፭ ኪሎ ግቢ ጉባኤ

@amstkilogg


በኢ/ኦ/ተ/ቤ/የሰ/ት/ቤ/ማ/መ/ማኅበረ ቅዱሳን አ.አ ማዕከል
መርሐ ግብራት ፥
#የቅዱሳን_ታሪክ
#መጽሐፍ_ትረካ
#መጽሐፍ_ጥቆማ
#ብሒላተ_አበው

https://t.me/amstkilogbigubae

በዩትዩብ ቤተሰብ እንሁን ☟☟☟https://www.youtube.com/@5kilogbigubae

፭ ኪሎ ግቢ ጉባኤ

19 Oct, 11:17


ኑ ቸርነት እናድርግ

ሊያመልጠን የማይገባ " በጎ ዕድል ''

ሉቃ 10 ÷ 42

፭ ኪሎ ግቢ ጉባኤ

16 Oct, 12:00


ኦርቶዶክሳዊ የፆታ ትምህርት (ኦፆት)

የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች እንደምን ሰነበታችሁ 🙏🏻🙏🏻

ሳምንታዊው የአንድነት ጉባኤአችን በተለመደው ሰዓትና ቦታ የሚቀጥል ይሆናል።

የዚህ ሳምንት የት/ቱ ርዕስ ፦ ኦርቶዶክሳዊ የፆታ ትምህርት (ኦፆት)....ሲሆን ሁላችሁም በሰዓቱ በመገኘት የጉባኤው ተሳታፊ ትሆኑ ዘንድ በእግዚአብሔር ስም ተጋብዛችኋል ።

ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን 🙏🏻

፭ ኪሎ ግቢ ጉባኤ

፭ ኪሎ ግቢ ጉባኤ

16 Oct, 11:35


https://forms.gle/dt8xBLsTMevy6KkX9

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

የተወደዳችሁ የግቢ ጉባኤአችን ተማሪዎች የድሮይንግ ቁሳቁስ(drawing materials)  ያላችሁ ይህን google ፎርም በመሙላት ሌሎች እህት ወንድሞቻችንን እንድናግዝ በእግዚአብሔር ስም እንጠይቃለን !!!

ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን 🙏🏻

የ፭ ኪሎ ግቢ ጉባኤ ልማት ክፍል

፭ ኪሎ ግቢ ጉባኤ

16 Oct, 08:17


መጽሐፍ ቅዱስ

ከ1500 ቅ.ል.ክ በፊት ነበር አንድ በፈርኦን ስር ያደገ ከአብረሃም ወገን የሆነ እስራኤላዊ፣ ቤተ ያእቆብን ከግብጽ ያወጣ  ኮልታፋ የእግዚአብሔር ሰው "ሙሴ"፤ አምስት የሕግ መጻሕፍትን በመጻፍ  የሰውን ልጅ ታሪክ ከሕገ ልቦና ወደ ሕገ ኦሪት ያሸጋገረ እንዲሁም የመጽሐፍ ቅዱስን መሰረት የጣለ አሻራ ያኖረው።

ከዚያን ጊዜ ጀምሮ በ1600 ዓመታት ውስጥ መጽሐፍ ቅዱስ ተጻፈ። ይኸውም ከመጅመርያው የሙሴ መጽሐፍ አንስቶ እስክ መጨረሻው መጽሐፍ ራዕየ ዮሐንስ እስከ ተጻፈበት 98 ዓ.ም. ድረስ ያለው ዘመን ነው። ይህም መጽሐፍ ቅዱስን ለመጻፍ 1600 ዓመታትን የፈጅ ብቸኛው መጽሐፍ ያደርገዋል።  ጸሐፊዎቹ ደግሞ ከ40 በላይ ናቸው።

ጸሐፊዎቹ የኖሩበት ዘመን፣ የሥራቸው ዘርፍ፣ የትምህርትና የእውቀት ደረጃቸው ሁሉ አንድ አይነት አልነበረም። ከመጽሐፍ ቅዱስ ጸሐፊዎች በጣም የተማሩና ጠቢባን የነበሩ (ሊቀ ነቢያት ሙሴ፣ ጠቢቡ ሰሎሞን፣ ነቢዩ ዳንኤል፣ ቅዱስ ሉቃስ፣ ቅዱስ ጳውሎስ)፤ ከእረኝነትና ከዓሳ አጥማጅነት የተጠሩ (ነቢዩ አሞጽ፣ ንጉሥ ዳዊት፣ ቅዱስ ማቴዎስ፣ ቅዱስ ዮሐንስ . . ) የተለያዩ ዓይነት ሰዎች ነበሩ።

#ለምን_የሕይወት_መንገድ?

