ትምህርት ሚኒስቴር @timihert_minister Channel on Telegram

ትምህርት ሚኒስቴር

@timihert_minister


ተጨማሪ መረጃዎችን
በዌብሳይት - www.moe.gov.et


በሊንክዲን - https://www.linkedin.com/company/ministry-of-education-ethiopia

በትዊተር - http://twitter.com/fdremoe

በፌስቡክ -https://www.facebook.com/fdremoe/

በቴሌግራም-https://t.me/timihert_minister
ይከታተሉ።

ትምህርት ሚኒስቴር (Amharic)

የስራውን ስነ-ምህረት አስቸጋሪ እና ከላይ እንዴት እንደሚፈልግ የሚወቅ ስልጣን፡፡ ከዚህ በታች ከትምህርት መንግሥት ጋር የሚያደርጉት ትውልድ፡፡ በዚህ ክፍል በትክክል የሚገልጹ መረጃዎች ለመጠቀም ምን እንደሚፈልጋቸው እና ለአስተያየታቸው ስልጣን ተመልከቱ፡፡ በአሁኑ በሰዓት ትምህርት ሚኒስቴር እንዲሁም ተጨማሪ መረጃዎችን እና አገልግሎትን ከእኛ ለማግኘት በመጠቀም የሚያስችል መረጃዎችን ያሳያል፡፡ በትዊተር፣ ፌስቡክ፣ ቴሌግራሜም እና ሊንክዲን በቪዲዮ እንደሚቀንብላቸው እናም ተጨማሪ ምንድን ነው የሚሳተፉት በመጠቀም ብሎ መደበል ችሎት ይሆናል፡፡ በቴሌግራም ትምህርት ሚኒስቴር እንዲሁም እርስዎ ምንቸቫን ለመጠቀም በመሆን የተዘጋጀ እና አገልግሎት ተብሎ ተጨማሪህን መረጃዎች እና አስተዳደሮችን ለመሸጥ እና ለመመረጥ መርምር ችላት ይሆናል፡፡

ትምህርት ሚኒስቴር

11 Jan, 02:33


ማስታወቂያ
የድህረምረቃ ፕሮግራሞች (NGAT) የመግቢያ ፈተና ለመውሰድ የተመዘጋባችሁ በሙሉ ይህንን ሊንክ ( https://ngat.ethernet.edu.et) በመጫን መረጃ ማግኘት ትችላላችሁ።

ትምህርት ሚኒስቴር

04 Jan, 14:18


በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚካሄዱ የማህበረሰብ ጉድኝት ሥራዎች የህብረተሰቡን ፍላጎት መሠረት ያደረጉና ችግር ፈቺ ሊሆኑ እንደሚገባ ተጠቆመ፡። (ታህሳስ 26/04/2017 ዓ.ም) ከ47 ዩኒቨርስቲዎች ለተውጣጡ የማህበረሰብ ጉድኝት ዳይሬክተሮች ስልጠና ተሰጥቷል። በትምህርት ሚኒስቴር የምርምርና ማህበረሰብ ጉድኝት ጉዳዮች ተወካይ መሪ ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ሠራዊት ሃንዲሶ በስልጠናው ወቅት እንደገለጹት የማህበረሰብ ጉድኝት ስራዎች የህብረተሰቡን ፍላጎት መሠረት ያደረጉ ፣ ሙያዊ ፣ ሳይንሳዊና ችግሮችንም በአግባቡ የሚፈቱ ሊሆን ይገባል። ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በአካባቢያቸው ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጫና የንቅናቄ ስራዎችን በማከናወን በማህበረሰብ ጉድኝት ስራዎች የተቆጠረ ተከታታይነትና ወጥነት ያለው ውጤት እንዲመዘገብ በትጋት መስራት እንደሚጠበቅባቸውም ዶ/ር ሠራዊት ተናግረዋል፡፡
የማህበረሰብ ጉድኝት እና አገር በቀል እዉቀት ዴስክ ሃላፊ ወ/ሮ ሰላም አለሙ በበኩላቸው በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከሚከናወኑ ቁልፍ ተልዕኮዎች መካከል የማህበረሰብ ጉድኝት ሥራ አንደኛው መሆኑን አመልክተው ተቋማቱ የአካባቢያቸውን ማህበረሰብ በማሳተፍ ችግሮች እንዲቀረፉ በትጋት መስራትና የማህበራዊ ሀላፊነታውን መወጣት እንደሚገባቸው ተናግረዋል። የስልጠናው ዓላማም አሳሳቢ እየሆኑ በመጡና ተለይተው በተቀመጡ ማህበራዊ ጉዳዮች ማለትም የአእምሮ ጤናና አደንዛዥ እጽ፣ የመንገድ ትራፊክ ደህንነት፣ ህገወጥ ስደትና የሰዎች ዝውውር ላይ የምርምርና ግብዛቤ ፈጠራ ስራ እንዲሰሩ ለማስቻል መሆኑን አመልክተዋል።። ተቋማቱ የትምህርት ጥራትን ለማሳደግ በአካባቢያቸው ያሉ ትምህርት ቤቶችን እንዲደግፉ ፣ የማህበረሰቡ ዲጂታል ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ግንዛቤ እንዲያሳዳድጉ እና እንዲያግዙ ማስቻልም ሌላኛው አላማ መሆኑን ጠቅሰዋል። በስልጠናው ላይ ሁሉም የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች የማህበረሰብ ጉድኝት ዳይሬክተሮች የተሳተፉ ሲሆን ከትምህርት ሚኒስቴር ፤ ከጤና ሚኒስቴር ፣ከመንገድ ደህንትና መድህን ፈንድ ፣ ከስደተኖች ጉዳይ አስተዳደር እና ከጅማ ዩኒቨርስቲ በመጡ ባለሙያዎች ስልጠና ተሰጥቷቸዋል።

