የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት @fenoteselam27 Channel on Telegram

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

@fenoteselam27


ይህ ገፅ የቡራዩ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ትምህርት ቤት መልዕክቶችን ዘመኑ በሚፈቅደው መንገድ እንዲተላለፍበት በህዝብ ግንኙነት ክፍል የሚመራ ይፋዊ ገጽ ነው።
📞+251944247165 ሀሳብ አስተያየት ካሎት @finoteselam27PR በinbox አድራሻችን ያድረሱን።

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት (Amharic)

የቡራዩ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ትምህርት ቤት መልዕክቶችን ዘመኑ በሚፈቅደው መንገድ እንዲተላለፍበት በህዝብ ግንኙነት ክፍል የሚመራ ይፋዊ ገጽ ነው። እናቴን ያረጋግጡ፡ +251944247165 ሀሳብ አስተያየት ካሎት @finoteselam27PR በinbox አድራሻችን ያድረሱን።

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

06 Feb, 17:38


🎲 Quiz ''ፍኖት ጥያቄ እና መልስ - ጥር 29 / 2017 ዓ.ም''
answered 👉 "Start this quiz "  የሚለውን ይጫኑ     👉 "I am ready" የሚለውን ሲጫኑ ጥያቄ እና መልሱ ይጀምራል።         #መልካም_ዕድል      | ፍኖተ ሰላም ሰ/ት/ቤት ሚዲያ
🖊 5 questions · 30 sec

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

06 Feb, 15:21


#እንኳን ደስ አላችሁ
#የመጀመሪያ ዙር የመሠንቆ ዜማ መሣሪያ ሥልጠና
#ፈጥነው ይመዝገቡ
#ሥልጠናው የካቲት 30 ይጀምራል።

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

05 Feb, 13:14


#ፍኖት_ከሰሞኑ_በረከት

ጥር 28 ቅዱስ አማኑኤል

በዚህች ቀን ቅዱስ አማኑኤል ተአምራትን በማድረግ ሰባት እንጀራና በሁለት ዓሣ ሴቶችና ህፃናት ሳይቆጠሩ አምስት የገበያ ህዝብ አበርክቶ ያጠገበበት አመታዊ ክብረ በአል መታሰቢያ ነው።

***

በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ የተመዘገበው ይህ የጌታችን ተአምር በውስጡ ብዙ ምሥጢራትን የያዘ ነው እንጂ ስለ ሥጋዊ ምግብ ብቻ የተነገረ አይደለም። ማቴ.14፥13-23

የተመገቡትና የተቆጠሩት አምስት ሺህ ወንዶች ብቻ ናቸው እንጂ ሴቶችና ሕጻናት አልተቆጠሩም ይህስ ለምን ነው ቢሉ ሴቶች በአደባባይ ሲበሉ በሃፍረት ዳር ዳር ስለሚሉ ነው ሕፃናት ደግሞ ከሚበሉት የሚፈረፍሩት ይበዛልና ነው። ጌታችን ያንን ሁሉ ሕዝብ በመንደር አጠገብ ሊመግባቸው ሲችል ለምን አርቆ ወደ ምድረ_በዳ ወሰዳቸው ከተባለ ስለ ሁለት ምክንያት ነው።

አንድም ‹‹ጥንት አባቶቻችሁን ከመንደር (ከግብፅ) አውጥቼ አርባ ዘመን ሙሉ መና የመገብኳቸው እኔ ነኝ አሁንም በሥልጣኔ በተአምራቴ መገብኳችሁ›› ሲላቸው ነው።

አንድም ጌታችን ተአምራቱን ከመንደር አጠገብ አድርጎት ቢሆን ኖሮ ሁልጊዜ ክፋትንና ጠማማ ነገርን ማሰብ ለአይሁድ ልማዳቸው ነውና ‹‹ፈጣን ፈጣን ደቀ መዛሙርቱን በጎን ወደ መንደር እየላከ ያስመጣው ነው›› ይሉት ነበር።

ስለሆነም ጌታችን ለጥርጥር ምክንያት እንዳይኖራቸው አድርጎ ነው ተአምራቱን የገለጠላቸው ጊዜውም አመሻሽ ላይ ነበርና ምሽት ላይ ያደረገበትም ምክንያት ጠዋት ላይ ቢሆን ኖሮ ‹‹የበላነው ሳይጎድል ነው ያበላን›› ብለው ከማመን ይርቁ ነበር።

በተጨማሪም በበረሃ ያውም በምሽት ሕዝቡን በውኃ አጠገብ በሣር ላይ አስቀምጧቸው መመገቡ ‹‹በፍጻሜው ዘመን በምቹ ስፍራ  በመንግሥተ ሰማያት መንፈሳዊ ምግብ እመግባችኋለሁ በውኃ በጥምቀት በሚገኝ ክብርም አከብራችኋለሁ ሲላቸው ነው።

ተአምራቱን ከውኃ ዳር ማድረጉ ‹‹መታጠቢያ ብናጣ በደንብ ሳንበላ ቀረን›› እንዳይሉ ነው ሳር የበዛበት ቦታ ላይ ማድረጉም ‹‹መቀመጫ ብናጣ በደንብ ሳንበላ ቀረን›› እንዳይሉ ነው።

አምስቱ እንጀራ የአምስቱ አዕማደ ምሥጢር ማለትም የምሥጢረ ሥላሴ፣ የምሥጢረ ሥጋዌ፣ የምሥጢረ ጥምቀት፣ የምሥጢረ ቁርባንና የምሥጢረ ትንሣኤ ሙታን ምሳሌዎች ናቸው፡፡

ሁለቱ ዓሣ ደግሞ የፍቅረ እግዚአብሔርና የፍቅረ ቢፅ ምሳሌዎች ናቸው። ፍቅረ እግዚአብሔር ማለት እግዚአብሔር አምላክን በፍፁም ነፍስና በፍፁም ሐሳብ መውደድ ነው ፍቅረ ቢፅ ደግሞ ባልንጀራን እንደራስ አድርጎ መውደድ ነው አንድም ደግሞ እንጀራውና ዓሣው የቅዱስ ሥጋውና የክቡር ደሙ ምሳሌ ነው።

ቅዱስ አማኑኤል ስለ አባቶቻችን ስለ ቅዱሳኑ አብርሐም፣ ይስሐቅ፣ ያዕቆብ ብሎ በበረከት በረድኤት ይጎብኘን ምህረት ቸርነቱ አይለየን "አሜን"

_
ፍኖተ ሰላም ሚዲያ

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

04 Feb, 15:07


#5ተኛ ዙር የበገና ሥልጠና እና
#ለአዳጊያን ልዩ የበገና ሥልጠና መርኃግብር

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

03 Feb, 07:32


የሐዘን መልእክት
------------------
በፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት አገልጋይ ወንድማችን የሆነው ወጣት ቴዎድሮስ ሰለሞን አርፏል።

ሥርዓተ ቀብሩ ዛሬ ጥር 26/2017 ዓ.ም ከቀኑ 9:00 ላይ በቡራዩ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል የሚፈጸም ይሆናል።

ሰንበት ትምህርት ቤታችንም በወንድማችን ሞት የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን እየገለጠ፤የወንድማችንን ነፍስ በደጋጎቹ ወገን እንዲያሳርፍልን እየተማጸንን ለቤተሰቡ፣ ለወዳጅ ዘመድ ፣ለሰንበት ት/ቤታችን አባላት ለሁሉም መጽናናትን እንመኛለን።

❖❖❖❖❖❖❖❖❖❖❖❖❖❖❖
  የቡራዩ ደ/ሰ መድኃኔዓለም ካቴድራል
  ፍኖተ ሰላም ሰንበት ትምህርት ቤት

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

02 Feb, 08:12


በኢቲቪ አፋን ኦሮሞ የጥምቀት የበዓል መርኃግብር ላይ የፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት የበገና ክፍል አባላት ያደረጉት ልዩ የበዓል ቆይታ።

_
ፍኖተ ሰላም ሚዲያ🎬

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

01 Feb, 18:14


#የአንድነት (እሁድ ) ጉባኤ
#3:30 - 5:30

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

01 Feb, 10:42


"ይትፌነሁ  ለሳሕል ለሳሕል እም ኀበ ልዑል"
ጥር 22/2017 ዓ.ም በፍኖተ ሰላም ሰ/ት/ቤት መዘምራን የቀረበ አመላለስ

👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://youtu.be/Esfjz2k5abo?si=08kQQDhjZoCR2fAI

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

31 Jan, 14:38


"ድኅረ እረፍተ ኪዳነ እስመ ተወከፍከ ባቲ
እምርት እለት በዓለ ሲመትከ ሊቀ መላእክት"
ጥር 22/2017 ዓ.ም በካህናት የቀረበ ያሬዳዊ ዝማሬ

👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://youtu.be/n-xvliljNV4?si=nDZjxVT7ayquQclP

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

31 Jan, 13:54


#የአባላት መዋጮ
#ከጥር 23-30

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

31 Jan, 06:31


#ጥር 22/2017 ዓ.ም
#የቅዱስ ዑራኤል በዓለ ንግስ ሥርዓተ ዑደት
_
ፍኖተ ሰላም ሚዲያ🎬

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

30 Jan, 21:53


የመልአኩ የቅዱስ ዑራኤል በዓለ ሲመት  በቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል በድምቀት ተከበረ።
----------
የመልአኩ የቅዱስ ዑራኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በቡራዩ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል የወረዳ ቤተክህነት የሥራ ሃላፊዎች፣ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን አባቶች፤ የሰንበት ትምህርት ቤት መዘምራን በርካታ ምዕመናን በተገኙበት በድምቀት ተከብሯል።

ጥር 22 /2017 ዓ.ም
-------------------------
📷 ፍኖተ ሰላም ሚዲያ

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

07 Jan, 15:17


አእላፋት ዝማሬ 2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

07 Jan, 05:02


◉◉◉✞✞✞◈◈◈✞✞✞◈◉◈◉◈

"ነገሥተ ተርሴስ ወደሰያት አምኃ ያበውዑ፤
ነገሥተ ሳባ ወዐረብ ጋዳ ያመጽኡ፤
ወይሰግዱ ሎቱ ኩሎሙ ነገሥተ ምድር።"
__
ሠናይ በዓለ ልደት ዘእግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ
ይኩን ለክሙ ወምስለ ኩሎሙ ፍቁራኒክሙ።
_
እንኳን ለብርሀነ ልደቱ በሰላም አደረሳችሁ።

መልካም በዓል

◉◉◉✞✞✞◈◈◈✞✞✞◈◉◈◉◈

|ፍኖተ ሰላም ሰንበት ትምህርት ቤት

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

06 Jan, 18:24


አእላፋት ዝማሬ መርኃግብር 2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

06 Jan, 17:11


የመረጃ ሰዓት

#መልእክተ_ቅዱስ_ፓትርያርክ
~
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡

• በሀገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ የምትኖሩ፤
• ከሀገር ውጭ በተለያዩ አህጉር የምትገኙ፤
• የሀገራችንን ዳር ድንበር ለመጠበቅና ለማስከበር በየጠረፉ የቆማችሁ፤
• በሕመም ምክንያት በየፀበሉና በየሆስፒታሉ ያላችሁ፤
• እንዲሁም የሕግ ታራሚዎች ሆናችሁ በየማረሚያ ቤቱ የምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያት በሙሉ፤
በምሉእ ፍቅሩ ሰውን ከባርነት ወደ ነጻነት ለመመለስ በሥጋ ሰብእ የተወለደው ጌታችን  ኣምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንኳን ለሁለት ሺሕ ዐሥራ ሰባት ዓመተ ምሕረት የልደት በዓል በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ፡፡

