SABBATH SCHOOL(ሰንበት ትምህርት )

@sabbathschool


@TekalignSorato
+251913070430

SABBATH SCHOOL(ሰንበት ትምህርት )

23 Oct, 03:01


ረቡዕ
ጥቅምት 13
Oct 23

ፊልጶስ እና ናትናኤል

ዮሐንስ 1:43-46ን ያንብቡ። የፊልጶስ መልእክት በኢየሱስ ላይ ስላለው እምነት ምን አሳይቷል?


Save Notes

ልክ እንደ እንድርያስና እንደ ጴጥሮስ ሁሉ፣ ፊሊጶስም የቤተሳይዳ ሰው ነበር። ወዳጁ ናትናኤልን አግኝቶ ስለ ኢየሱስ ነገረው። መጥምቁ ዮሐንስ ኢየሱስን “የእግዚአብሔር በግ” ብሎ ጠርቶታል። እንድርያስ ለጴጥሮስ “መሲሑን” እንዳገኘ ነግሮት ነበር። ፊልጶስ ግን ሙሴና ነቢያት የጻፉለትን ኢየሱስን “የናዝሬቱ ኢየሱስ” ሲል ጨምሮ ጠርቷል። ናዝሬት የሚለውን ሥም መጥቀሱ ከጓደኛው የሰላ ምላሽን አስከትሏል። ናትናኤል ለትንሿ ናዝሬት ከተማ ጭፍን ጥላቻ የነበረው ይመስላል። በእርግጥ ንጉሥ ከእንዲህ ዓይነቱ መንገድ ዳር ላይ ከለ ሥፍራ እንደማይመጣ የታወቀ ነው። ጭፍን ጥላቻ በእውነት ዋጋ ያለውን ነገር እንዳያዩ ሰዎችን በቀላሉ አይናቸውን ያሳውራል። ፊልጶስ ቀደም ሲል ከናትናኤል ጋር ካደረገው ውይይት ምናልባትም ጭፍን ጥላቻን ለመቋቋም ትክክለኛው መንገድ ከፍ ያለ ፍልስፍናዊ ወይም ሥነ-መለኮታዊ ክርክር ሳይሆን ግለሰቡ እውነቱን ለራሱ እንዲያውቅ መጋበዝ እንደሆነ የተገነዘበ ይመስላል። ዝም ብሎ “መጥተህ እይ” አለው። ያደረገውም ይህንኑ ነው። ሄዶ አየ። ዮሐንስ 1:47-51ን ያንብቡ። ኢየሱስ ናትናኤልን ማንነቱን ያሳመነው እንዴት ነበር? የናትናኤልስ ምላሽ ምን ነበር?


Save Notes

በቁጥር 46 እና 47 መካከል የሌለው ነገር ናትናኤል ለፊልጶስ ግብዣ የሰጠው ምላሽ ወሳኝ ዝርዝር ጉዳይ ነው። ምንም ቢሆን ግን ተነሥቶ ለማየት ሄደ። ከፊልጶስ ጋር የነበረው ወዳጅነት ከጭፍን ጥላቻ ይልቅ የበረታ ነበር፤ እናም ሕይወቱ ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ተለወጠ። ኢየሱስ ስለ ናትናኤል ጥሩ ቃላት ተናግሯል፣ “ተንኰል የሌለበት በእውነት የእስራኤል ሰው” ብሎ ጠራው (ዮሐ. 1:47); ይህ ናትናኤል (በዮሐ. 1:46) ስለ ኢየሱስ ከተናገረው በጣም የተለየ ነው። ናትናኤል ኢየሱስን ከዚህ በፊት አግኝቶት ስለማያውቅ በመገረም መለሰ። ከዚያም ኢየሱስ ከበለስ ዛፍ ሥር እንዳየው የተናገረ ሲሆን፣ ይህ ጥቂት ንግግር ናትናኤልን አሳምኖታል። ናትናኤል እውነትን በመሻት በዚያ ዛፍ ሥር ሲጸልይ ኢየሱስ በመለኮታዊ መገለጥ ተመልክቶታል። ናትናኤልም መልሶ፦ “መምህር ሆይ፥ አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ነህ፤ አንተ የእስራኤል ንጉሥ ነህ” ሲል ከፍ ያለ ኑዛዜን ተናገረ። ትንሽ የሚመስለው መገለጥ ወደ ትልቁ የእምነት ኑዛዜ እንዴት እንደሚመራ አስተውሉ።

@SabbathSchool @TekalignSorato

SABBATH SCHOOL(ሰንበት ትምህርት )

22 Oct, 18:40


Live stream finished (1 hour)

SABBATH SCHOOL(ሰንበት ትምህርት )

