት ወቅት የፍጆታ መጠናቸው ከ200 ኪሎ ዋት ሰዓት በላይ ከሆነ እላፊ የመጣው የፍጆታ መጠን የተጨማሪ እሴት ታክስ ተሰልቶ ሂሳባቸው ላይ የሚደመር እንደሚሆን ተሰምቷል።

ተቋሙ የተጨማሪ እሴት ታክስ ( VAT)  ተግባራዊ ያደረገው ከህዳር ወር የክፍያ ደረሰኝ ጀምሮ ሲሆን፤ የድህረ ክፍያ ተጠቃሚ ደንበኞች ከመስከረም ወር ጀምሮ ያለባቸውን የኋላ ክፍያ በታህሳስ ወር በሚወጣው ቢል ላይ ተጨምሮ እንደሚከፍሉ ተገልጿል ።

በተመሳሳይ የቅድመ ክፍያ ተጠቃሚ ደንበኖችም ከመስከረም ወር ጀምሮ ባላቸው የፍጆታ መጠን መሠረት የኋላ ክፍያ በቀጣይ የሚከፍሉ ሲሆን ከዚህ በተጨማሪ ደንበኞች ለተቋሙ በሚከፍሉት ልዩ ልዩ ክፍያዎች ላይም ተግባራዊ የሚደረግ መሆኑን ነዉ ከተቋሙ የተገኘው መረጃ የሚያሳየዉ።

የገንዘብ ሚኒስቴር ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነፃ የሚሆነውን መኖሪያ ቤት የኤሌክትሪክ ኃይልና የውኃ የፍጆታ መጠን ለመወሰን ባወጣው አዋጅ ቁጥር 1341/2016 መመሪያ እና አዋጁን ለማስፈፀም በወጣው መመሪያ ቁጥር 1021/2016 መሠረት ክፍያዉ ከመስከረም ወር ጀምሮ ከ200 ኪሎ ዋት ሰዓት በላይ የተጠቀሙ ደንበኖች ላይ ተግባራዊ መደረግ መጀመሩን ነዉ ለማወቅ የተቻለው ።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

19 Dec, 18:46


አማራ ባንክ የባለአክስዮኖችን ጠቅላላ ጉባኤ በበይነ መረብ አማካኝነት የማድረግ እቅድ እንዳለው አስታወቀ

አማራ ባንክ ባለአክሲዮኖች በአካል ስብሰባ ላይ መገኘት ሳይጠበቅባቸዉ ከየትኛውም ቦታ ሆነው ዲጂታል መድረኮችን በመጠቀም መሳተፍ የሚያስችላቸውን አሰራር ሊዘረጋ መሆኑን አስታውቋል ።

አሁን ላይ ከ 169 ሺህ በላይ ባለአክሲዮኖች ያሉት ባንኩ የበጀት ዓመቱን ጠቅላላ ጉባኤ በሚያደርግበት ወቅት በቂ መሰብሰቢያ ቦታ እና መሰል አሰራሮች አለመኖራቸው አስቸጋሪ ማድረጉን ጠቁሟል።

ባንኩ ከፍተኛ የሆነ ባለአክሲዮኖች ያሉት በመሆኑ እነርሱን ማስተናገድ የሚያስችል ስፍራዎች አለመኖር አሰራሩን እንዲቀር ካደረገዉ ምክንያት መካከል ይገኝበታል።

የአማራ ባንክ ዋና ስራ አስፈፃሚ ዮሐንስ አያሌው ( ዶ/ር) ሌሎች ሀገሮች እየሰሩበት ያለዉን አሰራር እኛ ጋር እንዲፈቀድልን ጥያቄ አቅርበናል እና ተስፋ መኖሩን አስረድተዋል ።

የዘንድሮው የባንኩ 3ኛዉን መደበኛ የባለአክስዮኖች ጠቅላላ ጉባኤ ላይ በተሳታፊዎች መጨናነቁን ያስታወሱት ዮሐንስ አያሌዉ (ዶ/ር) ዘንድሮ የነበሩ ችግሮች እንደ መማሪያ አድርገን ወስደናቸዋል ሲሉም ተደምጠዋል ።

አሁን ግን ይህንን ለማስቀረት ወደ ዲጅታል አማራጮች የመሄዱ ጉዳዮች መኖራቸውን ዮሐንስ አያሌዉ ጨምረዉ ተናግረዋል ።

ምናባዊ ( Virtual) አመታዊ አጠቃላይ ስብሰባ ባለአክሲዮኖች እና ተኪዎቻቸው በአካል ሳይገኙ ሙሉ በሙሉ በበይነ-መረብ ላይ የሚያካሄዱ ሲሆን በሰልፍ የነበረዉ የምዝገባ ሂደት በተመሳሳይ በኪዉ አር ስርዓት አማካኝነት መመዝገብ የሚችሉበት አሰራር በዚህ ዓመት እንደሚዘረጋ እና ይህን ለማሳካት ወደ ዝግጅት እየገባ መሆኑን ባንኩ አስታውቋል ።

ይህ የተገለፀው ባንኩ ያበለፀገዉን ፈጣን ምላሽ ( QR) መተግበሪያ አባ ኪዉ አር (ABa QR) ስራ ባስጀመረበት ወቀት ነዉ።

መተግበሪያዉ ተገልጋዮች ማንኛውንም አይነት ግብይት ሲፈጽሙ የእጅ ስልካቸውን ብቻ ተጠቅመው በግብይት ማዕከሉ የሚገኘውን የነጋዴውን (QR Code) ቅኝት በማድረግ ያለ ጥሬ ገንዘብ ከማንኛውም የባንክ ሂሳባቸው በቀላሉ ክፍያ መፈጸም የሚችሉበት እንደሆነም ለማወቅ ተችሏል። Capital newspaper

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

19 Dec, 18:44


የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን ከሁለት ቀናት በፊት ለ10 (አሥር) የመድኃኒት ምርቶች የመድኃኒት ደህንነት ማስጠንቀቂያ ሰጠ።

በኢትዮጵያ ገበያ የሚዘዋወሩ አሥር (10) የፀረ ወባ መድሐኒቶች በመመሪያው በተቀመጡት ዝቅተኛ የጥራት መመዘኛዎች የጥራት ቁጥጥር ወድቀው መገኘታቸውን የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን አስታወቀ።

ባለስልጣኑ ህብረተሰቡ እና ባለድርሻ አካላት በማንኛውም መልኩ መጠቀማቸውን እንዲያቆሙ ጥሪ አቅርቧል። ኤጀንሲው በምርቶቹ ወይም በምርቶቹ አቅራቢዎች ላይ የተወሰደውን የቁጥጥር እርምጃ አልገለጸም።

እባክዎን ኤጀንሲው ያወጣውን ዝርዝር እና የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ ያግኙ።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

18 Dec, 07:21


ባንኮች ያለምንም ማስያዣ ከብሔራዊ ባንክ እንዲበደሩ ይፈቅድ የነበረዉ ድንጋጌ ከረቂቅ አዋጁ ተሰረዘ

ብሔራዊ ባንክ ጊዜያዊ የገንዘብ እጥረት የገጠመው ሆኖ ዕዳውን ግን መክፈል ለሚችል ባንክ ጊዜያዊ ብድር ሊሰጥ እንደሚችል የሚገልጸው ድንጋጌ ከረቂቅ አዋጁ ላይ እንዲሰረዝ ተደርጓል።

በዚህም ማዕከላዊ ባንኩ ያለመያዣ ለባንኮች ይሰጥ የነበረዉ ብድር የሰረዘ ሲሆን እንደምክንያት ያስቀመጠዉ የመንግስትን ገንዘብ ያለ በቂ ዋስትና መስጠት ተገቢነት ያለው አሠራር ባለመሆኑ እና  የህዝብን ጥቅም እንደሚጎዳ ስለታሰበበት መሆኑን ጠቁሟል።

ይህን ተከትሎ ብሔራዊ ባንክ ያለመያዣ ይሰጥ የነበረዉ የብድር አሰራር እንዲቀር የተደረገ ሲሆን ባንኮችም ብድር ሲፈልጉ ዋስትና ማቅረብ እንዳለባቸው በአዋጁ አሳስቧል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ረቂቁ ባንኮች ከብሔራዊ ባንክ የወሰዱትን ብድር የመመለሻ ጊዜ በ 6 ወራት ዉስጥ መሆን አለበት የሚል ሲሆን አሁን ግን " የብድር መመለሻ ጊዜ በአዋጅ ከመደንገግ ይልቅ በመመሪያ እንዲሆን መወሰኑን በተሻሻለዉ የብሔራዊ ባንክ ማቋቋሚያ አዋጅ ላይ አስቀምጧል ።

Via Capital Newspaper

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

16 Dec, 15:42


የውጭ ሀገራት ባንኮች ወደ ሀገር ውስጥ እንዲገቡ የሚፈቅደው የባንክ ሥራ ረቂቅ አዋጅን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ነገ መርምሮ እንደሚያፀድቅ ተገለፀ፡፡

6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን በ11ኛ መደበኛ ስብሰባው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ረቂቅ አዋጅን አስመልክቶ ከተወያየ በኋላ እንደሚያፀድቅ ይጠበቃል፡፡

በነገው መደበኛ ስብሰባ የፕላን በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና የባንክ ስራ ረቂቅ አዋጅን አስመልክቶ ለምክር ቤቱ ሪፖርትና የውሳኔ ሀሳብ የሚያቀርብ ይሆናል፡፡

ረቂቅ አዋጁ ሰኔ 18 ቀን ፣ 2ዐ16 ዓ/ም ለፕላን በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የተመራ ሲሆን ምክር ቤቱ፤ ቋሚ ኮሚቴው የሚያቀረበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሀሳብ መርምሮ አዋጁን እንደሚያፀድቅም ይጠበቃል፡፡

ረቂቅ አዋጁ ሲጸድቅ የውጭ ባንኮች በሃገር ውስጥ ተቀጥላ ወይም ሰብሲዲያሪ ጽህፈት ቤታቸውን እንዲከፍቱ ከመፍቀዱ በተጨማሪም የሀገር ውስጥ ባንኮችን ድርሻ መግዛት እንዲችሉ የሚፈቅድም ነው፡፡

ከዚህም ባሻገር የውጭ ባንኮች ቅርንጫፎቻቸውን እንዲከፍቱ፣ ኢትዮጵያውያንና የውጭ ሀገራት ዜጎችም በባንኮቻቸው የሥራ እድልን ማግኘትና የቦርድ ሊቀመንበር አባላት እንዲሆኑ መንገዱን የሚያቀናላቸው ነው ይኸው ረቂቅ አዋጅ፡፡

መንግስትም የአዋጁን መጽደቅ ተከትሎ ለአምስት የውጭ ባንኮች ፈቃድ ለመስጠት ያስችለዋል፡፡

በኢትዮጵያ ገበያ ለመሥራት ፍላጎት ካሳዩ የውጭ ባንኮች ውስጥ የኬንያው ኬሲቢ እንዲሁም ስታንዳርድ ባንኮች ይጠቀሳሉ፡፡

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

16 Dec, 15:26


የቀድሞው ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን የመሠረቱት ፋውንዴሽን ይፋ ሆነ

የቀድሞው ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን የመሠረቱት "የአዳም ፋውንዴሽን" የተሰኘ መንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት ምሥረታውን ይፋ አድርጓል።

አቶ ደመቀ መኮንን በቦርድ ሊቀመንበርነት የሚመሩት "የአዳም ፋውንዴሽን"፤የመንግስት ባለስልጣናት እና ዓለም አቀፍ ተቋማት በተገኙበት ይፋዊ የማብሰሪያ ሥነ ሥርዓቱን በዛሬው ዕለት ተከናውኗል።

ለኢትዮጵያ ብሎም ለአፍሪካ ልማትና እድገት በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ የገለፁት የፋውንዴሽኑ መስራች አቶ ደመቀ መኮንን፤ በተለይ ህፃናትና እናቶች ላይ በመስራት ብሎም መቀንጨርን በመዋጋት ደህንነቱ የተጠበቀ ትውልድ ለመፍጠር በትኩረት እንደሚሰሩ ገልፀዋል።

"በአፍሪካ መቀንጨርን መግታት" የሚል መሪ ሀሳብ ያለው ፋውንዴሽኑ፤ ከኢትዮጵያ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ባለሥልጣን የምዝገባ የምስክር ወረቀት ያገኘው ባለፈው ዓመት ግንቦት ወር ላይ እንደነበር ተገልጿል።

"የአዳም ፋውንዴሽን" በሥነ ምግብ ላይ መስራት ዋና ዓላማው ያደረገ ሲሆን መቀንጨርን ለመግታት የሚያስችሉ ባለብዙ ዘርፍ ፕሮግራሞችን በመቅረፅ ይሰራል ተብሏል።

EBC

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

16 Dec, 13:39


የቱርኩ ፕሬዝዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን ኢትዮጵያን ሊጎበኙ ነው!

የቱርኩ ፕሬዝዳንት ጣይብ ኤርዶጋን፣ በኢትዮጵያና ሱማሊያ ይፋዊ ጉብኝት ሊያደርጉ ማቀዳቸውን አስታውቀዋል። ፕሬዝዳንት ኤርዶጋን በኹለቱ አገራት ጉብኝት ለማድረግ ያቀዱት፣ ከቀጣዩ ጥር እስከ የካቲት ወር ባለው ጊዜ ውስጥ እንደኾነ ገልጸዋል። ፕሬዝዳንቱ ይፋዊ ጉብኝት እንደሚያደርጉ የገለጡት፣ ኢትዮጵያ ባለፈው ዓመት ጥር ወር ከሶማሌላንድ ራስ ገዝ ጋር በተፈራረመችው የባሕር በር የመግባቢያ ስምምነት ሳቢያ በኹለቱ አገራት መካከል በባሕር በር ዙሪያ የተፈጠረውን ዲፕሎማሲያዊ ቁርሾ አንካራ ላይ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይንና ፕሬዝዳንት ሐሰን ሞሐመድን በማሸማገል በፈቱ ማግስት ነው።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

16 Dec, 13:39


የኦሞ ኩራዝ ቁጥር 3 ስኳር ፋብሪካ ስኳር የማምረት ሥራውን ጀመረ

የኦሞ ወንዝን በሚያዋስኑ በካፋና ቤንች ማጂ ዞኖች የሚገኘው የኦሞ ኩራዝ ቁጥር 3 ስኳር ፋብሪካ የክረምት ጥገናው ከተጠናቀቀ በኋላ የ2017ዓ.ም የስኳር ምርት ሥራ መጀመሩን የኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ አስታውቋል።ፋብሪካው ከታህሳስ 5 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮም ስኳር በማውጣት ላይ እንደሚገኝ የግሩፑ መረጃ አመላክቷል።

ጥቅምት 4 ቀን 2011 ዓ.ም. ስራ የጀመረው ፋብሪካው በቀን 12,000 ኩንታል ስኳር የማምረት አቅም እንዳለው ይታወቃል።የኦሞ ኩራዝ ቁጥር 3 ስኳር ፋብሪካ ስኳር የማምረት ሥራውን ከመጀመሩ በፊት በኢትዮጵያ ካሉ ስምንት የስኳር ፋብሪካዎች መካከል በስራ የበነረው አንዱ ብቻ እንደነበር ዘገባዎች አመላክተዋል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

09 Dec, 14:23


በታክስ ደረሰኞች ላይ ልዩ መለያ ኮድ ተካቶበት እንዲታተም የሚያስገድደዉ መመሪያ ከቀጣይ ወር ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚደረግ ተገለፀ!

መንግስት ከታክስ የሚያገኘው ገቢ ለማሳደግ ዓላማ ያደረገዉ እና ሁሉም ግብር ከፋዮች የደረሰኝ ህትመት ላይ ልዩ መለያ ኮድ (QR-Code) እንዲኖረዉ የሚያስገድደዉ መመሪያ ተግባራዊ መሆን የሚጀምረው ከየካቲት ወር ጀምሮ መሆኑን የገቢዎች ሚኒስትር በሰጠዉ ማሳሰቢያ አስታውቋል ።

የታክስ ደረሰኝ አጠቃቀም እና አስተዳደር መመሪያን ለማሻሻል የወጣውን መመሪያ 188/2017 ያስታወሰዉ ሚኒስትሩ ሚስጥራዊነቱ በተጠበቀ መልኩ እያንዳንዱ የደረሰኝ ቅጠል ሲታተም ልዩ መለያ ኮድ (unique QR code) ተካቶ እንዲመታተም እና ጥቅም ላይ እንዲውል ለማድረግ የመጨረሻው ምዕራፍ ላይ መድረሱን ገልጿል።

ይህን ተከትሎ በህትመት ዘርፉ ከ 100 ዓመታት በላይ ልምድ ካለዉ እና ከመንግስታዊዉ የህትመት ድርጅት ከሆነዉ ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ጋር የመግባቢያ ሰነድ ስምምነት ማድረጉን ጠቁሟል።

ባለፉት ጊዜያት የማንዋል ደረሰኝ አስተዳደርን ውጤታማ ለማድረግ ዘርፈ ብዙ ስራዎች የተሰሩ ቢሆንም የሀሰተኛ ደረሰኝ ህትመት መበራከት በግብር አሰባበሰቡ ላይ ፈተና ሆኖ ስለመቆየቱ ተሰምቷል።

ሁሉም የታክስ ከፋዮች ከታህሳስ 01 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ የማንዋል ደረሰኝ የመሳተም ጥያቄያቸውን ማቅረብ የሚቻል መሆኑን የተመላከተ ሲሆን  ከየካቲት 01 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ደግሞ ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮችን ጨምሮ በመላው ሀገሪቱ በብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት ብቻ የታተም የማንዋል ደረሰኝ መጠቀም እንዳለባቸው ሚኒስትሩ ማሳሰቢያ ሰጥቷል።

Capital

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

09 Dec, 14:22


"...አርቲስት ሀረገወይን አሰፋ ህዝብን ዋሽታለች። ለአዲስ አበባ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ስራ አስፈፃሚነት በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በእጩነት ተወክላ ስትመጣ ፎቶግራፏን እና ፊርማዋን አስፍራ ወዳ እና ፈቅዳ ራሷ የክፍለ ከተማው ነዋሪ ነኝ እጩ መሆን እፈልጋለሁ ብላ ጠይቃ ነው። እሷ ግን እኔ ሳላውቅ ነው የመረጡኝ ፣ስለ ምርጫው አላውቅም በሶሻል ሚዲያ ነው መመረጤን ያወኩት ብላ መናገሯ እጅግ ከእሷ የማይጠበቅ ነው።"

- የአዲስ አበባ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ስለ አርቲስት ሀረገወይን አሰፋ "ለሲዲ ስፖርት" የሰጠው ምላሽ

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

08 Dec, 17:56


በአዲስ አበባ ከተማ በተለያዩ አከባቢዎች የተሰማው የጦር መሣሪያ ድምፅ የመንግስትን የሰላም ጥሪ ተቀብለው ወደ ተሃድሶ ሥልጠና ማዕከላት በሚጓዙ የቀድሞ የኦነግ ታጣቂ ቡድን አባላት የተሰማ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ         

በአዲስ አበባ ከተማ በተለያዩ አከባቢዎች የተሰማው የጦር መሣሪያ ድምፅ የመንግስትን የሰላም ጥሪ ተቀብለው ወደ ተሃድሶ ሥልጠና ማዕከላት በሚጓዙ የቀድሞ የኦነግ ታጣቂ ቡድን አባላት የተሰማ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል፡፡

መንግሥት በሀገሪቱ የተለያዩ አከባቢዎች ታጥቀው ለሚንቀሳቀሱ ቡድኖች ባቀረበው የሠላም ጥሪ መሠረት የኦነግ ታጣቂ ኃይል አባላት የሰላም ጥሪውን ተቀብለው በስፋት እየገቡ መሆኑ ይታወቃል። 

የታጣቂ  ቡድኑ አባላትን ወደ ተዘጋጀላቸው የተሃድሶ ስልጠና ማዕከላት የማጓጓዝ ስራ በስኬት እየተከናወነ ይገኛል። 

በዚህ መሀል ታጣቂዎቹ አዲስ አበባ ከተማን አቋርጠው ወደ ስልጠና ማዕከላት በሚንቀሳቀሱበት ወቅት እየጨፈሩና የደስታ ስሜት እያሰሙ ሲንቀሳቀሱ የተኩስ ድምጽ በማሰማታቸው በከተማው ነዋሪ ህዝብ ላይ ድንጋጤና መረበሽ ሊፈጠር መቻሉን ፖሊስ ገልጿል።

ለተፈጠረው የዜጎች ድንጋጤና መረበሽ ይቅርታ የጠየቀው የአዲስ አበባ ፖሊስ፤ በቀጣይ ተመሳሳይ ችግሮች እንዳይፈጠሩ ከፍተኛ ጥንቃቄና የማስተካከያ እርምጃ የሚወሰድ መሆኑን አስታውቋል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

08 Dec, 10:09


የተማሪዎች የምግብ በጀት ተመን ማሻሻያ ተደረገ

መንግስት የተማሪዎች የምግብ በጀት ተመን በነፍስ ወከፍ ለአንድ ተማሪ ወደ 100 ብር ማሳደጉን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታውቋል ።

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በተደጋጋሚ ይህን የተማሪዎች የምግብ ተመን ጉዳይ ሲያነሱ እንደነበረ ያስታወሰው ጽህፈት ቤቱ በቀጣይም በጀቱን ለተፈለገው አላማ እንዲውል አሳስቧል ።

ከመጪው ታህሳስ 1 ቀን 2017  ጀምሮም ይህ መመሪያ ተግባራዊ እንደሚሆን ነው የተገለጸው ።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

08 Dec, 07:56


የሶሪያው ፕሬዚዳንት ዋና ከተማዋን አስረክበው ፈረጠጡ

የሶሪያ አማፅያን የአገሪቱን መዲና ደማስቆን በእጃቸው ማስገባታቸውን ተከትሎ  ፕሬዝዳንቱ መሸሻቸው ተነግሯል።

ደማስቆን መቆጣጠራቸውን ያወጁት አማፅያኑ  አሁን ከተማዋ ከአሳድ ነፃ ነች ብለዋል።

የአገሪቱ ጦርም ይሄንኑ አረጋግጧል ።

ፕሬዝዳንት በሽር አላሳድ ከተማዋን ለቀው መሸሻቸውን አርቲ ዘግቧል ።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

07 Dec, 18:20


የተቋረጠው ኃይል ወደነበረበት እየተመለሰ ነው

ዛሬ ማምሻውን በሲስተም አለመረጋጋት ምክንያት ተቋርጦ የነበረው ኃይል ወደነበረበት እየተመለሰ መሆኑን የብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል አስታወቀ።

ማዕከሉ እንዳስታወቀው የሲስተሙን ቮልቴጅ በማረጋጋት የተቋረጠውን ኃይል ደረጃ በደረጃ ለመመለስ የሚያስችል ሥራ እየተከናወነ ነው።

በአዲስ አበባ በአንዳንድ አካባቢዎች እንዲሁም በክልል ከተሞች የተቋረጠው ኃይል ወደነበረበት መመለሰ መጀመሩን ገልጿል።

ስለሆነም የተፈጠረው ችግር ሙሉ በሙሉ እስኪፈታ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁን በአክብሮት እንጠይቃለን ብሏል ተቋሙ ።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

07 Dec, 18:19


ደብረጺዮን ገ/ሚካኤል የሚመሩት የሕወሓት ክንፍ ውክልናቸውን አንስቼባቸዋለኹ ባላችው የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዝዳንትት ጌታቸው ረዳ ምትክ፣ ምክትል ፕሬዝዳንቱ ጄኔራል ታደሠ ወረደ እንዲተኩ ሰሞኑን ከጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ ጋር በተደረገ ስብሰባ ጠይቆ እንደነበር መስማቱን ቢቢሲ አማርኛ ዘግቧል።

ዐቢይ ግን የደብረጺዮን ቡድን ያቀረበውን ጥያቄ እንዳልተቀበሉት ምንጮች መናገራቸውን ዘገባው አመልክቷል። ዐቢይ በዚኹ ስብሰባ ላይ፣ ጊዜያዊ አስተዳደሩ ሥራውን እንዳይሠራ የደብረጺዮን ቡድን እንቅፋት ኾኗል በማለት ወቅሰዋል ተብሏል።

የደብረጽዮን ቡድን ግን፣ ጌታቸው ከጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዝዳንትነታቸው መነሳት አለባቸው በሚለው አቋሙ አኹንም እንደጸና መኾኑን ምንጮቹ መግለጣቸውን ዘገባው ጠቅሷል።

በጌታቸው ምትክ ማን መሾም እንዳለበት ከፌደራል መንግሥቱ ጋር እየተነጋገረ መኾኑን የደብረጺዮን ቡድን ለወራት በተደጋጋሚ ሲናገር እንደነበር አይዘነጋም።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

07 Dec, 16:11


በመላው ሀገሪቱ ኃይል መቋረጡ ተገለፀ

በኢትዮጵያ በሚገኙ በሁሉም አከባቢዎች ኃይል መቋረጡን ሁሌ አዲስ ሚዲያ የደረሰው መረጃ ያመለክታል ።

ይህን ተከትሎ ጉዳዩ የሚመለከተው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በመላዉ ሀገሪቱ ኃይል መቋረጡን በመግለፅ በድጋሚ ለመመለስ ጥረት እያደረገ እንደሚገኝ ጠቁሟል።

ተቋሙ እንዳለው  በሲስተም አለመረጋጋት በተፈጠረ ችግር  የተነሳ በመላው ሀገሪቱ የኃይል መቋረጥ አጋጥሟል ብሏል።

ችግሩን በመፍታት የተቋረጠውን ኃይል ወደነበረበት ለመመለስ በኃይል ማመንጫዎች እና በማከፋፈያ ጣቢያዎች ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን አስታውቋል ።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

06 Dec, 20:51


"አንድም ጫኝ እና አውራጅ የሚባል ነገር እንዳይኖር። ነግሬያችኃለሁ !! " - ኮሚሽነር ዓለሙ

የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ዓለሙ መግራ ድሬ ውስጥ ሰዎች ቤት ሲቀይሩ " ጫኝ አውራጅ ነን እያሉ የሚከተሉ ጎረምሶች እንዳይኖሩ " ሲሉ ትዕዛዝ አስተላለፉ።

ይህን እጅግ ጠንካራ ትዕዛዝ የሰጡት ከከተማውን የፀጥታ አመራሮች ጋር በመከሩበት ወቅት ነው።

በህዝብ ላይ እንግልትና ዘረፋ በሚፈፅሙ ጫኝና አውራጆች ላይ የተጠናከረ እርምጃ ይወሰዳል ተብሏል።

ኮሚሽነር ምን አሉ ?

