የፍቅር ታሪኮች ❤ @ye_fkr_tarikoche Channel on Telegram

የፍቅር ታሪኮች

@ye_fkr_tarikoche


የፍቅር ታሪኮች (Amharic)

እንኳን ወደ የፍቅር ታሪኮች ቻናል በደህና መጡ። የፍቅር ታሪኮች የገና መብትና የፍቅር ተሪፊም ከመሰለ ጀምሮ እንድማይሆን እናመሰግናለን። የፍቅር ታሪኮች በትምህርት ቤቶች እንደሚያበረርና ወደ ቅናት ሊኖረው እንደሚችል የሚታይበት ሁኔታ ነው። የሚፈልጉት የቻናል ቁጥር የፍቅርና ሰምተኛ ተንኮለኛ የፍቅር ውካታ ለሆነው ይመለከታል።

የፍቅር ታሪኮች

11 Feb, 16:29


Channel name was changed to «የፍቅር ታሪኮች »

የፍቅር ታሪኮች🌒

08 Feb, 09:55


Farhan ozil ✍️:
#የማይፋቅ #ስህተት
#ክፍል #አስር
(ፉአድ ሙና)
.
አዳሪ ትምህርት ቤቱ ከገባሁ አስር ቀናት አለፉ። አስር ቀን ሙሉ አንድ ግቢ ዉስጥ ከመምህሮቹ እና ከተማሪዎቹ ጋር እየተዛዛግኩ አሳለፍኩት። አምሪ እና እነሚኪ የሌለ ናፍቀዉኛል። ከግቢ የምንወጣዉ ከትምህርት ቤቱ አቅራቢያ ያለዉ መስጂድ ለመስገድ ብቻ ነዉ። እሱንም ቀን ላይ ብቻ! ስግደት ይከብደኝ የነበርኩት ልጅ ከግቢ የመዉጫ ሰበቤ እሱ ብቻ ሲሆን ይናፍቀኝ ጀምሯል። ከተማሪዎቹ በእድሜ ለኔ ከሚቀርበዉ ነስሩ ከሚባለዉ ልጅ ጋር በጣም ተመቻችተናል። ኡስታዞቹ ያስተማሩኝን ነስሩ መኝታ ክፍል ለብቻችን ሆነን በደንብ ያስረዳኛል። ኡስታዝ ማለት መምህር ማለት ነዉ። ኡስታዞቹ ከሚያስረዱኝ በበለጠ የሱ ይገባኛል። ነስሩ የደሴ ልጅ ነዉ። በትምህርት ቤቱ ዉስጥ ከአመት በላይ ቆይቷል። ባለፉት ቀናት በልጅነቴ አዉቃቸዉ የነበሩ ብዙ ነገሮችን አስታዉሻለሁ። ቁርአንን እያየሁ ማንበብ እየቻልኩ ነዉ። ነስሩ ሁሌም ሲያስረዳኝ "አንተ ስለምትፈራ ነዉ እንጂ ገርቶልሀል!" ይለኛል። በርግጥ በልጅነቴ በደንብ ቁርዓንን ማንበብ እችል ነበር። የገባሁ ቀን ፈጣሪ ፍትሀዊ አይደለም ብዬዉ ቢሮ እፈልግሀለሁ ብሎኝ የነበረዉ መምህር ያባረኛል ስል እንደዉም ከትምህርት ሰዓት ዉጪ ሁሉ ለብቻዬ እየጠራ ያስተምረኝ ጀምሯል። ለመባረር ከሞከርኩ የትምህርት ሰዓቴ እየጨመረ እንደሚመጣ ስለገባኝ መረበሽ አቁሜያለሁ።
ባለፉት ቀናት ከግቢ ለመዉጣት ብፈልግም ከስግደት ሰዓት ዉጪ መዉጣት አልቻልኩም። አስተማሪዎቹ ደግሞ በአይነቁራኛ ይከታተሉኛል። ከሁሉም ነገር የከበደኝ ለሊት ዘጠኝ ሰዓት ከእንቅልፍ ተነስቶ መማር ነዉ። አስር ቀን ሙሉ እየተበሳጨሁ ተነስቻለሁ።
እድሜ ለአምሪያ ይሁንና ከፌቨን ጋር ማታ ማታ ፌስቡክ ላይ እናወራለን። ፌቪ ናፍቆቴ ሊያሳብዳት ምንም አልቀራትም። እኔ ደግሞ የአምሪያ ናፍቆት ሊገለኝ ነዉ።  እዚህ ግቢ ከገባሁ አንዴ እሁድ ልትማር ስትመጣ ነዉ የተገናኘነዉ!
.
ዛሬ ከፌቪ ጋር ማታ ፌስቡክ ላይ ለማዉራት ተቀጣጥረናል። ትንሽ ካመሸሁ ለሊት መነሳት ሊከብደኝ እንደሚችል ገብቶኛል። ስለዚህ ቆንጆ መላ ዘየድኩ። ማታ ሁሉም በተኛበት መብራቱን ከቆጣሪዉ ማጥፋት! መችስ በጨለማ ቀስቅሰዉ አያስተምሩንም።
ማታ ሶስት ሰዓት ላይ ትምህርታችንን ስንጨርስ እራት በልተን ወደ መኝታችን ተበተንን።  ከላይኛዉ አልጋ ላይ ነስሩ፤ እኔ ደግሞ ከታች ነዉ የምንተኛዉ! ሁሉም ከተኙ በኋላ የስልኬን ብርሀን በብርድልብሱ ሸፍኜ ከፌቪ ጋር መፃፃፍ ጀመርኩ። ፌቪ በመጥፋቴ ተከፍታለች። ነገ አስር ተኩል ላይ ኦፊስ እንዳገኛት ጠየቀችኝ። እኔ ግን ከፌቪ ለመራቅ ከዚህ የተሻለ ጊዜ ስለማላገኝ መዉጣት እንደማልችል ነገርኳት። ፌቪ በቅታኛለች። ሀሳቤ ሁሉ አምሪያ ጋር ነዉ። አዉርተን ስንጨርስ ከለሊቱ ስድስት ሰዓት ሆነ። ተነስቼ መብራቱን ከቆጣሪዉ መለስኩትና ተኛሁ። አስራአንድ ሰዓት ሲል ኡስታዞቹ እየዞሩ ከመኝታችን ቀሰቀሱን። ነስሩ ለሊት ዘጠኝ ሰዓት ተነስተዉ መብራት ስለሌለ ተኙ እንደተባሉ ነገረኝ። አሁንም ከቆጣሪዉ እንደሆነ አላወቁትም። ከእንቅልፋችን የቀሰቀሱን የስግደት ሰዓት ስለደረሰ ነዉ። ሰግደን እንደጨረስን አንዱ ኡስታዝ ቆጣሪዉን አይቶ እንዲመጣ ነስሩን ላከዉ። ነስሩ አብርቶት መጣ። ቆጣሪዉ መልሶ ነዉ ተባለና ታለፈ። እቺ ሙድ በጣም ተመችታኛለች። ለአምሪ የሰራሁትን ገድል ነገርኳት።
.
አምሪያ አዲስአበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርቷን እየተከታተለች ነዉ። ሰሞኑን ተኝቼ ሳይቀር የማስበዉ እሷን ነዉ። እዚህ ሆኜ ሀጂ ቢድሯትስ ብዬ እፈራለሁ። ቢያንስ ስሜቴን ልነግራት ይገባል ብዬ ዉስጤን አሳምነዋለሁ። ደሞ እሷን መከጀሌ ቢያስከፋት ላጣት እንደምችል አስብና እተወዋለሁ። ቀኑ መቁጠሩን ቀጥሎ ሶስት ወራትን በእስልምና ትምህርት ቤቱ ዉስጥ አሳለፍኩ። አሁን ቁርዓንን በአግባቡ ከማንበብም አልፌ በቃል መሸምደድ ጀምሬያለሁ። ብዙ አይነት የትምህርት ዘርፎችን እንማራለን። አረብኛ ቋንቋ፣ የእስልምና ታሪክ ፣ህግጋት(ፊቅሂ) ፣ የነብዩ ሙሀመድ ታሪክ (ሲራ) እና ሌሎችንም የትምህርት አይነቶች እንወስዳለን። በቀን ዉስጥ ከስምንት ሰዓት በላይ አናርፍም። ስምንቱም ሰዓት የእንቅልፉ ነዉ። ለኔ ደግሞ ከሌሎቹ በተለየ መልኩ ተጨማሪ ክትትል ይደረግልኛል። የሀጂ ትዕዛዝ መሆኑን መረዳት አልከበደኝም። ባለፉት ሶስት ወራት ዉስጥ ከአምሪ ጋር አራቴ ተገናኝተናል። ግን ግቢዉ ዉስጥ ስለሆነ ከሰላምታ በዘለለ ማዉራት አልቻልንም። በነገራችን ላይ ስልኬን ተደርሶብኝ ተቀምቻለሁ። አምሪ በጣም በሽቃብኛለች። ሀጂ በየቀኑ የትምህርት ቤቱን ሁኔታ ለማየት ወደ ማታ ብቅ ስለሚሉ ሳያገኙኝ አይሄዱም። ያመጣሁት የፀባይ ለዉጥ በጣም አስደስቷቸዋል። ለሊት ዘጠኝ ሰዓት መነሳቱንም ለምጄዋለሁ። ለሁለተኛ ቀን ቆጣሪ አጥፍቼ ስተኛ አንዱ ኡስታዝ ወዲያዉ መለሰዉና ከዚህ በኋላ እንዳልደግመዉ አስጠነቀቀኝ። ሳጠፋ አላየኝም። እኔ መሆኔን እንዴት እንዳወቀ ፈጣሪ ነዉ የሚያዉቀዉ።
እነሚኪያስ መዉጣት እንደማልችል ስለተረዱ ግቢዉ በር ጋር እየመጡ ትንሽ አዉርተዉኝ ይሄዳሉ። ፌቪ በጣም እንደተጎዳች ነግረዉኛል። አንዳንዴ ኦፊስ መጥታ ረዥም ሰዓት አልቅሳ ትሄዳለች አሉ። ስልኬን መቀማቴም እንዳላገኛት ረድቶኛል። በቅታኛለች ተገላገልኳት።  "አስራሁለተኛ ክፍል ሙድ አለዉ!" ይላል አብነት። ትምህርታቸዉን ቀጥለዋል። የአረብ ሀገሮቹንም ቺኮች ማለቡን ተያይዘዉታል። ሚኪ ሁሌ መጥቶ ሲያገኘኝ "በሀይማኖት ስም ዘመናዊ ሸቤ መግባት ይሉታል ያንተ ነዉ።" ይለኛል።  እኔ ግን ከአምሪያ ናፍቆት በቀር ትምህርቱም ሆነ የትምህርት ቤቱ ህይወት ተመችቶኛል። ከልጆቹም ጋር በጣም ተመቻችተናል። በሙዚቃ የተሞረደዉ ድምፄ በጣም ስለሚያምር ቁርዓን ሳነብ ከበዉ ያደምጡኛል። የሸመደድኩትን ለመለማመድ ስፈልግ የሚሰማኝ ሰዉ አልቸገርም። ተሻምተዉ ነዉ የሚያዳምጡኝ።
.
ህይወት ቀጥሎ በእስልምና ትምህርት ቤቱ ዉስጥ አምስት ወራትን አስቆጠርኩ። በቃሌ አምስቱን ረዣዥም የቁርዓን ምዕራፎች ሸመደድኩ። ይህ ማለት ከአንድ መቶ ሰላሳ ገፅ በላይ በቃሌ ሸምድጃለሁ ማለት ነዉ። ሀጂ በጣም ከመደሰታቸዉ የተነሳ የሚያምር ካባ ሸለሙኝ። ጥር አልፎ መጋቢት ሊገባ ሲል የሁለት ሳምንት እረፍት ተሰጥቶን ወደ ቤታችን እንድንሄድ ተፈቀደልን። ከነስሩ ጋር መለያየቴ ቢከፋኝም አምሪያን ሁለት ሳምንት ሙሉ ላገኛት መሆኑን ሳስብ ከደስታዬ ብዛት መላ ሰዉነቴ ነዘረኝ።
ጁምዓ(አርብ) ሊመሽ ሲል ሀጂ በመኪናቸዉ ይዘዉኝ ወደ ቤት ሄዱ። ቤት ስደርስ በጣም ድምቅ ብሏል። እንደገባሁ ማየት የፈለግኩት አምሪያን ቢሆንም ሰፈር መስጂድ ለመማር ሄዳ ስለነበር ገላዬን ለመታጠብ ወደ ሻወር ቤት ሄድኩ። ተጣጥቤ እንደጨረስኩ ጀለቢያዬን ለብሼ ሳሎን ከሀጂ ጋር ተቀመጥኩ። ጀለቢያ ቀሚስ ስለሆነ በጣም ቅልል ይላል። ትምህርት ቤት እያለሁ ሁሌም እሱኑ መልበስ ይቀናኛል።
ትንሽ እንደተቀመጥኩ አምሪ መጣች። ጥቁር አባያ በነጭ ሂጃብ ለብሳለች። አባያ ሙስሊም ሴቶች የሚያዘወትሩት ጥቁር ልብስ ነዉ። ሂጃብ ደግሞ ፀጉራቸዉን ላይ የሚጠመጥሙት ሻሽ! እንዳየችኝ ፈገግ አለች። ጥርሷ አሁንም ዙሪያዉን እንደታጠረ ነዉ። ጥርሷን ያጠረዉን ሽቦ በከንፈሯ እየሸፈነች "ሀቢብ ሀፊዙ!" አለች። ሀፊዝ የሚባለዉ ቁርዓንን ሙሉ ለሙሉ የሸመደደ ሰዉ ነዉ።  እየሳቅኩ "ኧረ ገና ነኝ።" አልኳት።

የፍቅር ታሪኮች🌒

08 Feb, 09:55


ወይዘሮ ለይላ ፈገግ ብለዉ "አብሽር ትጨርሰዋለህ ከባዱን አልፈኸዋል።" አሉ።
ሀጂ የአረቢያን መጅሊሱን መከዳ አስተካክለዉ እየተደገፉ "ሀቢቤ አሁን አምሪያዬም ስለመጣች እስኪ ከሸመደድከዉ ትንሽ አስማን" አሉኝ።
ሀጂ አዘዉ እምቢ ማለት ስለደበረኝ ከኢምራን ምዕራፍ ጥቂት አሰማኋቸዉ። አምሪያ ግርም ብሏት ፍዝዝ ብላ አዳመጠችኝ። ስጨርስ "ሀቢብ የእዉነት አንተ ነህ እንደዚህ በሚያምር ድምፅ የቀራኸዉ?" አለችኝ። መቅራት ማለት ማንበብ ነዉ።
እየተሽኮረመምኩ አንገቴን ደፋሁ። ወ/ሮ ለይላም በጣም ተገርመዉ "አጂብ ተምሮ የማይለወጥ የለም ማለት ነዉ?" አሉ።
ሀጂ እጃቸዉን ከፍ አድርገዉ ዱዓ አደረጉ። ዱዓዉ ለኔም ለአምሪያም ነበር። አሚን አልን። ልቤ ዉስጥ የፈጣሪ ፍቅር በትንሹ ጠብ ሲል ተሰማኝ።
.
ብዙ ከተጨዋወትን በኋላ መኝታ ክፍሌ ገብቼ ተኛሁ። ለምዶብኝ ለሊት ዘጠኝ ሰዓት ላይ ከእንቅልፌ ተነሳሁ። ተጣጥቤ ክፍሌ ዉስጥ ቁርዓን መሸምደድ ጀመርኩ። እስከ አስራ አንድ ሰዓት ከሸመደድኩ በኋላ የሱብሂ ስግደት ስለደረሰ ሀጂን ልቀሰቅሳቸዉ ወደ ክፍላቸዉ ሄድኩ። ከዉጪ ሆኜ አንኳኳሁ። ሀጂ ተነስተዉ ከመኝታ ክፍል ወጥተዉ ሲያዩኝ እኔዉ ነኝ። ገርሟቸዉ "በስንት ጭቅጭቅ ትነሳ የነበርከዉ ልጅ እኔን ለመቀስቀስ በቃህ? እኔ እኮ አምሪያዬ መስላኝ ነበር።" አሉና ፈገግ ብለዉ "ፈጣሪ ቀናትን በሰዎች መካከል ያዘዋዉራል። እናም ዛሬ አንተ ቀስቃሽ እኔ ተቀስቃሽ ሆንን!" አሉ።
ከሀጂ ጋር መስጂድ ሄደን ሰግደን ተመለስን። ስንመጣ እንደተለመደዉ እነአምሪያ ቤቱን ፏ አድርገዉታል።
አምሪ ልክ ስንገባ "ዛሬ ሀቢቤ ትጋበዛለህ!" አለችኝ። ወ/ሮ ለይላም እየሳቁ "ይገባዋል!" አሉ።
እኔ ከአምሪ ጋር ብቻችንን ሆነን የምናወራበትን ሰዓት እየናፈቅኩ ነዉ። የፈለገዉ ይምጣ እንደምወዳት እነግራታለሁ። ቢያንስ ምናልባት የምትወደኝ ከሆነ ሌላ ወንድ እንዳታገባ ያደርጋታል። ቆይ ግን ያልታጨች ልጅ ብታገባስ ብዬ የምጨነቀዉ ምን ያህል ብሳሳላት ነዉ? እኔንጃ!
.
ጠዋቱን ሀጂ ወደ ስራ ሄዱ። ወ/ሮ ለይላም አብረዋቸዉ ሄደዋል። ወደ ማታ መጥተዉ እኔና አምሪን ሊጋብዙን ቃል ገብተዋል። አምሪ ፈተና ጨርሳ ዕረፍት ላይ ነበረች። ግቢዉ ዉስጥ ትንሽዬ የፕላስቲክ ወንበር ላይ ተቀምጬ ፀሀይ እየሞቅኩ እያለ አምሪ ወንበር ይዛ መጥታ ከኔ ትንሽ ራቅ ብላ ተቀመጠች።
"ሀቢቤ የናንተን ቤት የተከራዩት ሰዎች አዲስ ሙሽራዎች እንደሆኑ ታዉቃለህ?" አለችኝ።  አንገቴን በአዎንታ ነቀነቅኩት። ባልየዉን የገቡ ሰሞን አይቼዉ አዉቃለሁ። አዲስ ሙሽራ መሆናቸዉን እንኳ ወ/ሮ ለይላ ሲያወሩ ነዉ የሰማሁት።
ስለቤታችን ሲነሳ እማዬ ትዝ ትለኛለች። እንጀራ ተሸክሜላት ወደ ላስቲኩ ምግብ ቤቷ ሳደርስላት ትዝ ይለኝና እንባ አይኔን ይሞላዋል።
አምሪ ስፈዝባት "ሀቢቤ ምነዉ ተከዝክ?" አለችኝ። የመጣዉ ይምጣ ብዬ ላፈርጠዉ ወሰንኩ።
አንገቴን አቀርቅሬ ምራቄን እየዋጥኩ "አምሪ" አልኳት።
ለሆሳስ በሚመስል ድምፅ "ወዬ" አለችኝ።
ልቤን እያደፋፈርኩ "አንድ ነገር ልነግርሽ ነበር ብትወጂዉም ብትጠይዉም ላታኮርፊኝ ቃል ትገቢልኛለሽ?" አልኳት።
"ንገረኝ አብሽር አላኮርፍህም!" አለችኝ።
"እወድሻለሁ!" አልኳት ድምፄ እየተንቀጠቀጠ። መልሷን ለመስማት አንገቴን ቀና አድርጌ አየኋት። በልቤ እንዳትከፋብኝ ፈጣሪዬን ለመንኩት። ለሚወዱት ሰዉ ፍቅርን እንደመግለፅ የሚከብድ ምን አለ? በተለይ ፆታዊ ፍቅር ሲሆን!

ይቀጥላል...

Join👇👇👇
https://t.me/ye_fkr_tarikoche

የፍቅር ታሪኮች🌒

03 Feb, 08:25


ፀጉሬን እየጠቀለልኩ "ኧረ አምሪ ስራዬ ነዉ አትጨነቂ! ብቻ ስልኩ ይግባ!" አልኳት።
"ደሞ ለካርዱ አታስብ እኔ እልክልሀለሁ። የምመጣ ቀን ደግሞ አስቀድሜ እነግርሀለሁ።" አለችኝ። ይህን ሁሉ ለምን ታደርግልኛለች? እሷም እንደኔ እናፍቃት ይይሆን እንዴ? አላዉቅም። ፍዝዝ ስልባት "ሀቢብ ይህን ሁሉ የማደርገዉ አንተ በጣም ጨለማ ዉስጥ ያለህ ሰዉ ስለሆንክ በአንዴ ወደ ብርሀኑ ሲወረዉሩህ ጨረሩ በዝቶ እንዳይጎዳህ ብዬ ነዉ። ህይወትህን እንደልብህ ስትሆን እንዳሳለፍክ አዉቃለሁ። አሁን መታፈኑ እንዳይከብድህ ትንሽ ማስተንፈሻ እያመቻቸሁልህ ነዉ።" አለችኝ።
"ልክ ነሽ!" አልኳት ብስለቷ ግርም እያለኝ። ቆይ ግን ስለኔ ህይወት እንዴት እንደዚህ በድፍረት ልትናገር ቻለች? ዋናዉ ግን ያቀረበችዉ ሀሳብ መልካም መሆኑ ነዉ።                                  .
በነጋታዉ ጠዋት ላይ በሀጂ መኪና ወደ ትምህርት ቤቱ ሄድን። ከአምሪያ እንደተነጠልኩ ሳስብ በጣም ሆድ ባሰኝ። ሀጂን ገፍቼ የራሴን መንገድ ለመከተል አሰብኩ። ደሞ የእናቴ አደራ ትዝ ሲለኝ እንደምንም ለመጋፈጥ ወሰንኩ። ግቢዉ ዉስጥ ገብተን ከመኪናዉ እንደወረድኩ አንድ ሰዉዬ መጥቶ ከሀጂ ጋር ትንሽ አወራና ሀጂን ተሰናብቶ "ኡስታዝ ሰዒድ እባላለሁ ተከተለኝ።" ብሎኝ ከፊት ከፊቴ መራመድ ጀመረ። ሀጂን ተሰናብቼ ሰዉየዉን ተከተልኩት። አምሪያ እንዳለችዉ ግን ፍተሻ አልተደረገብኝም። ስገምት ሀጂ ስላስገቡኝ ነዉ። ስልኬን አምሪ ወደ ማታ ልታቀብለኝ ተቀጣጥረናል።
ኡስታዙ ወደ ቢሮዉ አስገብቶኝ አንዳንድ ጥያቄዎችን ከጠየቀኝ በኋላ የትምህርት ቤቱን ህጎች መናገር ጀመረ። "እዚህ እስካለህ ድረስ የመኝታ እና የትምህርት ሰዓቶችን ማክበር አለብህ።" አለኝ እና ከተማሪዎች ጋር ሊኖረኝ ስለሚገባዉ ግንኙነት አብራራልኝ።
አዉርተን ስንጨርስ የምተኛበትን ክፍል አሳየኝ። ተደራራቢ አልጋዎች ያሉበት ሰፊ ክፍል ነዉ። ሻንጣዬን አልጋዬ ላይ ካስቀመጥኩ በኋላ የአንድ ክፍል በር እያሳየኝ "አሁን አንድ ልጅ ቁርዓን ሸምድዶ ስለጨረሰ የእንኳን ደስ አለህ ዝግጅት ተዘጋጅቶ ሁሉም እዛ ናቸዉ። ሂድ ግባ!" አለኝ። ወደ ክፍሉ ልገባ በሩን በትንሹ ከፍቼ ሳይ ትንሽዬ መድረክ ላይ አንድ ነጭ ጀለቢያ የለበሰ  ሰዉ ቆሞ ያወራል። ተማሪዎቹ ሁሉም ነጭ ጀለቢያ ለብሰዉ እግራቸዉን አጠላልፈዉ በሰልፍ ተቀምጠዋል። ጀለቢያ የሚባለዉ ወንድ ሙስሊሞች የሚለብሱት ቀሚስ ነዉ። ተማሪዎቹ  እንዳለ ልጆች መሆናቸዉን ሳይ በጣም ተበሳጨሁ። አሁን ከነዚህ ጋር ማነዉ ሚዛዛገዉ? ከከሪሜ የሚበልጥ አንድ ልጅ ብቻ ነዉ ያለዉ። በጣም ተበሳጨሁ። እቅዴ ከቻልኩ ዛሬ ለመባረር ነዉ። በሩን ከፍቼ ስገባ መድረኩ ላይ ያለዉ ሰዉዬ "አላህ ማንንም አይበድልም። በጣም ፍትሀዊ ነዉ። ሁላችንም የተሰጠንን ፀጋ ብንቆጥረዉ የጎደለን የለም!" አለ። ድምፄን ከፍ አድርጌ "አትዋሽ ፍትሀዊ አይደለም! ከፊሉን እያሰቃየ አንተን ስላስደሰተህ ፍትሀዊ ነዉ አትበል!" አልኩ። ተማሪዎቹ ዞር ብለዉ አዩኝና አጎንብሰዉ ሳቁ። ኡስታዙ አየኝና "ስምህ ማነዉ?" አለኝ። በንቀት እያየሁት "ሀቢብ" አልኩት። "አዲስ ተማሪ ነህ መሰለኝ። በኋላ ቢሮ እፈልግሀለሁ።" አለኝ። 
ሊያባረኝ ሊሆን ይችላል ብዬ በጣም ደስ አለኝ።
.
ማታዉን አምሪ መጥታ አስጠራችኝ። ኡስታዙ የሀጂ ልጅ ስለሆነች እንደልቧ እንድትገባ ይፈቅድላታል። በእጇ ፌስታል ይዛለች። "ጀለቢያ አቢ ገዝቶልሀል። አድርሺለት ብሎኝ ነዉ።" አለችና ፌስታሉን ሰጥታኝ ሄደች። ኡስታዙ አጠገባችን ቆሞ ስለነበር ምንም ማዉራት አልቻልንም። እንደሄደች ጀለቢያዎቹን እያወጣሁ ስመለከታቸዉ የአንዱ ኪስ ዉስጥ ስልኬን አገኘሁት። የአምሪ ጥበብ ገረመኝ።  ከልጆቹ ተደብቄ ለአምሪ እንዳገኘሁት የሚገልፅ መልዕክት በሚሴጅ ላኩላት።
.
ለሊት ዘጠኝ ሰዓት ሲል አንዱ ኡስታዝ መጥቶ ቀሰቀሰኝ። በጣም ተበሳጭቼ "ምን ፈለግክ?" ስለዉ ዉሀ እየረጨ ከተኛሁበት አስነሳኝ። አሀ ለካ የመኝታ ህግ የተባለዉ ይሄ ነዉ? ለሊት ዘጠኝ ሰዓት ተነስቶ መማር? ሰዉ አይደሉም እንዴ? በጣም ቀፈፉኝ።
.
ይቀጥላል...

