Nejashi Tv // ጄይሉ ቲቪ @jeilumedia Channel on Telegram

Nejashi Tv // ጄይሉ ቲቪ

@jeilumedia


የጄይሉ ሚዲያ ቤተሰብ ስለሆኑ እናመሰግናለን ። የተለያዩ መረጃዎችና እውቀቶች ይገበያሉ ። ተቀላቀሉን ! Facebook: https:// Jeilumedia.com
Telegram: https://t.me/Jeilumedia
E-mail: [email protected]
Subscribe: https://www.youtube.com/c/JeiluTube/videos
t.me/Jeilumedia

ጄይሉ ቲቪ // Jeilu Tv (Amharic)

ጄይሉ ቲቪ // Jeilu Tv የጄይሉ ሚዲያ ቤተሰብ ስለሆኑ እናመሰግናለን። የተለያዩ መረጃዎችና እውቀቶች ይገበያሉ። በጄይሉ ቲቪ ላይ የተለያዩ የሚዲያ መረጃዎችን እና ሰብን ለመለዋወጥ ይህንን ላንተም በተጨማሪ ምርጥ መረጃዎችን ማግኘት ይችላሉ። እናመሰግናለን! በፈቃዱ ይህም እባኮት ሊነሱት የሚያመልኩት መረጃዎችን እንዴርግ።nnእስከዚህበሚባለን አዝናኝ ታይቷል። በአማርኛ ብቻ የተመለከተው እባኮት፣ ጄይሉ ቤተሰብ፣ ፡፡እያንዳንዱም ተዋናይ ቅምሻዎችን በመላክ ተመልክተው እና በአዝናኝ የአገልግሉ የሚዲያዎችን ይዘምቱ። በታችኛላችሁ፣ ትክክለኛላችሁ፣ ከዚህ ቀጣይነት እና ልቅሶዎትን ወደ ተከታዮች እንጠብቁ።nnየፌስትቫል ገቢጫ፣ ቴሌግራም ።። ኢሜል፣ ።፣ ዝርዝር፦፦፡፡nnማንኛውም በዚህበሚባለን አዝናኝ ታይቷል ።፤ በአማርኛ ብቻ የተመለከተው, ጄይሉ ቤተሰብ ። ፡፡ እያንዳንዱም ተዋናይ ቅምሻዎችን በመላክ ተመልክተው እና በአዝናኝ የአገልግሉ የሚዲያዎችን ይዘምቱ ።nnየትክክለኛዶች ለእይለቤተሰብ፣ ቆመው መረጃዎቹ፣ በዓለምላካችች አገልግሎታዊነውና።

Nejashi Tv // ጄይሉ ቲቪ

15 Feb, 18:24


የጅቡቲው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ኾኑ

ነጃሺ ቲቪ የካቲት 8/2017

ጅቡቲን ለብዙ ዓመታት በውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነት ያገለገሉት መሐመድ ዓሊ ዩሱፍ ቀጣዩ የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ኾነው ተመረጡ። ‘
አዲስ አበባ ውስጥ በሚገኘው የአፍሪካ ኅብረት ዋና ጽሕፈት ቤት እየተካሔደ ባለው 38ኛው የአፍሪካ ኅብረት ጉባኤ ላይ፣ መሪዎቹ በሚስጥር በሰጡት ድምጽ የጅቡቲው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፣ ኮሚሽኑን በሊቀመንበርነት እንዲመሩ ተመርጠዋል።
ኮሚሽኑን እንዲመሩ በሊቀመንበርነት የተመረጡት የጅቡቲው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፣ በአፍሪካ ኅብረት አዳራሽ በተካሔደውና ብርቱ ፉክክር በታየበት፣ እንዲኹም እስከ ሰባተኛ ዙር ድረስ በዘለቀ ምርጫ ሁለት ሦስተኛ ድምጽ አግኝተው ነው።
ከሳምንት በፊት 60ኛ ዓመት የልደት በዓላቸውን ያከበሩት ዩሱፍ፣ በምርጫው አሸናፊ የኾኑት የኬንያውን የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ራይላ ኦዲንጋ እና የማዳጋስካር የቀድሞ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሪቻርድ ራንድሪያማንድራቶን በማሸነፍ ነው።
ዩሱፍ በመጀመሪያዎቹ ሁለት ዙሮች በ18 እና በ19 ድምፅ አግኝተው ከራኢላ ጋራ በተቀራረበ ሁኔታ ሁለተኛ ዙር ላይ ነበሩ። ከሦስተኛው ዙር ጀምሮ በተካሔዱት የድምጽ አሰጣቶች ግን ዩሱፍ በመሪነት ቀጥለዋል። በመጨረሻም ለአሸናፊት የሚያበቃው 33 ድምጽ በማግኘት የመሪነቱ ቦታ ተረክበዋል።
አዲሱ የኅብረቱ ተመራጭ ኮሚሽነት እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር፣ከ2005 ዓ.ም ጀምሮ የጅቡቲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኾነው አገልግለዋል። በአፍሪካ አህጉር ረዥም ጊዜ ያገለገሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርም ናቸው።
ከኅብረቱ ከታገዱት ስድስት ሀገራት በስተቀር 55ቱም የአባል ሀገራት በ38ኛው የኅብረቱ መሪዎች ጉባኤ ላይ እየተሳተፉ ነው።

Nejashi Tv // ጄይሉ ቲቪ

15 Feb, 10:36


ሊባኖስ የኢራን መንገደኞች አውሮፕላን ወደ ቤይሩት እንዳይገባ አገደች

እስራኤል ኢራን የሲቪል ማመላለሻ አውሮፕላኖችን በመጠቀም ለ ሂዝቦላህ ቡድን ገንዘብ ታቀብላለች የሚል ክስ ከአቀረበች ከአንድ ቀን በኃላ፣ ሊባኖስ ማሃን የተሰኘው የኢራን አየር መንገድ ንብረት የሆነ በረራ ወደ ቤይሩት እንዳይገባ አግዳለች።

ሊባኖስ የማረፍ ፍቃድ መከልከሏን ተከትሎም፣ የኢራኑ አየር መንገድ ወደ ቤይሩት ሊያደርገው የነበረውን በረራ አውሮፕላኑ ከመነሳቱ በፊት መሰረዙን፣ የታህራን ኢማም ኮሜይኒ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሰኢድ ቻላንድሪ ለኢራን መንግሥት የዜና ወኪል ተናግረዋል።

አንድ የኢራን ጋዜጠኛ ኤክስ በተሰኘው መተግበሪያ ላይ ባጋራው እና የቪኦኤ የፋርስ ቋንቋ አገልግሎት ትክክለኛነቱን ባረጋገጠው የቪዲዮ መረጃ፣ በአውሮፕላኑ ተሳፍረው የነበሩ መንገደኞች ሲጠባበቁ እና ትእግስቱ ያለቀ አንድ ግለሰብ በመቆየቱ ተሰላችቶ ሲጮህ ያሳያል።

የሊባኖስ ሲቪል አቪዬሽን በውሳኔው ዙሪያ ከአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ አርብ እለት ለቀረበለት ጥያቄ ምላሽ አልሰጠም።
ሆኖም መስሪያቤቱ ባወጣው መግለጫ፣ ሊባኖስ መካከለኛው ምስራቅ አየር መንገድ ከተሰኘው ብሔራዊ አየር መንገድ ጋር በመተባበር፣ በታህራን የሚገኙት ዜጎች ወደ ቤይሩት የሚመለሱበትን መንገድ እያመቻቸ መሆኑን ገልጿል።

ሊባኖስ ርምጃውን የወሰደችው የእስራኤል ጦር ቃል አቀባይ አቪቻይ አድራኤ፣ ረቡዕ ዕለት በአረብኛ በሰጡት መግለጫ፣ የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ጋርድ ኃይል ወደ ቤይሩት የሚበሩ የመንገደኞችን በረራ በመጠቀም ለሂዝቦላህ ገንዘብ ያዘዋውራል በማለት መክሰሳቸውን ተከትሎ ነው።

ማሃን የተሰኘው የኢራን አየር መንገድ፣ ዩናይትድ ስቴትስ ለሂዝቦላህ የገንዘብ እና ጦር መሳሪያ ድጋፍ ያደርጋሉ በማለት ማዕቀብ ከጣለችባቸው የኢራን ተቋማት አንዱ ነው።

Nejashi Tv // ጄይሉ ቲቪ

15 Feb, 10:33


ኩዌት ዝቅተኛውን የትዳር እድሜ ወደ 18  አመት ከፍ አደረገች


ነጃሺ ቲቪ የካቲት 8/2017

ኩዌት የህጻናትን መብት ለማስጠበቅ እና የቤተሰብ መረጋጋትን ለማጠናከር በሚል የህግ ማሻሻያዎች ማድረጓን ተከትሎ ለጋብቻ የሚፈቀደውን ዝቅተኛ እድሜ ወደ 18  አመት በይፋ ማሳደጓን የሀገሪቱ  የፍትህ ሚኒስትር ናስር አል ሱማይት አስታውቀዋል።

በሀገሪቱ  ምንም ዓይነት ጋብቻ 18 ዓመት ሳይሞላው እንደማይፈጸም ተደንግጓል።

እርምጃው የህጻናት መብቶች እና  በሴቶች ላይ የሚደርሰውን  ሁሉንም አይነት መድልዎ ለማስወገድ ነው ተብሏል።

  የ ስታቲስቲክስን መረጃ እንደሚያመላክተው   እ.ኤ.አ. በ2024  1 ሺ 145 ለአቅመ አዳም ያልደረሱ ትዳሮች የተመዘገቡ ሲሆን ከእነዚህም መካከል 1,079 ሴት ልጆች እና 66  ደግሞ ወንዶች  ናቸው።

ጥናቶች እንዳመለከቱት ለአካለ መጠን ያልደረሱ ልጆች የፍቺ መጠን ከአዋቂዎች በእጥፍ እንደሚበልጥ ያመላከተ ሲሆን ይህም የትዳር ጓደኞቻቸው ከጋብቻ በፊት ስሜታዊ እና ማህበራዊ እድገት  ላይ እንዲደርሱ የህግ ጣልቃ ገብነት ያስፈልጋል ነው የተባለው።

የህግ ማሻሻያው ኩዌት ቤተሰብ እና ህጻናትን ለመጠበቅ ባላት ህገ-መንግስታዊ ቁርጠኝነት ላይ መሆኑን ሚኒስትሩ አፅንዖት ሰጥተዋል።

አክለውም የጋብቻ እድሜን በማሳደግ ፣ኩዌት ወጣቶችን ለመጠበቅ ፣ፍቺን ለመቀነስ እና የቤተሰብ መረጋጋትን ለማሳደግ ወሳኝ እርምጃ እየወሰደች ነው ብለዋል ።

Nejashi Tv // ጄይሉ ቲቪ

15 Feb, 10:32


ኩዌት ዝቅተኛውን የትዳር እድሜ ወደ 18  አመት ከፍ አደረገች


ነጃሺ ቲቪ የካቲት 8/2017

ኩዌት የህጻናትን መብት ለማስጠበቅ እና የቤተሰብ መረጋጋትን ለማጠናከር በሚል የህግ ማሻሻያዎች ማድረጓን ተከትሎ ለጋብቻ የሚፈቀደውን ዝቅተኛ እድሜ ወደ 18  አመት በይፋ ማሳደጓን የሀገሪቱ  የፍትህ ሚኒስትር ናስር አል ሱማይት አስታውቀዋል።

በሀገሪቱ  ምንም ዓይነት ጋብቻ 18 ዓመት ሳይሞላው እንደማይፈጸም ተደንግጓል።

እርምጃው የህጻናት መብቶች እና  በሴቶች ላይ የሚደርሰውን  ሁሉንም አይነት መድልዎ ለማስወገድ ነው ተብሏል።

  የ ስታቲስቲክስን መረጃ እንደሚያመላክተው   እ.ኤ.አ. በ2024  1 ሺ 145 ለአቅመ አዳም ያልደረሱ ትዳሮች የተመዘገቡ ሲሆን ከእነዚህም መካከል 1,079 ሴት ልጆች እና 66  ደግሞ ወንዶች  ናቸው።

ጥናቶች እንዳመለከቱት ለአካለ መጠን ያልደረሱ ልጆች የፍቺ መጠን ከአዋቂዎች በእጥፍ እንደሚበልጥ ያመላከተ ሲሆን ይህም የትዳር ጓደኞቻቸው ከጋብቻ በፊት ስሜታዊ እና ማህበራዊ እድገት  ላይ እንዲደርሱ የህግ ጣልቃ ገብነት ያስፈልጋል ነው የተባለው።

የህግ ማሻሻያው ኩዌት ቤተሰብ እና ህጻናትን ለመጠበቅ ባላት ህገ-መንግስታዊ ቁርጠኝነት ላይ መሆኑን ሚኒስትሩ አፅንዖት ሰጥተዋል።

አክለውም የጋብቻ እድሜን በማሳደግ ፣ኩዌት ወጣቶችን ለመጠበቅ ፣ፍቺን ለመቀነስ እና የቤተሰብ መረጋጋትን ለማሳደግ ወሳኝ እርምጃ እየወሰደች ነው ብለዋል ።

Nejashi Tv // ጄይሉ ቲቪ

15 Feb, 06:49


ሳውዲ አረቢያ የዘንድሮውን የሐጅ መመሪያዎች ይፋ አደረገች

ነጃሺ ቲቪ የካቲት 7/2017

የሳዑዲ አረቢያ የሃጅ እና ዑምራ ሚኒስቴር የ1446ኛውን  ሀጅ ለመፈፀም ለሚፈልጉ ዜጎች እና የውጭ ሀገር ነዋሪዎች  መመሪያዎችን ይፋ ያደረገ ሲሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ሀጅ ለሚያደርጉ  ሀጃጆች ቅድሚያ መስጠትን  ፣የጤና ሁኔታን  እና ህጋዊ ሰነዶች መሆን አለባቸው ሲል አፅንዖት ሰጥቷል።

ሀጃጆች  እስከ ዙልሂጃህ 10 ድረስ የሚቆይ  ብሄራዊ መታወቂያ ወይም የመኖሪያ ፍቃድ መያዝ አለባቸው  የተባለ ሲሆን ጊዜው ያለፈባቸው ሰነዶች ተቀባይነት እንደሌለላቸውም ተገልጿል።

የቅድሚያ ምዝገባ የሚከናወነው ሐጅ አድርገው ለማያውቁት እና ለአረጋውያን፣ ለአካል ጉዳተኞች መሆኑ ተገልጿል።

ሚኒስተሩ  የግል እና የህዝብ ደህንነትን ሊጎዱ የሚችሉ አጣዳፊ እና ሥር የሰደደ  ተላላፊ በሽታዎች ያለባቸው ሰዎችም ከጉዞው እንደሚከለከሉ አስታውቋል።

የማጅራት ገትር በሽታ እና ወቅታዊ የኢንፍሉዌንዛ በሽታ ተጠቂዎችም  ክትባት ለመውሰዳቸው  ማረጋገጫ ግዴታ ነው ተብሏል።

 

Nejashi Tv // ጄይሉ ቲቪ

14 Feb, 16:39


12 አመታት ማየት ያልቻለችው ሳዑዳዊቷ እንስት ማየት ቻለች

ነጃሺ ቲቪ የካቲት7/2017

ኑፍ አል ራሺዲ የተባለችው ሳዑዳዊት የአይኗ ብርሀን  ከተመለሰ በኋላ በአንድ ቀን የሦስቱ ወንድ ልጆቿን ሰርግ  ማየቷ ተነግሯል።

ከ12 አመት በፊት አይኗ የጠፋባት ሳውዲያዊት ሴት በሀገሯ ቀዶ ጥገና ከተደረገላት በኋላ በቅርቡ ለማየት ችላለች።

  በኬሚካል ሳቢያ እይታዋን ያጣችው  ኑፍ አል ራሺዲ ማየት ባለመቻሏ  የደረሰባትን ስቃይ ስታስታውስ እንባዋን መቆጣጠር አልቻለችም።

ኑፍ አል ራሺዲ የተባለችው ሳዑዳዊት የአይኗ ብርሀን  ከተመለሰ በኋላ በአንድ ቀን የሦስቱ ወንድ ልጆቿን ሰርግ  ማየቷ ተነግሯል።

ከ12 አመታት የስቃይ ጊዜ በኋላ የማየት ግለሰቧ    ከቅድስቷ ከተማ መዲና መኪናዋን ከሴት ልጆቿ ጋር በመንዳት ወደ ዋና ከተማዋ ሪያድ አድርሳለች።

ኑፍ ከሳውዲው ቴሌቪዥን ጋር ባደረገችው ቃለ ምልልስ መኪናዋን ወደ ሪያድ እራሷ ለመንዳት ቃል መግባቷን እና አስደሳች እና ደህንነቱ የተጠበቀ ጉዞ የመሄድ ህልሟ እውን መሆኑን ገልጻለች።

ዓይኔን ካገኘሁ ወደ መካ ሄጄ ዑምራ እንደማደርግ  ቃል ገብቻለሁ ያለችው ግለሰቧ   "አላህን የተመሰገነ ይሁን ዑምራን አደረኩ" ብላለች።

በመኪናዬ ከመዲና ወደ ሪያድ ለመሄድም ቃል ገብቸ ነበር ምኞቴም ተፈጽሟል፣ ከሴት ልጆቼ  ጋርም   ጥሩ አሳልፌያለሁ ስትትል ተናግራለች።

ኑፍ የተሳካ ቀዶ ጥገና ያደረገችበትን  የሆስፒታሉን ሰራተኞች  ያመሰገነች ሲሆን ለሰራተኞቹ የክብር ስነ ስርዓት ለማድረግ እንደምትፈልግ ተናግራለች።

ዶ/ር ሳሚ ቢን ሃሚድ የተባሉት የኮርኒያ አማካሪ አንዳንድ የቤት ውስጥ ኬሚካሎች ለዓይን እይታ ስለሚያደርሱት አደጋ አስጠንቅቀዋል።

ለእይታ መጥፋት ከሚዳርጉ ዋና ዋና ምክንያቶች መካከል የቤት ውስጥ ሳሙናዎች እና የመኪና ባትሪዎች መሆናቸውን ጠቁመው ከእነዚህ ንጥረ ነገሮች ጋር በተያያዘ ጥንቃቄና የደህንነት እርምጃዎችን መከተል ያስፈልጋል ብለዋል።