መጽሐፍ ቅዱስ የክርስትና ሃይማኖት መሰረት፣ የቤተክርስቲያን ዶግማ ምንጭ፣ የእውነተኛ አምላክ መንፈስ ያለበት መጽሐፍ ነው። ነገር ግን በምድራችን ላይ እልፍ አእላፋት መጽሕፍት እያሉ ስለምን መጽሐፍ ቅዱስ እውነተኛ የእግዚአብሄር መንገድ ስለመሆኑ እርግጠኞች ሆንን?  በምድራችን ላይ አምላካዊ መጽሐፍ ስለ መሆኑ አማኞቹ የሚናገሩለት መጽሐፍ፣ መጽሐፍ ቅዱስ ብቻ አይደለም።  የሙስሊሞቹ ቁርኣን፣ የሂንዱዎቹ የቬዳ ድርሳናት፣ እንዲሁም የሞርሞኖች መጽሐፍ፤ የእነዚህ የሁሉም አማኞቻቸው በመለኰታዊ መገለጥ የተሰጡ አምላካዊ መጻሕፍት ናቸው ይላሉ። ታድያስ  የክርስትና መጽሐፍ ቅዱስስ እውነት ለመሆኑ ማስረጃ አለውን? አዎን፣ በመቀጠልም መጽሐፍ ቅዱስን የእግዚአብሔር መንፈስ ያለበት እውነተኛ የህይወት መንገድ ያሰኘውን። ክርስትናን ደግሞ የመዳን ጉዞ ያደረገውን እውነት እንቃኛለን።

አንድ ሃይማኖት እውነት ስለ መሆኑ አማኙ ከአምላኬ ጋር አለኝ ከሚለው ግንኙነትና የሕይወት ልምድ ባለፈ ለማንኛውም ሰው ግልጽና ተጨባጭ የሆነ ማስረጃ ሊኖረው የግድ ይላል።  ቅዱስ ጴጥሮስ "ክእርሱም ይልቅ እጅግ የጸና የትንቢት ቃል አለን" ብሎ እንደ ገለጸው፣ የክርስትና ሃይማኖት ከአምላኩ ጋር ያለውን የሕይወት አብሮነት ከእነ ማስረጃው የሚያቀርብ ሃይማኖት ነው። (2 ጴጥ 1÷16) እነዚህንም ማስረጃዎችና ምስክሮች በሁለት ከፍለን እናያለን፤ የውስጥ እና የውጭ ምስክሮች ናቸው።

#የውስጥ_ምስክሮች

በብሉይ ኪዳን የተነገሩ በሐዲስ ኪዳን ተፈጻሚነት ያገኙ ትንቢቶች። እነዲሁም የመጽሐፍ ቅዱስ ወጥነት እና ስምምነት፣ መጽሐፍ ቅዱስን ሕያው የሕይወት መንገድ አድርገን እንድንቀበል የሚረዱን የውስጥ ምስክሮቻችን ናቸው።

#ትንቢት

ከመሆኑ አስቀድሞ በትንቢት የተነገረ ነገር፣ ጊዜው ሲደርስ ልክ እንደ ተነገረው ሆኖ ሲፈጸም በእርግጥም ያን የተነገረውን ቃል የያዘው መጽሐፍ እውነተኛ መሆኑን እናረጋግጣለን። ይህ የመጽሐፍ ቅዱስ ልዩ መገለጫ ነው። ሌሎች ምንም እንኳን ትክክል ነን ቢሉም፣ ከትርክት ውጪ ትንቢት የላቸውም። ትንቢት ከማንኛውም የሰው ልጅ የእውቀት አድማስ ውጭ የሆነና ትንቢት የተነገረለት ነገሩ ያን ጊዜ ገና ያልተወሰነ ሲሆን። ማለትም ወደፊት የሚሆንና እርሱም በአድራጊው ሰው ነጻ ፈቃድ ላይ የተመሠረተ ሲሆን ከሰው መላምታዊ-ግምት እና የእውቀት አድማስ ውጪ የሆነ ትክክለኛ ትንቢት ይሆናል።

