ገዳማውያን @gedamaweyan Channel on Telegram

ገዳማውያን

@gedamaweyan


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሕዱ አምላክ አሜን።
ይህ ገዳማውያን የተሰኘው ስለ ነገረ ምንኩስና ተባህትዎ የምንነጋገርበት የምንማማርበት የቴሌግራም ቻናል ነው። ኑ እንደ አባቶቻችን በጥብዓት በተባሕትዎ እንኖር ዘንድ ሕይወታቸውን እንመርምር ሥርዓታቸውንም እንማር በፍኖተ አበው እንጓዝ በረከታቸውንም እናግኝ።

አስተያየት እንዲሁም ጥያቄ ካላችሁ በዚህ👇
@gedamaweyan_bot አስቀምጡልን

ገዳማውያን (Amharic)

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሕዱ አምላክ አሜን። ይህ ገዳማውያን የተሰኘው ስለ ነገረ ምንኩስና ተባህትዎ የምንነጋገርበት የምንማማርበት የቴሌግራም ቻናል ነው። ኑ እንደ አባቶቻችን በጥብዓት በተባሕትዎ እንኖር ዘንድ ሕይወታቸውን እንመርምር ሥርዓታቸውንም እንማር በፍኖተ አበው እንጓዝ በረከታቸውንም እናግኝ። አስተያየት እንዲሁም ጥያቄ ካላችሁ በዚህ 👇 @gedamaweyan_bot አስቀምጡልን. የገዳማውያን እንዴት መልከወን ያለበት ነገር ነው? ይህ ቴሌግራም ቻናል ይሆናል እና በዚህ ቦታ ስለሚለዋወጥ የገዳማውያን ውስጥ የሂደት ነው። ገዳማውያን ለመመዝገብ የምንጉረመት ቻናል ነው። በትክክልም ገዳማውያን በሚሰበሰባቸው ጥያቄዎችና ህዝብ በሚሰሩ በቀጥታ ጊዜያዎች ለሚዘገቡት ቻናል ነን።

ገዳማውያን

14 Feb, 04:58


መዝሙር 25
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ አቤቱ፥ ወደ አንተ ነፍሴን አነሣለሁ።
² አምላኬ፥ አንተን ታመንሁ፤ አልፈር፥ ጠላቶቼ በእኔ አይሣቁብኝ።
³ አንተን ተስፋ የሚያደርጉ አያፍሩም፤ በከንቱ የሚገበዙ ያፍራሉ።
⁴ አቤቱ፥ መንገድህን አመልክተኝ፥ ፍለጋህንም አስተምረኝ።
⁵ አንተ የመድኃኒቴ አምላክ ነህና በእውነትህ ምራኝ፥ አስተምረኝም፤ ቀኑን ሁሉ አንተን ተስፋ አድርጌአለሁ።
⁶ አቤቱ፥ ምሕረትህንና ቸርነትህን አስብ፥ ከጥንት ጀምሮ ናቸውና።
⁷ የልጅነቴን ኃጢአትና መተላለፍ አታስብብኝ፤ አቤቱ፥ ስለ ቸርነትህ ብዛት እንደ ምሕረትህ አስበኝ።
⁸ እግዚአብሔር ቸር ቅንም ነው፤ ስለዚህ ኃጢአተኞችን በመንገድ ይመራቸዋል።
⁹ ገሮችን በፍርድ ይመራል፥ ለገሮችም መንገድን ያስተምራቸዋል።
¹⁰ የእግዚአብሔር መንገድ ሁሉ ቸርነትና እውነት ነው። ቃል ኪዳኑንና ምስክሩን ለሚጠብቁ።
¹¹ አቤቱ፥ ኃጢአቴ እጅግ ነውና ስለ ስምህ ይቅር በለኝ።
¹² እግዚአብሔርን የሚፈራ ሰው ማን ነው? በሚመርጠው መንገድ ያስተምረዋል።
¹³ ነፍሱ በመልካም ታድራለች፥ ዘሩም ምድርን ይወርሳል።
¹⁴ እግዚአብሔር ለሚፈሩት ኃይላቸው ነው፥ ቃል ኪዳኑንም ያስታውቃቸዋል።
¹⁵ እርሱ እግሮቼን ከወጥመድ ያወጣቸዋልና ዓይኖቼ ሁልጊዜ ወደ እግዚአብሔር ናቸው።
¹⁶ እኔ ብቻዬንና ችግረኛ ነኝና ፊትህን ወደ እኔ አድርግ ማረኝም።
¹⁷ የልቤ ችግር ብዙ ነው፤ ከጭንቀቴ አውጣኝ።
¹⁸ ድካሜንና መከራዬን እይ፥ ኃጢአቴንም ሁሉ ይቅር በለኝ።
¹⁹ ጠላቶቼ እንደ በዙ እይ፥ የግፍም ጥል ጠልተውኛል።
²⁰ ነፍሴን ጠብቅና አድነኝ፤ አንተን ታምኛለሁና አልፈር።
²¹ አንተን ተስፋ አድርጌአለሁና የውሃትና ቅንነት ይጠብቁኝ።
²² አቤቱ፥ እስራኤልን ከመከራው ሁሉ አድነው።

ገዳማውያን

10 Feb, 03:34


🕊                        💖                      🕊

            [      ጾ መ ነ ነ ዌ !      ]

▬▬▬▬▬▬   ♱    ▬▬▬▬▬▬

❝ እግዚአብሔርም ከክፉ መንገዳቸው እንደ ተመለሱ በሥራቸውን አየ ፤ እግዚአብሔርም ያደርግባቸው ዘንድ በተናገረው ክፉ ነገር ተጸጽቶ አላደረገውም። ❞

[ ት.ዮናስ ፫፥፭ -፲ ]


[  እንኳን ለጾመ ነነዌ በሰላም አደረሳችሁ ! ]


🕊                       💖                     🕊

ገዳማውያን

29 Jan, 04:10


​​ሞት በጥር ነሐሴ መቃብር

የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ሞትና ትንሣኤ በነገረ ማርያም አበው እንደሚያስረዱት ዕረፍቷ በጥር ፳፩ እሑድ ነው። አባቶቻችን በጾመ ፍልሰታ ውዳሴ ማርያም ቅዳሴ ማርያም ሲተረጉሙ የእረፍቷን ነገር እንዲህ ብለው ይተርካሉ። የእረፍቷስ ነገር እንደምን ነው ቢሉ ስድሳ አራት ዓመት በዚህ ዓለም ኖራ ጥር ፳፩ በእሑድ ቀን ጌታ እልፍ አዕላፋት መላእክቱን አስከትሎ መጥቶ እናቴ ሆይ ከዚህ ዓለም ድካም ላሳርፍሽ መጣሁ አላት።

ልጄ ሰማይና ምድር የማይወስኑህ ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን በማህጸኔ ተሸክሜ በድንግልና ወልጄህ እሞታለሁን? አለችው። በሲዖል የሚሰቃዩ ነፍሳትን አሳይቶ እናቴ ሆይ ሞትሽ ለእነዚህ ቤዛ ይሆንላቸዋል አላት። እሊህን ከማርክልኝስ ይሁን አለችው። ቅድስት ሥጋዋን ከቅዱስ ነፍሷ ለይቶ በቃለ አቅርንት በዝማሬ መላእክት አሳረጋት።

ደቀመዛሙርቱንም ከያሉበት በደመና ጠቅሶ ካለችበት አድርሶ እመቤታችሁን ስጋዋን በክብር አሳርፉ አላቸው። ሐዋርያት በአጎበር አድርገው ወደ ጌቴሰማኒ ይዘው ሲሄዱ አይሁድ ቀድሞ ልጇን ተነሳ ዐረገ እያሉ ሲያውኩን ይኖራሉ አሁን ደግሞ እሷን ተነሳች ዐረገች እያሉ ሊያውኩን አይደለምን በእሳት እናቃጥላታለን ብለው ተነሱ።

ታውፋንያ የሚባል አይሁዳዊ ተራምዶ አጎበሩን ጨበጠው። መልአክ መጥቶ በሰይፍ ሁለት እጁን ቀጣው ከአጎበሩ ተንጠልጥሎ ቀረ። በድያለሁ ማሪኝ ብሎ ቢማጸናት እጁ ተመልሶለታል። ከዚህ በኋላ ዮሐንስን ጨምሮ በደመና ነጥቆ ከገነት አግብቶ ከዕፀ ሕይወት ሥር አኖራት። ቅዱስ ዮሐንስን እንደምን ሆነች አሉት ከገነት ከዕፀ ሕይወት ሥር አለች አላቸው ቅዱስ ዮሐንስ አይቶ እኛ ሳናይ ብለው በነሐሴ መባቻ ጾም ጀመሩ ሁለት ሱባዔ ሲፈጸምም እሑድ አምጥቶ ሰጥቷቸው ቀብረዋታል በሶስተኛው ቀን ማክሰኞ “ከመ ትንሳኤ ወልዳ” እንደ ልጇ ተነሥታለች።

ቅዱስ ቶማስ አልነበረም ደመና ጠቅሶ ከሀገረ ስብከቱ ሲመጣ ስታርግ አገኛት ቀድሞ የልጅሽን ትንሳኤ ሳላይ ቀረሁ ዛሬም ደግሞ ያንችን ትንሳኤ ሳላይ ቀረሁን ብሎ “ወፈቀደ ይደቅ እምደመናሁ” ከሀዘኑ የተነሳ ሊወድቅ ወደደ እመቤታችንም አይዞህ አትዘን እሊያ ትንሳኤየን ዕርገቴን አላዩም አንተ አይተሃል ተነሣች ዐረገች ብለህ ንገራቸው ብላ የያዘችውን ሰበን ሰጥታ ሰደደችው።

ከዚህ በኋላ ሂዶ የእመቤታችን ነገር እንደምን ሆነ አላቸው አግችተን ቀበርናት አሉት ሞት በጥር በነሐሴ መቃብር ተው ይህ ነገር አይመስለኝም አላቸው። ቅዱስ ጴጥሮስ አንተ እንጅ ልማድህ ነው አንተ ብቻ ተጠራጥረህ አትቀርም ሰውን ሁሉ ስታጠራጥር ትኖራልህ ብሎ ተቆጥቶ ወደ መቃብሩ ሂዶ ቢከፍተው አጣት ደንግጦ ቆመ ሐዋርያው ቶማስም አታምኑኝም ብየ እንጅ እመቤታችንስ ተነሣች ዐረገች አላቸው የያዘውንም ሰበን ሰጣቸው ለበረከትም ተካፍለውታል።

በዓመቱ ሐዋርያት ቅዱስ ቶማስ ትንሣኤሽን ዕርገትሽን አይቶ እኛ ሳናይ ብለው ጾም ጀመሩ በ፲፮ኛው ቀን እመቤታችንን መንበር አድርጎ ቅዱስ ጴጥሮስን ካህን ዘይትራድኦ ቅዱስ እስጢፋኖስን ሠራዒ ዲያቆን አድርጎ በዚያው ላይ ቀድሶ አቁርቧቸዋል። ቤተክርስቲያንም ይህንን መታሰቢያ አድርጋ በየዓመቱ ታከብረዋለች።

ሰአሊ ለነ ቅድስት
የኃጥአንን ለቅሶና ሐዘን አይተሽ ስለእነርሱ ድኅነት(መዳን) ዕረፍትሽን በሀሴት የተቀበልሽ እመቤታችን ሆይ ሐዋርያት በሱባዔ ትንሣዔሽን ለማየት በቅተዋልና እኛም በዓለ ዕረፍትሽን አክብረን ልጅሽ በሰጠሽ ቃል ኪዳን በቀኙ እንቆም ዘንድ ለምኝልን። አሜን።

በቀሲስ ኃይለኢየሱስ ተመስገን
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
#Share
@Gedamaweyan         @Gedamaweyan
@Gedamaweyan         @Gedamaweyan

ገዳማውያን

29 Jan, 04:10


​​ጥር ፳፩ የእመቤታችን በዓለ ዕረፍት (አስተርእዮ ማርያም)

”አስተርእዮ ማርያም“

አስተርእዮ ማለት መታየት፣ መገለጥ ማለት ነው። ቃሉ አስተርአየ ታየ፣ ተገለጠ ከሚለው የግዕዝ ግሥ የተገኘ ነው። ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በገባው ቃል ኪዳን መሠረት በሥጋ የተገለጠበት(የታየበት) ፣ አንድነት ሦስትነቱም የተገለጠበት ወቅት በመሆኑ ከልደት በዓል እስከ ጥር መጨረሻ በሙሉ ዘመነ አስተርእዮ በመባል ይታወቃል። የእመቤታችን በዓለ ዕረፍት በዘመነ አስተርእዮ ውስጥ ስለሚከበር “አስተርእዮ ማርያም” ተብሏል።

ልቡናዋ በይኩነኒ የጸና ንጽሐ ሥጋ ፣ ንጽሐ ነፍስ፣ ንጽሐ ልቡና አስተባብራ የያዘች ወላዲተ አምላክ ምንም እንኳን የአምላክ እናት ብትሆንም ሞተ ሥጋ ለሁሉም ዕጣ ፈንታ በመሆኑ በቃል መነገሩ በልብ መታሰቡ ከፍ ከፍ ይበልና ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ “ተንሥኢ ወንዒ”  የነፍሴ ደስታ የኾንሽ ውድ እናቴ ሆይ ተነሥተሽ ወደ እኔ ነዪ (መኃ ፪፥፲) ብሏታል።

ሞታ ለማርያም የዐጽብ ለኲሉ

ቅዱስ ዳዊት “ነኪር ነገሩ በእንቲአኪ ሀገረ እግዚአብሔር “ መዝ.፹፮፥፫ እግዚአብሔር ማህጸንሽን ከተማ አድርጎ ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን የኖረብሽ ሆይ ስለ አንቺ የተነገረው የተደረገው ነገር ዕጹብ ድንቅ ነው እንዳለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የአምላክ እናት ሆና ማረፏ ይደንቃል። ታላቁ የቤተክርስቲያናችን አባት ቅዱስ ያሬድ ሞቷ የሚያስደንቅ መሆኑን «ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ ሞታ ለማርያም የዐጽብ ለኲሉ፤ ሞት ለማናቸውም ሰው ሁሉ የተገባ ነው የማርያም ሞት ግን ሁሉን ያስደንቃል» በማለት ገልጾታል።

በቀሲስ ኃይለኢየሱስ ተመስገን
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
#Share
@Gedamaweyan         @Gedamaweyan
@Gedamaweyan         @Gedamaweyan

ገዳማውያን

26 Jan, 04:32


​​​​✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን፡፡ ✞

ቅዱስ ጊዮርጊስ ልዳዊ

መጽሐፈ ገድሉ እንደሚለው የሰማዕታት አለቃቸው: አንድም ሞገሳቸው ታላቅና ክቡር ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ ከ7 ዓመታት ስቃይ በኋላ ተሰይፏል:: ይህስ ጥንተ ነገሩ እንደምን ነው ቢሉ:-

ቅዱሱ የተወለደው ከአባቱ ዘረንቶስ (አንስጣስዮስ) እና ከእናቱ ቴዎብስታ የድሮው ፋርስ ግዛት ፍልስጥኤም (ልዳ) ውስጥ ነው:: የተባረኩ ወላጆቹ ክርስትናን ጠንቅቀው አስተምረውት አባቱ ይሞታል::

ቅዱስ ጊዮርጊስ 20 ዓመት ሲሞላው የአባቱን ስልጣን እጅ ለማድረግ ሲሔድ የቢሩት (የአሁኗ ቤይሩት-ሊባኖስ) ሰዎች ዘንዶ/ደራጎን ሲያመልኩ አገኛቸው:: እርሱ ግን የከተማውን ሕዝብ አስተምሮ: አሳምኖ: ደራጎኑንም በፈጣሪው ኃይል ገድሎ መንገዱን ቀጥሏል::

ቅዱስ ጊዮርጊስ ወደ ዱድያኖስና 70 ነገሥታት ዘንድ ሲደርስ ክርስቶስ ተክዶ ለጣዖት ይሠገድ ነበር:: በዚያች ሰዓት ድንግል እመቤታችን ወደ ሰማዕቱ መጥታ መከራውንና ክብሩን ነገረችው:: እርሱም በክርስቶስ ስም መሞት ምርጫው ነበርና ከእመቤታችን ተባርኮ ወደ ምስክርነት አደባባይ (ዐውደ ስምዕ) ደረሰ::

ከዚያም ለተከታታይ 7 ዓመታት ብዙ ጸዋትወ መከራዎችን ተቀበለ:: 3 ጊዜ ሙቶ ተነሳ:: ከሰው ልጅ የተፈጥሮ ትዕግስት በላይ የሆነ ስቃይን ስለ ቀናች ሃይማኖት ሲል በመቀበሉ የሰማዕታት አለቃቸው: ፀሐይና የንጋት ኮከብ በሚል ይጠራል:: "ተውላጠ ጻማሁ ወሕማሙ: ዘተለዐለ ሞገሰ ስሙ" እንዲል መጽሐፍ::

ከ7 ዓመታት መከራ በኋላም ከብዙ ተዓምራት ጋር ተሰይፎ ደም: ውሃና ወተት ከአንገቱ ፈሷል:: 7 አክሊላትም ወርደውለታል::

"ዝርወተ ዓጽሙ"

ይህቺ ዕለት ለሰማዕቱ 'ዝርወተ አጽሙ' ትባላለች:: በቁሙ 'አጥንቱ የተበተነበት' እንደ ማለት ነው:: ቅዱስ ጊዮርጊስን ለዘመናት በብዙ ስቃያት ሲያስጨንቁት ኖረው በጽናቱ አሸነፋቸው:: 70 ነገሥታትን ከነ ሠራዊታቸው ከማሳፈሩ ባሻገርም በርካታ (በመቶ ሺ የሚቆጠሩ) አሕዛብን ማርኮ ለሰማዕትነት አበቃ::

በዚህ የተበሳጨ ዱድያኖስም ኮከበ ፋርስ ቅዱስ ጊዮርጊስን እንዲቆራርጡት አዘዘ:: ወታደሮቹም ቅዱሱን ቆራርጠው በብረት ምጣድ ላይ ጠበሱት:: ያለ ርሕራሔም አካሉን አሳረሩት:: ቀጥለውም ፈጭተው አመድ አደረጉት::

በአካባቢው ወደ ነበረው ትልቅ ተራራ ጫፍ (ደብረ ይድራስ) ወጥተውም በነፋስ በተኑት:: "ሐረድዎ ወገመድዎ: ወዘረዉ ሥጋሁ ከመ ዓመድ" እንዲል:: (ምቅናይ)

እነርሱ ይህንን ፈጽመው ዘወር ሲሉ ግን የቅዱሱ ዓጽም ባረፈባቸው ዛፎች: ቅጠሎችና ድንጋዮች ሁሉ "ቅዱስ ጊዮርጊስ ሊቀ ሰማዕታት" የሚል ጽሑፍ ተገኘ:: ስለዚህም ይህቺ ዕለት ቅዱሱ አለቅነትን የተሾመባት ናት ማለት ነው::

ወዲያው ግን ኃያል ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ ከተበተነበት ተነስቶ ወታደሮችን አገኛቸውና "በክርስቶስ እመኑ" ብሎ: አስደንቆ ወደ ሕይወት መራቸው:: 70ው ነገሥታት ግን አፈሩ::

ዝክረ ቅዱሳን
ወስብሐት ለእግዚአብሄር

#Share
@Gedamaweyan         @Gedamaweyan
@Gedamaweyan         @Gedamaweyan

ገዳማውያን

20 Jan, 04:35


ወይን እኮ የላቸውም ብለሽ የለምንሽልን

🎙ዘማሪ ገብረዮሀንስ

ገዳማውያን

19 Jan, 18:48


ቃና ዘገሊላ

ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በጥር ፲፪ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቃና ዘገሊላ በተደረገ ሠርግ ቤት ያደረገውን ተአምር በማሰብ በዓልን ታደርጋለች፡፡ ጌታችን ከጥምቀቱ በኋላ በዶኪማስ ሠርግ ቤተ
ከእናቱ ቅድስት ድንግል ማርያም እንዲሁም ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ታጋብዞ በነበረበት ጊዜ ለእንግዶች ወይን ጠጅ አለቀባቸው፡፡ በዚህም ጊዜ “እናቱ ጌታችን ኢየሱስን የወይን ጠጅ እኮ የላቸውም” አለችው፡፡ ጌታችን ኢየሱም “ አንቺ ሆይ ካንቺ ጋር ምን አለኝ? ጊዜዬ ገና አልደረሰም” አላት፡፡ እናቱም ለአሳላፊዎቹ “የሚላችሁን ሁሉ አድርጉ” አለቻቸው፡፡ በዚይም እንደ አይሁድ ልማድ የሚያነጹባቸው ስድስት የድንጋይ ጋኖች ነበሩ፡፡ ከእነርሱም እያንዳንዱ ሁለት ወይም ሦስት እንስራ ይይዙ ነበር፡፡ ጌታችን ኢየሱስም “ጋኖቹን ውኃ ሙሉአቸው” አላቸው፤ እስከ አፋቸውም እስከ ላይ ሞሉአቸው፡፡ አሁንም ቅዱና ወስደውም ሰጡት፡፡ አሳዳሪውም ያን የወይን ጠጅ የሆነውን ውኃ ቀምሶ አደነቀ፤ ከወዴት እንደመጣም አላወቀም፤ የቀዱት አሳላፊዎች ግን የወይን ጠጅ የሆነውን ያን ውኃ ያውቁ ነበር፡፡ ውኃውን የሞሉ እነርሴ ነበሩና፡፡ አሳዳሪውም ሙሽራውን ጠርቶ “ሰው ሁሉ መልካሙን የወይን ጠጅ አስቀድሞ ያጠጣል፤ ከጠገቡ በኋላም ተርታውንም ያመጣል፤
አንተ ግን መልካሙን የወይን ጠጅ እስከአሁን አቆየህ” አለው፡፡ ጌታችን ኢየሱስም በቃና ዘገሊላ ያደረገው የተአምራት መጀመሪያ ይህ ነው፤ ክብሩንም ገለጠ፤ ደቀ መዛሙርትም አመኑበት፡፡ (ዮሐ.፪፥፩-፲፩)
ከበዓሉ በረከት ያሳትፈን፤ አሜን፡፡

©ማኀበረ ቅዱሳን

ሼር ያድርጉ

ገዳማውያን

19 Jan, 16:53


†        †        †


❝ ያን ጊዜ ኢየሱስ በዮሐንስ ሊጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ መጣ። ❞ — [ ማቴዎስ ፫፥፲፫ ]

                      🌸                     


እንኳን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ጥምቀት በሰላምና በጤና አደረሳችሁ

Congratulations on the baptism of our Lord and Savior Jesus Christ in peace and health

Baga gooftaa fi fayyisaa keenya Iyyasuus Kiristoos nagaa fi fayyaan cuuphame

እንኳዕ ጥምቀት ጎይታናን መድሓኒናን ኢየሱስ ክርስቶስ ብሰላምን ብጥዕናን ኣብጽሓና።

تهانينا على معمودية ربنا ومخلصنا يسوع المسيح بسلام وصحة
Félicitations pour le baptême de notre Seigneur et Sauveur Jésus-Christ dans la paix et la santé

Herzlichen Glückwunsch zur Taufe unseres Herrn und Erlösers Jesus Christus in Frieden und Gesundheit

🤲🏼💐

[ TMC ]

ገዳማውያን

19 Jan, 03:08


በዓለ ጥምቀት

እንኳን አደረሳችሁ!

