ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ @henok_haile1 Channel on Telegram

ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ

@henok_haile1


ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ (Amharic)

ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ በእንግሊዝ በብዙ መንገዶች ላይ ገና በመተንፈስ ስስት ገዛ ኃይሌ መደብና መመልከት እንዲሆን የሚያደርጉ እና ፈቃደኛዎች መዋጋት እንዲሆን በጣም ስለ ኃይሌ ከማወቅ ትገኛለህ። ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ ለርዕስ ምናልባትም ሌላ ይደግፉባቸዋል። እሱ የኃይሌ መረጃዎችን አላያይ ማንኛውም ነገር ላይ ከለዛዋ እንደሚላይ እና ምንኩለኛውን ማህበረሰብ እንደሚሰጥ ተጨማሪ ነው። ይህን የሚከተለውን ልናቀርበን እንደሚችል በማናቀርብ አስቀድሞ ለአንዳች ሰንበቴ በጣም እንዳሰጥህ ተመዝግበናል።

ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ

08 Feb, 07:02


ምንም ያኽል ብናድፍ ከበረዶ ይልቅ ሊያነፃን የሚችል አምላክ ዐለን!

ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ

07 Feb, 12:21


መናኙ ተማሪ
🌿🌿🌿🌿

የጥንት(የቆሎ) ተማሪ ኑሮው እንደ ባህታዊ ነው እንዴት ሆኖ ቢሉ ከቤተሰብ ተለይቶ በበርሀ በገጠር ተማሪ ቤት ይኖራልና።


ከቤቱ እና ከቀየው ሲሰደድም ተቸግሮ አይደለም በገዛ ፈቃዱና በመንፈስ ቅዱስ አነሳሽነት ነው። የሚለብሰው የበግ ደበሎ የሚበላው ቆሎ እሱንም በጥቂቱ ቀሪው ፀሎት ነው ምግቡ።

ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ

26 Jan, 15:07


" ገና ደካሞች ሳለን ክርስቶስ ዘመኑ ሲደርስ ስለ ኃጢአተኞች ሞቶአልና።ስለ ጻድቅ የሚሞት በጭንቅ ይገኛልና፤ ስለ ቸር ሰው ግን ሊሞት እንኳ የሚደፍር ምናልባት ይገኝ ይሆናል።ነገር ግን ገና ኃጢአተኞች ሳለን ክርስቶስ ስለ እኛ ሞቶአልና እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን የራሱን ፍቅር ያስረዳል።ይልቁንስ እንግዲህ አሁን በደሙ ከጸደቅን በእርሱ ከቍጣው እንድናለን።ጠላቶች ሳለን ከእግዚአብሔር ጋር በልጁ ሞት ከታረቅን፥ ይልቁንም ከታረቅን በኋላ በሕይወቱ እንድናለን" ሮሜ 5:6-10
………………………………………………
https://t.me/henok_haile1
ቻናሉን ተቀላቅለው ኦርቶዶክሳዊ ክርስትና ወንጌል ይማሩ...!

ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ

25 Jan, 16:32


📷 እርግጠኛ ነኝ ፕሮፍይሎን ለመቀየር ፈልገው ፕሮፍይል የሚያደርጉት ጠፍቶ  ተቸግረው ያውቃሉ።

የናንተን ችግር ለመፍታት በአይነቱ ለየት ያለ አዲስ መንፈሳዊ ቻናል ይዘንላችሁ መተናል ከናንተ የሚጠበቀው ከታች ባለው ሊንክ join ማድረግ ብቻ ነው👇👇👇👇👇👇📷

https://t.me/addlist/gpX29GzfGs43MWE0

ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ

25 Jan, 15:57


🏆 ለ ኦርቶዶክሳዊያን ብቻ የተከፈቱ በኢትዮጵያ የመጀመርያዎቹ ኦርቶዶክሳዊ ቻናሎች ❤️❤️❤️

ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ

22 Jan, 15:56


« ክርስቲያን ነኝ። » ቅዱስ ቂርቆስ



... ያንንም ህጻኑን ይዘው ወደ መኮንኑ ወሰዱት ፡፡
መኮንኑም: « ደስ የምትል ደስተኛ ሕጻን ሰላምታ ይገባሃል አለው፡፡ »

