✞ ፀሐየ ጽድቅ ✞ @tsehaye_tsidk Channel on Telegram

✞ ፀሐየ ጽድቅ ✞

✞ ፀሐየ ጽድቅ ✞
👉ፀሐየ ጽድቅ
የሕይወት መብራት የጽድቅ ብርሃን

በዚህ channel ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን የጠበቁ ትምህርቶች እና መዝሙሮች እንዲሁም ቅዱሳንን እንዘክራለን ስለቅዱሳን እንማማራለን ዕለታዊ ዜና ቤተ-ክርስቲያ ስንክሳር ግጻዌ ጥያቄና መልስ እንዲሁም በየእለቱ አጥንትን የሚያጠነክሩ መንፈስን የሚያለመልሙ ጽሁፎችን ወደ እናንተ እናደርሳለን፡፡
ቻናሉን ይቀላቀሉ
@Tsehaye_Tsidk
ሼር ያርጉ!!
1,807 Subscribers
816 Photos
7 Videos
Last Updated 06.03.2025 07:56

The Spiritual Significance of Light in Christian Faith

በክርስቲና ዘርፍ መረጃ ሐሳብ እና ዕውቀት የሚያወቃቸው ወደ ዕለታዊ አመራር ይበረከት፡፡ የሕይወት መብራት እና የጽድቅ ብርሃን ቅርጸ እውቀታችንን ይወላቸዋል፡፡ ወቅታዊ ትምህርቶችን ለመለክከት ሁሉም እንደ መዝሙር መዋቅር ይቀላቀሉ፡፡ ወደ ጻዕቅ ማህበረ ክርስቲን ባለሞያ ትምህርት ይነሳል፡፡ የዚህ ተናገር ህብረት ከሚነሳው ወይንም ከምንነ-ርዕይታ እንደ ዚህ ወደ የሆነ ሀሳብ ይወሰድ ይዞረዋል፡፡

ክርስቲን ቤተ ክርስቲያን ነው?

የቤተ ክርስቲያን ፍትሀት ወደ መነሻው ወይንም ወደ መረመር ይቀመጥ፡፡ በዚህ ሀሳብ ውስጥ የቤተ ክርስቲያን በአማርኛ የሚገኝ፡፡

ቤተ ክርስቲያን ወደ አንዳች ቤተ መድኃኒት ይርዳበት፡፡ እንዲህ የሚል ሳይታይ ምን ተቀመጥ፡፡

የክርስቲን መርሐግብር ምንድን ነው?

ከመወርወሪ ራዕይታ ይነወውና ለማሉሲቱ ጉዳይ ወደ ተሕፈሞ አብል፡፡

ለትናንት ዘንቀን ምን ናቸው ይሁን ህይወት በመለኪያ ለማጣራት ባሰፈ ይሁን ይችላል፡፡

መዝሙር ምን ነው?

መዝሙር የቅዱስ መዋቅርና ዝማሬዎች በነዚህ ጊዜ ውስጥ ይኒዳሉ፡፡

መዝሙር ወይም መዝገብ ድንጋዩ አለው፡፡ ይህ በመረመር ውስጥ ይቀመጥና መዝሙር ይወዳደራሉ፡፡

የመንፈሳዊ ዕድል ዋስትና?

አለው በመንፈሳዊ በበነቀ፡፡ ይህ ይለይያል ወይንም ማለት ወምላል፡፡

ወደ አለም ዘይሱ በዘንቀን ይሁን ስለ ይብልም ከላዕለ ሆኖም ይንፈነ ይነቃላል፡፡

ክርስቲናዊ መልስ እንዴት ይሆናል?

ወይ ኢይነማል ወይንነ ወደ ሕይወት ይምሉኤ፡፡ ይህ መረጃ በተለመደ ዕዱ አተርቂ ይቁል፡፡

ይህ ወይንም በዚህ ውስጥ ይምሉ እና ይታይቃል ወይ በመለስ ይነሳል፡፡

✞ ፀሐየ ጽድቅ ✞ Telegram Channel

ምንድን ነው ይህ የቴሌግራም ቻናል ዝግጅት ነው? እንዴት በዚህ ቻናል እንደሚሰሩ ለምን ይህን ጽሁፎች መለየት ይቻላል? ኢትዮጵያን በተመለከተ በዚህ ቻናል ሥርዓት ቤተ ክርስቲያን እና መዝሙሮች እንዲሁም ቅዱሳን እንዘክራለን፡፡ በዚህ ቻናል ተመልክታዊ መረጃዎች ያለን እና ጽሁፍን ለመዋጋት በጣም በእናንተ ላይ እንወዳለን፡፡ ያስተዋወቃል በ@Tsehaye_Tsidk ለመቀላቀል፡፡

✞ ፀሐየ ጽድቅ ✞ Latest Posts

Post image

+ ቅዱስ አጠራር +

ቅዱስ ጳውሎስ ፦ ያዳነን በቅዱስም አጠራር የጠራን እግዚአብሔር ነውና፥ ይህም እንደ ራሱ አሳብና ጸጋ መጠን ነው እንጂ እንደ ሥራችን መጠን አይደለም ሲል ተናገረ፡፡ /2ጢሞ 1፡9/
መጠራትን ሁላችንም ተጠራርተን እናውቃለን፡፡ በጩኸትም በፉጨትም በእጅ ምልክትም በጥሪ ወረቀትም በስልክም ተጠራርተን እናውቃለን:: ቅዱስ አጠራር ግን እንደምን ያለ ነው? እግዚአብሔር ቅዱስ ነውና እርሱ ሰውን የሚጠራበት ጥሪም የተቀደሰ ነው፡፡ ይህ ጥሪ እንደምን ያለ ነው? ቅዱስ ጳውሎስ የእግዚአብሔርን ጥሪ ለምን ቅዱስ አጠራር አለው?