Join👇👇👇
https://t.me/ye_fkr_tarikoche

የፍቅር ታሪኮች🌒

03 Feb, 08:25


#የማይፋቅ #ስህተት
#ክፍል #ዘጠኝ
(ፉአድ ሙና)
.
ከአምሪ ጋር ምንጣፉን አጥበን እንደጨረስን ፀሀይ እንዲያገኘዉ ከግቢ ዉጪ አሰጣነዉ። አምሪ ግቢዉን ጠርጋ ስትጨርስ "ያዉ ዝናብ ከዘነበ ምንጣፉን ብቻዬን ማስገባት ስለማልችል ዛሬ የትም መሄድ አትችልም!" አለችኝ። ማዕቀብ ቢመስልም ደስ በሚል ሰዉ የተጣለ ደስ የሚል ማዕቀብ ስለሆነ ወድጄዋለሁ። አምሪ የግቢዉን በር ዘጋችና በረንዳዉ ላይ ከአጠገቤ እየተቀመጠች "ሀቢቤ ታዉቃለህ አንዳንዴ በህይወትህ ዉስጥ አንዴ ተሳስተህ የምትሰራዉ ስራ ህይወትህን ምስቅልቅል ሊያደርገዉ ይችላል።" አለችኝ።
አንገቴን አቀርቅሬ "ምን ተሳስተሽ ነዉ?" አልኳት። መልስ ሳትሰጠኝ "ከሱ የሚከፋዉ ደግሞ ያንተ መልካም ያልሆነ ምግባር ለሌላዉ ህይወት መበላሸት ምክንያት ሲሆን ነዉ!" አለችኝ። ልትነግረኝ የፈለገችዉን ነገር ከመተንፈስ በዘለለ ለማብራራት እንዳልፈለገች ስለተረዳሁ ላስጨንቃት አልፈለግኩም። ዝም ብዬ "ልክ ነሽ!" አልኳት። ሳቀች። ምን አሳቃት? እኔንጃ አልጠየቅኳትም።
ከአምሪ ጋር እየተጨዋወትን ሚኪያስ ደወለ። እየሳቀ "ሀቢብ ራህመቶ!" አለኝ። ሰሞኑን ሙድ መያዣ አድርገዉኛል። ዛሬ ከሄለን ጋር ኦፊስ ስለሚያሳልፉ ወደ ኦፊስ ድርሽ እንዳልል ሊያስጠነቅቀኝ ነዉ የደወለዉ። እኔ እንኳ ሲጀመርም ቆንጆ እስር ላይ ነኝ።
አምሪ በወሬያችን መሀል "ሀቢቤ ግን እኔና አንተ አብረን እንዲህ ረዥም ሰዓት ስንቀመጥ ቢያዩ ኡሚም አቢም እንደሚቆጡ ታዉቃለህ?" አለችኝ። ዛሬ ወ/ሮ ለይላ ከሀጂ ራህመቶ ጋር በጠዋቱ ወጥተዋል። 
ግርም እያለኝ "ለምን?" አልኳት። "ሀይማኖታችን አይፈቅደዉም!" አለችኝ።
"ይገርማል ታዲያ ለምን አብረሽኝ ተቀመጥሽ?" አልኳት።
"እኔ እንኳን..." አለችና በረዥሙ እየተነፈሰች "ይለፈኝ!" አለችኝ። እኔ ሰዉ ማስጨነቅ ብዙም አይመቸኝም። አለፍኳት።
ደስ የሚለዉ ምንም ክረምት ቢሆንም ዛሬ ጠዋት ምንጣፉን ከማጠባችን በፊት የዘነበ ቀኑን ሙሉ አልዘነበም። ከአምሪ ጋር ባዶ ቤት ብቻችንን መሆናችንን ሳስብ ስለሷ የሚሰማኝን ስሜት ልነግራት አሰብኩ። ደሞ ነግሬያት ቢደብራት ወዳጅነታችንም ሊቀር ይችላል ብዬ ስለፈራሁ ተዉኩት።
.
እነአምሪያ ቤት እየኖርኩ ትንሽ እንደቆየሁ የኛ ቤት የቤት እቃዎች በሙሉ ተሸጡ። ትናንሽ የቤት ዉስጥ መገልገያዎችን ሰፈራችን ላለች አንድ ሴትዮ  ሰጠናቸዉ። ቤቱም ተከራየ። አዲስ ባለትዳሮች ናቸዉ ቤታችንን የተከራዩት። የአስራሁለተኛ ክፍል መልቀቂያ ዉጤት ወጣ። አምሪ አምስት መቶ ዘጠና ሁለት አመጣች። ወንድሞቿ በሽልማት አንበሸበሿት። እኔም ከአረብ ሀገሯ ታላቢዬ ከተሚማ ባጨድኩት ብር የእንግሊዘኛዉ ኤ መሀሉ ላይ የተንጠለጠለበት የብር የአንገት ሀብል ስጦታ ሰጠኋት። አምሪ ስጦታዬን በጣም ወዳዋለች።
.
ክረምቱ እያለቀ ሲሄድ ከአምሪያ ጋር ያለን ቅርርብ በጣም እየጠበቀ ሄደ። ፈጣሪ ይባርካት በህይወቴ በልቼ የማላዉቀዉን በርገር የሚባል ምግብ ሱስ አስያዘችኝ። ብር እኔም ሀጂ ስለሚሰጡኝ እሷም ከወንድሞቿ እና ከሀጂ ስለሚሰጣት አንዳንዴ ካልሆነ አጥተን አናዉቅም። ወጣ ብላ ስትመለስ ለኔ ገዝታ ይዛልኝ ትመጣለች።
እኔ አስራአንደኛ ክፍልን እንደምንም ባልፍም ላለመማር ወስኛለሁ። ሀጂ ሀይማኖታዊ ትምህርት በግድ ሊያስተምሩኝ ወስነዋል። እኔም የእማዬ አደራ ሆኖብኝ ሳልወድ በግዴ እሺ ብያቸዋለሁ። እነሚኪያስ ትምህርት እንደማልቀጥል ስነግራቸዉ በጣም ተበሳጩ። ሀጂ ነፃነቴን እንደገፈፉኝ ተሰማቸዉ። በርግጥ ሀጂ ሀይማኖታዊ ትምህርት እንድማር እንጂ አለማዊ ትምህርት እንዳቋርጥ አላስገደዱኝም። መማር እንደማልፈልግ ስላወቁ ነዉ ይህን የፈረዱብኝ።
ፌቪ ቢያንስ በሳምንት ሶስት ቀን ኦፊስ ዉስጥ አብራኝ ታሳልፋለች። እነሀጂ ቤት መኖር መጀመሬን አልወደደችዉም። አንዳንዴ ትምህርታችንን ትተን የሆነ ነገር እየሰራን አብረን እንኑር ትለኝ ነበር። በጣም የሚገርመኝ ቀን ከሌት የሚለፉላት እና የሚያንቀባርሯትን ቤተሰቦቿን ከቁብም ሳትቆጥር እነሱን ትታ ከኔ ጋር ለመኖር ማለሟ ነዉ።
ሴት ልጅ ከወደደች፣ ከተያዘ ነፍሷ፣
የቤተሰብ ክብር ፣ ጨዋታ ነዉ ለሷ። አይደል የሚባለዉ። ይሄን ግጥም ፌስቡክ ላይ አንዷ ለጥፋዉ ነዉ ያነበብኩት። የማን እንደሆነ አላዉቅም። ከስሩ ግን ከበደ ሚካኤል የሚል ፅሁፍ ያየሁ መሰለኝ። ግጥሙ ፌቪን በደንብ ይገልፅልኛል።
ክረምቱ ተጠናቆ አዲስ አመት ተበሰረ። የነአምሪ የዩኒቨርሲቲ ምድብ ወጣ። አምሪ ክፍለሀገር ቢደርሳት በጣም ሊደብረኝ እንደሚችል ይሰማኝ ነበር። ግን ቢደርሰኝም እዚሁ የግል ዩኒቨርሲቲ እማራለሁ ስላለችኝ ተረጋጋሁ። ደስ የሚለዉ ምድብ ሲወጣ ህክምና አዲስአበባ ዩኒቨርሲቲ ደረሳት። ሁላችንም በጣም ደስ አለን።
.
ዛሬ የአዲስ አመቱ ፀሀይ ፈገግ ያለ ይመስላል። በጠዋቱ ተነስቼ ግቢዉ ዉስጥ ፑሽአፕ እየሰራሁ ነዉ። ሀጂ የንጋት ስግደት እንድሰግድ ሲቀሰቅሱኝ እሺ ብዬ መብራቱን አበራና ሲሄዱ አጠፋዋለሁ። ያዉ ግን ስለለመደብኝ አስራሁለት ሰዓት ላይ ቻት ማድረግ እጀምራለሁ። ሀጂ ለቁርስ ሊጠሩኝ ሲመጡ ነቃ ብዬ ስልክ ስጎረጉር ስለሚያዩኝ የሰገድኩ ይመስላቸዋል። ዛሬ ፑሽአፕ ስሰራ አምሪ መጥታ ሀጂ እየጠሩኝ እንደሆነ ነገረችኝ። ስሄድ ፈገግ ብለዉ ተቀበሉኝና "ሀቢቤ ነገ  ወደ መርከዙ ትሄዳለህ። ልብስህን አምሪያ ታዘገጃጅልሀለች።" አሉኝ። መርከዝ ያሉት የሀይማኖት ትምህርት ቤት ማለታቸዉ ይመስለኛል።
"ልብስ ምን ያደርግልኛል?" አልኳቸዉ።
ሀጂ ፈገግ እንዳሉ "አዳሪ ነዉ እኮ ትምህርቱ!" አሉኝ። ዉስጤ ንዴት ቅጥልጥል ሲል ይሰማኛል። እንዴት ነዉ እንደዚህ አይነት ህይወት የማሳልፈዉ? አዳሪ ይላሉ እንዴ?
ምርር እያለኝ "አዳሪ ማለት?" አልኳቸዉ።
"ያዉ አዳሪ ማለት ትምህርቱ እስኪያልቅ አዳርህም እዛዉ ነዉ ማለት ነዋ!" አሉኝ።
የሆነ ስሜት ዉስጤ ላይ ጥፋ ጥፋ ሲለኝ ይሰማኛል። የእናቴን ቃል ከምጥስ ትምህርት ቤቱን ብጥብጥ አድርጌዉ ለመባረር ወሰንኩ። ሀጂ ከሄዱ በኋላ ለአምሪ ያሉኝን ነገርኳት። "ባክህ ልብሱን አስተካክይለት ብሎ ነግሮኛል።" አለችኝ። ሳላስበዉ "አምሪ ትናፍቂኛለሽ እኮ!" አልኳት። ፈገግ ብላ አየችኝና "ሀቢቤ አትጨነቅ መድረሳዉ የአቢ ነዉ። እኔም እሁድ እሁድ ስለምማር እየመጣሁ አገኝሀለሁ።" አለችኝ። የሆነ ትልቅ ሸክም የወረደልኝ ያክል ቅልል አለኝ። አምሪ እንዲህ አቅልላ ያየችዉ እዛ ያለዉን ህይወት ስለምታዉቀዉ ይመስለኛል።
ከልቤ ፈገግ እንዳልኩ "እሺ!" አልኳት።
.
ወደ ማታ ከነሚኪያስ ጋር ተገናኝቼ የተፈረደብኝን ነገርኳቸዉ። በጣም አዘኑ። ሚኪ "ያዉ አንተ እንደምንም እያመቻቸህ ትወጣና ኦፊስ ትከሰታለህ። እኛ ፌቪን አመቻችተን እንጠብቅሀለን። አትጨነቅ!" አለኝ። በርግጥ እኔን ያስጨነቀኝ ነፃነቴ እንጂ የፌቪ ጉዳይ አይደለም።
ወደ ቤት ስመለስ አምሪን መኝታ ክፍሌ ዉስጥ ልብሴን በሻንጣ ስታስተካክል አገኘኋት። "ሀቢብ እስከምጨርስ ሳሎን ሁን!" አለችኝ። አሳሳች ቦታዎች ላይ ብቻችንን ስንሆን በጣም ትጠነቀቃለች። ዛሬ እንኳ እናቷም ነበሩ። አስተካክላልኝ ስትጨርስ ዉጪ በረንዳዉ ጋር ሆና ጠራችኝ። ስሄድ "ስማ ሀቢብ እዛ ስልክ መጠቀም አይፈቅዱልህም። ስለዚህ መላ መፈለግ አለብህ። ስትገባ ይፈትሹሀል። እኔ ከፈተሹህ በኋላ ላቀብልህ እሞክራለሁ። በፍፁም ግን እንዳይታወቅብህ!" አለችኝ።

የፍቅር ታሪኮች🌒

02 Feb, 13:46


የመጣዉ ይምጣ አልኩና "እስከዛሬ የተማርኩት እናቴን ደስ እንዲላት ነበር። ከዚህ በኋላ ባልማር ደስ ይለኛል።" አልኩት።
ረመዳን የሚባለዉ ታናሽ ወንድማቸዉ ፈገግ አለና "ካልተመቸህ ካሁኑ የሚጠቅምህ ህይወት ላይ ትኩረት አድርግ።" አለኝ። ከረመዳን ጋር ትንሽ ሙዳችን እየገጠመ ሳይመጣ አልቀረም።
ትንሽ ከተጫወቱ በኋላ ሶስቱም ተያይዘዉ ወደየቤታቸዉ ሄዱ። እኔም ከአምሪያ መኝታ ክፍል ጎን ወዳለዉ መኝታ ክፍሌ ገብቼ ሳዑዲ የምትኖር ብዙ ጊዜ ብር የምትልክልኝን ተሚማ የምትባል ሚስኪን ታላቢዬን መጀንጀን ጀመርኩ። በመሀል ፌቪ እንደለመደችዉ ደዉላ ረዥም ሰዓት አወራችኝ። ክፍሉ አስተማማኝ ስለሆነ እንደልብ ለመጀናጀን ይመቻል።
.
ሊነጋጋ ሲል ሀጂ ራህመቶ የንጋት ስግደት እንድሰግድ በሩን አንኳክተዉ ለመቀስቀስ ሞከሩ። እንቅልፍ ብዙም ባይዘኝም ላለመስገድ ብዬ ባልሰማ ተኛሁ። አስራሁለት ሰዓት ሲል እንደለመድኩት ቻት ላይ ተጥጄ ከፌቪ እና ከተሚማ ጋር መጀናጀን ጀመርኩ። ተሚማ ፎቶዋን ልካልኛለች። አሪፍ ነገር ናት። በድምፅ የምንላላካቸዉ መልዕክቶች ልብስ ያስወልቃሉ። ትንሽ እየተፃፃፍኩ እንደቆየሁ አምሪያ የመኝታ ቤቴን በር አንኳኳችና " ሀቢቤ ተነስ ቁርስ ብላ!" አለችኝ። እዚህ ቤት ከአስራአንድ ሰዓት በኋላ እንቅልፍ የለም። ተነስቼ ልብሴን ቀያየርኩና ተጣጥቤ ወደ ሳሎን ሄድኩ። ቤቱ ፏ ብሏል። ደስ ይላል። ሀጂ ቁርስ እንድንበላ እየጠበቁኝ ነበር። አጠገባቸዉ ስቀመጥ "እንቅልፎ ሰገድክ?" አሉኝ። ፈገግ ብዬ "አዎ!" አልኳቸዉ። አለመስገዴን ማን ያዉቃል? ማንም! ፈጣሪ ነዉ እሱ እንደሆነ ይበለዉ።
በልተን እንደጨረስን "ሀቢቤ ማታ መማር እንደማትፈልግ ተናግረሀል። እኔ ከልጆቼ ጋር መክሬበት መስከረም ሲመጣ የሀይማኖት ትምህርት እንድትጀምር ወስኛለሁ። እኔ ሀይማኖታዊ ትምህርት ቤት ስላለኝ እዛ ትገባለህ።" አሉኝ። በህይወቴ ከዚህ በላይ የምጠላዉ ነገር ያለ አይመስለኝም። ሀጂ ደግሞ እሺ እሺ ስላቸዉ የሌለ አበዙት።
ምርር እያለኝ "ሀጂ ግን ስራ ብጀምር አይሻልም?" አልኳቸዉ።
"ሀቢብ ይሄ ለድርድር የሚቀርብ ጉዳይ አይደለም! ትማራለህ! የእናትህን አደራ አትርሳ!!" አሉኝ። በእናቴ ስም ይነግዳሉ እንዴ ብሽቅ ነገር ናቸዉ።
በልተን ስንጨርስ ሀጂ የወጪ ብለዉ መቶ ብር ሰጡኝ። ባይሆን ይሄ ሙዳቸዉ የሌለ መስጦኛል። ዛሬም ከፌቪ ጋር ተገናኝቼ በእናቴ ህመም ምክንያት ያላገኘኋትን ለማካከስ አሰብኩ። አዲስ ሴት እስከማሰምጥ ከሷዉ ጋር ልዛዛግ!
.
ሀጂ እንደወጡ አምሪ ፈገግ ብላ "ዛሬ ምንጣፍ አጥባለሁ አታግዘኝም?" አለችኝ።
ቀይ ምንጣፍ ላይ ህዝብ ተሰብስቦ እያጨበጨበልህ ትራመዳለህ ያለችኝ ያህል ደስ አለኝ። ፈገግ ብዬ "በጣም ደስ ይለኛል!!" አልኳት።
እነአምሪ ቤት ሰራተኛ አለመኖሩ ግርም ይለኛል። አንዴ አምሪን ጠይቄያት "ሁለት ሴት ያለበት ቤት ለሶስት ሰዉ ተብሎ ሰራተኛ እንዴት ይቀጠራል?" ብላኛለች። እኛ ለስራዉ አናንስም አይነት ነገር!
ምንጣፉን አዉጥቼ ግቢ ዉስጥ ዘረጋሁት። አምሪ ምንጣፉ ላይ ወጥታ በጎማ ዉሀ እያፈሰሰች በብሩሽ ማሸት ጀመረች። ጫማዬን አዉልቄ አምሪ በሰጠችኝ ብሩሽ ልክ እንደሷዉ ማሸት ጀመርኩ። ሁሉ ነገሯ ልቤን ይዞታል። እንደሌላዉ ሴት እንኳ ለማስመጥ ክብድ ብላኛለች።
ምንጣፉን እያየሁ "አምሪ" አልኳት።
ቀና ብላ አይታኝ ፈገግ አለችና በከንፈሮቿ ጥርሷን ያጠረዉን ሽቦ እየሸፈነች "አርፈህ እሽ!" አለችኝ። እየገባት ነዉ ልበል? እኔንጃ!
ፈገግ እያልኩ "ምኑን?" አልኳት።
ሳቋን መቆጣጠር አቅቷት እርጥቡ ምንጣፍ ላይ እየተቀመጠች "አመዳም ምንጣፉን ነዋ!" ብላ ብሩሿን ወረወረችብኝ።
እየሳቅኩ የወረወረችብኝን ብሩሽ መልሼ አቀብያት እሷ እንደምትቦርሸዉ ምንጣፉን መቦረሽ ጀመርኩ።
.
ይቀጥላል...

