Kolfe education official channel🇪🇹 @kolfekeranioeducationbureau Channel on Telegram

Kolfe education official channel🇪🇹

@kolfekeranioeducationbureau


We are delighted to inform our members about kolfea keranio Education bureau.🇪🇹

Kolfe Education Official Channel (English)

Are you looking for a reliable source of information and updates on education in Kolfe Keranio? Look no further, as the Kolfe Education Official Channel is here to provide you with all the latest news and updates from the education sector in this region. As the official channel of the Kolfe Keranio Education Bureau, we aim to keep our members informed about the latest developments in the education system, upcoming events, important announcements, and much more. Whether you are a student, teacher, parent, or simply interested in education in Kolfe Keranio, this channel is the perfect place for you to stay connected and updated. By joining our channel, you will have access to exclusive content, such as educational resources, tips for students, job opportunities in the education sector, and much more. Our goal is to create a community of individuals who are passionate about education and are committed to making a positive impact in the lives of students in Kolfe Keranio. So, what are you waiting for? Join the Kolfe Education Official Channel today and be a part of this thriving community dedicated to promoting education in Kolfe Keranio. Together, we can work towards building a brighter future for the students in our region. We look forward to having you on board!

Kolfe education official channel🇪🇹

17 Feb, 14:04


የክፍለ ከተማው ትምህርት ፅቤት ሰራተኞች በኤች አይ ቪ/ ኤድስ የሜይንስትሪሚንግ ዓይነቶች ዙሪያ ውይይት አደረጉ፡፡

የካቲት 10/ 2017 ዓ.ም

የኤች አይ ቪ/ ኤድስ ቫይረስ በደማቸው የሚገኘው እና ለበርካታ አመታት ራሳቸውን አጋልጠው ማህበረሰቡን እያስተማሩ የሚገኙት አቶ ነብዩ ብርሌ ስለቫይረሱ አስከፊነት እና አስቀድመን እንደት መከላከል እንደሚገባን ተሞከሯቸውን አጋርተዋል፡፡


የፅ/ቤቱ ሰራተኞች በውስጣዊ ሜይንስትሪሚንግ (Internal Mainstreaming እና ውጫዊ ሜይንስትሪሚንግ (External Mainstreaming የተቋሙ ፖሊሲዎች፣ ፕሮግራሞች፣ አሠራሮችና እንቅስቃሴዎች በኤች አይ ቪ/ኤድስ ስርጭትና በሚያስከትለው ተጽዕኖ ላይ የሚኖራቸው አሉታዊና አዎንታዊ ጎኖች ምንድናቸው? በሚሉ እና አሉታዊ ተጽዕኖዎችን ለመቀነስና አዎንታዊ ተጽዕኖችን ለማጠናከር ተቋሙ ምን እርምጃዎች መውሰድ አለበት?በሚሉ ሀሳቦች ዙሪያ በፅሁፍ እና በቃል ማብራሪያ በመስጠት ውይይት አድርገዋል፡፡

Kolfe education official channel🇪🇹

16 Feb, 04:22


https://www.youtube.com/live/VcXGMB1oDlI?si=pQhxCPr90zNDkieK

Kolfe education official channel🇪🇹

08 Feb, 12:09


ለሁሉም የመንግስት ቅድመ አንደኛ እና አንደኛ ደረጃ ት/ቤቶች ሰኛ የካቲት 3/2017 የተማሪ ምገባ ይጀመራል ሜኑ ሳይዛባ በአግባቡ ጥራቱን ጠብቆ ለተማሪ እንዲቀርብ  አናሳስባለን።

Kolfe education official channel🇪🇹

07 Feb, 09:46


በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2017 የትምህርት ዘመን የሁለተኛ ወሰነ ትምህርት የካቲት 3/2017 ዓ.ም ይጀምራል፡፡

ጥር 30/2017 ዓ.ም

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2017 የትምህርት ዘመን የሁለተኛ ወሰነ ትምህርት የካቲት 3/2017 ዓ.ም የሚጀምር መሆኑን እናሳውቃለን፡፡

Kolfe education official channel🇪🇹

07 Feb, 07:10


ለሁሉም የመንግስት ት/ቤቶች በሙሉ
ጉዳዩ፡-የመምህራን መረጃ በጥንቃቄ ተሞልቶ እንዲመጣ ስለመጠየቅ ይመለከታል።
ከላይ በርዕሱ ለመግለጽ እንደተሞከረው የ2017ዓ.ም የመምህራን የሙያ ፍቃድ ምዘና ለማድረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን  በዝግጅት ላይ መሆናቸው ይታወቃል። በመሆኑም  በተሰጠው ኦረንቴሽን መሰረት ቅፁን በጥንቃቄ  በመሙላት እስከ ቀን 05/06/2017ዓ.ም ድረስ በሶፍት እና በሀርድ ኮፒ ክ/ከተማ ት/ት ፅ/ቤት ገቢ እንድታደርጉ እናሳስባለን።

Kolfe education official channel🇪🇹

06 Feb, 14:02


ለቅድመ አንደኛ የመንግሥት መምህራን የቀዳማይ ልጅነት በጨዋታ የማስተማር ስነ-ዘዴ ለተከታታይ 4 ቀን ሲሰጥ ቆይቶ በዛሬው ዕለት ተጠናቀቀ።

ጥር 29/2017 ዓ.ም

በክፍለ ከተማውም በ1ኛ ዙር ለመንግሥት  የቅድመ አንደኛ መምህራን በንድፈ ሃሳብና በተግባር ስልጠና ለተከታታይ 4ቀናቶች ሲሰጥ ቆይቶ በዛሬው ዕለት ተጠናቋል።

በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ጽ/ቤት በትንቢተ ኤርሚያስ ቅድመ አንደኛና 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ሲሰጥ የነበረው ህፃናትን በጨዋታ የማስተማር ስነ-ዘዴ ሥልጠናውን የወሰዱ መምህራን ከዚህ ቀደም በተለያዩ ምክኒቶች ስልጠናው ያመለጣቸው ፣በ2017 ዓ.ም አዲስ ቅጥር የተቀጠሩ እና ከዩኒቨርስቲ ተመርቀው የተመደቡ መምህራን ሥልጠናውን ተከታትለዋል።

የስልጠና ተሳታፊ የነበሩት የቅድመ አንደኛ መምህራን ስለስልጠናው አስፈላጊነት እንዳሉት  መንግስት በቅርብ ዓመታት የጀመረው የቅድመ አንደኛ ደረጃ ሁለንተናዊ ድጋፍ የሚያበረታታ ነው ብለዋል።ተሳታፊወቹ አክለው እንደተናገሩት ህፃናትን በጨዋታ መልክ የማስተማር ስነ-ዘዴ ለህፃናት ስነልቦናዊ፣አካላዊ፣ስሜታዊ እና ማህበራዊ እድገታቸውን ለማደበር ወሰኝ የማስተማሪያ ዘዴ ነው ብለዋል።


በቀጣይ የግል  ትምህርት ቤቶች መምህራን በጨዋታ የማስተማር ሥልጠና  እንደሚቀጥል የወጣው  መርሃግብር ያሳያል።

Kolfe education official channel🇪🇹

31 Jan, 17:45


ከብልፅግና ጉባኤ በፊት የፓርቲው ፕሬዝዳንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተማሪዎች የተሰሩ የስዕል አውደ ርዕይን ጎብኝተዋል



(ጥር 23/2017 ዓ.ም)


ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacaebc

Kolfe education official channel🇪🇹

31 Jan, 14:49


ቀን 23/5/2017 ዓ/ም
ማስታወቂያ
የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ የመምህራንና ትምህርት ቤት አመራር ልማት ዳይሬክቶሬት በ2017 ዓ.ም ትምህርት ዘመን ለቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለአማርኛና አፋን ኦሮሞ ተማሪዎች ሞግዚትነት ተመድበው በመስራት ላይ ያሉትን አጠቃላይ መረጃ በማደራጀት የትምህርት ዝግጅታቸውን እና ሌሎች ለቀጣይ ትምህርት ማሻሻያ ተግባራትን እንዳስፈላጊነቱ ጥያቄ ለማቅረብ ይረዳን ዘንድ በትምህርት ደረጃቸው እና አገልግሎታቸው መሰረት በማደራጀት ለቀጣይ ውሳኔ መነሻ ለማቅረብ እንዲያመች መረጃውን በቅፁ መሰረት ብቻ በመሙላት እጅግ ቢዘገይ እስከ 28/5/2017 ዓ.ም ድረስ ለክፍለ ከተማ መምህራን ትምህርት አመራር ልማት ቡድን ተጠምሮ እንዲላክልን ስንል ከዚህ ጊዜ ገደብ ውጪ ለሚመጣ መረጃ ለሚፈጠረው ማንኛውም እንግልት ጽ/ቤቱ ኃላፊነት የማይወስድ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
የመምህራን ትምህርት አመራር ልማት ቡድን
BEEKSISA
Daayireekoteetiin Biiroo Barnootaa Magaalaa Finfinnee bara barnootaa 2017 manneen barnoota sadarkaa 1ffaa tiif Afaan Amaariffaa fi Afaan Oromiffaatiin kunuunsitummaa ramadamanii kan hojjechaa jiraniif gara fuula duraa gaaffii barnoota isaanii fooyyeffachuuf gargaaru gaafachuuf akka nugargaaruf jecha raga barnootaa fi tajaajila isaanii bu’uura godhachuun guca gad buusne kanaan guutuun yoo ture hanga 28/5/2017 tti misooma Barsiisotaa kutaa Magaalaa Kolfee Qaraaniyootiif akka ergamu beeksisaa yeroo jedhametti kan hin ergamne yoota’e waajjirri keenya gaafatamummaa kan hin fudhanne ta’uu isin beeksifna
Misooma Barsiisotaa