" ሰፈር ላይ ቁጭ ብሎ ሰው ቤት ሲቀይር ጫኝ አውራጅ ብሎ የሚከተል ጎረምሳ እንዳይኖር።

በየቀጠናችን ያለው የጫኝ አውራጅ ስቃይ ህዝቡን ብታዩ አንድም ጫኝ እና አውራጅ የሚባል አደረጃጀት የለም።

ይሄን ያደራጀ ሰው ካለ ኃላፊነቱን አናውቀውም።

አንድም ጫኝ እና አውራጅ በየትኛውም ቀጠና የውሃ ፋብሪካ ምናም ካልሆነ በስተቀር ሰፈር ላይ ቁጭ ብሎ ሰው ቤት ሲቀይር ጫኝ አውራጅ ብሎ የሚከተል ጎረምሳ እንዳይኖር።

ይሄ ከተገኘ እወቁ ! አንድም ቦታ ሰውዬው ሲፈልግ ተሸክሞ ያውርድ ሲፈልግ ይስበረው።

በቀደም አንዱ መጥቶ ነገረኝ ትንሽ እቃ ነው በዳማስ ሄዶ ቀስ ቀስ እያለ አወረደ ... ከዛ ሮጠው መጡና አንኳኩ ' ክፈቱ ' አሉ ግር ብለው ገቡ ፤ እቃው ወርዷል ከዛ ' ስጡን  (ብር) ' አሉ ለምን ? ' የደንቡን ' የምን ደንብ ? እኛ አውርደናል እቃችንን አላቸው ' ሊሰጠን ይገባል አታውቅም እንዴ ይሄ የሰፈሩ ደንብ ነው ' አሉ።  ሰውዬው ወደ ፖሊስ ሲደውል ከግቢ ወጥተው በር ላይ ቁጭ አሉ። ትንሽ ሲቆይ አንድም ሁለትም እየሆኑ ሄዱ።

እኚህ ወጣቶች ሌላ ቀን ወንጀል ከመስራት ወደኃላ አይሉም። ለዚህ ነው ሰግቶ የነገረኝ።

ሰው በፍርሃት ነው ያለው።

አይቻልም አንድም ጫኝ እና አውራጅ የሚባል !! ነግሬያችኃለሁ።

ቤት ሲቀየር ገና ሰው እዛ ጋር መጥቶ የሚያወርደውን ነገር ታሳቢ ተደርጎ ነው ሰው የሚደራጀው ስራ ?

አይቻልም !

ብሎኬት ማውረድ ከፈለገ ሰውየው ቤት ሲሰራ እዛው ጋር የሚሰሩትን ሰዎች ማስወረድ ይችላል ፤ ሌላ ሰው ጠርቶ ዋጋ ተደራድሮ እሱ ባለው ዋጋ ማስወረድ ይችላል አለቀ።

' እኔ ማህበር ነኝ ፤ እኔ እንደዚህ ነኝ ' ማን እንዳደራጃቸው የማይታወቁ።

አንድም እንዳይኖር ይሄን ሰፈራችሁ ላይ አወያዩ ፤ ማህበረሰቡ ይሄን ይወቅ ለናተ መረጃ ይስጣችሁ። ሰፈር መድረስ ማለት ይሄ ነው።

ጫኝ እና አውራጅ ጣጣው በጣም ብዙ ነው " ብለዋል።

ይሄ የጫኝ እና አውራጅ ስቃይ የድሬዳዋ ብቻ አይደለም። በአዲስ አበባ በየሰፈሩና በክልል ከተሞች ተመሳሳይ ነው።

ገና ሰው እቃ ይዞ ሲመጣ " እኛ ካላወረድን ማንም ማውረድ አይችልም " በሚል አምባጓሮ የሚፈጡ አሉ።

አውርዱ ሲባሉ ደረታቸውን ነፍተው የሚጠሩት ብር ደግሞ አስደንጋጭ ነው።  ሰው በስንት ድካም ገንዘቡን እንደሚያገኝም አይረዱም።

ሰው ከፍራቻ የተነሳ በስንት መከራና ጭቅጭቅ ከፍተኛ ዋጋ ከፍሎ እቃውን ያስወርዳል። " ነገ የት እኖራለሁ " ብሎ በመፍራት።

እራሱና ቤተሰቦቹ፣ ጓደኞቹ በጋራ የገዛ እቃቸውን እንዳያወርዱ ዛቻ ሁሉ ሊፈጸምባቸው ይችላል።

ይህንን ስርዓት አልበኝነትና ድንፋታ እንዲያስቆሙ የሚጠሩ አንዳንድ የፀጥታ አባላት ነገሩን ለማስተካከል እርምጃ ከመውሰድ ይልቅ የሚሉት ' ከነሱ ጋር ተስማሙ ' ነው።

ሰው ከፍራቻ የተነሳ ለሊት እቃውን ይዞ ይገባል። በገዛ ሀገሩ በገዛ ከተማው በገዛ እቃው ተሳቆ ነው የሚኖረው። ስቃዩ ብዙ ነው ! Tikvha

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

06 Dec, 20:49


የኢትዮጵያ የባንክ ዘርፍ ከጥቂት ሳምንታት በኋላ ለውጭ ውድድር ሊከፈት መሆኑ ተሰማ

ኢትዮጵያ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ የባንክ ዘርፉን ለውጭ ውድድር ለመክፈት በዝግጅት ላይ ትገኛለች። ይህን ተከትሎ በአሁኑ ወቅት አዲስ ህግ በፓርላማ እየተገመገመ እና በሚቀጥለው ወር ይፀድቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተገልጿል።

ይህ ወሳኝ ውሳኔ በሀገሪቱ ኢኮኖሚያዊ ገጽታ ላይ ከፍተኛ ለውጥን የሚያመለክት ሲሆን ይህም ውድድርን ለማሳደግ፣ የአገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻል እና የውጭ ኢንቨስትመንትን ለመሳብ ያለመ ነዉ ተብሏል ።

ርምጃው በኢትዮጵያ መንግስት እና በብሄራዊ ባንክ የተጀመሩት የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያዎች አካል ሲሆን እነዚህ ማሻሻያዎች የተነደፉት የፋይናንስ ሴክተሩን ለማዘመን እና ለሀገር ውስጥ እና ለአለም አቀፍ ንግዶች የበለጠ ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር ጭምር ነዉ።

የውጭ ባንኮችን ወደ ኢትዮጵያ የፋይናንስ ምኅዳር ማስገባቱ ፉክክር እንደሚያመጣ የሚጠበቅ ሲሆን ይህም ለተጠቃሚዎች የተሻሻሉ አገልግሎቶችን እና ምርቶችን ሊያመጣ ይችላል ተብሎ ይጠበቃል።
Capital

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

06 Dec, 15:44


በአስቸኳይ ስብሰባው ላይ አርቲስት ማስተዋል ወንዶሰን አልተገኘችም

ከሰአታት በፊት በተደረገው የአዲስአበባ እግርኳስ ፌደሬሽን አስቸኳይ ስብሰባ በጥሩ ሁኔታ መጠናቀቁ የደረሰኝ መረጃ ያመለክታል።

በዚህ አስቸኳይ ስብሰባላይ በምክትል ፕሬዝዴንትነት የተሾመችው አርቲስት ማስተዋል ወንዶሰን እንዲሁም አቃቢተ ነዋይ ተብላ የተመረጠችው ሀረገወይን አሰፋ እንዳልተገኙ ታውቋል።

ዛሬ በተደረገው ስብሰባ አሁን ላይ ስለሚራገበው አጀንዳ በመተው በቀጣይ ስለሚሰሩ ስራዎች አቅጣጫ ተሰጥቶበት ተጠናቋል።

ይህ ማለት ቀጣዮቹን አራት አመታት በተመረጠው ስራ አስፈፃሚ የአዲስአበባ እግርኳስ ፌደሬሽን የሚቀጥል ይሆናል።

ምንጭ:- የስፖርት ጋዜጠኛ ይገደብ አባይ

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

06 Dec, 14:52


የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በነበረበት ይቀጥላል ተብሏል።

የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ፤ የታህሳስ ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በህዳር ወር በነበረበት የመሽጫ ዋጋ እንዲቀጥል በመንግሥት መወሰኑን አሳውቋል።

ሚኒስቴሩ " የነዳጅ ማደያዎች እና ኩባንያዎች ያልተገባ የነዳጅ ክምችት ከመያዝ እና የዋጋ ጭማሪ ከማድረግ ተቆጥበው ውሳኔውን ተግባራዊ በማድረግ ህብረተሰቡን በቅንነትና በታማኝነት እንዲያገለግሉ "  ሲል አሳስቧል።

የነዳጅ ምርቶች ዋጋ ስንት ነው ?

➡️ ቤንዚን - ብር 91.14 በሊትር
➡️ ነጭ ናፍጣ - ብር 90.28 በሊትር
➡️ ኬሮሲን - ብር 90.28 በሊትር
➡️ ቀላል ጥቁር ናፍጣ - ብር 100.20 በሊትር
➡️ ከባድ ጥቁር ናፍጣ - ብር 97.67 በሊትር 
➡️ የአውሮፕላን ነዳጅ - ብር 77.76 በሊትር ሆኗል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

06 Dec, 13:03


አማዞን ኖቫ የሚል መጠሪያ የሰጠው የባለብዙ አገልግሎት የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ሞዴል ይፋ አደረገ፡፡

ሞዴሉ ጽሑፍ ማመንጨት፣ ምስሎችን እና ተንቀሳቃሽ ምስልን (ቪዲዮ) መፍጠር የሚችሉ ማይክሮ፣ላይት፣ፕሮ እና ፕሪሜር የተባሉ ጥምር ሞዴሎች ውጤት ነው፡፡

በተጨማሪም ምስል እና ቪዲዮን ለመፍጠር ጥቅም ላይ የሚውሉ ኖቫ ካንቫ እና ኖቫ ሪል የተባሉ ሞዴሎች ለአገልግሎት እንደሚበቁ የአማዞን ዋና ስራ አስፈፃሚ አንዲ ጃሲ መናገራቸውን ባሮን ድረገፅ ዘግቧል፡፡

ኖቫ ለጊዜው በ15 የተመረጡ ቋንቋዎች አገልግሎት እንደሚሰጥ ተመላክቷል፡፡ ከአገልግሎቶቹም መካከል ጥያቄዎችን መመለስ፣ ፎቶን ወደ ተንቀሳቃሽ ምስል መቀየር፣ ቪዲዮዎችን ማመንጨት እና መተንተን፣ ሀሳቦችን ማሳጠር እና መግለጫዎቸን ማጠቃለል ይገኝበታል፡፡

አማዞን ዌብ ሰርቪስ ቀደም ብሎ ከሚታወቅበት የክላውድ ወይም የዳታ ማከማቻ አገልግሎቶቹ በተጨማሪ በጄኔሬቲቭ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ቴክኖሎጂ በኩል እየተካሄደ ያለውን ፉክክር በመቀላቀል ተወዳዳሪነቱን ለማስጠበቅ እየሰራ ስለመሆኑ ተዘግቧል፡፡

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

06 Dec, 07:41


#NewsinBrief

https://www.youtube.com/watch?v=skFsKYVnKNc

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

18 Nov, 16:20


ትምህርት ሚኒስትር " የመምህራን ባንክ"  ለማቋቋም ሀሳብ እንዳለዉ አስታወቀ

ወደ መምህርነት ሙያ የሚገቡ ሰዎች ቁጥር ዝቅተኛ መሆኑን የገለፀው ትምህርት ሚኒስትር
መምህራን "በአገሪቱ የፋይናንስ ሥርዓት ውስጥ የራሳቸው ድርሻ እንዲኖራቸው የሚያስችል የመምህራን ባንክ" የማቋቋም ሀሳብ እንዳለዉ ፍንጭ ሰጥቷል።

ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ ( ፕ/ር) እንደተናገሩት ወደ መምህርነት ሙያ የሚገቡ ሰዎች ቁጥር ዝቅተኛ በመሆኑ ይህንን ለማስተካከል " ዘርፈ ብዙ የማትጊያ ስርዓቶች ይዘረጋሉ" ብለዋል።

እንደ ሚኒስትሩ ገለፃ የትምህርት ጥራት ችግርን ለመቅረፍ በመንግሥትና በግል ትምህርት ቤቶች መካከል ያለውን ልዩነት ማጥበብ እንደሚገባም አስረድተዋል ።

ይህ የተባለዉ የትምህርት ሚኒስቴርን የበጀት ዓመቱ የ3 ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ዙሪያ በሚመለከት ከሚመለከተዉ አካል ጋር ዉይይት ባደረገበት ወቀት ነዉ።

ካፒታል ጋዜጣ

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

18 Nov, 16:19


የኢትዮጵያ አየር መንገድ 2025 የዓለም አራት ኮከብ አየር መንገድ ደረጃ እውቅና እና ሽልማት አገኘ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በዓመታዊው አፔክስ የመንገደኞች ምርጫ 2025 የዓለም አራት ኮከብ አየር መንገድ ደረጃ ዕውቅና እና ሽልማት ማግኘቱን አስታውቋል፡፡

የዓለም አራት ኮከብ አየር መንገድ ሽልማት ከአንድ ሚሊየን በላይ ከተረጋገጡ ጉዞዎች ከበረራ በኋላ ከመንገደኞች በተሰጡ ድምፆች መሰረት የተበረከተና በአቪዬሽኑ ዘርፍ ትልቅ ስፍራ የሚሰጠው ዓለም አቀፍ ዕውቅና መሆኑ ተገልጿል፡፡

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

18 Nov, 15:37


በአዲስ አበባ መርካቶ ገበያ ተደጋጋሚ የእሳት አደጋ ያጋጠመው አካባቢ፤ “በመልሶ ማልማት እንዲለማ” ምክረ ሃሳብ ቀረበ

ከአንድ ወር ባነሰ ጊዜ ውስጥ በትላንትናው ዕለት ለሁለተኛ ጊዜ የእሳት አደጋ ያጋጠመው በአዲስ አበባ ከተማ መርካቶ ገበያ የሚገኝ አካባቢ፤ “በመልሶ ማልማት እንዲለማ” ምክረ ሃሳብ ቀረበ። ምክረ ሃሳቡን ያቀረበው የአዲስ አበባ ከተማ የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ነው።

ትላንት እሁድ ህዳር 8፤ 2017 እኩለ ቀን ገደማ የእሳት አደጋ የደረሰበት የመርካቶ ገበያ ስፍራ፤ በተለምዶ “ድንች ተራ” የሚል ስያሜ ያለው ነው። ስፍራው ከሁለት ሳምንት በፊት በተመሳሳይ አደጋ ከፍተኛ ጉዳት ደርሶበት ከነበረው “ነባር የገበያ ማዕከል” በቅርብ ርቀት ላይ የሚገኝ ነው።

የእሁዱ ቃጠሎ የደረሰበት ስፍራ፤ “በነባር የገበያ ማዕከል” ላይ የሚነግዱ ነጋዴዎች ንብረቶቻቸውን የሚያስቀምጡበት መጋዘን እንደነበር የአካባቢው ነዋሪዎች ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። የእሳት አደጋው “ጌሾ ግቢ” ተብሎ በሚጠራው ስፍራ ከሚገኘው መጋዘን በተጨማሪ በአቅራቢያው የሚገኙ መደብሮች እና መኖሪያ ቤቶች ላይ ውድመት አድርሷል።

በአንድ ሰዓት ተኩል ውስጥ በቁጥጥር ስር የዋለውን የትላንትናውን የእሳት አደጋ ለመከላከል፤ ሰባት የውሃ ቦቴዎች እና 18 የአደጋ መቆጣጠር ተሽከርካሪዎች ተሰማርተው እንደነበር የአዲስ አበባ ከተማ የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ንጋቱ ማሞ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ገልጸዋል።

ከእነዚህ ተሽከርካሪዎች በተጨማሪ የኮሚሽኑ እና የቀይ መስቀል ማህበር አምቡላንሶች፤ በአደጋው ጉዳት የደረሰባቸውን ግለሰቦች ወደ ህክምና ተቋማት በመውሰድ ተሳትፈዋል። በትላንቱ የእሳት አደጋ ሶስት የአካባቢው ነዋሪዎች እና ሁለት የኮሚሽኑ ሰራተኞች ላይ ቀላል ጉዳት መድረሱን አቶ ንጋቱ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል።

Ethiopia insider

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

18 Nov, 14:50


በካፒታል ገበያ ከመቶ ዓመት በላይ ልምድ ያለው የአሜሪካው የሴክዩሪቲስ ኤክስቼንጅ ኮሚሽን ባለሞያዎች አዲስ አበባ መሆናቸውን ሰምተናል።

ኮሚሽኑ በኢትዮጵያ መንገዱን የያዘው የካፒታል ገበያ እንዴት መጓዝ አለበት? ፈተናዎቹ ምን ሊሆኑ ይችላሉ? በሚለው ጉዳይ እየመከረ ነው።

የውጪ ሀገር ልማዶች ምንድናቸው በሚለው ዙሪያም ሀሳብ ተዋጥቷል።

የአሜሪካ ሴክዩሪቲስ ኤክቼንጅ ኮሚሽን በካፒታል ገበያው ያጋጠመውን መልካም እድል ለኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ለማቀበል መምከራቸውንም ሰምተናል።

ከገበያው የቁጥጥር ማእቀፍ ማእዘንም አደናቃፊውን ቀድሞ ለመለየትም ጉባኤው እንደተዘጋጀ ተነግሯል።

በካፒታል ገበያ ኦዲተሮች፣ የኢንቨስትመንት አማካሪዎች፣ የስቶክ ብሮከሮች(ደላሎች) እና ሌሎችም እንዴት በገበያው መሳተፍ አለባቸው በሚለው ጉዳይም ምክክር ቀርቧል።

በጉባኤው ባንኮች፣ የኢንሹራንስ ባለሞያዎች፣ የኢንቨስትመንት አማካሪዎችና ሌሎችንም ያሳተፈ ነው።
(ተህቦ ንጉሴ - ሸገር)

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

18 Nov, 13:11


የነዳጅ ማስተካከያ ባለመደረጉ ምክንያት በ 2 ወራት ዉስጥ ብቻ ከ 30 ቢሊዮን ብር በላይ እዳ ሊመጣ እንደቻለ ተገለፀ

የነዳጅ ግብይትን  እና የነዳጅ ማደያዎችን ተደራሽነት ህጋዊነት ለማረጋገጥ የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር እንዲሁም የነዳጅ እና ኢነርጅ ባለስልጣን ርብርብ ማድረግ እንደሚገባቸው ተነግሯል።

የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) እንደተናገሩት " የጎረቤት ሀገራትን በነዳጅ ለመቀለብ የተዘጋጁ ማደያዎች መኖራቸውን በመጥቀስ በሁለት ወራት ብቻ የነዳጅ ማስተካከያ ባለመደረጉ 35 ቢሊዮን ብር እዳ ሊመጣ እንደቻለ" አስረድተዋል።

ይህ የተገለፀዉ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የንግድ እና ቱሪዝም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የነዳጅ ውጤቶችን የግብይት ሥርዓት ለመደንገግ የወጣ ረቂቅ አዋጅን በተመለከተ ከአስረጂዎች ጋር በተወያየበት ወቅት ነዉ።

ሚኒስትሩ እንዳሉት አሁናዊ የነዳጅ አቅርቦት ፣ ስርጭት እና አጠቃቀም ላይ ብክነት ስላለ ይህ ችግር ለመፍታት ረቂቁ የማይተካ ሚና እንዳለው በአፅንኦት ተናግረዋል ።

የዋጋ ማስተካከያ ይደረጋል በሚል እሳቤ ነዳጅ እያለ ነዳጅ የለም ብለው የሚዘጉ ማደያዎች መኖራቸውን የጠቀሰው ሚኒስትሩ ረቂቁ በአስመጭዎች፣ አከፋፋይ እና ማደያዎች ላይ ህጋዊ  ስርዓት ለመዘርጋት አስፈላጊ መሆኑን አብራርተዋል፡፡ Capital

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

18 Nov, 11:41


ከኤርትራ ጋር ሰላም መፍጠር እንፈልጋለን፣ ዳግም ስለ ጦርነት ማውራት የለብንም” - አቶ ጌታቸው ረዳ

#የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ከኤርትራ ጋር ሰላም መፍጠር እንደሚፈልጉ እና ዳግም ከኤርትራ ጋር ጦርነት ስለመግጠም ማውራት እንደማያስፈልግ አስታወቁ።

ከኤርትራ ጋር ሰላም መፍጠር እንደሚፈልጉ ያስታወቁት አቶ ጌታቸው ከድርድሩ በፊት ግን ኤርትራ ለተፈጸሙ ጥፋቶች ሃላፊነት መውሰድ እንደሚገባ አመላክተዋል፤ “በሰላማዊ ሰዎች እና በሴቶች ላይ ጥቃት የፈጸሙት መያዝ አለባቸው” ሲሉ ጠቁመዋል።

ስለፕሪቶርያው ስምምነት በጋዜጣው የተጠየቁት አቶ ጌታቸው “በርካታ ጦርነቱ እንዲቀጥል ለማድረግ ግፊት የሚፈጥሩ ሁኔታዎች ቢኖሩም በበርካታ የትግራይ ግዛቶች ላይ ጦርነት እንዳይኖር አድርጓል፣ የጥይት ድምጽ አስቁሟል” ሲሉ በመግለጽ ጠቃሚ ውጤት አስገኝቷል ብለዋል።

የምዕራብ ትግራይ ጉዳይ ሰላማዊ መፍትሄ ይኖረው ይሆን? ተብለው የተጠየቁት ጌታቸው ረዳ “ምንም ሌላ አማራጭ የለም” ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል፤ ዋና ግቡ ሰላሙ በሁሉም ዘንድ የሚከበር እና ዘላቂነት ያለው ሊሆን ይገባል ሲሉም አስታውቀዋል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

18 Nov, 09:00


በአፋር እና ሲዳማ ክልሎች ያሉ የመንግስት ሰራተኞች ለገዢው ፓርቲ በግድ ከደሞዝ አዋጡ ተባልን ብለው ተናገሩ

በአፋር ክልል አዋሽ አካባቢ ያሉ የመንግስት ሰራተኞች ለመሠረት ሚድያ እንደተናገሩት በጥቅምት ወር ለብልፅግና መዋጮ በሚል ከመምህራን ላይ የ20 ፐርሰንት የደሞዝ መዋጮ በግዴታ እንደተቆረጠ ተናግረዋል።

ከሌሎች የመንግስት ቢሮ ሰራተኞች ላይ ደሞ 50 ፐርሰንት ተቆረጠ ሲሆን መዋጮው በህዳር ወርም ይቀጥላል ተብሏል።

"ተስፋ ቆርጠናል፣ አዲሱን የደሞዝ ጭማሪ ስንጠብቅ ጭራሽ ደሞዛችንን መቁረጥ ተጀምሯል" ያሉት ሰራተኞች የመምህራን የደረጃ እድገት እርከን እንኳን በክልሉ ከቆመ 2 አመት እንደሞላው ጨምረው ገልፀዋል።

በሌላ በኩል በሲዳማ ክልል ደራራ ወረዳ ለብልፅግና ፓርቲ የህንፃ ግንባታ ተብሎ የፓርቲ አባል ያልሆኑትን ጭምር የአንድ ወር ደሞዝ እንዲቆረጥ መወሰኑ መሠረት ሚድያ ዘግቧል።

"ደሞዛችን እንዲቆረጥ አንፈርምም" ያሉ መምህራን ደሞዛቸው ጭራሽ እንዳልተከፈላቸው ገልፀው ችግር ላይ እንዳሉ ጠቁመዋል።

በ2017 ዓ.ም የወረዳው የብልፅና ፅ/ቤት በወረዳው ውስጥ የሚገኙ የመንግስት ሰራተኞችን በማስተባበር የወረዳውን የብልፅግና ፓርቲ ፅህፈት ቤት ህንፃ ለመስራት ገንዘብ እየሰበሰበ እንደሚገኝ በተደረገው ዳሰሳ ተረጋግጧል።

"እስካሁን የአብዛኛው የወረዳው መምህራን ደሞዝ በግዳጅ እንዲፈርሙ ተደርጎ ደሞዛቸው ተቆርጦ ተከፍሏል። እኛ አንፈርምም ያልን ሁለት መቶ የምንጠጋ መምህራን ግን በግድ ካልፈረማችሁ ተብለን እስከ ዛሬ ድረስ ደሞዛችን ተይዟል" ያሉ ሲሆን የታሰሩም ሰዎች እንዳሉ ጠቁመዋል።

ጉዳዩን ከወረዳ እስከ ክልል መምህራን ማህበር ብናመለክትም እስከዛሬ ድረስ ሊከፈለን አልቻለም በማለት ተናግረዋል።

Mesert media

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

18 Nov, 08:54


በመርካቶ የሱቅ መዝጋት አድማ ተጀምሯል ። ለ6 ቀን ይቆያል እየተባለ ሲሆን መንግስት ህገወጦችን እንዲያስታግዝ ተጠይቋል

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

18 Nov, 08:50


ሳዑዲ አረቢያ 7 ኢትዮጵያውያንን በሞት መቅጣቷ ተገለጸ!

ሳዑዲ አረቢያ በፈረንጆቹ 2024 ዓ/ም 7 ኢትዮጵያውያን ጨምሮ ከ100 በላይ የውጪ ዜጎች በሞት ቀጣች መቅጣቷን የአገሪቱን ዜና ወኪሎች ጠቅሶ አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ ዘግቧል።ከሰባቱ ኢትዮጵያውያን በተጨማሪ የሞት ቀጣት ተፈጻሚ ከተደረገባቸው የውጭ ዜጎት መካከል 1 ኤርትራዊ፣ 3 ሱዳናውያን፣ 10 ናይጄሪያውያን፣ 9 ግብጻውያን፣ 21 ፓኪስታናውያን፣ 20 የመኒ፣ 14 ሶርያውያን ይገኙበታል።

በዘገባው መሰረት በውጪ ዜጎች ላይ ተግባራዊ የሚሆነው የሞት ቅጣት ከአደንዛዥ ዕጽ ጋር በተያያዙ ወንጀሎች ምክንያት ነው።በሳዑዲ አረቢያ በፈረንጆቹ በ2023 ዓ/ም 34 የውጪ ሀገራት ዜጎች በሞት መቅጣቷም ተገልጿል፣የአውሮፓ-ሳዑዲ የሰብአዊ መብቶች ድርጅት በበኩሉ ከ101 የውጭ ዜጎት ላይ የተፈጸመው የዘንድሮው የሞት ፍርድ ክብረ ወሰን የሰበረ ነው መሆኑን ገልጿል።

[Addis Standard]

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

18 Nov, 08:49


ባይደን በሩሲያ ላይ ጥቃት እንዲፈጸም ፈቃድ ሲሰጡ እጃችንን አጣጥፈን አንቀመጥም - ቭላድሚር ፑቲን

የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን ዩክሬን ከአሜሪካ የተሰጣትን ረጅም ርቀት ተወንጫፊ ሚሳኤሎችን ሩሲያን ለመምታት እንድትጠቀምበት ፍቃድ ሰጥተዋል።

በዚህ ጉዳይ ላይ ምላሽ የሰጡት የሩሲያ ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ሞስኮ ተገቢ ምላሽ እንደምትሰጥ አስጠንቅቀዋል።

የሩሲያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ማሪያ ዛካሮቫ፤ ፕሬዚዳንት ፑቲን ከወራት በፊት የውጭ ሃይሎች ለዩክሬን ያቀረቧቸው የረዥም ርቀት ሚሳኤሎች ጥቅም ላይ እንዲውሉ ፈቃድ ሊሰጡ እንደሚችሉ እምነታቸውን ገልጸው እንደነበር አስታውሰዋል።

ኒውዮርክ ታይምስ በስም ያልጠቀሳቸውን የአሜሪካ ባለስልጣንን ምንጭ አድርጎ በሰራው ዘገባ፤ ፕሬዚዳንት ባይደን ዩክሬን በሚሳኤሎቹ የሩሲያን ግዛት እንድትመታ ፈቃድ መስጠታቸውን የሚገልጽ መረጃ መውጣቱን ተከትሎ ፕሬዚዳንት ፑቲን በጉዳዩ ላይ አስተያየት መስጠታቸውን ገልጸዋል።

ለዩክሬን ፈቃድ መስጠት ብቻ ሳይሆን ጥቃቱን ለመፈጸም የውጭ ሃይሎች ድጋፍ ካልታከለበት በስተቀር ዩክሬን በሩሲያ ላይ ጥቃት መሰንዘር እንደማትችል ተናግረዋል።

ቃል አቀባይዋ ፕሬዚዳንቱ ሰጡት ባሉት ምላሽ፥ ትልቁ ጥያቄ ዩክሬን በተሰጣት መሳሪያዎች ሩሲያን እንድትመታ መፈቃዱ ሳይሆን የኔቶ ሀገራት በዚህ ጦርነት ውስጥ በቀጥታ እንዲሳተፉ ወይም እንዳይሳተፉ መወሰን መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ፑቲን አክለውም ውሳኔው ከተሰጠ ሞስኮ ተገቢ ምላሿን ትሰጣለች ሲሉም ገልጸዋል፡፡

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

17 Nov, 06:13


""ሥልጣን በቃኝ፤ በድጋሚ አልወዳደርም!"

