Yasin nuru's hadis @yasin_nuru_hadis Channel on Telegram

Yasin nuru's hadis

@yasin_nuru_hadis


This is not Official
ይሄ ቻናል የያሲን ኑሩ አይደለም!

"በጃሂሊያ (ብሄርተኝነት) ጥሪ የተጣራ እርሱ በእንብርክክ ጀሃነም የሚገባ ነው ፤ ቢፆምና ሙስሊም ነኝ ብሎ ቢሞግት እንኳን።

Yasin nuru's hadis (Amharic)

የያሲን ኑሩ አዝናኝ ቻናል

የይህን ቻናል ለመደበኛ ያሰገዱት ተከታይ ስለእናንተና ስለእኛ ምንጭ። በጃሂሊያ (ብሄርተኝነት) ጥሪ የተጣራ እርሱ በእንብርክክ ጀሃነም የሚገባ ነው ፤ ቢፆምና ሙስሊም ነኝ ብሎ ቢሞግት እንኳን። ስለዚህ እናንተን ለእናንተ የያሲን ኑሩ ትምህርት ቻናል እና በተለያዩ መረጃዎች እንዲሰጡ ተለቅቻለው። የኑሩን በየከተማው ለምስላከንም መረብ ከሆኑ፣ ስለጎና መረጃዎች ማስጫን እንዲችሉ በቴሌግራም መልክም በሁለቱም ተቀብለው ማድረግ።

Yasin nuru's hadis

16 Feb, 04:07


Morning Adhkar | أذكار الصباح | Morning Supplications

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

15 Feb, 04:59


አላህን ማስደሰት የሚፈልግ ብቻ ይፀፀት

ኡስታዝ ያሲን ኑሩ

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

14 Feb, 05:35


أكثِروا من الصَّلاة على النبي ﷺ 🤍


اللَّهمَّ صَلِّ عَلَى مُحَمَّدٍ وَعَلَى آلِ مُحَمَّدٍ، كَمَا صَلَّيْتَ عَلَى إِبْرَاهِيمَ، وَعَلَى آلِ إِبْرَاهِيمَ، إِنَّكَ حَمِيدٌ مَجِيدٌ، اللَّهمَّ بَارِكْ عَلَى مُحَمَّدٍ وَعَلَى آلِ مُحَمَّدٍ، كَمَا بَارَكْتَ عَلَى إِبْرَاهِيمَ وَعَلَى آلِ إِبْرَاهِيمَ، إِنَّكَ حَمِيدٌ مَجِيدٌ».

Yasin nuru's hadis

13 Feb, 06:15


ታላቁን እንግዳ እንዴት እንቀበለው?
ክፍል ② አላህ የፈለገውን ይመርጣል ከሌሎችም ያስበልጣል

በሸይኽ ዶ/ር ዑሥማን አል-ኸሚስ
ትርጉም በፅሁፍ

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

13 Feb, 03:32


ተጠጋሁህ በሺ ወንጀል
እዝነትህን በመከጀል😊

Yasin nuru's hadis

12 Feb, 17:35


☞በአንድ ድጋፍ 3 ወፍ


ነገ ከፆምን 3 ነጥቦችን እናሳካለን።

1ኛ አያመል ቢድ ነው።

2ኛ ሀሙስ ነው።

3ኛ ሸዕባን ከሚፆምባቸው እንዱ ነው።

የቻልን እንፁም! ሌሎችንም እናስታውስ!

👉 ወዳጆቼ መፆም እየቻሉ ያላስተዋሉ ሊኖሩ ስለሚችሉ በማስታወስ በኸይር ማመላከት ላይ እንጠንክር።

የረመዷን ቀዷ ካለባችሁም በዛው
እንዳረሱ ረመዳን እየደረሰ ስለሆነ

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

12 Feb, 05:50


Ustaz Yasin Nuru

ረመዳንን እንዴት እንቀበለው?

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

11 Feb, 18:53


ኧረ! ጉድ ነው ጎበዝ!

ጆርዳን የትራምፕን እቅድ ማስፈፀም ልትጀምር ነው ማለት ነው?

ወሏሁ-ል-ሙስተዓን!
ሐስቡነ-ል'ሏህ!

አሁን ያሉት አረቦች እኮ በቁማቸው ከሞቱ ቆዩ

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

11 Feb, 06:26


ሴቶች እስከ መጨረሻው ያንብቡ
አሰላም አለይኩም ወራመቱላሂ ወበረካቱ
   ነፃ.........ነው
     ለረመዳን የተዘጋጀ ልዩ የሴቶች ኮርስ በቴሌግራም በኦንላይን የተዘጋጀ ከ ማታ ከ 3:00 እስከ 4:00 በስራ ምክንያት በቤተሰብ አጃ ቀጥታ ካልቻሉ በድምፅ የተለቀቀውን በፈለጉት ሰዓት ማዳመጥ ይችላሉ
ኪታቡ የያዛቸው እርእሶች

💧ከመጥፎ ህይወት አላህ ወደ ሚወደው ጥሩ ህይወት የምንለወጥበትን ሂደት የሚያስተምር ነው
💧ከመጥፎ ህይወት እንዴት እንደሚወጣ ያስተምርሻል
💧የአላህን ሱ.ወ ይቅር ባይነት እና አዛኝነት እንድታምኚ ያረግሻል
💧ከመጥፎ ህይወት የመውጣት ጥቅሞችን ያብራራልሻል (ከመጥፎ ነገሮች ተላቀሽ ጀነት የምናገኝበትን ይጦቅመናል)
💧ከመጥፎ ህይወት ካልወጣሽ በዚህም አለም በቀጣዩም ዓለም የሚያጋጥሙሽን ቅጣት ያብራራል
💧ስለ ጥሩም ህይወት መጥፎም ህይወት ስለ አላቂው ህይወት እና ሞት ያስተምርሻል
 📚የኪታቡ ስም፦ ሚን ሁና ነብደ ወፊልጀነቲ ነል ተቂ ትርጉም 👉ካለንበት እንነሳ ጀነት እንገናኝ
( ያለንበት መጥፎ ሁኔታ ላይ ሰላት አለመስገድ፣ ሱስዝ፣ ዝሙት የትኛውም ዓይነት መጥፎ ሁኔታ ላይ ቢሆኑ እንዴት ህይወታችንን ተለውጦ ጀሀነም ከመግባት ጀነት እንዴት እንደምንገባ መንገድ የሚያመላክተን ምርጥ የለውጥ ኪታብ ነው
   በሁስታዝ ፦ሙሀመድ አህመድ
 
    👉ትምህርቱም ለ 20 ቀን ነው የሚቆየው አረበኛም መቻል አይጠበቅብሽም
    👉ትምህርቱ ረመዳን ሲደርስ ያበቃል
    👉ሰርተፍኬት ትምህርቱን ሲጨርሱ ይሰጣል

       ምንም አይነት ክፍያ የለውም!!!
ትምህርቱም በቴሌግራም ላይቭ ነው ከ 3:00 እስከ 4:00 ለመመዝገብ
በዚህ ያናግሩን👉 @Abcde0427

Yasin nuru's hadis

11 Feb, 05:52


አሳፋሪው ! የኢትዮጵያ አየር መንገድ 🇪🇹🇪🇹!

ኢትዮጵያን ማን ነው የነሱ ብቻ ያደረጋት ቆይ🤔

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

10 Feb, 12:40


ለፈገግታ

አንድ ቆለኛ ሙስሊምና አንድ ደገኛ ክርስቲያን ጓደኛሞች ይሆናሉ። ክርስቲያኑ ሙስሊሙን ግብዣ ጠራው። የገና በአል ነበር። ሙስሊሙ ሲመጣ ምግቡ፣ መጠጡ፣ ሁሉ ነገር ተትረፍርፏል። ሰዎቹ ፌሽታ በፌሽታ፣ ፈንጠዝያ በፈንጠዝያ ሆነዋል።
·
* ሙስሊሙ:– "ድግሱ ምንን ምክንያት በማድረግ ነው?" ብሎ ጠየቀ።
– "ጌታ ተወልዶ ነው" አሉት።
·
ለሙስሊሙ ይሄ አስደንጋጭ ነበር። ጌታ ይወለዳል?! ግን ከሰው ቤት ነው ያለው ምን ይላል? "ህምምም" ብሎ የሆዱብ በሆዱ አድርጎ ዝም ይላል። ይህን ጉድ አይቶ ተመለሰ።
·
ሌላ ጊዜ ተጠራ። ጥምቀት ነበር። ሲመጣ ድግሱ አሁንም እንደባለፈው የደመቀ ነው። ሰዎቹም ደስታ በደስታ ናቸው።
* "እሄስ በአል ምንድን ነው ምክንያቱ?" ብሎ ጠየቀ።
– "ጌታ ተጠምቆ ነው" አሉት። ዘንድሮ ጉድ ተአምር እያየ ነው። እንዲያም ነው፤ እንዲህም ነው ሳይል ወደ ቤቱ ተመለሰ።
·
አሁንም ተጠራ። ስቅለት ነበር። ሲመጣ ከወትሮው የተለየ ነገር አየ። ሰዎቹ የባለፈው አይነት ደስታ አይታይባቸውም። አዝነዋል። በባዶ እግር ይሄዳሉ። የሚበሉት ንፍሮ ነው። ግንባራቸውን በሳር መሳይ ነገር አስረዋል። ምን ጉድ ነው?! ቆለኛው ግራ ገብቶታል።
·
* "ምንድን ነው የሆናችሁት?" አላቸው።
– "ጌታ ሞቶ ነው" አሉት።
* "ያ ባለፈው የተወለደው?" ሲል ጠየቀ።
– "አዎ" አሉት።
·
ከዚያ ምን ቢል ጥሩ ነው:–
"እኔኮ ቀድሞም ፌሽታ ስታበዙ እንደማያድግ አውቄያለሁ!!!

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

10 Feb, 05:07


እጅግ በጣም የሚማርከኝ ሃዲስ

#ኡስታዝ_ያሲን_ኑሩ

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

09 Feb, 05:00


የጥዋት ዱዓ

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

08 Feb, 08:59


እኛ ግን ጉዳት ወይም ችግር እሰኪገጥመን አላህን አንታዘዝም።

ሙሉ ጤና እያለህ አላህን ተገዛ!

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

07 Feb, 16:53


1000340185308 

ኡስታዝ ካሚል ጠሀ ጀማል

የአቅመችንን እናስገበለት 😊


ከ10 ብር ጀምሮ እንርደቻዉ

Yasin nuru's hadis

07 Feb, 03:23


⛳️ #ጁምዓ!!  ⛳️  
   
,
🍃እናንተ ያመናችሁ ሆይ በአርብ ቀን ወደ ስግደት  በተጠራ ግዜ አላህን ወደ ማውሣት ሂዱ  መሸጥንም ተው ይህ የምታውቁ ከሆነ ለናንተ በላጭ ነው።
,  《ሡረቱል ፦ አል ጁሙአህ》
                                                                                            በላጭ ቀናቹ የጁመዐ ቀን ነው
  ረሡል ሠለላሁ አለይሒ ወሠለም
"ፀሀይ ከወጣችባቸው ቀናቶች ሁሉ በላጩ ቀን የጁመዐ ቀን ነው
ረሡል ሠለላሁ አለይሒ ወሠለም
,

~ከላይ ያለፋት መለኮታዊ ንግግሮች በኢስላም ከሌሎች ቀናቶች ለይቶ  ለጁመአ ለት  የሠጠውን ደረጃ ያሣዩናል ይህን የተከበረ ቀን በምን መልኩ ማሣለፍ እንዳለብን ከነብዩ ሠለላሁ አለይሒ ወሠለም ዘንድ የመጡት በማውሣት እንተዋወስ
ወደ መልካም ነገር ያመላከተ    እንደሠሪው ያክል መንዳ ያገኝበታል ።
,
=•የጁመአ ለት ሡብሒ ሠላት ያለው ደረጃ ,አላህ ዘንድ በላጩ ሠላት የጁመአ ቀን ሡብሒ በጀመአ መስገድ
   
        《📚ሢልሢለቱ ሰሒህ》

~ጁመአ ለት ሡብሒ ሠላት ላይ
    ምንምን ሡራ ይቀሩ ነበር ?
  ,
~የአላህ መልዕክተኛ ሠለላሁ አለይሒ ወሠለምበጁመአ ሡብሒ ላይ
  《አሊፍ ላም ሚም ተንዚሉ: ሠጅዳ》
እና   「ሀል አታ አለል ኢንሣኒ」
              ይቀሩ ነበር
      《📚ቡሀርና ሙስሊም》
,

🔺 በጁመአ ቀን ሠለዋት ማውረድ
     ያለው ጥቅም ∴
,
~የጁመአ ቀን እና ማታ በኔ ላይ
  ሠለዋትን አብዙ,በይሀቅይ
~በላጭ ቀናቹ የጁመአ ቀን ነው የዛ ቀን:     "አደም ተፈጠረ "ሞተ "ጡሩንባ ይነፋል "በህይወት ያለ ሁሉ ይሞታል በኔ ላይ ሠለዋትን አብዙ ሠለዋታቹ በኔ ላይ    የምትቀረብ ናት "
   ~አስሀቡ ሡነንነወውይ
       📚ሰሒህ ብለውታል

🚿የጁመዓ ቀን ገላን መታጠብ
                                       አንደኛቹ ወደ መስጂድ ሢመጣ ገላውን
ይታጠብ ,
      《📚ቡሀርና ሙስሊም 》
,
የጁመአ ቀን ሽቶ መቀባት ፣ ጥሩውን መልበስ ፣ረጋ ብሎ ሣይጣደፍ
ወደ መስጂድ መሔድ በሁጥባ ወቅት ዝም ብሎ ማዳመጥ  ያለው ጥቅም ~የጂመአ ቀን የታጠበ, ሽቶ ካለውና ከተቀባ ,ጥሩ ልብስ የለበሰ , ወደ መስጂድ ሢሔድ በተረጋጋ መንፈስ ከሔደ ,ከተመቸውና ከሠገደ ,አንድንም ሠው ካላስቸገረ , ኢማሙ ሚንበር ላይ  ከወጣበት እስኪሠገድ ድረስ ዝም ያለ  በሁለት ጁመአዎች መሀል ያለውን ወንጀል ይማርለታል "
,
🕐በግዜ መስጂድ መሔድ,የጁመአ ቀን መላይካዎች የመስጂድ በር ላይ ይቆማሉ ከዛ መጀመርያ ቀድሞ የሚገባውን ይፅፋሉ : መጀመርያ መስጊድ የሚገባው ግመል እንደሠጠ ከሱ ቀጥሎ ከብት ከሡ ቀጥሎ በግ ከዛም ዶሮ ከዛም እንቁላል ኢማሙ ሚንበር ላይ ሢወጣ መዝገቡን ዘግተው ሊያዳምጡ ይገባሉ  "
       《📚ቡኸርና ሙስሊም 》