ሕጻኑ ቅዱስ ቂርቆስ: « እኔን ደስተኛ ማለት መልካም ተናገርክ ፤ላንተ ግን ደስታ የለህ ፤የእግዚአብሔር ለዝንጉዎች ደስታ የላቸውም ብሏልና » ብሎ መለሰለት ፡፡

መኮንኑም: ሕጻኑን « ሳልጠይቅህ ይህን ያህል ትመልስልኛለህን ? » አለው፡፡

ሕጻኑ ቅዱስ ቂርቆስ: « ገና ከዚህ የሚበዛ ነገር እመልስልሃለሁ » አለው፡፡

መኮንኑም ሕጻኑን: « ስምህ ማን ነው ? » አለው፡፡

ሕጻኑ ቅዱስ ቂርቆስ: « ከንጹህ ዐዘቅት ፤ ከማይለወጥ ከማይጠፋ ውኃ የተገኘ ስሜ #ክርስቲያን መባል ነው » ብሎ መለሰለት ፡፡

/ እኛስ ይህን ብንጠየቅ መልሳችን ምን ይሆን ?? መልሱ ለሁላችን ይቆየን፡፡//

መኮንኑም: « ዳግመኛ እንዳትሞት ስምህን ንገረኝ!? » አለው ።

የከበረ ሕጻን ቅዱስ ቂርቆስ: « ስሜ ክርስቲያን መባል እንደሆነ ነገርኩህ ፤ሞክሼ ስም የምትሻ ከሆነ እናቴ የሰየመችኝ ቂርቆስ ነው » አለው፡፡

መኮንኑም: « እሽ በለኝና ለአማልክት ሠዋ ፤ በሥጋህም ስታድግ እሾምሃለሁ ፤ በብዙ ወርቅና ብርም አከብርሃለሁ » አለው፡፡

ሕጻኑ ቅዱስ ቂርቆስ: « የሰይጣን መልእክተኛ ለእውነትም ጠላቷ የሆንክ ከእኔ ራቅ አለው » ።

መኮንኑም: « ሰምቶ ተቆጣ ፤ ደሙ እንደ ውኃ እስኪፈስ ቆዳውን እንዲጨምቁትና እንዲገፉት አዘዘ። » የከበረች ኢየሉጣም የልጅዋን ትዕግሥት በዐየች ጊዜ እግዚአብሔርን አመሰገነችው፡፡ «ከዚህ በኃላ መኮንኑ ጨውና ሰናፍጭ አምጥተው በአፍንጮቻቸው እንዲጨምሩባቸው አዘዘ፡፡ » ያን ጊዜ ሕጻኑ ቅዱስ ቂርቆስ « ትዕዛዝህ ለጉረሮዬ ጣፋጭ ሆነ ፤ከማርና ከስኳርም ለአፌ ጣመኝ » ብሎ ጮኸ፡፡

—// ነገረ ቅዱሳን የግቢ ጉባኤ ማስተማርያ መጽሐፍ ክፍል ሦስት //

ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ

20 Jan, 19:36


የምስራች

እነሆ በTikTok በYoutube እናበተለያዩ ሶሻል ሚዲያዎች የምናውቀው ወንድማችን ልጃችን መምህራችን ዲያቆን ዘላለም ታየ በቴሌግራም መጥቷል ትምህርቶችን እንዲሁም እርሱ የሚጽፋቸውን ጦማሮች እንከታል ለህይወት ስንቅ ናቸውና::

Link👉https://t.me/dn_zelalem_taye

ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ

19 Jan, 06:35


ኦርቶዶክስ ኖት ?

ለመሆኑ እስካሁን በቴሌግራም ትልቁን የኦርቶዶክስ ቻናል ተቀላቅለዋል ? ካልተቀላቀሉ አሁኑኑ ይቀላቀሉ ።

➱ የብራና መፃህፍት በpdf ፣
➱ የታላላቅ መምህራን ስብከቶች በቮይስ ፣
➱ አስተማሪ ፅሁፎች ፣
➱ መንፈሳዊ ግጥምና ልቦለዶች ፣
➱ መንፈሳዊ ፊልሞች ፣
➱ ኦርቶዶክሳዊ መዝሙሮች ይቀርቡበታል።
ኦርቶዶክሳዊ የሆነ ሁሉ ሊቀላቀለው የሚገባ ቻናል ነው።

◤◢◤◢◤◢◣◥◣◥◣◥
█ 🇯 🇴 🇮 🇳  █
◣◥◣◥◣◥◤◢◤◢◤◢

ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ

16 Jan, 19:02


እኛ ስንት ክፍል ቤት ውስጥ እንኖራለን? አንድ ክፍል እንኳን ብንል ስንት ቤተሰብ ነን? ቢበዛ 10 ነው!