Nejashi Tv // ጄይሉ ቲቪ

14 Feb, 14:03


የእስራኤል ፓርላማ የኤርትራ መንግሥትን የሚደግፉ ስደተኞችን ከሀገር የሚያባርር ረቂቅ ሕግን አሳለፈ

ነጃሺ ቲቪ የካቲት 7/2017

የእስራኤል ፓርላማ መንግሥታቸውን የሚደግፉ የኤርትራ ስደተኞችን ከአገር ለማባረር ያለመውን ረቂቅ ሕግ የመጀመሪያውን ዙር በሙሉ ድጋፍ አሳልፏል።

ክኔሴት ተብሎ የሚጠራው የእስራኤል ፓርላማ ኤርትራውያን ስደተኞችን ከአገር ለማባረር ያለመውን ረቂቅ ሕግ የመጀመሪያ ዙር 51 ለ 0 በሆነ ድምጽ ማሳለፉን የእስራኤሉ ጋዜጣ ዘ ታይምስ ኦፍ እስራኤል ዘግቧል።

ያለ ምንም ተቃውሞ ያለፈው ይህ ረቂቅ ሕግ ለኤርትራ መንግሥት ድጋፋቸውን የሚገልጹ ኤርትራውያን ስደተኞችን ከእስራኤል የማባረር ሥልጣንን ለሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር ለመስጠት ያለመ እንደሆነ ዘገባው አስነብቧል።

የኤርትራ መንግሥትን የሚደግፉ በእስራኤል ያሉ ስደተኞች ጥገኝነት የሚጠይቁበት ምንም ምክንያት እንደሌላቸው ተደርጎ እንደሚቆጠርም ተገልጿል።

የተለያዩ የእስራኤል የመንግሥት ባለሥልጣናት ከዚህ ቀደም የተለያዩ ተከታታይ እርምጃዎችን የወሰዱ ሲሆን፣ አንዳንዶቹም በፍርድ ቤት ታግደዋል።

በእስራኤል ውስጥ ወደ 20 ሺህ የሚጠጉ ኤርትራውያን ስደተኞች ይኖራሉ። ስደተኞቹ በሀገራቸው ያለውን ጭቆና እንዲሁም ጦርነት ሸሽተው በእስራኤል ጥገኝነት የሚጠይቁ ናቸው።

ከባለፉት ጥቂት ዓመታት ጀምሮ እስራኤልን ጨምሮ በተለያዩ አገራት የሚኖሩ ኤርትራውያን ስደተኞች በአገዛዙ ደጋፊዎች እና በተቃዋሚዎች ጎራ ተከፋፍለው ተደጋጋሚ ግጭቶች ውስጥ ገብተዋል። ባለፈው ዓመት ነሐሴ ወር በሁለት ኤርትራውያን ቡድኖች መካከል በቴል አቪቭ በተፈጠረ የጎዳና ላይ ግጭት ሁለት ሰዎች ተገድለዋል።

በእስራኤል ከሁለት ዓመታት ገደማ በፊት በኤርትራ መንግሥት ደጋፊዎች እና ተቃዋሚዎች መካከል በተነሳ ግርግር እንዲሁም ከፖሊስ ጋርም በተፈጠረው ግጭት ከ170 በላይ ሰዎች ቆስለዋል።

በርካቶች ተጎድተውበታል እንዲሁም ከፍተኛ የንብረት መውደም ተከስቶበታል በተባለውም በዚህ ግርግር ተሳትፈዋል የተባሉ ኤርትራውያን ጥገኝነት ጠያቂዎችን በአስቸኳይ ከሀገር ማባረርን ጨምሮ ጠንከር ያለ እርምጃም ይወሰድባቸዋል ተብሎ ነበር።

Nejashi Tv // ጄይሉ ቲቪ

13 Feb, 15:03


ፑቲንና የሶሪያ ፕሬዝዳንት አል ሻራ ለመጀመሪያ ጊዜ መነጋራቸው ተሰማ

ነጃሺ ቲቪ የካቲት 6/2017

የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ከአዲሱ የሶሪያ የሽግግር መንግስት ፐሬዝዳንት አህመድ አል ሻራ ጋር ለመጀመሪያ ጊዜ መነጋራቸው ተሰምቷል።
ፕሬዝዳንት ፑቲንና የሶሪያ ፕሬዝዳንት አል ሻራ የመጀመሪያ ውይታቸውን በስልክ እንዳደረጉም የሶሪያ ፕሬዝዳንት ጽህፈት ቤት ባወጣው መግለጫው አስታውቋል።

በውይይቸውም አል-ሻራ "በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ጠንካራ ስትራቴጂያዊ ግንኙነት ያነሱ ሲሆን፤ ሶሪያን ህዝብ ጥቅም በጠበቀ መልኩ እንዲሁም የሶሪያን መረጋጋት እና ደህንነትን ማጠናከር ላይ ሀገራቸው ከሁሉም ወገኖች ጋር ለመስራት በሯ ክፍት መሆኑን ገልጸዋል።
በተጨማሪም ፑቲን የሶሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሳድ አል-ሻይባኒ ሩሲያን እንዲጎበኙ ይፋዊ ግብዣ ማቅረባቸውን የሶሪያ ፕሬዝዳንት ጽህፈት ቤት አስታውቋል።

"የሩሲያ የሶሪያን ሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት እንደምትደግፍ በውይይቱ ላይ መነሳቱን ክሬምሊን ባወጣው መግለጫው አስታውቋል።
በአል ሻራ የሚመራው ሃያት ታህሪር አል ሻም ቡድን የሩሲያ የቅርብ አጋር የነበሩትን የቀድሞ የሶሪያ ፕሬዝዳንት በሽር አል አሳድን ባሳለፍው ታህሳስ ወር ከስልጣን ማስወገዱ ይታወሳል።

የሞስኮ የቅርብ አጋር የነበሩት በሽር አል አሳድ ከስልጣን መወደቃቸውን ተከትሎ በሶሪያ የሚገኙ ሁለት የሩሲያ ወታደራዊ ጣቢያዎች እጣ ፈንታ ጥያቄ ሲነሳበት መቆየቱም ይታወቃል።

Nejashi Tv // ጄይሉ ቲቪ

13 Feb, 15:01


አል አዝሀር ዩኒቨርስቲ ፍልስጤማውያንን ለማፈናቀል የሚደረገውን እቅድ  ውድቅ እንዲሆን ጠየቀ

ነጃሺ ቲቪ የካቲት 6/2017

መቀመጫውን  ግብጽ ያደረገው አል-አዝሀር ዩኒቨርስቲ  የአረብ ሙስሊም እና የአለም መሪዎች ፍልስጤማውያንን ከመሬታቸው ለማፈናቀል የሚደረገውን እቅድ ውድቅ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርቧል።

ታዋቂው  የግብጽ ዩኒቨርሲቲ አል-አዝሃር፤ ሙስሊም ሀገራት ፍልስጤማውያንን ከመሬታቸው ለማፈናቀል የሚደረገውን “ማንኛውንም ሙከራ እንዲቃወሙ” ጥሪ ያቀረበው አዲስ ባወጣው መግለጫ ነው፡፡

ዩኒቨርሲቲው መላው ዓለም“የፍልስጤማዊያን መብት እንዲከበር ከጎናቸው እንዲቆም” እንዲሁም “ቁድስን ዋና ከተማ ያደረገ የራሳቸው ሀገር እንዲመሠርቱ ሊደግፋቸው ይገባል” ብሏል፡፡

ተቋሙ ባወጣው መግለጫ  የጋዛ ሰርጥን መልሶ ለመገንባት   አረቦች  የግብጽን አቋም  እንዲደግፉ እና ህዝቡን ወደ ሌላ ቦታ ሳያፈናቅሉ በአካባቢው የተኩስ አቁም ስምምነትን ተግባራዊ ለማድረግ ግፊት እንዲደረግ ጠይቋል።

ዕቅዱን የተቃወመው ዩኒቨርሲቲው፤ “ማንም ቢሆን የፍልስጤም ሕዝብ የማይጨበጡ ምክረ ሐሳቦችን እንዲቀበል ግፊት የማድረግ ወይም የማስገደድ መብት የለውም” ብሏል፡፡

በመላው ዓለም የሚገኙ የሃይማኖት አባቶች ፍልስጤማዊያንን ለመከላከል ድምጽ እንዲያሰሙ ጠይቋል፡፡ አሀይማኖት አባቶቹ  በተጨማሪም የሃይማኖት ተቋማት ተቆርቋሪነት እንዲያሳዩ ተጠይቀዋል፡፡

የሙስሊሙ ዓለም ከፍልስጤማዊያን ጎን እንዲቆም ጥሪ ያቀረበው አል-አዝሃር ዩኒቨርሲቲ፤ መቀመጫውን ካይሮ በማድረግ በሙስሊሙ ዓለም የሃይማኖት ትምሕርት ማዕከል በመሆን የሚታወቅ ነው፡፡

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋዛን ተቆጣጥረው ፍልስጤማውያንን በግብፅ እና በዮርዳኖስ እንዲያሰፍሩ ደጋግመው ጠይቀዋል።

Nejashi Tv // ጄይሉ ቲቪ

08 Feb, 13:35


የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስተር  ፍልስጤማውያን በሳውዲ አረቢያ ግዛት ሊኖራቸው እንደሚችል ጠቆሙ

ነጃሺ ቲቪ የካቲት 1/2017

የእስራኤል ጠቅላይ ሚንስትር  በሰጡት መግለጫ አሜሪካ ፍልስጤማውያንን ለማፈናቀል ያቀረበችውን ሃሳብ አውግዞ የነበረውን የሳዑዲ መንግስት የሚቃረን ነው


የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ባለፈው ሐሙስ የፍልስጤማውያን የራስን ዕድል በራስ የመወሰን መብት በማጣጣል ፍልስጤማውያን በትውልድ አገራቸው ሳይሆን በሳውዲ አረቢያ ውስጥ መንግስት መመስረት እንዳለባቸው  ጠቁመዋል።

ኔታንያሁ ከእስራኤል ቻናል 14 ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ  "ሳውዲዎች በሳውዲ አረቢያ የፍልስጤም መንግስትን መፍጠር ይችላሉ፣ ሲሉ ተናግረል።

ይህ አስተያየት የመጣው ሳዑዲ አረቢያ እና እስራኤል ግንኙነታቸውን መደበኛ ከማድረግ የራቁ በሚመስሉበት ወቅት ነው

ሪያድ የፍልስጤም ሀገርነት እስካልተመሰረተ ድረስ  ከእስራኤል ጋር መደበኛ ግንኙነት እንደማይኖራት    ደጋግማ አስታውቃለች።

ኔታንያሁ ግን የሳዑዲን  ሃሳብ ውድቅ በማድረግ “ለእስራኤል የጸጥታ ስጋት” በማለት መግለጻቸውን ሚዲል ኢስት አይ ዘግቧል።

ቃለ ምልልሱ የተካሄደው ኔታንያሁ በአሜሪካ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ላይ በነበሩበት ወቅት ነው።

የትራምፕ አማካሪዎች የባህረ ሰላጤው ሀገራት በጋዛ ላይ እንዲተባበሩ ግፊት ያደርጋሉ ነገር ግን ምንም ተቀባይነት አላገኙም።

ፕሬዚዳንት ትራንፕ  ፍልስጤማውያንን ከጋዛ ለማስወጣትና  የፍልስጤማውያንን ግዛት ለመቆጣጠር ማሰባቸውን ይፋ ካደረጉ በኋላ በርካታ ትችትና ተቃውሞ ገጥሟቸዋል።

የሳዑዲ አረቢያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው  መግለጫ መንግሥቱ በፍልስጤም ግዛት ላይ ያለው አቋም "ጽኑ እና የማይለወጥ" ነው ማለቱ ይታወሳል።

Nejashi Tv // ጄይሉ ቲቪ

08 Feb, 13:31


አሜሪካ ለእስራኤል 7 ነጥብ 4 ቢሊየን ዶላር የሚያወጡ የጦር መሳሪያዎችን ልትሸጥ ነው

ነጃሺ ቲቪ የካቲት 1/2017

አሜሪካ ለእስራኤል 7 ነጥብ 4 ቢሊየን ዶላር የሚያወጡ የጦር መሳሪያዎችን ለመሸጥ መስማማቷ ተነግሯል።

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የጦር መሳሪያ ሽያጩን ማጽደቁን ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በትናንትናው እለት ተናግረዋል።
6 ነጥብ 75 ቢሊየን ዶላር የሚያወጡ የተለያዩ የጦር መሳሪያዎችን የሚያቀርበው ቦይንግ ኩባንያ ነው ተብሏል።

የጦር መሳሪያ አምራቹ ሎክሄድ ማርቲን ደግሞ 660 ሚሊየን ዶላር የሚያወጡ "ሄልፊር" ሚሳኤሎችን ያቀባል ብሏል ሬውተርስ በዘገባው።


ፕሬዝዳንት ትራምፕ ለኮንግረንሱ ሳያሳውቁና ሳያጸድቁ በሺዎች የሚቆጠሩ ሚሳኤሎችና ቦምቦችን ሽያጭ ማጽደቃቸው ዴሞክራቶች ትችት እንዲያነሱባቸው አድርጓል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ማርኮ ሩቢዮም የኮንግረንሱን መደበኛ የምርመራ ሂደት ለመተላለፍ የሚያስችል አሳማኝ ማስረጃ ማቅረብ አልቻሉም ነው ያሉት በህዝብ ተወካዮች ምክርቤት ዴሞክራቶችን የወከሉት ግሪጎሪ ሚክስ።
ተወካዩ "እስራኤል ለተደቀነባት ቀጠናዊ የደህንነት ስጋት ምላሽ እንድትሰጥ ወታደራዊ ድጋፍ ማድረግ እንዳለብን አምናለሁ፤ ነገር ግን የረጅም አመታት ልምዳችን እየተጣሰ መሄዱ ያሳስበኛል" ብለዋል።

ይሁን እንጂ በዴሞክራቱ ጆ ባይደን የስልጣን ዘመንም የኮንግረንሱ ይሁንታ ሳይጠበቅ ለእስራኤል የጦር መሳሪያ ሽያጭ ጸድቆላታል።

የባይደን አስተዳደር ባለፈው አመት 50 ኤፍ -15 ጄቶችን ጨምሮ 20 ቢሊየን ዶላር የሚያወጣ የጦር መሳሪያ ሽያጭ ማጽደቁን ሲኤንኤን አስታውሷል።
በመጀመሪያ የስልጣን ዘመናቸው በቴል አቪቭ የሚገኘውን የአሜሪካ ኤምባሲ ወደ እየሩሳሌም ያዛወሩት ትራምፕ ዳግም ወደ ዋይትሃውስ ከተመለሱ በኋላም ለእስራኤል ድጋፋቸውን እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል።

ከሰሞኑ ከእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ጋር በዋሽንግተን ሲመክሩ ጋዛን ለመቆጣጠር ማቀዳቸውን መግለጻቸውም ከአለማቀፉ ማህበረሰብ ከፍተኛ ነቀፌታ አስተናግዶባችዋል።

የትራምፕ አስተዳደር አዲስ የጦር መሳሪያ ሽያጭም የጋዛውን ጦርነት ዳግም አስነስቶ የቴህራን እና ቴል አቪቭ ፍጥጫንም እንዳያንረው ተሰግቷል።

Nejashi Tv // ጄይሉ ቲቪ

19 Jan, 19:43


የተኩስ አቁም ስምምነቱን የተቃወሙ እስራኤላዊ አመራሮች ስራ እየለቀቁ ነው ተባለ
ነጃሺ ቲቪ ጥር 12/2017

በእስራኤል እና በሃማስ መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም ውል ዛሬ እሁድ ሥራ ላይ ውሏል። ስምምነቱ ጋዛ ላይ ለዐስራ አምስት ወራት የቀጠለውን ጦርነት ለስድስት ሳምንታት በሚገታው የተኩስ አቁም ውል መሠረት የሃማስ ታጣቂዎች የያዟቸውን በርካታ ታጋቾች እንዲለቅቁ ይጠይቃል።

ዛሬ የተኩስ አቁም ስምምነቱ ተግባራዊ መሆኑን ተከትሎ በሰዓታት ውስጥ ሃማስ የመጀመሪያዎቹን ሦስት ወጣት ሴቶች የለቀቀ ሲሆን ቀይ መስቀል በአጀብ ወደ ጋዛ በመግባት የተለቀቁትን ታጋቾች ተረክቧል።

የእስራኤል ጠቅላይ ሚንስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ ሃማስ ዛሬ እሁድ ይለቃል የተባለውን ሦስት ታጋቾች ስም ዝርዝር ሳይሰጠን ስምምነቱ ተግባራዊ አይሆንም በማለታቸው ተግባራዊ የሆነው ከታቀደው ሰዓት በሦስት ሰዓት ገደማ ዘግይቶ ነው።

ኔታንያሁ በአገሩ ሰዓት ጠዋት ሁለት ተኩል ላይ ተግባራዊ እንዲሆን የታቀደው ተኩስ አቁም ሃማስ "እሰጣለሁ" ያለውን የሚለቀቁ ታጋቾች ስም ዝርዝር ሳይሰጥ ተግባራዊ እንዳይሆን ለመከላከያ ኃይሎች ትዕዛዝ ሰጥተዋል ሲል ከጠቅላይ ሚንስትሩ ጽህፈት ቤት የወጣው መግለጫ አስታውቋል።

ይህንኑ ተከትሎ ሃማስ ስም ዝርዝሩን ከሰጠ በኋላ እስራኤል ተኩስ አቁሙ አምስት ሰዓት ተኩል ላይ ተግባራዊ እንደሚሆን አስታውቃለች።

ሃማስ ስም ዝርዝሩ የዘገየው በቴክኒክ እክል ምክንያት እንደሆነ ጠቅሶ ስምምነቱን እንደማከብር በድጋሚ አረጋግጣለሁ ሲል መግለጫ አውጥቷል።

ይህ በዚህ እንዳለ አክራሪ ብሔርተኛው የእስራኤል የብሔራዊ ጸጥታ ሚንስትር ኢታማር ቤን ጋቪር የተኩስ አቁም ውሉን በመቃወም ሥራ መልቀቃቸው ተዘግቧል።

