ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official) @tunbi_media Channel on Telegram

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

@tunbi_media


MIIDIYAA TUNBII እንኳን ደህና መጣችሁ! ይህ የኢትዮ ቱንቢ ሚድያ ይፋዊ የቴሌግራም ገጽ ነው። የቱንቢ ዋና አጀንዳ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን እና የሁላችንም ሀገር፣ ባለ ብዙ ፈተና እና ባለ ብዙ ተስፋ ስለ ሆነችው የኢትዮጵያ ህልውና ጉዳይ ነው። የመረጃ፣ ማስረጃ፣ የቀጥተኛ ምልከታና መፍትሔ ተኮር ጋዜጠኝነት ቤት።

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official) (Amharic)

ምርጥ ልዩ ቴሌግራም ገጽ ሶስተኛ ስለ ኢትዮ ቱንቢ ሚድያ Ethio Tunbi ጥሩ ገጽ ያለባችሁ በእንቅስቃሴው ላይ መረሳለሁ። ኢትዮ ቱንቢ ሚድያ ለሁለት ቤተክርስቲያንና ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን እና ሀገር ወንጌል አስተያየት ተቋቋሚ ነው። የህልውና ጉዳይን እና ምስራቅ አገልግሎትን የገለጹትን ቴሌግራማችን በሙሉ እንዲሰልጥ ካሉቅ ኢትዮጵያውያን ጋር ይህን ገጽን ይመልከቱ። ከላይ እንዲሸጡላችሁ እናገናኛም ተማሪዎችም ብቻ እንዲተካላና ልታደርሱ እንችላለን።

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

07 Feb, 11:20


#ኦርቶዶክስተዋሕዶ #ጾመነነዌ

አባታዊ መልዕክት !

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የ2017 ዓ.ም የጾመ ነነዌ የሰላምና የጸሎት አዋጅ መግለጫ ሰጥተዋል።

ከመግለጫቸው የተወሰደ ፦

" ለችግሮች ሁሉ መፍትሔ አላቸው፤ መፍትሔውም የሚገኘው ከእግዚአብሔርና ከእኛ ነው፤ ከእኛ በንስሓ ተመልሰን ከልብ እግዚአብሔርን ይቅርታ መጠየቅና ከክፉ ተግባራችን በእውነት መጸጸት ይጠበቃል፤ እግዚአብሔር ደግሞ ይህንን ዓይነቱ ንስሓ ከኛ መኖሩ ሲመለከት ምሕረትና ይቅርታን ይለግሰናል፤በዚህም መፍትሔና ፈውስ ይገኛል።

ከዚህ አንጻር በአሁኑ ጊዜ ለሀገራችንና ለዓለማችን ስጋት የሆኑ የጦርነት ክሥተቶች፣ የመሬት መንቀጥቀጥ፣ የአየር መዛባት፣ የድርቅ መከሠት፣ የጎርፍ መጥለቅለቅ የሰላም መደፍረስ፣ የሰላማውያን ወገኖች መጎዳት፣ የፍቅርና የአንድነት መላላት ወዘተ. . . . ከምድራችን ተወግደው ፍጹም ምሕረትና ሰላም እናገኝ ዘንድ በኃጢኣታችን ተጸጽተን በምህላ ንስሓ መግባት አለብን።

ከዚህ አኳያ ከጥንት ጀምሮ በቤተክርስቲያናችን ቀኖናዊ ሥርዓት መሠረት በየዓመቱ የሚጾመው ጾመ ነነዌ ለዚህ አመቺ ጊዜ ስለሆነ ከየካቲት 3 ቀን 2017 ዓመተ ምሕረት ጀምሮ ለሦስት ቀናት ከልኂቅ እስከ ደቂቅ ሁላችንም ጠዋትና ማታ በየቤተክርስቲያኑ ዐውደ ምሕረት እየተገኘን በንስሓ በዕንባ በጸሎት በምህላ የእግዚአብሔርን ምሕረትና ይቅርታ እንድንጠይቅ፤ እንደዚሁም በሀገራችንና በውጭ ያላችሁ ሊቃውንተ ሕዝብ ቀኖናውን ጠብቃችሁ ይህንን በማስፈጸም ምህላውን በቀኖናው መሠረት እንድታከናውኑ በእግዚአብሔር ስም አባታዊ መልእክታችንን እናስተላልፋለን። "

(የቅዱስነታቸው ሙሉ መግለጫ ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

06 Feb, 19:35


#የ29_ሚሊዮን_ኢትዮጵያውያንን_ህይወት_ጥያቄ_ውስጥ_ያስገባው_የትራምፕ_ውሳኔና #ሰው_ጠሉ_የብልጽግና_አገዛዝ_ገመና_በአሜሪካ_ውሳኔ_መጋለጥ #ልዩ_ዝግጅት https://youtu.be/fHGQlPmfzWQ?si=vb23ZcgS3URZQI-C

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

06 Feb, 08:45


የቀጠለ👆👇
ጊዜው አልረፈደም እንዲስተካከል እንጠይቃለን። ካልተስተካከለ የእርስ በእርስ የአገልጋዮች ዕልቂት እንደሚፈጠር አስረግጨ መናገር እፈልጋለሁ። የአጥማቂው ጀሌዎች ሐሳብና ዕውቀት የሌላቸው መሆኑን ስንቶችን የአካል ጉዳተኛ እንዳደረጉ ሕይወት እንዳጠፉ የሚያውቅ ያውቀዋል። ዛሬም ያንን ሲደግሙትና አጥቢዎችን በጉልበት ሲወሩት ዝም የምንልበት ምክንያት አይኖርም።
እነ መምህር ገብረ መድኅን ዋጋ ከፍለው ሰጥ ያሰኙትንና ከምዕራብ ጎጃምና ከሌሎች ሀገረ ስብከቶች እንዳይንቀሳቀሱ ያደረጉትን ጉድ እናንተ በማን አለብኝነት ነፍስ ስትዘሩባቸው ማንም ዝም አይልም። ጦርነት ላይ ላለ ሕዝብ ሌላ ጦርነት አንፈልግም። ግን አይ ካላቸው አሁን ድሮ አይደለምና ዋጋ ትከፍላላችሁ።
ማኅበረ በኩራት ማለት የሐሳዊ መሲሕ መንገድ ጠራጊዎች ቡድን ነው።

ይድረስ
ለባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና ሥራ አስኪያጅ
የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት
Mahibere Kidusan - ማኅበረ ቅዱሳን ባሕር ዳር ማእከል
  ቤተ ክርስትያን ስትወረር ቁመን አናይም

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

06 Feb, 08:45


እስከዛሬ ድረስ ለዓመታት ዋጋ እየከፈልሁ ያለሁት በአጥማቂው ዮሐንስ ምክንያት ነው። ከምወደው መሥሪያ ቤትም የተፈናቀልሁት በእሱ ጀሌዎች እንግርግሪያ ነው። ግን ባንተ ስሜት ልክ የሚጓዝ መሪ ከሌለህ ሁለመናህም ይወረስብሃል። ይኸው ከጠቅላይ ቤተ ክህነት ጀምሮ እስከ ባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ድረስ ወረሩን። የመጨረሻውን ጦርነት አድርገን ግልብጥ ብለን መጥተን ሀገረ ስብከት የምትሉትን እንበትነዋለን። ብፁዕ አአቡነ አብርሃም ሆይ ከእርስዎ ጋር ስለ አጥማቂያን ገመና ከማስረጃ ጀምሮ አውርተን ነበርና እኔ በግሌ እንደሚያስተካከሉት ተስፋ ነበረኝ። ስለ ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን፣ ስለ ንዋዕያተ ቅድሳት ዝግጅትና ሽያጭ፣ ስለ አእምሯዊ ንብረት፣ አጠቅላይ መንፈሳዊ ሕትመቶች ማእከላዊ ሆነው እንዲታተሙና ሌሎች ጉዳዮችም ጭምር አውርተን በእርስዎ የሥራ አስኪያጅነት ዘመን እንደሚስተካከሉ ተስፋ ነበረኝ። ግን ብፁዕነትዎ የተለወጠ ነገር የለም ይባሱን ይኸው ሀገረ ስብከት ላይ ሃይማኖተኛ መሳይ ከሃይማኖቱ መንገድ ውጭ ለሚንቀሳቀሱ ጎረምሶች ዕውቅና ሰጥተው እሾህ እንዲተከል አመቻችተዋል ወይም በቀጥትታ ፈቅደዋል ወይም በዝምታ አልፈዋል።

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

05 Feb, 21:32


የጅማው ድብቅ ስብሰባ ሙሉ ሰነድ

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

05 Feb, 17:15


የጅማው የብልጽግና አመራር ግምገማ

በግምገማው ያልተነሣ ጉዳይ የለም። ኦርቶዶክስን በተመለከተ የተነሣውን ብቻ አሰፍረዋለኹ። 

“ቤተ እምነታችን በተመለከተ”

ለብልጽግና ጉዟችን እንቅፋት የኦርቶዶክስ እና  የእስልምና ቤተ እምነቶች ነበሩ። ይል እስልምና መጅሊስ እኛ ባቀድነውና ባሰብነው መንገድ አዲስ መጂሊስ እንዲመረጥና ሰላማዊ የሥልጣን ሽግግር እንዲካሄድ ተደርጓል ስለሆነም አሁን ያለው መጅሊስ ከማንኛውም መጅሊስ አባል በላይ ለኦሮሞ ሕዝብ ጥቅም እየሠራ ይገኛል። 

በኦርቶዶክስ ዙሪያ ከዚኽ በፊት ከነበረው አንጻር በጥቅም በመያዝና በማስፈራራት አሁን የተሻለ ስሜት መፍጠር ቢቻልም በምንፈልገው ደረጃ መቆጣጠር የቻልንበት ሥራ ገና ብዙ  ይቀረናል። በቀጣይም የኦርቶዶክስን ሲኖዶስን እኛ በምንፈልገው መሪዎች ለመቆጣጠር በተጠና መንገድ በመሥራት ላይ እንገኛለን።

በአጠቃላይ የኦርቶዶክስን ቤተ ክርስቲያን በተመለከተ በእምነት አባቶችና ምእመናን መካከል ያለው ግንኙነትና መተማመን ለብልጽግና ጉዟችን እንቅፋት የሚኾኑበት ደረጃ ላይ የደረሱ ቢኾንም የእምነቱ አባቶች እርስ በርስ እንዳይተማመኑና እንዲከፋፈሉ ብሎም በተከታዮቻቸው ዘንድ እምነት እንዲያጡ በስፋት እየተሠራ ይገኛል።


መምህር ንዋይ ካሳሁን

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

04 Feb, 19:45


#በተለይ_ለኢትዮጵያውያን #የነፃ_ተሳፋሪነት_ጽንሰ_ሐሳብ #Free_Rider_Theory #የምንፈልገው_ሀገራዊ_ሁኔታ_ቁልፍ_ጉዳይ #በያሬድ_ኃይለመስቀል።። https://youtu.be/wfjZKbYHQG4?si=_5W_1Mb_CM1eSG5T

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

04 Feb, 11:32


ሻሸመኔ

👉ጥር 27 ቀን 2015 ዓ.ም ሻሸመኔ
ቆብ ያጠለቁ ፓለቲከኞች ቤተክርስቲያንን ጦርሜዳ ካደረጉና ካህናትን ምእመናንን ካስገደሉ በኋላ ዛሬም የሲኖዶስ አባል ኾነው መቀጠላቸው ብቻ ሳይሆን

የሚገርመው ከብዙ ደም አፍሳሹ እና ለብዙዎች ኅልፈተ ሕይወት ምክንያት የሆነ ጳጳስ ዛሬ የዚህ ሕዝብ መሪ እና ጠባቂ ሆነው መመደባቸው ታሪክ የማይረሳው ፣ልብን እያደማ የሚኖር ክስተት ነው ፣ እግዚአብሔር ግን ዛሬም ፍርድ አለው ።

የዖዛ ስብራት መጽሐፍ ይህንን በመረጃ ሰንዶ ይዞል ለታሪክ ገዝተው ቢያናቡት ይጠቅማል አማዞን ላይ ያገኙታል

የዖዛ ስብራት: በሀገራችን በኢትዮጵያ እና በኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ላይ የደረሰውን ስብራት በመረጃ የሚያሳይ መጽሐፍ (Afrikaans Edition) https://a.co/d/9DdkIuZ

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

04 Feb, 11:00


የ #ኬንያ መንግስት በ #ኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ላይ 'ልዩ የፀጥታ ዘመቻ' መጀመሩን አስታወቀ‼️
የኬንያ ብሔራዊ ፖሊስ አገልግሎት በማርሳቢት እና ኢሲዮሎ ግዛቶች በኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ላይ 'ልዩ የፀጥታ ዘመቻ' መጀመሩን አስታወቀ።

አገልግሎቱ ትናንት ባወጣው መግለጫ የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት የሚጠቀምባቸውን መሸሸጊያዎች ለቆ እንዲወጣ ለማድረግ “ኦንዶአ ጃንጊሊ ኦፖሬሽን” የተባለ ዘመቻ ከትናንት ጥር 26 ቀን ጀምሮ እንደሚያካሄድ ገልጿል።

በከፍተኛ ደረጃ የሚካሄደው ዘመቻ ለኬንያ ብሔራዊ ደህንነት ከፍተኛ ስጋት የሚጥሉ እንደ የጦር መሳሪያ፣ የአደንዛዥ ዕፅ እና የሰዎች ዝውውር፣ ህገወጥ የማዕድን ማውጣት ያሉ ህገወጥ ስራዎችን የሚያከናውኑ ወንጀለኞችን ዒላማ ያደረገ ነው ተብሏል።
=====================
💎⬇️⬇️⬇️👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

03 Feb, 20:29


የሻሸመኔ ሰማዕታት

"…አምስተኛውንም ማኅተም በፈታ ጊዜ፥ ስለ እግዚአብሔር ቃልና ስለ ጠበቁት ምስክር የታረዱትን የሰዎች ነፍሳት ከመሠዊያ በታች አየሁ። በታላቅ ድምፅም እየጮኹ፦ ቅዱስና እውነተኛ ጌታ ሆይ፥ እስከ መቼ ድረስ አትፈርድም ደማችንንስ በምድር በሚኖሩት ላይ እስከ መቼ አትበቀልም? አሉ።”ራእ 6፥ 9-10

በጥር 27/2015ዓ.ም በእነ ሳዊሮስ ፥ዜና ማርቆስና ኤዎስጤቴዎስ ትዕዛዝ ሰጭነት፥ በኦሮሚያ ልዪ ኀይል፥በኦሮሚያ ፖሊስ ፥በኦሮሚያ ሚሊሻ፥በአክራሪ  እስላም ወሀቢያ፥በጽንፈኛ  ጴንጤዎችና የዋቄፈታዎች ጥምረት በሻሸመኔ  ከተማ በግፍ ተጨፍጭፈው ሰማዕትነትን ተቀብለዋል።

         በረከታቸው ይደርብን!

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

03 Feb, 18:40


ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official) pinned «ይህን ሰሞን ስለ ዓለማወ ዘፈንና ሙዚቃ የሚወዛገዱ መምህራኖችን ተመልክቻለሁ። እኔ የቀኖና ሊቅ አይደለሁም። ነገር ግን በሃይማኖት የማስብ ስለሚመስለኝ አስተያየት መስጠት አስፈላጊ መስሎ ታየኝ። ቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ሃይማኖትን ሕይወቱ ስላደረገ ሰውና ማኅበረሰብ ስንነጋገር የሰሞኑን ፖለቲካና ከመንፈሳዊ ዓላማ ውጭ የሆኑ ድብቅ ፍላጎታችን በተቻለ መጠን ያልተቀላቀለበት ትምህርት መስጠት ምእመናንን በማሳሳት…»

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

03 Feb, 18:36


4 ወር ተፈረደባቸው‼️
በ3ቱ በአምቦ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች የተሰጠ ፍርድ
በጥምቀት ሰሞን በቅዱስ ሚካኤል ታቦት
እያሾፉ እና እየቀለዱ በቲክ ቶክ ቪዲዮ ለቀው የነበሩት እነዚህ ሶስት ተማሪዎች:
1ኛ. ተማሪ ገመቹ ምትኩ
2ኛ. ተማሪ ካሳን አድቬንቸር
3ኛ. ተማሪ ጋዲሳ ኢቲና
ዛሬ በአምቦ ዳዳቻ ወረዳ ፍርድ ቤት ቀርበው የነበረ ሲሆን እያንዳንዳቸው በ4 ወር እስር እንዲቀጡ ተወስኗል።
[አዩዘሀበሻ]
=====================
💎⬇️⬇️⬇️👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

03 Feb, 18:35


#አገር_በሕግና_በሕግ_አግባብ_ብቻ_እንድትመራ_እንታገላለን!"

#የጣሪያ_ግድግዳ/የንብረት ግብር ተብሎ የወጣውን መመሪያ አስመልክቶ ፍርድ ቤት ባሳለፈው ውሳኔ ላይ የእናት ፓርቲ መግለጫ።

እናት ፓርቲ የአዲስ አበባ ከተማ ፋይናንስ ቢሮ ላይ ክስ የመሰረተው ሐምሌ 17 ቀን 2015 ሲሆን በቀን 29/2/2016 ችሎቱ ክሳችንን እንድናሻሽል ብይን በመስጠቱ ክሳችንን አሻሽለን አቅርበናል ። ስለሆነም የክሱ ሂደት ምን እንደነበረና ምን እንደሚመስል በየደረጃው የነበሩ ክርክሮችን በተመለከተ በጥቅሉ በዚህ መግለጫ እናቀርባለን።
የክሱ ምንነት፦ የንብረት ግብር ማስተባበሪያ ጊዜያዊ ፕሮጀክት ጽ/ቤት አጥንቶ ያቀረበውና በአዲስ አበባ ፋይናንስ ቢሮ አማካይነት ሚያዚያ 3 ቀን 2015 በተጻፈ ደብዳቤ ሸኝነት ለሁሉም የከተማው አስተዳደር መዋቅሮች የተላለፈው የንብረት ግብር መመሪያ ሕግን ባልተከተለ መንገድና የከተማ አስተዳደሩ ባልተሰጠው ስልጣን የወጣ መመሪያ በመሆኑ ፓርቲያችን የአዲስ አበባ ከተማ ሕዝብን በመወከል መመሪያው እንዲሻርልን ለፍርድ ቤቱ ክሳችንን አቅርበናል።

የክሱ አመሰራረት፦ እናት ፓርቲ ለኢትዮጵያ ሕዝብ መብት መከበር በሰላማዊ ፖለቲካ ለመታገል በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተመዘገበ አገራዊ ፓርቲ ሲሆን በማንኛውም የኢትዮጵያ ዜጋ ላይ በደል አጋጥሟል ብሎ ሲያስብ ፖለቲካውን በፖለቲካ ሂደት፤ ፍትሕ ማግኘት የሚገባውን ...

..... Continue reading
👇🏾👇🏾👇🏾
https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid0Wq4nmLufcN3oNrjUDHjUBMfvU1uTatzCr1WsboWUvp9cpD4t8RUSQmW6NJCf1L8xl&id=100069788562070&mibextid=Nif5oz

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

03 Feb, 18:35


ይህን ሰሞን ስለ ዓለማወ ዘፈንና ሙዚቃ የሚወዛገዱ መምህራኖችን ተመልክቻለሁ።

እኔ የቀኖና ሊቅ አይደለሁም። ነገር ግን በሃይማኖት የማስብ ስለሚመስለኝ አስተያየት መስጠት አስፈላጊ መስሎ ታየኝ።


ቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ሃይማኖትን ሕይወቱ ስላደረገ ሰውና ማኅበረሰብ ስንነጋገር የሰሞኑን ፖለቲካና ከመንፈሳዊ ዓላማ ውጭ የሆኑ ድብቅ ፍላጎታችን በተቻለ መጠን ያልተቀላቀለበት ትምህርት መስጠት ምእመናንን በማሳሳት ምክንያት ከበጎቹ ጌታ ከእየሱስ ክርስቶስ ቅጣት ያድናል።
ቤተ ክርስቲያን ከሁሉ በላይ የቅዳሴ የጸሎት ዜማን እስከነ ዓላማውና መንፈሳዊ ግቡ፥ ከእነ ጥልቅ ምሥጢሩ ተረድተን እንድናዜም ትፈልጋለች። ታስተምራለች፥ በተግባርና በህይወት ታሳያለች። በሂደቱ ሁሉ ህሊናችን፥ ዓይነ ልቦናችን እና መላው ተስፋችን ሁሉ ሰመያዊ ማንነታችንን አንጾ በመገኘት ላይ ታተኩራለች። ልጆቿም እንዲሁ በግልና በጋራ ድምፍ አውጥተው ወይንም በአርምሞ ሲያዜሙና ሲናገሩ ቅዳሱው ባመለከታቸው መሠረት ነፍሳቸውን ወደ ሰማዩ አባታቸው እንድታተኩር አድርገው ፈጣሪያቸውንና መድኀኒታቸውንን ክፍ ክፍ ማድረግና ማመስገን እንዲሆን እንደምታስተምር የቅዱሳን ሕይወት ሁሉ ይጠቁማል።
ቤተ ክርስቲያን በግልጽና በአትቃላይ ዓለማዊ/ሥዝም ዘፈንን ኣታወግዝም። በመጽሐፍ ቅዱስ የሚሰጠን ምልክት በጥንቃቄ መመልከት ያስፈልጋል፦
ሮሜ 13፡13-14 “በቀን እንደምንመላለስ በአግባብ እንመላለስ። በጭፈራና በስካር አይሁን፤ በዝሙትና በመዳራት አይሁን፤ በክርክርና በቅናትም አይሁን። ይልቁንም ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን ልበሱት፤ ምኞቱንም ይፈጽም ዘንድ ለሥጋ በዐሳባችሁ አትመቻቹለት። “
1 ጴጥሮስ 4:3 “አሕዛብ ፈቅደው እንደሚያደርጉት በመዳራት፣ በሥጋዊ ምኞት፣ በስካር፣ በጭፈራ፣ ያለ ልክ በመጠጣት፣ በአስጸያፊ የጣዖት አምልኮ የተመላለሳችሁበት ያለፈው ዘመን ይበቃል። “
ገላትያ 5:16-25፤ ነገር ግን እላለሁ፥ በመንፈስ ተመላለሱ፥ የሥጋንም ምኞት ከቶ አትፈጽሙ። 17፤ ሥጋ በመንፈስ ላይ መንፈስም በሥጋ ላይ ይመኛልና፥ እነዚህም እርስ በርሳቸው ይቀዋወማሉ፤ ስለዚህም የምትወዱትን ልታደርጉ አትችሉም። 18፤ በመንፈስ ብትመሩ ግን ከሕግ በታች አይደላችሁም። 19፤ የሥጋ ሥራም የተገለጠ ነው እርሱም ዝሙት፥ ርኵሰት፥ 20፤ መዳራት፥ ጣዖትን ማምለክ፥ ምዋርት፥ ጥል፥ ክርክር፥ ቅንዓት፥ ቁጣ፥ አድመኛነት፥ 21፤ መለያየት፥ መናፍቅነት፥ ምቀኝነት፥ መግደል፥ ስካር፥ ዘፋኝነት፥ ይህንም የሚመስል ነው። አስቀድሜም እንዳልሁ፥ እንደዚህ ያሉትን የሚያደርጉ የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም። 22፤ የመንፈስ ፍሬ ግን ፍቅር፥ ደስታ፥ ሰላም፥ ትዕግሥት፥ ቸርነት፥ በጎነት፥ እምነት፣ 23፤ የውሃት፥ ራስን መግዛት ነው። እንደዚህ ያሉትን የሚከለክል ሕግ የለም። 24፤ የክርስቶስ ኢየሱስም የሆኑቱ ሥጋን ከክፉ መሻቱና ከምኞቱ ጋር ሰቀሉ። 25፤ በመንፈስ ብንኖር በመንፈስ ደግሞ እንመላለስ።
የመጽሐፍ ቅዱስ መልእክትና የቤተ ክርስቲያናችን የምንመለከተው ተግባራዊ ሕይወት የሚናበቡና የሚተረጓጞሙ መስለው ይታያሉ። የጠቀስናቸው ጥቅሶች በአንድ መሥመር ቢጠቃለሉ ገላ 5፥25 ይሆናሉ። እርሱም “በመንፈስ ብንኖር በመንፈስ ደግሞ እንመላለስ፨“ የሚለው ይሆናል።
እንግዲ ቤተ ክርስቲያን ልጆቿ በመንፈስ የመኖር አቅም እንዲያዳብሩ፥ ጎጂውንና ጠቃሚውን በራሳቸው እየለዩ አምላካቸውን እንዲያስደስቱ፥ የመንፈስ ቅዱስ ማኅደርበነታቸውን በሕይወት እንዲቀምሱ ታበረታታለች።
እንደ ኣይሁንና እንደ እስላም ወይንም እንደ ሌሎች ሰው ሠራሽ እምነቶችና ድርጅቶች ንካ-ኣትንካ፥ ቁም-ተቀመጥ እያለች በትምቀት በክርስቶስ ሞትና ትንሳዔ በጥምቀት ተካፍለው ዓለምን ሊዋጁ በውትድርና የተሠማሩ ልጆቿን በመንፈሳዊ ተጋድሎ ውስት አልፈው እንዲኣድጉላት “በመንፈስ ኑሩ!” ብላ የገዳማውያንን ሕይወት እንደ ምሳሌ በተግባር እያሳየች በጎቿን ትመግባለች።
እንግዲህ ዘፈን ይፈቀዳል ወይስ አይፈቀድም የሚለውን እሰታ ገባ ለሊቃውንት ጉባኤ ብያኔ ትቼ እኔ የበለጠ እስክማርና እስክረዳ አሁን እንደምረዳው ከሆነ ዘፈንን በሚመለከት የሚከተሉትን ነጥቦች ልብ እንድንል ትፈልጋለች፦
1. የዘፈኑ ዓላማ ይዘት፦ ክርስቲያኖች ዘፈን ሲሰሙ (ሲዘፍኑ አላልኩም) የዘፈኑን ዓላማና ይዘትን በሚመለከት በክርስቲያናዊ መንፈሳዊ ሚዛን ሊለኩ ይገባል። ይዘቱ ከመንፈሳዊ ዓላማ የሚያዘናጋ፥ ሥጋዊ ስሜት የሚቀሰቅስ፥ አሉታዊ ጠባይ እንድንለማመድ ምክንያት የሚሆን እና መንፈሳዊ ተመስጦን በሚያዳክም መንገድ በአእምሮ ምስለ-ዘማን (ፖርኖገራፊክ ምስሎች) የሚያትም እንዳይሆን አትብቃ እንደምታስጠነቅቅ ከአባቶቻችን ትንቃቄ እንማራለን።