ትምህርት ሚኒስቴር

13 Dec, 13:29


የትምህርት ሚኒስቴር ከICDL Africa እና kepler ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ተፈራረመ፡፡
-------------------------- // ----------------------------
(ታህሳስ 04/2017 ዓ.ም) ስምምነቱ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችና ምሩቃንን የዲጂታልና ሶፍት ሰኪል በማጎልበት ብቁና ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ድጋፍ ለማድረግ ያለመ መሆኑ ተገልጿል።

በሂደትም የዩኒቨርሲቲ እና ኢንዱስትሪ ትብብርን በማሳደግ ምሩቃን የተሻለ ክህሎት እና የስራ እድል የሚያገኙበትን ሁኔታዎች ለማመቻቸት እንደሚያስችል ተገልጿል፡፡

በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሹኔ በፊርማ ስነ-ስርዓቱ ላይ ባደረጉት ንግግር የተፈረመው የመግባቢያ ስምምነት የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችና ምሩቃን ያለባቸውን የዲጂታልና ሶፍት ስኪል ክህሎት ክፍተቶች በመለየት ድጋፍ ለማድረግ የሚያስችል መሆኑን አብራርተዋል።

ሚኒስተር ድኤታው አክለው እንደገለጹት የተፈረመው የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከኢንዱስትሪ ዘርፉ ጋር ያላቸውን ትስስርና ትብብር በተለየ መልኩ ለመደገፍ እገዛ እንደሚኖረውም አብራርተዋል።

የአይሲዲኤል አፍሪካ ዋና ስራ አስፈጻሚ ሶሎንዥ ኢሚዩሊሳ በበኩላቸው ድርጅታቸው አፍሪካውያን ተገቢውን የዲጂታል ክህሎት የተላበሱ እንዲሆኑ ለማድረግ የሚሰራ ደርጅት መሆኑን በመጥቀስ ባለው አቅም ድጋፍ ለማድረግና አብሮ ለመስራት ፍላጎት ያለው መሆኑን ገልጸዋል።

በኢትዮጵያ የኪፕለር ዳይሬክትር በበኩላቸው የተፈረመው የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችና ምሩቃንን በመደገፍና በማሰልጠን ብቁና ተወዳዳሪ ዜጋ እንዲሆኑ ለማስቻል ያለመ መሆኑን ገልጸዋል።

ትምህርት ሚኒስቴር

12 Dec, 16:56


የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የጀኔራል ዋቁ ጉቱ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤትን ጎበኙ።
----------------------//--------------

(ታህሳስ 03 / 2017 ዓ.ም) የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኦሮሚያ ክልል ባሌ ዞን ሮቤ ከተማ የሚገኘውን ጀኔራል ዋቆ ጉቱ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤትን ጎብኝተዋል።

በጉብኝታቸው ወቅትም ለተማሪዎች ባስተላለፉት መልዕክት ትምህርት የሚፈልገው ጥረት መሆኑን በመገንዘብ ሁሉም ተማሪዎች ጠንክረው መማርና ማጥናት ይኖርባቸዋል ብለዋል።

በትምህርት ሥርዓቱ የፈተና አስተዳደር ስርዓቱን ማስተካከል ያስፈለገው የትምህርት ጥራት እንዲሻሻልና ሀገር የሚረከቡ እውነተኛ ዜጎችን ለማፍራት መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል ብለዋል።

ኩረጃ ለጊዜው የሚጠቅም ሊመስል ይችላል ነገር ግን ሄዶ ሄዶ ራስንም ሀገርንም ይጎዳል ያሉት ሚኒስትሩ ኩረጃን የሚጸየፉ በራሳቸው የሚሰሩና የሚተማመኑ ተማሪዎች መሆን እንዳለበቸውም አሳስበዋል።

የትምህርት ጥራት እንዲሻሻልና ትውልዱ ይህችን ሀገር የመገንባት የወደፊት ሀላፊነቱን በታማኝነት እንዲወጣ የሚያስችሉ በርካታ ተግባራት በትምህርት ሴክተሩ እየተከናወኑ መሆኑንም አብራርዋል ።

አክለውም ነገ ብቁ ሀገር ተረካቢ ብሎም በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ሆኖ ለመገኘት ተማሪዎች ትምህርታቸው ላይ ብቻ አተኩረው እንዲማሩ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

ትምህርት ሚኒስቴር

09 Dec, 11:10


በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የምግብ ሜኑ ተመሳሳይ እንዲሆን ተወሰነ።
------------------- // -------------------

ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተውጣጡ ባለሙያዎች የዩኒቨርስቲ ተማሪዎችን የምግብ ሜኑ ተቀራራቢ እንዲሆን እየሰሩ ነው።
ወቅታዊውን የምግብ ዋጋ መጨመር መነሻ በማድረግ ትምህርት ሚኒስቴር ጥናት ያደረገ ሲሆን በጥናቱ ውጤት መነሻነትም የከፍትኛ ትምህርት ተቋማት የምግብ በጀት በቀን ወደ 100 ብር ከፍ እንዲል ተደርጓል። በተደረገው የበጀት ማሻሻያ መሰረት በተቋማቱ የምግብ ሜኑ ተመሳሳይ እንዲሆን በባለሙያዎች ስራዎች እየተሰሩ እንደሚገኙ ተገልጿል።
በትምህርት ሚኒስቴር የአስተዳደርና መሰረተ ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ሰለሞን አብርሃ ወቅታዊ የምግብ ዋጋ ንረትን ግምት ውስጥ በማስገባት የምግብ በጀት ማሰተካከያ መደረጉን ገልጸዋል።
ዶ/ር ሰለሞን አክለውም በሀገራችን ባሉ ዩኒቨርስቲዎች ያለው የምግብ ሜኑ ተቀራራቢ እንዲሆን እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው በአዲሱ የበጀት ተመን መሰረት ለዩኒቨርስቲዎቹ ባላቸው ተማሪ ቁጥር ልክ ገንዘቡ እንደሚለቀቅላቸው ጠቁመዋል።