እርሱ ራሱ ከተጠራበት አጠራር እንጀምር ይሆን? ሳውል/ ጳውሎስ ክርስቲያኖችን ሊያስርና ሊያሰቃይ ከበላይ አካል ደብዳቤን ተቀብሎ በደስታ እየቸኮለ ሲሔድ የበላዮች በላይ ደማስቆ ላይ አስቆመውና ጠራው፡፡ ለብዙዎች ሞት ፈቃድ ተቀብሎ ተሹሞ ሲመጣ ጌታ ከመንገድ አስቁሞ ለብዙዎች መዳንን እንዲሰብክ ፈቃድ ሠጠው፡፡ የጦር ዕቃ ጭኖ እየዛተ ሲመለስ ጦርና ጋሻውን አስጥሎ ራሱን ምርጥ ዕቃ አደረገው፡፡ በቅዱስ አጠራር የጠራው እግዚአብሔር ነውና!

ስለ ጴጥሮስ አጠራርስ ምን እንናገር? የሃምሳ አምስት ዓመቱ ዓሣ አጥማጅ ጎልማሳ ፣ ሌሊቱን ሙሉ መረቡን ጥሎ የሚያድረው ትዕግሥተኛ እንዴት እንደተጠራ ልብ በሉ፡፡ ለእርሱ ብዙ ዓሣ ከመያዝ በቀር ምንም ሕልም አልነበረውም፡፡ የታንኳዎቹን ቁጥር ከማብዛት የዓሣዎቹን ገበያ ከማስፋፋት በቀር በጎልማሳ ዕድሜው አዲስ ሕልም አልነበረውም፡፡

የመጦሪያ ዘመኑን እንዴት እንደሚያሳልፍና የዕድሜ ፀሐዩ ስትጠልቅ መረቡን አጥምዶ ለመመልከት ዝግጁ ከመሆን በቀር ምንም አዲስ ዕቅድ አልነበረውም:: ጀልባው ላይ ተሳፍሮ ደግ ደጉን የሚያወራው ናዝራዊ ግን ድንገት መጥቶ ጎልማሳነቱን እንደ ንሥር አደሰው፡፡ ሕይወቱን እንደ አዲስ አሁን እንደተወለደ ሕፃን ከሃምሳ ዓምስት ዓመቱ አስጀመረው፡፡ በዚያ ዕድሜው የሦስት ዓመት መንፈሳዊ ኮሌጅ ገብቶ በእሳትና በነፋስ ታጅቦ ተመርቆ : በሰባ ሁለት ቋንቋ እንደ አዲስ አፉን ፈትቶ እንዲያወራና ዓሣ ማስገሩን እርግፍ አድርጎ ትቶ በወንጌል መረብ ሰውን አጥማጅ እንዲሆን አደረገው፡፡ በድንቅ አጠራሩ የጠራው እግዚአብሔር ነውና!

  ስለ ሐዋርያው ናትናኤልስ እንናገር ይሆን? ጓደኛው ፊልጶስ "የናዝሬቱን ኢየሱስን አገኘነው" ብሎ ሲጠራው ብዙም ደስ አላለውም ነበር፡፡ የናዝሬቱ መሲሕ የሚል ቃል ሲስማ ከይሁዳ ቤተልሔም መሲህ እንደሚመጣ ከሚያውቀው ትንቢት ጋር አልገጥም ብሎት ‘ደግሞ ከናዝሬት መሲህ ይነሣል እንዴ?’ እያለ በምሁራዊ ትዝብት ተውጦ እስቲ ልየው በሚል ንቀት ሳይዋጥለት ነበር የመጣው፡፡ እስቲ ልየው ብሎ ያገኘው ናዝራዊ ግን ራሱን ልቡ ድረስ ተመለከተው፡፡ ሳያውቅ የጠቀሰውን ጥቅስ አስጥሎ የሚያውቀውን የራሱን የተሸሸገ ማንነት  ሲነግረው መቋቋም አልቻለም፡፡ አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ነህ ብሎ መሰከረ፡፡  እርሱ እንደመሰለው የጠራው ጓደኛው ፊልጶስ አልነበረም ፤ በቅዱስ አጠራሩ የጠራው እግዚአብሔር ነውና!