ጥምቀት ሥርዓቱ ከብሉይ ኪዳን ይጀምራል፡፡ አንድ አይሁድነትን ያልተቀበለ አዲስ ሰው ወደ ይሁዲነት ሲመጣ ከማኅበረ አይሁድ ከመቀላቀሉ አስቀድሞ ግዝረትን እና በውኃ  መታጠብን (መጠመቅ) እንዲፈጽም ይደረጋል፡፡ ይህም ለመንጻት ሥርዓት በዘሌዋውያን ካህናት  አማካኝነት  ይፈፀም ነበር፡፡ ውኃ መንጽኢ ነውና ማንም ሰው በተለያየ ምክንያት ቢረክስ  የሚነጻበት  (የኅፅበት) ሥርዓት ለእያንዳንዱ  ምክንያት ነበረው፡፡  (ዘሌ. ፲፬፥፲፭-፳፪) ይህንንም ተዘርዝሮ እናገኘዋለን፡፡ ይህም በእውነት በውኃ ላይ የእግዚአብሔር  መንፈስ እንዳደረበት  ያስረዳል፡፡ (ዘፍ.፫፥፪) ተያይዞ እስከ ዘካርያስ ልጅ ቅዱስ ዮሐንስ ደርሷል፡፡

በመልአኩ  ቅዱስ ገብርኤል  ብሥራት የተወለደው  ጻድቅ፣ ቅዱስ ሐዋርያ ሰማዕት፣ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ የዮሐንስ በረሃ በሚባለው እና ከሕፃናቱ ጀምሮ ባደገበትምድረ በዳ በሚገኝ ዋሻ ውስጥ በብሕትውና ተወስኖ ሲኖር ቆይቶ ለክርስቶስ  መንፈቅ ሲቀረው  በ፴  ዘመኑ የዮርዳኖስ  አውራጃ  በምትሆን በይሁዳ  ‹‹ነስሑ  እስመቀርበት መንግሥተ ሰማያት፤ መንግሥተ ሰማያት በልጅነት፣  ልጅነት  በሃይማኖት ልትሰጥ ቀርባለችና በወንጌል አምናችሁ ንስሐ እያለ ሰበከ፤ በነቢይ ‹‹የጌታን መንገድ አዘጋጁ፤  ጥርጊያውንም አቅኑ  እያለ  በምድረ በዳ  የሚጮህ  ሰው ድምፅ›› እንደ  ተባለለት፡፡ (ኢሳ.፵፥፫፣ማቴ.፫፥፫)

ቃሉን የተቀበሉም ስለ ኃጢአት ስርየት ኃጢአታቸውን እየተናዘዙ በፈለገ ዮርዳኖስ በእደ ዮሐንስ ይጠመቁ ነበር፡፡ ይህም አማኞችን  ለክርስቶስ  ጥምቀት የሚያዘጋጅና በእግዚአብሔር  መንግሥት ውስጥ ለመሆን የሚያበቃ ነበር፡፡ ‹‹እኔስ ለንስሐ በውኃ አጠምቃችኋለሁ፤ ጫማውን እሸክም ዘንድ የማይገባኝ ከእኔ በኋላ የሚመጣው ግን ከእኔ ይበረታል፤  እርሱ በመንፈስ ቅዱስና በእሳት ያጠምቃችኋል›› (ማቴ.፫፥፲፩) ክርስቶስም ናዝራዊ ከተባለበት (ማቴ. ፥፳፫) ከናዝሬት  ወደ ዮርዳኖስ  ጥር ፲፩   ቀን  ወረደ፤  ቅዱስ  ዮሐንስም  ስለ  እርሱ  መሰከረ  ‹‹ነዋ በግዑ ለእግዚአብሔር  ዘያአትት ወያሴስል ኃጢአተ ዓለም፤ እነሆ  የዓለምን ኃጢአት  የሚያስወግድ የእግዚአብሔር  በግ፡፡›› (ዮሐ.፩፥፳፱)

ዮሐንስም ክርስቶስ በእርሱ እንዲጠመቅ መምጣቱን ባየ ጊዜ ወትሮ ባሪያ ወደ ጌታው ይሄዳል  እንጂ እንዴት ይህ ይሆናል?  አለው፤ ትሕትናን ከእናቱ ተምሯልና፤  ‹‹የጌታዬ  እናት ወደ  እኔ ትመጣ ዘንድ  እንዴት  ይሆንልኛል?››  እንዳለች ቅድስት ኤልሳቤጥ፡፡ (ሉቃ.፩፥፵፫)  ደግሞስ ሌላውን ሁሉ በስምህ አጠምቃለሁ፤  አንተን  በማን ስም አጠምቃለሁ?  ቢለው  ‹‹ወልዱ  ለቡሩክ ከሣቴ ብርሃን ተሣሃለነ››፤ ‹‹አንተ  ካህኑ ለዓለም በከመ  ሢመቱ  ለመልከ  ጼዴቅ››  ብለህ  አጥምቀኝ ብሎታል፤  ብርሃንን  የምትገልጥ የቡሩክ  አብ የባሕርይው  ልጅ ይቅር  በለን፤  እንደ  መልከ  ጼዴቅ  የዓለም ሁሉ ካህን  አንተ  ነህ››  እያልክ  አጥምቀኝ ብሎታል፤  ከዚያም ዮሐንስ ሊያጠምቀው ወደ ዮርዳኖስ ገብቷል፡፡

ዮርዳኖስ  የጥምቀቱ ቦታ  እንዲሆን  ጌታ የፈቀደው  አስቀድሞ  ትንቢት  አናግሮ  ምሳሌ መስሎ ‹‹ባሕርኒ ርእየት ወጎየት ወዮርዳኖስኒ ገብአ ድኅሬሁ ርእዩከ ማያት እግዚኦ  ርእዩከ ማያት ወፈርሁ፤ አቤቱ ውኆች አዩህ፤ ውኆችም አይተውህ ፈሩህ፤ ጥልቆችም ተነዋወጡ፤ ውኆችም ጮሁ፡፡›› (መዝ. ፸፮፥፲፮) ‹‹ባሕር  አየች፤  ሸሸችም፤  ዮርዳኖስም  ወደ ኋላ  ተመለሰ፤››  (መዝ.፻፲፫፥፫) ዮርዳኖስ መነሻው ከላይ ነቁ፤ አንድ ነው፤ ዝቅ ብሎ በደሴት ይከፈላል፤  ከታች ወርዶ ይገናኛል፡፡ የሰውም ልጅ አባቱ አንዱ አዳም ሲሆን እስራኤልና  አሕዛብ በግዝረት በቁልፈት  ተለያይተዋልና፡፡ ከታች ወርዶ እንደገና በወደብ እንዲገናኝ ሕዝብ እና አሕዛብ  በክርስቶስ  ጥምቀት አንድ  ሆነዋል፤  ከዚህም  የተነሣ  ጌታ የሁለቱ  ወንዝ  መጋጠሚያ  ላይ  በመጠመቅ አንድነታችንን  መልሶልናል፡፡  ይህንን  ውለታ በማሰብ (ይህን  የነጻነት  በዓል)  እናከብራለን፡፡

ከዚህም በላይ  የሥላሴ  ምሥጢር እኛ በምንረዳው መልኩ ያየንበትን በዓል የዕዳ ደብዳቤያችን የተፋቀበትን ቀን፣ ነጻነታችንን ያወጅንበትን፣ የእግዚአብሔር  ልጆች የሆንበትን  ዕለት  ከበዓልም  የሚበልጥ  ዐቢይ  በዓል  አድርገን  አናከብረዋለን፡፡  ይህንንም  ቀን  ቀድሶ  የሰጠን  ቅዱስ አምላክ ምስጋና ይድረሰው፤ አሜን፡፡🤲🏻
ከበዓሉ በረከት ረድኤት ያሳትፈን!🤲🏻💐

#Share
@Gedamaweyan         @Gedamaweyan
@Gedamaweyan         @Gedamaweyan

ገዳማውያን

18 Jan, 04:16


ጾመ ገሀድ

  በየኔታ ዘለዓለምሐዲስ



ከዘጠኙ ዓበይት የጌታ በዓላት ሁለቱ የልደትና የጥምቀት በዓላት ተጠቃሾች ናቸው  በሁለቱ በዓላት ቀን ክርስቲያን የሆነ ሁሉ በኀዘን ማሳለፍ እንደሌለበት ቅዱሳት መጻሕፍት ይናገራሉ ምክንያቱም የክርስቶስ ልደትና ጥምቀት የዕዳ ደብዳቤያችን የተቀደደባቸው የድኅነታችን መሠረት የተጣለባቸው ዐበይት በዓላት  ስለሆኑ ነው እነዚህ በዓላት በረቡዕና በዓርብ ቀን ከዋሉ አስቀድመን በዋዜማው ለውጥ አድርገን እንጾማቸዋለን ልደት ረቡዕ ከሆነ ማግሰኞ በዋዜማው፣ ዓርብ ከሆነ ሐሙስ በዋዜማው እስከምሽቱ አንድ ሰዓት (13 ሰዓት) እንጾማቸዋለን በሌሎችም ቀናት በዋዜማቸው በየዓመቱ ይጾማሉ ቀናቱ ሁለት ቢሆኑም  ቁጥራቸው ግን ከሰባቱ አጽዋማት አንዱ ተብለው ነው የሚቆጠሩት፡፡
ገሀድ ሁለት መጠሪያ ስሞች አሉት ገሀድና ጋድ፡፡ ገሀድ ማለት መገለጥ መታየት መታወቅ ማለት ነው ተገለጠ ታየ ታወቀ የተባለውም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው ምንም ከዚያ በፊት አምላክነቱ የተገለጠባቸው ብዙ መንገዶችና ተአምራት ቢኖሩም አብ በደመና ሁኖ የምወደው ልጄ ይህ ነው በማለት፣ መንፈስ ቅዱስም በርግብ አምሳል ወርዶ በራሱ ላይ በመቀመጥ የክርስቶስ አምላክነት የተገለጠበት ዕለት ስለሆነ ገሀድ መገለጥ ተብሎ ተሰይሟል
በሌላም በኩል ጋድ ማለት ለውጥ ማለት ነው ልደትና ጥምቀት ረቡዕና ዓርብ ሲሆኑ ለውጥ ሁኖ የሚጾምበት ማለት ነው ስለዚህ ገሀድ ስንል የክርስቶስን አምላክነት በዕለተ ጥምቀት መገለጥ፣ ጋድ ስንል ደግሞ ለዓርብና ለረቡዕ ጾም ለውጥ ሁኖ የተጾመውን ጾም ማለታችን ነው፡፡ ይህንን ጾም ጥር 10 ቀን የሚነበበው ስንክሳር እንዲህ ሲል ይገልጸዋል፡፡
ወበእንተዝ አዘዙነ አበዊነ ከመ ይደሉ ንጹም እሎንተ ክልኤተ ዕለታተ ዘእምቅድመ በዓለ ልደት ወበዓለ ጥምቀት እስመ እላ ዕለታት ህየንቴሆሙ ለረቡዕ ወዓርብ ሶበ ይከውን ላዕሌሆሙ በዓለ ልደት ወጥምቀት ወበዝንቱ ይትፌጸም ለነ ክልኤቱ ግብር ግብረ ጾም ወግብረ በዓል ወከመዝ ሥሩዕ ውስተ አብያተ ክርስቲያኖሙ ለግብፃውያን
ወለእመ ኮነ ዕለተ በይረሙን ዘውእቱ አስተርእዮ በዕለተ እሑድ አው በዕለተ ሰንበተ አይሑድ ይጹሙ በዕለተ ዐርብ እምቅድሜሁ እስከ ምሴት በከመ ተናገርነ ቅድመ ወለእመ ኮነ በዓለ ልደት ወበዓለ ጥምቀት በዕለተ ሰኑይ ኢይትከሀል ከመ ይጹሙ በዕለተ ሰንበት ዳዕሙ ይትዐቀቡ እምነ በሊዕ ጥሉላተ፡፡ 
ስለዚህ ከልደትና ከጥምቀት በዓል በዋዜማ ያሉትን ሁለቱን ዕለታት እንድንጾም አዘዙን የልደትና የጥምቀት በዓል በረቡዕና በዓርብ ላይ በሚሆን ጊዜ በረቡዕና በዓርብ ፈንታ እንድንጾማቸው ይገባልና በዚህም ሁለት ሥራ ይፈጸምልናል የጾም ሥራና የበዓል ማክበር ሥራ ነው እንዲሁም በግብፃውያን አብያተ ክርስቲያን የተሠራ ነው
በይረሙን (መገለጥ፣ ገሀድ) በእሑድ ወይም በአይሁድ ሰንበት ቀን ቢሆን ይህም ጌታ የተገለጸበት ጥር ዐሥር ቀን ነው በዋዜማው ዓርብ እስከምሽት ይጹሙ አስቀድመን እንደተናገርን ጥሉላትን ከመብላት ይጠበቁ፡፡ በማለት ይገልጸዋል፡፡
ከላይ እንዳየነው ጥምቀት ወይም ልደት እሑድና ቅዳሜ ከዋሉ ጾሙ መጀመር ያለበት ዓርብ መሆኑን ተመልክተናል ይህንም መነሻ በማድረግ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ጥምቀት ሰኞ ሲሆን ዓርብ እስከ አንድ ሰዓት፣ ቅዳሜ እስከ ስድስት፣ እሑድ እስከ ቅዳሴ መውጫ እስከ ሦስት በመቁጠር የጾሙን ሰዓት 13 ሰዓት ያደርጉታል ይህም ከላይ የተገለጠውን ስንክሳር መነሻ በማድረግ የመሚናገሩት ስለሆነ አክብረን እንቀበለዋለን ቅዳሜ እስከ ስድስት ለመጾሙም ሃይ ምዕ 20 ተጠቃሽ ነው  
በሌላ በኩልም ጋድ አንድ ቀን ነው ሰኞ ሲሆን እሑድን ብቻ ከጥሉላት እንከለከላለን እንጅ ቅዳሜን አይጨምርም በማለት ይህን የሚቃወሙ አሉ ስንክሳር የተናገረውን ምን እናድርገው ተብለው ሲጠየቁም ስንክሳር የታሪክ እንጅ የሥርዓት መጽሐፍ አይደለም የሚል መልስ ነው የሚሰጡት፡፡ ይህ ጥያቄ ወደሌሎች ሊቃውንት ሲቀርብ የሚሰጡት መልስ ደግሞ ስንክሳር ታሪክ ብቻ ሳይሆን ሥርዓትም የተካተተበት መጽሐፍ መሆኑን ይናገራሉ በእርግጥ ስንክሳር ማለት እስትጉቡእ ስብስብ ማለት ስለሆነ ሥርዓተ ቤተ ክርስተቲያንን ከሠሩ አበው ታሪክ የተሰበሰበ መሆኑን መዘንጋት የለብንም ከላይም እንዳየነው ወበእንተዝ አዘዙነ አበዊነ ስለዚህ አባቶቻችን አዘዙን በማለት ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን የጻፉ አበው አዘዙን አለ እንጅ ስንክሳርን የጻፉ ሰዎች የራሳቸውን ሐሳብ ያንጸባረቁበት አይደለም ስንክሳርም ቢሆን ምንም ቁጥሩ ከአዋልድ መጻሕፍት ቢሆን የቤተ ክርስቲያን መጽሐፍ ነውና ጥምቀትና ልደት ሰኞ ከሆኑ ቅዳሜና እሑድን ከጥሉላት ተከልክለን ቅዳሜንም እስከ ስድስት ሰዓት ጹመን የአበውን ትዕዛዝ ማክበር አለብን፡፡
በሌላም በኩል ጋድ አንድ ነው እሱም የጥምቀት ዋዜማ ብቻ ነው የልደት ዋዜማ የለውም የሚሉም አሉ   እንዲህ ለሚሉት መልሱ አጭር ነው ጾመ ነቢያት ስንት ነው የሚል ጥያቄ ማንሣት ነው እንደሚታወቀው ጾመ ነቢያትን ስንጾም ቀናቱ አርባ አራት ናቸው 40 ጾመ ነቢያት፣ 3ቱ የፊልጶስ ደቀ መዛሙርት የጾሙትና አብርሐም ሦርያዊ ተራራ ያፈለሰበት ጾም፣ አንዱ ጾመ ገሀድ ነው ስለዚህ በበዓለ ልደት ዋዜማ የምንጾመው ገሀድ መሆኑን ሁሉም የሚያውቀው ሀቅ ነው፡፡


"" መልሱ እንዲህ ከምስክር መምህራን ሲሆን ይሻላል፡፡ እኛ ከምንናገረው፡፡
የኔታ ዘለዓለም ሐዲስ ማለት የክቡር ሊቀ ሊቃውንት ዕዝራ ሐዲስ ምክትልና የ፬ቱ መጻሕፍተ ትርጓሜ መምህር ናቸው፡፡ (እንዲያው የኔ ብጤ የፌስቡክ አርበኛ እንዳይመስሉህ ብዬ ነው!)
      Dn Yordanos


ዝክረቅዱሳን (ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት)

" ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::/የቅዱሳንን ዜና(ታሪክ) እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል::
       አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/

ገዳማውያን

17 Jan, 15:39


አንተኑ ብለው ነው ግጥም

🎙ቢንያም ብርሐኑ እንዳነበበው

📚ከደንገጡሯ እመቤት መጽሐፍ የተወሰደ

የመጽሐፉ ጽሐፊ :-  ዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ እና ትግስት ታፈረ

ገዳማውያን

17 Jan, 04:35


                                              

        🥀    ጾ መ ገ ሃ ድ       
🥀

የዚህ ዓመት የገሃድ ጾም የራሱ አዋጅ አለው ስንክሳር ዘጥር ፲ እንዲህ ብሎ ያዛል ፦

❝ ወለእመ ኮነ ዕለተ በይረሙን ዘውእቱ አስተርእዮ በዕለተ እሁድ አው በዕለተ ሰንበተ አይሁ ይጹሙ። በእለተ ዓርብ እምቅድሜሁ እስከ ምሴት በከመ ተናገርነ ቅድመ ዳዕሙ ይትዓቀቡ እምነ በሊዕ ጥሉላተ። ❞

በዚህ ዓመት

ጥምቀት እሁድ ስለዋለ አስቀድሞ ነገ አርብ እስከ 12 [ ፲፪ ] ሰአት ይጾማል። በዋዜማው ደሞ ቅዳሜ ከቅዳሴ በኃላ ምግብ መመገብ ይቻላል። ግን ጥሉላት አይበሉም። ሥጋ ፣ ወተትና የወተት ተዋጽኦን ከመሰሉ የፍስክ ምግቦች እንጾማለን።

ገዳማውያን

15 Jan, 04:07


                        †                             

†          ዘላለም  ሥላሴ        †


እንኩዋን ለአጋእዝተ ዓለም ሥላሴ  ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ  🤲


❝ በሥላሴ ገመድ ፍጹም ታስረናል ፤ ከልባችን በማይነቀል በቅንዋተ ፍቅሩ ተቸንክረናል ፣ እርሱ ወዶናል አይጠላንም። እኛም በእምነት ይዘነዋል አንተወውም። ❞

[  አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ  ]

🕊

❝ እምነታችንም እንዲህ በባሕርይ በመለኮት አንድ ፤ በአካል ፤ በገጽ ሦስት ብለን ነው፡፡ እነዚህ በቅድምና የነበሩ አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ናቸው፡፡ አስቀድመን መላልሰን እንደ ተናገርን ቀዳማዊ ወልድ ሰው ስለ መሆኑና ስለ ቅድስት ሥላሴ የምናምነው እምነት ይህ ነው ፤ ከተማሩ ከሚያስተምሩ ተስፋን ከሚያስረዱ ቅዱሳን ሊቃውንት ለምዕመናን ሁሉ ገልጠን የምናስተምረው ፤ እውነተኛ ሃይማኖትን ከሚያስተምሩ የሰማይ አምላክ ከሾማቸው ከሐዋርያትም ሲያያዝ የመጣልን እጅ ያደረግነው እምነት ነው፡፡ በንጹሕ ልቡና በአፋችንም በልባችንም በዚህ ሃይማኖት እንመን ፤ ያለ ጥርጥርም በበጎ ግብር በቅን ሕሊና እናስተውል ፤ በዚህ እንድንድን መንግሥተ ሰማያትንም እንድንወርስ እንረዳለን፡፡ ❞

[    ሃይማኖተ አበው   ]

🕊

ጥር ፯ [ 7 ] ፦

ሕንጻ ሰናዖርን ማፍረሳቸውና ቅዳሴ ቤታቸው በዓል ይከበራል።

የሰናዖርን ሕንጻ ያፈረሱ ሥላሴ : የኃጢአታችንን ሕንጻም በቸርነታቸው ያፍርሱልን . . . አሜን !🤲💐

ገዳማውያን

11 Jan, 18:22


❤️እንኩዋን ለፍቁረ እግዚእ ዮሐንስ ሐዋርያ: ወልደ ነጐድጉዋድ ዓመታዊ የፍልሠት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ❤️

እናት ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ዮሐንስን ስትጠራው እንዲሕ ነው:-

🦅🦅🦅🦅🦅🦅🦅🦅🦅🦅

*ወንጌላዊ
*ሐዋርያ
*ሰማዕት ዘእንበለ ደም
*አቡቀለምሲስ (ምሥጢራትን ያየ)
*ታኦሎጐስ (ነባቤ መለኮት)
*ወልደ ነጐድጉዋድ
*ደቀ መለኮት ወምሥጢር
*ፍቁረ እግዚእ
*ርዕሰ ደናግል (የደናግል አለቃ)
*ቁጹረ ገጽ
*ዘረፈቀ ውስተ ሕጽኑ ለኢየሱስ (ከጌታ ጎን የሚቀመጥ)
*ንስር ሠራሪ*ልዑለ ስብከት
*ምድራዊው መልዐክ
*ዓምደ ብርሐን
*ሐዋርያ ትንቢት
*ቀርነ ቤተ ክርስቲያን
*ኮከበ ከዋክብት


=>በቅዱስ ዮሐንስ ላይ ያደረ የእመቤታችን ድንግል ማርያምና የአንድ ልጇ ፍቅር በእኛም ላይ ይደር::

=>ቅዱስ ዮሐንስን የወደደ ጌታ በፍቅሩ ይጠግነን:: ከእናቱ ፍቅር አድርሶ በሐዋርያው በረከት ያስጊጠን::🤲

ገዳማውያን

06 Jan, 18:01


እንኳን ለብርሃነ ልደቱ አደረሳችሁ
          "አንበሳ ተንሥአ እምገዳም
           ውእቱኬ ወልድ ውእቱ"
ድንግል ማርያም ገዳመ ዕዝራ ናት። ዕዝራ ከገዳም አንበሳ ሲወጣ አይቷል። አንበሳ የተባለ ክርስቶስ ነው።

አንበሳ ሲጮኽ አራዊት ጸጥ ይላሉ። ክርስቶስ ሲናገር አጋንንት ይጠፋሉ። በጨለማ ለነበረች ዓለም ብርሃን ተወለደላት። በባርነት ለነበረች ዓለም ነጻነቷን የሚያጎናጽፋት አምላክ በሥጋ ተወለደላት።

ዮም ተወልደ እግዝእነ
ዮም ተወልደ አምላክነ
ዮም ተወልደ ቤዛነ
ዮም ተወልደ ሕይወትነ
ዮም ተወልደ ትምክህትነ
ዮም ተወልደ ፍሥሓነ

የጌታ ልደት ለእኛ ለሰው ልጆች ሁሉ ልዩ ቀን ናት።
በድጋሚ እንኳን አደረሳችሁ።

© በትረ ማርያም አበባው

ገዳማውያን

01 Jan, 18:43


​​አቡነ ተክለ ሃይማኖት ጻድቅ

ቅዱሳን ጻድቃን በመንፈሳዊ አርአያነታቸው፣ በጸሎታቸውና በትምህርታቸው ከከበቡን የነፍስ ጠላቶች፤ ከርኲሳን መናፍስትና ከጨለማው ልጆች፣ ከክፉ ሰዎች ሽንገላና ተንኰል ለመሰወርና ለመጠበቅ ከእግዚአብሔር የተቀበሉት ሥልጣን ምን ጊዜም ይሠራል፡፡ በጻድቃን መኖር ሀገር ከጥፋት ትድናለች፡፡ የጻድቃንን ስም ጠርቶ እግዚአብሔርን በመለመን በረከትና ረድኤት ይገኛል፡፡ ስለ ጻድቃን ብሎ እግዚአብሔርም ምሕረቱን ያድላል፡፡ ጻድቃንን ማሰብ ሥራቸውን መዘከር ክርስቲያናዊ ሕይወታችንን ያጐለምሳል፡፡ በነፍስ በሥጋ ይታደገናል፤ ይረባናል፤ ይጠቅመናል፡፡

ስለዚህም ነው ቤተ ክርስቲያናችን ጻድቃንን እንድናስባቸው፣ በስማቸውም ለድሆችና ለጦም አዳሮች እንድንመጸውት፣ መታሰቢያቸውን እንድናደርግ የምትመክረን፤ የምታስተምረን /ማቴ.፲፥፵፩-፵፪/፡፡ ቅዱሳን ጻድቃን በሕይወተ ሥጋ ሳሉም ኾነ ከሞቱ በኋላ በዐጸደ ነፍስ ኾነው በጸሎታቸው ለሚታመኑ፣ በቃል ኪዳናቸው ለሚማጸኑ ምእመናን በመጸለይና ወደ እግዚአብሔር በማማለድ ድኅነተ ሥጋ፣ የድኅነት ነፍስን የሚያስገኙልን የችግር ጊዜ አማላጆቻችንና አስታራቂዎቻን ናቸው፡፡ ከእነዚህ ቅዱሳን መካከል ኢትዮጵያዊው ጻድቅ አቡነ ተክለ ሃይማኖት አንደኛው ናቸው፡፡

‹ተክል› ማለት ፍሬያማ ዕንጨት፣ ዛፍ፣ ቅመም፣ ቅጠላ ቅጠል፣ የሚበላ፣ የሚሸተት፣ ገነታዊ ዕፅ፣ እንዲሁም ሕግ ሥርዓት ማለት ነው /ማቴ.፲፭፥፲፫/፡፡ ‹ሃይማኖት› ማለት ደግሞ በሀልዎተ እግዚአብሔር፣ እግዚአብሔር የዅሉ አስገኚ መኾኑን፣ በሥላሴ አንድነትና ሦስትነት፣ በቅዱሳን ተራዳኢነት ማመን አምኖም መመስከር ማለት ሲኾን ተክለ ‹ሃይማኖት› የሚለው ሐረግም የሃይማኖት ተክል፣ ይኸውም የጽድቅ ፍሬን ያፈራ፣ ከኃጢአት ሐሩር ማምለጫ ዛፍ፣ ምእመናንን በቃለ ወንጌል ያጣፈጠ ቅመም፣ መዓዛ ሕይወቱ የሚማርክ፣ ቢመገቡት ረኃበ ነፍስን የሚያስወግድ ቅጠል፣ የጻድቃን መጠለያ ዕፅ የሚል ትርጕም አለው፡፡ ገድለ ተክለ ሃይማኖትም ‹‹ተክለ ሃይማኖት ማለት የአብ፣ የወልድ፣ የመንፈስ ቅዱስ ተክል ማለት ነው›› ሲል የጻድቁን ስም ይተረጕመዋል፡፡

ጻድቁ አባታችን ሕይወታቸዉን ሙሉ ለእግዚአብሔር በመስጠት፣ እንደ በሬ ተጠምደው፣ እንደ ገበሬ ታጥቀው፣ ይህንን ዓለም ንቀው፣ በጾም በጸሎት ተወስነው በብሕትውና በመኖራቸው፤ እርሳቸው በአሚነ ሥላሴ ጸንተው ሌሎችንም እንዲጸኑና እንዲያምኑ በማድረጋቸው፤ እንደዚሁም እንደ ቅዱሳን ሐዋርያት ወንጌልን በመላው ኢትዮጵያ እየተዘዋወሩ በመስበክ በጌታችን በመድኀኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ድውያነ ሥጋን በተአምራት፣ ድውያነ ነፍስን በትምህርት የፈወሱ ሰባኬ ወንጌል በመኾናቸው ‹‹ተክለ ሃይማኖት›› ተብለው ይጠራሉ፡፡

አቡነ ተክለ ሃይማኖት በእግዚአብሔር ድንቅ ጥበብ፣ በሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ብሥራት፤ በኢትዮጵያ ምድር በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ልዩ ስሙ ኢቲሳ በሚባል ቦታ ከአባታቸው ከካህኑ ጸጋ ዘአብና ከእናታቸው ከቅድስት እግዚእ ኀረያ መጋቢት ፳፬ ቀን ተፀንሰው ታኅሣሥ ፳፬ ቀን ፲፪፻፲፪ ዓ.ም ተወለዱ፡፡ በተወለዱ በሦስተኛው ቀን እሑድ ከጠዋቱ ሦስት ሰዓት ከእናታቸው ዕቅፍ ወርደው ‹‹አሐዱ አብ ቅዱስ፤ አሐዱ ወልድ ቅዱስ፤ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ፤ አንዱ አብ ቅዱስ ነው፤ አንዱ ወልድ ቅዱስ ነው፤ አንዱ መንፈስ ቅዱስ ቅዱስ ነው›› በማለት ሥላሴን አመስግነዋል፡፡

ወላጆቻቸው ያወጡላቸው ስም ‹‹ፍሥሐ ጽዮን›› የሚል ሲኾን ‹‹ተክለ ሃይማኖት›› ደግሞ የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ያወጣላቸው ስም ነው፡፡ በተወለዱ በ፲፭ ዓመታቸው ዲቊናን፤ በ፳፪ ዓመታቸው ደግሞ ቅስናን ከግብፃዊው ጳጳስ ከአባ ጌርሎስ (ቄርሎስ) ተቀብለዋል፡፡

አንድ ቀን ወደ ጫካ ለአደን በሔዱበት ዕለት ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱ ክርስቶስ ተገልጦላቸው ጸጋ መንፈስ ቅዱን ካሰደረባቸው፤ እንደዚሁም ‹ሐዲስ ሐዋርያ› ብሎ ወንጌል ወዳልተዳረሰበት ቦታ እንደሚልካቸው ከነገራቸው፤ ቅዱስ ሚካኤልም ከአውሬ አዳኝነት ሰውን ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ለመመለስ እንደ ተመረጡና አጋንንትን የማውጣት፣ ተአምራትን የማድረግ ሥልጣን እንደ ተሰጣቸው፤ ስማቸውም ‹ተክለ ሃይማኖት› እንደሚባልና ትርጓሜውም ተክለ አብ፣ ተክለ ወልድ፣ ተክለ መንፈስ ቅዱስ ማለት እንደ ኾነ ካስረዳቸው በኋላ ወደ ቤታቸው ተመልሰው ያላቸውን ንብረት ኹሉ ለቤተ ክርስቲያንና ለነዳያን ሰጥተው ‹‹አቤቱ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ! የመንግሥተ ሰማያትን በር ትከፍትልኝ ዘንድ እነሆ ቤቴን እንደ ተከፈተ ተውኩልህ›› በማለት ቤታቸውን ትተው ወንጌልን ለማስተማር ፈጥነው ወጡ፡፡