🚫 የጁመአ ቀን የተከለከሉ ነገሮች  ❗️

ኢማሙ ሁጥባ ሢያደርግ ማንኛውም አይነት ንግግር ክልክል ነው በመልካም ማዘዝም ከመጥፎ መከልከልም  ቢሆን  "ለጎደኛህ የጁመአ ቀን ኢማሙ ሁጥባ እያደረገ ዝም በል ካልከው ውድቅ የሆነ ነገር ሠርተሀል "ቡሀርና ሙስሊም አህመድ "ውድቅን ነገር የሠራ ከጁመአው ምንም ነገር የለውም "
   የሚል ጨምረው ዘግበዋል
,
~ዘግይቶ መስጂድ መምጣት እና ሠዎች አዛ ማድረግ "ረሡል ሠለላሁ አለይሒ ወሠለም ሁጥባ እያደረጉ አንድ ሠው በሠዎች ጀርባ ላይ እየተረማመደ ሢመጣ "ተቀመጥ! ሠዎችን አስቸገርክ" አሉትኝ
,
አላህ የተጠየቀውን ነገር የማይመ ልስባት አንድ ወቅት አለች #በጁምአእለት አንድ ሠአት አለች እሧን ሠአት አንድ ሙስሊም የሆነ ባርያ አያገኛትም  እሡ የሚሠግድ ሢሆን አላህን አንዳች ነገር አይጠይቀውም
የሠጠው ቢሆን እንጂ "
《 ቡኻር እና ሙስሊም 》
,
~ ያቺ ሠአት መቼ ናት?
በዚህ ዙርያ ኡለሞች የተለያየ አመለካከት ሠንዝረዋል ከሙስሊም በተዘገበ ሀዲስ ኢማሙ ሁጥባ ከጨረሰበት ሠላት እስኪሰገድ ያለው ክፍተት ነው "አቡ ዳውድ እን ነስእይ በዚህ መልኩ ዘግበዋል
,
~ከጁመአ የመጨረሻው ወቅት ላይ ፈልጓት "በሌላ ዘገባ "ከአስር ቡሀላ
والله اعلم وصلى الله على نبينا محمد وعلى آله وأصحابه وسلم.

Yasin nuru's hadis

06 Feb, 06:16


የቀልብ ሰኪና እና የደስታ ስሜቶች ከሰዎች መሰረቅ ቢችሉ ኖሮ ሰጋጆች ሁሌም እንደተዘረፉ ነበር 🥰

@yasin_nuru

Yasin nuru's hadis

05 Feb, 04:15


👉ቆንጆ ካልሆነች አትበል‼️

መልከኛ ካልሆነች አናገባም የግድ መልከኛ መሆን አለባት እያልን ቆመን የቀረን ሰወች ከዚህ ታሪክ መማር አለብን⁉️

የኢማሙ ማሊክ አባት አንድት እንስት አገቡ ሲገቡባት አላማረቻቸውም ነገር ግን ሴትዮዋ እጂግ መልካም ሴት እና ንፁህ ነበረች።

በሱ አለመወደድን ያየች ጊዜ ከእግሩ ላይ ተቀመጠችና እንዲህ አለች፦

ውበቴ ባያስገርምህም መልኬ ባይማርክህም ከአሏህ መልካም ዝርያ ከእኔ እንደሚሰጥህ አስባለሁ አለችው ......

ሰውየውም የዋዛ አልነበረምና መልካም ዝርያን አስቦ አስቀራት አሷም #ኢማሙ ማሊክን ወለደችለት ...ኢማሙ ማሊክ ማለት በእውቀቱ ዱንያን ያጥለቀለቀ ጀግና አሊም ነው።

ሰወች ዛሬ ድረስ ከኢማሙ ማሊክ እውቀት ከመቅሰም ዛሬ ድረስ አልተወገዱም።

በነገራችን ላይ መልከኛ ሷሊህ አይወልድም ባይባልም በተለምዶም ሆነ በብዙ ታሪክ ላይ እንደምንሰማውና እንደምናየው #ጀግኖችንና እና#ታሪክ_ሰሪወችን የሚፀንስ ማህፀን በብዛት ውጫዊ ገፅታቸው ብዙም የማይስቡ ሴቶች ናቸው።

ምክንያቱም...

መልከኞቹ በውበታቸው ሲኮፈሱ
እነዛ ግን በተቅዋ ተውበው ይገኛሉ።
መልከኞቹ አንዱን ካንዱ ሲያማርጡ
እነዚያ ጌታቸው ዘንድ ይሮጣሉ፡፡

ደግሞ ወላሒ በብዛት ቆንጆ ወንዶችን የሚይዙት ሴቶች እንድሁ ጎረድረድ ያሉት ናቸው።

መልከኛዋ ምርጫ ስታበዛ፣አንዱን እያነሳች ስትጥል፣አንችን የመሰልሽ ልጅ እየተባለች ስትኮራና..በየደረሰችበት ጭራዋን ስትቆላ.!!በመጨረሻ ቁመሽ መቅረትሽ ነው ተብላ አንዱ ጂል ላይ አይኗን ጨፍና ትገባና ስትነፍር ትኖራለች ይገርማል ።


.....✍️ኑረዲን አል አረብ

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

04 Feb, 05:20


🤍የትክክለኛ ፍቅር መነሻው ኒካህ💍

መድረሻው ደግሞ ጀነት ነው ።

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

03 Feb, 04:32


ረመዳን መጣላችሁ😍

በኡስታዝ ያሲን ኑሩ

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

02 Feb, 16:41


የሲር ለናን ለመደገፍ የሚከተሉትን የባንክ አካውንቶች ይጠቀሙ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ              1000455851746
ዘምዘም ባንክ                         0011133210301
ሂጅራ ባንክ                             1003047120001
ዳሽን ባንክ                              7902719139811
አዋሽ ባንክ                              01308692060200
አቢሲንያ ባንክ                          89752787
ኦሮሚያ ባንክ                           1697175800001
ኦሮምያ ህብረት ስራ በንከ          1026400088414
ስንቄ ባንክ                               1058722501214
ግሎባል ባንክ                          8210116220561
ህብረት ባንክ                           4729714192259014 

        
        9757 ላይ Ok ብለው በመላክ አጋር ይሁኑ!

        Email: [email protected]

አድራሻ: -  ከሳባ መስጅድ ከፍ ብሎ ከሚገኘው ኢትዮ ፓረንት  ት/ቤት አጠገብ ያገኙናል።   

በቴሌግራም:_👇👇👇
https://t.me/yesirlena

በፌስቡክ: _👇👇👇
https://www.facebook.com/yesirlena/

በቲክቶክ:_👇👇👇
https://www.tiktok.com/@yesir_lena
follow ያድርጉን።

እርሶም በነዚህ መልካም ስራዎች ይሳተፋ።

ለበለጠ መረጃ:  +251912490006
                        +251947636323

"መኖሬን ያወኩት ለሰው የኖርኩ ቀን ነው"

Yasin nuru's hadis

02 Feb, 05:43


ጥር 25፣ 2017 ዓ.ል | ሻዕባን 3፣ 1446 ዓ.ሒ
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••

በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የበላይ ጠባቂነት የሚካሄደው 2ኛው ዙር ዓለም አቀፍ የቁርአን እና የአዛን የፍፃሜ ውድድር በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ ስታዲየም የሚካሄድ ሲሆን የውድድሩ ታዳሚዎች በብዛት ወደ ስታዲየሙ እየገቡ ነው።

ዝርዝር መረጃውን እየተከታተልን እናቀርባለን።

••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት።

@yasin_nuru

Yasin nuru's hadis

02 Feb, 05:22


መስጂድ ብትርቅ... ሌሎች ይመጣሉ!

ለቁርአን ጀርባ ብሰጥ.. ሌሎች ያነቡታል!

ለእስልምና መስራት ብትተው...ህይወታቸውን ሚሰጡ ባሮች የግል።

እወቅ!!

ከመልካም ቦታዎች መራቅ ተጎጁው አንተ እንጂ ዲኑ ብዙ ደጋግ ባሮች አሉት።

አላህ ፅናቱን ይስጠን🙌🙌

@yasin_nuru

Yasin nuru's hadis

01 Feb, 07:02


ቀናቶች የቀሩት ረመዳን..የጁመአኹጥባ|በኡስታዝ ካሚል ጣሀHarunMedia|| →

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

31 Jan, 07:47


ጀምዓው ማክሰኞ exit exam እፈተናለው ዱዓ አርጉልኝ🥰🥰

Yasin nuru's hadis

31 Jan, 03:09


﴿إِنَّ اللهَ وَمَلَائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا﴾.

«اللَّهُمَّ اجْعَلْ صَلَاتَكَ وَسَلَامَكَ وَبَرَكَتَكَ وَرَحْمَتَكَ عَلَى سَيِّدِ المُرْسَلِينَ وَإمَامِ المُتَّقِينَ وَخَاتَمِ النَّبِيِّينَ مُحَمَّدٍ عَبْدِكَ وَرَسُولِكَ أكْرَمِ الخَلْقِ وَإمَامِ الخَيْرِ وَرَسُولِ الرَّحْمَةِ ، اللَّهُمَّ ابْعَثْهُ مَقَامًا مَحْمُودًا يَغْبِطُهُ بِهِ الأوَّلُونَ وَالآخِرُونَ ، اللَّهُمَّ تَقَبَّلْ شَفَاعَتَهُ الكُبْرَى وَارْفَعْ دَرَجَتَهُ العُلْيَا وَآتِهِ سُؤْلَهُ فِي الآخِرَةِ وَالأُولَى كَمَا آتَيْتَ إبْرَاهِيمَ وَمُوسَى .. اللَّهُمَّ صَلِّ عَلَى مُحَمَّدٍ وَعَلَى آلِ مُحَمَّدٍ كَمَا صَلَّيْتَ عَلَى إبْرَاهِيمَ وَعَلَى آلِ إبْرَاهِيمَ إنَّكَ حَمِيدٌ مَجِيدٌ ، اللَّهُمَّ بَارِكْ عَلَى مُحَمَّدٍ وَعَلَى آلِ مُحَمَّدٍ كَمَا بَارَكْتَ عَلَى إبْرَاهِيمَ وَعَلَى آلِ إبْرَاهِيمَ إنَّكَ حَمِيدٌ مَجِيدٌ».

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

30 Jan, 18:23


አላህ ማለት እኮ

የቤትህን በሮች ዘጋግተህ ልታምፀው እንደሆነ እያወቀ በበሩ በታች በኩል እንድትተነፍስ አየር የሚልክልህ አዛኝ የሆነ ጌታ ነው።

አልሀምዱሊላህ ❤️‍🩹🫶

Yasin nuru's hadis

30 Jan, 08:56


ኮብራው እባቡ ላይ ተጠምጥሞ አንቆ ገደለው። ኮብራውም በእባቡ ተነድፎ ነፍሱ ተላቀቀች። ማንም ድል ሳያደርግ ሁለቱም ሞቱ። ከአንድ ቤት የወጡ ተመሳሳይ ዝርያዎች እርስ በርስ ሲናከሱ ተያይዘው አለቁ።

የሙስሊሞች ምሳሌም ይህ ነው እርስ በርሳቸው ሲጣሉ አሸናፊ አይኖርም ሁሉም ይሸነፋሉ ሁሉም ይከስራሉ

ኢብኑ ቁተይባ ዑዩኑል አኽባር በተሰኘው ኪታባቸው ላይ ያሰፈሩትን ታሪክ እንካችሁ
  ዐብዱላህ ኢብኑ ዙበይርና ዐብዱልመሊክ ኢብኑ መርዋን እርስ በርስ መዋጋት በጀመሩበት ሰዓት የሮማዊያን መኳንንቶችና የጦር አበጋዞች ተሰባስበው ንጉሳቸው ዘንድ አመሩ።

  "ንጉስ ሆይ! ሙስሊሞች እርስ በርስ መጣላት ጀምረዋል። ይህ ዕድል ሳያመልጠን በተዳከሙበት እንፋለማቸው" አሉት። ንጉሱ ግን "በፍፁም!" በማለት ግርምትን የሚያጭር መልስ ሰጣቸው።

መኳንንቶቹ በመልሱ በመደነቅ ምክኒያቱን ጠየቁ። ንጉሱም ሁለት ውሻዎችን አስመጣና እንዲያናክሷቸው አስደረገ። ውሻዎቹ እርስ በርስ እየተናከሱ ፀባቸው ሲፋፋም ቀበሮ አስመጣና ወደ ውሾቹ ላከ። በዚህ ጊዜ ውሻዎቹ ፀባቸውን ትተው በመተባበር ቀበሮውን አሳደው ገደሉት። በዚህ ጊዜ ንጉሱ
"የኛና የሙስሊሞች ምሳሌ ይህ ነው! ካጠቃናቸው አንድ ሆነው ይጨርሱናል! ከተውናቸው ግን እርስ በርስ ይጨራረሳሉ" አላቸው።

ይኸው ነው ምሳሌያችን እርስ በርስ መናከሳችን ትርፉ ለጠላት መሆኑን ነው የሚነግረን ታሪካችን

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

29 Jan, 07:30


ወላሂ! አሁን ያለንበት አሳዛኝና አሳፋሪ ተጨባጭ!

«በተለይም» ዲን ላይ አለን የምንል ሰዎች!

