ቀን :17/6/2016 ዓ.ም
ጤግሮስ ትሬዲንግ ከፍኖት የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃ/የተ/ህ/ስ/ማኅበር ጋር በመሆን በዛሬው እለት በኢትዮጵያ ሆቴል የአባልነት መስፈርታቸውን ላሟሉ እና ቁጠባቸውን ለአጠናቀቁ የተወሰኑ መምህራን የመጀመሪያ ዙር ዘመናዊ የኤሌትሪክ መኪኖች ብድር የመስጠት ዝግጅት እና የፕሮጀክት ማስጀመሪያ መርአገብር አካሄዷል።
ጤግሮስ ትሬዲንግ "የእውቀት ባለቤት ውለታ እንመልስ" በሚል መሪ ቃል ለሀገር ባለውለታ ለሆኑ መምህራን ቁጠባና ብድርን መሰረት ያደረገ "ደራሽ" የተሰኘ የመኪና ግዥ ፕሮጀክት በመቅረፅ እና በማስተባበር ላለፉት ዓመታት ቁጠባን በማበረታታትና ብድር በመስጠት ማኅበረሰባዊ እና ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም የአካባቢ ልማት ላይ የድርሻውን በመወጣት ላለፉት ተከታታይ ዓመታት የሰርተፊኬት እና የዋንጫ ተሸላሚ ከሆነው ፍኖት የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃ/የተ/ህ/ስ/ማኅበር ጋር በመሆን የኅብረት ሥራ ማኅበሩን የአባልነት መስፈርት አሟልተው ለሚገኙ እና በጤግሮስ ትሬዲንግ የደራሽ የመኪና ብድር ፕሮጀክት ለታቀፉ አባላት የመኪና ግዥ ብድር አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡
ዛሬ በኢትዮጲያ ሆቴል እንደተገለጸው ይህ የደራሽ የመኪና ብድር ፕሮጀክት ቅድመ ቁጠባ 25% ለቆጠቡ መምህራን በ10 አመት የሚከፈል ብድር ነው።
በመርሐግብሩ ላይ የተገኙት የበላይነህ ክንዴ ጄነራል ትሬዲንግ ባለቤት አቶ በላይነህ ክንዴ ለመምህራኑ የመኪኖቹን ቁልፍ ሰጥተዋል
በተጨማሪም በነገው ዕለት የመጀመሪያው የኤሌክትሪክ አውቶቡስ ስራ እንደሚጀምር ባለሀብቱ በመድረኩ ላይ ገልጸዋል።
#mars@abc