🏃‍♂ረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉ ለህዝቡ የገባችውን ቃል እጠብቃለሁ አለች

"🏃‍♂"የስልጣን ዘመኔን ስለጨረስኩ በድጋሚ ለፕሬዝዳንትነት አልወዳደርም ስልጣኔንም እለቃለሁ አለች

"🏃‍♂"እኔም በቃኝ፤አዲስ ሠው ወደ ኃላፊነት ይምጣ"አትሌት ገዛኸኝ አበራ

በእርግጥ ዛሬ በነበረው የባለድርሻ አካላት ስብሠባ አመራሮቹ ላይ የትችት ዝናብ ቢወርድም ጀግናዋ አትሌት ደራርቱ ቱሉ በስልጣን ዘመንዋ ስሟን ከፍ አድርጎ የሚያስጠራ ስራ መስራቷን መደበቅና መካድ አይቻልም፤

ምንአልባት ከኦሎምፒክ ጋር በተያያዘ በተፈጠሩ ችግሮችና በያዘችው አቋም እነዚህ መልካም ነገሮቿ ቢሸፈኑም በእሷ የስልጣን ዘመን በአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና፣በአለም የወጣቶች ሻምፒዮና፣በሀገር አቋራጭ፣በመላ አፍሪካ ጨዋታዎች እጅግ አስደማሚ የሀገርን ስምና ባንዲራ ከፍ ያደረጉ አንፀባራቂ ውጤቶች መመዝገባቸው የፕሬዝዳንቷን የአመራር ብቃት ጠቋሚ ናቸው።

አሁን ግን ነገሮች የመጨረሻው ሠዓት ላይ የደረሱ ደራርቱም የቀድሞ የአትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት በሚል ለመጠራት የተቃረበች ይመስላል፤ላለፉት ስድስት አመታት በአትሌቲክስ ፌዴሬሽን የፕሬዝዳንትነት ወንበር ላይ የተቀመጠችው ረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉ "ተርሜን ጨርሻለሁ፤ስልጣን በቃኝ"በማለት ቀደም ሲል ለህዝቡ የገባችውን ቃል እንደምታከብር በዛሬው ስብሰባ ማሳወቋ ከብዙዎች አርአያነት ያለው በጎ ተግባር በሚል ውዳሴ እየቀረበላት ነው።

ለወንበራቸው ሲሉ ሀገርንም፣ስፖርቱንም ዋጋ የሚያስከፍሉ ሠዎች ባየንበት የስፖርቱ መንደር ረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉ"ተርሜን ጨርሻለሁ፤ከዚህ በኃላ በአመራርነት ወደ ፌዴሬሽኑ አልመጣም፤አንድም ሁለት ወር እንዲሁም ሁለት ዓመት የሠራ ሙሉ ተርሙን እንደሠራ ነው የሚቆጠረው"በማለት በዛሬው የባለድርሻ አካላት ስብሰባ ላይ የተናገረችው ረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉ"ተርሜን ጨርሻለሁ፤በቃኝ"ካለች በኋላ "በቀጣይ ለሚኖረው የስራ አስፈፃሚና የፕሬዝዳንት ምርጫ የምትልኳቸው ሶስት ሶስት ሠዎች ላይ ከፍተኛ ጥንቃቄ አድርጉ፤ስፖርቱንና ሀገሩን የሚጠቅም ትክክለኛ ሠው መርጣችሁ ላኩ"በማለትም የጉባኤው አባላትን መክራለች።

አትሌት ደራርቱ ቱሉ "ስልጣኔን እለቃለሁ"ከማለቷ በፊት ብዙ ያልተረጋገጡ ወሬዎች ሲናፈሱ የነበረ ሲሆን ከኦሮሚያ ውክልና የተነፈገችው ደራርቱ ቱሉ ከአዲስ አበባ ውክልና አግኝታ ለፕሬዝዳንትነት እንደምትወዳደርም በስፋት ሲናፈስ የነበረው መረጃ መሠረተ ቢስ መሆኑን ደራርቱ በውሳኔዋ አሳይታለች።

ከፌዴሬሽኑ ፕሬዝዳንት ደራርቱ ሌላ ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝዳንቱ አትሌት ገዛኸኝ አበራ በስራ አስፈፃሚው ላይ የቀረበውን ትችት አምኖ በመቀበል እሱም በተመሳሳይ"እኔም ስልጣን በቃኝ፤አዲስ ፊት ወደአመራርነት ይምጣ"ሲል መናገሩም ታውቋል።

በተያያዘ ዜና የዕለቱ ትኩሳት የነበረው የአትሌቶች ማህበር ሁለት የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ውክልናን የማስነሳት አጀንዳ በተፈጠረው ከፍተኛ ተቋውሞ በታሠበው መልኩ ለውይይት ያልቀረበ ሲህን ጉዳዩን አስመልክቶ ረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉ ማብራሪያ ሠጥታበታለች"እኔ ውክልናየው ይነሳ አላልኩም ከመቼው ወደሚዲያ ሄደ ትንታኔ እንደተሠጠበት ሳይ ገርሞኛል፤ እባካችሁ ባልተረጋገጠ ነገር ወደ ሚዲያ አትሩጡ" በማለት ወቀሳ ያቀረበችው ፕሬዝዳንቷ"እኔ ያልኩት የአትሌቶች ውክልና ይነሳ ሳይሆን የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ደንብ ላይ ያለ ድምፅ ይሳተፉ የሚለው በድምፅ እንዲሆን እንዲደረግ እንስራ ነው ያልኩት እንጂ እንዴት እኔን ወደስልጣን ያመጣኝ ማህበር ውክልና እንዲነጠቅ አደርጋለሁ"በማለት አስረድታለች።

ዛሬ ሙሉ ቀን በፍሬንድሺፕ በነበረው ስብሰባ የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት ላይ ውርጅብኝ የወረደ ሲሆን በተለይ አመራሩ የዓሣ ግማቱ ከአናቱ በሚል ለተፈጠረው ችግር ተጠያቂ ነው በሚል የሠላ ትችት የቀረበበት ሲሆን ፌዴሬሽኑም ያቀረበው የጥናት ሠነድ የነበረባቸውን ጉድለት ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ በመሆኑ ጥናቱን ያዘጋጁትም እንዲዘጋጅ የፈቀዱትም ምስጋና ቀርቦላቸዋል።

የደራርቱ "ሥልጣን በቃኝ፤ በድጋሚ አልወዳደርም"ካለች በኋላ ማን ቀጣዩ የፌዴሬሽኑ ፕሬዝዳንት ይሆናል? የሚለው የብዙዎችን ትኩረት የሳበ ሲሆን የቀድሞ አትሌቶች ስለሺ ስህንና አትሌት አሠፋ መዝጠቡን ወደኃላፊነት ለማምጣት ስራዎች መጀመራቸው ተሠምቷል።

Via በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ (ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል)

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

16 Nov, 13:42


ለ24ኛ ጊዜ የተዘጋጀው ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ የተወሰኑ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚሆኑ አዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ።

በርካታ የሀገር ውስጥና የውጪ ሀገራት ተሳታፊዎች ፣ አምባሳደሮች ፣ ተጋባዥ አትሌቶች የሚታደሙበት መነሻና መድረሻውን መስቀል አደባባይ ያደረገው ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ያዘጋጀው የሩጫ ውድድር ህዳር 8 ቀን 2017 ዓ/ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል፡፡ ውድድሩ ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ የተወሰኑ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚሆኑ አዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡

ለጋራ ደህንነት ሲባል ፍተሻ እንደሚኖር የውድድሩ ተሳታፊዎች ተገንዝበው አስፈላጊውን ትብብር ማድረግ እንዳለባቸው ፖሊስ ገልፆ የወድድሩ ተሳታፊዎች በሚያልፉት አካባቢ የሚኖሩ ነዋሪዎች እንደ ከዚህ ቀደሙ ከፀጥታ ኃይሉ ጎን በመቆም ትብብራቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ አዲስ አበባ ፖሊስ ጥሪውን እያስተላለፈ ውድድሩ የከተማችንን ዋና ዋና መንገዶች የሚያካልል በመሆኑ ሩጫው ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ የተወሰኑ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚሆኑ አዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቆ ውድድሩ በሰላም እንዲጠናቀቅ የፀጥታ አካላት አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት አጠናቀው ስራ መጀመራቸውን አዲስ አበባ ፖሊስ ገልጿል።

ከውድድሩ ዓላማ ውጪ ህገ-ወጥ ተግባራትንና መልእክቶችን ማስተላለፍ የውድድሩን መንፈስ የሚረብሽ ስለሆነ አዘጋጅ ተቋሙ እና ተሳታፊዎች ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግ እንደለባቸው እያሳሰበ ውድድሩ ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ፡-

-ከኦሎምፒያ አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ (ኦሎምፒያ አደባባይ )
- ከጥላሁን አደባባይ ወደ ሳንጆሴፍ መብራት (ጥላሁን አደባባይ ) ለከባድ ተሽከርካሪ አጎና ሲኒማ
- ከአፍሪካ ህብረት መብራት ወደ ሜክሲኮ አደባባይ (ጥይት ቤት መስቀለኛ )
-ከፓርላማ መብራት ወደ ኮንሰን መታጠፊያ (ፓርላማ መብራት )
- ከኮንሰን መታጠፊያ ወደ ገብርኤል (ኮንሰን መታጠፊያ )
ከጥይት ቤት ወደ ገብርኤል በጀርባው (ጥይት ቤት መታጠፊያ )
ከሴቶች አደባባይ ወደ ካዛንቺስ (ሴቶች አደባባይ )
- ከሴቶች አደባባይ ወደ ካዛንቺስ ቶታል (ሴቶች አደባባይ )
- ከ22 አደባባይ ወይም ዘሪሁን ህንፃ ወደ ዑራኤል አደባባይ (ዘሪሁን ህንፃ መስቀለኛ )
- ከፒኮክ አዲሱ መንገድ ወደ ዑራኤል አደባባይ (ፒኮክ መብራት)
- ከጋዜቦ አደባባይ ወደ ደንበል (ጋዜቦ አደባባይ)
- ከቂርቆስ ቤ/ክርስቲያን መስቀለኛ ወደ ለገሃር መብራት (ቂርቆስ ቤ/ክርሰቲያን ነርክ ተራ )
- ከላንድ ማርክ ሆስፒታል መታጠፊያ ገነት ሆቴል ወይም ወደ ገነት መብራት (ላንድ ማርክ ሆስፒታል መስቀለኛ )
- ከጠማማ ፎቅ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ (ጠማማ ፎቅ መስቀለኛ )
- ከአፍሪካ ህብረት መብራት ወደ ሜክሲኮ አደባባይ (ሜክሲኮ ጥይት ፋብሪካ መስቀለኛ )
- ከፈረሰኛ መብራት ወደ ጨፌ ሜዳ (ፈረሰኛ መብራት )
- ከሞላ ማሩ መስቀለኛ ወደ ጌጃ ሰፈር (ጌጃ ሰፈር መስቀለኛ )
- ከከፍተኛ ፍ/ቤት አደባባይ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ (ከፍተኛ ፍ/ቤት አደባባይ)
- ከሠንጋ ተራ 40/60 ወደ ሠንጋ ተራ መብራት (ሠንጋ ተራ 40/60 መታጠፊያ)
- ከጎማ ቁጠባ መብራት ወደ ብ/ቲያትር (ጎማ ቁጠባ መብራት)
- ከሜትሮሎጂ መታጠፊያ ወደ ፖስታ ቤት መብራት (ሜትሮዎሎጂ መታጠፊያ )
- ከጥቁር አንበሳ ሼል ወደ ኢምግሬሽን (ጥቁር አንበሳ ሼል)
- ከጎላ ሚካኤል መስቀለኛ ወደ ኢምግሬሽን (ጎላ ሚካኤል መስቀለኛ)
- ከቴዎድሮስ አደባባይ ወደ አገር አስተዳደር መብራት (ቴዎድሮስ አደባባይ)

ከንጋቱ 11:30 - ሰዓት ጀምሮ ውድድሩ እስከሚጠናቀቅ የተጠቀሱት መንገዶች የሚዘጉ ሲሆን በተጨማሪም በተገለፁት መስመሮች ላይ ቅዳሜ ከምሽቱ 12:00 ሰዓት ጀምሮ መኪና ለአጭርም ይሁን ለረጅም ጊዜ ማቆም የተከለከለ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ እያስታወቀ የፖሊስን አገልግሎት ለማግኘት 011 1110111 ወይም ነጻ የስልክ መስመር 991 መጠቀም እንደሚቻል ፖሊስ አስታውቋል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

16 Nov, 11:33


የቻይናው ኤፍ ኤንድ ቲ በኢትዮጵያ ሶኬቶችን ዩኤስቢ እና ታይፕ ሲ የሞባይል ቻርጅ የሚቀበል  የኤሌትሪክ ማከፋፈያ አምርቶ ለገበያ ሊያቀርብ መሆኑን ገለፀ

በለቡ ባርኔሮ የሚገኘው ይሄ  ፋብሪካ  ለገበያ ይዤ እቀርባለው ያለው የኤሌትሪክ ማከፋፈያ በሁለት መልኩ የተዘጋጀ ሲሆን አንደኛው አራት ሶኬት ፣ ስድስት ዪኤሲቢ እና ሁለት ታይፕ ሲ መሰኪያ ቦታዎች አሉት።

ሌላኛው ሶስት ሶኬት ፣ አራት  ዪኤሲቢ እና ሁለት ታይፕ ሲ መሰኪያ ቦታዎች እንዳሉት የድርጅቱ ማርኬቲንግ ሀላፊ ፍራንክ ዢያ ገልፀዋል።

ማከፋፈያው እስከ 250 ቮድረስ ቮልቴጅ ሲኖረው ሀይል መጠኑ ደግሞ 2,500 ዋት ነው ተብሏል።

ምጣድ ፣ስቶቨ  የሞባይል ቻርጅን ፣ላፕቶፕን እና ሌሎች የኤለክትሮኒክስ እቃዎችን መሰካት ይቻልበታል  የተባለው ማከፋፈያን ድርጅቱ በወር ሀምሳ ሺ ለማምረት ማቀዱንም ተናግሯል።

  ማከፋፈያው ለሁሉም ሀገር ሆኖ የተመረተ ነውም ተብሏል።

Fidel post

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

16 Nov, 07:05


ቦክሰኛ ማይክ ታይሰን በጄክ ፖውል ተሸነፈ

የ58 ዓመቱ አሜሪካዊ የከባድ ሚዛን ቦክሰኛ ማይክ ታይሰን ከ27 ዓመቱ ጄክ ፖውል ጋር ባደረገው ግጥሚያ ተሸንፏል፡፡

ታይሰን ዛሬ ማለዳ ያደረገው ግጥሚያ ራሱን ከፕሮፌሽናል ውድድር ካገለለ ከ19 ዓመታት በኋላ የተከናወነ ነው፡፡

የግጥሚያውን ውጤት ተከትሎም ታይሰን 20 ሚሊየን እና ጄክ ፖውል 40 ሚሊየን ዶላር አግኝተዋል፡፡

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

16 Nov, 03:37


#ከዜናዎቻችን| የቢሾፍቱ ከተማ አብዛኛው ስፍራ ለዱባይ ባለሀብቶች በሊዝ እንደተሸጠ የተነገራቸው ነዋሪዎች በአንድ ሳምንት እንዲነሱ መታዘዛቸውን ተናገሩ

ከተማዋን 'በምስራቅ አፍሪካ የቱሪዝም ማዕከል' ለማድረግ እየተሰራ ካለው ስራ ጋር በተያያዘ በርካታ የከተማው ቦታ ለተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ባለሀብቶች ሊሰጥ እንደሆነ በመጀመርያ የተሰማው የዛሬ ሁለት ወር ገደማ ነበር።

"እስከ 80 ፐርሰንት የሚደርስ የከተማው ቦታ ለኤምሬትስ ኢንቨስተሮች ሊሰጥ ነው የሚል መረጃ አለን፣ በዛ ላይ ትንሽ የቤት እድሳት ለማድረግ እንኳን ስንሞክር በከተማው አስተዳደር 'እዚህ ብዙ ስለማትቆዩ ማደስ አትችሉም' እየተባልን ነው" ብለው ነዋሪዎቹ በወቅቱ ለመሠረት ሚድያ ተናግረው ነበር።

ይህን በተመለከተ መሠረት ሚድያ የቢሾፍቱ ከተማ ማዘጋጃ ቤት ሀላፊ የሆኑትን አቶ ገብሬ ዳቢን አነጋግሮ የነበረ ሲሆም "እኔ የከተማው ኢንቨስትመንት ቦርድ ውስጥ አባል ነኝ፣ ግን በዚህ ደረጃ እንዲህ አይነት ኢንቨስትመንት ይመጣል የሚል መረጃ የለኝም" ብለው ተናግረው ነበር።

ሀላፊው የቤት እድሳት ክልከላውም ምናልባት ከተማው ውስጥ ወጥነት ያለው የቤት አሰራር እንዲሆን ከሚሰራው ስራ ጋር የተያያዘ ሊሆን እንደሚችል ገልፀው ነበር።

ነዋሪዎቹ ግን ትነሳላችሁ የሚለው ቃል ከመንግስት እስካሁን ባይወጣም ወደፊት ግን ሊነሱ እንደሚችሉ ስጋታቸውን ገልፀው ነበር።

አሁን በደረሰን መረጃ መሰረት ደግሞ ከ15 እና 20 አመት በላይ በቢሾፍቱ የኖሩ ነዋሪዎች "ቦታው ለዱባይ ባለሀብት በሊዝ ተሽጧል፣ ስለዚህ በአንድ ሳምንት ውስጥ ልቀቁ ተብለናል" በማለት ተናግረዋል።

ይህን ተከትሎ ለገበሬ ባለይዞታዎች ከሳ መክፈል እንደተጀመረ የታወቀ ሲሆን ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ህዝቡን ሰብስበው የአየር ካርታ ላላቸው 105 ካሬ መሬት እንደሚሰጡ ተናግረዋል።

በአንድ ሳምንት ውስጥ ልቀቁ የተባሉት እነዚህ ነዋሪዎች የገበሬ ቤት የሆነውን አረንጓዴ ቀለም፣ የሌላውን ህዝብ ደግሞ ቀይ ቀለም እየቀቡ ለይተው እንደጨረሱ ታውቋል።

የኦሮሚያ ክልልም ሆነ የፌደራሉ መንግስት እስካሁን በግልፅ ምን ያህል መሬት ለኤምሬትስ ባለሀብቶች እንደሸጡ ይፋ አላደረጉም።

Mesert media

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

16 Nov, 03:29


ብዙ መጠሪያ ስሞች ያሉት ማይክ ታይሰን የሚሉት ቡጢኛ መቼስ ጉደኛ ሰው ነው። በጉብዝናው ዓመታት ከ400 ሚሊየን ዶላር በላይ ከስፖርቱ አግኝቷል። እንደ Rolls-Royce እና ፌራሪን የመሳሰሉ ከመቶ በላይ ውድ መኪኖች፣ ስድስት ቅንጡ ቤቶች፣ በርካታ የዳይመንድ ጌጣጌጦችን ሲሰበሰብ ኖረዋል። ለልብስ ብቻ ከሶስት ሚሊየን ዶላር በላይ ያወጣ እንደነበር ይነገራል።
ሲዝናና እና ሲገዛ ለነገ አይልም። ከጓደኞቼ ጋር ዎክ እያረኩ ድንገት ወደሆነ መዝናኛ ቦታ እንሂድ ሲሉኝ ለሰከንድ ሳላቅማማ ወዲያው አዲስ መኪና ገዝቼ ይዣቸው ሄዳለሁ ይላል።

ብራዘር እኔ እኮ ገንዘብ አጠፋለሁ..አይበረክትልኝም አትበል። ማይክ ታይሰን አለልህ። ይበትናል ቢባል እንኳ አይገልጸውም። የሚስቱን ገላ መታጠቢያ ገንዳ በተለየ ሁኔታ ለማሰራት ያወጣውን ብትሰማ ታብዳለህ። ለልደቷ ድግስ ብቻ ከ400K ዶላር በላይ አውጥቷል። [ያውም በእነሱ 80'ዎቹ ውስጥ]። በስፖርቱ እጅግ ስኬታማ ነበር። ከ56 ግጥሚያዎች ውስጥ 50ውን አሸንፈዋል። ያውም 44ቱን በዝረራ።

የጉብዝና ወራቱ ሲያልፉ ጡረታ ወጣ። ቁጭ ብሎ ጥሪቱን መብላት ጀመረ። ሱስ አጧጧፈ። ከዕፅ ጋር ተመቸቸ። ቁማር አስከተለ። ዝነኛው ቡጢኛ በአጭር ጊዜ ቀውስ ላይ ቀውስ እየጨመረ ተቃወሰ። በዚህ ላይ አስገድዶ የመድፈር ክስ እና እስር። የሃብቱ ተራራ በፍጥነት ተናደ። የገላ መታጠቢያን በወርቅ ያሰራላት ሚስቱ 9 ሚሊየን ዶላር ወስዳ ተሸበለለች። ተለየችው። ሌላ አገባ። እሷም ሃብቱን ተካፍላ እብስ አለች። ቀሪ ሃብቱን ቁማር እና መጠጥ ቤቶች ተከፋፈሉት። ጭራሽ መኪኖቹን እና ቤቶቹን በሙሉ በመሸጥ ወደ ዕዳ ገባ። 400 ሚሊየን ዶላሩ ጨርሶ ከ30 ሚሊየን በላይ ዕዳ ተሸካሚ ሆነ። በብድር የተገዘችን መኪና ይዞ ለማደሪያ ጓደኛው ቤት በጥገኝነት ገባ።

በወቅቱ በሰጠው አንድ ቃለመጠይቅ እንዲህ አለ
[ ለሰላምታ የሚጠይቀኝ ሰው አልነበረም። የሚፈልጉኝ በሙሉ አበዳሪዎቼ ናቸው። እራሴን ጠላሁ። በጥልቀት መውደቄን አየሁ። የባከነ ሕይወት መምረጤን ተረዳሁ። እንደምንም በምንም ዋጋ ዕዳዬን ከፍዬ ከሰው ዓይን ዞር ማለት..ከአሜሪካ መራቅ ፈልግኩ ]

ዘመን አልፎ ዘመን ሲተካ አዲስ ፀሐይ ወጣች።
ከሱስ አገገመ። ከቁማር እና ዕፅ ራቀ።
በተቋማት ታግዞ ዕዳውን ለመክፈል ዳግም ወደ ቦክሱ ሪንግ ተመለሰ። በተለያዩ ስፖንሰሮችም ታገዘ። ዕዳውንም መክፈል ቻለ። እንዳውም አሁን እስከ 10 ሚሊየን ዶላር የተጣራ ሃብት አፈራ።

እነሆ...
ዛሬ ንጋት በ58 ዓመቱ ከወጣቱ ጄክ ፓውል ጋር ዳግም ቡጢ ይጋጠማል። በዚህም ተጨማሪ ሚሊየን ዶላሮችን ይዝቃል። 70 ሺህ ተመልካች ፊት የሚደረገውን የቡጢ ግጥሚያ Netflix ለ280 ሚሊየን ደንበኞቹ በቀጥታ ያስተላልፋል።

እኔ ጠብ፣ ጠበኞች፣ ቡጢ እና ቡጢኞችም አይመቹኝም። ሰው እንዴት በድብድብ እንደሚዝናና አይገባኝም። ሞሐመድ አሊ በፖለቲካዊ ሃሳቦቹ እና በቀጥተኝነቱ ደስ ይለኛል። በርግጥ ታይሰንም ፖለቲካዊ እሳቤዎቹን በንቅሳቶቹ ይነግረናል። ብዙ ንቅሳቶች አሉት።

[ አርቱር አሼ: በቴኒስ የገነነ ጥቁር
Spike Lee: ነጮች በፊልሞቻቸው ያሳነሳቸውን ጥቁር አሜሪካዊንን በፊልሞቹ ለማቃናት የተጋ
.
.
ማኦ ዜዶንግ
ቼ ጉቫራ
ፊቱ ላይ የ{Maori} ጎሳ ታጋይነት ምልክት ]
እነዚህ ነቅሳቶቹ Political statement ናቸው።

የሆነ ሆኖ...
በዚህኛው ግጥሚያ ግምቴ ለወጣቱ Jake Paul ነው። በመካከላቸው የ30 ዓመት የዕድሜ ልዩነት አለ። ታይሰን ነገሩ ከከበደው ከዚህ ቀደም የሆሊፊልድን ጆሮ ነክሶ ደም በደም እንዳረገው ታሪክ እራሱን ልደግም ይችላል። በተረፈ ማይክ ታይሰን ወድቆ የመነሳት ተምሳሌት ነው።

ፀሐፊ ጥላዬ ያሚ #FastMereja

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

15 Nov, 17:20


የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ የወጣ ወጣት በተአምር ህይወቱ ተርፏል
…….///…….
በከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ላይ የወጣ ወጣት ኃይል እንዲቋረጥ ማድረጉን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታውቋል፡፡

በዘርፉ የደቡብ ሁለት ሪጅን እንደገለፀው ወጣቱ ዛሬ ከቀኑ 8:00 ጀምሮ ከወላይታ ሶዶ ወደ ሳውላ በሚሄደው ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ ወጥቶ አልወርድም በማለቱ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በሚገኙ ጎፋ ዞን፣ አሪ ዞን፣ ባስኬቶ ዞን እና ኦሞ ዞን ሙሉ በሙሉ እንዲሁም ጋሞ ዞን በከፊል ከሦስት ሰዓታት በላይ ኃይል ተቋርጦ ቆይቷል፡፡

በምን ምክንያት የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ላይ እንደወጣ ያልታወቀው ወጣት በአካባቢው ሽማግሌዎችና የመስተዳድር አካላት ቢለመንም ለመውረድ ግን አስቸግሮ እንደነበር መምሪያው ገልጿል፡፡

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ባለሙያዎች ኃይል በማቋረጥ ወጣቱ ሳይጎዳ በገመድ አስረው በማውረድ በተአምር ህይወቱን ታድገዋል፡፡

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

15 Nov, 14:20


የደቡብ ወሎ እና ሰሜን ሸዋ ዞኖች መምህራን የጸጥታ ችግር ባለባቸው አካባቢዎች ሥራ እንዲጀምሩ አስገዳጅ መመሪያ እንደወጣባቸው ገለጹ

በአማራ ክልል ደቡብ ወሎና ሰሜን ሸዋ ዞኖች የሚገኙ መምህራን የጸጥታ ችግር ወደአለባቸውና ወደተመደቡባቸው የገጠር ት/ቤቶች ሄደው ሥራ እንዲጀምሩ በአካባቢው ባለሥልጣናት አስገዳጅ መመሪያ እንደወጣባቸው ገለጹ፡፡

መምህራኑ የተመደቡባቸው ቀበሌዎች በፌደራል መንግሥቱ እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል ከፍተኛ ግጭት የሚካሄድባቸው በመኾናቸው ለደህንነታቸው እንደሚሰጉ ተናግረዋል፡፡ እንዳይቀሩ ደግሞ ወደምድብ ቦታቸው ካልሄዱ ደሞዝ እንደማይከፈላቸው እንደተነገራቸው ገልጸዋል፡፡ መምህራኑ በዚህ መሃል ችግር ላይ መውደቃቸውን አመልክተው የጸጥታው ሁኔታ እስኪስተካከል መንግሥት ችግራቸውን እንዲረዳላቸው ጠይቀዋል፡፡

የአማራ ክልል መምህራን ማኅበር በመምህራኑ ስለተነሳው ቅሬታና ስጋት መረጃ እንዳለው ጠቅሶ በትጥቅ ትግል ውስጥ ያሉ አካላት የመማር ማስተማሩ ሂደት ከጸጥታ ችግር የጸዳ እንዲሆን በማድረግ የበኩላቸውን ድርሻ እንዲያበረክቱ ጥሪ አስተላልፈዋል፡፡

Via VoA

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

15 Nov, 14:20


"የውጭ ባንኮች እንዲገቡ ቢፈቀድም፣ እንዲቆጣጠሩን አልተፈቀደም" ብሔራዊ ባንክ

የውጭ ባንኮች ወደ ኢትዮጵያ የፋይናንስ ዘርፍ ገብተው እንዲቀሳቀሱ እንጂ የቁጥጥር ስራን እንዲሰሩ ፍቃድ እንዳልተሰጠ ተነግሯል፡፡

ይህ የተሰማው የህዝብ እንደራሴ ምክር ቤት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና የፕላን በጀት እና ፍይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዎች ከተለያዩ የባንክ ባለ ድርሻ አካላት ይፋዊ የሆነ ውይይት ባደረጉበት ወቅት ነው።

በዚህ ወቅት የብሔራዊ ባንክ ገዢው ማሞ ምህረቱ የውጭ ባንኮች ወደ ሀገር ውስጥ መግባታቸው በሚያመጣው እድል እና ስጋት ለቀረበላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ምላሽ " ክፍት ማድረግ ማለት ተጨማሪ ተዋናዮችን መጋበዝ ሲሆን፣ ይቆጣጠሩናል ማለት ከቁጥጥር ነፃ ማድረግ ነው። እኛ ከቁጥጥር ነፃ እናድርጋቸው እያልን ሳይሆን፣ እየተቆጣጠርን ዘርፉን ክፍት እናደርጋለን ነው ያልነው" ሲሉም መልሰዋል።

አክለውም የውጭ ባንኮች በመግባታቸው ለዘርፉ የተሻለ ተጠቃሚነትን የፍይናንስ ጤናማነት በተጠበቀ መልኩ ሲሆን ነው ብለዋል።

ከዚህ በተጨማሪ ስለ ባንኮች ውህደት ለቀረበላቸው ጥያቄ እንደ መመሪያ ህግ ስርዓት ታስቦ የተቀመጠ እንጂ የፖሊሲ ውሳኔ አይደለም ሲሉም ነው ያብራሩት።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

14 Nov, 13:57


አልሸባብን የማዳከም ስራ እንደሚቀጥል የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለፀ!