Kolfe education official channel🇪🇹

31 Jan, 12:21


የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ኮልፌ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ሀገሬ አበባው በበኩላቸው የግል ትምህርት ተቋማት አስፈላጊውን የሥታንዳርድ ግብዓት በማሟላት የመንግስትን ፖሊሲ ማስፈፀም እና ሥርዓተ ትምህርቱን ተግባራዊ ማድረግ ይገባቸዋል ብለዋል።

Kolfe education official channel🇪🇹

31 Jan, 10:45


መንግስት የትምህርት ጥራት እና ተደራሽነት ለማረጋገጥ በሚያደርገው እንቅስቃሴ የግል ትምህርት ተቋማት እና የወላጅ ተማሪ መምህራን ህብረት አመራሮች ሚና ከፍተኛ መሆኑ ተገለፀ።

ቀን ጥር 23/2017 ዓ.ም

የኮልፌ ቀራራኒዮ ትምህርት ጽ/ቤት እና ትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ኮልፌ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በጋራ ባዘጋጁት መድረክ በክፍለ ከተማው አስተዳደር ሥር የሚገኙ የግል አንደኛ እና አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የወላጅ ተማሪ መምህራን ህብረት (ወ.ተ.መ.ህ) አመራሮች  በአዲስ መልክ መልሶ የማደራጀት ስራ በየትምህርት ተቋማቱ እየተሠራ መሆኑ ተገልጿል።

በመድረኩም እስካሁን በትምህርት ቤቶች በቀድሞ የወ.ተ.መ.ህ አመራሮች የተሰሩ የልማት፣የመልካም አስተዳደር፣ ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደት እንዲፈጠር ከማድረግ አንፃር የተሰሩ ስራዎች ቀርቦው ውይይት ተደርጓል።

መድረኩን የመሩት የክፍለ ከተማው ትምህርት ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ገነነ ዘውዴ  መንግስት የትምህርት ጥራትና ተደራሽነት ለማረጋገጥ፣ ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደት እንዲኖር፣ በስነ ምግባር የታነፀ የነገው ሀገር ተረካቢ ትውልድ ለማፍራት በትኩረት እየሰራ ይገኛል ለዚህም የግል ትምህርት ተቋማትና ወላጅ፣ተማሪ ፣መምህር ህብረት አስተዋፅኦ ከፍተኛ ነው ብለዋል።

ሀላፊው ጨምሮው እንደገለፁት በአዲስ መልክ መልሶ የእየተደራጀ የሚገኘው የግል ትምህርት ቤቶች የወ.ተ.መ.ህ አመራር  የተማሪ ወላጆች በማስተባበር በየት/ቤቱ የሚነሱ የልማትና የመልካም አስተዳደር ችግሮች በመመለስ የራሳቸውን ሚና መወጣት አለባቸው ሲሉ መልእክታቸውን አስተላልፏል።

Kolfe education official channel🇪🇹

31 Jan, 09:24


🗣👆👆👆

Kolfe education official channel🇪🇹

31 Jan, 06:28


ከ11ዱ ወረዳ የቀዳማይ ልጅነት(የኬጅ)ሱፐርቫይዘር ከሁሉም ወረዳወች አንድ አንድ ተወካይ በተጠቀሰው ቀን ማለትም ሰኞ እና ማክሰኞ(26-27/2017 ዓ.ም)እንድትልኩልን እናሳውቃለን።

Kolfe education official channel🇪🇹

22 Jan, 14:02


Akkam jirtu? Ragaa barsiisota Og-Aartii Manneen Barnootaa irraa haala guca kennameen funaanuun yoo baay`ate hanga guyyaa 16/05/2017tti akka nuuf ergitan kabajaan isin gaafanna.

Kolfe education official channel🇪🇹

21 Jan, 12:38


በ2018 ዕድሜያቸው መታወቂያ ለማውጣት የደረሱ ተማሪዎች ለትምህርት ቤት ምዝገባ የፋይዳ መታወቂያ ይጠየቃሉ ተባለ።

በሚቀጥለው ዓመት ትምህርት ቤት ከሚመዘገቡ ዕድሜያቸው መታወቂያ ለማውጣት የደረሱ ተማሪዎች ከልደት ካርድ ውጭ የፋይዳ መታወቂያ እንደሚጠየቁ ሰምተናል።

የሲቪል ምዝገባ እና አገልግሎት ኤጀንሲ ከብሔራዊ መታወቂያ አገልግሎት ጋር በጋራ እየሰሩ መሆናቸውን ተከትሎ በሚቀጥለው አመት ተግባራዊ እንደሚደረግ የኤጀንሲው ዳይሬክተር ዮናስ አለማየሁ ገልፀዋል።

ኤጀንሲው ከአገልግሎቱ ጋር መስራት ከጀመረበት 2 ወር ጊዜ አንስቶ በአዲስ አበባ 1.8 ሚሊየን የሚሆኑ ነዋሪዎች የፋይዳ መታወቂያ መመዝገባቸውን አስታውቀዋል።

ከተለያዩ ተቋማት ጋር በመሆን የምዝገባው ሂደት የሚከናወን ሲሆን፤ 40 በመቶ የሚሆነው ምዝገባ በኤጀንሲው መከናወኑን ገልፀዋል።

የተማሪዎች የፋይዳ መታወቂያ ምዝገባን ከመንግስት ትምህርት ቤቶች በተጨማሪ ወደ ግል ትምህርት ቤቶች ለማስፋፋት ዕቅድ መያዙንም ነው ዳይሬክተሩ የተናገሩት።

በሚቀጥለው 6 ወራት ጊዜ ውስጥ የነዋሪነት መታወቂያ የሆነ የፋይዳ መታወቂያ ቁጥር የያዘ፣ የመንጃ ፍቃድ ቁጥር ያለው እንዲሁም እንደ ኤቲ ኤም ካርድ የሚያገለግል ሁሉንም በአንድ የያዘ ስማርት ካርድ ወደ ስራ እንደሚገባም ተናግረዋል።


ETHIO FM 107.8

ጥር 13 ቀን 2017 ዓ.ም

Kolfe education official channel🇪🇹

21 Jan, 06:30


🎯                                               🎯
                             ቀን 12/05/17
የ12ኛ ክፍል የደጋሚ ተፈታኞች(private )ምዝገባ የፊታችን ሐሙስ ጥር 15/2017 ዓ.ም የሚጠናቀቅ ይሆናል፤  መረጃውን ተደራሽ በማድረግ  ያልተመዘገቡ ካሉ የእድሉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ እናድርግ
::

🎯                                               🎯

Kolfe education official channel🇪🇹

19 Jan, 09:28


የጥምቀት በዓል አከባበር በጃንሜዳ በምስል

(ጥር 11/2017 ዓ.ም)


#ከአ.አ ትምህርት ቢሮ ገጽ የተወሰደ።

Kolfe education official channel🇪🇹

18 Jan, 11:20


ለመላዉ የክርስትና እምነት ተከታዮች
እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ በሰላም አደረሳቹ፡፡ በአሉ የሰላም ፣ የደስተና የጤና እንዲሆንላቹ እመኛለሁ፡፡

አቶ ገነነ ዘውዴ
በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ

Hordoftoota Amantaa kiristaanaa hundaaf, Baga ayyaana cuuphaaf isiniin gahe. Ayyaanichi kan nagaa,gammachuu fi fayyaa isiniif haa ta'u!

Obbo Gannana Zaawudee

Ittigaafatamaa Waajjira Barnootaa Kutaa Magalaa Kolfee Qaraaniyoo

Kolfe education official channel🇪🇹

17 Jan, 09:52


በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማው ትምህርት ፅ/ቤት የሥርዓተ-ትምህርት ትግበራ ቡድን የፈተና ዝግጅት አስተዳደር የ2017 ዓ.ም የግማሽ አመት ሥራዎችን ገመገመ፡፡

ቀን ጥር 09/2017 ዓ.ም

የክፍለ ከተማው የሥራዎች አስተባባሪ የሆኑትን አቶ በፍቃዱ ኤርጋቡስ ጨምሮ የመንግስት አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የመማር ማስተማር ምክትል ርዕሰ መምህር፣የሁሉም ወራዳዎች የሥርዓተ ትምህርት ቡድን መሪዎች እና የክፍለ ከተማው የፈተና ዝግጅት እና አስተዳደር ባለሙያዎች በተገኙበት ሥራዎችን ገምግሟል፡፡

የ8ኛ ክፍል የበይነ መረብ(online)ምዝገባ ሂደት ያለበት ደራጃ እና የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል የሞዴል ፈተና አፈፃፀም ምን እንደሚመስል በአቶ በርሄ ኃጎስ በሪፖርት ከቀረበ በኋላ ተሳታፊዎች የተለያዩ ጥያቄወችን እና አሰተያቶችን አቅርበዋል፡፡