የቀሬናዊው ስምዖን አጠራር ግን ከሁሉ የባሰ ነበር ፤ እርሱ መንገደኛ ነበረ ፤ መንገድ አላፊ እንደሚጣደፍ እየተጣደፈ ነው፡፡ ሰንበት ሳይገባበት ለመጓዝ ከኢየሩሳሌም እየቸኮለ ሲወጣ አንድ ብዙ ሕዝብ አጅቦት ግማሹ በማዘን የሚጮኽለትና ግማሹ በጥላቻ የሚጮኽበት የሕማም ሰው ሲንገላታ ተመለከተ::

መንገዱን ገታ አድርጎ ትንሽ ሊመለከት እንጂ ሊቆይ ሃሳብ አልነበረውም:: ነገር ግን ወታደሮች ግድ አሉት:: ሳያስበው የጌታ የሕማሙ ተካፋይ የመስቀሉ ተከታይ ሆነ:: ዓለም የዳነበትና የጌታ ደምና ወዝ የፈሰሰበትን ቅዱስ መስቀል ተሸክሞ አንድ ምዕራፍ ተጉዋዘ:: ያገዝነው ሲመስለን የሚያግዘንን ያገለገልነው ሲመስለን የሚያከብረንን ክርስቶስን ተጠግቶ መቼም የማይገኝ ክብርን ተጎናጸፈ:: በዚያች ዕለት መስቀሉን ተሸከም ብለው የጠሩት እንደመሰለው ሮማውያን ወታደሮች አልነበሩም:: በቅዱስ አጠራር የጠራው እግዚአብሔር ነውና!

ጌታ ሆይ እኔ ባሪያህን የጠራህበት ቅዱስ አጠራር እንዴት ያለ ይሆን?  ስንቴ ጠርተኸኝ እንዳልሰማ ጥዬ ሔጄ ይሆን? የአንተን ጥሪ ገፍቼ ለዓለም ጥሪ ጉዋጉቼ ስንቴ ሔጄ ይሆን? "አብዝቼ ብጠራቸው አጥብቀው ከፊቴ ራቁ" ካልካቸው መካከል እሆን ይሆን?

እባክህን ባልሰማህም ጥራኝ : ባልመጣም ጥራኝ : ጴጥሮስ በባሕር ላይ እንደለመነህ "ወደ አንተ እመጣ ዘንድ እዘዘኝ" : እንደ አልዓዛር "ውጣ" ብለህ በቅዱስ አጠራር ጥራኝ:: እንደ ማቴዎስ ከቀራጭነት ገበታዬ ላይ : እንደ ዘኬዎስ ከዛፍ ላይ : እንደ ኢትዮጵያዊው ጃንደረባ በሰረገላዬ ላይ ብቻ ባገኘኸኝ ቦታ ጥራኝ::

ሙት በሚቀሰቅስ ማዕበል በሚገሥፅ ድምፅህ ባልሰማህም ጥራኝ : ጆሮዬ አልሰማ ካለህ እንደ ማልኮስ ጆሮ ሠጥተህ አንተን ብቻ በሚሠሙ ጆሮዎች ፈውሰኝና ጥራኝ:: ዓይኔ ዓላይ ካለህ ከአፈር በምራቅህ ለውሰህ እያየሁ እንድመጣ አድርገህም ቢሆን ጥራኝ:: አሁን በቅዱስ አጠራርህ ስትጠራኝ ካልሰማሁህ በኁዋላ ልትፈርድ ስትመጣ "እናንተ የአባቴ ቡሩካን ወደ እኔ ኑ" የሚለው ቅዱስ አጠራርህንም ሳልሰማ መቅረቴ አይደል? አሁን ጥሪህን ካልሰማሁ በኁዋላ ቃለ ሕይወትን አልሰማምና እንደ ሥራዬ ሳይሆን እንደ አንተ አሳብና ጸጋ መጠን ጥራኝ!

"ያዳነን በቅዱስም አጠራር የጠራን እግዚአብሔር ነውና፥ ይህም እንደ ራሱ አሳብና ጸጋ መጠን ነው እንጂ እንደ ሥራችን መጠን አይደለም"

#ዲ/ን _ሄኖክ_ኃይሌ

@Tsehaye_Tsidk
@Tsehaye_Tsidk

03 Mar, 17:28
83
Post image



የዐቢይ ጾምን መግባት ምክንያት በማድረግ የተሰጠ ትምህርት
(በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)