#የማይፋቅ
#ስህተት



#የልጅነት_ፍቅሬ
@ye_fkr_tarikoche

የፍቅር ታሪኮች🌒

02 Feb, 13:46


#የማይፋቅ #ስህተት
#ክፍል #ስምንት
(ፉአድ ሙና)
.
ዝም ብዬ እስቃለሁ። ከዛም አለቅሳለሁ። ቆይ ለምን? ፈጣሪን ምን አደረግኩት? ለሌላዉ ሀብትም ጤናም ሰጥቶ ቤተሰቦቹንም ይጠብቅለታል። እኔን ምነዉ ድሀ መሆኔ ሳያንስ ቤተሰብ አልባ አደረገኝ? ይሁና! መች ሀይ ባይ አለዉ!? እንደልቡ ይሁን!! ቆይ ለኔ ምን ሰጠኝ? ጠይም መልክ? ረዥም ቁመት? ሉጫ ፀጉር? ጉልበት? ምላስ? ይሄ ኮተት ለኔ ምን ያደርግልኛል? ሰዉ ከጎኔ ሳይኖር መልክ ፣ ቁመት ወላ ጉልበት ለኔ ምኔ ነዉ? ለነገሩ መች ከሳሽ አለዉና! እንዳሻዉ ይሁን!
.
እማዬ ከተቀበረች ሳምንት ሞላት። ሚኪ ሁሌም አብሮኝ ያድራል። ፌቪ ሰሞኑን ከጓደኞቿ ጋር አብራ እየመጣች ታዳብረኛለች። አምሪ ለቅሶ ለመድረስ የሚመጣዉን ሰዉ በማስተናገድ ተጠምዳለች። ዘመድ ባይኖረኝም ጎረቤትና ጓደኛ ሞልቷል። ለአምሪያ ለየት ያለ ስሜት ዉስጤ ላይ እየተፈጠረ ነዉ። ማታ ላይ ሁሉም ሰዉ ወደቤቱ እንደተበተነ አምሪ እኔና ሚኪ ወዳለንበት ክፍል መጣችና "ሀቢቤ በቃ ቤት ልገባ ነዉ። ደህና እደሩ!" አለችኝ። ልትወጣ ስትል ተከተልኳት። የዉጪዉ በር ጋር ስትደርስ "አምሪ ለምን እዚህ አታድሪም?" አልኳት። አምሪ ቀልዴን መስሏት "አዝግ!" ብላኝ ልትወጣ ስትል እጇን ያዝኳት። እንደመቆጣት እያለች "ሀቢብ!" አለችኝ። ለምን እንደያዝኳት እኔ ራሱ አላዉቅም። ቀስ ብዬ እጇን ለቀቅኳት። በቃ የሆነ ለማንም ሴት ተሰምቶኝ የማያዉቅ አይነት ስሜት ለሷ ልቤ ዉስጥ እየተቀጣጠለ ነዉ። አምሪ ፈገግ እንደማለት አለችና "ደህና እደር ሀቢቤ!" ብላኝ ወጥታ በሩን ዘጋችዉ። በረዥሙ ተነፈስኩና እዛዉ ቁጢጥ አልኩ። ሚኪ ሳሎን ቤት ሆኖ መስታወቱን አንኳኳዉ። ስዞር ሚኪ የሳሎን ቤቱን በር መስታወት መጋረጃ ገልጦ የማደርገዉን እየታዘበ ነበር። ተነስቼ ወደ ቤት ገባሁ። ሚኪ ዝም ብሎ አየኝና "ሀቢቤ ልጅቷ ጎረቤት ነህ ብላ እንዲህ መልፋቷ አይበቃም? አተርፋለሁ ብለህ እንዳትከስራት!" አለኝ።
"ሚኪ እኔ ራሴን ማዘዝ አልቻልኩም። እሷ ስትሄድ በጣም ነዉ የሚጨንቀኝ።" አልኩት።
ሚኪ ሳቀና "እና ፎንቃ አስጨመድዳታለሁ ብለህ ዝተህ የነበርከዉ ልጅ ፎንቃዋ ጨምድዶህ አረፍከዋ!?" አለኝ።
እየሳቅኩ ተቀመጥኩ። ሚኪ እየሳቀ ለአብነት እና ለከሪም ደዉሎ ነገራቸዉ። ምንም አላልኩትም እንደዉም ደስ አለኝ። ከፈለገ ለምን አምሪያን አፈቀረ ብሎ በየፖሉ አይለጥፍም፤ እንኳን በሷ በስንቱ ታምቻለሁ።
.
በነጋታዉ ሀጂ ደዉለዉ ወደ ቤታቸዉ ጠሩኝ። አምሪ እጇን ስለያዝኳት ተናዳ  ነግራቸዉ ከሆነ ብዬ በጣም ፈራሁ። ቤታቸዉ ስሄድ አምሪ ፈገግ ብላ ስትቀበለኝ በሷ ምክንያት እንዳልሆነ ገመትኩና ቀለል አለኝ። ሀጂን ሰላም ብያቸዉ ተቀመጥኩ። ትንሽ ከተጨዋወትን በኋላ "ሀቢቤ ከዚህ በኋላ እንደአባትህ እየኝ! ያዉ እናትህ ባስገባችኝ ቃል መሰረት ላንተ መልካም ያልኩትን አደርጋለሁ። አሁን የናንተ ቤት እየተከራየ ገንዘቡ ባንክ እንዲቀመጥ ብናደርግ፤አንተ ደግሞ እኛ ቤት ብትኖር ምን ይመስልሀል?" አሉኝ። ሳስበዉ ትንሽ ነፃነቴን የሚጋፋኝ መሰለኝ። ደግሞ ከአምሪያ ጋር አብሮ መኖር ልጀምር መሆኑ ጥሩ ነዉ። አይሆንም ለማለት የማቀርበዉ ምንም አይነት ምክንያት ስላልነበረኝ ፈገግ አልኩና "ጥሩ ሀሳብ ነዉ።" አልኳቸዉ።
"በቃ ከተስማማን ጥሩ! አምሪያዬ ክፍልህን ታሳይሀለች። ልብሶችህን ታመጣቸዋለህ። የቤቱን እቃም ተከራይ ሲገኝ የሚሸጠዉ ይሸጣል።" አሉኝ። ተስማማሁ።
.
እነሀጂ ቤት የተሰጠኝ ክፍል ደስ ይላል። ልብሴን አምጥቼ ክፍሌ አስቀመጥኩት። አምሪ ቆንጆ አድርጋ ቁምሳጥኑ ዉስጥ አስተካክላ አስቀመጠችልኝ።
.
  ሀዘኑ ቀለል ሲልልኝ ወደ ቀደመዉ ህይወቴ ተመለስኩ። ኦፊሳችን ስሄድ እነ አብነት የሌለ አሳብደዉታል። ትልቅ ፍራሽ፣ ገራሚ ትራሶች ምናምን ቤቱን ሞልተዉታል። የአዲስ ጎጆ ወጪ ቤት ይመስላል። ፌቪን ቀጥሬ ነበር የመጣሁት። እንደተቀመጥኩ ፌቨን መጣች። ሁለታችንም ምን እንደምንፈልግ ተግባብተናል። አብሮ መተኛት! በሩን ዘግተነዉ ሰላም እንኳ ሳንባባል የልባችንን ወደ ማርካቱ ሄድን። የምንግባባበት ዋናዉ ጉዳይ ይሄዉ ነዉ። አላፈቅራትም፤ለሷ ምንም ስሜት የለኝም።  አሁን ከዚህ በላይ ከፌቪ ጋር መዛዛግ ስለደበረኝ ላሰናብታት ፈልጌያለሁ። እሷን ከማሰናበቴ በፊት ግን ሌላኛዋን ማዘጋጀት ይኖርብኛል። አምሪያን ማስመጡ እንደዚህ ቀላል አይሆንም። ለምን አምሪያ ጋር ስደርስ አቅም እንደማጣ ፣ ለምን ከሌሎች ሴቶች ተለይታ ክብድ እንደምትለኝ አላዉቅም። አጠገቧ ተቀምጬ ሳያት ብዉል አይቆጨኝም። ከፌቪ ጋር ያነፋፈቀንን የስጋችንን ጥሪ ምላሽ ከሰጠን በኋላ ወደ ቤቷ ሸኘኋት። ልንለያይ ስንል አይኖቿን አይኖቼ ላይ እያቁለጨለጨች "ሀቢቤ ላርግዝልህ?" አለችኝ። የሆነ እብደት የተጠናወታት መስሎኝ በግርምት እያየኋት "ፌቪ ግን ደህና ነሽ?" አልኳት።
ፈገግ ለማለት እየሞከረች "ሀቢቤ የእናትህ ሞት የብቸኝነት ስሜት ከፈጠረብህ የኔ የምትለዉ አንድ የስጋ ዘመድ ይኑርህ ብዬ እኮ ነዉ።" አለችኝ።
ግርም እያለችኝ "ሀሳብሽ ጥሩ ነዉ ግን ያንቺ ህይወት ላይ የሚፈጥረዉ ቀዉስ አልታየሽም?" አልኳት።
ፊቷ ላይ እልኋን እያስነበበችኝ "ዲቃላ ወለደች ይላሉ። አለቀ! አንተን ካስደሰተህ ምንም አደርጋለሁ።" አለችኝ።
ቆይ ምንድነዉ ልቧን እንደዚህ የሰቀለዉ? መተት አሰራሁባት እንዴ? ራሴን መጠርጠር ጀምሬያለሁ።
"ፌቪ ስላሰብሽልኝ አመሰግናለሁ። በዚህ ሰዓት ልጅ መዉለዱ ግን ለኔም ላንቺም ስለማይጠቅም ደግመሽ እንዳትጠይቂኝ!" አልኳት።
ፈገግ አለች! ምንም የተጋነነ ዉበት ባይኖራትም የደስ ደስ አላት። ፈገግ እንዳለች "ካልክ እሺ!" አለችኝ። ተሰናብቼያት ወደ አዲሱ ቤቴ ወደነአምሪያ ቤት ሄድኩ።
.
ዛሬ ወንድሞቿ መጥተዉ ቤቱ ደመቅመቅ ብሏል። ኢስማኢል የሚባለዉ ታላቅ ወንድሟ ገና ስገባ ፈገግ ብሎ ተቀበለኝ። ለቅሶ መጥቶ ጠይቆኝ ነበር። ሁለቱ ሰላሀዲን እና ረመዳን ይባላሉ። ለቅሶ አልመጡም ነበር። ገብቼ ትንሽ እንደቆየሁ ሁለት ሰዓት ሊሆን አካባቢ የ"ኢሻ" ሰላት ለመስገድ ሁሉም ብድግ አሉ። እኔ ብቻ ቁጭ አልኩ። ታላቅ ወንድማቸዉ ኢስማኢል "ሀቢቤ ዉዱዕ የለህም መሰለኝ። እንጠብቅህ ሂደህ አድርገህ ና!!" አለኝ። ዉዱዕ ከስግደት በፊት የሚደረግ ትጥበት ነዉ። ሽክክ አለኝ። አልሰግድም ማለቱ ደግሞ አሳፈረኝ። ተነስቼ ተጣጥቤ ተከተልኳቸዉ። ስግደት ላይ የሚባሉት ዉዳሴዎች ብዙዎቹ ጠፍተዉኛል። ልጅ ሆኜ አባቴ ሳይሞት ከሰገድኩ እስከዛሬ ሰግጄ አላዉቅም። ይኸዉ ነፃነቴን መጋፋት ጀመሩ። የእናቴ ቃል ሆኖብኝ እና የሀጂ ራህመቶ ዉለታ ባይዘኝ አብሬያቸዉ አልኖርም ነበር።
ሰግደን እንደጨረስን አምሪያ ምግብ አቀረበች። ምግቡን እያቀራረበች ፈገግ ብላ ታየኛለች። ስሰግድ ስላየች ሙድ እየያዘች መሆኑ ገባኝ። ቆይ ይሂዱ ብቻ የሆነች ተምች የሆነች ልጅ!
  ምግቡን በልተን እንዳበቃን የኢስማኢል ታናሽ ሰላሀዲን "ሀቢቤ ትምህርትህ ላይ እንዴት ነህ?" አለኝ።
ምን ልበለዉ ግራ ገባኝ። ግራ ስጋባ አየኝና "በትምህርትህ የመቀጠል ህልም አለህ ወይስ ሰዉ ስለሚማር ነዉ የምትማረዉ?" አለኝ።

የፍቅር ታሪኮች🌒

20 Jan, 18:00


     ሀጂ ወጥተዉ ትንሽ እንደቆየን ፌቪ ከጓደኞቿ ጋር ሆና መጣች። መኝታ ቤት ገብተዉ እማዬን ጠይቀዋት ሳሎን ተቀመጡ። ለካ ሚኪ የትምሮ ቤት ልጆች ያለዉ ላለማስጠቆር ብሎ ነዉ። አምሪ ፌቨንን አየቻትና "ፎቶ ላይ ያየኋት ናት አይደል?" አለችኝ። ፈገግ ብዬ "አዎ" አልኳት። እኛን ሳሎን ትታን ወደ መኝታ ክፍል ገባች። ፌቪ ልክ አምሪያ ስትወጣ መጥታ አቀፈችኝና ተቀመጠች። ተርባኝ የነበር ይመስላል። እኔ ግን ብዙም ትዝ አላለችኝም። 
.
በነጋታዉ እሮብ እማዬ ድክም አለች። አስሬ መጣራት ጀመረች። መጨረሻ ላይ ድምጿም እየጠፋ መጣ። እኔናአምሪ ከአጠገቧ አንጠፋም። ዛሬ ወ/ሮ ለይላም አብረዉን ናቸዉ። እማዬ ደክማለች። ሀሙስ ጠዋቱን ወደ ሁለት ሰዓት ገደማ እማዬ ፊቷ በላብ ጥምቅ ማለት ጀመረ። እግሮቿ ይፋተጋሉ። ወ/ሮ ለይላና አምሪ ቁርስ አምጥተዉልኝ ከአጠገቧ ተቀምጠዋል። አይናችን እያየ ሰዉነቷ ቀዘቀዘ። አይኖቿ ፈጠጡ። ወ/ሮ ለይላ በእጆቿ የእማዬን አይኖች ከደነቻቸዉ። እንባዬ ልብሴን አጠበዉ። ፈጣሪ ጨካኝ እንደሆነ ተሰማኝ። እንዴት ምድር ላይ ያለ አንዳች ዘመድ ብቻዬን ያስቀረኛል? እንዴት? አምሪያ ወንበሩ ላይ ተቀምጣ ታነባለች። ሀጂ ተደዉሎላቸዉ መጡ። እናቴ ታጥባ በከፈን ተጠቀለለች። ወደ ሰባት ሰዓት ገደማ ተሰግዶባት ተቀበረች።
እማዬን ቀብረን ስንመለስ በጣሙን ተስፋ ቆረጥኩ። ፈጣሪን የከለከላቸዉን ነገሮች ሁሉ በመዳፈር ልበቀለዉ ወሰንኩ። እነሚኪ ቤት ተቀምጠዉ ጠበቁኝ። ትንሽ ደስታ የሚሰማኝ እነሱን ሳይ ነዉ። ገና እንዳየኋቸዉ እንባዬ ይባሱን መዉረድ ጀመረ። ወይኔ ሀቢብ!
.
ይቀጥላል...

#የማይፋቅ
#ስህተት


#የልጅነት_ፍቅሬ
@ye_fkr_tarikoche

የፍቅር ታሪኮች🌒

20 Jan, 18:00


#የማይፋቅ #ስህተት
#ክፍል #ሰባት
(ፉአድ ሙና)
.
እማዬን ከሆስፒታል አዉጥተን ቤት እንዳስተኛናት ሌሎች ጎረቤቶቻችንም እየተመላለሱ መጠየቅ ጀመሩ። ሆስፒታልም መጥተዉ ጠይቀዋል። እኔ ግን ሲጠይቋት አልነበርኩም። ሲጀመርም አባቴ ከሞተ በኋላ ብዙም ከጎረቤቶቻችን ጋር አንቀራረብም። አጥራቸዉን አስረዝመዉ ከመኖር በዘለለ ጉርብትናን በቅጡ የሚረዱ አይደሉም። እድሜ ለነሀጂ እማዬም ቆንጆ ዘመድ አገኘች። እማዬ ቅዳሜ ከሆስፒታል ከወጣች ይኸዉ ዛሬ ማክሰኞ አራተኛዋ ቀን ሆነ።
.
አምሪያ ሰሞኑን ከኛ ቤት አትጠፋም። ቤቱን ማፅዳት እና ለእማዬ የሚያስፈልጋትን ነገር ማቀራረብ የዘወትር ስራዋ ሆኗል። ዛሬ እንዲህ መድሀኒቴ ልትሆን ነገር ትናንት ለአምሪያ እንጨት እየተማረርኩ የፈለጥኩበት ጊዜ አበሳጨኝ።
ዛሬም መኝታ ክፍል እማዬ ከተኛችበት አልጋ ጎን ተቀምጣለች። ሰማያዊ ሂጃብ ጠምጥማለች። ፈገግታዋ ደስ ይላል። ቀኝ እግሯን ግራ እግሯ ላይ ሰቅላዋለች።
"ሀቢቤ!" አለችኝ። ድምጿ ደስ ይላል።
"ወዬ?" አልኳት። እማዬ እስከአሁን ምግብ በደንብ መብላት ስላልቻለች ከጭንቀቴ የተነሳ ድምፄ ርቆኛል።
አምሪያ ትክ ብላ እያየችኝ "ልብስህን ከቀየርከዉ ቆየህ እንዴ? ቆሽሿል እኮ!" አለችኝ።
"አዎ ባክሽ ደሞ ሸሚዞቼ እንዳለ ቆሽሸዋል።" አልኳት።
ከመቀመጫዋ ብድግ እያለች "በቃ ስጠኝ ልጠባቸዉ!" አለችኝ። "ኧረ አምሪ አይነፋም! ሹራብ ነገር እለብሳለሁ ተይዉ።" አልኳት። ዉለታዋ ሲበዛ ከብዶኛል። ልታዳምጠኝ ፈቃደኛ አልሆነችም። "ባክህ አታካብድ ብዙ አይደለም እኮ!" አለችና ቆሻሻ ልብሶቼን አልጋዉ አጠገብ ያለዉን ቁምሳጥን እየከፈተች መፈለግ ጀመረች።
"በቃ እሺ እዛ ዉስጥ ነዉ።" አልኳት የኔ ልብስ ወዳለበት እጄን እየጠቆምኳት።
ልብሶቹን እያወጣች ቁምሳጥኑ ጥግ ላይ የተቀመጡትን ፎቶዎች አነሳችና "እነዚህ ደሞ እነማን ናቸዉ?" አለችኝ። ቀና ብዬ ሳይ ፎቶዎቹ የሰላም፣ የሜሮን ፣ የሰሚራ እና የፌቨን ነበሩ። ምላሴ እየተሳሰረ "የትምሮ ቤት ልጆች ናቸዉ።" አልኳት። ቆይ ምን አስደነገጠኝ? አምሪን ለምን ፈራኋት?
የሰላምን ፎቶ እያሳየችኝ "ስንት ትምህርት ቤት ነዉ የተማርከዉ? ማለቴ የዚች ልጅ ዩኒፎርምና ያንተ ዩኒፎርም ይለያያል።" አለችኝ።
የፈጣሪ ያለህ በጣም አስጨነቀችኝ። ዝም ስላት ልብሶቹን ይዛ ለማጠብ ወጣች። አምሪ እንደወጣች እማዬ በደከመ ድምፅ "ሌላ እናት አገኘህ አይደል?" አለችኝ። አምሪያን ማለቷ ነዉ። ፈገግ ብዬ ዝም አልኳት።
.
እማዬ አምሪያ ወጥታ ትንሽ እንደቆየች በደከመ ድምፅ ሀጂን እንድጠራላት ጠየቀችኝ። ስራ ስለሆኑ ማታ ቢመጡ እንደሚሻል ብነግራትም አሁን ካልሆነ ብላ ተቆጣች። ከመኝታ ክፍል ወጥቼ ለአምሪያ ነገርኳት። ግቢ ዉስጥ ልብሶቼን እያለቀለቀች ነበር። በረንዳዉ ላይ የተቀመጠዉን ስልኳን እያሳየችኝ "አቢ የሚል ፈልግና ደዉለህ አገናኘኝ።" አለችኝ። አባቷን አቢ ነዉ የምትላቸዉ። ደወልኩና ሲጠራ ጆሮዋ ጋር አስጠግቼ ያዝኩላት። እጇ አረፋ ስለነበር ስልኩን እንዳይነካዉ መሆኑ ነዉ። ስልኩን ይዤላት ስታወራ በትኩረት አያታለሁ። ደስ ስትል። አለ አይደል የሆነ እርጋታዋ፣ የአይኖቿ እንቅስቃሴ ፣ ፈገግታዋ የሆነ ያዝ ሲያደርገኝ ተሰማኝ። ምን እየሆንኩ ነዉ? አምሪያ "አንተ እብድ ልጠብበት አታዝገኝ።" አለችኝ። ለካ እሷ አዉርታ ጨርሳለች። እኔ ስልኩን ጆሮዋ ላይ ለጥፌ ይዤ ፈዝዣለሁ። ደነገጥኩና ስልኩን ከጆሮዋ ላይ እያነሳሁ "እና ምን አሉ?" አልኳት።
"አሁን ይመጣል። የሚገርምህ ደሞ ለምሳ እየመጣ ነበር።" አለችኝ።
ላግዛት መዘፍዘፊያዉን ወደራሴ ስስበዉ "በአላህ አታዝግ ሂድና ማዘርን አጫዉታቸዉ።" አለችኝ። ለምን እንደሆነ ባላዉቅም አጠገቧ መቀመጥ ፈልጌያለሁ። "ስማ ሂድ! ማዘርን አታስደብራቸዉ!" ብላ ስትኮሳተር ተነስቼ ወደ እማዬ ክፍል ሄድኩ።
ወደ እማዬ ክፍል ስገባ በር ተንኳኳ። አምሪ እጇ ላይ ዉሀ አፍስሳ ልትከፍት ስትሄድ የመስኮቱን መጋረጃ ገልጬ አያታለሁ። ከፈተችዉ። እነሚኪ ነበሩ። ሶስቱም እንደሀብታም ልጅ የመዓት ኮተት ምናምን በፌስታል ይዘዉ ገቡ። አብነት አምሪያ ላይ ዉሀ ረጭቶባት አለፈ። አናደደኝ። ለምን ተናደድኩ? "ኧረ ሀቢቤ ተረጋጋ ሲቀልድ እኮ ነዉ!" አልኩት ለራሴ!
.
ቤት እንደገቡ የያዙትን ኮተት ሳሎን አስገብተዉ ቤቱን ፏ ማድረግ ጀመሩ። ሀቢብ ብለዉ እንኳ አልተጣሩም። ድፍረታቸዉ አንደኛ ደረጃ ነዉ። ከመኝታ ቤት ወጥቼ ወደ ሳሎን ገባሁ። የጁስ መዓት ብስኩቶች ቸኮሌት እና ምግብ ለመስራት የሚያስፈልጉ ነገሮችን ሳይቀር ይዘዉ መጥተዋል።
"አራስ ምትጠይቁ መሰላችሁ እንዴ ብስኩት፣ ቸኮሌት ምናምን? ላደጉት ልጆች ነዉ?" አልኳቸዉ።
ሚኪ ፈገግ ብሎ እያቀፈኝ "የሸመጠጥካቸዉ ልጆችህ አያታቸዉን ሊጠይቁ ከመጡ ብለን እኮ ነዉ።" አለኝ።  እኔ እኮ የሚገርመኝ የሚኪ መልስ ነዉ። ምላሱ ጫፍ ላይ ተቀባብላ የተቀመጠች ነዉ የሚመስለዉ።
ትንሽ እንደቆየን አምሪ ልብሶቹን አጥባ ጨርሳ ወደ ቤት መጣች። ካመጡት ቸኮሌት ትልቁን አንስቼ ሰጠኋት። ተቀብላኝ ወደ መኝታ ክፍል ሄደች። ከኔ ጋር ሲሆን ነዉ እንጂ ወንድ ሲበዛ አብራ መቀመጥ አትወድም።
የቤቱ በር ሲንኳኳ ልከፍት ወጣሁ። ሀጂ ነበሩ። ሰላም ብለዉኝ ወደቤት ገባን። ሀጂ እነሚኪ እንዲህ ተሰብስበዉ ቤቱን ሲያደምቁት ሲያዩ ደስ አላቸዉ። አብረን ወደ መኝታ ክፍል ገባን። እማዬ ሀጂን ስታያቸዉ ፈገግ እንደማለት አለችና "አምሪ እና ሀቢቤ አንዴ ዉጪ ቆዩ!" አለችን። እኔና አምሪ ተያይተን ፈገግ አልንና ወደ ሳሎን ሄድን። እነሚኪ ያመጡትን ኩኪስ ብስኩት ምናምን ፈትተዉ  እያመቻቹ ነዉ። አምሪ ወከባ መፍጠራቸዉ ገርሟት "ማን ሊመጣ ነዉ?" አለችኝ።
አብነት ከሪምን እያየ "ዛሬ ልደቱ ነዉ።" ብሎ ሳቀና "ስቀልድ ነዉ የትምሮ ቤት ልጆች ሊጠይቁ ሊመጡ ነዉ። ለዛ ነዉ የምንሯሯጠዉ!" አላት። አምሪ ፈገግ አለችና "ኦኬ ፎቶዉ ላይ ያሉት ልጆች?" አለች። ነገር ትበላለች። ሳቅኩና ፈገግ ብዬ "ኧረ በቃ አምሪ ፍቺ!" አልኳት።
.
ሀጂ ራህመቶ ከእማዬ ጋር አዉርተዉ ጨረሱ መሰለኝ ጠሩኝ። እኔን መኝታ ክፍል አስገብተዉ በሩን ዘጉት። እማዬ አየችኝና እያቃሰተች "ሀቢቤ ዛሬ በደንብ አዳምጠኝ!" አለችኝ። ዝም ብዬ አያታለሁ። ቀጠለች "ሀቢቤ እኔ አዝዤህ አንድም ቀን እንቢ ብለኸኝ አታዉቅም። እንዳከበርከኝ አላህ ክብር ያድርግህ። አሁን ግን እኔ ባልኖር ሀጂ እንደ አባትህ ናቸዉ። እኔን እንደምትታዘዘዉ ታዘዛቸዉ። ገደል ግባ ቢሉህ እንኳ እሺ በል። ያኔ እኔ እደሰታለሁ።" አለችኝ። ንግግሯ የስንብት ይመስላል። እንባ ከአይኖቼ ያለማቋረጥ ፈሰሰ። መንሰቅሰቅ ጀመርኩ። ሀጂ አቅፈዉ አባበሉኝ። ስረጋጋ የእማዬን እጅ ጭምቅ አድርጌ ይዤ "እማዬ አንቺ አዘሽኝ የማልቀበለዉ የለም።" አልኳት። እማዬ ፈገግ አለች። ፈገግታ ደስታ ነዉ? ፈገግታ ምንድነዉ? ፈገግታ ስንብት ይሆን እንዴ? ጨነቀኝ። ከመኝታ ቤት እንደወጣን ሀጂ ፈገግ ብለዉ ከቀረበዉ ላይ አንድ ብስኩት አንስተዉ እየበሉ ከቤት ወጡ። ልክ ሀጂ እንደወጡ አብነት እየተገረመ "ባለአጥሯ ግን አባትሽ ሙድ አላቸዉ።" አለ። ባለአጥሯ የሚላት አምሪያ  ጥርሷ በሽቦ ስለታጠረ ነዉ።