Nejashi Tv // ጄይሉ ቲቪ

19 Jan, 18:25


ሙስሊሙ ማህበረሰብ ተቋማቱን በማጠናከርና ሰላሙን በማስጠበቅ ሀገራዊ ሀላፊነቱን ሊወጣ እንደሚገባ የስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዘይኔ ቢልካ አሳሰቡ።

ነጃሺ ቲቪ ጥር 11/2017

ሙስሊሙ ማህበረሰብ ኢስላማዊ ተቋማትን ከማጠናከር ባለፈ የእርስ በርሱን ከሌሎች ጋር ያለውን ሰላም በማስጠበቅ በሀገር ልማት ላይ ያለውን ሚና አጠናክሮ እንዲያስቀጥል የስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዘይኔ ቢልካ ተናግረዋል።

የስልጤ ዞን እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ከስልጤ  ዞን ሙስሊም ወጣቶች ሊግ ጋር በመተባበር "ዲናችንን እንጠብቅ መጅሊስን እናጠንከር"  በሚል መሪ ሀሳብ በተዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዘይኔ ቢልካ የለውጡ መንግስት ሙስሊሙን የተቋም ባለቤት ከማድረግ አንጻር ሰፊ ስራ መስራቱን አንስተዋል።

የሙስሊሙ ተቋማት መጠናከር የሀገር ግንባታ አካል መሆኑን ያነሱት አቶ ዘይኔ ለተቋማቱ መጠናከር አስፈላጊው እገዛ ሲደረግ መቆየቱን ገልጸዋል።

ሰላም የሁሉም እምነቶች መሰረታዊ አስተምህሮ መሆኑንና የሀገርን ሰላም በማስጠበቅ በኩል ሙስሊሙ ማህበረሰብ እርስ በርሱና ከሌሎች እምነቶች ጋር በቅንጅት እንዲሰራም ዋና አስተዳዳሪው አሳስበዋል።

የስልጤ ዞን ሰላምና ጸጥታ መምሪያ ሀላፊው አቶ ከድር አብደላህ በበኩላቸው በዞን ደረጃ ከምንጊዜውም በተሻለ ኢስላማዊ አደረጃጀቶች መመስረታቸውን አንስተው የዞኑን ሰላም ከማስጠበቅ አንጻር ከአደረጃጀቶቹ ጋር እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

ሙስሊሙ ማህበረሰብ ኢስላማዊ አንድነቱን ማስጠበቅ ተቋማቱን ማጠናከርና በልማት እንቅስቃሴዎች ላይ አጋዥ ሃይል ሆኖ መቀጠል እንዳለበትም አቶ ከድር አሳስበዋል።

በመድረኩ ላይ ኢስላማዊ አንድነትን ስለማጠናከር፣ ኢስላማዊ እሴቶችን ስለማስጠበቅ፣ መጅሊስን ስለማጠናከር እንዲሁም አብሮነትና መቻቻል የሚያጎለብቱ ጽሁፎችና መርሃ ግብሮች ቀርበው ውይይት እየተደረገ ይገኛል። 

በመርሃ ግብሩ ላይ በፌዴራል መጅሊስ የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ሊግ ሀላፊ ኡስታዝ ሀይደር ከድር፣ የስልጤ ዞን እልስምና ጉዳዮች ምክር ቤት ሰብሳቢ ሸይኽ አብዱረሂም አህመዲን፣ የስልጤ ዞን ከፍተኛ ሸሪዓ ፍርድ ቤት ቃዲ ሸይኽ ሙስጠፋ ጀማል፣ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የኡለማ ጉባኤ ጸሃፊ ሸይኽ ሙሐመድ ሙስጠፋ እና ሌሎች የዞን የወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች ባለድርሻ አካላት ተሳታፊ ሆነዋል።

(ስልጤ ዞን ኮሙኒኬሽን)

Nejashi Tv // ጄይሉ ቲቪ

19 Jan, 17:39


እስራኤል ዞልፋካር በተሰኘ ተምዛግዛጊ ሚሳኤል ተመታች

ነጃሺ ቲቪ ጥር 11/2017

በኢራን የሚደገፈው የየመኑ ሃውቲ ታጣቂ ቡድን የሚያደርስባት ዙሪያ መለስ ጥቃት ያንገሸገሻት ኢስራኤል፣ አሁን ይባስ ብሎ የየመን መንገስት ጥቃት ስለባ ሆናለች እየተባለ ነው፡፡

በዚህም የየመን መንግስት ጦር በቴል አቪቭ ከባድ የባላስቲክ ሚሳኤል ጥቃት መፈጸሙ እየሩሳለምን ክው አድርጓታል፡፡

የየመን ጦር ሃይል ቃል አቀባይ ብርጋዴር ጄኔራል ያህያ ሳሬ እንደተናገሩት፣ የየመን ጦር የእስራኤል መንግስት መከላከያ ሚኒስቴር ግቢን፣ ዞልፋካር በተሰኘ ተምዛግዛጊ ሚሳኤል መምታቱን እስታውቀዋል፡፡

የየመን ጦር ሃይል ቃል አቀባይ ባወጣው መግለጫ እንዳመላከቱት፣ “በቴላቪቭ የሚገኘውን የእስራኤል መከላከያ ሚኒስቴር፣ በሚሳኤል ጥቃት ኢላማ አድርገናል” ብለዋል።

ኦፕሬሽኑ የተካሄደው 'ዞልፋካር' በተሰኘ ባላስቲክ ሚሳኤል ሲሆን፣ ጥቃቱ በጥንቃቄ የተፈጸመ እና ግቡን የመታ ትክክለኛ ድብደባ ነው ሲሉም አክለዋል፡፡

የጠላት መከላከያ ስርአቶች ሊመከቱት ያልቻሉትን፣ ከባድ ጥቃት ፈጽመናል ሲሉ ቃል አቀባዩ ፎክረዋል።

Nejashi Tv // ጄይሉ ቲቪ

19 Jan, 17:38


ሀማስና እስራኤል  ዛሬ የመጀመሪያው ምዕራፍ  የእስረኞች ልውውጥ አድርገዋል
ነጃሺ ቲቪ ጥር 11/2017

ከሃማስ ጋር በተደረገው የእስረኞች ልውውጥ ስምምነት መሰረት ቀይ መስቀል የመጀመሪያዎቹን ሶስት እስረኞች እንደተቀበለ የእስራኤል ጦር ይፋ አድርጓል

በሌላ በኩል ዜናውን የሚከታተሉ እስራኤላውያን ዘመዶቻቸውን አደባባይ ወጥተው በመጠባበቅ ላይ ይገኛሉ።

ስምምነቱን ምክንያት  በማድረግ በጋዛ የሰብአዊ እርዳታ ለፍልስጤማውያን  እየደረሰ ይገኛል

ተንቀሳቃሽ ምሥሉ ከማህበራዊ ትስስር ገጽ እና አልጀዚራ የተገኙ ናቸው።

Nejashi Tv // ጄይሉ ቲቪ

19 Jan, 16:28


በወንዶ ወረዳ "ጎቱ ኦኖማ" አካባቢ በተራሮች ላይ የሰደድ እሳት መነሳቱን የወረዳው ኮሚዩኒኬሽን አስታወቀ
ነጃሺ ቲቪ ጥር 11/2017

በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ አርሲ ዞን ወንዶ ወረዳ "ጎቱ ኦኖማ" በተባለው አከባቢ ከሰዓት 10 ሰዓት ላይ በተራሮች ላይ የሰደድ እሳት መነሳቱን የወረዳው ኮሚኒኬሽን ቢሮ አስታውቋል።

የሰደድ እሳቱ መከሰት መንስዔው በድርቅ ምክንያት የተከሰተ ስለመሆኑ ገልጿል።

ቢሮው የተከሰተውን ቃጠሎ በህብረተሰቡ ተሳትፎ ለማጥፋት እየተሞከረ ነው ሲልም አስታውቋል።

ሆኖሞ የተከሰተውን የእሳት አደጋ ተከትሎ በማኅበራዊ ሚዲያው በ 'እሳተ ገሞራ' የተከሰተ ነው በሚል የተሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ ነው ብሏል።

በተራሮቹ ላይ የተከሰተው ሰደድ እሳት ከመስፋፋቱ እና ከፍተኛ ችግር ከማስከተሉ በፊት ህብረተሰቡ እንዲሳተፍ እና አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርግም ቢሮው ባወጣው መግለጫ ጠይቋል።

Nejashi Tv // ጄይሉ ቲቪ

19 Jan, 09:54


ቲክቶክ በይፋ ከመዘጋቱ በፊት አሜሪካ ውስጥ አገልግሎት መስጠት አቆመ

ነጃሺ ቲቪ ጥር11/2017

ቲክቶክ እንዲዘጋ የሚያዘው ሕግ ተግባራዊ ከመደረጉ ከሰዓታት በፊት መተግበሪያው አሜሪካ ውስጥ አገልግሎት መስጠት ማቆሙ ታውቋል።

ተጠቃሚዎች ስልካቸውን ሲከፍቱ መተግበሪያው አሜሪካ ውስጥ ጥቅም ላይ እንዳይውል በመታገዱ ምክንያት "ለጊዜው ቲክቶክን መጠቀም አትችሉም" የሚል መልዕክት ያሳያል።

አክሎ "ፕሬዝደንት ትራምፕ ሥልጣን ሲይዙ ከእኛ ጋር በመሥራት ቲክቶክ ድጋሚ ክፍት እንዲሆን መጠቆማቸው ዕድለኛ ያደርገናል" ሲል ይነበባል።

ኩባንያው የፕሬዝደንት ዳይደን አስተዳደር ቲክቶክ እንደማይታገድ ማስረገጫ ካልሰጡ ከእሑድ ጀምሮ አገልግሎት መስጠት እንደሚያቆም አስጠንቅቆ ነበር።

ተመራጩ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ከዚህ ቀደም ሰኞ ሥልጣን ከያዙ በኋላ ለቲክቶክ የ90 ቀናት የእፎይታ ጊዜ እንደሚሰጡት ተናግረው ነበር።

ትራምፕ ቅዳሜ ኤንቢሲ ኒውስ ለተሰኘው ጣቢያ "የ90 ቀናት ማራዘሚያው መካሄዱ የሚቀር አይደለም፤ ምክንያቱም ትክክለኛው እምጃ ነው" ሲሉ ተናግረዋል።

"ይህን ለማድረግ ከወሰንሰኩ ሰኞ ዕለት የማደርገው ይሆናል።"

ዋይት ሐውስ በሰጠው መግለጫ የቲክቶክ ዕጣ ፈንታ በመጪው አስተዳደር እርምጃ ላይ የሚወሰን ነው ብሏል።

የአሜሪካ ጠቅላይ ፍርድ ቤት አርብ ዕለት ቲክቶክ ያቀረበውን ይግባኝ ውድቅ በማድረግ ባለፈው ሚያዚያ የፀደቀው ሕግ እንዲፀና ወስኗል።
ተጠቃሚዎች እንደሚሉት ቲክቶክ ከአፕል እና ጉግል መተግበሪያ ማውረጃ ቋቶች እንደተወገደ ተመልክተዋል።

በተጨማሪም መተግበሪያው ቪድዮ ማሳየት አቁሟል።

ባለፈው የአውሮፓውያኑ ዓመት ነው የአሜሪካ ሕግ አውጭዎች ቲክቶክ ከቻይና መንግሥት ጋር ግንኙነት ስላለው መታገድ አለበት ሲሉ አዋጅ ያፀደቁት።

Nejashi Tv // ጄይሉ ቲቪ

17 Jan, 11:20


ለመልካም ስነ ምግባር ብሔራዊ  ንቅናቄ  ትግበራ መሰረት የሚሆን ረቂቅ ሰነድ ላይ ውይይት ተደረገ

ነጃሺ ቲቪ

በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት  የትምህርትና ማሕበራዊ  አገልግሎት ዳሬክቶሬት  የሥነምግባር ጥናት ብድን ያዘጋጀው ረቂቅ ሰነድ ላይ ውይይት ተደረገ።

የስነ ምግባር ጥናት ቡድኑ ያዘጋጀው ረቀቅ ሰነድ  በሀገር አቀፍ ደረጃ በመልካም ስነ ምግባር (አኽላቅ) ዙሪያ ብሔራዊ ንቅናቄ ለመፍጠር ጠንካራ መነሻ ሊሆን እንደሚችል ተገልጿል።

በውይይት የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት በዳይሬክቶሬቱ የማኀበራዊው ዘርፉ ሀላፊ ዶክተር ተውፊቅ ቢራራ ጠቅላይ ምክር ቤቱ እንደ መሪ ሃይማኖታዊ ተቋምነቱ የስነ ምግባር ጉዳይ ቅድሚያ ትኩረቱ መሆኑን ገልፀው በኃላፊነት የሚመሩት ዘርፍ የስነ ምግባር እሴቶች የሚሻሻሉበትን ሁኔታ የሚያሳይ ረቂቅ ሰነድ እንዲዘጋጅ ማድረጉን ጠቅሰዋል።

በጥናት ረቂቅ ሰነዱ ላይ ማብራሪያ ያቀረቡት ዑስታዝ አህመድ ሙስጠፋ ጥናቱ ኢስላማዊ አስተምህሮዎችን መሰረት ያደረገ መሆኑን አንስተዋል። ረቂቅ የጥናት ሰነዱ ዳብሮ ወደ ትግበራ ሲገባም ብልሹ ስነምግባርን በማስተካከል መልካም ስነምግባራዊ እሴት የተላበሰ ማኀበረሰብ ለመገንባት እንደሚያግዝም ኡስታዙ አክለዋል።

ጥናትና ምርምር እንዲሁም የስረዓተ ትምህርት (ካሪኩለም) ዝግጅት ከማስፈፀሚያ ስልቶች ዋናዎቹ  እንደሆኑም ተነስቷል።

የስነ ምግባር ጥናት ቡድኑ የአኽላቅ ብሔራዊ ንቅናቄ  የተሻለ መነቃቃት እንዲፈጥርና ተልዕኮው ከፍ ያለ ትውልድ ለማፍራት በጠቅላይ ምክር ቤቱ እውቅና የሚቋቋመው የአኽላቅ ግብረ ኃይል ከዑለማ ጉባኤ ጽፈት ቤት ጋር በመቀናጀት የሚሰራበት አቅጣጫ እንዳለም ተመላክቷል።

የውይይቱ ተሳታፊዎች ለጥናቱ ግብዓት የሚሆኑ ሀሳቦችን እና ተጨማሪ ማብራሪያ የሚያስፈልጋቸውን ጥያቄዎች አንስተው ማብራሪያ ተሰጥቷቸዋል።

በመጨረሻም የተሻለ ስነ ምግባር የተላበሰ  ማኅበረሰብ ለመፍጠር ጥናቱ እንዲተገበር ሁሉም የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ አቅጣጫ ተሰጥቷል።

መረጃው የኢ.እ.ጉ.ጠ. ም/ቤት ነው

Nejashi Tv // ጄይሉ ቲቪ

17 Jan, 08:29


አሜሪካ በ ሱዳን የጦር አዛዥ አአል ቡርሃን ላይ ማዕቀብ ጣለች
ነጃሺ ቲቪ ጁማዓ ጥር 9/2017

አሜሪካ የሱዳን የጦር አዛዥ ጄኔራል አብዱል ፈታህ አል ቡርሃንን በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች የተገደሉበትንና በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎች የተፈናቀሉበትን የእርስ በእርስ ጦርነት በማባባስ ከሳለች። የአሜሪካ ግምዣ ቤት፤ የቡርሃን አመራር የሲቪል መሰረተ ልማትን ጨምሮ በትምህርት ቤቶች፣ በገበያዎች እና በሆስፒታሎች ላይ ጥቃቶች መፈጸማቸውን እንዲሁም ያለፍርድ ቤት ትዕዛዝ ግድያ መፈጸማቸውን ገልጿል።

በዚህም ትናልንት በአልቡርሃን ላይ ማዕቀብ የተጣለ ሲሆን ይህም የሱዳኑ ፈጥኖ ደራሽ ኃይል አዛዥ በሆኑት ሞሐመድ ሀምዳን ዳጋሎ ላይ ተመሳሳይ እርምጃ ከተወሰደ ከአንድ ሳምንት በኋላ ነው።

"የቡርሃን አመራር ሰራዊት ከድርድር ይልቅ ጦርነትን መርጧል" ያለው የአሜሪካ ግምጃ ቤት፤ እርምጃው ከቡርሃን ጋር የተያያዙ የአሜሪካን ንብረቶች በሙሉ እንደሚያግድ እና አሜሪካውያን ከእሳቸው ወይም ከተዛመጅ አካላት ጋር እንዳይገናኙ የሚከለክል መሆኑንም አክሎ ገልጿል።

በተጨማሪም  ዋሽንግተን የሱዳን-ዩክሬን ዜግነት ያላቸውን እና በሆንግ ኮንግ የሚገኘውን ኩባንያ ጨምሮ የጦር መሳሪያ አቅራቢዎችን ለሱዳን ጦር መሳሪያ በሚያቀርቡ አካላት ላይም ትኩረት አድርጋለች።

የቡርሃን በአልጀዚራ በተላለፈው ንግግራቸው “እቺን ሀገር ለማገልገል ማንኛውንም ማዕቀብ  እንቀበላለን" ሲሉ ተደምጠዋል። የሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በበኩሉ የአሜሪካን እርምጃ "ግራ የሚያጋባ እና ደካማ የፍትህ ስሜት" ሲል ተችቷል።

   

Nejashi Tv // ጄይሉ ቲቪ

17 Jan, 07:54


እስራኤል መስማማቷን ገለጸች

ጄይሉ ቲቪእስራኤል ታጋቾችን የማስለቀቅ ውል ላይ መስማማቷን የኔታንያሁ ቢሮ አስታወቀ

ነጃሺ ቲቪ ጁማዓ ጥር 9/2017
ታጋቾችን ለማስለቀቅ ከሐማስ ጋር ስምምነት ላይ መደረሱን የጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታንያሁ ቢሮ አስታወቀ።