“ስብሐት ለእግዚአብሔር በሰማያት ወሰላም በምድር ለዘሠምሮ ለሰብእ፤ ክብር በሰማያት ለእግዚአብሔር ይሁን›› በምድርም እጅግ ለወደደው የሰው ልጅ ሰላም ይሁን” (ሉቃ ፪÷፲፬)
ይህ ቃለ ሰላም በጌታችን ዕለተ ልደት የተነገረ ነው፣ ቃሉ የተነገረው እንዲሁ እንደ ተራ ነገር ሳይሆን በቃለ መዝሙር እየተደጋገመ ነው፡፡ የተዘመረውም በምድራውያን ደራሲዎች ሳይሆን በሰማያውያን መላእክተ እግዚአብሔር ነው፣ የያዘው መልእክትም ሰማያውያንና ምድራውያንን ሁሉ ያካለለ ነው፡፡ የመልእክቱ ገዢ ሓሳብም አምላክ ከሰውነታችን ጋር ባለመለያየት፣ ባለመጠፋፋት፣ ባለመቀላቀል፣ ባለመዋዋጥ፣ ባለመለዋወጥና ያለባዕድና አንድ አካል፣ አንድ ክዋኔ፣ አንድ ጠባይ ሆኖ በተዋሕዶ ተገልጾኣልና እግዚአብሔር ይክብር ይመስገን፡፡ የተዋሕዶውም ምስጢር ሰላምን ያሰፍናልና እግዚአብሔር ሰውን በእጅጉ መውደዱ ከዚህ ተዋሕዶ ዓውቀናል የሚል ነው፡፡

በእርግጥም እግዚአብሔር ሰውን ለመውደዱ ከዚህ የበለጠ ማሳያ ወይም ማስረጃ የለም፤ እንከን የለሽ ንጹህ አምላክ የእኛን ኃጢአተኛ ሰውነት አካሉ አድርጎ ተወለደ ሲባል ላስተዋለው ሰው ምንኛ ቢወደን ነው የሚለው ጥልቅ አድናቆትን ያጭራልና ነው፡፡ይህ ብቻም አይደለም በዚህ ነገረ ተዋሕዶ ምክንያት ሰውነታችን አምላክ ሆኖ በመንበረ ጸባኦት እንዲቀመጥ መብቃቱ የድኅነታችንና የክብራችን ከፍታ ምን ያህል አስተማማኝ ደረጃ ላይ እንደደረሰ መንፈሳችን በአንክሮ ይረዳዋል፡፡ድምር ውጤቱም በእግዚአብሔርና በሰው መካከል ፍጹምና አስተማማኝ ሰላም መፈጠሩን ያስረዳናል፤ ሰማያውያኑ መላእክተ እግዚአብሔር በመዝሙራቸው ያበሰሩን ይህንን የምስራች ነው፡፡

• የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት!
እኛ ክርስቲያኖች እግዚአብሔር ፍቅር ነው፣ እግዚአብሔር በእጅጉ ይወደናል ስንል እንዲሁ ከሜዳ ተነሥተን ኣይደለም፡፡ በበደላችንና በኃጢአታችን ሳይጸየፈን ሰውነታችንን በረድኤት ወይም በኅድረት ያይደለ በኩነት ተዋሕዶ ወደ አምላክነት ደረጃ ከፍ ስላደረገው  ነው እንጂ፡፡ እግዚአብሔር በዚህ ፍጹምና ምሉእ ፍቅሩ ሰውነታችንን በመበረ ጸባኦት ኣስቀምጦ መላእክት ሳይቀሩ ፍጥረታትን በሙሉ እንድንገዛ አድርጎናል፤ ምክንያቱም መላእክት በዕለተ ልደት የዘመሩለት በተዋሕዶ አምላክም ሰውም ለሆነ ለቤተ ልሔሙ ሕፃን እንጂ ለመለኮት ብቻ ኣይደለምና ነው፡፡ የዕለተ ልደት መዝሙር ዛሬም በሰማያትም ሆነ በምድር በተዋሕዶ ሰውም ኣምላክም የሆነ አንዱ ኢየሱስ ክርስቶስ ይመለክበታል፣ ይመሰገንበታል፡፡የሰማዩና የምድሩ ዕርቅ ወደ ኋላ ላይመለስ ላንዴና ለመጨረሻ ጊዜ በዚህ ተከናውኖኣል፣ የእግዚአብሔር ፈቃድ የሰውም አዋጭ ምርጫ ይህ ዕርቅ ተጠብቆ እንዲኖር ነው፣ ያለ ዕርቅ ሰላም ሕይወት የለውምና፡፡

• የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት!
የእግዚአብሔር ክብርና ሰላም በእጅጉ የተሳሰሩና የተቆራኙ ናቸው፤ እኛ እግዚአብሔርን ካከበርነው፣ ካዳመጥነው፣ ከታዘዝነውና ከተከተልነው ሰላም አለ ማለት ነው፡፡ ለሱ ካልታዘዝንና እሱን ካላከበርን ግን ዘላቂ ሰላምን ማግኘት ፈጽሞ የማይታሰብ ነው፤ ምክንያቱም ሰላምን ጨምሮ መልካም ነገር ሁሉ ያለው በእግዚአብሔር እጅ ነውና፡፡ ዛሬ በሁሉም የዓለማችን ማዕዘን የሚታየው የሰላም መደፍረስ እግዚአብሔርን ካለማክበራችንና ለሱ ካለመታዘዛችን የተነሣ እንደሆነ መዘንጋት የለብንም፡፡ ዓለም ከእግዚአብሔር ቃል ርቃ ለመሄድ በእጅጉ እየኳተነች ነው፤ በዚህ እኩይ ተግባርዋ ደግሞ እግዚአብሔር ለስጋትና ለጉስቁልና አሳልፎ እየሰጣት ነው፡፡ እግዚአብሔር በምስጢረ ሥጋዌው ቢታረቃትም ዕርቁን ማክበር አቅቶአታል፤ ይህንን የእግዚአብሔር ጸጋ ቸል ብላ የምታደርገው ሩጫ የትም ሊያደርሳት እንደማይችል ብታውቅና በንስሓ ብትመለስ እግጅ ተጠቃሚ ትሆናለች፡፡
• የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት!
የእግዚአብሔር ቃል “እናንተስ ከማይጠፋ ዘር ተወለዳችሁ” ብሎ ተስፋውን እንደነገረን ምድባችን ከማይጠፋ ዘር እንዲሆን ክርስቲያኖች የሆን ሁላችን በአእምሮ ጐልብተን፣ በሥነ-ምግባር ኣምረን፣ ጤናማ ሕይወትን ልንመራ ይገባናል፡፡

የአምላካችንን በዓለ ልደት ስናከብር ነገረ እግዚአብሔርን፣ ነገረ ፍቅርን፣ ነገረ ዕርቅንና ነገረ ሰላምን በማኅበረሰባችን የማሥረጽ አጀንዳ ይዘን ልናከብር ይገባል፡፡
ጠቡ ፣ ጥላቻው፣ መለያየቱ፣ መጠፋፋቱ፣ ለወንድሜ  ከማለት ይልቅ ለኔ ለኔ ማለቱ ሲጎዳን እንጂ ሲጠቅመን ኣላየንም፡፡ አሁንም ወደ ልባችን እንመለስና በፍቅር፣ በዕርቅና በእኩልነት፣ በስምምነትና በወንድምነት ወደሚገኝ አንድነት እንምጣ፤ የልደቱ መዝሙር ያስተማረን ይህና ይህ ብቻ ነውና፡፡ በሌሎቹ ክፍለ ዓለማት እንደሆነው ሁሉ በሀገራችን የተከሠተው አላስፈላጊ ግጭት ብዙዎችን አሳጥቶናል፤ ብዙዎችንም ከቤት ንብረታቸው አፈናቅሎ ሜዳ ላይ ፈሰው የሰቆቃ ኑሮ እንዲገፉ አድርጎብናል፡፡ የሀገር ሀብት እንዲወድም ሆኖአል፤ ልጆቻችን ምናለ ከእንግዲህ ወዲህ ቢበቃንና ምድሪቱን የሰላም አየር እንድትተነፍስ ብንፈቅድላት፤ ይህ የወቅቱ የቤተክርስቲያናችን ዋነኛ መልእክትና ጥሪ ነው፡፡    
                         በመጨረሻም፡-
በዓለ ልደት የእግዚአብሔር በዓል ነውና፣ እግዚአብሔር በምድራችን ሰላምን ያወርድ ዘንድ ካለን ከፍለን ለተፈናቃዮች፣ ለነዳያን እና ለአካል ጉዳተኞች በመለገስ በዓሉን በመንፈሳዊ ደስታና በሰላም እንድናከብር አባታዊ መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን፤
መልካም በዓለ ልደት ያድርግልን፡፡

እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ
ወስብሐት ለእግዚአብሔር  አሜን!

  አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም
ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት

ታኅሣሥ ፳፱ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ

_
ፍኖተ_ሰላም_ሚዲያ

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

06 Jan, 05:38


#ፍኖት_ምን_አዲስ

በመዝሙርና ኪነጥበብ ክፍል፤  በዜማ መሣሪያ ንዑስ ክፍል የሚዘጋጀው የሰንበት ት/ቤቱ የበገና ቤተሰብ ወርሃዊ የ'ዝክረ ቅዱስ ዳዊት' መርኃግብር መጋቤ ስብሐት ዓለሙ አጋ በእንግድነት በተገኙበን ተካሄደ።

በዕለቱም ታኅሣሥ 20/2017 ዓ.ም ያስመረቃቸውን 51 የበገና ዜማ መሣሪያ ምሩቃን የእንኳን ደህና መጣችሁ እና ቀጣይ የአገልግሎት ሁኔታን ገለፃ በማድረግ መርኃግብሩ ተጠናቋል።
_
ፍኖተ_ሰላም_ሚዲያ📸

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

26 Dec, 17:02


🎲 Quiz '''ፍኖት ጥያቄ እና መልስ - ታኅሣሥ 17 / 2017 ዓ.ም'''
👉 "Start this quiz "  የሚለውን ይጫኑ     👉 "I am ready" የሚለውን ሲጫኑ ጥያቄ እና መልሱ ይጀምራል።     #መልካም_ዕድል    |ፍኖተ ሰላም ሰ/ት/ቤት ሚዲያ
🖊 5 questions · 30 sec

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

26 Dec, 08:29


#ታኅሣሥ 12/2017 ዓ.ም በነዳያን መርኃግብር የተሰጠ ትምህርተ ወንጌል _ፍኖተ ሰላም ሚዲያ🎬

https://youtu.be/I07tOrz684A?si=TCxnLR7YQpVDVhFO

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

25 Dec, 17:01


እንኳን ደስ አላችሁ!!
4ኛ ዙር የበገና ሠልጣኞች የምርቃት መርኃግብር

#ታኅሣሥ 20/2017 ዓ.ም

|ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

25 Dec, 14:12


#የመረጃ_ሰዓት

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ከሰላም ሚኒስቴር ሚንስትር አቶ መሐመድ እድሪስ ጋር ተወያዩ !

