መልካም ወጣት @excellent_youth Channel on Telegram

መልካም ወጣት

@excellent_youth


ዓላማችን ወጣቱን ትውልድ የተቀደሰ እና ለእግዚአብሔር የተለየ ማድረግ ነው።

በቻናሉ ውስጥ መንፈሳዊ ትምህርቶች፤ አነቃቂ ጽሑፎች፤ ግጥሞችና የተመራረጡ መዝሙሮች ይገኛሉ። እኛ ለመስራት እንነሳ እንጂ ጌታ ሁሌም ይረዳናል!

መልካም ወጣት (Amharic)

መልካም ወጣት በአማርኛ እየተገናኘ እና የሚቀጥለውን ስምምነት ማስተማር ነው። አሁንም ባለፈው ውጤት በተጨማሪ መንፈሳዊ ትምህርቶች፤ አነቃቂ ጽሑፎች፤ ግጥሞችና የተመራረጡ መዝሙሮች ላይ እና የስሜቶችን ለሚፈጽሙ የምስጋና ትምህርቶች የተሻለ ነው። መልካም ወጣት በቻናሉ መሆኑን እና እኛው በእርስዎ ላይ በመስክ ላይበሚገኙት ጽሑፎች እና የተሻለ መዝሙሮች በመከታተል እኛ ከፈጠራችን ፈለግን የቻናሉ ወጣቱን የመንፈሳዌት ይሆናል።

መልካም ወጣት

11 Feb, 18:57


🗞ይገርማል

ዕዳ የተሻረለት ሎሌ ፤
ምነው ዕዳ ይጠይቃል።
ቀንበር ያነሱለት በሬ ፤
እንዴት ቀንበር ይናፍቃል።
ባለወተት የማር ምድር ፤
እየሸተተን መሃዛው፤
የግብፅ ባርነት ሽንኩርት ፤
እንዴት ቀልባችንን ገዛው።

ይገርማል...
የሞተን እባብ ቢቀብሩት
እንደሚቆም አፈር ልሶ፤
አንገታችን ምነው ቀረ
እንደ ሎጥ ሚስት ተመልሶ።

ክብር የተረፈው አምላክ
ለሱ ክብር ቢያስለቅቀን፤
ምነው በጣዖት ቀየርነው
የሰጠንን ወርቅ አድቅቀን።
ያለውን ለሰጠን ወዳጅ
ለምን ትራፊ እንሰጣለን፤
ጊዜ ላይ ላቆመን አምላክ
እንዴት ጊዜን እናጣለን።

እጦት ሲዘን ከእግሮቹ ስር
ቀንም ሌትም እንዳለፋን፤
ቤታችንን ሲጎበኘው
ምነው ከቤቱ ደጅ ጠፋን

እባካችሁ ..!
የአዳም እና ኤዋን ጥፋት ፤
በኛም ዘመን ሳይሠለስ
በእርሱ መንገድ ብቻ እንጓዝ ፤
ከራስ መንገድ እንመለስ
ይብቃን ይብቃን የራስ ተስፋ፤
የራስ ባህር፣ የራስ መረብ
በጉድለት መባዘን ይብቃን ፤
ወደ ሙላቱ እንቅረብ
ሙሉ እንጀራ አይጋግርም ፤
ሰባራ የሸክላ ምጣድ
ክርስቲያን ፍቃዱን እንጂ ፤
አይኖርም የራሱን ፍቃድ።

የሱመልስ

      @Excellent_youth
      @Excellent_youth

መልካም ወጣት

07 Jan, 19:17


ልደተ እግዚእ! { የጌታ ልደት! }

አምላክ በሚያስደንቅ ትሕትና ሰው ሆነ። በእግዚአብሔር መልክ የሚኖረው የሁሉ ጌታ ዛሬ የባርያን መልክ ያዘ።

አዳምን ከምድር አፈር ያበጀው ያ አምላክ ዛሬ በትሕትና ያንን ሥጋ ለበሰ የሰማይን ጣራ ያለ ካስማ የወጠራት ይህ አምላክ ዛሬ በበረት ጣራ ስር በሥጋ ተኛ! ምድርን ያለ ሸማ የዘረጋት ሕያው ጌታ ዛሬ ሰው በማይኖርባት በከብቶች በረት በትሕትና ተገኘ።

የኪሩቤል ጀርባ ዙፋን የሆነለት አምላክ ዛሬ ሣር ቅጠል ላይ በግርግም ተኛ።

የተዋረድነውን እኛን ሊያከብር አምላክ ሰው ሆነ።

እንኳን ለጌታችን ለመዳንታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!