በሶማሊያ የሚገኘውን አሸባሪ ቡድን አልሸባብ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ሥጋት እንዳይሆን "በየትኛውም ሁኔታ አሸባሪ ቡድኑን የማዳከም ሥራ የሚቀጥል ይሆናል" ሲል መንግሥት አስታወቋል፡፡

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል ዐቀባይ አምባሳደር ነቢያት ጌታቸው ዛሬ በሰጡት መግለጫ ሶማሊያ የኢትዮጵያ ሠራዊት በአዲሱ የአፍሪካ ሕብረት የድጋፍ እና የማረጋጋት ተልዕኮ ውጪ መሆኑን ባለፈው ሳምንት በይፋ ማስታወቋን በተመለከተ የኢትዮጵያን አቋም ሲጠየቁ ነው ይህንን ያሉት።

ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ "የማይነጣጠሉ ሕዝቦች እንደመሆናቸው ጊዜያዊ ችግሮችን የመባባስ ፍላጎት የለንም" ያሉት ቃል አቀባዩ የሶማሊያ ማንግሥት ይፋ ላራመደው አቋም አልሸባብን እናዳክማለን ከማለት በቀር ቀጥተኛ ምላሽ አልሰጡም።

ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ የተካረረ የዲፕሎማሲ ግንኙነት ውስጥ እንዲገቡ ምክንያት የሆነው የኢትዮጵያ እና የራስ ገዟ ሶማሊላንድ «የባሕር በር እውቅና» የመግባቢያ ስምምነት እስካሁን በሂደት ላይ መሆኑ ሲገለጽ በአንድ በኩል፣ አልሸባብን በመዋጋት ለዓመታት የጋራ ግብ እና ጥብቅ ወዳጅነት የነበራቸው ኢትዮጵያ እና ሶማሊያን ሆድና ጀርባ አድርጎ ከቃላት ያለፈ የዲፕሎማሲ ውጥረት ውስጥ ከቷቸዋል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

10 Nov, 12:51


የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የውጭ ምንዛሬ ቢሮ ተገልጋዮችን በአገልግሎቱ ቅሬታ እየቀረበበት ነው

የባንኩ አዲስ አበባ ቅርንጫፍ፤ ወይም የውጭ ምንዛሬ የሚሰጥበት ክቡ ህንፃ ያሉ አንዳንድ ሰራተኞች ደንበኞችን በማንጓጠጥ፣ በመሳደብ እና በማጉላላት ላይ መሆናቸውን የደረሱን ተደጋጋሚ ጥቆማዎች ያሳያሉ።

"እኔ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የረጅም ጊዜ ደንበኛ ስሆን በቅርቡ የውጭ ምንዛሬ ለመውሰድ አዲስ አበባ ቅርንጫፍ ያለበት የምንዛሬ ቢሮ እንደማንኛውም ደንበኛ ማሟላት ያለብኝን ነገሮች ማለትም ፓስፖርት፣ ቪዛ እና ትኬት ይዤ ብሄድም ያጋጠመኝን ነገር ለማመን ተቸግሬያለሁ" ያሉን አንድ ግለሰብ የባንኩ የስራ ሐላፊዎች ደንበኞችን በአግባቡ እንኳን አያናግሩም፣ "ከፈለክ ውሰድ ካልፈለክ መተው ትችላለክ" በማለት ደንበኛን እንደሚያንጓጥጡ ተናግረዋል።

"ምክትል ስራ አስኪያጅ ተብሎ የተቀመጠው ግለሰብ ለደንበኛ የሚያሳየው ንቀት በጣም የተጋነነ ነው። እሺ ብለህ ምክትሉን ትተህ ዋና ሐላፊው ጋር ስትሔድ ጭራሸ የባሰበት እና ለሰው ክብር የሚባል የሌለው ነው፣ እያወራኸው ጥሎህ ይሔዳል፣ እኔ ባንክ ሳይሆን ፖሊስ ጣቢያ ወንጀል ሰርተህ የሔድክ ነው የሚመስለው" ያሉት ደግሞ ሌላኛው ጥቆማ ሰጪ ናቸው።

ሶስተኛው ግለሰብ ደግሞ የራሱ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሰራተኛ መሆኑን በመግለፅ እንዲህ ብሏል: "እኔ የምሰራው አዲስ አበባ ውስጥ በሚገኝ አንድ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፍ ነው። በቅርቡ ወደ ዱባይ የመሔድ እድል ነበረኝ እና ምንዛሬ ለመግዛት ብሔራዊ ወደ ሚገኘው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የውጭ ምንዛሬ ቢሮ መሔድ ነበረብኝ። ነገር ግን ምንዛሬውን የሚፈቅደው የባንኩ የስራ ሐላፊ እኔ በብሬ የምገዛ ሳይሆን ከኪሱ አውጥቶ የሚሰጠኝ ነው የሚመስለው። በጣም በሚገርም ሁኔታ ሰው ሲያመናጭቅ አይደለም ለደንበኛ እና ለሰራተኛ እንኳን ክብር የሌለው ፣ ይጨመርልን አነሰን ብለው የሚገቡ የባንኩ ደንበኞችን በጥበቃ አስወጣችኋለሁ ከፈለጋችሁ የተፈቀደላችሁን ውሰዱ በማለት ማመናጨቅ ላይ ይገኛሉ። መቼም ባንኩ ይኸን ጉዳይ ሳያውቅ ቀርቶ ሳይሆን የሆነ ሰው እንዳለው ያስታውቃል፣ ምክንያቱም የባንኩ ዋና መስሪያ ቤት እዛው አፍንጫው ስር ነው" በማለት ትዝብቱን ለመሠረት ሚድያ አጋርቷል።

መሠረት ሚዲያ

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

10 Nov, 12:49


በሰቃ ሐይቅ ዙሪያ ተደብቆ የኖረው ውበት ብርሃን አግኝቷል - አቶ ሽመልስ አብዲሳ

በምስራቅ ሸዋ ዞን ፈንታሌ ወረዳ በሰቃ ሐይቅ ዙሪያ ተደብቆ የኖረው ውበት ብርሃን አግኝቷል ሲሉ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር ሽመልስ አብዲሳ ገለጹ፡፡

ርዕሰ መስተዳድሩ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው፤ የሀገራችንን የኋላ ቀርነት ታሪክ ከሁሉም በላይ ከኢኮኖሚያዊ ችግሮች የሚመነጨውን ለመቅረፍ የለውጡ መንግሥት ጠንከር ያሉ ርምጃዎችን በመውሰድ በፍጥነት እየተንቀሳቀሰ ይገኛል ብለዋል፡፡

በዚሁ መሠረት ሁሉን አቀፍ የሆነ ኢኮኖሚ ለመገንባት በተያዘውን ዕቅድ፣ የቱሪዝም ሴክተር እንደ አንድ የትኩረት አቅጣጫ ተይዞ ፈጣን ለውጥ እያስመዘገበ ይገኛል ነው ያሉት፡፡

የቱሪዝም ሴክተር ሰፊ እምቅ አቅም ያለውና ለሀገራችን ትልቅ ውጤት የሚያስገኝ ሆኖ ሳለ የማልማቱ ስራ ለዘመናት ትኩረት ተነፍጎት ቆይቷል ሲሉም አስታውሰዋል።

በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የላቀ የፖሊሲ አቅጣጫ ወደ ሥራ ከተገባ በኋላ በአስገራሚ አፈጻጸም ሀገራችን በዚህ ረገድ ማግኘት የሚገባትን ጥቅም እውን የሚያደርግ ስራ በስፋት እየተከናወነ ነው ብለዋል፡፡

በምስራቅ ሸዋ ዞን ፈንታሌ ወረዳ በሰቃ ሐይቅ ዙሪያ ተደብቆ የኖረው ውበት ብርሃን አግኝቷል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ ይህ አፈጻጸም ከማይናወጥ የሀገር ትልምና ዓላማ ተኮርነት የመነጨ ነው ሲሉ ገልፀዋል፡፡

በቀጣይም ለሀገራችን መሠረታዊ ችግሮች መሠረታዊ መፍትሔ በማምጣት ብልጽግናን እውን ለማድረግ ጠንክረን እንደምንሠራ አረጋግጣለሁ ብለዋል፡፡በበሰቃ ሐይቅ ዙሪያ የተከናወነውን ሥራ ለማሳካት አስተዋጽኦ ላበረከቱ የአመራር አባላትና ባለድርሻ አካላትም ምስጋና አቅርበዋል፡፡

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

10 Nov, 11:10


<<...እንባዬን መቆጣጠር አልቻልኩም ነበር..>>ዶ/ር ዳዊት ወንድማገኝ

"ተርፏቸው ሳይሆን ካላቸው ላይ ነበረ ለኔ ስጦታ ብለው ያመጡልኝ"

ዶ/ር ዳዊት ወንድማገኝ ሸገር ሬዲዮ ላይ ከመዓዛ ብሩ ጋር በነበረው የጨዋታ ፕሮግራም  እንዲህ ስትል ጠየቀችው ፦ ዶ/ር ዳዊት ላንተ የተሰጠህ  ትልቁ ስጦታ የቱ ነው ?

ዶ/ር ዳዊት፦ ሁሌም ይህን ጥያቄ ስጠየቅ በተደጋጋሚ የምመልሰው መልስ ይህንን ነው።

ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ፕሬዝዳንት ሆኜ ስሰራ አንድ ምስኪን ገበሬ ከአምቦ አካባቢ ልጃቸው ታሞ ይዘው መተው እንከታተልላቸው ጀመር ። ልጁም ከቀን ወደ ቀን ለውጥና መሻሻል ማሳየት ጀመረ።

አባትም ቢሮዬ መጡ። ዶክተር እንደው እባክህ  ከድፍረት እንዳታይብኝ እባክህ ብለው ተጨናነቁ፤ ምንድነው አባቴ? አልኳቸው እሳቸውም ወጣ ብለው ማዳበሪያ ተሸክመው መጡ ።

ማዳበሪያ ውስጥም በቆሎ እሸት ነበረ ።ይሄ ነው የደረሰው ብለው  እሱን ሲሰጡኝ እንባዬን መቆጣጠር አልቻልኩም ነበር።

ተርፏቸው ሳይሆን ካላቸው ላይ ነበረ ለኔ ስጦታ ብለው ያመጡልኝ።
(✍️ጌጡ)

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

10 Nov, 06:18


ኢትዮጵያ ውስጥ የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ደንበኞች ኤምፔሳን ባብዛኛው የኢንተርኔት ዳታ እና የአየር ሰዓት ለመግዛት እንጅ ገንዘብ ለመላላክ፣ ለመበደር ወይም ኢንሹራንስ ለመክፈል እንደማይጠቀሙበት መናገሩን ቢዝነስ ደይሊ አስነብቧል።

ኩባንያው 8 ነጥብ 3 ሚሊዮን ደንበኞቹ ኤምፔሳን በዋናነት ገንዘብ ለመላላክ ወይም ክፍያዎችን ለመክፈል የማይጠቀሙበት፣ ለአንስተኛ የገንዘብ ልውውጦች ጥሬ ገንዘብ ብቻ መጠቀምን ስለሚመርጡና ከከተማ ወደ ገጠር ገንዘብ የመላክ ልምድ ስለሌላቸው ነው በማለት መናገሩን ዘገባው ጠቅሷል።

ከከተማ ወደ ገጠር ከፍተኛ ገንዘብ በኤምፔሳ በሚላክባት ኬንያ፣ ለሳፋሪኮም ከፍተኛውን ገቢ የሚያስገኘው ኤምፔሳ ነው።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

09 Nov, 21:47


በፑቲን እና ኔታንያሁ ላይ የእስር ማዘዣ እንዲወጣ የጠየቁት የአይሲሲ አቃቤህግ በወሲባዊ ትንኮሳ ምርመራ ተጀመረባቸው

ዋና አቃቤ ህጉ ምርመራው እስኪጠናቀቅ ድረስ ከሃላፊነት ሊነሱ እንደሚችል ተነግሯል።

በእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ እና በሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ላይ የጦር ወንጀል ክስ እንዲመሰረት የጠየቁት የአለም አቀፉ ወንጀለኞች ፍርድ ቤት ዋና አቃቤ ህግ ካሪም ካን በፆታዊ ጥቃት ምርመራ ላይ እንደሚገኙ ተነግሯል።

ጉዳዩ የተሰማው በግንቦት ወር ሲሆን ዋና አቃቤ ህጉ በኔታንያሁ እና በተሰናባቹ የመከላከያ ሚንስትር ዮአቭ ጋላንት ላይ የእስር ማዘዣ ከመጠየቃቸው ከጥቂት ሳምንታት በፊት ነበር።

የአይሲሲ ዳኞች በአሁኑ ወቅት አቃቤ ህጉ በግንቦት ወር በእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር፣ በመከላከያ ሚንስትሩ እና በሃማስ መሪዎች ላይ የእስር ማዘዣ ኢንዲወጣ ያቀረቡትን ጥያቄ እየገመገሙ ነው።

ካን የጥፋተኝነት ውንጀላው በጽህፈት ቤታቸው ላይ እየተካሄደ ከሚገኘው የተሳሳተ መረጃ ዘመቻ ጋር የተገናኘ ነው ሲሉ አስተባብለዋል።

ጥቃት እንደተፈጸመባቸው ሪፖርት ያደረጉት ሁለት ሴቶች ለድርጅቱ የውስጥ ምርመራ ክፍል ቃላቸውን የሰጡ ሲሆን አጣሪ ቡድኑ ተፈጽሟል የተባለውን ትንኮሳ ለውጭ የህግ አካላት አሳልፎ ከመስጠቱ በፊት ማጣርያዎችን እያደረገ ነው ተብሏል፡፡

በውንጀላው ዙርያ ለውይይት የተሰራጨው የውስጥ ሰነድ የሥነ ምግባር ጉዳዮችን የሚመረምረው የፍርድ ቤቱ ገለልተኛ አካል ክሱ መጀመሪያ ላይ በቀረበበት ወቅት መደበኛ ምርመራ ማድረግ ነበረበት ሲል ተከራክሯል።

የጾታዊ ጥቃት ክሶቹ ባለፈው ወር በፍርድ ቤቱ የበላይ አካል ምርመራ እንዲደረግባቸው ትዕዛዝ ከተሰጠ በኋላ ድርጊቱን ፈጽመዋል የተባሉት የፍርድ ቤቱ ዋና አቃቤ ህግ ካን ድርጊቱን እንዳልፈጸሙ በመግለጽ ምርመራው እንዲቋረጥ ጠይቀዋል፡፡
በዚህ ሳምንት ለድርጅቱ አባል ሀገራት የተላከው ደብዳቤ ምርመራው እስከሚጠናቀቅ ድረስ አቃቤ ህጉ በጊዜያዊነት ከሀላፊነታቸው ሊነሱ እንደሚችሉ ማመላከቱን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡

የስነ ምግባር ጉዳዮችን የሚያጣራው የህግ አካል የሚመሩት ሃላፊ በዋና አቃቤህጉ ቢሮ ውስጥ ሲሰሩ የነበሩ በመሆናቸው ተበዳዮቹ በውስጥ ምርመራው ላይ እምነት እንደሌላቸው ገልጸዋል፡፡

በዚህም አጣሪ ኮሚቴው በእጁ ላይ የሚገኙትን መረጃዎች ለኔዘርላንድ መደበኛ የፍትህ ሰዎች በማስተላለፍ ጉዳዩ ማጣርያ እንዲደረግበት ጠይቀዋል፡፡
Via : Alain

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

09 Nov, 14:58


የሩሲያ የወርቅ ክምችት ዋጋ በታሪክ ከፍተኛ ደረጃ ላይ መድረሱ ተገለጸ

የሩሲያ የወርቅ ክምችት ዋጋ ለመጀመሪያ ጊዜ በጥቅምት ወር ውስጥ ከ200 ቢሊዮን ዶላር በላይ ያለፈ ሲሆን ሀገሪቱ በአለም አቀፍ ክምችት ያላት ድርሻ 32.9 በመቶ መጨመሩን የሩሲያው አርቲ የሀገሪቱን ብሔራዊ ባንክ መረጃ ጠቅሶ ዘግቧል።

'ባንክ ኦፍ ሩሲያ' የወርቅ ክምችት ዋጋው በ4 በመቶ ማደጉን እና ባለፈው መሰከረም ወር የተመዘገበውን ሪከርድ መስበሩን በትናንትናው እለት ባወጣው ሪፖርት ገልጿል። ባንኩ እንደገለጸው  የክምችቱ ዋጋ እስከ ህዳር አንድ ድረስ 207.7 ቢሊዮን ዶላር ደርሷል።

ባለፈው ጥቅምት ወር የወርቅ ዋጋ በ4 በመቶ የጨመረው አንድ አውንክ ሪከርድ በሰበረ 2800 ዶላር ከተሸጠ በኋላ ነው። የወርቅ ዋጋ በጂኦፖለቲካዊ ውጥረት ምክንያት በቅርብ ጊዜያት ሲዋዥቅ ቆይቷል።

የሩሲያ አለምአቀፍ የወርቅ ክምችት ጭማሪ 34 በመቶ ከተመዘገበበት ከህዳር 1999 ወዲህ ባለፈው ወር ነው ከፍተኛ ሆኖ የተመዘገበው። በአጠቃላይ በሀገሪቱ ዘመናዊ ታሪክ ከፍተኛ ሆኖ ተመዘገበው 59.9 በመቶ ጭማሪ በጥር 1993 ነው።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

09 Nov, 14:39


ኤፍቢአይ በመላው አሜሪካ ለጥቁሮች የተላኩ ዘረኛ የጽሑፍ መልዕክቶች ላይ ምርመራ ጀመረ

በመላው አሜሪካ ለሚገኙ ጥቁሮች የተላኩ ዘረኛ የጽሑፍ መልዕክቶች ላይ ምርመራ መክፈቱን የአሜሪካው የፌደራል የምርመራ ቢሮ አስታወቀ።

የተላኩት የጽሑፍ መልዕክቶች በባርነት ዘመን እንደነበረው “ወደ ማሳ ሄደው ጥጥ ለቅመው ለጌቶቻቸው ሪፖርት” እንዲያደርጉ የሚጠቅስ ነው።

የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እና የዩኒቨርስቲ ጥቁር ተማሪዎችን ጨምሮ በአላባማ፣ ሰሜን ካሮላይና፣ ቨርጂኒያ፣ ኒውዮርክ እና ፔንስልቬንያ ግዛቶች ነዋሪ የሆኑ ጥቁሮች እነዚህ የጽሑፍ መልዕክቶች ደርሷቸዋል ተብሏል።

“ኤፍቢአይ ለነዋሪዎች የተላኩትን አጸያፊ እና ዘረኛ የጽሑፍ መልዕክቶችን ያውቃል እናም በጉዳዩ ላይ ከፍትህ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እና ከሌሎች የፌደራል ባለስልጣናት ጋር እየመከረ ነው” ብሏል የፌደራል ምርመራ ቢሮው
የጽሑፍ መልዕክቶቹ መላክ የጀመሩት አሜሪካ ካደረገችው ብሄራዊ ምርጫ ማግስት እንደሆነ ይታመናል።

አንዳንድ መልዕክቶች የትራምፕ የምርጫ ቅስቀሳ ዘመቻ ቡድንን ቢጠቅስም ቡድኑ በበኩሉ ንክኪ የለኝም ሲል ውድቅ አድርጓል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

09 Nov, 14:36


የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለክልሉ መምህራን እንዲከፈል ፌደራል መንግስት የፈቀደውን የአምስት ወር ደመወዝ ለሌላ አላማ አውሎታል በሚል ክስ ተመሰረተበት!

የትግራይ ክልል የመምህራን ማህበር በክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር እና በፌደራል መንግስቱ ላይ የመሰረተው ክስ ህዳር 12 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚታየ ተገለጸ።በነሀሴ ወር 2016 ዓ.ም ክሱን የመሰረተው ማህበሩ፣ ሁለቱም አካላት ለ17 ወራት ለክልሉ መምህራን መከፈል የነበረበትን ደመወዝ ባለመክፈላቸው መሆኑ ይታወቃል።የትግራይ መምህራን ማህበር ጠበቃ የሆኑት አቶ ዳዊት ገብረሚካኤል ለአዲስ ስታንዳርድ እንደተናገሩት በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር እና በፌደራል መንግስት ላይ የቀረበው ክስ በጠቅላይ ፍርድ ቤቱ እየታየ ነው።

"ክስ ከተመሰረተባቸው መካከል የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር፣ የክልሉ ትምህርት እና ፋይናንስ ቢሮዎች ይገኙበታል፣ ክሱም የፌደራል መንግስት ለመምህራን የላከውን የአምስት ወር ደሞዝ ለሌላ አገልግሎት በማዛወራቸው የተሰጣቸውን ስልጣን ያለአግባብ ተጠቅመዋል” የሚል ነው ሲሉ ገልጸዋል።በተጨማሪ የፌዴራል መንግስት ደግሞ “የ12 ወራት ደሞዝ ባለመልቀቁ ነው ክሱ የተመሰረተው" ሲሉ አቶ ዳዊት አስረድተዋል፡፡

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

09 Nov, 14:02


ኢትዮጵያ የብሪክስ ሀገራት ዩኒቨርስቲዎች ማህበር መስራች መሆን መቻሏ ተነግሯል

ኢትዮጵያን በመወከል የብሪክስ አገራት ዩኒቨርስቲዎች ማህበርን መመስረት የቻለው የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሲሆን ይህም ከሌሎች ሃገራት ጋር በጥናትና ምርምር እንዲሁም በፈጠራ ስራ በጋራ መሰራት የሚያስችላቸው መሆኑ ተመላክቷል።

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሩሲያ፣ ህንድና ብራዚልን ጨምሮ ከብሪክስ ሀገራት ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በመሆን በጣምራ የብሪክስ ሀገራት ዩኒቨርሲቲዎች ማኅበርን በመመስረት የመጀመሪያው የምስራቅ አፍሪካ ሀገር ዩኒቨርስቲ መሆኑን ዩኒቨርስቲው አስታውቋል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

08 Nov, 17:24


የገዛ ወንድሙን አግቶ ገንዘብ የጠየቀው ግለሰብ  በፅኑ  እስራት  ተቀጣ

ተከሳሽ የኔው ብርሀኑ የእንጅባራ ከተማ አሰተዳደር  ነዋሪ ሲሆን  በጥቅምት 19/ 2017 ዓ.ም  ከቀኑ 6.30 ሰዓት ከቢዳ ጀጎላ ት/ቤት የሚማረውን ወንድሙን ስልክ በመደወል የእናታችንን ልብስ ውሰድ ብሎ ከት/ቤት ከአሰወጣ በኋላ የ14 ዓመት ወንድሙን በማገት ከወላጅ ቤተሰቦቹ 1,000,000/አንድ  ሚሊዮን  ብር/ መጠየቁን የፖሊስ መረጃ ያሳያል።

በሁኔታው የተደናገጡት የታጋች ቤተሰቦች ወዲያውኑ ለእንጅባራ ከተማ  አስተዳደር  ፓሊስ  በሰጡት ጥቆማ  በተደረገ ብርቱ ክትትልና ቁጥጥር በሶስተኛው ቀን ጥቅምት 21/2017 ዓ.ም ከንጋቱ  11 ሰዓት  ሲሆን  ከተደበቀበት ቢዳጀጎላ ቀበሌ  ልዩ ስፍራ አማያስቲ ጎጥ ላይ እጅ ከፍንጅ  ተይዟል።

ፖሊስ ምርመራውን አጣርቶ  ለሚመለከተው የፍትህ  አካል የላከ ሲሆን መዝገቡ  የቀረበለት  የአዊ ዞን ከፍተኛ  ፍ/ቤትም ጥቅምት 29/2017 ዓ.ም  በዋለው  ችሎት  ተከሳሹ የኔው ብርሃኑ በ7 ዓመት  ከ8 ወር ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ተወስኖበታል ሲል አዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን ፖሊስ ሚዲያና  ኮሚኒኬሽን ዋና ክፍል ያደረሰን መረጃ ያሳያል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

08 Nov, 17:22


አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለድህረ ምረቃ ትምህርቶች በሰዓት ከ900 ንር እስከ 4,615 ብር ሊያስከፍል መሆኑ ተሰምቷል

ዩኒቨርሲቲው ራስ ገዝ መሆኑን ተከትሎ ለድኅረ ምረቃ ፕሮግራሞች አዲስ የትምህርት ክፍያ ፖሊሲን እና መመሪያን ነሐሴ 2016 በሴነቱ አጽድቋል።

በዚሁ መሰረት ለማስተርስ (ወይም ሁለተኛ ዲግሪ) መርኃ ግብር በሰዓት ከ900 እስከ 3,462 ብር እንደ ሙያ መስኩ የክፍያ ተመን አስቀምጧል።