ታኅሣሥ 16 ቀን 2017 ዓ.ም

**
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የሰላም ሚኒስቴር ሚንስትር አቶ መሐመድ እድሪስን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል ።

በውይይቱ ወቅትም በሀገሪቱ የተጀመረውን ሰላም አጠናክሮ ለማሰቀጠል በጋራ ምክክር ያደረጉ ሲሆን ቤተ ክርስቲያኗ ከመንግሥት ጋር በመደጋገፍና በመቀራረብ በሰላም ዙሪያ በትጋት እንደምትሠራ ቅዱስ ፓትርያርኩ በማረጋገጥ የሰላም ሚንስትር አቶ መሐመድ እድሪስ ለትውውቅና ለመወያየት ወደ መንበረ ፓትሪያርክ በመምጣታቸው አድናቆትና ምስጋና አቅርበዋል፡፡

ክቡር ሚንስቴሩ በበኩላቸው አሁን ያለው ሰላም እንዲጎለብት ቤተ ክርስቲያኗ በሰላምና በሀገረ መንግሥት ግንባታ ካላት ልምድ  እየታዩ ያሉ የሰላም ፈተናዎች እንዲፈቱና ዘላቂ መፍትሔ እንዲመጣ ሀገራዊ የሰላም ጸሎት ጥሪ እንዲደረግ ጠይቀዋል።

በመጨረሻም የሰላም ሚኒስቴርና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በሀገራዊ የሰላም ግንባታ ሥራዎች ዙሪያ በጋራ እንደሚሠሩ አስታውቀዋል።


ምንጭ:- (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ)

____
ፍኖተ ሰላም ሚዲያ

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

24 Dec, 12:27


በሰንበት ት/ቤቱ ገፀ በረከት መሸጫ ሱቅ ያገኙታል።

|የሰንበት ት/ቤቱ ልማት ክፍል

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

23 Dec, 12:24


የፍኖተ ሰላም ሰንበት ትምህርት ቤት
የሚዲያ አማራጮች


TIKTOK👇👇👇👇👇👇👇
https://vm.tiktok.com/@fenoteselam27

YOUTUBE👇👇👇👇👇👇👇

https://www.youtube.com/@fenoteselamsundayschool27

FACEBOOK👇👇👇👇👇👇👇

https://www.facebook.com/profile.php?id=100078694373211

INSTAGRAM👇👇👇👇👇👇👇

https://www.instagram.com/fenoteselam27/profilecard/?igsh=MXZydXFuMXIyY2RoZQ==

TELEGRAM👇👇👇👇👇👇👇

https://t.me/fenoteselam27

_
ፍኖት ሚዲያ

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

21 Dec, 18:02


#ፍኖት_ምን_አዲስ

በፍኖተ ሰላም ሰ/ት/ቤት  የነዳያን ጉባኤ ተካሄደ ።

በዛሬው ዕለት በተሰናዳው የነዳያን ጉባኤ ላይ በርካታ ነዳያን የተገኙ ሲሆን በጉባኤውም ትምህርተ ወንጌል የተሰጠ እና የበገና ዝማሬም እንዲሁ የቀረበ ሲሆን በቀጣይነትም ዘላቂ ድጋፎችንና በቤተክርስቲያናቱ የሰበካ ጉባኤ አባልነት መታወቂያ ይኖራቸው ዘንድ ክትትል ማድረግ የሚያስችል የመረጃ ፎርም በማስሞላት ጉባኤው ተጠናቋል።

ሁነቱን በጥቂቱ በፎቶ ተያይዟል።

_
ፍኖት ሚዲያ

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

20 Dec, 19:30


#ፍኖት_ቅዱሳት_መካናት
👇🎬
https://youtu.be/IefUC7H2MNc?si=dhiJawi8OnRAYECF

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

20 Dec, 17:00


#ወርሃዊ የነዳያን ጉባኤ
#ነገ ታኅሣሥ 12/2017 ዓ.ም
#ጠዋት 3:00
#በመርኃግብሩ ላይ በሃሳብ ፣በሙያ እንዲሁም በገንዘብ በመሳተፍ በረከት ያግኙ።

| ሙያ እና በጎ አድራጎት ክፍል

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

15 Nov, 10:40


#ደብረ_ቁስቋም

ኅዳር ፮ ቀን የአርያም ንግሥት፣ የፍጥረታት ሁሉ እመቤት፣ የአምላክ እናት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ይዛ አረጋዊ ቅዱስ ዮሴፍንና ቅድስት ሰሎሜን አስከትላ ለ3 ዓመታት ከ6 ወራት የስደት እና የመከራ ዓመታት በኋላ በስተደቡብ የምትገኘው ደብረ ቁስቋም ላይ ያረፉችበት ዕለት ይከበራል፡፡

ደብረ ቁስቋም በደቡብ ግብጽ የሚገኝ ተራራ ነው፡፡ ይህ ተራራ የተቀደሰ ተራራ ስለመሆኑ የእስክንድርያው ሊቀ ጳጳስ ቅዱስ ታኦፊሎጎስ በድርሳነ ማርያም ‹‹ይህም ከሀገሮቹ ሁሉ ተራሮች የሚበልጥ (የተለየ) ከፍ ያለ ተራራ ነው፡፡ በውስጡ ቅዱስ አግዚአብሔር ያድራል፡፡ ይህንን ተራራ የእግዚአብሔር ልጅ ወዶታል፤ አክብሮታልምና፤ ከዓለም ሀገሮች ሁሉ ከተቀደሰች እናቱ ጋር አድሮባታልና፡፡ ከመላእክት ቤት ያድር ዘንድ አልወደደም፤ ቢታንያንም አልመረጠም፡፡ ከተራራው ላይ ባለች ገዳም ቤት ውስጥ አደረ እንጂ፤ ነቢዩ ዳዊት የጽዮንን ተራራ ወደደ፤ በአርያምም መቅደሱን ሠራ እንዳለ፡፡››

በቅዱስ ወንጌል እንደ ተጻፈ ሄሮድስ ክርስቶስን ለመግደል በፈለገ ጊዜ የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ለአረጋዊው ዮሴፍ በሕልሙ ‹‹ሕፃኑንና እናቱን ይዘህ ወደ ግብጽ ሽሽ›› ባለው መሠረት የተፈጸመ ነው፡፡ (ማቴ. ፪፥፲፫-፲፭)

በስደቱም ጣዖታተ ግብጽ እየተሰባበሩ ሲወድቁ፤ በእነርሱም አድረው ሰውን ሲያስቱ የነበሩ አጋንንትም ሲሸሹ ታይተዋል፤ ደግሞም ጌታችን ዳግማዊ አዳም ነውና በምክረ ከይሲ (ዲያብሎስ) ምክንያት ተሰዶ የነበረው ቀዳማዊ አዳምን ለመካስ ተሰደደ፤ በዚህም አጋንንትን ከሰው ልቡና አውጥቶ አሳደደ፡፡

እመቤታችን ቅድስት ማርያም ከጌታችን ኢየሱስ ጋር ከመሰደዷ አስቀድሞ ነቢዩ ኢሳይያስ ‹‹ወይወርድ እግዚእነ ውስተ ምድረ ግብጽ እንዘ ይጼዐን ዲበ ደመና ቀሊል፤ ጌታችን በፈጣን ደመና (በእመቤታችን ጀርባ) ተጭኖ ወደ ግብጽ ይወርዳል›› ተብሎም በተናገረው መሠረት ትንቢቱ ተፈጽሟል፡፡ (ኢሳ. ፲፱፥፩)

ጌታችን ኢየሱስ በደብረ ቁስቋም ቅዱሳን ሐዋርያቱን ሰበሰባቸው፤ታቦትንና ቤተ ክርስቲያንንም አክብሮ የቁርባን መሥዋዕትንም ሠርቶ ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን ሰጥቷቸዋል፡፡

እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም ከጌታችን ኢየሱስ ጋር በቁስቋም ተራራ ስድስት ወራትን ያረፈች ሲሆን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ኅዳር ፮ የእነርሱን ስደትና ወደ ሀገራቸው እስራኤል መመለሳቸውን በማስታወስ ታከብራለች፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን!!!

ምንጭ፤ ድርሳነ ማርያም (ትርጉም ፳፻፫ ዓ.ም)
ስንክሳር ዘወርኃ ኅዳር

ፍኖተ ሰላም ሚዲያ

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

15 Nov, 10:16


ኅዳር 6 ቁስቋም ማርያም

ክብር ይግባውና ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም፣ ከአረጋዊው ዮሴፍና ከሰሎሜ ጋር ከስደት በሚመለሱ ጊዜ ወደ ደብረ ቊስቋም ገብተው በመንገድ ጒዞ ካገኛቸውም ድካም ላረፉበት ዓመታዊ መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ።
-------------------------------

ከ3 ዓመት የስደት ውጣ ውረድ በኋላ የአምላክ እናት ልጇ አምላካችን ክርስቶስን ይዛ አረጋዊ ዮሴፍና ሰሎሜን አስከትላ ከመዐዲ ወደ ላዕላይ ግብጽ በጀልባ ደግሞ ከካይሮ በስተደቡብ 320 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በላዕላይ ግብጽ በምትገኘው ወደ ደብረ ቊስቋም ገብተው በመንገድ ጒዞ ካገኛቸው ድካም 6 ወር ከ10 ቀናት ዐርፈዋልና ኅዳር 6 በደመቀ መልኩ በዓሏ ይከበራል፡፡

በደብረ ቁስቋም ሳሉ ጨካኙ ሄሮድስ እንደሞተ የጌታ መልአክ በግብፅ ለዮሴፍ በሕልም ታይቶ "የሕፃኑን ነፍስ የፈለጉት ሞተዋልና ተነሣ፥ ሕፃኑን እናቱንም ይዘኽ ወደ እስራኤል አገር ኺድ" ብሎታል (ማቴ 2፡19-20)።
-----------------
ፍኖተ ሰላም ሚዲያ

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

14 Nov, 18:32


#ፍኖት ጥያቄ እና መልስ መርሐግብር

መርሐግብሩ እስከ 5:00 የሚቆይ ሲሆን ተሸላሚ የሚሆነው ቀድሞ የመለሰ ሳይሆን የተቀመጡትን ጥያቄዎች ሙሉ በሙሉ #በፍጥነት የመለሰ ይሆናል። ስለዚህ በቀሩት ሰዓታት ያልተሳተፋችሁ መሳተፍ ትችላላችሁ።

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

14 Nov, 17:08


🎲 Quiz ''ፍኖት ጥያቄ እና መልስ - ህዳር 5''
👉 "Start the quiz "  የሚለውን ይጫኑ... 👉 "I am ready" የሚለውን ሲጫኑ ጥያቄ እና መልሱ ይጀምራል። #መልካም_ዕድል |ፍኖተ ሰላም ሰ/ት/ቤት ሚዲያ
🖊 5 questions · 30 sec

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

14 Nov, 16:51


#ከደቂቃዎች በኋላ ይጀምራል።
#ጥያቄዎቹን ቀድሞ ሙሉ በሙሉ ለመለሰ የመጀመሪያው ሰው የካርድ ሽልማት ይኖረዋል።

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

13 Nov, 09:46


#የመረጃ_ሰዓት

Time መጽሔት በልዩ እትሙ "የአእላፋት ዝማሬ"ን ምስል አወጣ

በአሜሪካን ሀገር ኒውዮርክ የሚታተመውና ከ1923 ዓ.ም. ጀምሮ ኅትመቱ ያልቆመው 105 ሚልዮን አንባቢያን ባሉት ቁጥር አንዱ "Time” መጽሔት የኢትዮጵያን የገና በዓል በማስመልከት በጻፈበት አንቀጽ የአእላፋት ዝማሬን ከፊል ገጽታ በውስጥ ገጹ ላይ አካትቶአል:: "Jesus” በሚል ዐቢይ ርእስ የታተመው የ2024 ዓ.ም. የመጽሔቱ ልዩ ዕትም ላይ "የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች በታኅሣሥ 27 (January 6, 2024) በገና ቅዳሴ ላይ ሲካፈሉ በማለት የአእላፋት ዝማሬ ላይ ጧፍ ይዘው እየዘመሩ የነበሩ ምእመናንን ይዞ ወጥቶአል::