ኔታንያሁ ሐሙስ ዕለት ድምጽ እንደሚሰጥበት ሲጠበቅ የነበረውን የጋዛን የተኩስ አቁም ስምምነት 'ሐማስ በመጨረሻ ሰዓት ሃሳቡን ለመለወጥ እየፈለገ ነው' በማለት ስምምነቱን ለማፅደቅ የሚሰጠውን የምክር ቤት ድምፅ እንዲዘገይ አድርገው ነበር።

ሆኖም አርብ ጥዋት፣ ጥር 9/ 2017 ዓ.ም ተደራዳሪው ቡድን ስምምነት ላይ መደረሱን ለኔታንያሁ እንዳሳወቃቸው የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቢሮ ገልጿል።

ይህንንም ተከትሎ ኔታንያሁ የፖለቲካ እና የፀጥታ አባላት ያሉበት ምክር ቤት አርብ እንዲሰበሰቡ ትዕዛዝ የሰጡ ሲሆን በዚያም ስምምነቱ እንደሚያፀድቅ የኔታንያሁ ቢሮ አስታውቋል።

የታጋቾች ቤተሰቦችም ከሐማስ ጋር ስምምነት ላይ መደረሱ እንደተነገራቸው ቢሮው ጨምሮ ገልጿል።

በዶሃ የተገኙት የእስራኤል ፣ የሐማስ፣ የአሜሪካ እና የኳታር ተወካዮችም ስምምነቱ ላይ መፈረማቸውን የእስራኤል መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።


የተኩስ አቁም ስምምነቱ በአሜሪካ እና በኳታር አሸማጋዮች መጀመሪያ ላይ የተገለጸው ረቡዕ ዕለት ነበር።


ሐማስ በበኩሉ ለስምምነቱ ቁርጠኛ መሆኑን የገለጸ ሲሆን በስምምነቱ መሠረት በእስራኤል የሚፈቱ ፍልስጤማውያን ዝርዝር ውስጥ የተወሰኑ አባላቱን ማካተቱን ቢቢሲ ተረድቷል።


ምንም እንኳን የእስራኤል ተደራዳሪዎች ለወራት ሲካሄድ በነበረው ስምምነት ቢስማሙም በእስራኤል ምክር ቤት ካልጸደቀ ተግባራዊ ሊሆን አይችልም።

Nejashi Tv // ጄይሉ ቲቪ

11 Jan, 10:08


ሴኩላሪዝም በኢትዮጵያ

ጄይሉ ቲቪሴኩላሪዝም እና  የሀይማኖት ነፃነት በሚል ውይይት ተካሄደ

     ኢማን ኢስላሚክ አሶሲየሽን ዛሬ ቅዳሜ 3/05/2017ለግማሽ ቀን የዋለ የምርምር አውደ ጥናት አከናውኖል ።  ካፒታል ሆቴል በተዘጋጀው የምርምር አውደ ጥናት ላይ መንግስታዊ  አካላት የመጅሊሱ አመራሮች በተለያየ ዘርፍ የሚገኙ ምሑራን እና ባለድርሻ አካላት ተሳታፊ ሆነዋል።

       ኢማን  ኢስላሚክ አሶሴሽን  በተለያዩ ዘርፍ የራሱ የሆኑ አሻራዎችን ያሉት ሲሆን በተለይ ደግሞ በሰላም ግንባታ ዘርፍም የራሱ የሆነ ጉልህ ሚና እያሰፈረ ይገኛል:: ማህበሩ ከ2021 ጀምሮ ግጭት አፈታት እና የሰላም ግንባታ የሀይማኖትና የእምነት ነፃነትን መሰረት ባደረገው የጋራ ትብብርና ተነሳሽነት በሀይማኖቶች ውስጥ በሀይማኖቶች መካከል ከሀይማኖቶች ውጪ ካሉ ባለድርሻ አካላት ጋር ሰላማዊ መስተጋብር በመገንባት ግጭቶችን ለመፍታት ሀገራዊ ሰላም ለማሳካት ታቅዶ በኢትዮጵያ 11 ከተለያዩ ቤተ እምነቶች የተወጣጡ ማህበራት ከሰላም ሚኒስተር ጋር በትብብር የሚከናወኑ ፕሮጀክቶች አካል በመሆ ንየተለያዩ መርሀግብሮችን ሲያከናውን ቆይቷል::


  ማህበሩ የፕሮጀክቱ አካል የሆነውን ጥናትና ምርምር ለ1 አመት Islamic research and cultural center (ircc)በተባለ ተቆም ሲያስጠና ቆይቶል የጥናቱ ስያሜ "ሴኩላሪዝም እና  የሀይማኖት ነፃነት በኢትዮጵያ የትምህርት ስርአት መስተጋብር  ተግዳሮቶች እና ተስፍዎች ሲሆን የጥናቱ ውጤት የሚመለከታቸው አካላት ተገኝተው ለቀረቡት ጥናታዊ ፁሁፎች እና ማብራሪያዎች የተለያዩ ጥያቄዎች  አንስተውም በቀረበው ምርምር ዙሪያ ሀሳብ አስተያየት አቅርበዋል

Nejashi Tv // ጄይሉ ቲቪ

11 Jan, 09:25


በኬኒያ አውሮፕላን ተከስክሶ የ3 ሰዎች ሕይዎት አለፈ
ነጃሺ ቲቪ ጥር 3/2017

በኬኒያ ማሊንዲ አውሮፕላን ማረፊያ አቅራቢያ በምትገኘው ክዋቾቻ ከተማ በደረሰ የአነስተኛ አውሮፕላን አደጋ የሦስት ሰዎች ሕይዎት ማለፉ ተሰምቷል፡፡

የዐይን እማኞች አውሮፕላኑ በአካባቢው የነበሩ ሰዎችን መምታቱንና ከዚያም በእሳት መያያዙን ገልጸዋል፡፡

ሁለት ሰዎች በአውሮፕላኑ ስብርባሪዎች ተመትተው ወዲያውኑ ሕይዎታቸው ሲያልፍ፥ አንዱ በእሳት ከባድ ጉዳት ከደረሰበት በኋላ መሞቱን የአካባቢውን ባለስልጣናት ዋቢ አድርጎ አፍሪካ ኒውስ ዘግቧል፡፡

በሌላ በኩል በአውሮፕላኑ ውስጥ የነበሩ አንድ ፓይለት እና ሁለት ተማሪዎች አደጋው ከመድረሱ በፊት መውጣታቸውን እና አሁን ላይ የሕክምና ክትትል እየተደረገላቸው መሆኑን የዘገበው ደግሞ አሶሺየትድ ፕሬስ ነው፡፡

ሰሞኑን በተለያዩ የዓለም ሀገራት በተደጋጋሚ እየተከሰተ ያለው የአውሮፕላን አደጋ የአቪየሽን ዘርፉን እየፈተነው ነው ተብሏል፡፡

Nejashi Tv // ጄይሉ ቲቪ

10 Jan, 09:35


የኢትዮጵያ የስፔስ ሳይንስ ሶሳይቲ በኢትዮጵያ ወደ ምድር ሲንቀሳቀሱ የታዩት የቁስ አካላት ስብስብ የጠፈር ፍርስራሾች አልያም የሚቲዮር አለቶች ሊሆኑ እንደሚችሉ አስታወቀ!

የኢትዮጵያ የስፔስ ሳይንስ ሶሳይቲ በትናንትናው ዕለት ከምሽቱ 1፡30 ገደማ በደቡብና ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክፍሎች በሰማይ ላይ እየተቀጣጠሉ በከፍተኛ ፍጥነት ሲንቀሳቀሱ የታዩት የቁስ አካላት ስብስብ የጠፈር ፍርስራሾች አልያም የሚቲዮር አለቶች ሊሆኑ እንደሚችሉ አስታውቋል።የታየው ስብስብ ወደ ደቡባዊ የሃገሪቱ አቅጣጫ በከፍተኛ ፍጥነት በሰማይ ላይ ሲምዘገዘግ እንደነበረም ለማወቅ ተችሏል ሲል ተቋሙ ገልጿል።

የእነዚህ አካላት ስብስብ  ክስተት ተፈጥሮ በእርግጠኝነት ለማብራራት ያስችል ዘንድ ሁኔታውን በቅርበት እያጣራ እንደሚገኝም አክሎ አስታውቋል።በቅርቡ በኬንያ በማኩኒ ካውንቲ ሙኩኩ በተባለችው መንደር ክብ ቁስ 2 ነጥብ 5 ሜትር ስፋት ያለው ሲሆን 500 ኪሎግራም ክብደት ያለው ግዙፍ ብረት ከሰማይ መወደቁ ይታወቃል።

Nejashi Tv // ጄይሉ ቲቪ

10 Jan, 09:33


የእስራኤል አዲሱ ካርታ ተቃውሞ አስነሳ

ጄይሉ ቲቪእስራኤል  ያሳተመችው አዲሱ የአረብ ግዛቶችን ያጠቃለለው ካርታ ተቃውሞ  ገጠመው
ነጃሺ ቲቪ


እስራኤል የአለም አቀፍ ህጎችን በመጣስ  በአረብ ሀገሮች ላይ የምታደርገው መስፋፋት ሊቆም ይገባል ተባለ
በቅርቡ ይፋ የተደረገው አዲሱ የእስራኤል ካርታ ሉአላዊነትን የሚጋፋና በአካባቢው ያለውን  የሰላም ዕድል ሊያደናቅፍ  እንደሚችል የባህረ ሰላጤው  ሀገራት ስጋታቸውን  ገልፀዋል።

የእስራኤል መንግስት ፍልስጤምን፣ ዮርዳኖስን፣ ሊባኖስን እንዲሁም ሶሪያን የእስራኤል አካል አድርጎ የሚገልጽ ካርታ መታተም
ሳውዲ አረቢያ የተባበሩት  አረብ ኢምሬትስ ኳታርን ጨምሮ የባህረሰላጤው ሀገራትን አሰቆጥቷል

እስራኤል ይፋ ያደረገችው አዲሱ ካርታ የፍልስጤም የዮርዳኖስ የሊባኖስ እና የሶሪያን   ሰፊ ይዞታዎች በእስራኤል ግዛት ውስጥ ተጠቃለው እንደሚገኙ ጠቅሷል


የኳታር የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እስራኤል ይፋ ያደረገችው አዲሱ ካርታ  "የዓለም አቀፍ ህጎችንና ውሳኔዎችን  በግልፅ ይጣረሳል ሲሉ ተቃውመዋል

እስራኤል በአረብ አገሮች ያላትን የመስፋፋት ምኞት እንድታቆም ግፊት እንዲደረግ   የኳታር የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ጥሪ አቅርበዋል


የኳታር የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በኤክስ ገፃቸው ላይ ባወጡት መግለጫ "በእስራኤል ይፋ የተደረጉ ካርታዎች መታተም በአካባቢው ያለውን የሰላም እድል ሊያደናቅፋ እንደሚችሉ አስጠንቅቀዋል።

በሌላ በኩል
የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መግለጫ  በበኩሉ የእስራኤልን እርምጃ “ወረራውን ለማስፋት ሆን ተብሎ የተደረገ ጥረት እና የአለም አቀፍ ህግን በግልጽ የጣሰ ተግባር ነው ሲል ገልጿል

በአዲሱ ካርታ  የተጠቃለሉት ግዛቶች   የአለም አቀፍ ህጎችን የሚቃረን በመሆኑ የ እስራኤል ግጭት ቀስቃሽ ድርጊቶችን በሙሉ ውድቅ እንደሚያደርግ የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ   አሰታውቋል።በቀጠናው ሰላምና መረጋጋትን ለማስፈን ለተጀመሩ ጥረቶች እንቅፋት ይፈጥራል ሲሉም አስጠንቅቀዋል ።

በተጨማሪም የዮርዳኖስ መንግስት "ታሪካዊቷ እስራኤል" በሚል የጎረቤት ግዛቶችን በሚያጠቃልለው ይፋዊ ማህበራዊ ሚዲያ ላይ የታተሙትን ካርታዎች አውግዟል።

የዮርዳኖስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ሱፊያን ኩዳህ “እነዚህ ጸብ ቀስቃሽ ድርጊቶች እና መሠረተ ቢስ የይገባኛል ጥያቄዎች በእስራኤል መንግሥት ውስጥ ባሉ ጽንፈኞች የሚበረታቱ ሁከትና አለመረጋጋትን የሚያስቀጥሉ ናቸዉ” ብለዋል።
ሳውዲ በበኩሏ እስራኤል ግዛቶቿን ለማጠናከር ስትል  በሀገሮች  ላይ የሉአላዊነት ጥሰት ፈፅማለች ስትል አውግዛ ካርታውንም ውድቅ አድርጋለች
እስራኤል በቀጠናው ሀገራት እና ህዝቦች  ላይ የምትፈፅመውን የህግ ጥሰት ለማስቆም አለም አቀፋ ማህበረሰብ ሀላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪዋን አሰተላልፋለች

Nejashi Tv // ጄይሉ ቲቪ

08 Jan, 17:27


አዲስ አበባ የሚገኙ ዲፕሎማቶች ለመንግሥት ሳያሳውቁ ከከተማ እንዳይወጡ ደብዳቤ ተላከላቸው

ነጃሺ ቲቪ ታህሳስ 30/2017
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መቀመጫውቸን በአዲስ አበባ ላደረጉ ዲፕሎማቶች ለመንግሥት ሳያሳውቁ ከከተማ እንዳይወጡ ማሳሰቢያ ሰጠ፡፡

ሪፖርተር የተመለከተውና ከአንድ ሳምንት በፊት በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በኩል ለዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ የተላከው ደብዳቤ እንደሚያስረዳው፣ ዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ ድርጅቶች በአገሪቱ ድንበር ውስጥ ለሚያደርጓቸው ማናቸው እንቅስቃሴዎች ቅድመ ፈቃድ እንዲጠይቁ አሳስቧል፡፡

በአዲስ አበባ ለሚገኙ ዓለም አቀፍና ቀጣናዊ ተቋማት፣ ዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ ድርጅቶችና መንግሥታዊ ያልሆኑ ዓለም አቀፍ ተቋማት፣ ከአዲስ አበባ ውጭ የሚያደርጓቸውን ጉዞዎች በተመለከተ በሚኒስቴር መሥሪያ ቤት በተቀመጠ የቅድሚያ ማሳወቂያ ፎርም ከሞሉ በኋላ መሆን እንዳለበት አመላክቷል፡፡

ይሁን እንጂ ለዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ የተጻፈው ደብዳቤ ማስጠንቀቂያው ለሥራ ወይም ለግል ጉዳይ የሚጓዙትን እንደሆነ በግልጽ አያስረዳም፡፡

ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ እንደሚያስረዳው ከዚህ ተመሳሳይ ድበዳቤ ተጽፎ የነበረ ቢሆንም ፣ አንዳንድ ዲፕሎማቶች አሁንም ከፌዴራል መንግሥቱ ዕውቅና ውጭ ሲንቀሳቀሱ በመገኘቱ እንደሆነ ተገልጿል፡፡

ከዓመት በፊት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሪፖርቱን ባቀረበበት ወቅት፣ ክልሎች በአገሪቱ ሕገ መንግሥት ለፌዴራል መንግሥቱ ብቻ በተሰጠው የውጭ ግንኙነት ሥራ ላይ እየተሳተፉ በመሆኑ ፓርላማው ማሳሰቢያ እንዲሰጥ ተጠይቆ ነበር፡፡

Nejashi Tv // ጄይሉ ቲቪ

07 Jan, 16:15


የድምፃችን ይሰማ ባለውለታ ስጦታ ተበረከተላቸው

በኢትዮጵያ ሰላማዊ የመብት ትግል ውስጥ ጉልህ ሚና ለነበራቸው አንጋፋው የታሪክ ባለሙያ የመኪና ስጦታ ተበረከተ
ነጃሺ ቲቪ ታህሳስ 29/2017

ረጅሙን የእድሜያቸውን ክፍል በታሪክ አጥኚነት ላሳለፉት ሼይኽ አደም ካሚል (ረ/ፕሮፌሰር) በዛሬው እለት በየሲር ለና የበጎ አድራጎት ድርጅት በተካሄደው መርሐ ግብር ላይ ለታሪክ አጥኚው ሥጦታ የተበረከተው ለማኅበረሰብ ላበረከቱት አስተዋጽኦ መሆኑ ተገልጿል፡፡ሥጦታውን ያበረከቱት አካላት ሥማቸው አልተገለጸም ተብሏል፡፡

በሰሜን ወሎ ዞን ገፍራ ወርሳ ሜንሳ ተብሎ በሚጠራ ቦታ በ1948 ገደማ የተወለዱት ሼንህ አደም ካሚል (ረ/ፕሮፌሰር)፤ በአሁኑ ሰዓት ዕድሜያቸው 69 ደርሷል፡፡

ሼይኽ አደም ካሚል በኢትዮጵያ ከቀሰሙት የእስልምና ትምሕርት በኋላ የከፍተኛ ትምሕርታቸውን በቀዳሚነት የተከታተሉት በሳዑዲ ዐረቢያ ኪንግ ሮያል ዩኒቨርሲቲ ነው።

ሼይኽ አደም ካሚል በኢትዮጵያ ሙስሊሞ ሰላማዊ የመብት ትግል ውስጥ ጉልህ ሥፍራ በሚሰጠው የ“ድምጻችን ይሰማ” እንቅስቃሴ ውስጥ በሙስሊም መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ ውስጥ ከነበሩ 17 ግለሰቦች ውስጥ አንደኛው አባል ነበሩ፡፡ ከመጻሕፍት ዝግጅት፣ ከጥናታዊ ጽሑፎች፣ ከአደባባይ ንግግሮች ውጪ የመጽሔት አዘጋጅ ሆነው ሠርተዋል፡፡

ባለፉት በርካታ ዐስርት ዓመታት በተለይ የኢትዮጵያ ሙስሊሞችን የተመለከቱ ጉዳዮችን የሚዳስሱ መጻሕፍትን ማበርከትም ችለዋል፡፡ ለኅትመት ከበቁት መካከል “ኢትዮጵያ መካከለኛው ምሥራቅ እና ነጃሺ”፣ “እስልምና እና ዓለማችን”፣ “ሀበሾች እና የሀበሻ ክብር በእስልምና”፣ “ሀበሾች በነቢዩ (ሰ.ዓ.ወ) ዙርያ”፣ የሀበሾች አሻራ በእስልምና እንዲሁም ቱሪዝም እና ኢንቨስትመንትን የተመለከቱት ተጠቃሽ ናቸው፡፡