በተመሳሳይ ለፒኤችዲ መርኃ ግብር በሰዓት ከ1,200 እስከ 4,615 ብር እንደ ሙያ መስኩ የክፍያ ተመን ማዘጋጀቱ ታውቋል።

ለመመረቂያ እና ለምርምር ለማስተርስ ከ675 እስክ 900 ብር፣ ለፒኤችዲ ደግሞ 18,000 ብር በሴሚስትር ተመን አውጥቷል።

አዲሱ የክፍያ ተመን ተግባራዊ የሚሆነው ከዘንድሮው የ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ1ኛ ወሰን ትምህርት ጀምሮ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል፡፡

በተጨማሪም የድኅረ ምረቃ ተማሪዎች በየሴሚስትሩ 300 ብር የመመዝገቢያ ክፍያ ተጥሎባቸዋል። ሁሉም ክፍያዎች ለኢትዮጵያዊያን ተማሪዎች ብቻ መሆናቸውን ዩኒቨርሲቲው ያስታወቀ ሲሆን ክፍያዎቹ በዚህ ከፍተኛ መጠን ለምን እንደጨመሩ የሰጠው ማብራርያ የለም።
መሰረት ሚዲያ

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

08 Nov, 10:13


በንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር በኩል ይደረግ የነበረዉ #የሲሚንቶ ግብይት ትስስር ስራ ከዛሬ ጀምሮ እንዲቀር መደረጉ ተገለጸ

ከዚህ ቀደም በንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር በኩል ይደረግ የነበረዉ የሲሚንቶ ግብይት ትስስር ሥራ ከዛሬ ጥቅምት 29 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ እንዲቀር መደረጉን ሚኒስትሩ ዶ/ር ካሳሁን ጎፌ አስታወቁ።

አምራቾች በራሳቸዉ ኃላፊነት በሚመርጧቸዉ አከፋፋዮችና ቸርቻሪዎች በኩል ለተጠቃሚዎች በተመጣጣኝ ዋጋ ማቅረብ ይችላለሁ የሚል ውሳኔ መተላለፉን ሚኒስትሩ ገልጸዋል።

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ዶ/ር ካሳሁን ጎፌ ይህንን የመንግስት ውሳኔ ያስታወቁት የሲሚንቶ ምርት አቅርቦትና ፍላጎት ለማጣጣም እንዲቻል ከሲሚንቶ አምራቾች ጋር ዛሬ ጥቅምት 29 ቀን ባካሄዱት ውይይት ወቅት ነው።

የግብይት ሥርዓቱም ሙሉ በሙሉ ከካሽ ክፍያ ነጻ ሆኖ በዲጂታል ክፍያ ሥርዓት እንዲፈጸም አቅጣጫ መቀመጡንም አመላክተዋል።

አምራቾችም የሥራቸዉን የአፈጻጸም ሪፖርት ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እንዲያቀርቡ እንደሚገደዱ አና በማያቀርቡ በማናቸዉም የሲሚንቶ አምራች ላይ ግን መንግሥት የማያዳግም እርምጃ እንደሚወስድ ማሳሰቢያ መሰጠቱን ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

አመታዊው የስሚንቶ አቅርቦቱ ከ7 ሚሊዮን ቶን አለመዝለሉን ያስታወቁት ሚኒስትሩ አምራቾች በአቅርቦት በኩል ያለዉን ማነቆ ለመፍታት የማምረት አቅማቸዉን ወደ 80 በመቶ በማድረስ 20 ሚሊዮን ቶን ሀገራዊ የሲሚንቶ ምርት ዓመታዊ ፍላጎትን ለማሟላት በትኩረት እንዲሰሩ በአጽንኦት ማሳሰባቸውንም የሚኒስቴሩ መረጃ አካቷል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

08 Nov, 09:28


ኢንተርኔቱን ያጨናነቀው ሰውዬ

ከ400 ሴቶች ጋር አሸሼገዳሜ ሲል የከረመው ሰውዬ ከስጣኑ ተባሯል

ባልታሳር ኢባንግ ኢንጎንጋ የኢኳቶሪያል ጊኒ ብሄራዊ የፋይናንስ ምርመራ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተርነት ሀላፊነት መባረራቸውን እና በቦታው በዜኖን ኦቢያንግ መተካቱ ተገጿል።

ይህ ውሳኔ የተላለፈው ከ400 በላይ ሴቶች ጋር የነበረው ያልተገባ ግንኙነት በአለም መሰራጩትን ተከትሎ እንደሆነ የሀገሪቱ ሚዲያዎች እየዘገቡት ይገኛሉ ።

በሙስና ቅሌት ተጠርጥረው በእስር ቤት የሚገኘውን ገለሰብን በተመለከተ ትላንት ማምሻውን መግለጫ የሰጠው የሀገርቱ ፍርድቤት ፕሬዚደንት ግለሰቡ ከብዙ ሴቶች ጋር ለፈፀመው ግንኙነት ሴቶቹን አስገድደው ካላደረገ በቀር ምንም በወንጀል የሚጠየቅበት ድንጋጌ በወንጀል ህጋችን ውስጥ አልተካተተም  ማለቱ ተዘግቧል።ነገር ግን ህጋዊ ምስቱ በኔ ላይ ደርቦብኛል ብላ ከከሰሰች ቢቻ ሊጠየቅ ይችላል ያለው ፕሬዝዳንቱ ሚስቱም ይህንን ታደርጋለች የሚል እምነት አይኖረኝም ማለታቸውን የሀገርቱ ሚዲያዎች ይፋ አድርጎል።

የሰው ባለቤትም በማህበራዊ ሚዲያ የሚዘዋወረውን የባለቤቱዋ ቅሌት የሚያሳዩ የተወሰኑ ቪዲዮችን ከተመለከተች በኅላ እራሱዋን ስታ ሀኪም ቤት መግባቱዋም ተገልፆል ።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

08 Nov, 07:42


Capital Newspaper: ዩኒሊቨር ሰራተኞችን ሊቀንስ ነዉ | በተመሳሳይ ምርቶች እንዳትሸወዱ | የሰራተኞች ደ...
https://youtube.com/watch?v=vx5qfswOHkQ&si=YXxplWIPNYbDYF72

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

08 Nov, 04:33


“አሁን ላይ የሚጨምር እንጂ የሚቀንስ ነገር ፈጽሞ የለም። የምግብ ዋጋ ይጨምራል፤ የትራንስፖርት ታሪፍ ይጨምራል። ወርሃዊ ገቢያችን እዚያው ባለበት ሆኖ ኑሮ ውድነቱ ግን እያደር ብሶበታል” ያሉት ነዋሪዋ አሁን በቅርቡ ተግባራዊ መደረግ የጀመረው የትራንስፖርት ታሪፍ ጭማሪ ወትሮውንም የዕለት ተዕለት ወጪ ገቢያቸውን በጥንቃቄ አስልተው ለሚጠቀሙ ሁሉ “ዱብዳ” እንደሆነ ይገልጻሉ።

“የየዕለት ወጪዬ ተመዝግባለች። አውቃታለሁ። ከዚች ፈቀቅ ማለት አልችልም። አምስት ብር ባጎድል ያቺ እየተጠራቀመች ወር እስከ ወር ቀርቶ ደመወዝ በወጣ በአስራ አምስት ቀን ውስጥ እንቅስቃሴዬ ሁሉ ሊቆም ይችላል። ደመወዜ ባለበት ነው። ትራንስፖርት ታሪፍ ግን ጨምሯል። እኔ ደግሞ ከቱሉ ዲምቱ ጀምሮ እስከምሰራበት መሥሪያ ቤት ድረስ ቢያንስ በትንሹ ሁለት ታክሲ እይዛለሁ። በየጊዜው የሚደረገው የታሪፍ ጭማሪ ኑሮዬን አክብዶታል። ምኑን ከምኑ እንደማደርገው መላ ቅጡ ጠፍቶኝ ደንዝዤ ቁጭ ያልኩበት ሁኔታ ነው ያለው” ብለዋል።

የታክሲ ሾፌር የሆኑት አቶ ፈለቀ ጌታሁን በቅርቡ የተደረገው የታሪፍ ጭማሪ ለሾፌሮች ተመጣጣኝ ቢሆንም በህዝቡ ላይ ጫና እንደሚፈጥር ይገልጻሉ።

“እውነት ለመናገር ለእኛ ለሾፌሮች ተመጣጣኝ ነው አሁን። ህዝቡ ግን ያሳዝንሃል። በቃ ብዙ ግዜ ጭቅጭቅ ነው ተሳፋሪ ጋር። ጫናውን ለመቀነስ በመንግሥት በኩል ድጎማ ወይም በሌላም መንገድ ቢታሰብበት ጥሩ ይመስለኛል” ብለዋል።

ሌላ ስማቸውን እንዳንጠቅስ የጠየቁ አሽከርካሪ “ነዳጅ በሊትር 91 ብር ገብቷል። ያለው ብቸኛ አማራጭ በመንግሥት በኩል ድጎማ ማሳደግ ወይም ተሳፋሪው ላይ ታሪፍ መጨመር ነበረ። ያው ተሳፋሪው ላይ ታሪፍ ጨምሯል። እና ለሹፌሩ ቢበቃም ለህዝቡ ግን ከባድ ነው” ብለዋል።

አያይዘውም “ታሪፍ በአንዴ እስከ 10 ብር ድረስ ነው የጨመረው። ይሄ ያልተለመደ ነው። ከዚህ በፊት ነዳጅ ዋጋ ሲጨምር ታክሲ ታሪፍ ላይ 2 ብር 3 ብር ይጨምር ይሆናል እንጂ እንደዚህ አልነበረም። ሕዝቡ አለመደውም ይህንን። ተሳፋሪው ላይ ነው የዘረገፉት ዕዳውን እና ለአንተ ያው አንተም ስራ ስለሆነ የያዝከው የምትመራው ቤተሰብም ስለሚኖር ጭማሪው ለነዳጅ የምታወጣውን ወጪ ቢሸፍንልህም ተሳፋሪው ያሣዝንሃል። ወገንህ ነው እሱም። እና መንግሥት እዚህ ላይ ቢያስብበት ማለት እፈልጋለሁ።” ሲሉ ገልጸዋል።

የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትር አማካሪ የሆኑት አህመድ ቱሳ መስከረም 28 ቀን 2017 ዓ.ም የነዳጅ ዋጋ ጭማሪን አስመልክተው በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፤ የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ በገበያ ላይ ሊያስከትል የሚችለውን ተጽዕኖ ያገናዘበ መሆኑን ገልጸዋል።

በተጨማሪም መንግሥት ከፍ ያለውን ድጎማ የሚያደርግበት ለአንድ ዓመት የሚዘልቅ የተሟላ የነዳጅ ድጎማ ሥርዓት ተግባራዊ መደረጉን ተናግረዋል። በዚህም መሠረት በነጭ ናፍጣ ላይ 80 በመቶ ድጎማ እንዲሁም በቤንዚን ላይ 75 በመቶ ድጎማ የሚደረግ ይሆናል ማለታቸው ይታወሳል፡፡

በነዳጅ የችርቻሮ ዋጋ ላይ በሌትር እስከ ስምንት ብር የሚደርስ ጭማሪ ማድረጉን ተከትሎ በወቅቱ አስተያየታቸውን ለአዲስ ስታንዳርድ ያጋሩ ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ የማክሮ ኢኮኖሚ ባለሞያ፤ የተደረገው የነዳጅ ችርቻሮ ዋጋ ጭማሪ በሀገሪቱ በመታየት ላይ ያለውን አሳሳቢ የዋጋ ግሽበት በከፍተኛ ሁኔታ ሊያባብሰው ይችላል ሲሉ ስጋታቸውን ገልጸዋል።

“ከታሪክ እንዳየነው የነዳጅ የችርቻሮ ዋጋ ጭማሪ ከዋጋ ግሽበት ጋር እጅግ የተቆራኘ ነው” ሲሉ ጠቁመው “በቅርቡ በሀገሪቱ የተደረጉ የዋጋ ማሻሻያዎች በግሽበቱ ላይ ጫና ፈጥረው አልፈዋል” ሲሉ ገልጸዋል።

እንደ ማክሮ ኢኮኖሚስቱ ገለጻ፣ ነዳጅ ምግብ ነክ ባልሆኑ እቃዎች ላይ ከፍተኛ የዋጋ ለውጥ የሚያስከትል መሆኑን በየወሩ ይፋ ከሚደረገው “ወሳኝ የኢኮኖሚ ስታቲስቲክስ መረጃ መረዳት ይቻቻል ሲሉ አመላክተዋል።

“በሌሎች ሸቀጦች ላይ የሚኖረው ተዘዋዋሪ ተፅዕኖ ቀደም ሲል የነበረውን ከባድ የኑሮ ውድነት የበለጠ ሊያባብሰው ይችላል” ሲሉም አስጠንቅቀዋል።

ዘገባው የተዘጋጀው በአዲስ ስታንዳርድ ነው።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

06 Nov, 12:45


ወደ ብሄራዊ ባንክ ገቢ የተደረገው 400 ኪ.ግ ወርቅ የሚሸጥ ሳይሆን  በአደራ መልክ የሚቀመጥ ነው ተባለ

ጠቅላይ ሚኒስትር  አብይ አህመድ  በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት 3ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ በቤተመንግስቱ ዕድሳት ወቅት ተቆልፎበት የተቀመጠ 400 ኪሎ ግራም ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ አስገብተናል ማለታቸው የሚታወስ ነዉ፡፡

ወርቁ ብሄራዊ ባንክ እንዲቀመጥ የተደረገበት ምክንያት ለሽያጭ ሊቀርብ አሊያም ለሌላ ዓላማ የሚዉል ሳይሆን የሀገር ሀብት በመሆኑ  ለጥንቃቄ ሲባል ለብሄራዊ ባንክ ገቢ መደረጉን ያስታወቀው የቅርስ ጥናት እና ጥበቃ ባለስልጣን ነው፡፡

የባለስልጣኑ የብሄራዊ ሙዚየም መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ አንዷለም ግርማ፤ ኢትዮጵያ ቅርሶቿን ከማስጠበቅና  ለጥንት ታሪኮቻችን ቦታ ከመስጠት አንጻር ስራዎችን በመስራት ላይ ነን ብለዋል፡፡ አቶ አንዷለም አክለውም  የተገኘው ወርቅ ቅርስ እንደመሆኑ መጠን በቀጣይ ባሉት ጊዜያት በተለያየ መንገድ ለህዝቡ እይታ ክፍት የሚሆንበት ሁኔታ እንደሚመቻች ገልጸዋል፡፡
                                      
ወደ ብሄራዊ ባንክ የተላከዉ  ወርቅ በኢትዮጵያ የንጉሳዊ ስርዓት ወቅት ለበርካታ መቶ አመታት ነገስታት ሲገለገሉባቸው የነበሩ በወርቅ እና በሌሎች የከበሩ ማዕድናት የተሰሩ ቁሳቁሶች እንዲሁም ከሌሎች ሀገራት በስጦታ የተሰጡና በተጨማሪም በነገስታቱ ታዘው የተሰሩ እና የተገዙ ናቸው ተብሏል፡፡

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

06 Nov, 12:41


በኢኳቶሪያል ጊኒ ከታዋቂ ሴቶች ጋር ሲፈፅም የነበረውን ወሲብ፤ በቪዲዮ ካሴቶች ያከማቸው ባለስልጣን

የኢኳቶሪያል ጊኒ የፋይናንስ ምርመራ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ባልታሳር ኢንጎንጋ ከታዋቂ ሴቶች እና የባለስልጣናት ዘመዶች ጋር ከቢሮ እና በተለያዩ ቦታዎች ወሲብ ሲፈፅም የሚያሳዩ ቪዲዎች አከማችቶ ተገኝቷል።

ቪዲዮው የሀገሪቱን ፕሬዝዳንት እህት ጨምሮ የታዋቂ ሰዎችን የወሲብ ህይወት የሚያሳይ ነው የተባለ ሲሆን ከ400 በላይ የወሲብ ካሴቶችን በባለስልጣኑ ቢሮ እና መኖሪያ ተገኝቷል ተብሏል።

ድርጊቱ የተጋለጠው የ54 አመቱ ኢንጎንጋ በተጠረጠረበት የማጭበርበር ወንጀሎች ላይ ተመስርቶ በተደረገ ፍተሻ ነው።

በዚህም ባለስልጣኑ በቤቱ እና በቢሮው ውስጥ ወሲባዊ ግንኙነቶችን በቢሮው እና በተለያዩ ቦታዎች ሲፈፅም የሚያሳዩ ቪዲዮዎች በማህበራዊ ትስስር ገጾች ተሰራጭተዋል።

በቪዲዮ ቅጂው ከታዩት ውስጥ የፕሬዝዳንት ቴዎዶሮ ኦቢያንግ ንጉማ ምባሶጎ ​​እህት፤ የከፍተኛ ባለስልጣናት የትዳር አጋሮች ጨምሮ የቅርብ የቤተሰብ አባላት እና ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ዘመዶች እንደሚገኙ አፍሪካ ኒውስ ዘግቧል።

ሮይተርስ በበኩሉ በቪዲዎቹ ላይ የሚታዩትን ባለስልጣናት እና ትክክልኝነት ማረጋገጥ እንዳልቻለ ገልጿል።

የቪዲዮ ቅጂዎቹ በማህበራዊ ትስስር ገጾች ከወጡ በኃላ ከፍተኛ የህዝብ ቁጣ በመቀስቀስ የብዙሃን መገናኛዎችን ቀልብ ስቧል።

የአገሪቱ ምክትል ፕሬዝደንት ቴዎዶሮ ኦቢያንግ ማንጉ ማንኛውም ሰራተኛ በስራ ቦታ የወሲብ ድርጊት ሲፈጽም ከተገኙ “የሥነ ምግባር ደንቡን በመጣስ” እንደሚታገድ ገልፀዋል።

እኚህን መሰል ድርጊቶች ለመከላከልም የክትትል ካሜራዎችን በፍርድ ቤት እና በሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች እንዲገጠሙ አዘዋል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

06 Nov, 12:39


በሥራ ቦታቸው ወሲባዊ ግንኙነት ሲፈጽሙ የሚያዙ የመንግሥት ሠራተኞች “ከባድ እርምጃ” እንደሚጠብቃቸው የኢኳቶሪያል ጊኒ ምክትል ፕሬዝዳንት አስጠነቀቁ።

ይህ የምክትል ፕሬዝዳንቱ ማስጠንቀቂያ የተሰጠው በመቶዎች የሚቆጠሩ የወሲብ ቪዲዮዎች በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ከተሰራጩ በኋላ ነው።

ቪዲዮዎቹ ከፍተኛ የመንግሥት ባለስልጣን የሆነውን ባልታዛር ኢባንግ ኢንጎንጋ የከፍተኛ ባለሥልጣናት ሚስቶችን ጨምሮ ከተለያዩ ሴቶች ጋር በቢሮው ውስጥ ወሲብ ሲፈጽም የሚያሳዩ ናቸው ተብሏል።

ኢንጎንጋ የአገሪቱ ብሔራዊ የፋይናንስ ምርመራ ኤጀንሲ ኃላፊ እና የአገሪቱ ፕሬዝዳንት ዘመድ መሆናቸው ተነግሯል።

በጉዳዩ ላይ የተከሰሱት ባለሥልጣን አስተያየት እንዲሰጥ ቢቢሲ ጥያቄ አቀርቧል።

ኢንጎንጋ በፌስቡክ ገጹ ላይ የእሱን የአንዲት ሴትን እና የልጆችን ፎቶ በመለጠፍ “ቤተሰብ ሁሉም ነገር ነው” የሚል ጽሁፍ አስፍሯል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

06 Nov, 08:59


ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለዶናልድ ትራምፕ የእንኳን ደስ አለህ መልዕክት አስተላለፉ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በኤክስ ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት “በእርስዎ የስልጣን ዘመን የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት የበለጠ ለማጠናከር በጋራ እንሰራለን” ሲሉ አስፍረዋል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

06 Nov, 07:00


ሰበር ዜና!!

ዶናልድ ጆን ትራምፕ 47ተኛው የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ሆነው መመረጣቸውን ፎክስ ዘግቧል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

06 Nov, 05:33


የዶላንድ ትራምፑ ፓርቲ ሪፐብሊካኖች የዩኤስ ሴኔት አብላጫ ድምፅን አሸንፈው ከ4 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ  ምክር ቤቱን መቆጣጠራቸውን ሲል አሶሼትድ ፕሬስ ዘግቧል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

05 Nov, 16:31


የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአፍሪካ በአይነቱ የመጀመሪያው ነው የተባለውን ኤይርባስ A350-1000 የተሰኘውን አዲስ አውሮፕላን ተረክቧል፡፡

አየር መንገዱ በፈረንሳይ ቱሉስ በተከናወነው ስነስርዓት ከአውሮፕላን አምራቹ ኤርባስ ኩባንያ የተረከበውን የመጀመሪያውን አውሮፕላን ዛሬ በአዲስ አበባ ቦሌ ዓለማቀፍ አየር ፣ማረፊያ አስተዋውቋል፡፡

አቪየሽን ሳንስ ፊሮንተርስ ከኤርባስ ጋር በመሆን ለኢትዮጵያ አየርመንገዶች ፋውንዴሽን የተበረከተውን በ100 ሺህ ዩሮ የሚገመት የህክምና ቁሳቁስ ተሸክሞ በአየርመንገዱ ባለስልጣናት ከሰዓቱን አዲስ አበባ የደረሰው አውሮፕላኑ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት እና ዲፕሎማቶች በተገኙበት በደማቅ ስነስርዓት አቀባበል ተደርጎለታል፡፡

በአውሮፕላኑ አቀባበል ስነስርዓት ወቅት ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው ዛሬ አየር መንገዱ የተቀበለው ኤይርባስ A350-1000 አውሮፕላን አየር መንገዱ ካዘዘው አራት አውሮፕላኖች አንዱ ነው፡፡

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

05 Nov, 08:05


ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የውጭ ብድር ሰጠች!

በአለም አዲስ አገር ለሆነችው ደቡብ ሱዳን የተሰጠው ብድር በሁለቱ አገራት መካከል አገናኝ ለሚሆን መንገድ ግንባታ የሚውል ነው።የአራት አመት እፎይታ ኖሮት በ10 አመታት ተከፍሎ የሚጠናቀቀው ብድር ከ738 ሚሊየን ዶላር በላይ ነው።

በደቡብ ሱዳን ድንበር ውስጥ የሚገነባው 220 ኪሜ መንገድ በኢትዮጵያ ተቋራጮች እና አማካሪዎች እንዲከናወን በሁለቱ አገራት ከስምምነት መደረሱ ተገልጿል።የብድር አመላለሱም በካሽ እና በድፍድፍ ነዳጅ እንደሚሆን ነው የተጠቀሰው።

Via Capital

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

04 Nov, 16:25


ሰበር .. ቤተመንግሥት የተደበቀው 400 ኪ/ግ ወርቅ ሚስጥር 😲 | ነገስታቶችን ያስወቀሰዉ ጉዳይ | እዉነታዉ ምን...
https://youtube.com/watch?v=auBVBrJWu_g&si=eA85_REy6galxjCP

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

04 Nov, 14:12


የREMEDIALፕሮግራም ምደባ ይፋ ሆነ።

በ2016 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስደው ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች የREMEDIAL ፕሮግራም ለመከታተል የሚያስችል ማለፊያ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች የተቋም ምደባ ይፋ ተደርጓል።

ከአሁን ሰዓት ጀምሮ ተማሪዎች ምደባቸውን ፦
➡️ በዌብሳይት : https://placement.ethernet.edu.et 
➡️ በቴሌግራም : https://t.me/moestudentbot ላይ መመልከት እንደሚችሉ ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።

ተማሪዎች ተቋማት በሚያስተላልፉት ጥሪ  መሰረት የREMEDIAL ፕሮግራሙን እንዲከታተሉ ተብሏል።

ትምህርት ሚኒስቴር የተቋም ይቀየርልኝ ጥያቄ የማያስተናግድ መሆኑን ገልጿል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

28 Oct, 15:38


በርካታ ነዳጅ የሚጠቀሙ ቅንጡ እና ውድ መኪናዎች ወደ ሀገር ውስጥ እየገቡ እንደሆነ ታወቀ

በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገቡ በታገደበት በአሁኑ ወቅት በርካታ ነዳጅ የሚጠቀሙ ቅንጡ እና ውድ መኪናዎች ወደ ሀገር ውስጥ እየገቡ እንደሆነ ተነግሯል ።

ታድያ ከሁሉም በላይ መነጋገርያ የሆነው በታዋቂው የንግድ ሰው አቶ ሻቃ ጉርሜሳ ወደ ሀገር ውስጥ ሊገቡ ፕሮሰስ ላይ የሚገኙት 700 ይደርሳሉ የተባሉት V8 መኪናዎች ጉዳይ ነው። 

የ Shaka Mall ባለቤት የሆኑት አቶ ሻቃ መኪና በማስመጣት እና በመሸጥ ከበርካታ አመታት በፊት ጀምሮ ልምድ ያላቸው ቢሆኑም በዚህ ወቅት በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን በብዛት ማስገባት መቻላቸው ለብዙዎች እንቆቅልሽ እንደሆነ ሰምተናል።

በቅርቡ 700 V8 ላንድ ክሩዘር መኪናዎችን ሊያስገቡ ሂደት ላይ እንደሆኑ የታወቀ ሲሆን ከእነዚህ ውስጥ ከ40 በላይ የሚሆኑት በአዲስ አበባ የኮሪደር ልማት ላይ ጥሩ የአመራር ብቃት ላሳዩ የመንግስት ተሿሚዎች በስጦታ መልክ የሚበረከቱ መሆናቸው ተሰምቷል።

"መድሃኒት ፈልጎ ማግኘት ከባድ በሆነበት፣ ብታገኝም ዋጋው በማይቀመስበት አገር እንዲህ አይነት የሃብት ብክነት እየተፈፀመ ይገኛል" ያሉት አንድ ጉዳዩን የሚያውቁ የመረጃ ምንጫችን ናቸው።

የመንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችን የተሽከርካሪ አጠቃቀም አስመልክቶ የሚኒስትሮች ምክር ቤት የዛሬ ስድስት አመት ያወጣው መመሪያ በበርካታ ተቋማት እየተተገበረ አለመሆኑ ተደጋግሞ እየተነሳ ይገኛል።

በመመሪያው ቁጥር 4 ንዑስ ቁጥር 1 ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች ወጪ ቆጣቢና ውጤታማ የፋይናንስ አጠቃቀም እንዲኖር ለከተማ ውስጥ ስራ አውቶሞቢል ተሽከርካሪዎችን እንዲጠቀሙ ተደንግጓል።

በዚህ መሰረት የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች ቪ8፣ ቪ9፣ ፕራዶና ፓጃሮ ተሽከርካሪዎችን ከሚጠቀሙ ይልቅ አውቶሞቢል ተሽከርካሪዎችን ቢጠቀሙ ከፍተኛ ወጪ በመቀነስ ውጤታማ አገልግሎት መስጠት እንደሚቻል ተገልፆ ነበር።

ይሁንና አሁን ድረስ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች ቪ8 እና ሌሎች ተመሳሳይ መኪናዎችን ከተማዎች ውስጥ እንደሚጠቀሙ መ መዘገቡ ይታወሳል።
መሰረት ሚዲያ