በሜቄዶንያ በአንድ ክፍል ውስጥ ከ7ዐዐ በላይ አረጋውያን ይኖራሉ:: ሌላ ሕመማቸውን ትተን በዚህ ሁኔታ መኖር ብቻ የሚያመጣው ብዙ ሕመም አለ::

የካቲት 1 የሜቄዶንያን ሕንፃ ለመጨረስ በሰይፉ ኦን ኢቢኤስ የዩቲዩብ ቻናል ላይ እንዘምታለን:: በዚህም ትልቁን ሆስፒታልና የአረጋውያን ማረፊያ እንሠራለን!

ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን በቂ ነው!

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ

የመቄዶንያ የክብር አምባሳደር

ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ

08 Jan, 18:17


ልደቱም እንደ ሰው ልደት አይደለም!


ከሰው ባሕርይ ጋር አይመሳሰልምና ልደቱም እንደ ሰው ልደት አይደለምና ረቂቅ ምሥጢር ነው አይመረመርም። እርሱን መመርመር ከቻልንና ካወቅንስ ረቂቅ የሚሆን የእርሱን ገናናነት በአጐደልን ነበር፤ ነገር ግን ከቻልን የሥጋዊውን ምሥጢር እናውቅ ዘንድ እንመርምር፤ ይህም ከልብ የሕሊና መገኘት ነው፤ እንደምን ነው? ወይም የፍጡራንን ተፈጥሮ እናወቅ ዘንድ እንመርምር ከአንደበት የቃል መገኘትስ ምን ይመስላል? በእኛ ባሕርይ ያሉ እሊህን ማወቅ ከአልተቻለን ሕሊናት የማይመረምሩት ያልተፈጠረ የፈጣሪን ምሥጢር እንደምን እናውቃለን?

ይህን ምሥጢር ያውቅ ዘንድ ለሰው ቢገባው ኖሮስ አንድነቱን ሦስትነቱን የተናገረ ወንጌላዊ ዮሐንስ እግዚአብሔርንስ ፈጽሞ ያየው የለም ባላለም ነበር፤ ማንም ፈጽሞ የማያየውን በማን እንመስለዋለን? ከአብ የተወለደውን ልደትሰ ዛሬ እናውቅ ዘንድ እንደምን እንመረምራልን?

ልደቱ እንደምንም እንደሆነ ለማወቅ አያስተላልፈንም፤ ከነቅዕ እንደሚገኝ ነቅዕ ከብርሃን እንደሚገኝ ብርሃን፤ ከቀዳማዊ አብ የተገኘ ቀዳማዊ ወልድ ከፍጡራን ሁሉ አስቀድሞ የነበረ ነውና።  ከእመቤታችን ከንጽሕት ድንግል ማርያም ሥጋችንን ነሥቶ የተዋሐደው እርሱ ነው፤ ሥጋ ከመሆን በቀር ያለመለየት ያለመለወጥ ከአብ ጋር አንድ ነው፤ በሥጋም ያለመለየት ከእኛ ጋር አንድ ነው።

— የአበው ሃይማኖት ቅዱስ ጎርጎርዮስ እንደተናገረው


ማስረጃ : ኢሳ ፵፥፳፭። መዝ ፹፱ (፹፰)፥፮። ግብ፡ሐዋ ፲፯፥፳፱። ዮሐ ፲፮፥፳፯ እና ፳፰ ፤ ኢሳ ፵፭፥፲፭። ሮሜ ፲፩፥፴፫-፴፭ ፤ ኢሳ ፵፥፲፰-፳፭። ዮሐ ፩፥፲፰። ግብ፡ ሐዋ ፲፯፥፳፱ ፤  መዝ ፻፲ (፻፱)፥፫ ፤ ዮሐ ፩፥፩-፲፬። ፰፥፲፪። ፲፪፥፴፭። ፩፡ዮሐ ፪፥፰። ቈላ ፩፥፲፭፥፲፯።