ከዚያ ጊዜ ጀምረው በመላው ኢትዮጵያ እየተዘዋወሩ ወንጌልን በመስበክና ተአምራትን በማድረግ ብዙ አሕዛብን ከአምልኮተ ጣዖት ወደ አምልኮተ እግዚአብሔር፤ ከገቢረ ኀጢአት ወደ ገቢረ ጽድቅ መልሰዋል፡፡ ቤተ ክርስቲያንንም አንጸዋል፡፡ ‹ሐዲስ ሐዋርያ› የተባሉትም በዚህ ተልእኳቸው ሲኾን፣ ትርጕሙም ሐዲስ ኪዳንን ወይም ሕገ ወንጌልን እየተዘዋወረ የሚያስተምር ሰባኬ ወንጌል፤ በክርስቶስ ስም ድንቅ ድንቅ ተአምራትን የሚደርግ የክርስቶስ ተከታይ (ሐዋርያ) ማለት ነው፡፡

በአጠቃላይ አባታችን ተክለ ሃይማኖት ሕይወታቸዉን ሙሉ ለእግዚአብሔር በመስጠት፣ እንደ በሬ ተጠምደው፣ እንደገበሬ ታጥቀው ይህንን ዓለም ንቀው በጾም በጸሎት ተወስነው በብሕትውና ከመኖራቸው በተጨማሪ እንደቅዱሳን ሐዋርያት ወንጌልን በመላው ኢትዮጵያ እየተዘዋወሩ የሰበኩ፣ በጌታችን በመድኀኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ድውያነ ሥጋን በተአምራት፣ ድውያነ ነፍስን በትምህርት የፈወሱ ሐዋርያ ናቸው፡፡ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ከሚታወሱባቸው በዓላት መካከልም ታኅሣሥ ፳፬ ቀን የሚከብረው በዓለ ልደታቸው አንደኛው ነው፡፡ መጽሐፈ ስንክሳር ዜና ልደታቸውን ሲናገር ‹‹ብፁዕ ወቅዱስ ሐዲስ ሐዋርያ›› በማለት በክብር ጠርቷቸዋል፡፡

ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለደቀ መዛሙርቱ ‹‹እናንተን የሚቀበል እኔን ይቀበላል፤ እኔንም የሚቀበል የላከኝን ይቀበላል፡፡ ነቢይን በነቢይ ስም የሚቀበል የነቢይን ዋጋ ያገኛል፡፡ ጻድቅንም በጻድቅ ስም የሚቀበል የጻድቁን ዋጋ ያገኛል፡፡ ማንም ከእነዚህ ከተናናሾቹ ለአንዱ ቀዝቃዛ ጽዋ ብቻ በደቀ መዝሙር ስም የሚያጠጣ እውነት እላችኋለሁ፤ ዋጋው አይጠፋበትም፤›› /ማቴ.፲፥፵-፵፪/ በማለት የተናገረውን መለኮታዊ ቃል ኪዳን ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን መሠረት አድርጋ መጋቢት ፳፬ ቀን ፅንሰታቸውን፤ ታኅሣሥ ፳፬ ቀን ልደታቸውን፤ ጥር ፳፬ ቀን ሰባረ ዐፅማቸውን፤ ግንቦት ፲፪ ቀን ፍልሰተ ዐፅማቸውን፣ ነሐሴ ፳፬ ቀን ደግሞ ዕለተ ዕረፍታቸውን በመንፈሳዊ ሥርዓት በደስታ ታከብራለች፡፡

የአቡነ ተክለ ሃይማኖትና የኹሉም ጻድቃን ጸሎትና በረከት ረድኤትና ምልጃ በመላው ሕዝበ ክርስቲያን ላይ ለዘለዓለሙ ጸንቶ ይኑር፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡
ምንጭ፡- ማኅበረ ቅዱሳን

#Share
@Gedamaweyan         @Gedamaweyan
@Gedamaweyan         @Gedamaweya

ገዳማውያን

27 Dec, 16:10


#ሊቀ_መላእክት_ቅዱስ_ገብርኤል (#ታኅሣሥ_19)

ታኅሣሥ ዐስራ ዘጠኝ በዚህች ቀን ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ሠለስቱ ደቂቅ ያዳነበት ነው፡፡ ንጉሥ ናቡከደነፆር ከአባታቸው ከይሁዳው ንጉሥ ከኢዮአቄም ጋር የማረካቸው አናንያ፣ ሚሳኤልና አዛርያ እግዚአብሔር በዚህች ዕለት መልአኩን ልኮ ታላቅ ተአምር አድርጎላቸዋል፡፡

ንጉሥ ናቡከደነፆር እነዚህን ወጣቶች በቤተ መንግሥቱ ውስጥ ጥበብን እያስተማረ ካሳደጋቸው በኋላ በባቢሎን ሀገሮች ሁሉ ውስጥ ሾማቸው፡፡ ከዚህም በኋላ ንጉሡ የወርቅ ምስል በሠራ ጊዜ መኳንንቱንና በግዛቱ ውስጥ ያሉ ሁሉ ለዚያ ምስል እንዲሰግዱ አዘዘ፡፡ በዚህም ጊዜ ለጣዖቱ ባለመስገድ እግዚአብሔርን ብቻ በማምለክ የጸኑት እነዚህ ሦስት ወጣቶች ብቻ ነበሩ፡፡ ስለ እነርሱ በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ እንዲህ ተብሎ ነው የተጻፈው፡-
‹‹ንጉሡ ናቡከደነፆር ቁመቱ ስድሳ ክንድ ወርዱም ስድስት ክንድ የሆነውን የወርቁን ምስል አሠራ፤ በባቢሎንም አውራጃ በዱራ ሜዳ አቆመው፡፡ ንጉሡም ናቡከደነፆር መኳንንትንና ሹማምቶችን፥ አዛዦችንና አዛውንቶችን፥ በጅሮንዶችንና አማካሪዎችን፣ መጋቢዎችንም፣ አውራጃ ገዦችንም ሁሉ ይሰበስቡ ዘንድ፣ ንጉሡም ናቡከደነፆር ላቆመው ምስል ምረቃ ይመጡ ዘንድ ላከ፡፡ በዚያን ጊዜም መኳንንቱና ሹማምቶቹ፣ አዛዦቹና አዛውንቶቹ፣ በጅሮንዶቹና አማካሪዎቹ፣ መጋቢዎቹና አውራጃ ገዦቹ ሁሉ ንጉሡ ናቡከደነፆር ላቆመው ምስል ምረቃ ተሰበሰቡ፤ ናቡከደነፆርም ባቆመው ምስል ፊት ቆሙ፡፡ አዋጅ ነጋሪውም እየጮኸ እንዲህ አለ፡- ‹ወገኖችና አሕዛብ በልዩ ልዩ ቋንቋም የምትናገሩ ሆይ! የመለከትንና የእንቢልታን፣ የመሰንቆንና የክራርን፣ የበገናንና የዋሽንትን፣ የዘፈንንም ሁሉ ድምፅ በሰማችሁ ጊዜ፣ ተደፍታችሁ ንጉሡ ናቡከደነፆር ላቆመው ለወርቁ ምስል እንድትሰግዱ ታዝዛችኋል፡፡ ተደፍቶም የማይሰግድ በዚያን ጊዜ በሚነድድ እሳት እቶን ውስጥ ይጣላል፡፡› ስለዚህ በዚያን ጊዜ አሕዛብ ሁሉ የመለከቱንና የእንቢልታውን፣ የመሰንቆውንና የክራሩን፣ የበገናውንና የዘፈኑንም ሁሉ ድምፅ በሰሙ ጊዜ፣ ወገኖችና አሕዛብ በልዩ ልዩ ቋንቋም የተናገሩ ሁሉ ተደፉ፤ ንጉሡም ናቡከደነፆር ላቆመው ለወርቅ ምስል ሰገዱ፡፡

በዚያን ጊዜም ከለዳውያን ቀርበው አይሁድን ከሰሱ፡፡ ለንጉሡም ለናቡከደነፆር ተናገሩ እንዲህም አሉ ‹ንጉሥ ሆይ! ሺህ ዓመት ንገሥ፡፡ አንተ ንጉሥ ሆይ የመለከትንና የእንቢልታን፣ የመሰንቆንና የክራርን፣ የበገናንና የዋሽንትን፣ የዘፈንንም ሁሉ ድምፅ የሚሰማ ሰው ሁሉ ተደፍቶ ለወርቁ ምስል ይስገድ፤ ተደፍቶም የማይሰግድ በሚነድድ እሳት እቶን ውስጥ ይጣላል ብለህ አዘዝህ፡፡ በባቢሎን አውራጃ ሥራ ላይ የሾምሃቸው ሲድራቅና ሚሳቅ አብደናጎም የሚባሉ አይሁድ አሉ፤ ንጉሥ ሆይ! እነዚህ ሰዎች ትእዛዝህን እንቢ ብለዋል፤ አማልክትህን አያመልኩም፥ ላቆምኸውም ለወርቁ ምስል አይሰግዱም፡፡› ናቡከደነፆርም በብስጭትና በቍጣ ሲድራቅንና ሚሳቅን አብደናጎንም ያመጡ ዘንድ አዘዘ፤ እነዚህንም ሰዎች ወደ ንጉሡ ፊት አመጡአቸው፡፡ ናቡከደነፆርም ሲድራቅና ሚሳቅ አብደናጎም ሆይ! አምላኬን አለማምለካችሁ ላቆምሁትም ለወርቁ ምስል አለመስገዳችሁ እውነት ነውን? አሁንም የመለከቱንና የእንቢልታውን የመሰንቆውንና የክራሩን የበገናውንና የዋሽንቱን የዘፈኑንም ሁሉ ድምፅ በሰማችሁ ጊዜ ተደፍታችሁ ላሠራሁት ምስል ብትሰግዱ መልካም ነው፤ ባትሰግዱ ግን በዚያ ጊዜ በሚነድድ እሳት እቶን ውስጥ ትጣላላችሁ፤ ከእጄስ የሚያድናችሁ አምላክ ማን ነው?›› ብሎ ተናገራቸው፡፡ ሲድራቅና ሚሳቅ አብደናጎም መለሱ ንጉሡን ‹ናቡከደነፆር ሆይ! በዚህ ነገር እንመልስልህ ዘንድ አስፈላጊያችን አይደለም፡፡ የምናመልከው አምላካችን ከሚነድደው ከእሳቱ እቶን ያድነን ዘንድ ይችላል፤ ከእጅህም ያድነናል፡፡ ነገር ግን ንጉሥ ሆይ! እርሱ ባያድነን አማልክትህን እንዳናመልክ ላቆምኸውም ለወርቁ ምስል እንዳንሰግድለት እወቅ› አሉት፡፡

የዚያን ጊዜም ናቡከደነፆር በሲድራቅና በሚሳቅ በአብደናጎም ላይ ቍጣ ሞላበት፡፡ የፊቱም መልክ ተለወጠባቸው፡፡ እርሱም ተናገረ የእቶንም እሳት ይነድድ ከነበረው ይልቅ ሰባት እጥፍ አድርገው እንዲያነድዱት አዘዘ፡፡ ሲድራቅንና ሚሳቅንም አብደናጎንም ያስሩ ዘንድ ወደሚነድድም ወደ እቶን እሳት ይጥሉአቸው ዘንድ በሠራዊቱ ውስጥ ከነበሩት ኃያላን አዘዘ፡፡ የዚያን ጊዜም እነዚህ ሰዎች ከሰናፊላቸውና ከቀሚሳቸው ከመጐናጸፊያቸውም ከቀረውም ልብሳቸው ጋር ታስረው በሚነድድ በእቶን እሳት ውስጥ ተጣሉ፡፡ የንጉሡም ትእዛዝ አስቸኳይ ስለሆነ የእቶኑም እሳት እጅግ ስለሚነድድ፣ ሲድራቅንና ሚሳቅን አብደናጎንም የጣሉአቸውን ሰዎች የእሳቱ ወላፈን ገደላቸው፡፡ እነዚህም ሦስቱ ሰዎች ሲድራቅና ሚሳቅ አብደናጎም ታስረው በሚነድደው በእቶኑ እሳት ውስጥ ወደቁ፡፡ የዚያን ጊዜም ንጉሡ ናቡከደነፆር ተደነቀ ፈጥኖም ተነሣ፤ አማካሪዎቹንም ‹ሦስት ሰዎች አስረን በእሳት ውስጥ ጥለን አልነበረምን?› ብሎ ተናገራቸው፡፡ እነርሱም ‹ንጉሥ ሆይ! እውነት ነው› ብለው ለንጉሡ መለሱለት፡፡ እርሱም ‹እነሆ እኔ የተፈቱ በእሳቱም መካከል የሚመላለሱ አራት ሰዎች አያለሁ፤ ምንም አላቈሰላቸውም፤ የአራተኛውም መልክ የአማልክትን ልጅ ይመስላል› ብሎ መለሰ፡፡ የዚያን ጊዜም ናቡከደነፆር ወደሚነድደው ወደ እሳቱ እቶን በር ቀርቦ ‹እናንተ የልዑል አምላክ ባሪያዎች ሲድራቅና ሚሳቅ አብደናጎም! ኑ ውጡ› ብሎ ተናገራቸው፡፡ ሲድራቅና ሚሳቅም አብደናጎም ከእሳቱ መካከል ወጡ፡፡

መሳፍንቱና ሹማምቶቹም አዛዦቹና የንጉሡ አማካሪዎች ተሰብስበው እሳቱ በእነዚያ ሰዎች አካል ላይ ኃይል እንዳልነበረው፣ የራሳቸውም ጠጕር እንዳልተቃጠለች ሰናፊላቸውም እንዳልተለወጠ፣ የእሳቱም ሽታ እንዳልደረሰባቸው አዩ፡፡ ናቡከደነፆርም መልሶ ‹መልአኩን የላከ ከአምላካቸውም በቀር ማንም አምላክ እንዳያመልኩ ለእርሱም እንዳይሰግዱ ሰውነታቸውን አሳልፈው የሰጡትን የንጉሡንም ቃል የተላለፉትን በእርሱ የታመኑትን ባሪያዎቹን ያዳነ፣ የሲድራቅና የሚሳቅ የአብደናጎም አምላክ ይባረክ፡፡ እኔም እንደዚህ የሚያድን ሌላ አምላክ የለምና በሲድራቅና በሚሳቅ በአብደናጎም አምላክ ላይ የስድብን ነገር የሚናገር ወገንና ሕዝብ በልዩ ልዩም ቋንቋ የሚናገሩ ይቈረጣሉ፣ ቤቶቻቸውም የጕድፍ መጣያ ይደረጋሉ ብዬ አዝዣለሁ› አለ፡፡ የዚያን ጊዜም ንጉሡ ሲድራቅንና ሚሳቅን አብደናጎንም በባቢሎን አውራጃ ውስጥ ከፍ ከፍ አደረጋቸው፡፡›› ትንቢተ ዳንኤል 3፡1-30፡፡

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በመልአኩ አማላጅነት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

( ስንክሳር ዘተዋሕዶ ፌስቡክ ገጽ)

ገዳማውያን

21 Dec, 09:04


ገዳማውያን pinned «🥀መዝሙረ ዳዊት ክፍል 7🥀 🌹መዝሙር ፭ መዝሙር 5 ስለትሩፋን የተጻፈ ነው፡፡ ትሩፋን የሚላቸው አሥሩ ነገድ ተማርከው በኢየሩሳሌም የቀሩ ሁለቱ ነገድ ናቸው፡፡ አንድም ሁሉም ተማርከው አበው አልቀው የቀሩ ውሉድ ናቸው፡፡ አቤቱ ልመናዬን ስማኝ፡፡ ጌታ ሆይ የእኔ ንጉሤም ፈጣሪዬም አንተ ነህ፡፡ እግዚኦ ምርሐኒ በጽድቅከ፡፡ ሰውን መበደል እግዚአብሔርን ማሳዘን ነው፡፡                   …»

ገዳማውያን

21 Dec, 09:04


ሰጠ፡፡ አካላዊ ቃልም ሰው ሆኖ ወንጌልን አስተማረ፡፡ ከጻድቅ ሰው ጋር ጻድቅ ትሆናለህ፡፡ ከንጹሕ ሰው ጋር ንጹሕ ትሆናለህ፡፡ ከደግ ሰው ጋር ደግ ትሆናለህ፡፡ ጌታ ሆይ ማናቸውንም ትሑት ሕዝብ ታድነዋለህ፡፡ ትዕቢተኞችን ታዋርዳቸዋለህ፡፡ የፈጣሪዬ መንገዱ ፍጹም ነው፡፡ ሕገ እግዚአብሔርን ቢጠብቁት ይጠብቃል ባይጠብቁት ያጠፋል፡፡ እግዚአብሔር ላመኑበት ሁሉ የታመነ ወዳጅ ነው፡፡ ፈጣሪዬ እግዚአብሔር ክቡር ምስጉን የባሕርይ አምላክ ነው፡፡
                   🌹መዝሙር ፲፰
ሰማያት የእግዚአብሔርን ጌትነት ይናገራሉ፡፡ አሁን እነርሱ ግእዛን ኖሯቸው የሚናገሩ ሆነው አይደለም፡፡ ተዘርግተው በመታየታቸው ሰው ጌትነቱን ተአምራቱን ምስጋናውን የሚናገር ስለሆነ እንዲህ አለ፡፡ አንድም ሊቃነ መላእክት ጌትነቱን ተአምራቱን ምስጋናውን ይነግራሉ ያስተምራሉ፡፡ ሕጉ ለእግዚአብሔር ንጹሕ ወይመይጣ ለነፍስ፡፡ ኵነኔሁ ለእግዚአብሔር ርቱዕ ወያስተፌሥሕ ልበ፡፡ ትእዛዙ ለእግዚአብሔር ብሩህ ወያበርህ አዕይንተ፡፡ ፈሪሀ እግዚአብሔር ንጹሕ ወያሐዩ ለዓለም፡፡ ፍትሑ ለእግዚአብሔር ጽድቅ ወርትዕ ኅቡረ፡፡ ለወርቅ ለዕንቊ ብሎ ፈጣሪን መካድ አይገባም፡፡ እግዚአብሔር ምሳሌውን በፀሐይ አኖረ፡፡ በክበቡ አብ፣ በብርሃኑ ወልድ፣ በሙቀቱ መንፈስ ቅዱስ ይመሰላልና፡፡ ወንጌል የተሠራ ጌታ የተወለደ ለሁሉ ነው፡፡ ጻድቃን ሰማዕታት ወርቅ ዕንቊ እንሰጣችኋለን ፈጣሪያችሁን ካዱ ሕጋችሁን አፍርሱ ቢሏቸው ፈጣሪያቸውን አይክዱም ሕጋቸውን አያፈርሱም፡፡ ፀሐይ በምሥራቅ መውጣቷ ሰው የመወለዱ ምሳሌ፣ ፀሐይ በምዕራብ መግባቷ ሰው የመሞቱ ምሳሌ፣ ፀሐይ ተመልሳ መውጣቷ የትንሣኤ ዘጉባኤ ምሳሌ ነው፡፡
                   🌹መዝሙር ፲፱
በመከራህ ጊዜ እግዚአብሔር ልመናህን ይስማህ፡፡ ከሰማያዊት መቅደሱ ያለ ረድኤቱን ይላክልህ፡፡ መሥዋዕትህን ሁሉ ይቀበልልህ፡፡ የሀብከ እግዚአብሔር ዘከመ ልብከ፡፡ እግዚአብሔር የልቡናህን ይስጥህ፡፡ ምነው ልብማ ክፉውንስ በጎውንስ ያስብ የለምን ቢሉ ክፉውን ትቶ በጎውን ይስጥህ፡፡ በፈጣሪያችን በእግዚአብሔር ስም አምነን ከብረን ገንነን እንኖራለን፡፡ እግዚአብሔር ልመናህን ሁሉ ይፈጽምልህ፡፡
                   🌹መዝሙር ፳
አቤቱ እግዚአብሔር ሆይ ለከሃሊነትህ ምስጋና እናቀርባለን፡፡ በንባብ፣ በዜማ፣ በበገና እናመሰግንሀለን፡፡
                   🌹መዝሙር ፳፩
ፈጣሪዬ ፈጣሪዬ በዓይነ ምሕረትህ እየኝ ተመልከተኝ፡፡ አባቶቻችን በአንተ አምነው ነበር፡፡ አንተም ከመከራ ሥጋ ከመከራ ነፍስ አድነሀቸው ነበር፡፡ እግዚአብሔርን በሕግ በአምልኮ የምትፈሩት አንድም የምታመልኩት አመስግኑት፡፡ በሰው ፊት የተሳሉትን ስእለት በሰው ፊት ለብቻ የተሳሉትን ለብቻ መስጠት ይገባል፡፡ የባሕርይ መንግሥት የእግዚአብሔር ገንዘብ ናት፡፡
                   🌹መዝሙር ፳፬
አቤቱ እግዚአብሔር ሆይ ሕግህን ግለጽልኝ አስተምረኝ፡፡ ወምርሐኒ በጽድቅከ፡፡ ዘወትር አንተን ተስፋ አደርጋለሁና፡፡ በሕፃንነቴ በስንፍናዬ የሠራሁትን ኃጢአቴን ዕዳ አታድርግብኝ፡፡ እንዲህ ማለት የሚገባ ከሚመጣው ተጠብቆ ነው እንጂ ከሚመጣው ሳይከለከሉ መጸለይ ባለፈው ይቅር በለኝ በሚመጣው ቅሠፈኝ ማለት ነው፡፡ ኵሉ ፍኖቱ ለእግዚአብሔር ሣህል ወጽድቅ፡፡ የእግዚአብሔር ሥራው ሁሉ ይቅርታ ቸርነት ነው፡፡ ብዙ ነውና ኃጢአቴን ይቅር በለኝ፡፡ እግዚአብሔር ለሚፈሩት ለሚያመልኩት ኃይላቸው ነው፡፡ እግዚአብሔር ስሙን ለሚጠሩት ለሚያመሰግኑትም ኃይላቸው ነው፡፡ ጌታ ሆይ ሰውነቴን ከመከራው ጠብቀህ አድናት፡፡
                   🌹መዝሙር ፳፭
በአምልኮተ ጣዖት እንዳልደክም በእግዚአብሔር አመንኩ፡፡ በኃጢአት እንዳልደክም በእግዚአብሔር አመንኩ፡፡ አቤቱ በትድግናህ ደስ አለኝ፡፡ በማኅበር እባርከከ እግዚኦ፡፡ አቤቱ በጉባኤ አመሰግንሀለሁ፡፡
                   🌹መዝሙር ፳፮
ከመከራ ያድነኝ ዘንድ እግዚአብሔር ብርሃነ ረድኤቱን ያበራልኛል፡፡ እግዚአብሔር ለሰውነቴ ወዳጇ ድኅነቷን የሚያደርግላት ነው ምን ያስፈራኛል?፡፡ እግዚአብሔርን አንዲት ነገር ለመንኩት እርሷኑ እሻለሁ በመንግሥተ ሰማያት እንድኖር ያደርገኝ ዘንድ፡፡ አንድም እግዚአብሔርን ደስ የማሰኝበትን ነገር ይገልጽልኝ ዘንድ እንዲያደርገኝ መሆን ናት፡፡ ለእግዚአብሔር ምስጋና አቀርባለሁ፡፡ አቤቱ የለመንኩትን ልመናዬን ስማኝ፡፡ አቤቱ ሕግህን ግለጽልኝ አስተምረኝ፡፡
                   🌹መዝሙር ፳፯
አቤቱ ወደአንተ የለመንኩትን የልመናዬን ቃል ስማኝ፡፡ የለመንኩትን የልመናዬን ቃል ሰምቶኛልና እግዚአብሔር ይክበር ይመስገን፡፡ እግዚአብሔር የታመነ ረዳቴ ነው፡፡ እግዚአብሔር ለሕዝቡ ኃይላቸው ረዳታቸው ነው፡፡
                   🌹መዝሙር ፳፰
እግዚአብሔርን ክቡር ስቡሕ እያላችሁ አመስግኑት፡፡ ለስሙ ምስጋና አቅርቡ ማለት ስሙን እየጠራችሁ አመስግኑት፡፡ ስግዱ ለእግዚአብሔር በአፀደ መቅደሱ፡፡ እግዚአብሔር ይባርኮሙ ለሕዝቡ በሰላም፡፡ እግዚአብሔር ወገኖቹን በአንድነት በፍቅር ያከብራቸዋል ያበዛቸዋል፡፡
                   🌹መዝሙር ፳፱
አቤቱ እግዚአብሔር ሆይ በረድኤት ተቀብለኸኛልና አመሰግንሃለሁ፡፡ በኦሪት ልቅሶ ይደረጋል ማለት ልጅነት አልተገኘባትም፡፡ በወንጌል ተድላ ደስታ ይደረጋል ማለት ልጅነት ተገኝቶባታል ሀብት ሥርየት ተሰጥቶባታልና፡፡ እግዚአብሔር ልመናዬን ሰምቶ ይቅር አለኝ፡፡ እግዚአብሔር ረዳት ሆነኝ፡፡
                   🌹መዝሙር ፴
አቤቱ በይቅርታህ በቸርነትህ ፈጽመህ አድነኝ፡፡ ሠውረው ከመከሩብኝ ምክር ከሸመቁብኝ ጦር አድነኝ፡፡ የክብር ባለቤት እግዚአብሔር ሆይ አድነኝ፡፡ በትድግናህ ፈጽሞ ደስ ይለኛል፡፡ በመናቅ በማቃለል ዕሩቅ ብእሲ እያሉ በባሕርይ አምላክ በክርስቶስ ላይ ዐመፅን ለሚናገሩ ለአይሁድ አንደበቶች ወዮላቸው፡፡ በብዙ መከራዬ ጊዜ ለእኔ ቸርነቱን የገለጠልኝ እግዚአብሔር ይክበር ይመስገን፡፡ እግዚአብሔርን እውነት ይዛችሁ አንድም ትሕትና ይዛችሁ ውደዱት፡፡ እግዚአብሔር እውነትን ትሕትናን ይወዳልና፡፡ ሐሰተኞችን ትዕቢተኞችን ተበቅሎ ያጠፋቸዋል፡፡
                   🌹መዝሙር ፴፩
ኃጢአታቸው በንስሓ የተሠረየላቸው ሰዎች ንዑዳን ክቡራን ናቸው፡፡ ኃጢአታቸው በጥምቀት የተሠረየላቸው ሰዎች ንዑዳን ክቡራን ናቸው፡፡ በልቡናው ቂም በቀል ክዳት ሽንገላ የሌለበት ምእመን ንዑድ ክቡር መባል ይገባዋል፡፡ ልብ እንደሌላቸው እንደ ፈረስ እንደ በቅሎ አትሁኑ፡፡ አእምሮ ለብዎ እንደሌላቸው እንደ እንስሳት አትሁኑ፡፡
                   🌹መዝሙር ፴፪
መሰንቆ እየመታችሁ ለእግዚአብሔር ተገዙ፡፡ አሥር አውታር ያለው በገና እየደረደራችሁ ተገዙ፡፡ እግዚአብሔርን በጎ ምስጋና አመስግኑ፡፡ የእግዚአብሔር ቃሉ እውነት ነው፡፡ እግዚአብሔር እውነትን፣ ምጽዋትን፣ ሃይማኖትን፣ ምግባርን የያዘ ሰውን ይወዳል፡፡ ሣህሉ ለእግዚአብሔር ብሎ አብን፣ ወበቃለ እግዚአብሔር ብሎ ወልድን፣ ወእምእስትንፋሰ አፉሁ ኵሉ ኃይሎሙ ብሎ መንፈስ ቅዱስን ይገልጻል፡፡ የእግዚአብሔር ምክር ግን ለዘላለም ጸንቶ ይኖራል፡፡ ፈጣሪው እግዚአብሔር የሆነለት ሰው ንዑድ ክቡር ነው፡፡ ንጉሥ በሠራዊቱ ብዛት አይድንም፡፡ ልቡናችን እግዚአብሔርን ተስፋ ያደርጋል፡፡