      @Excellent_youth
      @Excellent_youth

መልካም ወጣት

07 Jan, 19:08


እንኳን አደረሳችሁ!

በረት ሳይንቅ፣ ቤተልሄምን ሳይጠየፍ፣ ናዝሬትን ጀርባ ሳይሰጥ የተወለደው የናዝሬቱ ኢየሱስ ሕይወታችንን ሳንጠየፍ በፍቅር ይወለድበት።

የዓለምን ታሪክ ለሁለት የከፈለ የምህረት ዓመትን ያወጀ ጌታ በሕይወታችን ውስጥ የምስራች የሆነውን ምህረቱን ያውጅበት።

ሊኖር ሳይሆን ሊሞት ተወልዷልና ለእርሱ ኖረን የምናልፍበትን ጸጋና አቅም ይስጠን።

ለዓለም ሰላምን ሊሰጥ እንደመጣ ዛሬ በቤታችሁ አዕምሮን የሚያልፈውን ሰላሙን ይስጣችሁ፣ የማይነጥፍ ፍቅሩን ያድላችሁ።

በመወለዱ የምስራች እንደሰማን ምስራችን ስሙ። ልባችሁን ደስ ያሰኛችሁ። መልካም በዓል። እወዳችኃለሁ።

አዶኒ

      @Excellent_youth
      @Excellent_youth

መልካም ወጣት

01 Jan, 19:16


May you experience God’s grace in abundance and may your faith deepen as you journey through this year. a year filled with joy, purpose and divine blessings!

"May the Lord bless you and keep you; the Lord make his face shine on you and be gracious to you; the Lord turn his face toward you and give you peace."  
    - Numbers 6:24-26


HNY 2025!

መልካም ወጣት

01 Jan, 19:01


Happy New Year Excellent youth family! The help of God's blessing and mercy we enter the New Year! it's a wonderful time to reflect on renewal, hope and God's promises.

▎1. Renewal and Transformation

Embrace the new beginnings that God offers. May this year bring you renewal and transformation in Christ.

"Therefore, if anyone is in Christ, he is a new creation. The old has passed away; behold, the new has come." -2 Corinthians 5:17

▎2. Hope and Future

Trust in God's plan for your life. May you find hope and assurance in God's plans for you this year.

"For I know the plans I have for you, declares the Lord, plans to prosper you and not to harm you, plans to give you hope and a future."
- Jeremiah 29:11

▎3. Strength and Courage

Rely on God's strength in all situations. May you be filled with strength and courage as you face the challenges of the new year.

" I can do all things through him who strengthens me." - Philippians 4:13

▎4. Peace and Joy

Seek God’s peace and joy in your life. May this year overflow with God’s peace and joy in your heart.

"The Lord bless you and keep you; the Lord make his face shine on you and be gracious to you." - Numbers 6:24-25

▎5. Faithfulness

Commit your plans to the Lord. May you seek God’s guidance and faithfulness in every step you take this year.

"Commit your work to the Lord, and your plans will be established." - Proverbs 16:3

▎Closing Prayer

May this New Year be filled with blessings, joy, and a deeper relationship with God as we walk in His light and truth.

HAPPY NEW YEAR! 2025G.C

@Excellent_youth
@Excellent_youth

መልካም ወጣት

28 Dec, 20:27


ማንነት ሲጨመቅ!

“ሎሚ ትክክለኛ ማንነቱ እና መራራው ጣእሙ የሚወጣው ሲጨመቅ ነው” ይባላል፡፡

የሚያጋጥማችሁ ነገርና የምትገቡበት ሁኔታ የውስጥ ማንነታችሁን ያወጣዋል እንጂ የሌላችሁን ማንነት አይሰጣችሁም፡፡

የማንነት ለውጥ ሆን ተብሎ ተሰርቶበት የሚመጣ ነገር ነው፡፡

ለምሳሌ . . .

•  ገንዘብ ማግኘት ለጋስም ስግብግብም አያደርገንም፣ በውስጣችን የነበረውን ለጋስነት ወይም ስግብግብነት እድል ሰጥቶ ነው የሚያወጣው፡፡

•  ማሕበራዊ ሚዲያ የመጠቀም መድረክ አስተማሪም ተሳዳቢም አያደርገንም፣ በውስጣችን የነበረውን አስተማሪነት ወይም ተሳዳቢነት እድል ሰጥቶ ነው የሚያወጣው፡፡

•  በሰው መተው እና ብቻ መሆን ጠንካራም መራራም አያደርገንም፣ በውስጣችን የነበረውን ጠንካራን ወይም መራራነት እድል ሰጥቶ ነው የሚያወጣው፡፡

•  ስልጣን ማግኘት ትሁትና ሰው ጠቃሚም ሙሰኛና በሰው ተጠቃሚ አያደርገንም፣ በውስጣችን የነበረውን ጠቃሚነት ወይም ጥቅመኛነት እድል ሰጥቶ ነው የሚያወጣው፡፡

ምንም አይነት ነገር ከማግኘታችሁና የትኛውም ሁኔታ ውስጥ ከመግባችሁ በፊት ራሳችሁን ፈትሹ፣ ራሳችሁ ላይ ስሩ!