"መጽሔቱ የአእላፋት ዝማሬን ገጽታ ይዞ መውጣቱ ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ የቀረበ የሚታይ ማስታወቂያ መሆኑ ደስ ይለናል" ያሉት የአእላፋት ዝማሬ የሕዝብ ግንኙነት አስተባባሪ ወ/ሮ ቤርሳቤሕ ደረጄ "ሆኖም መጽሔቱ ዝማሬውን "ቅዳሴ ሲያስቀድሱ" ብሎ መግለጹ በቅዳሴ ላይ ምእመናን መብራት ይዘው የሚሳተፉበት ሥርዓት የሌለ ከመሆኑ አንጻር ዘግባውን ያጎድለዋል ብለዋል::

በዘገባው ላይ ታይም መጽሔት "የኢትዮጵያ ስድሳ በመቶ የሚሆን ሕዝብ ኦርቶዶክስ ክርስቲያን ነው" ሲል የገለጸ ሲሆን "ከራሽያ ቀጥሎ የዓለም ትልቁ ኦርቶዶክስ ሕዝብ ቁጥር ያለባት ሀገር ናት" ብሎአል:: በ2024 ጃንዋሪ 6 የተካሔደውን የአእላፋት ዝማሬ በመስቀል አደባባይ እንደተካሔደ አድርጎ ቢገልጸውም በቦሌ ደብረ ሳሌም መድኃኔዓለም የተካሔደ መሆኑ ይታወሳል:: የዘንድሮው የአእላፋት ዝማሬ በመሐረነ አብ ዑደት እና በመዝሙር ጥናት ከጾመ ነቢያት ጋር አብሮ እንደሚጀመር የኢጃት ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ኢየሩሳሌም ዳግማዊት ገልጸዋል::

ፍኖተ ሰላም ሚዲያ
-------------------
ኅዳር 4/2017 ዓ.ም

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

12 Nov, 16:37


በጉባኤውም የመጀመሪያ ቀን ብፁዕነታቸው የእንኳን ደህና መጥታችሁ በማለት የመክፈቻ ቃለ በረከት የሰጡ በቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ውሳኔ እንድንመራው ኃላፊነት የተጣለብንን የሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት በከፍተኛ ለውጥ ላይ ይገኛል ።

ሀገረ ስብከቱ አዲስ ከመሆኑ አንጻር ለማደራጀትና በሀገረ ስብከቱ የሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት ያለባቸውን ውስብስብ ችግር ለመፍታት ብዙ አስቸጋሪ ሁኔታዎች ቢያጋጥሙንም በእግዚአብሔር እርዳታ ዘርፈ ብዙ ችግሮችን አስወግደናል።

ለዚህም ነው ሀገረ ስብከቱ ከተቋቋመ ገና አንድ ዓመቱ በመሆኑ መሰብሰብያ አዳራሽ እንዲሁም የራሱ የሆነ የጽሕፈት ቤት ስፍራ የሌለው መሆኑን በመገንዘብ ብፁዕ አቡነ ሔኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በተውሶ የሀገረ ስብከቱን መሰብሰብያ አዳራሽ ስለፈቀዱልን እናመሰግናቸዋለን ብለዋል ።

  በመቀጠልም መጋቤ ጥበባት ደምሰው መርሻ የደቡብ ምዕራብ ሸዋ እና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ አጠቃላይ የሥራ ሪፖርት ያቀረቡ ሲሆን በመቀጠልም የክፍላተ ከተማ ሊቃነ ካህናት በክፍለ ከተማቸው የተከናወኑትን ዓመታዊ የሥራ ክንውን ሪፖርት የብፁዕ አባታችን አቡነ ሳዊሮስ ሐዋርያዊ ጉዞ ፣ የስብከተ ወንጌል እና ሐዋርያዊ አገልግሎት ፣ ምግባረ ሠናይ ፣ ሰበካ ጉባኤ አደረጃጀት እና አወቃቀር ፣ የሰንበት ትምህርት ቤት አደረጃጀት ፣ የአብነት ትምህርት ቤቶች እንቅስቃሴ ፣ መልካም አስተዳደር ፣ የቅርሳ ቅርስ አጠባበቅን ፣ የፋይናንስ አያያዝ እና ቁጥጥር ፣ ዓመታዊ የገቢ ውጤት ፣ ያጋጠሙ ችግሮች ፣ እንዲሁም የ2017 ዓ/ም ዕቅድን በተመለከተ  አቅርበዋል ።

" የስብከተ ወንጌል ተደራሽነት ለዘመናችን "በሚል ርዕስ በመልአከ ሰላም ቆሞስ አባ ቃለፅድቅ ሙልጌታ (ዶ/ር ) በጠቅላይ ቤተክህነት የስብከተ ወንጌል እና ሐዋርያዊ ተልዕኮ መምሪያ ክፍል ኃላፊ ልዩ ስልጠና ሰጥተዋል ።
 
"መልካም አስተዳደር ለቤተ ክርስቲያን" በሚል ርዕስ በመ/ር ግርማ ባቱ የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩንቨርሲቲ መምህር  እና የጥናት እና ምርምር ኃላፊ ልዩ ሥልጠና ሰጥተዋል ።

በመልካም አስተዳደር ፣የቤተ ክርስቲያንን ችግር በመቅረፍ ፣ የቤተ ክርስቲያን ሀብት ንብረት እንዳይባክን ፣ ስብከተ ወንጌል እንዲስፋፋ የበኩላቸውን ድርሻ ለተወጡ የሀገረ ስብከቱ  ሰራተኞች የሰርተፍኬት እንዲሁም ልዩ ልዩ ሥጦታ ተበርክቶላቸዋል።

በብፁዕ አባታችን አቡነ ሳዊሮስ መመሪያ ቃለ ምዕዳን እንዲሁም መልዕክት በማስተላለፍ የጉባኤው ፍጻሜ ሆኗል ።
   
ዘገባው:የምስካየ መድኃኔዓለም ሚዲያ ነው ▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
ህዳር 3/2017 ዓ.ም
ፍኖተ ሰላም ሚዲያ

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

12 Nov, 16:37


#የመረጃ_ሰዓት

ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የቆየው  የሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት ዓመታዊ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ተጠናቀቀ ------------------------------------------------
   በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት የመጀመሪያ የሆነው ዓመታዊ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የደቡብ ምዕራብ ሸዋ እና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የምስካዬ ኅዙናን መድኅኔዓለም ገዳም የበላይ ኅላፊ እና  የሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት የየመምሪያ ኅላፊዎች፣ የ5ቱ ክፍላተ ከተሞች ሊቃነ ካህናት ፣ሰባኪያነ ወንጌል፣ የሰበካ ጉባኤና የሰ/ት ቤት ተወካዮች እንዲሁም የህንፃ አሰሪ ኮሚቴ ተወካዮች በተገኙበት በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የመሰብሰቢያ አዳራሽ ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የቆየው ጉባኤ
ተጠቋል።

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

12 Nov, 11:28


#ህዳር_5 ይጠብቁን
____
ፍኖተ ሰላም ሚዲያ

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

11 Nov, 17:02


Walgahiin waligalaa Sabakaa Gubaa'ee Waggaa 1ffaa Biyya Lallaba Magaalaa Shaggar Bakka Eebbifamoo Abuune Saawiroos Argamanitti Eegalameera.

የሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት 1ኛ ዓመት የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ  ብጹዕ አቡነ ሳዊሮስ የሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ በተገኙበት  መካሄድ ጀምሯል።

|ፍኖተ ሰላም ሚዲያ

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

01 Nov, 19:00


#የማስታወቂያ_ሰዓት
-------------------------------
የጥቅምት ወር ወርኀዊ የአባላት መዋጮ
------------------------------------
#ከ23-30 ባሉት ቀናት  በኮርስ መርኃግብራት፣በመዝሙር ጥናት፣በወርኃዊና ሰርክ ጉባኤያት እንዲሁም በእሑድ መደበኛ የአንድነት ጉባኤያት ላይ በመገኘት ወርኃዊ የአባላት መዋጮ በመክፈል የምትችሉ ሲሆን

#ከጀማርያን_ጀምሮ

👉 ለወጣት አባላት 25 ብር

👉👉 በአካል መገኘት የማትችሉ አባሎቻችን ካሉበት ሆነው በቴሌ ብር መክፈል ትችላላችሁ ።

   👉 የቴሌ ብር ስልክ ቁጥር ፦ 
+251985071216 ዳግም አበበ

👉በቴሌ ብር ክፍያ ከፈጸማችሁ ቡኃላ የከፈላችሁበትን ደረሰኝ በዚሁ ስልክ በቴሌ ግራም በመላክ / በመደወል መክፈላችሁን እንድታሳውቁ በእግዚአብሔር ስም እናሳስባለን ።

ወርኃዊ መዋጮዬን በመክፈል የአባልነት ግዴታዬን እወጣለሁ የሰንበት ትምህርት ቤታችን መንፈሳዊ አገልግሎት እደግፋሁ

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

01 Nov, 04:12


የቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡
-------------------------
ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ፡፡

በመንፈስ ቅዱስ የሚመራው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በዓመት ሁለት ጊዜ እንዲሆን በፍትሕ መንፈሳዊ አንቀጽ 5 ቁጥር 164 በተደነገገው መሠረት ምልዓተ ጉባኤው ከጥቅምት 11 እስከ ጥቅምት 20 ቀን 2017 ዓ.ም. ድረስ መደበኛ ስብሰባውን ሲያካሂድ ሰንብቷል፡፡

ምልዓተ ጉባኤው ልዑል እግዚአብሔርን አጋዥና መሪ በማድረግ ስለ ቤተ ክርስቲያናችን መንፈሳዊና ማኅበራዊ አገልግሎት፣ ስለምጣኔ ሀብት እድገት፣ በሀገራችን እየተከሰቱ ስላሉት ውስጣዊና ውጫዊ ፈተናዎች፣ ስለ ሀገር ሰላምና አንድነት፣ ስለ ቤተ ክርስቲያን አስተዳደርና ሐዋርያዊ ተልእኮ ስለ ሰው ልጅ ሁሉ ደኅንነት በስፋት በመወያየት ለቤተ ክርስቲያንና ለሀገር ጠቃሚ የሆኑ ውሳኔዎችን
አሳልፏል፡፡

በዚሁ መሠረት፡-

1. ከጥቅምት 4 ቀን እስከ ጥቅምት 9 ቀን 2017 ዓ.ም. ድረስ የተካሄደው ዓለም አቀፍ ጉባኤ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ 43ኛው አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ዓለም አቀፍ ስብሰባ ተሳታፊዎች የቀረበው ቃለ ጉባኤና የአቋም መግለጫ በሁሉም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አህጉረ ስብከት የበጀት ዓመቱ የሥራ መመሪያ እንዲሆን ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ አስተላልፏል፡፡

2. በተለያዩ የሀገራችን አካባቢዎች እየተከሰተ ባለው የሰላም እጦት፣ የእርስ በርስ ግጭት ምክንያት የሰው ሕይወት እየተቀጠፈ፣ አካል እየጎደለ፣ ማኅበራዊ ትሥሥር እየተናደ፣ ሰብአዊ ክብር እየተጎዳ፣ መብት እየተጣሰ፣ በዜጎች ላይ ሥጋትና አለመረጋጋት እየበዛ ሀብትና ንብረት እየወደመ ስለሆነ ጉዳዩ አስቸኳይ መፍትሔ የሚያስፈልገው መሆኑ አጠያያቂ አይደለም፡፡ ስለሆነም በጦርነትና በግጭት የመጣ ሰላም፣ የተገነባ ሀገር የለምና በሀገራችን እያጋጠመ ያለውን ችግር ለመፍታት ካለፈው በመማር በጥበብ፣ በማስተዋልና በሰለጠነ አካሄድ በሰላማዊ መንገድ በመወያየት ችግሩ በእርቅ እንዲፈታ ለሁሉም ወገኖቻችን ቅዱስ ሲኖዶስ የሰላም ጥሪውን በአጽንኦት ያቀርባል፡፡

3. በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከትና በሥሩ ባሉ ገዳማትና አድባራት ውስጥ እየቀረቡ ያሉ መጠነ ሰፊ የአስተዳደር ችግሮች እንዲፈቱ ለማድረግ ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት ጀምሮ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት፣ በክፍላተ ከተሞችና ችግር አለባቸው ተብለው በጥናት በሚለዩት አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ላይ የማጣራት ሥራ እንዲሠራና ውጤቱ ለውሳኔ እንዲቀርብ በሦስት ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የሚመራ ኮሚቴ ቅዱስ ሲኖዶስ ሰይሟል፡፡

4. የኦሲኤን ቴሌቪዥን ስርጭት የተቋረጠ በመሆነ በአዲስ መልክ ሁሉንም የአፋን ኦሮሞ ቋንቋ ተናጋሪዎች ማህበረሰብ ባቀፈ መልኩ አገልግሎት እንዲሰጥ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአፋን ኦሮሞ ኔትወርክ በሚል ስያሜ በጠቅላይ ቤተ ክህነት በኩል ውል ተፈርሞ በአዲስ መልክ የሳተላይት ግዥ እንዲፈጸም ሆኖ አስተዳደሩን በተመለከተ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መገናኛ ብዙኃን ድርጅት ጋር በአንድ ሊቀ ጳጳስና ቦርድ ራሱን በቻለ ሥራ አስኪያጅ እየተመራ አገልግሎቱ ከነበረው በተሻለ ሁኔታ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡

5. የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ ለደቀ መዛሙርት የሚሰጠው የምስክር ወረቀት አድቫንስ ዲፕሎማና ዲግሪ እንዲሆን ሥርዓተ ትምህርቱ ለሚሰጠው የትምህርት ማስረጃ በሚመጥን መልኩ ተሟልቶ፣ ሊኖረው የሚገባው የሰው ኃይል በየዘርፉ ተጠናክሮ ወደ ትግበራ እንዲገባ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፣

6. የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በሥነ ሕንጻና በኪነ ጥበብ በዓለም ደረጃ ከፍተኛ አድናቆትና ክብር የሚሰጠው ከመሆኑ በተጨማሪ በመዐርገ ጵጵስና ፕትርክና የሚሾሙ አባቶች ሥርዓተ ሲመት የሚፈጸምበት፣ ጥንታዊና ታሪካዊ ካቴድራል መሆኑን ታሳቢ በማድረግ ለዕድሳት ሥራው የገንዘብ ድጋፍ እንዲደረግለት ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፤ በተጨማሪም ምእመናን እስከ አሁን እንደሚያደርጉት ሁሉ ለእድሳት ሥራው አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ቅዱስ ሲኖዶስ
ያሳስባል፡፡

7. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዐቢይ ኮሚቴ ሥራውን አጠናክሮ እንዲቀጥልና በንቃት እንዲሳተፍ ሁሉንም አህጉረ ስብከት ባቀፈ ሁኔታ የአጀንዳ መረጣና ተሳታፊ የመለየት ሥራ እንዲከናወን ሆኖ ዐቢይ ኮሚቴው የሥራ ዕቅዱንና አፈጻጸሙን ለቋሚ ሲኖዶስ እያቀረበ በማስወሰን እንዲሠራ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡

በአጠቃላይ ቅዱስ ሲኖዶስ በመንፈስ ቅዱስ እየተመራ ላለፉት ተከታታይ ቀናት በመንፈሳዊ፣ በማኀበራዊና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ተገቢውን ውሳኔ በማስተላለፍ መደበኛ ስብሰባውን ጥቅምት 21/2017 ዓ.ም በጸሎት አጠናቅቋል፡፡ መሐሪና ሁሉን ቻይ የሆነ እግዚአብሔር አምላካችን ለሀገራችን፣ ለሕዝባችን፣ ለዓለሙ ሁሉ ሰላሙን፣ ፍቅሩንና አንድነቱን ይስጥልን፡፡

እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ
ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን
አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ
ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም
ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
ጥቅምት ፳፩ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም.
ኢትዮጵያ አዲስ አበባ
----------------
ፍኖተ ሰላም ሚዲያ
ጥቅምት 21/2017 ዓ.ም

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

01 Nov, 04:07


የቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

30 Oct, 19:53


#ታላቅ የንግስ በዓል ጥሪ!!!
#ልዩ_ጉባኤ
#ጥቅምት 22-27

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

26 Oct, 17:50


ሥርዓተ ማኅሌት ዘዘመነ ጽጌ አራተኛ ሳምንት (ጥቅምንት ፲፯) ከሊቃውንቱ ጋር አብረን ለማመስገን ይረዳን ዘንድ እንደሚከተለው ተዘጋጅቷል።
#ለወዳጆ_ሼር ማድረጎን እንዳይረሱ
-----------
ፍኖተ ሰላም ሚዲያ

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

26 Oct, 16:54


#መልዕክት 17/02/2017

ነገ እሑድ 17/02/2017 ዓ.ም የእሑድ (የአንድነት) መደበኛ ጉባኤ #በአዳራሽ ውስጥ እና ጊቢ ውስጥ ባሉ ተደራራቢ መርሐግብራት ምክንያት የማይኖር መሆኑን እናሳውቃለን።

#መደበኛ የኮርስ መርሐግብርና
#መደበኛ መዝሙር ጥናት በሰዓታቸው ይቀጥላሉ።

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

25 Oct, 14:51


#ቅዱስ_ሲኖዶስ_በኢትዮጵያ 

ቅዱስ ሲኖዶስ አበው ሊቃነ ጳጳሳት ስለቤተክርስቲያን ዶግማ ቀኖና ሥርዓትና ትውፊት እንዲሁም አስተዳደር የሚመክሩበት በመንፈስ ቅዱስ የሚቃኝ ጉባኤ ነው፡፡ ይህም “ቅዱስ ሲኖዶስ ማለት ፓትርያርክ ሊቃነ ጳጳሳት ጳጳሳትና ኤጲስ  ቆጶሳት የሚያደርጉት ዓቢይ ጉባዔ ነው፡፡” ተብሎ በሕገ ቤተ ክርስቲያን የተገለጸው ነው፡፡ /ሕገ ቤተክርስቲያን፤ አንቀጽ ፪/፡፡
                                                                  የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን በራሷ ሲኖዶስ መመራት ከጀመረች ከግማሽ ምዕት ዓመት በላይ ሆኗል፡፡ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋነኛ ዓላማ የቤተ ክርስቲያንን አንድነት መጠበቅ ነው፡፡ ቅዱስ ሲኖዶስ የቤተ ክርስቲያን የአንድነቷ መገለጫ ነው፡፡ በየጊዜው በሚመጡ ክስተቶች ዶግማዊ፣ ቀኖናዋ ሥርዐቷ፣
ትውፊቷ እንዲሁም አስተዳዳሯ እንዳይፈታ መጠበቂያ ነው፡፡ አዳዲስ አስተምህሮዎች ሲመጡ በዶግማዊ መሠረት ማረቅ፣ ማቅናት፤ ልጆቿን የሚመሩ አበው ሊቃነ ጳጳሳትን መሾም የቅዱስ ሲኖዶስ ዋነኛ ተግባራት ናቸው፡፡  

          #ማጠቃለያ
  በየዓመቱ በጥቅምት ወር በሚካሔደው የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ ለቅድስት ቤተክርስቲያን አገልግሎት የሚጠቅሙ፣ ለመንፈሳዊ አስተዳደሯም የሚበጁ መሠረታዊ ጉዳዮች ይነሣሉ፤ መመሪያዎችና ውሳኔዎች  በአባቶች የሚጸድቁበት ታላቅ ጉባኤ ነው፡፡ 

ቅዱስ ጴጥሮስ በመልእክቱ “ለመንጋው ምሳሌ ኹኑ እንጂ ማኅበሮቻችሁን በኃይል አትግዙ፡፡ የእረኞችም አለቃ በሚገለጥበት ጊዜ የማያልፈውን የክብርን አክሊል ትቀበላላችሁ” (፩ኛ ጴጥ.፭፥፫-፬) ተብሎ እንደተጻፈው ግብረ ኖሎት (የመንፈሳውያን እረኞች ተግባር) ለምድራዊ ጥቅም እና ዝና በመጨነቅ ሳይኾን፤ ከእግዚአብሔር ዘንድ የሚያገኙትን ዋጋ በማሰብ በበግ የሚመሰሉ ምእመናን በተኩላዎች እንዳይነጠቁ፣ በቅድስት ቤተ ክርስቲያን እየተሰባሰቡ ምግበ ሥጋ ምግበ ነፍስ የኾነውን ቃለ እግዚአብሔር እንዲመገቡ፣ ሰማያዊ ሕይወት የሚያስገኘውን ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን እንዲቀበሉ በማድረግ ወደ ዘለዓለማዊ ማረፊያቸው ገነት (መንግሥተ ሰማያት) እንዲገቡ የድኅነት መንገዱን ማመቻቸት ነው፡፡
                                                                  ቅዱስ ሉቃስ “በገዛ ደሙ የዋጃትን የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ትጠብቋት ዘንድ መንፈስ ቅዱስ እናንተን ጳጳሳት አድርጎ ለሾመባት ለመንጋው ዅሉና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ” (ሐዋ. ፳፥፳፰) በማለት እንዳስተማረው አባቶቻችን በሥርዐትና በጥንቃቄ በጎች ምእመናንን መምራት ይገባል፡፡ ምእመናኑም አባቶቻችንን ማክበር፣ትእዛዛቸውንም መፈጸም ይጠበቅብናል፡፡ ከዚሁ ዂሉ ጋርም እያንዳንዳችን፣ በቤተክርስቲያን አስተዳደር የመጨረሻው ወሳኝ አካል በኾነው ቅዱስ ሲኖዶስ የሚወጡ ውሳኔዎችን ተቀብለን የመፈጸምና የማስፈጸም ክርስቲያናዊ ግዴታ አለብን፡፡

  |ፍኖተ ሰላም ሚዲያ
ጥቅምት 15/2017 ዓ.ም

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

25 Oct, 14:49


ቅዱስ ሲኖዶስ

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

24 Oct, 16:58


#ቅዱስ_ሲኖዶስ

ሲኖዶስ” ማለት ጉባኤ ኖሎት ጉባኤ አበው(የአባቶች ጉባኤ) ማለት ሲኾን፤ ቅዱስ ፓትርያርኩ የሚመሩት ጉባኤ ማለት ነው፡፡

የቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ የተጀመረው በቅዱሳን ሐዋርያት ነው፡፡ በጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ትእዛዝ ወደ አራቱም አቅጣጫ ማዕዘናት የተላኩት ቅዱሳን ሐዋርያት ከአሕዛብና ከአይሁድ ወደ ክርስትና በመጡት መካከል የተፈጠረውን አለመግባባት ለመፍታት በ፶ ዓ.ም በኢየሩሳሌም ተሰብስበዋል፡፡ /የሐዋ.፲፭፥፩/፡፡
                                                                  ከሐዋርያት ቀጥሎ የተነሡት አባቶችም በየአብያተክርስቲያናቱ የሚከሰቱ ችግሮች ለመፍታት ይሰበሰቡ ነበር፡፡ ታሪክን ወደ ኋላ ስንመለከት በጥንቷ ቤተክርስቲያን አንድ ጊዜ ለቅዱሳን የተሰጠውን ሃይማኖት ከመናፍቃን ለመጠበቅ አካባቢያዊ (Local Council) እና ዓለም አቀፋዊ (Ecumenical Council) የሆኑ የሲኖዶስ ጉባኤያት እንደተደረጉ እንረዳለን፡፡ ከእነዚህም መካከል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሦስት ዓለም አቀፋዊ ጉባኤያትን ትቀበላለች፡፡ እነሱም፡- ጉባኤ ኒቂያ (በ፫፻፳፭ ዓ.ም)፣ ጉባኤ ቁስጥንጥንያ (በ፫፻፹፩ ዓ.ም) እና ጉባኤ ኤፌሶን (በ፬፻፴፩ ዓ.ም) ናቸው፡፡

