እለተ ቅዳሜ ሰኔ 01, 2016 ዓ.ም
ከቀኑ 7:00 ሰዓት
በቅዱስጊዮርጊስ ጉዳይ ላይ ተቀራርበን የተወያየን ደጋፊዎች በአሁኑ ጊዜ በስፖርት ማህበራችን አካባቢ የተከሰተውን ችግር ለመቅረፍ በማሰብ የተለያዩ እንቅስቃሴዎች መጀመራችንን ከዚህ ቀደም በተለያዩ ፅሁፎቻችን መግለፃችን ይታወሳል ።
ከነዚህም እንቅስቃሴዎች አንዱ የሆነው ለመላው የቅዱስጊዮርጊስ ደጋፊዎች መጠይቅ አዘጋጅቶ ምላሽ በመሰብሰብ ለምናዘጋጀው ሰነድ ጥሩ ግብዓት ማግኘትና በተቻለ መጠን የሁላችንም ሀሳብ ምን እንደሆነ ተረድቶ ተገቢ የሆነ የመፍትሄ ሀሳብ ማቅረብ ነው ።
ስለሆነም እስከፊታችን ቅዳሜ ሰኔ 08, 2016 ከምሽቱ 4 ሰዓት ድረስ ከዚህ በታች በተያያዘው ሊንክ ወይም በባር ኮዱ በመግባት ለቀረቡ ጥያቄዎች ተገቢ እና የተሟላ ምላሽ በመስጠት ለጀመርነው እቅድ መሳካት ትብብር እንዲያደርጉ እንዲሁም ክለባችን ካጋጠመው ችግር እንዲወጣ የመፍትሄው አንድ አካል በመሆን የበኩልዎን አስተዋፅኦ እንዲያበረክቱ እንጠይቅዎታለን ።
✌ እናመሰግናለን !!!
https://forms.gle/kUawdiSWkpHMLWLE7