ራስ ላይ መስራት ማለት . . . 

1.  ጨዋ የሆነ፣ የከበረ እና ለሕብረተሰቡ የሚጠቅምን ዓላማ መያዝ

2.  ለዚያ የከበረ ዓላማ የሚጥን ባህሪይ ላይ መስራት

3.  ለዚያ ዓላማ የሚመጥን ዲሲፕሊን ማዳበር
ማለት ነው፡፡

ኢዮብ ማሞ

      @Excellent_youth
      @Excellent_youth

መልካም ወጣት

15 Nov, 03:38


እንኳን በሕይወት ነቃችሁ!

በሰላም ስላደራችሁ ደስ ይበላችሁ!

በዓለም ላይ በቀን ወደ አንድ መቶ ሺህ (100 ሺህ) አካባቢ አይሮፕላኖች እየተነሱ በሰላም ያሰቡበት በመድረስ ያርፋሉ፡፡ ከእነዚህ በረራዎች መካከል ግን የአንዱም እንኳን በሰላም መግባት በዜናዎች ላይ ሲነገር አንሰማም፡፡ ሆኖም፣ አንድ በረራ ላይ አደጋ ከደረሰ ግን ትኩረት ይስባል፣ ዜናውን ይሞላዋል፣ ወሬው ይሸጣል፡፡  

የአንድ ጤናማ ሰው ልብም ቢሆን በቀን ወደ አንድ መቶ ሺህ (100 ሺህ) አካባቢ ይመታል፡፡ ይህንን ያህል ጠንክሮ የሚሰራው አካላችን ግን በቀን ውስጥ ትዝም አይለን፡፡ የምናስታውሰው መምታት ለማቆም ሲዳዳውና የምቱ ድግግሞሽ ሲለይብን ነው፡፡ ለምን? መልካሙ ነገር ተለምዷል፡፡ የምስራች የሆነው ነገር ትዝም አይለን፡፡ 

ዛሬ መልካም መልካሙን ላስታውሳችሁ፡፡ ዛሬ የምስራቹ ትዝ ይበላችሁ፡፡ በሰላም የመንቃታችሁ ጉዳይ፣ በሌሎች ላይ የደረሰ እናንተ ላይ ያለመድረሱ ጉዳይ፣ የደረሰባችሁ ነገር ከዚህ የከፋ ያለመሆኑ ጉዳይ . . . ትዝ ይበላችሁ፡፡

ከደረሰብን ክፉ ነገር የሆነልን መልካም ነገር ይበዛልና ደስ ይበላችሁ፡፡

ፈጣሪን አመስግኑ! ቤተሰቦቻችሁን፣ ጓደኞቻችሁንና በሕይወታችሁ ላይ መልካም ተጽእኖ ያደረጉ ሰዎችን አድንቁ!

መልካም ቀን!

ኢዮብ ማሞ

      @Excellent_youth
      @Excellent_youth

መልካም ወጣት

13 Nov, 03:29


በማለዳ - Hanna Tekle

መልካም ወጣት

13 Nov, 03:29


ሳበኝ - Selam Desta

መልካም ወጣት

31 Oct, 19:50


ላልተጠበቀው ነገር መዘጋጀት

ሁል ጊዜ አንድን ነገር ስትጀምሩ በመንገድህ ላይ ያልተጠበቀ ነገር እንደሚገጥማችሁ አትዘንጉ፡፡ እነዚህ የማትጠብቋቸው ነገሮች አብዛኛዎቹ ምንጫቸው ከእናንተ ቁጥጥር ውጪ የሆኑ ነገሮች ናቸው፡፡ ሊገመት የማይችል የሁኔታዎች መለዋወጥ፣ ሊተነበይ የማይችል የሰዎች ባህሪይ መቀያየርና የመሳሰሉት ሁኔታዎች ከመንገዳችሁ ላይ እንቅፋት እንዳይጠፋ ያደርጉታል፡፡