2. በነፍስ ላይ የሚኣሳድረው ተጽእኖ፦ ከኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ተግባራዊ ሕይወት እንደምንረዳው ቅዳሴውና ማኅሌቱ ከይዘቱና አካል እንቅስቃሴ፥ ዝውውርና ሂደት ሁሉ የክርስቲያኖችን ነፍስ (ካህን በዓብይ ዜማ “ልባችሁን ወደ እግዚአብሔር ከፍ አድርጉ” ሲል ምእመናን ደግሞ “ብግዚአብሔር ዘንድ አለን/ነን” ማለታቸው የማዜማችንን ዓላማ ያመለክታል። ዜማ/ሙዚቃ በነፍስ ላይ ከፍተኛ ተጽእኖ እንደሚኣሳድር ከቤተ ክርስቲያን የበለጠ የሚረዳ ያለ አይመስለኝም። የቅዱስ ያሬድ ክግዚአብሔር የአገልግሎት፥ የውዳሴና የቅዳሴ ዜማ መቸሩ ይህንነኑ ተጽእኖ ያመለክታል። ከዚህ ተነስታ ቤተ ክርስቲያን ልጆቿ ዓለማዊ ዜማና ዘፈንን ከእግዚአብሔር ጋር ከሚኖረን የቀና ግኑኝነትና ከመንፈሳዊ እድገታችን አንጻር እንድንመረምር ታስተምረናለች።

3. አቅመ-ማንጸር፦ ምእመናን ሙዚቃ ወይንም ዘፈን ለማዳመጥ የትኛው ለነፍስ የሚጠቅም ወይንም እንደሚጎዳ የማንጸር አቅም እንዲያዳብሩ ታበረታታለች እንጂ እንደዚህ እንደ ኣሁኑ ትውልድ በጭፍን መንጋነት ብዙኃን የወደዱትን መከተል፥ ዘመኑ ያገለለውን መጥላት፥ ማስታወቂያ ያገነነውን በጭፍን መጋትን እንድንጸየፍ ታሳየናለች። ማንጸሪያችን ዘፈኑ ከክርስትና እሤት፥ ዓላማና የመኖር ትርጉም ጋር ያለውን ግኑኝነት በመመዝን መሆን አለበት። ጥያቄውም ዘፈኑ ወደ እግዚአብሔር ፍቅርና ምስጋና የሚመራ ነው ወይስ ለመንሳዊነት እንቅፋት ነው? በሚል ማንጸር ያሻል።
4. ከመምህረ ንስሐ መመሪያ መቀበል፦ የኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ልጆቿ በተለያዩ መንፈሳዊ አቅም፥ በተለያዩ የኑሮ ሁኔታ ውስጥ ስለሚኖሩ አንድ አስገዳጅ ሕግና መመሪያ የሰጠቸን ኤእመስለኝም። በዚህ ምትክ ክርስቲያኖች በሚኣደርጉት ብቻ ሳይሆን በሚኣስቡትና ባቀዱት ጉዳይ ከንስሐ አባቶቻቸው ከካህን ጋር በመምከር ለነፍሳቸው የሚበጀውን መመሪያ መቀበል አንደሚገባቸው እንደምታስተምር ቤሌሎች የትዳርና የግል ሁኔታዎች ውስጥ ሁላችንም እናውቀዋለን። ለክርስቲያን “መዝናኛ” በሚል ዓለማዊ ስሜት ቀስቃሽ፥ ርኩሰትና ኃጢአትን የሚኣበረታታ የዘመኑን ዘፈን ከክርስትና መንፈሳዊ ሕይወት ጋር ፈጽሞ የማይስማማ በመሆኑ ከንስሐ አባት ጋር መምከርን ታዛለች።
ሲጠቃለል ኦርቶዶክሳዊ ቤተ ክርስቲያን ዘፈንን ሁሉ ስታወግዝ አልመለከትም። ግልጽ ሆኖ የሚታየኝ ምእመናን ሙዚቃን/ዘፈንን በሚመለከት የመጀመሪያ ጥያቄያቸው “የምሰማው ወይንም የምዘፍነው ዘፈን ለመንፈሳዊ ሕይወቴ እድገትና ከእግዚአብሔር ጋር ያለኝን ግኑኝነት ያሳድግልኛል ወይስ መንፈሳዊ ሕይወቴን ይጎዳል?” ብሎ በመጠየቅ፥ እንዲሁም ከመምህረ ንስሐ ጋር በመምከር መበየን ይኖርባቸዋል።

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

02 Feb, 19:04


የጉልበት ስራ ሰርቼ ይቺን ቀን ሳይርበኝ ባሳልፍ ብሎ በየመንገዱ የሚንከራተት የሀገሬ ወጣት እየታፈሰ የሚደርስበት የግፍ ፅዋ ሞልቶ እየፈሰሰ ነው

@EliasMeseret

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

02 Feb, 09:22


በመንግስት ታጣቂዎች የተገደለው ሀኪም ጋር አብረውት የተማሩ እና የሰሩ ጓደኞቹ ከሰጧቸው አስተያየቶች መካከል !!

******
ቀዳሚው ሰው

ጅማ ዩኒቨርሲቲ፣ ልፋትህን አፈር በላው እኮ። አንዱ ተቀጠፈ! አይ ርጋታ! አዬ ትህትና! 2005 ዓ/ም የወርቅ ሜዳልያ ሸልመህ፣ ህዝብህን አገልግል ብለህ የሸኘኸው ፍሬህ በአጭር ቀረ።

የጅማዋ ኪዳነ ምህረት ደጅሽን በነጋ በነጋ 6 ዓመት ሙሉ ይሳለምሽ የነበረው ልጅሽ፣ ደሙ በከንቱ ፈሰሰች!!! የሰማይ ቤቱን አደራሽን!!!

ሌላው ጓደኛ

1 ሚሊዮን ሰው ነው የሞተው ብቻውን አልሞተው። ትህትናው እውቀቱ እርጋታው ሁሉን ጥበብ የታደለ ሀኪም ነበር። እግዚአብሔር ለልጆቹ እና ለዚ ምስኪን ህዝብ ሲል ባቆየልን የነበር። ያሳዝናል በጣም በጣም። ወንድማለም እግዚአብሔር ነፍስህን ይቀበላት። ነፍስ ይማር

ሶስተኛው ሰው

በእውቀት በፀባይ በትህትና በሁሉም ነገር የባረከህ እንዲህ በአጭር ሊወስድህ ነው ???

ወይኔ እኔ አፈር ልብላልህ የኔ ትሁት !!

አራተኛው አስተያየት ሰጭ

ዶር አንዷለም ዳኜ አብሮኝ የተማረ ባቼ ነው። የጠቅላላ ቀዶ ሕክምና ስፔሻሊስት እና የጉበት፣ የቆሽት እና የሃሞት መስመር ሰብ ስፔሻሊት ሃኪም ነው። በትምህርት ጀግንነቱ በዘመናት መካከል እንደ አጋጣሚ ልታገኘው የምትችለው እንቁ ልጅ ነው። ባህርዳር ሲሰራ አምሽቶ ሲወጣ ገደሉት እያሉኝ ነው😪😪😪 እጅግ በጣም ያማል። ነፍስህ በሰላም ትረፍ ወንድማለም!!!

አምስተኛው አስተያየት ሰጭ

"አንዱ"ን አይደለም ያጣነው ሚሊዮኖችን እንጂ።
አይ ወንድሜ እንደዚህ በቅርቡ ትጠራለህ ብዬስ አስቤም አላውቅ ነበር። ላንተስ ከዚህ ከንቱ የመባላት ዓለም ነው የተገላገልህ። ወዮ ለሚሊዮኖች! ወዮ ለሀገሬ! ወዮ ለወገኔ! 😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

02 Feb, 08:43


ዶክተሩ ተገደለ‼️
የጉበት ፣ የቆሽትና የሀሞት ከረጢት ከፍተኛ እስፔሻሊስት ሀኪም ፣ መምህር፣በባህር ዳር ዩኒቨርስቲ በጥበበጊዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ውስጥ የቀዶ ህክምና አገልግሎት ክፍል ዳይሬክተር እና ተመራማሪ የሆነው ዶ/ር አንዷለም ዳኜ በባህርዳር ጥበበ ጊዮን እስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ሲሰራ አምሽቶ ወደ ፈለገ ህይወት ሆ/ል ሌላ የሚሰራው ኬዝ ኑሮት እየሄደ ባለበት ሰአት ከምሽቱ 1:00 አካባቢ ማንነታቸው ያልታወቁ ሰዎች ቆሼ በሚባል አካባቢ ከመኪናው አስወርደው ገድለውታል።
ዶ/ር አንዷለም ዳኜ 37 አመቱ ሲሆን በባህርዳር ዩኒቨርሲቲ፣ ብሎም በአገራችን አሉን ከምንላቸው በቁጥር ትንሽ የዘርፉ ሰብ ስፔሻሊስት ሐኪሞቻች ውስጥ አንዱ ነበሩ። እጅግ አሳዛኝ ዜና ነው።
ነፍስ ይማር
ለቤተሰቦቻቸውና ለስራ ባልደረቦቻቸው መፅናናትን እንመኛለን።
አዩዘሀበሻ
=====================
💎⬇️⬇️⬇️👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

01 Feb, 19:14


#ላሊበላን_እንደ_ካምቦዲያው_አንኮር_ዋት? #በሰውም_በቅርሱም_ላይ_የተደቀነው_አደጋ ! #ያልተሰሙ_በብርቱ_ርብርብ_የሚታለፉ_ጉዳዮች! https://www.youtube.com/live/EbrAuurIXa0?si=rkhSJNzNdBMIoxqQ

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

01 Feb, 19:02


https://gofund.me/e791ace6 በወሎ ቡግና ወረዳ እና አካባቢው የተከሰተው ሰው ሰራሽ ርኃብ እያሰከተለ ያለውን ሞት ለመከላከል የቀረበ አስቸኳይ የድጋፍ ጥሪ
ሁላችንም እንደምናውቀው በአገራችን ኢትዮጵያ ዐማራ ክልል በወሎ ክፍለ ሀገር በቡግና ወረዳ እና አካባቢው በተፈጥሮ እና ሰው ሰራሽ ችግር ምክንያትእጅግ አሰቃቂ የሆነረሀብ ተከስቷል። በዚህምሳቢያ ብዙ ወገኖቻቸን የሚልሱት የሚቀምሱት አጥተው በሞት እያለቁ ነው።በዚህ ክፉ ረሀብ ከመቶ ሺዎችእስከ ሚልዮን የሚደርሱ ወገኖቻችን በቀጥታ ተጠቂዎች ሆነዋል። በተለይም አሁን ያለውጦርነት እና የሰላም እጦት እርዳታ ለማሰባሰብና በበቂ ሁኔታ ለማድረስ አዳጋች ስላደረገው ጉዳቱተባብሶ ሕፃናትና ነፍሰ ጡሮችን እንዲሁም የሚያጠቡ እናቶች ጨምሮ ክቡር የሆነውን የሰውንሕይወት በብዛት ወደመቅጠፍ ተሸጋግሯል።በጥቂት ድጋፍ መትረፍ ይሚችሉ ነፍሳት በአሰቃቂ ሁኔታ እየረገፉ ነው።

የችግሩን መጠን አጥንቶ አስቸኳይ ድጋፍ ማድረግ ሲገባ በተቃራኒው የአገዛዙ ሚዲያዎች፣ የፖለቲካአክትቪስቶች እንዲሁም ጉዳዩ በቀጥታ የሚመለከታቸው ባለሥልጣናት ግን ጉዳዮን በማድበስብስ ረሀብ እንደሌለና በተገቢጦሽም ምርት ተትረፍርፎ ዜጎችን አጥግቦ ወደ ውጪ እየተላከ እንደሆነአድርገው ዜና በመሥራት የእርዳታ ድርጅቶች ተገቢውን ትኩረት እንዳይሰጡት እንቅፋት ሆነዋል።

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

01 Feb, 17:43


#ላሊበላን_እንደ_ካምቦዲያው_አንኮር_ዋት? #በሰውም_በቅርሱም_ላይ_የተደቀነው_አደጋ ! #ያልተሰሙ_በብርቱ_ርብርብ_የሚታለፉ_ጉዳዮች! https://www.youtube.com/live/EbrAuurIXa0?si=rkhSJNzNdBMIoxqQ

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

01 Feb, 12:49


በአርትስ ቴሌቪዥን የጦቢያ ግጥም በጃዝ ፕሮግራም አዘጋጅነት የምናውቃት ምስራቅ ተረፈ "ለጥያቄ ትፈለጊያለሽ? በሚል በፖሊስ የተወሰደች ሲሆን ፖሊስ የ7 ቀናት የምርመራ ጊዜ መጠየቁ ተሰማ‼️
ፖሊስ፣ ምሥራቅን አዲስ አበባ፣ የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት አራዳ ምድብ ችሎት እንዳቀረባት፣ ፍርድ ቤቱም ፖሊስ ያቀረበውን ጥያቄ በመቀበል፣ "ምርመራውን አጠናቆ እንዲያቀርባት" በሚል ለጥር 30 ቀን 2017 ዓ.ም ቀጠሮ መስጠቱን ተከትሎ፣ ምሥራቅ አሁን በአዲስ አበባ ፖሊስ እስር ላይ እንደምትገኝ ወዳጆቿ ገልጸዋል።
=====================
💎⬇️⬇️⬇️👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

31 Jan, 18:58


“ ቦሩ ሜዳ” የፊት ለፊት የጥያቄና መልስ መድረክ በማኅበረ ቅዱሳን ሚዲያ

“ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ለምን የአዋልድ መጻሕፍትን ትጠቀማለች ?''

በማኅበረ ቅዱሳን ወርኃዊ የስብከተ ወንጌል ጉባኤ ላይ

ጥር 25 ቀን 2017 ዓ.ም
ከቀኑ 7፡30 ጀምሮ በጠቅላይ ቤተክህነት አዳራሽ

በዕለቱ ስብከተ ወንጌልን ጨምሮ የአዋልድ መጻሕፍት መነሻ እና መድርሻ ከየት ወዴት እንደሆነ በሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ምላሽ ይሰጣል፡፡

እርስዎም የእምነት ልዩነት ሳይገድብዎ ከአዋልድ መጻሕፍት ጋር ተያይዞ ያሎዎትን ጥያቄ በማንሳት ምላሽ ያገኙ ዘንድ ተጋብዘዋል፡፡

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

31 Jan, 16:52


🔈#የአርሶአደሮችድምጽ

🔴 “ አምና 3,600 ብር ስንገዛው የነበረውን ማዳበሪያ ዘንድሮ በ8,400 ብር ለመዛት ተገደናል ” - አርሶ አደሮች

➡️ “ ከኢኮኖሚ ማሻሻያ ጋር ተያይዞ የማዳበሪያ ዋጋ ጨምሯል ” - የሲዳማ ክልል ግብርና ቢሮ

የሲዳማ ክልል አርሶ አደሮች ማዳበሪያና ምርጥ ዘር በቆሎ የቀረበላቸው በውድ ዋጋ በመሆኑ ለመግዛት መቸገራቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ቅሬታ አቅራቢዎቹ በዝርዝር ምን አሉ ?

“ አምና የአንድ ኩንታል ማዳበሪያ (ዳፕ) ዋጋ 3,600 ብር ነበር። ዘንድሮ ግን 8,400 ገብቷል። አምና 1,800 ብር የነበረው ምርጥ ዘር በቆሎ የአንድ ፕሎት ዋጋ ዘንድሮ 4,600 ብር ገብቷል። ይህ ለበቆሎ ብቻ የሚከፈል ነው።

በቆሎ ስንወስድ ለብልጽግና ቤት ግንባታ 1,500 ብር፣ ለማኀተም 1,000 ብር፣ ለግብር እስከ 3,000 ብር፣ ለብልጽግና ፓርቲ መዋጮ 300፣ ለቀይ መስቀል 200 ብር ወረዳው በግዴታ የሚያስከፍለን ወጪዎችም አሉ።

በአጠቃላይ ለአንድ ፕሎት ምርጥ ዘር በቆሎ አንድ አርሶ አደር ከ10,000 ሺሕ ብር በላይ እንዲያወጣ ተገዷል።

ስለዚህ የሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ በተለይ በቆሎን በስፋት በማምረት የሚትታወቀው የሻመና አርሶ አደሮች ዘንድሮ በቆሎ ማምረት ይቸገራሉ"
ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ አርሶ አደሮች ላቀረቡት ቅሬታ ምላሽ እንዲድሰጥ የሲዳማ ክልል ግብርና ቢሮን ጠይቋል።

የቢሮው ኃላፊ አቶ መምሩ ሞኬ ምን መለሱ ?

“ ከኢኮኖሚ ማሻሻያ ጋር ተያይዞ የማዳበሪያ ዋጋ ጨምሯል። እኛ የጨመርነው ነገር የለም የትራንስፓርት ብቻ ነው። ስለዚህ ያለ ዋጋ ነው፤ ያሳወቅነው ዋጋ።

ሌሎች ጋ አሁን ላይ ስርጭት ስላልጀመረ እንጅ ተመሳሳይ ነው። እነርሱ ቀድመው ስለሚገቡ በሚል እንጅ ፎርማሊ አሳውቀናል እኛ በደብዳቤ። አገራዊ ነው።

አምና ላይ ወደ 4,000 ገደማ ነበር። አሁን ላይ ከ7,500 - 8,000 ብር ይሄዳል እስከ ትራንስፓርት ታሳቢ ተድርጎ
ማለት ነው።

የበቆሎም አዎ በመሳሳይ ነው ይጨምራል። ፕሮዳክሽን ኮስት በየጊዜው ይጨምራል። ባለበት አይሆንም

ስለዚህ ለምሳሌ የአንድ ትራክተር ዋጋ፣ የነዳጅ ዋጋ ታሳቢ አድርጎ በየአመቱ ይጨምራል። መጨመር ያለ ነው። ከሌላ ጋ ካልሆነ በስተቀር ከኛ ጋ ኦፊሻሊ ታይቶ ዋጋ እንደ ሀገር ወጥቶለት በዚያ የምናቀርበው ስለሆነ ችግር ያለው አይደለም።

ለምሳሌ በትራክተር ለሚያርስ ነዳጅ፣ የጉልበት.. ካችአምናና አምና የነበረ ተመሳሳይ አይደለም። ያምና እና የዚህ ዓመት ተመሳሳይ አይሆንም። በዚያ ምክንያት የተወሰኑ መጨመሮች አሉ።

ማዳበሪያ ከአገር ውጪ የሚመጣ ስለሆነ እኛ መተመን አልችልም። መንግስት ሳብሲድ አድርጓል። እንደመንግስት እንዲያውም ከድጎማ በፊት 12 ሺህ ብር ነው የሚሆነው የአንድ ኩንታል ማዳበሪያ ዋጋ። 

በድጎማው ቀንሶ ነው ወደዛም የወረደው። 4,000 ከአንድ ኩንታል ድጎማ ነው ”
ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

06 Jan, 19:50


#ተስፋዬ_ታላቅ_ነው! #ብቻዬን_እንደሆንኩ_አላስብም #ብፁዕ_አቡነ_ሉቃስ_ልዩ_የበዓል_መልእክት! https://youtu.be/n3JmHYkucyQ?si=f-Y_ESiiUTyRbnbZ

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

03 Jan, 20:42


በዛሬው እለት የመንግስት አመራሮችን ጨምሮ አምስት ሰዎች በሰሜን ሸዋ ግድያ ተፈፀመባቸው

(መሠረት ሚድያ)- በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ዛሬ ጠዋት ገደማ ለስራ እየተንቀሳቀሱ የነበሩ የመንግስት አመራሮችን ጨምሮ አምስት ሰዎች በአካባቢው በሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎች መገደላቸውን ምንጮች ለመሠረት ሚድያ ጠቁመዋል።

በተተኮሰባቸው ጥይት የሞቱት ግለሰቦች ለስራ ጉለሌ ወረዳ 3 ላይ ቆይተዉ ወደ ፍቼ ከተማ እየተመለሱ በነበረበት ወቅት ነው ተብሏል።

የዞኑ የውሃ ሀብት ቢሮ ሀላፊ፣ የመስኖና ተፋሰስ ሀላፊ፣ የቡሳ ጎንፋ ሀላፊ እንዲሁም አንድ የቀበሌ ሊቀንመበር እና ሹፌራቸው በአጠቃላይ አምስት ሰዎች በኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት ወይም መንግስት 'ኦነግ ሸኔ' በሚላቸው ታጣቂዎች መገደላቸውን ምንጮቻችን ጨምረው ገልፀዋል።

የሰሜን ሸዋ ዞን በቅርብ ወራት በመንግስት ጦር እና በኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት አባላት መሀል ከፍተኛ የሆነ ግጭት እያስተናገደ ይገኛል።

ከዚህ በፊት በአንፃራዊ ሰላሙ የሚታወቀው ይህ የሰላሌ አካባቢ አሁን ላይ ከፍተኛ እገታ፣ ግድያ እና ተያያዥ ጉዳቶችን በህዝቡ ላይ እያስከተለ እንደሆነ ይታወቃል።

መረጃን ከመሠረት!