ገዳማውያን

21 Dec, 09:04


                   🌹መዝሙር ፴፫
እግዚአብሔርን በሰባቱ በአሥራ ሁለቱ በሃያ አራቱ ጊዜያት አመሰግነዋለሁ፡፡ ጌትነቱ ክብሩ ተአምራቱ ዘወትር በአንደበቴ ሲነገር ይኖራል፡፡ ሰውነቴ በእግዚአብሔር አምና ከብራ ገንና ትኖራለች፡፡ እግዚአብሔርን ከእኔ ጋራ እንደእኔ አመስግኑት አክብሩት፡፡ ክቡር ልዑል እያልን እግዚአብሔርን እናመስግነው፡፡ በሕግ በአምልኮ ወደ እግዚአብሔር ቅረቡ ብርሃነ ረድኤቱን ያበራላችኋል፡፡ አንድም ከመከራው አድኖ ደስ ያሰኛችኋል፡፡ ፊታችሁ አያፍርም፡፡ አዳም ወደ እግዚአብሔር በለመነ ጊዜ እግዚአብሔር ልመናውን ሰማው፡፡ ከመከራው ሁሉ አዳነው፡፡ እግዚአብሔርን ለሚፈሩት ለሚያመልኩት ሰዎች ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ በዙሪያቸው ይከትማል ያድናቸውማል፡፡ ጠዓሙ ወታእምሩ ከመ ኄር እግዚአብሔር፡፡ እግዚአብሔርን በሕግ በአምልኮ ፍሩት አክብሩት፡፡ ልጆቼ ኑ ምክሬን ትምህርቴን ስሙኝ አምልኮተ እግዚአብሔርን አስተምራችሁ ዘንድ፡፡ አንደበትህን ከማማት ተከልከል፡፡ ተገሐሥ እምእኩይ ወግበር ሠናየ፡፡ ክርስቶስን ዕሩቅ ብእሲ ወንጌልን ዲቃላ ሕግ አትበል፡፡ ክርስቶስን የባሕርይ አምላክ ወንጌልን ፍጽምት ሕግ በሉ፡፡ ፍቅርን ሻት ተከተላት፡፡ ጻድቃን ለመኑ እግዚአብሔርም ልመናቸውን ሰማቸው፡፡ ካገኛቸው መከራ ሁሉ አዳናቸው፡፡ እግዚአብሔር ቅን ልቡና ላላቸው ሰዎች ቅርብ ነው ማለት ልመናቸውን ፈጥኖ ይሰማቸዋል፡፡ ትሑት ሰብእና ያላቸውንም ይሰማቸዋል፡፡ የጻድቃን መከራቸው ብዙ ነው፡፡ ወእምኵሉ ያድኅኖሙ እግዚአብሔር፡፡ እግዚአብሔር ግን ካገኛቸው መከራ ሁሉ ያድናቸዋል፡፡ እግዚአብሔር ወገናቸውን ሁሉ ይጠብቃል፡፡ ኃጥእ ሰው ከዛሬ ነገ ከዘንድሮ ከርሞ ኃጢአቴን ለመምህረ ንስሓዬ ነግሬ የወዲያ ዓለም ቤቴን ሠርቼ ከፈጣሪዬ ጋራ ታርቄ እሞታለሁ ሲል ንስሓ ሳይገባ ከፈጣሪው ሳይታረቅ ንግድም ቢሉ ዘመቻም ቢሉ በሔደበት ግልድው ብሎ ይቀራል፡፡ ጻድቅ ግን ኃጢአቱን ለመምህረ ንስሓው ነግሮ ከፈጣሪው ጋር ታርቆ የወዲያ ዓለም ቤቱን ሠርቶ ይሞታል፡፡ የጻድቅ ነፍስ በመዓዛ ገነት በመዝሙረ ዳዊት በይባቤ መላእክት ትለያለች፡፡ የኃጥእ ነፍስ ግን ዲያብሎስ ጽሉም ገጹን ሕሡም ራእዩን ይለውጥባታል ትደነግጣለች ደም ይደርቃል ነፍስ ትለያለች፡፡
                   🌹መዝሙር ፴፬
ዳዊት ይህን መዝሙር ስለኤርምያስ ተናግሮታል፡፡ ኤርምያስ እስራኤልን ቢመክራቸው ቢያስተምራቸው ምክሩን ትምህርቱን የማይቀበሉት ሆነ፡፡ ጌታ ሆይ ሰውነቴን ረዳትሽ እኔ ነኝና አይዞሽ በላት፡፡ ሰውነቴን ለማጥፋት የሚሿት ሁሉ ይፈሩ ይዋረዱ፡፡ የእኛ ሰውነት ግን በእግዚአብሔር አምና ደስ ይላታል፡፡ ጌታ ሆይ የሐሰት ምስክሮች በጠላትነት ተነሱብኝ፡፡ በእኔ ላይም የማላውቀውን ነገር ተናገሩብኝ፡፡ ጸሎት ያለዋጋ አይቀርም፡፡ አቤቱ የምትፈርድልኝ መቼ ነው፡፡ አቤቱ በብዙ ሰዎች ጉባኤ እገዛልሃለሁ፡፡ ሳልጣላቸው በግፍ የሚጣሉኝ ደስ አይበላቸው፡፡ አቤቱ ከእኔ በረድኤት አትራቅ፡፡ በእኔ መከራ ደስ የሚላቸው ይፈሩ ይዋረዱ፡፡
                   🌹መዝሙር ፴፭
ክፉ ሰው በአንደበቱ የሚናገረው ነገር ሁሉ ዐመፃ ክዳት ሽንገላ ነው፡፡ ክፉ ሰው ኃጢአትን ቢሠራት ቢሠራት አይሰለቻትም፡፡ አቤቱ ጌታ ሆይ ይቅርታህ ሰማይን በመፍጠርህ ታወቀ፡፡ ቸርነትህም ደመናትን በመፍጠር ታወቀ፡፡ ፍርድህ እጅግ ጥልቅ ነው፡፡ የአዳም ልጆች በክንፈ ረድኤትህ አምነው ተጠብቀው ይኖራሉ፡፡
                   🌹መዝሙር ፴፮
ሰርቀው ቀምተው አስረው ፈትተው በሚኖሩ ሰዎች አትቅና፡፡ በእነዚህ መቅናት እኔም የእነርሱን ሥራ ልሥራ ማለት ነውና፡፡ ጣዖት በሚያመልኩ ሰዎች አትቅና፡፡ እንደ ሣር ፈጥነው ከብዕላቸው ይለያሉና፡፡ እንደ ጎመን ቅጠል ፈጥነው ይወድቃሉ፡፡ አንተ ግን በእግዚአብሔር እመን በጎ በጎውን ሥራ ሥራ፡፡ በእርሱ እመን እርሱም የለመንከውን ያደርግልሀል፡፡ ቁጣን ተዋት፡፡ ክፉ የሚያደርጉ ተነቃቅለው ይጠፋሉ፡፡ ቅኖች ኀዳግያነ በቀል መንግሥተ ሰማያትን ወርሰዋት ይኖራሉ፡፡ በፍጹም ተድላ ደስታ ደስ ይላቸዋል፡፡ ሰርቀው ቀምተው ሸፍጠው ተሟግተው ከሰበሰቡት ከባለጸጎች ብዙ ብዕል ይልቅ ወጥቶ ወርዶ ነዶ በርዶ በእውነት የተገኘ ጥቂት የድኃ ገንዘብ ይበልጣል፡፡ የባለጸጎች ገንዘብ ፈጥኖ ይጠፋልና፡፡ ጻድቅ መምህር ከእግዚአብሔር ትምህርትን ይበደራል፡፡ ሐዲስ የተማረ እንደሆነ ሐዲሱን እያስተማረ ብሉዩን ይማራል፡፡ ብሉይ የተማረ እንደሆነ ብሉዩን እያስተማረ ሐዲሱን ይማራል፡፡ የሰው ሥራው ከእግዚአብሔር ዘንድ ዋጋውን ተቀብሎ ይጠብቀዋል፡፡ ከልጅነት እስከ ሽበት ደረስኩ ጻድቅ ሰው ሲጎዳ አላየሁም፡፡ ከክፉ ሥራ ተለይ በጎውን ሥራ ሥራ፡፡ እግዚአብሔር እውነትን አንድም እውነትን የያዘ ሰውን ይወድዳል፡፡ ጻድቃንን በመከራው አይጥላቸውምና ለጊዜውም ቢጥላቸው እንደ ጣላቸው አይቀርምና፡፡ በነፍስ በሥጋ ይጠብቃቸዋል፡፡ ለንጹሓን ይፈርድላቸዋል፡፡ የጠቢብ ሰው አንደበቱ ጥበብን አንድም ሕግን ይማራል፡፡ እግዚአብሔር በሃይማኖት ለፈተና መከራ ቢያመጣብህ መከራውን ታግሠህ ተቀበል ሕጉን ጠብቅ፡፡ እንዲህ ያደረግህ እንደሆነ በነፍስ በሥጋ ያከብርሃል፡፡
                   🌹መዝሙር ፴፯
አቤቱ እግዚአብሔር ሆይ በነፍስ በሥጋ አታጥፋኝ፡፡ አቤቱ በአንተ አምኛለሁና ልመናዬን ስማኝ፡፡ የጠላቶቼ መዘበቻ አታድርገኝ፡፡ ኃጢአት ስለሠራሁ አዝናለሁ፡፡ አቤቱ ፈጣሪዬ በመከራው አትጣለኝ በረድኤትም አትለየኝ፡፡ እኔን ወደ መርዳት ተመልከት፡፡
                   🌹መዝሙር ፴፰
ለአንደበቴ አርምሞን ትዕግሥትን ገንዘብ አደረግሁ፡፡ ራሴን ዝቅ ዝቅ አደረግሁ፡፡ ለበጎ ነገር ዝም አልኩ፡፡ ሰው ሁሉ እንደ ጥላ ይመላለሳል፡፡ ጥላ ጠዋት ሰባ ሰማንያ ክንድ ይሆናል፡፡ በቀትር ጊዜ ከዚህ ደረሰ አይባልም፡፡ ሰውም ታይቶ ይጠፋልና፡፡ ነገር ግን እንደ ጥላ መሆን ሳለ እንኑር እንክበር በማለት ይታወካሉ፡፡ አሁንስ አለኝታዬ ማን ነው እግዚአብሔር አይደለምን? አቤቱ መዓትህን ሁሉ ከእኔ አርቅልኝ፡፡ አቤቱ ከኃጢአት አርፍ ዘንድ በንስሓ አሳርፈኝ፡፡
                   🌹መዝሙር ፴፱
እግዚአብሔርን በጸሎት በቀኖና ደጅ ጸናሁ፡፡ ከቁጣ ወደ ትዕግሥት ከመዓት ወደ ምሕረት ተመልሶ ልመናዬን ሰማኝ፡፡ በአንደበቴ እንግዳ ምስጋናን እንዳመሰግነው አደረገኝ፡፡ ብፁዕ ብእሲ ዘስመ እግዚአብሔር ትውክልቱ፡፡ እምነቱ በእግዚአብሔር ስም የሆነለት ሰው ንዑድ ክቡር ነው፡፡ አቤቱ ቸርነትህን በብዙ ጉባዔ ነገርኩ፡፡ ይቅርታህ ቸርነትህ ሁልጊዜ ያግኙኝ፡፡
                   🌹መዝሙር ፵
በነዳይ በምስኪን ላይ ያለውን መከራ አስቦ ምግቡን በከርሠ ርኁባን፣ መጠጡን በጕርዔ ጽሙዓን፣ ልብሱን በዘባነ ዕሩቃን የሚያኖር ሰው ንዑድ ክቡር ነው፡፡ እንዲህ ያለውን ሰው እግዚአብሔር ከዕለተ ሞት ከዕለተ ምጽአት ያድነዋል፡፡
                   🌹መዝሙር ፵፩
ዋልያ የውሃ ምንጮችን እንደሚወድ እንደዚሁም ሁሉ የእኔም ሰውነት እግዚአብሔርን ናፈቀች ወደደች፡፡ ሰውነቴ ሕያወ ባሕርይ ፈጣሪዬን ናፈቀች ወደደች፡፡ ነቢያት ይወርዳል ይወለዳል ብለው የተናገሩት ሐዋርያት ወረደ ተወለደ ብለው ያስተማሩት አንድ ሆነ፡፡ መከታዬ ፈጣሪዬ ነው፡፡

ገዳማውያን

21 Dec, 09:04


አቤቱ እግዚአብሔር ሆይ እኔ አንተን አመንኩ፡፡ በእግዚአብሔር አምኛለሁና አልፈራም፡፡ ሥጋዊ ደማዊ ሰው ምን ያደርገኛል ብዬ አልፈራም፡፡
                   🌹መዝሙር ፶፮
እግዚአብሔር ረድኤቱን ከሰማይ ልኮ አንድም ልጁን በሥጋ ልኮ አዳነኝ፡፡ ይቅርታውን ቸርነቱን አደረገልኝ፡፡ ነፍሴን ከአጋንንት እጅ አዳናት፡፡ አቤቱ በሕዝብ ጉበኤ ምስጋና አቀርብልሃለሁ፡፡ እግዚአብሔር ሰማያትን በመፍጠር ልዕልናውን ገለጸ፡፡
                   🌹መዝሙር ፶፯
ኃጥኣን ከእናታቸው ማኅፀን ጀምረው በእናታቸው ማኅፀን ሳሉ በደሉ፡፡ አሁን ሕፃናት በማኅፀን ሳሉ የሚበድሉ ሐሰት የሚናገሩ ሆነው አይደለም፡፡ ነቢይ ኋላ የሚሠሩትን ያውቃልና እንዲህ አለ እንጂ፡፡ እግዚአብሔር የነገሥታቱን ሥልጣን ያጠፋል፡፡
                   🌹መዝሙር ፶፰
አቤቱ ከጠላቶቼ አድነኝ፡፡ የፈጣሪዬ ይቅርታው ይደረግልኝ፡፡ አቤቱ እግዚአብሔር ሆይ ከሃሊነትህን አመሰግናለሁ፡፡ በቸርነትህ ዕለት ዕለት ደስ ይለኛል፡፡
                   🌹መዝሙር ፶፱
አቤቱ ከ5500 ዘመን በኋላ ይቅር አልከን፡፡ አቤቱ ልመናዬን ሰምተህ በሥልጣንህ አድነኝ፡፡ አቤቱ በመከራችን ጊዜ መከራችንን ለማራቅ ረድኤትህን ስጠን ማለት እርዳን፡፡ በሰው መታመን ከንቱ ስለሆነ በእግዚአብሔር አምነን ኃይልን እናደርጋለን፡፡
                   🌹መዝሙር ፷
እግዚአብሔር ሆይ አንተ ፈጣሪዬ ነህና ልመናዬን ሰማኸኝ፡፡ እውነት ለሚፈርድ ሰው ይቅርታ ቸርነት ማድረግህና ለዘለዓለሙ በባለሟልነት ጸንቶ እንዲኖር ማድረግህን እያሰብኩ ለዘለዓለሙ ለስምህ ምስጋና አቀርባለሁ፡፡
                   🌹መዝሙር ፷፩
ነፍሴ ለእግዚአብሔር ትገዛለች፡፡ ረዳቴ እግዚአብሔር ነውና በመከራ አልታወክም፡፡ ክብሬ በሚሆን በእግዚአብሔር አምናለሁ፡፡ እግዚአብሔር ረድኤትን የሚያደርግልኝ ፈጣሪዬ ነው፡፡ እግዚአብሔር ለሁሉ እንደሥራው ይከፍለዋል፡፡
                   🌹መዝሙር ፷፪
አቤቱ ነፍሴ አንተን ትናፍ*ቃ-ለች፡፡ አቤቱ በስምህ አምኜ እደ ቃሌን ለጸሎት እደ ሥጋዬን ለመሥዋዕት እደ ልቡናዬን ለአንክሮ ለተዘክሮ አነሣለሁ፡፡ ደስ ያላቸው አንደበቶቼ ደስ እያላቸው ለስምህ ምስጋና ያቀርባሉ ስምህን ያመሰግናሉ፡፡
                   🌹መዝሙር ፷፫
እግዚአብሔር በዕውቀት ከሁሉ ይበልጣል፡፡ ይትፌሣሕ ጻድቅ በእግዚአብሔር፡፡
                   🌹መዝሙር ፷፬
ጌታ ሆይ በልጅነት የተቀበልከው ምእመን ንዑድ ክቡር ነው፡፡ አቤቱ ከቤተ ክርስቲያን የተገኘውን ሥጋውን ደሙን ተቀብለን ልጅነትን አግኝተን ደስ አለን፡፡ ድኅነትን የምታደርግልን ፈጣሪያችን ሆይ ልመናችንን ስማን፡፡ አቤቱ ምእመንን ከአምስት ሺህ አምስት መቶ ዘመን በኋላ በልጅነት ጎበኘሀት፡፡
                   🌹መዝሙር ፷፭
በአራቱ መዓዝን መልቶ ያለ እግዚአብሔርን አመስግኑ፡፡ ለእግዚአብሔር ምስጋና አቅርቡ፡፡ ወዘምሩ ለስሙ ለስሙም ምስጋና አቅርቡ ማለት ስሙን አመስግኑ፡፡ እግዚአብሔርን ሥራህ ግሩም ነው በሉት፡፡ የእግዚአብሔርን ሥራ ታዩ ዘንድ ኑ፡፡ ልመናዬን ቸል ያላለ እግዚአብሔር ይክበር ይመስገን፡፡ ይቅርታውን ከእኔ አላራቀምና፡፡ አንድም ይቅርታውን ከእኔ ያላራቀ እግዚአብሔር ይክበር ይመስገን፡፡
                   🌹መዝሙር ፷፮
አቤቱ እግዚአብሔር ሆይ አሕዛብ ሁሉ ይገዙልሀል፡፡ ፈጣሪያችን እግዚአብሔር ያከብረናል ያበዛናል፡፡ እግዚአብሔር ያክብረን ያብዛን፡፡
                   🌹መዝሙር ፷፯
ጻድቃን በፍጹም ተድላ ደስታ ደስ ይላቸዋል፡፡ ለእግዚአብሔር ምስጋና አቅርቡ፡፡ ምእመን በልጅነት የለመለመ ነው፡፡ አቤቱ ነፍሳትን ይዘህ ከሲኦል ወደ ገነት ወጣህ፡፡ ለምእመናንም ልጅነትን ሰጠኻቸው፡፡ ፈጣሪያችን እግዚአብሔር ክቡር ምስጉን ነው፡፡ ይረድአነ አምላክነ ወመድኃኒነ፡፡ ፈጣሪያችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይረዳናል፡፡ የዚህ ዓለም ነገሥታት እግዚአብሔርን አመስግኑት፡፡ ለፈጣሪያችን ምስጋና አቅርቡ፡፡ እግዚአብሔር በወዳጆቹ አድሮ የሚሠራው ሥራ ድንቅ ነው፡፡
                   🌹መዝሙር ፷፰
ሳልጣላቸው በግፍዕ የሚጣሉኝ ጠላቶቼ ከራስ ፀጉሬ ይልቅ በዙ፡፡ አቤቱ እግዚአብሔር ሆይ በአንተ ስላመንኩ ስድቡን ታግሼ ተቀብያለሁ፡፡ የእግዚአብሔር ይቅርታው በጊዜው ጊዜ ይደረጋል፡፡ እውነተኛው መድኃኒቴ እግዚአብሔር ሆይ እውነተኛ ልመናዬን ስማኝ፡፡ ከጠላቶቼ አድነኝ፡፡ አቤቱ ቸርነትህ ያማረ የተወደደ ነውና ልመናዬን ስማኝ፡፡ መከታዬ እግዚአብሔር ሆይ በረድኤት ተቀበለኝ፡፡ እግዚአብሔርን በሕግ በአምልኮት ሹት እንዲህ የሆነ እንደሆነ ሰውነታችሁ ትድናለች፡፡
                   🌹መዝሙር ፷፱
አቤቱ እግዚአብሔር ሆይ ሰውነቴን ለሞት ለጥፋት የሚሿት ሁሉ ይፈሩ ይዋረዱ፡፡ በእኔ ክፉ የመከሩብኝ ሰዎች ሁሉ ይፈሩ ይዋረዱ፡፡ አንተን በሕግ በአምልኮ የሚሹህ ሁሉ ግን በአንተ አምነው ጸንተው ፈጽመው ደስ ይበላቸው፡፡ አቤቱ ፈጣሪዬ ረዳቴ አምባ መጠጊያዬ አንተ ነህ፡፡
                   🌹መዝሙር ፸
አቤቱ በአንተ አምኛለሁና አላፍርም፡፡ አቤቱ ከኃጥኣን እጅ አድነኝ፡፡ አንተ አለኝታዬ ነህና፡፡ አቤቱ እግዚአብሔር ሆይ ለአንተ ምስጋና ባቀረብኩ ጊዜ አንደበቶቼ ደስ ይላቸዋል፡፡