ይህን አብነት በማድረግ የቤተክርስቲያናችን ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ከየሀገረ ስብከታቸው ተጠርተው በየዓመቱ ኹለት ጊዜ በወርኃ ጥቅምትና ግንቦት ተሰብስበው በአብያተ ክርስቲያናት ጉዳይ በጋራ ይመክራሉ፡፡
------------------------------
ፍኖተ ሰላም ሚዲያ
ጥቅምት 14/2017 ዓ.ም

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

24 Oct, 16:56


ቅዱስ ሲኖዶስ

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

24 Oct, 14:36


#የማስታወቂያ_ሰዓት
የርቀት ትምህርት በቅድስት ሥላሴ ዩንቨርሲቲ
መማር ለምትፈልጉ ሙሉውን ያንብቡ

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

23 Oct, 03:27


#የክራር ዜማ መሣሪያ ሥልጠና
#ምዝገባ ተጀምሯል
#ምዝገባው ለአጭር ጊዜ የሚቆይ ነው።
#ለበለጠ መረጃ   0947535941

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

22 Oct, 13:13


የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ፣የባሕር ዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ አብርሃም በመርካቶ ሸማ ተራ አካባቢ በደረሰው የእሳት ቃጠሎና ቃጠሎውን ተከትሎ በንብረቶቻችው ላይ ጉዳት ላጋጠማቸው ወገኖች የተሰማቸውን ጥልቅ ሐዘን ገልጸዋል።

ምንጭ :- የ/ኢ/ኦ/ተ/ቤተ ክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

ፍኖተ ሰላም ሚዲያ
ጥቅምት 12/2017 ዓ.ም

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

22 Oct, 05:48


#ማኅሌተ_ጽጌ ምስለ ሰቈቃወ ድንግል በግእዝና አማርኛ

በሰንበት ት/ቤቱ የልማት ሱቅ ያገኛሉ።

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

18 Oct, 07:32


https://youtu.be/NdDeh5ldhmo?si=qG-FBfaYEUveFvZ6

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

18 Oct, 06:27


#የክራር ዜማ መሣሪያ ሥልጠና
#ምዝገባ ተጀምሯል
#ምዝገባው ለአጭር ጊዜ የሚቆይ ነው።
#ለበለጠ መረጃ   0947535941

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

16 Oct, 10:08


በ43ኛው አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ የሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት ሪፖርት
----------------------------------------
" የሀገረ ስብከታችን ሊቀ ጳጳስ የብፁዕ አቡነ ሳዊሮስን ሐዋርያዊ ጉዞ በተመለከተ፡-

የሀገረ ስብከታችን ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ ከሐምሌ 01/2015 ዓ.ም ጀምሮ በሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት ውስጥ ብዙ ቤተ ክርስቲያን ከልማት ሥራ ለመንግሥት ከሚከፈል ግብር ጋር ተያይዞ ከፍተኛ ችግር የነበረበት ሲሆን ብፁዕነታቸው ለጉዳዩ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥተው ከሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ጋር በመነጋገር የታሠሩ አስተዳዳሪዎችን አስፈትተው እንዲሁም የልማት ሱቆች ተዘግተው የታሸጉት ሱቆች ተከፍተው ሥራቸውን እንዲጀምሩ ከፍተኛ ድርሻ ሰጥተዋል፡፡ በተመሳሳይ የሌሎችንም አድባራት ችግሮች በዚሁ አይነት እንዲቀረፉ አድርገዋል፡፡

በወይብላ ማህደረ መለኮት ቅድስት ማርያም ካቴድራል የጥምቀት በዓል አከባበር ላይ ያለውንም ችግር በቅርበት በመከታተል የጥምቀት ማክበሪያ ቦታ እንዲሰጥና ችግሩ ሙሉ በሙሉ እንዲቀረፍ አድርገዋል፡፡ 

የስብከተ ወንጌል አገልግሎትን በተመለከተ፡-

ወጣትነት ለቤተ ክርስቲያን ከሚለው ስያሜ የጉባኤ አዘገጃጀት ጀምሮ በየአድባራቱ ወርኃዊና ሳምንታዊ ታላላቅ ጉባኤያት ተደርገዋል፡፡ በየአድባራቱም የሰርክ ጉባኤያት እንዲጠናከሩና ሕዝበ ክርስቲያኑ ስብከተ ወንጌልን በበቂ ሁኔታ እንዲያገኝ ተደርጓል፤በዚህም በተደረገው ጥረት ከኢ-አማንያን የተመለሱ ወንድ 54 ሴት 77 ድምር 131 ወደ እናት ቤተ ክርስቲያን ተመልሰዋል፡፡

የሰንበት ት/ቤት አገልግሎትን በተመለከተ፡-

በየአድባራቱ ያሉ ሰንበት ት/ቤቶች ተጠናክረው መንፈሳዊ አገልግሎታቸውን እንዲሰጡ ተደርጓል፡፡

የልማት ሥራን በተመለከተም፡-

በሀገረ ስብከቱ ውስጥ እየተገነቡ ያሉ አዳዲስ ሕንፃ አብያተ ክርስቲያናት በተጠናከረ መልኩና በፍጥነት እንዲሰሩ የተደረገ ሲሆን የተለያዩ ራስ አገዝ የገቢ ማስገኛ የልማት ሥራዎችም በተሻለ መልኩ እየተሠሩ ይገኛሉ፡፡ የገዳማት አገልግሎትና የአብነት ት/ቤቶችም እንዲጠናከሩ እየተደረገ ይገኛል፡፡

የፋይናንስ አያያዝና ቁጥጥር በተመለከተ፡-

ከቀድሞ በተሻለ ሁኔታ እየተሠራ የአድባራቱ ገቢ እንዲያድግ ከፍተኛ ጥረት ተደርጎ አመርቂ ውጤት ተገኝቷል፡፡ በበጀት ዓመቱ ያጋጠሙ ችግሮችንም እንደየሁኔታው መፍትሔ ተሰጥቶበታል፡፡

የ2017 ዓ.ም ዕቅድን በተመለከተ፡-

በዋናው ሪፖርት አጠቃለን ያስገባን ሲሆን የታቀዱትን ዕቅዶች በሥራ ላይ ለማዋልም ሙሉ አቅማችንን ተጠቅመን ጥረት በማድረግ ላይ እንገኛለን። "

|ፍኖተ ሰላም ሚዲያ
ጥቅምት 06/2017 ዓ.ም

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

16 Oct, 10:07


በ43ኛው አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ የሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት ሪፖርት
----------------------------------------

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

16 Oct, 09:53


https://youtu.be/ufHU1v_ig3I?si=2DC1OidxljSm49wg

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

15 Oct, 08:31


አባታችንም አንበሶችና ነብሮች፣ ድብና ዘንዶ ወዳሉበት ምድረ ከብድ ተመለሱ፡፡

ጻድቁ ከዚህ ዓለም ድካም የሚለዩበት በቀረበ ጊዜ፤ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገልጦ ቃል ኪዳን ገባላቸው፡፡ ዕድሜያቸውም አምስት መቶ ስድሳ ሁለት ሲሆን፤ በሰላም በፍቅር ዐረፉ፤ጌታችንም ነፍሳቸውን በመላእክትና በቅዱሳን ሁሉ ምስጋና አሳረጋት፡፡

የአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፤ አሜን፡፡

ጥቅምት ፭  ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

1.አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ጻድቅ
2.ቅዱስ ኪራኮስ አረጋዊ (ዻዻስ ወሰማዕት)
3.ቅድስት ሐና ሰማዕት (እናቱ)
4.ቅዱስ ያዕቆብ ወልደ እልፍዮስ (ከ12ቱ ሐዋርያት)
5.አባ ዻውሎስ ሰማዕት (አርዮሳውያን አንቀው የገደሉት አባት)

#ወርሐዊ_በዓላት

1.ቅዱስ ዼጥሮስ ሊቀ ሐዋርያት
2.ቅዱስ ዻውሎስ ብርሃነ ዓለም
3.ቅዱስ ዮሐኒ ኢትዮዽያዊ
4.ቅዱስ አሞኒ ዘናሒሶ
5.ቅድስት አውጋንያ (ሰማዕትና ጻድቅ)
       
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ዋቤ መጻሕፍት፡-
✍️ ገድለ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ፣
✍️ የቤተክርስቲያን መዝገበ ቃላት
-----------------------------
ፍኖተ ሰላም ሚዲያ
ጥቅምት 5/2017 ዓ.ም

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

15 Oct, 08:28


በሀገረ ግብጽ የተወለዱት ጻድቁ አባት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ የእግዚአብሔር ትእዛዝ ሆኖ ስለ ኢትዮጵያ ይለምኑና ይማልዱ ዘንድ ፈቃዳቸውም ስለነበር ቤተሰቤ፣ ሕዝቤ ወይንም ሀገሬ ሳይሉ ወደ ሀገራችን በመምጣት በጭንቅላታቸው ተዘቅዝቀው ደማቸው ፈሶ እስኪያልቅና ሥጋቸውም አልቆ አጥንቶቻው እንደበረዶ እስኪሆን ድረስ የጸለዩ ታላቅ አባታችን ናቸው፡፡

አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ሀገራቸው ንሂሳ ግብጽ ነው፡፡ አባታቸው ስምዖን እናታቸው አቅሌስያ ይባላሉ፡፡ ልጅ አጥተው ፴ ዘመን ሲያዝኑ ኖረዋል፡፡ አንድ ቀን አቅሌሲያ ቤተ እግዚአብሔር ገብታ ከሥዕለ ሥላሴ ሥር ወድቃ ስትማጸን ክብሩ ከሰማይ ከፍታ የሚበጥ ልጅ እንኪ ተቀበይ የሚል ድምጽ ሰማች፡፡  አቅሌስያም በመጋቢት ፳፱ ቀን ፀንሳ በታኅሣሥ ፳፱ ቀን ደም ግባቱ እጅግ የሚያምር ወንድ ልጅ እንደወለደች መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል በሰው አምሳል መጥቶ ‹‹የዚህ ልጅሽ ስሙ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ይሁን›› አላት፡፡ ወዲያውም ሕፃኑ ተነሥቶ ከእናቱ ጭን ወርዶ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ሦስት ጊዜ ሰገደ፡፡ ዳግመኛም ‹‹ከጨለማ ወደ ብርሃን ለአወጣኸኝ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ምስጋና ይሁን›› አለ፡፡