22 Oct, 17:36


https://www.youtube.com/live/yQmy_xJjh4I?si=0XhrGH-YNy6MhQw8

SABBATH SCHOOL(ሰንበት ትምህርት )

22 Oct, 17:28


Live stream started

SABBATH SCHOOL(ሰንበት ትምህርት )

22 Oct, 03:00


ማክሰኞ
ጥቅምት 12
Oct 22

ሁለቱ የዮሐንስ ደቀ መዛሙርት

ኢየሱስ በዚያ ሲያልፍ ሁለት የመጥምቁ ዮሐንስ ደቀ መዛሙርት አብረውት ቆመው ነበር። ዮሐንስ (በዮሐ. 1፡36) “እነሆ የእግዚአብሔር በግ!” ሲል አውጆ ነበር። ሁለቱ ደቀ መዛሙርት የዮሐንስን መልእክት ሰምተው ነበር; እርሱም ስለሚመጣው መሲሕ የብሉይ ኪዳን ትንቢቶችን ይፈጽማል። ደቀ መዛሙርቱ ኢየሱስ ከመጥምቁ ዮሐንስ እንደሚበልጥ እና እርሱ የዮሐንስ መልእክት ፍጻሜ መሆኑን አውቀው ዮሐንስን ትተው ኢየሱስን ተከተሉት። ዮሐንስ 1:35-39ን ያንብቡ። እነዚህ ሁለት ደቀ መዛሙርት ዮሐንስ ስለ ኢየሱስ የሰጠውን ምስክርነት ከሰሙ በኋላ ምን አደረጉ?


Save Notes

ከኢየሱስ ጋር ለመሆን በመሻት ቀኑን ሙሉ ከእርሱ ጋር አብረው አሳልፈዋል። ያን ጊዜ የተማሩትን እና ያጋጠሟቸውን አስደናቂ ነገሮች ማን ያውቃል? በጣም ድንቅ ነገሮች መሆን አለባቸው፣ ምክንያቱም ብዙም ሳይቆዩ ፍላጎታቸው ልምዳቸውን ለሌሎች ማካፈል ነበር። ከሁለቱ ደቀ መዛሙርት አንዱ የሆነው እንድርያስ እርሱ አስቀድሞ የራሱን ወንድም ስምዖንን አገኘውና፦ “መሢሕን አግኝተናል አለው፤ ትርጓሜውም ክርስቶስ ማለት ነው” (ዮሐ. 1፡41)። እንድርያስ ወንድሙን ወደ ኢየሱስ ባመጣው ጊዜ፣ ወዲያው ኢየሱስ እንደሚያውቀው እንዲህ ሲል ነገረው፦ “አንተ የዮና ልጅ ስምዖን ነህ። አንተ ኬፋ ትባላለህ” (ዮሐ. 1:42)። ኢየሱስ ጴጥሮስን አውቆ ተረድቶታል። ኢየሱስ ሰውን እንደሚያውቅ ማሳየት የዮሐንስ ወንጌል የተደጋገመ ጭብጥ ነው (ለምሳሌ ዮሐንስን 2:24፣ 25ን እንመልከት)። “ዮሐንስና እንድርያስ እንደ ካህናቱና መኳንንቱ ያለማመን መንፈስ ቢኖርባቸው ኖሮ በየሱስ እግር አጠገብ ተቀምጠው የመማር ዕድል አይኖራቸውም ነበር። በቃሉ ላይ ለመተቸት ስህተት ፍለጋ ወደ እርሱ ይመጡ ነበር። … እነዚህ የመጀመሪያ ደቀ መዛሙርት ግን ይህን አላደረጉም። በዮሐንስ መጥምቁ ስብከት አማካይነት የመንፈስ ቅዱስን ጥሪ ተቀበሉ። አሁን የሰማያዊውን መምህር ድምፅ ለማወቅ ቻሉ። … በብሉይ ኪዳን ውስጥ በሚገኙት ትምህርቶች ላይ መለኮታዊ ብርሃን ፈነጠቀባቸው። ብዙ ርዕስ ያለው እውነት በአዲስ ብርሃን ጎልቶ ወጣ” (ኤለን ጂ ዋይት፣ የዘመናት ምኞት ገጽ 124)። የዮሐንስ ወንጌል በጠቅላላው አጽንዖት የሰጠው ይህ የምሥራች ለዓለም ይነገር ዘንድ የኢየሱስን ማንነት ወደ ብርሃን ማምጣትን ነው። ክርስቶስ እና በክርስቶስ ያለን እምነት ህይወታችንን በምን መንገድ ለውጦታል? አሁንም ምን ሌሎች ለውጦች እንዲከሰቱ እንፈልጋለን?