Nejashi Tv // ጄይሉ ቲቪ

07 Jan, 16:11


በነዳጅ ዋጋ ላይ ጭማሪ ተደረገ

ጄይሉ ቲቪበአዲስ አበባ ከተማ ተግባራዊ የሚሆን  የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ጭማሪ ተደረገ


ነጃሺ ቲቪ 29/2017

የሚኒስትሮች ም/ቤት ታህሳስ 20 ቀን 2014 ዓ.ም ባደረገው መደበኛ ስብሰባ ባስተላለፈው የነዳጅ ውጤቶች የዋጋ ግንባታ የአፈጻጸም ውሳኔ መሠረት፤

ከታኅሣሥ 29/2017 ዓ.ም ከምሽቱ 12፡00 ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ ተግባራዊ የሚሆነው የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ እንደሚከተለዉ እንዲሸጥ በመንግስት መወሰኑ ተገለጿል።                        

በዚህም መሰረት  በአዲስ አበባ የችርቻሮ የመሽጫ ዋጋ

ቤንዚን  በ101.47 ብር/ሊትር

ናፍጣ   በ98.98 ብር/ሊትር

ኬሮሲን  በ98.98 ብር/ሊትር

የአውሮፕላን ነዳጅ በ109.56 ብር/ሊትር

የከባድ ጥቁር ናፍጣ  በ105.97 ብር/ሊትር

የቀላል ጥቁር ናፍጣ   በ108.30 ብር/ሊትር በመሆን ከዛሬ ታህሳስ 29/2017 ዓ/ም ጀምሮ በአዲስ አበባ እንዲሸጥ ተወስኗል።

Nejashi Tv // ጄይሉ ቲቪ

06 Jan, 11:20


ሶሪያ ማዕቀብ ይነሳልኝ አለች

ጄይሉ ቲቪየሶሪያ ሚኒስትሮች የአሜሪካ ማዕቀብ እንዲነሳ ጠየቁ
ነጃሺ ቲቪ ታህሳስ 28/2017

የሶሪያ የሽግግር መንግስት ሚኒስትሮች ፕሬዝዳንት በሽር አል አሳድን ከስልጣን ካነሱ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በኳታር ባደረጉት ጉብኝት ዩናይትድ ስቴትስ በደማስቆ ላይ የጣለችውን ማዕቀብ እንድታነሳ አሳስበዋል፡፡

የኳታር ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ የባህረ ሰላጤው ሀገራት ጠቅላይ ሚኒስትሮች ከሶሪያ ጊዜያዊ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሳድ አል-ሻይባኒ፣ የመከላከያ ሚኒስትር ሙርሃፍ አቡ ቃስራ እና ከአዲሱ የስለላ ሃላፊ አናስ ኻታብ ጋር መነጋገራቸውን አስታውቋል።

ኳታር እንደሌሎች አረብ ሀገራት ሶርያ በአሳድ አስተዳደር ስር እያለች የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቷን ወደነበረበት አልመለሰችም።

ከኳታር የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር መሐመድ ቢን አብዱላዚዝ አልኩላይፊ ጋር ያደረጉትን ውይይት ተከትሎ የሶሪያ ጊዜያዊ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሳድ አል-ሻይባኒ አሜሪካ በሶሪያ ላይ የጣለችው ማዕቀብ እንዲነሳ በድጋሚ ጥሪ አቅርበዋል።

ጊዜያዊ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ እርምጃዎቹን ለሃገራቸው ፈጣን ማገገም እንቅፋት ነው ሲሉ መንግስታቸው “ዩናይትድ ስቴትስ እነዚህን ማዕቀቦች እንድታነሳ በድጋሜ ይጠይቃል” ሲሉ ለሃገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ተናግረዋል።

በታህሳስ ወር መጨረሻ ላይ ኳታር በሶሪያ ላይ የተጣለውን ማዕቀብ በፍጥነት እንዲነሳላት ጥሪ አቅርባ እንደነበረም ዘገባው አስታውሷል፡

ጄይሉ ቲቪ // Jeilu Tv

08 Dec, 19:19


ሐላል ኬተሪንግ ተመረቀ!

በአምባሳደር ሞል በተዘጋጀው በዚህ ልዩ የምረቃ መርሃ ግብር ላይ ጥሪ የተደረገላቸው የክብር እንግዶች፣ የሃይማኖት አባቶች እንዲሁም የንግዱ ማህበረሰብ አባላት ተገኝተዋል፡፡

የሀላል ቱሪዝም እንዲያድግ የበኩላቸውን እየተወጡ እንደሚገኙ የገለጹት አዘጋጆቹ ሌሎች የክብር እንግዶችም ንግግር አድርገዋል፡፡

በፕሮግራሙ ላይ አንጋፋው ጋዜጠኛ ጀማል አህመድ ንግግር አድርጎ ለፕሮግራሙ መሳካት የበኩላቸውን የተወጡ ባለድርሻ አካላትን ሸልሞ የሀላል ኬተሪንግን መርቆ ከፍቷል።

(ቢላል ቲቪ)

ጄይሉ ቲቪ // Jeilu Tv

08 Dec, 19:06


ፖሊስ በአዲስ አበባ የተለያየ አካባቢ ለተሰማው የተኩስ ድምጽ መግለጫ አወጣ

ጄይሉ ቲቪዛሬ በአዲስ አበባ አንዳንድ አካባቢዎች የተሰማውን ተኩስ አስመልክቶ የአዲስ አበባ ፖሊስ መግለጫ አውጥቷል።

የመግለጫው ሙሉ ቃል ከዚህ እንደሚከተለው ቀርቧል :-

በአዲስ አበባ ከተማ በተለያዩ አከባቢዎች የተሰማው የጦር መሣሪያ ድምፅ የመንግስትን የሰላም ጥሪ ተቀብለው ወደ ተሃድሶ ሥልጠና ማዕከላት በሚጓዙ የቀድሞ የኦነግ ታጣቂ ቡድን አባላት የተሰማ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ያስታውቃል።


መንግሥት በሀገሪቱ የተለያዩ አከባቢዎች ታጥቀው ለሚንቀሳቀሱ ቡድኖች ባቀረበው የሠላም ጥሪ መሠረት የኦነግ ታጣቂ ኃይል አባላት የሰላም ጥሪውን ተቀብለው በስፋት እየገቡ መሆኑ ይታወቃል።

የታጣቂ ቡድኑ አባላትን ወደ ተዘጋጀላቸው የተሃድሶ ስልጠና ማዕከላት የማጓጓዝ ስራ በስኬት እየተከናወነ ይገኛል። በዚህ መሀል ታጣቂዎቹ አዲስ አበባ ከተማን አቋርጠው ወደ ስልጠና ማዕከላት በሚንቀሳቀሱበት ወቅት እየጨፈሩና የደስታ ስሜት እያሰሙ ሲንቀሳቀሱ የተኩስ ድምጽ በማሰማታቸው በከተማው ነዋሪ ህዝብ ላይ ድንጋጤና መረበሽ ሊፈጠር ችሏል።

ለተፈጠረው የዜጎች ድንጋጤና መረበሽ ይቅርታ እየጠየቅን በቀጣይ ተመሳሳይ ችግሮች እንዳይፈጠሩ ከፍተኛ ጥንቃቄና የማስተካከያ እርምጃ የሚወሰድ መሆኑን ለመግለጽ እንወዳለን።

አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን
ህዳር 29 ቀን 2017 ዓ.ም

ጄይሉ ቲቪ // Jeilu Tv

08 Dec, 18:36


2ኛውን አለም አቀፍ የቁርአንና የአዛን ውድድር ዝግጅት በሙያቸውና በተለያየ አገልግሎት ለመደገፍ እየተመዘገቡ መሆኑ ተገለጸ ።

ጄይሉ ቲቪ 29/03/2017
ጥር 25 ቀን 2017 በድምቀት በአዲስ አበባ ስተዲየም እንደሚካሄድ የሚጠበቀው 2ኛው አለም አቀፍ የቁርአንና የአዛን ውድድርን በሙያቸው አገልግሎት ለመስጠት ፍላጎት ያላቸው ወጣቶችና የበጎ አድራጎት ማህበራት እየተመዘገቡ መሆኑን አዘጋጁ ዘይድ እብን ሳቢት አስታውቋል ።

በውድድሩ ለሚሳተፉ የውጭ እና የሀገር ውስጥ ተወዳዳሪዎች እንዲሁም ተመልካቾች በማስተናገድ ፣ የጤና ድጋፍ በማድረግ ፣ በአስተርጓሚነትና በሌሎችም መስኮች አገልግሎት በመስጠት አለም አቀፍ ውድድሩን ለመደገፍ ቢሮ ድረስ በመምጣት እየተመዘገቡ መሆኑን አስረድተዋል ።

ጄይሉ ቲቪ // Jeilu Tv

08 Dec, 04:17


በሽር አላሳድ ሶሪያን ጥለው ጠፉ

ጄይሉ ቲቪየሶሪያ መሪ በሽር አላሳድ አማጺያኑ የሀገሪቱን ከተሞች በመቆጣጠራቸው ለሊቱን በአውሮፕላን ሀገሪቱን ለቀው መሸሻቸውን ዘገባዎች አመልክተዋል።

ለ50 አመታት የቆየው የበሽር አልአሳድ መንግስት እንዳበቃለትና አመጻያኑ ኡመያድ አደባባይ ገብተው በደስታ ሲጨፍሩ ማደራቸው ተዘግቧል።
የአሳድ ሠራዊት አመጻኒያኑ ወደ ከተማ ሲገቡ ለመፋለም ምንም አይነት ሙከራ አለማድረጋቸውን የሬውተርስ ዘገባ ያመለክታል ።
@jeilutv

ጄይሉ ቲቪ // Jeilu Tv

02 Dec, 18:19


ሐጂ ሙስጠፋ አወል "የገራድነት " ማዕረግ ተሰጣቸው

ጄይሉ ቲቪየሀገራቸውንንና የህዝባቸው በመደገፍ የሚታወቁት ሐጂ ሙስጠፋ አወል ለታላቅ ባለውለታዎች የሚሰጥ የክብር ማዕረግ ስም ተሰጣቸው ።

የሙለጌ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር መስራችና ባለቤት የሆኑት ሐጂ መስጠፋ አወል በተለይ ለስልጤ ህዝብ የልማት ስራዎች ላደረጉት እጅግ የላቀ አስተዋጽኦ "ገራድ " በሚል የክብር የማዕረግ ስያሜ እንዲጠሩ የሀገር ሽማግሌዎች ፣ የሃይማኖት አባቶች ፣ ከፍተኛ የመንግስት ኃላፊዎች በተገኙበት በይፋ  እውቅና ተስጥቷቸዋል ።

ገራድ ሐጂ ሙስጠፋ አወል በስልጤ ዞን ትምህርት ቤቶችን በመገንባት ፣ የትምህርት ግብአቶችን በማሟላት ፣ ከፍተኛ ውጤት ለሚያስመዘግቡ ተማሪዎች ማበረታቻ ሽልማት በመስጠት ፣ በዞኑ የመንገድ ልማት እንዲስፋፋ ፣ ለሆስፒታል ግንባታዎች እና ለስልጤ ልማት ማህበር ልዩ ልዩ ፕሮጅክቶች ድጋፍ በማድረግ ይታወቃሉ ።

ገራድ ሐጂ ሙስጠፋ አወል በስልጤ ዞን የሚከናወኑ ልማቶችን ከመደገፍ ጎን ለጎን ለሀገሪቱ ልዩ ልዩ የድጋፍ ጥሪዎች ግንባር ቀደም በመሆን እንዲሁን ባደጉባት ወላይታ የተለያዩ ልማቶችን በመደገፍ የሀገርና የህዝብ ባለውለታ መሆናቸው ይታወቃል ።
@jeilutv

ጄይሉ ቲቪ // Jeilu Tv

01 Dec, 08:17


ካፒቴን መሐመድ አህመድ

ጄይሉ ቲቪካፒቴን መሐመድ አህመድ የኢትዮጵያ አየር መንገድን ወደ እመርታ የመሩ (1924-2017)
=================

ኢትዮጵያ ወደ ምዕት ዓመት የሚጠጋ የካበተ የንግድ አቪዬሽን ታሪክ አላት። በተለይ የሁለተኛው የዓለም ጦርነት ማብቃቱን ተከትሎ የተቋቋመው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከሁለት ዓመት በኋላ ሰማንያ ዓመት ይሞላዋል፡፡


በነዚህ የስምንት አሠርታት ያህል ጉዞው የኢትዮጵያ አየር መንገድን በዋና ሥራ አስፈጻሚነት ለመምራት ኢትዮጵያውያን የተሰየሙት ከሩብ ክፍለ ዘመን ቆይታ በኋላ ነው፡፡ በኮሎኔል ስምረት መድኃኔ የተጀመረው አመራርነት እስካሁኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው ዘንድ ደርሷል፡፡ ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ በዘለቀው የኢትዮጵያውያን በብቃት አየር መንገዱን የመምራት ጉዞ በዓለም አቀፍ ደረጃ ልዕልናን ከግንባር ቀደምነት ጋር ተያይዞ ስሙ እንዲነሳ አድርጎታል፡፡

ይሁን እንጂ መንገዱ ሁሉ አልጋ ባልጋ አልነበረም፡፡ የንጉሠ ነገሥት መንግሥቱ በ1967 ዓ.ል. ያስወገደው አብዮትን ተከትሎ ሥልጣኑን የጨበጠው ወታደራዊው የደርግ መንግሥት የተከተለው ሶሻሊስታዊ ርዕዮት ለአየር መንገዱ ፈተና መሆኑ አልቀረም፡፡

በአብዮቱ የመጀመርያ አምስት ዓመታት ፖለቲካዊ ጣልቃገብነት መባባሱ በአየር መንገዱ ውስጥ ተፈጥሮ የነበረው መንገዳገድ ኪሳራም አስከትሎ ነበር፡፡

ይህን አሳሳቢ ሁኔታ የተገነዘበው መንግሥትም በውጭ አገር የሚገኙ የቀድሞ አመራሮች ፍጡነ ረድኤት ሆነው አየር መንገዱን እንዲታደጉ መንቀሳቀሱ አማራጭ ሆኖ ያገኘው፡፡ በዚህ አጋጣሚም 1972/73 ዓ.ል (1980) ላይ አዲሱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው ካፒቴን መሐመድ አህመድ ብቅ ያሉት፡፡

የቀድሞው ደርግ የወለደው የኢሕዲሪ መንግሥት (1980-83) ምክትል ፕሬዚዳንት የነበሩት ሌተና ኮሎኔል ፍሥሐ ደስታ ‹‹አብዮቱና ትዝታዬ›› በሚል ርዕስ በጻፉት መጽሐፍ ትውስታቸውን አጋርተዋል።

 ‹‹የ1966ቱ ሕዝባዊ አመፅ ሲፈነዳ የፖለቲካው ወላፈን አየር መንገዱ ውስጥም ገብቶ ያምሰውና ያተራምሰው ገባ፡፡ ተራማጅ ነን የሚሉ የደርግ አባላት፣ ሚኒስትሮችና ካድሬዎች አየር መንገዱ ከቦይንግ [አሜሪካ] ወደ ኤሮፍሎት [ሶቪየት ኅብረት] እንዲሰጥ›› ያደርጉት የነበረው ጥረት የከሸፈው ‹‹ሊቀመንበር መንግሥቱ ኃይለ ማርያም አየር መንገዱ ወደ ውድቀት ማምራቱን ሲገነዘቡ ሥር ነቀል ዕርምጃ በመውሰድ መፍትሔ እንዲያስገኙ ለፍሥሐ ደስታ፣ ለአማኑኤል ዐምደሚካኤልና የሱፍ አህመድ ጥብቅ መመርያ በመስጠታቸው እንደሆነ በታሪካቸው ላይ ሰፍሯል፡፡

ከአገር ወጥተው በተለያዩ አገሮች በኃላፊነት ይሠሩ የነበሩት የአየር መንገዱ የቀድሞ ኃላፊዎች ኮሎኔል ስምረት መድኃኔ፣ ካፒቴን መሐመድ አህመድ፣ አሰፋ አምባዬና ወልደ ገብርኤል ፀሐይ በሦስቱ ከፍተኛ ሹማምንት አማካይነት እንዲመጡ በማድረግ አየር መንገዱ ከውድቀት መታደጋቸው ተጽፏል፡፡

የካፒቴን መሐመድ መንበር

ካፒቴን መሐመድ በኢትዮጵያ አየር መንገድ ውስጥ ሥራ የጀመሩት በ1950ዎቹ የአውሮፕላን ዋና መሐንዲስነት (chief aeronautical engineer) ሲሆን፣ ከቴክኒካዊ ዕውቀታቸውና ከእይታቸው በመነሳት ለአየር መንገዱ ዕድገት መሠረታዊ ሚና መጫወታቸው በገጸ ታሪካቸው ተመዝግቧል።

ካፒቴን መሐመድ እ.ኤ.አ. በ1980 የዋና ሥራ አስፈፃሚነት መንበሩን ከተረከቡ በኋላ በአሠርት ውስጥ የፈጸሟቸው ተግባራት አየር መንገዱን ወደ አዲስ ከፍታ እንዳደረሰ ይወሳል፡፡  

ዜና ዕረፍታቸውን ተከትሎ አፍሪካን ትራቭል ኳርተርሊ ላይ የተጻፈ ማስታወሻ ይህንኑ ያመለክታል፡፡ ‹‹በእሳቸው መሪነት አየር መንገዱ በወታደራዊ አገዛዝ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ፈተናዎች ውስጥ ቢሆንም እያደገ ሄደ። የካፒቴን አህመድ ቅልጥፍናና የማይናወጥ ቁርጠኝነት የኢትዮጵያ አየር መንገድን ከአላስፈላጊ ጣልቃገብነት ከለለው፡፡ ይህም በአፍሪካ በጣም ስኬታማ ከሆኑ አየር መንገዶች አንዱ እንዲሆን አስችሎታል።››

ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ዘላቂ ስኬት መሠረት የጣሉትን ካፒቴን መሐመድን በይበልታ ያወደሰው እናት መሥሪያ ቤታቸው ነው፡፡