ከዚህም በኋላ ጻድቁ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ መጋቢት ፳፱ ቀን ተፀንሰው ታኀሣሥ ፳፱  ተወለዱ፡፡ አባታችን ዐይን በገለጹ ጊዜ ከሚታይ ነገር ላይ እንዲያርፍ እርሳቸውም በተወለዱ ጊዜ ተነሥተው «ስብሐት ለአብ ስብሐት ለወልድ ስብሐት ለመንፈስ ቅዱስ ዘዓውፃእከኒ እምጽልመት ውስተ ብረሃን» ብለው አመስግነዋል። ቅዱስ አባታችን ለአምላካቸው ሰግዶ አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ካመሰገነ በኋላ እናታቸው አላቀፈቻችውም፤ ጡትም አልጠቡም፡፡ ሦስት ዓመት ሲሞላቸው እግዚአብሔር አምላክ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤልን እንዲህ ብሎ አዘዘው፡- ‹‹ሕፃኑን ከእናቱ ክንድ ተቀበል፣ ብዙ ገዳማውያን ወዳሉበት ገዳም ውሰድና ከበራቸው አስቀምጠው፤ አበ ምኔቱንም ሕፃኑን ከበር አንሥተህ ካንተ ዘንድ አኑረው፤ ስለ ልብሱ ስለ ምግቡ አታስብ፤ ሕፃኑ የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ ነውና ምግቡም መንፈሳዊ ነው፡፡ ይኸውም ከእግዚአብሔር የሚወጣ ቃል ነው፤ ሰው በእንጀራ ብቻ እንደማይኖር ዕወቅ በለው › በማለት አዘዘው፡፡ ቅዱስ ገብርኤልም እንደታዘዘው ከሰማይ ወርዶ ሕፃኑን ከእናቱ ክንድ ወስዶ በክንፎቹ አቅፎ እስከ ሰባቱ ሰማይ አውጥቶ በሥሉቅ ቅዱስ ፊት አቅርቦት አስባረከው፡፡

መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ዳግመኛ ተገልጦላቸው ወደ ሰማይ አሳረጋቸውና ከእግዚአብሔር ፊት አቆማቸው፡፡ ያን ጊዜም ጌታችን ክቡራን የሆኑ እጆቹን ዘርግቶ ከባረካቸው በኋላ  በጸሎትህ ከሲኦል የምታወጣቸው ብዙ ነፍሳት አሉ፤ ድውያንንም ትፈውሳለህ፤ ከእንግዲህ ወዲህ ከሰው ተለይተህ ወደ ጫካ ገብተህ ከአንበሶችና ከነብሮች ጋር ኑር› አላቸው፡፡ አባታችንም ጌታችንን ‹‹የሰጠኸኝ እነዚህ አንበሶችና ነብሮች ምን ይመገባሉ?› አሉት፡፡ ጌታችንም ‹‹የረገጥከውን መሬት ይልሳሉ በዚያም ይጠግባሉ፡፡ ከዚህ በኋላ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ከራሳቸው እስከ እግራቸው ድረስ ጠጉር በቀለላቸው፡፡ የጠጉራቸውም ርዝመቱ አንድ ክንድ ከስንዝር ነው፡፡ አባታችንም በታላቅ ተጋድሎ ሲኖሩ በጸጋ ላይ ጸጋ ተጨመረላቸው፡፡ ከዕለታት በአንደዋ ቀን የፈወሳቸው ሕሙማን ብዛታቸው እልፍ ሆነ፡፡
                                                                                                                                                                                                                                    ከዚህም በኋላ አባታችን ወደ ጫካ ገብተው ብቻቸውን የበጋውን ሐሩር የክረምቱን ቁር ታግሠው ምንም ልብስ ሳይለብሱ ራቁታቸውን ሆነው በተጋድሎ ኖሩ፡፡ ከጽኑው ተጋድሎአቸውና ከጫካው ቅዝቃዜ የተነሣ ሰውነታቸው አልቆ ከአጥንታቸው ጋር ተጣበቀ፡፡ ምንም ነገር አይመገቡም፤ ውኃም ፈጽሞ አይጠጡም ነበር፡፡ አባታችን በምድረ በዳ እንደሰው ሳይሆን እንደመላእክት ኖሩ፡፡ ቅዱሳን መልእክትም ዘወትር ይጎበኟቸው ነበር፡፡

ጻድቁ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ በኢትዮጵያ

ጌታችንም ‹‹በተወለድሁባት፣ በተጠመቅሁባትና ከሞት በተነሣሁባት ዕለት እልፍ እልፍ ነፍሳትን እምርልሃለሁ›› አላቸው፡፡ ከዚህም በኋላ አባታችን ስድሳ አንበሶችና ስድሳ ነብሮች እየተከተሏቸው ወደ ሀገራችን ኢትዮጵያ መጡ፡፡ ቅዱስ ገብርኤልም ከእነዚሁ ተከታዮቻቸው ጋር በነፋስ ሠረገላ ጭኖ ምድረ ከብድ አደረሳቸው፡፡ ዳግመኛም ደብር ቅዱስ  ወደሚባለው ወደ ዝቋላ ወሰዳቸው፡፡ አባታችንም በውኃው ዳር ቆመው ምሥራቁን፣ ምዕራቡን፣ ሰሜኑን፣ ደቡቡን በመለከቱ ጊዜ የኢትዮጵያ ሰዎች ኃጢአታቸው በፊታቸው የተገለጠ ሆነ፡፡ ሰው የገዛ ፊቱን በመስታወት እንደሚያይ የኃጥአንም ሥራቸው በአባታችን ፊት እንዲሁ የተገለጠ ነውና፡፡ አባታችንም የኢትዮጵያን ሰዎች ኃጢአታቸውን በግልጽ በተመለከቱ ጊዜ ተወርውረው ወደ ባሕሩ በመግባት ተዘቅዝቀው መጸለይ ጀመሩ፡፡ ‹‹ከባሕር እንዳልወጣ፣ በእግሬም እንዳልቆም በሕያው ስምህ ምያለሁ›› ብለው ዐርባ መዓልት ዐርባ ሌሊት ቆዩ፡፡ በ፵  ቀናቸው የታዘዘ መልአክ መጥቶ ‹‹ስምህን የጠራ መታሰቢያህን ያደረገውን እምርልሃለሁ ብሎሃል›› አላቸው፡፡ አባታችንም መልአኩን ‹‹መላ ኢትዮጵያን ካልማረ ከዚህ ባሕር አልወጣም›› አሉት፡፡ መልአኩም ከእሳቸው ተለይቶ ከሄደ በኋላ አባታችን በዚያ ባሕር ውስጥ መቶ ዓመት ተዘቅዝቀው ሲጸልዩ ኖሩ፡፡ አባታችንም በባሕሩ ውስጥ ተዘቅዝቀው መቶ ዓመት ሲጸልዩ ከኖሩ በኋላ ደማቸው ፈሶ አለቀና ውኃው ደም መሰለ፡፡ ሥጋቸውም አልቆ አጥንቶቻው እንደበረዶ ሆኑ፡፡

ጌታችን መጥቶ ከባሕሩ ዳር በመቆም ‹‹ወዳጄ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ሆይ! መላ ኢትዮጵያን ምሬልሃለሁና ተነሥ ከባሕሩ ውጣ›› አላቸው፡፡ ጌታችን በክቡራን እጆቹ ሁለንተናቸውን ቢዳስሳቸው እንደቀድሞው ደህና ሆኑ፡፡ ጌታችንም ከባረካቸው በኋላ ወደ ምድረ ከብድ እንዲሄዱ ነገራቸው፡፡ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ምድረ ከብድ እንደደረሱ እንደ ዓምድ ተተክለው ሰባት ዓመት ቆመው ጸለዩ፡፡ በዚህም ጊዜ ሰይጣን በቁራ ተመስሎ መጥቶ ሁለት ዐይኖቻቸውን አንቁሮ አጠፋቸው ነገር ግን አባታችን ጸሎታቸውን ሳያቋርጡ ሁለት ሳምንት በጸሎት ቆዩ፡፡ ከሁለት ሳምንት በኋላ ቅዱስ ሚካኤልና ቅዱስ ገብርኤል መጥተው በዐይኖቻቸው ላይ እፍ ብለው ብርሃናቸውን ከመለሱላቸው በኋላ አባታችንን ‹‹ከሰማይ ፍጹም ኃይል ይሰጥሃልና ጠላቶችህን ትበቀል ዘንድ ወደ ዝቋላ ሂድ›› ብለዋቸው ዐረጉ፡፡

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

15 Oct, 08:25


ጥቅምት ፭
---------------------
እንኳን ለአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ዓመታዊ በዓል (ጥቅምት ፭) በሰላም አደረሳችሁ
============================
የኢትዮጵያ ኦርተዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በዝቋላ ተራራ ባለው ባሕር ውስጥ መቶ ዓመት ተዘቅዝቀው ለኢትዮጵያ ሰዎች ምሕረትን የለመኑ አባታችን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቃል ኪዳን የተቀበሉበትን ጥቅምት ፭ ቀን በታላቅ ድምቀት ታከብራለች፡፡

|ፍኖተ ሰላም ሚዲያ
ጥቅምት 5/2017 ዓ.ም

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

15 Oct, 06:25


#ጥቅምት_5
እንኳን ለጻድቁ አባታችን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ዓመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ።
---------------------------
የኢትዮጵያ ኦርተዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በዝቋላ ተራራ ባለው ባሕር ውስጥ መቶ ዓመት ተዘቅዝቀው ለኢትዮጵያ ሰዎች ምሕረትን የለመኑ አባታችን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቃል ኪዳን የተቀበሉበትን ጥቅምት ፭ ቀን በታላቅ ድምቀት ታከብራለች፡፡

አንድም የጻድቁ አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ የእረፍታቸው መታሰቢያ በዓል ነው። ጻድቁ አባታችን እረፍታቸው መጋቢት 5 ቀን ነው ይህ ደግሞ በታላቁ ዓብይ ጾም ወቅት ነው ፍትሃ ነገስት አንቀጽ 15 ላይ በዓብይ ጾም በዓል ማክበር ይከለክላል የሀዘን ወቅት ነውና ከበሮ አይመታም እልልታና ጭብጨባ የለም ፍጹም ሀዘን እንጂ ስለዚህም ወደ ጥቅምት 5 ቀን ተዛውሮ እንዲከበር የመጋቢት 27 ስቅለት ደግሞ ጥቅምት 27 ቀን እንዲከበር ተደረገ፤ ከዚያን ጊዜ አንስቶ ይህ ስርዓት ሆነ ይህንንም  ስርዓት አባቶታችን ሰሩልን

አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ (አቦ፥ አቡዬ)፤

◈ እንደ ቅዱስ ጳውሎስ ብርሃነ ዓለም የኾኑ፤
◈እንደ ቅዱስ እስጢፋኖስ ጸጋንና ክብርን የተሞሉ፤

◈ ኰከበ ገዳም፥ መናኔ ዓለም፥ ምድራዊ መልአክ፤
◈ስማቸውን ሊቀ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ያወጣላቸው፤

◈በአክናፈ መባርቅት ተጭነው የሚጓዙ፤
◈60 አናብስትና 60አናብርት ይታዘዙላቸው የነበሩ፤ የእግራቸው ትቢያ ለአራዊቶቹ ምግብ የኾነላቸው፤

◈ ለብዙ አእላፍ ቅዱሳን ወላዴ የኾኑና በረከትን የሰጡ ታላቅ አባት (ለአብነትም፤ ለቅዱስ #ላሊበላ፥ ለአቡነ #ሳሙኤል ዘዋልድባ፥ ለአባ #አንበስ ዘደብረ ሐዘሎ፥ ለአባ ብንያም ዘግብፅ)

#ምድረ_ከብድ_እና_ዝቋላ

#ምድረ_ከብድ ወደ ኢትዮጵያ ሲመጡ ለመጀመሪያ ጊዜ ያረፉባት ቦታ ናት፤ ቀጥሎ ወደ ደብር ቅዱስ #ዝቋላ (#ዝ_ቆላ) ለጸሎት ሂደው ለሃገራችን ኢትዮጵያና ለዓለማችን ምሕረትና በረከትን ከአምላካችን #ለ100 ዓመታት በባሕር ውስጥ ሆነው ለምነዋል፤