@SabbathSchool @TekalignSorato

SABBATH SCHOOL(ሰንበት ትምህርት )

21 Oct, 18:43


https://www.youtube.com/live/U0-t8in61zo?si=pTaovqHIAjAtbQIL

SABBATH SCHOOL(ሰንበት ትምህርት )

21 Oct, 03:02


ሰኞ
ጥቅምት 11
Oct 21

የእግዚአብሔር በግ

የእሥራኤል ሕዝብ ከሮም ነጻ የሚያወጣቸውን መሲሕ ይፈልጉ ነበር። የዮሐንስ ወንጌል ዓላማ ስለ መሲሑ ያላቸውን ግንዛቤ በመቀየር ስለሚመጣው ንጉሥ የሚነገሩትን ትንቢቶች በኢየሱስ አማካይነት እንዲገነዘቡ ማድረግ ነበር። መሲሑ ምድራዊ ገዥ አይሆንም። እርሱ የመጣው ስለ ራሱ የገባውን የብሉይ ኪዳን ተስፋዎች ሁሉ ሊፈጽም ነው፤ ይህም ስለ ዓለም ራሱን መስዋዕት ማድረግን እንዲሁም በእግዚአብሔር እና በሕዝቡ መካከል ያለውን ግንኙነት ማደስን ይጨምራል። ዮሐንስ 1:29-37ን ያንብቡ። መጥምቁ ዮሐንስ ስለ ኢየሱስ ምን ዐዋጅ ይናገራል? እርሱን ለመግለጽስ ምን ዓይነት ምስል ይጠቀማል? ደግሞስ ይህ የኢየሱስን ማንነትና የተልዕኮውን ምንነት ከማስረዳት አንጻር ያለው ጉልህ ፋይዳ ምንድን ነው?


Save Notes

መጥምቁ ኢየሱስን የእግዚአብሔር በግ መሆኑን አስመልክቶ የሰጠው መግለጫ የዮሐንስ ወንጌል ዓላማን ይደግፋል፣ እርሱም ስለመሲሑ ሥራ እና ማንነት አዲስ ግንዛቤ ለማምጣት ነው። ኢየሱስ በእርግጥም በዘፍጥረት 3፡15 ወደነበረው ወደ ቤዛነቱ ተስፋ መጀመሪያ በመመለስ፣ የመሥዋዕቱ ሥርዓት የተስፋ ቃል ፍጻሜ ይሆናል። “የሱስ በተጠመቀ ጊዜ ዮሐንስ የሱስ የእግዚአብሔር በግ እንደሆነ ሲናገር ስለ መሲሑ ሥራ አዲስ ብርሃን መከሰቱ ነበር። የነቢዩ አእምሮ “እንደ በግ ለመታረድ ቀረበ” ወደሚለው የኢሳይያስ ቃል ነበር (ኢሳ. 53:7)” (ኤለን ጂ ዋይት፣ የዘመናት ምኞት፣ ገጽ 121)። ማርቆስ 10:45፣ ሮሜ 5:6፣ እና 1ኛ ጴጥሮስ 2:24ን ያንብቡ። እነዚህ ጥቅሶች የኢየሱስን ሚና “እንደ እግዚአብሔር በግ” እንደ እንድንገነዘብ የሚረዱን እንዴት ነው?


Save Notes

መጥምቁ ዮሐንስ ምንም እንኳ ስለኢየሱስ አገልግሎት ይበልጥ ለማወቅ ቢፈልግም፣ ነገር ግን ኢየሱስ ቃል የተገባውና የትንቢት ፍጻሜ ሆኖ የመጣው መሲሕ እርሱ ስለመሆኑ እርግጠኛ ነበር። ኢየሱስ “የእግዚአብሔር በግ” ተብሎ የተጠራበትን ይህን የማዕረግ ስም በጥልቀት እንመልከት። ወደ አእምሯችን ያመጣቸው ምስሎች ምንድን ናቸው? ከብሉይ ኪዳን የመሥዋዕት ሥርዓት ጋር ያለው ትስስር የመዳናችንን ታላቅ ዋጋ እንድናደንቅ የሚረዳን እንዴት ነው?