በቀረቡት ጥያቄዎች ዙሪያ መልስና ማብራሪ የሰጡት አቶ በፍቃዱ ኤርጋቡስ እንዳሉት የበይነ መረብ የ8ኛ ክፍል የተማሪዎች ምዝገባ በአመዛኙ በጥሩ ሁኔታ እየተከናወነ ይገኛል፡፡ይሁን እንጂ አልፎ አልፎ የሚታዩ የኔቶርክ መቆራረጥ እና የአንዳንድ ተቋማት በተጠበቀው ልክ ያለመስራት በእቅዳችን እንዳንሄድ ወደኋላ የመጎተት አዝማሚያዎች ይስተዋላሉ ብልዋል፡፡ኃላፊው አክለው እንዳሉት ሞዴል ፈተና በፍፁም ሰላማዊ እና ኩረጃን ለመቀነስ የተሰራው ተግባር የሚበረታታ ነው፡፡ሆኖም አንዳንድ የግል እን የመንግስት ተቋማቶች አስቀድመው ለፈተናው ምቹ ክፍሎችን ባለማመቻቸት የተስተዋሉ ጥቃቅን ችግሮች ነበሩ ስለሆነም በቀጣይ እነኘህን ችግሮች ሁሉም የትምህርት ቤት አመራር ተቋማት ሊያርማቸው ይገባል ብለዋል፡፡

Kolfe education official channel🇪🇹

16 Jan, 03:57


https://www.facebook.com/100064163554112/posts/1039272188221557/?mibextid=UuH66acrLgeVUPia

Kolfe education official channel🇪🇹

16 Jan, 03:53


የሀዘን መግለጫ
መምህር መክብብ ንጉሴ ባሳለፍነው እሁድ በደረሰ ድንገተኛ የመኪና አደጋ በሞት አጥተነዋል።

መምህር መክብብ ንጉሴ ላለፉት ዘጠኝ አመታት በመምህርነት ሙያ ያገለገለ ሲሆን በረጲ ቅ/አ/አ/መ/ደ/ት/ቤት እና ህይወቱ ካለፈበት ጥቂት ወራት ቀደም ብሎ በህዳሴ ቅ//አ/አ/መ/ደ/ት/ቤት በማኀበራዊ ሳይንስ የትምህርት ዘርፍ ሀገሩን እና ማኀበረሰብን ሲያገለግል ቆይታል።
መምህር መክብብ ባለትዳር እና የሁለት ልጆች አባት ነበረ። በደረሰበት ድንገተኛ አደጋ ህይወቱ አልፋል።

የህዳሴ ቅድመ አንደኛ አንደኛ እና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አጠቃላይ ሰራተኞች  ፣መምህራን ፣  ተማሪዎች  ፣ እና የተማሪ ወላጅ/አሳዳጊዎች በወንድማችን እና በስራ ባልደረባችን መምህር መክብብ ንጉሴ ድንገተኛ ህልፈት የተሰማንን ሀዘን እንገልፃለን።

ለስራ ባልደረቦቹ ለቤተሰቦቹ ለወዳጅ ጓደኞቹ መጽናናትን እየተመኘን የወንድማችንን ነፍስ  ፈጣሪ በአጸደ ገነት ያኑርልን!


ነፍስ ይማር

የህዳሴ ቅ/አ/አ/መ/ደ/ት/ቤት

Kolfe education official channel🇪🇹

15 Jan, 09:44


የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ አስተዳዳደር ትምህርት ጽ/ቤት  የ6 ፣8ኛ እና 12ኛ ክፍል  የሞዴል ፈተና መልስ

Kolfe education official channel🇪🇹

10 Jan, 10:40


የክፍለ ከተማው ትምህርት ጽ/ቤት የሁለተኛ ሩብ ዓመት ክትትል ፣ድጋፍ እና እና ግብረ መልስ እንዲሁም የ6ወር እቅድ አፈፃፀም  ገመገመ።

ቀን ጥር 02/217 ዓ.ም

የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት የሁለተኛ ሩብ ዓመት ክትትል ፣ድጋፍ እና እና ግብረ መልስ እንዲሁም የ6ወር እቅድ አፈፃፀም የገመገመ ሲሆን በመድረኩ  የመንግሥት አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ዋና ር/መምህራን ፣ የወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት  ተወካዮች እና የፅ/ቤቱ ሠራተኞች ተሳታፊ ሆነዋል።

በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እና በወረዳ ት/ፅ/ቤቶች በተደረገ የ2ኛ ሩብ ዓመት የድጋፍ፣ክትትልና ግብረ-መልስ  ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ውይይት የተደረገ ሲሆን በተቋማት የታዩትን ጠንካራና መስተካከል የሚገባቸውን ክፍተቶች በማየት ግብረ-መልሱ ለተቋማቱ በደብዳቤ እንደሚላክ አቅጣጫ ተቀምጧል።
በመድረኩ የ6ወር እቅድ አፈፃፀም የተገመገመ ሲሆን ከተሳታፊዎችም በእቅድ አፈፃፀሙ ዙሪያ ጥያቄና አስተያየቶች ተነስተዋል።ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ የሰጡት የጽ/ቤቱ የቡድኖች የሥራ አስተባባሪ የሆኑት አቶ ሠይፈሚካኤል ባርጠማ  ናቸው።

Kolfe education official channel🇪🇹

08 Jan, 09:00


https://forms.gle/hGzdvbWtJCmLSAH78ይህንን መጠይቅ ለቀጣይ አገልግሎት አሰጣጥ ለማሻሻል እንዲረዳን
• ከተማሪዎች
• ከመምህራን
• ከር/መምህራን
እንዲታስሞሉልን በታላቅ አክብሮት እንጠይቃለን፡፡

Kolfe education official channel🇪🇹

06 Jan, 09:04


Dear all, this is HPV MAC vaccination campaign plan performance in School student girls by school name

Kolfe education official channel🇪🇹

06 Jan, 07:34


የሰኞ/ማክሰኞ ማለዳ የሰራተኞች የዕውቀት ሽግግር መርሀ ግብር ተካሄደ፡፡

ታህሳስ 28/2017 ዓ.ም

የከፍለ ከተማው ትምህርት ፅ/ቤት የሰኞ/ማክሰኞ ማለዳ ከስራ ሰዓት መግቢያ አስቀድሞ የሚያዘጋጀው የሰራተኞች የዕውቀት ሽግግር መርሀ ግብር የተካሄደ ሲሆን በመድረኩ የፅ/ቤቱ አጠቃላይ ሠራተኞች ተሳታፊ ሁነዋል፡፡

የማለዳ የሠራተኞች የእውቀት ሽግግር መርሃ ግብር የአመራርነት ክህሎት እና የማስፈፀም አቅም በሚል ርእስ ዙሪያ የቀረበ ሲሆን የዕለቱን ሰነድ ያቀረቡት አቶ ሚካኤል ገ/ሚካኤል የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ሱፐርቫይዘር ሲሆኑ የትምህርት አመራሩ በክህሎት እና በጥበብ የተሞላ ከሆነ ብልሹ የሆኑ አሰራሮችን ማረም እና ማስተካከል ይችላል ብለዋል፡፡አቅራቢው አክለው እንደተናገሩት በመንግስት የትምህርት ተቋማት የተማሪዎች ውድ ሰዓት ወይም የከፍለ ጊዜ ብክነት እንዳይፈጠር በአመራርነት ጥበብ የማስፈፀም አቅማችንን ከፍ በማድረግ የሚፈጠሩትን ችግሮች መቀነስ ከቻልን በተማሪዎች ውጤት ላይ አውንታዊ ተፅዕኖ እንደሚኖረው ገልፀዋል፡፡

Kolfe education official channel🇪🇹

04 Jan, 19:26


በዓሉን ስናከብር ድጋፍ የሚሹ ወገኖችንም በመርዳት እና በማሰብ መሆን አለበት የአቡነ ባሲሊዮስ ትምህርት ቤት አካባቢ ወጣቶች።

ቀን ታህሳስ 26/2017 ዓ.ም

የአቡነ ባስልዮስ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ቀና ልቦና ያላቸውን የአካባቢውን ወጣቶች በማስተባበር የገና በአልን ምክንያት በማድረግ ልዩ ድጋፍ ለሚሹ እና ልዩ ፍላጎት ላላቸው ለ26 ለት/ቤታችን ተማሪዎች ለ1ተማሪ ግምቱ 3150 ብር ግምት ያላቸው
ዶሮ
ዱቄት
ዘይት
እንቁላል እና የኪስ ገንዘብ ብር 700 ተበርክቶላቸዋል ። የተደረገላቸውንም ድጋፍ የተመሪዎች ወላጆች በአካል በመቅረብ ተረክበዋል። ከላይ ለተገለጹት ድጋፍ በድምሩ ብር 81900ብር ድጋፍ ተደርጓል።