☘️መጨካከኑ በዛ!
🎙ኡስታዝ ኢብራሂም ሙሳ

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

18 Jan, 04:10


ረጀብን ለረመዳን ስንቅ! | በኡስታዝ ካሚል ሸምሱ | የጁሙዓ ኹጥባ | የጁሙዓ መልእክቶች | خطبة الجمعة | Jume'a Sermon

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

17 Jan, 17:16


የጌታህ ሰራዊት جنود ربكየ09/05/2017 (17/07/1446ሒ) የጁሙዓህ ኹጥባ በኡስታዝ ያሲን ኑሩ በነጃሺ ኢንተርናሽናል መስጅድ (አፍሪካ ህብረት)

👤 USTAZ YASSIN NURU ኡስታዝ ያሲን ኑሩ

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

17 Jan, 03:13


•_🌺ፏ ያለ ጁማአ ይሁን ላችሁ 🌺_•

የጁመዓ ቀን ሱናዎች

↩️ ‏سنن يوم الجمعة
🌹➊ الغسل
🌹➋ الطيب
🌹➌ السواك
🌹➍ لبس الجميل
🌹➎ قراءة سورة الكهف
🌹➏ التبكير لصلاة الجمعة
🌹➐الإكثار من الدعاء والصلاة على النبي

🌹➊ መታጠብ
🌹➋ ሽቶ መቀባት
🌹➌ ሲዋክ መጠቀም
🌹➍ ጥሩ ልብስ መልበስ
🌹➎ ከህፍን መቅራት
🌹➏ ለጁመዓ ሶላት መጣድ
🌹➐ በነብዩ ﷺ ላይ ዱዓና ሰለዋት ማብዛት

↩️ قَالَ رَسُولَ اللَّهِ ﷺ من قرأ سورةَ الكهفِ في يومِ الجمعةِ ، أضاء له من النورِ ما بين الجمُعتَين

የአላህ መልዕክተኛ ነብያችን ﷺእንዲህ ብለዋል፦ ((የጁምዓ ቀን ሱረቱል ከህፍን የቀራ ሰው አላህ በሁለቱ ጁምዓዎች መካከል ብርሃንን ያበራለታል።))
📚 صحيح الجامع - رقم : (6470)

لقولهﷺ أكثروا من الصلاة عليَّ ليلة الجمعة وىوم الجمعة فإنَّ صلاتكم معروضة عليَّ

እንዲሁም ብለዋል ﷺ የጁመዕ ሌሊትና  ቀኑ ለይ በኔ ሰለዋትን  አብዙ። ሶለዋታችሁ እኮ ለኔ ይቀርብልኛል።

اللهم صل وسلم وبارك على نبينا وحبيبنا محمد وعلى آله محمد كما صليت على ابراهيم وعلى آل إبراهيم إنك حميد مجيد اللهم بارك على محمد وعلى آل محمد كما باركت آل إبراهيم وعلى إبراهيم إنك حميد مجيد

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

15 Jan, 19:27


ከ464 የግፍ ቀናት በኃላ የጋዛ ንጹሀን ሰላማዊ ሌሊትን በአላህ ፍቃድ ዛሬ ምሽት ያሳልፋሉ። ሰማዕቶቻችሁን አላህ ይቀበል፣ ቅዋችሁንም የበለጠ ኃያል ያድርገው..!


الله اكبر

Yasin nuru's hadis

15 Jan, 10:55


Update!‼️

የአክሱም ከተማ ትምህርት ቢሮ ኋላፊ ወይዘሮ ፀጋ የአክሱም ከተማ ፍርድቤት ያስተላለፈው የእግድ ውሳኔ አልቀበልም ብለዋል። ሙስሊም ሴት ተማሪዎቹ ዛሬ ከሒጃባቸው ጋር ተመሳሳይ የሆነ ዩኒፎርም ለብሰው ለማማር ወደ የትምህርትቤቶቻቸው ሂደው የነበሩ ቢሆንም ዛሬም ተከልክለዋል። የ12ኛ ክፍል ተማሪዎቹም ፎርም የመሙላት እድል ይኖራል ብለው ዛሬ ጠይቀው የነበረ በቢሆንም ጊዜው እንዳበቃ ተነግሮአቸው ተመልሰዋል። ሁለት ትምህርት ቤቶች የፍርድቤቱ የእግድ ደብዳቤ አንቀበልም ብለው መልሰዋል። 

ሙስሊም ሴት ተማሪዎቹ እየተበደሉ ያሉት የአላህ ትእዛዝ በማክበራቸው ነው፤ የአላህን ትእዛዝ በማክበሩ ደግሞ የተሸነፈ አካል የለም። በመሆኑም በመጨረሻ ላይ እነዚህ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች አሸናፊ ሆነው እንደሚወጡ አልጠራጠርም። ይህ ታሪክ በወርቃማ እና በጥቁር እየተፃፈ ነው። የሴቶቹ በወርቃማ የከልካዮቹ ደግሞ በጥቁር። የሙስሊም ሴት ተማሪዎቹ የሒጃብ ትግል "የአክሱም ሙስሊም ሴት ተማሪዎች የፃነት ትግል" ተብሎ የታሪካችንን አካል ሆኖ ተጽፎ ይነበባል።

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

15 Jan, 06:09


ተወዳጁ ነቢይ [ﷺ] እንዲህ ብለዋል: ‐
«በተምር ቁራጭ ቢሆንም እንኳን እሳትን ተጠንቀቁ።» ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።

ኢማም ኢብኑል‐ቀዪም [ረሒመሁላህ] እንዲህ ይላሉ: ‐

«ሶደቃ ሰውየውን ከአላህ ቅጣት ይታደጋል። ወንጀሉና ኃጢኣቱ ጥፋት ሲፈርድበት። ሶደቃ ይመጣና ከቅጣት ያድነዋል። ከጥፋት ያላቀዋል።»

#በተምር ቁራጭም ቢሆን ነፍሳችሁን ከእሳት ጠብቁ!…

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

14 Jan, 08:48


(وَقَالُوا۟ ٱتَّخَذَ ٱلرَّحۡمَـٰنُ وَلَدࣰا * لَّقَدۡ جِئۡتُمۡ شَیۡـًٔا إِدࣰّا *  تَكَادُ ٱلسَّمَـٰوَ ٰ⁠تُ یَتَفَطَّرۡنَ مِنۡهُ وَتَنشَقُّ ٱلۡأَرۡضُ وَتَخِرُّ ٱلۡجِبَالُ هَدًّا *  أَن دَعَوۡا۟ لِلرَّحۡمَـٰنِ وَلَدࣰا *  وَمَا یَنۢبَغِی لِلرَّحۡمَـٰنِ أَن یَتَّخِذَ وَلَدًا *  إِن كُلُّ مَن فِی ٱلسَّمَـٰوَ ٰ⁠تِ وَٱلۡأَرۡضِ إِلَّاۤ ءَاتِی ٱلرَّحۡمَـٰنِ عَبۡدࣰا *  لَّقَدۡ أَحۡصَىٰهُمۡ وَعَدَّهُمۡ عَدࣰّا *  وَكُلُّهُمۡ ءَاتِیهِ یَوۡمَ ٱلۡقِیَـٰمَةِ فَرۡدًا )

«አር-ረሕማንም ልጅን ያዘ (ወለደ)» አሉ፡፡ ከባድ መጥፎን ነገር በእርግጥ አመጣችሁ፡፡ በእርሱ (በንግግራቸው ምክንያት) ሰማያት ሊቀደዱ፣ ምድርም ልትሰነጠቅ፣ ጋራዎችም ተንደው ሊወድቁ ይቃረባሉ፡፡ ለአልረሕማን ልጅ አለው ስለአሉ፡፡ ለአልረሕማን ልጅን መያዝ አይገባውም!! በሰማያትና በምድር ያለው ሁሉ (በትንሣኤ ቀን) ለአልራሕማን ባሪያ ኾነው የሚመጡ እንጂ ሌላ አይደሉም!)

[መርየም:88–95]

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

14 Jan, 04:24


ኢብኑ ሐዝም እንዲህ ይላሉ፦

"ወደ ጓደኛህ ነፍሱን የሚያሳምመው እና በማወቁ የማይጠቀምበት የሆነን ነገር አታድርሰው። ይሄ የወራዶች ተግባር ነው።" [ረሳኢሉ ኢብኒ ሐዝም፡ 106]

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

13 Jan, 16:54


ይሄን ነሺዳ የሚያስታውስ🥹🥰

ቡኒየል ኢስላሙ...

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

13 Jan, 06:29


በጋዛ  ወንድሞች እና እህቶቻችን መንገላታትና በቤቶቻቸው መቃጠል ሲሳለቁ የነበሩ የሆሊውድ ዱርየዎች የዘነጡ ቤቶቻቸው  ሲነድዱ እና እነሱም ሲነፋረቁ  ማየት ምንኛ ያስደስታል ?!!

አልሐምዱሊላህ  !!

አላሁ አክበር !! 

ገና አላህ ብዙ ያሳየናል - አንጠራጠርም !

አሜሪካን ያሉ ወንድሞች  እና እህቶችን አላህ ይጠብቃቸው

Muhammedsirage

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

12 Jan, 17:49


ነገ ሰኞ ነው .......

ይፆማል🫶

Yasin nuru's hadis

12 Jan, 07:33


#አዝካር
ከፈጅር አዛን ቡኋላ

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

11 Jan, 08:08


አትንኩ ሒጃቤን!

ግጥም በሕፃን- ዚክራ እሸቱ

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

10 Jan, 17:39


https://t.me/sabr_spring



Islamic chennl new join

Yasin nuru's hadis

10 Jan, 15:49


የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
"እናንተ ነጋዴዎች ሆይ! አደራ ውሸትን ተጠንቀቁ።" [ሶሒሑ ተርጊብ፡ 1793]

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

10 Jan, 05:30


﴿إِنَّ اللهَ وَمَلَائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا﴾.

«اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ عَلَى مُحَمَّدٍ وَعَلَى آلِ مُحَمَّدٍ».

Yasin nuru's hadis

10 Jan, 05:28


ወላሂ እያንዳንዱ ፈተና ለኸይር ነዉ ...

በማጣት ይፈትነናል ከእሱ ዉጭ ማንንም
መጠየቅ እንደሌለብን እንድናዉቅ !...

ተስፋ በመቁረጥ ይፈትነናል ከእሱ ዉጭ
ማንንም ተስፋ እንዳናደርግ !...

ሰዎችን ከእኛ ያርቃል ከእሱ ዉጭ ማንም
አብሮን እንደማይቆይ ሊያሳየነሰ ።🤍

ما أجملك يا الله الحمد لله☝️

Yasin nuru's hadis

09 Jan, 18:29


ማግባትሽ ካልቀረ......

ጩኸት አትከተይ ጥመት አያፍዝዝሽ፡
አዳዲስ ፈጠራ ተይ አያደንዝዝሽ፡
የዋህ አትሁኝ ማንም አይጠምዝዝሽ፡
በተውሒድ በሱና ሰትሮ ይያዝሽ፡
የስኬትሽ ጣሪያ ሐቅ ይሁን መቅረዝሽ፡
---------------------------------
ከአህባሽ ከኢኽዋን ከሀጁሪ አደጋ፡
ፊትናን ከሚያራግብ ከቆላ አስከ ደጋ፡
የኔ ይሁን ከሚል ጭፍንተኛ መንጋ፡
----------------------------------
ተጠንቀቂ እህቴ ጫት ካዛገው ወጣት፡
ይገጥምሻል እና ሁለት ሀገር ቅጣት፡
ሰለፍዩን ምረጭ ያንን አንድ ቅንጣት፡
--------------------------------
መቼም ሰው ነውና ስህተት ባያጣውም፡
መንሀጁ ንፁህ ነው ኮተት አያውቀውም፡
ሽርክና ቢዲዐ ኹራፋት የለውም፡
---------------------------------
ፈጥነሽ አትደሰች ፈጥነሽ አትክሰሚ፡
ከሐቅ ጠላቶች ነገር አትቅሰሚ፡
በትዳርሽ ጉዳይ ነገረኛ አትስሚ፡
---------------------------------
አግቢ ጎበዝ ጀግና የሱና ሰባኪ፡
ከዘመኑ ፊትና የሌለው ንክኪ፡
የተውሒድ አፍቃሪ የሐቅ ነበልባል፡
በሩቅ ያስታውቃል ምን ግራ ያጋባል፡
ማግባትሽ ካልቀረ አግቢ የሱና ባል፡
-------------------------------
በዘመኑ ፊትና ያልተደናቆረ፡
በስሜት ተጠምዶ ውስጡ ያልጠቆረ፡
በማይችለው ጉዳይ ያልተሰነቀረ፡
ጀግና ሰው ምረጭ ማግባትሽ ካልቀረ፡

      በኑረዲን አል-አረቢ1444

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

09 Jan, 10:51


ሙስሊም ተማሪዎችን ከትምህርት ተቋማት ማገዳቸው ሲገርመን ጭራሽ ህዝበ ሙስሊሙን ከአክሱም እናባርራለን እያሉ እየዛቱ ነው። የነዚህ ሰዎች ድን.ቁ ^ርና ደግሞ የተለየ ነው። ሙስሊሙ ምን በወጣውና ነው ለናንተ የእርስ በርስ ሽኩቻ ማወራረጃ የሚሆነው? ለምን በዚህ ዘመን የጅ.ል ፖለቲካ ትጫወታላችሁ?

IbnuMunewor

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

08 Jan, 17:40


ያለ ፍትህ ድፍን አንድ አመት ሞላቸው

ተወዳጁ ሸይካችን ሸይክ አብዱ ያሲን የዛሬ  አንድ አመት በዚህ ሰዐት ከኢሻዕ ሰላት ቦኋላ ነበር ተtኩሶባቸው የተገ'ደ'ሉት።

እነሆ ሸይኽ አብዱ ምንም ፍትህ ሳያገኙ ገዳይም ሳይያዝ አመት ሞላቸው ።

ጉዳያቸውን ለማስፈፀም ሀላፊነት የወሰዱ አካላት ይኸው እስካሁን ዝምታ እንጂ ቃል አልተነፈሱም።

አላህ ይዘንላቸው ጀነተል ፍርደውስም ይወፍቃቸው

#ፍትህ

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

08 Jan, 12:33


「𑁍📲አዲስ አፕ | ተለቀቀ 𑁍」
╭┄┈┈⟢
│❏ የሶስቱ አሕካሞች ማብራሪያ

│  በኢብኑ ሀሽም(امير هاشم) የቴሌግራም ቻናል የተዘጋጀ
╰─────────────────╯    

🖇 ሙሉ ማብራሪያ የተሰጠባቸዉ ፀሁፎች በአንድ ላይ ሰብስቦ የያዘ!