« በዚች የእርቅ ሌሊት ማንም በቁጣና በቂም አይሁን። ሁሉንም ጸጥ ባደረገች በዚች ሌሊት የሚያስፈራራና የሚያውክ አይኑር። ይህች  ሌሊት ከጣፌጩ ናትና መራራና አስቀያሚ የሆነ ሁሉ አይገኝባት። ለትሁታን በሆነች በዚች ሌሊት ትዕቢተኛና ራሱን ከፍ ከፍ የሚያደርግ አይኑር። በዚች የይቅርታ ቀን የሌሎችን ስህተትና መተላለፍ አናስብ።

በዚች የደስታ ቀን ቁጣን አናስፋፍ። በዚች እጅግ ጣፋጭ በሆነች ሌሊት ክፉዎችና መራራዎች አንሁን። የሰላም እረፍት በተገኘባት በዚች እለት በሁከት የተሞላን አንሁን። በዚች እግዚአብሔር ወደ ኃጢአተኞች በመጣባት ቀን ኃጢአተኞችን የምናስወጣ የምንገፋ አንሁን። እነሆ ጌታ ወደ አገልጋዮች በመጣባት በዚች ቀን ጌቶች ለአገልጋዮቻቸው በፍቅር ይታዘዙላቸው። ለእኛ ሲል ሁሉ በእጁ የሆነ ባዕለጸጋ  አምላክ ወደ እኛ ወደ ድሆች  በመጣባት በዚች እለት ባዕለጸጎች ድሆችን በማዕዳቸው አብረው ይቀመጡ ዘንድ ይጋብዟቸው።

ሳንጠይቅ ታላቁ ስጦታ ወደኛ በመጣባት በዚች ሌሊት እጃቸውን ዘርግተው በእንባ ለሚማጸኑን ሁሉ እጃችንን ለምጿት እንዘርጋ። በላይ በአርያም ለጸሎታችን በሮች በተከፈቱባት በዚች ዕለት እኛም ለበደሉንና ይቅርታ አድርጉልን ብለው ለሚማጸኑን የይቅርታ ልቡናችንን እንክፈት። »

                              ቅዱስ ኤፍሬም

እንኳን አደረሰን አደረሳችሁ!!

ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ

02 Jan, 10:58


«ተክለ ሃይማኖት ሆይ፤ የስምህ የመነሻ ፊደሉ ትእምርተ መስቀል ለሆነው ስም አጠራርህ ሰላም እላለሁ። እሱም ገናና ና የከበረ ስም ነው።»

መልክአ ተክለሃይማኖት

ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ

31 Dec, 19:22


ማርያምን አለመውደድ ትችላለህ?

አንድ ቀን ንስሐ አባቴ ላይ ምክር ለማግኘት ወደ ቤተክርስቲያን መንገዴን አቀናሁ ንስሐ አባቴም ከቤተ ክርስቲያን ደጃፍ ቁጭ ብለው ዳዊት ይደግማሉ በእድሜም ያረጁ ስለነበሩ ለረጅም ጊዜ መቆም አይችሉም:: እኔም ጸሎታቸውን እስኪጨርሱ ድረስ ራቅ ብዬ መጠበቅ ጀመርኩ እኔም በሃሳብ ከአንዱ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ እየተንከራተትኩ ከቆየሁ በኋላም ንስሐ አባቴ ከሩቅ አይተውኝ ነበርና ጠሩኝ እኔም ከሃሳቤ ደንግጬ ተነሳሁና ወደ እሳቸው መሄድ ጀመርኩ እሳቸው ጋር ደርሼም መስቀል ተሳለምኩ ከቤተክርስቲያኗ ከአንዲት ዛፍ ስር ቁጭ አሉና ከእግራቸው ስር እንድቀመጥ ጋበዙኝ እኔ ሄድኩ እና ቁጭ አልኩ እሳቸውም ፌቴን አዩና ልመከር እንደመጣሁ ስለገባቸው ምክራቸውን ጀመሩ እኔም ፌቴ ቀስ በቀስ እየፈካ ከሄደ በኋላ አዩኝና እኔ ግን አሉ የሚያስደንቅ ነገር ሊነግሩኝ እንደሆነ አውቄ ለመስማት ተዘጋጀሁ:- እሳቸውም ቀጠሉ