እነዚህ ሁኔታዎች አንድን ነገር ለመጀመር፣ ከጀመርን በኋለ ለመቀጠል፣ አልፎም ወደፍጻሜ ስንደርስ እንዳንጨርስ ሲጋረጡብን እናገኛቸዋለን፡፡ ይህንን አይነቱን የማይቀር የሕይወት ሂደት የተለያዩ ሰዎች በተለያየ መልኩ ምላሽ ይሰጣሉ፡፡ አንዳንዶች ለደረሰብን እንቅፋት ሁሉ በሰዎች፣ በሁኔታዎችና በፈጣሪ የማማረር ልማድ አለብን፡፡ በዚያም ሁኔታ ተደብቀን በተስፋ መቁረጥ እርምጃችንን እንተዋለን ወይም ለሌላ ጊዜ እናስተላልፈዋለን፡፡

ሶስት አይነት እንቅፋቶች አሉ . . .

1. አንዳንዱ እንቅፋቶች ቀድሞውን ሊደርሱ የሚችሉ እንቅፋቶችን በማጤንና በማቀድ ልታስወግዷቸው የምትችሏቸው ናቸው፡፡

2. ሌሎቹ እንቅፋቶች አስቀድማችሁ አቀዳችሁም አላቀዳችሁም ከመምጣት የማታስወግዷቸው እንቅፋቶችና እንደአመጣጣቸው ልትመልሷቸው የምትችሏቸው ናቸው፡፡

3. ሌሎቹ ግን እንቀፋቱና ችግሩ እያለ መንገዳችሁ ላይ ብቻ በማተኮር ወደፊት ልትቀጥሉ የሚገባችሁ አይነት እንቅፋቶች ናቸው፡፡

ከላይ በተጠቀሱት የእንቅፋት አይነቶች መካከል የመለየታችሁ አስፈላጊነት እንደተጠበቀ ሆኖ፣ በተጨማሪ እነዚህን አትርሱ፡-

1. ሁል ጊዜ አንድ ነገር ለመጀመር እቅድ ሰታወጡ በእቅዳችሁ ውስጥ ለድንገተኛውና ላልተጠበቀው እንቅፋት ማቀድን አትርሱ፡፡

2. ያልተጠበቀና ድንገተኛ እንቅፋት ሲያጋጥማችሁ ትክክለኛውን ምላሽ በመምረጥ ምላሽን ለመስጠት ሞክሩ፡፡

3. አንድ እንቅፋት ካጋጠማችሁና አስፈላጊውን ምላሽ ከሰጣችሁ በኋላ ወደ ዓላማችሁና ወደስራችሁ በመመለስ እሱ ላይ ማተኮርን አትርሱ፡፡

ኢዮብ ማሞ

@Excellent_youth
@Excellent_youth

መልካም ወጣት

11 Sep, 05:23


ሰላም የተወደዳችሁ የመልካም ወጣት ቤተሰቦች እንኳን ለአዲሱ ዓመት በሰላም አደረሳችሁ።

ዘመን ተጨመረልን፤ እድሜ ተጨመረልን አዲስ ቀን፤ አዲስ ማለዳ ተጀመረልን እግዚአብሔር ይመስገን።

አዲሱ ዓመት የሰላም፤ የፍቅር፤ የጤና እንዲሁም ይበልጥ ከእግዚአብሔር ጋር የምንጠጋበት፤ ጸሎታችንን እድገት የሚያገኝበት፤ ብዙ ፍሬ የሚናፈራበት ዓመት ይሁንልን።

መልካም አዲስ ዓመት ይሁንላችሁ

      🌻🌼 @Excellent_youth 🌼🌻
      🌻🌼 @Excellent_youth 🌼🌻

መልካም ወጣት

14 Aug, 18:59


አገኘሁ ይደግ አይለወጥም የምል መዝሙር ነው ተባረኩበት

መልካም ወጣት

14 Aug, 18:58


አቤት ጌታ ባለመላ - አገኘሁ ይደግ

መልካም ወጣት

08 Aug, 19:57


ደሙ እንደ ውሃ - አስቴር ተፈራ

መልካም ወጣት

08 Aug, 19:56


ሙሉ መዝሙሩ ይኸው ተባረኩበት

መልካም ወጣት

29 Jul, 19:32


📜እንግዳዬ

በቀኔ ጅማሬ ላገኝህ ቀጥሬ
ሳስውብ ሳሰናዳ ራሴን አሳምሬ

በቀጠርኩህ በቀጠርከኝ
አንተን ማየት ሲናፍቀኝ

ኩሌን አየተኳልኩ ቀሚሴን ለብሼ
እግሮቼን ታጥቤ እድፌን ቀንሼ

በር በር አያየሁ  ስጠብቅ እንግዳ
ድምፅህን ለመስማት ጆሮዬን ሳሰናዳ
        እየጠበኩህ.....
አይኔ ሲንከራተት ማማተር ሲደክመኝ
ሰዓቱ ሲያልፍብኝ የቀረህ ሲመስለኝ

