(ከቀደሙት ልጥፎች የቀጠለ ...)
ቀደምት ዐሊሞቻችን ፉቀሐዎቹ፣ የመዝሐብ ሊቃውንቶች ኹሉ ከጌታቸው በሚያገኙት የኢጅቲሀድ (ምርምር) ሥጦታ በተጨማሪም እንደ ከሽፋና ከራማቸውን ኹሉ አፍነው ይዘው፤ ሰው እንዳያቅባቸው ተደብቀው እንደ ተርታ ኾነው ነው የኖሩት። እርግጥ ኪታቦቻቸው የሚለው ዒልም በተርቢያ ይታከማል ፥ ከአላህ የሚመጡ መንፈሳዊ ሽልማቶች እንደ ከራማ የመሰሉ ደግሞ በሸሪዓ ልጓም ይያዛል የሚለውን ነው።
ከርሱ በባሰ መልኩ ደግሞ ከራማቸውን ልክ ሴት ልጅ ውበቷን የምትደብቀውን ያህል ደብቀው ነበር የኖሩት። (ፈተና አለውና) ከፍ ሲልም ከራማ ማለት በሐቅና ሸሪዓ ላይ ጽኑ መኾን ነው አሉ። ዒልማቸውንም ኾነ ይህን ታላቅ የጌታ ስጦታ በዚህ ልክ ጠበቁት ሕዝባቸውን ለማዳን ብቻ ሲሉ ይጠቀሙበት ነበር። ለሆዳቸው ኾነ ለዱንያቸው የጌታቸውን ይህን ጸጋ ሳይጠቀሙበት ብዙዎቹ አመለጡን። ዛሬም በአይኔ ያየኋቸው ከባባድ ሰዎች አሉ። (አላህ ንጽሕናቸውን ይባርክልን)
በተቃራኒው ... ዛሬ ዛሬ ....
የኾነ ቲዩብ ከፍቶ ሺህ ቪዲዮ ከኾነ ሰው ከቃረመ እንደአደገኛ ዐሊም እራሱን ይሰቅላል። ትንሽ የአድናቆትና ጭብጨባ ማአት ሲጎርፍለት እንደአደገኛ ባለከራማ ጉዳይ ካልፈታሁ ይላል። በዚህ አያቆምም ሆዱንም ይሞላበታል፣ ይነግድበታል። የሰው ኢማንና ልብ አድርቆ ሰዎች ትክክለኛ ዓሊሞች ጋር እንዳይገናኙ ሽፍታ ይኾናል። ባለ መዝሐቦቹን፣ ፉቀሀዎቹን፣ ሱፍይ ዐሪፎቹን እንደ ተራ ጓደኞቹ ይወዳደራቸዋል። ልካቸውን ሳይረዳ፣ ከሰንሰለታቸው ሳይቋደስ በአቋራጭ ይነግድባቸዋል።
በእስልምና ስም ከእስልምና ከሚያወጡ ሰዎች አላህ ይጠብቀና!
አሚይንንን ♥