@SabbathSchool @TekalignSorato

SABBATH SCHOOL(ሰንበት ትምህርት )

20 Oct, 05:48


እሑድ
ጥቅምት 10
Oct 20

የመጥምቁ ዮሐንስ ምስክርነት

ባለፈው ሳምንት ትምህርት እንደተገለጸው፣ የዮሐንስ ወንጌል የሚጀምረው ከፍጥረት በፊት ጀምሮ ህያው በነበረውና የእግዚአብሔር ቃል በሆነው በኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ነገር ግን በዚያው መቅድም ላይ፣ መጥምቁ ዮሐንስ የኢየሱስ ምስክር ሆኖ ቀርቧል። በኢየሱስ ዘመን የነበሩ አንዳንድ አይሁዶች፣ አንዱ ካህን ሌላኛው ደግሞ ንጉሣዊ የሆኑ ሁለት መሲሖችን ይጠባበቁ ነበር። የዮሐንስ ወንጌል መጥምቁ ዮሐንስ ከእነዚህ መሲሖች አንዱ መሆኑን እንዳልተናገረና ይልቁንም የአንዱ የእውነተኛው መሲሕ ምሥክር እንደነበር በግልጽ ያስተምራል። ዮሐንስ 1:19–23ን ያንብቡ። መጥምቁ ዮሐንስ አገልግሎቱንና ተልእኮውን እንዴት ነበር የገለጸው?


Save Notes

የኃይማኖት መሪዎቹ ዮሐንስን እንዲጠይቁት ካህናትንና ሌዋውያንን ላኩ። አይሁድ መሲሑን በከፍተኛ ጉጉት ይጠብቁ ስለነበር፣ መጥምቁ ዮሐንስ ከዚህ አንጻር ያለውን ዝምድና መግለጹ አስፈላጊ ነበር። እርሱ ብርሃን አልነበረም፣ ነገር ግን ስለ ብርሃን ሊመሰክር እና ለመሲሑ መምጣት መንገድን እንዲጠርግ፣ ከእግዚአብሔር ተልኮ ነበር (ዮሐ. 1፡6-8)። ለዚህም ነው የቻለውን ያህል ግልጽ በሆነ መንገድ እንዲህ ሲል የመለሰላቸው፦ “እኔ ክርስቶስ አይደለሁም” (ዮሐ. 1:20)። ደግሞም፣ ዮሐንስ በውኃ አጠመቀ፣ ክርስቶስ ግን በመንፈስ ያጠምቅ ነበር (ዮሐ. 1፡26፣ 33)። ዮሐንስ የኢየሱስን የጫማ ማሰሪያ ሊፈታ የተገባው አልነበረም (ዮሐ. 1፡27)። ክርስቶስ ከዮሐንስ ይልቅ ይመረጣል፣ ምክንያቱም እርሱ ከዮሐንስ በፊት ነበር (ዮሐ. 1፡ 30)። ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ ነው፣ እናም ዮሐንስ ወደ ክርስቶስ ብቻ አመለከተ (ዮሐ. 1፡34)። ኢሳይያስ 40:1-5 እና ዮሐንስ 1:23ን ያንብቡ። ዮሐንስ እነዚህን ጥቅሶች የተጠቀመባቸው እንዴት ነው?


Save Notes

የተበላሹና በድንጋይ የተሞሉ መንገዶች በነበሩበት ጊዜ የንጉሡን መንገድ ለማስተካከል አንዳንድ ጊዜ አገልጋዮች ከንጉሡ ፊት ይላኩ ነበር። ስለዚህ፣ በትንቢቱ ፍጻሜ፣ ዮሐንስ የመጣው የሰዎችን ልብ ለኢየሱስ ለማዘጋጀት ነበር። እንደ ሰባተኛ ቀን አድቬንቲስቶች፣ የመጥምቁን ዮሐንስ ዓይነት አገልግሎት የምንሠራው በምን መንገድ ነው? ከዚህ ጋር ተነጻጻሪ የሆኑ ነገሮች ምንድን ናቸው?

@SabbathSchool @TekalignSorato

SABBATH SCHOOL(ሰንበት ትምህርት )

19 Oct, 19:10


ቅምት 9 - 15
4ኛ ትምህርት
Oct 19 - 25




ክርስቶስ መሲሕ የመሆኑ ምሥክሮች


ሰንበት ከሰዓት በኋላ
ለዚህ ሳምንት የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የሚተከሉትን ጥቅሶች ያንብቡ፡ ዮሐ.1:19–23፤ ኢሳ. 40:1–5፤ ዮሐ.1:29–37፤ ሮሜ. 5:6፤ ዮሐ.1:35–39፤ ዮሐ. 1:43–51፤ ዮሐ. 3፡1-21።