ትምህርት ሚኒስቴር

07 Dec, 08:12


#የእንግሊዝኛ ቋንቋ ክህሎትን ለማሳደግ በትኩረት መስራት እንደሚገባ ተጠቆመ።


(ሕዳር 28/ 2017 ዓ.ም) በትምህርት ሥርዓቱ የሚስተዋለውን የእንግሊዝኛ ቋንቋ ክህሎት ችግር ለመቅረፍ በሚቻልበ ጉዳይ ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ ተካሂዷል። በምክክር መድረኩ የተገኙት የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በእንግሊዝኛ ቋንቋ ክህሎት ላይ የሚስተዋለውን ችግር መቅረፍ ካልተቻለ የሚፈለገውን የትምህርት ጥራት ማረጋገጥና አለም አቀፍ ተወዳደሪ የሆኑ ተማሪዎችን ማፍራት እንደማይቻል ጠቅሰው ሁሉም ባለድርሻ አካላት በትኩርት ሊሰሩ እንደሚገባ ጠቁመዋል። በተለይም ተማሪዎች የሚማሩትን ትምህርት በአግባቡ እንዲረዱና ውጤታማ እንዲሆኑ እንግሊዝኛ ቋንቋን የማንበብ፣ የመጻፍ፣ የመናገርና የማዳመጥ ክህሎታቸውን በሚገባ ማሳደግ ይገባል ብለዋል።

የቀጣዩ ትውልድ እጣ ፈንታ የሚወሰነው አሁን በሚሰራው ሥራ መሆኑን በመገንዘብ የመማር ማስተማር ሥነ - ዘዴውን ማስተካከል እንዲሁም ተማሪዎች የእንግሊዝኛ ቋንቋ ክህሎታቸውን የሚያዳብሩበትን ምቹ ሁኔታ በትምህርት ቤቶች መፍጠር ይገባልም ብለዋል። በትምህርት ሚኒስቴር የመምህራንና የትምህርት ቤት አመራር ልማት መሪ ሥራ አስፈጻሚ ሙሉቀን ንጋቱ (ዶ/ር) በበኩላቸው የእንግሊዝኛ ቋንቋ በትምህርት ዓይነትና በማስተማሪያ ቋንቋነት በትምህርት ሥርዓቱ እየተሰጠ እንደሚገኝ ጠቅሰው ነገር ግን ከፍተኛ የእንግሊዝኛ ቋንቋ ክህሎት ችግር መኖሩን የሚያመላክቱ ጥናቶችን አቅርበዋል። በዚህም የእንግሊዝኛ ቋንቋ ክህሎት ችግር በተማሪዎችና በመምህራን ዘንድ እንደሚስተዋል አንስተው ይህንን ችግር ለመቅረፍ የሚያስችል ትምህርት ቤትን መሰረት ያደረገ ሥልት ቀይሶ መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል።

ትምህርት ሚኒስቴርም https://learn-english.moe. gov.et የተሰኘ ያለ ምንም የኢንተርኔት ክፍያ የሚሰራ የእንግሊዝኛ ቋንቋ ማሻሻያ ፓርታል አልምቶ ወደ ሥራ ማስገባቱን የጠቀሱት መሪ ሥራ አስፈጻሚው ይህንን ፖርታል ተማሪዎች፣ መምህራን እንዲሁም የእንግሊዝኛ ቋንቋ ክህሎታቸውን ማሳደግ የሚፈልጉ ዜጎች እንዲጠቀሙበት በሚገባ በማስተዋወቅ ረገድ ሚድያዎችን ጨምሮ ባለድርሻ አካላት ሃላፊነታቸውን እንዲወጡ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። በመድረኩም የተለያዩ ጽሁፎች ቀረበው በተሳታፊዎች ውይይት የተደረገባቸው ሲሆን ተሳታፊዎችም ተማሪዎች በክፍል ውስጥና ከክፍል ውጪ ቋንቋውን እንዲጠቀሙበት እና ክህሎታቸውን እንዲያሳድጉ የሚያበረታታ ሁኔታ አለማኖሩ ችግሩን የጎላ እንዳደረገው ገልጸው ይህንን ለመፍታት መምህራንና ተማሪዎች በድፍረት ቋንቋውን እንዲጠቅሙና ክህሎታቸውን እንዲያሳድጉ የሚያደርጉ ስልቶችን መቀየስ እንደሚገባም ተናግረዋል። በመጨረሻም የቋንቋ ክህሎትን በማሳደግ ረገድ የተሰሩ ሥራዎችና ሥልቶችን መሰረት በማድረግ ተሞክሮዎች መቀመርና ማስፋት በተለይም ክልል ከክልል፣ ትምህርት ቤት ከትምህርት ቤት ልምድ የሚለዋውጡበት ሥርዓት መዘርጋት እንደሚገባም ተመላክቷል።

በምክክር መድርኩ ከሁሉም ክልልና ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የመጡ አመራሮችና ባለሙያዎች እንዲሁም ጉዳዩ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።

https://t.me/timihert_minister

ትምህርት ሚኒስቴር

06 Dec, 13:09


የአምስት የዘርፍ ኢንዱስትሪዎች የትስስር ፎረም ተመሰረተ።
በቀጣይ ሁለት አመታት የየዘርፉን ፎረም የሚመሩ አመራሮችም ተመርጠዋል።

-------------------- // ---------------------

(ሕዳር 27/2017 ዓ.ም) የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ በፎረሞቹ ምስረታ ላይ ባደረጉት ንግግር የትምህርትና ስልጠና ተቋማትና የኢንዱስትሪ ትስስር ተወዳዳሪ ዜጋና ሀገርን ለማበልጸግ ቁልፍ ሚና ያላቸው በመሆኑ የዘርፉ ተዋንያኖች ሚናቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።

ሚንስትር ዴኤታው አያይዘው እንደገለጽት ትስስሩ ሀብትን በጋራ በማመንጨትና በመጠቀም የተሻለ አቅም ለመፍጠር የሚያስችል በመሆኑ የከፍተኛ ትምህርት ምርምርና ስልጠና ተቋማትና ኢንዱስትሪው ተጣምረው በጋራ መሥራት እንደሚጠበቅባቸው አመላክተዋል።