‹‹ካፒቴን መሐመድ አህመድ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሆነው ባገለገሉበት ወቅት አየር መንገዱ ዛሬ ለደረሰበት የስኬት ደረጃ እንዲበቃ መሠረት የጣሉ ውሳኔዎችን በማሳለፍ የማይተካ የመሪነት ሚናቸውን ተጫውተው አልፈዋል። በሕይወት ዘመናቸው ለአየር መንገዱ ባበረከቱት የመሪነት አስተዋፅዖ ምንጊዜም ያስታውሳቸዋል።››

በሐምሌ 1924 ዓ.ል. በሐረር ከተማ የተወለዱት ካፒቴን መሐመድ አህመድ በኢትዮጵያ አየር ኃይል ውስጥ ለአጭር ጊዜ ካገለገሉ በኋላ የከፍተኛ ትምህርታቸውን ተከታትለው በሳይንስ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን በኤሮኖቲካል ኢንጂነሪንግ ከአሜሪካ ሴንት ሉዊስ ዩኒቨርሲቲ አግኝተዋል። በኋላም በስታንፎርድ ዩኒቨርሲቲ የሥራ አስፈፃሚ ፕሮግራም ሥልጠናን አጠናቀዋል፡፡

በእርሳቸው አመራር የኢትዮጵያ አየር መንገድ በ1970ዎቹ መጨረሻ ወደ መረጋጋትና ልዕልና ገብቷል። የሰው ኃይል ማሻሻያዎችንና ስልታዊ አጋርነትንን ጨምሮ የወሰዷቸው ወሳኝ ተግባሮች የአየር መንገዱን የልዕልና ስም በላቀ ደረጃ መልሰውታል።

የካፒቴኑ ሰብዕና ለዓለም አቀፍ ዕውቅናና ውርስም የበቃ ሆኗል፡፡ ስኬታቸው በኢትዮጵያ አየር መንገድ ብቻ ሳይወሰን አኅጉር አቀፍ ሆኗል። እ.ኤ.አ. በ1992 የአፍሪካ አየር መንገድ ማኅበር ዋና ጸሐፊ በመሆን የአፍሪካን አቪዬሽን በዓለም አቀፍ መድረክ ላይ አስቀምጠውታል።

ከሦስት አሠርታት በፊት በማደግ ላይ ካሉት አገሮች ውስጥ ከሚገኙ ከፍተኛ ሥራ ፈጣሪዎች አንዱ፣ ለትውልድ አገራቸውና ለዕድገቷ በከፍተኛ ቁርጠኝነት የሠሩ መሪ እንደነበሩ በመግለጽ ስለ ካፒቴን መሐመድ የጻፉት አሜሪካዊው ጸሐፊ ፖል ሄንዝ ናቸው።

 በ92 ዓመታቸው ኅዳር 17 ቀን 2017 ዓ.ል. ያረፉት ካፒቴን መሐመድ አህመድ ሥርዓተ ቀብር በአዲስ አበባ ኮልፌ ሙስሊም መካነ መቃብር በማግስቱ የተፈጸመው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰውና የአየር መንገዱ ከፍተኛ አመራሮች፣ ሠራተኞችና የቀድሞ ባልደረቦች በተገኙበት ነው፡፡

‹‹የካፒቴን መሐመድ አህመድ ሕይወት የጽናት፣ የፈጠራና ለላቀ ሥራ የማይናወጥ ቁርጠኝነት ማረጋገጫ ነበር። የርሳቸው ትሩፋት በኢትዮጵያ አየር መንገድ ውስጥ ያሉትን ብቻ ሳይሆን በዓለም አቀፍ መድረክ የራሳቸውን አሻራ ለማሳረፍ የሚጥሩትን አፍሪካውያን ትውልዶችን ማበረታታቱን ይቀጥላል፤›› ያለው አፍሪካን ትራቭል ኳርተርሊ ነው።

‹‹መሪ ብቻ ሳይሆኑ ፈር ቀዳጅ ነበሩ፡፡ በኢትዮጵያ አየር መንገድና በአጠቃላይ የአፍሪካ አቪዬሽን ላይ ያበረከቱት ከፍተኛ ተፅዕኖ ለዘላለም ሲታወስ ይኖራል፤›› የተባለላቸው ካፒቴን መሐመድ አህመድ፣ እ.ኤ.አ. በ2009 በአኩዋባ አፍሪካ የጉዞ ገበያ ከቀድሞው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ግርማ ዋቄ ጋር መሸለማቸው ይታወሳል፡፡
#ሪፖርተር

ጄይሉ ቲቪ // Jeilu Tv

28 Nov, 18:13


አለም አቀፍ የቁርአን ውድድሩ የሚካሄድበት ቀን ይፋ ሆነ

ጄይሉ ቲቪ2ኛው አለም አቀፍ የቁርአንና የአዛን ውድድር የሚካሄድበት ተለይቶ ጥር 25 ቀን 2017 መሆኑን ይፋ መደረጉን አዘጋጁ ዘንድ እብን ሳቢት አስታውቋል ።
ጄይሉ ቲቪ 19/03/2017

በዘይድ እብን ሳቢት የቁርአን ማህበር አዘጋጅነትና በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳይ ጠቅላይ ምክር ቤት የበላይ ጠባቂነትና ክትትልና ድጋፍ የሚካሄደው ይህው አለም አቀፍ ውድድር ጥር 25 ቀን እንደሚካሄድ ያስታወቁት ኡስታዝ ኑረዲን ቃሲም ናቸው ።

የዘይድ እብን ሳቢት የቁርአን ማህበር ዋና ስራ አስኪያጅ ኡስታዝ ኑረዲን እንዳሉት የዘንድሮ ውድድር የአለም አቀፍ ውድድሩ አብይ አስተባባሪ ኮሚቴ ከመጅሊስ ዑለማ ምክር ቤት ጋር ዝግጅቱን የተሳካ ለማድረግ እየሰሩ መሆኑን ፣ የአለም አቀፍ ውድድሩ የበላይ ጠባቂም ክቡር ሼህ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ መሆናቸውን አስረድተዋል ።

በውድድሩ የሚሳተፉ ሀገራት ምዝገባና ልየታ መጀመሩን ገልጸው ኢትዮጵያን ወክለው የሚወዳደሩ ተወዳዳሪዎችን በቅርቡ የማጣሪያ ውድድሮች በማድረግ እንደሚለዩ ጠቁመዋል ።
ለውድድሩ ዝግጅት ስኬት በተለይ ደግሞ ለውጪ እንግዶች መስተንግዶ ፣ ለውድድሩ አሽናፊዎች ሽልማት እና ለሌሎችም አስፈላጊ ወጪዎች ድጋፍ ሊያደርጉ የሚችሉ ተቋማት አብረዋቸው እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል ።

ጄይሉ ቲቪ // Jeilu Tv

26 Nov, 17:41


የህዝበ ሙስሊሙ ጥያቄ ለመንግስት ቀረበ

ጄይሉ ቲቪየኢትዮጵያ እስልምና ጉዳይ ጠቅላይ ምክር ቤት   የህዝበ ሙስሊሙን ጥያቄ ለመንግስት  አቀረበ ።

ጄይሉ ቲቪ :- 17 /03/2017

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳይ ጠቅላይ ምክር ቤት ከፍተኛ አመራሮች ለውጭ ጉዳይና ለአዲስ አበባ ከንቲባ ወቅታዊና ለረጅም ጊዜ ምላሽ ያላገኙ  የህዝበ ሙስሊሙን ጥያቄዎች ማቅረቡንና በአጭር ጊዜ  ምላሽ እንደሚያገኝ  ቃል እንደተገባላቸው ከመጅሊስ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

የመጅሊስ ፕሬዝደንት ሼህ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ ፣ ምክትላቸው ሼህ አብዱልከሪም ሼህ በድረዲን ፣ ዋና ጽሐፊው ሼህ ሐሚድ ሙሳና የጽ/ቤት ኃላፊው ኡስታዝ አቡበከር አህመድ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶክተር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ የኢትዮጵያ የአረብ ሊግ የአባልነት ጥያቄ በተመለከተ ፣ በዲፕሎማቶች ምደባ የሙስሊሙ ውክልና ፣ የመጅሊሱ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በተለያዩ ሀገራት ስለመክፈት ጥያቄ መቅረቡንምና መወያየታቸው ተገልጿል።
በተመሳሳይ መልኩ ከአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ጋር ባካሄዱት ውይይት በአዲስ አበባ ከተማ በተለያዩ የመንግስት ሹመቶች የሙስሊሙን አካታችነት ፣ በአዲስ አበባ መሐል ገቢ የሚያስገኝ ህንጻ ለመገንባት የቦታ ጥያቄ ፣ሌሎችም ጉዳዮያዎች ላይ ለቀረቡት ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ  በአጭር ጊዜ ውስጥ ምላሽ እንደሚሰጥባቸው እንደተነገራቸውና የተገኘውንም ውጤት ለህዝበ ሙስሊሙ ወደፊት ይፋ እንደሚሆን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል ።

ጄይሉ ቲቪ // Jeilu Tv

26 Nov, 11:00


የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ግድያውን አወገዘ

ጄይሉ ቲቪየኢትዮጵያ ሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ በደራ ወረዳ የተፈፀመውን አሰቃቂ የግድያ ድርጊት አወገዘ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 17፣ 2017 የኢትዮጵያ ሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ በሰሜን ሸዋ ዞን ደራ ወረዳ የተፈፀመውን አሰቃቂ እና ጭካኔ የተሞላበት የግድያ ድርጊት አወገዘ፡፡

የጉባኤው ዋና ፀሀፊ ቀሲስ ታጋይ ታደለ ሁሉም ሀይማኖቶች የሰው ልጆች ሁሉ ፍቅርን፣ መታዘዝን፣ ይቅርታንና ዕርቅን አስቀድመው እንደሚያስተምሩ ተናግረዋል።

ከቅርብ ግዜ ወዲህ ግን በአንዳንድ የሀገራችን አካባቢዎች ንፁሀን ላይ ያነጣጠሩ የግድያ እና የእገታ እንዲሁም ማፈናቀል ድርጊቶች እየተፈፀሙ ነው ብለዋል።

ኤፍ ቢ ሲ

ጄይሉ ቲቪ // Jeilu Tv

22 Nov, 08:24


የአለም አቀፍ የቁርአን ውድድር ዝግጅት ተጠናክሮ እንዲቀጥል መመሪያ ተላለፈ

ጄይሉ ቲቪ2ኛው አለም አቀፍ የቁርአንና የአዛን ውድድር ዝግጅት ተጠናክሮ እንዲቀጥል ክቡር ሼህ ሐጂ ኢብራሂም መመሪያ አስተላለፉ ።
ጄይሉ ቲቪ :- ህዳር 13 ቀን 2017

የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዝደንት መመሪያውን ያስተላለፉት ሰሞኑን የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት እና  አለም አቀፍ የቁርአንና አዛን ውድድር አብይ አስተባባሪ ኮሚቴ አባላት በቀጣይ አሰራር ላይ ምክክር ባካሄዱበት ወቅት ነው ።

በዘይድ እብን ሳቢት የቁርአን ማህበር አዘጋጅነት በመጅሊስ የበላይ ጠባቂነት ፣ ድጋፍና የቅርብ ክትትል ከሁለት ወራት በኋላ የሚካሄደው ሁለተኛው አለም አቀፍ የቁርአንና የአዛን  ውድድር በተመለከተ ክቡር ዶክተር  ሼህ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ በተገኙበት ምክክር ተካሄዷል ።

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ኡለማዎች እና የአለም አቀፍ የቁርአንና የአዛን ውድድር አብይ አስተባባሪ ኮሚቴ አባላት በቀጣይ ህዝብን የሚያሳትፍና የሀገር ገጽታን የሚጠብቅ ውድድር በቅንጅ መስራት እንደሚኖርባቸው ክቡር ዶክተር ሼህ ሐጂ ኢብራሂም አሳስበዋል ።

አለም አቀፍ የቁርአን ውድድሩ በቅድመ ዝግጅት እስከአሁን የተሰሩ ስራዎች አበረታች መሆናቸውን ለዚህም የመጅሊሱ የቅርብ ክትትልና ድጋፍ መሆኑን እንዲሁም ክቡር ዶክተር ሼህ ሐጂ ኢብራሂም አለም አቀፍ ውድድሩ በቅድመ ዝግጅትም ሆነ ቀጥሎ ለሚስራውም ዋና የዝግጅት ምዕራፍ ላደረጉት አስተዋጽኦ አብይ አስተባባሪ ኮሚቴው ምስጋናውን ገልጾአል ።

በመጨረሻም ክቡር ዶክተር   ሼህ ሐጂ ኢብራሂም ዝግጅቱ ህዝበ ሙስሊሙን ያሳተፈ፣ የደመቀና የተሳካ እንዲሆን  አብይ አስተባባሪ ኮሚቴው ከጠቅላይ ምክር ቤቱ የዑለማ ምክር ቤት ጋር በቅንጅት እንዲሰራና ዝግጅቱን በተጠናከረ መልኩ እንዲቀጥል መመሪያ በመስጠት ስብሰባው ተጠናቋል ።

2ኛው አለም አቀፍ የቁርአንና የአዛን ውድድር ጥር 25 ቀን 2017 በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ ይፋ ሆኖአል ።

ጄይሉ ቲቪ // Jeilu Tv

22 Nov, 06:40


ሱቃቸው ለተቃጠለባቸው ድጋፍ ተደረገላቸው

ጄይሉ ቲቪመርካቶ ሸማ ተራ አካባቢ በእሳት አደጋ ንብረታቸው ለወደመባቸው ወገኖች 20 ሚሊየን ብር ድጋፍ ተደረገ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 13፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ)

ጄይሉ ቲቪ // Jeilu Tv

17 Nov, 20:53


በስልጤ ዞን ምስራቅ አዘርነት በርበሬ ወረዳ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ተመረቀ ።

ጄይሉ ቲቪበጤናው ዘርፍ የላቀ ውጤት ለማስመዝገብ የህብረተሰቡን ተሳትፎ ማሳደግ ይገባል - አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን!

ወራቤ፣ህዳር 8/2017 -ስልጤ ዞን ኮሙዩኒኬሽን

በስልጤ ዞን ምስራቅ አዘርነት በርበሬ ወረዳ ከ165 ሚሊየን በላይ ብር ወጪ የተደረገበት የቂልጦ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል

የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ዳይሬክተር ጀነራል አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ እንደገለጹት
በጤናው ዘርፍ የላቀ ውጤት ለማስመዝገብ የህብረተሰቡን ተሳትፎ ማሳደግ ይገባል ብለዋል።

በወረዳው ከዚህ ቀደም በጤና ተቋማት እጦት ምክንያት ህይወታቸውን ያጡ እናቶች እንደነበሩ ተናግረዋል።

የአካባቢው ማህበረሰብ ቀደም ሲል በነበረው ስርአት ከመንግስት ጋር እየተሽቀዳደመ በልማት ስራ ላይ የላቀ ሚና ተጫውቷል ብለዋል።

ባለፉት ስርኣተ መንግስታት ወረዳው እንደ ደሴት ተነጥሎ በመሰረተ ልማት ዘርፍ ተጠቃሚ አልነበረም ያሉት አቶ ሬድዋን አሁን ግን በመንግስት እና በህብረተሰብ ተሳትፎ ልዩ ልዩ የመሰረተ ልማት ተቋማት ተገንብተው ለአገልግሎት መብቃታቸውን በአብነት ጠቅሰዋል።

መንግስት ከሚያደርገው አስተዋጽኦ በተጓዳኝ በግለሰብ ደረጃ የጤናውን ዘርፍ ለመደገፍ አብነታዊ ስራዎችን ያከናወኑ አካላትን አመስግነዋል።

ጄይሉ ቲቪ // Jeilu Tv

16 Nov, 11:00


ከፍተኛ ውጤት ያመጡ ተማሪዎች ተሸለሙ

ጄይሉ ቲቪበሀይረንዚ ልዩ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2016 የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች የሽልማት መርሃ ግብር እየተካሄደ ነው።

ህዳር 7/2017 (ስልጤ ዞን ኮሙኒኬሽን)

በስልጤ ዞን ወራቤ ከተማ በሚገኘው ሀይረንዚ ልዩ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2016 የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎችና ለውጤቱ መመዝገብ የላቀ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ባለድርሻ አካላት የማበረታቻ ሽልማትና የምስጋና መርሃ ግብር እየተካሄደ ይገኛል።

መርሃ ግብሩ በይፋ ያ
ስጀመሩት የስልጤ ዞን ዋና አኣተዳዳሪ አቶ ዘይኔ ቢልካ የሀይረንዚ መመስረት በሁሉም የዞኑ ትምህርት ቤቶች የውድድር መንፈስ እንዲፈጠር አድርጓል ብለዋል።

ሀይረንዚ ለዞኑ ትምህርት መነቃቃት የራሱን አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ያነሱት አቶ ዘይኔ ጅምሩን ይበልጥ በማጠናከር የትምህርቱን ዘርፍ ጉድለቶች መሙላት ይገባል ብለዋል።

ሀይረንዚ በየተኛውም መልኩ የስልጤን ህዝብ ስም የሚያስጠራ ተቋም መሆኑን በመግለጽ ትምህርት ቤቱንና ስልማን ማጠናከር ልዩ ትኩረት የሚሰጠው ተግባር መሆኑን ዋና አስተዳዳሪው አንስተዋል።

ጄይሉ ቲቪ // Jeilu Tv

14 Nov, 11:03


የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ተመሰረተ

ጄይሉ ቲቪየኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ምስረታ ተከናወነ ።

አስራ አንድ አባላት ያሉት የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል

ዑስታዝ ሐይደር ከድር አብድር ቃድር ንበዋና ሰብሳቢነት ዐስታዝ(ኸጢብ) አብዱላዚዝ መሐመድ ሰዒድ ን ምክትል ሰብሳቢ

ኢንጂነር ዑስታዝ ከማል አረቦ አህመድ በዋና ጸሐፊ በመምረጥ መጣናቀቁን የዘገበው የኢ/እ/ጉ/ጠ/ም/ቤት ነው።

ጄይሉ ቲቪ // Jeilu Tv

10 Nov, 16:34


የ2ኛው አለም አቀፍ የቁርአንና የአዛን ውድድር አሽናፊው የሚለይበት የመጨረሻ መድረክ መቼ እንደሚካሄድ መወሰኑን  ዘይድ እብን ሳቢት የቁርአን ማህበር አስታወቀ ።