የመታሰቢያ ጥቅስ፡ “ኢየሱስም መለሰ እንዲህም አለው፦ እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር የእግዚአብሔርን መንግሥት ሊያይ አይችልም” (ዮሐ. 3፡3)።
“ እውነት እውነት እላችኋለሁ፣ በእኔ የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው” የሚለውን ጨምሮ ኢየሱስ ስለራሱ የተናገራቸውን ነገሮች ለማጽናት ኃይል ያለውን የእግዚአብሔርን ቃል ከቅዱሳን መጻሕፍት ለሰዎች በማስረጃነት ያቀርብ እንደነበር ምንም ጥያቄ የለውም (ዮሐ. 6:47)። ግን ደግሞ ሌላም አለ፦ ውሃን ወደ ወይን መለወጥ፤ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን በጥቂት እንጀራ መመገብ፤ የመኮንኑን ልጅ መፈወስ፤ በቤተሳይዳ መጠመቂያ አጠገብ የነበረውን ሰው መፈወስ፤ ዕውር ሆኖ የተወለደውን ሰው ዓይኖች እንዲያዩ ማድረግ፣ አልዓዛርን ከሙታን ማስነሣት። ወንጌላዊው የተለያዩ ክንውኖችን እና ሰዎችን—ከአይሁዳውያን፣ ከአሕዛብ፣ ከባለ ጠጎች፣ ከድሆች፣ ከወንድ፣ ከሴት፣ ከገዥዎች፣ ከተራ ሰዎች፣ ከተማሩ እና ካልተማሩ ሰዎች ጎራ፣ ስለ ኢየሱስ ማንነት እንዲመሰክሩ ጥሪ አቅርቧል። እግዚአብሔር አብና መጽሐፍ ቅዱስም እንኳ ሁሉም ማንነቱን የሚያረጋግጡ መሆናቸውን ዮሐንስ አመልክቷል። ይህ ሳምንት የሚጀምረው በመጥምቁ ዮሐንስ ኃያል ምስክርነት ነው። ሌሎች ምስክሮችም ወደ መድረኩ ይመጣሉ፦ እንድርያስና ስምዖን ጴጥሮስ፣ ፊልጶስ እና ናትናኤል፣ እንዲሁም ማንም ያልጠበቀው ምስክር፣ ፈሪሳዊው ኒቆዲሞስ። ነገር ግን በጥላ ውስጥ የተደበቀ ሌላ ምሥክር ነበር፤ ከእንድርያስ ጋር ያለው ሌላ ደቀ መዝሙር ዮሐንስ ራሱ (ዮሐ. 1:35፣ 40)። የዚህን ሳምንት ትምህርት በማጥናት ለጥቅምት 16 ሰንበት ተዘጋጁ።

@SabbathSchool @TekalignSorato

SABBATH SCHOOL(ሰንበት ትምህርት )

18 Oct, 18:55


Live stream finished (1 hour)

SABBATH SCHOOL(ሰንበት ትምህርት )

18 Oct, 18:17


https://youtube.com/live/KWAUFaeIT98?si=reoBDCGfwZHGAzxB

SABBATH SCHOOL(ሰንበት ትምህርት )

18 Oct, 17:35


Live stream started

SABBATH SCHOOL(ሰንበት ትምህርት )

18 Oct, 14:55


ዛሬ Live በ YouTube ና Telegram Channel ይጠብቁን
#Subscribe #Share #Like #Comment

SABBATH SCHOOL(ሰንበት ትምህርት )

18 Oct, 08:11


SABBATH SCHOOL ሰንበት ትምህርት Live Stream 3ኛ ትምህርት የኋላ ታሪክ፡ መቅድም
https://youtube.com/live/nM0xd3EOBZg?si=pTQtb8UeAkoYF1U3

#Subscribe #Like #Share #Comment

SABBATH SCHOOL(ሰንበት ትምህርት )