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

03 Jan, 20:39


ግቢ ገብርኤል ለንግሥ ስሳለም ሰረቅ አድርጌ አይቼ ማፍረሱ በአጥሩ ተወስኖ የሚቀር መስሎኝ ተስፋ አድርጌ ነበር። ዛሬ ስደውል ሙሉ ለሙሉ በመነሣት ላይ መሆኑን ሰማሁ። ተለዋጭ ቦታ ተገኝቷል። መልሶ መገንቢያ ገንዘብ አይሰጥም፣ የተጻፈውን ሕግ በሻረው ያልተጻፈ ሕግ መሠረት።
--

ግን ግን...ከሠላሳ በላይ ጳጳሳት የወጡበት እጅግ ታሪካዊና የበርካታ ሊቃውንት መፍለቂያ እንዲህ ሲሆን ለቤተ ክህነት ሰዎች ብቅ ብሎ፥ መምህራኑና ደቀ መዛሙርቱን ማጽናናት፣ እንዴት ሆናችሁ ማለት ያስኮንናል? ቦታው ላይ ያለው የባይተዋርነት አይዞህ ባይ አባት የማጣት ስሜት ይከብዳል። በጠቅላይ ቤተ ክህነት ያላችሁ የሥራ ኃላፊዎች ከገዳሟ ጋር በመቀናጀት ጉዳዩን በባለቤትነት ያዙት፣ የምንችለውን እንታዘዛለን። እናምናለን፣ ታቦቷም ለልጇቿ መሆን ይቻላታል።

በአማን ነጸረ

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

01 Jan, 23:09


https://youtu.be/66O3t7CxqsE?feature=shared

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

01 Jan, 16:24


ታዕካ ነገሥት

ዛሬ ታኅሣሥ 22 ቀን 2017 ዓ.ም የ 92 ዓመተ ምሕረቱ አንጋፋው የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ መንፈሳዊ ትምህርት  ቤት በዕለተ ሠሉስ በሦስት ሰዓት ማፍረስ ተጀመረ።

በውስጡ ያሉት ካህናት፣ አዳሪ ተማሪዎች፣ ጡረተኞች፣ መምህራንና ልዩ ልዩ በገዳሙ ውስጥ ነዋሪ የሆንን ኹሉ አንዳችም ማረፊያ ሳይሰጠን ነው ገዳሙ እየፈረሰ ያለው። (የኔታ የማነ ብርሃን ጌታሁን (ዘበአታ), Jan 1 at 08:19)

በውስጡ የነበሩ ካህናት አዳሪ የማሪዎች፣ መምህራን፣ ጡረተኞች ምንም አይነት መጠለያ ሳይሰጻቸው ነው ፈረሳው የተካሄደው።

ከመጀመሪያው ነበር ሕንጻ የሚታነጽ ከኾነ ሕዝቡ ከቤተክርስቲያን አካባቢ ሳይርቅ ልማት እንዲሠራ አድርጉ ብለን የነበረው። እነ አቡነ አብርሃም አቤላዊ መሥዋዕት ነው ብለው ቡራኬ የሰጡት የኮሪደር መዓት መሠረቱን እየናደው ነው።

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

31 Dec, 19:16


ባለሀብቱ በራቸው ላይ በተተኮሰባቸው ጥይት ተገደሉ

(መሠረት ሚድያ)- ታዋቂው የአክሰስ ኮም ኩባንያ ባለቤት እና የሸበል በረንታ ሲሚንቶ ፋብሪካ ስራ አስኪያጅ አቶ ቢረሳው ምናለ ትናንት ምሽት 1:30 ላይ ቤታቸው በር ላይ በጥይት ተመትተው እንደተገደሉ ታውቋል።

መሠረት ሚድያ የደረሰው መረጃ እንደሚጠቁመው ባለሀብቱ በለሚ ኩራ፣ ወረዳ ዘጠኝ 'አትሌቶች መንደር' መውረጃ አስፓልት አጠገብ በሚገኝ መኖሪያ ቤታቸው በር ላይ መኪና ውስጥ ሆነው የግቢው በር እንዲከፈት ክላክስ እያደረጉ ባሉበት ወቅት በጥይት ጥቃት ተፈፅሞባቸዋል።

"በሰዓቱ የአስፓልቱና የአካባቢው መብራት ጠፍቶ ነበር" የሚሉት የአካባቢው ነዋሪዎች በአካባቢው ምንም የፀጥታ አካል አልነበረም፣ በስፍራው የደረሱትም ነግቶ ነው ብለዋል።

የምስራቅ ጎጃም ቢቸና ወረዳ ተወላጅ የሆኑት እና የ 'ምናሉ ሆቴል' ባለቤት አቶ ቢረሳው የቀብር ስነስርዐት በዛሬው እለት በሳሊተ ምህረት ቤተክርስቲያን ተፈፅሟል።

መሠረት ሚድያ የአዲስ አበባ ፖሊስን በግድያው ዙርያ መረጃ የጠየቀ ሲሆን "መረጃው አልደረሰንም" የሚል ምላሽ አግኝቷል።

መረጃን ከመሠረት!

@MeseretMedia

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

31 Dec, 19:13


#በወላይታ_ሁምቦ_እና_አበላ_አባያ ወረዳዎች ከሰሞኑ የተፈጠሩ ኹለት ክስተቶች ትኩረት ይሻሉ!

ፓርቲያችን ከቦታው በደረሰው መረጃ በወላይታ ዞን፣ አበላ አባያ ወረዳ፣ አባያ ክላስተር በሚባል የእርሻ ልማት ከሲዳማ ክልል መጡ በተባሉ የልዩ ኃይል አባላት እንደተከፈተ በተገለጸ ተኩስ የሰው ሕይወት ጠፍቷል፤ በርካቶችም ቆስለው ሆስፒታል ይገኛሉ። እስከ አኹንም በአካባቢው ከፍተኛ ውጥረት እንደነገሰ መሆኑን መረዳት ችለናል። "ችግሩ ትኩረት ሰጥቶ የሚፈታው አጥቶ እንጂ የሰነበተ ነው" የሚሉት ነዋሪዎች "የአኹኑ ግን ኃይል የቀላቀለና ለአገር ብዙ ውለታ የዋሉ የቀበሌው አስተዳደር ጭምር በተኩስ የተገደሉብት ጭምር ነው" በሚል የችግሩን ሥር ሰደድነት ያስረዳሉ። ፓርቲያችን ለሟች ቤተሰቦች ሐዘኑን ይገልጻል፤ መጽናናትንም ይመኛል።  

እንዲኹ በዚያው በወላይታ ዞን፣ ሁምቦ ወረዳ፣ ጠበላ ከተማ አስተዳደር ሥር ከጥምቀተ ባህር ይዞታ ጋር በተያያዘ ከፍተኛ ውጥረት እንዳለ ፓርቲያችን መረዳት ችሏል። ከዚኽ ቀደም ከጥንት ጀምሮ የጥምቀተ ባህር የነበረ ይዞታ በቀበሌው አስተዳደር ድፍረት በተሞላበት አኳኋን ጠረጴዛ ልማት ማኅበር ለሚባል የተወሰነ ቆርሶ የሰጠና ልማት ማኅበሩም ቀጥሎ ሙሉ በሙሉ በማጠሩ በተፈጠረ ችግር ተበደልን ባሉ ካህናትና ምዕመናን ላይ ፖሊስ እሥርና ከፍተኛ እንግልት እያደረሰ እንደሚገኝ ከአካባቢው ኗሪዎች መረዳት ችለናል። መለየት በሚያስቸግር አኳኋን ተዋልዶና ተፋቅሮ በሚኖር ማኅበረሰብ መሐል ኹኔታውንም ሃይማኖታዊ ለማስመሰል የቀበሌው አስተዳደርና የፀጥታ ኃይሉ ከፍተኛውን ሚና ተጫውቷል።  

በተጠቀሱ በኹለቱም አካባቢዎች በማኅበረሰቡ ላይ እየደረሰ ያለው እንግልት በአካባቢውም ከአካባቢውም ውጭ ሕዝቡን እረፍት መንሳት ሲሆን በተጠና መልኩ ለአሥርት ዓመታት እየተተገበረ ያለውና ሕገ መንግሥታዊ  ማዕቀፍ ያለው የከፋፍለህ ግዛ ፖሊሲ ውጤት እንደሆነ እናት ፓርቲ በጽኑ ያምናል።

ፓርቲያችን የተፈጠረውን ችግር የክልሎቹ መንግሥታት እንዳላዩ ከማለፍ በአፋጣኝ ገለልተኛ፣ ሚዛናዊና ሕጋዊ መፍትሔ እንዲሰጡ፤ ማኅበረሰቡም በክልሉም ከክልሉም ውጭ እረፍት የሚያገኝበትን ኹኔታ እንዲመቻች በአጽንዖት ያሳስባል። 

እግዚአብሔር አገራችን ኢትዮጵያንና ሕዝቧን ይጠብቅ! 

እናት ፓርቲ
ታኅሣስ ፳፪ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

31 Dec, 07:32


ይህ ቤት እየተመራ የሚገኘው ከኢአማኒና ከሐዲ ቤተመንግሥት ደብዳቤ ተቀብሎ ፥ የሐዋርያትን ቀኖና ሽሮ "ንጹሕ እገሌ ብሔር ሾምኩ" የሚል፥ የጥምቀት ልጆችን ከዘረኛ ሥርዓት ጋር ተባብረው ያስፈጁ፥ ክህነት የማይገባቸ ውክህነት አልባዎች ሁሉ ጳጳስ"ብፁዕ" (ለምሳሌ ከተወገዘ በሗላ መልሶ የክህነትን ሥራ የሰራ (በወሰሶ ከተወገዜና ክህነታቸውን ከአጡ በኋላ ወደ ኋላ ያወገዙ ጳጳሳት) ተብለው የሲኖዶስ አባላት በሚባሉበት የሕገወጦች ጉባኤ አንድ መልካም ሰው ለውጥ ያመጣል የሚለው የዋህነት ልክ አብይ አህመድ አንድ በወቅቱ በብወቸ ችየዋሃ ንአእምሮ በመልካምነት የሚታይን አቶ "ዳንኤል ክብረትን" አስጠግቶ ሚሊዮቸችን የኦእቶዶክስ ተከታዮች ቢያን ስለ6 ዓመታት ያደነዘዘበት አይነት የማታለል እርምጃ ነው።

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

31 Dec, 07:32


መምህር የምሰማው እውነት ከሆነ እግዚአብሔር ያውጣዎት።

ተወዳጅ መምህር የጠቅላይ ቤተ ክህነት ምክትል ሥራ አስኪያጅ አደረጓቸው ሲባል ሰማሁ። እጅግ ደነገጥሁ፣ እጅግም አዝናለሁ።

ያ ቦታ ህሊና ላለው፣ እምነት ላለው፣ የቤተ ክርስቲያን ተልእኮ ለገባው፣ ከዘረኝነት ደዌ ለሚሸሽ፣ ሙስናን ለሚጸየፍ፣ አድርባይ ለማይስማማው፣ ለቤተመንግሥቱ ለማያሸረግድ፣ የሰማዩን አባት እግዚአብሔርን "አባቴ" ብሎ ራሱን በልጅነት ለመግለጥ ለሚፈልግ ሰው እንደማይሆን ባለፉት ፲፯ ዓመታት በቀጥታ በመሳተፍ አይቼዋለሁ።

እንደኔ ሙሉው የቤተ ክህነት አስተሳስብ፣ አሠራር፣ የሙስናው ማኅበር፣ የዘር ፖለቲካ አገልጋዮች ተጠራርግው እንዲወጡ ማድረግ እስከሚቻል ድረስ እንዲህ አይነቶች መልካም ወገኖቻችን ምንም ለውጥ ላያመጡ ሄደው ረገረጉ ውስጥ በመግባት ራሳቸውን ባያበላሹ የሚል ምኞትና ምክር አለኝ።

መምህር እግዚአብሔር ያውጣዎ። ምንም አይነት ለውጥ ማምጣት እንደማይችሉ ብቻ ሳይሆን እርስዎም ችግር እንደሚደርስብዎ ላረጋግጥልዎ እወዳለሁ።

======== በእኔ መረዳትና ልምድ
መዋቅራዊ ለውጥ የሚመጣው አንድ ደህና ግለሰብ በመሳብ ሳይሆን ጨክኖ የጠፋውን ቀነኖና ወደ ቦታው በመመለስ፥ የዘር ጳጳሳትን መሻር፥ የከተማ መነኮሳትን ወደ ገዳም መመለስ፥ ሕገ ቤተ ክርስቲያንን ከከሀድያን ማፍያ እጅ ነጻ አድርጎ በትርህምት በሚኖሩ አባቶችና ምእመናን ተሳትፎ መምራት ሲቻል ብቻ ነው።

ቤተ ክህነታነን እንድን ጤናማና ተወዳጅ ሰው ወደ ተበላሸ ረገረግ አስገብቶ አሳምሞ የማስወጣት ፋብሪካ ነው ከመሰለ ቆይቷል።👇👇👇

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

28 Dec, 15:15


ፎቶ ፦ ዓመታዊው የታህሣሥ 19 የሊቀ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል የንግሥ በዓል በሐዋሳ ከተማ ተከብሯል።

የንግሥ በዓሉ እጅግ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ኦርቶዶክሳውያን በተገኙበት ነው የተከበረው።

የሲዳማ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ በዓሉ ያለ አንዳች ኮሽታ በሰላም በከፍተኛ ድምቀት ተከብሯል ብሏል።

የፎቶ ባለቤት ፦ የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር

@tikvahethiopia

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

28 Dec, 15:15


ፎቶ ፦ የታኅሣሥ 19 የሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ክብረ በዓል በቁልቢ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ገዳም በሰላም በድምቀት ተከብሮ ውሏል።

በበዓሉ ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ፣ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ተገኝተው ነበር።

በክብረ በዓሉ ላይ ቅዱስነታቸው ቃለ ምዕዳን እና ቡራኬ ሰጥተዋል።

በቁልቢ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል በዓል ላይ እጅግ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ምእመን ተገኝቶ ነበር።

ዓመታዊው የታሥሣ 19 የሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ክብረ በዓል በተለያዩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አህጉረ ስብከቶችም ተከብሮ ውሏል።

የፎቶ ባለቤት ፦ የኢ/ኦ/ተ/ዋ/ቤተ ክርስትያ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ


@tikvahethiopia

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

26 Dec, 16:39


#የሰብአዊ_መብት_ተቋማት_መታገድ #ገላዊ_ኃላፊነትና_የምንፈልገው_ለውጥ! https://www.youtube.com/live/yGtRUEIJRDs?si=X7gZ4E5cm9-PmmWz

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

26 Dec, 10:07


ሐሙስ ታህሳስ 17ቀን 2017 (አዲስ ማለዳ) የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ባለሥልጣን አንጋፋውን የሰብዓዊ መብት ተሟጋች የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባኤን ማገዱ ተገልጿል፡፡

ኢሰመጉ የታገደው ከተቋቋመለት ዓላማ ውጭ ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ አድርጓል በማለት ሲሆን የመንግሥት ጸጥታ ኃይሎች በአመራሮቹና ሠራተኞቹ ላይ ማስፈራሪያና ዛቻ እንደሚፈጽሙ ለበርካታ ወራት ሲገልጽ መቆየቱ ይታወቃል፡፡

የኢሰመጉ ዋና ዳይሬክተሩ ዳን ይርጋ በዚሁ ዛቻና ማስፈራሪያ ሳቢያ ከአገር ለመሰደድ እንደተገደዱ በቅርቡ መግለጹ ማስታወሱን እና በትናንትናው እለት መታገዱን ዋዜማ ዘግቧል፡፡

ባለሥልጣኑ በዲሞክራሲና መብቶች ዕድገት ማዕከል እና ጠበቆች ለሰብዓዊ መብቶች በተሰኙት ሲቪል ማኅበራት ላይ ባለፈው ኅዳር ወር በተመሳሳይ ምክንያት ጥሎት የነበረውን እገዳ ካነሳ በኋላ፣ ድርጅቶች የተሰጧቸውን የማስተካከያ ርምጃዎቾ ተግባራዊ አላደረጉም፤ ይልቁንም የቀድሞ ጥፋታቸውን ቀጥለውበታል በማለት በቅርቡ በድጋሚ እንዳገዳቸው አይዘነጋም።

በተመሳሳይ የመብቶች እና ዴሞክራሲ ዕድገት ማዕከል (ካርድ) ጨምሮ ሶስት የሰብዓዊ ተሟጋች ድርጅቶች ላይ እገዳ ተጥሎ እንደነበር እና ቆይቶም እገዳው የተነሳ ቢሆንም በድጋሚ እገዳው ተጥሏል የሚል መረጃዎች ሲዘዋወሩ ቆይተዋል፡፡

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

25 Dec, 19:49


ከ13 ቀናት እስር በኃላ ተፈተናል።

ሳንደባልቅ፣ሳንለይ ዝንት ዓለም ርዕሳችን ቅድስት ቤተክርስቲያን ናት።

ክብሯ ብርሃን፣ቅድስናዋ ጸዳል፣ንጽህናዋ ምልክት ከሆነችው ቅድስት ቤተክርስቲያን ውጪ ምን የሚያከብር ርዕስ አለ?

ወደ መስዋትነት እና መከራ በፍጹም አንሄድም። መሰዋት እና መከራ ግን አፍጦ ከመጣ መንፈስቅዱስ ያጸናንን ዘንድ ብቻ እንማጸናለን!!!

ከነገድ ከቋንቋ፤ከዓለም ክብር እና ሞገስ ነጥቆን የብርሃን ልጆች ላደረገን የድንግሊቱ ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስ ክብር ምስጋና ይገባው።

🙏🙏🙏

Kune Demelash kassaye -Arba Minch

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

23 Dec, 20:45


#ቱንቢ_ዜና_ልዩ_ዘገባ "#ኦርቶዶክስ_እንደሆን_ግደሉን" የሰላሌ የኦሮሞ ኦርቶዶክሳውያን ሰማእታት ጽናት "ባሎቻችሁን አምጡ በሚል #የእናቶች_የጅምላ_እስር_በአማራ "የትግራይ አሁናዊ ቀውስ ዋነኛው መንስኤ የመዓድን ጉዳይ እና #በትግራይ_ሦስት_ሰዎች_ግድያና_የመዓድን_ጉዳይ #ሌሎችም_አሁናዊ https://youtu.be/DZFgLyeiHZE

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

23 Dec, 12:15


መከራ የትንሣኤ ምልክት ነው።
የዛገ ብረት ከዝገቱ የሚነጻው በእሳት ኃይል ነው።የዛገ ህሊናም ዝገተ ስንፍናውን ወደ ትንሣኤ ህሊና የሚቀይረው በመከራ መስቀል ነው።
በመስቀል ከውር ላይ ከዝገተ ኃጢአት ከዝገተ ነፍስ ከዝገተ ትሩፋት እንላቀቃለን።
ብረት ከቅዝቃዜውም የሚግለው በእሳት ግለት ነው።እሳቱ የብረቱን ዝገቱንም ቅዝቃዜውንም ያስወግድለታል።
ወይም በእሳቱ ሙቀት ብዛት ብረቱ ይታደስበታል።
በመስቀል ሕይወት እና በፈተና ውስጥ ያለ አማኝም እንዲሁ ነው።ይበልጥ ሲፈተን ይበልጥ ይግላል።ይበልጥ ሲግል ይበልጥ ቅዝቃዜው ድንዛዜው ይለቀዋል።
ጽኑዕ አማኝ እንደ ንሥር የሚታደረው በሕይወቱ ውስጥ በሚያገኘው የመስቀል ፈተና ነው።እግሩን ለጠጠር ደረቱን ለጦር፣እጁን እግሩን ለተሳለ ቀኖት፣አፉን ለመራራ ሀሞት ሰጥቶ፦ሊደርስባት የፈለጋትን የተስፋ መስቀል ዓላማውን እስኪያሳካ ድረስ ያጋጠመውን ፈተና ታሪክ እያደረገ እንደ ነቢይ ወደፊት እያየ መጓዝ ይጠይቀዋል። ሐዋርያ ትሩፋት ቅዱስ ጳውሎስ፦"ወንድሞች ሆይ እኔ ገና እንዳልያዝሁት እቈጥራለሁ ነገር ግን አንድ ነገር አደርጋለሁ በኋላዬ ያለውን እየረሳሁ በፊቴ ያለውን ለመያዝ እዘረጋለሁ።"ፊል.፫፥፲፫ እንዳለ።
የወርቅ ጽርየት በእሳት ግለት የመዶሻ ብዛት እንደሆነ የእውነት የመስቀል መገለጫዋም በብዙ መከራ እና ፈተና ውስጥ ነው።
ሳይሰቀሉ ክብር ሳይሞቱ ትንሣኤ ሳይነሡ ዕርገት የለም።
ደጉ ገበሬ እንኳን የዘራው ዘር ከልበሰበሰ አይበቅልም።ይበልጥ ለመብቀል ዘሩ ይበልጥ ወደ ጭቃው መጣል አለበት።
ይበልጥ በጸጋ ዓላማ ውስጥ ለማደግ ማለፍ ያለብንን የፈተና በር ማለፍ ግድ ይላል።
አንበጣ ከሞተበት  ቦታ ሽህ ሁኖ ይወለዳል ዓላማ ያለው ሰውም ከዋለበት ቦታ ሽሁን ባለ ራዕይ በለ ሃይማኖት ያደርጋል።ቢሞት እንኳ ከመስቀሉ ሥር ብዙ ሕያዋን እንደተነሡ ከተግባረ መስቀሉ ሥር መስለውት የሚሠሩ ይነሣሉ። ከቀደመው የበረቱ ይሆናሉ።መጽሐፍ፦"በውርደት ይዘራል በክብር ይነሣል በድካም ይዘራል በኃይል ይነሣል።"
፩.ቆሮ.፲፭፥፵፫ እንዲል።
ለጊዜው በመከራ መስቀል ማማጥ ግድ ነው።መከራው ተለውጦ በክብር መወለድ ግን አይቀሬ ነው።የወንጌል ተስፋ ከመስቀል በኋላ ባለ ትንሣኤ የተሰበከ ብሥራት ነውና።ያ ብሥራት ደግሞ "ሕያውን ከሙታን ጋራ ምን ትሹታላችሁ? ተነሥቶአል እንጂ በዚህ የለም።"ሉቃ.፳፬፥፭ እየተባለ የሚነገርለት እውነት ነው።
ኃይል መንፈሳዊት ስታድር መግነዘ መከራን ፍቱልኝ መቃብረ ፍርሀትን ክፈቱልኝ ማለት ይቀርና በሕይወት መመላለስ ይሆናል።
ስለሆነም ለምን መከራ መስቀሉ አገኘን? ለምን ፈተናው መጣብን? ማለቱ ይቀርና እንዴት የመስቀል ሕይወትን መለማመድ? እንዴት ማለፍ እንችላለን? የሚለው የተግባር ጥያቄ ይሆናል።