የፍቅር ታሪኮች🌒

11 Jan, 19:31


#የማይፋቅ #ስህተት
#ክፍል #ስድስት
(ፉአድ ሙና)
.
በህይወት ዉስጥ ምንም አይነት መደነቃቀፍ ባይኖር ኖሮ የሰዉ ልጅ አምላክ መሆኑን የሚጠረጥር ይመስለኛል። አንድም ቀን እንደዚህ ይጨንቀኛል ብዬ ገምቼ አላዉቅም። እናቴ ሁሉንም ቀዳዳዎቼን ሸፍና አንደላቃኝ ነበር። ዛሬ ግን እናቴ መተማመኛ እንደማትሆነኝ ሊያሳየኝ ሲፈልግ ንቁዋ እናቴን ድንዝዝ አድርጎ ከአልጋ አጋደማት። አሁን ከእናቴ ዉጪ ዞር ብዬ አይቼዉ የማላዉቀዉን ጌታ እየተማፀንኩት ነዉ። ችግር ሲጨመድደን ትናንት ዞር ብለን ያላየነዉን አምላክ ከመማፀን በቀር ምን አማራጭ አለ? ምንም!
.
ማክሰኞ ጠዋቱን እማዬን ከተኛችበት የሆስፒታል አልጋ ላይ እንደተጋደመች ክፍሉ ዉስጥ ካለዉ የኦክስጅን ሳጥን ጎን ተቀምጬ አያታለሁ። እማዬ ፊቷ ሙሉ ለሙሉ ወደ ቢጫነት ተቀይሯል። ፈጣሪ ግን ምነዉ አለ? ያለአባት በመከራ ያሳደገችኝን እናቴን ለምን ያሰቃይብኛል? ለነገሩ ጉልበተኛ ነኝ አይደል የሚለዉ እንዳሻዉ! ብቻ ዝም ብዬ እናቴን አያታለሁ። ያላደላት ሚስኪን ፍጡር!
አብነት እንቅልፍ በዘጋዉ ጎርናና ድምፅ "ስማ ቁርስ አያመጡልንም እንዴ?" አለ። ማታ አብረን ያደርነዉ እኔናአብነት ነበርን።
ቀና ብዬ የተቀመጠበትን ነጭ ባለስፖንጅ ወንበር የእጅ መደገፊያ እያየሁ "አንተ አስታዉሰኸዉ እነሱ የሚረሱት ይመስልሀል?" አልኩት። አብነት ሳቁን ለቀቀዉና "ኧረ ባክህ? ፈጣሪህን ይህን ያህል ብታምነዉ ወርቅ ከሰማይ ያዘንብልህ ነበር።" አለኝ።
ዉስጤ ላይ ብሶቴ እየተቀጣጠለ "ባክህ እሱ መከራ ያዝንብ ተወዉ!" አልኩ።
እኔና አብነት እየተጨዋወትን ብዙም ሳንቆይ አምሪያ የክፍሉን በር ከፍታ ገባች። በእጇ ሰማያዊ ዘንቢል አንጠልጥላለች። አብነትን ዞር ብዬ አየሁትና ሳቅኩ።
አምሪያ በሩን ዘግታ ወደኛ እየዞረች "ምን ያስቅሀል? ለነገሩ ሲጀማምር እንደዚህ እኮ ነዉ።" አለች።
አብነት ወዲያዉ ዘንቢሉን ተቀብሎ ምግቡን ማቀራረብ ጀመረ። እንደሆዱ የሚያፈቅረዉ ነገር ያለ አይመስለኝም።
አምሪያ ከእማዬ አጠገብ ያለዉ ወንበር ላይ እየተቀመጠች "ሀቢቤ አሁንም ምግብ መዉሰድ አልጀመሩም?" አለችኝ። "አዎ ባክሽ ግልኮስ ነዉ የያዛት! ምንም አላማረኝም።" አልኳት። እማዬ በሲቃ በታጀበ ድምፅ "ተዉ ሀቢቤ እንደሱ አይባልም። ፈጣሪ አለ።" አለችኝ። እማዬ መናገር ተራራ ከመግፋት እየከበዳት መጥቷል። እንደዉም ዛሬ ትንሽ አነጋገሯም ተስተካክሏል። አይ እማዬ ፈጣሪ አለ ነዉ ያለችዉ? ፈጣሪማ ለማሰቃየት ሲሆን መች ይጠፋል!? አብነት ምግቡን አቀራርቦ ሲጨርስ አምሪያን "ባለአጥሯ ነይ እንብላ!" አላት። ሳቅኩኝና ወደ አብነት ተጠጋሁ። አምሪን በአንገቴ ነይ ስላት ወንበሯን ይዛ ከኛ ጋር ተቀመጠች። አብነት ገና እጁን ወደ ምግቡ ሲሰነዝር አምሪያ "ወይኔ ስጋ ነዉ እንደዛኛዉ ልጅ ነህ አይደብርህም አይደል?" አለች። እንደዛኛዉ ልጅ ያለችዉ ሚኪያስን ነዉ። አብነት የጠቀለለዉን እየጎረሰ "በፈጣሪ ስም ነዉ የታረደዉ አይደል እንዴ? በእግዚአብሔር ይሁን በአላህ እነሱ ይስማሙበት። የኔ ሀላፊነት መብላት ነዉ።" አለ። እኛ አንድም ቀን የሙስሊም የክርስቲያን ስጋ ብለን ለይተን በልተን አናዉቅም። ያገኘነዉን ማተራመስ ነዉ።
አምሪያ የአብነት ንግግር ስቅጥጥ እያላት "አይ እምነት እንኳ እንዲህ ድንበር የሚታለፍበት ጉዳይ አይደለም። ማንነትህን በደንብ የምትረዳዉ ስታከብረዉ ነዉ።" አለች።
አየር ስለያዙብኝ እየበሸቅኩ "ይቅርታ እንብላበት!" አልኩ።
"እሺ እጃችሁን አትታጠቡም? ከመድሀኒት ጋር አድራችሁ?" አለች።
"አምሪ ኧረ ምንም አንሆንም ይኸዉ ሀያ አመት ሊሞላኝ ነዉ አንድም ቀን ታጥቤ አላዉቅም። ምን ሆንኩ?" አልኳት።
ካልታጠባችሁ አልበላም ብላ ስታሸማቀን ተነስተን ታጠብንና መብላት ጀመርን።
አብነት የአምሪያን ፊት የሚያክል ጉርሻ ጠቅልሎ ላጉርስሽ ሲላት ከአይኗ እንባ እስከሚፈስ ድረስ ሳቀች። በመሀል እማዬ እያየችን ፈገግ ስትል አየኋት። ወደሷ ስዞር "ሀቢቤ ለሴት ልጅ የሚሆን ጉርሻ በመጠኑ አጉርሳት!" አለችኝ።
እማዬ ብላኝ እንቢ ብዬ አላዉቅም። አጎረስኳት። አምሪ መጉረስ አልፈለገችም ነበር ግን እማዬን ላለማስከፋት ብላ ጎርሳልኝ ፈገግ አለች።
.
አምሪያ ከሄደች በኋላ የክፍል ተማሪዎች እየተንጋጉ ሆስፒታሉን ወረሩት። የኢምባሲ በር ጋር ተቃዉሞ የወጡ እንጂ በሽተኛ ሊጠይቁ የመጡ አይመስሉም። እየመሯቸዉ የመጡት ሚኪያስናከሪሜ ናቸዉ። አምስት አምስት እየሆኑ እየገቡ እናቴን አይተዋት ወጡ። እኔም እናቴም በጣም ደስ ብሎናል። ሆስፒታሉ ዉስጥ ግርግር ላለመፍጠር ብለን ግቢዉ ዉስጥ ወርደን ማዉራት ጀመርን። ሀብታሙ እንባ እየተናነቀዉ "ሀቢቤ አብሽር እሺ ለፈተና እንዳታስብ እኔ አለሁልህ።" አለኝ። ሀብታሙ እና እኔ እኮ በወጉ እንኳ ክፍል ወስጥ አዉርተን አናዉቅም። ብቻ ሀበሻ በችግር ሰዓት መልዓክ ካልሆንኩ የሚል ሚስኪን ፍጡር ይመስለኛል። ፈገግ ብዬ አየሁት። ሴቶቹ በየተራ ምግብ ካላመላለስን አሉ። እኔ ግን ምንም የምግብ ችግር ስለሌለ እንዳይለፉ ነገርኳቸዉ። ብቻ ብቅ እያሉ እንደሚጠይቁ ነግረዉን ነገ ለፈተና እንዳላረፍድ አስጠንቅቀዉኝ ሄዱ። ሰብስበዉ የሰጡኝን ብር ደስ እንዲላቸዉ ብዬ ተቀብያቸዋለሁ።
.
ማታዉን ወ/ሮ ለይላ መጥተዉ እማዬን በደንብ ፈታ አደረጓት። ሀጂ ቀጣዩን ሶስት ቀን ፈተና መሆኔን ስለተረዱ ለሊት ስድስት ሰዓት ድረስ እየተኙ የቀረዉን ለሊት አምሪያን ሆስፒታል አድርሰዉ እኛን ወደቤት መልሰዉን ከአምሪያ ጋር እማዬን ሲጠብቁ ለማደር አሰቡና አማከሩን። ምንም ቢከብደንም አማራጭ ስላልነበረን ተቀበልነዉ። ፈተናዉ ተጀመረ። የረቡዕ እለትን ሙሉ ፈተና የሰራልኝ ሀብታሙ ነበር። ትምህርት ብቻ ሳይሆን ማስኮረጅም አንደኛ ነዉ። ሀሙስ ጠዋት ወደ ፈተና ልገባ ስል ሁለት ሀይማኖተኛ ሀይማኖተኛ የሚሰራራቸዉ የግቢያችን ልጆች አገኙኝና "ሀቢብ አሁንስ የትም ብትዘል የማታመልጠዉ አምላክ መኖሩ ገባህ?" አሉኝ። ሸምድደዉት የመጡ እስከሚመስለኝ ድረስ ሁለቱም ደጋገሙልኝ። ዉስጤ በጣም ቆስሏል። ሌላ ጊዜ ቢሆን አንስቼ አፈርጣቸዉ ነበር። አሁን ግን ቅስሜ ስብር ስላለ ትቻቸዉ ሄድኩ። ምን ራሳቸዉን የፈጣሪ መልአክተኛ ያስመስላሉ?  የሆኑ አመዳሞች። 
.
እማዬ ከሆስፒታል መዉጣት የነበረባት እነሚኪ በነገሩኝ መሰረት ከሆነ ማክሰኞ ወይም ረቡዕ ነበር። ግን ምግብ ስለማትወስድ ትንሽ ትቆይ ብለዉ እስከአሁን አልወጣችም። ፌቪዬ በቀን ከአስሬ በላይ የምትደዉልበት ጊዜ ሁሉ አለ። እማዬን ለማሳየት ምቹ ጊዜ አላገኘሁላትም እንጂ አስጎበኛት ነበር። ወይ እንደክፍል ልጆች ሰብሰብ ብለዉ ቢመጡ ያመች ነበር። ለነገሩ ነግሬያት ቅዳሜ ትምህርት ቀርተዉ ከጓደኞቿ ጋር እንደሚመጡ ነግራኛለች። የግል ስለምትማር ቅዳሜም ቀኑን ሙሉ ትምህርት አላቸዉ። 
ቀኑ እየቆጠረ ሄዶ አርብ ደረሰና ፈተና ጨረስን። እኔ እኮ ባልማርም ግድ የለኝም። የምማረዉ እማዬን ደስ እንዲላት ብዬ ነዉ።
.
አርብ ከፈተና መልስ አራታችንም ተሰብስበን ወደ ሆስፒታል ሄድን። ልክ ስንደርስ እናቴ የተኛችበት አልጋ አጠገብ ዶክተሯ እና አምሪያ አብረዉ ቆመዋል። ነርሷ በተቃራኒ አቅጣጫ በኩል ቆማ ዶክተሯ የምትነግራትን ትመዘግባለች። እንደገባን ዶ/ር ቀመሪያ ፈገግ እያለች "ሄይ ሀቢብ" አለች። እየሳቅኩ "እሺ ዶ/ር አለሽ ግን?" አልኳት።

የፍቅር ታሪኮች🌒

11 Jan, 19:31


"አለሁ ባክህ አንተ መች ትገኝና ነዉ ሰሞኑን ኤግዛም ቢዚ አድርጎሀል አሉ።" አለችኝ።  ስታወራኝ የታካሚዋ ልጅ ሳልሆን ጓደኛዋ ነዉ የምመስለዉ።
እማዬን አይታ ስትጨርስ "ሀጂ መች ነዉ ሚመጡት?" አለችኝ።
አምሪያ "ከፈለግሸው አሁን እደዉልለታለሁ።" አለቻት። ሀጂን አንተ ስትላቸዉ ልደነግጥ አልኩና ትዝ ሲለኝ ለካ አባቷ ናቸዉ።
ዶ/ር ቀመሪያ ስልኳን አየችና "አሁን ኦሬዲ ኢትስ ኤይት በቃ ቴን ሰርቲ ላይ ቢሮ ይምጡ!" አለች።
ምናልባት ከክፍያ ጋር የተያያዘ ከሆነ ስምንትሺህ ብሩን ሀጂ አልቀበልም ስላሉን እግረመንገዴን ለመክፈል በማሰብ "ምነዉ ግዴታ እሳቸዉ የሚያስፈልጉበት ነዉ? እኔ መምጣት አልችልም?" አልኳት።
ከነርሷ ጋር ሆነዉ ከክፍሉ እየወጡ "ኖ እሳቸዉን ፐርፐዝሊ ስለፈለግኳቸዉ ነዉ።" አለች።
አምሪ ለሀጂ ደዉላ ነገረቻቸዉ። አስር ከሩብ አካባቢ መጡ።
ከሪሜ ዛሬ አብሮኝ ስለሚያድር ቤት ልብስ ቀይሮ ሊመጣ ሄደ።
ሀጂ ዶክተሯ ቢሮ ቆይተዉ ከመጡ በኋላ ፈገግ ብለዉ "ኢንሻአላህ ነገ ወደ ቤት እንወስዳቸዋለን።" አሉኝ። ደስ አለኝ። ቢያንስ የእነ ሀጂ እንግልት ይቀንሳል። ለእማዬም ቤት መሆኗ ይሻላታል። ቢያንስ እንደተሻላት ይሰማታል።
.
በነጋታዉ ጠዋቱን ከከሪሜና አብነት ጋር ተቀምጠን እያወራን ፌቪ ሶደሬ አብረን ከሄድናቸዉ ጓደኞቿ ጋር ሆና መጣች።  ገብተዉ እናቴን ጠይቀዋት እንደወጣን ጓደኞቿ ቀደም ብለዉን ሲሄዱ ፌቪ ጥምጥም አለችብኝና ከንፈሬን ሳመችኝ። እኔ እንኳ ለእንደዚህ አይነት ነገር ያለኝ ስሜት ወርዷል። ግን እንዳይደብራት በሚል በወጉ አስተናገድኳት። ሆስፒታል ዉስጥ የተሳሳሙ ብቸኛ እብዶች ሳንሆን አንቀርም።
አይን አይኔን እያየች "ሀቢቤ ሁሉም ይስተካከላል አይዞን እሺ!" አለችኝ።
.
እነፌቪ ሄደዉ ትንሽ እንደቆየን ሀጂ እና ወ/ሮ ለይላ መጡ። ዶ/ር እስከምትገባ ትንሽ ጠበቅንና ያለዉን ነገር ጨራርሰን እማዬን ወደቤት ይዘናት ሄድን። እማዬ ዉሀ ነገር ካለዉ ከረጢት በመርፌ ወደ ሰዉነቷ እንደተሰካላት ነዉ። ዶ/ር ቀመሪያ አየችኝና "ሀቢቤ ችግር ካለ ደዉልልኝ" ብላ ስልኳን ሰጠችኝ።
እማዬን ወደቤት እየወሰድናት ሚኪ ደወለልኝ። "ሀቢቤ እናትህ ይሻላቸዉ እንጂ ሀብታም ሆነናል።" አለኝ። ያዉ የፈረደበት ከአረብ ሀገር ሴቶች የተነጨ ብር ተገኝቶ ነዉ። በልቤ "እማ ይሻላት እንጂማ የኔዎቹንም አልባቸዋለሁ" አልኩ።
እነሀጂ እንዳይገባቸዉ እየተጠነቀቅኩ "ቆይ ስንት ታዝኖ ነዉ?" አልኩት።
"በኔ በኩል አምስት ሺ በከሪሜ ደሞ ሰባት ሺህ!" አለኝ። ተሰናብቼዉ ስልኩን ዘጋሁት።
ይሄ ቢዝነስ እያጓጓኝ ነዉ። ቆይ ብቻ እማዬ ይሻላት። ቤት ስንደርስ አምሪ ቤታችንን ፏ አድርጋዉ እየጠበቀችን ነበር። ፈጣሪ መልዓክ ማዉረድ አይጠበቅበትም እኮ! የሰዉ መልአክ ምድር ላይ አለ። ደስ ሲሉ የሚያስቀና ቤተሰብ!
.
ይቀጥላል...

#የማይፋቅ
#ስህተት


#የልጅነት_ፍቅሬ
@ye_fkr_tarikoche

የፍቅር ታሪኮች🌒

09 Jan, 04:48


#የማይፋቅ #ስህተት
#ክፍል #አምስት
(ፉአድ ሙና)
.
እማዬን ያስገባንበት የግል ሆስፒታል ዶክተሮች ይሯሯጣሉ። ዶክተሯ አስጠርታ አየችኝና "ምኗ ነህ?" አለችኝ። ይሀ ስንት ሴት እንደ ቅቤ የሚያቀልጠዉ ምላሴ እየከዳኝ "ልጇ!" አልኳት። ፈገግ አለችና "ከቤተሰብ አባላችሁ ዉስጥ ካንተ ከፍ ያለ ሰዉ አለ?" አለችኝ።
"ቤተሰብ እንኳ የለም ጎረቤት ግን አሉ።" አልኳት።
የተቀመጠችበትን ወንበር ወደ ጠረዼዛዋ እያስጠጋች "ስምህ ማነዉ?" አለችኝ።
"ሀቢብ ከማል" አልኳት።
ዶክተሯ በረዥሙ ከተነፈሰች በኋላ  እንግሊዘኛ የቀላቀለ የረዥም ሰዓት ማብራሪያ መስጠት ጀመረች። እኔ ሀሳቤ ብትንትን ብሏል። የምትለዉን ሁላ ማዳመጥ አልቻልኩም።
መጨረሻ ላይ "...ስለዚህ ሀቢቤ የእናትህ ጉበት አሁን ባልኩህ መልኩ ለረዥም ጊዜ የቆየ ጉዳት ስላስተናገደ አሁን ሙሉ ለሙሉ ፌል ወደማድረጉ ተቃርቧል። በቀዶ ጥገና የቻልነዉን ለማድረግ እንሞክራለን። ሌላ ሰዉ ከሌለ አንተ ትፈርምልናለህ።" አለችኝ። የሆነ ድንዝዝ ስል ይታወቀኛል። ከተቀመጥኩበት ብድግ ብዬ ወደ ዉጪ ወጣሁ። ኮሪደሩ ላይ ሀጂ ራህመቶና ሚኪ ተቀምጠዋል። ከዶክተሯ ቢሮ ስወጣ ሁለቱም ከመቀመጫቸዉ ብድግ ብለዉ ተጠጉኝ።
ሀጂ ራህመቶ "ምን አሉ?" አሉኝ። ዝም ብዬ መተላለፊያዉ ላይ ያለዉ ወንበር ላይ ዘፍ አልኩኝ።
.
ሀጂ ራህመቶ ፈጠን ብለዉ እየተራመዱ ወደ ዶክተሯ ቢሮ ገቡ። ሚኪ ከአጠገቤ እየተቀመጠ "ሀቢቤ ጠንከር በል እንጂ ያንተ መፍዘዝ ችግር ሊፈጥር ይችላል።" አለኝ። እንባዬን ለመቆጣጠር እየሞከርኩ "እንደመምከር ቀላል ቢሆን ጥሩ ነበር።" አልኩት።
ሀጂ ራህመቶ ከዶክተሯ ጋር አንድ ላይ ሆነዉ ከቢሮ ወጡ። ዶክተሯ እጇ ላይ ወረቀት ይዛለች። ከአጠገቤ ተቀመጠችና "ዶ/ር ቀመሪያ እባላለሁ።" አለችኝ። ስገምት ሀጂ ራህመቶ ብቸኛ መሆኔን ምናምን ነግረዋት መሆን አለበት።
ወረቀቱን እያስጠጋችልኝ "እኛ እናትህን ለማዳን የምንችለዉን እናደርጋለን። አንተ ግን ፍቃድህን ልትሰጠን ይገባል።" አለችኝ።
ሀጂ ራህመቶ "ሀቢቤ መቆየታችን ችግር ይፈጥራል። ቶሎ ወረቀቱ ላይ ፈርምላት።" አሉኝ። እጄ እየተንቀጠቀጠ ወረቀቱ ላይ ፈረምኩ። ወዲያዉ ሀጂ እና ዶክተሯ እየተጣደፉ ወደ ፎቅ ወጡ። እኔና ሚኪ ተክዘን ተቀምጠናል። ክፍያዉን ሁሉ የከፈሉት ሀጂ ራህመቶ ናቸዉ።
ሚኪ ስልኩ በተደጋጋሚ ይጠራል። ዞር ብዬ ሳየዉ በአንድ እጁ የኔን ስልክ በሌላኛዉ እጁ የራሱን ይዟል። መች ስልኬን እንደሰጠሁት ፈጣሪ ነዉ የሚያዉቀዉ። ትንሽ ቆይቶ የኔም ስልክ ሲጠራ ሰማሁ። ሚኪ ወዲያዉ ዘጋዉ። ያዉ ፌቨን ናት የምትሆነዉ። ምሽቱን ቻት ላይ ስጠፋ ጨንቋት መሆን አለበት። አንገቴን እንዳቀረቀርኩ "ሚኪ ስንት ሰዓት ሆነ?" አልኩት። "ዘጠኝ ከሩብ" አለኝ። የፈጣሪ ያለህ ፌቪ እስከአሁን አልተኛችም።
"ከዚህ በኋላ ከደወለች አንሳና አናግራት።" አልኩት። ብዙም ሳይቆይ ደወለች ሚኪ ከመቀመጫዉ ተነስቶ ወደ ታች ደረጃዉን እየወረደ ማናገር ጀመረ።
.
ለሊቱን ይሀ የፈረደበት ወንበር ላይ እንደተቀመጥኩ አነጋሁት። ሀጂ ራህመቶ ለሊቱን ሙሉ ሲሯሯጡ ቆዩ። እኔ እንደሆነ ከመንቀሳቀሴ በቀር በድን ሆኛለሁ ብል ይቀላል። ሚኪ ባይኖር ሀጂ በጣም የሚቸገሩ ይመስለኛል። ጎህ እንደመቅደድ ሲል ሚኪ እና ሀጂ ራህመቶ ከላይኛዉ ፎቅ ወረዱ። ሚኪ ከአጠገቤ እየተቀመጠ "ቀዶ ጥገናዉን ጨርሰዋል።" አለኝ። ልቤ ትንሽ ሲረጋጋ ይሰማኛል። "እና እማዬ ደህና ናት?" አልኩ። በስንት መከራ ከአፌ የወጣች ቃል ነበረች። "ገና አልነቁም ግን ደህና ናቸዉ።" አለኝ።
ሀጂ ራህመቶ ለሊቱን ሙሉ ሲንቀጠቀጥ ያደረዉን ወገባቸዉን ለማሳረፍ ቀስ ብለዉ ወንበሩ ላይ ተቀመጡ። 
ሀጂ ፈገግ ካሉ በኋላ "ሀቢቤ አንተ ደክሞሀል አረፍ በል እኛ እንቆያለን።" አሉኝ። የሚገርሙ ሰዉ ናቸዉ። ይሄን ያህል ለሰዉ መኖር ማን ይሆን ያስተማራቸዉ? ምንም ቢደክመኝም እናቴ ሆስፒታል ተኝታ እኔ ወደ ቤት መሄድ አልፈለግኩም። ባይሆን እሳቸዉ አረፍ እንዲሉ ጠየቅኳቸዉ ግን አሻፈረኝ አሉ። ወዲያዉ ዶክተሯ ቦርሳዋን ይዛ እየወጣች "እዚህ ተቀምጣችሁ ምንም አትሰሩም። ከነቁ ነርሶቹ ስላሉ ችግር የለም። እስከ አራት ሰዓት አረፍ ብላችሁ ተመለሱ።" አለችን።
ወዲያዉ ሀጂ ራህመቶ ሰዓታቸዉን ተመለከቱና "ዉይ አስራ ሁለት ተኩል ሆኗል። እስከዛ አፋችን ላይ ምግብ ጣል አድርገን እንመለስ።" አሉ። በሀጂ መኪና ሶስታችንም ወደነ ሀጂ ቤት ሄድን።
.
እነሀጂ ቤት ስንደርስ ሁሉም ከእንቅልፋቸዉ ተነስተዋል። ቤቱ ተሰነዳድቷል። በልቤ "ለሊቱን አይተኙም እንዴ?" አልኩ።  ማታ አምሪያና ወ/ሮ ለይላ አብረዉን ሊመጡ ሲሉ ሀጂ እኛ እንበቃለን ብለዉ እንደመለሷቸዉ ትዝ አለኝ። ሀጂ መንገድ ላይ ሆነን ደዉለዉ ስለነበር ይመስለኛል ገና እንደገባን አምሪያ መጥታ ምንጣፉ ላይ የሚያምር ላስቲክ አነጠፈች። ሚኪ በአይኑ "ምንድነዉ?" ብሎ ጠየቀኝ። ያዉ ምግብ ሲቀርብበት ይገባዋል ብዬ ዝም አልኩት። ወዲያዉ አምሪያና ወ/ሮ ለይላ ምግቡን አቀራረቡና መብላት ጀመርን። ወ/ሮ ለይላ ስለ እናቴ ሁኔታ ጠየቁ።  ሀጂ ሁሉንም በዝርዝር አስረዷቸዉ። የአምሪያ ፊት ላይ የሀዘን ድባብ ይታያል። ምግቡን በልተን እንደጨረስን እኔና ሚኪ እኛ ቤት ገብተን አረፍ አልን። ወገብ ለማሳረፍ ያክል ነዉ እንጂ በወጉም እንቅልፍ አልወሰደኝም ነበር። ትንሽ ካንገላታኝ በኋላ ግን እንቅልፍ ይዞኝ እብስ አለ።
.
ከእንቅልፌ ስነቃ ሚኪያስ አጠገቤ የለም። ከአጠገቤ ስልኬ ተቀምጧል። አነሳሁና ሰዓቱን ተመለከትኩት። ስድስት ሰዓት ሆኗል። ደንግጬ ከአልጋዉ ላይ ተስፈንጥሬ ተነሳሁ። የአልጋዉ ጫፍ ላይ ወረቀት ተቀምጧል። አንስቼ አነበብኩት። የሚኪ ፅሁፍ ነዉ። "ሀቢቤ አረፍ ብለህ ና እኔናሀጂ እዛዉ ስለሄድን አትጨነቅ።" ይላል። ወዲያዉ ተነስቼ ተጣጠብኩና ወደ ሆስፒታሉ ለመሄድ ከቤት ወጣሁ። ወዲያዉ ፌቨን ደወለችልኝ።
አነሳሁትና "ወዬ ፌቪ" አልኳት።
ፌቪ እያለቀሰች "ሀቢቤ በጌታ የት ሆስፒታል ነዉ ያላችሁት ጓደኛህ አልነግርም አለኝ። ፕሊስ መረጋጋት አልቻልኩም ልምጣና ልያቸዉ።" አለችኝ። ለቅሶዋ ልብ ይነካል። ልነግራት አሰብኩና ሀጂ ራህመቶ መኖራቸዉን ሳስብ መምጣቷ አግባብ እንዳልሆነ ተሰማኝ።
"ፌቪ አንቺ መምጣትሽ ለኔ ጥሩ አይደለም። ባይሆን ሰዓት ካገኘዉ እኔ ወጥቼ አገኝሻለሁ።" አልኳት። ምንም መምጣት ብትፈልግም ለኔ ጥሩ አይደለም ስላልኳት ተስማማች።
"ግን ሀቢቤ ስደዉል ስልክ አንሳልኝ እሺ!" አለችኝ።
እሺ ብያት ተሰነባበትን።
.
ሆስፒታል ስደርስ ሀጂ እና ሚኪ እማዬ የተኛችበት ክፍል ዉስጥ ተቀምጠዋል። እማዬ ነቅታለች። የሆነ የሆነ ነገር ተሰካክቶላት ተጋድማለች። መናገር ምናምን ግን አልጀመረችም። ሳያት የማላዉቀዉ ስሜት ዉርር አደረገኝ። ወዲያዉ ግንባሯን ሳምኩና ከነሚኪ ጋር ተቀመጥኩ።  ወዲያዉ ሀጂ ፈገግ ብለዉ "ዶክተሯ ነገ ይወጣሉ ብላለች።" አሉኝ። በጣም ደስ አለኝ። እማዬ እንደዚህ በአጭር ቀን ከሆስፒታል ትወጣለች ብዬ አልገመትኩም ነበር።
"እና ዉጤቷን ነገሯችሁ?" አልኩ በጉጉት የሚሉትን ለመስማት እየጠበቅኩ።
.
ይቀጥላል