18 Oct, 03:01


ዓርብ
ጥቅምት 8
Oct 18


ተጨማሪ ሀሳብ

ኤለን ጂ ዋይት፣ «እግዚአብሔር ከእኛ ጋር» በዘመናት ምኞት፣ ገጽ 19-26። “ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ፣ መለኮት የሆነው የእግዚአብሔር ልጅ፣ ከዘላለም ጀምሮ የነበረ፣ ግላዊ፣ ነገር ግን ከአባቱ ጋር የሆነ ነው። እርሱ የሰማይ ታላቅ ክብር ነበር። እርሱ ሰማያዊያን የሆኑ ጠቢባን አዛዥ ነበር፤ የመላእክትንም ስግደት እንደ መብቱ ተቀብሎታል። ይህ ከእግዚአብሔር የተቀማ አልነበረም (ምሳ. 8፡22-27 ተጠቅሷል።] “ዓለም ሳይፈጠር ክርስቶስ ከአብ ጋር አንድ የመሆኑ እውነት ውስጥ ብርሃንና ክብር አሉ። ይህ በመለኮታዊ የመጀመሪያ ክብር፣ በጨለማ ቦታ ውስጥ የሚያበራውን ብርሃን ያማረ ያደርገዋል። ይህ እውነት፣ በራሱ የማይደረስበት ምሥጢር ያለው ሆኖ ሳለ፣ ሌሎችን ሚስጥራዊ እና በሌላ መንገድ ሊገለጹ የማይችሉ እውነቶችን ያብራራል፣ እሱ ግን ማንም ሊቀርበው በማይችል እና ለመረዳት በማይቻል ብርሃን ውስጥ ተቀምጧል” (Ellen G. White Com- ments, The Seventh-day Adventist Bible Commentary, vol. 5, p. 1126)። “ኢየሱስም አለ፦ እኔ ከምድር ከፍ ከፍ ያልሁ እንደ ሆነ ሁሉን ወደ እኔ እስባለሁ” (ዮሐ. 12፡32)። ክርስቶስ ለኃጢአተኛው ሰው ስለ ዓለም ኃጢአት የሚሞት አዳኝ ሆኖ መገለጥ አለበት፤ እናም የእግዚአብሔርን በግ በቀራንዮ መስቀል ላይ ስናይ፣ የቤዛነት ምስጢር በአእምሯችን መገለጥ ይጀምራል፤ የእግዚአብሔርም ቸርነት ወደ ንስሃ ይመራናል። ለኃጢአተኞች ሲሞት ክርስቶስ ለመረዳት የማይቻል ፍቅር አሳይቷል፤ ኃጢአተኞች ይህን ፍቅር ሲያዩ፣ ልባቸው ይለዝባል፣ አእምሯቸውም ይደነቃል፣ እና በነፍሳቸው ውስጥ መጸጸት ይቀሰቀሳል። … (ሰዎች) ጽድቅን ለማድረግ በእውነተኛ መሻት ተነሳስተው ለመለወጥ ጥረት ባደረጉ ጊዜ ሁሉ፣ የክርስቶስ ኃይል ነው የሚስባቸው። እነርሱ ሳያውቁት ተጽእኖ በነፍስ ላይ ይሠራል፣ እናም ሕሊና ሕያው ይሆናል፣ ውጫዊው ህይወትም ይሻሻላል። ደግሞም ክርስቶስ መስቀሉን እንዲመለከቱ፣ ኃጢአታቸው የወጋውን እርሱን እንዲያዩ ሲስባቸው፣ ትእዛዙ ወደ ሕሊናቸው ይመጣል” (ኤለን ጂ ዋይት፣ ወደ ክርስቶስ የመሚመራ መንገድ፣ ገጽ 26፣ 27)።
የመወያያ ጥያቄዎች


1. ዮሐንስ ኢየሱስን በፈጣሪነት ሚናው ገልጾ በመናገር የጀመረው ለምንድን ነው? ይህ በሁሉም ሥነ-መለኮት ውስጥ ስለ ፍጥረት አስፈላጊነት ምን ይነግረናል? ታዲያ ለምንድን ነው በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እንደተገለጠው ስለ ፍጥረት ትክክለኛ ግንዛቤ እንዲኖረን የሚያስፈልገው? 2. በእሁድ ጥናት መጨረሻ ላይ በተጠየቀው ጥያቄ ላይ የበለጠ ጊዜ ወስዳችሁ ተወያዩ። በመስቀል ላይ የሞተው በዘለአለማዊው አምላክ ፋንታ ፍጡር ቢሆን ኖሮ ምን ይሆን ነበር? ኢየሱስ የዘላለም አምላክ ባይሆን ኖሮ የምናጣው ምን ነበር?

@SabbathSchool @TekalignSorato

SABBATH SCHOOL(ሰንበት ትምህርት )

17 Oct, 03:00


ሐሙስ
ጥቅምት 7
Oct 17

እንደገና የሚታዩ ጭብጦች - ክብር

ዮሐንስ 17:1-5ን ያንብቡ። ኢየሱስ፣ “አባት ሆይ፥ ሰዓቱ ደርሶአል፤ ልጅህ ያከብርህ ዘንድ፥ በሥጋም ሁሉ ላይ ሥልጣን እንደ ሰጠኸው፥ ለሰጠኸው ሁሉ የዘላለምን ሕይወት ይሰጣቸው ዘንድ ልጅህን አክብረው።” ሲል ምን ማለቱ ነበር?