የተዋበው ቤቴ መዝረከረክ ጀመረ
አንድ ሁለት እያለ በእድፍ ተወረረ
  
ሰለቸኝ ደከመኝ እኔው አቅም አጣሁ
እስክትመጣ ብዬ አልጋዬ ላይ ወጣሁ
        እየጠበኩህ.....
ያጋደልኩት ጀርባ ያሳረፍኩት ጎኔ
ማሸለብ ሲጀምር ተንከራታች አይኔ

ሳላስብ በድንገት ተንኳኳ መዝጊያየዬ
ከደጃፌ ቆሞ ጠራኝ እንግዳዬ

ልቤ ንቁ ሆኖ ሰውነቴ ደክሟል
ቀኔ ተገባድዶ ወደማለቅ ቀርቧል

እግሬ ይቆሽሻል ከወረድኩ ከአልጋዬ
ቀሚሴን አውልቄ ተራቁቷል ገላዬ
      እንዴት ልውረድ?....

ግን እርሱ አሁንም ከበራፌ ቆሟል
ድምፁን አያሰማኝ እንድከፍት ያንኳኳል

ብዙ አቆይቼው .....
በሀሳብ ስታገል ከበሬ አቁሜው...

እንደምንም ብዬ ለመክፈት ስማቅቅ
መንኳኳቱ ቆሟል ውዴም ብሏል ፈቀቅ
         አመለጠኝ.....
ናፍቆቴን እንዳላይ ስንፍናዬ ያዘኝ
        ስፈልግ አጣሁት...
በሬን እየዘጋሁ ሲጠራኝ ገፋሁት

እንግዳዬ እያልኩ ብዙ እቆጥረዋለሁ
ሲመጣ ግን መልሴ እንዴት እወርዳለሁ ?...

ነፃነት አናቶ

@Excellent_youth
@Excellent_youth

መልካም ወጣት

23 Jul, 18:40


📜አንዳንድ ወዳጅማ

ወዳጅ መስሎ ቀርቦ፣ ሀሳብን ጠይቆ
ማብዛት መሰናክል፣ እንዳትጓዝ ርቆ
ለራስ ጥቅም ብሎ፣ ሌላን ማሰናከል
እይታውን ጋርዶ፣ እይታን መከለል

ልብን የምያየውን፣ አምላክን ማይፈራ
አፈሙዝ አዙሮ፣ የሚሸርብ ሴራ
ያስደሰተ መስሎ፣ ምያበስር ምሥራች
ከላይ ሀውልት ሰርቶ፣ መቃብር ሥር ከታች

በልቡ ገንዞ፣ ይመስላል አፍቃሪ
የሰው ልብ አስይዞ፣ ህይወት ላይ ቆማሪ
ለጥቅሙ ይቀርባል፣ አይቆይም ይሄዳል
እሱን ሸኘሁ ስትል፣ ሌላኛው ይመጣል

በዝህም አያቆምም፣ ህይወት ይቀጥላል
እኔ ያገኘኝ ፍቅር፣ ከዚኛው ይለያል

ወዳጅ ሆኖ መቶ፣ የሚሆነኝ ወዳጅ
በፍቅሩ ጠፍሮ፣ ጠላትን አናዳጅ
ከቶ የማይለየው፣ ኤኬለን ከኤኬሌ
ማስመሰል የሌለው፣ የፍቅር ምሳሌ

ህይወትን የሰጠኝ፣ ሞቴን ተቀብሎ
ፍጹም ያልቀረበኝ፣ ለጥቅሙ ብሎ
ጠላትነት ልያስቀር፣ ልያስታርቀን ከአብ
ሰማያዊ ዜጋ፣ እኛን ልያደርግ ስያስብ

XY ከሚባል፣ የባዮሎጂ ጣጣ
ቁርኝት ሳይፈጥር፣ ወልድ ወደኛ መጣ

የማሪያም ልጅ እሱ፣ መንፈስ የፀለለው
ስሙም ድንቅ መካር፣ ቃላት የማይገልፀው
በእውነተኛ ፍቅር፣ ልጆቹን የሚወድ
ነገስታትን ሿሚ፣ በረት የሚወለድ

እውነተኛ ፍቅር፣ እራስን ያሰጣል
ከሰው ፍቅር ይልቅ፣ የኢየሱስ ይበልጣል።

ዳዊት ማዕረጉ

@Excellent_youth
@Excellent_youth

መልካም ወጣት

21 Jul, 19:00


📚ምክንያተ ብዙ...