#🙏🙏🙏

Kolfe education official channel🇪🇹

04 Jan, 17:45


Muddee 26/04/2014
Waajjira barnootaa kutaa magaalaa Kolfee Qaraaniyootti sagantaan gaaffii fi Deebii barattootaa kutaa 6, 8 fi 12ffaa gaggeeffamee jira. Saganticha irratti manneen barnootaa mootummaa fi dhuunfaan kan hirmaatan yoo ta'u , sagantaa kana irratti namoota 530 kan ta'uu argamanii jiru.Sirna Gaaffii fi Deebii Kana irratti Ittigaafatamaa Waajjira Barnootaa Kabajamoo Obbo Gannanaa Zawudee gaaffii fi deebiin barattoota giddutti taasifamuu miiraa wal dorgommii barattootaa kan cimsuu fi kakaasuu waan ta'eef kun mul'istuu foyya'insa qabxii barattootaa hunda galeessaan kan fidu jedhan. kanamalees, barattoota qacalee sadarkaa 1ffaa hanga sadaffaa ba'aniif badhaasa, kitaabolee wabii, sertifimeetiin kan kenname yoo ta'uu, manneen barnootaa sadarkaa 1ffaa hanga 3ffaa ba'an Geebni Waancaan kan kenname jira.
Haaluma kanaan kutaa 8ffaa irraa
1 Lalii Abbabaa Mana barumsaa J/Waaqoo Guutuu lakk 2 1ffaa
2 Mo'iiboon Hundeessaa Mana barumsaa Salaam Bar irraa 2ffaa
3 Ifaa Lataa Mana barumsaa Gaaraa Furii irraa 3ffaa yoo ba'an
Kutaa 6ffaa irraa
1 Rabbirraa Fayyisaa mana barumsaa J/Waaqoo Guutuu Lakk 3 1ffaa
2 Olbiraat Dassaaleenyi Mana barumsaa J/Waaqoo Guutuu lakk 2 irraa 2ffaa
3 Raadeet Taddasaa mana barumsaa Raphii Jaappan irraa 3ffaa ba'aanii jiru
Kutaa 8ffaa irraa Geebaa Waancaa kan argatan
1.Mana barumsaa J/Waaqoo Guutuu lakk 2 1ffaa
2 Mana Barumsaa Salaam Bar 2ffaa yoo ba'an
Kutaa 6ffaa irraa Geeba Waancaa Kan Argatan
1 Mana barumsaa J/Waaqoo Guutuu lakk 3 1ffaa
2 Mana barumsaa J/Waaqoo Guutuu Lakk 2 2ffaa ba'anii Geeba Waancaa argataniidha
Akkaa Waajjira Barnootaa Aanaaleetti
Waajjiraa barnootaa Aanaa 7 kutaa 8ffaa irraa 1ffaa ba'uun Sertiifikeetii yeroo argatan Waajjira barnootaa Aanaa 9 kutaa 6ffaa irraa 1ffaa ba'uun Sertiifikertii argatanii jiru

Kolfe education official channel🇪🇹

02 Jan, 15:21


ቀን 24/4/2017
🆕ማሳሰብያ
🫴🏼ለ1ኛ ደረጃ የመንግስት ት/ቤቶች
↖️የሁሉም 1ኛ ደረጃ መምህራን ልማት ም/ር/መምህራን  በሙሉ
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ት/ቢሮ የመምህራንና ት/ት አመራር ዳይሬክቶሬት  ቅዳሜ 26/04/17 ዓ/ም  የ ስልጠና መድረክ አዘጋጅቷል።
ስለሆነም ጠዋቱ 2:30 ስዓት  በዳግማዊ ሚኒሊክ 2ኛ ደረጃ ትልቁ አዳራሽ እንድገኙ   እናሳስባለን።
                                                 ከሰላምታ ጋር
Beeksisa
Manneen barnoota mootummaa sad.1ffaatii
Misooma barsiisotaa manneen barnootaa sad.1ffaa hundaa Daarikteerri misooma barsiisotaa biiroo barnoota Finfinnee gaafa guyyaa 26/4/2017 leenjii ni kenna.
kanaafuu ganama sa'aatii 2:30 irratti m/b/DAAGIMAAWII MINILIK sad 2ffaa galma guddaa keessatti akka argamtan isin beeksifna.
nagaa wajjin

Kolfe education official channel🇪🇹

02 Jan, 03:37


በገዳይነቱ በሁለተኛ ደረጃ የተቀመጠ በሽታ

ምንጭ :- ፋና ቴሌቪዥን

Kolfe education official channel🇪🇹

01 Jan, 03:01


ተማሪዎች ትምህርት ቤት ለመመዝገብ የፋይዳ  ምዝገባ  አስገዳጅ  ቅድመ ሁኔታ ይሆናል ተባለ


በከተማው ውስጥ ባሉ ትምህርት ቤቶች ሁሉ ለ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የፋይዳ ምዝገባ እንደ ልደት ምዝገባ አስገዳጅ እንደሚሆንም ተገልጿል።


ይህ የተገለፀው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲና የብሄራዊ መታወቂያ ፕሮጀክት ጽ/ቤት ከከተማው ትምህርት ቢሮ ጋር በመሆን  የፋይዳ እና የልደት ምዝገባን በተመለከተ ውይይት ባከናወነበት ወቅት ነው።

በዚህም በቀጣይ ግዚያት የፋይዳ ዘመቻ ምዝገባ ስራ በይፋ በግል ትምህርት ቤቶቹ በሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ አስተባባሪነት ይከናወናል ተብሏል።

የፋይዳ ምዝገባ እንደ ልደት ምዝገባ ለ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የተማሪዎች ቅበላ የምዘገባ ቅድሙ ሁኔታ እንደሚሆን ተነግሯል

Kolfe education official channel🇪🇹

31 Dec, 08:41


የሰኞ/ማክሰኞ ማለዳ የሰራተኞች የዕውቀት ሽግግር መርሀ ግብር ተካሄደ፡፡

ታህሳስ 22/2017 ዓ.ም

የከፍለ ከተማው ትምህርት ፅ/ቤት የሰኞ/ማክሰኞ ማለዳ ከስራ ሰዓት መግቢያ አስቀድሞ የሚያዘጋጀው የሰራተኞች የዕውቀት ሽግግር መርሀ ግብር የተካሄደ ሲሆን በመድረኩ የፅ/ቤቱ አጠቃላይ ሠራተኞች ተሳታፊ ሁነዋል፡፡

የማለዳ የሠራተኞች የእውቀት ሽግግር መርሃ ግብር በሌሰን ስተዲ አተገባበር ሂደት ዙሪያ የቀረበ ሲሆን የዕለቱን ሰነድ ያቀረቡት አቶ ወርቁ ጫላ የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ሱፐርቫይዘር ሲሆኑ የሌሰን ስተዲ አተገባበርን የትምህርት ባለሙያው እና ሱፐርቫይዘሮች በእውቀት ላይ የተመሰረተ ድጋፍ እና ክትትል ለማድረግ ያስችላል ብለዋል፡፡አቅራቢው አክለው እንደተናገሩት መንግስት የእግሊዘኛ እና ሂሳብ ትምህርቶችን ውጤት ለማሻሻል በሚያደርገው ርብርብ መምህራን በሌሰን ስተዲ እቅድ እያቀዱ አተገባበሩን እየገመገሙ ሳይንሳዊ ሂደቱን ጠብቆ ከተተገበረ ውጤት ማምጣት እንደሚቻል ገልፀዋል፡፡

Kolfe education official channel🇪🇹

30 Dec, 13:01


እስካሁን ከ499,000 በላይ ተማሪዎች በ2017 ዓ.ም የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ለመውሰድ ተመዝግበዋል፡፡ - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት

በ2017 ዓ.ም የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የማጠናቀቀቂያ ፈተና ለመውሰድ እስካሁን 499,200 ተማሪዎች መመዝገባቸውን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል፡፡

በመደበኛ እና በግል 750,000 ተማሪዎች ይመዘገባሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ በአገልግሎቱ የተፈታኞች ምዝገባ፣ የፈተና ዕርማትና ውጤት ጥንቅር ዴስክ ኃላፊ ማዕረፉ ሌሬቦ ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ተናግረዋል።

የመደበኛ ተፈታኝ ተማሪዎች ምዝገባ በኦንላይን ከታህሳስ 8/2017 ዓ.ም ጀምሮ እየተከናወነ ሲሆን፤ ጥር 6/2017 ዓ.ም እንደሚጠናቀቅ ኃላፊው ገልፀዋል።

በመደበኛው ፕሮግራም 600,000 ተማሪዎች ለመመዝገብ ዕቅድ መያዙን የገለፁት ኃላፊው፤ እስካሁን 82 በመቶ የሚሆኑ መደበኛ ተማሪዎች መመዝገባቸውን ጠቁመዋል። በግል የሚፈተኑ 150,000 ተማሪዎች እንደሚመዘገቡ ሲጠበቅ፤ እስካሁን 1,100 ተማሪዎች ብቻ ምዝገባ አድርገዋል፡፡

የኢንተርኔት አማራጭ በሌለባቸው አካባቢዎች ተማሪዎች በወረቀት ከተመዘገቡ በኋላ ኢንተርኔት የሚሠራበት አካባቢ በመሔድ መረጃቸውን ወደ ኦንላይን መጫን እንደሚችሉ ኃላፊው ተናግረዋል። #FMC

@tikvahuniversity

Kolfe education official channel🇪🇹

30 Dec, 11:07


ር/መምህራን ነገ ለስብሰባ ስትመጡ አስሞልታችሁ አንድትመጡ እናሳስባለን ።

Kolfe education official channel🇪🇹

30 Dec, 10:25


የክፍለ ከተማው ትምህርት ፅህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ገነነ ዘውዴ እንደገለፁት ትምህርት ፅህፈት ቤት ከጤና ፅህፈት ቤት ጋር በመቀናጀት ከሚሰራቸው ስራዎች መካከል አንዱ የማህፀን በር ካንሰር መከላከያ ክትባት አንዱ እንደሆነ አስታውሰው በዛሬው እለት በክፍለ ከተማው በሚገኙ ትምህርት ቤቶች ክትባቱ መሰጠት መጀመሩን ጠቁመዋል።

Kolfe education official channel🇪🇹

30 Nov, 10:34


የቀድሞ ተማሪዎች ህብረት በትምህርት ለትውልድ መርሀ ግብር የተለያዩ ድጋፎችን አደረጉ።

ህዳር 21/2017 ዓ.ም

የ1970 ዓ.ም የቀድሞ የአየር ጤና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ለትምህርት ቤቱ  ከውጭ ሀገር ያስመጡዋቸውን ለፊዚክስ ቤተ-ሙከራ የሚሆን የተለያዩ ግብአቶችን በዛሬው እለት ድጋፍ አድርገዋል።