በቅርቡ ይካሄዳል ተብሎ የሚጠበቀው አለም አቀፍ የቁርአንና የአዛን ውድድር መቼና የት እንደሚካሄድ በትብብር የሚያዘጋጁት ዘይድ እብን ሳቢትና የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በጋራ መወሰናቸውንና በቅርቡ በጋራ በሚሰጡት መግለጫ ይፋ እንደሚሆን ታውቋል ።
ለዚህ ኢትዮጵያ ለምታዘጋጀው አለም አቀፍ ውድድር ስኬት  ሁሉም   ተሳታፊ እዲሆን  ጥሪ ቀርቧል ።
ለበለጠ መረጃ :- 0953 949596

ጄይሉ ቲቪ // Jeilu Tv

02 Nov, 15:17


እናቶች ህክምና አገኙ ፣

ጄይሉ ቲቪየሲር ለና የበጎ አድራጎት ድርጅት ለእናቶች የህክምና ምርመራ እንዲያገኙ አደረገ ።

ጄይሉ ቲቪ :- ጥቅምት  23 ቀን 2017

ጥቅምትን ከየሲር ለና ጋር በሚል በየሲር ለና የበጎ  አድራጎት ድርጅት አዲሱ ግቢው  በመቶዎች የሚቆጠሩ እናቶች የህክምና ምርመራ እንዲያገኙ አድርጓል ።

በተለያየ የህክምና ዘርፍ ከተለያየ ከትማ የመጡ የህክምና ባለሙያዎች የውስጥ ደዌ እና የአይን ምርመራዎችን በማካሄድ ህክምና እንዲያገኙ አድርገዋል ።
በእለቱ  ታዋቂ አስታዞች ፣ የሚዲያ ባለሙያዎችና በጎ አድራጊዎች በስፍራው በመገኘት ለእናቶች እንክብካቤና ፍቅራቸውን ሲገልጹ ታይተዋል ።

ጥቅምትን ከየሲር ለና ጋር የሚቀጥለው ሳምንት ቅዳሜ ጥቅምት 30 ቀን 2017  በጎ ፍቃደኞች ሁሉ የሚሳተፉበት "ደማችንን ለእናቶቻችን"  በሚል የደም ልገሳ እንደሚካሄድ ታውቋል ።

ጄይሉ ቲቪ // Jeilu Tv

01 Nov, 10:30


በአዲስ አበባ አለም አቀፍ ጉባኤ ሊካሄድ ነው

ጄይሉ ቲቪበአዲስ አበባ ዓለምአቀፍ የሃይማኖት ጉባዔ ሊካሄድ ነዉ።
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
አዲስ አበባ | ጥቅምት 22 ቀን 2017

የሰላም ሚኒስቴር ከሙሐመድ ቢን ዛይድ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በአዲስ አበባ ዓለምአቀፍ የሃይማኖት ጉባዔ ሊያካሂድ መሆኑን ተናገረ።

ጥቅምት 25 እና 26፣ 2017 ዓ.ል (ሰኞና ማክሰኞ) በአዲስ አበባ ኃይሌ ግራንድ ሪዞርት የሚካሄደውን ይህን ዓለምአቀፍ ጉባዔ አስመልክቶ ሚኒስቴሩ ዛሬ ለመገናኛ ብዙኃን ተቋማት ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።

በሰላም ሚኒስቴር የሰላም ግንባታና ብሔራዊ መግባባት ዘርፍ ሚኒስትር ደዔታ ዶክተር ኸይረዲን ተዘራ በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ ሲናገሩ ኢትዮጵያ ቀደምት የሰዎች መገኛ ብቻ ሳትሆን፣ እስልምናና ክርስትና ለዘመናት በሰላምና በሃገር ግንባታ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያደረጉባት ታሪካዊ ሀገር መሆኗን አውስተዋል።

በዓይነቱ የመጀመሪያ የኾነው ይህ ዓለምአቀፍ ጉባዔ ሃይማኖቶች ለሀገራችን ሰላምና አብሮነት ያደረጉትን ጉልህ አስተዋፅዖ ይበልጥ ለማጠናከር የሚያግዝ መሆኑን ሚኒስትር ደዔታው ተናግረዋል።

ለዚህም ዓላማ መሳካት የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ከሁሉም የሃይማኖት ተቋማት ጋር ተቀራርቦ እየሠራ እንደሚቀጥል ሚኒስትር ደዔታው ተናግረዋል።

ለሁለት ቀናት በሚቆየው በዚህ ዓለምአቀፍ ጉባዔ ላይ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ አባል ቤተ እምነት አባቶች፣ አውሮጳና ኤዥያን ጨምሮ ከአሥራ ሦስት ሀገራት የሚመጡ የሃይማኖት ሊቃውንት፣ አሥራ አምስት ዩኒቨርሲቲዎችን ጨምሮ ሦስት መቶ ሰዎች በጉባዔው ላይ እንደሚሳተፉ ተነግሯል።


••••••••••••
የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት።

ጄይሉ ቲቪ // Jeilu Tv

24 Oct, 14:24


የሰላምና የአብሮነት መድረክ

ጄይሉ ቲቪየሃይማኖት ተቋማት ለሰላምና ለአብሮነት በሚኖራቸው ሚና ላይ ምክክር ማድረጋቸው ተገለጸ።
ጄይሉ ቲቪ :- ጥቅምት 14 ቀን 2017
በአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት እና በኢትዮጵያ ከኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ህብረት ጋር በመተባበር ባዘጋጀው የሰላምና የአብሮነት መድረክ የሃማኖት ተቋማት ከፍተኛ ሚና እንዳላቸውና መስራት እንዳለባቸው መክረዋል ።

ጄይሉ ቲቪ // Jeilu Tv

22 Oct, 13:51


የእሳት አደጋው መንስኤ እየተጣራ ነው ።

ጄይሉ ቲቪበመርካቶ ሸማ ተራ የደረሰውን የእሳት አደጋ መንስኤ እየመረመረ መሆኑን ፖሊስ አስታወቀ

ጄይሉ ቲቪ ፣ ጥቅምት 12፣ 2017 ትናንትና ምሽት በአዲስ አበባ አዲስ ክፍለ ከተማ መርካቶ ሸማ ተራ አካባቢ ባጋጠመ የእሳት አደጋ በንብረት ላይ ጉዳት መድረሱን የከተማዋ ፖሊስ አስታውቋል።

የአደጋውን መንስኤ ለማጣራት የአዲስ አበባ ፖሊስ ከፌዴራል ፖሊስ የፎረንሲክ ምርመራ ቡድን ጋር በመቀናጀት ምርመራ መጀመሩ ተጠቁሟል፡፡

አደጋውን ለመከላከልና በአደጋው ምክንያት ሌላ ወንጀል እንዳይፈፀም እንዲሁም የአደጋ ተከላከይ ሠራተኞች ተግባራቸውን በአግባቡ መወጣት እንዲችሉና ተጨማሪ ጉዳት እንዳያጋጥም አስፈላጊው ርብርብ መደረጉ ተጠቁሟል፡፡

በዚህም የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊስ፣ የመከላከያ ሠራዊት፣ ሪፐብሊካን ጋርድ፣ ብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት፣ የከተማ አስተዳደሩ አመራሮች፣ የሠላምና ፀጥታ መዋቅር፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ሌሎች ተቋማት አደጋው እንዳይባባስ ከፍተኛ ጥረት ማድረጋቸው ነው የተገለጸው፡፡

አደጋውን እንደ ምቹ ሁኔታ በመጠቀም የስርቆት ወንጀል የፈፀሙ 33 ተጠርጣሪዎችን ይዞ ምርመራ እያጣራ መሆኑን የገለጸው ፖሊስ÷ ከአደጋው ጋር በተያያዘ በ7 ሰዎች ላይ ቀላል በ2 ሰዎች ላይ ደግሞ ከባድ ጉዳት መድረሱንም አመልክቷል፡፡

አደጋውን ለመከለከል የፀጥታና ሌሎች ተቋማት እንዲሁም የአካባቢው ሕብረተሰብ ላደረገው ድጋፍና ተባባሪነት ፖሊስ ምስጋና አቅርቧል፡፡

የአዲስ አበባ ፖሊስ በደረሰው የእሳት አደጋ የተሰማውን ሃዘን ገልፆ፥ ወደፊት በምርመራ የደረሰበትን ውጤት ለህዝብ እንሚያሳውቅም በማህበራዊ ትስስር ገጹ አስታውቋል፡፡
ኤፍ ቢ ሲ

ጄይሉ ቲቪ // Jeilu Tv

21 Oct, 19:45


"ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫን የማዘጋጅት አቅም አላት !"

ጄይሉ ቲቪኢትዮጵያ የ2029 የአፍሪካ ዋንጫን የማዘጋጀት አቅም አላት ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ተናገሩ ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከአራት አመት በኋላ የሚካሄደውን የአፍሪካ ዋንጫ ለማዘጋጀትም በይፋ ለካፍ ጥያቄ አቅርበዋል ።

ጄይሉ ቲቪ // Jeilu Tv

21 Oct, 19:19


መርካቶ ሸማ ተራ በእሳት እየነደደ ነው

ጄይሉ ቲቪበመርካቶ ሸማ ተራ የተከሰተውን የእሳት አደጋ ለመቆጣጠር ሄሊኮፕተር ለመጠቀም ጥረት እየተደረገ ነው

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 11፣ 2017  በአዲስ አበባ አዲስ ክ/ከተማ መርካቶ በተለምዶ ሸማ ተራ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የተከሰተውን የእሳት አደጋ ለመቆጣጠር እየተሰራ መሆኑን የከተማዋ የእሳትና አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል፡፡

የኮሚሽኑ የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ እንዳሉት÷እሳቱን በቁጥጥር ስር ለማዋል የእሳት የአደጋ መከላከያ ተሽከርካሪዎችና ባለሞያዎች በስፍራው ተሰማርተዋል፡፡

የእሳት አደጋውን መንስዔና ያደረሰውን ጉዳት ምርመራ ከተጣራ በኋላ እንደሚያሳውቁም ባለሞያው ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ተናግረዋል፡፡

የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ÷ የእሳት አደጋውን ለመቆጣጠር የእሳት አደጋና ስጋት መከላከል ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር በመሆን ከፍተኛ ርብርብ እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

አደጋውን በፍጥነት ለመቆጣጠር እየተደረገ ባለው ጥረት የአካባቢው መንገድ የእሳት አደጋ መኪና በተሟላ ሁኔታ ለመንቀሳቀስ አስቸጋሪ በመሆኑ ሄሊኮፕተር ለመጠቀም ጥረት እየተደረገ መሆኑንም ጠቁመዋል።

ከንቲባ አዳነች በተከሰተው የእሳት አደጋ በንብረት ላይ ለደረሰው ጉዳት እጅግ ማዘናቸውንም ተናግረዋል፡፡

ኤፍቢሲ

ጄይሉ ቲቪ // Jeilu Tv

21 Oct, 18:59


እስላማዊ ዩኒቨርስቲ በባሌ

ጄይሉ ቲቪበኢትዮጵያ የመጀመሪያው እስላማዊ ዩኒቨርሲቲ በጠቅላይ ምክርቤቱ ፕሬዚደንት ተመርቆ ተከፈተ።
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
ጥቅምት 11ቀን 2017
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚደንት የክብር ዶክተር ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ በዛሬው ዕለት በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የኾነውን የባሌ ሮቤ እስላማዊ ዩኒቨርሲቲ መርቀው ከፈቱ።

በምረቃ ስነ ሥርዓቱ ላይ የጠቅላይ ምክር ቤቱ ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚደንት ሸይኽ አብዱልከሪም ሸይኽ በድረዲን እና ከፍተኛ ዓሊሞች ተገኝተዋል።

የባሌ ሮቤ እስላማዊ ዩኒቨርሲቲ መሥራችና ዋና አስተባባሪ ዶክተር ጀይላን ገለታ በምረቃ ስነ ሥርዓቱ ላይ ባደረጉት ንግግር፣ የዩኒቨርሲቲው መከፈት በአካባቢው ማኅበረሰብ የእስልምና እውቀት ላይ ትልቅ አሴት ይጨምራል ብለዋል።

የዩንቨርሲቲው መሥራች ለባሌ እስላማዊ ዩኒቨርሲቲ መከፈት ከአካባቢው ማኅበረሰብና ከበጎ አድራጊዎች ትብብር ባሻገር መንግሥትም ትልቅ ድጋፍ በማደረጉ ምስጋና አቅርበዋል።

የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዚደንት በዩኒቨርሲቲው ምረቃ ላይ ሲናገሩ፣ ባሌ ሮቤ በኢትዮጵያ የእስልምና ትምህርት ላይ ትልቅ አሻራ ያሳረፈ የዓሊሞች መፍለቅያና ትልቅ ታሪክ ያለው አካባቢ መኾኑን ጠቅሰው፣ ይህን መሰል ዩኒቨርሲቲ መከፈቱ ለእስላማዊው ትምህርት ጥራት ትልቅ የብርሃን ጎዳና እንደሚሆን ተናግረዋል።

በአሁኑ ጊዜ 80 በመቶ ግንባታው የተጠናቀቀው ይህ ዩንቨርሲቲ ከሃይማኖታዊ ትምህርት ባሻገር በተለያዩ የአካዳሚ ዘርፎች ትምህርት የሚሰጥበትና ማኅበረሰቡን የሚያገለግል በመኾኑ፣ ሙስሊሙም ሆነ ሙስሊም ያልሆኑ ወገኖች ዩኒቨርሲቲውን እንደ ሃብታቸው እንዲንከባከቡት ፕሬዚደንቱ መልዕክት አስተላልፈዋል።

የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዚደንት በዚሁ ጊዜ በዩኒቨርሲቲው ምሥረታ ሂደት ላይ የተሳተፉትን የአካባቢው ማኅበረሰብ አባላት፣ ከፍተኛ የመንግሥት ባለስልጣናትን፣ እንዲሁም ዓሊሞችን አመሥግነዋል።

መንግሥት የትምህርት ጥራትን ለማምጣት ከሚያደርገው ጥረት አኳያ የዩኒቨርሲቲው መከፈት ለሀገር ትልቅ ዕድል መኾኑ የተጠቀሰ ሲኾን፣ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በሚቻለው ሁሉ ከዩኒቨርሲቲው ጎን ለመቆም ቃል ገብቷል።

•••••••••••••
የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት

ጄይሉ ቲቪ // Jeilu Tv

21 Oct, 08:35


ፈቱላህ ጉለን ህይወታቸው ማለፉ ተገልጸ

ጄይሉ ቲቪእ.ኤ.አ. በ2016 በቱርክዬ በከሸፈው መፈንቅለ መንግስት አቀናባሪ ናቸው በሚል ተጠርጥረው የነበሩትና መኖሪያቸውን አሜሪካ ያደረጉት ፌቱላህ ጉለን መሞታቸውን የቱርክ የህዝብ ቴሌቪዥን ዛሬ ዘግቧል።
@ጄይሉ ቲቪ

ጄይሉ ቲቪ // Jeilu Tv

21 Oct, 08:24


ጠቅላይ ሚኒስትር አብይና አንቶንዮ ጉቴሬዝ

ጄይሉ ቲቪጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር) ከተመድ ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 11፣ 2017 ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ጋር ተወያይተዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ ÷የተባበሩት መንግሥታት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ወደ ኢትዮጵያ እንኳን በደህና መጡ ብለዋል፡፡

ዛሬ ማለዳ ዋና ፀሃፊውን በጽሕፈት ቤታቸው ተቀብለው በተለያዩ ቀጣናዊ እና ባለብዙ ወገን ጉዳዮች ላይ ውይይት ማድረጋቸውንም ገልጸዋል፡፡
ኤፍቢሲ

ጄይሉ ቲቪ // Jeilu Tv

20 Oct, 19:09


የዳሌ አጥንት ህክምና በወራቤ ሆስፒታል

ጄይሉ ቲቪበወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ እስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የሙሉ ዳሌ መገጣጠሚያ ቅየራ (Total Hip Replacement ) ተጀመረ!