Save Notes

የትናንቱ ጥናት በኢየሱስ ማንነት እና በሚሠራው ሥራ ላይ በማጠንጠን፣ የዮሐንስ ወንጌልን ምድራዊ፣ የሰው ታሪክ፣ በሰዎች መካከል ያለውን ግጭትና መስተጋብር አንስቶ ተመልክቷል። የዛሬው ጥናት የሚያተኩረው አሁንም በዮሐንስ ወንጌል ውስጥ በሚገኘው መለኮታዊ፣ ሰማያዊ ታሪክ ላይ ነው። መቅድሙ የሚጀምረው በዚያ የሰማይ ታሪክ ነው። ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ፣ የአጽናፈ ሰማይ ፈጣሪ ሆኖ ቀርቧል። አሁንም ከዚያ በፊት ያልነበረ ነገር ግን ወደ ሕልውና የመጣው ነገር ሁሉ የሆነው በኢየሱስ በኩል ብቻ ነው። “ሁሉ በእርሱ ሆነ ከሆነውም አንዳች ስንኳ ያለ እርሱ አልሆነም” (ዮሐ. 1:3)። ነገር ግን በሥጋ መልበስ (በተዋሕዶ) ሰው የመሆኑን ክብር እያስታወሰ ይቀጥላል (ዮሐ. 1፡14)። ዮሐንስ እነዚህ ትርጉሞች ያሏቸውን “ክብር” (“dox- sa” ብርሃን፣ ግርማ፣ ዝና፣ ክብር)፤ ማክበር (“doxsazo” ማሞገስ፣ ማክበር፣ ከፍ ማድረግ፣) የሚሉት ቃላትን ይጠቀማል። ከሰዎች ክብርን ስለማግኘት እና ከእግዚአብሔር ክብርን ወይም ግርማን ስለማግኘት ሁለቱንም ይናገራል። በዮሐንስ ወንጌል ውስጥ፣ ኢየሱስን የማክበር ሐሳብ ከእርሱ ሰዓት፣ ማለትም፣ ከመሞቱ ጊዜ ጽንሰ-ሐሳብ ጋር የተያያዘ ነው። (ከዮሐ. 2፡4፣ ዮሐ. 7፡30፣ ዮሐ. 8፡20፣ ዮሐ. 12፡ 23–27፣ ዮሐ. 13፡1፣ ዮሐ. 16፡32፣ ዮሐ. 17፡1 ጋር አነጻጽሩ) መስቀል የእርሱ የክብር ሰዓት ነው። ይህ ሐሳብ እርስ በርሱ የሚቃረን ነው፤ ምክንያቱም ስቅለት በጥንት የሮማውያን ዓለም እጅግ አሳፋሪ እና አዋራጅ የሞት ቅጣት መንገድ ነበር። ይህ የማይታመን ልዩነት፣ የአምላክ በመስቀል መሞት፣ የሰው ሴራ ታሪክ ከመለኮት ጋር መጠላለፉን ያሳያል። በሰው ደረጃ፣ ኢየሱስ፣ የተናቀው ወንጀለኛ በድካም “አምላኬ፣ አምላኬ፣ ለምን ተውከኝ?” ብሎ በሥቃይ በመጮህ ሞተ። ይህ ሰዋዊ የሆነ የመስቀሉ ጨለማ አንዱ ጎን በተለይ በማቴዎስ እና በማርቆስ ወንጌል ውስጥ ቀርቧል (ማቴ. 27፡46 ማር. 15:34)። ነገር ግን የመስቀሉ የክብር ሌላው ጎን በተለይ በሉቃስ እና በዮሐንስ ወንጌል ውስጥ ቀርቧል (ሉቃስ 23፡32–47፣ ዮሐ. 19፡25–30)። ይህም የመዳን፣ የምሕረት እና የእግዚአብሔር ልጅ ራሱን ለአባቱ የሚሰጥበት ቦታ ነው። እንዴት ያለ ተቃርኖ ነው! የእግዚአብሔር ታላቅ ክብር የሚገለጠው የዓለምን ኃጢአት በራሱ ተሸክሞ እጅግ በመዋረዱ ውስጥ ነው። እኛን ከኃጢአት ሊያድነን አምላክ ራሱ በመስቀል ላይ እንዲህ ያለ ከባድ ነገር ወሰደ ማለት ምን ማለት እንደሆነ አስቡ። ይህ ኃጢአት እንዴት መጥፎ እንደሆነ ምን ሊነግረን ይገባል?

@SabbathSchool @TekalignSorato

SABBATH SCHOOL(ሰንበት ትምህርት )

16 Oct, 03:01


ረቡዕ
ጥቅምት 6
Oct 16

እንደገና ብቅ የሚሉ ጭብጦች፡- ማመን/አለማመን

ዮሐንስ 3፡16-21፣ ዮሐንስ 9፡35-41፣ እና ዮሐንስ 12፡36-46ን ያንብቡ። እነዚህ ጽሑፎች በመቅድሙ ውስጥ የሚገኘውን የማመንን/አለማመንን ጭብጥ እንዴት ይደግማሉ?