© በትረ ማርያም አበባው


#Share
@Gedamaweyan         @Gedamaweyan
@Gedamaweyan         @Gedamaweya

ገዳማውያን

21 Dec, 09:04


                   🌹መዝሙር ፵፪
አቤቱ እግዚአብሔር ሆይ ዐመፀኛ ከዳተኛ ከሚሆን ከብልጣሶር አድነኝ፡፡ አንተ ፈጣሪዬ ብዋጋ ኃይሌ ነህና፡፡ ጠላቶቼ ባስጨነቁኝ ባስጠበቡኝ ጊዜ ብርሃነ ረድኤትህን ላክልኝ፡፡ ቸርነትህን አድርግልኝ፡፡ ፈጣሪዬ ሆይ መሰንቆ እየመታሁ እገዛልሃለሁ፡፡ አንድም በሃይማኖት በምግባር ጸንቼ እገዛልሃለሁ፡፡
                   🌹መዝሙር ፵፫
መቃብያን ማለት ዕጉሣን በስደት ፅኑዓን በምግባር ወበሃይማኖት ማለት ነው፡፡ አንጥያኮስ አልዓዛርን አስጠርቶ አንተ ጽዩፍ ነህ ሲሉ እሰማለሁና ለእኔና ለአንተ መሥዋዕተ በግዕ ትሠዋለህ፡፡ መሥዋዕተ እሪያ ሠውተህ በቀኝ እጅህ ቢላዋ በግራ እጅህ ሥጋ ይዘህ የበላህ መስለህ ሕዝቡን አሳምንልኝ አለው፡፡ አልዓዛርም ፈጣሪዬ የሃይማኖት አብነት ቢያደርገኝ የክሕደት የጥብዐት አብነት ቢያደርገኝ የክፋት አብነት እሆናለሁን አይሆንም አለው፡፡ ይመለስ እንደሆነ ብሎ ለክህነት የደረሱ ሰባት ልጆች ነበሩት ከፊቱ በሰይፍ አስመትቷቸዋል፡፡ የማይመለስ ሆነ ሚስቱን በኩላብ አሰቅሎ በሰይፍ አስመታት፡፡ የማይመለስ ቢሆን በቁመቱ ልክ ሻሽ ጠምጥሞ በሰም ጠምቶ ብረት ምጣድ አግሎ በራሱ ላይ ደፋበት፡፡ ተንጠቅጥቆ ሞቷል፡፡ ጌታ ሆይ በአንተ አምነን ጠላቶቻችንን ድል እንነሣለን፡፡ አባቶቻችን በሥልጣንህ በኃይልህ በረድኤትህ ነው እንጂ በጦራቸው አንደበት በፈረሳቸው አንገት ከነዓንን እንዳልወረሷት አውቄ እኔም በሥልጣንህ በኃይልህ በረድኤትህ ነው እንጂ በጦሬ አንደበት በፈረሴ አንገት የምታመን አይደለሁም፡፡ በእግዚአብሔር ንከብር ኵሎ አሚረ፡፡ በእግዚአብሔር አምነን ዕለት ዕለት ከብረን ገንነን እንኖር ነበር፡፡ በእግዚአብሔር ስም ስላመንን፣ በእርሱ ስም ስላስተማርን፣ በእርሱ ስም ስለተጠራን ዘወትር መከራ ያመጡብናል፡፡
                   🌹መዝሙር ፵፬
ልቡናዬ በጎ ነገርን አውጥቶ ይናገራል፡፡ የክርስቶስ መልኩ ከሰው ልጅ መልክ ይበልጣል፡፡ ተበድሎ መካስ የዋህነት ነው፡፡ ሐዋርያት በመንፈስ ቅዱስ የጋሉ የተቡ የተወደዱ ናቸው፡፡ ጌታ ሆይ ሰው መሆንን ወደድክ አለመሆንን ጠላህ፡፡ እንደ አንተ ያሉ ነቢያት ካህናት ከተቀቡት ልዩ የሚሆን ቅብዐ ትፍሥሕትን ቀባህ፡፡ ዘይኄይስ ማለቱ የእርሱ የማይነሣ ሕፀፅ የሌለበት የባሕርይ፣ የነቢያት የሚነሣ ሕፀፅ ያለበት የጸጋ ነው፡፡ የእርሱ ከራሱ የእነርሱ ግን ከእርሱ ነውና፡፡
                   🌹መዝሙር ፵፭
ፈጣሪያችን ብንዋጋ ኃይላችን ብንሸሽ አምባ መጠጊያችን ነው፡፡ ስለዚህም ምድር ብትናወጥ አንፈራም፡፡ አምባ መጠጊያችን የሚሆን የያዕቆብ ፈጣሪ የኃያላኑ ባለቤት በረድኤት ከእኛ ጋር አለ፡፡ ድንግል ማርያምን ሀገረ እግዚአብሔር አላት ንጉሥ በከተማው እንዲኖር ማኅፀኗን ዓለም አድርጎ ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን ሲመሰገንባት ኖሯልና፡፡ ፈለግ ዘይውኅዝ ያስተፌሥሕ ሀገረ እግዚአብሔር፡፡ ከሰማይ የወረደ ቅዱስ ገብርኤል ሀገረ እግዚአብሔር እመቤታችንን ትፀንሲ ወትወልዲ ወልደ ብሎ ደስ ያሰኛታል፡፡ ንዑ ትርአዩ ግብሮ ለእግዚአብሔር፡፡ የእግዚአብሔርን ሥራ ታዩ ዘንድ ኑ፡፡ በዚህ ዓለም ያደረገውን ድንቅ ሥራውን ታዩ ዘንድ ኑ፡፡ አምባ መጠጊያችን የሚሆን የያዕቆብ ፈጣሪ የኃያላኑ ባለቤት በረድኤት ከእኛ ጋር አለ፡፡
                   🌹መዝሙር ፵፮
ለእግዚአብሔር በደስታ ቃል ምስጋናን አቅርቡ፡፡ እግዚአብሔርን አመስግኑ፡፡ እግዚአብሔር ልዑል ግሩም ነውና፡፡ መንግሥተ ሰማያትን ለመውረስ መረጠን፡፡ የያዕቆብን ሥጋ ለመዋሐድ የወደደ እርሱ ነው፡፡ ዘምሩ ለአምላክነ ዘምሩ፡፡ ለፈጣሪያችን ምስጋና አቅርቡ፡፡ አንድም ፈጣሪያችንን ፈጽማችሁ አመስግኑ፡፡ ለንጉሣችን ለክርስቶስ ምስጋና አቅርቡ፡፡ እግዚአብሔር ለሰው ሁሉ ንጉሥ ነውና፡፡
                   🌹መዝሙር ፵፯
እግዚአብሔር ገናና አምላክ ነው፡፡ ምስጋናውም ፍጹም ነው፡፡ ለሰው ሁሉ ፀሐይን የሚያወጣ እግዚአብሔር ነው፡፡ አቤቱ በነቢያት በካህናት ጸሎት ይቅርታህን ቸርነትህን አገኘን፡፡
                   🌹መዝሙር ፵፰
በዕለተ ምጽአት በተነሣሕያን ፍርሀት የለባቸውም፡፡ ያን ጊዜ በዚህች ዓለም በገድል በትሩፋት የደከመ ይድናል፡፡ ሰው አዋቂ ሲሆን አላዋቂ ሆነ፡፡ አእምሮ እንደ ሌላቸው እንደ እንስሳት ሆነ እንስሳትን መሰለ፡፡ ላም ከአፋፍ ላይ ሆኖ ሲመገብ ከገደል ሥር ለምለም ሣር፣ ጥሩ ውሃ ያዬ እንደሆነ የረገጠው መሬት ካልከዳው በቀር ወርጄ ልመገበው አይልም፡፡ ሰው ግን ጽድቅ እንደሚጠቅም ኃጢአት እንደሚጎዳ እያወቀ ሊሰርቅ ሊቀማ ይሄዳል፡፡ ሰው ሲሞት ቤቱ ንብረቱ ገንዘቡም ሁሉ ከእርሱ ጋራ ወደ መቃብር አይወርድም፡፡
                   🌹መዝሙር ፵፱
ፈጣሪያችን እግዚአብሔር ተገልጦ ይመጣል፡፡ መጥቶም ዝም አይልም በበጎዎች ካህናት አድሮ ክፉዎች ካህናትን ይዘልፋል፡፡ አንድም እግዚአብሔር በሥጋ ማርያም ይመጣል፡፡ አንድም እግዚአብሔር ለፍርድ በክበበ ትስብእት ይመጣል፡፡ እግዚአብሔር ፈታሒ በጽድቅ ኰናኒ በርትዕ ነው፡፡ ዓለም በሙሉ በጥቅሉ የእኔ ገንዘብ ነው ይላል እግዚአብሔር፡፡ ሡዕ ለእግዚአብሔር መሥዋዕተ ስብሐት፡፡ የምሥጋና ጸሎትን ጸልይ፡፡ ስትጸልይም በንጹሕ ልቡና ከቂም ከበቀል ተለይተህ ይሁን፡፡
                   🌹መዝሙር ፶
አቤቱ እንደ ይቅርታህ ብዛት ይቅር በለኝ፡፡ ከኃጢአቴ ፈጽመህ ንጹሕ አድርገኝ፡፡ አቤቱ በማየ ንስሓ ታጥበኛለህ እኔም ከበረድ ይል ንጹሕ እሆናለሁ፡፡ አቤቱ ንጹሕ ልቡና ፍጠርልኝ፡፡ ልቡናዬን በዕውቀት አድስልኝ፡፡ አቤቱ አንደበቴ ቸርነትህን በመናገር ደስ ይለዋል፡፡ የእግዚአብሔር መሥዋዕቱ የየዋህ ሰው ልቡና ነው፡፡
                   🌹መዝሙር ፶፩
በቤተ እግዚአብሔር ያለ ዕፀ ዘይት ቀን ከአዕዋፍ ሌሊት ከአራዊት በአጥር ተጠብቆ እንደሚኖር እኔም በረድኤተ እግዚአብሔር ተጠብቄ እኖራለሁ፡፡ በእግዚአብሔር ቸርነት አመንኩ፡፡ አቤቱ እግዚአብሔር ሆይ ለዘለዓለሙ እገዛልሃለሁ፡፡ ይቅርታህን ተስፋ አደርጋለሁ፡፡
                   🌹መዝሙር ፶፪
ሰነፍ ሰናክሬም በልቡ አስቦ በቃሉ እግዚአብሔር የለም ይላል፡፡ እግዚአብሔር የግብዞች የእነሰናክሬምን ወገኖች አጥፍቷል፡፡
                   🌹መዝሙር ፶፫
አቤቱ እግዚአብሔር ሆይ በስምህ በማመኔ አድነኝ፡፡ በእውነተኛነትህ ፍረድልኝ፡፡ እነሆ ጌታዬ እግዚአብሔር ሰውነቴን ረድቶ ያድናታል፡፡ አቤቱ የምወደውን ከአሥር አንድ ሰጥቼ ደስ አሰኝሃለሁ፡፡ ዘእምፈቃድየ እሠውዕ ለከ፡፡ ስምህን ማመስገን ያማረ የተወደደ ነውና አቤቱ ለስምህ እገዛለሁ፡፡ ከመከራዬ ሁሉ አድነኸኛልና፡፡
                   🌹መዝሙር ፶፬
አቤቱ ልመናዬን ስማኝ፡፡ ልመናዬን ቸል አትበልብኝ፡፡ በዐይነ ምሕረትህ አይተህ ተመልክተህ ልመናዬን ስማኝ፡፡ አቤቱ ወዳጅ መስለው ከሚቀርቡኝ ከጠላቶቼ ሰውነቴን አድናት፡፡ ግድፍ ላዕለ እግዚአብሔር ኅሊናከ ወውእቱ ይሴስየከ፡፡
                   🌹መዝሙር ፶፭

ገዳማውያን

21 Dec, 09:04


🥀መዝሙረ ዳዊት ክፍል 7🥀

🌹መዝሙር ፭
መዝሙር 5 ስለትሩፋን የተጻፈ ነው፡፡ ትሩፋን የሚላቸው አሥሩ ነገድ ተማርከው በኢየሩሳሌም የቀሩ ሁለቱ ነገድ ናቸው፡፡ አንድም ሁሉም ተማርከው አበው አልቀው የቀሩ ውሉድ ናቸው፡፡ አቤቱ ልመናዬን ስማኝ፡፡ ጌታ ሆይ የእኔ ንጉሤም ፈጣሪዬም አንተ ነህ፡፡ እግዚኦ ምርሐኒ በጽድቅከ፡፡ ሰውን መበደል እግዚአብሔርን ማሳዘን ነው፡፡
                   🌹መዝሙር ፮
ዳዊት በቤርሳቤህ ምክንያት ያስገደለው ኦርዮ የጌታ ምሳሌ ነው፡፡ ኦርዮ ጦማረ ሞቱን ይዞ ከኢየሩሳሌም ወደ አራቦት እንደሄደ ጌታም ከሊቶስጥራ ወደ ቀራንዮ መስቀሉን ተሸክሞ ሄዷልና፡፡ በቀድሞው ዘመን ነቢያት ዘመነ ሣህል ወርኀ ሰላም ነው ሲሉ ኩፋር ለብሰው ኩፋር ጠምጥመው በአምባላይ ፈረስ ተቀምጠው መነሳንስ ይዘው ይታያሉ፡፡ ዘመነ ፀብዕ ወርኀ ኀዘን ነው ሲሉ ከል ለብሰው ከል ጠምጥመው ዘገር ይዘው ይታያሉ፡፡ ዳዊት ኦርዮን በማስገደሉ ተጸጽቶ ጉድጓድ ምሶ አመድ ነስንሶ ማቅ ለብሶ ንስሓ ገባ፡፡ በእንባው የበቀለ ሰርዶ ሰውነቱን ተብትቦ ይዞት ብላቴኖቹ በመቀስ እያረፉ አውጥተውታል፡፡ ዳዊት በነፍሱ ይቅር ሲባል በሥጋው ግን ኃጢአት ያለፍዳ አይነፃምና ልጁ እንዲያሳድደው ሆኗል፡፡

                   🌹መዝሙር ፯
ንጉሥ ዳዊት በእርሱ ላይ ክፉ ምክር ይመክር ነበረውን የአኪጦፌልን ምክር ለውጣት እያለ ይጸልይ ስለነበር መልካሙ የኵሲ ምክር ደረሰው፡፡ ይህ መዝሙር 7 ዳዊት ልጁ አቤሴሎም ባሳደደው ጊዜ ከወይራ ስር ሆኖ የጸለየው መዝሙር ነው፡፡ እግዚአብሔር በአሕዛብ ይፈርድባቸዋል፡፡ እግዚአብሔር ልብ ያሰበውን ኵላሊት ያጤሰውን መርምሮ ያውቃል፡፡ ቅን ልቡና ያላቸውን ሰዎች የሚያድናቸው እግዚአብሔር በእውነት ይረዳኛል፡፡ እግዚአብሔር ፈታሒ በጽድቅ ኰናኒ በርትዕ ነው፡፡ ኃያል ነው ታጋሽም ነው፡፡ አኪጦፌል ራሱ በመከረው ክፉ ምክር ጠፋ፡፡ ልዑል ለሚሆን ለእግዚአብሔር ምስጋና አቀርባለሁ፡፡
                   🌹መዝሙር ፰
ዳዊት ኢየሱስ ክርስቶስን ሕፃናት በሆሣዕና ሲያመሰግኑት ጊዜው ሳይደርስ ተገልጾለት እግዚኦ እግዚእነ ጥቀ ተሰብሐ ስምከ በኵሉ ምድር አለ፡፡ አቤቱ ከሕፃናት አንደበት ምስጋናን ተቀበልክ፡፡ ዲያብሎስ ለ5500 ዘመን የሰውን ልቡና እንደ ዙፋን ሰውነቱን እንደ ድንኳን ፍትወታት እኩያት ኃጣውእን እንደ አጥር እንደ ቅጥር አድርጎ ይገዛ ነበር፡፡ ጌታ ሰው ከሆነ በኋላ ግን እየወጣ ሄዷል፡፡

                   🌹መዝሙር ፱
ዳዊት ይህንን መዝሙር ዘጠኝን ጠላቶቹ ተካተው ከጠፉለት፣ መንግሥቱ ከተደላደለለት በኋላ ተናግሮታል፡፡ አቤቱ እግዚአብሔር ሆይ በፍጹም ልቡናዬ አመሰግንሃለሁ፡፡ ጌትነትህን፣ ተአምራትህን ሁሉ እነግራለሁ አስተምራለሁ፡፡ በአንተ በማመኔ ደስ ይለኛል፡፡ አጋንንት በመስቀል በጥምቀት ጠፉ ማለት ድል ተነሡ፡፡ ጌታ ሆይ ስምህን የሚወዱ ሁሉ በአንተ አምነው ፀንተው ይኖራሉ፡፡ በሕግ በአምልኮ የሚሹህን በመከራ አትጥላቸውምና፡፡ አቤቱ በትድግናህ ደስ ይለናል፡፡ አሕዛብ በሠሩት ሥራ ጠፉ፡፡ ሠውረው በመከሩት ምክር በሸመቁት ጦር ጠፉ፡፡ እግዚአብሔር ፍርድን መፍረድ ያውቃል፡፡ ማናቸውንም ድኻ የሚዘነጋ አይደለም፡፡ ለጊዜውም ቢዘነጋ እንደዘነጋ አይቀርም፡፡ ነዳያን ለዘለዓለሙ ዓስበ ትዕግሥታቸውን አያጡም፡፡ ዳዊት እግዚአብሔርን አቤቱ ለምን ርቀህ ቆመሀል ማለቱ በጌታ መራቅ መቅረብ ኑሮበት አይደለም መራዳቱን መቅረብ አለመራዳቱን መራቅ ብሎት ነው፡፡ ኃጢአት ሠርቶ ንስሓ አለመግባት እግዚአብሔርን ቅሠፈኝ ማለት ነው፡፡
                   🌹መዝሙር ፲
እግዚአብሔር በሰማያዊት መቅደሱ አለ፡፡ በሰማያዊት መንበሩ አለ ማለት ይፈርዳል ዝም አይልም፡፡ ሰው በዓይን ጥቅሻ በከንፈር ንክሻ የሚሠራውን እግዚአብሔር ያውቃል፡፡ እግዚአብሔር ጻድቁን ኃጥኡን ይመረምራል፡፡ መርምሮ ለጻድቁ ዋጋውን ይሰጠዋል ለኃጥኡ ፍዳ ያመጣበታል፡፡ እግዚአብሔር እውነትን ይወዳል፡፡ አንድም እውነትን የያዘ ሰውን ይወዳል፡፡

                   🌹መዝሙር ፲፩
ዳዊት ይህንን መዝሙር የስምንተኛው ሺህ ነገር ተገልጾለት ጸልዮታል፡፡ አቤቱ እግዚአብሔር ሆይ ከስምንተኛው ሺህ ዘመን ሰው በጎ ቸር ጠፍቷልና አድነኝ፡፡ አፄ ናዖድ የስምንተኛው ሺህ ነገር ተገልጾላቸው ከጊዜው አታድርሰኝ ከእህል ከውሃው አታቅምሰኝ እያሉ ይጸልዩ ነበር፡፡ ይኸውም ሊታወቅ ስምንተኛው ሺህ በመስከረም ሊገባ በነሐሴ ሰባት ቀን አርፈዋል፡፡ በከዳተኛ አንደበት የሚነጋገሩትን ሰዎች እግዚአብሔር ያጠፋቸዋል፡፡ መቀባጠር የምታበዛ አንደበትንም ነቃቅሎ ይጥላታል፡፡ እግዚአብሔር ለእኛ አንደበትን መስጠቱ እርሱን ልናመሰግንበት ነው እንጂ ሰውን ልንሰድብበት አይደለም፡፡ ቃለ እግዚአብሔር ቃል ንጹሕ፡፡ ቃለ እግዚአብሔር ከሐሰት ከዝርውነት ንጹሕ ነው፡፡ ብረቱን ሰባት ጊዜ ከከውር ወደ ከውር ያፀሩት እንደሆነ ከብር መዓርግ ይደርሳል፡፡ ብሩ ከወርቅ ወርቁ ከዕንቊ መዓርግ ይደርሳል፡፡ አቤቱ እግዚአብሔር ሆይ ጠብቀን፡፡

                   🌹መዝሙር ፲፪
አቤቱ ፈጣሪዬ ልመናዬን ሰምተህ በዓይነ ምሕረትህ እየኝ ተመልከተኝ፡፡ እኔ በይቅርታህ በቸርነትህ አመንኩ፡፡ በትድግናህም ልቡናዬ ደስ ይለዋል፡፡ የረዳኝን እግዚአብሔርን አመሰግነዋለሁ፡፡ እሴብሖ ለእግዚአብሔር ዘረድአኒ፡፡ ልዑል ለሚሆን ስሙም ምስጋናን አቀርባለሁ፡፡
                   🌹መዝሙር ፲፫
ይህ መዝሙር ትንቢት ስለሕዝቅያስ ነው፡፡ ሰነፍ ሰናክሬም በልቡ አስቦ በቃሉ እግዚአብሔር የለም ይላል፡፡ ከመንፈስ ቅዱስ የተለየ ሰውነት ርኩስ ነው፡፡ የአይሁድ እግራቸው ደመ ወልደ እግዚአብሔርን ለማፍሰስ ፈጣን ነው፡፡
                   🌹መዝሙር ፲፬
በንጹሕ ሥራ ጸንቶ የሚኖር፣ በልቡ አስቦ በቃሉ እውነትን የሚናገር፣ በአንደበቱ ምሎ ያልከዳ፣ በባልንጀራው ክፉ ያልሠራ ሰው መከራ ሥጋ መከራ ነፍስ መጥቶበት አይታወክም፡፡
                   🌹መዝሙር ፲፭
ሰው በጎ ሥራ ቢሠራ ራሱን ይጠቅማል ክፉ ሥራ ቢሠራ ራሱን ይጎዳል እንጂ በጎ ሥራ ቢሠራ እግዚአብሔርን የሚጠቅመው ክፉ ሥራ ቢሠራ እግዚአብሔርን የሚጎዳው አይደለም፡፡ እባርኮ ለእግዚአብሔር ዘአለበወኒ፡፡ የልቡና ደስታ ምሥጢር መመርመር የአንደበት ደስታ ምሥጢር መናገር ነው፡፡
                   🌹መዝሙር ፲፮
አቤቱ ልመናዬን ስማኝ፡፡ የዳዊት ልመና በክት ልቡና ነው፡፡ እግረ ልቡናዬን በአምልኮትህ አጽናው ሰኮና ልቡናዬ በአምልኮተ ጣዖት በገቢረ ኃጢአት እንዳይሰነካከል፡፡
                   🌹መዝሙር ፲፯
እግዚአብሔር ብዋጋ ኃይሌ ብሸሽ አምባ መጠጊያዬ ነው፡፡ ፈጣሪዬ እግዚአብሔር ረዳቴ ነው፡፡ የታመነ ወዳጄ የታመነ ረዳቴ ነው፡፡ በለመንኩት ጊዜ ከጠላቶቼ የምድንበት እግዚአብሔር ነው፡፡ መከራ ባገኘኝ ጊዜ እግዚአብሔርን ለመንኩ፡፡ ልመናዬንም በሰማያዊት መቅደሱ ሆኖ ሰማኝ፡፡ ልዑል ባሕርዩን ዝቅ ዝቅ አድርጎ ሰው ሆነ፡፡ በመስቀሉም መርገመ ሥጋ መርገመ ነፍስን አጠፋ፡፡ ሥጋ በተዋሕዶ ዐረገ፡፡ ከአለበት ዓለም ወደ አለበት ዓለም መጣ፡፡ ሰው ከቆመበት እግሩ ሳይነቀል የወደቀ ዕቃ ይዞ እንዲነሣ እርሱም (ወልድም) ከባሕርይ አባቱ ከአብ ከባሕርይ ሕይወቱ መንፈስ ቅዱስ ሳይለይ ሠላሳ ሦስት ዓመት ከሦስት ወር የሰውነት ሥራ ሲሠራ ኖሯል፡፡ ልዑል እግዚአብሔር በነቢያት አድሮ ልጄ ይወርዳል ይወለዳል የሚል ድምፅ አሰማ፡፡ ልጁን ለኵነተ ሥጋ

ገዳማውያን

21 Dec, 03:13


​​​​🕯እንኳን ለታላቁ አባት አባ ሳሙኤል ዘዋልድባ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ።🕯

⭐️የታላቁ ገዳም የዋልድባ ገዳም አቅኚ፤
⭐️ፍጹም ተሓራሚ መናኒ፤
⭐️ንጹሕ ካህን፤
⭐️የእመቤታችን ወዳጅ፤
⭐️አበ መነኮሳት፤
⭐️ከሰባቱ ከዋክብት አንዱ፤

ከሆኑት ከእኒህ አባታችን ረድኤት በረከት ያሳትፈን። ለሀገራችን ሰላም ፤ ለቤተክርስቲያናችን አንድነት ፤ ለእኛም ሱታፌ እግዚአብሔርን እንዲሰጠን ከልዑል እግዚአብሔር ያማልዱን።
አሜን።

#Share
@Gedamaweyan         @Gedamaweyan
@Gedamaweyan         @Gedamaweya

ገዳማውያን

15 Dec, 05:10


​​​ታኅሣሥ 6
ቅድስት አርሴማ(ቅዳሴ ቤቷ)


እናታችን ቅድስት አርሴማን በምን እንመስላታለን? እርሷ በአድማስ ላይ ተቀምጦ እንደሚያበራ እንቁ ናትና ክብሯ ብዙ ነው። 

መድኃኒታችን ክርስቶስ በወንጌል እንዳለው "በተራራ ላይ ያለች ከተማ ልትሠወር አይቻላትምና። "(ማቴ. ፭፥፲፩) የሰማዕቷ ሕይወት በፊታችን እንደ ብርሃን ተገልጦ ይታያል። ቅድስት አርሴማ እንደ ልጅ ወላጆቿን በመታዘዝ ደስ ያሰኘች ቡርክት ናት። ቅድስት አርሴማ ይህ ቀረሽ የማይሏት ውብ ናት።

ቅድስት አርሴማ ድንግል ናት። ቅድስት አርሴማ ባሕታዊት ጻድቅ ናት። ቅድስት አርሴማ ኃያል ሰማዕት ናት። ይህስ እንደ ምን ነው ቢሉ፦ አበው በትውፊት እንደ ነገሩን ቅዱሱ ጐርጐርዮስ የታላቋ ሰማዕት ቅድስት አርሴማ ትልቅ ወንድም ነው። በዜና ሰማዕታት ተጽፎ እንደሚገኘው በዚያ የመከራ ዘመን ቅዱስ ጐርጐርዮስ ሦስት ኃላፊነቶች ነበሩበት፦

፩.ቅድስት አርሴማን ጨምሮ ደናግሉን ማጽናት፤
፪.ትምሕርተ ቤተ ክርስቲያንን በሚገባ ማጥናት፤
፫.የሚመጣውን መከራ ለመቀበል ራሱን ማዘጋጀት። ቅዱሱ ሦስቱንም ኃላፊነቶች በሚገባ በመወጣቱ ከራሱ አልፎ ለሌሎቹ አርአያ መሆን ቻለ። ያቺን ንጽሕት አርበኛ ቅድስት አርሴማንም አጽንቶ የደናግሉ መሪ አደረጋት። 

መከራው ገፍቶ እስከ መጣበት ጊዜ በአንድ የደናግል ገዳም ውስጥ ሆነው ይጸልዩ፣ ይጾሙ፣ ገዳማዊ ሥራንም ይሠሩ ነበር። ለዚህም ነው ቅድስት አርሴማና ቅዱስ ጐርጐርዮስን ጻድቃን የምንላቸው። በኋላ ግን ማኅደረ ሰይጣን ዲዮቅልጢያኖስ በመልኳ ተማርኮ ቅድስት አርሴማን ካላገባሁ በማለቱ ቅዱስ ጐርጐርዮስ ድንግሏን አርሴማን ጨምሮ ክርስቲያኖችን ይዞ ወደ አርማንያ ተሰደደ።

በአርማንያም በአንድ ገዳም ውስጥ ተደብቀው በጾምና በጸሎት ለጥቂት ጊዜ ቆዩ። ነገር ግን ረሃብ ፈጃቸው። የሚላስ የሚቀመስ ነገር በአካባቢው ባለ መኖሩ ቅዱስ ጐርጐርዮስ ወደ ከተማ ለመውጣት ተገደደ። በዚያም በድርጣድስ ቤተ መንግሥት ውስጥ ባርነት ተቀጠረ። በሚያገኛት ገንዘብም ወገኖቹን ይረዳ ነበር። መከራው ግን አለቀቃቸውም።

ርጉም ዲዮቅልጢያኖስ ቅዱሳኑ ወደ አርማንያ መሔዳቸውን ስለ ሰማ ይዞ እንዲልክለት ድርጣድስን ላከው። ድርጣድስ ግን ቅድስት አርሴማን ባያት ጊዜ ከውበቷ የተነሳ መታገስ ባለመቻሉ "ካላገባሁሽ" አላት። ድንግሊቱ ግን "እኔ የክርስቶስ ሙሽራ ነኝ፤ አይሆንም።" አለችው። ሊያስፈራራት ሞከረ። ዓይኗ እያየ ደናግሉን ጨፈጨፋቸው። አልሳካልህ ቢለው በአደባባይ በግድ ሊያገባት ቢሞክር እጁን ጠምዝዛ በሰው ሁሉ ፊት መሬት ላይ ጣለችው።

እጅግ ስላፈረ አስገረፋት፣ አሰቃያት፣ ዓይኗንም አወጣ። በመጨረሻም አንገቷን አስቆርጦ ከሰማዕታቱ ጋር ተራራ ላይ ጣላት። ከነገር ሁሉ በኋላ ድርጣድስና ባለሟሎቹ ለአደን በሔዱበት ርኩስ መንፈስ ወደ አውሬነት (እሪያነት) ቀየራቸው። የንጉሡ እንስሳ (አውሬ) መሆን በአርማንያ ታላቅ ድንጋጤን ፈጠረ። የንጉሡ እኅት ስታለቅስ በራእይ "ለእመ ኢያዕረግምዎ ለጐርጐርዮስ አልብክሙ ድኂን - ጐርጐርዮስን ከተቀበረበት ካላወጣችሁት አትድኑም።" አላቸው። ወዲያውም ቆፍረው አወጡት። ቅዱሱ እንደ ወጣ ዕረፍትን አልፈለገም።

ለአሥራ አምስት ዓመታት ቀባሪ አጥቶ የተበተነውን የቅድስት አርሴማንና የሰማዕታቱን አጽም ሰብስቦ በክብር አኖረው። ድርጣድስና ባለሟሎቹንም ወደ በርሃ ሒዶ ፈወሳቸው። የሰማዕቷ ቅድስት አርሴማ አጽም በአሥራ አራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ከሌሎች ሰማዕታት አጽም ጋር ኢትዮጵያ እንደ መጣ አባቶቻችን በትውፊት ነግረውናል። ለዚህም ነው ቡርክቷ እናታችን ከሌሎች ሃገራት ለይታ ለኢትዮጵያውያን ልዩ ፍቅር ያላት። 

በዋናው ገዳሟ (ወሎ /ኩላማሶ/ ስባ ውስጥ የሚገኝ ነው።) ጨምሮ ስሟ በተጠራበት ሁሉ ኃይልን ታደርጋለችና። ነገር ግን ወንድሞቼና እኅቶቼ በቅድስቷ እናታችን ስም የሚነግዱ ሥጋውያን ሰዎች በዝተዋልና እንጠንቀቅ። የሰማዕቷ ክብር ብዙ ነውና በሕልም ላይ ብቻ አንታመን። አባ እንጦንስ እንዳሉት "በሕልሙ የሚታመን ሰው ከንቱ ነውና።" (መዝ. ፸፭፥፭)