"እኔ ማርያምን ለመውደድ ምንም አይነት የመጽሐፍ ቅዱስ ማስረጃ አያስፈልገኝም::

እኔ ከእናቴ ተለይቼ ትምህርቴን ስማር ከጎኔ እሷ ነበረች:: ሲርበኝ በስሟ ለምኜ ሲከፋኝ ከስዕሏ ስር አልቅሼ እውቀት እንቢ ሲለኝ ለአባ ሕርያቆስ ለአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ የገለጽሽ እመ ብርሃን የጌታዬ እናት ስላት አትዘገይም ስለምን እንኳን ውሻ እንዳይነክሰኝ ሰላም ለኪ እያልኩ እጠራታለሁ በእርሷ ምን ያላለፍኩት ነገር አለ:: ሲናገሩ ፍቅራቸው ምን አይነት እንደሆነ መነበብ ይችላል::

እኔ ከእርሷ በላይ እናት አላውቅም ለሁሉም አንድ አይነት እንዴውም እኮ አስተውለን ከሆነ እኛ ካህናት አሁን እንኳን ደሞዝ ተከፍሎኝ ህይወቴን የምመራው በማህሌቱ ማርያም ማርያም እያልኩ ነው::
በነፍሴ ደግሞ ከጌታዬ ከፊቱ መቆምን ሳፍር እናቴ የጌታዬ እናት የአምላኪዬ እናት ከልጅሽ አስታርቂኝ እናቴ እላታለሁ ከዚያም እና እናቴ ማርያምን አለመውደድ እችላለሁ? የአምላክ እናት ሆና የእኔ እናት መሆንን ያላፈረች ማርያምን እንዴት አለመውደድ እችላለሁ??
አሉኝ ከዚያም መጨረሻ ላይ ልጄ ከጸለይክ አይቀር መጨረሻ ላይ እንዲህ በል አቤቱ አምላኪዬ ሆይ የእናትህን ፍቅር ጨምርልኝ ብለህ ጸልይ አሉኝ:: በስተመጨረሻም ተሳልሜ ወደቤቴ ጉዞዬን አቀናሁ::……
"

ዲያቆን አክሊሉ ደርበው
ቅዱስ ማርቆስ
21/04/2017 ዓ.ም

ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ

31 Dec, 03:33


https://youtu.be/U8_9-0Ncpn4?si=rZNneG9ucuI8VyIz

ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ

29 Dec, 15:28


የምስራች

እነሆ በTikTok በYoutube እናበተለያዩ ሶሻል ሚዲያዎች የምናውቀው ወንድማችን ልጃችን መምህራችን ዲያቆን ዘላለም ታየ በቴሌግራም መጥቷል ትምህርቶችን እንዲሁም እርሱ የሚጽፋቸውን ጦማሮች እንከታል ለህይወት ስንቅ ናቸውና::

Link👉https://t.me/dn_zelalem_taye

ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ

28 Dec, 04:43


​​የቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል

በንጉሥ ናቡከደነፆር ዘመነ መንግሥት እስራኤላውያንን በባቢሎናውያን ቅኝ ግዛት ሥር በወደቁበት ጊዜ ከአይሁድ ወገን የሆኑ አዛርያ፣ አናንያ እና ሚሳኤል የተባሉ ሦስት ሕፃናትም ተማርከው በባርነት ተወሰዱ፡፡ ንጉሡም መልካቸው ያመረ፣ የንጉሣዊና የመሳፍንት ልጆች የሆኑትን መርጦ ሥነ ጥበብ፣ የመንግሥት አስተዳደርና የባቢሎናውያን ቋንቋዎችን እንዲሠለጥኑ ለማድረግ በቤተ መንግሥቱ አስቀመጦ ይቀልባቸው ጀመር፡፡ ሦስቱ ሕፃናት ግን እርሱን በመንቀፍ የንጉሡ አገልጋይ ጥራጥሬና ውኃ ብቻ እንዲሰጣቸው በማሰማን ለፈጣሪያቸው ታምነው ለዐሥር ቀናት ቆዩ፤ በኋላም ሲታዩ ጮማ ከሚበሉትና ጠጅ ከሚጠቱት ይልቅ ያምሩ ነበር፡፡ (መዝገበ ታሪክ ገጽ ፻፯)