#ወደ ምድረ ከብድ ተመልሰው ለ7 ዓመታት ጸልየዋል፤ ቊራም በሰይጣን ተመስሎ መጥቶ ዓይናቸውም ቢያጠፋውም ከ7 ሱባዔያት በኋላ ሊቀ መላእክት ሚካኤልና ገብርኤል ዓይናቸውን መልሰውላቸዋል፡፡

ወደ ዝቋላ በመመለስም አጋንንትም ከምድረ ዝቋላ አጥፍተዋል፤

እንደገና ወደ ምድረ ከብድ ተመልሰው በነበሩበት ጊዜ ታላላቆቹና በአንበሳ ዘባን ላይ የሚሄዱት #አቡነ_ሳሙኤል_ዘዋልድባ ፣ #አባ_አንበስ_ዘደብረ_ሐዘሎ_አፋር)፣ #አባ_ብንያም_ዘግብፅ ከአባታችን ቡራኬ ለመቀበል መጡ አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ ተሰውረው ነበርና፤ የአቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ አናብስት የ3ቱን አባቶች አናብስት በሉባቸው፤ በ7ኛው ቀን አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ ተገልጠው የኾነውን ነገር በማየት የተበሉትን አናብስት እንዲመልሱ የራሳቸውን አናብስት አዘዟቸው መልሰውም እንደነበሩ በተዓምራት አስነስተው ሰጧቸው፤ በደመና ጠቅሰው ቅዱስ ፋኑኤል 3ት ሰማያዊ ኅብስትና 3ት ጽዋዕ ይዞ ለእንግዶቻቸው ይዘው ሠረገላ በሚባለው ዋሻ አመጡላቸውና ሰጥተው ሸኟቸው፤ እነዚህን ቅዱሳን በሸኙ በ7ኛው ቀን ወደ ተለያዩ ሃገራት ሄደው አስተምረዋል፡፡

፠ ቅዱሱ ንጉሥ አፄ ላሊበላን ጨምሮ ሌሎችም ቅዱሳን ወደ ርሳቸው እየመጡ በረከትን ተቀብለዋል፡፡
፠#በግብፅ_300_ዓመታት_፥ #በኢትዮጵያ_ምድር_ላይ_262_ዓመታት (በዋነኛነት #በምድረ_ከብድና_በዝቋላ_ ቢኖሩም ሌሎችም የመሠረቷቸውና የኖሩባቸው ገዳማት አሉ፤ ለአብነትም ደቡብ ወሎ የሚገኘውን #ገዘዛ_አቦን_ መጥቀስ ይቻላል)
፠ በድምሩ 562 ዓመታት ከኖሩ በኋላ በንጉሥ ሕዝብናኝ(እንድርያስ) ዘመነ መንግሥት፤ መጋቢት 5 ቀን ቅዳሜ ለእሑድ አጥቢያ ብዙ ቃል ኪዳንን ጌታችን ሰጣቸው፥ 12 አክሊላትንም አቀዳጃቸው፤ የነበሩባት ምድረ ከብድ ገዳም ግን ራደች፥
ተንቀጠቀጠች፥ በብርሃንም ተጥለቀለች፤ ዝቅ እያለችም መንሸራተት ጀመረች፤ ጌታችንም አንቺ መሬት ሆይ ጽኚ ይህንን ኹሉ ስለቻልሽ ምድር ክቡድ /ኋላ ምድረ ከብድ/ ተብለሽ ተጠሪ አላት፤ የጻድቁም ነፍስ ከሥጋቸው ከሌሊቱ 6 ሰዓት ተለየች፡፡

፠ ይህችውም ምድረ ከብድ ጻድቁ የኖሩባትና የቀደሱባት፥ የመሠረቷትና ያነፅዋት፣ ሠራዊተ መላአክት የከተሙባት፣ ታላላቅ አበው መጥተው በረከት ከአባታችን የተቀበሉባት፣ አርምሞና ጸጥታ የማይለያት፤ አጸዷና ቅጥሯ ልቡናን የሚመስጥ፤ ከአ.አ 125 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የምትገኝ ናት፡፡

የጻድቁ አባታችን ረድኤት በረከታቸው አይለየን።
----------------------------------------------------
|ፍኖተ_ሰላም_ሚዲያ
ጥቅምት-5/2017ዓ.ም

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

14 Oct, 18:31


#የመረጃ_ሰዓት
--------------------------
“አሁን ባለን የአስተዳደር ክፍተቶችና በውስጣችን ያሉ ግልጽነት የጎደላቸው አሠራሮች ለአገልግሎታችን እንቅፋት እየሆኑብን ነው”ሲሉ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ገለጹ፡፡

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት 43ኛው ዓለም አቀፍ መደበኛ አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ መክፈቻ መርሐ ግብር ላይ ባስተላለፉት መልእክት ቤተ ክርሰቲያን በውስጥና በውጭ በብዙ ችግር ተወጥራ የሰበካ ጉባኤ ግቡን አሳክቷል ማለት አንችልም ብለዋል፡፡

ቅዱስነታቸው አክለውም በዚህ ጉባኤ በቤተ ክርስቲያናችን የሚታየውን ችግር ለመፍታት በጥናት ላይ የተመሠረተ መፍትሔ ማምጣት ይገባል ሲሉ አፅዕኖት ሰጥተዋል፡፡

ኦርቶዶክሳውያን በየአቅጣጫው እየተገደሉ ነው ያሉት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ ይህ ግድያና ሰቆቃ ቤተ ክርስቲያን አሁንም በትልቅ ችግር ውስጥ መሆኗን ያሳያል ሲሉ ገልጸዋል፡፡

|ፍኖተ ሰላም ሚዲያ
ጥቅምት 04/2017 ዓ.ም

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

14 Oct, 16:50


በሀገር አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ውጤት ያመጡ ተማሪዎች ተሸለሙ።

ማኅበረ ቅዱሳን ከሰ/ት/ቤቶች ጋር በመተባበር በተለያዩ ቦታዎች ሲያስተምራቸው የነበሩ እና በ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተናን ለተፈተኑ ተማሪዎች ጥቅምት 3 ቀን 2016 ዓ.ም የሽኝት መርሐ ግብር ተከናውኗል።

በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል አዳራሽ በተከናወነው የሽኝት መርሐ ግብር ላይ ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርስቲ ፕሬዝዳንት እና የደቡብ ኦሞና አሪ ዞኖች ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እና በ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተናን የወሰዱ ተማሪዎች ተገኝተዋል።

ብፁዕነታቸው በተሰጠው ሀገር አቀፍ ፈተና ከፍተኛ ውጤት ላመጡት ተማሪ ዮናስ ንጉሠ እና ተማሪ ሄለን በርሀ የተዘጋጀውን የላፕቶፕ ኮምፒዩተር ሥጦታ ያበረከቱ ሲሆን በመርሐ ግብሩ ላይ ለተገኙት ተማሪዎችም አባታዊ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።

ተማሪ ዮናስ ንጉሠ ከ700 ጥያቄዎች 675 በመመለስ ከወንድ ተፈታኞች መካከል አንደኛ እንዲሁም ተማሪ ሄለን በርሀ ከ700 ጥያቄዎች 662 በመመለስ ከሴት ተፈታኞች መካከል አንደኛ መውጣታቸው ያታወቃል።

ፍኖተ ሰላም ሚዲያ
--------------------------
ጥቅምት 04/2017 ዓ.ም

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

13 Oct, 19:57


የፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት ጠቅላላ ጉባኤ ሰንበት ትምህርት ቤቱን በሥራ አስፈጻሚነት የሚመሩ አባላትን መረጠ።
-----------------------------------------
የፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት ጠቅላላ ጉባኤ ሰንበት ትምህርት ቤቱን ለቀጣይ 3 ዓመታት በሥራ አስፈጻሚነት የሚመሩ አባላትን ዛሬ ጥቅምት 3/2017 ዓ.ም ባካሄደው ጉባኤ የካቴድራላችን አስተዳዳሪ ክቡር መልአከ ብርሃን ቀሲስ ገ/ኢየሱስ ስዩም ፣የሰበካ ጉባኤ አባላት በክብር እንግድነት በተገኙበት የሰንበት ት/ቤቱ የሥራ አመራር የምርጫ ሂደቱን እያስፈጸመ መርጧል።

በዚህም እጩ መጠቁም ሂደት  ውስጥ 40 የሚሆን አባላት የተጠቆሙ ሲሆን የሥራ አመራሩ መስፈርቱን አሟልተዋል ያላቸውን 20 እጩዎቸን ለይቶ ለጠቅላላ ጉባኤ ያቀረበ ሲሆን ጉባኤውም በእጩነት የቀረቡለትን አባላት ላይ ከተወያየ በኋላ ጸሎት ተደርጎ ወደ እጣ ማውጣቱ ተገብቷል በዚህም
14 አባላትን (3 የጽ/ቤት ፣1 የኦዲት እና ኢንስፔክሽን ኃላፊ እና 10 የአገልግሎት ክፍላት ኃላፊዎችን መርጦ አጽድቋል።
-------------------
1. አቶ አብርሐም ንጉሴ
  👉 የሰንበት ት/ቤቱ ሰብሳቢ

2.ወጣት ሀብታሙ ሳህሉ
  👉 የሰንበት ት/ቤቱ ም/ ሰብሳቢ

3.ወጣት ምሕረት አየለ
  👉 የሰንበት ት/ቤቱ ጸሐፊ

4. ትምህርት ክፍል
  👉መ/ር ታሪኩ ተካ

5. ሕዝብ ግንኙነት ክፍል
  👉ወጣት ሄኖክ ፍርዴ

6. መዝሙርና ኪነ ጥበብ
👉ዲ/ን ሱራፌል ግዛው

7. ሥልጠና ክፍል
👉ወጣት ምትኩ አጀማ

8. ሙያ አገልግሎት ክፍል
👉ወጣት ሐዊ ደራራ

9.ጥናት እና እቅድ ክፍል
👉 ወጣት ሩት አማረ

10.አባላት ጉዳይ ክፍል
👉ዲ/ን ኪሩቤል አበራ

11.ልማት ክፍል
👉ወጣት ኢየሩሳሌም ወርቁ

12.ጎልማሶችና ማኅበራት ማስተባበሪያ ክፍል
👉ወጣት ገመቹ ተፈራ

13.ሒሳብና ንብረት ክፍል
👉 ዲ/ን ኤርሚያስ መስቀሉ

እንዲሁም የሰንበት ትምህርት ቤቱ ኦዲትና ኢንስፔክሽን ክፍል ኃላፊ
#ወጣት ዘለዓለም አያሌው ሆነው ተመርጠዋል።
------------------------------------
ስለሁሉም ነገር እግዚአብሔር ይመስገን
ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን።

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

13 Oct, 19:57


የፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት ጠቅላላ ጉባኤ ሰንበት ትምህርት ቤቱን በሥራ አስፈጻሚነት የሚመሩ አባላትን መረጠ።

የቡራዩ ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ሰላም ሰንበት ት/ቤት

12 Oct, 20:01


የጠቅላላ ጉባኤ ጥሪ
------------------------------
#1ቀን ቀረው የፍኖተ ሰላም ሰንበት ትምህርት ቤት
የሥራ አስፈጻሚ ጉባኤ አባላት ምርጫ ነገ ጥቅምት 3 ይካሄዳል።

👉በእለቱ ተገኝታችሁ በመምረጥ የአባልነት መብት እና ግዴታዎን ይወጡ!

|ፍኖተ ሰላም ሰንበት ትምህርት ቤት
ጠቅላላ ጉባኤ

1,434

subscribers

4,275

photos

86

videos