ምሳሌ 6
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁶ አንተ ታካች፥ ወደ ገብረ ጕንዳን ሂድ፥ መንገድዋንም ተመልክተህ ጠቢብ ሁን።
⁷ አለቃና አዛዥ ገዢም ሳይኖራት፤
⁸ መብልዋን በበጋ ታሰናዳለች፥ መኖዋንም በመከር ትሰበስባለች።

አንድን ቤት ውስጥ የምታገለግልን ሴት ባለቤቱ ይመጣና "ምግብ አለ ወይ?" ይላታል እርሷም "መብራት ጠፍቶ አልሰራሁም" ትላለች። ባለቤቱም "በከሰልስ አትሰሪም ነበር ወይ" ቢላት ባለሱቁ ከሰል ጨርሶ ነበርና አልገዛሁም ትላለች... ምክንያቷ ከመብዛቱ የተነሳና ከስንፍናዋ ትልቅነት የተነሳ እርሷን አባሮ እራሱ ሰርቶ በልቶ ጠገበ።

ትጉ ሰው ጊዜውን፣ ሀብቱን እና ጉልበቱን በሚገባ የሚጠቀም ሰው ነው። ማለትም የሚተጋበት ሰአት ላይ የሚተኛ፤ የሚተኛበት ሰአት ላይ የሚተጋ ሰው አይደለም። ጊዜውን በሚገባ የተረዳ እና ያለውን አጋጣሚዎች ውጤት ሊያመጣ በሚችል መልኩ ወደ ፍሬአማነት የሚቀይር ነው።

ጊዜውን ያላማከለ ትጋት ያለው ቁፋሮ የሚታይ ፍሬ የለውም!

መጽሐፍ ቅዱስ ወደ ገብረ ጉንዳን በመሄድ ምክርን እንድንወስድ ይነግረናል። ጉንዳን ከእንስሳት ውስጥ የትጋት ምሳሌ የሆነ ሲሆን ነገር ግን ምክንያት መደርደር ቢፈልጉ ኖሮ ሊደረድሩአቸው የሚችሉባቸው ብዙ አሳማኝ ምክንያቶች ነበሩአቸው። ይህንን ምክንያት ግን አሸንፈው በስኬት ይኖራሉ።

ለምሳሌ ምክንያት ሊደረድሩ የሚችሉበትን ነገር ብንመለከት፤ አለቃ ገዢና አዛዥ የለንም፣ የመሸከም አቅም የለንም፣ በቀላሉ ውሃ እና የተለያዩ ነገሮች እንጎዳለን በማለት ለመስነፍ ምክንያት መስጠት ይችሉ ነበር።

ትጉ ሰው ግን ሁልጊዜ ምክንያት ከመደርደር ይልቅ መስራት እና መፈጸም ያለባቸውን ነገሮች ይፈጽማሉ። ሰነፎች ግን ስንፍናቸው ስንፍና በመሆኑ ሕይወታቸውን ብቻ ሳይሆን አካባቢያቸው ያለውን ነገር ሁሉ በመከራ ይሞሉታል። ታዲያ ጠቢብ ነክቶ ሳይሆን ምክርን ተቀብሎ ይማራልና በሰነፍ ላይ የሚደርሰውን ውርደትና አደጋ ተመልክተን ዋጋ መክፈል ሳያግደን በትጋት እንገለጥ።

ተዘራ ያሬድ

      @Excellent_youth
      @Excellent_youth

መልካም ወጣት

10 Jul, 19:04


ሰው ብቸኝነት የሚሰማዉ ከሰው ሳይሆን ከእግዚአብሔር ሲርቅ ነው!

ከዚህ ውጪ ምንክያት እያሰብን እራሳችንን አናስጨንቅ እግዚአብሔር ኖሮ ሌላው ቢቀር ምንም አይደል በቃ REALITY ነው! ሰው ይመጣል ደግሞ ይሄዳል

ግን የእግዚአብሔርን ህልውና ያጣን ጊዜ በቃ ብቸኝነት ሚለውን ቃል ሚገልፅልን ሌላ ቃል ሁላ እናጣለን።

ስለዚህ ብቸኝነት ሲሰማን ሰው አጥቼ ነው፣ ሰው ርቆኝ ነው አንበል። ችግሩ በራቁን ወይ በራቅናቸው ሰዎች ምንክያት እነሱን በማሰብ ጊዜ በማጣት ውስጥ ሆነን ለእግዚአብሔር ሚገባውን ጊዜ ስለቀማነው እና እርሱ ካዘጋጀልን የማፅናናት ጉልበት ስለራቅን ነው ብቸኝነት ሚባለው ስሜት እኛ ላይ ሚሰለጥነው።

ስለዚህ የብቸኝነት ስሜት መነሻው ሰዎች አይደሉም ከእግዚአብሄር መራቅ እንጂ

ካሌብ

      @Excellent_youth
      @Excellent_youth

መልካም ወጣት

09 Jul, 08:51


ለ2ተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ተፈታኞች በሙሉ መልካም የፈተና ሣምንት ይሁንላችሁ !

