Higher 12 Secondary & Preparatory School.

@wondale


Online teaching

Higher 12 Secondary & Preparatory School.

21 Oct, 16:23


ለ12ኛ ክፍል ለጨረሡ

Higher 12 Secondary & Preparatory School.

08 Oct, 19:30


የአቅም ማሻሻያ (ሬሜዲያል) ፕሮግራም ለመከታተል የሚያስችለው የመቁረጫ ነጥብ ስንት ነው ?

በመንግስት ተቋማት ወጪያቸው በመንግስት ተሸፍኖ የሪሚዲያል ፕሮግራም የሚከታተሉ ተማሪዎችን የመቁረጫ ነጥብ ፦

➡️ በተፈጥሮ ሳይንስ እና በማህበራዊ ሳይንስ የወንድ ተማሪዎች የሬሜዲያል የመግቢያ ውጤት ከ600ው 204 ነው።

➡️ በተፈጥሮ ሳይንስ እና በማህበራዊ ሳይንስ የሴት ተማሪዎች የሬሜዲያል የመግቢያ ውጤት ከ600ው 192 ሆኖ ተቆርጧል።

(ተጨማሪ የመቁረጫ ነጥብ ከላይ ተያይዟል)

ከዚህ ባለፈ ግን እንደተፈተኑት የትምህርት አይነት ብዛት 31% ከመቶና ከዚያ በላይ ውጤት ያመጡ ተማሪዎች በሁሉም አማራጮች (በግልና በመንግስት ተቋማት) በራሳቸው ክፍያ የሪሚዲያል ፕሮግራም መከታተል ይችላሉ።

ይህ ማለት ፦

➡️ ከ600ው የትምህርት ብዛት ፈተናቸውን ተፈትነው 31% እና ከዛ በላይ ውጤት ያመጡ (186 እና በላይ) ፤

ከ500 የትምህርት ብዛት የተፈተኑ (ዓይነስውራን ተማሪዎች) 31% እና በላይ ውጤት ያመጡ (155 እና በላይ) ፤

ከ700ው የትምህርት ብዛት የተፈተኑ 31% እና ከዛ በላይ ውጤት ያመጡ (217 እና በላይ) ... በፈለጉት አማራጭ ማለትም በግል ሆነ በመንግሥት ተቋማት ከፍለው የሬሜዲያል ፕሮግራም መከታተል ይችላሉ።

በ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና #በቀጥታ የሚያሳልፈው ውጤት 50% እና በላይ መሆኑ ይታወቃል።

የሬሜዲያል ፕሮግራም መቁረጫ ነጥብ (በመንግሥት ስፖንሰርሺፕ / ተመድቦ ለመማር) ከላይ በምስሉ ላይ ተያይዟል።

በግል ከፍለው በመንግሥትም ይሁን በግል ተቋም ለመማር የሚፈልጉ ከተፈተኑት ፈተና ውጤት 31% እና በላይ ውጤት ማምጣት አለባቸው።

@tikvahethiopia

Higher 12 Secondary & Preparatory School.

27 Sep, 06:42


Amen

Higher 12 Secondary & Preparatory School.

18 Sep, 04:09


ቀን 07/01/2017 ዓ.ም
                                                      አስቸኳይ ማስታወቂያ
     ለት/ቤታችን ተማሪዎች በሙሉ
የ2017 ዓ.ም መደበኛ ትምህርት እንደተጀመረ ይታወቀል፡፡ ይሁንና ዛሬ ማክሰኞ ባደረግነው ቁጥጥር የተስተዋሉ ክፍተቶች አስተካክላችሁ እንድትመጡ እያሳሰብን ነገ ረቡዕ በ08/07/2017 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ት/ቤት ቅጥር ግቢ ስትመጡ፡-
1.ነባርም ሆነ አዲስ ተማሪዎች ከዚህ በፊት የምትለብሱትን ዩኒፎርም መልበስ የግድ መሆኑን፤
2.ማንኛውም ተማሪ ትክክለኛ አለባበስና የፀጉር ሁኔታ አስተካክሎ መምጣት የግድ መሆኑን፡፡
3.ሴት ተማሪዎች ሱሪ ለብሶ መምጣት፤ ወንዶች ደግሞ ፀጉር ሳይስተካከሉ መምጣት የማይቻል መሆኑን፤
4.ማንኛውም ተማሪ በሁሉም የት/ት ቀናት ጠዋት እስከ 2፡10ድረስ ት/ቤት ቀጥር ግቢ ተጠናቆ መግባት ግዴታ መሆኑን፤
5.ማንኛውም ተማሪ በየትኛውም የት/ት ቀናት ከ2፡30 በኋላ የት/ቤቱ ቅጥር ግቢ በር ለተማሪ ዝግ የሚሆንበት ስለሚሆን ተማሪ የማናስገባ መሆኑን አውቆ ቀድሞ እንዲገኝ በር አካባቢ ላላስፈላጊ እንግልት እንዳይዳረግ ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ፡፡
6.የቀኑን ሙሉ ት/ት የጀመርን በመሆኑ ምሳ ይዛችሁ እንድትመጡ እና ምሳ አልያዝንም ብሎ መውጣት እንደማይቻል እንድታውቁ፡፡
7.በየትኛውም ሰዓት ድንገተኛ ፍተሻ ሊደረግ ስለሚችል በየትኛውም ቀን ሞባይል መያዝ የተከለከለ መሆኑን፤
8.ደብተር/የግል ማስታወሻ ሳይዙ መምጣት የተከለከለ መሆኑን አጥብቀን እናሳስባለን፡፡
                                              ት/ቤቱ

Higher 12 Secondary & Preparatory School.

17 Sep, 10:28


ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) በፕሮፌሰር በየነ ህልፈተ ህይወት የተሰማቸውን ሀዘን ገልጸዋል።

ፕሮፌሰር በየነ ረዘም ላለ ጊዜ በህክምና ሲረዱ ቆይተው ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸውንም ጠቁመዋል።

" በኢትዮዽያ ገንቢ የፖለቲካ ባህል ለመፍጠር ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያበረከቱ የሰላማዊ የፖለቲካ ትግል ምልክት ነበሩ " ሲሉም ገልጸዋል። 

@tikvahethiopia

Higher 12 Secondary & Preparatory School.

17 Sep, 09:04


Tentative period distribution 2017 E.C.