እንኳን ለአዲሱ ዓመት በሰላም አደረሰን።
በአዲስ ዓመት ውስጥ የሚመጡ ቀናት ከወትሮው የተለዩ ሊሆኑ አይችሉም። አየሩም ንፋሱም ከደመናው ጋር፤ ፀሓዩም ከብርሃኑ ጋር ሁሉ እስኪያበቃ ድረስ ይቀጥላሉ። በተለወጠ አስተሳሰብ፣ አመለካከትና በአዲስ ውሳኔ፣ ልብና አዕምሮ ይዘን ብሎም ትላንት የሰበሰብነውን ዛሬ አራግፈን ወደ አዲሱ ካልገባን በስተቀር ለየት ያለ ነገር መጠበቅ የለብንም ። ቀናት ረጃጅም ቢሆኑም ዓመት አጭር ናቸው እንደሚባሉ ዛሬን ለለውጥ ካልተጠቀምንበት አዲስ ዓመት ሳይሆን አሮጌውንም የመድገም አደጋ ያጋጥመናል። ለውጥ የሚጀምረው በመለኮት ጣልቃ ገብነት በክርስቶስ ደም በመስቀሉ ስር በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ቢሆንም የሚቀጥለው ግን ዕለት ዕለት መስቀልን በመሸከም ለዓለማዊ ምኞትና ኃጥአት ራሳችንን እየሰቀልን በመኖር የታደሰ የሕይዎት ዘይቤ በመኖር ውስጥ መሆን አለበት።
ለራስ ብቻ መኖር ሳይሆን ሌሎችንም ወደዚህ የወንጌል እውነት እንዲመጡ ብርሃንና ጨው በመሆን ሕይዎት ውስጥ የምንኖርበት የሰላም፣ የደስታና የጤንነት ዓመት ይሁንልን።
መልካም የአዲስ ሕይወት ዓመት ይሁንልን!!
🌻🌻🌻እንኳን ለ2017 ዓ.ም በሰላም አደረሳችሁ🌻🌻🌻
በዱራሜ ካምፓስ ወንጌላውያን ተማሪዎች ህብረት
👨💻 MEDIA CREW👩💻
✉️ እርስዎ አስተያየት ካልዎት እባክዎ በዚ @wcudc_comment ሊንክ ይላኩልን ይደርሰናል!
@wcudc
@wcudc
WcUDC-ECSF