የከፍተኛ ትምህርት የምርምርና ማህበረሰብ ጉድኝት ጉዳዮች ተ/ መሪ ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ሠራዊት ሀንዲሶ በበኩላቸው በዘርፍ የሚቋቋሙት የትስስር ፎረሞች የከፍተኛ ትምህርት ፣ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ፣ ምርምር ተቋማትና ኢንዱስትሪው በመቀናጀትና በመተባበር ሀገር የጣለባቸውን ሃላፊነት እንዲወጡ ለማስቻል ያለመ መሆኑን ገልጸዋል።

በመጨረሻም የተቋማት ትስስርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዴስክ ሃላፊ አቶ ተሾመ ዳንኤል የፎረሞቹ መቋቋም የከፍተኛ ትምህርት፣ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት፣ ምርምር ተቋማት እና ከኢንዱስትሪው ልምድና ተሞክሮዎችን እንዲቀስሙ የሚያስችል መሆኑን የገለጹ ሲሆን ኢንዱስትሪዎች በተመሳሳይ የሚመነጩ የምርምር ሀብቶችና ቴክኖሎጂዎችን ለመጠቀም የሚያስችላቸው እና የጋራ ተጠቃሚነትን መሰረት ያደረገ መሆኑን ጠቁመዋል።

ትምህርት ሚኒስቴር

04 Dec, 19:26


Telegram ላይ online business መስራት ትፈልጋላችሁ እንግዳውስ ከታች ያለውን በመንካት በስልካችሁ ብር ሰርታችሁ ወደ ባንክ ማውጣት ትችላላችሁ
ከታች ያለውን START በማለት ገንዘብ መስራት ጀምሩ ።

ትምህርት ሚኒስቴር

04 Dec, 17:36


🎚️ ቤቲንግ እየተበሉ ከተሸገሩ አሪፍ ቻናል ላስተዋውቅዎ 100℅ Sure የሆነ ቻናል ነው እኔ ከምነግራችሁ ገብተችሁ እዩት!!!

👇👇Join ብላችሁ ተመልከቱት 👇👇
💸💸 ለመመልከት ይጫኑት 💸💸

ትምህርት ሚኒስቴር

04 Dec, 16:14


ከ17 ደቂቃ ቦኃላ ይጠፋል


የ 200 ብር ካርድ የሚያስሸልም ጥያቄ!

በኢትዮጵያ በጣም አስቸጋሪ የነበረዉ  ረሀብ መች አመተምህረት ነበረ?

Add your channel » Darkwave1

ትምህርት ሚኒስቴር

04 Dec, 06:04


⛔️ ቀድሞ ለመለሰ የ 2⃣0⃣0⃣ ብር ካርድ ይሸለማል ‼️

በዓለማችን ረጅሙ የባቡር መስመር የሚገኘው በየትኛው አገር
ነው ?


Add your channel above 1k »» @Darkwave1

ትምህርት ሚኒስቴር

05 Nov, 06:06


ማስታወቂያ
*

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በ2017 ዓ.ም በመደበኛ የዲግሪ ፕሮግራም አዲስ የተመደባችሁ ተማሪዎች   የምዝገባ  ጊዜ ኀዳር 09-10/2017 ዓ.ም መሆኑን ይገልጻል፡፡

የምዝገባ ቦታ፦
• የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች በዋናው ግቢ
• የማህበራዊ ሳይንስ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት

ማሳሰቢያ፤
ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲው ሲመጡ የሚከተሉትን ይዘው መምጣት ይጠበቅባችኋል፡፡
• የ12ኛ ክፍል ፈተና ማጠቃለያ ፈተና ውጤት ዋናውና ኮፒው፣
• ከ9ኛ-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናውና ኮፒው
• አራት ጉርድ ፎቶግራፍ፣
• አንሶላ፣ ብርድ ልብስ እና ትራስ ጨርቅ፣
• የስፖርት ትጥቅ

ማሳሰቢያ:-

ከተጠቀሰው ቀን በፊትም ሆነ በኃላ የሚመጣ ተማሪ የማናስተናግድ መሆኑን በጥብቅ እናሳውቃለን፡፡
     
የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሬጅስትራር ጽ/ቤት

ትምህርት ሚኒስቴር

04 Nov, 12:52


Website: https://placement.ethernet.edu.et
Telegram: https://t.me/moestudentbot

ትምህርት ሚኒስቴር

01 Nov, 13:40


ትምህርት ሚኒስቴር ከሁዋዌና ሌሎች ተባባሪ አካላት ጋር የሚያዘጋጀው የአይሲቲ ውድድር አበረታች መሆኑ ተገለጸ።

ከሁዋዌ ጋር በመተባበር በተዘጋጀው ሀገር አቀፍ እና አህጉር አቀፍ የአይሲቲ ውድድር ፍጻሜ ለተወዳደሩ ተማሪዎች የማበረታቻ ሽልማት ተበርክቷል።

ሽልማቱ የተበረከተው የሁዋዌ የ2024/25 አይሲቲ የውድድር ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ ሲሆን በመርሃ-ግብሩ ላይ የተገኙት በትምህርት ሚኒስቴር የአይሲቲ እና ዲጂታል ትምህርት መሪ ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር ዘላለም አሰፋ ባስተላለፉት መልእክት ውድድሩ ለተማሪዎች የስራ እድልን በማመቻቸት እና የስራ ፈጠራ አስተሳሰብን ከማጎልበት አኳያ ሰፊ ሚና ያለው መሆኑን ገልጸዋል።

ዶ/ር ዘላለም አክለውም ሁዋዌ ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር የተማሪዎችን ክህሎት ለማዳበር እያደረገ ላለው አበርክቶ ምስጋናቸውን ያቀረቡ ሲሆን መሠል ጥረቶችን በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አጠናክሮ ማስቀጠል የሚገባ መሆኑን አስገንዝበዋል።