የ1970  የተማሪዎች ህብረትም  በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር ከሚገኙ  የቀድሞ ተማሪዎችን  በማስተባበር ለፊዚክስ ቤተ ሙከራ የሚሆን የተለያዩ ግብዓቶችንና የቤተ መፅሀፍት እድሳት ማካሔዱንም በመር-ግብሩ ላይ ተጠቅሷል።

የክፍለ ከተማው ትምህርት ፅህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ገነነ ዘውዴ በመርሀ ግብሩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት የትምህርት ቤቶችን የግብዓት ችግር በመቅረፍ ደረጃቸውን ለማሻሻል ትምህርት ለትውልድ መርሀ -ግብር ተግባራዊ በመደረጉ በርካታ ውጤቶች እየተመዘገቡ እንደሚገኝ አስታውሰው የ1970  የቀድሞ የአየር ጤና ትምህርት ቤት የተማሪዎች ህብረት ላደረገው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።

አክለውም ትምህርት ቤቱ በርካታ ተማሪዎችን ተቀብሎ የሚያስተምር በመሆኑ የተደረገው ድጋፍ  በቴክኖሎጂ የተደገፈ ተወዳዳሪ  ተማሪዎች እንዲኖር ሚና  እንዳለው አስገንዝበዋል፣መሰል ድጋፎችን  ሌሎች  የቀድሞ የተማሪዎች ህብረቶች  እንዲያደርጉም ጠይቀዋል ።

የ1970 ዓ.ም የቀድሞ  የተማሪዎች ህብረት ሰብሳቢ አቶ ሽመልስ ተስፋዬ  እንደገለፁት  ህብረቱ ተማሪዎች ከዘመኑ ጋር እንዲሄዱ የፊዚክስ ቤተ ሙከራ ግብዓቶችንና የቤተ መፅሀፍት እድሳት ማድረጉን የገለፁ ሲሆን ድጋፉም በቀጣይ በICT፣ በቤተ ሙከራ፣ የትምህርት ቤቱን ምድረ ግቢ የማስተካከል ስራዎችን እንደሚሰሩ ጠቁመው ለግብዓትና ለቤተ መፅፍት እድሳት በአጠቃላይ ከ6መቶ ሺ ብር ወጪ መደረጉን ገልፀዋል።

በመርሀ ግብሩም የቀድሞ የፊዚክስ ቤተ ሙከራ ጉብኝት የተካሔደ ሲሆን በርክክብ ስነ ስርዓቱም ላይ መምህራን ፣ተማሪዎች፣የቀድሞ ተማሪዎችን፣የወተመህ ተወካዮች ተገኝተዋል።

#ኮልፌ ኮሙኒኬሽን

Kolfe education official channel🇪🇹

29 Nov, 11:53


በኢ-ስኩል የተማሪዎች  ምዝገባ  በርካታ አውንታዊ ውጤቶች በመታየቱ የመምህራንን መረጃ በጥራት ለመስራት ጥቅም ላይ ሊውል ይገባል ተባለ።

ቀን ህዳር 20/2017 ዓ.ም


የኢ-ስኩል የመምህራን ምዝገባን አተገባበርን  በተመለከተ ለመንግስት አንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ለመምህራን ልማት ም/ር/መምህራን፣ለወረዳ እና ለክፍለ ከተማ መምህራን ልማት ባለሙያዎች  የኢ-ስኩል የመምህራን ምዝገባ አመዘጋገብ ሥልጠና ተሰጥቷል።

በስልጠና ሄደቱ ወቅት የተገኙት የክፍለ ከተማው ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ገነነ ዘውዴ እንዳሉት መንግሥት ለትምህርት ሴክተሩ በሰጠው ትኩረት የተማሪዎች ምዝገባ በቴክኖሎጂ(E-schools system)የonlineን ምዝገባ በማድረጋችን በርካታ እምርታዊ የሆኑ ለውጦችን ማየት ችለናል።በዚህም የማህበረሰቡን እንግልት ከመቀነስ ባለፈ የመረጃ ጥራት እንዲኖረን አድርጓል።በመሆኑም በቀጣይ የመምህራንን መረጃ በአንድ ቋት(በኢ-ስኩል)በመመዝገብ የመምህራንን እጥረት እና ትርፍ በማወቅ የትምህርት ፍትሐዊነትን እናረጋግጣለን ብለዋል።

Kolfe education official channel🇪🇹

25 Nov, 12:21


Hidase General Secondary school has started giving 2017 E.C mid-exam!
The seating arrangement can be taken as a model even for other schools since one student is in one seat(desk)!

Awareness creation has also been given to the whole examinees by displaying different sayings related to cheating!

Kolfe education official channel🇪🇹

25 Nov, 11:09


የመሰረተ ዕድገት ት/ቤት የሰኞ ማለዳ ዕውቀት ሽግግር መርሀ ግብር አካሄደ።

ህዳር 16/2017 ዓ.ም


በኮልፌ ቀ/ክ/ከተማ ወረዳ 10 ትምህርት ጽ/ቤት ሥር የሚገኘው የመሰረተ ዕድገት ቅ/አ/መ/ደረጃ ትምህርት ቤት የማለዳ የሠራተኞች የእውቀት ሽግግር መርሃ-ግብር አካሂደዋል፡፡በመርሃ ግብሩ ላይ የአገልግሎት አሠጣጥ ርዕስ የት/ቤቱ ርዕሰ መምህር የሆኑ አቶ ተገኝ ታምሩ መነሻ በሰነድ አቅርበዋል በቀረበው ሰነድ ዙሪያ መምህራን እና ድጋፍ ሰጭ ሰራተኞች ውይይት በማድረግ የእርስ በዕርስ እውቀት ልውወጥ ማድረግ ችለዋል፡፡
በመርሃ ግብሩ ላይ የተሳተፉት መምህራን እንደገለፁት የማለዳ የእውቀትሽግግር መርሃ-ግብር የተቋሙን ራዕይ,ተልዕኮና መሪ ዕቅድ ለማሳካት አይነተኛ ሚና ይኖረዋል ብለዋል፡፡


#መረጃው የትምህርት ቤቱ ነው፡፡

Kolfe education official channel🇪🇹

24 Nov, 14:10


Reference!

Kolfe education official channel🇪🇹

24 Nov, 13:43


በክፍለ ከተማው “ህፃናት የሚሉት አላቸው እናዳምጣቸው!!” በሚል መሪ ቃል አለም አቀፍ የህፃናት ቀን ተከበረ።

ህዳር 15/2017 ዓ.ም

በዛሬው ዕለት በክፍለ ከተማው ሴቶች፣ህፃናትና ማህበራዊ ጉዳይ ፅ/ቤት አዘጋጅነት ህዳር 11 የአለም ህፃናት ቀን በአለም ለ35ኛ ጊዜ “Listen To The Future!!” እንዲሁም በሀገራችን ለ19ኛ ጊዜ “ህፃናት የሚሉት አላቸው እናዳምጣቸው!!” በሚል መሪ ቃል ከሁሉም ወረዳዎች የተወጣጡ ህጻናት በተገኙበት በተለያዩ ደማቅ ዝግጅቶች ተከብሯል።

ወ/ሮ ይታይሽ ደነቀው የክፍለ ከተማው ሴቶች፣ህፃናትና ማህበራዊ ጉዳይ ፅ/ቤት ኃላፊ ባስተላለፉት መልዕክት ህጻናት የነገ የሀገር ተረካቢ በመሆናቸው መብታቸው እየተጠበቀ ፣እየተከበረ እና እየተረጋገጠ እንዲሁም ተገቢውን እንክብካቤ እንዲያገኙ እየተሰራ በመሆኑ ያላቸውን አምቅ ችሎታ እየተጠቀሙ በአዳዲስ የፈጠራ ስራዎች ላይ እየተሳተፉ ነው ብለዋል።

ጽህፈት ቤት ኃላፊዋ አክለውም እንደ መሪ ቃሉ ህጻናት የሚሉት አላቸው ስለዚህ ጆሮ ሰጥተን እናዳምጣቸው በማለት የገለጹ ሲሆን በተለይም ያሉባቸውን ችግሮችን ለመፍታት ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በጋራ በመሆን የተለያዩ ስራዎች እየተሰሩ ይገኛሉ ሲሉ ተናግረዋል።

ለበአሉ መከበር የበኩላቸውን አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት የምስጋና የምስክር ወረቀት እና የግጥም፣መነባነብ፣ችሎችና የስዕል ስራዎችን ሲያቀርቡ ለነበሩ ህፃናት ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።

🙏ኮልፌ ኮሙኒኬሽን

Kolfe education official channel🇪🇹

22 Nov, 12:28


የተማሪዎች ምዝገባን በተመለከተ
በምዝገባ ወቅት Resubmit እንዲያደርጉ ተጠይቀው ነገር ግን ሲስተም ላይ የምዝገባ ፎርማቸው ሳያጠናቅቁ ትምህርት የጀመሩ ተማሪዎች ያሏችሁ ትምህርት ቤቶች በሙሉ ተማሪዎች በአስቸኳይ STATUS ላይ ገብተው Admission ID እንዲሁም በምዝገባ ወቅት የተጠቀሙትን ስልክ በማስገባ Re-Apply የሚለውን አማራጭ ተጠቅመው የምዝገባ ፎርማቸው አጠናቀው እንዲያስገቡ አስገዳጅ መመሪያ እንድትሰጡ እየጠየቅን::
የምዝገባ ፎርም ተቀብላችሁ የማፅደቅ ስራ ያላጠናቀቃችሁ ትምህርት ቤቶችም እንድታጠናቅቁ እናሳስባለን::
ማሳሰቢያ:-
በትምህርት ቤታችሁ እየተማሩ ያሉ ተማሪዎች በሙሉ በሲስተም መመዝገባቸውን ያረጋግጡ::