We wish all the secondary school students a successful exam week!

መልካም ወጣት

25 Jun, 07:04


የማለዳ ስንቅ

     " የእግዚአብሔር በረከት ባለጠጋ ታደርጋለች፥ ኀዘንንም ከእርስዋ ጋር አይጨምርም። "ምሳሌ 10:22

በዚህ ክፍል ጠቢቡ ሰለሞን ስለ እግዚአብሔር በረከት ይናገራል ከእግዚአብሔር የምንቀበለው በረከት ባለጠጋ እንደሚያደርግ ሃዘንም እንደሌለበት ይናገራል ዛሬ እንዲህ ልመርቃችሁ፤

ሃዘን የሌለበት ባለጠግነት ፍጹምም የእግዚአብሔር በረከት ያግኛችሁ! ተባረኩ

      @Excellent_youth
      @Excellent_youth

መልካም ወጣት

13 Jun, 06:23


ያወራል ቀራኒዮ - Awtaru Kebede

መልካም ወጣት

09 May, 18:18


📚 ሦስት የሕይወት ትምህርቶች

1. አይበገሬነት

ኢየሱስ ክርስቶስ በሕይወት በነበረበት ጊዜ በስቅለትና ሞት የተረጋገጠ እጅግ ብዙ ተቃውሞና ስቃይን አሳልፏል። ነገር ግን ተስፋ አልቆረጠም፤ ከዛ ይልቅ እጅግ አስደናቂ አይበገሬነትንና ቻይነትን በማሳየት ለድል በቅቷል፤ እሱም ትንሳኤው ነው።

ይህን ተማር
አንተም በሕይወት እጅግ ብዙ ፈተናዎችና ስቃዮች ይገጥሙሃል። በአቅምህ ተስፋ እንድትቆርጥና እምነት እንድታጣ የሚያበረታቱ ብዙ ተግዳሮቶች ይገጥሙሃል። ትንሳኤው ግን አይበገሬነት ለስኬት እጅግ አስፈላጊ እንደሆነ ያስታውስሃል!

2. መስዋዕትነት

ሌላኛው የትንሳኤው ወሳኝ ትምህርት መስዋዕትነት ነው። ክርስቶስ ለሌሎች ሲል የራሱን ሕይወት ለመስጠት ፈቅዷል። ምቾቱን፣ ደህንነቱንና ሰላሙን ሰውን ከኃጥያትና ሞት ለማዳን ሰውቷል።

ይህን ተማር
ስኬት መስዋዕትነት ይፈልጋል። የአጭር ጊዜ መሻትና ምኞት በላይ የረዥም ጊዜ እቅዳችንንና ዓላማችንን ማሰብ አለብን። ከግል ፍላጎት በላይ ሌሎችን ማስቀደም የሚያስፈልግበት ጊዜም አለ። ብዙ ጊዜ ሕመም ቢኖረው እንኳ ከባድ ውሳኔን መወሰን ይኖርብናል።

ትንሳኤው መስዋዕትነት የደካማነት ሳይሆን የሐቀኛ የመሪነት አቅም ምልክት እንደሆነ ይነግረናል።

3. ተስፋ

በመጨረሻም፣ ትንሳኤው ለሁሉም ሰዎች አስፈላጊ የሆነን መልእክት ይነግረናል። ክርስቶስ በመስቀል ላይ ተሰቅሎ ከሞተ በኋላ ተነስቷል፤ ይህም ከኃጢያትና ሞት በላይ ያለውን ስልጣን ያሳያል። ይህ ሁኔታ ትልቅ የተስፋ ምልክት ነው። በጨለማ ሁኔታ ውስጥ እንኳ ቢሆን የመታደስና የመዳን እድል እንዳለ ይነግረናል።

ይህን ተማር
ሕይወት እጅግ ፈተና የሞላበትና አሰልች ሊሆን ይችላል። ውድቀቶች፣ መገፋቶች፣ ወደ ኋላ መቅረቶች ይገጥሙናል። ይህም ተስፋ እንደሌለን እንዲሰማን ያደርገናል። ትንሳኤው ግን ሁልጊዜ ወደ ፊት የተሻለ እንደሚሆን ተስፋ እንድናደርግ ያስታውሰናል።