የሁዋዌ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ በኢትዬጵያ ሚስተር ሊሚንግየ በበኩላቸው ውድድሩ ለወጣቶች ከፍተኛ ጠቀሜታ ያለው በመሆኑ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።

ትምህርት ሚኒስቴር

31 Oct, 16:51


____________________________
"በእሳቤና በንግግር ከፋፋይ የሆኑ ሀሳቦችን እያጠፉ ሰብሰብ ለማድረግ ይሰራል።
የሚያሰባስቡ የማይለያዩ እሳቤዎችን በታሪክ ትምህርት ካሪኩለም ውስጥ በማካተት ቀጣዩ ትውልድ እንዲገነባው ይደረጋል።"

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ(ዶ/ር) በ6ኛ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ የትምህርት ሴክተሩን በተመለከተ የተናገሩት።

ትምህርት ሚኒስቴር

24 Oct, 12:53


የ2017 ዓ.ም የዩኒቨርሲቲ ምደባ ይፋ ሆኗል።

በ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ በመደበኛው ፕሮግራም ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግሥት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርታችሁን ለመከታተል የሚያስችል የማለፊያ ውጤት ያስመዘገባችሁ ተማሪዎች የተቋም ምደባ ይፋ ሆኗል።

ከታች በተዘረዘሩት አማራጮች ምደባችሁን ማየት የምትችሉ መሆኑ ተገልጿል፦

በድረ-ገፅ 👇
https://placement.ethernet.edu.et

በቴሌግራም 👇
https://t.me/moestudentbot

የተቋም ይቀየርልኝ ጥያቄ የማያስተናግድ መሆኑን ሚኒስቴሩ አሳውቋል።

ትምህርት ሚኒስቴር

22 Oct, 17:28


የኦሮሚያ ትምህርት ቢሮ በ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስደው ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ የሰላሌ ዩኒቨርሲቲ ልዩ ትምህርት ቤት ሦስት ተማሪዎች ሽልማቶችን አበርክቷል፡፡

በኦሮሚያ ክልል ከፍተኛ ሆኖ የተመዘገበውን 568 ያመጣው ተማሪ ራጂ ተስፋዬ ዘመናዊ ላፕቶፕ እና የ30,000 ብር ሽልማት ተበርክቶለታል፡፡

በተመሳሳይ 545 ያመጣው ተማሪ ሁንዴሳ ፈይሳ እና 535 ያስመዘገበው ተማሪ ቶልቻ ቦጃ ዘመናዊ ላፕቶፕ እና የ20,000 ብር ሽልማት ተበርክቶላቸዋል፡፡

ትምህርት ሚኒስቴር

22 Oct, 17:28


#AAU

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለ2017 ዓ.ም በመደበኛው የቅድመ-ምረቃ ትምህርት መርሐግብር በትምህርት ሚኒስቴር እና በዩኒቨርሲቲው የቅድመ-ምረቃ ትምህርት መግቢያ መስፈርት መሠረት ቅበላ ያገኙና #ከአዲስ_አበባ_ውጪ የሚመጡ ተማሪዎችን ብቻ ከዛሬ ጥቅምት 5/2017 ዓ.ም ጀምሮ ለሁለት ቀናት በየተመደቡበት የዩኒቨርሲቲው ካምፓስ ምዝገባ ያካሒዳል፡፡

ነዋሪነታችሁ በአዲስ አበባ ሆኖ ቅበላ ያገኛችሁ ተማሪዎች ምዝገባ ጥቅምት 11/2017 ዓ.ም እንደሆነ ከዚህ በፊት መገለፁ ይታወቃል፡፡

ለሁሉም ተማሪዎች (በአዲስ አበባ ነዋሪ የሆናችሁትን ጨምሮ) አጠቃላይ ገለፃ (Orientation) ቅዳሜ ጥቅምት 9/2017 ዓ.ም ይሰጣል፡፡

ትምህርት ሚኒስቴር

22 Oct, 17:28


#BuleHoraUniversity

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ለነባር መደበኛ እና ለ2016 ሪሚዲያል ተማሪዎቹ ጥሪ አድርጓል።

በዚህም በ2016 ዓ.ም በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርታችሁን ስትከታተሱ ቆይታችሁ የማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ ተማሪዎች እንዲሁም ነባር የቅድመ ምረቃ እና የድኅረ ምረቃ መደበኛ ተማሪዎች የ2017 ትምህርት ዘመን ምዝገባ ጥቅምት 11 እና 12/2017 ዓ.ም እንደሚከናወን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።

ትምህርት ሚኒስቴር

22 Oct, 17:28


#ማስታወሻ

በ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች #በመደበኛ እና #በሪሚዲያል ፕሮግራም ለመከታተል የሚያስችል የማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ ተማሪዎች፣ የተቋም እና የትምህርት መስክ ምርጫችሁን በየትምህርት ቤታችሁ በተወከሉ መምህራን በኩል እንድትሞሉ ትምህርት ሚኒስቴር ያራዘመው የመሙያ ጊዜ ነገ ጥቅምት 6/2017 ዓ.ም ይጠናቀቃል፡፡

የተቋም እና የትምህርት መስክ ምርጫችሁን በቀሩት ጊዚያት ይሙሉ!