├⎙  አሁኑኑ ዳውንሎድ በማድረግ ይጠቀሙ!
╰───────────

Yasin nuru's hadis

08 Jan, 12:33


「𑁍📲አዲስ አፕ | ተለቀቀ 𑁍」
╭┄┈┈⟢
│❏ የሶስቱ አሕካሞች ማብራሪያ

│  በኢብኑ ሀሽም(امير هاشم) የቴሌግራም ቻናል የተዘጋጀ
╰─────────────────╯    

🖇 ሙሉ ማብራሪያ የተሰጠባቸዉ ፀሁፎች በአንድ ላይ ሰብስቦ የያዘ!


├⎙  አሁኑኑ ዳውንሎድ በማድረግ ይጠቀሙ!
╰───────────

Yasin nuru's hadis

08 Jan, 06:23


🖋የመሬት መንቀጥቀጥ የትንሳዔ መቅረብ ምልክት ነው። ቢሆንም ነገሩ ሲከሰት ወደ አላህ በተውበት (በንስሃ) መመለስ እንዳለብን ዑለማዎች ይመክራሉ። በተረፈ ለጥንቃቄ ይረዳን ዘንድ ከባለሙያዎች የሚተላለፉ መልዕክቶችን ከማድመጥ ባለፈ፤ ያገኙትን ሁሉ ከሚያወሩ የሶሻል ሚዲያ ገፆች በሚተላለፉ መልዕክቶች ልንረበሽ አይገባም!

ረሱል (📿) እንዲህ ብለዋል፦

﴿لا تَقُومُ السّاعَةُ حتّى يُقْبَضَ العِلْمُ، وتَكْثُرَ الزَّلازِلُ﴾

“ሰዓቲቱ ‘ትንሳዔ’ አትቆምም እውቀት እስከሚነሳና የመሬት መንቀጥቀጥ እስከሚበዛ ድረስ።”

📚 ቡኻሪ ዘግበውታል: 1036

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

07 Jan, 18:35


📹 ሙስሊሙ ወደመሪነት መምጣት አለበት|ኡስታዝ ሀይደር ኸድር Harunmedia

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

07 Jan, 08:26


ቂያማ እንዲወርድብን ቸኮላቹህ

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

07 Jan, 08:25


ቂያማ እንዲወርድብን ቸኮላቹህ

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

06 Jan, 06:27


"አክሱም ላይ የተከለከለው ሂጃብ ብቻ አይደለም እስልምናም ጭምር ነው"

▣ በፌደራል መጅሊስ የትግራይ ክልል ተወካይ እንዲሁም የትምህርትና ማኅበራዊ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ተጠሪ ኢንጅነር አንዋር ሙስጠፋ ለሀሩን ሚድያ ከገለፁት

- ሀሩን ሚድያ፣ ታህሳስ 27/2017

በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የትምህርትና ማኅበራዊ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ተጠሪ ኢንጅነር አንዋር ሙስጠፋ እንዳሉት ሂጃብ እና እስልምና የማይነጣጠሉ መሆናቸውን አንስተው በአክሱም ሙስሊም ተማሪዎች ላይ ይህን ያደረጉት አካላት የእስልምና ጥላቻ ያለባቸው መሆኑን ለሀሩን ሚድያ ተናግረዋል።

በአክሱም ሙስሊም ተማሪዎች በሂጃብ ምክንያት ከትምህርት ገበታ መገለላቸውን አስመልክቶ ፌደራል መጅሊሱ ምን እየሰራ ነው ብለን ለጠየቅናቸው ጥያቄም ከትግራይ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ጋር በጋራ በመሆን ጉዳዩ እልባት እንዲያገኝ እየሰራን ነው ብለዋል።

ሙስሊም ተማሪዎች ላይ በየጊዜው የሚፈፀሙ የመብት ጥሰቶችን ለማስቆም የጠቅላይ ምክር ቤቱ የትምህርትና ማኅበራዊ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዘላቂ መፍትሄ እንዲያገኝ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እየሰራ መሆኑንም አንስተዋል።

- ሀሩን ሚድያ ከጠቅላይ ምክር ቤቱ የትምህርትና ማኅበራዊ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ተጠሪ ከሆኑት ከኢንጅነር አንዋር ሙስጠፋ ጋር ያደረግነውን ቆይታ በቀጣይ ወደ እናንተ ምናደርስ ይሆናል።

© ሀሩን ሚድያ

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

05 Jan, 06:43


ፈገግታ ሱና ነው! ፈታ እያላቹ ስሙት... ስለ አንድ ታላቅ አንባቢ ሰው ታሪክ ያጫውተናል || ተወዳጁ ኡስታዝ ያሲን ኑሩ

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

04 Jan, 08:15


የፍጥረቱ ጅማሮ || بداية الخلق | በኡስታዝ ያሲን ኑሩ| የጁሙዓ ኹጥባ | @yassinuru የጁሙዓ መልእክቶች | خطبة الجمعة

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

03 Jan, 09:27


ሙስሊም ሴት ተማሪዎች መበረታታት እንጂ በሂጃብ ምክንያት ከትምህርት ሊስተጓጎሉ አይገባም - የትግራይ ክልል እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት

ሰሉ አለ ረሱል🥰🥰

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

02 Jan, 11:21


|አብደሏህ ኢብን ኡነይስ ረ.ዐ|

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

01 Jan, 16:46


መጅሊስ መግለጫ አውጥቷል

«በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት በሙስሊሙ ማህበረሰብ ላይ የሚፈፀሙትን የመብትና የሃይማኖት ጥሰቶችን በሚመለከት የተሰጠ ወቅታዊ መግለጫ!»

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

01 Jan, 08:32


#ማሰታወሻ

ረመዳን 2 ወር ገደማ ነው የቀረው!

በተለያዬ ምክንያት የባለፈ አመት ቀዷ ያለባችሁ ካላችሁ ከወዲሁ አሟሉ! ሌሎችንም አስታውሱ!
አላህ በሰላም ያድርሰን

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

31 Dec, 07:45


የሰማዩ በር ብቻ ክፍት ነው!

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

30 Dec, 15:16


በሰዎች ግፊት የተጣለ ሰው መውደቂያው አላህ እጅ ነው

አብሽሩ🤍

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

30 Dec, 08:41


የአንሷሮቹ አለቃ سيد الأنصار

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

29 Dec, 14:10


ደ-ካ-ማ ነን ስንል ለአላህ
እንጂ ለሰው አይደለም

@yasim_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

29 Dec, 05:18


የስኬታማ ሰዎች ቁልፍ ምስጢር

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

28 Dec, 16:48


ይመለሱ ዘንድ"لَعَلَّهمْ يَرْجِعُونَ

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

28 Dec, 04:31


ረሱል(ﷺ)እንዲህ ብለዋል፦
“ሰዓቲቱ ‘ትንሳዔ’ አትቆምም እውቀት እስከሚነሳና የመሬት መንቀጥቀጥ እስከሚበዛ ድረስ።”

[አል-ቡኻሪይ: 1036]

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

27 Dec, 11:05


ዉዱ ነብይ صلى الله عليه وسلم

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

26 Dec, 17:10


የመጽሐፍ ምርቃት

በቲክ ቶክ ማኅበራዊ መገናኛ ብዙኃን ላይ "አልገደሉትም አልሰቀሉትም" የሚለው መጽሐፍን የምርቃት መርሐግብር የፊታችን ዐርብ በኢትዮጵያ የሰዓት አቆጣጠር ከምሽቱ 3 ሰዓት እንዲገኙ በታላቅ አክብሮት እና ትህትና ጋር እንጠይቅዎታለን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

26 Dec, 06:46


Alawites | ሶሪያን የገዟት አለዊቶች

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

25 Dec, 18:15


ነገ ሐሙስ ነዉ የቻለ ይፁም ያልቻለ ያስታውስ🙌

Yasin nuru's hadis

25 Dec, 16:08


ሞት ስካር አለው።

ጭንቅና ፍርሀቱም የተለየ ነው። አንድ ቀን ከመለከለል መውት ጋር ፊት ለፍት መተያየታችን አይቀርም። ምን ይውጠን ይሆን? የዛን ቀን።

እንዴት ይሆን? በዛን ሰአት ሁኔታችን። ሞት የሚጀምረው ከታች ከእግር ነው። የሚጠናቀቀው እላይ አይን ላይ ነው። ህመሙ ከታች ከእግር ጫፍ ጀምሮ ሁሉ የሰውነት አካል ወደላይ ያዳርሳል።

የዚያ ቀን የመጥፎ ሰሪዎች ስቃይ ደሞ እጅግ የከፋ ነው። ነፍሱ መለከል መውትን ስታይ በድንጋጤ በሁሉ የሰውነት አካል ውስጥ ትበተናለች። ነገር ግን ወዳ ሳይሆን በግዷ እየተፈለቀቀች እንድትወጣ ትደረጋለች።

አላህ ዃቲማችንን ያሳምርልን።

ለአላህ ስትሉ በዱአ አትርሱኝ 🙌

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

25 Dec, 11:38


ኡስታዝ ያሲን ኑሩ - አስገራሚ የነብዩላህ ሙሳ እና የፊርዐውን መጨረሻ የማታውቁት እውነታ |

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

24 Dec, 13:10


ጥቂት ስለ ሀናን...


ሀናንን ማውቃት መድረሳ ውስጥ እንዲሁም በአማና ጀምዐ ዉስጥ ስትንቀሳቀስ ጀምሮ ነው።ጀምዐ ውስጥ አሉ ከተባሉ አስተባባሪዎች ውስጥ ምትጠቀስ ነበረች።አሁን ላይ በደረሰባት ከባድ የጆሮ ህመም ምክንያት እንደ በፊቱ ተሳተፎዋ መቀጠል ቢያቅታትም አሁንም ድረስ መርዳት ማገዟን አላቆመችም።በጣም ሚሮጥ ሰው ሲቆም ያማል!!

#በጳውሎስ ሆስፒታል በተደረገላት ህክምና መሰረት
ሁለቱም ጇሮዎቿ በነርቭ ችግር ምክንያት መስማት እንደማይችሉ
በዚህም ምክንያት ጆሮዋ በየጊዜው ኢንፌክሽን እየፈጠረ በመሆኑ
የኮክሊያር ኢምፕላንት ዲቫይረስ ተከላ እንደሚያስፈልጋት የነገሩን ሲሆን
ይህም ህክምና አገር ውስጥ እንደሌለና ወደውጭ ሀገር ሄዳ እንድትታከም ነግረውናል
🚫በመሆኑም እህታችን ሀናን ሙሰማ የቲም ልጅ በመሆኗ እና ውጭ ሀገር ሄዳ ለመታከም የተጠየቀችውን 3 ሚልየን 5 መቶ ሺህ ብር ከቤተሰቦቿ አቅም በላይ ስለሆነ ከአላህ በታች ለሰው ደራሹ ሰው ነውና አነሰች ሳትሉ ለአላህ ብላቹ እርዱን እንላለን😭

ቢያንስ አላህ ፊት ስትጠየቁ ምትመልሷት መልስ ትሆናለችና በራህማን ስም አነሰች ሳትሉ ተባበሩ!#ያልቻላችሁ ሼር ማድረግ ቀላል አደለም ባላቹበት ግሩፕ or ቻናል ሼር አርጉ አላህ በጀነት ያበስራችሁ #ሼር

ንግድ ባንክ 1000632691797
አዋሽ 014251483960400
አቢሲኒያ 59484702

Yasin nuru's hadis

24 Dec, 06:27


መርሃብ መርሃብ ያ ሂላል🥰

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

23 Dec, 07:46


ጌታዬ እዘንላቸዉ... ||... رَّب ِّ ارْحَمْهُمَا

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

22 Dec, 06:40


ዝም ያለ ነጃ ወጣ🤷‍♂

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

21 Dec, 05:45


300ሺህ ብር የጠፋው እየፈለኩ ነው🤔1ሚልየን ለመቀበል👀

ኡስታዝ #ያሲን #ኑሩ

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

20 Dec, 03:15


‏﷽
۝ إِنَّ اللَّهَ وَمَلائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى
النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا
عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا ۝
اللهم صل وسلم وبارك على سيدنا محمد وعلى اله وصحبه الطيبين الطاهرين


@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

19 Dec, 10:38


"አባ ዳቦ ግዛልኝ!" የሚሉትን ከቻላችሁ ዳቦ ግዙላቸው ካልሆነ ደግሞ በፈገግታ እለፏቸው::

"አባ የሳፋሪኮም ሲም ግዛኝ!" የሚሉትንም ከቻላችሁ ግዟቸው ካልሆነም አልችልም ብላችሁ በትህትና እለፏቸው::

"አባ አካውንት ክፈት!" የሚሉትንም ከቻላችሁ አካውንት ክፈቱላቸው ካልሆነ ደግሞ በመልካም ፊት እለፉ::

ወይ በችግር ወይ በስራ ነው የወጡት:: የቸገረውን በማመናጨቅ ችግር መጨመር ችግር ነው:: ባለስራንም ማክበር ግድ ነው::

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

18 Dec, 18:55


ነገ ሐሙስ ነዉ የቻለ ይፁም ያልቻለ ያስታውስ☺️

Yasin nuru's hadis

18 Dec, 13:00


📌አላህን መፍራት ጀግንነት ነው
📌እሱን መገዛት ነፃነት ነው
📌ለእርሱ መዋደቅ ክብር ነው
📌እሱን ማወቅ እርግጠኝነት ነው🫀


🥀አንተን ላሳወከን አልሃምዱሊላህ🤍

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

18 Dec, 07:01


♻️🔻🇵🇸🇮🇱 የዕብራይስጡ Ynet ጋዜጣ "የተኩስ አቁም ስምምነቱን በ3 ምዕራፍ ተፈፃሚ ለማድረግ ከሞላ ጎደል ስምምነት ላይ ተደርሷል" ብሏል።

የእስራኤሉ ተንታኝ ባራክ ራቪድ በበኩሉ “የቀሩት ልዩነቶች በበቂ ፍጥነት ካልተፈቱባቸው ምክንያቶች አንዱ በቀድሞው የሐማስ መሪ የህያ ሲንዋር ወንድም በመሐመድ ሲንዋር የሚመራው በጋዛ የሚገኘው የሐማስ አመራር የያዘው ጠንካራ አቋም መሆኑን የእስራኤል ከፍተኛ ባለስልጣናት ነግረውኛል ብሏል።

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

17 Dec, 17:59


በቻናሉ ላይ ማስታወቂያ/Promotion ማሰራት የምትፈልጉ  አናግሩኝ

@kiswet0

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

07 Dec, 03:55


ነብዩን ጥርስ ነከሰባቸው🥶🥶

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

06 Dec, 06:53


🦋ልቡ እንዲከፈትለት ፣ወንጀሉ እንዲማርለት ፣ ችግሩ እንዲነሳለት፣ጭንቁ እንዲወገድለት የፈለገ ሰው በሠይደልዉጁድ[ﷺ]🩵 ላይ አብዝቶ ሶለዋት ያውርድ

اللّهُمّ صَلّ عَلَىٰ سَيّدِنا مُحَمّدٍ عَدَدَ حِلْمِكَ🤍  وَصَلّ علَىٰ سَيّدِنا مُحَمّدٍ عَدَدَ عِلمِكَ🤍 وَصَلّ علَىٰ سيّدِنَا مُحَمّدٍ عَدَدَ كَلِمَاتِك🤍 وَصَلّ علَىٰ سَيّدِنَا مُحَمّدٍ عَدَدَ نِعْمَتِكَ.