በዚህ ዕለት ከሰማዕቷ ጋር የመንፈስ እናቷን ቅድስት አጋታን ልናስባት ይገባናል። ይህች እናት እመ ምኔት ስትሆን ቅድስት አርሴማን ታስተምራት፣ ታጸናት፣ ከጐኗም ትቆምላት ነበር። ረሃቧን፣ ጥሟን፣ ስደቷን፣ መከራዋንም ሁሉ አብራት ተሳትፋለች። በፍጻሜውም አብራት ተሰይፋለች። ይህች ዕለት ለቅድስት አርሴማና ለተከታዮቿ ሰማዕታት የፍልሰትና የቅዳሴ ቤት መታሰቢያ ናት። 

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
#Share
@Gedamaweyan         @Gedamaweyan
@Gedamaweyan         @Gedamaweyan

ገዳማውያን

12 Dec, 04:42


❝ ከመዝ ነበርኪ ውስተ ቤተመቅደስ ወመላእክት ያመጽኡ ወትረ ሲሳየኪ ከመ ነበርኪ ፲ወ፪ተ ዓመተ እንተ ትትናዘዚ እምኀበ መላዕክት ስቴኪኒ ስቴኪኒ ስቴ ህይወት ውእቱ ወመብልዕከኒ ኀብስት ሰማያዊ ❞

      ትርጉሙም

እንዲህ ኹነሽ በቤተመቅደስ ኖርሽ፤መላዕክትም ዘወትር ምግብሽን ያመጡ ነበር፤መላዕክት እየጎበኙሽ እንደዚህ ዐሥራ ሁለት ዓመት ኖርሽ

       ሊቁ ቅዱስ ያሬድ

ገዳማውያን

08 Dec, 06:50


ገዳማውያን pinned «🌹መዝሙረ ዳዊት ክፍል 6🌹                         🌹ምዕራፍ ፫ ሰይጣን ያስጀመረውን አያስፈጽምም፡፡ እግዚአብሔር ሆይ ዘውዴ አንተ ነህ፡፡ ዘውድ እንዲያስከብር የምታስከብረኝ አንተ ነህ፡፡ ልመናዬን ወደ እግዚአብሔር አቀረብኩ፡፡ (እርሱም) በሰማያዊት መቅደሱ ሆኖ ልመናዬን ሰማኝ፡፡                        🌹ምዕራፍ ፬ ሳዶቅ የሚባል አንድ ሰው ነበረ፡፡ ሰው ሙቶ መቃብር ከገባ በኋላ…»

ገዳማውያን

08 Dec, 06:50


🌹መዝሙረ ዳዊት ክፍል 6🌹
                        🌹ምዕራፍ ፫
ሰይጣን ያስጀመረውን አያስፈጽምም፡፡ እግዚአብሔር ሆይ ዘውዴ አንተ ነህ፡፡ ዘውድ እንዲያስከብር የምታስከብረኝ አንተ ነህ፡፡ ልመናዬን ወደ እግዚአብሔር አቀረብኩ፡፡ (እርሱም) በሰማያዊት መቅደሱ ሆኖ ልመናዬን ሰማኝ፡፡
                       🌹ምዕራፍ ፬
ሳዶቅ የሚባል አንድ ሰው ነበረ፡፡ ሰው ሙቶ መቃብር ከገባ በኋላ ፈርሶ በስብሶ ይቀራል ነፍሱም እንደ ጉም ሽንት በንና ትቀራለች የሚል ነው፡፡ የእርሱን ባህል የያዙ ሁሉ ሰዱቃውያን ተብለዋል፡፡ ማኒ ገንዘብ ጠፋበት ገንዘቡም አህያ ነው፡፡ በጾም በጸሎት በቀኖና ስኖር እንዴት የእኔ ገንዘብ ይጥፋ ብሎ በጸሎቱ ተመክቶ የሐሰት መሥዋዕት ሠውቶ ቀኖና ገባ፡፡ ገንዘቤ አህያዬ ቢገኝ ሠራዒ መጋቢ አለ እላለሁ ባይገኝ ግን የለም እላለሁ አለ፡፡ ጌታም በትሕትና ቢለምኑት ነው እንጂ በሐሰት ቢለምኑት አይሰማምና ይገኝ የነበረውን አጠፋበት ይቀርብ የነበረውን አራቀበት፡፡ ሱባኤው ሲፈጸም አልባቲ ሠራዒ ወመጋቢ ለዛቲ ዓለም፡፡ ለዚህች ዓለም ሠራዒ መጋቢ የላትም ብርሃናት በልማድ ይመላለሳሉ፣ አፍላጋት በልማድ ይፈሳሉ፣ ክረምትና በጋ ቀንና ሌሊት በልማድ ይፈራረቃሉ፣ ሰውም በልማድ ይወለዳል በልማድ ይሞታል ብሎ ተነሣ፡፡ መዝሙር 4ን ዳዊት የጻፈው ለማኒ ምላሽ ነው፡፡ የሚገባ ቁጣ ሕፃናት የተማሩትን እንዳይገድፉ፣ ከሓድያን ሃይማኖትን እንዳይነቅፉ መቆጣት ነው፡፡ የክርስቶስን ሥጋውን ደሙን ከመቀበላችን የተነሣ ሃይማኖት ፀናልን፣ ጸጋ ክብር ጸናልን፡፡

© በትረ ማርያም አበባው


#Share
@Gedamaweyan         @Gedamaweyan
@Gedamaweyan         @Gedamaweya

ገዳማውያን

02 Dec, 02:58


🌹23 ቅዱስ ጊዮርጊስ🙏

🌹
#ሰአል ለነ ጊዮርጊስ ኅበ እግዚአብሔር ወጸሊ በእንቲአነ ሀረድዎ ገመድዎ፣ ወዘረው ሥጋሁ ከመ ሀመድ ፣ ወወሰድዎ ሀበ ሰባ ነገሥት ረገጸ ምድረ አንስአ ሙታን አባ ጊዮርጊስ በሰላም አደወ መንግሥተ ክብር ወረሰ።🙏

#ጊዮርጊስ ሆይ ወደ እግዚአብሔር ስለ እኛ ለምንልን።አርደው ከፋፈሉት ሥጋውንም እንደ ትቢያ በተኑት ወደ ሰባ ነገሥታት ወሰዱት ።
ምድርን ረገጠ ሙታንን አስነሳ። አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
#በሰላም(በጽናት)ተሸጋግሮ የክብር መንግሥትን ወረሰ።

የሰማእቱ ጥበቃ አይለን🥀

ገዳማውያን

02 Dec, 02:52


ገዳማውያን pinned «💙መዝሙረ ዳዊት ክፍል 5💙                      💙መዝሙር ፪ ለምንት አንገለጉ አሕዛብ የሚለው ዓይነት ደረቅ ሐዲስ ይባላል፡፡ ለዳዊት የክርስቶስ ስቅለት ተገልጾለት የጻፈው ነው፡፡ ከንቱ ማለት አስበውት ሳይሠሩት የቀረ ነው፡፡ አብ ዝንቱ ውእቱ ወልድየ ብሎ የመሰከረለት ወልድን ዕሩቅ ብእሲ ማለት አብን ዕሩቅ ብእሲ ማለት ነው፡፡ መንፈስ ቅዱስ በአምሳለ ርግብ ወርዶ ለወልድ ከመሰከረለት በኋላ ዕሩቅ…»

ገዳማውያን

02 Dec, 02:52


💙መዝሙረ ዳዊት ክፍል 5💙
                     💙መዝሙር ፪
ለምንት አንገለጉ አሕዛብ የሚለው ዓይነት ደረቅ ሐዲስ ይባላል፡፡ ለዳዊት የክርስቶስ ስቅለት ተገልጾለት የጻፈው ነው፡፡ ከንቱ ማለት አስበውት ሳይሠሩት የቀረ ነው፡፡ አብ ዝንቱ ውእቱ ወልድየ ብሎ የመሰከረለት ወልድን ዕሩቅ ብእሲ ማለት አብን ዕሩቅ ብእሲ ማለት ነው፡፡ መንፈስ ቅዱስ በአምሳለ ርግብ ወርዶ ለወልድ ከመሰከረለት በኋላ ዕሩቅ ብእሲ ማለት መንፈስ ቅዱስንም የዕሩቅ ብእሲ ሕይወት ማለት ነው፡፡ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ፀወነ ሥጋ ፀወነ ነፍስ ፀወነ ጻድቃን ወኃጥኣን ናትና ጽዮን ትባላለች፡፡ ክርስቶስን የባሕርይ አምላክ ወንጌልን ፍጽምት ሕግ በሉ፡፡ ክርስቶስን ዕሩቅ ብእሲ ወንጌልን ዲቃላ ሕግ አትበሉ፡፡ ለእግዚአብሔር በመፍራት በመንቀጥቀጥ ተገዙ፡፡

© በትረ ማርያም አበባው


#Share
@Gedamaweyan         @Gedamaweyan
@Gedamaweyan         @Gedamaweya

ገዳማውያን

30 Nov, 05:47


++"++ አፄ #ፋሲል ያሰሩትና ለ300 ዓመታት ታቦተ ጽዮን የኖረችበት ቤተ ክርስቲያን (እዚያው #አክሱም) ++"++

"#ማርያም #ጽዮን ለእግዚአብሔር ታቦተ ሕጉ::
ያንጽሐኒ እምፍቅረ ወርቅ ለማየ ኪዳንኪ አይጉ::
እስመ ፍቅረ ንዋይ ተብሕለ ለሰይጣን ኤረጉ::" (መልክዐ ኪዳነ ምሕረት)

<< ክብሯ ይብዛልን >>

https://t.me/zikirekdusn

ገዳማውያን

30 Nov, 05:47


ቅዱስ ዘኬዎስ አጭሩ

¹-² ወደ ኢያሪኮም ገብቶ ያልፍ ነበር። እነሆም ዘኬዎስ የሚባል ሰው፥ እርሱም የቀራጮች አለቃ ነበረ፥ ባለ ጠጋም ነበረ።
³ ጌታ ኢየሱስንም የትኛው እንደ ሆነ ሊያይ ይፈልግ ነበር፤ ቁመቱም አጭር ነበረና ስለ ሕዝቡ ብዛት አቃተው።
⁴ በዚያችም መንገድ ያልፍ ዘንድ አለውና ያየው ዘንድ ወደ ፊት ሮጦ በአንድ ሾላ ላይ ወጣ።
⁵ ጌታ ኢየሱስም ወደዚያ ስፍራ በደረሰ ጊዜ፥ አሻቅቦ አየና፦ ዘኬዎስ ሆይ፥ ዛሬ በቤትህ እውል ዘንድ ይገባኛልና ፈጥነህ ውረድ አለው።
⁶ ፈጥኖም ወረደ በደስታም ተቀበለው።
⁷ ሁሉም አይተው፦ ከኃጢአተኛ ሰው ጋር ሊውል ገባ ብለው አንጐራጐሩ።
⁸ ዘኬዎስ ግን ቆሞ ጌታን፦ ጌታ ሆይ፥ ካለኝ ሁሉ እኵሌታውን ለድሆች እሰጣለሁ፤ ማንንም በሐሰት ከስሼ እንደ ሆንሁ አራት እጥፍ እመልሳለሁ አለው።
⁹ ጌታ ኢየሱስም፦ እርሱ ደግሞ የአብርሃም ልጅ ነውና ዛሬ ለዚህ ቤት መዳን ሆኖለታል፤
¹⁰ የሰው ልጅ የጠፋውን ሊፈልግና ሊያድን መጥቶአለና አለው። \ሉቃ፲፱÷፩\

     <<ከቅዱስ ዘኬዎስ በረከት ያድለን።>>

ገዳማውያን

30 Nov, 05:46


እንኳን አደረሰን!

☞በእንተ #እግዝእትነ #ማርያም ድንግል፤
ወበእንተ #ኢየሱስ #ክርስቶስ ወልዳ ፍቁር፤

☞ዝክሩ ስመ አበዊነ ቅዱሳን #ነቢያት #ሙሴ #ወአሮን #ዳዊት #ወሰሎሞን #ዕዝራ #ወዘካርያስ እለ አውኃዙ ተነብዮ በእንተ አማናዊት #እምነ #ጽዮን፡፡

"" ጸጋ ዘአብ ፥ ኂሩት ዘወልድ ሱታፌ ዘመንፈስ ቅዱስ እግዚአብሔር ፡ ወበረከታ ለእምነ #ጽዮን_ማርያም ፡ ተፋቅሮ #ዘነቢያት #ወዘሐዋርያት ወዘአበው ቀደምት ቅዱሳን ፡ ወትረ የኀሉ ምስሌየ ወምስለ ኩልክሙ፡፡ አሜን፡፡ ""

https://t.me/zikirekdusn

ገዳማውያን

30 Nov, 03:14


#ኅዳር_21

#ቅድስት_ጽዮን_ድንግል_ማርያም

ኅዳር ሃያ አንድ በዚች ቀን የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የበዓልዋ መታሰቢያ ነው።

"ጽዮን" ማለት "ጸወን - አምባ - መጠጊያ" ማለት ነው። አንድም በምሥጢሩ "ማሕደረ አምላክ" ማለት ነው። ጽዮን የሚለው ስም በቁሙ ለቅዱስ ዳዊት ተራራና ለኪዳኑ ጽላት ሲያገለግል በትንቢታዊ ምሥጢሩ ግን ለድንግል ማርያም ለቤተ ክርስቲያንና ለዘለዓለማዊት ርስት ያገለግላል።

እግዚአብሔር ከዘመነ አበው በሁዋላ በጊዜው ለእሥራኤላውያን ክብር፣ ሞገስ፣ አምባ የምትሆናቸውን ታቦተ ጽዮንን በቅዱስ ሙሴ አማካኝነት ሰጥቷቸዋል። (ዘጸ. 31፥18) ከዚያም ለ500 ዓመታት ከእነሱ ጋር በመሆኗ በፈጣሪና በእነሱ መካከል ድልድይ ሆና ኖራለች።

ከዚያም ባለቤቱ ሲፈቅድ በዘመነ ሳባ በቀዳማዊ ምኒልክ (እብነ መለክ-እብነ ሐኪም) አማካኝነት ወደ ኢትዮዽያ መጥታለች። እነሆ በሃገራችን የ3ሺ ዓመት ቆይታዋን ልትደፍን የቀራት ጥቂት ዓመታት ብቻ ናቸው። ጌታ እንደ ፈቀደ ቅዱስ መስቀሉንና ታቦተ ጽዮንን ይዘን ይሔው በቸርነቱ እንኖራለን።

ያም ሆኖ ታቦተ ጽዮንን መስረቅ የሚፈልጉ ብዙ ቀሳጢዎች እንዳሉ እናውቃለን። ግን አንጨነቅም። ምክንያቱም የመጣችውም የምትጠበቀውም በፈቃደ እግዚአብሔር ነውና እንጸልያለን እንጂ አንጨነቅም። በተለያየ ወሬም ራሳችንን አናማጥንም። ባለቤቱ እንድትሔድ ከፈቀደ ደግሞ ማንም ጉልበተኛ አያስቀራትም።

ታቦተ ጽዮን ብዙ ጊዜ "ጽላተ ኪዳን፣ ታቦተ ሕጉ" እየተባለች ትጠራለች። "ጽሌ" ማለት "ሰሌዳ" እንደ ማለት ሲሆን "ጽላት" ደግሞ በብዙ ቁጥር ነው። "ኪዳን" ደግሞ በፈጣሪና በሰው ልጆች መካከል ያለ "ውል - ስምምነት" ነው።

"ታቦት" ማለት "ማሕደር-ማደሪያ" እንደ ማለት ነው። ሕጉ የተጻፈባቸውን ሰላድው "ጽላት" ስንላቸው የጽላቱ ማደሪያ ደግሞ "ታቦት" ይባላል። ጽላት (ታቦትን) ያመጣ ፈጣሪ ነው። በሐዲስ ኪዳንም ምሥጢርና ሐተታ ቢኖረውም 2 ቦታ ላይ ስለ ታቦት ተጠቅሶ እናገኛለን። (2ቆሮ.6፥16 ፣ ራዕይ.11፥19)

በመጨረሻም ኅዳር ሃያ አንድ ቀን ጽዮን ማርያምን የምናከብርባቸውን ምክንያቶች እንመለከታለን።

#በዚህች_ቀን:-
✞ ታቦተ ጽዮን (ጽላተ ኪዳን) ለሊቀ ነቢያት ቅዱስ ሙሴ መሰጠቷን እናስባለን።

✞ ታቦተ ጽዮን በምርኮ በሄደችበት በሀገረ ፍልስጤም ዳጎን የተባለ የአህዛብን ጣኦት አድቅቃ በድል የተመለሰችበትን ዕለት በማሰብ።

✞ በዘመነ ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት በአሚናዳብ ሠረገላ ሁና ከአቢዳራ ቤት ስትመጣ ቅዱሱ ንጉሥ በታላቅ ሐሴት በፊቷ ዘመረ። አገለገለ። ምድራዊ ክብሩን እስኪረሳ ድረስ ለታቦተ አምላክ የተቀኘላት በማሰብ።

✞ ታቦተ ጽዮን ንጉሥ ሰሎሞን ወደ ሠራላት ቤተመቅደስ በክብር የገባችበትን ዕለት በማሰብ፤

✞ የቀደሙ ነብያት ስለእመቤታችን በተለያየ አምሳል ያዩበት ለምሳሌ፦ ነብዩ ዕዝራ በሃገር መንፈሳዊት፣ ሕዝቅኤል በተዘጋች ቤተመቅደስ፣ ዘካርያስ በተቅዋመ ወርቅ ወዘተ ያዩበትን ዕለት በማሰብ፤

✞ ቀዳማዊ ምኒሊክ ከዐሥራ ሁለቱ ነገድ እስራኤል የበኩር ልጅ ጋር ሊቀ ካህናቱን  አዛሪያስንና ታቦተ ጽዮንን ይዞ አክሱም የደረሰበትን ዕለት በማሰብ፤

✞ በዘመነ አፄ ባዜን (በ4 ዓ/ም አካባቢ) አማናዊት ጽዮን ድንግል ማርያም ወደ አክሱም ጽዮን በስደት መጥታ ገብታለች። በዚህ ጊዜም 2ቱ ጽዮኖች ሲገናኙ ታላቅ ብርሃን አክሱምን ውጧታልና ይህንንም በማሰብ፤

✞ በአብርሃ ወአፅብሃ ዘመነ መንግስት ክርስትና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሃይማኖት ሆኖ አዋጅ የታወጀበትን በማሠብ፤

✞ አብርሃ ወአጽብሃ በወርቅና በዕንቁ ያሠሩት ባለ አሥራ ሁለት ክፍል ቤተ መቅደስ ለመጀመሪያ ጊዜ ቅዳሴ ቤቱ የተከበረበት ዕለት በመሆኑ፤

✞ በዘጠነኛው መቶ ክፍለ ዘመን ዮዲት ጉዲት አብያተ ክርስቲያንን ስታቃጥል ታቦተ ጽዮንን ይዘው ወደ ዝዋይ ሀይቅ ከተሰደዱ በኋላ ዘመነ ሰላም ሲጀመር አክሱም በነበሩ ካህናት አስታዋሽነት ከዝዋይ ወደ አክሱም የገባችበት ዕለት በመሆኑ፤

በእነዚህ ምክንያቶች በመላው ኢትዮጵያ በተለይም በርእሰ አድባራት ወገዳማት አክሱም ጽዮን ከፍ ባለ መንፈሳዊ በዓል እናከብራለን።

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በእመቤታችን በጸሎቷ የሚገኝ በረከቷም ከሁላችን የክርስቲያን ወገኖች ጋር ይኑር።

( #ስንክሳር_ዘተዋሕዶ  እና #ዲያቆን_ዮርዳኖስ_አበበ)

እንኳን አደረሰን አደረሳችሁ!

ገዳማውያን

29 Nov, 03:52


የሚበሉና የማይበሉ ምግቦች

እግዚአብሔር አምላክ የነፍስም የሥጋም አምላክ ነው። በቅዱስ መጽሐፉም ለነፍሳችንም ለሥጋችንም የሚጠቅመንን ነግሮናል። በዘፍጥረት አንዳየነው እግዚአብሔር ለምግበ ሥጋና ለምግበ ነፍስ የሚሆነውን ሁሉ ፈጥሮልናል። ስለዚህም ከእንስሳትም ወገን ሆነ ከአትክልት ወገን የሚበላ እና የማይበላም አለ። እግዚአብሔር በነቢዩ በሕዝቅኤል እንደተናገረ ካህናት ይህንን ማስተማር አለባቸው። ምእመናንም ይህንን መረዳትና ማወቅ ይገባቸዋል።

“በተቀደሰውና ባልተቀደሰው መካከል ይለዩ ዘንድ ሕዝቤን ያስተምሩ፡ ንጹሕና ንጹሕ ባልሆነው መካከል ይለዩ ዘንድ ያሳዩአቸው።” ሕዝ. ፵፬፡፳፫ (44:23)

የሚበላው ንጹሕ ተብሎ ሲጠራ የማይበላው ደግሞ ንጹሕ ያልሆነ ተብሎ ተገልጿል። በተለይም በኦሪት ዘሌዋውያን ምዕራፍ ፲፩ (11) ዘዳግም ፲፬ (14) ላይ ተዘርዝሮ ተቀምጧል። ከዚህም የምንረዳው የሚበሉት የተሰነጠቀ ሰኮና ያላቸው ሆነው የሚያመሰኩ/የሚያመነዥኩ/ እንሰሳት ሁሉ ናቸው፡፡ ነገር ግን ከሚያመሰኩት ሰኮናቸው ስንጥቅ ያልሆነው ከነዚህ አትበሉም። ለምሳሌ ግመል ያመሰኳክ ነገር ግን ሰኮናው ሰላልተሰነጠቀ አይበላም። ሌሎችም እንደ ሽኮኮ፣ ጥንቸል፣ አሳማ (አርያ)፣ የነዚህ ሥጋ አይበላም። በውኃ ውሰጥም ካሉት ክንፍና ቅርፊት የሌላቸው አይበሉም። ከአእዋፍም አንደ ንስር፣ቁራ፣ ሰጎን፣ ጉጉት፣ አርኩም፣ ጋጋኖ፣ ጥምብ አንሣ በየወገኑ አይበላም። በዝርዝር ግን ከላይ ባሉት ሁለት ምዕራፎች መመልከት ያስፈልጋችኋል።

አንዳንድ ሰዎች ይህ ሕግ የተሰጠው በኦሪት ከሙሴ ብቻ ይመስላቸዋል። ሕጉ ግን ሰው ከተፈጠረበት ጀምሮ በሕገ ልቡና ጭምር የተገለጸ ነው። ለምሳሌ በኦሪት ዘፍጥረት ምዕራፍ ፯፡፪-፫ (7፡2-3) ከኖኅ እንደተነገረው ከኦሪቱ በፊት የሚበሉና የማይበሉ እንሰሳት አንደተጠቀሱ  እንመለከታለን።

“ከንጹሕ እንስሳ ሁሉ ሰባት ሰባት ተባዕትና አንስት፡ ንጹሕ ካልሆነ እንስሳም ሁለት ሁለት ተባዕትና አንስት፡ ከሰማይ ወፍ ደግሞ ሰባት ሰባት ተባዕትና አንስት እያደረግህ በምድር ላይ ለዘር ይቀር ዘንድ ላንተ ትወስዳለህ።

ይህ ሕግ የተጻፈው ከኦሪት በፊት በሕገ ልቡና ነውና የሚበሉና የማይበሉ እንስሳት ከኛ ጥቅም ይሆን ዘንድ እግዚአብሔር ያዘዘው መቼም የማይለወጥ ሕግ ነው። ስለዚህም ይህን የሚተላለፉ ፍርድ እንዳለባቸው በኢሳይያስ ፷፮÷፲፯ (66፡17) ላይ ተጽፏል።

በሐዋርያት ሥራ ፲ (10) ለጴጥሮስ የተነገረውን ይህንን ሕገ የማያውቁ አሕዛብ እንዳሻቸው ይበላሉና። ጴጥሮስ ሆይ ተነሣና አርደህ ብላ እግዚአብሔር ያነጻውን አንተ አታርክሰው መባሉ ጴጥሮስ እማይበሉ እንስሳትን ይበላ ዘንድ ሳይሆን የሚበሉትን ግን ወደ እግዚአብሔር መንግሥት እንዲያመጣ የተገለጸ ራእይ ነበር።

እግዚአብሔር እነዚህን ከእንስሳት፣ ከአትክልት፣ ከአዝርእትም ወገን እንዳይበሉ ያዘዘበት ምክንያት በፍትሐ ነገሥት አንቀጽ ፳፫፡፰፻፫ ስለ ምግብ በተገለጸው እንዲህ ተነግሯል።

እኒህንም የሚከለክሏቸው በውስጣቸው ነፍሰን (ሰዉነትን) የሚጎዳ ሕማም ስላለ ነው፡፡ ለጣዖታት የተሠዋውን በመብላት ጣዖትን ከሚያመልኩ ጋር አንድ መሆን በአምልኮታቸው አንድ የሚያደርጋቸው ይሆናልና። ይህም ጣዖትን ወደ ማምለክ ይስበዋል። ነፍስንም ሥጋንም የሚጎዳ ሕማም በውስጡ ስላለ ነው። ይህች መፈጠርን ወደማጥፋት በሚያደርስ ጥፋት የሥጋን ባሕሪያት ስምምነት ታጠፋለችና" ዳግመኛም አካልን ወደማጉደል ታደርሳለች።

እንግዲህ እግዚአብሔር የፈጠረው ሁሉ መልካም ሆኖ ያለ ሲሆን ሁሉንም ግን እንበላ ዘንድ አላሰናበተንም። እንጂ ፍጥረት ሁሉ
መልካም ነው። ሁሉ ተፈቅዶልኛል የሚል ሰው ቢኖር ግን ሰውን ሰው አንዳይበላው የሚያዘው ሕግ የት ነው። ስለዚህ የሚበሉና የማይበሉ ንጹሕ የሆኑና ያልሆኑ ተብለው ተለይተው ተጽፈዋል።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ፦ መጽሐፈ አሚን ወሥርዓት

#Share
@Gedamaweyan         @Gedamaweyan
@Gedamaweyan         @Gedamaweya

ገዳማውያን

28 Nov, 04:26


ገዳማውያን pinned «💙መዝሙረ ዳዊት ክፍል 4💙                      💙መዝሙር ፩ በረሲዓን ምክር ጸንቶ ያልኖረ ሰው ንዑድ ክቡር ነው፡፡ ረሲዓን የሚላቸው እንጨት ጠርበው ድንጊያ አለዝበው የሚያመልኩ ናቸው፡፡ በኃጥኣን ጎዳና ያልሄደ ሰው ንዑድ ክቡር ነው፡፡ ኃጥኣን የሚላቸው ሠርቀው ቀምተው አሥረው ፈትተው  ቋንጃ ቆርጠው ነፍስ ገድለው የሚኖሩ ናቸው፡፡ በመስተሳልቃን አደባባይ ያልተቀመጠ ሰው ንዑድ ክቡር ነው፡፡…»