የተሰቀለው ንጉሥ መጽሐፍ

@Excellent_youth
      @Excellent_youth

መልካም ወጣት

05 May, 18:31


ተቀሰቀሰ || በረከት ተስፋዬ ልዩ የትንሳኤ መዝሙር

መልካም ወጣት

05 May, 04:21


በዘመናት መካከል ክንዱ የማይዝል፤ የፍጥረት ሁሉ አምላክ እና ጌታ የሆነው የናዝሬቱ ኢየሱስ ለሰው ልጆች ኃጢአት ሲል በመስቀል ላይ ሞተ፤ ነገር ግን እንደ ሰው ሞቶ አልቀርም ሞትን ድል አድርጎ ተነስቷል።

“ፈርተውም ፊታቸውን ወደ ምድር አቀርቅረው ሳሉ፥ እንዲህ አሉአቸው፦ ሕያውን ከሙታን መካከል ስለ ምን ትፈልጋላችሁ? ተነሥቶአል እንጂ በዚህ የለም።”
— ሉቃስ 24፥5

እንኳን ለመዳኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ

𝐇𝐀𝐏𝐏𝐘 𝐄𝐀𝐒𝐓𝐄𝐑
መልካም ፋሲካ

🎁 @Excellent_youth 🎁
🎁 @Excellent_youth 🎁

መልካም ወጣት

21 Apr, 04:08


አጥብቀህ ልብህን ጠብቅ

የመልካም ነገር መፍለቅያ፣ የክፉ ነገርም ሁሉ ምንጭ በተለያዬ መንገድ ወደ ልባችን ያስገባነው ነገር ነው።

"እርሱም አለ። ከሰው የሚወጣው ሰውን የሚያረክስ ያ ነው። ከውስጥ ከሰው ልብ የሚወጣ ክፉ አሳብ።"(የማርቆስ ወንጌል 7፣20፥21)

ወደ ልባችሁ ስለምታስገቡት ስትጠነቀቁ፣ ከልባችሁ ስለሚወጣው ነገር መጠንቀቅ ትጀምራላችሁ፤ ያ ካልሆነ ትረክሳላችሁ።

ልባችሁን በደምብ ጠብቁ የሰው ሁለንተና ያለው እዛው ጋር ነውና። ልቡን የማይጠብቅ ሰው ለብዙ ውሸት የመጋለጥ እድሉ የሰፋ ነው። አጥብቃችሁ ተጠንቀቁለት።

" አጥብቀህ ልብህን ጠብቅ፥ የሕይወት መውጫ ከእርሱ ነውና። "(መጽሐፈ ምሳሌ 4:23)

ለልብህ ስትጠነቀቅ ሕይወትን ታገኛለህ እንዲሁም ሕይወትን ታፈልቃለህ።

@Excellent_youth
@Excellent_youth

መልካም ወጣት

23 Mar, 17:24


📚ሕይወት እንደ ማዕበል ሲሆን

አንዳንድ ጊዜ ሕይወት እንደ ማዕበል ነው፡፡ በሰላም ይሄዱ የነበሩ ነገሮች ልክ የተመካከሩ ይመስል በአንድ ላይ ይናጋሉ፡፡ የሁኔታዎች አልሳካ ማለት፣ ድንገተኛ ወጪዎች፣ የገንዘብ እጥረት፣ የጉዳዮች መጥመም፣ የሰዎች ክህደት፣ ስጋትን የሚፈጥሩ ሁኔታዎች መከሰት፣ የጤንነት መቃወስን የሚጠቁሙ ምልክቶች ልክ እንደ ማዕበል በአንድ ላይ ይመጣሉ፡፡

ይህ የተለመደ የሕይወት አካል የሆነ ክስተት በእኛም ላይ ሲደርስ መረጋጋት ወሳኝ ነው፡፡ ማዕበል ይመጣል፣ ልክ እንደመጣ ደግሞ ይሄዳል፡፡ ነፋስ ከየት እንደመጣ ሳናውቀው ወደ እኛ ይነፍሳል፣ ወደየት እንደሚሄድ ሳናውቀው ደግሞ ወደሌላ ቦታ ይነፍሳል፡፡

አይዟችሁ ጽኑ፤ አትናወጡ ተንጋግቶ የመጣው ተንጋግቶ ይሄዳል። መልካም ቀን
 
ዶ/ር ኢዮብ ማሞ

      @Excellent_youth
      @Excellent_youth