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

06 Dec, 18:19


https://www.youtube.com/live/6nYrBoTW71c?si=nA925RMiSiqftPTf

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

05 Dec, 20:07


🔈 በሻሸመኔ ከተማ ኢሰመኮ ባደረገው ክትትል እና ምርመራ ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በታች መሆኑን የገለጹ ሕፃናት " ወታደራዊ ስልጠና ትገባላችሁ " በሚል ወደ ማቆያ አዳራሾች እንዲገቡ መደረጋቸውን አረጋግጧል።

በሁሩፋ ክፍለ ከተማ፣ ሀሌሉ ወረዳ ውስጥ በማቆያ አዳራሽ ከነበሩ እና ኢሰመኮ ካነጋገራቸው 32 ሰዎች መካከል 14ቱ ዕድሜያቸው ከ15 እስከ 16 ዓመት መሆኑን የገለጹ ሲሆን አንድ ሕፃን ደግሞ ዕድሜው 11 ዓመት መሆኑን ገልጿል።

ከት/ቤት ሲወጡ #ከነዩኒፎርማቸው ፤ ሀሌሉ ወረዳ ወደ ሚገኘው ማቆያ አዳራሽ እንዲገቡ የተደረጉ የ5ኛ ክፍል ተማሪ የሆኑ ሁለት የ15 ዓመት ሕፃናት ወደ አዳራሽ ከገቡ ሁለት ሳምንት እንደሆናቸው ገልጸው የገቡበትን ሁኔታም አስረድተዋል።

ሕፃናቱ ፤ “ ከትምህርት ቤት ስንመለስ መከላከያ ለሚገቡ 25,000 ብር ይሰጣል ብሎ አንድ ግለሰብ በባጃጅ አሳፈረን፤ ከዚያ 010 ቀበሌ (ሀሌሉ ወረዳ) ወደ ሚገኘው አዳራሽ ገባን፤ ነገር ግን ከገባን በኋላ መውጣት አልቻልንም  ” ሲሉ ነው የገለጹት።

በጅማ ከተማ ኢሰመኮ ያነጋገረው የ14 ዓመት ሕፃን ስለተያዘበት ሁኔታ ሲያስረዳ፦

“ ኅዳር 2 ቀን 2017 ዓ.ም. ከምሽቱ 2፡30 ሰዓት አካባቢ ወደ ቤት እየሄድኩ እያለሁ መንገድ ላይ ቆመው የነበሩ ሚሊሻዎች ባትሪ አብርተውብኝ አስቆሙኝ፤ መታወቂያ ሲጠይቁኝ ዕድሜዬ ገና 14 ዓመት ነው፤ የ7ኛ ክፍል ተማሪ ነኝ መታወቂያ የለኝም ብዬ ስመልስ፣ ቀበሌ ሄደህ ጉዳይህ ይጣራል በማለት ወደ ቀበሌ ወስደው ብዛታቸው ከ20 በላይ ከሚሆኑ ወጣቶች መካከል ቀላቅለውኝ ሄዱ። ለመከላከያ ሰራዊት አባልነት መያዜንም ወጣቶቹ ናቸው የነገሩኝ። በማግስቱ በድብቅ ለቤተሰቦቼ ደውዬ ካሳወቅኩ በኋላ ለመውጣት ችያለሁ ” ብሏል።

#EHRC #OROMIA

@tikvahethiopia

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

05 Dec, 12:54


በቅርብ ዓመታት ጎጃም አካባቢ ሦስት አዳሪ የመጽሐፍ ጉባኤ ቤቶች ተቋቁመዋል። እነዚህ ጉባኤ ቤቶች እንዲቋቋሙ ደግሞ የየኔታ ገብረ መድኅን ድርሻ እንዲህ በቀላል የሚታይ አይደለም። እነዚህም ጉባኤ ቤቶች፦

፩ኛው.#ፈለገ #ሕይወት ጉባኤ ቤት ሲሆን የሚገኘውም በእንጅባራ ከተማ ነው። መምህሩ መምህር ሠናይ ክንዴ ይባላሉ። አሁን ላይ ጉባኤ ቤቱ ብዙ ደቀመዛሙርትን ይዞ እያስተማረ ይገኛል።

፪ኛው.#ፈለገ #አበው ጉባኤ ቤት ነው። ይህ ጉባኤ ቤት የሚገኝበት ቦታ በቡሬ ከተማ ሲሆን ወንበር ዘርግተው የሚያስተምሩትም ሊቀ ጉባኤ ኤርምያስ ወልዴ ይባላሉ። ይህም ጉባኤ ቤት በማስተማር ላይ ይገኛል።

፫ኛው.#ፈለገ #ጥበብ የሚባለው ጉባኤ ቤት ነው። ይህ ጉባኤ ቤት የሚገኘው በምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት በደብረ ማርቆስ ከተማ ሲሆን መምህሩም መምህር ለዓለም ብርሃኑ ይባላሉ። ሐዲስ ከየኔታ ስምዐ ኮነ ብሉይ ከየኔታ ገብረ መድኅን ተምረዋል።

ፈለገ ጥበብ ጉባኤ ቤት ከተመሠረተ የተወሰኑ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ወደ አደባባይ ወጥቶ በገሀድና በግላጭ አግዙኝ ብሎ አያውቅም። አሁን ግን አዳሪ ጉባኤ ቤት አንድመሆኑ መጠን ካለው ወቅታዊ ሁኔታ ጋር ተያይዞ በትልቅ ፈተና ውስጥ ይገኛል።

በእርግጥ በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ያሉ ጉባኤ ቤቶች የየዕለት መከራቸውና ስቃያቸው እንዲህ የሚነገር አይደለም። ሆኖም መከራቸውን ለማቅለልና የነገ ትውልድ እንዲደርስባቸው ድርሻው በዚህ ትውልድ ላይ ነው።

እናም ምሥራቅ ጎጃም ላይ ቤተ ክርስቲያኒቱ ካሏት የመጽሐፍ ጉባኤ ቤቶች መካከል አንዱ ፈለገ ጥበብ ጉባኤ ቤት በጸና ችግር ላይ ነው። ይህን ጉባኤ ቤት ማገዝ፣ ማበርታት፣ ከጎኑ መቆም ከእያንዳንዳችን ይጠበቃል።

የጉባኤ ቤቱ አካውንት፦
1000560124272

ለበለጠ መረጃ በዚህ ይደውሉ፦

0938312296
0978539652

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

03 Dec, 18:17


https://youtu.be/jzW0DzaOMCI?si=xjvDadd5xbEXMFTE

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

03 Dec, 14:56


#ዜና_ምሥራቅ_ወለጋ

“ከፈጠሪ በታች ራሳችንን እንከላከልበት ዘንድ የታጠቅነውን መሣሪያ ከበባ አድርገው ገፈውናል፤ አኹን ለእርድ ተዘጋጅተን በመጠበቅ ላይ ነን፡፡” 

በኦሮሚያ ክልል፣ ምሥራቅ ወለጋ ዞን፣ አንዶዴ ዲቾ፣ ደጋ ጂጊ ቀበሌዎች ትናንት ኅዳር ፳፬ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም መከላከያ ሠራዊት ነን ያሉ ኃይሎች ንጋት አሥራ አንድ ሰዓት እስከ ጠዋት ሦስት ሰዓት አዘናግተው ከበባ በማድረግ ራሳችንን እንጠብቅበታለን ብለን ከብቶቻችንን ሸጠን በመንግሥት እውቅና የገዛነውን መሣሪያ ገፈውናል ያሉት ነዋሪዎች አኹን ራሳችንን ለእርድ አዘጋጅቶ እንደመጠበቅ ነው የምንቆጥረው ብለዋል፡፡

ባለፈው እናት ፓርቲና ሌሎች የሕዝብ ሰቆቃ የሚገዳቸው ሚዲያዎች ቦታው ድረስ በመደወል ጭምር ድምጻችንን ካሰማችሁልን ወዲህ መከላከያው መሣሪያ ማስፈታቱን ትቶት ነበር፤ ተግባብተንም እንዲህ እንደማይሆንም ተነጋገረን ነበር ያሉት የቀበሌው ነዋሪዎች አዘናግተው ይኽንኑ በመሸሽ ወደ ጫካ ገብቶ የነበረውም ከጫካ ከተመለሰ በኋላ በተኛበት እንደሽፍታና ቀማኛ ከየቤቱ አውጥተው ከ80 የማያንስ የነፍስ ወከፍ መሣሪያችንን ወስደዋል ብለዋል፡፡ በአካባቢው ላሉት ወታደራዊ አዛዥ ደውለን ስንነግራቸው ‘ማን ነው ይህን ያደረገው?’ በሚል ንጋት ሦስት ሰዓት ላይ እንዳስቆሟቸው ነዋሪዎች ገልጸውልናል፡፡ በዚኽም የተወሰኑ የሠራዊቱ አባላት በወረዳና ዞን አመራሮች የተሳሳተ ሥምሪት እንደወሰዱ ማወቅ ችለናል ብለዋል፡፡ ይህ ደግሞ የበለጠ ሥጋት እንዲገባን አድርጓል ይላሉ፡፡ አኹንም መሣረያችንን አንሰጥም፣ ዐይናችን እያየ አንሞትም ያሉ መልሰው ጫካ ገብተዋል፡፡ የዞንና ወረዳ ካድሬዎችም ጫካ የገባውን ቤተሰቡን እናስራለን፣ እንቀጣለን እያሉ እንደሚዝቱ ነዋሪዎቹ ተናግረዋል፡፡

“መሣሪያውን ከእኛ ነጥቀው ‘የራሳችን’ ለሚሉት ሰው ነው የሚሰጡት” ያሉት ነዋሪዎች “ቢያንስ መሣሪያ ማስወረዱ ለመልካም ተፈልጎ ነው ካሉ ለምን ብሔር[ማንነት] ልዩነት ይደረጋል?” ብለዋል፡፡

ፓርቲያችን በተደጋጋሚ እንደገለጸው መንግሥታዊ መዋቅሩ ባልጠራበት፣ ጥቂት የማይባሉት በኹለት ቢላዋ በሚበሉበት፣ በድብቅም በገሃድም ከፍተኛ የጥላቻ ንግግሮችና ተግባራት እያስተዋልን ባለበት በአኹኑ ወቅት ሕዝቡ በራስ ተነሳሽነት ራሱን ለመጠበቅ እያደረገ ያለው ጥረት ሊደገፍና ሊበረታታ እንጂ እንደወንጀል ሊቆጠር አይገባም። የምሥራቅ ወለጋውም ጉዳይ ከዚኽ ተነጥሎ የሚታይ አይደለም፡፡ በአካባቢው ከፍተኛ ዘር ተኮር ጭፍጨፋ የተከሰተና ያለ በመሆኑ ለሕዝቡ አስተማማኝ ጥበቃ እስከሚደረግ ራስን መከላከል አማራጭ ተደርጎ፣ በሕግና በሥርዓት እንዲመራ ማድረግ እጅ ላይ ያለ የተሻለ አማራጭ መሆኑ መታወቅ አለበት። የጸጥታ ኃይሉ ትርጉም ያለው ጥበቃ ለዜጎች በማያደርግበት ኹኔታ ነዋሪው ራሱን የሚከላከልበትን መሣሪያ መቀማት በቅርቡ በአርሲ የተከሰተው ዓይነት ጥፋት ለማድረስ ካልሆነ ሌላ ትርጉም ሊሰጠው እንደማይችል ታውቆ የእርምት እርምጃ በአስቸኳይ እንዲወሰድ እናት ፓርቲ ያሳስባል።

እግዚአብሔር አገራችን ኢትዮጵያንና ሕዝቧን ይጠብቅ!

እናት ፓርቲ
ኅዳር ፳፬ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

01 Dec, 14:56


የእኛ አባቶች የደስታ ምንጭ ዛሬም ሕንጻና ገንዘብ ነው። የሕንጻ ማማር የገንዘብ ብዛት የቤተክርስቲያንን ማደግ የምእመናንን መንፈሳዊነት አያሳይም። ምእመናኑንም ካህናቱንም እንደ ትልቅ የቅድስና ሥራ ስኬት የምናየው ሕንጻ ማነጽ ነው።

አረጋዊው አባት አቡነ ቀውስጦስ በማምሻ እድሜያቸው ሀገረ ስብከታቸው አዲስ አበባ ዙሪያ ኾና ሳለ 132 አብያተክርስቲያናት ተዘግተዋል። እሱ አያሳስባቸውም፣ ቤተክህነት ያቆመው ሕንጻ ግን ከሞታቸው ቀድሞ ስለተሰበሰቡበት ተደስተዋል።

ያንሳል ብለው ያሰቡት ገንዘብ ጨምሯል። ይኽ ነው አዳራሹን ኹሉ የሚያስጨበጭቡት። ጥቁር ድንኳን ተክለን ማልቀስ ባለብን ሰዓት በሕንጻ እናጨበጭባለን።

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

30 Nov, 19:57


https://youtu.be/NRggn_vxyzo

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

30 Nov, 16:57


የሽርካ ወረዳ ነዋሪዎች ምን አሉ ?

" ከዚህ ቀደም ሰዎች ይታገታሉ የሆነ ብር ተከፍሎ ይለቀቁ ነበር። አሁን የተፈጸመው ግን እጅግ አስከፊ ነው " - ነዋሪዎች

የሽርካ ወረዳ፣ ፈረቀሳ ነዋሪዎች ትላንት ለሊት 9 ሰዎች በአሰቃቂ ሁኔታ መገደላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ቃላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡ ነዋሪዎች ምን አሉ ?

" በዚህ ሳምንት ሞት አላቋረጠም፤ ቢያንስ ላለፉት ሦስት ቀናት በአከባቢው በተለያዩ ቀበሌያት የሞት አላቋረጠም።

ትላንት ደግሞ በእኛ ቀበሌ ፈረቀሳ የእነዚህ 9 ሰዎች ተገድለዋል። እጅግ አሳዛኝ ነው።

5 ሰዓት ላይ ተኩስ ተጀመረ ግድያው ለሊት 8:00 ገደማ ነው የተፈጸመው።

በየቤታቸው በመሄድ ለቅመው አንድ ላይ ካከማቿቸው በኋላ ነው ጅምላ ጭፍጨፋ ያደረጉባቸው።

ከዚህ ቀደም ሰዎች ይታገታሉ የሆነ ብር ተከፍሎ ይለቀቁ ነበር። አሁን የተፈጸመው ግን እጅግ አስከፊ ነው።

ሰዎቹ ምንም አይነት የሌላ ንክኪ የላቸውም ፤ በኃንማኖት ተለይተውነው ይህ ጥቃት የተፈጸመባቸው።

ከሞቱት መካከል አባትና ልጅ እንዲሁም ባልና ሚስት ይገኙበታል።

3ቱ አብረው ታግተው ሳለ 9ኙን ሲገድሉ ይኑሩ ይሙቱ አይታወቅም።

ድርጊቱን የፈጸሙት የሸኔ አባላት ናቸው። ሆኖም ግን ምንም እንኳን ስሙ በሸኔ ይነገድ እንጂ በስሩ ሌላ ቡድን የተደራጀ አለ። ሙሉ ለሙሉ ሸኔ ለማለት ያስቸግራል።

በሌላ ቦታ ላይ የሸኔ አድራጎት ሲሰማ ብር ይጠይቃል ሰዎችን ይለቃል ፤ እዚህ ያለው ኃይማኖትን በመቃወም ጥቅም ለማግኘት የሸኔ ስም በመጠቀም የተደራጀ ቡድን አለ ብለን ነው የምናስበው።

የመንግስት አካላት ከዞንም መጥተው ዛሬ ላይ ደርሶ ' አይዟችሁ ነገ ላይ አጸፋውን እንመልሳለን አሳልፋችሁ ከሰጣችሁን ' በሚል የማጽናኛ ተስፋ ሰጥተውናል።

መከላከያውም የመንግስት አመራሩም አለ ገፋ አድርጎ ግን ለህዝብ መፍትሔ የሰጠ የለም።

ጫካውን ደኑን ተገን በማድረግ ግድያ ይፈጸማል።

ባለፈው ዓመት በነሐሴ ወር ነው የተጀመረው አለፍ እያለ እያረሳሱ አሉ የሚባሉ ሰዎች ሽማግሌ አይሉም አሉ የተባሉ ሰዎችን ተገድለዋል።

9ኙ የተገደሉት የአንድ ኃይማኖት አባላት ሲሆኑ ቀብራቸውም ዛሬ 9 ሰዓት ነው የተፈጸመው።

ህብረተሰቡ ነግ በኔ ነው እያለ ነው። ከቀብር መልስ የመንግስት አባላት ከዞን መጥተው አጽናንቶ ነው የሄደው።

አዝመራ ልንሰበስብ አንችልም። የቀበሌው አመራር ተደራጅተን አንድ ላይ ሆነን እንሰብስብ እያለን ነው። እንደዚህ በተደራጀ መልኩ የምንቀሳቀስ ከሆነ እንጂ ለዛሬውም አዳር ሰግተን ነው ያለነው።

በተለይ ወጣቱ በአሳዛኝ ሁኔታ ላይ ነው ያለው፤ ይኸው ይሄ ጩኸት 2 ዓመት ያስቆጠረ ነው ምንም የተደረገ ነገር የለም።

ሰርግ ኃዘን አንድ ላይ ነበር ያሳለፍነው ይሄ ተረስቶ አንድ ቢላ ነበር የሚለየን አሁን ላይ ግን በገቢያም በምንም ያለው ነገር ጎራ መከፈሉን ያሳያል።

በሃይማኖት አባቶች በኩል ህብረተሰቡን ለማቀራረብ ሞክረዋል። በተደጋጋሚ በተደረጉ ስብሰባዎች ግን ስብሰባዎች እየተበተኑ፤ ስብሰባውን ረግጠው እየወጡ ሳይሳካ ቀርቷል።

በድርድሩ ምንም አይነት መፍትሔ የሚመጣ አይመስለኝም የሃይማኖት አባቶች እንዳሉት ከፈጣሪ ከመጠበቅ በቀር ሌላ ምንም ተስፋ የምናደርገው ነገር የለም።

በቀጣይ ቀናትም በተመሳሳይ ጥቃት ይፈጸማል በሚል የአከባቢው ሰው ንብረቱን ትቶ አከባቢውን ለቆ ወደ ቤተክርስቲያንም ወደ ከተማ ቤት ተከራይቶም እየሄደ ነው ያለው።

አሁን ያለው ሁኔታ እንኳን ለወጣቱ ለአዛውንቱም የሚዘገንን ሁኔታ ነው። ምን አይነት ሰዓት ላይ ተፈጠርን በሚል ወጣቱ በኃዘን ተውጦ ነው ያለው።

በአከባቢያችን ካሉ 4 ቀበሌዎች ላይ ካሉ 5 እና 6 ደብሮች አገልግሎት የሚሰጠው አንድ የሚካኤል ደብር ነው። ቀብርም ካለ የሚፈጸመው እዛ ነው። ይህ ከሆነ አንድ አመት አልፎታል።

እንደ ወረዳው ግን ከ35 አብያተ ክርስቲያናት በላይ ተመሳሳይ እጣ ደርሷቸዋል። ሦስት አራት ደብሮች ናቸው አገልግሎት የሚሰጠው። ይህም በጸጥታው ምክንያት ነው።

ከ32 ቀበሌ ከየአቅጣጫው ተመርጦ የሚገደለው ግን የሀገር ሽማግሌ ነው ከዚህ ቀደምም እየተመረጠ አልቋል። ይሄን ያህል ነው ጥቃት የደረሰብን።

የሚመለከተው አካል ከፈጣሪ ጋር የድረሱልን ጥሪ አሰሙልን ወገን ለወገን ደራሽ ነው። "

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

29 Nov, 18:49


ሌላው አሳዛኝ ዜና

ዉብሸት አስቤ ይባላል የምሥራቅ አርሲ ዞን ሽርካ ወረዳ ተወላጅ ነው።የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኮምፒዩተር ሳይንስ ዲፓርትመንት የ4ኛ ዓመት ተማሪ ሲሆን በዕለተ ማግሰኞ(ማግስተ ሰኞ) ኅዳር 18/2017 በዶርም ውስጥ ሞቶ ነው የተገኘው። ይህ ልጅ ምንም ሳይታመም እንዴት በዶርም ውስጥ ሞቶ ሊገኝ ቻለ?
በነገራችን ላይ ብዙ ኦርቶዶክሳውያን ተማሪዎች በየዩኒቨርሲቲው ይገደላሉ ለአንድ ቀን አጀብ አጀብ ይባላል በቃ በዚያው ይረሳሉ ዋላጆቻቸው ግን እድሜ ዘለዓለማቸውን በኀዘን ተኮራምተው ይኖራሉ።
ነፍስህ በሰላም ትረፍ😭

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

29 Nov, 15:53


በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን ዘጠኝ ሰዎች በታጣቂዎች መገደላቸውን የተጎጂ ቤተሰቦች ተናገሩ‼️
በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን ሽርካ ወረዳ ሐሙስ ዕለት ታጣቂዎች ዘጠኝ ሰዎችን ከቤታቸው በመውሰድ መግደላቸውን የተጎጂ ቤተሰቦች እና ነዋሪዎች  ተናገሩ።
ግድያው የተፈጸመው ሐሙስ ኅዳር 19/ 2017 ዓ.ም. ከሌሊቱ 6፡00 አካባቢ መሆኑን ቤተሰቦች ገልጸው፤ ታጣቂዎቹ ዘጠኝ ወንዶችን ከቤታቸው ከወሰዱ በኋላ ወንዝ አካባቢ እንደገደሏቸው ገልጸዋል።

ቤተሰቦች እንሚሉት ግድያው የተፈጸመው በአካባቢው በተደጋጋሚ ተመሳሳይ ጥቃቶችን ይፈጽማል ባሉት “በሸኔ ታጣቂዎች” መሆኑን ተናግረዋል።

በወረዳው ሶሌ ፈረንቀሳ በተባለ ቀበሌ ተፈጽሟል የተባለው ግድያ “ሃይማኖት ተኮር” እንደሆነ ነዋሪዎች እና ቤተሰቦች ገልጸዋል።

“በየቤቱ ይዘው በማገት ወደ ወንዝ አካባቢ ወስደዋቸው፤ ዘጠኙን አንድ ላይ አሰልፈው ነው የገደሏቸው” ያሉ አንድ የአካባቢው ነዋሪ፤ ከከሟቹች ውስጥ አንዱ የ42 ዓመት ዕድሜ ያላቸው አጎታቸው መሆናቸውን ተናግረዋል።

ከሟቾቹ መካከል ሁለት የ70 ዓመት አዛውንቶች እንደሚገኙ የተናገሩ አንድ ነዋሪ፤ ሌሎቹ ደግሞ ከ45 ዓመት በታች የሆኑ እና በግብርና ሥራ የተሰማሩ የአካባቢው ነዋሪዎች ናቸው ብለዋል።

ነዋሪዎች በጥቃቱ ቀን ከአካባቢው ሌሎች አምስት ሰዎችም ታግተው እንደተወሰዱ ገልጸው እስካሁን ታጋቾቹ እንዳልተገኙ ተናግረዋል።
⬇️⬇️⬇️👇👇👇👇⬇️⬇️
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

28 Nov, 13:51


“…ሀኪሞች ቀጠሮ ይዘን እና በአንድነት ተነጋግረን ተቃውሟችንን ገልፀን ራሳችንን ማጥፋት የሚለው ከብዙዎች ዘንድ ተነስቷል ይላል።
በዚህ መልኩ "እኛ ባንኖር ለሚኖሩት መፍትሄ እንሁን" በማለት ደብዳቤው ይጠቅሳል።”
+++++++++++++++++++++++++++++++++++++++
#ከዜናዎቻችን| የጤና ባለሙያዎች ለአመታት ለጠይቀናቸው ችግሮቻችን መፍትሄ ካልተሰጠን ራሳችንን ወደ ማጥፋት እንሄዳለን ብለው አስጠነቀቁ