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

05 Dec, 10:47


ሰላም አለይኩም ውዶቼ ዛሬ አንድ ያስገረመኝን ነገር ልንገራችሁማስ ::
በተለይ እህቶቼ ይሄ ለናንተ ነው 🫵...ባለፈው በተቀመጥኩበት ቦታ ላይ አንድ የ ክላሴ ልጅ መቶ አጠገቤ ተቀመጠ እና ሞቅ ያለ ወሬ ይዘን በመሃል ስልክ ተደወለለት እናም አውርቶ ሲጨርስ ሚስቴ ነች ማንሳት ነበረኝ አለኝ እኔም አብሽር ብዬው ወሬአችንን ቀጠልን በመሃል ሚስቴ ስላለው ነገር ጠየቁት::

ያው ባሌ ሚስቴ መባባል የዘመኑ ፋሽን እንደሆነ አውቃለው ግን ያለውን አመለካከት ለማወቅ ስል እኔ ሳላውቅ አገባክ እንደ አልኩት:: እሱም ፈገግ እያለ የምፈልገው እስከሰጠቺኝ ድርስ ሚስቴ ነች አለኝ ያው ማለት የፈለገው ስሜቴን አስካበረደቺልኝ ድረስ ሚስቴ ናት ማለቱ ነው 🤦‍♂ እናም እዚህ ላይ መፃፍ ማልፈልጋቸው ብዙ ነገሮችን ነው የነገረኝ ያው መቼም ትረዱኛላችሁ በተለይ የግቢ ተማሪዎች ::

ከዛም በጣም እየገረመኝ ታገባታለህ አልኩት....በጣም እየሳቀ ትቀልዳለህ እንዴ አለኝ::ምነው ስለው የጨዋ ልጅ እና ድንግል የሆነችን ሴት እንደሚያገባ ነገረኛ እኔም አላስገረመኝም ማንስ እንደዚህ አይነቷን ያገባል::

ያው ከግቢ እስኪመረቅ ነው ወይ ደሞ ፍሬሽ ተማሪዎች እስኪገቡ ነው እስከዛው ስሜቱን ያበርድባታል ምስኪን 💔
በጣም ሚያስገርመኝ ነገር ምን እንደሆነ ታቃላችሁ ሁሉንም ነገር ምታረገው በሷ ፍላጎት መሆኑ ነው 😣 ሃታ እሱ እንዳለኝ ከሆነ አንዳንዴ የቤርጎ እራሱ እሷ እንደምከፍል ነው የነገርኝ 🤦‍♂

በርግጥ ሁለቱም ካፊር ናቸው ግን ግቢ ላይ አንዳንድ ኢስላምን ሚያሰድቡ ሰዎች አጋጥመውኛል::እናም እህቶቼ ምን ልላችሁ ፈልጌ ነው ህይወት ይቀጥላል ከተመረቃቹ ቡሃላ ትዳር ሚባል ነገር አለ ልጅ መውለድ አለ ብቻ ብዙ ኃላፊነት ይጠብቃቹሃል::
ሃቂቃ እኔ ያየውትን ካየው ቡሃላ ወደፊት አግብቼ ሴት ልጅ ከወለድኩኝ መቼም ግቢ አልካትም ይሄ የኔ አመለካከት አይደለም ብዙ ሰውን ጠይቄ ሁሉም በኔ ሃሳብ ነው ሚስማማው::

እናም ውዴ....እህቴ ላይ እንዲደርስ ማልፈልገውን ነገር አንቺም ላይ እንዲደርስ ስለማልፈልግ ይሄን ምክሬን ተቀበይኝ አንዴ መተሻልና በቃ ለመጣሽበት አላማ ጠንተሽ ስሪ 🥰  አስቢው ወላጆችሽ እዚህ እንድትደርሽ ብዙ ዋጋ ከፍለዋል... ለአንድ ለማታቂው ወንድ ብለሽ ውለታቸውን አትብይ 🙌

ትምህርትሽ ላይ ብቻ አቶክሪ ❤️

©ሪያድ

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

04 Dec, 18:53


ነገ ሐሙስ ነዉ ለምን አንፆምም ?

ያልቻለ ያስታውስ

Yasin nuru's hadis

04 Dec, 06:28


ሙስሊሞች የረሱት የመጨረሻው ስዓት |ኡስታዝ ያሲን ኑሩ |

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

03 Dec, 05:24


ነቢዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፡-
«ما من مسلم يتوضأ فيُحسن وضوءه، ثم يقوم فيُصلي ركعتين، يُقبل عليهما بقلبه ووجهه إلا وجبت له الجنة» [رواه مسلم]

“ማንኛውም ሙስሊም ውዱዑን አሳምሮ በማድረግ ፤ ከዚያም በቀልቡም ሆነ በፊቱ ወደ አላህ ተመልሶ ሁለት ረከዓ አይሰግደም። ለሱ ጀነት የተወሰነች ብትሆን እንጂ።”


@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

02 Dec, 07:19


#ስጥ
#ustaz_nuru_turki

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

02 Dec, 06:34


እስኪ ስለዚህ ቻናል በቀናነት አስተያየት
ስጡን ምናስተካክለው ነገር ካለ?

ዝም ማለት አይቻልም!!

Yasin nuru's hadis

01 Dec, 17:58


ለዛሬ እዚህ አበቃን ኢንሻአላህ በሌላ ቀን እስክንገናኝ ወሰላም ዓለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካትሁ ደህና እደሩ 🙌

Yasin nuru's hadis

01 Dec, 17:56


መልስ

ጅብሪል አለይሂ ሰላም

ማሻ አላህ ሁላችሁም መልሳችሁታል ቀድማ የመለሰችውን በውስጥ ሽልማቱን እናደርሳለን ።

Yasin nuru's hadis

01 Dec, 17:51


ጥያቄ 1

በጣም ቀላል ጥያቄ

የሐበሻውን ንጉሥ ህልፈት ለነብዩ صل الله عليه وسلم የነገራቸው ማን ነበር?

Yasin nuru's hadis

01 Dec, 17:47


መልስ

1,ኛ ሶፊያ ቢንት ሁየይ ቢን አኽጠብ

2,ኛ ሱረቱል ዩሱፍ

ማሻ አላህ አብዛኛዎቻችሁ መልሳችሁታል ግን ቀድሞ የመለሰ ነው አሸናፊው ብለን ነበር ቀድሞ/ቀድማ የመለሰችው kunfeyekun ሚል አካውንት ነው ነገር ግን ሙሉ ስም አልፃፈቸም ስለዚህ ለሁላችሁም አንድ ዕድል ይሰጣችሁ እና አንድ ጥያቄ ይጨመር ቀድሞ በትክክል ሙሉውን የመለሰ እንሸልማለን እና መማሪያም ይሆናችኋል ምትስማሙ ከሆነ React በ አሳዩን ።

Yasin nuru's hadis

01 Dec, 17:35


መልስ ስትፁፉ ሙሉውን

Yasin nuru's hadis

01 Dec, 17:34


ሞክሩ እንጂ እስከ 3.00 እንጠብቅ ።

Yasin nuru's hadis

01 Dec, 17:30


1, ኛ ጥያቄ

ረሱል صل الله عليه وسلم በኸይበር ዘመቻ ያገኟቸዉ ሚስታቸዉ ማን ናቸዉ

2, ኛ ጥያቄ

ከመቶ በላይ አንቀፆችን የያዘች እና ስለ ጀነትም ሆነ ስለ እሳት (ጀሀነም) ያልተወሳባት ብቸኛ የቁርዐን ምዕራፍ ምንድን ናት ?

2ቱንም ቀድሞ የመለሰ ነው አሸናፊው

መልካም ዕድል

Yasin nuru's hadis

01 Dec, 17:20


2.30 ሲል ምንጀምር ይሆናል 2 ጥያቄ ነው ሁለቱንም ቀድሞ የመለሰ 1 ሰው ካርድ እንሸልማለን።

Yasin nuru's hadis

01 Dec, 15:24


እስከዛው ወደ አዲሱ ቻናላችን ጎራ እያላችሁ☺️


https://t.me/islamic_remeinder

Yasin nuru's hadis

01 Dec, 11:44


አሰላም ዓለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካትሁ እንዴት ናችሁ ያ ጀምዐ ? ኢንሻአላህ ማታ ላይ ቀለል ያሉ ጥያቄዎች ይኖሩናል ቀድሞ የመለሰ አንድ ሰው ተሸላሚ ይሆናል።

Yasin nuru's hadis

01 Dec, 07:01


#ሰብር

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

30 Nov, 04:13


አላህን ከያዝክ ያዘዘውን ከፈፀምክ ምንም አትሆንም!

እናትህን እጇን ይዘክ ዱአ አርጊልኝ በላት🥰🥰

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

26 Nov, 05:15


📌ሰዎችን ለማስደሰት ስትኖር አላህ (ሱ.ወ) አንተን ለማስደሰት የሚኖር ሰው ይልክልሀል!
የመልካም ነገር ምንዳው መልካም ነውና 🤍


♡ ㅤ     ❍ㅤ       ⎙ㅤ      ⌲  
ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ   ˢᵃᵛᵉ      ˢʰᵃʳᵉ

@islamic_remeinder

Yasin nuru's hadis

25 Nov, 06:48


«በሰዎች ስሜት ላይ ጉዳት እንዳታደርስ ጥንቃቄ አድርግ፡፡ ማለትም፡-

× ስለሃብትህ በድሃ ፊት፤
× ስለጤንነትህ በህመምተኛ ፊት፤
× ስለጥንካሬህ በደካማ ፊት፤
× ስለደስታህ በሃዘንተኛ ፊት
× ስለነጻነትህ በታሰረ ሰው ፊት
× ስለልጆችህ በመካን ፊት
× ስለአባትህ በየቲሞች ፊት
× ስለትዳርህ ትዳር ባልተሳካላቸው ሰዎች ፊት አታውራ፡፡

በቁስላቸው ላይ የምትጨምር ከሆነ በቁስል ላይ ቁስል እየጨመርክ በአላዋቂነትህ ትጎዳቸዋለህ»



@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

24 Nov, 14:31


Aselam aleykum werahmetulahi weberekathu Addis yetekefete chennl new ke krb gize buhala in'sha'allah astemari negerochn enlekalen join and share bemareg tebaberun 😊

Yasin nuru's hadis

24 Nov, 14:31


https://t.me/islamic_remeinder

Yasin nuru's hadis

24 Nov, 07:40


መንገድ ጠፍቶን ስንደናበር ላረጋጉን ፣ ወደቅን ስንላቸው ላልፈረዱብን ። በድለናቸው ይቅርታን ለሰጡን ፦

ሚስጥራቸውን ላጋሩን፣  ደስታችን ለተካፈሉ፣ ሃዘናችንን ቦታ ለሰጡት ፣ ለተጠነቀቁልን ፣አጋርነታቸው ወረት ለሌለበት ፣ በቆሚነት የኛ ለሆኑ ።

እንድናምናቸው ለሆኑ ፣ ደግነታቸው ለማይስተን ፣ ለሚወዱን ፣  ሊረዱን ግማሽ መንገድ ለሚመጡ ፣  ለሚያበረቱን

ኑሩልን

   ©Adhanom Mitiku

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

23 Nov, 05:44


ሴት ልጅን አግቢ እንጂ አይባልም። አልፎ አልፎ እየሰማች ለዱንያ አኼራዋ የሚበጀውን ትዳር ግጠማት ብሎ ዱአ ይደረጋል። ማስተዳደር የሚችልን ወንድ ልጅን ግን አግባ እንጂ ቁመህ ቀረህኮ ይባላል።

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

22 Nov, 05:38


‏﷽
۝ إِنَّ اللَّهَ وَمَلَائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ ۚ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا ۝ 🌷


@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

21 Nov, 09:30


አይናችሁ የቱ ጋር አረፈ🥹?

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

20 Nov, 17:31


ነገ ሐሙስ ነዉ የቻለ ይፁም
.
ያልቻለ ለመቻል ይሞክር ☺️
.
.
መልካም ነገርን የጠቆመ ከሰሪው እኩል አጅር ያገኛል እና ሌሎችንም አስታውሱ 🙌

መልካም ለይል

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

20 Nov, 11:33


100 days until Ramadan!
اللهم بلغنا رمضان
ረመዷንን 100 ቀናት ቀሩት

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

20 Nov, 05:32


የማንንም ልብ ለማሸነፍ ስትይ
ማንነትሽን አትቀይሪ   አንችን የሚወድሽ ሰዉ
ከነ ማንነትሽ ይቀበልሻል

Yasin nuru's hadis

20 Nov, 05:30


﴿للهِ مُلْكُ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ وَمَا فِيهِنَّ وَهُوَ عَلَى كُلِّ شَيْءٍ قَدِيرٌ﴾.