ከዚህ በኋላም ወጣት ምርኮኖቹ በሙሉ ወደ ንጉሥ ናቡከደነፆር ፊት ቀርበው ዕውቀታቸው በተለካበት ጊዜ ሦስቱ ሕፃናት ጥበባቸውና ማስተዋላቸው ከሌሎቹ እጅጉን በልጦ ተገኘ፡፡ በዚህም ንጉሡ በዚህ ነገር በመደነቅ በሦስት አውራጃዎች ላይ ሾማቸው፡፡ በዚህም ጊዜ ባቢሎናውያን በሕፃናቱ መመረጥና መሾም ከመቅናታቸው የተነሣ ከንጉሡ ጋር ቀንተው ለማጣላት፣ ንጉሡ ወዳጅና ጠላቱን ይለዩ ዘንድ ራሱን የሚመስል ምስል ሠርቶ እንዲያቆም መከሩት፡፡ እርሱም  ምክራቸውን ተቀብሎ ‹‹ቁመቱ ስድሳ ክንድ፣ ወርዱም ስድስት ክንድ የሆነ ወርቅ ምስል አሠራ፤ በባቢሎንም አውራጃ በዱራ ሜዳ አቆመው፡፡ መኳንንትንና ሹሞችን፥ አዛዦችንና አዛውንቶችን፥ በጅሮንዶችንና አማካሪዎችን፥ መጋቢዎችንም፥ አውራጃ ገዢዎችንም ሁሉ ይሰበሰቡ ዘንድ፥ ንጉሥ ናቡከደነፆርም ላቆመው ምስል ምረቃ ይመጡ ዘንድ ላከ፡፡›› (መዝገበ ታሪክ ገጽ ፻፯-፻፰፣ዳን. ፫፥፩-፪)

አሕዛብ በሙሉም ንጉሡ ለሠራው ምስል ምረቃ ተገኙ፤ ዐዋጅ ነጋሪውም እንዲህ በማለት ተናገረ፤ ‹‹ሕዝቡምና አሕዛብ፥ በልዩ ልዩ ቋንቋም የምትናገሩ ሆይ! ንጉሥ ይላችኋል፥ የመለከትና የእንቢልታን፥ የመሰንቆንና የክራርን፥ የበገናንና የዋሽንትን፥ የዘፈንንም ሁሉ ድምፅ በስማችሁ ጊዜ ወድቃችሁ ንጉሡ ናቡከደነፆር ላቆመው ለወርቅ ምስል ስገዱ፤ ወድቆም የማይሰግድ በዚያን ጊዜ በሚነድድ እሳት እቶን ውስጥ ይጣላል፡፡›› እነርሱም ንጉሡ እንዳዘዘው ማድረግ ጀመሩ፡፡ (ዳን. ፫፥፬-፮)

ሆኖም ግን ሦስቱ ሕፃናት የንጉሥ ናቡከደነፆርን ትእዛዝ እንዳልተቀበሉ ሕዝቡ በሰማ ጊዜ ንጉሡ ጋር ሄደው ከሰሷቸው፡፡ እንዲህም አሉት፤ ‹‹ንጉሥ ሆይ፥… በባቢሎን ሀገሮች ለሚሠራ ሥራ የሾምካቸው፥ ለአይሁድ ወገን የሚሆኑ ትእዛዛትህን እምቢ ያሉ፥ አምላክህን ያላመለኩ፥ ለሠራኸውም ለወርቁ ምስል ያልሰገዱ አዛርያ፣ አናንያ እና ሚሳኤል የተባሉት ሰዎች አሉ›› ብለው ነገሩት፡፡ (ዳን. ፫፥፱-፲፪)