እንግዲህ አሁን ራስን አለመግዛት እንዴት አደገኛ እንደ ኾነ ተገነዘባችሁን? አሁን ደግሞ ጾም እንዴት ያለ በረከትን እንደሚያመጣ እንመልከት፡፡ ሊቀ ነቢያት ሙሴ አርባ ቀን ስለ ጾመ የእግዚአብሔር ሕግ የተጻፈበትን ጽላት ሊቀበል ችሏል /ዘጸ.24፥18/፡፡ ከተራራው ሲወርድ ግን አብዝቶ የሚበላና ኃጢአተኛ የኾነ ሕዝብ የእግዚአብሔርን ሕግ ቢቀበል ምንም ትርጉም የለውም በማለት በብዙ ምልጃ የተቀበለውን ጽላት ከእጁ ጥሎ ከተራራው በታች ሰበረው /ዘጸ.32፥19/፡፡ በመኾኑም፥ ይህ ታላቅ ነቢይ በሕዝቡ ኃጢአት ምክንያት በሰበረው ጽላት ፈንታ እንደ ቀድሞ ያለ ሌላ ጽላት ለመቀበል አርባ ቀንና አርባ ሌሊት መጾም ነበረበት /ዘጸ.34፥28/፡፡ በእሳት ሠረገላ ተነጥቆ ወደ ሰማያት የተወሰደው፣ እስከ ዛሬ ድረስም ሞትን ያልቀመሰው ታላቁ ነቢይ ኤልያስም ልክ እንደ ሙሴ አርባ ቀንና አርባ ሌሊት ጾሟል /1ኛ ነገ.19፥8/፡፡ ልክ እንደዚሁ መንፈሰ ብርቱው ዳንኤልም አያሌ ቀናትን ይጾም ነበር፤ እንደ ሽልማትም እጅግ የሚያስደንቅ ራእይን ተቀብሏል፡- ቍጡዎቹን አንበሶች እንደሚያስለምዳቸው፣ ጥንተ ተፈጥሯቸው ተለውጦ ሳይኾን ከእነ ተናጣቂ ባሕርያቸው እንደ የዋህ በጎች እንደሚኾኑለት ዐየ፡፡ የነነዌ ሰዎችም እንደዚሁ በጾም መድኃኒትነት ከእግዚአብሔር ዘንድም ምሕረትን አግኝቷል፡፡ እንዲያውም በነነዌ የጾሙት ሰዎች ብቻ አልነበሩም፤ እንስሳቱም ጭምር እንጂ፡፡ በዚህም ምክንያት እግዚአብሔር ሊያደርገው ከተናገረው ክፉ ነገር ተጸጽቶ አላደረገውም /ዮና.3፥10/፡፡ ከብሉያትና ከሐዲሳት እንዲህ በመጾማቸው ምክንያት የተጠቀሙ ብዙ ሰዎችን መጥቀስ እንችላለን፤ ነገር ግን የኹላችንም ጌታ ወደ አደረገው መምጣት ሲገባን አገልጋዮቹን የምናየው ለምንድን ነው? እንደምታውቁት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አርባ ቀንና አርባ ሌሊት ጾሟል (ማቴ.4፥2፣ ሉቃ.4፥2)፡፡ ሲጾምም ዲያብሎስን ድል አድርጎ አሳይቶናል፡፡ ይኸውም የጾምን ትጥቅ ልንታጠቅ እንደሚገባንና ከዚህ በምናገኘው ኃይልም ብርቱ የሚኾን ጠላታችንን ድል ማድረግ እንደሚቻለን አርአያ ሲኾነን ነው፡፡

እዚህ ላይ ምናልባት ነገሮችን ጠለቅ አድርጎ የሚመረምርና ሐሳበ ልቡናዉን ንቁ ያደረገ ሰው፡- “ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ልክ እንደ አገልጋዮቹ አንዲት ቀንስ እንኳን ሳይጨምር የጾመው ስለ ምንድን ነው?” ብሎ ጥያቄ ሊያነሣ ይችላል፡፡ ጌታችን ይህንን ያደረገው ያለ ምክንያት ሳይኾን ከጥበቡና ሰውን ከመውደዱ የተነሣ ነው፡፡ ይኸውም፦ “ወደዚህ ምድር የመጣው ሥጋን ሳይለብስ ነው፤ ሰውም የኾነው በምትሐት ነው” ብለው ለሚነሡ ዐብዳን ሐሳባቸውን ይገታ ዘንድ አስቦ ልክ እንደ አገልጋዮቹ አንዲት ቀንስ እንኳን ሳይጨምር ጾመ፡፡ እንግዲህ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንደዚህ በገቢር ጾሞ ሳለ እንኳን እንደዚህ ያለ ምክንያት የሚያመጡ ከኾነ ከቸርነቱ የተነሣ ሊያመጡት የሚችሉትን ሰበብ አስቀድሞ ባይጥለው’ማ እንደ ምን የከፋ ነቀፋን ባመጡ ነበር? በመኾኑም፥ የእኛን ባሕርይ ገንዘብ እንዳደረገና ከእኛ የራቀ እንዳልኾነ ሲያስተምረን ከቀደሙት አባቶች ሳያተርፍ አርባ ቀን ጾመ፡፡