ገዳማውያን

28 Nov, 04:25


💙መዝሙረ ዳዊት ክፍል 4💙
                     💙መዝሙር ፩
በረሲዓን ምክር ጸንቶ ያልኖረ ሰው ንዑድ ክቡር ነው፡፡ ረሲዓን የሚላቸው እንጨት ጠርበው ድንጊያ አለዝበው የሚያመልኩ ናቸው፡፡ በኃጥኣን ጎዳና ያልሄደ ሰው ንዑድ ክቡር ነው፡፡ ኃጥኣን የሚላቸው ሠርቀው ቀምተው አሥረው ፈትተው  ቋንጃ ቆርጠው ነፍስ ገድለው የሚኖሩ ናቸው፡፡ በመስተሳልቃን አደባባይ ያልተቀመጠ ሰው ንዑድ ክቡር ነው፡፡ መስተሳልቃን የሚላቸው ዓይኑ በፈረጠ እጅ እግሩ በተቆረጠ የሚዘብቱ ናቸው፡፡ ፈቃዱ ሕገ እግዚአብሔር የሆነለት ሰው ንዑድ ክቡር ነው፡፡ ሕጉንም በመዓልት በሌሊት የሚመለከት ሰው ንዑድ ክቡር ነው፡፡ እንዲህ ያለው ሰው በፈሳሽ ውሃ እንደተተከለች ዕፅ ይሆናል፡፡ ሰውነቱ በረድኤተ እግዚአብሔር ተጠብቆለት የሚኖር ሰው ንዑድ ክቡር ነው፡፡ የጀመረውን የሚፈጽም ሰው ንዑድ ክቡር ነው፡፡ መፈጸም እንጂ መጀመር አያስመሰግንምና፡፡ ኃጥኣን ግን ነፋስ ከመሬት እንደሚጠርገው ትቢያ ናቸው፡፡ ዕፀ ከንቱ በነግህ ትበቅላለች በሠለስት ታብባለች በቀትር ታፈራለች በተስዓት ትደርቃለች በሠርክ ኳኰርኳ ብላ ትወድቃለች፡፡ ዕፀ ከንቱ የሰው ምሳሌ ናት፡፡ ኃጥኣን ጻድቃን በመከሯቸው ምክር ጸንተው አይኖሩም፡፡ የጻድቃን ምክር ፍቅር፣ ትሕትና፣ ጾም፣ ጸሎት፣ ሰጊድ፣ ምጽዋት ነው፡፡ የኃጥኣን ምክር ስርቆት፣ መግደል፣ ዝሙት ነው፡፡ እግዚአብሔር የጻድቃንን ሥራ ይወዳል፡፡ የኃጥኣንን ሥራ ግን አይወድም፡፡

© በትረ ማርያም አበባው


#Share
@Gedamaweyan         @Gedamaweyan
@Gedamaweyan         @Gedamaweya

ገዳማውያን

23 Nov, 13:25


​​​​ጾመ ነቢያት (የገና ጾም)
ኅዳር ፲፭ ቀን

ጾመ ነቢያት በየዓመቱ ከኅዳር ፲፭ ቀን ጀምሮ እስከ በዓለ ልደት ዋዜማ ድረስ የሚጾም፤ ከሰባቱ አጽዋማት መካከል አንደኛው ጾም ነው፡፡ እግዚአብሔር አምላክ ዓለምን ለማዳን ሲል የሰውን ሥጋ ስለ መልበሱ፤ ወደ ግብጽ ስለ መሰደዱ፤ በባሕረ ዮርዳኖስ ስለ መጠመቁ፤ በትምህርቱ ብርሃንነት ጨለማውን ዓለም ስለ ማብራቱ፤ ለሰው ልጆች ድኅነት ልዩ ልዩ መከራን ስለ መቀበሉ፤ ስለ መሰቀሉ፣ ስለ ሞቱ፣ ትንሣኤው፣ ዕርገቱና ዳግም ምጽአቱ በየዘመናቱ የተነሡ ቅዱሳን ነቢያት በመንፈስ ቅዱስ ተቃኝተው ትንቢት ተናግረዋል፤ ትንቢቱ ደርሶ፣ ተፈጽሞ ለመመልከትም ‹‹አንሥእ ኃይለከ ፈኑ እዴከ፤ ኃይልህን አንሣ፤ እጅህን ላክ›› እያሉ በጾም በጸሎት ተወስነው አምላክ ሰው የሚኾንበትን ጊዜ በቀናት፣ በሳምንታት፣ በወራትና በዓመታት እያሰሉ ሲጠባበቁ ቆይተዋል፡፡

ይህ ጾም የእግዚአብሔርን ሰው መኾን ሲጠባበቁ የኖሩት የነቢያት ትንቢትና ጸሎት በጌታችን መወለድ ፍጻሜ ያገኘበት ወቅት በመኾኑ ‹‹ጾመ ነቢያት (የነቢያት ጾም)›› እየተባለ ይጠራል፡፡ ለአዳም የተነገረው የድኅት ተስፋ ስለ ተፈጸመበትም ‹‹ጾመ አዳም (የአዳም ጾም)›› ይባላል፡፡

ስለ እግዚአብሔር ሰው መኾን በስፋት ትምህርተ ወንጌል የሚሰጥበት ወቅት በመኾኑም ‹‹ጾመ ስብከት (የስብከት ጾም)››፤ የጾሙ መጨረሻ (መፍቻ) በዓለ ልደት በመኾኑ ደግሞ ‹‹ጾመ ልደት (የልደት ጾም)›› በመባል ይታወቃል፡፡

እንደዚሁም ‹‹ጾመ ሐዋርያት›› ይባላል። ቅዱሳን ሐዋርያት ‹‹በዓለ ትንሣኤን ዐቢይ ጾምን ጾመን እናከብረዋለን፤ በዓለ ልደትንስ ምን አድርገን እናከብረዋለን?›› በማለት ነቢያት የጾሙትን ከልደተ ክርሰቶስ በፊት ያለውን ጾም ጾመዋልና፡፡

በተመሳሳይ መልኩ ይህ ጾም ‹‹ጾመ ፊልጶስ (የፊልጶስ ጾም)›› ተብሎ ይጠራል፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ፊልጶስ በአፍራቅያና አውራጃዋ ዅሉ እየተዘዋወረ በጌታችን አምላካችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ወንጌልን በማስተማር፣ ድንቅ ድንቅ ተአምራትን በማድረግ ብዙዎችን ወደ አሚነ እግዚአብሔር ሲመልስ ቆይቶ ትምህርቱን በማይቀበሉ የአፍራቅያ ሰዎች አማካይነት በሰማዕትነት ዐርፏል፡፡

ደቀ መዛሙርቱ ሥጋውን ሊቀብሩ ሲሉም ስለ ተሰወረባቸው የሐዋርያውን ሥጋ ይመልስላቸው ዘንድ ሱባዔ ይዘው፣ በጾም በጸሎት ተወስነው በለመኑት ጊዜ እግዚአብሔር ልመናቸውን ተቀብሎ በ፫ኛው ቀን መልሶላቸው ሥጋውን (አስከሬኑን) በክብር አሳርፈውታል፡፡ ደቀ መዛሙርቱ የሐዋርያውን ሥጋ ካገኙ በኋላ እስከ ጌታችን ልደት ድረስ ጾመዋል፡፡ ስለዚህም ጾመ ነቢያት ‹‹ጾመ ፊልጶስ›› እየተባለ ይጠራል፡፡

ከዚሁ ዅሉ ጋርም ወልደ አምላክ ክርስቶስን በግብረ መንፈስ ቅዱስ እንደምትፀንሰው እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ካበሠራት በኋላ እመቤታችን ‹‹ሰማይና ምድር የማይወስኑትን አምላክ ፀንሼ ምን ሠርቼ እወልደዋለሁ?›› በማለት ጌታችንን ከመውለዷ አስቀድማ ጾማዋለችና ይህ ጾም ‹‹ጾመ ማርያም›› በመባልም ይታወቃል፡፡

በአጠቃላይ በዚህ በገና ጾም ነቢያትም ሐዋርያትም ጾመው በረከት አግኝተውበታል፡፡ እኛ ምእመናንም እንደ እነርሱ በረከትን እናገኝ ዘንድ ይህንን ጾም መጾም እንደሚገባን የቤተ ክርስቲያን አባቶች ሥርዐት ሠርተውልናል፡፡

በዚህም መሠረት የነቢያት፣ የሐዋርያት፣ የጻድቃንና የሰማዕታት አምላክ ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም፣ ከቅዱሳን ነቢያትና ሐዋርያት በረከት እንዲያሳትፈን፤ መንግሥቱንም እንዲያወርሰን ዅላችንም በዚህ በጾመ ነቢያት ወቅት በጾም በጸሎት ተወስነን እግዚአብሔርን ልንማጸነው ይገባል፡፡

ምንጭ፡- ፍት.ነገ ንባቡና ትርጓሜው፣ አንቀጽ ፲፭፡
ጾምና ምጽዋት፣ ዲያቆን ቃኘው ወልዴ፤ ገጽ ፵፯ -፶፡

ጾሙን የበረከት እና የምሕረት ያድርግልን! አሜን

ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡

ገዳማውያን

22 Nov, 18:01


ገዳማውያን pinned «💙መዝሙረ ዳዊት ክፍል 3💙 የመዝሙረ ዳዊት ጸሎት ለሕያዋን ዕቅበት ለሙታን ጸሎት ነው፡፡           እስመ መዝሙረ ዳዊት ትመስል ገነተ           ወታርኅቅ (ትሰድድ) አጋንንተ፡፡           ዘትጸጊ ጽጌያተ ወትፈሪ ፍሬያተ፡፡ በገነት አትክልት ሰባት ነገር አለበት። እነዚህም ጣዕም፣ ልምላሜ፣ ጽጌ፣ ስን፣ ፍሬ፣ መዓዛ፣ ቈጽል ነው፡፡ በዚህ በመዝሙረ ዳዊትም ሰባት ነገር አለበት። እነዚህም፦ …»

ገዳማውያን

22 Nov, 18:01


💙መዝሙረ ዳዊት ክፍል 3💙
የመዝሙረ ዳዊት ጸሎት ለሕያዋን ዕቅበት ለሙታን ጸሎት ነው፡፡
          እስመ መዝሙረ ዳዊት ትመስል ገነተ
          ወታርኅቅ (ትሰድድ) አጋንንተ፡፡
          ዘትጸጊ ጽጌያተ ወትፈሪ ፍሬያተ፡፡
በገነት አትክልት ሰባት ነገር አለበት። እነዚህም ጣዕም፣ ልምላሜ፣ ጽጌ፣ ስን፣ ፍሬ፣ መዓዛ፣ ቈጽል ነው፡፡ በዚህ በመዝሙረ ዳዊትም ሰባት ነገር አለበት። እነዚህም፦
               ፩.አፍቅሮ ጸላእት
               ፪.ትሕትና
               ፫.ሃይማኖት
               ፬.ተስፋ መንግሥተ ሰማያት
               ፭.ተአምኖ ኃጣውእ
               ፮.ሥርየት
               ፯.ምጽዋት ናቸው፡፡
አፍቅሮ ጸላእት አነ ዐቀብኩ ፍናወ ዕፁባተ ያለው ነው (መዝ.16፣4)፡፡ ትሕትና አንሰ ዕፄ ወአኮ ሰብእ ያለው ነው (መዝ.21፣6)፡፡ ሃይማኖት እምከርሠ እምየ አንተ አምላኪየ ያለው ነው (መዝ.21፣10)፣ ተስፋ መንግሥተ ሰማያት እትአመን ከመ እርአይ ሠናይቶ ለእግዚአብሔር በብሔረ ሕያዋን  ያለው ነው (መዝ.26፣13)፣ ተአምኖ ኃጣውእ እስመ ኖኀ እምሥዕርተ ርእስየ ጌጋይየ ያለው ነው (መዝ.37፣4)፣ ሥርየት ሕፅበኒ ወአንጽሐኒ እምኃጢአትየ ያለው ነው (መዝ.50፣2)፣ ምጽዋት ዘረወ ወወሀበ ለነዳይ ያለው ነው (መዝ.116፣29)፡፡

© በትረ ማርያም አበባው


#Share
@Gedamaweyan         @Gedamaweyan
@Gedamaweyan         @Gedamaweya

ገዳማውያን

20 Nov, 16:38


ገዳማውያን pinned «💙መዝሙረ ዳዊት ክፍል 2💙 ዳዊት መዝሙሩን በዋናነት ስለዐሥር ነገሮች ዘምሮታል፡፡ እነዚህም፦           ፩.ተግሣጽ ለኵሉ (መዝ.1፣1)           ፪.በእንተ ክርስቶስ (መዝ.2፣1)           ፫.በእንተ ርእሱ (መዝ.3፣1)           ፬.በእንተ መነናውያን (መዝ.4፣1)           ፭.በእንተ ትሩፋን (መዝ.5፣1)           ፮.በእንተ ሕዝቅያስ (መዝ.13፣1)          …»

ገዳማውያን

20 Nov, 04:09


💙መዝሙረ ዳዊት ክፍል 2💙
ዳዊት መዝሙሩን በዋናነት ስለዐሥር ነገሮች ዘምሮታል፡፡ እነዚህም፦
          ፩.ተግሣጽ ለኵሉ (መዝ.1፣1)
          ፪.በእንተ ክርስቶስ (መዝ.2፣1)
          ፫.በእንተ ርእሱ (መዝ.3፣1)
          ፬.በእንተ መነናውያን (መዝ.4፣1)
          ፭.በእንተ ትሩፋን (መዝ.5፣1)
          ፮.በእንተ ሕዝቅያስ (መዝ.13፣1)
          ፯.በእንተ ኤርምያስ (መዝ.34፣1)
          ፰.በእንተ መቃብያን (መዝ.43፣1)
          ፱.በእንተ ዘለፋ ካህናት (መዝ.49፣1)
          ፲.በእንተ ሰሎሞን ወልዱ (መዝ.71፣1)
ናቸው። በእነዚህ በአሥሩ አርእስት ደግሞ አምስት ነገር አለባቸው፡፡ እነዚህም፦
              ፩.ተግሣጽ ለኵሉ (መዝ.1)
              ፪.ምዕዳን (መዝ.37)
              ፫.ጸሎት (መዝ.101)
              ፬.ትንቢት (መዝ.109)
              ፭.አኰቴት (መዝ.29) ናቸው፡፡

© በትረ ማርያም አበባው


#Share
@Gedamaweyan         @Gedamaweyan
@Gedamaweyan         @Gedamaweya


ገዳማውያን

19 Nov, 15:49


ገዳማውያን pinned «💙መዝሙረ ዳዊት ክፍል 1💙 ይህን መዝሙረ ዳዊት መነኮሳት፣ ካህናት፣ መዘምራን በዜማ በንባብ በቤተክርስቲያን በመዓልትም በሌሊትም ሳያቋርጡ እንዲጸልዩበት ምእመናንም ከሌላው ጸሎት ይልቅ እርሱን መላልሰው እንዲጸልዩ ታዝዘዋል፡፡ ዳዊት ማለት ልበ አምላክ፣ ኅሩይ፣ መስተሳልም፣ መስተፋቅር (የሚያዋድድ) ማለት ነው፡፡ እስራኤል አሥራቱን በኵራቱን ሳያወጡ መሥዋዕት አይሠዉም ነበረ፡፡ ልብስን ቀዶ ትቢያ ነስንሶ መሄድ…»

ገዳማውያን

19 Nov, 04:11


💙መዝሙረ ዳዊት ክፍል 1💙
ይህን መዝሙረ ዳዊት መነኮሳት፣ ካህናት፣ መዘምራን በዜማ በንባብ በቤተክርስቲያን በመዓልትም በሌሊትም ሳያቋርጡ እንዲጸልዩበት ምእመናንም ከሌላው ጸሎት ይልቅ እርሱን መላልሰው እንዲጸልዩ ታዝዘዋል፡፡ ዳዊት ማለት ልበ አምላክ፣ ኅሩይ፣ መስተሳልም፣ መስተፋቅር (የሚያዋድድ) ማለት ነው፡፡ እስራኤል አሥራቱን በኵራቱን ሳያወጡ መሥዋዕት አይሠዉም ነበረ፡፡ ልብስን ቀዶ ትቢያ ነስንሶ መሄድ በእስራኤል ባህል ትእምርተ ኀዘን ነው፡፡ ከሰው ቤት ማዘዝ አይገባም፡፡ ቢጠቅምም ባይጠቅምም ባለቤት ያውቃል እንጂ እንግዳ አያውቅምና፡፡ ቆርሶ ያላጎረሱትን ቀዶ ያላለበሱትን ብላቴና ማዘዝ አይገባም፡፡ ከመሥዋዕት የእግዚአብሔርን ትእዛዝ መስማት ይሻላል፡፡ የሳሙኤል አጋግን መግደል፣ የፊንሐስ ክስቢንና ዘምሪን መግደል ያጠመሙትን ከማቅናት ያጎደሉትን ከመምላት ተቆጥሮላቸዋል እንጂ እዳ አልሆነባቸውም፡፡ ሰው የመልክን ደም ግባት ያያል እግዚአብሔር ግን የልቡናን ቅንነት ያያል፡፡ ሳሙኤል ዳዊትን በቅብዐት ቀብቶ አነገሠው፡፡ ዳዊትም ሲቀባ ሰባት ሀብታት አድረውበታል፡፡ እነዚህም፦
          ፩.ሀብተ መንግሥት
          ፪.ሀብተ ክህነት
          ፫.ሀብተ ኃይል
          ፬.ሀብተ መዊዕ
          ፭.ሀብተ በገና
          ፮.ሀብተ ፈውስ
          ፯.ሀብተ ትንቢት ናቸው፡፡

© በትረ ማርያም አበባው


#Share
@Gedamaweyan         @Gedamaweyan
@Gedamaweyan         @Gedamaweya


ገዳማውያን

30 Oct, 17:39


🤑💵 🇫 🇴 🇷 🇪 🇽 𝗧𝗿𝗮𝗱𝗶𝗻𝗴 መማር የምትፈልጉ የሚገርም የ Forex  ቻናል ያውቃሉ

💶  𝗖𝗶𝘁𝘆 𝗙𝗼𝗿𝗲𝘅 𝗘𝘁𝗵𝗶𝗼𝗽𝗶𝗮 💶

@City_Forex_Ethiopia ይባላል ።
ተመዝገባችሁ መማር የምትፈልጉ አናግሯቸው እስከ 𝟰𝟬% Discount የሚደርስ ቅናሽ አድርገዋል !

    ☎️   +251977338586       🇪🇹
    ☎️   +251977338586       🇪🇹


      ይህን ይጫኑት  ይህን  ይጫኑት  ይህን ይጫኑት
      
👇👇 ይህን ተጭነው መመዝገብ ይችላሉ   !👇👇


█▓▒░        ►OPEN◄░►OPEN       ▒▓█
█▓▒░         ►OPEN◄░►OPEN      ▒▓█
█▓▒░         ►OPEN◄░►OPEN      ▒▓█
█▓▒░        ►OPEN◄░►OPEN       ▒▓█
💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸


👆 ይህን ይጫኑት  ይህን  ይጫኑት  ይህን ይጫኑት 👆

🇫 🇴 🇷 🇪 🇽    🇹 🇷 🇦 🇩 🇮 🇳 🇬

🇫 🇴 🇷 🇪 🇽    🇹 🇷 🇦 🇩 🇮 🇳 🇬


🎯 𝗔𝗱𝗱 𝗬𝗼𝘂𝗿 𝗖𝗵𝗮𝗻𝗻𝗲𝗹

👇 ምርጥ ምርጥ ቻናሎችን ከፈረጉ ከስር ያለውን ይጫኑ 👇

ገዳማውያን

30 Oct, 03:44


"መጥፎ ቀን እና ጥሩ ቀን የሚባል ነገር የለም። ያለው ጸሎት አድርገህ የወጣህበት ቀን እና ጸሎት ሳታደርግ የወጣህበት ቀን ነው። ያልጸለይክባቸው ቀናት በክፉ ምኞትና የሥጋ ፍላጎት የተሞሉ ስለሆኑ ክፉ ቀናት ናቸው።"


— ቅዱስ ቄርሎስ ሳድሳዊ

#Share
@Gedamaweyan         @Gedamaweyan
@Gedamaweyan         @Gedamaweyan

ገዳማውያን

15 Oct, 17:50


🤑💵 🇫 🇴 🇷 🇪 🇽 𝗧𝗿𝗮𝗱𝗶𝗻𝗴 መማር የምትፈልጉ የሚገርም የ Forex  ቻናል ያውቃሉ

💶  𝗖𝗶𝘁𝘆 𝗙𝗼𝗿𝗲𝘅 𝗘𝘁𝗵𝗶𝗼𝗽𝗶𝗮 💶

@City_Forex_Ethiopia ይባላል ።
ተመዝገባችሁ መማር የምትፈልጉ አናግሯቸው እስከ 𝟰𝟬% Discount የሚደርስ ቅናሽ አድርገዋል !

    ☎️   +251977338586       🇪🇹
    ☎️   +251977338586       🇪🇹


      ይህን ይጫኑት  ይህን  ይጫኑት  ይህን ይጫኑት
      
👇👇 ይህን ተጭነው መመዝገብ ይችላሉ   !👇👇


█▓▒░        ►OPEN◄░►OPEN       ▒▓█
█▓▒░         ►OPEN◄░►OPEN      ▒▓█
█▓▒░         ►OPEN◄░►OPEN      ▒▓█
█▓▒░        ►OPEN◄░►OPEN       ▒▓█
💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸


👆 ይህን ይጫኑት  ይህን  ይጫኑት  ይህን ይጫኑት 👆

🇫 🇴 🇷 🇪 🇽    🇹 🇷 🇦 🇩 🇮 🇳 🇬

🇫 🇴 🇷 🇪 🇽    🇹 🇷 🇦 🇩 🇮 🇳 🇬


🎯 𝗔𝗱𝗱 𝗬𝗼𝘂𝗿 𝗖𝗵𝗮𝗻𝗻𝗲𝗹

👇 ምርጥ ምርጥ ቻናሎችን ከፈረጉ ከስር ያለውን ይጫኑ 👇

ገዳማውያን

06 Oct, 19:22


🤑💵 🇫 🇴 🇷 🇪 🇽 𝗧𝗿𝗮𝗱𝗶𝗻𝗴 መማር የምትፈልጉ የሚገርም የ Forex  ቻናል ያውቃሉ

💶  𝗖𝗶𝘁𝘆 𝗙𝗼𝗿𝗲𝘅 𝗘𝘁𝗵𝗶𝗼𝗽𝗶𝗮 💶

@City_Forex_Ethiopia ይባላል ።
ተመዝገባችሁ መማር የምትፈልጉ አናግሯቸው እስከ 𝟰𝟬% Discount የሚደርስ ቅናሽ አድርገዋል !

    ☎️   +251977338586       🇪🇹
    ☎️   +251977338586       🇪🇹


      ይህን ይጫኑት  ይህን  ይጫኑት  ይህን ይጫኑት
      
👇👇 ይህን ተጭነው መመዝገብ ይችላሉ   !👇👇


█▓▒░        ►OPEN◄░►OPEN       ▒▓█
█▓▒░         ►OPEN◄░►OPEN      ▒▓█
█▓▒░         ►OPEN◄░►OPEN      ▒▓█
█▓▒░        ►OPEN◄░►OPEN       ▒▓█
💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸


👆 ይህን ይጫኑት  ይህን  ይጫኑት  ይህን ይጫኑት 👆

🇫 🇴 🇷 🇪 🇽    🇹 🇷 🇦 🇩 🇮 🇳 🇬

🇫 🇴 🇷 🇪 🇽    🇹 🇷 🇦 🇩 🇮 🇳 🇬


🎯 𝗔𝗱𝗱 𝗬𝗼𝘂𝗿 𝗖𝗵𝗮𝗻𝗻𝗲𝗹

👇 ምርጥ ምርጥ ቻናሎችን ከፈረጉ ከስር ያለውን ይጫኑ 👇

ገዳማውያን

03 Oct, 19:48


🤑💵 🇫 🇴 🇷 🇪 🇽 𝗧𝗿𝗮𝗱𝗶𝗻𝗴 መማር የምትፈልጉ የሚገርም የ Forex  ቻናል ያውቃሉ

💶  𝗖𝗶𝘁𝘆 𝗙𝗼𝗿𝗲𝘅 𝗘𝘁𝗵𝗶𝗼𝗽𝗶𝗮 💶

@City_Forex_Ethiopia ይባላል ።
ተመዝገባችሁ መማር የምትፈልጉ አናግሯቸው እስከ 𝟰𝟬% Discount የሚደርስ ቅናሽ አድርገዋል !