ንጉሡም ይህን ሲሰማ ተቆጥቶ ሦስቱን ሕፃናት ያመጧቸው ዘንድ አዘዘ፤ ካሉበትም ተጠርተውም  ወደ እርሱ ቀረቡ፡፡ እርሱም ስለምን የእርሱን አምላክ የቀረቡትንና እንደቀሩና ላቆመው ምስል ያልሰገዱበትን ምክንያት ጠየቃቸው፡፡ የመለከቱንና የእንቢልታውን፥ የመሰንቆውንና የክራሩን፥ የበገናውንና የዋሽንቱን የዘፈኑንም ሁሉ ድምፅ በሰሙ ጊዜ ወድቀው  ላሠራው ምስል ቢሰግዱ መልካም እንደሆነ፤ ባይሰግዱ ግን በዚያ ጊዜ በሚነድድ እሳት እቶን ውስጥ እንደሚጣሉ ነገራቸው፡፡  እነርሱም እንዲህ ሲሉ መለሱለት፤ ‹‹ናቡከደነፆር ሆይ! በዚህ ነገር እንመልስልህ ዘንድ አንፈልግም፡፡ ንጉሥ ሆይ! እኛ የምናመልከው አምላክ በሰማይ አለ፥ ከሚነድደው ከእሳት እቶን ያድነን ዘንድ ይችላል፤ ከእጅህም ያድነናል፤ ንጉሥ ሆይ! ይህም ባይሆን፥ አማልክትህን እንዳናመልክ፥ ላቆምከውም ለወርቁ ምስል እንዳንሰግድለት ዕወቅ›› አሉት፡፡ (ዳን.፫፥፲፮-፲፰)

ንጉሥ ናቡከደነፆርም እጅጉን ተቆጣ፤ የእቶኑን እሳት ይነድድ ከነበረው ሰባት እጥፍ የሚያቃጥል እንዲሆን ካደረገ በኋላ ሦስቱ ሕፃናትን በዚያ የእሳት ነበልባል ውስጥ አምላካቸው እግዚአብሔርን ከእሳቱ ያወጣቸውም ዘንድ ጸለዩ፤ ወዲያውኑም የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ገብርኤል እሳቱ ወደ ሚነድበት ምድጃ ወርዶ እሳቱን በበትረ መስቀል መታው፡፡ ነበልባሉንም እንደ ቀዝቃዛ ነፋስ አደረገው፤ አናንያ፣ አዛርያና ሚሳኤልም እሳቱ ምንም ሳይነካቸው የራስ ጠጉራቸውን እንኳን ሳይለበልባቸው ዳኑ፤ በእሳቱ ጉድጓድ ውስጥም ያለፍርሃት እየተመለሱ ‹‹የአባቶቻችን ፈጣሪ እግዚአብሔር ይክበር ይመስገን፤ ስሙ የተመሰገነ ነው፤ ለዘለዓለም የከበረ ነው›› እያሉ አመሰገኑት፡፡ (ዳን.፫፥፲፱-፳፫)

ንጉሥ ናቡከደነፆርም የእነርሱን መዳን አይቶና ሲያመሰግኑም ሰምቶ ተደነቀ፤ አማካሪዎቹንም ሦስቱ ሕፃናት ታስረው በእሳት ከተጣሉ በኋላ እንዴት ሊፈቱ እንደቻሉ በመገረም ጠየቃቸው፤ ከአማካሪዎቹ አንዱ ‹‹እኔ የተፈቱ በእሳትም መካከል የሚመላለሱ አራት ሰዎችን በዚያ አያለሁ፤ ምንም የነካቸው የለም፤ የአራተኛውም መልክ የእግዚአብሔርን ልጅ ይመስላል›› አላቸው፡፡ ወደ ምድጃውም ቀርቦ ሦስቱ ሕፃናትን ይወጡ ዘንድ አዘዛቸው፤ እነርሱም ከእሳቱ መካከል ወጡ፡፡ በዚያ የተሰበሰቡት ሁሉም ሰውነታቸውም ጠጉራቸው እንዳልተነካ አዩ፡፡ (ዳን.፫፥፳፭-፳፯)

ንጉሡም በፊታቸው ለእግዚአብሔር ሰገደ፤ ለሕዝቡም ከእግዚአብሔር በስተቀርም ሌላ አማልክት እንዳያመልኩ ለጣዖታትም እንዳይሰግዱ ትእዛዝ አስተላለፈ፡፡ እንዲያውም አናንያ፣ አዛርያንና ሚሳኤልንም ያዳናቸውን አምላክ የስድብን ነገር የሚናገር እንደሚቀጣም አስታወቀ፤ ሦስቱ ሕፃናትን ደግሞ አይሁድን ሁሉ አስገዛላቸው፡፡ (ዳን.፫፥፳፰-፴)