Save Notes

በዮሐንስ ወንጌል ውስጥ፣ የሰው ልጅ በሁለት ዋና ዋና ቡድኖች የተከፈለ ይመስላል፦ በኢየሱስ አምነው እንደመሲህ የተቀበሉት እና የማመን እድል አግኝተው፣ ነገር ግን ላለማመን የመረጡት። ደቀ መዛሙርቱ ከመጀመሪያው ጎራ ውስጥ ናቸው፤ ልክ እንደ ኒቆዲሞስ (ቀስ በቀስ ወደ እምነት የመጣው)፣ በውኃ ጉድጓዱ አጠገብ የነበረችው ሴት፣ እና ዐይነ ሥውር ሆኖ የተወለደው ሰው። በሁለተኛው ቡድን ውስጥ ፈሪሳውያን እና ሊቃነ ካህናት፣ አምስት ሺህ ሰዎችን ሲመግብ ተአምር የተመለከቱ ሰዎች እና ሌላው ቀርቶ ከደቀ መዛሙርቱ አንዱ የሆነው ይሁዳ ይገኙበታል። የሚገርመው፣ “እምነት” ወይም በግሪክ “ፒስቲስ” (pistis) የሚለው ሥማዊ አገባብ ያለው ቃል በዮሐንስ ወንጌል ውስጥ ፈጽሞ አለመታየቱ ነው። ይሁን እንጂ “ማመን” “ፒሲቲኦ” (pisteu) የሚለው ግስ 98 ጊዜ ተጠቅሷል። በአጠቃላይ በሐዲስ ኪዳን ውስጥ ደግሞ ከ241 ጊዜ በላይ! ይህ ግስ በዮሐንስ ወንጌል ውስጥ በጣም ትልቅ ጭብጥ ነው። ከሥም ይልቅ የዚህ የግስ አጠቃቀም ክርስቲያን የመሆንን በጣም ንቁ ስሜት ሊያመለክት ይችላል። በኢየሱስ ማመን እኛ የምንተገብረው ነገር ነው፣ እናም እንዴት እንደምንኖር ይገለጻል እንጂ እንዲሁ በኃይማኖቶች ውስጥ መሆንን አይደለም። እንደምናውቀው፣ ዲያብሎስም እንዲሁ በየሱስ ያምናል (ያዕቆብ 2፡19 ይመልከቱ)። በዮሐንስ ወንጌል ውስጥ፣ በሁለቱ ቡድኖች መካከል ያለው ዋነኛው ልዩነት ከኢየሱስ ጋር ያላቸው ግንኙነት ነው። አማኞች፣ ወይም ያመኑት፣ ሲቃወማቸው ወይም ሲገስጻቸውም፣ ለእርሱ ግልጽነት አላቸው። ወደ ኢየሱስ ይመጣሉ እንጂ ሸሽተው አይሄዱም። እርሱ የሚያበራላቸው ብርሃን ነው። እናም በእምነትና በማመን የእግዚአብሔር ልጆች ይሆናሉ። የማያምኑት ግን በተለምዶ እርሱን ለመቃወም ወደ ኢየሱስ ይመጣሉ። ከብርሃን ይልቅ ጨለማን የሚወዱ ሰዎች በመሆን ተለይተው ይታወቃሉ። ንግግሩን መቀበል ይከብዳቸዋል ወይም ያረጁ ወጎቻቸውን ሲጥስ እና የጠበቁትን ሳይፈጽም ያዩታል። የእርሱ ብርሃን እንዲዳኛቸውና እንዲመዝናቸው ከመፍቀድ ይልቅ በእርሱ ላይ ለመፍረድ ይቆማሉ። ነገር ግን እንደ ሕዝቡ መንፈሳዊ መሪዎች ኢየሱስን ለመቀበል የመጀመሪያዎቹ ሊሆኑ ሲገባ፣ ይህ አመለካከት በኃይማኖት መሪዎች ዘንድ በተደጋጋሚ ታይቷል። የሱስ መሲሕ መሆኑን በአእምሮ ከማወቅ ባለፈ፣ እምነታችሁን እንዴት ነው በሕይወታችሁና በኑሯችሁ የምትገልጡት? ልዩነቱን ማወቅ ለምን አስፈለገ?(ማቴ. 7:21–23 ተመልከቱ)።

@SabbathSchool @TekalignSorato

SABBATH SCHOOL(ሰንበት ትምህርት )

15 Oct, 18:48


Live stream finished (8 minutes)

SABBATH SCHOOL(ሰንበት ትምህርት )

15 Oct, 18:40


Live stream started

SABBATH SCHOOL(ሰንበት ትምህርት )

15 Oct, 18:39


Live stream finished (1 hour)