እጅግ የምወዳችሁ ምእመናን ሆይ! የጾም ጥቅምዋ ምን ያህል የበዛ እንደ ኾነና ነፍሳችን ከዚህ ብዙ ጥቅምን እንደምታገኝ ከጌታችን እና ከአገልጋዮቹ ተምረናል፡፡ ስለኾነም የጾም ወራት ሲቃረብ ግድየለሽነትንና ሞራለ ቢስነትን ከእኛ አስወግደን ንዑድ ክቡር የሚኾን ጳውሎስ፡- “የውጭው ሰውነታችን ይበልጥ ሲጠፋ የውስጡ ሰውነታችን ይበልጥ ይታደሳል” ብሎ እንዳስተማረን እጅግ ደስ ተሰኝተን ልንቀበለው ይገባናል ብዬ እማልዳችኋለሁ /2ኛ ቆሮ.4፥16/፡፡ ጾም የነፍስ ምግብ ነው፡፡ ምግበ ሥጋ ሰውነታችን እንዲወፍር እንደሚያደርግ ኹሉ ጾምም ነፍስን ያበረታል፤ ፈጣንና መንፈሳዊ ክንፍን ይሰጣታል፤ ወደ ሰማያዊ ምሥጢር ገብታ በፅሞና እንድትያዝ ያደርጋታል፤ የዚህን ዓለም ተድላና ደስታ እንድትንቅ ያስችላታል፡፡ ቀላል ጭነትን የተሸከሙ መርከቦች ፈጥነው ባሕሩን እንደሚሻገሩ፣ እጅግ ብዙ ጭነትን የተሸከሙት ግን ባሕሩንና ወጀቡን ቶሎ ማለፍ እንደሚያቅታቸው ኹሉ ልክ እንደዚሁ ጾምም ውሳጣዊ ዓይናችን እንዲበራ፣ የዚህ ዓለም ፈተናዎችን በቀላሉ መቋቋም እንድንችል፣ ወደ ሰማያዊ ምሥጢር እንድንገባ በዚያም ስላሉ አይነገሬ በረከቶችን እንድናስብ፣ በዚህ ዓለም ላይ ያሉት ኹሉም ነገሮች እንደ ጠዋት ጤዛ ፈጥነው የሚያልፉ እንደ ኾኑ እንድንገነዘብ ታደርለች፡፡ ከዚሁ በተቃራኒ አብዝቶ መብላትና ራስን አለመግዛት ደግሞ አእምሯችን የጠፋ፣ ሥጋችን የወፈረ፤ ውስጣችን በእግር ብረት የተጠፈረ፣ በዚህ ኹሉ ተከበንም እጅግ በከፉ ምግባራት የተያዝን፣ የዘለዓለማዊ ሕይወታችን ጠላቶች ኾነን እንድንጓዝ ያደርጉናል፡፡

ይቀጥላል....

(ኦሪት ዘፍጥረት ቅጽ 1 ገጽ 23-31 በገብረ እግዚአብሔር ኪደ የተተረጎመ)


@Tsehaye_Tsidk
@Tsehaye_Tsidk

03 Mar, 16:14
88
Post image

#ቅድስት
#የዐቢይ_ጾም_ሁለተኛ_ሳምንት

የቅድስና ባለቤት የሆነው እርሱ እግዚአብሔር አምላክ ነው። እቀደስ አይል ቅዱስ፣ እባረክ አይል ቡሩክ ነው። በእርሱ የባሕርይ ቅድስና እኛን በአርአያውና በአምሳሉ ፈጥሮ ቡሩክ ሆኖ ባረከን፣ ቅዱስ ሆኖ ቀደሰን፣ሕያው ሆኖ ሕያዋን አደረገን። የጸጋ ቅድስናንም ከእርሱ አገኘን። ቅድስናው የተለየ፣ የከበረ፣ የሚመሰገን፣ የሚሰጥ/የሚያድል፣ የሚያነጻ፣ የሚባርክ እናም የሚያስተሰርይ ስለሆነ እንከን፣ ጉድለት የሌለበት ምሉዕ ነው። ለባለሟሎቹ ቢሰጠው የማይጎድል፣ ተከፍሎ የሌለበት ቅድስና ሆኖ እኛም የቅድስና በጸጋ ተካፋይ ሆነናል።

የተሰጠንን ቅድስና ገንዘብ እንድናደርግ እና እንድንጠቀምበት ደግሞ በጾም፣ በጸሎት፣ በስግደት፣ በምጽዋትና በሌሎች በጎ ምግባራት መትጋት ይገባናል። ‹‹እኔ እግዚአብሔር አምላካችሁ ቅዱስ ነኝና እናንተም ቅዱሳን ሁኑ›› እንዲል፡፡ (ዘፍ.፪፥፫፣ ዘሌ.፲፱፥፪) የት መሄድ እንዳለብንም በግልጽ ልበ አምላክ ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ዳዊት ‹‹ወደ ቅዱስ መቅደስህ እሰግዳለሁ፤ ስለ ትምህርትህና ስለ እውነትህ ስምህን አመሰግናለሁ፤ በሁሉ ላይ ቅዱስ ስምህን ከፍ ከፍ አድርገሃልና›› ይላል። (መዝ.፻፴፯÷፪) የተቀደሰን መሥዋዕት በተቀደሰ ቦታ እንፈጽማለን። መቼ ቢሉ፣ በሰንበት፣ በበዓላት በማኅበረ ዐቢይ/ክርስቲያኖች በሚሰበሰቡበት፣ ስመ እግዚአብሔር በሚጠራበት፣ ታቦት  ባለበት፣ እግረ እግዚአብሔር በቆመበት ቅዱስ ስሙን ከፍ ከፍ በማድረግ ቅድስናን ገንዘብ እናደርጋለን።

ሊቁ ቅዱስ ያሬድ ለዐቢይ ጾም ሁለተኛው እሑድ በአዘጋጀው ምስጋና አማካኝነት ዕለቱ ‹‹ቅድስት›› የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡ ትርጉሙም ‹‹የተለየች፣ የተመረጠች፣ የከበረች›› ማለት ነው።  (መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገበ ቃላት ገጽ ፯፻፹፬) ቅድስት የሚለው ቃል ዕለቱ ‹‹ቅድስት›› ተብሎ የተሰየመበት ምክንያት ስለ ዕለተ ሰንበት እንዲሁም ስለ እግዚአብሔር አምላክ ፍጹም ቅድስና የሚያወሳ በመሆኑ ነው፡፡ እግዚአብሔር አምላክም ፍጥረታቱ የእርሱን ስም በማመስገን ይኖሩ ዘንድ ለቅድስና ሕይወት ፈጥሯቸዋልና በሰንበት እሑድ ክርስቲያኖች የቅድስና ተግባራትን ከሌላው ቀን አብዝተው ይፈጽማሉ፡፡ ዕለት ከተግባር፣ ስም ከክብር የተባበረባት ክብርት ሰንበት ቅድስት ስለሆነች ቅዱስ ያሬድ “ቅድስት” ብሎ ጠራት። ይኸውም የምትቀድስ፣ ከብራ የምታከብረን፣ አክብረናት የምንከብርባት በመሆኗ ነው።