«سُبْحَانَكَ اللَّهُمَّ وَبِحَمْدِكَ ، أشْهَدُ أنْ لَا إلَهَ إلَّا أنْتَ ، تَبَارَكْتَ وَتَعَالَيْتَ ، أسْتَغْفِرُكَ وَأتُوبُ إلَيْكَ ، وَلَا حَوْلَ وَلَا قُوَّةَ إلَّا بِكَ».

Yasin nuru's hadis

19 Nov, 18:49


ሐላል ትዳር እና ሐላል ሥራ ላሳሰበው ሁሉ ቆንጆ ዱዓዕ -
~
"አልላሁምመ-ክፍኒ ቢሐላሊከ ዐን ሐራሚከ ወአግኒኒ ቢፈድሊከ ዐምመን ሲዋከ"
ትርጉም:–
ጌታዬ ሆይ ከሐራምህ በሐላልህ አብቃቃኝ። በችሮታህም ካንተ ውጭ ያለውን እንዳላስብ ብቃኝ ።

Yasin nuru's hadis

19 Nov, 03:47


በሁሉ ነገራችን አላህ ባይሠትረን ኖሮ ከእፍረት              ብዛት አንገታችን ተሰብሮ በቀረ ነበር ።
 
ሲትራከ ያ ረሕማኑ


@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

19 Nov, 03:47


﴿قَدْ أَفْلَحَ الْمُؤْمِنُونَ﴾.

«اللَّهُمَّ إنَّا نَسْألُكَ إيمَانًا دَائِمًا وَيَقِينًا ثَابِتًا وَعِلْمًا نَافِعًا وَهَدْيًا قَيِّمًا».

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

18 Nov, 15:14


ማስታወሻ 

1- ሸሪዓዊ ስርዓቶችን ባማከለ መንገድ መተራረም በሙስሊሞች መካከል ሊሰፍን የሚገባ የወንድማማችነት መገለጫ ነው! አላህ እንዲህ ብሏል፦
{وَالْمُؤْمِنُونَ وَالْمُؤْمِنَاتُ بَعْضُهُمْ أَوْلِيَاءُ بَعْضٍ يَأْمُرُونَ بِالْمَعْرُوفِ وَيَنْهَوْنَ عَنِ الْمُنْكَرِ..}
«ወንድ አማኞችም ሴት አማኞችም ከፊላቸው የከፊላቸው ረዳት ናቸው፤ በበጎ ያዛሉ፤ ከመጥፎም ይከለክላሉ…» [አት-ተውባህ ፡ 71]

2- ምክር በመሰረቱ በግል መተላለፉ ቢመረጥም በተሰራጩና በይፋ በሚተገበሩ ጉዳዮች ዙሪያ እውቀት ላይ የተመረኮዘ ገንቢ ምክር በይፋ መለገሱ ብዙዎችን የሚያርምና የሚያስተምር ይሆናል። ሆኖም፦

3- ስህተት የፈፀመን ለይተው ሳይጠቅሱ ጥቅል ምክሮችን በይፋ ማስተላለፍ የመልዕተኛውን ፈለግ የተከተለ አንድ ስልት ነው። የሙእሚኖች እናት ዓኢሻህ እንዲህ ትላለች፦
كَانَ النَّبِيُّ -صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ- إِذَا بَلَغَهُ عَنِ الرَّجُلِ الشَّيْءُ لَمْ يَقُلْ: مَا بَالُ فُلَانٍ يَقُولُ؟ وَلَكِنْ يَقُولُ: مَا بَالُ أَقْوَامٍ يَقُولُونَ كَذَا وَكَذَا؟
= «ነብዩ (ﷺ) ስለ አንድ ግለሰብ አንድ ወሬ ሲደርሳቸው “እገሌ ምን ሆኖ ነው እንዲህ የሚለው!” አይሉም ነበር! ነገር ግን “እንዲህ የሚሉ ወገኖች ምን ሆነው ነው?” ይሉ ነበር።»
[አቡ ዳዉድ (4788) በትክክለኛ ሰነድ ዘግበውታል፤ (“ሲልሲለቱ’ል-አሓዲሥ አስ-ሶሒሓህ” ቁጥር 2064)]

ለዚህ ምሳሌ የሚሆኑ ሐዲሦች እጅግ ብዙ መሆናቸው ይታወቃል።
እንዲያውም ለአስር አመታት የነብያችን አገልጋይ (ኻዲም) የነበሩት አነስ ኢብኑ ማሊክ ስለ እርሳቸው እንዲህ ማለታቸው ተዘግቧል፦
"وَكَانَ لَا يَكَادُ يُوَاجِهُ أَحَدًا فِي وَجْهِهِ بِشَيْءٍ يَكْرَهُهُ.."
«አብዛኛውን ጊዜ አንድን ሰው በሚጠላው ጉዳይ ፊት ለፊቱ አይጋፈጡትም ነበር።» [(አህመድ (12573)፣ (12367)፣ (12628) አቡ ዳዉድ (4182)፣ (4789)] (በሰነዱ ውስጥ ያለው “ሰልም አል-ዐለዊ” የተባለውን ግለሰብ በተመለከተ የሐዲሥ ሊቃውንት ዘንድ ውዝግብ ያለ ሲሆን ብዙሃኑ ደካማ እንደሆነ ፈርደዋል።)

4- በትምህርታዊ ምክር ተጠቃሚ እንዳንሆን ከሚያግዱን እንቅፋቶች አንዱ መልዕክቱን አገናዝቦ ራስን በመፈተሽ ፈንታ “ለማን ታስቦ ነው? ማንን ደግፎ ነው? ማንንስ ነቅፎ ነው?..” በሚል ሀሳብ መዋለልና አልፎም በዚህ ላይ መነታረክ ነው። ከዚህ ይልቅ ለሁሉም የሚበጀው፦
" فإمَّا أَن تنطق بِعِلم، وَإِمَّا أَن تسكت بحِلم "
((ወይ በእውቀት ተናገር፤ አሊያም ችለህ ዝም በል!))
[ከአል-ኢማም አዝ-ዘሀቢይ ንግግሮች ነው።]

5- ከአንድ ሰው ንግግር በተዘዋዋሪ የተረዳነውን ግንዛቤ ከአንደበቱ እንደወጣ ቀጥተኛ ንግግር ወይም አቋም መቁጠር እንደማይፈቀድ የኢስላም ሊቃውንት አስፍረዋል! [ለምሳሌ፦ “መጅሙዑ’ል-ፈታዋ” (20/217) ይመልከቱ!]
አደራ! ያልተፃፈ አይነበብም፤ የተፃፈውም ያለ አግባብ አይመነዘርም!

6- የመካሪም ሆነ የሌላ ስህተት ባለቤቱን እንጂ ሌላን አይመለከትም፤ በግልፅ መረጃዎች ያልተቋጨ ጉዳይ ላይ የሚሰነዘርም ቃል ተናጋሪውን እንጂ ሌላን አይወክልም!

7- በፌስ ቡክ ላይ የሚፃፉ አስተያየቶችና መልዕክቶች ለሺዎች እንደሚደርሱና እንደሚዳረሱ አንዘንጋ! በዚህ ላይ የተለያዩ አመለካከቶች፣ አላማዎች፣ የግንዛቤ ደረጃዎችና ስሜቶች ያሏቸው ተጠቃሚዎች የሚስተናገዱበት መድረክ ነው።

===================
በምፅፋቸው መልዕክቶች የማቅደው ጥቅል ትምህርታዊ ምክርን እንጂ ወቀሳንና ተራ ትችትን አይደለም፤ ገለፃዎቹም ገንቢ እንጂ አፍራሽ ቃና እንደሌላቸው ተስፋ አለኝ፤ ለዚህም ነው በአብዛኛው የዑለማዎችን ንግግር በማጣቀስ ላይ የምገደበው።
{إِنْ أُرِيدُ إِلَّا الْإِصْلَاحَ مَا اسْتَطَعْتُ وَمَا تَوْفِيقِي إِلَّا بِاللَّهِ عَلَيْهِ تَوَكَّلْتُ وَإِلَيْهِ أُنِيبُ}
አላህ ለርሱ ብለው ከሚዋደዱ ያድርገን!
أخوكم في الله: إلياس أحمد

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

18 Nov, 08:06


Mohammed Ali👊👊

አላህን ከያዝክ ምንም ነገር አያስፈራክም

@yasin_nuru_hadis‌‌‌‌

Yasin nuru's hadis

17 Nov, 18:26


የሰነፍ ወንድ ህልም
ሀብታም ሴት ማግባት ነው

አንተ ምታገባት ጠብ እርግፍ ብለህ
    ልታስቱዳድራት  እንጂ
ልታስተዳድርህ መሆን የለበትም

ወንድ ሁን

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

17 Nov, 14:03


አንድ ሰው ካማኸው ምንድን ነው መፍትሄው?

እንዳማኸው ካወቀ በግልፅ ወዳማኸው ሰው ሂድና ይቅርታ (ዐውፍታ) ጠይቀው።

ካላወቀ፦ አላህ ወንጀሉን እንዲምርለት ዱዓእ አድርግለት፣ በዛ ባማኸው ቦታ ስለርሱ ጥሩ ጎን አውራና አወድሰው። መልካም ሥራ መጥፎን ያብሳልና!

ኢብኑ ዑሠይሚን

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

16 Nov, 07:25


እናቴ🥰🥰🥰

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

15 Nov, 17:41


☀️رَبَّنَا آتِنَا فِي الدُّنْيَا حَسَنَةً وَفِي الآخِرَةِ حَسَنَةً وَقِنَا عَذَابَ النَّار

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

15 Nov, 09:29


ሰሉ አለ ረሱል🥰🥰

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

15 Nov, 06:06


በነገራችን ላይላይ

ጁሙዐ ቀን ኹጥባ እየተደረገ ማውራት እንደማይፈቀድ ይታወቃል።

ሌላው ቀርቶ ወሬ የያዘን ሰው "ዝም በል" ብሎ ማናገር እንኳ አይገባም። "ታዲያ እንዴት አድርገን ዝም እንዲል እናድርግ?"

ከተባለ ያለ ንግግር በእጅ በማመላከት መጠቆም ይቻላል። የምልክት ጥቆማ በኹጥባ ቀርቶ በሶላትም ውስጥ ይፈቀዳል።

ኢብኑ ዑመር እና መጅዘአ ብኑ ዛሂር አልአስለሚይ - ረዲየላሁ ዐንሁም - ኹጥባ እየተደረገ በጥቆማ ያመላክቱ እንደነበር ተጨባጭ መረጃ መጥቷል። [ሙሶነፍ ዐብዲረዛቅ፡ 3/225] [ሙሶነፍ ኢብኒ አቢ ሸይባህ፡ 2/117]

ኢብኑ ረጀብ አልሐንበሊይ ረሒመሁላህ "በጥቆማ ማመላከት እንደሚቻል በዑለማእ መካከል ልዩነት የለም" ብለዋል። [ፈትሑልባሪይ ፡ 5/496]

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

14 Nov, 07:39


እስልምና ፀጋ ነዉ
ኢብራሂም ለአባቱ ተመኘ ኑህ ለልጁ
ሙሀመድ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ለአጎቱ
አላህ ይህንን ፀጋ ሳናስበዉ ሳንጠይቀዉ ለኛ ሰጠን!

ይህንን ፀጋ እኛ ግን አስተንትነነዉ እናቃለን....?

አላህ በባሪያወቹ ላይ በርካታ መልካም ነገሮችን
ሰቶቸዋል በርካታ ሰወች ግን አያመሰግኑም!💔


@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

14 Nov, 07:32


አላህ ከጀሃነም ቅጣት ይጠብቀን🥹🥹

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

13 Nov, 04:36


እርሷ ንግስት ናት

ጌታዋን በብቸኝነት ያመለከች፣ ለርሱም ጊዜውን ጠብቃ ሰላቷን የሰገደች!!

ሂጃቧን በስርአት የለበሰች እና በሀያዕ ያሸበረቀች ሴት በርግጥም  እርሷ ንግስት ናት👌



               
@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

12 Nov, 12:07


ለነፍሳችን እንድረስለት

ሰሌን ደህና ማረፊያ አይደለም ። አካልን ምቾት የሚነሳ መሻከር እንዳለበት የታወቀ ነው ….

ነብዩ ይሄው ሰሌን ላይ ይተኙ ነበር ።  ሰሌኑም ጎናቸው ላይ ምልክትቱን ይጥል ነበር ።
ባልደረቦቻቸው “ ለምን የተሻለን ምንጣፍ አናደርግልህም ?”  ሲሏቸው

ما لي وللدنيا؟ ما أنا في الدنيا إلا كراكب
استظل تحت شجرة، ثم راح وتركها

“ እኔና ዱንያ ምንና ምንድን ነን ? እኔ እኮ ዱንያ ውስጥ ዛፍ ስር ( ለማረፍ ) እንደተጠለለ አንድ ( መንገደኛ ) ጋላቢ ነኝ .. ከዚያም ሄደ ተዋትም ….

አንዳንዴ ቤታቸው ውስጥ የሚላስ የሚቀመስ ይጠፋ ነበር … በርግጥ ነው አንዳንዴ በርከት ያለ ነገር የነብዩ እጅ ውስጥ ይገባ ነበር ። ነገር ግን እጃቸው ውስጥ የገባውን ሪዝቅ በአላህ መንገድ ላይ ያከፋፍሉት ነበር ….

የነብዩ ባልደረቦች የሚለበስ በማጣት ተፈትነዋል ፣ ረሃብን አብዝተው አስተናግደዋል … ግባቸው የአላህን ውዴታ ማግኘት ነበርና ታገሱ ፣ ፈተናውን በአግባቡ ተወጡ …  ግን ከነ ችግራቸው የደስታን ህይወት ገፍተዋል  …

የኛ ነገርማ

ትልማችን አለማዊ ሆኗል ! ህልማችን የዱንያው ሸቀጥ ብቻ ሆኖ አኺራን ዘንግተናል … ወጋችን ባንክ ነው .. ሚዛናችን ሃብትና ዘር ነው - አላህ ያዘነት ሲቀር ጠፍተናል  እየጠፋን ነው ።

ለነፍሳችን እንዘን ፣ ወደ አላህ መንገድ እንመለስ  …

አላህ ይመልሰን !!