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

28 Oct, 15:37


በጀርመን የወፏ ቤት እንዳይፈርስ ተደረገ

በጀርመኗ ቲዩቢንገን ከተማ በሚገኝ የዩኒቨርሲቲ ክሊንክ ጣሪያ ላይ አንዲት ወፍ ጎጆዋን ቀልሳ መኖር ከጀመረች ከራርማለች። ይህች ወፍ እንደሌሎች ዝርያቸው በመጥፋት አደጋ ላይ ከሚገኙ የወፍ ዓይነቶች አንዷ ናት። የዩኒቨርሲቲ ክሊኒኩ የሕንጻ ማስፋፋት ሥራ ለማከናወን በተሰናዳበት አጋጣሚ በጣሪያው ጎጆዋን ቀልሳ የምትኖረውን ወፍ ይደርሱባታል። ክሊኒኩም በማስፋፋት ፕሮጀክቱ መቀጠሉን ይገታል። 250 ሚሊየን ዩሮ የሚያወጣው ፕሮጀክትም ለዘጠኝ ዓመታት ባለበት ቆመ። በአካባቢው የሚገኘው ደን ጥበቃውም ቀጠለ፤ ወፏም ያለ ስጋት በጣሪያው ላይ ትኖር ጀመር። የወፎን ሁኔታ በቅርብ የሚከታተሉ ባለሙያዎች ታዲያ ድንገት ወፏ ትሰወርባቸዋለች።

ዘሯ ሊጠፋ ነው የተባለላት ወፍ አለመኖር ግን ወዲያው የታቀደውን የሕንጻ ማስፋፋት ፕሮጀክት መጀመር አላስቻለም። በጥንቃቄና በትዕግሥት ወፏ ወደ ቀለሰችው ጎጆዋ ትመለስ ይሆናል በሚል ተጠበቀች። ጉዳዩ የግዛቷ ፖለቲከኞችና ምክር ቤት መነጋገሪያ ሆነ። ድመት በልቷት ይሁን ወይም አካባቢውን ለቃ ባልታወቀ ምክንያት የወፏ ከጎርጎሪዮሳዊው 2022 ጀምሮ አለመታየት በደስታ የማስፋፋት ሥራውን ለመጀመር አላጣደፈም። ይልቁንም የለመደችው አካባቢ ነውና ተመልሳ ብትመጣ ጎጆዋ ከፈረሰ የት ትገባለች የሚል ክርክር አስነሳ።

የከተማዋ ከንቲባ ወፏ አሁን እኛ ሳናባርራት ቦታውን ስለለቀች ሥራው መቀጠል ይችላል ቢሉም የጀርመን የተፈጥሮ ጥበቃ ሕግ ባለሙያዎች ግን አንቀጽ እየጠቀሱ ሞገቱ። የአእዋፍ ጥናት ባለሙያዎችም በዚህ እየተሳተፉ ነው።

ይህች ወፍ ፈጣሪ አድሏት ጀርመን ሀገር በመኖሯ ጎጆዋ ሳይፈርስ የዩኒቨርሲቲ ክሊኒኩን የማስፋፊያ ፕሮጀክት አጓተተ። ግንባታውን ለማድረግ በአካባቢው ከሚገኘው ደን የተወሰነው ይወገዳል መባሉም ሌላ ሙግት አስነስቷል። በጀርመን ወፍም መብት አላት። DW

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

28 Oct, 13:53


‹‹በዘፈቀደ የሚሰጡ ሹመቶች ከባድ ቅጣትን ያስከትላሉ›› የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር

ከጊዚያዊ አስተዳደሩ ፍቃድና እውቅና ውጪ የሚደረጉ ሹምሽሮች እስከ በጀት መገደብ የሚደርስ ቅጣት ሊጣል ይችላል ሲል በጌታቸው ረዳ የሚመራው ጊዚያዊ አስተዳደር አስጠንቅቋል፡፡

ጊዚያዊ አስተዳደሩ በአቶ ጌታቸው ረዳ ፊርማ ተፈርሞ ባሰራጨው መመሪያ ፤ " የጊዚያዊ አስተዳደሩን እቅዶች ማደናቀፍ እና በዘፈቀደ ህጋዊ ያልሆነ ሹመት መስጠትና መንሳት የበጀት ቅጣትና የህግ ተጠያቂነት ያስከትላል " ሲል ነው ማስጠንቀቂያ የሰጠው።

መንግስታዊ ስልጣን እና ሃላፊነት የሌለው ' ቡድን ' በማለት የተጠቀሰው በዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል የሚመራው ህወሓት የሚሰጠው ሹመት የመሻርና ሹመት የመስጠት ተግባር ፍፁም ተቀባይነት የለውም " ብሏል።

በመሆኑም ቡድኑ የሚያካሄዳቸውን ህጋዊ ያልሆኑ ተግባራት እንዲቆም ይህንን የጊዚያዊ መንግስቱ መመሪያ በመቀበል ፍርድ ቤት ጨምሮ የዞን እና የወረዳ የመንግስት መዋቅሮች ህጋዊ አሰራር እንዲከተሉና ህግ በሚጥስ ላይ ህጋዊ እርምጃ እንዲወስዱ እንዲሁም በክልሉ በየመዋቅሩ ያሉ ምክር ቤቶች ጊዚያቸው ያለፈ እና ህጋዊ መሰረታቸው ያበቃ መሆኑን በመቀበል ሹመት ከመስጠትና ከመሻር እንዲቆጠቡ ሲል ነው ያሳሰበው፡፡

ላለፉት ወራት የዘለቀው የህወሃት አመራሮች ፍትጊያ አሁንም እንደቀጠለ ሲሆን እኔ ብቻ ነኝ እውቅና ያለኝ የሚለው የሁለቱ ቡድኖች መካረርም ምንም አይነት መፍትሄ አላገኘም፡፡

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

28 Oct, 12:37


ማንቼስተር ዩናይትድ አሰልጣኝ ኤሪክ ቴን ሃግን አሰናበተ

#Ethiopia | የማንቼስተር ዩናይትድ ዋና አሰልጣኝ ኤሪክ ቴን ሃግ ከኃላፊነታቸው ተሰናበቱ፡፡

በቀያይ ሰይጣኖቹ ቤት አሰልጣኝ ቴን ሃግ ስኬታማ ጉዞ እያደረጉ አይደለም በሚል ትችት ሲሠነዘርባቸው ቆይቷል፡፡

ቀያይ ሰይጣኖቹ ትናንት ባደረጉት የፕሪሚየር ሊጉ ዘጠነኛ ሣምንት ጨዋታ በዌስት ሃም 2 ለ 1 መሸነፋቸው ይታወሳል፡፡

በክለቡ ቀደም ሲል በተጫዋችነት ከዚያም በምክትል አሰልጣኝነት ሲያገለግል የቆየው ሆላንዳዊው ሩድ ቫን ኒስተልሮይ በጊዜያዊነት ማንቼስተር ዩናይትድን በዋና አሰልጣኝነት እንዲመራ ኃላፊነት ተሰጥቶታል፡፡

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

28 Oct, 10:54


በኢትዮጵያ በቂ የኮንዶም አቅርቦት እና ስርጭት እንደሌለ ተገለጸ

በኢትዮጵያ በየዓመቱ ከ21 ሺህ በላይ አዳዲስ ሰዎች በኤች አይ ቪ ኤድስ እንደሚያዙና 26 ሺህ ሰዎች ኤች አይ ቪን ጨምሮ ተያያዥ በሆኑ የጤና እክሎች እንደሚሞቱ ጥናቶች ያመላክታሉ፡፡

ከሁለት አመት በፊት በተከሰተው የኮንዶም እጥረት ምክንያት በአንዳንድ የክልል ከተሞች ምርቱ በውድ ዋጋ ሲሸጥ እንደነበርም ተገልጿል፡፡

በኢትዮጵያ በሃገር አቀፍ ደረጃ ከ250 ሚሊዮን በላይ የኮንዶም አቅርቦት እና ስርጭት እንደሚያስፈልግ በኤም ኤስ አይ ሪፕሮዳክቲቭ ቾይዝ ካንትሪ ዳይሬክተር ዶ/ር አበበ ሽብሩ ገልጸዋል፡፡ አሁን ያለው ስርጭት ከ50 በመቶ በታች እንደሆነም አስታውቀዋል፡፡

የአቅርቦት እጥረቱ በተለያዩ ክልሎች የኤች አይቪ ኤድስ ስርጭት በከፍተኛ ሁኔታ እንዲጨምር እና እንዲስፋፋ አድርጎታልም ነው ያሉት፡፡

ዶ/ር አበበ አክለውም፤ አቅርቦት እና ፍላጎት ባለመመጣጠኑ ምክንያት በክልሎች እና በሃገሪቱ የገጠር ክፍል በተጋነነ ዋጋ እንዲሸጥ እንዳደረገው ተናግረዋል፡፡ በተለይም የኤች.አይ.ቪ ኤድስ ስርጭት ከፍተኛ በሆኑባቸው አካባቢዎች እጥረቱ እና የዋጋ ውድነቱ እንደሚስተዋል አመላክተዋል፡፡

በዚህም ኤም ኤስ አይ ኢትዮጵያ ከአጋር ድርጅቶች ጋር በመሆን በማህበራዊ ግብይት አማካኝነት በሁሉም የሃገሪቱ ክፍሎች ለማዳረስ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

በኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2022 እና በ2023 በተሠራው አገራዊ የኤች.አይ.ቪ ሥርጭት ግምታዊ የዳሰሳ ጥናት 8ሺ 257 ሰዎች በኤች.አይ.ቪ መያዛቸው መገለጹ ይታወቃል፡፡

(መናኸሪያ ሬዲዮ)

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

27 Oct, 11:10


አትሌት ዮሚፍ ቀጀልቻ የዓለም የግማሽ ማራቶን ክብረ ወሰንን ሰበረ

አትሌት ዮሚፍ ቀጀልቻ በቫሌንሺያ ሜዲዮ በተካሄደው የግማሽ ማራቶን ውድድር የዓለም ክብረወሰንን በመስበር ጭምር አሸነፈ፡፡

አትሌቱ ርቀቱን ያጠናቀቀው 57 ደቂቃ ከ30 ሰከንድ በመግባት መሆኑን የዓለም አትሌቲክስ መረጃ አመላክቷል፡፡

የዓለም የግማሽ ማራቶን ክብረወሰን በዑጋንዳዊው አትሌት ጃኮብ ኪፕሊሞ ተይዞ መቆየቱ ይታወቃል፡፡

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

27 Oct, 11:10


የኢትዮጵያ ሕዝብ 76 በመቶው የሞባይል ኢንተርኔት እንደማይጠቀም ተገለፀ

ከኢትዮጵያ ሕዝብ 76% ኔትወርክ ባለበት አካባቢ ቢኖርም አሁንም የሞባይል ኢንተርኔት እንደማይጠቀም የግሎባል ሲስተም ፎር ሞባይል ኮምዩንኬሽንስ ማኅበር ጥናት ይፋ አደረገ።

የኢትዮ-ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ በበኩላቸው ክፈቱትን ለመቀነስ መሠረተ-ልማት ማስፋፋትን ጨምሮ የተለያዩ ጥረቶች እየተደረጉ መሆኑን አስረድተዋል።

ምንጭ : _ ዶቼቬሌ

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

27 Oct, 10:23


የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ከአማራ ክልል ጋር የሚወዛገብባቸውን ግዛቶች የሚመለከት መመሪያ አፀደቀ

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ካቢኔ አዲስ በማኅበራት የሚገነቡ ቤቶችን በሚመለከት ባዘጋጀው መመሪያ፣ ክልሉ በአሁን ወቅት ከአማራ ክልል ጋር የሚወዛገብባቸውን ግዛቶችን የተመለከቱ አንቀጾችን አካቶ ማፅደቁ ታወቀ።

የጊዜያዊ አስተዳደሩ ካቢኔ መስከረም 3 ቀን 2017 ዓ.ም. ያፀደቀውና በፕሬዚዳንቱ አቶ ጌታቸው ረዳ ተፈርሞ ሥራ ላይ የዋለው በትግራይ ክልል የሚገነቡ የማኅበር ቤቶችን የሚመለከተው መመሪያ፣ ከጦርነቱ አንስቶ እስካሁን ድረስ በኤርትራ ኃይሎች ተይዘው የሚገኙ እንዲሁም፣ ክልሉ ከአማራ ክልላዊ መንግሥት ጋር እየተወዛገበባቸው የሚገኙና በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት መሠረት መፍትሔ ያገኛሉ የሚላቸው ግዛቶች ላይ መከተል የሚያስፈልጉ አሠራሮችንም የሚያብራራ አንቀጽም ይዟል።

የመመሪያው ክፍል አራት ‹በትግራይ በኅብረት ሥራ ማኅበራት የሚሠሩ ቤቶች› በሚል ሥር የተካተቱ ተከታታይ አራት አንቀጾች፣ ከተሞችን በአራት ክፍል በመመደብ ከቪላ ቤት እስከ አራት ወለል ሕንፃ የሚደርሱ የግንባታ ዓይነቶች በኅብረት ሥራ ማኅበራት ተፈጻሚ ስለሚሆኑበት ያስረዳል።

አምስተኛው አንቀጽ በትንንሽ ከተሞች የሚገነቡ የሕንፃ ዓይነቶችን ደረጃና የግንባታ ሁኔታ የተመለከተ ሆኖም ተደንግጓል።

በዚህም መሠረት በመመሪያው አንቀጽ 12፣ ከ80 ካሬ ሜትር እስከ 132 ካሬ ሜትር ስፋት ባለው መሬት ላይ ባለ አራት ወለል ሕንፃ ግንባታ እንደሚካሄድባቸው የሚገልጽ ሲሆን፣ የተጠቀሱት ከተሞች መቀሌ፣ ዓዲግራት፣ አክሱም፣ ሽረ እንዳ ሥላሴ፣ ዓብይ ዓዲ፣ ዓድዋ፣ ኮረም፣ ውቅሮና አላማጣ ናቸው።

በተከታዩ አንቀጽ ለንግድ አገልግሎት የሚሰጡ ተጨማሪ ወለሎችን መገንባት የሚፈልጉ ማኅበራት፣ ግንባታውን መፈጸም የሚያስችል የገቢ ምንጭ እንዳላቸው ለሚመለከተው አካል ማረጋገጫ ማቅረብ እንደሚኖርባቸው በመጥቀስ፣ ባለ ሦስት ወለል ሕንፃ ግንባታ የሚካሄድባቸው ከተሞች ሁመራና ሽራሮ እንደሆኑ ተጠቅሷል።

በአንቀጽ 14 ሥር ባለአንድ ወለል ሕንፃ እንደሚገነቡና ተጨማሪ የንግድ ወለል ከፈለጉ ከላይ ከተጠቀሰው አንቀጽ ጋር ተመሳሳይ አካሄድ እንደሚከተሉ አብራርቶ፣ በመመሪያው ላይ የተጠቀሱት ከተሞች ደግሞ ማይካድራ፣ ዳንሻ፣ ማይፀብሪ፣ ቆራሪትና ማይጋባ መሆናቸውን ገልጿል፡፡

የከተሞችን ዝርዝር ካስቀመጡት አንቀፆች የመጨረሻው ከቀደመው ጋር በተመሳሳይ፣ በማኅበራት ባለአንድ ሕንፃ ወለል እንደሚገነቡ የሚጠቅስ ሲሆን፣ የተካተቱትም እንትጮ፣ ዕዳጋ ዓርቢ፣ ፍረ ወይኒ፣ መኾኒ፣ ዕዳጋ ሓሙስ፣ እንዳባጉና፣ ሀገረ ሰላም፣ ሓውዜን፣ ዛላንበሳ፣ እንዳስላሰ ኣጽቢ፣ ራማ፣ ዓዲ ዳዕሮና ዓዲ ጉደም ናቸው።

መመሪያው ማኅበራቱ በመረጡት ተቋራጭ ቤቶቹን ማስገንባት እንደሚችሉ ሲጠቅስ፣ የግንባታ ወጪ ግምት ግን በየከተማ አስተዳደሮቹ የሚወሰን እንደሆነ ይገልጻል። የከተማ አስተዳደሩ የግንባታ ዲዛይን ለማኅበራቱ እንደሚያቀርብ፣ ነገር ግን ማኅበራቱ የራሳቸውን ዲዛይን የመጠቀም ፍላጎት ካላቸው ለሚገኙበት ከተማ አስተዳደር በማቅረብ ማፀደቅ እንደሚችሉም ተጠቅሷል።

ለግንባታ በቅድሚያ የሊዝ ቁጥር እንደሚያስፈልግ፣ በተጨማሪም የሚመለከተው የከተማ አስተዳደሩ ተቋም በማኅበሩ ስም ዕዳ አለመኖሩን ማረጋገጥ እንደሚኖርበት ተገልጿል።

የትግራይ የመሬትና ማዕድን ቢሮ በመመሪያው ወሳኝ ሠልጣኖች የተሰጡት ሲሆን፣ እነዚህም ለማኅበራቱ የማልሚያ ቦታ የመስጠት፣ የማኅበር ምዝገባ ፈቃድ የመስጠት፣ ማኅበራት ለግንባታ ከሚያስፈልጋቸው ገንዘብ 15 በመቶውን በዝግ የባንክ ሒሳብ ማስቀመጣቸውን ማረጋገጥና እነዚህን መሠረት በማድረግ ለተጠቃሚዎች መሬት በዕጣና በሊዝ ማስተላለፍ ናቸው።

ምንም እንኳን መመሪያው የፀደቀው በመስከረም ወር 2017 ዓ.ም. ቢሆንም ጉዳዩ ይመለከታቸዋል የተባሉት ማኅበራት ግን ከጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም. በፊት የተመዘገቡና ገንዘብ ሲቆጥቡ የቆዩትን ብቻ እንደሆነ፣ እንዲሁም የአዲስ ማኅበራት ምዝገባም በጊዜያዊነት እንዲቆም መደረጉ ታውቋል፡፡
Via Ethiopian Reporter

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

26 Oct, 16:16


የባንክ ሰራተኞች ዝቅተኛ የብድር ወለድ ቀርቶ ህዝቡ በሚጠቀምበት ምጣኔ እንዲሆን ሊወሰን ነው

በኢትዮጵያ ባንኮች ውስጥ የሚሰሩ ሰራተኞች አዲስ ሊወጣ በተዘጋጀ መመርያ መሰረት ከዚህ በኋላ እንደማንኛውም ደንበኛ 15 ፐርሰንት ሆኖ በሚሰላ ወለድ የብድር ተጠቃሚ ሊሆኑ መደረግ መሆኑን ለመሠረት ሚድያ የደረሰው መረጃ ያሳያል።

የባንክ ሰራተኞች እንደ አንድ ከፍተኛ ጥቅም የሚያዩት ይህን ጥቅማ ጥቅም ቢሆንም አሁን ላይ የገንዘብ ሚኒስቴር ያዘጋጀው ይህ መመርያ ይህን ጥቅማቸው ሊነጥቃቸው መሆኑ ተሰምቷል።

በዚህ ዙርያ ቅሬታቸውን ያደረሱን በርካታ የባንክ ሰራተኞች በአሁን ሰአት ያለው የኑሮ ውድነት ተጨምሮበት ይህ መመርያ ወደባሰ ድህነት እንደሚከታቸው ተናግረዋል።

"የባንክ ሰራተኛ ትልቁ ጥቅሙ ብድር ነበር፣ አሁን ግን አዲስ የወለድ ተመን ክፈሉ የሚል ህግ ሊወጣብን ነው፣ ይህም በተገልጋይ ልክ ማለትም 15 ፐርሰንት ታስቦ የሚሰላ ይሆናል" ያለ አንድ የባንክ ባለሙያ በዚህ ምክንያት አብዛኛው ሰው ቤቱን ለመሸጥ እያሰበ መሆኑን ጠቁሟል።

ባንኮች ከዚህ በፊት ከ7 እስከ 7.5 ፐርሰንት በሚደርስ የብድር ምጣኔ ለሰራተኞቻቸው የቤት፣ የመኪና ወዘተ ግዢ ሲያመቻቹ ቆይተዋል።

ይህ ጥቅማ ጥቅም በርካታ የባንክ ሰራተኞች ስራቸው ላይ ረዘም ላለ ግዜ እንዲቆዩ ማበረታቻ ሆኖ መቆየቱ የሚታወቅ ሲሆን ከዚህ በኋላ ግን በዘርፉ ላይ የመቆየታቸው እድል አነስተኛ መሆኑን ተናግረዋል።

"ብቸኛው ማትጊያ ሆኖ ብዙዎቻችንን የያዘን ይህ የብድር አቅርቦት ነበር፣ ከዚህ በኋላ መክፈል የሚችል ከፍሎ፣ ያልቻለ ንብረቱን ሸጦ ዞር እንደሚል ግምቴ ነው" ያለው ሌላኛው የባንክ ባለሙያ መንግስት የህብረተሰቡ የመግዛት አቅም እጅግ በተዳከመበት በዚህ ወቅት ለምን ተደጋጋሚ ጫና እንደሚያደርግ እንቆቅልሽ እንደሆነበት ተናግሯል።

ኢትዮጵያ በቅርቡ ከአለም አቀፍ አበዳሪ ተቋማት በርካታ ገንዘብ በብድር ባገኘችበት ወቅት ለብድሩ አንድ ቅድመ ሁኔታ ሆኖ የተቀመጠው የታክስ ምጣኔን በእጅጉ ማሳደግ እና የመንግስትን ገንዘብ የመሰብሰብ አቅም ማሳደግ ነበር።

ይሁንና አስተያየት ሰጪዎች መንግስት ብድሩን ለማግኘት ከአበዳሪዎች ጋር ያደረገው ስምምነት በቀጥታ እየጎዳ ያለው ህዝቡን መሆኑን በመግለፅ ምሬታቸውን ገልፀዋል።
Mesret media

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

26 Oct, 12:03


ደመመዝ እንዲከፈላቸው ፊርማ ያሰባሰቡ የ #ዎላይታ ዞን መምህራን ለእስር ተዳረጉ

በ #ደቡብ_ኢትዮጵያ ክልል ዎላይታ ዞን ደመወዝ እንዲከፈላቸው ፊርማ በማሰባሰብ ላይ የነበሩ መምህራን ለእስር መዳረጋቸውን የታሳሪ ቤተሰቦች ገለፁ።

እስሩ የተፈጸመው መምህራኑ ከደመወዝ ጥያቄ ጋር በተያያዘ ፊርማ በማሰባሰብ ለኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አቤቱታቸውን ለማስገባት በሚንቀሳቀሱበት ወቅት መሆኑ ተገልጿል።

ፖሊስ መምህራኑ "አመፅ ለመቀስቀስ ተንቀሳቅሰዋል" እንዲሁም "የዞኑን ገጽታ አጥፍተዋል" በሚል ማሰሩን የታሳሪ ቤተሰቦች ገልፀዋል።

"ፖሊሶች ወደ ቤት ሲመጡ ምንም አይነት የፍርድ ቤት መያዣ ወረቀት አላሳዩም" ያሉት የመምህራኑ ቤተሰቦች አክለውም መምህራኑ ደሞዝ ይሰጠን ብለው የዳቦ ጥያቄ በማንሳታቸው ብቻ ታሰረውብናል ሲሉ ገልጸዋል።

እንዲሁም አንድ የዳሞት ወይዴ ወረዳ መምህር በበኩላቸው የፊርማ ማሰባሰብ ስራውን ሲያስተባብሩ ከነበሩት መካከል ሶስት በቅርብ የሚያውቋቸው መምህራን ለእስር መዳረጋቸውን ገልጸው፤ ከመታሰራቸው በፊት "እረፉ" የሚል ማስጠንቀቂያ ከወረዳው ባለሥልጣናት ተሰጥቷቸው እንደነበረ ገልጸዋል።

የዎላይታ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ግንባር ዎህዴግ ሊቀመንበር የሆኑት አቶ ጎበዜ ጎኣ በበኩላቸው መምህራኑ ያነሱት የደመወዝ ጥያቄ ተገቢ መሆኑን ጠቅሰው፤ "ደመወዝ የጠየቀን አመፅ ቀስቀሰሃል ብሎ ማሰር ከሥነምግባር ውጭ የሆነ ድርጊት ነው" ብለዋል። DW

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

26 Oct, 10:37


"ህወሓት ከሦስት ወራት በኃላ ጉባኤ አዘጋጅቶ እንዲጠራን እንጠብቃለን" ምርጫ ቦርድ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ነሐሴ 3/2016 ዓ.ም. በቁጥር አ1162/11/15180 ለህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) በጻፈው ደብዳቤ ፖርቲው በልዩ ሁኔታ በመመዝገብ የህጋዊ ሰውነት ማረጋገጫ ምስክር ወረቀትም መስጠቱ ይታወሳል፡፡

በመሆኑም ሰርተፍኬቱ ከሰጠበት ቀን ጀምሮ ታሳቢ በማድረግ በቀጣይ ሦስት ወራት ለጉባኤ እንዲጠሩን እንጠብቃለን ሲሉ የቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ዉብሸት አየለ ተናግረዋል።

ሰርተፍኬቱ ሁለት መሰረታዊ ሃላፊነት ህወሓት ላይ ይጥላል ያሉት አቶ ውብሸት፤ የመጀመሪያው በ6 ወራት ውስጥ ጉባኤ እንዲያደርጉ መሆኑን ተናግረዋል። ጉባኤ ከማድረጋቸው ቀደም ብሎ ከ21 ቀን በፊት ለቦርዱ ማሳወቅም ይገባቸው ነበር ብለዋል።

ጉባኤ አድርገው አመራሮቻቸውን የምርጫ ቦርድ ታዛቢዎች ባሉበት መመርጥ ይጠበቅባቸው ነበር ሲሉም ነግረውናል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ጠቅላላ ጉባዔውን ሊያደርግ መሆኑን በመገናኛ ብዙኃን መነገሩን ተከትሎ፤ ቦርዱ ለፓርቲው የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ ጽፎ እንደነበር መዘገቡ ይታወሳል፡፡

ህወሓት የቦርዱን ማሳሰቢያ ወደ ጎን በመተው ጉባኤውን ካደረገ፣ ለጉባኤው እና በጉባኤ ለሚተላለፉ ውሳኔዎች እውቅና እንደማይሰጥ ቦርዱ አሳስቦ ነበር፡፡

ነገር ግን ህወሓት የምርጫ ቦርድን ማሳሰቢያ ወደ ጎን በመተው 14ኛ ጠቅላላ ጉባኤውን አካሂዷል፡፡

ከዚህም ጉባዔው ማብቂያ ላይ የድርጅቱን ምክትል ሊቀመንበር እና የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳር ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ረዳን ጨምሮ 17 የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ከስልጣን ማንሳቱን ማስታወቁ ይታወሳል፡፡

አሁን ላይ የቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ዉብሸት፤ "ህወሓት የዕውቅና ሰርተፍኬቱን ካገኘበት ቀን ጀምሮ ታሳቢ በማድረግ በቀጣይ ሦስት ወራት ውስጥ አስፈላጊ ቅድመ ሁኔታዎችን አሟልቶ ለጉባኤ እንዲጠራን እንጠብቃለን" ሲሉ ነው የተናገሩት፡፡

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

25 Oct, 19:58


"ልማት የሰውን ልጅ ሲያፈርስ በዓይኔ አየሁት" በማለት አርቲስት አዜብ ወርቁ ታሪካቸውን የፃፈችላቸው የእድሜ ባለፀጋ ህይወታቸው አለፈ

"ልማት የሰውን ልጅ ሲያፈርስ በዓይኔ አየሁት" በማለት አርቲስት አዜብ ወርቁ ታሪካቸውን የፃፈችላቸው የእድሜ ባለፀጋ ህይወታቸው ማለፉ ታወቀ።