#የማይፋቅ
#ስህተት

#የልጅነትን_ፍቅሬ
#@ye_fkr_tarikoche

የፍቅር ታሪኮች🌒

29 Nov, 20:20


"ሽኩሪያዬ አምሪያ ጓደኞቿ ጋር ሄዳ አረፈደችብኝ እንጂ ቶሎ ነበር ለመምጣት ያሰብኩት!" አሉ። ሽኩሪያ የእናቴ ስም ነዉ። ሁሌም እማ ስለምላት ሽኩሪያ ሲባል ሌላ ሰዉ የተጠራ ነዉ የሚመስለኝ። አምሪያ በአይኗ "አፍህን ዝጋ!" የሚል ቆንጆ ማስጠንቀቂያ ሰጠችኝ።
እናቴ አምሪያን እያየች "ቆይ አምሪያዬ ብዙ ጊዜ እሁድ እሁድ አላይሽም የት ነዉ የምትዉይዉ?" አለች።
አምሪያ "ጠዋት ጠዋት መስጂድ ትምህርት አለኝ ከዛ በኋላ ደግሞ ወንድሞቼ ቤት ስለምሄድ ይሆናል።" አለች። እንግዲህ አሁን ስለመስጂድ ከተነሳ የአምሪያ እናት ወይዘሮ ለይላ መስጂድ ለምን አትሄድም ብለዉ ስለሚነዘንዙኝ ቀድሜ ብወጣ ይሻላል ብዬ ወደ መኝታ ክፍሌ ሄድኩ።
ወዲያዉ አብነት ጋር ደዉዬ እንዴት ስምንት ሺህ ብር ሁሉ ልትልክለት እንደቻለች ጠየቅኩት።
"እናቴ ታመዋል ለኦፕራሲዮን ብር አጣሁ ስላት ከእናትህ ምንም አይበልጥብኝም ብላ ላከችልኝ።" አለኝ። ብሽቅ አልኩ። የሆነ ለማኝ ነገር ነዉ። እናቴ ታመዋል ብሎ ብር ከሚያስልክ ብሩ ጥንቅር ብሎ ቢቀርብን ይሻል ነበር።
የኔዎቹ ለልብስህ መግዣ ፣ ስጦታ ይሁንህ ምናምን እያሉ ነዉ የሚልኩት። እኔ ሲጀመር ማለቃቀስ አይመቸኝም። ጠብረር ስልባቸዉ ወደነሱ ለመሳብ ሲሉ የሆነ ነገር ይልካሉ። አለቀ!
.
እኔ መኝታ ክፍል ተቀምጬ ፌስቡክ ላይ እጀናጀናለሁ። እነእማዬ ደግሞ ሳሎን ቡናቸዉን እየጠጡ ይጨዋወታሉ። መጀናጀን ከጀመርኩ ትንሽ እንደቆየሁ ሁሉም በአንዴ ፀጥ አሉ። ጫጫታቸዉ ጠፋ። እማዬ ስታቃስት ሰማሁ። አምሪያ "ሀቢብ!" ብላ ጮኸች። ከአልጋዉ ላይ ተስፈንጥሬ ተነስቼ ወደ ሳሎን ተንደረደርኩ። እማዬ ፍራሹ ላይ ተዘርራ በእጆቿ ሆዷን ጨምድዳ ይዛ እግሮቿን እያፋተገች  ታቃስታለች። ወይዘሮ ለይላ ተደናግጠዉ አንገቷን ደግፈዉ ይዘዉ ያዩኛል። የማደርገዉን ነገር ነዉ ያጣሁት። አጠገቧ ተቀምጬ አያታለሁ። ወይዘሮ ለይላ "አምሪ አባትሽ ጋር ደዉይለት!" አሉ። አምሪያ ወዲያዉ አባቷ ጋር ደወለች። አላማዉ መኪና ይዞ እንዲመጣ እና ሀኪም ቤት እንድንወስዳት ነዉ። ድንዝዝ ብያለሁ! እማዬ እንደዚህ ስትታመም አይቼ አላዉቅም። አንዳንዴ ያማት ነበር። ታይታዉ ጉበትሽ ላይ ነዉ  ችግሩ ብለዋት ነበር። ከዛ በኋላ ህክምናዉን የወሰደችም አይመስለኝም። ግን አልፎ አልፎ ቢያማትም እንዲህ እንደዛሬዉ አሰቃይቷት አያዉቅም። ፊቷ ሙሉ ለሙሉ ነዉ ቅይር ያለዉ።
ከአምስት ደቂቃ በኋላ የአምሪያ አባት ሀጂ ራህመቶ ደረሱ። እማዬን መኪናዉ ዉስጥ አስገብተን ወደ ሆስፒታል ሄድን። ለሚኪ የተፈጠረዉን ነገር ደዉዬ ነገርኩት። ሰፈራችን ያለ አንድ የግል ሆስፒታል ነበር የሄድነዉ። ሀኪሞቹ እማዬን አስገብተዉ ማከም ጀመሩ። እኛ ዉጪ ሆነን እንጠብቃለን። ጭንቅ ብሎኛል። ሚኪ ሲከንፍ ደረሰ፤ የአምሪያ አባት ሀጂ ራህመቶ አብረዉኝ አሉ። የሆነ የማላስበዉ ስሜት ዉርር አደረገኝ። ተጨንቄ አላዉቅም! በጣም ጨነቀኝ።
.
ይቀጥላል...

የፍቅር ታሪኮች🌒

29 Nov, 20:19


#የማይፋቅ #ስህተት
#ክፍል #አራት
(ፉአድ ሙና)
.
ከማክሰኞ እስከ አርብ አስራሁለተኛ ክፍሎች የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ስለሚፈተኑ ትምህርት አልነበረንም። ለሙድ ብለን እሮብ ተገናኝተን ቃምን። ለነገሩ ትንሽ ቅጠል ስለነበር የጎረስኩት አልመረቀንኩም። ከሪሜ ግን አይኑ ቦግ ብሏል። ጥርሴን እየፋቅኩኝ ቅዳሜ እና እሁድን ሶደሬ ስለማሳልፍ   ሚኪ ቅዳሜ በጠዋት እኛ ቤት ሄዶ ለእማዬ እንጀራዉን ወደ ምግብ ቤት እንዲያደርስላት አደራ አልኩት። አርብን እዚሁ የተከራየነዉ ቤት አድሬ በለሊት ለመሄድ ነዉ ያሰብኩት።
የጎፈረ ፀጉሩን እየፈተለ "ስታይል ሀቢቤ ደሞ ለዚህ አንሳለሁ እንዴ?" አለኝ። እንዳያረፍድባት ደጋግሜ አደራ አልኩት።
አብነት የመጨረሻዋን ቅጠል እየጎረሰ "ስማ ሀቢቤ ያቺ የጎረቤታችሁ ልጅ አስራሁለተኛ ክፍል ናት ምናምን ያልከዉ ፈተና እንዴት ነዉ አለችህ? ሰርተዉታል?" አለኝ። እዉነት ለመናገር አምሪያ ተፈታኝ መሆኗን በራሱ ረስቼዉ ነበር።
.
ማታ ከእማዬ ጋር ወደ ቤት ስንገባ አምሪያ በራቸዉ ላይ እንጨት አጋድማ ለመፍለጥ ስትሞክር ደረስን። ሲጀመር መፍለጥ አይደለም መጥረቢያ መያዝ ራሱ አትችልም። እናቴ ሂድ አግዛት ማለቷ አይቀርም ብዬ ቀድሜ "እንኪ ሰፌዱን ላግዛት!" አልኳት።
እማዬ ፈገግ ብላ "ተወዉ ደክሞሀል!" አለችኝ። በጣም ደስ አለኝ! ግልግል አልኩ በልቤ። ወዲያዉ እናቴ ሳቀችና "አመዳም ሂድና ፍለጥላት! ሴት ልጅ የጉልበት ስራ ስትሰራ ይሰማህ!" አለችኝ። እየተበሳጨሁ ወደነአምሪያ ቤት በር ሄድኩና መጥረቢያዉን እየተቀበልኳት "አምሪ ግቢያችሁ ዉስጥ አትፈልጪም ነበር? ዉስጥ አይሻልም?" አልኳት። እዉነት ለመናገር ምርር ብሎኛል።
አምሪ ጥርሷን ያጠረዉ ሽቦ እስኪታይ ድረስ ፈገግ እያለች "ቴራዞ ነዉ ሙሉ ግቢዉ! እንጨት ቢፈለጥበት ይሰበራል።" አለችኝ። ቴራዞዉ አየር ላይ አልቆመ የሚሰበረዉ! የሆነች ብሽቅ።
በመጥረቢያዉ የሰነጠቅኩትን እንጨት በእጆቼ ለመለያየት እየሞከርኩ "ፈተና እንዴት ይዞሻል?" አልኳት።
"ምንም አይልም! ያዉ ዉጤት ሲመጣ ነዉ እንዴት እንደነበረ የሚታወቀዉ።" አለችኝ።  እኔ እየፈለጥኩ አምሪያ ቆማ እያወራችኝ አባቷ ከቤት ወጡ። እንጨቱን እያዩ "ይሄ ደግሞ ለምንድነዉ?" አሉ።
አምሪያ እየተሽቆጠቆጠች "ለማንደጃ ፈልገነዉ ነዉ።" አለች። አባቷ ለቤቱ እንጨት ሲያስፈልግ አለማወቃቸዉ ገረመኝ። ለነገሩ እሳቸዉ ኩሽና አይገቡ! አባቷ መኪናቸዉ ዉስጥ ገብተዉ እንደሄዱ "ቆይ አባትሽ ወዴት ነዉ ሁሌ በዚህ ሰዓት የሚሄዱት?" አልኳት።
"ትልቅ የሀይማኖት ትምህርት ቤት አለዉ። ቀን ንግድ ላይ ስለሚዉል አይመቸዉም ፤ አሁን ነዉ ሄዶ ያለዉን ነገር የሚያየዉና ለአስተማሪዎቹ የሚያስፈልገዉን ነገር የሚያሟላላቸዉ።" አለችኝ።
ፈልጬላት ስጨርስ ወደ ግቢያቸዉ እንጨቱን እያስገባሁላት "መልካም ፈተና!" አልኳት።
እሷም መልሳ "መልካም ፈተና!" አለችኝ። እኔ ተፈታኝ አልነበርኩም። የሆነች ቀዉስ ነገር።
.
ቅዳሜ አይደርስ የለ ደረሰ። እነፌቪ ቀደም ብለዉ ሚኒባስ ኮንትራት አናግረዉ ስለነበር ከያለንበት ለቃቀመን።  እማዬ የምታዉቀዉ ከሪሜ ቤተሰቦቹ ለቅሶ ለመድረስ ክፍለሀገር ስለሚሄዱ ከሱ ጋር ለመሆን መሄዴን ነዉ። በነገራችን ላይ ከፌቪ ዉጪ ሌሎች አራት ልጆች አብረዉን አሉ። አንዷ ፍቅር ናት የፌቪ ጓደኛ! ባለፈዉ ካፌ ያገኘኋት! ስገምት እሷም ከፍቅረኛዋ ጋር ናት። አብሯት የተቀመጠ ቀላ ያለ ልጅ አለ። ሁለቱ የቀሩትም ፍቅረኞች ናቸዉ። ሶስት ወንድ ሶስት ሴት ነን። ደብረዘይትን እንዳለፍን እማዬ ጋር ደዉዬ ሚኪ መጥቶ እንጀራዉን እንዳደረሰላት አረጋገጥኩ። ሶደሬ እንደደረስን ፌቨን እና አንድ ፍራኦል ነኝ ብሎ የተዋወቀኝ ልጅ አልጋ ለመያዝ ተሯሯጡ። ሶስት አልጋ ያዝን። እቃችንን አስተካክለን ፈታ ማለት ጀመርን። ቅዳሜ መሽቶ የቁርጡ ሰዓት ደረሰና ከፌቪ ጋር ከአዲስ አበባ አዳማ ድረስ ያስመጣንን ጉዳይ ተገበርነዉ። ማንም ያልነካት ልጃገረድ ነበረች። እኔ የመጀመሪያዋ ሆንኩኝ። አብረን አደርን።
.
እሁድ ጠዋቱን እኔ እየዋኘሁ ፌቪ ገንዳዉ አጠገብ ተቀምጣ እያየችኝ እያለ ትልቁ መዋኛ ፊትለፊት በፍፁም ያልጠበቅኩትን ሰዉ አየሁ። አምሪያ ነበረች። ረዥም ቀሚሷን እንደለበሰች ከዋና ገንዳዉ ፊት ለፊት ቆማለች። ምን ልትሰራ መጣች? ደሞ አይታኛለች። ፌቪን ትቼ ወደ ትልቁ መዋኛ ብረቱን ዘልዬ ገባሁ። እየዋኘሁ አምሪያ ወደ ቆመችበት ጥግ ሄድኩ።  ዉሀዉ ዉስጥ እንደሆንኩ ቀና ብዬ እያየኋት "እንዴት መጣሽ?" አልኳት።
ትልቁ ገንዳ ዉስጥ የሚዋኙትን ልጆች እያሳየችኝ "ፈተና ስለጨረስን ዘና ለማለት ከጓደኞቼ ጋር መጥተን ነዉ። አንተ እዚህ ምን ትሰራለህ?" አለችኝ።
እነፍራኦልን እያሳየኋት "አንዳንዴ ዋና ጥሩ ነዉ ብዬ ከጓደኞቼ ጋር መጥቼ ነዉ።" አልኳት።
በሽቦ የታጠረዉ ጥርሷ እስኪታይ ሳቀችና በከንፈሮቿ ሽቦዉን ለመሸፈን እየሞከረች "ደስ ይላል! በርታበት። ለማንኛዉም ቤት ሌላ ቦታ እንጂ እዚህ እንደምዝናና ስለማያዉቁ እዚህ እንደተገናኘን እንዳታወራ!" አለችኝ።
እየሳቅኩ "አላወራም! ባይሆን ክፍያዉን አስቢበት!" አልኳትና ወደነፌቪ ተመለስኩ። ለፌቪ ማንነቷን በደንብ አስረዳኋት። ፌቪ በጣም ስለምታምነኝ በመሄዴ ብትቀናም አልጠረጠረችኝም።
.
ከሴቶች እየዋኘች የነበረችዉ ፍቅር ብቻ ነበረች። ሌሎቹ የማታዉ የሞት ሽረት ትግል አልፈስፍሷቸዋል። ከመዋኛ ገንዳዉ ወጥቼ ከፌቪ ጋር ወደ መኝታ ክፍላችን ሄድን። ስልኬን ስመለከተዉ ሶስት ሚስኮል አለ። ከፍቼ አየሁት። ሁለቱ ከሚኪያስ ነዉ። አንዱን አብነት ነዉ። ሚኪ ጋር ደወልኩኝ። እየተበሳጨ "እሷ ልጃገረድ ለሆነችዉ አንተን ምን ያሽኮረምምሀል!? ስልክ አታነሳም!?" አለ።
"ባክህ እየዋኘን ነበር አትጩህ!" አልኩት። ሚኪ ስለነበረዉ ነገር ጠይቆኝ ፌቪ አጠገቤ ስለነበረች በማያስባንን ቋንቋ አዳራችንን ነካካሁለት። የሚኪን እንደዘጋሁት አብነት ደወለና "ሀቢቤ ነዳጅ እንደፈለቀልን ቁጠረዉ ሜሮን ማለቴ ራቁቷን ፎቶ የላከችልኝ ልጅ ስምንት ሺህ ብር ላከችልኝ።" አለኝ። ፌቨን አጠገቤ ስለነበረች ማታ ስመለስ እንደምደዉል ነግሬዉ ዘጋሁት። እንዴት ብታብድለት ይሄን ሁሉ ብር እንደላከችለት ገርሞኛል።
.
ከሶደሬ እንደተመለስን ከፌቪ ጋር ልንለያይ ስንል ፌቪ አይን አይኔን እያየች "አትራቀኝ እንጂ ገና ነብሴንም እሰጥሀለሁ!" አለችኝ። ቻዉ ተባብለን መንገድ ስጀምር መልሳ እየሮጠች መጥታ ተጠመጠመችብኝ። ሁሉነገሯ እኔ ጋር ያለ ይመስላል። አይኗ ዉስጥ ፍርሀት እና አክብሮት በደንብ ይታያል። በደንብ አቅፌ ተሰናበትኳትና ወደ ቤት ሄድኩ። መንገድ ላይ እያለሁ ፌቪ ደወለችልኝ። ሁኔታዋ ሁሉ ገርሞኛል። አዳሩ ሁሉ ነገሯን ቀያይሮታል። ፍቅሯ በዝቶባት ወደ አምልኮት እንዳያድግ ፈራሁ። በቃ የሷን ስሜት የሚገልፅላት ሙዚቃ ነዉ። ዘፈነችልኝ። አዳመጥኳት። ልብ ትበላለች።
.
ቤት ስገባ እማዬ፣የአምሪያ እናትና አምሪያ ተቀምጠዉ ይጨዋወታሉ። አምሪያ ቡና እየቀዳች ነዉ። ከመቼዉ ደርሳ እንደሆነ ፈጣሪ ነዉ የሚያዉቀዉ። ምናልባት ቀደም ብላ መጥታ ይሆናል። ሰላም ብያቸዉ ተቀመጥኩ።

የፍቅር ታሪኮች🌒

10 Oct, 17:42


https://t.me/notpixel/app?startapp=f6470027413_s573809

የፍቅር ታሪኮች🌒

10 Oct, 17:42


https://t.me/notpixel/app?startapp=f6470027413_s573809

የፍቅር ታሪኮች🌒

10 Oct, 17:41


https://t.me/notpixel/app?startapp=f6470027413_s573809

የፍቅር ታሪኮች🌒

23 Sep, 20:32


#የማይፋቅ #ስህተት
#ክፍል #ሶስት
(ፉአድ ሙና)
.
አረብ ሀገር ካሉ ሴቶች ብር መቀበል ከጀመርን በኋላ ሱስ ላይ ሳንወድቅ አንዳንዴ ለሙድ ብለን እንቃም ተባብለን መቃም ጀመርን። እኔናሚኪ ሄለንን እና ፌቨንን አብረዉን እንዲተኙ ለማድረግ ጉትጎታዉን ጀምረናል።
.
አርብ ቀን ከፌቪ ጋር እንደተገናኘን ኦፊሳችንን እንድትጎበኘዉ ወደተከራየነዉ ቤት ይዣት ሄድኩ። ቀድሜ ከነአብነት ጋር አዉርቼበት ስለነበር ቤቱን አስተካክለዉ ወደ ፑል ቤት ሄደዋል። በነገራችን ላይ ኦፊሳችን ዉስጥ ያሉት ነገሮች ከሪም ከቤቱ ያመጣዉ አንሶላ ፣የገዛናቸዉ ፍራሽ ፣ ትራስ እና ትናንሽዬ የፕላስቲክ ወንበሮች ናቸዉ።
ገና እንደገባን ፌቪ "ዋዉ ፍራሻችሁ ደስ ትላለች።" አለችና ጫማዋን አዉልቃ ፍራሹ ላይ ተቀመጠች። እኔ በሩ ጋር ቆሜ አያታለሁ። የዛሬዉ እቅዴ ከተሳካልኝ አብሪያት መተኛት ካልሆነም መንገዱን ማመቻቸት ነዉ። ሄጄ ከአጠገቧ ተቀመጥኩኝ። ፌቪ ዩኒፎርሟን አዉልቃ ቦርሳዋ ዉስጥ አድርጋዋለች። ከዉስጥ ሱሪ ለብሳ ስለነበር በሱሪ ናት። ከላይ ደግሞ የሚያምር ሰማያዊ ሹራብ ለብሳለች። በቦርሳዋ ይዛዉ የመጣችዉ ነዉ። ቲቸር እያሱ ካስደነገጣት በኋላ ሁሌም እንዲህ ነዉ የምታደርገዉ።
.
ከአጠገቧ እንደተቀመጥኩ "ፌቪዬ ምን ያህል ትወጂኛለሽ?" አልኳት።
የሚካኤልን "ዉዴ እወድሻለሁ" የሚለዉን ዘፈን በወንድ አድርጋ ዘፈነችልኝ። ለጥያቄዬ በቂ ምላሽ ነበረዉ። በደንብ ወደሷ እየተጠጋሁ "ማለቴ ራስሽን አሳልፈሽ ትሰጪኛለሽ?" አልኳት። ደረቴ ላይ እየተኛች "ህይወቴ እኮ አንተ ነህ ምን ህይወት አለኝና ራሴን ካንተ እከለክላለሁ?" አለችኝ።
"እወድሻለሁ!" አልኳት። ፌቪ እወድሻለሁ ስላት ደስ ይላታል። ከደረቴ ላይ ተነስታ ወደ ከንፈሮቼ ሄደች። ለኔናለሷ መሳሳም ቀልድ ነዉ። እንኳን እንደዚህ ባዶ ቤት አግኝተን ይቅርና መንገድ ላይ ጭር ሲልልን ራሱ እድሉን ከመጠቀም ወደኋላ ብለን አናዉቅም።
.
እየተሳሳምን እጆቼ  አጉል ወደ ሆነ ቦታ ሲቃብዙ ፌቪ ያዘቻቸዉ። ትንፋሿን ሰበሰበችና አይኖቿን እየገለጠች ሹክሹክታ በሚመስል ድምፅ "ሀቢቤ አብረን እንድንተኛ ፈልገሀል እንዴ?" አለችኝ። እጆቼ እየተርመሰመሱ የነበረበት ቦታ ለመተኛት የሚገፋፋ በመሆኑ የገመተች ይመስለኛል።
"አዎን ፌቪ! እኔ ሁሉም ነገር ካንቺ ተሟልቶልኝ ወደ ሌላ ሴት የማይበት ምክንያት ማጣት እፈልጋለሁ።" አልኳት። ድሀ ሆንኩ እንጂ ንግግርማ ታድሎኛል።
ለመዉለቅ ምንም ያልቀረዉን ሹራቧን እየለበሰች "ሀቢቤ ትንሽ አትታገስም?" አለችኝ።
ሙከራዬ እንዳይከሽፍ እየተመኘሁ "ፌቪ ምን እስኪፈጠር ድረስ ልታገስ?" አልኳት።
"በቃ እሺ ላስብበት እና እነግርሀለሁ።" አለችኝ።
እየሳቅኩ "እና እስከዛ መሳሙንም ተከለከልኩ ማለት ነዉ?" አልኩ።
ፌቪ እንዳልነካት እጆቼን ወደ ኋላ ጠፍራ ይዛ ሳመችኝ።
.
ፌቪን ሸኝቼያት ሚኪያስ ጋር ደወልኩ። ከፑል ቤት መጥቶ ወደ እማዬ ምግብ ቤት ሄድን። "አብነትናከሪሜ ይመሽብናል ብለዉ ወደ ሰፈራቸዉ ሄዱ!" አለኝ። ከፌቪ ጋር እንዳልተኛን ስነግረዉ የሌለ ተናደደ። እንደዉም እንድዘጋት መከረኝ። እኔ ግን አስባበት የምትለዉን ከሰማሁ በኋላ ለመወሰን ነዉ ያሰብኩት።
እማዬ ምግብ ቤቷን መዝጊያ ሰዓቷ ሲደርስ እንደተለመደዉ ሰፌዶቹን ይዤ ወደ ቤት ተመለስን። ሚኪ ወደ ቤቱ ተቀነጠሰ።
.
ሰፈር ስንደርስ አምሪያ ሰላሳ ሊትር ጀሪካን የግቢዉ በር ጋር አስቀምጣ በጆግ ዉሀ እየቀዳች የተከልናቸዉን ችግኞች ታጠጣለች። እማዬ እንደተለመደዉ የያዝኳቸዉን ሰፌዶች ተቀብላ "ሂድ ቢያንስ ሰላሳ ሊትር ጀሪካን ሴት ስትነቀንቅ ይሰማህ! ዉሀዉን በጆግ እየቀዳህ ስጣት!" አለችኝ። የእዉነት ተናድጃለሁ። ምናባቷ የማትችለዉን ስራ ያሰራታል? ብሽቅ! እየደበረኝም ቢሆን የእናቴን ትዕዛዝ ተቀብዬ አምሪያን ለማገዝ ወደ በራቸዉ ሄድኩኝ።
በጆግ ዉሀ ቀድቼ እያቀበልኳት "አምሪ ቧንቧ የላችሁም እንዴ?" አልኳት።
"እሱማ አለን ግን ሀይል ስለሚኖረዉ በጎማ ስቤ ባጠጣቸዉ ስላልጠነከሩ ይሰብራቸዋል ብዬ ነዉ።" አለችኝ። በልቤ ምናባቷ ሀይል መቀነሻ የሌለዉ ቧንቧ ነዉ እንዴ ያላቸዉ? እያልኩ እበሽቃለሁ።
አበባዎቹን ዉሀ አጠጥታ ስትጨርስ ጥርሶቿን ያጠረዉን ሽቦ እያየሁ "ቆይ ይሄን ነገር ምን እያደረግሽ ስታስቸግሪ ነዉ ዙሪያዉን ያጠሩት?" አልኳት።
ሳቀችና "እንዳሰብከዉ እንኳ አይደለም ጥርሴን ለማስተካከል ነዉ።" አለችኝ።
"ኦኬ ገጣጣ ነበርሽ ማለት ነዉ?" አልኳት።
አምሪያ የምጠቀማቸዉ ቃላት እና ድፍረቴ የሌለ እያሳቃት "እንደዛ ነገር ፣ የሆንክ አመዳም!" አለችኝ።
ጀሪካኑን ወደቤታቸዉ አስገብቼላት ልሄድ ስል አምሪ እየሳቀች "ጥጋበኛ ነገር ነህ!" አለችኝ። እየሳቅኩ "የምግብ ቤት ባለቤት ልጅ ስለሆንኩ ይሆናል!" አልኳት።
እናቴ ከአምሪያ ቤተሰቦች ጋር የሌለ ተመቻችታለች። የአምሪያ እናት ሲጀመርም ሙድ አላቸዉ። ከእማዬ ጋር ተጠፋፍተዉ የተገናኙ እህትማማቾች ነዉ የሚመስሉት። ባይሆን ያልመሰጠኝ ሙዳቸዉ መስጂድ ለምን አትሄድም እያሉ የሚያዝጉኝ ነገር ነዉ።
.
እሁድ ዕለት አንድ የፌቨን ጓደኛ ደዉላ ልታገኘኝ እንደምትፈልግ ነገረችኝና አገኘኋት። አንድ ካፌ ገብተን እንደተቀመጥን ራሷን ማስተዋወቅ ጀመረች። "ፍቅር እባላለሁ የፌቪ የልብ ጓደኛዋ ነኝ። ሜይቢ ትምህርት ቤት ልትወስዳት ስትመጣ አይተኸኝ ሊሆን ይችላል።" አለችኝ። በርግጥ ልጅቷን ብዙ ጊዜ ፌቪን ከትምህርት ቤቷ ልወስዳት ስሄድ አይቻታለሁ። ግን አልተቀራረብንም።
ቀጠለችና "ዛሬ የፈለግኩህ ያዉ አርብ እለት ከፌቪ ጋር ያወራችሁትን ፌቪ አጫዉታኝ ነበር እና የምትወዳት ከሆነ ልጅቷ ቨርጅን ስለሆነች ባለፈዉ የጠየቅካትን ነገር አሪፍ ቦታ ላይ ብታደርጉት ብዬ ላማክርህ ነዉ!" አለችኝ።
ያለችዉ ስላልገባኝ "አሪፍ ስትይ?" አልኳት።
"አሪፍ ስልህ ያዉ ለሴት ልጅ የማይረሳት ትዝታዋ ድንግልናዋን ያጣችበት ቅፅበት ነዉ። እና አሪፍ ሆቴል ኦር ሪዞርት ዉስጥ ብታደርጉት አሪፍ ትዝታ ይሆናታል። እሷ ልትነግርህ ሼም ስለያዛት ነዉ እኔ የነገርኩህ። እንደማገኝህ አታዉቅም!" አለችኝ። 
እየሳቅኩኝ "ስለዚህ በድርጊቱ ላይ ተስማምታለች አደራረጉ ላይ ነዋ ድርድሩ?" አልኳት። የዛ ቀን ኦፊሳችን ዉስጥ ማድረጉ ደብሯት ነዉ ማለት ነዉ።
እሷም እየሳቀች "አሁን በደንብ ገብቶሀል!" አለችኝ። ልጅቷን አተኩሬ አየኋት! ሙሉ ለሙሉ ጥቁር ናት። የሆነ ናይጄሪያዊ ነዉ የምትመስለዉ። ግን ደስ የሚል ነገር አላት። የፌቪ ጓደኛ ባትሆን አሰምጣት ነበር።
እዉነት ለመናገር እኔ ከፌቪ ጋር ለመተኛት ብዬ ሆቴል በሉት ወላ ሪዞርት መሄድ አልፈልግም ነበር። የተስማማሁት ጓደኛዋ ስለገንዘቡ አትጨነቅ እሷ ጋር አለ ስላለችኝ ነዉ።
.
ማታ ማታ አምስት ሰዓት ድረስ ፌቪንናየአረብ ሀገሮቹን ሴቶች በአንድነት እያዋራሁ አመሻለሁ። እናቴ እንዳትሰማኝ በፅሁፍ ብቻ ነዉ የማስተናግዳቸዉ። ሰሞኑን ከሪሜ የሚያወራት ልጅ ደሞዜን ባንክ አስቀምጥልኝ ብላ ስለላከችለት ብር በብር ሆነናል። ወር ሙሉ የለፉበትን እንዲህ ለኛ ሲያስረክቡ በጣም ነዉ የሚገርሙኝ! እንዴት ለማንም አንስተዉ የለፉበትን ይልካሉ? የሚያስቅ የዋህነት!