ለዚህም ሊቁ ቅዱስ ያሬድ በጾመ ድጓ “ግነዩ ለእግዚአብሔር ወጸውዑ ስሞ ወንግርዎሙ ለአሕዛብ ምግባሮ፤ ሀቡ ስብሐተ ለስሙ፤ አክብሩ ሰንበተ ተገበሩ ጽድቀ፤ ዝግቡ ለክሙ መዝገበ ዘበሰማያት ኀበ ፃፄ ኢያማስኖ ወኢይረክቦ ሰራቂ፤ ድልዋኒክሙ ንበሩ ዘበላዕሉ ጸልዩ ኀበ ሀሎ ክርስቶስ” ትርጉም፦ “ለእግዚአብሔር ተገዙ፤ ስሙንም ጥሩ፤ ሥራውንም ለአሕዛብ ንገሯቸው፤ ለስሙም ምስጋናን አቅርቡ ሰንበትን አክብሩ፤ እውነትንም አድርጉ፤ ብል የማያበላሸው ሌባም የማያገኘው በሰማያት ያለ መዝገብን ለእናንተ ሰብስቡ፤ ተዘጋጅታችሁም ተቀመጡ፤ ክርስቶስ ወዳለበት ወደ ላይ አስቡ፡፡“  ስለዚህ ሰው ሰንበትን አክብሮ ጾሞ ጸልዮ፣ ቅድስናን ጠብቆ መኖር እንዲችል እግዚአብሔር የፍቅሩ መገለጫ የሆኑ ትእዛዛቱ ይነግሩናል።

#ቅዱስ_ያሬድም_ወቅቱን “#ቅድስት” ብሎ ሲሰይም፦

፩. #የአርባ_ቀን_ጾም_መጀመሪያ_በመሆኑ፦ ዕለቱ ከዐቢይ ጾም ቀናት ውስጥ አርባው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የጾመው ጾም መጀመሪያ ስለሆነች፣

፪. #ቅድስት_ሰንበት_ላይ_በመዋሉ፣ እንግዲህ “የሰንበትን ቀን ትቀድሰው ዘንድ አስብ” ተብሏል፡፡ (ዘፀ.፳፥፰) የሰንበትን ቀን አስቀድሞ የቀደሰ የባረከ ራሱ እግዚአብሔር ነው፡፡ እግዚአብሔርም ሰባተኛውን ቀን ባረከው፤ ቀደሰውም፤ እግዚአብሔር ሊያደርገው ከፈጠረው ሥራ ሁሉ በእርሱ ዐርፎአልና፡፡” (ዘፍ.፪፥፫)

“ከምእመናን ወገን አንድስ እንኳን በእሑድ ቀን ለገንዘብ መትጋት፣ ገንዘቤን አምጣ ብሎ መጣላት እና ዋስ መያዝ አይገባውም። ሁሉም ምእመናን ወደ ቤተ ክርስቲያን በንጽሕና በትሕትና ሆነው። ዳኛ ግብሬን፣ አበዳሪ ብድሬን፣ ኤጲስ ቆጶስ ዐሥራት በኵራት፣ ነጋ ድራስ ቀረጥ አምጡ ይሉናል ብለው ሳይፈሩ ይምጡ።

፫. #ወቅቱ_ወርኃ_ጾም_በመሆኑ፦ ምእመናን ይህንን ወቅት በጾም፣ በጸሎት፣ በእንባ፣ በስግደት፣ በአርምሞ፣ በመልካም ሥራ ቅድስናን የምናገኝበት፣ ጊዜው ሰው ወደ እግዚአብሔር አብዝቶ የሚተጋበት ወቅት በመሆኑ፣ ለእግዚአብሔር የሚገባ ነገር ለማድረግ የነገር ሁሉ መጀመሪያ፣ ለመልካም ነገር መነሻው በቅድስና በንጹሕ ልቡና መቅረብ ስለሆነ ቅድስት ብሏታል።  “እስመ ጾም እማ ለጸሎት ወእኅታ ለአርምሞ ወነቅዓ ለአንብዕ መቅድመ ኩሉ ግብር ሠናይት፤ ጾም ማለት የጸሎት እናት፣ የትሕትና እኅት፣ የእንባ ምንጭ፣የመልካም ሥራ ሁሉ መጀመሪያ ናት” እንዳለው ቅዱስ ያሬድ። ”ጾምን ቀድሱ፤ ጉባኤውንም ዐውጁ” የተባልን የተሰጠንን የጸጋ ቅድስና በእጃችን ላይ መኖሩን አመላካች ቃል ነው። (ኢዩ.፩፥፲፬)