    ☎️   +251977338586       🇪🇹
    ☎️   +251977338586       🇪🇹


      ይህን ይጫኑት  ይህን  ይጫኑት  ይህን ይጫኑት
      
👇👇 ይህን ተጭነው መመዝገብ ይችላሉ   !👇👇


█▓▒░        ►OPEN◄░►OPEN       ▒▓█
█▓▒░         ►OPEN◄░►OPEN      ▒▓█
█▓▒░         ►OPEN◄░►OPEN      ▒▓█
█▓▒░        ►OPEN◄░►OPEN       ▒▓█
💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸


👆 ይህን ይጫኑት  ይህን  ይጫኑት  ይህን ይጫኑት 👆

🇫 🇴 🇷 🇪 🇽    🇹 🇷 🇦 🇩 🇮 🇳 🇬

🇫 🇴 🇷 🇪 🇽    🇹 🇷 🇦 🇩 🇮 🇳 🇬


🎯 𝗔𝗱𝗱 𝗬𝗼𝘂𝗿 𝗖𝗵𝗮𝗻𝗻𝗲𝗹

👇 ምርጥ ምርጥ ቻናሎችን ከፈረጉ ከስር ያለውን ይጫኑ 👇

ገዳማውያን

22 Aug, 15:59




[ አርያም በጣፋጭ የመላእክት ዝማሬ ተሞላ
]

" ልጃቸው ተሰብስበው ወዳሉበት መጥታለችና አዳምና ሔዋን ዛሬ ደስ አላቸው። በዚህች ቀን ታላቁ ዳዊት በራሱ ላይ የተዋበ አክሊል የደፋችለትን ሴት ልጁን አይቶ ደስ አለው። በዚህች ቀን ነቢዩ ኢሳይያስ ትንቢት የተናገረላት ድንግል ወደ ሙታን ሥፍራ ልትጎበኘው መጥታለችና ደስ አለው።

በዚህች ቀን ብርሃን ሲበራባቸው አይተዋልና ነቢያት ሁሉ ከመቃብራቸው ራሳቸውን ቀና አደረጉ። አርያም በጣፋጭ የመላእክት ዝማሬ ተሞላ ፣ ምድር ደግሞ ኀዘንን በተሞሉ በሐዋርያት ለቅሶ ተሞላች፡፡ ሙታንም ሕያዋንም ትርጉሙን ሊገልጹት በማይችሉት [ የተለያየ ] ዜማ ሰውና መላእክት በዚያች ዕለት አብረው ጮኹ።"

[  ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ ]

†                      †                     


[ መጽሐፍ እንደተናገረ በፈጣሪ እና በፍጡራን መካከል ለዕረፍት የቃል ኪዳን ማደሪያ [ ምልክት ] የሆንሽ የብርሃን ቀን ሰንበተ ሰንበታት ማርያም ሆይ በገነት ያሉ ጻድቃን በአንቺ ደስ ይላቸዋል፡፡ ኃጥአንም ከደይን በአንቺ ይወጣሉ፡፡ ]

[   አባ ጽጌ ድንግል   ]

እንኳን አደረሳችሁ🌹

ገዳማውያን

20 Aug, 06:32


https://youtu.be/D2_KSDTpkUk?si=06DEwDquvxoQe4Nf

ገዳማውያን

18 Aug, 16:59


​​​​#ቡሄ

ቡሄ ማለት ብራ፣ ብርሃን፣ ደማቅ ማለት ነው፡፡ ጌታችን ብርሃነ መለኮቱን የገለጠበት በዓል የሚዘከርበት እና ለበዓሉም ችቦ ስለሚበራ የብርሃን በዓል በማለት የቡሄ በዓል እንላለን፡፡ ወቅቱ የክረምት ፤ጨለማ አልፎ የብርሃን የሚወጣበት፤ ሰማይ ከጭጋጋማነት ወደ ብሩህነት የሚለወጥበት የመሸጋገሪያ ወቅት ነው፡፡ “ቡሄ ከዋለ የለም ክረምት፤ ዶሮ ከጮኸ የለም ሌሊት” እንዲሉ፡፡ በሌላ በኩልም “ቡኮ/ሊጥ” ተቦክቶ ዳቦ የሚጋገርበት “#ሙልሙል” የሚታደልበት በዓል በመሆኑ ቡሄ ተብሏል፡፡

#ጅራፍ

በደብረ ታቦር በዓል በትውፊታዊ መልኩ የሚታየው ምስጢር፤ በኢየሩሳሌም ስለሚሆነው የጌታችን ምስጢራዊ ሞቱ ነው፡፡ ጅራፍ መገመድ(መጥለፍ) እና ጅራፍ ማጮኽ ሁለት ዓይነት ምስጢር የያዘ ትውፊታዊ ተግባር ነው፡፡

የመጀመሪያው ግርፋቱንና ሞቱን እናስብበታለን፡፡ ሁለተኛው ደግሞ ፤ድምፁን ስንሰማ የባሕርይ አባቱን የአብን ምስክርነት ቃል፤ እንደ ነጎድጓድ ድምፅ ያስታውሰናል፡፡

የጅራፍ ትውፊታዊነት /ውርስ/፣ መጽሐፋዊ ትምህርትና ምስጢር ጠብቆ ለትውልድ እንዲተላለፍ ለማድረግ ጨዋታውን በተራራማ አካባቢ፣ ከመኖሪያ ቤት ርቆና፣ በሜዳ ማድረጉ ጠቃሚ ነው፡፡ ጅራፍን #በርችት መቀየር የሚያመጣውን የምስጢር ተፋልሶ ብቻ መመልከት ከማኅበራዊ ጎጂ ገጽታው በላይ እንድናስወግደው ያስገድደናል፡፡

#ችቦ

ችቦ የጌታችንን ብርሃነ መለኮት መገለጥ የሚያመለክት ነው፡፡ በመሆኑም ችቦ ለኩሰን በዓሉን እናከብራለን፡፡ የዚህ ትውፊታዊ አመጣጥ በብርሃኑ ድምቀት የቀኑን መምሸት ያልተረዱ እረኞች በሜዳ ቀርተዋልና ወላጆች ከመንደር ችቦ ለኩሰው ልጆቻቸውን ፍለጋ ሔደዋልና ታሪኩን እያዘከርን በዓሉት እናከብራለን፡፡

የችቦው መንደድም ሌላ ትርጉም አለው፡፡ አንድ ምእመን ለሌላው ምእመን መካሪ አስተማሪ መሆኑን፣ መከራ እየተቀበለም አርአያ፣ ምሳሌ፣ ብርሃን መሆኑን ያሳያል፡፡ በሃይማኖትም አርአያ ምሳሌ ይሆንላቸዋል፡፡ ከዚህ ጋርም ተያይዘዞ ችቦ በ13 ምሽት ይበራል ፣ብርሃኑ የተገለጠው በዚችው ዕለት ነውና ፡፡

#ሙልሙል

በችቦ ብርሃን ልጆቻቸውን ፍለጋ የወጡ ወላጆች ዳቦ ጋግረው ይዘውላቸው ወጥተዋል፡፡ ስጦታው ቤተሰባዊነትን፣ ፍቅርንና መተሳሰብን መግለጫ ነው፡፡ ወደ ቤታችን “ ቡሄ ” እያሉ ለሚመጡ አዳጊዎችም፤ ዘምረው እንዳበቁ የሚሰጥ “ሙልሙል” ዳቦ አለ፡፡ ሕፃናቱም ሊዘምሩ ሲመጡ ዳቦ መስጠት ልማዳዊ ብቻ አይደለም፡፡

ሕፃናቱ የደቀመዛሙርት ምሳሌ ናቸው፡፡ መዝሙራቸው ደግሞ ሐዋርያት “የምሥራች” ይዘው የመምጣታቸው ምሳሌ ነው፡፡ ሐዋርያት በገቡበት አገር አስተምረው አጥምቀው የጸጋ ልጅነትን አሰጥተው በረከት አድለው እንደሚሔዱም፣ ልጆችም ዘምረው፣ አመስግነው፣ መርቀው “ውለዱ ክበዱ፣ ሀብት አግኙ፣ የመንግሥተ ሰማያት ወራሾች ያድርጋችሁ ….” ይላሉ፡፡

በአጠቃላይ በዓለ ደብረ ታቦር ከእነዚህ ምስክር ካላቸው ትምህርቶቹ፣ ምሥጢር ከሚራቀቅባቸው ትርጓሜያቱና ከትውልድ ትውልድ በቅብብል በተላለፈው ቅዱስ ትውፊት ጋር ሃይማኖታዊ ባሕል ሆኖ ሊቀጥል ይገባዋል፡፡

ይህን ማድረግ የሚቻለው ግን አዳጊዎች ሃይማኖታዊ ትውፊቱን ይዘው እንዲያድጉ ጥቆማ በመስጠት፣ ግጥም በመግጠምና ምሥጢሩን በማብራራት የመጀመሪያዎቹ ባለድርሻዎች ወላጆች ናቸው፡፡

አንዳንድ ጊዜ የሚሰሙ ግጥሞች ስድብ፣ ፌዝና ሥላቅ የተቀላቀለባቸው ይሆናሉ፡፡ ሕፃናቱም ዝማሬውን ሲጀምሩ “ከሰጡን እንነሣ ከነሱን እናርዳ” ብለው ይጀምሩታል፡፡ ከሰጡን እንመርቃለን ካልሰጡን እንራገማለን በማለት፡፡

አሳሳቢው ነገር ደግሞ ሃይማኖታዊ ሥርዓቱን ወደ ገንዘብ ማግኛነት የቀየሩ ሁኔታዎች መታየታቸው ነው፡፡ ዳቦ /ሙልሙል/ ትምህርቱንም፣ ምስጢሩንም፣ ትውፊቱንም በአግባቡ ልንጠቀምበት ይገባል።

ከዚም ጋር ተያይዞ ሰንበት ት/ት ቤታችን ለበረካታ ዓመታት ሲወርድ የመጣውን የዝማሬ ሥርዓት ለአጥብያው ምእምን በየቤቱ በመሄድ የብሄን ዝማሬ ከነሥርዓቱ በመዘመር አገልግሎት ይሰጣል ፤የደብር ታቦርን በዓል በተመለከትም የወረቀት ጽሑፎችን ይበትናል በዝማሬ መኃል ያድላል፡፡

ቤተክርስቲያን የምሥጢር ግምጃ ቤት ናት፤ የምታከናውነውን ሁሉ ከበቂ መረጃ ጋር ነው ተግባራዊ የምታደርገው፡፡ በተለይ ወጣቱ ክፍል ይህንን አውቀን ተረድተን ለቀሪው ትውልድ ማስተላለፋ እንችል ዘንድ ከክፉ ጠላት ከሰይጣን ፈተና፣ በሽታ ከመሳሰሉት ችግሮች ለመዳን ወደ ተራራዋ ወደ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በመሸሽ ከክፉ ነገሮች ሁሉ ማምለጥ ይቻላል፡፡

በቤተ ክርስቲያን ጥላ ሥር የሚጠለሉ ሁሉ ዕድሜያቸው ይረዝማል፡፡ አስተዋዮችም ይሆናሉ ሁሉን ማየትና የሚጠቅማቸውን መምረጥ ይችላሉ በሥነ-ምግባር የታነፁ አገርንና ወገንን የሚጠቅሙ ወደ ቅድስት ቤተክርስቲያን በመጠጋት ከክፉ ሁሉ የሚያመልጡ ይሆናሉ ለዚህም የቅዱሳን አምላክ እግዚአብሔር ይርዳን፡፡

#Share
@Gedamaweyan         @Gedamaweyan
@Gedamaweyan         @Gedamaweya


ገዳማውያን

17 Aug, 15:44


አንድ ወንድም አባ ሙሴን «አንድን አገልጋይ ባጠፋው ጥፋት የተነሣ ጌታው መታው፡፡ አገልጋዩ ምን ማለት አለበት?» ብሎ ጠየቀው፡፡ አባ መሴም «አገልጋዩ ብፁዕ ከሆነ፣ አጥፍቻለሁና ይቅር በለኝ ማለት አለበት፡፡›› አለው፡፡ «ሌላ አይጠበቅበትምን?» ሲል ያ ወንድም ጠየቀው፡፡ «አይጠበቅበትም፣ ለጊዜው ለጥፋቱ ሓላ ፊነቱን ወስዶ አጥፍቻለሁ ካለ ጌታው ይቅር ይለዋል፡፡ የዚህ ሁሉ ዓላማው በባልንጀራ ላይ ላለመፍረድ ነው፡፡ በእውነቱ ጌታችን የግብጽን በኩራት ሁሉ ሲመታ ሰው ያልሞተበት አንድም ቤት አልነ በረም›› አለና መለሰለት፡፡ ያም ወንድም ‹‹ምን ማለት ነው?» አለው፡፡ «ሁላችንም የየራሳችንን ጥፋቶች ካየን የባልንጀራችንን ለማየት ዕ ድል አንሰጥም፡፡ በራሱ ቤት ሰው የሞተበት በጐረቤቱ ልቅሶ ለማ ልቀስ አይሄድም፡፡ ለባልንጀራ መሞት ማለት ለራስ ጥፋት ትኩረት በመስጠት፣ የሌላውን ጥፋት ከቁም ነገር አለመቁጠር ነው፡፡ ማን ንም አትጉዳ፣ በማንም ላይ ክፉ አታስብ፣ ክፉ የሚሠራውን ሰው አ ትናቀው፤ በባልንጀራው ላይ ክፉ በሚሠራ ሰው ላይ አትተማመን፤ በባልንጀራው ላይ ክፉ ከሚሠራ ሰው ጋር አትደሰት፤ ለባልንጀራ መዋቲ መሆን ማለት ይህ ነው፡፡ በማንም ላይ አትማረር፤ ነገር ግን «ሁሉንም እግዚአብሔር ያወቃል፡፡» በል፡፡ ከሚያማ ሰው ጋር አትተ ባበር፤ በሐሜቱም አትደሰት፤ ወንድሙን የሚያማውን ሰውም አት ጸየፈው፡፡ አትፍረድ÷ ማለት ትርጉሙ ይህ ነው፡፡ በማንም ላይ የጥላቻ ሓሳብ አይኑርህ፤ ጥላቻ ልብህን እንዲያሸንፈውም አትፍቀ ድለት፡፡ ባልንጀራውን የሚጠላውን አትጥላው፤ ሰላም ማግኘት ማለት ይህ ነው፡፡ የሚከተለውን እያሰብክ ልብህን አበርታው «ፈተና በቶሉ ያልፋል፣ ሰላም ግን ለዘለዓለም ይጸናል፤ በእግዚአብሔር ወልድ ጸጋ ፡፡አሜን፡፡»

#Share
@Gedamaweyan         @Gedamaweyan
@Gedamaweyan         @Gedamaweya


ገዳማውያን

12 Aug, 17:25


የውኃ ጠባይ ለስላሳ ነው፣ የድንጋይ ጠባይ ጠጣር ነው፡፡ ነገር ግን ውኃ በጠር ሙስ ተደርጉ ከድንጋዩ በላይ ከተያዘና ውኃ የሚያጠንጠባጥብ ከሆነ፣ ቀስ በቀስ ድንጋዩ መሰባበሩ አይቀርም፡፡ ቃለ እግዚአብሔርም ለስላሳ ነው፤ ልቡናችን ደግሞ ጠጣር ነው፡፡ ነገር ግን ሰው ቃለ እግ ዚአብሔርን አዘውትሮ የሚሰማ ከሆነ ልቡናው ከጥቂት ጊዜ በኋላ ለፈሪሃ እግዚአብሔር ቦታ መስጠቱ አይቀሬ ነው»
አባ ጴሜን

ገዳማውያን

11 Aug, 14:42


🕯🕯🕯

በጸሎትሽም እረዳትነት ይህንን ላገኝ እወዳለሁ ሆይ! በሃይማኖት ጭንጫ ላይ የተመሠረተች መሠረቷ የማትፈርስ የነፋሳት ኃይል የጎርፍ ፈሳሽ የዝናምም ወጀብ የማይበረታ ፈሳሽ የዝናምም ወጀብ የማይበረታ ታቦት አጥር ቅጽር ሆይ እኔን ከጥፋት ጎርፍ በዓመፀኞችና በበደለኞች ላይ ከምትመጣው የመቅሠፍት ኃይል አድኝኝ፡፡

የመለኮት አዳራሽ ድንግል ሆይ! የሰማይ ሠራዊት ፆታ ያደረብሽ ንጽሕት ሆይ! ሕብሩ ልዩ ልዩ በሚሆን ብርሃን በተጌጸ የቅዱሳን አዳራሽ ውስጥ መኖርን ክፈይኝ፡፡

ከቤት ሕንፃ በላይ የታነጽሽ ሰገነት ድንግል ሆይ! ወደ አርያም ከፍ ከፍ እንድል በልጅሽም በምስጋናው አዳራሽ ውስጥ የተሠወረውን ምሥጢር መርምሬ ለማወቅ ወደ ሰማይ ዳርቻ ከፍ ከፍ እንድል ወደ ላይ እንድመሰጥ አድርጊኝ፡፡

ለዘለዓለሙ የማትገፊ የማትፈርሽ አምባ ድንግል ሆይ! በአንቺ የተጠጉትም ከሚቃረናቸው ጠላት ፀብ፣ ክርክር አድኚኝ፡፡

የትንቢት አዝመራ ድንግል ሆይ! የቤተ ክርስቲያን ለውዝ ገውዝ በጨረቃ ጊዜ የምታፈራ የወይን ፍሬ አበባ የሚሻተትብሽ ፍሬውም የሚከማችብሽ የጽድቅ ፍሬን እንዳፈራ የወንጌል ቡቃያ አድርጊኝ፡፡

📖አርጋኖን ድንግል- ቅዱስ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ

ገዳማውያን

11 Aug, 14:41


ውዳሴ ማርያም ትርጓሜ ዘሰንበተ ክርስቲያን

ገዳማውያን

11 Aug, 04:47


https://t.me/JOSI_CREATIVE

ገዳማውያን

10 Aug, 09:34


ለ ናቲ ቴክ የተሰራ Logo የቱ ያምራል
ማሰራት ለምትፈልጉ 👉 @Jogeez
@Josi_Info

ገዳማውያን

09 Aug, 18:57


"ኦ ማርያም በእንተዝ ናፈቅረኪ"
"ማርያም ሆይ እንወድሻልለን"
       ቅዱስ አባ ሕርያቆስ

በአዳም ዘር መካከል በእሾህ ውስጥ እንዳጌጠች ጽጌረዳ በማዕዛ ቅድስና ተጠብቃ የንጉስ ክርስቶስ አማናዊት መቅደስ በመሆን ዓለም ሁሉ የሚድንበትን እውነተኛውን መብልና መጠጥ ስላስገኘችልን ዛሬም እንላታለን እንደ ቅዱስ  አባ ሕርያቆስ

" ኦ ማርያም በእንተዝ ናፈቅረኪ ወናዐብየኪ እስመ ወለኪ ለነ መብልዐ ጽድቅ ዘበአማን ወስቴ ሕይወት ዘበአማን"

ገዳማውያን

09 Aug, 05:08


ውዳሴ ማርያም ትርጓሜ ዘአርብ

ገዳማውያን

09 Aug, 05:08


ቅዳሴ ማርያም አንድምታ ክፍል 3

ገዳማውያን

08 Aug, 17:36


ቅዳሴ ማርያም አንድምታ ክፍል 2

ገዳማውያን

08 Aug, 08:31


ውዳሴ ማርያም ትርጓሜ ዘእለተ ሐሙስ

ገዳማውያን

08 Aug, 04:27


ገዳማውያን pinned «🍃🍃🍃 ቅዱስ ዮሐንስ - ድንግልን ተቀብሎ የወሰደ ሐዋርያ ድንግልን በስጦታነት የተቀበለው ፣ ተቀብሎም ወደ ቤቱ የወሰዳት ፍቁረ እግዚእ ዮሐንስ ነው፡፡ ዮሐንስ ጌታ የሚወደው እርሱም ጌታን የሚወድ ሐዋርያ ነው፡፡ ከሌሎቹም ሐዋርያት ይልቅ ለጌታ ፍቅሩ የጸና ስለ ነበር ፣ ጌታም እርሱን ይወደው ስለ ነበር ፍቁረ እግዚእ - የጌታ ወዳጅ ተባለ፡፡ ለዚህም ነው … “የሚወደውን ደቀ መዝሙሩን” ተብሎ የተነገረለት፡፡…»

ገዳማውያን

07 Aug, 18:08


🍃🍃🍃

ቅዱስ ዮሐንስ - ድንግልን ተቀብሎ የወሰደ ሐዋርያ

ድንግልን በስጦታነት የተቀበለው ፣ ተቀብሎም ወደ ቤቱ የወሰዳት ፍቁረ እግዚእ ዮሐንስ ነው፡፡ ዮሐንስ ጌታ የሚወደው እርሱም ጌታን የሚወድ ሐዋርያ ነው፡፡ ከሌሎቹም ሐዋርያት ይልቅ ለጌታ ፍቅሩ የጸና ስለ ነበር ፣ ጌታም እርሱን ይወደው ስለ ነበር ፍቁረ እግዚእ - የጌታ ወዳጅ ተባለ፡፡ ለዚህም ነው … “የሚወደውን ደቀ መዝሙሩን” ተብሎ የተነገረለት፡፡ ታዲያ ጌታ ለምን እመቤታችንን ለዮሐንስ ሰጠ? ለምን የመንግሥተ ሰማያትን ቁልፍ ለሰጠውና ብፁዕ ነህ ብሎ ላመሰገነው ለጴጥሮስ አልሰጠውም? (ማቴ.16፡17-19)፡፡ እርሱስ ቢሆን ጌታን መውደዱን “እንድወድህ አንተ ታውቃለህ” ብሎ የሚመሰክር አይደለምን? (ዮሐ.21፡15-17)፡፡ ቅዱስ ሥጋውን ከመስቀል አውርደው ለገነዙት ለዮሴፍና ለኒቆዲሞስስ ለምን አልሰጣቸውም? ለሌሎቹ ሐዋርያትስ ለምን አልሰጣቸውም? ድንግልን ይወስዷት ዘንድ ቤት የላቸውምን? አይደለም፡፡…

ዮሐንስ የሚሰጠውን ስጦታ ለመጠበቅ ከሌሎቹ ሐዋርያት ይልቅ ብቁ ስለነበርም ድንግልን ለመቀበል በመስቀሉ ሥር እንዲገኝ እግዚአብሔር ፈቀደ፡፡ ሐዋርያት በጌታ መከራ ሞት ጊዜ አይሁድን ፈርተው እንደ ሸሹ ከዮሐንስ በቀር በእመቤታችን ሞትም ጊዜ አይሁድን ፈርተው ከጌቴሴማኒ የሚሸሹ ናቸውና ድንግልን እንደ ፍቁረ እግዚእ ለመቀበል አልቻሉም፡፡ ራሱን የሰጣቸውን ጌታ በቀራንዮ ጥለውት እንደ ሔዱ ሁሉ ከመስቀሉ ሥር የምትሰጣቸውን እመቤታችንንም በጌቴሴማኒ ጥለው የሚሔዱ ናቸውና በቀራንዮም በጌቴሴማኒም ለሚጸና ለዮሐንስ ተሰጠች፡፡…

…በርግጥ በዮሐንስ በኩል ድንግል ለተጠቀሱትም ላልተጠቀሱትም ለሁሉም ተሰጥታለች፡፡ ነገር ግን በዮሐንስ በኩል እንዲሆን ዮሐንስን የመረጠበት የተለየ ምክንያት አለው፡፡ ከማይመረመረው ከመለኮታዊው ምክንያቱ ባሻገር ዮሐንስን ከላይ እንደገለፅነው ይወደው ነበር፡፡ እመቤታችንን በስጦታነት ለመቀበል በጌታ መወደድ ያስፈልጋል፡፡ ማርያም ማርያም ለማለት በክርስቶስ መወደድ ያሻል፡፡ ድንግል ታማልዳለች ብሎ ምልጃዋን ለመቀበል በመድኃኔዓለም መወደድ ግድ ነው፡፡ ስሟ ሲጠራ ፊታቸው የሚጠቁር ሰዎች ምንም እንኳን እርሱ እንደሰው ቢወዳቸውም በተሳሳተ መንገድ ውስጥ ናቸውና እንደ ዮሐንስ ስላልተወደዱ ድንግልን ለመቀበል ብቁ አይደሉም፡፡ ጴጥሮስ እንዳለው ቆይተው “እንድወድህ አንተ ታውቃለህ” የሚሉ እንኳን ቢሆኑ መከራ ሞቱ በጾም ሲታሰብ ፣ ሕማማቱ በሥርዐተ ቤተ ክርስቲያን ሲዘከርና ቤተ ክርስቲያን ስሟ ሲጠራ ጴጥሮስ “የምትሉትን ሰው አላውቀውም” ብሎ ገና ዶሮ ሳይጮህ ነገር በሚጸናባት ቁጥር ሦስት ጊዜ እንደ ካደ እነርሱም “የምትሉትን ሃይማኖት አናውቅም ፣ የምትሉትን ጾምና ሥርዐት አናውቅም” ብለው በጽናት ክደዋልና መስቀሉ ሥር ተገኝተው “እነኋት እናትህ” ሊባሉ አልቻሉም፡፡ (ማር.14፡71)፡፡…

…ጌታ በመስቀል ላይ እመቤታችንን ለዮሐንስ ከመስጠቱ በፊት ዮሐንስን ለእመቤታችን ሰጥቶ ነበር፡፡ አንድ ሰው ድንግልን ለመቀበል አስቀድሞ ራሱ ለድንግል መሰጠት አለበት፡፡ ለውዳሴዋ ፣ ለብፅዕትነቷ ፣ ለንጽህናዋ ፣ ለድንግልናዋ ፣ ለቅድስናዋ መጀመሪያ ራሱን መስጠትና ማስገዛት ይኖርበታል፡፡ ዮሐንስን መምሰል ያስፈልገዋል፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በድርሳነ ማርያም ማንን ለድንግል እንደሚሰጥ ሲገልፅ የሚከተለውን ብሏል፤

“በኢየሩሳሌም ትነግሺ ዘንድ ነይ፡፡ መታሰቢያሽን የሚያደርግ በቃሉ የማይዋሽ ፣ መጽሐፍሽን የጻፈ ኃጢአቱን እደመስስለታለሁ፡፡ ለአንቺም ይሆን ዘንድ እሰጠዋለሁ፡፡”

“…አንድ ሰው ራሱ ለእርሷ ለመሰጠት ሲበቃ ከዚያ በኋላ እርሷን ለመቀበል የሚችል ዕደ-ልቡና ይኖረዋል፡፡…

…ድንግልን ለመቀበል መሰጠት ያስፈልጋል፤ እመቤታችንን ለመቀበል ሞት በመጣ ጊዜ ከክር ይልቅ አንገትን የምታስቀድም በ”እንኩ” ባይ ፍቅር ፣ በቅዱስ ጥብዐትና በሰማያዊ ተስፋ የሠለጠነች የክርስትና እምነትን መሰነቅ ግድ ነው፡፡ ድንግልን ለመቀበል ቤትን ማዘጋጀት ሳይሆን እንደ ዮሐንስ የተወደደች ሃይማኖትን ይዞ መገኘት ያስፈልጋል፡፡ ድንግል በዮሐንስ በኩል ለሁሉ እንደ ተሰጠች በተወደደች ሃይማኖት በኩል እንጂ በሌላ በምንም በኩል አትሰጥም፡፡ …

…ከዚህ በተጨማሪም ጌታ የሚወዳት እናቱን በመስቀል ላይ ሳለ ነፍሱን ከሥጋው በፈቃዱ ከመለየቱ በፊት ሊያያት እንደወደደ እመቤታችንም በሞቷ ጊዜ ነፍሷ ከሥጋዋ ከመለየቱ በፊት ልጇ በመስቀሉ ሥር ልጅሽ ይሁን ብሎ የሰጣትን ውድ የመንፈስ ልጇን ፣ ስጦታዋን - ዮሐንስን ልታየው ወዳ ነበር፡፡ እንዲህ ብላም ጸለየች፤

“‘በሰማይ የምትኖር ጌታዬ አምላኬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ፣ ጸሎቴን ልመናዬን ስማኝ፣ ታናሹ ዮሐንስንም ላክልኝ፣ አይቼው እደሰት ዘንድ እወዳለሁና፤ ዳግመኛም ወንድሞችህ ሐዋርያትን ሁሉ ላክልኝ፤ በሰጠኸኝ ጸጋም አምናለሁ፤ እንደምትሰማኝ በአንተ ዘንድ የፈለግሁትን ሁሉ እንደምትሰጠኝ አምናለሁ’ እያለች ጸለየች፡፡”

ከ'የመሰጠት ሕይወት' መጽሐፍ ፣ ከገጽ 71-92 ድረስ ከሚገኘው በጥቂቱ የተወሰደ

[ዲ/ን ሕሊና በለጠ]

#Share
@Gedamaweyan         @Gedamaweyan
@Gedamaweyan         @Gedamaweyan

1,485

subscribers

60

photos

6

videos