መስከረም 4 ቀን አርቲስት አዜብ የልማት ተነሺ ተብለው ሰዎች ድንገት ቤታቸው ሲፈርስ ስለገጠማቸው ጉዳት ለማሳየት ታሪካቸውን ያጋራችላቸው ግለሰብ ታሪክ እንዲህ ይነበባል:

"ገና ጎረምሳ እያለ ከተወለደበት ገጠር ወጥቶ 250 ኪሎሜትር በእግሩ ተጉዞ አዲስ አበባ ገባ። አዲስ አበባ የግለሰቦች ንግድ ቤት ተቀጥሮ ከጽዳት አንስቶ የተለያዩ ስራዎችን ሰርቶ ከራሱ አልፎ  ወላጆቹን ቤተሰቡን ረድቶ፣ ትዳር መስርቶ፣ ልጆች አፍርቶ፣ የግል ንግድ ከፍቶ ሲኖር ቆይቶ የዛሬ 60 ዓመት አካባቢ ከፈረንሳይ ኢምባሲ ወረድ ብሎ ከሃይዌዩ ድልድይ ስር የግንብ ግድግዳ ላይ “ስንኖር ኢትዮጵያዊ ስንሞት ኢትዮጵያ” የሚለው ጽሁፍ በደማቁ በቀይ ቀለም ከተጻፈበት ፊትለፊት ወደ ቤላ በሚወስደው ቀኝ መታጠፊያ መንገድ ላይ መሬት ገዝቶ ቆንጆ ቤት ሰርቶ ኑሮውን መሰረተ።

12 ልጆችን አሳድጎ፣ አስተምሮ ለወግ ለመዓረግ አበቃ፣  የልጅ ልጅ አየ። አሁን የ 94 ዓመት አዛውንት ነው። ጠንካራ፣ ደግ፣ ሰራተኛ፣ ተጫዋች፣ ቀልድ አዋቂ፣ ሰው ሁሉ የሚወደው፣ ሰውን ሁሉ የሚወድ፣ ሃይማኖቱን አክባሪ እምነቱን አጥባቂ ነው። የግቢ አትክልት ይወዳል፣ ግቢው በወይን፣ በአቩካዶ፣ በኮክ፣ በአፕል፣ በቡና ዛፍ የተሞላ የሚያምር ግቢ ነው። የአትክልት ፍቅሩ ለራሱ ቤት ብቻም አይደለም፤ ሰፈር ውስጥ እየዞረ በሰው ቤት በዘመድ ቤትም ችግኝ  ከቤቱ እየወሰደ ይተክላል።

ይህ ጠንካራ ሰው በቅርቡ በህመም አልጋ ላይ ዋለ ፥ “በቂ ኖሬያለሁ ሆስፒታል እንዳትወስዱኝ በኖርኩበት ባረጀሁበት ቤት አስከሬኔ ይውጣ” አለ። ልጆቹ ቃሉን አከበሩለት ቤቱ ውስጥ እንዳለ ሀኪም እያየው በልጆቹ፣ በልጅ ልጆቹ  በቤተዘመድ በጎረቤት ተከቦ እንዲያስታመሙት አደረጉ። ጳጉሜ 5 ቀን 2016 ዓ.ም የ አዲስ ዓመት ዋዜማ በሰፈሩ አንድ ዜና ተሰማ፣ ከወረዳ የመጡ ሰዎች እየዞሩ ለልማት እየመዘገቡ ነው የሚል። የአዲስ ዓመት በዓል ማግስት መስከረም 2 መጥተው በ20 ቀን ውስጥ ቤታችሁ ለልማት ሊፈርስ ስለሆነ ለመስከረም 3 ጠዋት ለስበሰባ ኑ የሚል መልእክት በቃል ብቻ ተነገረ።

እንዲህ ያለ ዱብ እዳ ሲሰማ ለህግ ጉዳይ መዋሉ ቢቀር እንኳን ህልም ይሆን እንዴ ብሎ ድጋሚ አይቶ ለማረጋገጥ የሚያስችል ብጣቂ ወረቀት አልተሰጠም፣ ልክ እንደ ክፉ መርዶ ነጋሪ በር አንኳኩተው በቃል ትዕዛዝ ሰጥተው ሄዱ።

መስከረም 3 በስብሰባው ላይ ስልክም ሆነ ማንኛውም ድምጽ እና ምስል መቅጃ ይዞ መግባት ባልተፈቀደበት ስብሰባ ላይ ለተሰብሳቢዎቹ  ቤታችሁ ለልማት ይፈርሳል የሚለው መርዶ ተነገራቸው። ለምን? ለጫካ ፕሮጀክት ልማት። መቼ? እስከ መስከረም 20። ተሰብሳቢው ደነገጠ “ልጆቻችንን ትምህርት ቤት አስመዝገበናል፣ ዩኒፎርም አሰፍተናል፣ የደከመ ታማሚ  ቤታችን ስላለ ጊዜው አይበቃንም፣ የእለት ጉርሴ ከቤት ኪራይ የማገኘው ብቻ ነው፣ ምን ልሁን? የሚሉ አዛውንቶች፣ እናቶች፣ አባቶች፣ ጮኸው አልቅሰው ተናገሩ። ሁለት ሳምንት አላችሁ ተባሉ። ይህ ቤተሰብ የመራ፣ ሀገር ያቀና፣ ስንቱን ያስተማረ፣ የዳረ፣ አስታሞ በክብር የቀበረ፣ የተጣላን አስታራቂ የሐገር ሽማግሌ፣ አልጋ የያዘ መንቀሳቀስ፣ መንቃት የማይችል፣ ፈጣሪው ጋ እስኪሄድ ቀኑን የሚጠብቅ አረጋዊ እስከ መስከረም 20 ይነሳ ቤቱ ይፈርሳል ተባለ።"

አርቲስት አዜብ ወርቁ በዚህ መልኩ ታሪካቸውን ካጋራች በኋላ ለእስር ተዳርጋ ነበር።

አሁን ላይ መሠረት ሚድያ በደረሰው መረጃ እኚህ ግለሰብ ቤታቸው ይነሳል በተባለበት እለት፣ ማለትም መስከረም 20 ቀን ህይወታቸው አልፏል።

የአካባቢው ነዋሪዎች የሰጡን መረጃ እንደሚጠቁመው የእድሜ ባለፀጋው ግለሰብ ቤታቸው ከመፍረሱ በፊት እንደ ምኞታቸውም አስከሬናቸው ከመኖሪያ ቤታቸው ተሸኝቷል፣ ቤተሰቦቻቸውም፣ ጎረቤት፣ እድሩም ሀዘናቸውን በመኖሪያ ቤታቸው በተገቢው ሁኔታ አስተናግደዋል።
Meseret Media

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

25 Oct, 19:57


'ሴት ባክ' የተባለው አነጋጋሪ የግንባታ መመርያ ከኮሪደር ልማት ውጪ ባሉ ዋና ዋና መንገዶች እና በንዑስ ዋና መንገዶች ላይ ጭምር ተግባራዊ ይደረጋል ተባለ

መሠረት ሚድያ ከሶስት ሳምንት በፊት ባወጣው አንድ ዘገባው በዚህ መመርያ መሰረት ህንፃዎች ከመንገድ መራቅ ያለባቸው ርቀት (ወይም set back)፣ የመሬት ስፋት እና ዝቅተኛው ገደብ እና የህንፃ የጎን ስፋት (ወይም frontage) መወሰኑን ዘግቦ ነበር።

በወቅቱ በሰራነው ዘገባችን በሴት ባክ ህጉ መሰረት ከ15 ሜትር እና በላይ ስፋት ያላቸው መንገዶች የሚያዋስኗቸው ይዞታዎች ዝቅተኛው የቦታ ስፋት ሴት ባክ ከተቀነሰ በኋላ ቢያንስ 500 ሜትር ካሬ መሆን እንዳለበት መደንገጉን ገልፀን ነበር።

በተጨማሪም በነዚህ መንገዶች ላይ ዝቅተኛው የህንፃ የጎን ስፋት ከ20 ሜትር ያላነሰ መሆን እንዳለት ህጉ እንደሚጠቅስ መረጃ አቅርበን በዚህም ምክንያት በርካታ የህንፃ ኮንስትራክሽን ስራዎች ከተማው ውስጥ እንደቆሙ ጠቁመን ነበር።

ይህ መስከረም 3 ቀን በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የግንባታ ፈቃድ እና ቁጥጥር ባለሳጣን የወጣ የአተገባበር መመርያ ለአስራ አንዱም ክ/ከተሞች ተልኮ የነበረ ቢሆንም አሁን ደግሞ አዲስ ማሻሻያ እንደተደረገበት ሰምተናል።

በዚህም መሰረት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፕላን እና ልማት ቢሮ አዲስ በፃፈው ደብዳቤ የኮሪደር ልማቱ ለ5 አመት የተያዘ እቅድ መሆኑን በመግለፅ ከ15 ሜትር እና በላይ ስፋት ያላቸው መንገዶች የሚያዋስኗቸው ይዞታዎች ዝቅተኛው የቦታ ስፋት ሴት ባክ ከተቀነሰ በኋላ ቢያንስ 500 ሜትር ካሬ መሆን እንዳለበት የሚደነግገው መመርያ ከኮሪደር ልማት ውጪ ባሉ ዋና ዋና መንገዶች እና በንዑስ ዋና መንገዶች ላይ ለሚገኙ ይዞታዎች ጭምር የሚመለከታቸው መሆኑን ገልጿል።

በተጨማሪም ከኮሪደር ውጪ ከሰብሳቢ መንገድ እና ከውስጥ ለውስጥ መንገዶች ጋር የሚዋሰኑ ይዞታዎች ግንባታቸውን በተመለከተ የተሻሻለውን የሴት ባክ ህግ መጠበቅ እንዳለባቸው ጠቅሶ 500 ካሬ ሜትር አነስተኛ የይዞታ ስፋት ውሳኔ እና 20 ሜትር የመንገድ ፊት ለፊት ገፅታ አስገዳጅ የማይሆን መሆኑን አብራርቷል።

Meseret Media

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

25 Oct, 18:52


አንጋፋው የእግር ኳስ ሰው አሥራት ኃይሌ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ
**

በኢትዮጵያ እግር ኳስ ታሪክ በተጫዋችነት እና በአሰልጣኝነት ለረጅም ጊዜ በማገልገል ግዙፍ አሻራቸውን ያሳረፉት አንጋፋው የእግር ኳስ ሰው አሥራት ኃይሌ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።

አሥራት ኃይሌ በተጫዋችነት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን፣ በጥጥ ማህበር እና በቅዱስ ጊዮርጊስ አገልግለዋል።

በአሰልጣኝነትም በተለያዩ ጊዜያት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን እና የሀገሪቱን ክለቦች በመምራት የሴካፋ ድልን ጨምሮ የተለያዩ ስኬቶችን ማስመዝገብ የቻሉ ናቸው።

ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ውስጥ የቆዩት አሥራት ኃይሌ ባደረባቸው ሕመም በሕክምና ሲረዱ ቆይተው ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸውን ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

25 Oct, 16:04


የይቅርታና ምኅረት ቦርድ 257 ታራሚዎች በይቅርታ እንዲወጡ የውሳኔ ሐሳብ መስጠቱን አስታወቀ፡፡

በፍትሕ ሚኒስቴር የይቅርታና ምኅረት ቦርድ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ተወካይ ዐቃቤ ሕግ ወይኒ ገብረሚካኤል በሰጡት ማብራሪያ ከይቅርታና አመክሮ አፈፃፀም ጋር በተያያዘና የይቅርታ ቦርዱ የውሳኔ ሐሳብ የመስጠትና የማፀደቅ ሥራን አስመልክተው የተከናወኑ ተግባራትን አብራርተዋል፡፡

በሰጡት ማብራሪያም ቦርዱ ከፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን እና ከክልል ፍትሕ ቢሮዎች ወይም ጠቅላይ ዐቃቤ ሕጎች የቀረቡ የይቅርታ ጥያቄ የውሳኔ ሐሳብ የተሰጠባቸውን 402 የፌዴራል ታራሚዎች የይቅርታ ጥያቄ መመርመሩን ገልጸዋል፡፡

ከምርመራው በኋላም 257 ታራሚዎች በይቅርታ እንዲወጡ የውሳኔ ሐሳብ በማሳለፍ በኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ፀድቆ ተፈፃሚ ሆኗል ማለታቸውን የፍትሕ ሚኒስቴር መረጃ አመላክቷል፡፡

እንዲሁም ቦርዱ የ89 ታራሚዎች የይቅርታ ጥያቄ ውድቅ ማድረጉን እና 51 ታራሚዎች ደግሞ በቦርዱ ትዕዛዝ የተሰጠባቸው መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

25 Oct, 16:04


የሕንፃ ሥር የተሽከርካሪ ማቆሚያ ስፍራዎችን ለሌላ አገልግሎት ባዋሉት ላይ እርምጃ ይወሰዳል ተባለ

የሕንፃ ሥር የተሽከርካሪ ማቆሚያ ስፍራዎችን ለሌላ አገልግሎት ባዋሉት ላይ እርምጃ  እንደሚወሰድ የአዲስ አበባ ከተማ የትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን አስታውቋል።

ባለስልጣኑ የተሸከርካሪ ማቆሚያ ስፍራዎችን ማስተዳደር የሚያስችለውን ደንብ ቁጥር 165/2016 ከተማ አስተዳደሩ ማጽደቁ ይታወሳል።

የባለሥልጣኑ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ አማረ ታረቀኝ በከተማው በህንጻዎች ስር የተገነቡ የመኪና መቆሚያ ስፍራዎች አብዛኞቹ ለታለመላቸው ዓላማ እየዋሉ አለመሆኑ ተናግረዋል።

ችግሩን ለመፍታት የህንጻ ባለንብረቶች፣ በዘርፉ ተሰማርተው የመኪና ማቆሚያ ያላቸውን ሰዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላትን ግንዛቤ የማስጨበጥና ችግሩ እንዲቃለል ሰፊ ስራ ሲሰራ መቆየቱን አንስተዋል።

ነገር ግን ችግሩ በግንዛቤ ማስጨበጥ ብቻ የሚመለስ ባለመሆኑ ተቋሙ በቅርቡ በተሰጠው ስልጣን መሰረት ህጋዊ እርምጃ መውሰድ እንደሚጀምር መናገራቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

25 Oct, 09:52


"  ከ2017 የትምህርት ዘመን ጀምሮ የሪሚዲያል ተማሪዎች የማጠቃለያ ምዘና ከ100% የሚሰጠው ከማዕከል ነው " - ትምህርት ሚኒስቴር

ትምህርት ሚኒስቴር በአቅም ማካካሻ (Remedial) ፕሮግራም ውጤት አያያዝ ላይ ማሻሻያ አደረገ፡፡

ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ ከ50 በመቶ በታች ውጤት ካገኙ የ12ኛ ክፍል የመልቀቂያ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎች መካከል የተሻለ ውጤት ያላቸውን በመምረጥ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማካካሻ (Remedial) ፕሮግራም ተመድበው የማካካሻ ትምህርት እንዲከታተሉ መደረጉ ይታወቃል።

በዚህ መሠረት ተማሪዎቹ 70% በማዕከል እና 30% በተቋማት የሚዘጋጁ ምዘናዎችን ተፈትነው ሲያልፉ የፍሬሽማን ፕሮግራም ተማሪዎች ሆነው እንዲቀጥሉ እየተደረገ ይገኛል።

ይሁን እንጂ ከ30% በተቋማት የሚሰጠው ውጤት አሰጣጥ ላይ ወጥነት የሌለ መሆኑን የትምህርት ሚኒስትሩ ለሁሉም የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች እና የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በፃፉት ሰርኩላር ገልፀዋል፡፡

በዚህም ዘንድሮ / ከ2017 የትምህርት ዘመን ጀምሮ የሪሚዲያል ተማሪዎች የማጠቃለያ ምዘና ፈተና ከ100% የሚሰጠው ከማዕከል እንዲሆን ተወስኗል፡፡

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

24 Oct, 13:01


#MoE

የ2017 ዓ.ም የዩኒቨርሲቲ ምደባ ይፋ ሆነ።

በ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስደው በመደበኛው ፕሮግራም ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግሥት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን ለመከታተል የሚያስችል የማለፊያ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች የተቋም ምደባ ይፋ ሆኗል።

ተማሪዎች ከታች በተዘረዘሩት አማራጮች ምደባቸውን ማየት እንደሚችሉ ትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል።

በድረ-ገፅ 👇
https://placement.ethernet.edu.et
በቴሌግራም 👇
https://t.me/moestudentbot

የተቋም ይቀየርልኝ ጥያቄ የማያስተናግድ መሆኑን ሚኒስቴሩ አሳውቋል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

23 Oct, 16:14


ጎግል የተሰረቁ ሞባይል ቀፎዎች ዳግም እንዳይሰሩ የሚያደርግ ፈጠራ መተግበሩን ገለጸ

የስልክ ንጥቂያ ወንጀል ኢትዮጵያን ጨምሮ በበርካታ ሀገራት እየተስፋፋ ያለ ወንጀል ነው፡፡ የብሪታንያ መዲና በሆነችው ለንደን ይህ ወንጀል አሳሳቢ ሆኗል፡፡ የለንደን ከንቲባ ሳዲቅ ካሃን በከተማቸው የተስፋፋውን የስልቅ ነጥቆ መሮጥ ወንጀል ለመቀነስ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች ለዚህ እና መሰል ወንጀሎች ለመከላከል መፍትሔ እንዲፈልጉ ጥሪ አቅርበውም ነበር፡፡

ጎግል ለዚህ ወንጀል መልስ በሚል በሰው ሰራሽ አስተውሎት የታገዘ ቴክኖሎጂ ይፋ ማድረጉን አስታውቋል፡፡ ይህ ቴክኖሎጂ ሰዎች ስልካቸውን በስርቆት ሲያጡ ለስልክ ቀፎ አምራች ድርጅት ወዲያውኑ ማመልከት የሚችሉበትን ስርዓት ዘርግቷል ተብሏል፡፡ ከዚህ በፊት ሰዎች ስልካቸውን ሲሰረቁ ቀፎው እንዳይሰራ ለማድረግ ማዘጋት የሚችሉት የይለፍ ቃላቸውን ካስታወሱ ብቻ ነበር የተባለ ሲሆን አሁን ግን ስልክ ቁጥራቸውን መናገር ከቻሉ የተሰረቀው ስልክ እንዳይሰራ ማድረግ የሚያስችል እንደሆነ ቢቢሲ በቴክኖሎጂ አምዱ ዘግቧል፡፡

እንደ ዘገባው ከሆነ ሌቦች የስልክ ቀፎን ከወሰዱ በኋላ ለመደበቅ ቢሞክሩ እና ዳግም ጥቅም ላይ ለማዋል ሲሞክሩ ኤአይን በመጠቀም ለዘለቄታው ከአገልግሎት ውጪ እንዲሆን የሚያደርግም ነው፡፡ለአንድሮይድ ስልክ የተገጠመለት ኤአይ ቴክኖሎጂ ቀፎው ላይ በተገጠመለት ሴንሰር አማካኝነት እንዳይከፈት አድርጎ መዝጋት ይችላልም ተብሏል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም ስልካቸውን የተሰረቁ ሰዎች የጠፋባቸውን መረጃዎች ወደ ሶስተኛ አካል ከመተላለፋቸው በፊት ያለምንም መቆራረጥ ዳም መልሰው እንዲያገኙ እንደሚያደርግ ተገልጿል፡፡

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

23 Oct, 16:13


መሳይ ተፈሪ የኢትዮጵያ ብሔራዊ በድን ጊዜያዊ ዋና አሰልጣኝ ሆነ!

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በአፍሪካ ሀገራት ዋንጫ (ቻን) ማጣርያ የሚያደርጋቸው ጨዋታዎችን በአሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ ጊዜያዊ ዋና አሰልጣኝነት እየተመራ እንዲያከናውን መወሰኑን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታወቀ፡፡

አሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ ላለፉት 12 ወራት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ምክትል አሰልጣኝ ሆነው ሲሰሩ ቆይተዋል፡፡የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከኤርትራ ጋር የሚያከናውናቸውን ጨዋታዎች ጨምሮ የቻን ማጣርያን በጊዜያዊ ዋና አሰልጣኝነት የሚመሩ መሆኑን ከፌዴሬሽኑ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

መሳይ ተፈሪ በክለብ ደረጃ ወላይታ ድቻን ከምስረታው ጀምሮ በፕሪምየር ሊግ ተሳታፊ እንዲሆንና በ8 ዓመት ቆይታው በ2009 የኢትዮጵያ ዋንጫን በማሳካት በአፍሪካ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ እንዲሳተፍ አስችሏል፡፡አርባ ምንጭ ከተማን በዋና አሰልጣኝነት በመምራት በ2015 ዳግም ወደ ኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ እንዲመለስም አድርጓል፡፡

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

23 Oct, 16:13


ብሊንከን የሃማስ መሪ ከተገደሉ በኋላ ታጋቾቹን ለማስለቀቅ "እውነተኛ ዕድል ይኖራል" አሉ!

የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንተኒ ብሊንከን፣ እስራኤል የሃማሱን መሪ ያህያ ሲንዋርን መግደሏ አሁንም ጋዛ ውስጥ በታጣቂው ቡድን እጅ ያሉትን ቀሪዎቹን ታጋቾች የሚያስለቅቅ ስምምነት ላይ ለመድረስ እውነተኛ እድል ማምጣቱን ተናገሩ።ብሊንክን ይህን የተናገሩት፣ ዛሬ ረቡዕ ከቴል አቪቭ ወደ ሳኡዲ አረብያ ከመብረራቸው በፊት ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ነው።

"እስራኤል ሃማስ ላይ በምታካሂደው ጦርነት ወታደራዊ ዓቅሙን ማዳከም ጨምሮ ብዙ ስኬት አግኝታለች" ያሉት ብሊንከን "የቀረው ታጋቾቹን ማስለቀቅ እና ጦርነቱን ማጠናቀቅ ነው" ብለዋል።ጦርነቱ ሃማስን ከጋዛ በሚያስወጣ እና የእስራኤል ወታደሮችም እዚያ እንዳይቆዩ በሚያደርግ መንገድ መጠናቀቅ እንዳለበትም ብሊንክን አሳስበዋል።

ከጦርነቱ በኋላ ለጋዛ የሚኖረው እቅድ አስተዳደር፣ ደህንነት፣ መልሶ ግንባታ፣ እንዲሁም ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ፍልስጤማውያንን ለመርዳት ማድረግ የሚችለውን ጨምሮ በሚቀጥሉት ቀናት ከአረብ አገሮች ጋራ የሚወያዩበት ርዕስ እንደሚሆን ብሊንከን ተናግረዋል፡፡ብሊንከን ነገ ሐሙስ ወደካታር ይሄዱ እና አርብ በለንደን ከአረብ ሀገራት አቻዎቻቸው ጋራ እንደሚገናኙ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።

ብሊንከን እና የመከላከያ ሚኒስትሩ ሎይድ ኦስተን እስራኤል ወደጋዛ የሚገባውንን የሰብአዊ ርዳታ መጠን እንድትጨምር፣ አለዚያ የአሜሪካን ወታደራዊ ርዳታ እንደምታጣ የሚያስጠነቅቅ ደብዳቤ ከላኩ አንድ ሳምንት በኋላ ሁኔታዎች መሻሻል ቢያሳዩም ብዙ እንደሚቀረውና ቀጣይነት እንደሚያስፈልገው የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ትላንት ረቡዕ በሰጡት መግለጫቸው ተናግረዋል፡፡

አምና የሰጡትን ተመሳሳይ ማስጠንቀቂያ ተከትሎ እስራኤል ወዲያውኑ የሰብአዊ ርዳታ አቅርቦቱ መጠን እንዲጨምር ብታደርግም እንዳልቀጠለ ብሊንከን አውስተዋል። አዲሱ ማስጠንቀቂያ "ባዶ ማስፈራሪያ" ይሆን እንደሆን የተጠየቁት የውጭ ጉዳይ ሚንስትሩ " በሕጉ መሠረት ለመሥራት ቁርጠኛ ነኝ" ብለዋል፡፡

ብሊንከን ከአንድ ዓመት በፊት ከተቀሰቀሰው የእስራኤል እና የሃማስ ጦርነት ወዲህ ባደረጉት 11ኛ ጉብኘታቸው ከእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ እና ሌሎች ባለሥልጣናት ጋራ ትላንት ማክሰኞ ተገናኝተው ተወያይተዋል።የሃማሱ መሪ ሲንዋርን ግድያ ተከትሎ ዩናትይትድ ስቴትስ ወደ አካባቢው ተመልሳ የተኩስ አቁም ጥረቱን እንድትገፋበት መልካም አጋጣሚ የተከፈተላት መሆኑ ተመልክቷል፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ የእስራኤል ኅይሎች ዛሬ ረቡዕ የሊባኖስ ደቡባዊ የወደብ ከተማ ታይር ላይ የአየር ጥቃት አካሂደዋል፡፡ ጥቃቱን ያደረሱት ነዋሪዎች ከተማዋን ለቅቀው እንዲወጡ ትዕዛዝ ከሰጡ ከሰዓታት በኋላ መሆኑ ተጠቁሟል፡፡ ሌሊቱን ቤይሩት ውስጥ ያሉ ከሄዝቦላህ ጋር ግንኙነት ያላቸውን አካባቢዎች ደብድበናል ስትል እስራኤል አስታውቃለች፡፡ዛሬ ረቡዕ ቤይሩትን የጎበኙት የጀርመን የውጭ ጉዳይ ሚንስትር አናሌና ቤርቦክ ለሊባኖሱ ጦርነት ዲፕሎማሲያዊ መፍትሄ እንዲፈለግ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

Via VoA

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

23 Oct, 16:12


በጦርነት ምክንያት ሥራ ያቆሙ መምህራንን ማዘዋወር ካልተቻለ ወደ ሥራቸው እስኪመለሱ ባሉበት ደመወዛቸው እንዲከፈላቸው የኢትዮጵያ መምህራን ማኅበር ጠየቀ፡፡

"መምህራን የኑሮ ውድነት በከፍተኛ መጠን እየፈተናቸው እንደሚገኙ፣ የረዥም ጊዜ አገልግሎት ያላቸው መምህራን የደረጃ ዕድገት ወይም ዕርከን እያገኙ አለመሆናቸው፣ በአንዳንድ ክልሎች የመምህራን ደመወዝ በጊዜ አለመከፈልና በፐርሰንት መቆራረጥ፣ ያለ መምህራን ፈቃድ በተለያዩ ምክንያቶች የደመወዝ መቆረጥና ይህንን ድርጊት የሚቃወሙትን ደግሞ ማዋከብና ማንገላታት እንዳለ" 37ኛ መደበኛ ጉባኤውን በቅርቡ ያካሔደው ማኅበሩ አሳውቋል፡፡

በተጨማሪም ከዓመታት በፊት የተጀመረው የመምህራን የመኖሪያ ቤትና የመሥሪያ ቦታ በሚፈለገው ፍጥነት እየተከናወነ አለመሆኑን፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መምህራን ደግሞ ጭራሽ አለመጀመሩን፣ በትርፍ ሰዓት ክፍያ ላይ ተደራራቢ ግብር መቆረጥ፣ የመጻሕፍትና ሌሎች ግብዓቶች እጥረት፣ የክረምት መምህራን ሥልጠናና ያጋጠሙ ችግሮች ማኅበሩ ባወጣው መግለጫ ተዳሰዋል፡፡

"መምህራን ክፍል ውስጥ ገብተው ማስተማር ባልቻሉበት ወቅት፣ አላሰተማሩም ተብሎ ደመወዛቸው ሊቆረጥባቸው አይገባም" ሲሉ የማኅበሩ ፕሬዝዳንት ዮሐንስ በንቲ (ዶ/ር) ለሪፖርተር ተናግረዋል።

ከወራት በፊት የ18 ወራት ውዝፍ ደመወዝ ስላልተከፈላቸው ለችግር መጋለጣቸውን የትግራይ ክልል መምህራን መጠየቃቸው ይታወሳል፡፡ በዚህም በቅርቡ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የአምስት ወራት ደመወዝ ለመምህራኑ እንደሚከፍል ቢናገርም፣ የቀሪው የአንድ ዓመት ውዝፍ ክፍያ ግን አሁንም መፍትሔ እንደሚፈልግ የማኅበሩ ፕሬዝዳንት ገልፀዋል፡፡

በጦርነት ምክንያት ሥራ ያቆሙ መምህራንን ማዘዋወር ካልተቻለ ወደ ሥራቸው እስኪመለሱ ባሉበት ደመወዛቸው እንዲከፈላቸው የጠየቁት የማኅበሩ ፕሬዝዳንት፤ መንግሥትም ሆነ ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት የመምህራኑን ችግር ሊረዱና መፍትሔ ሊሰጡት ይገባል ብለዋል፡፡

ከትግራይ ክልል በስተቀር በሌሎች ክልሎች እስከ ሦስት ወራት ደመወዝ ያልተለከፈላቸው በተለይም በቀድሞው ደቡብ ክልል ውስጥ የነበሩ ትምህርት ተቋማትም እንደሚገኙ የገለጹት ፕሬዝዳንቱ፤ በአማራ ክልል በሚካሄደው ጦርነት ደመወዝ ያልተከፈላቸውና ሥራ ያቆሙ መምህራን መረጃ ተጠናቅሮ አልደረሰም ብለዋል። #ሪፖርተር

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

23 Oct, 12:14


Capital News: አዲስ ነገር በሰራተኞች ደመወዝ ጉዳይ | የገንዘብ ሚኒስትር አነጋጋሪ ምላሽ | ጠ/ሚሩ አዲስ...
https://youtube.com/watch?v=_MWUf1zIK9M&si=C4LiaMg2cv1CmSSC

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

23 Oct, 08:05


የሞሪንጋ (ሽፈራው) ተክል በሕጻነት ላይ የሚከሰተውን የመቀንጨር ችግር እንደሚከላከል በጥናት መረጋገጡ ተገለጸ!