፬. #የወንጌል_ትእዛዝ_በመሆኑ፡ ዕለቱን ተጠቅሞ ዓለምን አስተምሮበታል። “ዛቲ ዕለት እንተ ገብረ እግዚአብሔር ንትፈሣሕ ወንትሐሠይ ባቲ”  ትርጉም፡- “ይህች ዕለት እግዚአብሔር የሠራት ቀን  ናት፤ ሐሤትን እናድርግ፥ በእርስዋም ደስ ይበለን።” (መዝ.፻፲፯፥፳፬) ቅዱስ ዮሐንስም በራእዩ ሰንበት የጌታ ቀን ስለመሆኗ እንዲህ ይላል፤ “በጌታ ቀን በመንፈስ ነበርሁ፡፡” (ራእ. ፩፥፲)

ሊቃውንቱ በፍትሐ ነገሥት “ተጋብኡ ኵሎ ዕለት ኀበ ቤተ ክርስቲያን ወፈድፋደሰ በዕለተ ሰንበት ወበበዓላት ወበዕለተ ትንሣኤ ዘውእቱ ዕለተ እሑድ” ትርጉም፦ “ሁልጊዜ በቤተ ክርስቲያን ተሰብሰቡ፤ ይልቁንም በዕለተ እሑድ፣ በዕለተ ቀዳሚት፣ በጌታ በዓላት ወደ ቤተ ክርስቲያን ተሰብሰቡ” በማለት አዘውናል፡፡ (ፍትሐ ነገሥት፣ ገጽ ፪፶፬)

በትጋት ጾመን፣ ጸልየን ርስቱን እንድንወርስ የእግዚአብሔር ቸርነት፣ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ምልጃ፤ የቅዱሳን በረከት ይጠብቀን።

የዕለቱ መዝሙር (ከጾመ ድጓ)፦ ግነዩ ለእግዚአብሔር

#ምንባባት
➛ ፩ኛ ተሰ.፬÷፩-፲፫
➛ ፩ኛ ጴጥ.፩÷፲፫-ፍጻ.
➛ ሐዋ. ፲÷፲፯-፴

#ምስባክ
“እግዚአብሔርሰ ሰማያተ ገብረ::
አሚን ወሠናይት ቅድሜሁ፣
ቅድሳት ወዕበየ ስብሐት ውስተ መቅደሱ፤

(እግዚአብሔር ግን ሰማያትን ፈጠረ፡፡ እምነትና በጎነት በፊቱ፣ ቅድስናና የክብር ገናናነት በመቅደሱ ውስጥ ናቸው፡፡”
(መዝ.፺፭÷፭)

#ወንጌል
(ማቴ.፮÷፲፮-፳፭)

#ቅዳሴ
ዘኤጲፋንዮስ 

(ማኅበረ ቅዱሳን)

@Tsehaye_Tsidk
@Tsehaye_Tsidk

01 Mar, 21:51
136
Post image



የዐቢይ ጾምን መግባት ምክንያት በማድረግ የተሰጠ ትምህርት
(በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)


የዛሬው ንግግሬ ለአንዳንዶቻችሁ አዲስና እንግዳ እንደሚኾንባችሁ ዐውቃለሁ፡፡ ነገር ግን በዓላማ (ድኅነትን ለማግኘት ብለን) እንጹም እንጂ እንዲሁ የልማድ ባርያዎች አንኹን ብዬ እማልዳችኋለሁ፡፡ በየቀኑ ከልክ በላይ በመብላትና በሆዳምነት የምታገኙት ጥቅም ምንድን ነው? ጥቅምስ ይቅርና ጭራሽ የከፋ ጉዳትን የሚያመጣባችሁ ነው፡፡ ተመልከቱ! ከልክ በላይ በመጠጣትና በመስከር የማስተዋል ልቡና ሲታወር የጾም ጥቅምዋም ምንም ምልክትን ሳያስቀር ያጠፋዋል፡፡ እስኪ ልጠይቃችሁ፦ እስከ እኩለ ሌሊት ድረስ ብዙ ወይንን ከሚጠጡ፣ በየመሸታ ቤቱ አድረው ፀሐይ ከምትወጣባቸው፣ ለሚያገኛቸው ሰው ኹሉ ደስ ከማያሰኙ፣ ለቤተ ሰቦቻቸው ግድ ከሌላቸው፣ ሕፃን ዐዋቂው ከሚሳለቅባቸው፣ ራሳቸውን ባለመግዛታቸውና ያለጊዜው በኾነ ደስታ ደስ በመሰኘታቸው ምክንያት ከእግዚአብሔር ዘንድ ባለሟልነትን ካጡ ከእነዚህ ሰዎች በላይ ማን ጎስቋላ ሰው አለ? ቅዱስ መጽሐፍስ እንዲህ የሚል አይደለምን?፡- “ሰካሮች የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም” /1ኛ ቆሮ.6፥10/፡፡ ወዮ! እንደ ጠዋት ጤዛ ለሚጠፋ፥ ያውም እጅግ ከባድ ጉዳትን የሚያመጣ እርካታን ለማግኘት ብለው፥ የዘለዓለምን መንግሥትን የሚያጡት እነዚህ ሰዎች ከሚያገኛቸው መከራ በላይ ምን መከራ አለ?