ክፍል 4 ይቀጥላል....
#የማይፋቅ
#ስህተት

#የልጅነትን_ፍቅሬ

የፍቅር ታሪኮች🌒

21 Sep, 11:40


#የማይፋቅ #ስህተት
#ክፍል #ሁለት
(ፉአድ ሙና)
.
ከሚኪያስ ባህሪዎች በጣሙን የሚገርመኝ ሙድ የሚፈበርከዉ ሲከለከሉ ከሰማቸዉ ነገሮች ዉስጥ መሆኑ ነዉ። ገና እንደተገናኘን "እስከአሁን በቺኮች ጉዳይ ላይ የሌለ ተበልተናል! ጥቅም የሌለዉ ስራ ነበር የሰራነዉ!" አለኝ። ደሞ ማናባቱ ፍቅረኛ መያዝ መጥፎ ነዉ ብሎት ይሆን?
በግርምት እያየሁት "እና ሄለንን ልትተዋት ነዉ?" አልኩት። ሄለን የሚኪ ፍቅረኛ ነች።
"ለምንድነዉ የምተዋት?" አለኝ።
ግራ እየተጋባሁ "እና ምንድነዉ የምታወራዉ?" አልኩት።
ሚኪ ተረጋግቶ ማስረዳት ጀመረ። "ይኸዉልህ ሀቢቤ እኛ እዚህ የትምሮ ቤት ሴቶችን ስናሯሩጥ በጣም ብዙ ገንዘብ አምልጦናል። ማታ እኮ ነዉ የገባኝ። የጎረቤታችን የጋሽ አክሊሉ ልጅ አረብ ሀገር ልትሄድ አያቴ ሲመክሯት ሰማሁ። ምን አሉ መሰለህ 'እዛ አረብ ሀገር ያሉ ሴቶችን እዚህ ቁጭ ብለዉ እያባበሉ የሚበሉ አመዳም ልጆች አሉ። እና ብርሽን ለማታዉቂዉ ሰዉ በወደድኩት ሰበብ አትላኪ!' አሏት። አያቴ አሁን ጎረቤት ከሚመክርበት ምናለ እኔን ነግሮኝ እያባበልኩ በበላሁ!? ለማንኛዉም ከዚህ በኋላ ሄለን እና ፌቪ ላይ እየተደበርን እነዛን ደሞ በፌስቡክ አሳደን ብናሰምጥና መላ ብናገኝስ?" አለኝ።
ምንም የማይወጣለት ቆንጆ ሀሳብ ነበር ያመጣዉ። ፈገግ ብዬ "ይኼማ አብነት እና ከሪሜን እራሱ ያሳትፋል። እንደዉም የቺክ ፎቢያቸዉን ይገፍላቸዋል።" አልኩት። ትምሮ ቤት እንደሄድን ከአብነትናከሪሜ ጋር ጮርናቄ የምንበላበት ሻይ ቤት ተገናኘን። ጮርናቄ በሻያችንን አዘን በደንብ ሚኪ ያመጣዉን ሀሳብ አስረዳናቸዉ። የመጀመሪያዉ ስራ አረብ ሀገር ያሉ ሴቶችን ለይቶ ፌስቡክ ላይ ጓደኛ ማድረግ ነዉ። በሀሳቡ ላይ ከተስማማን በኋላ በመሀል ሚኪ ወደኔ እየዞረ "አዲሶቹ ጎረቤቶቻችሁ ሙድ አላቸዉ?" አለኝ። ሚኪ ሌላ ሀሳብ አምጥቶ አስረሳኝ እንጂ እኮ ስለ አምሪያ መተርተር የመጀመሪያዉ እቅዴ ነበር። ወዲያዉ ማታ ስለነበረዉ ነገር እና ስለ አምሪያ በዝርዝር ነገርኳቸዉ። አብነት ኮስተር ብሎ "ይህቺን ልጅ ፎንቃ ካስጨመደድካት የዛኔ አንተን የፍቅር መምህር እንልሀለን!" አለኝ። እኔ የሚገርመኝ አብነት አንድ ቺክ እንኳ ሳይጠብስ እኔ አራተኛዬን ይዤ እልህ ሊያስይዘኝ መሞከሩ። ከሪሜን እያየሁ "ፌቪ ስትሰለቸኝ ወደ እሷ እዞራለሁ።" አልኩ። ከሪም ዝም ብሎ ያየናል።
ሚኪ ሀሳባችንን እየተቃወመ "ጎረቤት መጀንጀን እንኳ አይነፋም!" አለ።
"እሱን ለኔ ተውት!" አልኳቸዉና ስልካችን ላይ ተተክለን አረብ ሀገር የሚኖሩ የሀገራችን  ሴቶችን ማሰስ ጀመርን።
.
ከአራታችን በእድሜ የሚያንሰዉ ከሪሜ ነዉ። አስራሰባት አመቴ ነዉ ይላል። እዉነቱን ፈጣሪ ነዉ የሚያዉቀዉ! እኛ አስራ ዘጠኝ ላይ ነን። የክፍላችን የእድሜ ባለፀጋዎች እኛ ነን።  እኔ በአባቴ ሞት ምክንያት ለሁለት አመት ትምህርት አቋርጬ ነበር። ሚኪ ከመሸ ነዉ ትምህርት የጀመረዉ። አብነት ከክፍለሀገር ሲመጣ ተከልሶ ነዉ ወደ ኋላ የቀረዉ።
.
በቻልነዉ መጠን ለብዙ ሴቶች ፍሬንድሪኳየስት ላክን። እዛዉ ተጥደዉ ነዉ መሰለኝ የሚዉሉት ከግማሽ በላይ የሚሆኑት ወዲያዉ ተቀበሉን። እኔ የኔዎቹን በስማቸዉ ቅደም ተከተል እየሄድኩ መፃፃፍ ጀመርኩ። አንዳንዶቹ አይመልሱም ብዙዎቹ ግን መለሱልኝ። ተመቸኝ ፣ በደንብ መፃፃፍ ጀመርኩኝ። ክፍል ገብተን አስተማሪዉ እያስተማረ እኛ ከኋላ ቁጭ ብለን በፌስቡክ እንጀናጀናለን።
.
ዘጠኝ ሰዓት ላይ ከትምሮ እንደወጣን እኔ ፌቨንን እንደተለመደዉ ላገኛት ወደ ትምህርትቤቷ ሄድኩኝ። ደግሞ አርብ ነዉ። ቅዳሜ እሷ ትምህርት ቢኖራትም እኔ የለኝም። እሷን ብዬ እንዳልሄድ ደግሞ እናቴን ሳግዝ ነዉ የምዉለዉ። እሁድ እሷ ከቤት ስለማትወጣ አንገናኝም። ስለዚህ አርባችንን ያማረ አርብ ለማድረግ ብዙጊዜ እስከአስራሁለት ሰዓት እናመሻለን። ማምሻዉን ስንመለስ በሰፈራችን ዉስጥ ለዉስጥ እየተሽሎኮለክን ፣ጭር ያለ ቦታ ስናገኝ ደግሞ እየተሳሳምን እናብዳለን።  ፌቪ ለቤተሰቦቿ ከጓደኞቼ ጋር ነበርኩ ትላለች። እኔ እንኳ ሲጀመርም ሀይለኛ ቁጥጥር የለብኝም። ከጠየቀችኝም ያዉ ከነሚኪ ጋር ነበርኩ እላለሁ።
ዛሬ ፌቪን ገና ሳገኛት ተንሰቅስቃ ማልቀስ ጀመረች።
ቦርሳዋን እያወለቅኩላት "ኧረ ፌቪ እኔ የማስለቅስሽ ነዉ የሚመስለዉ አረጋጊዉ እንጂ!" አልኳት። ፌቪ አሁንም ለቅሶዋን አላቆመችም። አቅፌ እያባበልኳት እዛዉ ትምህርት ቤቱ አቅራቢያ ወዳለ ካፌ ሄድን። እንደተቀመጥን እንባዋን እየጠረግኩላት "በቃ ፌቪዬ አታልቅሺ! ምን ተፈጥሮ ነዉ?" አልኳት።
ሳግ እየተናነቃት "ቲቸር እያሱ ዩኒፎርም ለብሰሽ ከወንድ ጋር ስትዞሪ ታይተሻል። ለወላጆችሽ እናገራለሁ አለኝ።" አለች። ቲቸር እያሱ የነፌቪ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ነዉ።
በእጆቼ ፀጉሯን እያስተካከልኩላት "ግን ቤት አልደወለም አይደል?" አልኳት።
"አዎ እግሩ ላይ ወድቄ ስለምነዉ ሁለተኛ እንዳላገኝሽ ብሎ ማረኝ። ግን ከአስራአንደኛ ክፍል ተማሪ አይጠበቅም ምናምን ብሎ ቀወጠዉ።" አለችኝ።
"በቃ አትጨነቂ ከዚህ በኋላ ሌላ ልብስ በቦርሳ ይዘሽ መጥተሽ ስትወጪ ትቀይሪዋለሽ!" አልኳት።
ፌቪ ፊቷ በፈገግታ እየተሞላ "አሪፍ ሀሳብ ነዉ።" አለች።  በፍጥነቴ ተገርማለች። እሷን ያሰጋት ዳግመኛ የመያዙ ነገር ነበር። አሁን ቀለል አለላት።
ቀለል ሲልላት መዝፈን ጀመረች። ፌቪ ስትዘፍን በጣም ደስ ይለኛል።
.
ማታ ከእማዬ ጋር ምግብ ቤቱን ዘግተን ስንመለስ አምሪያ በራቸዉ ላይ ያለዉ የአበባ መትከያ ላይ ችግኝ ለመትከል ቦታዉን ስታመቻች ደረስን። እማዬ የያዝኳቸዉን ሰፌዶች እየተቀበለችኝ "ሂድ አግዛት በወንድ ያምራል!" አለችኝ። ትዕዛዟን ተቀብዬ አምሪያን ለማገዝ ወደነአምሪያ ቤት አጥር ሄድኩ። እናቴ ወደ ቤት ገባች። መሬቱን እያለሰለስኩ አምሪያን ቀና ብዬ አየኋትና "ሰዉ በሚገባበት ሰዓት የምትንደፋደፊዉ ጎበዝ ናት እንድትባይ ነዋ?" አልኳት። አምሪ ሳቋን ለቀቀችዉ። ትስቅና ጥርሶቿን የከለለዉን ሽቦ በከንፈሮቿ ትሸፍነዋለች።
ስቃ ስትጨርስ "ነገረኛ ነገር ነህ!" አለችኝ። የሆነ አነጋገሯ ለዛ ነገር አለዉ።
"ምን ያስደስትሻል?" አልኳት።
"መንፈሳዊ ህይወት!" አለችኝ። የሆነች የአባቷ ቢጤ ናት። ለማስመጥ ማገዶ እንደምትፈጅ አሰብኩ።
"እና ፍቅረኛ የለሽማ!" አልኳት።
ፊቷን እየጨመደደችዉ "የለኝም ምነዉ አንተ አለህ እንዴ?" አለችኝ።
"ኧረ የለኝም ነገሩን ነዉ እንጂ!" አልኳት።
አምሪያ በግርምት እያየችኝ "ግን በጣም ደፋር ነህ!" አለች። ቀጠለችና "ማለቴ በህይወትህ ለሁለተኛ ቀን ያገኘኸዉን ሰዉ ስለፍቅረኛዉ መጠየቅ አይከብድም?" አለችኝ።
እየሳቅኩ "ባክሽ የፍቅር ጥያቄ መጠየቅ ራሱ አይከብድም!" አልኳት። 
አምሪ ራሷን መቆጣጠር እስኪከብዳት ድረስ ሳቀች።
አባቷ ከቤት ሲወጡ እኛ አበባ እየተከልን ነዉ። አዩንና ፈገግ ብለዉ "ጎበዞች! ዛሬ መልካም ነገር ከዘራችሁ ፣ ነገ የምታጭዱትም መልካም ነገርን ነዉ። መጥፎ ከሆነም በተመሳሳዩ!" አሉና በሩ ላይ ቆሞ የነበረዉ መኪናቸዉ ዉስጥ ገቡ። እሳቸዉ እንደሄዱ ጨርሰን ስለነበር ከአምሪያ ጋር ቦታዉን አፀዳድተን ተሰነባበትን። ስንለያይ አምሪያ የቤታቸዉን በር ከዉስጥ ሆና ይዛ "ስማ ሀቢቤ!" አለችኝ።

የፍቅር ታሪኮች🌒

21 Sep, 11:40


እየዞርኩ "ወዬ" አልኳት።
"ትንሽ መሬት ያዝ! ተረጋጋ እሺ!" ብላኝ እየሳቀች በሩን ዘጋችዉ።
.
ቅዳሜን ከእናቴ ጋር ስንደፋደፍ አሳለፍኩት። ምግብ ስሰራ በጣም ጎበዝ ነኝ። ሴት አስንቃለሁ። እሁድን ከሚኪ ጋር አሳለፍን። አምሪያን ቅዳሜም ሆነ እሁድ አላየኋትም። ሰኞ በጣም ብዙ የምስራቾችን የምንሰማበት ቀን እንደሚሆን ተስፋ አድርጌያለሁ። ገና እንደተገናኘን ሚኪ ለሻይ ቤቷ አስተናጋጅ ስምረት ጮርናቄ እና ሻያችንን ካዘዘልን በኋላ "ኧረ ይሄን ሁለት ቀን ጉድ ነዉ ያየሁት!" አለ። አብነት እንደ እብድ ዝም ብሎ ብቻዉን ይስቃል።
"ምን አየሽ ሚኪ?" አልኩት ወደሱ እየዞርኩ። በፌስቡክ አረብ ሀገር ያሉ ሴቶችን ተዋዉቆ ሁለቱ ስልኩን ጠይቀዉት በዋትሳፕ ደዉለዉ እንዳወሩት ነገረን።
ሚኪያስ "ኧረ ሙቀቱ ይሁን እኔንጃ ብቻ የሌለ ነዉ ፍልት ያለባቸዉ። የአዳም ዘር ከሆንክ የሚምሩህ አይመስለኝም። አንዷ የሌለ ነዉ በአንዴ ጠብ ያለችልኝ። በስሜት ሁሉ አቃሰተች።" አለ።  እኔም መስመር ስለያዙልኝ ሶስት ሴቶች ነገርኳቸዉ። ከሪሜ አልቀናዉም። አብነት ግን አሁንም ብቻዉን እንደእብድ እየሳቀ ነዉ።
ሚኪ እያፈጠጠበት "ምናባህ ያንተከትክሀል?" አለዉ።
አብነት ስልኩን ከፈተና ራቁቷን ያለች ሴት ምስል አሳየን። ሁላችንም ተቀባብለን አየነዉ።
"እናላችሁ በአንድ ሳምንት ዉስጥ ብር እልክልሀለሁ ብላለች!" አለን። በሶስት ቀን ራቁት ፎቶ ማስላክ የሚደንቅ ነዉ።
.
ከአስራአምስት ቀን በኋላ ለሶስታችን አረብ ሀገር ከሚኖሩ ሴቶች ገንዘብ ተላከልን። የመጀመሪያዉ እቅዳችን አንድ የምንደበርበት ቤት መከራየት ነበር። ከሰፈር ራቅ ብለን ተከራየን። ኦፊስ እንለዋለን። ቤቱን ተከራይተን አንዳንድ ወሳኝ ነገሮችን እንዳሟላን ሚኪ ፌቨንናሄለንን እዚህ አምጥተን አብረናቸዉ እንድንተኛ ሀሳብ አቀረበ። የሰሞኑ እቅዶቹ ደስ የሚሉ ናቸዉ። ሄለንና ፌቨንን ለማሳመን ተነጋግረን ተለያየን።
ከሪሜ ምንም የአረብ ሀገር ሀበሻዎችን ባያሰምጥም አንዷን እየጀነጀናት 'በቪዲዮ ኮል' ሲያወሩ የዋህ የሚመስል ፊቱን አይታ ደሞዟን ባንክ እንዲያስገባላት በየወሩ ልትልክለት ተስማሙ።
የገልፍ ሀገራትን የተቆጣጠርን ያህል ደስ አለን።
አሁን ወሳኙ ነገር ፌቨንን አብረን እንድንተኛ ማሳመኑ ነዉ።
.
ክፍል 3 ይቀጥላል...


#የማይፋቅ
#የልጅነት_ፍቅሬ
#ስህተት

@ye_fkr_tarikoche

የፍቅር ታሪኮች🌒

20 Sep, 22:46


ፈልጌ

ሳይሆን ፌስቡክ ላይ ልፈልጋት ስላሰብኩ ነዉ።
ታጥቤ እየተመለስኩ ቆም አልኩና "ወንድም ምናምን የለሽም?" አልኳት። "ሶስት አሉኝ። ሳሎን ያሉት ሁለቱ ወንድሞቼ ናቸዉ። አንደኛዉ ልጁ ታማ ሄዷል። ሶስቱም አግብተዉ ወጥተዋል።" አለችኝ። የቤቱ ታናሽ መሆኗ ነዉ እንግዲህ! ለዛሬ ከበቂ በላይ መረጃ እንደሰበሰብኩ አሰብኩ። ነገ ለነሚኪ ይተረካል። ሳሎን ገብቼ በልተን ከጨረስን በኋላ አባቷ የጥያቄ መዓት አወረዱብኝ። ብዙዉ የሀይማኖት ትምህርት ለምን እንዳልተማርኩ ምናምን ነዉ። ሲጠይቁኝ ስወዛገብ አለመማሬ ገባቸዉ መሰለኝ። ሰዉየዉ ሀይማኖተኛ ነገር ናቸዉ።
ፌቪ አስሬ ትደዉላለች። ስልኬን ዘጋሁት። ደሞ በመጀመሪያ ቀን ልጠቆር እንዴ?
.
ሰዉየዉ አንድ በአንድ ሳሎን የነበሩትን ልጆች ካስተዋወቁኝ በኋላ አምሪያን ጠርተዉ ሰፈሩን እንዳላምዳት አደራ አሉኝ። ተመስገን! እንኳን አደራ ተብዬ ወትሮዉንም እንዲሁ ነኝ። አንገቴን ስደፋ ምንም የማላዉቅ መስያቸዋለሁ።
.
ከነአምሪያ ቤት እንደወጣሁ ፌቨን ጋር ደወልኩ። ፌቪ በጣም ተጨንቃ ነበር። ሁሌም ከሶስት ሰዓት በኋላ ስለምናወራ ስልክ አላነሳ ስላት ደንግጣለች። ድንጋጤዋ ሲበርድላት "አንድ አንድ እንዝፈን!" አለችኝ። ፌቪ ስዘፍን ድምፄን ትወደዋለች። አንድ አንድ ተዘፋፍነን ስልኩን ዘጋሁት።
ቤት ከገባሁ በኋላ አምሪያን ፌስቡክ ላይ አሰስኳት። መጨረሻ ላይ አንድ ፎቶ የሌለዉ አካዉንት የሷ ይሆናል ብዬ ገመትኩና ሪኳየስት ላኩኝ። ወዲያዉ ተቀበለችኝ። ትንሽ እንዳወራኋት እሷ አለመሆኗን አወቅኩ። ተበሳጨሁ።
.
ልተኛ ስል ሚኪ ደወለ "ኧ ሚኪ" አልኩ ስልኩን አንስቼ
"ሀቢቤ ያበደ እቅድ አለ ቸከሶቹን በተመለከተ! አሁን አያቴ ሰዉ ሲመክር ሰምቼ ነዉ። ጠዋት በሰፊዉ እተነትንልሀለሁ።" አለኝ። ሚኪ የሌለ ጓጉቷል። እኔም እስኪ ይንጋና ለነሚኪ ስለ አምሪያ ልተርተርላቸዉ።
.
ክፍል 2 ይቀጥላል...