በኢትዮጵያ 'ሽፈራው' እየተባለ የሚጠራው የሞሪንጋ ተክል በሕጻነት ላይ የሚከሰተውን የመቀንጨር ችግር እንደሚከላከል በጥናት መረጋገጡ ተገልጿል፡፡ጥናት እና ምርምሩ ተግባራዊ እንዲሆን የጣሊያን መንግሥት፣ የተባበሩት መንግሥታት የኢንዲስትሪ ልማት ድርጅት እንዲሁም የአርባ ምንጭ ዩንቨርስቲ በጋራ የሰሩትን ፕሮጀክት ይፋ አድርገዋል፡፡

በአርባ ምንጭ ዩንቨርስቲ በምግብ ቴክኖሎጂና ባዮቴክኖሎጂ ተባባሪ ፕሮፌሰር አዲሱ ፍቃዱ፤ የሞሪንጋ ወይም የሽፈራው ተክል በሕጻነት ላይ የሚከሰተውን የመቀንጨር ችግር ጨምሮ ብዙ የጤና ጠቀሜታ እንዳለው በጥናት እና ምርምር መረጋገጡን ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡

በተክሉ ውስጥ የተለያዩ ንጥረ ነገሮች የሚገኝበት በመሆኑ ከሌሎች ምግቦች ጋር በመቀላቀል በመጠቀም እንደሚቻል አንስተው፤ የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፍ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡ ምርቶችንም ማስቀረት እንደሚችል ጠቁመዋል፡፡

ፕሮጀክቱ በዋናነት ተግባራዊ የተደረገው ተክሉ በስፋት የሚበቅልበት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አርባ ምንጭ ከተማ ዘይሴ ቀበሌ ሲሆን፤ የክልሉ ርዕሰ መስተዳደር አቶ ገብረመስቀል ጫላ ከተክሉ የተለያዩ ምርቶች እንደሚገኝበት እና ዘርፍ ብዙ ጠቀሜዎች እንዳሉት ተናግረዋል፡፡

በተገኘው ጥናት እና ምርምር መሰረት፤ ተክሉ በብዙ መልኩ የሚቀነባበርበት የፋብሪካ ግንባታ ተጠቀናቆ የተለያዩ ማሽኖችም መግባታቻውን አሐዱ ማረጋገጥ ችሏል፡፡የተጀመረው ፕሮጀክት ተግባራዊ እንዲሆን ያሉትን የመሰረተ ልማት ችግር ለመቅረፍ ምን እየተሰራ ነው? ሲል አሐዱ ለክልሉ ርዕሰ መስተዳደር ላነሳው ጥያቄም፤ የመንገድ እና የኤሌትሪክ አገልግሎት ችግሮች እንደሚፈቱም ተናግረዋል፡፡

በተባበሩት መንግሥታት የኢንደስትሪ ልማት ድርጅት ተወካይ እና የፕሮጀክቱ ቴክኒካል አማካሪ ዶክተር ለምለም ሲሳይ በበኩላቸው፤ በገጠር ላሉ ሴቶች የኑሮ ማሻሻያ ያስፈልጋል በሚል ከመንግሥት በቀረበው ጥያቄ መሰረት ፕሮጀክቱ ተግባራዊ መደረጉን አንስተው ከክልሉ መንግሥት ጋር በጋራ እንደተሰራም አስረድተዋል፡፡የሞሪንጋ ወይም የሽፈራው ተክልን አብዛኛው የኢትዮጵያ የማህበረሰብ ክፍሎች የተለያዩ የካንሰር አይነቶችን እና ደምግፊትን ጨምሮ ሌሎች በሽታዎችን ለመከላከል እንደሚጠቀሙበት የሚታወቅ ነው፡፡

Via Ahadu

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

22 Oct, 16:17


ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በ11 የፖለቲካ ፓርቲዎች ላይ የዕግድ ውሳኔ ማሳለፉን አስታወቀ

#የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በጠቅላላ ጉባዔ፣ በኦዲት እና በሴት አባላት አማካኝነት ከሚገኝ የገንዘብ ድጋፍ ጋር በተያያዘ 11 የፖለቲካ ፓርቲዎችን ማገዱን ዛሬ ጥቅምት 12 ቀን 2017 ዓ.ም ባወጣው የዕግድ ደብዳቤ አስታውቋል።

የዕግድ ውሳኔ ከተሰጣባቸው ፓርቲዎች መካከልም የዎላይታ ብሔራዊ ንቅናቄ፣ የኦሮሞ ነጻነት ንቅናቄ፣ አንድ ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፖርቲ፣ ጌዲኦ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት፣ የሐረሪ ዲሞክራሲያዊ ድርጅት፣ የገዳ ሥራዓት ለኦሮሞ ነጻነት ፓርቲ፣ አዲስ ትውልድ ፓርቲ ይገኙበታል፡፡

በፓርቲዎቹ ላይ የተሰጠው የዕግድ ውሳኔ ቦርዱ የተለየ ውሳኔ እስከሚሰጥ ድረስ ለጊዜው ፓርቲዎችን ከማናቸውም ሕጋዊ እንቅስቃሴ ታቅበው እንዲቆዩ የሚያደርግ ነው ተብሏል፡፡

ቦርዱ በደብዳቤው ለኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት እንዳስታወቀው የሰጠውን የዕግድ ውሳኔ እስከሚያነሳ ድረስ በማናቸውም የጋራ ምክር ቤቱ በሚያዘጋጃቸው ጉባኤዎች ላይ ሊገኙ እንዲሁም ሊመርጡም ሊመረጡም ወይም በተለያዩ የኮሚቴ አባልነት ሊያገለግሉ አይችሉም ብሏል። የጋራ ምክር ቤቱ የእግድ ውሳኔ የተላለፈባቸውን ፓርቲዎች ከማናቸውም የምክር ቤቱ ሥራዎችም ሆነ እንቅስቃሴዎች እንዳይካፈሉ ተገቢውን ሁሉ እንዲያደረግ ቦርዱ በደብዳቤው አሳስቧል፡፡

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

22 Oct, 09:20


ዘለቀ ተመስገን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ሆነዉ ተሾሙ!

የተቋሙ ኮሚሽነር የሆኑት ሃና አርዓያስላሴ የፍትህ ሚኒስትር ሆነዉ በጠቅላይ ሚኒስትሩ መሾማቸውን ተከትሎ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽንን በምክትል ኮሚሽነርነት ሲመሩ የነበሩት ዘለቀ ተመስገን ( ዶ/ር) የኮሚሽነርነት ቦታን ተረክበዋል።

ዘለቀ ከጣልያን ቱሪን ዩኒቨርሲቲ በህዝብ አለምአቀፍ ሕግ የዶክትሬት ዲግሪ ማጠናቀቃቸው የተገለፀ ሲሆን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽንን ከመቀላቀላቸዉ በፊት የኢፌዲሪ የፌዴሬሽን ምክር ቤት የቢሮ ሃላፊ ሆነው አገልግለዋል።

በኢትዮጵያ የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ሆነው የሰሩት ዘለቀ ተመስገን ( ዶ/ር) የሀገሪቷን የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንትን ለመሳብና ለማበረታታት የተቋቋመውን ተቋም በኃላፊነት እንዲመሩ ተሹመዋል።

Via Capital

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

22 Oct, 09:11


ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በ#BRICS2024 የመሪዎች ጉባኤ ለመሳተፍ ካዛን ገቡ

ጠ/ሚኒስትር አብይ አህመድ በብሪክስ የመሪዎች ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ሩሲያ ካዛን መግባታቸው ተገለጸ!

ጠ/ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ #በብሪክስ (BRICS) የመሪዎች ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ሩሲያ መግባታቸውን የአዘጋጇ የሩሲያዋ ታታርስታን ግዛት ፐሬዝዳንት ጽ/ቤት ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።

"የኢትዮጵያ ጠ/ሚኒስትር አብይ አህመድ በ BRICS የመሪዎች ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ #ካዛን ገብተዋል፤ በካዛን አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የግዛቷ ፕሬዝዳንት ሩስታም ሚኒካኖቭ አቀባበል አድርገውላቸዋል" ሲል መግለጫው አትቷል።

በካዛን በሚካሄደው የመሪዎች ስብሰባ ከ30 ሀገራት በላይ ተወካዮች ይታደማሉ መባሉን ከሩሲያ የዜና አገልግሎት ታስ ያገኘነው መረጃ ያሳያል፤ የዩናይትድ አረብ #ኤሚሬቱ ፕሬዝዳንት ቢን ዛይድ፣ #የኢራኑ ፕሬዝዳንት ማሱድ ፔዜሽክያን፣ #የህንዱ ፕሬዝዳንት ናሬንድራ ሞዲ በካዛን ከተገኙ መሪዎች ይገኙበታል። ኢትዮጵያ በተያዘው የፈረንጆቹ 2024 መጀመሪያ ላይ ቡድኑን በይፋ መቀላቀሏ ይታወቃል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

22 Oct, 09:10


የፖለቲካ ፓርቲዎች በምርጫ ቦርድ የጊዜያዊ ዕውቅና ለማግኘት ሲከፍሉ የነበረው 100 ብር ከዚህ በኋላ 15ሺ መሆኑ ተገለጸ

የፖለቲካ ፓርቲዎች የጊዜያዊና ሙሉ ዕውቅና ለማግኘት የሚጠበቅባቸው ክፍያ መሻሻሉን ምርጫ ቦርድ አስታወቀ፤ ለጊዜያዊ ዕውቅና 15ሺ፣ ለሙሉ ዕውቅና 30ሺ ነው ብሏል።የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ጥቅምት 12 ቀን ባወጣው መግለጫ ለሀገር አቀፍ እና ለክልላዊ ፖለቲካ ፓርቲ ጊዜያዊ ሰርተፍኬት ለማግኘት 100 ብር ብቻ ያስከፍል እንደነበር አውስቶ ከጥቅምት 11 ቀን 2017 ዓ.ም በኋላ ግን ክፍያው 15ሺ ብር መሆኑን እወቁልኝ ብሏል።

በተመሳሳይ የሀገር አቀፍ እና ክልላዊ የፖለቲካ ፓርቲዎች ሙሉ ዕውቅና ለማግኘት እስከ ትላንት ጥቅምት 11 ቀን 2017 ዓ.ም ይከፍሉ የነበረው 200 ብር ብቻ መሆኑን አስታውሶ ከዚህ በኋላ ግን ክፍያው 30ሺ ብር ነው ሲል አስታውቋል።የተመዘገቡ ፖለቲካ ፓርቲዎች መሰረታዊ ሰነዶቻቸውን በጉባኤ አሻሽለው ሲያቀርቡ 30 ብር የአገልግሎት ክፍያ ሲያስከፍል እንደነበር ጠቁሞ ከዚህ በኋላ ግን ሰነዶቹን ያሻሻለ ፓርቲ 5ሺ እንዲከፍል ወስኛለሁ ሲል ገልጿል።

ምርጫ ቦርድ ክፍያውን ያሻሻልኩት የፖለቲካ ፓርቲዎች የምዝገባ እና የሰነድ ማሻሻያ አገልግሎት ክፍያ መጠኑ በቦርዱ እንዲወስን በአዋጅ ስልጣን ስለተሰጠኝ ነው ብሏል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

22 Oct, 05:09


ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ ( ዶ/ር ) ኢትዮጵያ በ2029 የአፍሪካ ዋንጫን ለማዘጋጀት ይፋዊ ጥያቄ አቀረቡ

ኢትዮጵያ በ2029 የሚካሄደውን የአፍሪካ ዋንጫ የማዘጋጀት አቅም እንዳላት የገለፁት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለካፍ ፣ለፊፋ ፕሬዚዳንቶች እና ለካፍ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ከፍተኛ አመራሮች በታላቁ ቤተ-መንግስት የእራት ግብዣ አከናውነዋል።

በፕሮግራሙ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ የ2029 አፍሪካ ዋንጫን እንድታዘጋጅ በይፋ ጠይቀዋል።

የካፍ ፕሬዚዳንት ፓትሪስ ሙትሴፔ በበኩላቸው ÷ በኢትዮጵያ ለተደረገላቸው ደማቅ አቀባበል ምስጋና አቅርበው፣ የኢትዮጵያውያን ባህል፣እሴትና እንግዳ ተቀባይነት ኢትዮጵያ ቤታችን እንደሆነች እንዲሰማን አድርጎናል ብለዋል፡፡

ኢትዮጵያ የ2029ኙን የአፍሪካ ዋንጫ ለማዘጋጀት ያቀረበችውን ጥያቄ ካፍ ከኮሚቴው ጋር እንደሚመክርበት ገልዋጸል።

የፊፋ ፕሬዚዳንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ ÷ የሰው ዘር መገኛ የሆነችው ኢትዮጵያ፤ የኛም ሀገር ነች ሲሉ ተናግረዋል።

በመርሐ ግብሩ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ለሁለቱም ፕሬዚዳንቶች የኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን መለያን በስጦታ አበርክተዋል፡፡

በተመሳሳይ የፊፋው ፕሬዚዳንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ 2029 የሚል ፊርማቸውን ያሳረፉበትን ኳስ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) አበርክተዋል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

22 Oct, 05:06


የመርካቶው የእሳት አደጋ አሁናዊ ሁኔታ ከቦታው

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

21 Oct, 19:34


አዲሱን የደሞዝ ጭማሪን ከታች ይመልከቱ

የተሻሻለው የመንግስት ደሞዝ ጭማሪ ስኬል ይፋ ሆኗል።

የጥቅምት ወር የመግስት ሰራተኞች ደመወዝ በተጠቀሰው ስኬል መሰረት ይተገበራል ተብሏል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

21 Oct, 19:21


ለ 56 ዓመት በሳምንት አንዴ እየተገናኙ ቢራ የጠጡት እንግሊዝያውያን ጓደኛሞች አነጋጋሪ ሆነዋል

ይህ የእንግሊዝ በ 80 ዎቹ እድሜ ላይ የጡረተኞች ቡድን በፈረንጆቹ ከ 1968 ጀምሮ ጠንካራ ትስስርን አስጠብቆ ቆይቷል፣።

በየሳምንቱ ሐሙስ በየመጠጥ ቤቱ ለ56 ዓመታት እየተሰበሰቡ ተገናኝተዋል።
በኮሮና ጊዜ እና በአንዳንድ በአሎች ላይ ባይገናኙም ረጅሙን አመት ግን ተገናኝተው ተጫውተዋል።
BBC

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

21 Oct, 19:21


በመርካቶ ሸማ ተራ አከባቢ የተከሰተውን የእሳት አደጋ እስከ አሁን መቆጣጠር ባለመቻሉ በሄሊኮፕተር እየተሞከረ መሆኑ ተገለጸ

👉 "በመርካቶ ሸማ ተራ አከባቢ በተከሰተው የእሳት አደጋ በንብረት ላይ ለደረሰው ጉዳት እጅግ አዝነናል" ከንቲባ አዳነች አቤቤ

የተከሰተውን የእሳት አደጋ ለመቆጣጠር ከእሳት አደጋ  እና ስጋት መከላከል እንዲሁም  ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር በመሆን ርብርብ እየተደረገ  ስለመሆኑ የገለጹት ከንቲባዋ አደጋውን ቶሎ ለመቆጣጠር እየተደረገ ያለዉን ጥረት  አዳጋች ያደረገዉ የአካባቢው መንገድ የእሳት አደጋ መኪና በተሟላ ሁኔታ ለመንቀሳቀስ አስቸጋሪ በመሆኑ ምክንያት ነው ብለዋል።

በመሆኑም የእሳት አደጋውን ለመቆጣጠር በሄሊኮፕተር ለመጠቀም እየጣርን  ነው ሲሉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገልጸዋል። 

ከንቲባዋ አክለውም ይህንን አደጋ ለመቀነስ ርብርብ እያደረጉ የሚገኙትን አካላት ሁሉ ጥረታቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ አሳስበዋል።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

21 Oct, 08:38


የኦጋዴን ብሄራዊ ነፃ አውጭ ግንባር (ኦብነግ) በብሔራዊ ምክክር ኮሚሽን ውስጥ የነበረውን ተሳትፎ ማቆሙን አስታወቀ!

የኦጋዴን ነጻ አውጪ ግንባር (ኦብነግ) አሳታፊነትና ግልጸኝነት ስላላየሁበት ከአገራዊ ምክክር ኮሚሽን ተሳታፊነት እራሴን አግልያለሁ ሲል ባወጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡በሶማሌ ክልል ገዢው ፓርቲ በቅርቡ የወሰዳቸው እርምጃዎች ተሳታፊዎችን አንድ ወገንን በመምረጥ፣ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ያለውን ስምምነት በመጣስ እና የተለያዩ ድምፆችን ወደ ጎን በመተው ሂደቱን አግላይ በማድረጉ ምክንያት ራሱን ከምክክር ሂደቱ ማግለሉን ነው የገለጸው፡፡

ሁሉንም ባለድርሻ አካላት በማሰባሰብ የግጭት መንስኤዎችን ለመፍታት የታቀደውን የብሔራዊ ውይይት ዓላማን የሚቃረን፣ ከአማራ፣ ከኦሮሚያ እና ከትግራይ የተውጣጡ ቁልፍ የፖለቲካ ተዋናዮች በሌሉበት እና እየተከሰቱ ያሉ ግጭቶችን ለመፍታት ጥረት እየተደረገ ባልሆነበት ሁኔታ፣ አሁን ያለው ውይይት የአንድ ወገንን ያማከለ በመሆኑ እውነተኛ ሰላም የማምጣት አቅም የሌለው መሆኑን ፓርቲው በመግለጫው አንስቷል።

ኦብነግ ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም ማምጣት የሚችል እውነተኛ፣ ሁሉን አቀፍ እና ግልጽ ውይይት ለማድረግ ቁርጠኛ ቢሆንም፤ እንዲህ ያለው ምክክር ሁሉን አቀፍ እና ታእማኒ እስኪሆን ድረስ አሁን ባለው ማዕቀፍ ውስጥ አልሳተፍም ሲል ገልጿል።የኦጋዴን ብሄራዊ ነፃ አውጭ ግንባር (ኦብነግ) በ2010 ዓ.ም ሰላማዊ የፖለቲካ እንቅስቃሴን ለማድረግ ከመንግሥት ጋር ስምምነት አድርጎ ወደሀገር ውስጥ መግባቱ የሚታወስ ነው፡፡

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

20 Oct, 14:02


" ትናንትና 2 ዛሬ ደግሞ 10 አስክሬን ተገኝቷል " - የጋሞ ዞን ፖሊስ

ከአቡሎ አርፋጮ ወደ አርባምንጭ ከተማ 16 ሰዎችን እና ሙዝ ጭና ስትጓዝ የነበረች ጀልባ ባሳለፍነው ሐሙስ 10 ሠዓት ከ20 ገደማ ጫሞ ሐይቅ ላይ ሰጥማ ነበር።

ይህ ተከትሎ እየተከናወነ ባለ የነፍስ አድን ሥራ ትናንት 2 ዛሬ ደግሞ 10 አስከሬን መገኘቱን የጋሞ ዞን ፖሊስ መምሪያ አሳውቋል።

እስከ ዓርብ ድረስ ባለው 3 ሰዎች በሕይወት መገኘታቸውን ገልጿል።

በአጠቃላይ በጀልባዋ ከተሳፈሩት መካከል እስከ አሁን የአንዱ ሰው ሁኔታ ስላልታወቀ ፍለጋው መቀጠሉ ተመላክቷል።

የጋሞ ዞን ፖሊስ የአደጋው መንስኤን በተመለከተ ፥ " የጀልባዋ የመጫን አቅም 35 ኩንታል ሆኖ ሳለ በዕለቱ 70 ኩንታል ሙዝ እና 16 ሰዎችን ጭና ነበር፤ ይህም ከልክ በላይ መጫን በመሆኑ ለአደጋው መከሰት መንስዔ ሆኗል " ብሏል።

መረጃው የኤፍ ቢ ሲ ነው።

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

20 Oct, 04:53


Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ) pinned «ሰበር ዜና ..😭 የግድያዉ ምክንያት ታወቀ ..አንቆ ገደላት | በአደባባይ ባለቤቱን አዋረዳት ! Ethiopia Ne... https://youtu.be/Na7qIYARZe8?si=82HiSqwDmXogtb9s»

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

20 Oct, 04:53


ሰበር ዜና ..😭 የግድያዉ ምክንያት ታወቀ ..አንቆ ገደላት | በአደባባይ ባለቤቱን አዋረዳት ! Ethiopia Ne...

https://youtu.be/Na7qIYARZe8?si=82HiSqwDmXogtb9s

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

19 Oct, 15:37


አዲሱ የመንግስት ስራተኞች ደመወዝ ከጥቅምት ወር ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚደረግ የገለፀው የገንዘብ ሚኒስትር ለዚህም የአፈፃፀም መመሪያ መዘጋጀቱን አስታወቀ!

የገንዘብ ሚኒስትር እንደገለፀው የጥቅምት ወር የደመወዝ ክፍያ በአዲሱ በተሻሻለው የደመወዝ ስኬል መሰረት መሆን ይጀምራል ብሏል። ለዚህም በቂ ዝግጅት ከመደረጉ በላይ የአፈፃፀም መመሪያ መዘጋጀቱን አስታዉቋል።

ካፒታል ከዚህ ቀደም በተደረገዉ ማሻሻያ ላይ የመንግስት ሰራተኞች ያቀረብትን ቅሬታ አስመልክቶ እንደዘገበው አዲሱ የደመወዝ ማሻሻያ ጥናት: የሚኒስትሮች ምክር-ቤት ከማፅደቁ አስቀድሞ ሰራተኞችን ማወያየት እንዳለበት እና በድጋሚ መታየት እንደሚኖርበት ተጠይቆ ነበር።እነዚሁ ሠራተኞች እንደገለፁት የደመወዝ ማሻሻያው አሁን ያሉበትን የኑሮ ሁኔታ እንደተባለውም ከግምት ያላስገባና እንደጠበቁት እንዳልሆነ ማስረዳታቸው ይታወቃል።

ይሁን እንጂ የገንዘብ ሚኒስቴር ደመወዝ ማሻሻያ ረቂቅ ለሚኒስትሮች ምክርቤት በቀን 28 /12/ 2016 ዓ.ም. ያቀረበዉ ከሰሞኑ በካቢኔው መፅደቁን አስታዉቋል።ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ እንዳስታወቁት " በአጠቃላይ ሪፎርሙ በህብረተሰቡ ላይ የተለየ ጫና አለማምጣቱን እና የተፈራው የዋጋ ንረት አለመድረሱን " የተናገሩት የካቢኔው የ 100 ቀን አፈፃፀም ግምገማ አስመልክተው በሰጡት ማብራሪያ ነዉ።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ካፒታል ማሻሻያው ተከትሎ በወቅቱ በሰራዉ ዘገባ የደሞዝ ጭማሪ መኖሩን መንግስት መናገሩን ተከትሎ በማግስቱ  የሁሉም ነገር ዋጋ በሁለት እጥፍ ጨምሯል። በዚህም ሰራተኛዉም ሆነ በዝቅተኛ ኑሮ ላይ የነበሩት ሰዎች ምንም የተሰጣቸዉ ነገር ሳይኖርና ጭማሪ እጃቸዉ ሳይገባ የኑሮ ዉድነቱ ተባብሶ ቀጥሏል ሲሉም ሁኔታዉን በምሬት ገልፀዉለት እንደነበር ይታወሳል።
Via Capital

Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

19 Oct, 11:50


ኢትዮጵያንና ሌሎች ወታደር አዋጭ የሆኑ ሃገራት በሶማሊያ በአዲሱ የሰላም ማስከበር ተልዕኮ ውስጥ ለመቀጠል ያላቸውን 'ፈቃደኝነት እና ዝግጁነት' ገለጹ

ኢትዮጵያን ጨምሮ ሌሎች በሶማሊያ የአፍሪካ ህብረት የሽግግር ተልዕኮ (አትሚስ) ወታደር አዋጭ የሆኑ ሀገራት የመከላከያ ሚንስትሮች በሶማሊያ የሰላም ማስከበር ጥረታቸውን በአዲሱ ተልዕኮ ለመቀጠል ያላቸውን “ፍላጎት እና ዝግጁነት” ገልጸዋል።

ሚንስትሮቹ ይህን የገለጹት ጥቅምት 6 ቀን 2017 ዓ.ም በኢትዮጵያ መከላከያ ሚኒስትር አይሻ መሀመድ ጋባዥነት ከተዘጋጀው የአፍሪካ መከላከያ ሚኒስትሮች ጉባኤ ጎን ለጎን የተካሄደው የሚኒስትሮች ስብሰባ መጠናቀቁን ተከትሎ ባወጡት የጋራ መግለጫ ነው።

ስብሰባው ከብሩንዲ፣ ጅቡቲ፣ ኢትዮጵያ፣ ኬንያ እና ዩጋንዳ የተውጣጡ የመከላከያ ሚንስትሮችን አካቷል ተብሏል።

አዲስ ስታንዳርድ የተመለከተው የጋራ መግለጫ እንዳስታወቀው ባለፉት አስራ ሰባት ዓመታት ወታደር አዋጭ የሆኑ ሃገራት በሶማሊያ ሽብርተኝነትን በመዋጋትና ሀገሪቱን በማረጋጋት የከፈሉትን መስዋዕትነት እውቅና ሰጥቶ፤ ለሶማሊያ ፌደራል መንግስት ተቋማትን በማጎልበት እንዲሁም በማሳደግ ረገድ አስተዋጽኦ አድረጓል ብሏል።