እዚህ ጉባኤ ከተሰበሰባችሁ ምእመናን መካከል አንድም ሰው እንኳን ቢኾን በዚህ ዓይነት ስንፍና መያ’ዝ የለበትም፤ እግዚአብሔር ይህን በፍጹም አይወደውም፡፡ ከዚህ ይልቅ እያንዳንዷን ቀን በትዕግሥትና ራስን በመግዛት እንዲሁም አብዝቶ መብላት ከሚያመጣው የመከራ አውሎ ነፋስ ተጠብቃችሁ ወደ ነፍሳችሁ ወደብ - ይኸውም ወደ እውነተኛ ጾም - ልትደርሱ ይገባችኋል፡፡ ይህን ያደረጋችሁ እንደኾነም ከእርስዋ የሚገኘውን ጥቅም በብዙ ታገኛላችሁ፡፡ በሌላ አነጋገር አብዝቶ መብላት የብዙ ውርደቶችና ኃጢአቶች ምንጭ እንደ ኾነ ኹሉ ጾምም የብዙ በረከቶችና ክብር ምክንያት ነው፡፡ እንደምታስታውሱት መጀመሪያ ላይ እግዚአብሔር የሰው ልጆችን ሲፈጥር ለነፍሳቸው ድኅነት የሚኾን አንድ መፍትሔ እንደሚያስፈልጋቸው ያውቅ ነበር፡፡ በመኾኑም፥ ገና ከመነሻው አንሥቶ ለመጀመሪያው ሰው (ለአዳም) አንድ ትእዛዝ ሰጠው፤ እንዲህ በማለት፡- “በገነት ካለው ዛፍ ኹሉ ብላ፤ ነገር ግን መልካምንና ክፉን ከሚያስታውቀው ዛፍ አትብላ” /ዘፍ.2፥16-17/፡፡ ይህ ስለ መብላትና ስለ አለመብላት የተገለጠው ኃይለ ቃል በምሥጢር ስለ ጾም የሚናገር ነው፡፡ ምንም እንኳን ሰው ይህቺን ትእዛዝ ይጠብቃት ዘንድ ቢታዘዝም እርሱ ግን አልጠበቃትም፡- ራሱን መግዛት አቃተው፤ ባለመታዘዝ ኃጢአት ውስጥ ወደቀ፤ በራሱ ላይም የሞት ፍርድን አመጣ፡፡ እንደምታስታውሱት ዲያብሎስ ክፉ መንፈስና የእኛ ጠላት ስለ ኾነ የመጀመሪያው ሰው አዳም በገነት ሲኖር እንዴት በነጻነት እንደሚኖርና ሥጋ ለብሶ ሳለ እንዴት የመላእክትን ኑሮ በምድር ላይ እንደሚኖር ተመለከተ፡፡ በመኾኑም፥ እንዴት እንደሚጥለው አሰበ፤ ታላቅ የኾነ ተስፋ በመስጠት ከልዕልናው አዋረደው፤ በዚህ ሽንገላዉም የነበረውን ሀብት ኹሉ ሰረቀው፡፡ በመጠን ያለመኖርና ከዓቅም በላይ የኾነን ነገር የመመኘት ክፋቱ ይኽን ያህል ነው፡፡ ጠቢቡ ሰውም ይህንን እንዲህ በማለት ግልፅ አድርጎታል፦ “በዲያብሎስ ቅንአት ምክንያት ሞት ወደ ዓለም ገባ” /ጥበ.2፥24/፡፡

ተወዳጆች ሆይ! ገና ከጥንቱ የሞት መግቢያው ራስን አለመግዛት መኾኑን ታያላችሁን? በኋላ ዘመን ላይም መጽሐፍ ቅዱስ አብዝቶ መብላትን እንዴት ደጋግሞ እንደሚነቅፈው አስተውሉ፡፡ በአንድ ስፍራ እንዲህ ተብሎ ተጽፏል፡- “ሕዝቡም ሊበሉና ሊጠጡ ተቀመጡ፤ ሊዘፍኑም ተነሡ” (ዘጸ.32፥6)፤ በሌላ ቦታም፦ “በላ፥ ጠጣም፤ ወፈረ፥ ደነደነም፤ የመድኃኒቱንም አምላክ ናቀ” ይላል /ዘዳ.32፥15/፡፡ የሰዶም ኗሪዎችም እንደዚሁ ያን የማይበርድ ቍጣ በራሳቸው ላይ ያመጡት በዚህ ኃጢአት ምክንያት ነው፡፡ ሌላውን በደላቸውን እንኳን ሳንገልጠው የነቢዩን ቃላት አድምጡ፤ እንዲህ ያለውን፡- “የሰዶም ኃጢአት ይህ ነበረ፡- እንጀራን መጥገብ” /ሕዝ.16፥49/፡፡ በአጭር አነጋገር መብል ብዙውን ጊዜ እንደ ምንጭ ውኃ ነው፤ ወይም የክፋት ኹሉ ሥር ነው፡፡

ይቀጥላል....

(ኦሪት ዘፍጥረት ቅጽ 1 ገጽ 23-31 በገብረ እግዚአብሔር ኪደ የተተረጎመ)


@Tsehaye_Tsidk
@Tsehaye_Tsidk

01 Mar, 18:40
124