(መሠረት ሚድያ)- መሠረት ሚድያ የተመለከተው እና እነዚህ የጤና ባለሙያዎች ውስጥ ለውስጥ በቴሌግራም መላላክያ የተቀባበሉት ደብዳቤ "በአንድነት ራስን በማጥፋት ተቃውሟችንን እናሰማ" የሚል መልዕክት ያለው ደብዳቤ እየተቀባበሉ ይገኛሉ።

"በሀገራችን ኢትዮጵያ ከኑሮ ውድነት ጋር ተያይዞ በመጣው ጭንቀት ምክንያት ብዙዎች 'ብንሄድ ይሻለናል' በማለት በግለሰብ ደረጃ ራሳቸውን ሲያጠፉ ማየት የተለመደ ሆኗል" የሚለው ደብዳቤው እነዚህ ሰዎች ድርጊቱን የሚፈፅሙት በግለሰብ ደረጃ በመሆኑብ ምክንያቱ ሳይጣራ እና ሳይፈታ እስካሁን ቆይቷል ይላል።

በመቀጠልም "በሀገሪቱ ለረጅም አመታት ከባዱን ስልጠና ወስደን የህክምና ሙያ ላይ የተሰማራን ሀኪሞች ግን ከመሄድ ይልቅ እናክማቸው በማለት ስናገለግል ቆይተናል። አሁን ግን ይበቃልናል፣ መኖር አልቻልንም። ኩላሊታችንን እንኳን እንሽጥ ብለን ብንሞክር በሀገራችን ያለው የንቅለ ተከላ ልምድ ከዘመድ በመሆኑ ለብዙዎቻችን አልተመቸንም" የሚለው የጤና ባለሙያዎቹ ደብዳቤ ያለባቸው ችግር ቀን ከቀን እየተባባሰ እንደመጣ ይጠቅሳሉ።

ደብዳቤው በመቀጠልም "በሀኪሞች ላይ የሚደረገው ስም የማጥፋት ሴራ ተጠናክሮ ቀጥሏል። ስለዚህ ቀን ከለሊት የምንሰራው ኑሯችንን ሊደጉም ካልቻለ ለሰጠነው አገልግሎት አገልግሎት ደግሞ ከምስጋና ይልቅ ስድብ ከወረደብን እንዲሁም መንግስት ባላቀረበው መድሀኒት እና ቁሳቁስ እኛ ከተደበደብን፣ የመልካም አስተዳደር እጦቱ እየባሰ ከሄደ፣ በሰላም መኖር ህልም ሆኖ ከቀረ ከመንግስትም ተሰሚነት ካጣን እስከ መቼ ነው የምንቆየው?" በማለት ጥያቄያቸውን አቅርበው ሀኪሞች ቀጠሮ ይዘን እና በአንድነት ተነጋግረን ተቃውሟችንን ገልፀን ራሳችንን ማጥፋት የሚለው ከብዙዎች ዘንድ ተነስቷል ይላል።

በዚህ መልኩ "እኛ ባንኖር ለሚኖሩት መፍትሄ እንሁን" በማለት ደብዳቤው ይጠቅሳል።

ይህን መረጃ ወደ መሠረት ሚድያ ያመጡት አንድ የጤና ባለሙያ ሲሆኑ ድርጊቱ ከተፈፀመ እጅግ አስደንጋጭ መሆኑ ስለማይቀር መፍትሄ እንዲፈለግ ወደ ሚድያ ማምጣት እንደፈለጉ ተናግረዋል።

ይህን ደብዳቤ ከሚቀባበሉ ሪዝደንቶች በአዲስ አበባ፣ ወላይታ፣ ሀዋሳ፣ አዳማ እና ሌሎች ቦታዎች የሚሰሩ የጤና ባለሙያዎች እንደሚገኙበት ታውቋል።

አደጋ ከደረሰ በኃላ ከንፈር ከመምጠጥ ምናልባት መፍትሄ ከተገኘለት በማለት መሠረት ሚድያ ወደ ህዝብ ሊያቀርበው ችሏል።



@MeseretMedia

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

28 Nov, 10:34


ፒኮክ መናፈሻ ምን ተፈጠረ‼️
በትላንትናው እለት በአዲስአበባ ፒኮክ አካባቢ ፖሊስ እና ወጣቶች እንደተጋጩ ተሰማ‼️
👉አንድ ሰው ከቀናት በፊት እራሱን ማጥፋቱ ተሰምቷል።
በአዲስአበባ ጭርቆስ ክ/ከተማ የሚገኘዉ ፒኮክ መናፈሻ አካባቢ የሚገኙ በከተማ ግብርና የሚተዳደሩ ዜጎች እና የመንግስት የፀጥታ አካላት የተጋጩት ነዋሪዎቹ ለበርካታ አመታት ከኖሩበት ቦታ በአስቸኮይ እንዲነሱ ና ቤት እንዲያፈርሱ በመደረጉ ነዉ ተብሎል።
በግጭቱ በርካታ ወጣቶች መጎዳታቸው የተሰማ ሲሆን ሁለት ፖሊሶችም መጠነኛ ጉዳት እንደደረሰባቸዉ ተሰምቷል።
#አዩዘሀበሻ
⬇️⬇️⬇️👇👇👇👇⬇️⬇️
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

27 Nov, 18:28


https://www.youtube.com/live/C76jBSxNC5w?si=o88mVRP4jTeg_6jc

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

26 Nov, 17:16


በሐይማኖት ሽፋን የተፈጸም ፖለቲካዊ ነውር!

በደራ ወረዳ የተፈፀመውን አሰቃቂ ግድያ አስመልክቶን ግድያው በማንም ይፈፀም በማንም አጥብቆ ሊወገዝ የሚገባው ነው። "የኢትዮጵያ ሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ"የግፍ ግድያውን ድርጊት ማወገዛችሁ ጥሩ ነው! በትክክል መወገዝ ያለበት ሰይጣናዊ ድርጊት ነው!

ሆኖም ግን እነዚህ የሐይማኖት ተቋማት ተብየዎች ከቀናት በፊት በዛው በደራ ወረዳ የተፈፀመውን የታላቁን የመስጅድ ኢማም እና 12 የሚሆኑ ቤተሰቦቻቸው አንድ ላይ የግፍ ግድያ ሳያወግዙ አለፉት?ይህን የመሰለ ጉዙፍ የግፍ ጭፍጨፋ እንዲሁ በዋዛ የሚታለፍ አልነበረም ፤ያ'ው ጉዳዩ በሐይማኖት ሽፋን የተፈጸም ፖለቲካዊ ነውር ስለ መሆኑ አንዱ ማሳያ ይህ ነው!

ይህን "የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ" ፖለቲካዊ ነውር ሌላው ማሳያ ባለፉት 7ዓመታት ፣በሃገራችን ኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች በተለይ በኦሮሚያ ለቁጥር የሚታክት ዘግናኝ የግፍ ጭፍጨፋ ድርጊቶች ተፈጽሟል! የኢትዮጵያ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እንደ ጧፍ በየቦታው እንድትነድ ተደርጓል። ምዕመናን በጭካኔ አንዴ አይደለም ለቁጥር በሚታክት በግፍ ተገድለዋል።እነኚህ የሐይማኖት ተቋማት ነን የሚሉ አንድም ቀን ድምጻቸው አልተሰማም። ለምን ይሆን?

በደራ ወረዳ የተፈፀመውን አሰቃቂ የግድያ አስመልክቶ ከመንግሥት እስከ ሐይማኖቶች ኅብረት የውግዘት መግለጫ አውጥተዋል።ይሁን ተገቢ ነው።ነገር ግን በኢትዮጵያ በተደጋጋሚ ለተፈጸሙ ዘግናኝ ጭፍጨፋዎች
መንግስትም ሆነ የሐይማኖት ተቋማት ዝምታን የመረጡት ለምንድነው?

"የኢትዮጵያ ሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ"ከፖለቲካ አሻጥር ነጻ ነን ካሉ፤በመንግስት የሚፈፅመውን  ዘር ተኮር ጭፍጨፋ ለምን አያወግዙም? እስካሁንም አውግዘው አያውቅም ፣ይህ ለምን ሆነ? (ይድነቃቸው)

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

26 Nov, 15:36


https://youtube.com/shorts/MPKV3YK9y7w?feature=share

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

26 Nov, 15:09


የተመለከትነው ዘግናኝ ቪዲዮ የሽብር ጥግ ማሳያ ነው። በአንጻሩ መንግሥታዊ መዋቅሩ ድርጊቱን ለፖለቲካ ትርፍ ያዋለበት መንገድ የሚወገዝ ተግባር ነው።
(በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ከእናት ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ)

ከሰሞኑ በማኅበራዊ ሚዲያ ሲዘዋወር የተመለከትነውና ከየት መጣውን ለማጣራት ጥረት እያደረግን ያለውን ምስል ወድምጽ(video) እጅግ ዘግናኝና በጽኑ ቃል የሚወገዝ ተግባር ሆኖ አግኝተነዋል። ፓርቲያችን ድርጊቱ በማን፣ የትና መቸ እንደተፈጸመ ለማጣራት ጥረቶችን እያደረገ ሲሆን በዚሁ አጋጣሚ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና ሰብዓዊ መብቶች ጉባኤ በተለመደው መልኩ በገለልተኝነት ጥረታቸውን አድርገው ለሕዝብ ይፋ እንደሚያደርጉ ጽኑ እምነታችን ነው።

ከዚኹ ጋር ተያይዞ እጅግ ጥርጣሬ ውስጥ የሚያስገቡና ከዚኽ ዘግናኝ ድርጊት ጀርባ ምን የተደገሰ ነገር አለ? ብለን እንድንጠይቅ የሚያደርጉ አንዳንድ ኹነቶችን ታዝበናል። ወለጋ የደም ምድር፣ የእልቂት ሜዳ ሲሆንና በመቶዎች የሚቆጠሩ ዜጎች በዘግናኝ ኹኔታ በአንድ ጀምበር ሲያልቁ፤ መላው የኦሮሚያ ሕዝብ የቀን ገዥና የጨለማ ገዥ እየተፈራረቀበት ቁምስቅሉን ሲያይ፣ ልጆቹን ሲነጠቅ፤ አፋርና ሶማሌ ሥርዓቱ በፈጠረው ግጭት ወገኖቻችን በመቶዎች ሲሞቱ፤ እዚኹ አፍንጫችን ሥር ምሥራቅ ሸዋ በአንድ ሌሊት 43 ሰው ቤት ተዘግቶ ሲቃጠል፤ ሞጆ ወረዳ ላይ አረጋዊ ካህን ከነቤተሰባቸው ለዘር እንዳይተርፉ ወንዝ ዳር እንደበግ ሲታረዱ፤ የዝቋላ አቦ ገዳማውያን አባቶች ተቆራርጠው ጭምር ሲገደሉ፤ ደራ ላይ የመስጅድ ኢማም ከነቤተሰባቸው ለዘር እንዳይተርፉ በዘግናኝ ኹኔታ ሲገደሉ፤ በመላው አማራ ሰው በተገኘበት ይገደል ተብሎ የታወጀ እስኪመስል ድረስ ነብሰ ጡሮችና ሕጻናት ሲያልቁ፤ ትግራይ የሞት ጥላ አንዣቦ በረሃብና በሰው ሠራሽ መንገድ ሕጻናት ጭምር ሲያልቁ፤ በአጠቃላይ በኢትዮጵያ በአራቱም ማዕዘናት በየቀኑ ሊባል በሚችል መልኩ ለመስማትም ለማየትም በሚዘገንን መልኩ እልቂት ሲፈጸም ምንም እንዳልተፈጠረ አሸሸ ገዳሜ ሲደልቁ የኖሩ የመንግሥት ሚዲያዎች በዚህ ጉዳይ ብቻ እንዴት ከደስታ እንቅልፋቸውና ፈንጠዝያቸው ነቅተው ሙሾ አውራጅ ሆኑ? "ለሞቱት ዛፍ እንተክላለን" እያለ በሞት ላይ ሲዘብት የነበረው መንግሥት እንዴት ተሰምቶት ሀዘን ተቀመጠ? ኦሮሚያ የደም መሬት ሲሆን የሕዝቡን ብሶት ተጋርቶ የማያውቀው፣ አትግደሉን እያለ ልጆቹን ቀንበር ጠምዶ ለወጣው ሕዝብ ጠብ የሚል መፍትሔ ያልሰጠውና ሲጠየቅም ጆሮ ዳባ ልበስ የሚለው የክልሉ መንግሥት እንዴት አኹን ነቅቶ ሕዝብን በሕዝብ ላይ የሚያነሳሳ መግለጫ አወጣ? የሚሉት በውል መታየት ያለባቸው  ሰበዞች ሆነው አግኝተናቸዋል። ከዚህ አስነዋሪ ድርጊት ጀርባ ማን ነው ያለው የሚለውንም ፍንጭ ይሰጡ ይሆን ወይ? ብለን እንድንጠይቅ አስገድዶናል።

ዘግናኝ ድርጊቱን አውግዞ፣ ተገቢው ማጣራት ተደርጎበት አጥፊዎችን ለፍርድ አደባባይ ማቅረብ፣ ድርጊቱም በምድራችን ዳግም እንዳይከሰት ተባብሮ መሥራት ሲገባ ሀኪም አጥቶ በጽኑ ደዌ ተይዞ የሚሰቃየውን ፖለቲካችንን መንግሥታዊ መዋቅሩና መንግሥት የሚዘውራቸው ሚዲያዎቹ ጊዜያዊ የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ሲባል ያደረጉት እሳት ላይ ቤንዚን ማርከፍከፍና እልቂት ጠመቃ ውሎ አድሮ  ከተጠያቂነት እንደማያድን በእርግጥ መናገር ይቻላል።

በአንጻሩ ከዚህ በፊት ጽንፍ በወጣ የፖለቲካ አቋማቸው የምናውቃቸው ግለሰቦች ተው ባይ ሆነው መታየታቸው እጅጉን የሚደነቅ ተግባር ሆኖ አግኝተነዋል። ኢትዮጵያ የሚያስፈልጋት ይሄው ስክነትና ፖለቲካዊ መቀራረብ መሆኑን በተግባር ለማስተማር ጅምር ሙከራዎች ታይተዋል። በመሆኑም

፩. እናት ፓርቲ ድርጊቱንና የድርጊቱን ፈጻሚዎች በጽኑ ያወግዛል፤ በገለልተኛ አካል ተጣርቶም ፍትሕ እንዲሰፍን አጥብቆ ይጠይቃል።

፪. መንግሥትና የመንግሥት ሚዲያዎች ለጊዜያዊ የፖለቲካ ትርፍ ሲባል ሕዝብን በሕዝብ ላይ ማነሳሳት እንዲያቆሙ እናሳስባለን።

፫. መንግሥትን ጨምሮ ኹሉም ታጣቂ ኃይሎች ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ እንደገለጽነው ንጹሓን ዜጎችን ዒላማ ማድረግ የጦር ወንጀል መሆኑንና ይዋል ይደር እንጂ ተጠያቂነትን እንደሚያስከትል በመረዳት ከዚህ መሰል ጥፋት እንዲታቀቡ አጽንዖት ሰጥተን እናሳስባለን።

እግዚአብሔር አገራችን ኢትዮጵያንና ሕዝቧን ይጠብቅ!

እናት ፓርቲ
ኅዳር ፲፭ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

26 Nov, 15:08


አራት የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅት መሪዎች በመንግሥት የፀጥታ አካላት በደረሰባቸው ዛቻ እና ወከባ ምክንያት ከአገር መሰደዳቸውን ተነገረ።


የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ተሟጋቾች ማዕከል ባወጣው መግለቻ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅት መሪዎች በፀጥታ ኃይሎች “ተደጋጋሚ ማስፈራሪያ እና ወከባ” እየደደረሰባቸው እንደሆነ አስታውቋል።
በዚህም ሳቢያ በአገሪቱ ያለው የሲቪል ምኅዳር ሊጠብ እና አደጋ ላይ ሊወድቅ እንሚችል ምክልቶች እየተስተዋሉ ነው አለ።
በአካል እና በስልክ ይደርሳል የተባለውን ማስፈራሪያ እና ወከባ በመስጋት አራት የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅት መሪዎች አገር ጥለው መሰደዳቸውን ማዕከሉ በመግለጫ ላይ አመልክቷል።
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ተሟጋቾች ማዕከል ደረሱኝ ባላቸው አቤቱታዎች እና ጥቆማዎች ተሰደዱ የተባሉትን መሪዎች ስም ዝርዝር አውጥቷል።
የመብቶች እና የዲሞክራሲ እድገት ማዕከል (ካርድ) መሥራች እና የፕሮግራም ዳይሬክተር አቶ አጥናፍ ብርሃኔ፣ ስብስብ ለሰብዓዊ መብቶች በኢትዮጵያ ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ኤደን ፍስሐ እና እሳቸውን የተኩት ወ/ት መሠረት አሊ እንዲሁም ከ30 ዓመት በላይ ያስቆጠረው የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባኤ (ኢሰመጉ) ዳይሬክተር አቶ ዳን ይርጋ በደረሰባቸው “ከፍተኛ ጫና፣ ወከባ እና ማስፈራሪያ” እንደተሰደዱ ገልጿል።
ከስድስት ዓመታት በፊት የተመሠረተው ማዕከሉ ከዚህም በተጨማሪ የኢሰመጉ ሠራተኞች በሚደርስባቸው ተመሳሳይ ዛቻ እና መስፈራሪያ ሥራቸውን ተረጋግተው ለመሥራት መቸገራቸውን ጠቁሞ፤ ሠራተኞቹ ሥራቸውን ለመልቀቅም እየተገደዱ ነው ብሏል።
ኢሰመጉ ከዚህ ቀደም ባወጣቸው ተደጋጋሚ መግለጫዎች ጫና፣ ድብደባ፣ ዝርፊያ እና ወከባ ሥራውን ለመሥራት እንቅፋት እየሆኑበት እንደሆነ አስታውቋል።

የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋቾች ማዕከል መሻሻሎችን ሲጠብቅ እንደነበር ጠቁሞ ባለፈው ሳምንት በተቆጣጣሪው የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ባለሥልጣን የታገዱ ሦስት የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶችን ጉዳይም አንስቷል።
የመብቶች እና የዲሞክራሲ እድገት ማዕከል (ካርድ)፣ ስብስብ ለሰብዓዊ መብቶች በኢትዮጵያ እና የሕግ ባለሙያዎች ለሰብዓዊ መብቶች ከፖለቲካ ገለልተኛ አልሆኑም በሚል ታግደዋል።
ድርጅቶቹ “ከፖለቲካ ገለልተኛ መሆን ሲገባቸው፣ ከዓላማቸው ውጪ በመንቀሳቀስ የአገርን ጥቅም የሚጎዱ ተግባራት ላይ ተሰማርተዋል” የሚል የእግድ ደብዳቤ እንደደረሳቸው ታውቋል።
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ተሟጋቾች ማዕከል በሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች እና መሪዎች ላይ የሚደርሱ ጫናዎች እና እገዳዎች “ምኅዳሩን የሚያጠብ፣ ፍራቻ የሚፈጥር እና ተሳትፎን የሚያኮስስ ነው” ሲል ኮንኗል።
እገዳው ሕገ መንግሥቱ የሰጣቸውን የመደራጀት፣ የመሰብሰብ እና ሀሳብን በነጻነት የመግለጽ መብቶችንም የሚጎዳ እንደሆነ ጠቁሟል።
የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች አዋጅ ከእገዳ በፊት ማስጠንቀቂያ መሰጠት እንዳለበት የሚደነግግ መሆኑንም ያነሳ ሲሆን፤ እርምጃው “ሕግን ያልተከተለ እና ግልጽነት የጎደለው” እንደሆነ አመልክቷል።
እግድ የተጣለባቸው ሦስቱም ድርጅቶች ባወጧቸው መግለጫዎች ምርመራ እንደተደረገባቸው የሚያውቁት ነገር እንዳልነበረ ጠቁመው እግዱ ሕግ እና ሥርዓትን ያልተከተለ መሆኑንም አስታውቀዋል።
መንግሥት የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ላይ እየደረሰ ያለውን ጫና በአፋጣኝ እልባት እንዲሰጠውም ማዕከሉ አሳስቧል።
ከዚህ በተጫማሪም ማዕከሉ ኃላፊነት የተጣለባቸው አካላት ለሲቪል ማኅበረሰብ አባላት ጥበቃ እንዲያደርጉ እና ለምኅዳሩ መስፋት አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ጠይቋል።

@BBC

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

25 Nov, 19:54


https://www.youtube.com/live/2YEbNH3cAaM?si=pyvbeHQOH85lPcxm

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

25 Nov, 17:42


በአንድ ወቅት የሪቻርድ ፓንክረስት ወዳጅ የሆነው ኤድዋርድ ኡሉንዶርፍ ወደ አንዱ የኢትዮጵያ ገጠራማ ክፍል ለጥናት ሄደ፡፡ አንድ ገበሬ ቤት ገባ፡፡ እግሩን ሊያጥቡት ሲሉ አንገራገረ፡፡  አስተርጓሚው ባህል እንደሆነ ነገረው፡፡ በደንብ ታጠበ፡፡ እግሩን ተሳመ። እንግዳ ክቡር ነው። ያ እንግዳ በረከት ነው ብለው ያምናሉ። ቤቱም የእግዜር ነው።

ምሳ አበሉት፡፡
"ስንት እንከፈላቸው" ብሎ ጠየቀ
"ነፃ ነው" ብሎ ነገረው አስተርጓሚው።
መሸ፡፡ መጠጥ ይዘው አምሽተው እንደገና እራት በሉ።

ማታ ባልና ሚስት አልጋቸውን ለእንግዶች ለቀው መሬት ላይ ተኙ፡፡
ጥዋት ቁርስ በሉ፡፡
"የአልጋ እና የቁርስ እንከፈል" አለ ኡሉንዶርፍ
"ነውር ነው" አለው አስተርጓሚው፡፡

ከዚያ ስመው ተሰናብተው ወደሚሄዱበት ሀገር በራሳቸው በቅሎ ሸኟቸው፡፡

በመጨረሻ ኡሉንዶርፍ አንድ ታላቅ ነገር ተናገረ-እንዲህ ሲል  <<ዓለም መፅሐፍ ቅዱስን ያነበዋል፥ ኢትዮጵያውያን ግን ይኖሩታል>>

መንፈሳዊ ስልጣኔ፣ ሰብአዊነት፣ ሰውነት!

የላይኛው ያስባችሁ!