* ለሁለት ታካሚዎቸ የተሳካ የሙሉ ዳሌ መገጣጠሚያ ቅየራ(Total Hip Replacement ) ማድረግ ተችሏል።

በወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ እስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የሙሉ ዳሌ መገጣጠሚያ ቅየራ (Total Hip Replacement) በንዑስ ስፔሻሊስት (Sub specialist) የተጀመረ ሲሆን የአጥንት ህክምና ስፔሻሊስት እና የቀዶ ህክምና ክፍል ዳይሬክተር ዶ/ር አብዶ ዳመስ በግራ ዳሌ የመበስበስ (osteonecrosis) ችግር ተጠቂ ለሆነ የ45 ዓመት እድሜ ያለው ታካሚ ሶስት ሰዓት የፈጀ ስኬታማ ውስብስብ ቀዶ ህክምና ማድረግ መቻሉን ገልጸዋል።

ከ6 ወር በፊት በግራ ዳሌ አንገት ስብራት ተጠቂ የሆነች የ50 ዓመት እድሜ ያላት ታካሚም እንዲሁ ሁለት ሰዓት የፈጀ ስኬታማ ቀዶ ህክምና እንደተደረገላት ዶ/ር አብዶ አክለዋል።

ታካሚዎቹ ከህክምና በኋላም በመልካም የጤና ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ የገለፁት ዳይሬክተሩ በቀዶ ህክምናው ለተሳተፉ የህክምና ባለሙያዎች በሙሉ ላቅ ያለ ምስጋና አቅርበዋል።

በሆስፒታሉ የአጥንት ህክምና ክፍል ላለፉት ዘጠኝ አመታት ከቀላል የአጥንት ህክምና ጀምሮ፣ ከአደጋ ጋር የተያያዙ የአጥንት ስብራቶች፣ ውልቃቶች እንዲሁም ከፍተኛ እና ውስብስብ ልዩ ልዩ የአጥንት ቀዶ ህክምናዎች እየተሰጡ መሆኑንም ጠቁመዋል።

ይህም ለተመሳሳይ ህክምና የሚደረግ ሪፈራልን በማስቀረት ህብረተሰቡን ከአላስፈላጊ ወጪና እንግልት ከመታደግ አንፃር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው የሚገልጹት ዶ/ር አብዶ የህክምና ክፍሉ እንደ ሲ-አርም እና አርትሮስኮፕ (C-ARM, Arthroscope) ያሉ አዳዲስ የህክምና መሳሪያዎችንና ዘመን አመጣሽ ቴክኖሎጂ ማሽኖችን በማስገባት አገልግሎት እየሰጠ መሆኑንም አስታውሰዋል።

ማህበረሰቡም ይህንን አውቆ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ እንዲሆን ጥሪ ቀርቧል ።

ጄይሉ ቲቪ // Jeilu Tv

18 Oct, 06:40


አገራዊ የምክክር ኮሚሽን፣ በአማራና ትግራይ ክልሎች ያሉት ወቅታዊ ኹኔታዎች ሥራዬን ባግባቡ እንዳላከናውን እንቅፋት ኾነውብኛል ማለቱን ዶቸቨለ ዘግቧል። ኮሚሽኑ፣ በአማራ ክልል አንጻራዊ ጸጥታ በሠፈነባቸው ወረዳዎች ተባባሪ አካላት የአጀንዳ መረጣ ተሳታፊዎችን ለመምረጥ ሙከራ ማድረጋቸውን መግለጡን ዘገባው አመልክቷል። ኾኖም የኮሚሽኑ አሰልጣኞችና ተባባሪ አካላት ተንቀሳቅሰው መስራት እንዳልቻሉ የጠቀሰው ኮሚሽኑ፣ አማራ ክልል በሂደቱ ሳይካተት አገራዊ የምክክር ጉባዔ ማካሄድ አስቸጋሪ መኾኑን ገልጧል ተብሏል።


እስራኤል በሶማሌላንድ ወታደራዊ ጦር ሠፈር የማቋቋም ፍላጎት እንዳላት ከምንጮች መስማቱን ጠቅሶ ሚድል ኢስት ሞኒተር ጋዜጣ ዘግቧል። እስራኤል በምላሹ፣ በሶማሌላንድ በግብርና፣ ኢነርጂና መሠረተ ልማት ኢንቨስትመንት ልትሳተፍ ትችላለች መባሉን ዘገባው አመልክቷል። እስራኤል በሶማሌላንድ ወታደራዊ ጦር ሠፈር እንድታቋቁም የግዛቲቱን መንግሥት የመግባባት ተልዕኮ የያዘችው የተባበሩት ዓረብ ኢምሬቶች እንደኾነች ጋዜጣው ከዲፕሎማቶች መስማቱን ጠቅሷል። እስራኤል ሶማሌላንድ ውስጥ ጦር ሠፈር ለማቋቋም ፍላጎት ያሳየችው፣ ከየመን የሚሠነዘርባትን ጥቃት ለመቋቋም ነው ተብሏል።


አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት
ድህረ ገጽ፡-   https://jeilumedia.com
  ዩትዩብ:-   https://www.youtube.com/c/JeiluTube/videos
ፌስቡክ:-   https://www.facebook.com/jeilutv
ኢሜል :-   [email protected]
ቴሌግራም :-  https://t.me/Jeilumedia
ጄይሉ ቲቪ ዛሬን ለተሻለ ነገ

ጄይሉ ቲቪ // Jeilu Tv

16 Oct, 16:10


በህንድ ሐሰተኛ የቦምብ ጥቃት ማስፈራሪያ በመሰንዘሩ በርካታ በረራዎች ለረጅም ሰዓታት እንዲዘገዩ እና አቅጣጫቸውን እንዲቀይሩ ተደርገዋል፡፡

ባለፉት 48 ሰዓታት ውስጥ ቢያንስ 10 የሕንድ አውሮፕላኖች ላይ ሐሰተኛ የቦምብ ጥቃት ማስፈራሪያ በመሰንዘሩ ምክንያት በርካታ በረራዎች ለረጅም ሰዓታት እንዲዘገዩ እና አቅጣጫቸውን እንዲቀይሩ መገደዳቸውን ተዘግቧል፡፡

ከሰዓታት በፊት ከዴልሂ ወደ ቺካጎ የሚሄደው አውሮኘላን ለቅድመ ጥንቃቄ ሲባል በካናዳ አውሮኘላን ማረፊያ አርፏል ሲል ቢቢሲ ዘግቧል፡፡

ሰኞ ዕለት ከሙምባይ የተነሱ ሦስት ዓለም አቀፍ በረራዎች ላይ የቦምብ ጥቃት ዛቻ በኤክስ (ትዊተር) ላይ ከተሰነዘረ በኋላ አቅጣጫቸውን እንዲቀይሩ ተደርጓል።

ከዚህ መልዕክት ጋር በተያያዘ ፖሊስ አንድ ታዳጊን በቁጥጥር ስር አውሏል።
በተመሳሳይ ማክሰኞ ሁለቱን የኤር ህንድ አውሮኘላንን ጨምሮ ሰባት በረራዎች ከX በተሰነዘሩ ዛቻዎች በረራቸው ተራዝሟል፡፡

በህንድ አየር መንገዶች ላይ የሚደርሰው የሃክስ ቦምብ ዛቻ የተለመደ ነው ያለው ቢቢሲ የመንግስት ሲቪል አቬዬሽን ጀነራል ዳይሬክቶሬት እና የሲቪል አቬዬሽን  ደህንነት ቢሮ ሃላፊዎች እስካሁን ምንም ምላሽ አልተሰጠም ሲል ቢቢሲ ዘግቧል፡፡

በሕንድ አየር መንገዶች ላይ የሚሰነዘር ሐሰተኛ የቦምብ ጥቃት ዛቻ ያልተለመደ ነገር አይደለም፤ ነገር ግን ከሰኞ ጀምሮ አሁን በድንገተኛ ሁኔታ የጨመረውን የቦምብ ጥቃት ማስፈራሪያ ምክንያቱ ምን እንደሆነ ግልፅ አይደለም።

ጥቅምት 6 ቀን 2017 ዓ.ም

ጄይሉ ቲቪ // Jeilu Tv

16 Oct, 15:35


መንግስታዊ የቴሌኮም አገልግሎት አቅራቢው ኢትዮ ቴሌኮም፤  “ለመጀመሪያ ዙር” እያንዳንዳቸው 300 ብር ዋጋ ያላቸውን 100 ሚሊዮን መደበኛ አክሲዮኖች ለሽያጭ አቀረበ። ተቋሙ ይህንን ያስታወቀው 10 በመቶ የባለቤትነት ድርሻውን በይፋ ለህዝብ መሸጥ መጀመሩን ዛሬ ረቡዕ ጥቅምት 6፤ 2017 ባስታወቀበት መርሃ ግብር ላይ ነው።

በካፒታል ገበያ በኩል ለሽያጭ የቀረበውን የኢትዮ ቴሌኮምን አክሲዮን መግዛት የሚፈልግ ኢትዮጵያዊ፤ እስከ 3,333 አክስዮን ድረስ መግዛት እንደሚችል ተገልጿል።

ጄይሉ ቲቪ // Jeilu Tv

15 Oct, 10:40


ብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሪ መግዣና መሸጫ መካከል ያለው ልዩነት ከሁለት በመቶ እንዳይበልጥ አሳሰበ
********************
ጄይሉ ቲቪ :- ጥቅምት 4 ቀን 2017

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሪ መግዣና መሸጫ መካከል ያለው ልዩነት ከሁለት በመቶ እንዳይበልጥ አሳሰበ።

ባንኩ ከውጭ ምንዛሪ ግብይት ጋር በተያያዘ ስለሚፈጸሙ ክፍያዎች የማሻሻያ ፖሊሲ አወጥቷል። በመሆኑም የውጭ ምንዛሬ መግዣና መሸጫ መካከል ያለው ልዩነት ከሁለት በመቶ በላይ መሆን እንደሌለበትም አስታውቋል።

ጄይሉ ቲቪ // Jeilu Tv

15 Oct, 07:25


ለህዝብ ሙስሊሙ የቀረበ ጥሪ

ጄይሉ ቲቪየኢትዮጵያ  ሙስሊሞች  አለም አቀፉ ውድድር ስለሚመለከታቸው ሁሉም ተሳታፊ እንዲሆኑ ጥሪ ቀረበ ።

ጄይሉ ቲቪ :- ጥቅምት 04 ቀን 2017

ሼህ አሚን ኢብሮ በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የዳዕዋ ዘርፍ ኃላፊ
ትላት ዘይድ እብን ሳቢት ባዘጋጀው የምክክርና የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት ባስተላለፉት መልእከት አለም አቀፍ የቁርአንና የአዛን ውድድሩ የሁሉም ኢትዮጵያዊ ሙስሊም አጃንዳ በመሆኑ ሊደግፈው ይገባል ብለዋል ።

የአለም አቀፍ ውድድሩ ስኬት የህዝበ ሙስሊሙ ስኬት  እንደመሆኑና  ቁርአን ሁሉም ነገር ሊሰጠው የሚገባ በመሆኑ ሁሉም  በእውቀቱ ፣ በገንዘቡና በጊዜው መሳተፍ እንደሚገባ አሳስበዋል።

በሌላው አለም ስንመኘው የነበረውን አለም አቀፍ ውድድር ቢያንስ በአፍሪካ ከተካሄዱ ውድድሮች በተሻለ ደረጃ ለማዘጋጀት ርብርብ ማድረግ ይኖርብናል ብለዋል ።

ሼህ አሚን ኢብሮ ባስተላለፉት በዚህ ጠንከር ባለ መልእከት የአለም አቀፍ  የቁርአን ውድድር ተሳትፎን ልክ እንደ ኑህ መርከብ ጥሪ በመመሰል በአለም አቀፍ ውድድሩ ሁሉም እንዲሳተፍ ጥሪ ቀርቦለት" የተሳተፈ  አተረፈ !  ያልተሳተፈ ከሰር ! " ካሉ በኋላ " መርከቡ እንዴ ጉዞ ከጀመረ በኋላ አልተሳፈርኩም " ብሎ መቆጨት የለም   በማለት ተናግረዋል ።

በዚህ ዘይድ እብን ሳቢት የቁርአን ማህበርና የአለም አቀፍ የቁርአንና የአዛን ውድድር አብይ አስተባባሪ ኮሚቴ ባዘጋጁት መድረክ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኋላፊዎች ፣ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ፣ ዲፕሎማቶች ፣  ከፌደራል ፣ከኦሮሚያን፣  ከአዲስ አባበ ከተማ ፣ ከሸገር ፣ ከፉሪና ከተለያዩ የክፍለ ከተማ መጅሊሶች ከፍተኛ የስራ ኋላፊዎች ፣ የአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች ሊግ ተወካዮች ፣ የተለያዩ ባለሀብቶች ፣ ባርካታ እንግዶች ተገኝተዋል ።

በእለቱ ከተላለፉት መልእክቶችና ምክክሮች በተጨማሪ ለዝግጅቱ ወጪ መሽፈኛ የገቢ ማሰባሰቢያ ተካሄዷል።
የዝግጅት አስተባባሪዎቹ ቀጣይ ወድረኮችም ወደፊት እንደሚኖሩ ጠቁመዋል ።

ጄይሉ ቲቪ // Jeilu Tv

14 Oct, 18:05


https://youtu.be/5OmK-4Qdk-o

ጄይሉ ቲቪ // Jeilu Tv

11 Oct, 19:54


የቢላል ሀገር ኢትዮጵያ !
አለም አቀፍ የቁርአን ውድድር ኢትዮጵያ በእስልምና ታሪክ ያለትን ቦታ የምታሳይበት መድረክ !

ለ 2ኛው አለም አቀፍ  የቁርአንና የአዛን ውድድር የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት  !

ጥቅምት 3 ቀን 2017 ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ
በኤሊያና ሆቴል
0953929394

ጄይሉ ቲቪ // Jeilu Tv

11 Oct, 11:40


የፖስፖርት የግዜ ቆይታ ከ5 ዓመት ወደ 10 ዓመት ከፍ እንደሚል ተገልጿል።

የኢሚግሬሽን ዜግነትና አገልግሎት የፖስፖርት የግዜ ቆይታ ከ5 ዓመት ወደ 10 ዓመት ከፍ እንደሚል ገልጿል።

ፖስፖርት ለማደስ 5 ዓመት ይጠበቅ የነበረ ሲሆን ከአንድ ወር በኃላ ወደ ሥራ በሚገባው አሰራር መሰረት ግን ከ25 ዓመት በላይ ለሆናቸው ዜጎች በየ10 ዓመቱ እንደሚታደስ አገልግሎቱ ገልጿል።

ጄይሉ ቲቪ // Jeilu Tv

10 Oct, 18:06


ከ 24 ሺህ በላይ የሚሆኑት ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ገብተዋል

ከአዲስ አበባ የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተናና የሪሜዲያል መርሀ ግብር ከወሰዱ ተማሪዎች ውስጥ ከ 24 ሺህ በላይ የሚሆኑት ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ገብተዋል፡-ትምህርት ቢሮ

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በ2016 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተናን በመውሰድ የሪሜዲያል መርሀ ግብርን ጨምሮ 24 ሺህ 469 ወይም 48.87 % ተማሪዎች ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መግባታቸውን የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ አስታወቀ።

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በ2016 የትምህርት ዘመን በበይነ መረብና በወረቀት የተሰጠውን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተናን 50 ሺህ 69 ተማሪዎች የወሰዱ ሲሆን ከነዚህ መካከል 10 ሺህ 690 ወይም 21.4 %/ተማሪዎች ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለመግባት የሚያስችል ነጥብ አስመዝግበዋል።

በሪሜዲያል መርሀ ግብር ደግሞ 13 ሺህ 779 /27.52 %/ተማሪዎች ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመግባት ትምህርታቸውን ለመከታተል የሚያስችላቸውን ውጤት ያስመዘገቡ ሲሆን በጥቅሉ 24 ሺህ 469 ወይም 48.87% ተማሪዎች ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለመግባት መቻላቸውን ነው ትምህርት ቢሮ በመረጃው ያመለከተው።

ጄይሉ ቲቪ // Jeilu Tv

10 Oct, 16:05


"የራይድ መንደር" ይፋ ሆነ

በዛሬው እለት የራይድ መንደር ይፋ ሆኗል

ጄይሉ ቲቪኦቪድ ሪል ስቴት ከራይድ ትራንስፖርት ጋር የራይድ ቤተሰብ መንደርን ለመገንባት ስምምነት በዛሬው እለት መስከረም 30/2017 ዓ.ም በስካይ ላይት ሆቴል ተፈራርሟል።

ኦቪድ ሪል ስቴት ለራይድ ሹፌሮች የሚሆን የራይድ ቤተሰብ መንደር በገላን ጎራ ከተማ ለመገንባት በዛሬው ዕለት ስምምነት የተፈራረመ ሲሆን ሁለቱ ተቋማት አዲስ እየተገነባ በሚገኘው የገላን ጎራ ከተማ ውስጥ ለራይድ አሽከርካሪዎች በአጭር ጊዜ ቤቶችን ገንብቶ ለማስረከብ ተስማምተዋል።

ከዚህ በተጨማሪ ኦቪድ ሪል ስቴት ከሰዋሰው መልቲሚዲያ ጋርም ስምምነት የፈረመ ሲሆን
በዚህ ስምምነት ከሰዋሰው መልቲሚዲያ ጋር የተፈራረሙ አርቲስቶች በቅናሽ የቤት ባለቤት መሆን እንደሚችሉም በፊርማ ሥነ ሥርአቱ ወቅት ተገልጿል ።

ኦቪድ ግሩፕ ከሚያደርገው የቤት ዋጋ ቅናሽ በተጨማሪ ሰዋሰው መልቲሚዲያ የፋይናንስ ድጋፍ እንደሚያደርግ ተገልጿል።

ኦቪድ ግሩፕ ከ70 ሺህ በላይ ቤቶችን በተለያዩ ሳይቶች እየገነባ መሆኑን የገለፁት የኦቪድ ሪል ስቴት ዋና ስራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ፍሬው በየነ  60 ሺህ የሚሆኑት በገላን ጎራ ከተማ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ግሩፑ ለኩባንያዎች በሚደረግ ሽያጭ ቤቶችን ከተቋማት ጋር በመፈራረም እየገነባ መሆኑን ገልፀው ከሃይብሪድ ዲዛይንስ ኃላ.የተ.የግ. ማህበር እህት ኩባንያ ከሆኑት ራይድ ትራንስፖርት እና ሰዋሰው መልቲሚዲያ ጋር መፈራረማቸው ገልፀዋል።

ኦቪድ ግሩፕ ከሁለቱ ተቋማት ጋር በገባው ስምምነት መሠረት 5 ሺህ ቤቶችን በ2 ዓመት ጊዜ ውስጥ ሰርቶ እንደሚያስረከብ አስታውቋል።

ጄይሉ ቲቪ // Jeilu Tv

10 Oct, 16:00


የትምህርት ሚኒስቴር የምርጫ መሙያ ጊዜውን እስከ ረቡዕ ጥቅምት 6/2017 ዓ.ም ድረስ ማራዘሙን ትምህርት ሚኒስቴር ገልፀ!

ጄይሉ ቲቪበ2016 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስደው  ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች በመደበኛ እና በ 'Remedial' ፕሮግራም ለመከታተል የሚያስችል ማለፊያ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች የተቋም እና የትምህርት መስክ ምርጫቸውን በየትምህርት ቤታቸው በተወከሉ መምህራን በኩል እስከ መስከረም 30/2017 ዓ.ም ድረስ ሞልተው እንዲጨርሱ መገለጹ ይታወሳል።

ይሁን እንጂ " አንዳንድ ትምህርት ቤቶች በሲስተም ችግር ምክንያት የተማሪዎቻችንን የትምህርት መስክ እና የዩኒቨርስቲ ምርጫ መሙላት ተቸግረናል " ባሉት መሰረት የትምህርት ሚኒስቴር የምርጫ መሙያ ጊዜውን እስከ ረቡዕ ጥቅምት 6/2017 ዓ.ም ድረስ ማራዘሙን ትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል።

7,523

subscribers

5,580

photos

104

videos