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

11 Nov, 08:32


🎖🎖ቢስሚላህ ብሎ የመጠጣትና የመብላት ጥቅሞች፡፡ነብዩ ሰዐወ ከ1400 አመት በፊት የተናገሩትን በዚህ ዘመን ሳይንቲስቶች ያረጋገጡት እዉነታ

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

10 Nov, 17:37


Imagine በባቡረያን የጀነት በር ሰብሰብ ብለን ስንገባ 😍
እኔ ከፊት ሆኘ 😁
ባቡ ረያን :- ፆመኞች የሚገቡበት የጀነት በር
.
ነገ ሰኞ ነዉ የቻለ ይፁም ያልቻለ ያስታውስ

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

10 Nov, 07:58


ዝነኛው የሲያትል Gum Wall በታሪኩ ለሁለተኛ ጊዜ ሊፀዳ ነው ።
.....

በ1990 ዎቹ መጀመሪያ ላይ በሲያትል በሚገኝ አንድ የገበያ አዳራሽ ውስጥ በሚገኝ  ሲኒማ ቤት ፡ ፊልም ለማየት የተሰለፉ ሰወች ያኝኩት የነበረውን ማስቲካ እንደቀልድ  በግድግዳው ላይ መለጠፍ ጀመሩ ።  በጥቂት ጊዜያት ውስጥም  ግድግዳው በሙሉ በማስቲካ ተሞላ
.....
በ2009 በተሰራው Love Happens በተሰኘው የፍቅር ፊልም ላይ ፡ ጄኔፈር አኒስተንና አሮን ኤከርት በዚህ ስፍራ ተገኝተው ያኘኩትን ማስቲካ በግድግዳው ከለጠፉ በኋላ ደግሞ ፡ ስፍራው ይበልጥ ዝነኛ ሆኖ ፊልሙን ያዩት ሁሉ እየሄዱ የማስቲካ አሻራቸው ያስቀምጡ ጀመር ።
.....
ሆኖም ፡ ከቀን ወደቀን  የሚለጠፈው ማስቲካ እየበዛ  በመሄዱና ግድግዳውን እንዳይጎዳው በማሰብ. .  በ2015 ለመጀመሪያ ጊዜ እንዲፀዳ በተደረገበት ወቅት  እያንዳንዱ ሰው የሚለጥፈው  ተጠራቅሞ  2,350 ፓውንድ የሚመዝን ማስቲካ ከግድግዳው ላይ ተነስቶ የተጣለ ቢሆንም ፡ ብዙም ሳይቆይ ግድግዳው እንደገና በማስቲካ ተሸፍኖ የጎብኝዎችን ትኩረት ሲስብ ቆይቷል ።

......
በተናጠል ቀላል የሚመስሉ ድርጊቶች በህብረት አስደናቂ ነገር መፍጠር እንደሚችሉ ማሳያ የሆነው ይህ የማስቲካ ግድግዳ ከዚህ በተጨማሪም, ውበት እና ጥበብ ባልተመለዱና እንግዳ በሆኑ መንገዶች እንደሚፈጠሩ የሚያሳይ ነገር ነው ።

©መንቁል

የማይሰማ ጉድ የለም መቼስ

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

09 Nov, 07:49


🚫እንዲህ አይነቱን ሰው ከመሆን ተጠንቀቅ!

ረሱል (📿) እንዲህ ብለዋል፦

﴿أَتَدْرُونَ مَا الْمُفْلِسُ ؟ " قَالُوا : الْمُفْلِسُ فِينَا مَنْ لَا دِرْهَمَ لَهُ وَلَا مَتَاعَ. فَقَالَ : " إِنَّ الْمُفْلِسَ مِنْ أُمَّتِي يَأْتِي يَوْمَ الْقِيَامَةِ بِصَلَاةٍ وَصِيَامٍ وَزَكَاةٍ، وَيَأْتِي قَدْ شَتَمَ هَذَا، وَقَذَفَ هَذَا، وَأَكَلَ مَالَ هَذَا، وَسَفَكَ دَمَ هَذَا، وَضَرَبَ هَذَا ؛ فَيُعْطَى هَذَا مِنْ حَسَنَاتِهِ، وَهَذَا مِنْ حَسَنَاتِهِ، فَإِنْ فَنِيَتْ حَسَنَاتُهُ قَبْلَ أَنْ يُقْضَى مَا عَلَيْهِ ؛ أُخِذَ مِنْ خَطَايَاهُمْ فَطُرِحَتْ عَلَيْهِ، ثُمَّ طُرِحَ فِي النَّارِ﴾

“ድሃ ማን እንደሆነ ታውቃላችሁን?! ሶሐቦችም እንዲህ ሲሉ መለሱ፦ ‘እኛ ውስጥ ድሃ ማለት ድርሃም (ገንዘብ) እና መጠቃቀሚያ የሌለው ነው።’ የዚህን ጊዜ ነቢዩ እንዲህ አሉ፦ ከኔ ህዝቦች ድሃ ማለት፦ በሶላት፣ በጾምና በምጽዋት (በዘካ) በተሰሩ መልካም ስራዎች የቂያም ቀን የሚመጣ ነው። በርግጥ አንዱን ሰድቧል፣ አንዱን አነውሯል፣ የአንዱን ገንዘብ በልቷል፣ የአንዱን ደም አፍሷል፣ አንዱን መቷል (ደብድቧል)። ለእዚያም ከመልካም ሥራው ይሰጠዋል፣ ለእዚያም ከመልካም ሥራው ይሰጠዋል። ያለበትን እዳ ሳይከፍል በፊት መልካም ሥራው ካለቀ፤ ከነርሱ ወንጀል ይያዝና እርሱ ጀርባ ላይ ይወረወራል። ከዚያም ወደ እሳት ይወረወራል።”

📚 ሙስሊም ዘግበውታል፡ 2581

Yasin nuru's hadis

05 Nov, 04:36


ጨለማው ብቻ ሳይሆን ሲትሩም ሸፍኖን አድረናል።
የቱን፣ ስንቱን ፀጋዉን እናመስግን ?


አልሃምዱሊላህ❤️‍🩹🤍

Yasin nuru's hadis

04 Nov, 08:16


ያህያ ሲንዋር ማነው?

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

03 Nov, 16:42


ነገ ሰኞ ነዉ የቻለ ይፁም ያልቻለ ያስታውስ 🤍

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

03 Nov, 06:35


የአለማት እዝነት🥰

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

02 Nov, 17:17


ጀነትን ተመኘሁላችሁ 🖤


ለኔም እስኪ ዱዓ አድርጉልኝ🥰

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

02 Nov, 04:37


.
አላህ ሆይ🤲

እነዛ ደስታን የናፈቁት ልቦች❤️‍🩹
ማዘናቸው ትዝ እስከማይላቸው ድረስ
በደስታ ሙላቸው....

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

01 Nov, 13:19


https://t.me/islamicprofilepicture1

Yasin nuru's hadis

01 Nov, 11:43


እኔ ቅርብ ነኝ🥰🥰

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

31 Oct, 12:43


አላህን የያዘ ምን ያጣል🥰

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

31 Oct, 07:09


ነገ መልካም ይሆናል ....ነገሮች ይስተካከላሉ ደስተኛም እንሆናለን ።

ኢንሻአላህ!

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

30 Oct, 18:32


ነገ ሐሙስ ነዉ የቻለ ይፁም ያልቻለ ያስታውስ🤞

መልካም ለይል አህባቢ 🙌

Yasin nuru's hadis

30 Oct, 06:15


አንድ ፓስተር በነብዩ ﷺ እና ሙስሊሞችን በምሳሌ በመጥቀስ እንዴት አማኞችን እንደሚያተምር ይመልከቱ

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

30 Oct, 02:59


አላህ ለሊቱን ወደ ቀን መቀየር ከቻለ
ሸክማችንን ወደ ፅጋ ሊለውጠው ምን ይሳነዋል?


❤️‍🩹....


@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

29 Oct, 09:04


.
የተበዳይን ዱዐ ፍሩ! በሱ እና በአሏህ መካከል ግርዶሽ የለምና! ረሱል ﷺ 🤍

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

28 Oct, 13:07


- ላለፈው አታስብ

ያለፉት ቀናት ላይመለሱ ሄደዋል..💝
ላይመለሱ ለሚመጡት ቀናት አስብ🤍


@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

27 Oct, 05:34


የቴሌግራም መስራች Pavel Durov እንዲህ ሲል ተናገረ

”የሚቆጨኝ ነገር ግን ማቆም ያልቻልኩት ነገር ቢኖር McDonald’s ገብቼ በርገር አዝዤ የምትጠቀው 5 ደቂቃ ነው። 5 ደቂቃ ሙሉ ያለምንም ስራ መቀመጥ ማለት ለ 5 ደቂቃ መሞት እንደማለት ነው።

ልጆች Game አጨዋወት ሳይሆን Game አሰራር ተማሩ!

ወጣቶች የፊልም Recommendation ሳይሆን የስራ ፈጠራ Recommendation ተመልከቱ ወደፊት ታመሰግኑኛላቹ”።

@islam_in_school

Yasin nuru's hadis

27 Oct, 01:32


አሰላም አለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካትሁ እንዴት ናችሁ? ይህ መፅሀፍ በ @IbnuHashm channel የተዘጋጀ ሲሆን የመፀሀፉ ርዕስ ''በኢስላም ዉስጥ የሴትን ልጅ መብትና ግዴታ እና ማረጋገጫ'' የሚል ነዉ።

ይህ መፅሀፍ ዋናዉ ዓላማዉ ምዕራብያዉያን እንደሚሉት ሴት ልጅ በእስልምና ተጨቁናለች ለሚለዉ አጠር ያለች እና አጥጋቢ መልስ የያዘች መፀሀፍ ነች። እንድታነቡት ጋበዝኳችሁ።

ሁላችሁም ሼር አድርጉት በተለይ ለUniversity ሙስሊም ሴት ተማሪዎች በጣም ያስፈልጋቸዋል።

የ University የተማሪዎች አሚሮች ይህንን መፅሀፍ በጀመአዉ ቻናል ወይም በግል አሰራጩት።

ጀዛኩመላሁ ኸይረን

Yasin nuru's hadis

27 Oct, 01:29


@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

26 Oct, 16:35


ሰላም ለነዛ 🖤



ቀጥሉት እስኪ 😌

Yasin nuru's hadis

26 Oct, 05:09


የቀኑ ሶስቱ ሃዲሶች

ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፡‐
1️⃣📚
"በጁምዓ ቀንም ሆነ በሌሊት የሚሞት ሙስሊም የለም አላህ ከቀብር ፈተና ይጠብቀዋል"

2️⃣📚
“አንድ ሰው ለቤተሰቡ አስቦ የሚያወጣው ወጪ ለሱ ሰደቃ ይሆንለታል።”


3️⃣📚
“አንዳችሁም አላመናችሁም ለራሱ የሚወደውን ነገር ለወንድሙ እስካልወደደ ድረስ።”

📚1️⃣【 ቲርሚዚ 1074】
📚2️⃣【ሳሂህ ሙስሊም 1002】
📚3️⃣【ሳሂህ ሙስሊም 45】


@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

25 Oct, 06:07


አንተ አሏህን ማመስገን እስካላቆምክ ድረስ ተመስጋኙም(አሏህ) አንተን ማስገረሙን አያቆምም💫

Yasin nuru's hadis

24 Oct, 14:39


ወንድ ልጅ ሴት ልጅን
ማፍቀሩ ተፈጥሮ ነው

በሃላል ሰትሯት ጠበቅ ማድረጉ ግን
ወንድነት ነው
              

Yasin nuru's hadis

24 Oct, 09:43


ዝነኛና ታዋቂዋ የ MMA (mixed martial arts) ተደባዳቢ አምበር ሊብሮክ (AMBER LEIBROCK) እስልምናን ተቀብላለች። ማሻአላህ!❤️🌷🥰

በሒጃብ ውበቷ እጥፍ ሆኗል!😊

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

23 Oct, 00:09


አላህ ከፍጥረታት ሁሉ መረጠንና የሰው ልጅ አደረገን...

ከሰውዎችም መካከል መረጠንና እስልምናን ለገሰን

ከሙስሊማች መካከል መረጠና የተወዳጁ ነብዬﷺ ኡመት አደረገን...

ወላሂ ወቢላሂ  ቆጥረን ማንዘልቀው ትልቅ እድል ውስጥ ነን።

አላህን በብዛት እናመስገን !🤲

{وَإِن تَعُدُّوا نِعْمَةَ اللَّهِ لَا تُحْصُوهَا ۗ إِنَّ اللَّهَ لَغَفُورٌ رَّحِيمٌ}
"የአላህንም ጸጋ ብትቆጥሩ አትዘልቋትም፡፡ አላህ በእርግጥ መሓሪ አዛኝ ነውና፡፡"
                [ሱረቱ ነህል:18]

ብዙ ለሰጠን አላህ ብዙ ምስጋና የተገባው ነው🌱

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

22 Oct, 13:43


ተው ግን እየገባቹ ኮድ 56ን 👍 አርጉልኝ አላሳዝናቹም

Yasin nuru's hadis

22 Oct, 04:55


🦋❝ጀነት ስንገባ አንድም ሰው ከመካከላችን እንዲጎድል አንፈልግም..በሉ ተነሱ ልጆቼ❞ እያለች ልጆቿን ለሱብሒ ሶላት የምትቀሰቅስ አንዲት እናት ነበረች።

አሏህ ለልጆቻቹህ ምርጥ ዓርዐያ የምትሆኑ ያድርጋቹህ  ያድርገን🤲🦋

Yasin nuru's hadis

21 Oct, 06:23


➥ "በጥንቃቄና በእንክብካቤ ሊጠብቁት የሚገባ ሐብት ምንድን ነዉ?" የሚለዉን ጥያቄ ሶሐቦች (ረ.ዐ) ረሱልን (ሶ.ዐ.ወ) ጠይቀዉ ሲመልሱላቸዉ:-

"አላህን በማስታወስ(ዚክር በማድረግ) የተጠመደ ምላስ፤ አላህን የሚፈራ ልብ ፤ባሏን በዲን ሥራ ላይ ተግታ የምትረዳ ሚስት ናቸዉ" ሲሉ ገልፀዋል።

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

20 Oct, 05:35


ያ አላህ

ሰላም ፣እርዝቅ ለእነዚያ ይህንን ቻናል ሌት ከቀን ለሚከታተሉና <<ሼር>> ለሚያደርጉ🥰

Yasin nuru's hadis

19 Oct, 04:27


ሀቢቢ!
የጌታህን ፍቅር፣ የረሱሉን ውዴታ፣ የመልካም ሰዎችን ጉርብትና ከሻህ… በሰላትህ ጠንክር!