ዛሬ ግን ያደግ ህዝብ የእሳት ዝናብ እየወረደበት ነው እግዚአብሔር ሆይ በቃ በለን።

ሰላም አደራችሁ ውድ ኦርቶዶክሳዊያን

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

25 Nov, 17:19


መረጃ ‼️


የግብፅ ከፍተኛ የጦር ጀነራሎችና ባለስልጣናት ላለፉት ቀናት በአሰብ ይፋዊ  ያልሆነ ጉብኝት ማድረጋቸው ተሰማ

የኤርትራ መንግስት ለግብፅ በአሰብ የጦር ቤዝ እንድትገነባ ፍቃድ መስጠቱ የሚታወስ ነዉ ፡፡

ይህ ሁኔታ ከኤርትራ መንግስት ጋር የሻከረ ግንኙነት ያለዉ የፌደራሉ መንግስት የአባይን ግድብ በአንክሮ ከምትመለከተዉ ግብፅ ጋር ያፋጠጠ  ሆኖል ፡፡

በዲፕሎማሲዉ ሜዳ የተዋጣለት አይደለም የሚባለዉ የፌደራሉ መንግስት ከጎረቤት ሀገራት ጋር የገባበት እሰጣ ገባ የኢትዬጲያ ታሪካዊ ጠላቶች የሚባሉት ሀገራት መጠቀሚያ እንዳያደርጉት ስጋት አለ ሲሉ ዲፕሎማቶች ይናገራሉ ፡፡

#አንኳር_መረጃ  

@Ankuar_mereja
@Ankuar_mereja

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

25 Nov, 17:17


ፒያሳ የእሳት አደጋ ተከሰተ❗️

በተለምዶ ፒያሳ ደጃች ውቤ ተብሎ በሚጠራው ሰፈር ነው የእሳት አደጋው የተከሰተው።

የእሳት አደጋው የተከሰተበት ስፍራ ላይ ቻይኖች ሲሚንቶ እና ኮንክሪት የሚያዘጋጁበት ስፍራ ነው። በስፍራው ሲሚንቶና ኮንክሪት ለማዘጋጀት የሚጠቅሙ ኬሜካሎች እንዳሉ ነው የተነገረው።

እንደዚሁም ከፍተኛ መጠን ያለው ነዳጅም በዚሁ ስፍራ እንዳለ ነው የተነገረው።

ለተለያዩ አገልግሎት የሚያገለግሉ ተሽከርካሪዎችም አደጋው በደረሰበት ቦታ መኖሩን ተመልክተናል።

እሳቱን ለማጥፋት የእሳት አደጋ ሰራተኞች በቦታው ደርሰው እርብርብ እያደረጉ ይገኛል።

የአዲስ አበባ ፖሊስም ባካባቢው ደርሶ ጥበቃ እያደረገ ነው የሚገኘው።

#አንኳር_መረጃ  

@Ankuar_mereja
@Ankuar_mereja

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

20 Nov, 17:49


ተው ተናበቡ እንጂ  ኢጆሌ ኦነጎታ! 
ሚኖ  ኢርሳበሲ ታጋጫ😀 ባቢሎን

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

20 Nov, 14:00


በህግ አምላክ ክፍል 2፤  ኦርቶዶክስና እስልምና ምን አደረጉልን?
https://shorturl.at/WIDKT @zborkena #Ethiopia #News 

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

20 Nov, 13:51


ዛሬ ጎሮ አንደኛ ትምህርት ቤት ምን ተፈጠረ
ከደቂቃዎች በፊት ጎሮ አንደኛ ትምህርት ቤት የተወሰኑ ተማሪዎች ድንገተኛ ህመም አጋጥሟቸው በአንቡላንስ ወደ ጤና ጣቢያ መወሰዳቸውን የደረሰኝ መረጃ ያመላክታል፣ጤነኛ የሆኑት ደግሞ ወደ ቤታቸው እየተመለሱ ነው። የህመሙ መነሻ የምግብ መመረዝ ሳይሆን እንዳልቀረ የጠቆሙት የመረጃ ምንጮቼ አሁን የፌዴራል ፖሊስ ደርሷል፣ ወላጆች እነዲይገቡ ተከልክለዋል ብለዋል። ጎሮ አንደኛ ደረጃ ትምህርት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የምገባ ፕሮግራም ተጠቃሚ መሆኑ ይታወቃል። የእሳት አደጋ ደርሷል የሚባለው ውሸት ነው።
አዩዘሀበሻ
⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️👇👇👇👇⬇️⬇️
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

17 Nov, 19:45


#Urgent🚨

እየደበደቡት ጥርሱን አውልቀውታል። ሙሉውን ቪዲዮ ለመመልከ ሰቀጠጠኝ። አጋቾቹ 800 ሺሕ ብር ጠይቀዋል” - እርዱኝ ያሉ የታጋች ወንድም

በባህር ዳር ዩቨርቨሲቲ የ4 ዓመት የመካኒካል ኢንጅነሪንግ ተማሪ የነበረው ወጣት ሙላት ተቀባ አስረሴ በሊቢያ በአጋቾች ተይዞ በድብደባ አካላዊ ጉዳት እየደረሰበት መሆኑን ቤተሰቦቹና የቅርብ ሰዎቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጹ።

የታጋች ወንድም አቶ ደጉ ተቀባ አስረሴ፣ “ ጎንደር ጦርነት ስላለ ገንዘቡን ለመላክ ተንቀሳቅሶ መስራት አልተቻለም። ቦታ ነበረችኝ ለመሸጥ እንኳ በዚሁ በጸጥታው ችግር ገዢ የለም። እባካችሁ ወንድሜን አድኑልኝ ” ሲሉ ተማጽዋል።

ታጋቹ ያለበትን ሁኔታ ሲገልጹም፣ “ እየደበደቡት ጥርሱን አውልቀውታል። ሙሉውን ቪዲዮ ለመመልከት ሰቀጠጠኝ። አጋቾቹ 800 ሺሕ ብር ጠይቀዋል። ገንዘቡን መላክ አልቻልኩም። ወላጆቻችን አዛውንቶች ናቸው ” ነው ያሉት።

በሰሜን ጎንደር ዞን ጠለምት ወረዳ አቃቢ ሕግ በመሆን ተቀጥረው እንደሚሰሩ ገልጸው፣ አሁን ባላቸው አነስተኛ ደመወዝ የተጠየቀውን ገንዘብ ማሟላት እንደማይችሉ አስረድተዋል።

“ አጋቾቹ ‘ቶሎ ካላክ እንገለዋለን እያሉኝ’ ነው ” ያሉቴ አቶ ደጉ፣ ወጣቱ ዘንድሮ ተመራቂ እንደነበር፣ ወደ አውሮፓ ድንበር ሊያቋርጥ ሲል ከታገተ ወራቶች እንዳስቆጠረ ገልጸዋል።

በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ የሚገኙ ሁለት የታጋቹ የቅርብ ጓደኞች በበኩላቸው፣ ተማሪ ሙላት ታግቶ እየተደበደበ እንደሆነ፣ ከዩኒቨርሲቲው ደብዳቤ አጽፈው ገንዘብ እያሰባሰቡ መሆኑን ነግረውናል።

ከጓደኞቹ አንዱ በሰጠው ቃል፣ “ ተማሪ ሙላት ወደ አውሮፓ ሊወጣ ሲል ታግቶ ይገኛል። እንደኛ ተመራቂ ነው የነበረው በዚህ ዓመት። የሰሜን ጎንደር ዞን ጠለምት ወረዳ ነዋሪ ነው ” ብሏል።

የታጋቹ ወንድምና ጓደኞቹ፣ ታጋቹ በአጋቾች እየደረሰበት ያለውን ስቃይ የሚያሳይ ቪዲዮ የላኩ ሲሆን፣ ከላይ ተያይዟል።

መርዳት ለምትሹ 1000281326795 የአቶ ደጉ ተቀባ አስረሴ የንግድ ባንክ ሒሳብ ቁጥር ነው። አቶ ደጉን በዚህ ስልክ 0931494332 ማግኘት ይቻላል።

የፖሊ ግቢ ጉባኤም በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000660181036 እና በአቢሲንያ ባንክ 209476797 አካውንት በመክፈት ድጋፍ እያሰባሰበ ነው።

#TikvahErhiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

17 Nov, 18:24


https://www.youtube.com/live/5A0H16CMAdU?si=AIDk2RJzyEIhw7oh

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

16 Nov, 19:56


ምን እንሥራ???[የኔታ ገብረ መድኅን እንደ ጻፉት]
"የሚሠራ ሰው ከአንድ ሰይጣን ጋር ይዋጋል።
የማይሠራ ሰው ግን ከሺህ ሰይጣናት ጋራ ይዋጋል።
መከራችን የሚቀንሰውም ሆነ የሚጨምረው  በተግባራችን ነው።"መፍትሄው?
#1ኛ. መማር ፦አለማወቅን ያህል አስቸጋሪነት የለም  የተማረ ሰው ቢያንስ ለመካሪ አያስቸግርም።የኔታ ደጉ ዓለም ካሣ እንዲህ ይሉ ነበር፦"የተማረ ሰው እና የተገጠበ አህያ አንድ ነውደ የተገጠበ አህያ የሚጫነው እየተቁነጠነጠ ነው ።የተማረ ሰውም ቢያጠፋ እንኳን እየተጨነቀ እየተቁነጠነጠ ነው።"ብለዋል።ዕውቀት ከብዙ ችግር አርነት ታወጣለች። ሲያጠፉ እንኳን በህሊና ትገስጻለች።እውነተኛ ጥርት ያለ ኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮን መማር ዐይነ ብዙ ያደርጋል።በቀዳማውያን አበው ዐይን ያያል፣በአበው ልብ ያስባል፣በክርስትና አስተምህሮ የግል ዕውቀት የለምና። ከጥንት በቅብብሎሽ የወረደውን በመቀበል የምናውቀው  እና የምንኖረው ነው እንጂ።
#2ኛ.መረዳት፦ዕውቀት ብቻ መረዳት ከሌለው እንደ ሚሞሪ ካርድ መሆን ነው።ሚሞሪያችን ብዙ ቃላት ቢሸከምም ካልከፈቱት አይጮህም።ባልተረዳ ልብ ዕውቀት ብቻ  ካልከፈቱት የማይናገር ይሆናል ።ይህ ያልሰላ ሕይወት፦ የማይበላ ሀሳብ ነው።ያልተረዳ ልብ በድንቁርና ያዳቃል።የእህል ጣዕም በጉረሮ፣ የሀሳብ ጣዕም በአእምሮ ይታወቃልና።በደንብ መረዳት ጣዕመ አእምሮ ነው።
#3ኛ.ቅድሚያ ለሃይማኖት መስጠት፦ከማንም በፊት ከማንም በላይ ለክርስትናው ቅድሚያ መስጠት ። መቅደም የማይገባቸው ሲቀድሙብን ደጋፊ እና ከዳሚ ያደርጉናል።በዐይን ሌላውን ያዩበታል እንጂ እርሱን ዐያዩትም በሃይማኖትም ሌላውን ያዩበታል ሌላውን ያውቁበታል እንጂ እርሱን አያውቁትም።ልዑል ውእቱ ዘኢይትረከብ.. እንዲል።ዐይን ጤነኛ ከሆነ የምናየው ትክክል ነው።በሃይማኖችን ማያነት ካየንበት ምሥል ሳይሆን አካል እናያለን።
#4ኛ መለኪያ ማበጀት፦መለኪያ የሌለው ሰው የውኀ ስፍር ነው። ውኀ በጠርሙስ ቢቀዱት የጠርሙስ ቅርጽ ይይዛል።በሳፋ ቢያደርጉት የሳፋ ቅርጽ ይይዛል።እንዳደረጉት ከመሆን ውጪ የራሱ ቅርጽ የለውም።ቅርጽ የለሽ እንዳደረጉት የሚፈስ ልበ ቢስ ከመሆን በላይ ምን ችግር አለ! ? ሲያሞቁን የምንግል ሲያበርዱን የምንቀዘቅ መሆን የለብንም የሚያኖረን ዓላማችን ብቻ ነው።
#5ኛ  እየሆነብን ያለውን በትክክል ማወቅ፦ ትናንት  የሆነብንን። ዛሬ እየተደረገብን ያለውን። ነገ ሊያደርጉብን ያቀዱትን በፈጣን አእምሮ መገንዘብ ከማን?ለምን?የት?እንዴት?መቸ?ወዘተ በሚሉ መጠይቆች ማብሰል።
#6ኛ ከእኛ እና ከእግዚአብሔር ውጪ ምንም አዳኝ ረዳት እንደሌለን መገንዘብ ፦ እየጸለይን እንሠራለን እየሠራን እንጸልያለን እንደተባለ በእግዚአብሔር ረድኤት  መሥራት የምንፈልገውን ሁሉ ማድረግ።
#7ኛ ለችግራችን መፍትሄ እኛው መሆናችንን ማመን እና መተግበር፦በቁስላችን ላይ ጨው እየጨሠሩ አይዞህ እናድንኃለን  የሚሉን አዳኞች አይደሉም አፋዛዦች ናቸው እንጂ።
#8ኛ ስልብ ሀሳቦችን ማስወገድ ፦ ስንሞት እንበዛለን፣እርሱ ይሁነን።ወዘተ የመሳሰሉትን።
#9ኛ ከአንድ ሰው መጀመር ፦አንድ ሰው ከተነካ የሁላችን እንደሆነ እንዳለ መውሰድ። የክፉዎቹ ተግባር በተናጠል እያደከሙ ኅብረተ ክርስትናችንን ማማሰን ስለሆነ።
#10ኛ ሊለካ ሊጨበጥ የሚችል የመፍትሄ መተግበሪያ ማስቀመጥ እና ያስቀመጥነውን መሆን።
ነገ እንዲህ ለመወያየትም ሆነ አቅጣጫ ማስቀመጥ  ጊዜው ሊያልፍ ይችላል።
#11ኛ በሰው አጀንዳ ለማስታገስ እንጂ አቅምን አለማጥፋት ፦ መሆን የምንፈልገውን ለመሆን ብቻ ተግቶ መሥራት። የሚፈልጉት  ብኩን ሰው  እንድንሆን ስለሆነ።....
      ምን እንሥራ????????????ጨምሩበት
    ዛሬስ እንዲህ እያለፈ ነው ነገስ???

በድጋሚ የተለጠፈ
  https://t.me/+WhHGbVtEhipmYjA0

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

15 Nov, 15:44


https://youtu.be/RmrPNQZGGA8?si=kDzpwdaz5C3zMNBP

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

14 Nov, 21:50


በዚህ አይነት ደንቆሮ ለመመራት መፍቅድልችን የውድቀታችንን ደረጃ ጥልቀት ያሳያል:: ከሁሉም በላይ ክርስቶስን የዘነጉ ድንዙዛን ጳጳሳት ቤታችንን መሙላታቸውን በደማቁ ይምሰክራል:: እነ "አንገቴን ሰጣለሁ" እና "ችግር የለም እንጂ አትገዙ ማለት እንችላለን" በዚህ ንግግር አለመቆጣታቸው ምን ያህል የሐሰት እረኞች እንደሆኑ ያሳያል

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

14 Nov, 15:53


ዶ/ር ወንዶሰን አሰፋ


ዛሬ በፍርድ ቤት ያደረገው ታሪካዊ ንግግር

ከዚህ በመቀጠል በተከሰስኩበት ክስ የእምነት ክህደት ቃሌን እሰጣለሁ።
በቀዳሚነት የተከሰስኩት ጉዳይ የአማራ ህዝብ እኩል ከሌሎች ብሄሮችና ህዝቦች ጋር የአገር ባለቤት ሆኖ እያለ አገር ተወስዶበታል ብሎ ተናግሯል የሚል ነዉ።ክሴ ይሄን የሚል በመሆኑ አሁን ለፍርድ የቀረበዉ የአማራ ህዝብ የህልዉና ትግል ነዉ ማለት ነዉ።

የአማራ ህዝብ ላለፉት ሰላሳ አራት አመታት ፀረ አማራ ሀይሎች ተደራጅተው እና ተቀናጅተው ስልታዊ እና መንግስታዊ ጥቃት እያደረሱበት ያሉ ህዝብ ነዉ።
የአማራ ህዝብ የአገር ባለቤትነቱንበግልፅ በአደባባይ የተነጠቀዉ በ1983 ዓ.ም አማራ ጠል ሀይሎች የመንግስት ስልጣንን ተቆጣጥረዉ ባደረጉት የ ሰኔ 1983ቱ የቻርተሩ ጉባኤ ነበር።
ጉባኤው ያለምንም የአማራ ህዝብ ዉክልና የተካሄደ መሆኑን የስርአቱ ቁንጮ መለስ ዜናዊ በአደባባይ የመሰከረው ሀቅ ነዉ።በዚህ የቻርተር ጉባኤ የተመሰረተው የሽግግር መንግስት  ባደረገው የክልል አከላለል ዉስጥ ምንም አይነት የአማራ ህዝብ ዉክልና  ያልነበረው ሲሆን በዚህ የሽግግር መንግስት ዘመን የተዘጋጀው ህገመንግስትም የአማራን ህዝብ በማዉገዝ ተጀምሮ በማዉገዝ ያለቀ መሆኑን የቻርተሩ ጉባኤ ቃለጉባኤዎች ,የሽግግር ም/ቤቱ ቃለጉባኤዎች,የህገመንግስት ጉባኤ ቃለጉባኤዎች ዘላለማዊ ምስክር በመሆኑ ያስረዳሉ ።
በዘመኑ ትህነግ/ኢህአዴግ በአማራ ህዝብ ላይ የፈፀሙት አድሏዊ ድርጊቶች ,መፈናቀሎች,የንብረት ዉድመት,የዘር ፍጅትእና አገር አልባነት ልለፈዉና የዛ ስርአት ቀጥተኛ ወራሽ የሆነውን የብልፅግና ፓርቲ እና መንግስት በአማራ ህዝብ ላይ የፈፀመዉን እና እየፈጸመ ያለዉን በደል ልግለፅ።

የብልግና መንግስት በአማራ ህዝብ ተጋድሎ ወደ ስልጣን የመጣ ቢሆነም ህገመንግስታዊ ማሻሻያን ጨምሮ ፀረ አማራ የሆኑትን የመንግስት ፖሊሲዎች አስተካክላለሁ ብሎ ቃል ገብቶ የነበረ ቢሆንም በተግባር ግን አማራ ጠል መሆኑን ያስመሰከረዉ ጊዜ ሳይወስድ ነበር።
የብልፅግና መንግስት ከ ትህነግ ኢህአዴግ የወረሰውን የፌደራል እና የክልል ህገመንግስቶች ,ፖሊሲዎች እና መመሪያዎች ይዞ ቀጥሏል።ከ 50 በላይ በአማራ ህዝብ ላይ የዘር ፍጅት እንዲፈፀም ፀረ አማራነትን የሚቀሰቅሱ መፃህፍት አሳትሟል ።በምርምር መፅሄቶች ስም አማራ ጠልነትን ሰብኳል።በመንግስትነቱ በሚያስተዳድራቸው በኦሮምያ ቱሪዝም ቢሮ,በኦሮምያ ፕሬዝዳንት ፅ/ቤት,በኢትዮጽያ ፕሬስ ድርጅቱ ስር በሚታተሙ መፅሄትና ጋዜጦቹ በአማራ ህዝብ ላይ ለአመታት የቆየ የጥላቻ ዘመቻ አካሂዷል ።ከከፍተኛ እስከ ዝቅተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ፀረ አማረ ንግግሮች እና ትንኮሳዎች ተደርገዋል።

በተጨማሪም የብልፅግና መንግስት የአማራ ህዝብ የፖለቲካ ዉክልና እንዳይኖረው በማድረግ ዛሬ በአስር ሚሊዮኖች የሚቆጠረው ከአማራ ክልል ዉጭ የሚኖረው የአማራ ህዝብ ምንም አይነት የፖለቲካ ዉክልና የለዉም ።

ከመንግሥት የስራ ሀላፊነት ጠርጎ በማዉጣት አድሎአዊ አሰራርን በማስፈን በብዙ ሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች በማፈናቀል ፣ በቢሊዮኖች የሚገመት የአማራን ህዝብ ሀብትና ንብረት በማውደም እንዲሁም ዘግናኝ የሆነ እንኳን ሊያዩት ሊሰሙት እንኳ የሚከብድ የዘር ፍጅት እንዲፈፀም አድርጓል ። ይህ የዘር ፍጅትበመላው ኢትዮጵያ በሶማሌ ፣ በኦሮሚያ ፣ በትግራይ ፣ በሲዳማ ፣ በቀድሞ የደቡብ ክልል ፣ በጋምቤላ እና በቤኒሻንጉል ክልሎች የተፈፀመ ነው ።
ለዚህም በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ የአይን ምስክሮች በተጨማሪ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን ፣ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ጉባኤ ፣ በኢትዮጵያ የሰብአዊ መብቶች ላይ የሚሰሩ ጥምረት እንዲሁም አለም አቀፍ የሆኑት የተባበሩት መንግስታት ሰብአዊ መብት ኮሚሽን እና የሂውማን ራይትዎችን ዘገባዎች በማየት መረዳት ይቻላል ።
  ጉዳዩን ሊከታተል ይችላል ተብሎ ይታሰብ የነበረው የብልፅግናው የአማራ ክልል መንግሥት ደግሞ እንኳን የአማራን ህዝብ ሊታደግ የገዛ ስልጣኑን የማያውቅ ፣ የፖለቲካ ነፃነቱን አሳልፎ የሰጠ እንዲሁም ከውሳኔ ሰጪነት ወደ ፈፃሚነት የወረደ ነው ። (ከክልሉ ውጪ ያሉ አማራዎች እንታገላቸዋለን እንጂ አንታገልላቸውም)ከማለት የደረሰ ሎሌ ነዉ።

   በተደጋጋሚ ባጋጠሙ ጉዳዮችም ተፈትኖ የወደቀ ለምሳሌ በአማራ ልዩ ሃይል መፍረስ ፣ በፕሪቶሪያ ድርድር ፣ በሱዳን ወረራ ፣ በአጣዬ እና ሸዋሮቢት ፍጅት የአማራን ህዝብ መብት ማስከበር ያልቻለ ለተፈናቃይ ዱላ ለዘር ፈጂዎች ግን ካባ የሚሸልም ስብስብ ነው ።

     የፌደራል መንግሥቱ ደግሞ ያለምንም እፍረት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፣የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነሩ ፣ አቃቢ ህጉ ፣ መርማሪው ፣ ደህንነቱ ፣ የፍርድ ቤት አስተዳደር በአጠቃላይ የአንድ ብሔር/ሀይማኖት አባላት በመሆን ህግን የማጥቂያ መሣሪያ በማድረግ የአማርን ሕዝብ ልጆች ያጠቃል ።
   የአማራ ሕዝብ ከላይ በጠቀስኳቸው ምክንያት የሀገር ባለቤትነቱ የተወሰደበት ፣ ሀገሩን የተቀማ በመሆኑ ፣ ድርጊቱም ሥርአታዊና መንግሥታዊ ለመሆኑ የሚመሠክሩ በርካታ ማስረጃዎች ያሉ በመሆኑ የአማራ ህዝብ ከዚህ የህልውና አደጋ ለመውጣት መንቃት ፣ መደራጀትና እራስን ከጥቃቶች መከላከል ይገባዋል የሚል የፀና አቋም ያለኝ በመሆኑ ይሄንን ዘረኛ እና ነውረኛ አንባገነን ሥርዓት ለመጣል ትግል እንደሚያስፈልግ እምነቴ ነው ።

በጭብጦቹም ላይ

   * የሸዋ ፋኖን በማደራጀት በኩል የራሴን አስተዋፅኦ አድርጊያለሁ
  *የአማራ ፋኖን ወደ አንድነት ለማምጣት ሲባል የተመሠረተው አመቻች ኮሚቴ ሰብሳቢ ሆኜ ሠርቻለሁ
  *የአማራ ፋኖ ምክርቤት እንዲመሠረት የራሴን አስተዋፅኦ አድርጊያለሁ

  * አገሪቱ በተቀበለቻቸው ዓለምአቀፍ የሰብአዊ መብት ድንጋጌዎችና የብልፅግና መንግሥት እመራበታለሁ በሚለው ህገመንግስት በሰፈሩት ሰብአዊና እና ዲሞክራሲያዊ መብቶቹን መሰረት በማድረግ የህዝቤን ግፍ እና በደል ለማስቆም በህቡዕ ሳይሆን በአደባባይ ታግያለሁ።