ትምህርት ሚኒስቴር

22 Oct, 17:28


#AAU

ለ2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመንግስት ስኮላርሺፕ እንዲሁም በግል ከፍላችሁ ለመማር ቅበላ ያገኛችሁ የአንደኛ ዓመት የቅድመ-ምረቃ ተማሪዎች ሪፖርት አድርጉ ተብሏል።

ከአዲስ አበባ ውጪ የምትመጡ ተማሪዎች ጥቅምት 5 እና 6/2017 ዓ.ም በየተመደባችሁበት ካምፓስ በመገኘት ሪፖርት እንድታደርጉ ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡

ለምዝገባ የሚያስፈልጉ፦

- የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ዋናውና ኮፒው፣
- አራት ጉርድ ፎቶግራፍ፣
- የማደሪያ አገልግሎት ለተሰጣችሁ ብርድ ልብስና አንሶላ እንዲሁም የስፖርት ትጥቅ መያዝ አለባችሁ፡፡

ከአዲስ አበባ ውጪ ለምትኖሩ ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲው የተመደበላችሁን የመኝታ ክፍል https://portal.aau.edu.et/NewStudent/DormitoryPlacement በመግባት ማየት ትችላላችሁ።

ከአዲስ አበባ ውጪ ለምትመጡ ተማሪዎች በተጠቀሱት ቀናት በመርካቶ፣ በላምበረት፣ በአቃቂ እና በአስኮ የመኪና መናኸሪያዎች ዩኒቨርሲቲው የትራንስፖርት አገልግሎት የሚያቀርብ መሆኑን ገልጿል።

ነዋሪነታችሁ በአዲስ አበባ ሆኖ ቅበላ ያገኛችሁ ተማሪዎች ከላይ የተጠቀሱትን ማስረጃዎች እና ዶክመንቶች ይዛችሁ ሪፖርት የምታደርጉት ሰኞ ጥቅምት 11/2017 ዓ.ም መሆኑ ተገልጿል።

ለሁሉም ተማሪዎች አጠቃላይ ገለፃ (Orientation) ቅዳሜ ጥቅምት 9/2017 ዓ.ም ይሰጣል፡፡

የትምህርት ኮርሶች ምዝገባ ሰኞ ጥቅምት 11 ቀን 2017 ዓ.ም ሲሆን፤ የ2017 ዓ.ም የመጀመሪያ ሴሚስተር ትምህርት ማክሰኞ ጥቅምት 12/2017 ዓ.ም ይጀምራል፡፡

ትምህርት ሚኒስቴር

22 Oct, 17:28


አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በ2017 ዓ.ም ወደ ተቋሙ የሚገቡ አዲስ የመጀመሪያ ዓመት ተማሪዎችን ጥቅምት 3 እና 4/2017 ዓ.ም ይቀበላል፡፡

ዩኒቨርሲቲው ከተለያዩ አካባቢዎች ለሚመጡ ተማሪዎች መገናኛ እና ቃሊቲ ላይ የትራንስፖርት አገልግሎት ማዘጋጀቱን ገልጿል።

በዚህም እሑድ 5፡00 ሰዓት እንዲሁም ሰኞ 4፡00 ሰዓት በተጠቀሱት ቦታዎች በመገኘት፣ የዩኒቨርሲቲውን ሎጎና የእንኳን ደህና መጣችሁ ባነር የተለጠፈባቸው አውቶቡሶችን መጠቀም እንደምትች ተገልጿል፡፡

ትምህርት ሚኒስቴር

22 Oct, 17:28


#Update

ትምህርት ሚኒስቴር መስማት ለተሳናቸው የሪሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች የመቁረጫ ነጥብ ይፋ አድርጓል፡፡

በዚህም በ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ ፈተና ወስደው በመንግስት ተቋማት (ወጪያቸው ተሸፍኖ) የአቅም ማሻሻያ ፕሮግራም ለመከታተል የሚያስችል የመቁረጫ ነጥብ ያመጡ መስማት የተሳናቸው ተማሪዎች የማለፊያ ውጤት እንደሚከተለው ይሆናል፦

► የተፈጥሮ እና የማኅበራዊ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች ከስድስት መቶ 192
► የተፈጥሮ እና የማኅበራዊ ሳይንስ ሴት ተማሪዎች ከስድስት መቶ 186
በፕሪፓቶሪ ፕሮግራም የተፈጥሮ እና የማኅበራዊ ሳይንስ ወንድ ከሰባት መቶ 224
► በፕሪፓቶሪ ፕሮግራም የተፈጥሮ እና የማኅበራዊ ሳይንስ ሴት ከሰባት መቶ 217 እና ከዚያ በላይ መሆኑን ሚኒስቴሩ አሳውቋል፡፡

ትምህርት ሚኒስቴር

10 Oct, 13:18


#update

በ2016 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስደው  ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች በመደበኛ እና በ 'Remedial' ፕሮግራም ለመከታተል የሚያስችል ማለፊያ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች የተቋም እና የትምህርት መስክ ምርጫቸውን በየትምህርት ቤታቸው በተወከሉ መምህራን በኩል እስከ መስከረም 30/2017 ዓ.ም ድረስ ሞልተው እንዲጨርሱ መገለጹ ይታወሳል።

ይሁን እንጂ " አንዳንድ ትምህርት ቤቶች በሲስተም ችግር ምክንያት የተማሪዎቻችንን የትምህርት መስክ እና የዩኒቨርስቲ ምርጫ መሙላት ተቸግረናል " ባሉት መሰረት የትምህርት ሚኒስቴር የምርጫ መሙያ ጊዜውን እስከ ረቡዕ ጥቅምት 6/2017 ዓ.ም ድረስ ማራዘሙን ይገልጻል።

ትምህርት ሚኒስቴር!
@timihert_minister

ትምህርት ሚኒስቴር

09 Oct, 06:56


ማስታወቂያ
የተቋም እና የትምህርት መስክ ምርጫን ይመለከታል
በ2016 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች በመደበኛ እና በRemedial ፕሮግራም ለመከታተል የሚያስችል ማለፊያ ውጤት ያስመዘገባችሁ ተማሪዎች የተቋም እና የትምህርት መስክ ምርጫችሁን በየትምህርት ቤታችሁ በተወከሉ መምህራን በኩል እስከ መስከረም 30/2017 ዓ.ም ድረስ መሙላት የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።

በተጨማሪም
በምደባ ወቅት አዎንታዊ ድጋፍ ለሚሹ ተማሪዎች
በ2016 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች በመደበኛ እና በRemedial ፕሮግራም ለመከታተል የሚያስችል ማለፊያ ውጤት ያስመዘገባችሁ እና በምደባ ወቅት አዎንታዊ ድጋፍ ለምትሹ ተማሪዎች ማመልከቻችሁን በ https://student.ethernet.edu.et በኩል ብቻ እንድትልኩ እየገለጽን ምንም አይነት ማመልከቻ በአካል የማንቀበል መሆኑን እናሳውቃለን።

የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር

ትምህርት ሚኒስቴር

19 Sep, 12:05


በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የኢንኩንቬሽን ማዕከላት መጠናከር እንዳለባቸው ተገለጸ
--------------------------------------
በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የኢንኩንቬንሽን ማዕከላትን በማጠናከር ዙሪያ ስልጠና ተሰጥቷል።
ስልጠናውን ያስጀመሩት በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ የኢንኩንቬንሽን ማዕከላትን ማጠናከር በተቋማቱ ያለውን የተዛባ ሚዛን ያስተካክላል ብለዋል። አሁን ባለው ግምገማ በተቋሞቻችን ያለው የኢንኩንቬንሽን ማዕከላት አሰራር ከዘመኑ ጋር ያልተራመደ በመሆኑ ስልጠና ማዘጋጀት ማሰፈለጉን ጠቁመው በቀጣይ በዚህ ዘርፍ ላይ ስራዎች በትኩረት እንደሚሰሩ ገልጸዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር የተቋማት ትስስርና ቴክኖሎጂ ሽግግር   ዴስክ ሃላፊ አቶ ተሾመ ዳንኤል በበኩላቸው ለሁሉም ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የዩንቨርሲት ኢንዱስትሪ ትስስር፣ ቴክኖሎጂ ሽግግር እና እንኩንቤሽን ማዕከላት ኃላፊዎች የሚሰጠው ስልጠና ለዘርፉ የተሰጠውን ትኩረት እንደሚያሳይ ጠቁመው ሁሉም ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ይህንን የሪፎርም ተልዕኮ በብቃት መወጣት እንደሚገባ አሳስበዋል። አቶ ተሾመ አያይዘውም ስልጠናው በፈጠራ ስነምህዳር፣ በስራ ፈጠራ ማበልጸጊያ ማዕከላት እና የምርምር ውጤቶችን እና ቴክኖሎጂዎችን ወደ ገበያ ለማስገባት በሚከናወኑ አስተዳደራዊ ስራዎች  ላይ የሚስተዋለውን የግንዛቤ እጥረት መፍታትን ትኩረት ያደርገ መሆኑን ገልጸው ስልጠናውን በዘርፉ ልምድ ያካበቱ የተለያዩ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ሀገር ባለሙያች እውቀታቸውን ይጋሩበት መሆኑን ጠቁመዋል።
በመጨረሻም ከየተቋማቱ የመጡ የስራ ሃላፊዎች ማዕከላቱ በሚጠናከሩበት ዙሪያ ውይይት ያደረጉ ሲሆን በስልጠናው ብዙ ልምድ እንዳገኙ ጠቁመዋል።

ትምህርት ሚኒስቴር

17 Sep, 10:44


ማስታወቂያ

ረቂቅ መመሪያን በውይይት ለማዳበር አስተያየት እንዲሰጥ ስለመጠየቅ

የትምህርት ሚኒስቴር በትምህርት ዘርፍ ሁለንተናዊ እድገት እና ጥራትን ለማረጋገጥ ትክክለኛ እና ጥራት ያለዉ የትምህርት መረጃ የማይተካ ሚና ሰላለዉ በዘርፉ የትምህርት መረጃ አሰተዳደር ስርዓት ግልፅነት እና ተጠያቂነት የሰፈነበት አሰራር ለመፍጠር የሚያስችል የትምህርት መረጃ አሰተዳደር ስርዓት ረቂቅ መመሪያ አዘጋጅቷል።
የተዘጋጀው ረቂቅ መመሪያ ፀድቆ ስራ ላይ ከመዋሉ በፊት በቀጥታ ህብረተሰቡ በሚሳተፍበት መድረክ አስተያየት እና ግብአት እንዲሰበሰብ ማድረግ አስፈልጓል፡፡ በመሆኑም መሰከረም 08/2017 ዓ.ም ከጥዋቱ 4፡00 ሰዓት ጀምሮ አራት ኪሎ በሚገኘው የመስሪያቤታችን የመሰብሰቢያ አዳራሽ በመገኘት ይፋዊ የህዝብ የውይይት መድረክ ላይ ተገኝተው ሰነዱን ለማዳበር የሚያስችል ግብአት ይሰጡን ዘንድ በአክብሮት እንጋብዛለን።

ትምህርት ሚኒስቴር

15 Sep, 08:44


ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለነቢዩ መሐመድ የልደት በዓል መውሊድ በሰላም አደረሳችሁ።

ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ
የትምህርት ሚኒስትር!
@timihert_minister

ትምህርት ሚኒስቴር

13 Sep, 17:21


#DambiDolloUniversity

ደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ የመደበኛ ነባር ተማሪዎች የ2017 ትምህርት ዘመን ወደ ዩኒቨርሲቲ መግቢያ ቀናት መስከረም 22 እና 23/2017 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል፡፡

በ2017 ዓ.ም አዲስ ወደ ደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችው እና በ2016 ዓ.ም በሪሚዲያል ፕሮግራም በደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታችሁን ስትከታተሉ ቆይታችሁ ወደ ዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ያስመዘገባችሁ ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲ መግቢያ ቀን ወደ ፊት ይገለፃል ተብሏል፡፡

@timihert_minister

ትምህርት ሚኒስቴር

12 Sep, 13:45


#Cont.d_AAU_GAT

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ነገ አርብ መስከረም 3/2017 ዓ.ም የሚሰጠውን የድኅረ ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (GAT) መርሐግብር ይፋ አድርጓል፡፡

መስከረም 3/2017 ዓ.ም ከሰዓት ከ7፡30-11፡00 ሰዓት ለሚሰጠው ፈተና የተፈታኞች ዝርዝር፣ የመፈተኛ ካምፓስ፣ የመፈተኛ ላብ እንዲሁም የኮምፒውተር ክፍል ከላይ ከተያያዘው ኤክሴል ይመልከቱ፡፡