ትንቢት እውነተኛ ይባል ዘንድ ሶስት ነገሮችን እንዲያሟላ ግድ ይላል። እነዚህም ትንቢቱ የሚፈጸምበትን ትክክለኛ ጊዜ መጠቆምስለ ትንቢቱ ዝርዝር ሁናቴዎችን ማካተት እና ጊዜው ሲደርስ ትንቢቱ በምልአት መፈጸም ይኖርበታል። እንግዲህ የመጽሐፍ ቅዱስ ትንቢቶች እሊህን መስፈርቶች በሁለንታ ያሟላሉ። እንደውም አንዳንድ ነብያት ትንቢቶችን ሲናገሩ ነገሩ እንደተፈጸመ አድርገው በሃላፊ የጊዜ ግስ ይናገሩ ነበር።  ለምሳሌ ልዑለ ቃል ኢሳይያስ እግዚአብሔር ወልድ ሰው ሆኖ ከመወለዱ ከ700 ዓመታት አስቀድሞ የነበረ ቢሆንም “ሕፃን ተወልዶልናል” (ኢሳይያስ 9፡6) ብሎ ልክ እንደ ተፈጸመ አድርጎ አስረግጦ ነበር የተናገረው።

በመቀጠል መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ከተነገሩ ድንቅ ትንቢቶች መካከል የተወሰኑትንና በዓለም ታሪክ ጎላ ያሉትን ለአብነት ያህል ትንቢቶቹንና አፈጻጸማቸውን እንቃኛለን።

ይቀጥላል....

ሃይማኖት እና ሳይንስ
በዲያቆን ያረጋል አበጋዝ

፭ ኪሎ ግቢ ጉባኤ፣ ትምህርት ክፍል፣ ትምህርታዊ ስነ-ጽሑፍ ንዑስ ክፍል።

፭ ኪሎ ግቢ ጉባኤ

12 Oct, 19:53


እንዳልማር '' ... የሚከለክለኝ ምንድር ነው? .. ። ”   ሐዋርያት 8፥36

በ A2SV ፕሮግራም  እና ሌሎች ምክንያቶች መደበኛ የኮርስ መርሐ ግብራትን መከታተል ላልቻላችሁ የግቢ ጉባኤአችን ተማሪዎች የተዘጋጀ ልዩ ተከታታይ የኮርስ መርሐ ግብር ።

ግቢ ጉባኤአችን  ፭ ኪሎ ግቢ ጉባኤ  ዘወትር እሁድ  ከ 11: 30 ጀምሮ ጉባኤ ዘርግታ  “ልጆቼ ኑ፥ ስሙኝ፤ እግዚአብሔርን መፍራት አስተምራችኋለሁ።” ( መዝ 34፥11 )  ትለናለች !!

የመጀመሪያ ኮርስ መርሐግብርም ነገ  ጥቅምት 3 ከ 11 :30 ጀምሮ በማኅበረ ቅዱሳን ህንፃ 3 ተኛ ፎቅ ተዘጋጅቶ ይጠብቀናል

share በማድረግ ላልሰሙ እህት እና ወንድሞቻችን እናድርስ !!

ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን 🙏🏻

፭ ኪሎ ግቢ ጉባኤ

፭ ኪሎ ግቢ ጉባኤ

12 Oct, 15:58


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን 🙏🏻

የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች
ሰሞኑን በጉባኤያት ላይ ነገ እሁድ (በ03/2/2017ዓ.ም) የበጎ አድራጎት ጉዞ እንደሚኖር ሲገለጽ የቆየ ቢሆንም ለጊዜው የዚህኛው ሳምንት ጉዞ ወደቀጣይ ሳምንት የተራዘመ መሆኑን ለመግለጽ እንወዳለን ።

ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን 🙏🏻
፭ ኪሎ ግቢ ጉባኤ

፭ ኪሎ ግቢ ጉባኤ

11 Oct, 19:31


፭ ኪሎ ግቢ ጉባኤ pinned «https://forms.gle/oSvAhaVT2NSffCG39»

፭ ኪሎ ግቢ ጉባኤ

11 Oct, 11:58


ተወዳጆች
ይህችን ፎርም በመሙላት መንፈሳዊ ኃላፊነታችንን እንወጣ ።

፭ ኪሎ ግቢ ጉባኤ

11 Oct, 11:56


https://forms.gle/oSvAhaVT2NSffCG39

፭ ኪሎ ግቢ ጉባኤ

09 Oct, 07:54


“እኛም አይተናል አባትም ልጁን የዓለም መድኃኒት ሊሆን እንደ ላከው እንመሰክራለን።”

1ኛ ዮሐንስ 4፥14

ነገ  ሐሙስ  መስከረም 30
ከ 11 : 20 ጀምሮ
ማኅበረ ቅዱሳን 3ተኛ ፎቅ

፭ ኪሎ ግቢ ጉባዔ