*የሰራሁት በሙሉ በግልጽ በአደባባይ የተፈፀመ እንጂ ምንም አይነት ህቡዕ ድርጅት አቋቁሜ አልሰራሁ።

*በህቡዕ አደረጃጀት ተፈፀሙ የሚሉትን ተግባራት አላዉቅም።አልፈፀምኩም

የኢትዮጵያ ህዝብ የአማራን ህዝብ በደል በደንብ ይገነዘባል ብዬ አምናለሁ የኢትዮጵያ ህዝብ "የአማራ ህዝብ እንባ በዋንጫ"ቢሰጣቸዉ የማይጎፈንናቸዉን የብልፅግና ስርአት ቁንጮዎች በቃችሁ ሊላቸዉ ይገባል።

በተጨማሪም የአማራ ህዝብ የህልዉና ትግል ለነፃነት ለእኩልነትና ለፍትህ የሚደረግ ትግል እንጅ ጠላቶቻችን እንደሚያወሩት ሌላዉን ለመጨፍለቅ የሚደረግ ባለመሆኑ የኢትዮጵያ ህዝብ የአማራን ህዝብ የህልውና ትግል ደግፎ እንዲቆም እጠይቃለሁ።

አለማቀፉ ማህበረሰብም የአማራ ህዝብ እየተፈፀመበት ያለዉን የዘር ፍጅትና መፈናቀል ቸል በማለቱ በጣም እያዘንኩ ለአምባገነኑ መንግስት ጅምላ ጨራሽ ድሮዎኖች እና ተተኳሾችን የሚያቀብሉ አገራት ታሪክና እና እግዚአብሔር ፍርዱን ይሰጣችኋል እላለሁ።

አመሰግናለሁ ።
ኅዳር 5/2017 ዓ.ም

ዶ/ር ወንዶሰን አሰፋ

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

14 Nov, 14:16


በመንግስት የሚፈጸሙ የድሮን ጥቃቶች ሰላማዊ ዜጎችን ለህልፈት እየዳረገ ነው”- ኢሕአፓ

ሐሙስ ህዳር 05 ቀን 2017 (አዲስ ማለዳ) የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ “የዜጎችን ህይወት የመጠበቅ ሃላፊነት ያለበት መንግሥት ቢሆንም በሚያሰማራቸው የጸጥታ ሃይሎችና የአገር መከላከያ ሠራዊት አባላት ጭምር የዜጎች ህይወት በበርካታ የሀገሪቱ ክፍሎች እንደቅጠል እያረገፈ ይገኛል” ብሏል፡፡

ኢሕአፓ ዛሬ ባወጣው መግለጫ ህገመንግሥቱን የመንግሥት አካላት ራሳቸው ካላከበሩት እንዴት ሊያስከብሩት ይችላሉ “በንጹሀን ዜጎች ላይ የሚደረጉት ግድያዎች ይቁሙ” ሲል አሳስቧል፡፡

እንዲሁም የተለያዩ የመንግስት መገናኛ ብዙሀን ከመዘገብ ቢቆጠቡም በውጪ የመገናኛ ብዙሀን ጭምር ጥቃቱ መፈጸሙን እየገለጹ መሆኑን እና ፓርቲውም አጣርቻለሁ ያለውን በየክልሉ የደረሱትን ጥቃቶች አስታውቋል፡፡

ፓርቲው አጣርቻለው ባለው መሰረት ኦሮሚያ ክልልን ጨምሮ በተለያዩ አካባቢዎች የሚደርሱ ጥቃቶች የሟቾችን ቁጥር እያሻቀበ መሆኑን እና ጥቃት ከተፈጸመባቸው ውስጥም ነፍሰጡሮች፣ የጤና ባለሙያዎች እና በትምህርት ቤት ውስጥ የነበሩ ተማሪዎች እንደሚገኙበት አመላክቷል፡፡

በመሆኑም “ወደፊት ትውልድ እንዲከፍል በብድር በመጣ የጦር መሳሪያ ንጹሀን ዜጎች ላይ የጅምላ ጭፍጨፋ ማካሄድ አግባብነት የለውም”፤ መንግሥት ኃላፊነቱን እየተወጣ ነው ለማለት እንደዚህ ያለውን ሁኔታ በዝምታ ማስቀጠል አይችልም ሲል ኮንኗል፡፡

ኢሕአፓ መንግሥት በተለይ የጦርነት አውድማ በተደረጉት በአማራ፣በኦሮሚያ፣ በቤኒሻንጉል ጉምዝና በደቡብ ክልሎች ዉስጥ የሚደረገውን ህገመንግሥቱን እየጣሱ ያሉትን፣ መንግሥት መር የዜጎች ግድያዎችን በጥብቅ ማውገዙን እና ጦርነቶቹ አሁኑኑ ይቁሙ ሲልም አሳስቧል፡፡

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

13 Nov, 18:22


የአብይ አህመድ መዘባረቆች በእውቀት መነጽር ሲጋለጡ! እመራታለሁ ለሚላት ሀገር ጥላቻው እና ውሽቱ! #የአቶ_#ያሬድ_ኃየለመስቀል #ድንቅ_እይታዎች! https://youtu.be/ygPdj-XBY_U?si=vu1WW_NxipZd_8TM

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

13 Nov, 18:20


https://youtu.be/ygPdj-XBY_U?si=vu1WW_NxipZd_8TM

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

11 Nov, 19:31


https://www.youtube.com/live/Mi15dYZH3Cg?si=XHY_wxA8Ts29JFFt

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

11 Nov, 18:31


ጎጃም | ዲማ

አገዛዙ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የዲማ ጊዮወርጊስ  ፍቅር እስከ መቃብር ሙዚየምን አቃጥሎታል። ከዚህ በተጨማሪ አራት ንጹሀንን እና አንድ ካህን ገድሏል። በወራሪው ሰራዊት ዲማ ጊዮወርጊስ   አብቁተ ተቋምም ዝርፊያ ተፈጽሞበታል። መረጃው የጋዜጠኚ ተስፋዬ ወ/ስላሴ ነው!

#Amhara #Ethiopia

የግዮን አማራ የቲክቶክ ገፅ!👇
https://vm.tiktok.com/ZMhHdJPKC/

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

27 Oct, 17:54


https://www.youtube.com/live/tK2dl8f8u4Y?si=mG2fz3jXwlU54GJM "እውነታው ግን ይጋለጥ!" "ሲኖዶሱ ችግሩን አይፈታውም! ይግባኝ ለክርስቶስ! ይግባኝ ለኦርቶዶክሳውያን!" ዘርኝነትን፣ ከፖለቲካና ሌባ ባለሥጣናት ጋር መሻረክን... እኩያን፣ ደዌያትን ሁሉ እየጎተተ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የሚያስገባው ምዝበራና መዝባሪዎቹን ማጋለጥ እንቀጥላለን!

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

26 Oct, 17:39


https://www.youtube.com/live/kO5NtvB0p3w?si=nPwSlWBS8gFWzm1c #ሌብነት_ያሸነፈበት_የሐሙሱ_ድራማ #ተጠናክሮ_የቀጠለው_ #የበለጠ_የተመቻቸለት_የዘረፋው_ኤምፓየር
#ሌብነት_ያሸነፈበት_የሐሙሱ_ድራማ #ተጠናክሮ_የቀጠለው_"ኦርቶዶክሳውያንን የማጽዳት" _ዘመቻ፤ የቅ. ሲኖዶስ ነገር፤ #የበለጠ_የተመቻቸለት_የዘረፋው_ኤምፓየር! #ዛሬ_ስለ_መፍትሔ_እንነጋገር!

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

26 Oct, 16:06


ሰበር ዜና

በሰሜን ሸዋ ዞን በኩዩ ወረዳ  ገባ ሮቢ የሚባል ቦታ ላይ ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ብሎ የሚጠራው ጽንፈኛ ቡድን ታቦተ በዓለወልድን በመሰባበር  ካህናት ላይ ከፍተኛ ድብዳባ ማድረሱ ታውቋል።
++++++++++++++++++++++++
አሁንም ቢሆን አልረፈደም ዓላማቸው ኦርቶዶክስን ለማጥፋት መሆኑን ያልተረዳችሁ በጊዜ ወደ ቀልባችሁ ተመለሱ።ይህ የልብ ሙቀት መለኪያ ነው ነገ እንደ አርሲ ጭፍጨፋ ለመፈጸም ነው እየተዘጋጁ ያሉት። (t.me/Eyo21e)

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

26 Oct, 15:27


የማይፈወሰው ድውይ የማይመለሰው ጊጉይ! ++++++++++++++++++++++++++++++ ዕቅበተ እምነት ላይ እንጂ ተቋማዊ ጥበቃ ላይ ብቻ ማተኮር ማደክደክ ነው።
  ላይኛው ተቋም ለእውነት ሥራ ዝግጁ አይለም።
ከትናንት እስከ አሁን  በቤተ ክርስቲያን ላይ ለደረሰው ውስጣዊ መከራ ተቋሙ የችግር ባለቤት ሳይሆን ራሱ ችግር ነው።
በተለይም የውጭ መከራዎችን እንደ እባብ ሰይጠንን ተጭኖ እየመጣ አዳማውያንን የሚያስትበት ቤት ከሆነ ሰነባብቷል።
ህልው ሁኖ አጀንዳ የሚሰጣችሁ ማን ነው?ይሄንን የማያውቅ ሰው ይኖራል? ካላ በጣም ፈዛዛ ነው።
ይልቅስ እንደ ባለቅኔው የጥፋት መልእክቱ ደርሶና የላካችሁ ሰውየ ደኅና ነውወይ? አትሏቸውም?
ይሄንን የምጽፈው በግል ሁኖ አንዳንድ የቤቱን ተንኮል ያልተረዱ የዋሓን ምእመናን ዛሬም ሲደናገሩ በማየቴ ነው።
የማይፈወሰው ድውይ የማይመለሰው ጊጉይ ሁኖ መድኃኒቱን እያማሰነ እንደገና በደዌ እያመረቀዘ የጥፋት ቫይረስ ተሸካሚ ሁኖ ከተገለጸ ቆይቷል።
አሁንም የአትርሱኝ ጩኸት ወዲያ ወዲህ ሲያወራ ቢሰማም ምእመናንን ዕረፍት ለመንሳት፣ለማደናገር፣የንትርክ አጀንዳ ለመስጠት፣ለሥርዓቱ ጥበቃ ይጠቅማል ተብሎ የተሰጠውን የተልእኮ ዓላማ ለመፈጸም ሲባል..ነው እንጂ የቤተ ክርስቲያን ጉዳይ የሚመለከተው ሁኖ አይደለም።
ይሄ ጉዳይ በደንብ ተነጋግረውበት ተወያይተውበት የአትርሱኝ አስታውሱኝ አጀንዳ እንጂ የእውነት አይደለም።ሁሉም የሚሠሩት አብረው ነው።
ዋናው ጉዳይ ምእመናንን ማደናገር፣ዕረፍት መንሳት፣እምነቱን እንዲተው ማወክ፣ሥርዓቱን መጫን፣ምእመናንን ማሳቀቅ፣ጭር ሲል አልወድም...ነው።
ቢያንስ ሞቱ እንግልቱ ይቅርና ምእመናን ሀዘናቸውን እንኳን ዕርም አውጥተው እንዳያዝኑበት ዲሪቶውን አምጥቶ ይጭንባቸዋል።
እኔ በግሌ ከነነዌ ምህላ እና ከሐምል 9/1015 ዓ.ም.ጀምሮ ጨርሸ ትቻቸዋለሁ።ረቂቅ ውንብድናውን እስከ ጥግ አይቸዋለሁ።
እኔ ግን የለውጥ መንገዱን እስካገኘው እፈልገዋለሁ።ከሕይወቴ አብልጬጬ እጨነቅለታለሁ።ሁልጊዜም ቤተ ክርስቲያን የደረሰባትን ሳስበው አንጀቴ ይላወስብኛል።
ወደ መፍትሄው ብቻ ዓይናችንን እናዙር።
የቤቱ ስም የእኛ ነው ሥራው ግን የአጥፊዎች ነው።
ሁለንተናው ኦርቶዶክሳዊ እስኪሆን ድረስ ዓይናችንን ወደ መፍትሄው ብቻ እናዙር። (የግል ምልከታ፤ ከምሥራቀ ፀሐይ ገጸ )

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

26 Oct, 14:11


አስቸኳይ የድረሱልን ጥሪ

በምሥራቅ ወለጋ ዞን፣ ጊዳ አያና ወረዳ አንዶዴ ዲቾ ቀበሌ ማንነትን ማዕከል ያደረገ የከፋ እልቂት ከፊታችን ተደቅኗል፤ ድምፃችንን አሰሙልን ሲሉ የአካባቢው ነዋሪዎች ተማጽነዋል።

ጥቅምት ፲፪ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም ከአንድ የፀጥታ ኃይል አዛዥ ጋር ከጠዋቱ ፬ ሰዓት እስከ ፲፩ ሰዓት እንደ ተደረገ በተገለጸልንና እጅግ ውጥረት የተሞላበት ውይይት የቀበሌው ነዋሪዎች መሣሪያቸውን እንዲያወርዱ ካልሆነ ግን የከፋ ነገር እንደሚጠብቃቸው በእርሳቸው አባባል "ካላወረድክ ... ትታረሳለህ" ማለታቸው እጅግ ሥጋት እንዳሳደረባቸው ለፓርቲያችን የደረሰው መረጃ ያመለክታል። ሥጋቱ ይህ ብቻ ሳይሆን "እኛ መሣሪያ ካወረድን በሰዓታት ልዩነት ሸኔ መጥቶ ይጨፈጭፈናል፤ ይህ ደግሞ ያለፉ ዓመታት የቀን ተቀን ሰቀቀናችን እንደሆነ ማንም ያውቃል" ይላሉ ነዋሪዎቹ።
"መተማመን በሌለበትና እስከዛሬ ማን አሳልፎ እንደሚሰጠን ባወቅንበትና አኹን በጥቂቱ በመንግሥት ጥረትም፣ በሬያችንን እየሸጥንም ገዝተን በታጠቅነው መሣሪያ ራሳችንን ለማትረፍ የአልሞት ባይ ተጋዳይ በምናደርግበት ወቅት እንዲህ መባሉ እጅግ አስገርሞናል" ብለዋል። በአካባቢው በግምት 20 ኪ.ሜ ርቀት ላይ መንግሥት ሸኔ ብሎ የሚጠራውና ራሱን ኦ.ነ.ሰ የሚለው ኃይል ከፍተኛ እንቅስቃሴ የሚያካሂድበት ቦታ መሆኑንና እስከ አኹንም በጥቂቱም ቢሆን በዚኹ መንገድ ራሳቸውን እየተከላከሉ እንደቆዩ ነዋሪዎቹ ይናገራሉ። በጭንቀት ያሉት እነዚሁ የአንዶዴ ዲቾ ቀበሌ ነዋሪዎች ለሞት አሳልፎ የሚሰጠንን ውሳኔ "ብትቀበሉ ተቀበሉት" መባሉ አስገራሚ ነው ብለዋል።
"እጅግ ውጥረት የተሞላበት ውይይት ነበር። እባካችሁ መሐል ላይ ያለ የእኛን ደህንነት የሚያስጠብቅ መፍትሔ ስጡን" እያልን ብንማጸናቸውም ሊረዱን ዝግጁ አልነበሩም፤ ብቻ 'ታወርዳለህ ታወርዳለህ' እያሉ ይዝቱ ነበር" የሚሉት ነዋሪዎች "በመጨረሻም ባለመግባባት ሕዝቡም አዳራሹን ጥሎ ወጥቷል" ብለዋል።

በሰሜኑ ጦርነት ወቅት መላው የጸጥታ ኃይል አካባቢውን ሲለቅ መንግሥት እኛን አምኖ ራሳችንን እየተከላከልን አካባቢውንም እንድንጠብቅ ያደረገ ቢሆንም አኹን ምን ተገኝቶ ቃሉን አጠፈ ይላሉ።

ውይይቱን የመሩት የጸጥታ ኃይል ስምና ማዕረግ የደረሰን ሲሆን በብዙ ምክንያቶች ለጊዜው መጠቀም አላስፈለገንም።

ፓርቲያችን ጉዳዩን በቅርበት እየተከታተለው ሲሆን ይኽ አካባቢ የሞት ቀጠና ከሆነ የቆዬና አኹንም ምንም የተለወጠ ነገር ባለመኖሩ ከሰማናቸው ኹሉ የባሰ ዘግናኝ እልቂት ከመፈጸሙ በፊት በተለይ የመከላከያ ሠራዊት አመራሮች ጉዳዩን በገለልተኝነትና ከነባራዊ ኹኔታ ጋር የተገናዘበ መፍትሔ እንዲሰጡት በአደራ ጭምር ልናሳስብ እንወዳለን።

እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቧን ይጠብቅ

እናት ፓርቲ
ጥቅምት ፲፮ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ

@እናት ፓርቲ

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

26 Oct, 05:22


የአርሲ ኦርቶዶክላውያን ሰቆቃ


Gidiiraa Ortodoksootaa Arsii Irtaatti Raawwatamaa Jiru.


ኦሮምኛ ተናጋሪ ኦርቶዶክሳውያን አይናችሁን ግለጡ።ከዘረኝነት ዉጡ ኦርቶዶክሱ እያለቀ ነው።ሕዝባችሁን አድኑ።


በዚህ ሪፖርት ውስጥ ኦሮሚኛ ተናጋሪው ኦርቶዶክስ ያነሳቸው ዋና ዋና ነጥቦች መካከል ጥቂቶችን እንመልከት።

ripportii Kana Keessatti namni Ortodoksii Oromoo Kuni qabxiilee Ijoo Kasuuf Yaale Keessaa Murasa Isaanii Yoo ilaallu.

~ እኛ ኦሮሞዎች ነን የምንሄድበት ቦታ የለንም
~nuti Oromoodha Biyya Keenya Gadidhiifnee Eessaayyuu hin deemnu

~እየተፈጸምብን  ባለው ጭፍጨፋ የመንግሥት እጅ እንዳለበት እናውቃለን

ajjeechaa nurratti raawwatamaa jiruun  mootummaan harka keessaa  akka qabu ni beekna.

~ እነዚህ የሚጨፈጭፉን ሰዎች መጀመርያ ላይ አማራን እየመረጡ ሲጨፈጭፉ ነበር  አሁን ደግሞ  እኛን ክርስቲያን ኦሮሞዎችንም መጨፍጨፍ ጀምረዋል 

qaamooleen  ajjeechaa nurratti raawwataa jiran kunniin jalqaba irratti saba amaaraa  ajjeesaa turani  ammaa immoo nuyi oromoota ortodoksii ajjeesaa jiru.

~ የሕዝቡን(የ ክርስቲያኖችን) ሀብት እየዘረፉ እኛን እያደሀዩን እነርሱ እከበሩ ነው ያሉት

Ummata( kiristaanoota) Irraa Qabeenyaa Saamuun Nu Hiyyoomsanii Ofiisaaniitiif Duroomanii Jiru

~ እነዚህ ሰዎች ትግል ሲጀምሩ ጸባችን ከመንግሥት ጋር ነው አሉን  ከዚያን አማራ ላይ ያተኮረ ጭፍጨፋ ከፈቱ አሁን ደግሞ ሄዶ ሄዶ ሰፍቶ ሰፍቶ  ወደ ሃይማኖት (ኦርቶዶክን ወደ ማጥፋት)ዞሯል።
namoonni kunniin eennaa qabsoo jalqaban lolli keenya mootummaa waliin nun jedhani,itti aansanii saba Amhaaraa Irratt  Duguggaa Sanyii Raawwatan Amma Immoo deemee deemee Bal'atee Bal'atee gara amanraattii(ortodoksi balleeessutti)garagalee jira.

~  የክርስቲያን ማኅበረሰብ ኦሮሞም ሆኖ ክርስቲያን የሆነ ከፍተኛ ሰቆቃ ውስጥ ነው ያለው።

hawaasni Kiristaanaa  , Oromoos ta'ee  amantaan isaa kiristaanaa  kan ta'e gadadoo guddaa keessa jira.

~ቀን ቀን በመንግሥት ኀይሎች እንደደላለን እንዘረፋለን ማታ ማታ ደግሞ በታጠቂዎቹ(በአክራሪ የእስላም ወሀቢያዎች) እንገደላለን እንዘረፋለን።
guyyaa guyyaa qaamoolee mootummaatiin halkan halkan ammoo Qaamoolee finxaleeyyiin Qabeenyi Keenya Insaamama

~አዋሽን ተሻግራችሁ(ወደ  ሸዋ ተመለሱ )ሂዱ ኦሮሞ ብትሆኑም ይህ የእናንተ ሃገር አይደለም ወደ ሸዋ ተመለሱ

kuni biyya keessanii miti waan ta'eef  Gara Awaash Gamatti(shawaatti) deebi'aa oromoo taataanis kuni biyya keessanii miti gara shawaatti deebi'aa

~ እኔ እንደምታየኝ ኦሮሞ ነኝ ነገር ግን ክርስቲያን በመሆናችን ብቻ እየተገደልን ነው።የኦሮሞ ክርስቲያን ከምድረ ገጽ እየጠፋ ነው አልቀናል አልቀናል ኡኡኡ....

akkuma na argitu ani oromoodha haa ta'u malee kiristaana ta'uu keenya qofaaf ajjeefamaa jirra.kiristaanni oromoo lafarraa duguugamaati jira .dhumne dhumne uuuuuu...


https://www.youtube.com/live/jzmHMk0Pr80?si=5ng4HbblOOmXx0FC

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

25 Oct, 23:29


የፋሽስቱ አገዛዝ ህፃናት ግድያ ቀጥሏ‼️

የግፍ ተገዳዩ ህፃን ዳዊት መካሽ ይህ ነው።

ህፃን ዳዊት መካሽ ይባላል የ6 አመት ልጅ ነው በትናንቱ የድሮን ጥቃት ሸዋ-ይፋት-ራሳ የተገደለ ልጅ ነው። ይህ ህፃን በገዛ ቤቱ ውስጥ የተገደለው ታጣቂ ሆኖ ነው? አማራን ለማጥፋት እንደተነሱ ይህ ምስክር ነው።

The drone attack in Shoa Amhara-Yifat-Rasa that tragically killed six-year-old Dawit Mekash is a horrific act of inhumanity that must be stopped immediately.