#የማይፋቅ
#ስህተት
#የልጅነት_ፍቅሬ
@ye_fkr_tarikoche

የፍቅር ታሪኮች🌒

20 Sep, 22:43


#የማይፋቅ #ስህተት
#ክፍል አንድ
(ፉአድ ሙና)
.
የጠዋቷ ፀሀይ በየት በኩልም እንደወጣች እንጃ! ተፈጥሮን የማድነቅ ልምድ የለኝም። ብቻ ዋናዉ ነገር መዉጣቷ ነዉ። እኔም ሰዉነቴ ላይ የተለጠፈ የሚመስለዉን ስኪኒ ዩኒፎርሜን ለብሼ ፣ፀጉሬን ፈርዤና አንድ ደብተር አንጠልጥዬ ወደ ትምህርት ቤት እሄዳለሁ። እንደሌላዉ ተማሪ ቦርሳ ሙሉ ደብተርና መፅሀፍ ተሸክሞ መሄድ በጣም ነዉ የሚሸክከኝ። ቦርሳ የያዙ ልጆችን ሳይ ፋራ ነዉ የሚመስሉኝ። እነሱ ቦርሳ እየተሸከሙ እኔ በወጉ እንኳ ሳልፅፍ ይኸዉ ኩረጃ ዕድሜዉ ይርዘምና አስራአንደኛ ክፍል ደርሻለሁ። ጓደኞቼ አብነት ፣ ሚኪያስ እና ከሪም ይባላሉ። የትምህርት ቤታችን ጭሶች እኛ ነን። እኔ ፍቅረኛ ሳይኖረኝ አንድ ለሊት ካለፈ በጣም ነዉ የሚደብረኝ። ከአንዷ ጋር ስደባበር ሌላኛዋን ወዲያዉ ጠብ አደርጋታለሁ። ሚኪያስም የኔ ቢጤ ነዉ። ከሪም እና አብነት ግን የኛን ወሬ ከመስማት እና በአለባበስ ከመመሳሰል በዘለለ ብዙም ቺክ ማዉረድ አይቀናቸዉም። "ያለሙያችን አንገባም!" ይላሉ። እኛም የቺኮቻችንን ጓደኞች ልናስበላቸዉ እንሞክራለን። ግን እስካሁን አልቀናቸዉም።
.
ጠዋት አስራሁለት ሰዓት እንደደረሰ የማዉቀዉ እናቴ ቤት ዉስጥ መንጎዳጎድ ስትጀምር ነዉ። "ሀቢቤ ተነስ መቼስ ገና እስክትኳኳል መከራ ነዉ!" አለች። እኔ አልጋ ላይ ተጋድሜ በፌስቡክ ከፌቨን ጋር እጀናጀናለሁ። ፌቪ አዲሷ ፍቅረኛዬ ናት። ሁሌም ጠዋት ጠዋት እናቴ ለሊት የጋገረችዉን እንጀራ ከቤታችን ትንሽ ራቅ ብሎ ያለዉ የላስቲክ ምግብ ቤቷ ሳላደርስላት ወደ ትምህርት ቤት አልሄድም። አባቴ ከሞተ በኋላ በቻለችዉ ሁሉ እኔን ለማኖር ትለፋለች። ቤታችን ቢሸጥ ብዙ ብር የሚያወጣ ቢሆንም እማዬ "የከማሌን ማስታወሻ አልሸጥም!" ብላ ግግም አለች። ከማል የአባቴ ስም ነዉ። ያለኋት ልጅ እኔዉ ብቻ ስለሆንኩ በቻለችዉ መጠን ከማንም እንዳላንስባት ትጥራለች። የምይዘዉ ስልክ ፣ ልብሶቼ እና ኪሴ ዉስጥ የሚገኘዉ ብር የላስቲክ ምግብ ቤት ያላት እናት ያለችኝ አይመስልም። ለኔ ያላትን ከመስጠት ወደ ኋላ ብላ አታዉቅም። እናቴ ሁሌም "ሱስ የሚባል ላይ ትወድቅና አይኔን አታያትም!" ብላ ስለምታስፈራራኝ ሱስን በሩቁ ነዉ የምሸሸዉ። ጓደኞቼም እኔን ስለሚከተሉ ሱስ ሰፈር የሉበትም። ምድር ላይ ሁሉ ነገሬ እናቴ ናት። በጣም እወዳታለሁ። አዛኝ እምቢ ማለት ይከብደኛል። እየተነጫነጭኩም ቢሆን ያለችኝን እፈፅማለሁ።
.
ከአልጋ ላይ ተነስቼ ከተጣጠብኩና ፀጉሬን ከፈረዝኩ በኋላ ደብተሬን እናቴ ይዛልኝ፣ እንጀራዉን ፍሪዜ እንዳይበላሽ በእጆቼ አየር ላይ ተሸክሜ ወደ ምግብ ቤት አድርሼ ፤በዛዉ ሚኪያስን ጠርቼዉ ወደ ትምህርት ቤት ሄድኩ። አብነት እና ከሪሜ እኛ ሰፈር ስላልሆኑ ትምህርት ቤት ነዉ የምንገናኘዉ። ከክፍላችን ተማሪዎች በእድሜ ትንሽ ከፍ የምንለዉ እኛ ነን። ሰልፍ እስኪያልቅ ድረስ ዉጪ ላይ ያለዉ ሻይ ቤት ጮርናቄ በሻይ እየበላን እናረፍዳለን። ሰልፍ ሲያልቅ እንገባለን። ሚኪ ከቺኩ ጋር ሲዛዛግ ይቆይና ካሰናበታት በኋላ አብረን እናሳልፋለን። ከትምሮ ስንለቀቅ የኔዋ ፌቨን ከኛ ትምህርት ቤት አቅራቢያ ያለ የግል ትምህርት ቤት ስለምትማር አብሬያት እስከ አስራአንድ ሰዓት ቆይቼ ሸኝቼያት ወደ ቤት እመለሳለሁ። እኛ የምንማረዉ የመንግስት ትምህርት ቤት ነዉ። 
.
ፌቨን እዉነት ካወራን ቆንጆ አትባልም። ግን የሆነ የደስ ደስ አላት። ቅብጥብጥ ትላለች። ከሷ ጋር ፍቅረኛ ከሆንን ወር አልፎናል። ጓደኞቼ ፌቨንን ጠብ ሳደርጋት የሌለ ነዉ የኮሩብኝ። ምዕራባዊያንን ያንበረከክኩ ያህል! እሷ ትንሽ የሀብታም ልጅ ነገር ስለሆነች ጓደኞቼን ሳይቀር ትጋብዛቸዋለች። እዉነቱን ለመናገር ግን ከሶስት ወር በላይ ከአንድ ሴት ጋር መቆየት አይሆንልኝም። ከዚህ በፊት ሶስት ሴቶች ፍቅረኛዎቼ ሆነዉ ነበር። ሰላማዊት ፣ ሜሮን እና ሰሚራ ይባላሉ። ከሰላም እና ከሰሚራ ጋር ተኝቻለሁ። ከተዉኳቸዉ በኋላ ሁለቱም በጣም ተጎድተዋል። ሜሮን ስትገግምብኝ ነዉ የጫርኳት። ከዛ በኋላ ምን ትሁን ምን አላዉቅም። ብቻ ግን ከፍቅር ግንኙነቶች መቋረጥ በኋላ በጣም የሚጎዱት ሴቶቹ ናቸዉ። ሁለ ነገራቸዉ ብልሽትሽት ነዉ የሚለዉ።
.
ከፌቨን ጋር ዛሬ ከተገናኘን በኋላ አንድ ሰፈራችን ዉስጥ ደፍሬ ገብቼ ወደማላዉቅበት ካፌ ወሰደችኝ። ካፌዉ ግርማ ሞገስ አለዉ። ገብተን አንዱ ጥግ እንደተቀመጥን ፌቪ አይን አይኔን እያየች "የእዉነት ትወደኛለህ?" አለችኝ። ወዲያዉ ፈገግ ብዬ "አንቺን አለመዉደድ እንዴት ይቻላል?" አልኳት። ምላሴ እኮ ጤፍ ይቆላል።
"ግን እኮ እኛ ትምህርት ቤት ስላንተ ደስ የማይል ነገር ይወራል።" አለችኝ።
"ምን?" አልኳት ትኩር ብዬ እያየኋት
ፍርሀት አይኖቿን እኔን ከመመልከት እየሰበራቸዉ "ሴት አሯሯጭ ነዉ ፣ ብዙ ሴት ያተራምሳል! ምናምን" አለችኝ።
እንደመቆጣት እያልኩኝ "እሱ ትናንት ነዉ። ዛሬ አንቺ መጥተሽ ህይወቴን ሙሉ ለዉጠሽዋል። ተስተካክያለሁ። አታምኚኝም እንዴ?"  አልኳት።
ፈጥና እጆቼን በእጆቿ ጭምቅ እያደረገች "ኧረ አምንሀለሁ። ተዋቸዉ በቃ!" አለችኝ። የፌቪ ፍቅር ሁሉ ነገሯ ዉስጥ ይታያል። ጀንጅኜ ያሰመጥኳት እኔዉ ነኝ ግን እሷ ፎንቃዬ የሌለ ገብቶላታል። ፌቪ ስትዘፍን ድምጿ በጣም ያምራል። ብዙ ጊዜ ደዉላ ትዘፍንልኛለች። የልቧን የምትነግረኝ በዘፈን ነዉ። ዛሬም ዘፈነችልኝ። ድምጿ ዉስጥ የሆነ ለቅሶ አለ። እንዳታጣኝ ሰግታለች።
.
ከካፌዉ እንደወጣን ቦርሳዋን ይዤላት እያወራንና በየመሀሉ እየዘፈነችልኝ ወደ ቤቷ ሸኘኋት። ከሷ ጋር ስጨርስ ሚኪ ጋር ደወልኩለት። ፑል ቤት እየተጫወተ እየጠበቀኝ ነበር። ተገናኝተን ወደ እማዬ ምግብ ቤት ሄድን። እማዬ ምግብ ካቀረበችልን በኋላ "ከኛ ቤት ጎን የተሰራዉ ትልቁ ቤት እኮ ተሸጠ። ዛሬ ሰዎቹ ገቡበት።" አለችን።
እኔና ሚኪ ትምህርት በመሄዳችን እቃ አዉርደን የምናገኘዉን ብር ስላጣን ተበሳጨን። ለነገሩ ጎረቤት መቦጨቅ ደሞ አይነፋም። እማዬ ለሌላ ተስተናጋጅ ምግብ እያቀረበች "ደሞ ጥሩ ሰዎች ይመስላሉ። ሰዉየዉ ቁልፉን እንድሰጣቸዉ ደዉለዉ ሄጄ አይቻቸዉ ነበር።" አለች። እማዬ ቤቱ እስኪሸጥ ደላላ ሲመጣ እንድታሳይ አደራ ተብላ ቁልፉ እሷ ጋር ነበር።
.
ማታዉን እናቴ ቡና አፍልታ አዲሶቹ ጎረቤቶቻችን ጋር ሄድን። እኔ እንኳ ጀበናዉን እና ሽንብራዉን አድርሼላት ለመዉጣትና ከፌቪ ጋር ፌስቡክ ላይ ለመጀናጀን አስቤ ነበር። ሰዎቹ ጋር ስናንኳኳ አንድ ጠይም የሆነች፣ ረዥም ቀሚስ የለበሰች፣ ሂጃብ የጠመጠመችና ጥርሷ በብሬስ የታሰረ ወዛም ልጅ በሩን ከፈተችልን። እቃ አድርሶ የመመለሱን ሀሳብ ሰረዝኩት። ይህቺን የመሰለች ልጅ ያለችበት ቤት መቀመጡ ራሱ ደስ ይላል። እኔ ሴት ላይ ችግር አለብኝ። ያየሁት ሁሉ ያምረኛል። ለነገሩ ይህቺ እንኳ ትገባኛለች። የሰፈሬን ሴትማ ማንንም አላስበላም። እማዬ ሴቶቹ ጋር ገባች። እኔን ልጅቷ ወደ ሳሎን ወሰደችኝ።
ሳሎን ስገባ ምግብ ቀርቦ ነበር። አንድ ሸምገል ያሉ ሰዉዬ ስገምት አባቷ ይመስሉኛል "አምሪያ እጅ መታጠቢያዉን አሳይዉ ይቀላቀለን!" አሉ። አሀ ስሟ አምሪያ ነዉ ማለት ነዉ አልኩ በልቤ። ምናለ ስልኳንም በዛዉ ቢጠሩት። ፈገግ ብላ መታጠቢያ ቤት ወሰደችኝ። እየታጠብኩ "ስንተኛ ክፍል ነሽ?" አልኳት። ድፍረቴ ሳይገርማት አይቀርም። "ከወር በኋላ ኢንትራንስ እፈተናለሁ። አስራሁለተኛ ክፍል ነኝ።" አለችኝ በትህትና። ስለራሴ ትንሽ ነገርኳትና የአባቷን ስም ጠየቅኳት። "ራህመቶ" አለችኝ ፈገግ ብላ። ልጅቷ ፈገግታ ታበዛለች።  እኔ የአባቷን ስም የጠየቅኳት አባቷን መተዋወቅ

የፍቅር ታሪኮች🌒

20 Sep, 22:37


Channel photo updated

የፍቅር ታሪኮች🌒

20 Sep, 22:22


የልጅነት ፍቅሬ


     ክፍል 4

የደሬክተሩን ድምፅ ስንሰማ በመስኮት ዘለን ከክላስ ወጣን እየተሰሳቅን የት/ቤቱ አጥር ስር ደራስን አንድ ኢንጊልሽ አስተማሪ በመስኮት ስንወጣ አይቶን ነበር እናታ ዱርዬዎች ኑ ሲለን በአጥር ስር ሾልከን ወጣን ቤት ከሄድን ቤታሰብ ስለ ሚጠይቀን ተስቲ የሆነች ልጅ ገር ለምን አንሄድም ብሎኝ እሺ ብዬው አንድ ለይ ሄድን ልጅቶ ቤቶ  ድረስ ሄደን የሆና ድንገይ ለይ ቁጭ ብለን ጠበቅናት። እ ተስቲሻ ልጅቷ አትመጣም እንዴ ምን አናት እንደሆች ለማየት ጓግቼለው አልኩት ። አረ ብሮዬ ዝም ብለሽ እይው የበደ እቃ ነው አለኝ። ብዙ ከወራን ቦሃላ ልጅቶ ከቤት ውስጥ ወጣች። ይሄው ወጣች አለኝ።ልጅቶ ሺቲ ለብሳ እያሳቀች ወደኛ መጣችና ተስቲ ለይ ጥምጥም አለችበት ። ከዛን እጁን ገፍትራው አንታ እንደውም አታዋራኝ አለቺው ። ለምን ዉዴ አለት ። ስንት ቀን ሙሉ ሰደውልለኝ ስልክህንም

ክፍል 5 ይቀጥላል....
ደራሲ @farhan_ozil
#የማይፋቅ
#ስህተቴ
#የልጅነት_ፍቅሬ
@ye_fkr_tarikoche

የፍቅር ታሪኮች🌒

27 Jul, 00:41


Channel name was changed to «የፍቅር ታሪኮች🌒»

የፍቅር ታሪኮች🌒

04 Nov, 19:22


የልጅነት ፍቅሬ

ክፍል-ሶስት

ደራሲው ፈርሐን
ሁሉም በሰቅ ፈነዱ እኔ ልጅቶን እያየዋት ነበርኩኝ ትስቃለች ስትስክ በጣም ነው ምታምረው ልቤን በአንድ ቀን በአንድ እይታ ወሰደቺው ልጅቷ ወደ እኔ እያየች ትስቃለች በቃ እኔ ደስ አለኝ በዚ መሃል አስተማሪዋ በቃ በቃ ይበቃል አለችን ልቤን የሰረቀችኝ ልጅ ፊትለፊቴ ቁጭ ብለ ትስቃለች ፈገግታዋ አንደኛ ነው እንደምንም ብዬ የመጀመሪያ ቀን ክለስ እንደዛ አለፈ በትንሽ ግዛቶች ውስጥ ከሁሉም ተማሪዎች ገር ተግባበዉ ግን ከሁሉም በለይ እኔና ተስቲ በጣም ተቀራረብን ክለስ ውስጥ አንድ ለይ ነው ምንቀመጠው እንደ እኛ ረበሽ ተማሪ አልነበረም ክለስ ስንቀጣም አንድ ለይ ነው ምንቀጣው አስተማሪዎች በማስቸገር ት/ቤት ለይ ፈምሰናል የሆነ ቀን ክለስ ውስጥ ባዮሎጂ አስተማሪ ኖት እያፃፈች ነበር እኔና ጎደኛዬ ኖት እያፃፍን አይደለም ሲደብረን ተደብቀን ተማሪዋችን በቿክ መምታት ጀመርን ብዙ ልጆችን መታን ግን አንድም ሰው አለየንም ምክኔቱም ከሁሉም ተማሪዎች መጨረሻ ለይ ስለ ምንቀመጥ አሁን እኔ የሆነች ጎበዝ ተማሪ መዲና ምትበለዋን ልጅ ልመተት ብዬ ቿኬን አንስቼ ወረወርኩት ልጅቶን አልፎ የአስተማሪዋን መቀመጫ ለይ መተዋት አስተማሪዋ እንዴት እንደ አዞረች የምር የስደነግጣል መን ነው የመታኝ አለች ሁሉም ተማሪወች ዝም አሉ እያጮሀች ስጠይቀንም ዝም ሁሉም አስተማሪዋ እኔ እዚ ክላስ አላስተማረም ብላ ስትወጣ ሁሉም ተማሪዎች ይጮሃሉ በኛ ምክኔት ክላሱን ለቃ ወጣች ያሆና እንደ አለቃ ሚያረገው አቃጣሪ ተነስቶ እኛ ሁሌም በሁለታቹ ምክኔት ትምርት አንማርም እንዴ ቆይ ለገሽ ብራኑ ነግረለው ብሎ ሊወጣ ስል ሂድና አቃጥር ማቃጠር ስራክ አይደል ብለነው እሱ ሲወጣ እኛ ትንሽ ቁጭ ብለን የዳሬክተሩን ድምፆ ስንሰማ በመስኮት ዘለን ከክለስ ወጣን።

ክፍል 4 ይቀጥላል .........
#የማይፋቅ
#ስህተቴ
@ye_fkr_tarikoche

የፍቅር ታሪኮች🌒

20 Oct, 20:13


የልጅነት ፍቅሬ

ክፍል-ሁለት

ደራሲ ፈርሐን

አይኔን ከልጅቷ መንቀል አቃተኝ ግን ትንሽ ቆይቶ አስተማሪዋ ቦታ አስተካክሉ ብለን ሁላችንም ከመቀመጫችን ተነሳን አስተማሪዋ በgroup እያስቀመጠችን ነበር እንደ ድንገት እኔና እሷ አንድ group ደረሰን በጣም ደስ አለኝ ያእሷን በላውቅም እኔ ልቤ የፈነዳ ደረሰ እኔ ግን በተፈጥሮዬ ስሜቴን መደበቅ እችላለሁ ብቻ እሷ እንደት ነቃብኝ ብዬ ስሜቴን ደበኩኝ group5 ነው የደረሰን እኛ አጠቃላይ 6 ነን የልጅቶ ስም ሐምዲያ ትበላለች እሷ ከአንደኛዋ ገር ተቀመጠች እኔ ደሞ ከሖነ ተስቲ ሚበለው ልጅ ገር ቁጭ አልን class ውስጥ አዲስ ተማሪ ስለ ነበርኩ አስተማሪዋ ራስህን አስተዋወቅ አለችኝ እኔም ተነስቼ ፈርሓን አ/ጀበር እበላለሁ አልኩኝና ግን ሰንቼዝ ብለሽ ብጠሪኝ ደስ ይለኛል ቲቸሪዬ እንደአልኳት ተማሪዎች በሙሉ ሰቁ
አስተማሪዋም ስቃ እሺ ሰንቼዝ አሪፍ ስም ነው አለችኝ
ክፍል ሶስት ይቀጥላል .......

የፍቅር ታሪኮች🌒

16 Oct, 21:04


ዛሬ የምነግራችሁ እውናታኛ ታሪክ ነው።

የልጅነት ፍቅሬ
ደራሲ ፈርሐን አ/ጀባር
ክፍል 1
ተወልጄ የደኩት ሐረር ከተማ ነው ግን father የሻሸመኔ ልጅ ነው ትምህርቴን እስከ 3ተኛ ክፍል እዘው ሐረር ነው የተማርኩት ከዛን በአባቴ ምክኔት ወደ ሻሸመኔ ገባን ግን እኔ ሻሸመኔ የቆዩት ለ4 አመት ብቻ ነው ወደ ሐረር አያቴ ቤት ተመለስኩኝ ታሪኩ ሚጀምራውም ከዚ ቡሓለ ነው ጊዜው ትምርህት ሊከፈት ትንሽ ቀናቶች ብቻ ቀርተዋል እና እኔም ከልጅናት ጎደኞቼ ገር በጉጉት እየተጠባበቅን ነበር አልደረስ የለ ቀን ደረሰ እና ወደ class ገበሁኝ የልጅነት ጎደኞቼ አንደኛው 7ኛ ክፍል ነው ሁለተኛው ግን እንደኔው 8ኛ ክፍል ቢሆንም ግን አንድ ክፍል አልደረሰንም ነበር እኔ 8B ሲደርሰኝ እሱን ግን 8A ነበር የደረሰው ት/ቤት ገር ስንደርስ ትንሽ አርፍደን ነበር እኔ ወደ class ስገባ ኢንግልሽ አስታሪ እያስተማረ ነበር በሩን አንኳክቼ ገባሁኝ ተማሪዎች ሙልት ብለዋል ግማሹ የት/ቤት ዩኒፎርም ለብሰዋል የተቀሩት ግን የተለያዩ ልብስ ለብሰዋል እኔ ስገባ ማንንም ስለማለውቅ ዝም ብዬ ወደኋላ ሄጄ ቁጭ አልኩኝ ልክ ቁጭ እንደ አልኩኝ አይኔ ማመን አቅቶታል በጣም ደስ የምትል ልጅን አየው
ክፍል 2 ይቀጥላል።

የፍቅር ታሪኮች🌒

02 Oct, 19:32


🌺የድሀ ልጅ ፍቅር
🌸ምዕራፍ ሁለት ክፍል 25
🔥የመጨረሻ ክፍል🔚
ሜላትን ከስራ ስትወጣ ጠብቄ ተከትያት ሄድኩ ሆቴል ውስጥ ከሴቶቹጋ ተደባልቃ ስትጠጣ ወደ እሷ ተጠግቼ ሰላም ካልኳቸው በኃላ ...የሜላት በቁጣ እኔን ማየት የሴቶቹን ማፍጠጥ ሳይ የመጣሁበትን መናገር ጀመርኩ...
ሁሉም ዝምታን መርጠዋል ያጨሳሉ ይጠጣሉ...ሜላት በእውነት ብትዝናኚ ምንም አይመስለኝም ግን ከማን ጋ እየተዝናናሽ እንደሆነ አላወቅሽም አልኳት ...ምን ማለት ነው አለችኝ? ስለ ሴቶቹ ምንነት በደንብ ነገርኳት ሴቶቹ ደነገጡም ተናደዱ ምን አገባህ አሉኝ...ግን እኔ ሚስቴን ከእነሱ መንጋጋ ውስጥ ማውጣት ስለነበረብኝ ሁሉንም ምን እንደሚሰሩ ነግሪያት እሷም ከእነሱ ጋር ከቀጠለች ትዳራችን እንደሚያበቃለት ነግሪያት ደህና እደሩ ብዬ ወደ እናቴ ቤት ሄድኩ....
ሜላት እንደዛ ካልኳት በኃላ ወደ ቤቷ ተመልሳ ነገሮችን እንዴት ማስተካከል እንዳለባት እንደምታስብ እርግጠኛ ነበርኩ...ምክንያቱም ሳታውቅ ዝም ብላ ነበር ጏደኛ ያደረገቻቸው..... በሳምንቱ ስራ ውዬ ድክም ብሎኝ ወደ ቤት እየተመለስኩ እያለ ስልክ ተደወለልኝ አነሳሁት ሜላት ታማለች እቤት ቶሎ ድረስ የሚል ድምፅ አሰምተውኝ ስልኩ ተዘጋ...በጣም ደነገጥኩ ወደ እናቴ ቤት መሄዴን ትቼ ወደ እኛ ቤት በፍጥነት መንዳት ጀመርኩ ብዙ ነገር እያሰብኩ ነበር......
እቤት ደርሼ በሩን ከፍቼ ስገባ ግን የጠበቀኝ ነገር ሌላ ነበር የሜላት ቤተሰቦች እናቴ ቅዱስ ወንድሜ በአንድ ላይ ተሰብስበው አገኝኃቸው ..ሜላቴስ አልኳቸው ..ሜላት ከመኝታ ክፍል ወጣች ..ጉልበቴ ላይ ወድቃ ይቅርታ ጠየቀችኝ ..በዛውም የ 3 ወር ነፍሰጡር እንደሆነች ነገረችኝ ይቅርታዋን ተቀበልኩ እናቴንም ይቅርታ ጠየቀች ...
እናቴ ምንም እንኳን ይቅርታዋን ብትቀበል ተመልሳ ግን አብራን መኖር እንደማትችል ነገረችን እሽ አልን ምክንያቱም ድጋሚ ሌላ ፀብ እንዲፈጠር ስላልፈለግሁ ነበር በእናቴ ሀሳብ የተስማማሁት ...በጣም ደስ የሚል ምሽት አመሸን ፍቅራችን ወደ ድሮው ተመለሰ ...ቅዱስን የምትንከባከብ ሞግዚት ፈልገን አመጣን ..ስራ ከስራ እቤት መዝናናት ስንፈልግም አብረን ቤተሰብ መጠየቅ ብንፈልግም አብረን ..በቃ ሁሉም ድርጊታችን አንድ ላይ በመመካከር የተሞላ ሆነ.....
ቅዱሴም እጅግ በጣም ደስተኛ ሆነ ሌላ ልጅ እህት ሊወለድ እንደሆነ ስላወቀ እሱም ደስተኛ ነው ፍቅራችን ወደ በፊቱ ተመልሶ ቤታችን የደስታ ቤት ሆኗል ...ፍቅር መጣላት መኮራረፍ ..በቃላት አለመግባባት..ሊኖረው ይችላል ግን ከሁሉም በላይ ትዕግስት ይጠይቃል ..ከሁሉም በላይ ግን ""ፍቅር ያሸንፋል"
ተፈፀመ🔚
ፍቅር በገንዘብ ወይም በጌጣጌጥ ልንገዛው አንችልም ፍቅርን መግዛት የምንችለው በፍቅር ብቻ ነው ..ፍቅር ይበልጥ የሚጥመው በድህነት ሲሆን ነው."ድሀ ሲሰራ እንጂ ሲያፈቅር አያምርበትም""የሚባለው ሙሉ ለሙሉ ውሸት ነው እንዲያውም ድሀ ሲያፈቅር በጣም ነው የሚያምርበት "" ፍቅር ያሸንፋል"" ሁላችንንም የፍቅር ሰው ያድርገን ..ስለተከታተላችሁኝ አመሰግናለው በሌላ ታሪክ እስከምንገናኝ መልካም ቆይታ አስተያየታችሁ አይለየኝ,

ሌላ ታሪክ ቶሎ እንዲለቀቅ ላይክ እና ሼር ያድርጉ❤️🙏
:*:*••••••🌸:*:*🌹:*:🌸•••••••
┄┄┉┉✽̶»̶̥🌹🌹»̶̥✽̶┉┉┄┄