Kolfe education official channel🇪🇹

22 Nov, 06:15


የማለዳ የሰራተኞች የዕውቀት ሽግግር መርሀ ግብር ተካሄደ፡፡

ህዳር 13/2017 ዓ.ም

በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የትምህርት ጽ/ቤት ማለዳ ከስራ ሰዓት መግቢያ በፊት የሚያዘጋጀው የሰራተኞች የእውቀት ሽግግር መርሃ ግብር በክፍለ ከተማው ትምህርት ጽ/ቤት ሠራተኞች የእርስ በርስ የውቀት ልውውጥ መርሃ-ግብር ማድረግ ችለዋል።

የእለቱን የምርጥ የእውቀት ሽግግር ሠነድ ገለፃ ያቀረቡት አቶ ፀጋዬ ተስፋዬ በትምህርት ሊደርሽብ አፕሮች ዙሪያ በተግባር ተሰርቶ የተገኙ ልምዶችን በተቋማቶቻችን እንዴት እንተግብረው በሚል ለውይይት አቅርበው ሠፊ ውይይት ተደርጎበታል።

በመርሃ ግብሩ ማጠቃለያ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የክፍለ ከተማው የሥራ አስተባባሪ የሆኑት አቶ ሠይፈሚካኤል ባርጠማ ይህ መርሃ ግብር አንዳችን ለአንዳችን ያለንን መልካም ተሞክሮ ልምድ የምንለዋወጥበት መድረክ ስለሆነ ሁሉም ሠራተኛ በየሳምንቱ በንቃት መሳተፍ ይጠበቅበታል ብለዋል።

Kolfe education official channel🇪🇹

21 Nov, 14:29


#አስተዳደሩ_የመልካም_አስተዳደር_ጥያቄዎችን ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በጋራና በቅንጅት ፈጣን ምላሽ ለመስጠት የሚያደርገውን ርብርብ አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል።አቶ ገነነ ዘውዴ
የኮ/ቀ/ክ/ከተማ ትምህርት ፅ/ቤት ሀላፊ

ህዳር 12/2017ዓ.ም

የኮ/ቀ/ክ/ከተማ ወረዳ 09 አስተዳደር ከአዲስ አበባ ዉሃና ፍሳሽ መካኒሳ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ጋር በጋራ በመሆን በትንቢተ ኤርሚያስ ት/ቤት የከርሰ ምድር ዉሃ የጉድጓድ ቁፋሮ ተጠናክሮ ቀጥሏል።

የኮ/ቀ/ክ/ከተማ ትምህርት ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ገነነ ዘውዴ፣የኮ/ቀ/ክ/ከተማ ወረዳ 09 አስተዳደር ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ተስፋዬ ምስጋናው፣ የወረዳው አመራሮች ፕሮጀክቱ ያለበትን ሁኔታ ድንገተኛ ምልከታ በዛሬው እለት አድርገዋል።

ፕሮጀክቱ 400 ሜትር ጥልቀት ያለው ሲሆን አጠናቆ በአጭር ጊዜ አገልግሎት ለማስጀመር በእቅድ ተይዟል፡፡

ፕሮጀክቱ የዉሃ አቅርቦት ችግርን በትንቢተ ኤርሚያስ ት/ቤት እና የአካባቢውን ነዋሪ ችግር በዘላቂነት የሚፈታ ፕሮጀክት ነው ሲሆን በቅርቡ ተጠናቆ አገልግሎት እንደሚጀምር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

ፕሮጀክቱ በአጭር ጊዜ ተጠናቆ የማህበረሰቡን የመልካም አስተዳደር ጥያቄ እንዲፈታና ለማህበረሰቡ ፈጣን ምላሽ መስጠት እንዲያስችል የወረዳው ስራ አስኪያጅ ፅ/ቤትና ትምህርት ፅ/ቤት ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር የቅርብ ድጋፍና ክትትል እያደረጉ ነው።

🙏ኮልፌ ወረዳ 09 ኮሚዩኒኬሽን

Kolfe education official channel🇪🇹

15 Nov, 09:07


ቀን 06/03/2017 ዓ.ም
የስብሰባ ጥሪ
ቅድመ 1ኛ ላላቸው የመንግስት 1ኛ ደረጃ ት/ቤቶች ዋና ር/መ/ር
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ት/ቢሮ የቀዳማይ ልጅነትና ዘርፈ ብዙ ጉዳዮች ትግበራ ዳይሬክቶሬት ቅዳሜ በ7/03/2017 ዓ.ም ቅድመ 1ኛ ደረጃ ያላቸውን የ1ኛ ደረጃ ት/ቤቶች ዋና ር/መ/ር ሰብሰባ ስለጠራ በዕለቱ ጠዋት 2፡00 ላይ ፒያሳ አድዋ ዜሮ ዜሮ እንድትገኙ ጥሪ እናስተላልፋለን፡፡

Kolfe education official channel🇪🇹

14 Nov, 02:29


አስቸኳይ ማስታወቂያ
በመምህራንና የትምህርት አመራር ሙያ የጹኁፍ ምዘና ቅሬታ ላቀረባችሁ መምህራን በሙሉ
ከታች የተገለጹት የትምህርት ዓይነት ለ05/03/2017 ዓ.ም ቅሬታው ስለሚታይ 2፡30  ትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን መስሪያ ቤት 5ኛ ፎቅ እንድትገኙ እናሳስባለን
1.  አማረኛ
2.  እንግሊዘኛ
3.  ሂሳብ
አድራሻ ፡- አራት ኪሎ ሲፒዩ ኮሌጅ ፊትለፊት /ብርሃንና ሰላም አጠገብ/አራዳ ክፍለ ከተማ ወደ አራት ኪሎ አለፍ ብሎ

Kolfe education official channel🇪🇹

13 Nov, 03:22


Sadaasa 03,2017 Mana Barumsa Jeneraal Waaqoo Guutuu Sad.1ffaa Lakk.3tti Ayyaanni Sabaaf- Sablammootaa yeroo 19 ffaan kabajamaa oolera. Ayyanichis Sagantaa Gaafii fi Deebiin fi sagantaalee biroon dabaalamuun bakka hojjattoonni fi barattoonni mana barumsichaa argamanitti haala hoo'aan kabajameera.
ህዳር 03,2017ዓ.ም በጀነራል ዋቆ ጉቱ ቁ.3 አንደኛ ደረጃ ት/ቤት የብሔር፤ብሄረሰቦች በዓል በድምቀት ተከብሮ ዉሏል። ለ19ኛ ጊዜ የሚከበረው ይህ በዓል በተማሪዎች ጥያቄና መልስ ውድድር እና በሌሎች ትዕይንቶች የት/ቤቱ ሰራተኞችና ተማሪዎች በተገኙበት ተከብሮአል።

Kolfe education official channel🇪🇹

12 Nov, 07:52


ለሁሉም የማህደረ ተግባር ያልተመዘናችሁ ተመዛኝ መምህራን /ርሳነ መምህራን
1. ሁሉም የትምህርት ዓይነት ረቡዕ((04/03/2017 ዓ፣ም)ከጠዋቱ 2፡00 ጀምሮ በአየር ጤና ሁለተኛ ደረጃ በመሆኑ እንድትመዘኑ
2. የሰንፍላወርና የጀሞ ቁ፣2 የመጀመሪያ ደረጃ(የተዘጉ በመሆኑ) ተመዛኞች መረጃ ጠፍቷል ተቃጥሎል ባሉት መሰረት ለሚመለከተው አካላት በማሳወቅ በ2017 ሁሉንም መረጃ እስከደረሱበት አቅርበው እንዲመዘኑ የተወሰነ መሆኑን እንገልጻለን

Kolfe education official channel🇪🇹

10 Nov, 07:19


መምህርት ሳሮን ገብረማርያም የቀራኒዮ መድኃኔዓለም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህርት፣

Kolfe education official channel🇪🇹

09 Nov, 11:58


የተማሪዎች ውጤት ለማሻሻል ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ የክፍለ ከተማው ትምህርት ፅህፈት ቤት አስታወቀ።

ጥቅምት 30/2017 ዓ.ም

የክፍለ ከተማው ትምህርት ፅ/ቤት አሳታፊ የማስተማር ስነ -ዘዴ ላይ ትኩረት በማድረግ የኢንግሊዘኛና ሒሳብ ትምህርት አይነቶች ውጤት ለማሻሻል ታሳቢ ተደርጎ በተዘጋጀው ስልጠና ለሒሳብና እንግሊዝኛ መምህራን፣ለርዕሳነ መምህራን ፣ከክፍለ ከተማና ከወረዳ የተውጣጡ የትምህርት አመራርና ባለሙያዎች በተገኙበት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጥቷል ።

ስልጠናውን ያስጀመሩት የክፍለ ከተማው ትምህርት ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ገነነ ዘውዴ መንግስት ሰላማዊ የመማር ማስተማር በማስፈን ተከታታይነት ያለው የተማሪዎች የውጤት ትንተና በመስራት ከመደገፍ ባሻገር የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናዎች እያዘጋጀ መሆኑን ተናግረዋል ።

ሀላፊው አክለውም ኢንግሊዘኛ እና የሒሳብ ትምህርት አይነቶች ላይ የተማሪዎች ውጤት ማሻሻል ሀገራዊና አለም አቀፋዊ ፋይዳቸው የጎላ በመሆኑ የውጤት ማሻሻያ ስትራቴጂው ላይ ያገኛችሁትን ግንዛቤ በየትምህርት ቤታችሁ ተግባራዊ በማድረግ ተጨባጭ ውጤት እንዲመጣ በከፍተኛ ርብርብ መስራት ይገባል ሲሉ መልዐሰክታቸውን አስተላልፈዋል ።