ትምህርት ሚኒስቴር

12 Sep, 12:06


#AAU_GAT

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ነገ አርብ መስከረም 3/2017 ዓ.ም የሚሰጠውን የድኅረ ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (GAT) መርሐግብር ይፋ አድርጓል፡፡

መስከረም 3/2017 ዓ.ም ጠዋት ከ2፡00-8፡00 ሰዓት ለሚሰጠው ፈተና የተፈታኞች ዝርዝር፣ የመፈተኛ ካምፓስ፣ የመፈተኛ ላብ እንዲሁም የኮምፒውተር ክፍል ከላይ ከተያያዘው excel ይመልከቱ፡፡

ትምህርት ሚኒስቴር

12 Sep, 12:05


#NGAT_RE_EXAM

ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ጳጉሜን 1/2016 ዓ.ም ሳይሰጥ የቀረውን የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ትምህርት ብሔራዊ የድኅረ ምረቃ ፕሮግራም መግቢያ ፈተና (NGAT) ነገ አርብ መስከረም 3/2017 ዓ.ም ከሰዓት 8፡00 ይሰጣል፡፡ 

በመሆኑም ተፈታኞች ከዚህ ቀደም በተመደባችሁበት የኮምፒውተር ላብራቶሪ ተገኝታችሁ ፈተናችሁን እንድትወስዱ ይሁን።

@timihert_minister

ትምህርት ሚኒስቴር

10 Sep, 15:15


#Happy_New_Year
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
ለመላው ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን እንኳን ለአዲሱ አመት #2017 በሰላም እና በጤና አደረሳችሁ። መጪው አዲስ ዘመን የሰላም፣ የደስታ፣የፍቅር እና የስኬት ይሁንላችሁ።
🌼🌼መልካም አዲስ አመት!🌼🌼
ትምህርት ሚኒስቴር!

ትምህርት ሚኒስቴር

09 Sep, 16:59


የ12ኛ ክፍል ውጤት!

የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ተፈታኞች ውጤታችሁን ከዛሬ ጳጉሜን 4/2016 ዓ.ም ሌሊት 6:00 ጀምሮ ማየት እንደምትችሉ መገለፁ ይታወቃል።

ውጤታችሁንም በሚከተሉት አማራጮች ውጤታችሁን መመልከት ትችላላችሁ ፦

በፖርታል 👉 https://result.eaes.et

በአጭር የፅሑፍ መልዕክት 👉 6284

በቴሌግራም ቦት 👉 https://t.me/EAESbot

ከውጤት መግለጫ ፖርታል እና ቴሌግራም ቦት ላይ ጊዜያዊ ሰርቲፊኬት ማውረድና ማተም እንደምትችሉ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።

ተፈታኞች በውጤት እና ተያያዥ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ቅሬታ ካላችሁ ወደ አገልግሎቱ ቢሮ በአካል መሔድ ሳያስፈልጋችሁ ከSMS በስተቀር በውጤት መግለጫ አማራጮቹ ላይ Compliant የሚለውን በመጫን የቅሬታቸሁን ዓይነት በተዘጋጀ የቅሬታ ፎርም ላይ በትክክል በመሙላት ማቅረብ ትችላላችሁ።

አገልግሎቱ በቅሬታችሁ ላይ ምላሽ ቅሬታቸሁን ባቀረባችሁት ተመሳሳይ አድራሻ የሚያሳውቅ ይሆናል።

ትምህርት ሚኒስቴር!
https://t.me/timihert_minister

ትምህርት ሚኒስቴር

09 Sep, 11:05


የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ዛሬ ይገለጻል።

የትምህርት ሚኒስቴር በውጤቱ ዙሪያ ከደቂቃዎች በኃላ መግለጫ ይሰጣል።

ትምህርት ሚኒስቴር

06 Sep, 15:30


#MoE

የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና ውጤት የፊታችን ሰኞ ጳጉሜን 4/2016 ዓ.ም ይፋ የሚደረግ ይሆናል።

ትምህርት ሚኒስቴር

05 Sep, 14:30


#AAU #GAT
#Anouncement

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ
በተቋሙ የድኅረ ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (GAT) መስከረም 3/2017 ዓ.ም የሚሰጥ ሲሆን፤
በተቋሙ የሚሰጠውን ፈተና ለመውሰድ የአመልካቾች ምዝገባ ከዛሬ ነሐሴ 30/2016 ዓ.ም እስከ መስከረም 1/2017 ዓ.ም ይከናወናል።

ትምህርት ሚኒስቴር

05 Sep, 12:29


የትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ የአሜሪካ የረትገር ዩኒቨርሲቲ-ካምደን ቻንስለር በዶክተር አንቶኒዮ ዲ. ቲሊስ የተመራ የልዑካን ቡድን ተቀብለው በጽ/ ቤታቸው አነጋገሩ፡፡

ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው ቻንስለሩንና የልዑካን ቡድናቸውን ተቀብለው ባነጋገሩበት ወቅት ስለ አገራችን ዘመናዊ ትምህርትና የከፍተኛ ትምህርት ታሪክና መስፋፋት ዙሪያ ገለጻ አድርገውላቸዋል፡፡
የረትገር ዩኒቨርሲቲ ከትምህርት ሚኒስቴርና ከኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር በቴክኖሎጂና በሌሎችም የትብብር መስኮች በጋራ መስራት በሚቻልበት ሁኔታ ላይም ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው መክረዋል፡፡

ዶክተር አንቶኒዮ ዲ. ቲሊስ በበኩላቸው የረትገር ዩኒቨርሲቲ-ካምደን ከማላዊ፣ ኬኒያ ፣ ናይጄሪያና ከሌሎችም የአፍሪካ ዩኒቨርስቲዎች ጋር በትብብር እንደሚሰራ ጠቅሰው ከትምህርት ሚኒስቴርና ከኢትዮጵያ ዩኒቨርስቲዎች ጋር በተለያዩ መስኮቸ በትብብርና በጋራ ለመስራት ፍላጎት እንዳላቸው ተናግረዋል፡፡