@ye_fkr_tarikoche

የፍቅር ታሪኮች🌒

02 Oct, 19:31


💔የድሀ ልጅ ፍቅር❣️
🌺ምዕራፍ ሁለት
...........ክፍል 24
ሜላት የቅዱስን መኝታ ክፍል መግባት ተከትላ .ከእናትህ ቤትና ከእዚህ ቤት አንዱን ምረጥ ብላ ስትጮህብኝ ቅዱሴ የመኝታ ቤት በር ላይ ቆሞ ይሰማ ነበረ ...ሳየው ደነገጥኩ ...ሜላትም አየችው .ቅዱሴ ወደ መኝታ ክፍል ገብቶ ቁጭ አለ ተከትዬው ገባሁ .ሊያናግረኝ አልፈለገም... ሜላትም መጣች .እሷንም መልስ ሊሰጣት አልፈለገም....
ቅዱስ አኩርፏል ስንጨቃጨቅ አይቶን አያውቅም ሜላትም ስሜቷን መቆጣጠር አቅቷት ስለነበር በደንብ ተቆጥታ ነበር የተናገረችኝ...መቼም የእናቴን ቤት መተው አልችልም እናቴ ናትና ...የሚስቴንም ቤት አልችልም ሚስቴ የልጄ እናት ናትና ከዛም በላይ አሁን ላለሁበት ትልቅ መሰዋአትነት ከፍላለችና ብቻ ግራ ገብቶኛል ምን እንደማደረግ አላውቅም....
እኔና ሜላት ከቀን ወደ ቀን ጭቅጭቃችን እየባሰ ቅዱስም እናቴጋ መዋል ማደረን ከመረጠ ሰነባበትን .. ቅዱስ ወደ ቤት እንሂድ ሲባል እናቴ እግር ላይ ተጠምጥሞ አልሄድም ይላል..ግራ ገብቶኛል ፍቅራችን እየተናደ እየተሸረሸረ ከመጣ ቀናቶች አለፉ...የተፈጠረውን እየተፈጠረ ያለውን ለእናቴ እነግራታለው....
ሜላት ሁሉን ነገር እርስት አድርጋው ጠጥታ አምሽታ ትመጣለች በጣም ሰለቸኝ በቃ ከአቅሜ በላይ ሆነችብኝ ምን ላድርጋት... ብመክራት ባስመክራት ምንም ልትስተካከል አልቻለችም ...አንድ ቀን አምሽታ በጣም ሰክራ መጣች ያን ቀን ግን በጣም በሽቄ ስለነበር በቃ እኔ ከዚህ በኃላ እኔና አንቺ አብረን መሆን አንችልም እናቴ ጋ እሄዳለው አልኳትና እናቴ ክፍል አድሬ ጠዋት ሻንጣዬን አዘጋጅቼ ወደ እናቴ ቤት ሄድኩ.....
የእኔና የሜላትን እንደዚህ መሆን ሰው ሲሰማው እጅግ ልገረምበት ይችላል እንዳንድ ሰዎች ገንዘብ ሲበረክት ፍቅር ይጨምራል ይላሉ ግን ውሽት ነው ገንዘብ ሲበረክት ፍቅር ይጠፋል....እኔና ሜላት በድህነቴ የነበረን ፍቅር እጅ በጣም ደስ ይል ነበር ገንዘብ ስናፈራ ብር ወደኛ ሲመጣ ግን ፍቅራችን ተሸረሸረ ...ልጃችንን እንኳን በፍቅር ማሳደግ አቅቶን ሁለታችንም በተለያየ መንገድ መጎዝ ጀመርን....
ብዙውን ጊዜ ቅዱስ እናቴ ጋ ነው የሚውለው ሜላትም ስትፈልግ ትወስደውና አሷ ጋ አድሮ ውሎ ይመጣል ... እኔና ሜላት አንድ ነገር ተነጋግረናል ከቤት ሰወጣ ...መጠጧን ትታ ወደራሷ ተመልሳ ...ትዳራችንን ለመቀጠልም ሆነ ለመፋታት እንደምንወስን ነገር ግን በዚህ ሁኔታ ምንም ነገር መወሰን እንደማልችል ነግሪያት ነበር ...
ሜላት ሁሉንም ነገር አየችው ለሳምንታት ያክል እኔ እየተደበቅሁ እያየኃት እሷ እንዳታየኝ እየተጠነቀቅሁ ስከታተላት ከረምክ ..በጣም ተጎሳቁላለች የሚገርመው የያዘቻቸው ጏደኞች እልም ያሉ ጠጪዎች ናቸው አብዛኞቹ እንደ ሹገር ማሚ ነገር ይሰራሉ ..የተረፍት ደግሞ አግብተው የፈቱ ናቸው...ከእነሱ ጋር ሆና ነው እንደዚህ ቅይርይር ያለችብኝ ...
አንድ ቀን ማታ ከሰራ ስትወጣ ተከትያት ሄድኩኝ ሆቴል ውስጥ ስትገባ አብሪያት ገባሁ ...በጣም በብዛት ተሰብስበው ወደ ሚጠጡ ሴቶች ተደባልቃ ቁጭ አለች ...ብርጮቆ አምጥተው ቀዱላት ..በአንድ ትንፋሽ ጭልጥ አድርጋ ጠጣችው አጠጣጧ ያስፈራል ...ሳትሰክር ማናገር ስለነበረብኝ ...ተጠጋኃቸው ስታየኝ ደነገጠች ሁሉንም ሰላም አመሻችሁ አልኳቸው ...እዚህ ምን ትሰራለህ ብላ አፈጠጠችብኝ...ምንም አልሰራም መቼም መጠጥ እንደማልጠጣ ታውቂያለሽ ግን አንዳንድ ነገሮችን አንቺ ያላወቅሻቸውን ላሳውቅሽ ብዬ ነው አልኳት....ሴቶቹ ግራ ተጋቡ እሷም አይኗን አፈጠጠችብኝ.....
ይቀጥላል✍🏻.........

ቶሎ እንዲለቀቅ ላይክ እና ሼር ያድርጉ❤️🙏
:*:*••••••🌸:*:*🌹:*:🌸•••••••*:*:
••●◉Join us share @ye_fkr_tarikoche
┄┄┉┉✽̶»̶̥🌹🌹»̶̥✽̶┉┉┄┄

የፍቅር ታሪኮች🌒

02 Oct, 19:31


💔የድሀ ልጅ ፍቅር ❣️
🌺🌺ምዕራፍ ሁለት
___🌸🌸ክፍል 23
ከስራ አምሽቼ እናቴ ጋ ሄጄ ማምሸት እያማረኝ ሜላቴ ቀድማኝ ከገባች ትናደድብኛለች ብዬ ቅር እያለኝ ወደ ቤት ሄድኩኝ ,...እቤት ስገባ ግን ማንም ሰው የለም ...ቤቱ ጠዋት ትቼው እንደወጣሁት ነው ምንም የተቀየረ ነገር የለውም,...እናቴ ክፍል ስገባ የተኛንበት አልተስተካከለም,..ልብሳችንን አነሳስቼ መኝታውን አነጠፍኩት....
ወደ እኔና ሜላት ክፍልም ስገባ አልተነጠፈም የቀየረችውን ልብስ እንኳን አላነሳችውም... እሱንም አስተካከልኩ ስልኬ ቻርጅ ስላልነበረው እሱን እያደረግሁ ቤቱን ማስተካከል ጀመርኩ.... ማታ እራት የተበላበት ሰአን አልታጠበም,...ብቻ በአጠቃላይ ቤቱ በጣም ያስጠላል ያስፈራል... እሪ ብዬ ብጮህ ደስ ይለኝ ነበር ግን አልችልም.....
ስራውን ሰርቼ ጨረስኩ እራት መስራት ፈለግሁ ግን ቅድሚያ ሜላት ጋ ልደውል ብዬ ስልኬን ከፈትኩት ሜላት ደውላ ነበር ግን ባትሪ ዘግቶብኝ ስለሆነ አላየሁትም ...መልሼ ደወልኩ አታነሳም ትንሽ ልጠብቅ አልኩ ....ግን ማንም የመጣ ሰው አልነበረም ...በጣም ተበሳጨሁ ተናደድኩ ግን በቃ ትዕግስት ይኑርህ እያለች ነው እያቴ ያሳደገችኝ.....
ጠብቄ ጠብቄ ሰው ሳይመጣ የሜላት ስልክ አልነሳ ሲለኝ እናቴ ጋ ደወልኩ ሰላም አልኳት እቤት ማንም እንደሌለ ነገርኳት እራት ቀርቧል ና አለችኝ ...ተነስቼ እናቴ ጋ ሄድኩ .... እናቴ ጋ እራት በልቼ ትንሽ ተጫውቼ ወደ ቤት ተመለስኩ ... እቤት ስመለስ ሜላት ተኝታ አገኝኃት ቅዱስም ተኝቷል .....
ወደ ሜላት ተጠግቼ ሜላት አልኳት ምን ላድርግህ ?አለችኝ በጣም ደነገጥሁ....ስልክ ስደውልልሽ አታነሽም ስጠብቃችሁ ስትቀሩብኝ እናቴ ጋ ሄድኩ አልኳት ...አሪፍ ነው ደክሞኛል ማረፍ እፈልጋለው አለች....ሜላት እየጠየቅሁሽ ነው ስደውልልሽ ስልክ አታነሽም ለምንድነው? አልኳት....
ሜላት በጣም በመቆጣት ከመኝታዋ ተነስታ ቁጭ አለችና በመጀመርያ ስደውል ለምን አላነሳህም አለችኝ.... ስልኬ ባትሪ ዘግቶ ነበር እንደከፈትኩ ስደውልልሽ አታነሺም ሲጨንቀኝ እናቴ ጋር ሄድኩ አልኳት.... አሪፍ ነው እኔም ስልኬን መኪና ውስጥ እርስቼው ስለነበር ነው አሁን ደክሞኛል ደህና እደር ብላኝ ትታኝ ተኛች.....
ነገሩን ላለማክረር ብዬ እኔም ዝም አልኩ ልብሴን ቀይሬ ተኛሁ .....ጠዋት ስነሳ ሜላት ተኝታ ነበር እስከዛሬ እናቴ ነበረች በጠዋት ተነስታ ቁርስ ሰርታ ቅዱስን አልብሳ እኛን የምትቀሰቅሰን አሁን ግን ያ የለም..... እኔም ተነስቼ ቅዱስን ቀስቅሼ ሜላትን ቀሰቀስኳት .... ቅዱስን ልብሱን አልብሼው እኔም ለበስኩ ...ድንገት ቅዱስ አባቢ አባቢ እንደ ትላንትናው እነ እቴቴ ጋ ቁርስ እንበላለን አለኝ?.....
በጣም ደነገጥኩ ሜላት አፈጠጠችብኝ ... አይ ቅዱሴ ዛሬ ማሚ የሰራችውን ቁርስ ነው የምንበላው እሽ አልኩትና ወደ መኝታ ክፍል ገባሁ...ሜላት ተከትላኝ መጣች ...ትላንት በጠዋት ልጄን ይዘህ የሄድከው የት ነው አለችኝ ... እናቴ ጋ.. አልኳት ...በጣም ተበሳጨች ግን እናቴን እንደምወዳት ስለምታውቅ ምንም ማለት አልፈለገችም ነበር.....
ሜላት ቁርስ እስከምትሰራ እኔ መኝታችንን አነጠፍኩ የሚስተካከለእን አስተካከልኩ ...ቁርስ ደርሶ በልተን ቅዱስን ይዜ ወደ ትምህርት ቤት ሄድኩ በዛውስራዬ ገባሁ ....ስራ ውዬ ቅዱስን ወንድሜ ከትምህርት ቤት አውጥቶት ስለነበር ቅዱስን ላመጣ ሄድኩ ...በዛውም እራት ሳትበላ አትሄድም በለውኝ እራት በልቼ ወደ ቤት ሄድኩ .... እቤት ስንደርስ ሜላት እራት አዘጋጅታ ጠበቀችን ቅዱስ ጠግቧል እኔም ጠግቤያለው ግን በቃኝ ማለት ስላልፈለግሁ ቁጭ አልኩ..... ቅዱስ ወደ መኝታ ክፍል ሲገባ .. ሜላት በጣም ተቆጥታ ከዚህ በኃላ አንዱን ቤት ምረጥ እሺ ወይ እዚህ ወይ እናትህ ቤት ... ስትል ድንገት ቅዱስ መኝታ ቤት በር ላይ ሆኖ ሲሰማ አየሁት........
ይቀጥላል✍🏻.........

ቶሎ እንዲለቀቅ ላይክ እና ሼር ያድርጉ❤️🙏
:*:*••••••🌸:*:*🌹:*:🌸•••••••*:*:
••●◉Join us share @ye_fkr_tarikoche
┄┄┉┉✽̶»̶̥🌹🌹»̶̥✽̶┉┉┄┄

የፍቅር ታሪኮች🌒

02 Oct, 19:29


💔የድሀ ልጅ ፍቅር❣️
🌺🌺ምዕራፍ ሁለት
.....,,,🌸🌸ክፍል 22

እኔና ቅዱስ ወደ ቤት ተመለስን እቤት ስደርስ ያጋጠመኝ ነገር ግን ያልጠበቅሁት ነገር ነበር ...እናቴ እራት ሰርታ ጠረቤዛው ላይ አስቀምጣ በትንሽዬ ወረቀት ይቅርታ ልጄ,,ብላ ፀፉልኝ አገኝሁት በጣም ደነገጥኩ,...እናቴ ክፍል ተንደርድሬ ስገባ የእናቴም የወንድሜም ልብስ የለም,.እናቴ ቤቱን ትታ ሄዳለች ...በጣም ተበሳጨሁ እንባ ተናነቀኝ ቅዱስ ዝም ብሎ ቆሞ ያየኛል .....

በዛው ቅፅበት ሜላት መጣች ቤቱ እርጭ ብሏል ግራ ገባት የደነገጠች ትመስላለች ደህና ዋላችሁ አለች...ካጎነበርኩበት እንባዬን ጠርጌ ቀና በማለት ሰልይምታ ሰጠኃት ...ውዱሴም ማሚ ብሎ ሄዶ ተጠመጠመባት አቅፋ ሳመችው ...እንዴት በጊዜ እንደመጣች ገርሞኛል ግን ልጠይቃት አልፈለግሁም ..እንዳቀተቀርኩ ዝም አልኳት...

ሜላት ዝምታው ስለጨነቃት ምን እንደተፈጠረ ጠየቀችኝ እኔ ሳልሆን ቅዱስ እቴቴ ሌላ ቤት ሄደች..ስትናፍቀኝ መጥቼ አይሀለው ስናፍቅህ ና እሽ ብላኝ ሄደች አላት....እኔ ምንም አልተነፈስኩም..ሜላት ደነገጠች ..ትላንት ለተናገርኳቸው ነገር ይቅርታ ልጠይቃቸው ነበር በጊዜ የመጣሁ በጣም አዝናለው አለች,.ምንም ሳልላት ተነስቼ መኝታ ክፍላችን ገባሁ... ልብሴን ቀይሬ እናቴ መኝታ ላይ ጋደም አልኩ,...

ቅዱስ አባቢ ተነሳ እርቦኛል እራታችንን እንብላ አለኝ ....እንቢ ማለት ስላልፈለግሁ ተነስቼ ወደ ምግብ ጠረቤዛው ሄድኩ የቤቱ ቅዝቃዜ በጣም ያስፈራል ለመጀመርያ ጊዜ ነው እንደዚህ ቅዝቅዝ አለ ቤት ውስጥ ስናመሽ ሜላትም ጨንቋታል እንዳታንይግረኝ ምን ትበለኝ ዝም እንዳትል ዝም ማለት አልቻለችም...እሽ ግን የት ነው የሄዱት እኛ እንውጣ እንጂ መቼ እነሱ ይውጥ አልኩ አለች..... ልጎእስ በእጄ የጠቀለልኩትን ትቼ ምንም ሳልል ከመቀመጫዬ ተነስቼ እጄን ታጠብኩና ደህና እደሩ ብዬ እናቴ ክፍል ገብቼ ተኛሁ.....
ሜላት የምትይዘው የምትጨብጠው ጠፍቷታል ቅዱስም አባቢ ካንተ ጋር መተኛት እፈልጋለው ብሎኝ አጠገቤ መጥቶ ተኛ,.....ሜላት የበላንበትን አንስታ ክፍላችን ገብታ ተኛች,በአይኔ እንቅልፍ ሳይዞር ነጋ ....እናቴ ጋ ያልደወልኩት ምንም የምለው ነገር ስለሌለኝ ነበር ምክንያቱም እናቴ ቅር ብሏታል ስለዚህ ደውዬ ምንም አልላትም... ዝም ብዬ አደርኩ,ጠዋት ከመኝታዬ ተነስቼ ቅዱስን አስነስቼ ልብሳችንን ቀያይረን ልንወጣ ስንል ሜላት ነቃች ...

ወዴት ልትሄዱ ነው ቁርስ ልስራ ስትል አይ ተይው ውጪ እንበላለን ስራ እንዳይረፍድብሽ ብያት .ቅዱስን ይዝኡ ወጥይሁ...ወንድሜ ጋ ደውዬ የቤታቸውን አድራሻ ተቀብዬ እናቴ ጋ ሄድኩ..እናቴ ጋ ደርሰን ገና እናቴን ሳያት ቅዱስ ከመኪናው ወርዶ እየሮጠ እቴቴ ቁርስ ደርሷል እርቦኛል አላት ,...ና ልጄ ቁርስ ደርሷል ብላ እኔን ሰላም ብላኝ ወደ ውስጥ ገባን ....እናቴን ሳያት እንባ ተናንቆኛል ግን በፍፁም ማልቀስ አልፈለግሁም ምክንያቱም እናቴ ሳለቅስ ማየት እንደማትወድ ስለማውቅ.....

እናቴ የፊቷ ፈገግታ ምንም አልቀነሰ ...ገብተን የተዘጋጀውን ቁርስ በላን ወንድሜ ጎበዝ ነው ቤቱን አሟልቶታል,...ቁርስ በልተን ቅዱስን ይዜ ልወጣ ስል ሜላት ደወለች.ቅዱስ ከትምህርት ሲወጣ እኔ አወጣዋለው አለችኝ እሽ ብያት ቅዱስን ትምህርት ቤት አስገብቼ እኔም ወደ ስራዬ ገባሁ,..ስራዬን እንደምንም ስሰራ ዋልኩኝ .....ማታም ወደ ቤት ሄድኩ እቤት ስደርስ ግን ማንም ሰው አልነበረም......
ይቀጥላል✍🏻.........

ቶሎ እንዲለቀቅ ላይክ እና ሼር ያድርጉ❤️🙏
:*:*••••••🌸:*:*🌹:*:🌸•••••••*:*:
••●◉Join us share
┄┄┉┉✽̶»̶̥🌹🌹»̶̥

የፍቅር ታሪኮች🌒

02 Oct, 19:29


🌺🌺ምዕራፍ ሁለት
..........🌸🌸ክፍል 21
💖በእዉነተኛ የህይወት ታሪክ ላይ የተመሰረተ💞
እኔና ሜላት አብረን አምሽተን እሷም የእኔን ቀልብ ስትገፍና ስታስደነግጠኝ አምሽታ ሂሳብ ከፈለች ...ምንም አላልኩም አንዳንዴ ብዙ ከመናገር ብዙ ማዳመጥ ይባል የለ,... ለዛ ነበር ዝም ያልኩት,እቤት ገብተን እራት ስለበላን ወደ መኝታ ክፍላችን ተኛን ቅዱሴ ተኝቶ ነበር የደረስነው ምክንያቱም አምሽተን ስለደረስን.....
በዚህ ሁኔታ እስከመቼ መቀጠል እንዳለብን ባለውቅም ብቻ ስራ ስለበዛብኝ መጣደፍ ጀመርኩ.....በእኔና በሜላት መካከል የተፈጠረውን አለመግባባት እኔቴ በፈፁም እንድታውቅ አልፈለግሁም ስለዚህ እናቴ ፊት እኔና ሜላት ሰላማዊ እንሆናለን....ታናሽ ወንድሜ ግን አንድ ቀን ስንጨቃጨቅና እናቴን ተለይተን መኖር እንዳለብን ስትነግረኝ ስምቷታል ... እናቴን ማስጨነቅ ስላልፈለገ ብቻ ዝምታን መርጧል.....
እኔም ከስራ እቤት ከቤቴ ስራ እንጂ ሌላ የትም ቦታ አልሄድም ልጄን ሳጫውት ማምሸት እመርጣለው ...ለነገሩ የስራ ባልደርቦቼ እንኳን እንዝናና ሲሉኝ ደስታኛ አልሆንም.... እናቴ ሜላት የት ነው የምታመሸው ብላ ስትጠይቀኝ...ሰበብ እየፈጠርኩ እዋሻታለው .አንዳንዴ ቤተስብ ጋ እህቷ ጋ ከጏደኞቿ ጋ ስራ ቦታ ....ብቻ ያልዋሸሁበት መንገድ የለም ...
አንድ ቀን እንደተለመደው ቀድሜ ገብቼ ቀኑ ገብረኤል ስለነበር .እናቴ ብና አፍልታ ቤቱን አድምቃ ሜላትን መጠበቅ ጀመርን እንጠጣ ቡናውን ስላት ሜላት ሳትመጣ አይሆንም አለችኝ.....ጨነቀኝ መሽ ሲመሽ እናቴ ተስፋ ቆረጠች ቡናውን እኛው ጠጣንም...ቡናው ልክ ሲያከትም ሜላት መጣች ...እናቴ ሜላቴ ጠብቀንሽ ስትቆይብን ጠጣነው ይቅርታ አለቻት....
ሜላት ግን ትንሽ ጠጥታም ስለነበር ስደብቀው የከረምኩትን በመሀከላችን የተፈጠረውን አለመግባባት ምንም ሳታስቀር ለእናቴ ዘረገፈችላት ...ቀልቤ ተገፈፈ ወንድሜ ሁሉንም ያውቅ ስለነበረ ምንም አላለም እናቴን ወደ መኝታ ክፍል ይዟት ሄደ ...ሜላትን ምን እንደምላት ግራ ገባኝ ትቻት ክፍላችን ገብቼ ጥቅልል ብዬ ተኛሁ ...እንባም ተናንቆኛል ..እናቴ ለመጀመርያ ጊዜ አንገቷን ስትደፋ አየኃት ...በድህነቷ የምትኮራ ማዘን የማትወድ ባላት የምትደሰት ለሰዎች ብርታት የነበረችው እናቴ በሜላት ከልክ ያለፈ አነጋገር አንገቷን ስትደፋ ሳይ ልቤ ተሰበረ በጣም አዘንኩ ...ግን በቃላት ሜላትን ማስከፋት ስላልፈለግሁ ጥቅልል ብሎ መተኛትን ምርጫዬ አደረግሁ....
ጠዋት ከመኝታዬ ስነሳ ሜላት ተኚታለች ዝም ብዬ ልብሴን ለብሼ ወደ ሳሎህ ሄድኩ ማንም ሰው የለም እናቴ ክፍል ስገባ እናቴ ተኝታለች ደህና አደርሽ ብዬ ግንባሯን ስይምኳት ግን የተኛች ስላስመሰለች ዝም አለችኝ ወንድሜ የለም ... ወደ ቅዱስ መኝታ ክፍል ስሄድ ቅዱስ የለም ወንድሜ ትምህርት ቤት ሊያደርሰው ሄዷል....ከቤት ልወጣ ስጣደፍ በስልኬ ሜሴጅ ደረሰኝ ወንድሜ ነበር ላናግርህ እፈልጋለው ከቤት ከወጣህ የት እንገናኝ?ይል ነበር ደወልኩለት ...ቦታ ተቀጣጥረን ወደ ስራ ከመግባቴ በፊት እንዳገኝው ወደ ተቀጣጠርንበት ካፌ አመራሁ....
ቀድሞኝ ደርሶ ስለነበር የተቁመጠበትን በምልክት ነግሮኝ አገኝሁት ....ከቤት ለመጀመርያ ጊዜ ቁርስ ሳልበላ ወጣሁ ....ጠዋት ጠዋት የእናቴ ጉርሻ ሱስ ሆኖብኛል ግን ዛሬ ሳልጎርስም ቅርስም ሳልበላ ከቤት ወጣሁ... ቁርስ አዘዝንና እስከሚደርስልን ድረስ ...ወንድሜ ለምን እንደፈለገኝ መነጋገር ጀመርን ...ወንድሜ ሁሉንም ነገር ቀድሞ እንደሚያው ነገረኝ ቀልቤ ተገፈፈ ...እንዴት እንዳወቀና እስከዛሬም ዝም ያለው ቤት እየፈለገ ስለነበር ነገረኝ...አሁን ግን አታስብ ቤት አግንቻለው አለኝ.....
ቁርሳችን ደርሶ ቀረበልን ግራ ገባኝ እናቴ ሳታጎርሰኝ ቀድሜ ጎርሼ አላውቅም .ወንድሜ ልማዴን ስለሚያውቅ .እንካ ጉርስ እናቴ ከእንግዲህ የለችም ልመደው ብሎ አጎረሰኝ .ጉርሻውን ጎርሼ መብላት ጀመርኩ.... ቆይ ግን እስከዛሬ ቢያንስ ለእኔ እንዴት አትነግረኝም አልኩት ላጨናንቅህ ስለማልፈልግ ነው አለኝ ....አሁን ምንም እንዳትጨናነቅ አንተና ሚስትህ ሜላት በሰላም ትኖራላችሁ እኛም ስትናፍቅርን መጥተን እንጠይቃችኃለን አለኝ.....
ከስደት ተመልሼ ከቤተሰቤ ተደባለቅሁ ስል ድጋሚ ሌላ ጣጣ ይገርማል,....እኔና ወንድሜ ተነጋገርን ብር እስከዛሬ ለታክሲ ለትምህርት ቤት በቃ ለተለያዩ ነገሮች እያልክ የምትሰጠኝን አጠራቅሜ የ 3 ወር ቤት ኪራይ ከፍያለው አለኝ ደነገጥሁ ለምን አልኩት ችግር የለውም ከፈለግሁ ደግሜ እጠይቅሀለው አለኝ,... እሽ ብዬው እንኡም ወደ ስራ መግባት ስለነበረብኝ ወደ ስራ ሄድኩ..ስራ ከመድረሴ በፊት ለወንድሜ በባንክ አካወንቱ ብር አስገባሁለት,....ከዛም ወደ ስራ ሄድኩ.....
ስራ ቦታ ስራ በዝቶብኝ እየተጣደፍኩ ሜላት ደወለች,ሰላም አልኳትና ልታናግረኝ የምትፈልገው ነገር አንዳለ ስትነግረኝ ከስርይ በኃላ ብያት ስልኩን ዘጋሁት ..ስደክም ውዬ ማታ ወደ ቤት ልሄድ ስል ወንድሜ ደወለልኝ ስራ ቦታ በር ላይ ከቅዱስ ጋ እየጠበቅንህ ነው ና አለኝ እሽ ብዬ ወጣሁ ስላም አልኳቸውና ወደ ቤት እንሂድ ስለው እሽ እናንተ ሂዱ እኔ እዚህ ሰው ቀጥሪያለው ብሎኝ ወንድሜ ሄደ,..እኔና ቅዱስ እየተጫወትን ወደ ቤት ሄድን ,.. እቤት ስደርስ ያጋጠመኝ ነገር ግን ያልጠበቅሁት ነገር ነበር........
ይቀጥላል✍🏻.........

ቶሎ እንዲለቀቅ ላይክ እና ሼር ያድርጉ❤️🙏
:*:*••••••🌸:*:*🌹:*:🌸•••••••*:*:
••●◉Join us share
┄┄┉┉✽̶»̶̥🌹🌹»̶̥✽̶┉┉┄┄