@via፦ኮልፌ ኮሚኒኬሽን

Kolfe education official channel🇪🇹

08 Nov, 16:49


የትምህርት ቤቶች
መዋቅራዊ አደረጃጀት ጥናት
FINAL SCHOOL NEW STRUCTURE 21 11 2015.doc

Kolfe education official channel🇪🇹

08 Nov, 13:23


29/2/2017

   ማስታወቂያ
ለሁሉም የመንግስት 1ኛና 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች፤
በቀን 30/2/2017 ዓ/ም በወይራ 1ኛ ደረጃ ት/ቤት  በሰላማዊ መማር ማስተማር ስነዘዴ ላይ  በሚሰጠዉ ስልጠና በከተማ ደረጃ ከተዘጋው ስልጠና ጋር  የተጋጨ መሆኑ ታዉቆ መገኘት የማይችል አካል ት/ቤቱ ተወካይ መላክ የሚችል መሆኑን እናሳውቃን፡፡
                    ጽ/ቤቱ

Kolfe education official channel🇪🇹

08 Nov, 10:20


ለኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ 
2ኛ ደረጃ ት/ጽ/ቤቶች
አዲስ አበባ

ጉዳዩ፡-የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል አከባበር ዝግጅት እንድታደርጉ ማሳወቅን ይመለከታል፡፡

ከለይ በርዕሱ እነደተጠቀሰዉ የትምህርት ማሕበረሰብ ለበዓሉ ስኬት ቁልፊ ሚና አለዉ፡፡ በመሆኑም19ኛው የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል  ’’ሀገራዊ መግባባት ለህብረ ብሄራዊ አንድነት’’ በሚል መሪ ሃሳብ በቅርቡ እንደሚከበር ይታወቃል፡፡ ስለዚህም አስፈለግዉን ቅድመ ዝግጂት በት/ቤቶች ደረጃ ማካሄድ ተፈልገዋል፡፡ በክፍለ ከተማዉ የትምህርት ተቋማት የጥያቄና መልስ ውድድር ከህዳር 4-5/3/2017 የሚካሄድ ሲሆን በከተማ ደረጃ ከህዳር 15-25/2017 ይሆናል፡፡
ሰለዘህ በክፍለ ከተማችን የምትገኙ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች ትኩረት ሰታችዉ እንድትሰሩና ጊዜዉን ጠብቃችዉ የስራ ክንዉን ሪፖርት እነድታደርጉ በጥብቅ እናሳዉቃለን፡፡
ማሳሳቢያ፡ 
የበዓሉ አከባበር  በጥያቄና መልስ ውድድር ብቻ ሳይሆን በትምህርት ቤቶችደረጃ-
•  አገራዊ አንድነትን በሚያጠናክር መልኩ የፌዴራልዚምና የህገ መንግስት አስተምሮ ሥራዎች በሰፊው ይከናወናል፡፡
•  የህዝብ ለህዝብ ግንኙነቶች፣ ትስስርና አንድነት የሚያጠናክሩ እንዲሁም የብሄሮች፤ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቱባ ባህሎቻቸው፤ እሴቶቻቸው የሚተዋወቅበት መድረክ ይፈጠራል፡፡
በዉጤታማ የህዝብ ግንኑነት የታጀበ የገጽታ ግንባታ ስራ ይሰራል፡፡

ከሰላምታ ጋር

Kolfe education official channel🇪🇹

08 Nov, 09:25


Photo from Genene Zed

Kolfe education official channel🇪🇹

07 Nov, 13:13


በሒሳብና እንግሊዘኛ የትምህርት አይነቶች የተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ፡፡

ቀን ጥቅምት 28/2017 ዓ.ም

በሒሳብና እንግሊዘኛ የትምህርት አይነቶች የተማሪዎን ውጤት ለማሻሻል የወረዳ ት/ጽ/ቤት ኃላፊዎች፣የመንግስት አንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ዋና ር/መ/ራን ፣የአንደኛ እና የ2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች ክላስተር አስተባባሪ ሱፐርቫይዘሮች :የ2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች የቋንቋ እና የተፈጥሮ ሳይንስ ሱፐርቫይዘሮች ተሳትፊ በሆኑበት መድረክ 2016 ዓ.ም የእንግሊዘኛ እና ሒሳብ ትምህርት ውጤት ትንተና፣የድጋፍና ከትትል ግብረ-መልስ እንዲሁም የ2017 በጀት ዓመት የተማሪዎች ውጤት ማሻሻያ መደገፊያ፣መከታተያ እና መገምገሚያ ሰነድ ዙሪያ ውይይት ተደርጓ፡፡

በመርሃ-ግብሩ የተገኙት የክፍለ ከተማው ትምህርት ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ገነነ ዘውዴ ባስተላለፉት መልዕክት የሒሳብ እና እንግሊዘኛ ትምህርት የተማሪዎች ውጤት ለማሻሻል መንግሰት በከፍተኛ ትኩረት እየሰራ ይገኛል፡፡በመሆኑም ሁሉም የትምህርት አመራር፣መምህሩ እና ወላጁ የጋራ ግብ ይዘው መስራት ይኖርባቸዋል፡፡ኃላፊው አክለውም ሁሉም የትምህርት አመራር በቀጣይ በየተቋሙ ውጤታማ የሚያደርጉ ስልቶችን ቀይሶ ተግባራዊ ማድረግ ይገባዋል ብለዋል፡፡

Kolfe education official channel🇪🇹

01 Nov, 16:57


አስቸኳይ ማስታወቂያ
ለመንግስት ት/ቤቶች  በሙሉ

ከላይ በቅፁ ላይ ስማቸው የተዘረዘረው የአማርኛ እና አፋንኦሮሞ ቋንቋ  መምህራን ነገ ቀን 23/02/2017ዓ.ም  በኮተቤ ዩኒቨርስቲ  በሚሰጠው ስልጠና  2:00 ሰዓት ላይ እንዲገኙ መልህክት እንዲተላለፍ  ስንል  እናሳውቃለን ።
$ የስራ እና ተግባር ትምህርት ሰልጣኞች ቅዳሜ እና እሁድ በዳግማዊ ሚኒሊክ 2ኛ ደረጃ መሆኑን እናሳስባለን ።

Kolfe education official channel🇪🇹

01 Nov, 08:42


የማለዳ የሰራተኞች የዕውቀት ሽግግር መርሀ ግብር ተካሄደ፡፡

ጥቅምት 22/2017 ዓ.ም

በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የትምህርት ጽ/ቤት ማለዳ ከስራ ሰዓት መግቢያ በፊት የሚያዘጋጀው የሰራተኞች የእውቀት ሽግግር መርሃ ግብር የክፍለ ከተማው ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ገነነ ዘውዴ በተገኙበት ተካሂዷል።

በመርሃ ግብሩ የማለዳ የሠራተኞች የእውቀት ሽግግርን አስሠልክቶ ተሞክሯቸውን እና በሥራ ባህሪያቸው ያስተዋሉትን ያቀረቡት አቶ ምንይችል አዱኛ በሒሳብ እና እንግሊዘኛ ትምህርት ውጤት ለማሻሻል የአራትዮ ስምምነት አተገበባበር የሚያስገኘውን ፋይዳና ተግዳሮቶች በዝርዝር አቅርበዋል፡፡አቅራቢው እንዳስረዱት በሁለቱ ትምህርቶች ውጤት ማምጣት የሚቻለው በትምህርት ቤቶች ተግባራዊ ተደርጎ በስራ ላይ የዋለው የተማሪ፣መምህር፣ወላጅና ርዕሰ መምህር (4ዮሽ)ውል በተገቢው እና በትክክል መተግበር ሲችል እና ያስገኘው ውጤት በወቅቱ መገምገም ሲቻል ነው ብለዋል፡፡

የትምህርት ፅ/ቤት የሱፐርቪዥን፣ትምህርት ቤት መሻሻል፣መመምህራን ልማት እና ልዩ ፍላጎት ቡድኖች አስተባባሪ የሆኑት አቶ ሰይፈሚካኤል ባርጠማ በክፍለ ከተማችን ብሎም በከተማ ደረጃ ስትራቴጂክ እቅድ በማቀድ የሒሳብን እና እንግሊዘኛ ትምህርት ውጤት የላቀ እንዲሆን ጥረት እየተደረገ ይገኛል፡፡ሆኖም ይህ እቅድ ወደ ውጤት እንዲቀየር የትምህርት ባለሙያው ፣ሱፐርቫይዘሮች ጨምሮ ሁሉም የትምህርት ማህበረሰብ በጋራ ርብርብ ማድረግ አስፈላጊ ነው ብለዋል፡፡

በመድረኩ ማጠቃላያ ላይ ተገኝተው አጭር መልዕክት ያስተላለፉት የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ ገነነ ዘውዴ የማለዳ የእውቀት ሽግግር መርሃ- ግብር ዋነኛ አለማው ያለንን እምቅት ፣ ችሎታ እና ልምድ በማስፋት ወደ ተግባር በመቀየር በተማሪዎች ውጤት የሚታይ ለውጥ ማምጣት ይጠበቅብናል ብለዋል፡፡

Kolfe education official channel🇪🇹

31 Oct, 17:48


የአየር ጤና አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች የደምልገሳ መርሃ ግብር አደረጉ።

ቀን ጥቅምት 21/2017 ዓ.ም

"ከስጦታዎች ሁሉ የላቀውን ሥጦታ ደምን መለገስ ነው በሚል መሪ ቃል ከ425 በላይ የሚሆኑ ተማሪዎች የደም ልገሳ መርሃ ግብር አካሂደዋል።