#Dawit_Mekash

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

25 Oct, 18:28


በኮሪደር “ልማት” ሰበብ በአዲስ አበባና ዙሪያዋ ከተሞች የአምልኮ ሥፍራዎችን የማፍረስ ተግባር “ያደገው” ዓለም ያለፈበት የጥፋት ጎዳና አገራዊ መገለጫ አካል ነው ሲል የእናት ፓርቲ ገለጸ፡፡
++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++
ፓርቲው አብያተ እምነት የሰማያዊ መንግሥት ተልዕኮ ማስፈጻሚያ ኤምባሲዎች በመሆናቸው ጥበቃ ሊደረግላቸው ሲገባ የብልጽግና መንግሥት የወንዝ ዳር፣ ጫካ፣ ኮሪደር… ወዘተ በሚል ፕሮጀክት የማናለብኝነት ፈረሳና የማፈናቀል ተግባር እየተከናወነ መሆኑን ገልጾ ድርጊቱን አውግዟል፡፡

እየፈረሱ ካሉት በዋቢነት የሰበታ ጌቴሴማኒ ቤተደናግል ጠባባት የሴቶች ገዳም ይዞታ ከክብር በወረደ አኳኋን እንዲፈርስ የተደረገ ሲሆን ከየካቲት ፲፪ አደባባይ ከፍ ብሎ ያለውና ከአምስቱ ዓመት የፋሽስት ጣልያን ወረራ ወቅት ጋር ቀጥተኛ ተያያዥ ታሪክ ያለው የአገር ባለውለታው የምስካዬ ኅዙናን መድኃኔዓለም ገዳም ይዞታም ጠባብ የሆነውን ዐውደ ምሕረት የበለጠ በማጥበብ ከፊት ለፊቱ የገዳሙና የገዳሙ አገልግሎት መስጫ ተቋማት ፈረሳ ሊካሄድ መሆኑን መረጃ እንደደረሰው ገልጿል፡፡

በተጨማሪም ፓርቲው እነዚህን በዋቢነት ጠቀስን እንጂ ፈረሳው ያነጣጠረባቸው በአዲስ አበባ ከተማና አካባቢው የሚገኙ አብያተ እምነት ቁጥር ብዙ እንደሆነ ተረድተናል ብሏል።

ባለፉት ጥቂት ተከታታይ ዓመታት በአብያተ ክርስቲያንና መስጅዶች ላይ በተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች የደረሱ ቃጠሎዎች፤ በአገልጋዮችና ምእመናን ላይ የደረሱ አሰቃቂ ግድያዎች በኢትዮጵያ በትልቁ ሀገራዊ እሴታችን (ሃይማኖት) ላይ የተጋረጠውን ኹለንተናዊ ጥቃት ማሳያ ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል ሲል ጠቅሷል።
ከዚኹ የቀጠለ በሚመስል አኳኋንና በተቀናጀ መልኩ በአዲስ አበባና አካባቢው አብያተ ክርስቲያን ይዞታዎች ላይ እየተወሰደ ያለው የማፍረስ ተግባር ከውጭና ከውስጥ ተናቦ የሚተገበር መኾኑን መጠርጠር አያዳግትም። አብያተ እምነት ለሰው ልጅ አጠቃላይ መንፈሳዊና አእምሯዊ ልዕልና ያላቸው ሚና አይተኬ ነው። ይህ ደግሞ ለኢትዮጵያውያን ሲሆን ድርብ እውነት ያደርገዋል። እነዚኽ የእምነት ተቋማት እያንዳንዳቸው በዙሪያቸው የሚኖሩ በአማካይ ሃያ ሺህ ያክል ዜጎችን የሚያገለግሉ እንደሆነ የሚገመት ሲሆን በዚኽ ልክ የዕለት ተዕለት አገልግሎት የሚሰጡ ሌሎች ተቋማትን መጥቀስ አይቻልም ብላል ፓርቲው።

አውሮፓውያን በዘመነ አብርኆት(enlightenment) ሃይማኖትና አብያተ እምነትን አሽቀንጥረው ጥለው ነበር። ሆኖም ባለፉት ፶ ዓመታት በተለይ የደረሰባቸውን የሞራል ኪሣራ፣ የተመሳሳይ ጾታ ጋብቻ፣ ስግብግብነት፣ እርካታ ማጣት፣ ግለኝነት፣ የተዘወተረ ራስን ማጥፋትና መሰል ዘግናኝ ድርጊቶች በሕዝባቸው ላይ መንሰራፋት አካሄዳቸውን ቆም ብለው እንዲያጤኑት እንዳስገደዳቸው ያስታወሰው እናት ፓርቲ የቀድሞዋ ሶቪየት ኅብረት አብዮተኞች እንዲኹ ቅጽር መዳፈር፣ ማፍረስ፣ አሻራቸውን ማጥፋት፣ መጽሐፍትን ማቃጠል፣ የሃይማኖት አባቶችንና አማኞችን ማሳደድ በሰፊው ሞክረውት ነበር። ያ ኹሉ አልፎ ወደቀልባቸው የተመለሱ መሪዎች ሲመጡ ዛሬ ሕዝባቸውን ሃይማኖትና የሞራል ልዕልና ያለው በማድረግ፤ በስልጣኔ ስም ለሚመጣ ዘመናዊ ቅኝ ግዛት "አይሆንም" ባይ በማድረግ ይበልጡን የዓለሙን ሚዛን በማስጠበቅ ይጠቀሳሉ ሲል ገልጿል።

በአገራችን ኢትዮጵያ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በአብያተ እምነት እና በምእመናን ላይ እየደረሰ ያለው ተከታታይ ጥቃትና የመግለጫችን ጭብጥ የሆነው በአብያተ እምነት ይዞታዎች ላይ ያነጣጠረ የማፍረስ ዘመቻ ይኸው “ያደገው” ዓለም ያለፈበት የጥፋት ጎዳና አገራዊ መገለጫ ነውም ሲል አክሏል።

በመጀመሪያ ዙር የኮሪደር “ልማት” የተጠቀሰው የፈረሳ ሥራ መስመር ላይ ያሉ የምድራውያን የውጭ አገራት መንግሥታት ኤምባሲዎችን እንዳልነካቸው ኹሉ ይልቁን እነዚህን የሰማያዊ መንግሥት ኤምባሲ ሆነው የሚያገለግሉ ተቋማት የፈረሳው ሥራ ፈጽሞ እንዳይነካቸው እናት ፓርቲ በአጽንኦት ያሳስባል።
በብልጽግና መንግሥት የአብያተ እምነት ይዞታዎችን በማፈራረስ የሚተገበር የትኛውም ሥራ እንደ ማንኛውም ምድራዊ መንግሥት የሥርዓቱ እድሜ አብቅቶ በሌላ ሲተካ ወደ ቀደመ ይዞታቸው መመለሳቸው አይቀሬ ነው ያለው ይህ ፓርቲ በደርግ ዘመን ዋናው መግቢያ ተዘግቶ ቆይቶ ኢሕአዴግ ስልጣን በያዘ ማግስት የተከፈተውን የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል አስታውሷል።
ስለሆነም የብልጽግና መንግሥት ከዚኽ ነባር ሃይማኖት ጠል አካሄዱ እንዲታቀብና የአብያተ እምነት ቅጽሮችን ማፍረሱን በአፋጣኝ እንዲያቆም በጽኑ አሳስቧል፡፡
++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++ የቱንቢን ትክክለኛ የቴሌግራም ገጽ ይቀላቀሉ! ያስተዋውቁ!
https://t.me/tunbi_media
🎥💻📺🎙 YouTube በዩቲዩብ ዝግጅቶቻችንን 👁👁👂🏽👂🏽ይታደሙ!
www.youtube.com/@TunbiMedia_
በራምብል
rumble.com/c/c-3688912
በቲክቶክ
tiktok.com/@ethiotunbi

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

24 Oct, 16:35


በዛሬው የቅዱስ ሲኖዶስ ውሎ በአጭሩ ነገሩን ለመቀልበስ 60 ሚሊዮን ብር ገደማ መድቦ የተነቀሳቀሰው የሙስና ኤማፓየሩ አዲስ አ/ሀ/ ስብከት በአሸናፊነት ወጥቷል!። ቅ. ሲኖዶሱ በርካታ መረጃና ማስረጃዎች የቀረቡበትን ጥናት "ባለቤት ያልቀረበበት ክስ" ሲል ውድቅ አድርጎ የሊቃነ ጳጳሳት ኮሚቴ አቋቋሟል። ይሄም አጀንዳውን በስልት ከመድረኩ የማሸሽ አካሄድ መሆኑን ከሲኖዶሱ ያለፉት አካሄዶች ለመረዳት ቀላል ነው።

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

23 Oct, 18:33


https://www.youtube.com/live/vPrNhwiAho4?si=xGAmZP9pHhc80bm9

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

23 Oct, 15:25


https://youtu.be/QMlC_WffDiM

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

22 Oct, 19:52


https://youtu.be/QMlC_WffDiM?si=ABclpslfAUumt39e ++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++ የቱንቢን ትክክለኛ የቴሌግራም ገጽ ይቀላቀሉ! ያስተዋውቁ!
https://t.me/tunbi_media
🎥💻📺🎙 YouTube በዩቲዩብ ዝግጅቶቻችንን 👁👁👂🏽👂🏽ይታደሙ!
www.youtube.com/@TunbiMedia_
በራምብል
rumble.com/c/c-3688912
በቲክቶክ
tiktok.com/@ethiotunbi

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

22 Oct, 13:49


“...ነገሩ ሁሉ ግራ የሚያጋባና የተመሰቃቀለ ሆኖ ይታያል፡፡ ችግሩ ከሕዝብ አልፎ የአምልኮ ስፍራዎችንና የአምልኮው ፈጻሚዎችን ዒላማ ያደረገ እግዚአብሔርን መዳፈር እየተለመደ መጥቶአል፤ ይህ ለአንድ ሀገር ወይም ሕዝብ የውድቀት ምክንያት ከሚሆን በቀር ከቶውኑም የዕድገት ምልክት ሊሆን አይችልም፡፡”
የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያሪክ አቡነ ማትያስ የጥምቅት ሲኖዶስ የመክፈቻ መልእክት!
ጥቅምት ፲፪ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም. ቱንቢ ሚዲያ
++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++
በጥቅምት 2017 ዓም የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ
መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
•ብፁዕ አቡነ አብርሃም
የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የባሕር ዳርና የሰሜን ጐጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤
•ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤
•ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት፤
ዓመቱን ጠብቆ ስለ አጠቃላይ ተልእኮአችን ለመወያየት በዚህ ጉባኤ የሰበሰበን አምላካችን ስሙ የተመሰገነ ይሁን፤
“ወይእዜኒ ግብኡ ኀበ ኖላዊሃ ወዓቃቢሃ ለነፍስክሙ፤ አሁንም ወደ እረኛችሁና ወደ ነፍሳችሁ ጠባቂ ተመለሱ” (1 ጴጥ 2÷!5)
ሁሉን የሚችል አምላካችን እግዚአብሔር በፍቅሩና በፍቅሩ መነሻነት ብቻ ፍጥረታትን በሙሉ እንደፈጠረ ቅዱስ መጽሐፍ ያስተምረናል፤ ከፈጠረም በኋላ የክብሩ ተሳታፊ እንዲሆኑ ወዶ ክብሩን አድሎአቸዋል፡፡ እግዚአብሔር ለፍጡራኑ ካደላቸው ነገሮች አንዱ በየዓይነታቸው ጠባቂና መሪ እያደረገ በፍጡራን ላይ ፍጡራንን መሾሙ ነው፤ ይህ ስጦታ በሰማይም ሆነ በምድር ላሉ ፍጥረታት የተሰጠ የሱታፌ መለኮት ስጦታ ነው፡፡
ይህም በመሆኑ ሁሉም ፍጡራን አራዊትም ሆኑ እንስሳት ይብዛም ይነስ ጠባቂና መሪ እንዳላቸው እናስተውላለን፤ በተለይም የፍጥረታት ቁንጮ የሆኑ መላእክትና ሰዎች መሪና ሹም እንዳሏቸው የማንክደው ሓቅ ነው፡፡ ቅዱስ መጽሓፍም ይህንን ደጋግሞ ያስረዳል፤ የእነዚህ ሁሉ ላዕላዊ ጠባቂና መሪ ደግሞ እግዚአብሔር ነው፤ እግዚአብሔር በፍጡራን ላይ ፍጡራንን ጠባቂዎች አድርጎ ሲሾም ፍጡራንን የክብሩ ተሳታፊ ለማድረግ እንጂ የእሱ ጥበቃ አንሶ ወይም ድጋፍ ሽቶ አይደለም፡፡ ስለሆነም ፍጹምና ላዕላዊ የሆነ ጥበቃው ሁሉንም ያካለለ ነውና ከእሱ ቊጥጥርና ጥበቃ ውጭ አንድም ነገር እንደሌለ የምንስተው አይደለም ፡፡
•ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት
•የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት!
በአምሳለ እግዚአብሔር በተፈጠረውና በክብር መልዕልተ ፍጡራን በሆነው ሰው ላይ በዚህ ዓለም የተሾሙ ሁለት አካላት አሉ፤ እነሱም የመንፈስና የዓለም መሪዎች ናቸው፡፡ በተለይም የመንፈስ መሪዎችና ጠባቂዎች የተባሉት በመንፈስ ቅዱስ ተሹመን በዚህ ክርስቶሳዊ ጉባኤ የተሰበሰብነው እኛ የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ነን፡፡
ይህ ጉባኤ በሀገር ውስጥና በውጭ ለሚገኙና በሚሊዮኖች ለሚቆጠሩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምእመናን መሪና ጠባቂ ነው፤ ከዚያም ባሻገር እንደ ቃሉ እስከ ዓለም ዳርቻ ድረስ ቃሉን በመስበክ ፍጥረተ ሰብእን በሙሉ የመጥራት ተልእኮ ለእኛ የተሰጠ የቤት ስራ ነው፡፡ ከዚህ አኳያ የተሰጠን ኃላፊነት እጅግ በጣም ታላቅ እንደመሆኑ የሚጠበቅብን ውጤትም በዚያው ልክ ትልቅ ነው፤ ብዙ ከተሰጠው ብዙ ይፈለግበታል ያለው የጌታችን አስተምህሮም ይህንን ያስታውሰናል፡፡
ሁላችን እንደምንገነዘበው አሁን የምንገኝበት ዘመን የጸላኤ ሠናያት መንፈስ በእግዚአብሔር ሕዝብ ላይ ከምንም ጊዜ በበለጠ ጦሩን ሰብቆ የተነሣበት ጊዜ ነው፤ አሁን ያለው ዓለም በሀገራችንም ሆነ በሌላው ክፍለ ዓለም ላሉ ኦርቶዶክሳውያን ከባድ ፈተና ደቅኖብናል፡፡ ክፉው መንፈስ የሰውን አእምሮ በማዛባት ምእመናንን በቅዱስ መጽሐፍና በሕገ ተፈጥሮ ከተመደበላቸው የጋብቻ ሕግ በማስወጣት እንስሳት እንኳ የማይፈጽሙት ነውረ ኃጢአት እንዲፈጽሙ በመገፋፋት ላይ ይገኛል፡፡ በአማንያን ልጆቻችን ላይም በረቀቀ ስልት ግድያ፣ እገታ፣ አፈና፣ የመብት ተጽዕኖ እና አድልዎ በማድረግ እንደዚሁም በአስመሳይ ስብከትና አምልኮ ጣዖትን በማለማመድ ሕዝቡ ሳይገባውና ሳይጠነቀቅ ከእግዚአብሔር መንግሥት እንዲወጣ እያደረገ ነው፡፡
•ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት
•የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት!
ክፉው መንፈስ በተራቀቀና በተራዘመ ስልት ሊውጠን በተነሣ ልክ እኛም ከእሱ እጥፍ በሆነ መለኮታዊ ኃይል ልንመክተው ካልቻልን በፈጣሪም ሆነ በትውልድ እንደዚሁም በታሪክ ፊት በኃላፊነት መጠየቃችን አይቀርም፡፡ መከላከል የምንችለውም ችግሩን በውል ከመረዳት አንሥቶ ሕዝቡን በደምብ በማስተማርና በመጠበቅ እንደዚሁም ለመሪነታችን ዕንቅፋት ከሚሆኑን ዓለማዊ ነገሮች ራሳችንን በማራቅ ነው፡፡ ሕዝቡም በዚህ ዙሪያ ሊያደምጠንና ሊከተለን የሚችለው መስለን ሳይሆን ሆነን ስንገኝለት ነው፡፡ ሕዝቡ ሊከተለን የሚችለው እሱን በብቃት ለመጠበቅ ዓቅሙም ተነሣሽነቱም ቁርጠኝነቱም እንዳለን ሲመለከት፣ እንደዚሁም ከዕለት ተዕለት ተግባራችንና አኗኗራችን የሚያየው ተጨባጭ እውነታ ኅሊናውን ሲረታ እንደሆነ አንርሳ፡፡
የምናስተምረው ሌላ የምንሰራው ሌላ ከሆነ ግን ከሕዝቡ አእምሮ መውጣታችን እንደማይቀር መገንዘብ አለብን፤ በመሆኑም በሰብእናችን፣ በአስተዳደራችን፣ በአመራራችንና በጥበቃችን ሁሉ እንደቃሉና እንደቃሉ ብቻ ለመፈጸም መትጋትና በቁርጥ መነሣት ጊዜው አሁን ነው እንላለን፡፡ ይህ ሲሆን በምእመናንና በእኛ መካከል ያለው ግንኙነት አስተማማኝና እንከን የለሽ ይሆናል፤ ይህ ከሆነ እውነትም የመሪነት፣ የእረኝነትና የመልካም ተምሳሌነት ኃላፊነታችንን በትክክል ተወጥተናል ማለት እንችላለን፡፡
•ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት
•የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት!
የሰው ልጆች በዚህ ዓለም ሲኖሩ የተሟላ ሰላምና ጣዕመ ሕይወት ሊኖራቸው የሚችለው በመንፈሳዊ ኑሮአቸው የተሻለ ነገር ስላገኙ ብቻ አይደለም፡፡ ሰዎች ከሥጋዊ ክዋኔም ጭምር የተፈጠሩ እንጂ እንደመላእክት ሥጋ የሌላቸው መንፈስ ስላይደሉ ለኑሮአቸውና ለሥጋዊ ክዋኔአቸው የሚሆን ነገር ያስፈልጋቸዋል፡፡ በዚህም ዓለማዊው አስተዳደር የተመቻቸ መደላድል ሊፈጥርላቸው ግድ ነው፤ ዓለማዊው አስተዳደርም የመለኮትን ተልእኮ ለመፈጸም የተሾመ ሹመኛ እንደመሆኑ የእግዚአብሔርን ሕዝብ በትክልል መምራት ይጠበቅበታል፡፡ ምንም ቢሆን የተቀበለው ኃላፊነት የእግዚአብሔር ነውና በሚሰራው ሁሉ በሿሚው አምላክ ከመጠየቅ አያመልጥም፡፡
እኛም በዚህ ዓለም የእግዚአብሔር ወኪሎች ስለሆንን ቢሰሙንም ባይሰሙንም ዓለማውያን ሹማምንትን የማስተማርና የመምከር ኃላፊነት አለብን፡፡ ይህ የሁለታችን ኃላፊነት እንደ እግዚብሔር ፈቃድ ስንፈጽም የሕዝብ ሰላምና በረከት፣ ፍቅና አንድነት፣ ዕድገትና ልማት በአስተማማኝ ሁኔታ ይረጋገጣል፡፡ ነገር ግን በአሁኑ ጊዜ በሀገራችንም ሆነ በአካባቢያችን እየሆነ ያለው ይህ አይደለም፤ አለመግባባት በዝቶአል፣ ማኵረፍና መቀያየም ሰፍቶአል፤ ነገሩ ሁሉ ግራ የሚያጋባና የተመሰቃቀለ ሆኖ ይታያል፡፡ ችግሩ ከሕዝብ አልፎ የአምልኮ ስፍራዎችንና የአምልኮው ፈጻሚዎችን ዒላማ ያደረገ እግዚአብሔርን መዳፈር እየተለመደ መጥቶአል፤ ይህ ለአንድ ሀገር ወይም ሕዝብ የውድቀት ምክንያት ከሚሆን በቀር ከቶውኑም የዕድገት ምልክት ሊሆን አይችልም፡፡

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

22 Oct, 13:49


ከሁሉም በላይ የሚያሳዝነው ደግሞ ይህ ክፉ ድርጊት እየተፈጸመ ያለው በእኛው ልጆች በኢትዮጵያውያን መሆኑ ነው፤ ስለሆነም በከተማም፣ በጫካም፣ በገጠርም በየትኛውም ስፍራ የምትገኙ ልጆቻችን ምንም ይሁን ምን ሀገርንና ሕዝብን ከመጉዳት ተቆጠቡ፡፡ በተለይም ከቤተ ክርስቲያንና ከሀገር እንደዚሁም ሕዝቡን ከሚያገለግሉ ካህናትና ሲቪል ሰራተኞች እባካችሁ እጃችሁን አንሡ፤ ቤተ ክርስቲያን እኮ የእናንተና የሕዝቡ ሁሉ እናት ናት፤ በእናታችሁ ላይ መጨከንን እንዴት ተለማመዳችሁት? አሁንም ንስሐ ግቡ ያለፈው ይበቃል፡፡ ልብ በሉ ከእግዚአብሔር ጋር መጣላት አይበጅም፤ ሰውን መጉዳትና እግዚአብሔርን መዳፈር አቁሙ፤ የእግዚአብሔር ገንዘብ የሆነውን ሥርዓተ አምልኮም ያለቦታው አታውሉ፤ ጥያቄአችሁን በሰላማዊ መንገድ
ለመፍታት ዕድል ስጡ፡፡ በእግዚአብሔር ስም ለመላው ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችንና ልጆቻችን የምናስተላፈው ወቅታዊ መልእክታችን ይህ ነው፡፡
በመጨረሻም
በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ሁለንተናዊ አገልግሎትና የስራ አፈጻጸም ላይ ለመምከርና ለመወሰን ኃላፊነት ያለው ቅዱስ ሲኖዶስ በዛሬው ዕለት መደበኛና ዓመታዊ ጉባኤውን የጀመረ መሆኑን ለሕዝበ ክርስቲያኑ እናበስራለን፡፡
እግዚአብሔር ጉባኤያችንን ይባርክ!
እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን::
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም
ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
ጥቅምት ፲፪ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም.
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ፤
++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++ የቱንቢን ትክክለኛ የቴሌግራም ገጽ ይቀላቀሉ! ያስተዋውቁ!
https://t.me/tunbi_media
🎥💻📺🎙 YouTube በዩቲዩብ ዝግጅቶቻችንን 👁👁👂🏽👂🏽ይታደሙ!
www.youtube.com/@TunbiMedia_
በራምብል
rumble.com/c/c-3688912
በቲክቶክ
tiktok.com/@ethiotunbi

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

22 Oct, 13:32


ያሳዝናል!

ደም የተጠማው አየር ኃይል ዛሬ ጥቅምት ፲፪ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም. በእናርጅና እናውጋ ወረዳ ፈለገ ብርሃን ከተማ ንዋየ ማርያም ፩ኛ ደረጃ ት/ቤት አጠገብ ወደ ማክሰኞ ገበያ በማቅናት ላይ በነበሩ ንጹሐን ላይ የድሮን ጥቃት ፈጽሟል።

እንዲሁም በመከረኛው ደብረ ኤልያስም የቀጋት ት/ቤት ላይ ተመሳሳይ የድሮን ጥቃት አድርሷል።

የጉዳቱ ዝርዝር መረጃ እየተጣራ ነው። ባሕሩን የማድረቅ ሥራውን "ጊንጥን" መቆርጠም በሚለው መርሕ እያስፋፋው ቀጥሏል።

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

21 Oct, 20:36


መርካቶ ገበያ ላለፉት 5 ሰዓታት በላይ እየነደደ ነው!!! "መንግሥት" ተብሎ በሚጠራው የሴራና የግፈኞች ስብስብ በኩል "ከአቅም በላይ ሆኖ ነው" "ቦታው አስቸጋሪ_ስለሆነ ነው" ወዘተ. የሚል መልስ እየተሰጠ ነው። የሆነው ሆኖ ኢትዮጵያ ውስጥ እንዲህ ያለ ውድመት የማያደርስ መንግሥት አለን ተብሎ ስለማይታመን! ነጋዴዎች ዘግተው ከውጡ በኋላ የተነሳ እሳት፣ 5 ሰዓታት ሙሉ ፣ አሁንም እየነደደ ያለ እሳት ብዙ ጥያቄ የሚፈጥር ነው!

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

21 Oct, 19:18


https://www.youtube.com/live/2ApOvhi6RY4?si=xn4Rh9d9tBnZr0F3

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

21 Oct, 17:55


https://www.youtube.com/live/Ygpq65GOTxU?si=Plx_bMlJzA6C-rcX

ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)

19 Oct, 19:41


https://www.youtube.com/live/IXceUvnegiU?si=-ZuQZ4WSWzcjock-