ነገ ብርሀንን፣ ኑርን፣ ምስክርን ከፈለክ ዛሬ ሰላትህን አስውብ!

ቅር ቢልህም አንድ ዕውነታ ልንገርህ!
ካልሰገድክ… ነገ ብርሀንም፣ ኑርም፣ ምስክርም አይኖርህም። ከዚያም ብሶ በዓለም ላይ እንደነሱ ክፉ ታይቶ ከማይታወቅ ከነ ፊርዖን፣ ከነ ሀማን፣ ከነ ኡብይ ኢብኑ ከለፍ ጋር ነው ምትጎዳኘው።

ወይኔ! እንዲህ ባረኩ ኖሮ ብለህ የምትፀፀትበትና ፀፀትህም የማይጠቅምህ ቀን ሳይመጣ በጊዜ ተዘጋጅ! በጊዜ ሰንቅ!

[[ሀቢቢ! ነገ ከዱንያ የበለጠ ዕጅግ ያማረ ቦታ ይጠብቀናልና… #ሰላትን_አደራ!]]

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

18 Oct, 03:54


ከሱረቱል ከህፍ የመጀመሪያ አስር አያዎችን የሀፈዘ ከደጃል ፈተና መጠበቂያ ይሆነዋል❗️

روى الحاكم في المستدرك مرفوعا إن من قرأ سورة الكهف يوم الجمعة أضاء له من النور ما بين الجمعتين. وصححه الألباني

📌ረሱል ﷺ በጁሙዓ ቀን ሱረቱል ከህፍን ያነበበ በሁለት ጁምዓዎች መካከል ብርሃን ያበራለታል ብለዋል።

📌ነብዩ ﷺ በእኔ ላይ ሰለዋት አብዙ የናንተ ሰለዋት እኔ ዘንድ ይቀርባልና ብለዋል።

ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦

﴿إنّ في الجُمُعَةِ لَساعَةً، لا يُوافِقُها مُسْلِمٌ، يَسْأَلُ اللهَ خَيْرًا، إلّا أعْطاهُ إيّاهُ.﴾

“በጁምዓ ቀን አንዲት ሰዓት አለች። በዛች ሰዓት አንድ ሙስሊም አላህን መልካምን ነገር እየጠየቀ አይገጥምም፤ ለሱ የጠየቀው የሚሰጠው ቢሆን እንጂ።”

ሙስሊም ዘግቦታል

📌በጁሙዓ ቀን ኹጥባ በሚደረግበት ጊዜ ሰዎች ላይ መረማመድ እና ማውራት የተከለከለ መሆኑን አንዘንጋ።


እንዲሁም ከሚስተዋሉ ስህቶች አንዱ ጁሙዓ ሙባረክ መባባል ነው ይሄ መሰረት የለውም።

#ጁመዓ_ነው_ሰለዋት_እናብዛ

اللهم صلي على محمد وعلى آل محمد ،
كما صليت على إبراهيم وعلى آل إبراهيم ،
وبارك على محمد وعلى آل محمد ،
كما باركت على إبراهيم وعلى آل إبراهيم، في العالمين إنك حميد مجيد


@yasin_nuru_hadis
@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

18 Oct, 02:28


አላህና መላእክቱ በነቢዩ ላይ የአክብሮት እዝነትን ያወርዳሉ፡፡ እናንተ ያመናችሁ ሆይ! በእርሱ ላይ የአክብሮት እዝነትን አውርዱ፡፡ የማክበርንም ሰላምታ ሰላም በሉ፡፡



@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

17 Oct, 12:24


ሸይጧን ሸቀጡን በኸይር ገበያ ነው የሚሸጠው።

🔻ፆም ሁሉ ዒባዳ አይደለም። ፆም መዕሲያ ወንጀል የሚሆንበት ጊዜያቶች አሉ።

🔻ሶላት ሁሉ አምልኮ ታዛዥነት አይደለም። መስገድ ወንጀል ሀራም የሆኑባቸው ጊዜያቶች አሉ።

📌📌ደግሞ ስራው ልክ ሆኖ አርካኑ ሸርጦቹ በሙሉ አሟልቶ ተቀባይነት ያግኝ አያግኝ አይታወቅም።

📌📌📌ስራው ተቀባይነት ካገኘ እራሱ ሒስድ ካለ እሳት እንጨትን አመድ እንደሚያደርገው ስራው በሙሉ አመድ ይሆናል።

📌📌📌📌በብዙ ኢጅቲሃድ እራስህን ከሒስድ አጥርተ ተቀባይነት ያለው ዒባዳ መልካም ስራ ብትሰራ ከዛም የሰዎችን ክብር ብትነካ ነገ በአኼራ ለነሱ ይሰጣቸውዋል። ይህ እራሱ አላህ የተቀበለህ ኸይር ስራ ካለህ ነው።

🟢ምንም ባትሰራ የሰዎች ሀቅ ከሌለብህ ትልቅ ሸረፍ ነው። ሙፍሊስ ከመሆን አላህ ይጠብቀን።

🔰ዋናው ነገር አደብ ይኑርህ። ታላላቆችህ አንተ ስትወዳቸው ብቻ ሳይሆን ባትወዳቸውም አክብራቸው። አንተን ሲገጥሙ ብቻ ሳይሆን ሲኻልፉህም አክብራቸው። ለማክበር መውደድ መስፈርት ሆኖ አያውቅም። ታላቅ ማለት፦ በእድሜ፣ በዒልም ና በተለያዩ መልካም ነገሮች የሚበልጡህ ታላላቆችህ ናቸው። ብታከብራቸው ትከብራለህ።

🖍ትልቁ ነገር አደብ ነው። አደብ የሌለው እምነትም የለው።
ኡስታዝ ካሚል ሰልማን

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

16 Oct, 05:47


ጊዜ ምን አስተማረሽ?

* እኔ መቼም እንደዛ አልሆንም
* እኔ ላይ መቼም አይደርስም
* እኛ ቤት መቼም አይሆንም

  አለማለትን💔❤️‍🩹

©yuti

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

15 Oct, 17:14


ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦

 ﴿أدِّ الأمانةَ إلى منِ ائتمنَكَ، ولا تخُنْ من خانَكَ﴾

“አምኖ ለሰጠህ አማናውን አድርስ። የካደህን አትካድ።”

📚 ሲልሲለቱ አሶሂሃ፡ 423

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

15 Oct, 06:44


🌷"የቆምኩ ያህል ይሰማኛል ከሶሓቦቹ ጎራ፣
የስንብት ቃሉ ሲናኝ አማናዎ ሲዘራ፣
ምን ባጎድል አደራዎን ባይሳካልኝም፣ አልሰማሁም የምልበት አንደበት ግን የለኝም።"🌷

🌺"ከተሰጡት ምን ቀርቶብኝ ካንቱ ምን አጥቼ፣
በጨለማ የምባክን ብርሃኖን ትቼ፣
የስንብት ሕያው ቃሎ ደርሷል ከኔም ደጅ፣
ምስክር ነኝ ባአደባባይ ነብይ የኔ ወዳጅ።"🌺


እኛም ድርሶናል መልእክቶ ያ ነቢየላህ!🌺

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

14 Oct, 11:41


የሰው መልኩ ልቡ ነው

አላህ ልብ ይስጠን 🤲

Yasin nuru's hadis

14 Oct, 08:04


قال رسول الله ﷺ :

اقرؤا سورة البقرة، فإن أخذها بركة، وتركها حسرة، ولا يستطيعها البطلة .
صحيح مسلم - ٨٠٤ -

البطلة : هم السحرة .

የአላህ መልእክተኛ ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል፦

ሱራ አልበቀራን አንብቡ፣ እሷን መውሰድ በረካ ነው፣ እሷን መተው ፀፀት ነው፣ ሳሂሮችም(ጠንቋዮችም)  አይችሏትም።

ሳሂህ ሙስሊም - 804 -

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

13 Oct, 07:41


ሰው ለሚስቱ በ50 ሚሊዮን ዶላር ደሴት እየገዛ አንተ 50 ሺህ የወረቀት ብር መህር መክፈል ከበደኝ ትላለህ¡


ለአንዷ ደሴት መግዣ ብሎ ብር ከሚያባክን 3 አይጨምርበትም ነበር ወይ? የሚል አይጠፋም¡

Murad

@yasin_nuru_hadis

Yasin nuru's hadis

12 Oct, 06:03


ከዚህ በፊት ስለ ገንዘብ ፈተና እና ስለ ልጅ ፈተና አይተናል ። ሌላውና ትልቁ ፈተና ደግሞ "ሸህዋ" ነው ..

ዛሬ ዘመናችን እንደውም የሸህዋ አብዮት ዘመን ተብሎ ቢጠራ ማጋነን አይሆንም ። ለምን ብትሉ ሸህዋን ተንኳሽ ፣ ቀስቃሽ የሆኑ ነገራት በየቦታው ያጋጥማችኋል .. ሰው መቼስ አይኑን ጨፍኖ አይሄድም ።

ሁለት አይነት ሰዎች ይመጣሉ ፥ እኔ አላየኋቸውም .. አንደኛው እንደ ከብት ጂራት የሚመስል አለንጋ ይዘው ሰውን በአደባባይ የሚገርፉ ፣ የሚቀጠቅጡ ሰዎች ወደፊት ይመጣሉ አሉ .. ሁለተኛው ደግሞ የለበሱ ግን የተራቆቱ ሴቶች ፥ የጠመሙ ሌላውን የሚያጠሙ ፣ ራሳቸው እንደተዘነበሉ የግመል ሻኛዎች ያጋደለ የሆኑ ሴቶች ይመጣሉ አሉ ።

“የለበሱ እርቃኖች” የሚለው አገላለፅ ራሱ ይአጅባል .. በሰውነታቸው ላይ የሚያንጠላጥሉት ልብስ ዋጋው ሲታይ ውድ ዋጋ ነው የወጣው ፤ ስለዚህ እንደነሱ ድንቅ ልብስ ነው የለበሱት .. ግን እርቃን ናቸው (መሸፈን ያለበት የሰውነት አካል ስላልተሸፈነ) ደረት ተገልጦ .. እስከ ባት ድረስ ተሰብስቦ .. ከዚያም የተለያየ ነገር ተቀብቶ .. በሚገርም ሁኔታ ይሄን ሁሉ አድርገው ምናልባት ወንዱ ላያየን ይችላል ብለው ደግሞ ጫማቸው ላይ ሚስማር ሰክተው ቋ ቋ እያደረጉ ይሄዳሉ ። ተጋልጬ ወጣሁኝ አላየኸኝም ቆርቁሬ አሰማሃለሁ እያሉ ነው :) አዳምጥ ¡

ይሄንን ያየ ትዳር አልባ ወጣት ይፈተናል .. አንዳንዱ ግብዝ ራሱንም አታሎ ሌላውንም ለማታለል ይፈልግና ምን ይልሃል? እኔኮ ራሴን እቆጣጠራለሁ ፤ ነፍሴን አውቃታለሁ ይላል .. ነፍስን መቆጣጠር መከላከያውን አበጅቶ ነው ። ረሱል እንዳሉት ሴት አይቶ በጣም ከማረከችው ቶሎ ቤት ይመለስ .. እቤት ባለትዳር ስለሆነ ከባለቤቱ ጋር ተገቢውን ነገር በማድረግ ያንን መስበር ይቻላል ። ውጭ ያለውና ውስጥ ያለው አንድ አይነት ነገር ነው ። መመለሻ የሌለውስ .. ወደ ቤት ይመለስ አሉ .. ቤት ሲመለስ ምንም የለም :(

ይሄን ፈተና ማን ይቋቋመዋል እስኪ?!
"ዙይነ ሊናስ ሁቡሸሃዋት" ብሏል አሏህ .. ይሄኮ አብሮን የተፈጠረ ነገር ነው ። ብዙወቹ ሳያገቡ የሚኖሩ ሰዎች ራሳቸውንም አታለው ሰውንም ለማታለል እኛ እራሳችንን እንቆጣጠራለን ይላሉ ። እዚህ ቦታ ላይ ራስን መቆጣጠር ከባድ ነው ። አይን ያያል የሱን ስራ ጨረሰ እሱ ፣ አይንህ እንዳይቃብዝ ረሱል ምን አሉ «መን ኢስተጧዓ ሚንኩም አልባዓተ ፈልየተዘወጅ» ከናንተ የጋብቻውን ጣጣ መክፈል የቻለ ሰው ቶሎ ያግባ ። አይኑን ይሰብርለታል!
አይን መጨፈን የሚቻለው አይንን በመክደን አይደለም (ያ ከሆነ አትራመድማ) ይልቅ መከላከያውን በማበጀት ነው ።

አጠቃላይ የሰው ልጆችን ከፊሉን በከፊሉ ፈትኗል «ወጀአልና በዕዶኩም ሊበዕዲን ፊትና አተስቢሩን» ይላል ። ሴቷ በወንዱ፤ ወንዱ በሴቷ .. ሀብታሙ በድኻው ፣ ድኻው በሃብታሙ .. ጤነኛው በበሽተኛው ፣ በሽተኛው በጤነኛው እየተፈተነ ነው ። የሸህዋው የሚለው ጊዜ አይሰጥም ፣ እንደ እሳተ ጎመራ ድንገት ነው ። ራሴን እቆጣጠራለሁ ይል የነበረው ሰውዬ ይወድቃል ። ነብዩም “ዲናቸው ጎደሎ ፣ አቅላቸው ጎደሎ ግን የጠንካራን ልቦና ባለቤት የሚያሸንፉ እንደናንተ አላየሁም” አሉ ሴቶችን .. በጦር ሜዳ ማይበገረው ጀግና በሸህዋ ላይ ጠብ ብሎ ታየዋለህ .. ያዳግታል ፣ ይፈታተናል

@yasin_nuru_hadis
@yasin_nuru_hadis