ተማሪዎቹ ያደረጉት በጎ ተግባር በመሰል የትምህርት ተቋማት መደረግ እንደሚገባው አውስተው በቀጣይም ይህኑ በጎ ተግባር አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል።

Kolfe education official channel🇪🇹

31 Oct, 08:30


አስቸኳይ ማስታወቂያ
----------------------------
ለመንግስት ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች በሙሉ
1ኛ . ከት/ቢሮ ተቀጥረው ለእኛ የተላኩ እና በየት/ቤቱ የተመደቡ አዲስ የCTE መምህራን እና የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ት/ት ፅ/ቤት አወዳድሮ በየት/ቤቱ የተመደቡ የCTE መምህራን በሙሉ ቅዳሜና እሁድ ቀን (23-24/02/17) በዳግማዊ ሚኒሊክ 2ኛ ደረጃ ት/ት ቤት ስልጠና ስለሚሰጥ በስልጠናው እንዲሳተፉ ት/ት ቤቱ መልእክት እንዲያስተላልፍ አናሳውቃለን።
2ኛ. አማርኛ እና አፋን ኦሮሞን እንደ 2ኛ ቋንቋ  እያስተማሩ ያሉ እና ዝርዝራቸው ወደ እኛ የተላኩ መምህራን ደግሞ ቅዳሜና እሁድ (23-24/02/17) በኮተቤ ት/ት ዩኒቨርሲቲ ስልጠና ስለሚሰጥ መልእክቱ ከዛሬ ጀምሮ ተጠናክሮ ይተላለፍ።

Kolfe education official channel🇪🇹

31 Oct, 06:32


ቀን 21/2/ 2017
Guyyaa

የሰላም በር ቅድመ አንደኛ ፣ የመጀመሪያ ደረጃና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት የ መምህራን እና የተማሪዎች የአካል እንቅሰቃሴ በፎቶ

Mana Barumsa Salaam Barrii Sadarkaa Tokkoffaa durraa, sadarkaa tokkoffaa fi jiddu galeessatti Sochii qaamaa barsiisotaafi barattootan hojjataman suuraadhaan

Kolfe education official channel🇪🇹

27 Oct, 09:11


ለሁሉም የማህደረ ተግባር መዛኝ፣ ተመዛኝ ሱፐር ቫይዘር እና የምዘና ጣቢያ የተመረጣችጡ ትምህርት ቤት አመራሮች
1. ምዘናው የሚጀምርበት ቀን በ18/02/2017 ዓ.ም
2. የጠዋት ምዘና የሚጀምርበት ሰዓት 2፡30
3. የተመዛኝ መዛኝ እና ሱፕር ቫይዘር መግቢያ ሰዓት 2፡00
4. ከሰዓት ምዘና የሚጀመርበት 7፡30
5. ምዘናው የሚሰጠው የየትምህርት ዓይነቱ በተጠቀሰው ምዘና ጣቢያ መሆኑ
6. የማህደረ ተግባር ምዘና የሚመዘን ውጤቱ 62.5 እና በላይ ያመጣ ሲሆን በድምር ስህተቱ ማስተካከያ ተደርጎ መስፈርቱን ካሟሉ ይመዘናሉ
7. በቀን18/02/2017 ዓ.ም ለጊዜው መዛኝ የሌላቸው የትምህርት ዓይነቶች
i. Environmental science/affan oromo
ii. ሙዚቃ (አማረኛ)
iii. አርት(አማረኛ)
iv. ቋንቋ
v. Special need education መዛኝ ሲስተካከል ፕሮገራሙን እናሳውቃለን።


@ የኮልፌ ሬጉራቶሪ ኤጀንሲ ቢሮ

Kolfe education official channel🇪🇹

26 Oct, 18:58


የኮልፌ ቀራኒዮ ክ/ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት እና የክ/ህብረተሰብ ተሳትፎ ጽ/ቤት  ከጤግሮስ ትሬዲን የግል ህበረት ስራ ማህበር ጋር በመተባበር ላቅመ ደካሞች ነፃ ህክምና ተደረገ።

ቀን 16/2/2016 ዓ.ም

ማህበሩ ከዚህ ቀደም በክፍለ ከተማችን እና በከተማችን የሚገኙ የትምህርት ማህበረሰብን በረጂም አመት በሚከፈል ብድር አገልግሎት የኤሌክትሪክ መኪና ባለቤት ማድረጉ ይታወሳል።
አሁን ደግሞ 50 የክፍለ ከተማችን አቅመ ደካማ ነዋሪዎችን በቻይና ሀኪሞች የነፃ ህክምና እንዲያገኙ የክፍለ ከተማው ትምህርት ጽ/ቤት እና የህብረተሰብ ተሳትፎ ጽ/ቤት በጋራ በመሆን ተሰጥቷል ።

ይህ በጎ ተግባር እንዲሳካ ጥረት ያደረጉትን አቶ ማስቻል በቀለ የረጲ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ዋና ር/መምህር ጽ/ቤቱ ምስጋናው አቅርቧል ።

Kolfe education official channel🇪🇹

26 Oct, 16:19


የ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የተማሪዎች ምዝገባ ከጥቅምት 15/ 2017 ዓ.ም ጀምሮ የቆመ መሆኑ ተገለፀ።

Kolfe education official channel🇪🇹

25 Oct, 13:14


የሥልጠና ጥሪ
ቀን ጥቅምት 15/2017 ዓ.ም
በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ሥር ለምትገኙ የመንግስት አንደኛ ደረጃ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በሙሉ፣
የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ የቀዳማይ ልጅነትና ዘርፈ ብዙ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት በቀን 16/02/2017 ዓ.ም ስልጠና ይሠታል፡፡በመሆኑም ከሁሉም ትምህርት ቤቶች የሚሳተፉ
👉🏿የትምህርት ቤት መሻሻል ምክትል ር/መምህር=1
👉🏿የጠየና ክበብ ተጠሪ መምህር=1
👉🏿የሥልጠና ቀን 16/02/2017 ዓ.ም
🫱🏿ቦታ ትምህርት ቢሮ ካፌ አዳራሽ
ሠዓት ከጠዋቱ 2፡30

Kolfe education official channel🇪🇹

25 Oct, 11:57


በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የብሔራዊ መታወቂያ (ፋይዳ) ምዝገባን አስመልክቶ  ከርዕሰ መምህራን ጋር ውይይት ተካሔደ። 

ጥቅምት 15/2017 ዓ.ም

የክፍለ ከተማው  አስተዳደር  ሥር ከሚገኙ ርዕሰ መምህራን   ፤ የሃይማኖት አባቶች እና   ሌሎች ባለድርሻ አካላት  በተገኙበት የብሔራዊ መታወቂያ (ፋይዳ) ምዝገባን አስመልክቶ ምክክር አካሂዷል፡፡

በክፍለ ከተማው የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ምክትልና የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አቶ አለማየሁ ፍቃዱ እንዳሉት የብሔራዊ መታወቂያ (ፋይዳ) ምዝገባ ለዲጂታል ኢኮኖሚ እየገነባነው ላለው ሂደት አስፈላጊ እንደሆነ የገለፁ ሲሆን የመረጃ ችግሮችን  በመፍታት እና አገልግሎቶችን በማስተሳሰር የተገልጋዮችን ጊዜ ለመቀነስ ሚና እንዳለው አስገንዝበዋል፡፡
አቶ አለማየሁ ጨምረው ብሔራዊ መታወቂያ ምዝገባ(ፋይዳ)  በትምህርት ቤቶች በሚማሩ ተማሪዎች ጭምር ተግባራዊ ስልሚደረግ  የትምህርት አመራሩ አስፈላጊውን ትብብር እና ድጋፍ ማድረግ ይገባዋል ብለዋል፡፡
የክፍለ ከተማው ስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዳኛቸው አበበ በበኩላቸው ብሔራዊ መታወቂያ(ፋይዳ)  ማህበረሰቡን የሚጠቅም፤ለሌሎች ስራዎች አጋዥ በመሆኑ ማህበረሰቡ በተዘጋጁ ቦታዎች በመገኘት ያለምንም እንግልት   ምዝገባ ማካሄድ እንደሚችል ገልፀዋል፡፡

@ Via:-ኮልፌ ኮሙኒኬሽን

Kolfe education official channel🇪🇹

25 Oct, 11:23


ማስታወቂያ
ዛሬ ልንሰራ የነበረው የቅ/መደበኛ መምህራን ምደባ ስማችሁ ስላልመጣ ሰኞ የምንመድባችሁ መሆኑን እናሳውቃለን ።

Kolfe education official channel🇪🇹

25 Oct, 11:13


የሥልጠና ጥሪ
ቀን ጥቅምት 15/2017 ዓ.ም
በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ሥር ለምትገኙ የመንግስት አንደኛ ደረጃ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በሙሉ፣
የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ የቀዳማይ ልጅነትና ዘርፈ ብዙ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት በቀን 16/02/2017 ዓ.ም ስልጠና ይሠታል፡፡በመሆኑም ከሁሉም ትምህርት ቤቶች የሚሳተፉ
👉🏿የትምህርት ቤት መሻሻል ምክትል ር/መምህር=1
👉🏿የጠየና ክበብ ተጠሪ መምህር=1
👉🏿የሥልጠና ቀን 16/02/2017 ዓ.ም
🫱🏿ቦታ ትምህርት ቢሮ ካፌ አዳራሽ
ሠዓት ከጠዋቱ 2፡30