ይህ ድንቅ ተአምር ያደረገው የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ገብርኤል በዕለቱ ታኅሣሥ ፲፱ ዓመታዊ በዓሉ በመላው የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ይከበራል፡፡

አናንያ፣ አዛርያንና ሚሳኤልንም ከእሳት ያወጣቸው አምላክ አሁን ካለንበት ችግር፣ መከራ እና ሥቃይ ያወጣን እንዲሁም ከዘለዓለማዊ እሳት ይታደገን ዘንድ እኛም አማላጅነቱ ተረዳኢነቱ ያስፈልገናልና እንማጸነው፤ በእርሱም ስም እንመጽውት፤ በጎ ምግባርንም አብዝተን እንፈጽም፡፡

ከሃይማኖት ርቀን የምንገኝና ባዕድ አምልኮት የምንፈጽም ሰዎች ደግሞ ለግዑዝ ነገር መገዛት አቁመን ወደ እውነተኛው አምላክ ወደ እግዚአብሔር በንስሓ እንመለስ፤ ቸርነቱን ምሕረቱን እንዲያበዛልን ለእርሱም ተገዝተን እንድንኖር ያበቃን ዘንድም የእርሱ ፈቃድ ይሁንልን፤ እንማጸነው፤ አሜን፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ፦ ማኅበረ ቅዱሳን

ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ

25 Dec, 03:54


ከ60 second በኋላ ሰለሚጠፋ አሁኑኑ 🆗በማድረግ የፈለጉትን የመጽሐፍ ስም 📕 በመንካት የመጽሐፉን pdf 📖 ያግኙ።

ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ

23 Dec, 13:17


https://youtu.be/0lU8-cmTYwc

ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ

19 Dec, 05:30


ልዩ የጉዞ መርሐ ግብር
ወደ ቦሌ ቡልቡላ ፈለገ ዮርዳኖስ ቅዱስ ሚካኤል እና አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም

አዘጋጅ :- አድማስ ግቢ ጉባኤ መገናኛ ካምፓስ
የጉዞ ዋጋ ፦ 300 ብር
      የጉዞው ዋጋ ምሳን ጨምሮ
የጉዞ መነሻ ቀን :- ታህሳስ 20  እሁድ 2017 ዓ.ም
የጉዞ መነሻ ቦታ ፦ የካ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን
መነሻ ሰዓት ፦ ከጠዋቱ 12:00
ለበለጠ መረጃ
      0953932301
      0919373257
     

ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ

18 Dec, 17:50


https://youtu.be/6jKaBJvbg1w?si=lum8j-GYt148sNvm

ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ

14 Dec, 04:07


#ዕለታዊ_መልዕክት

1, ጠንካራ ሰው ሁን ማለት አትውደቅ ማለት አይደለም ወድቀህ መነሳትንም ልመድ ማለት እንጂ!
2. ዝም በል ማለት አትናገር ማለት አይደለም ሌሎችን ለመስማት ጆሮ ስጥ ማለት እንጂ!
3. ሆዳም አትሁን ማለት አትብላ ማለት አይደለም በሰው ሀቅ አትለፍ ማለት እንጂ!
4. አትቆጣ ማለት ስሜት አይኑርህ ማለት አይደለም ከቁጣ ቶሎ ተመለስ ማለት እንጂ!

5. ይቅርታ አድርግ ማለት አልተጎዳህም ፣ አልተናደድክም ማለት አይደለም በሆድህ ቂም መያዝ ሌላ ጉዳት ስለሆነ ነው እንጂ!
6. ጠላትህን ውደድ ማለት ጠላት ጥሩ ነው ማለት አይደለም ከጥላቻ ይልቅ ፍቅር ስለሚያሸንፍ ነው እንጂ!
7. ደስተኛ ሁን ማለት ሁሉ ይኑርህ ምን አይጉደልብህ ማለት አይደለም ባለህ ትንሽ ነገር ቢሆን ደስ ይበልህ ማለት እንጂ!
8. ሥራህን ውደድ ማለት የምትሰራው ሥራ ጥሩ ነው ማለት አይደለም ነገ ጥሩ ሥራ እንዲኖርህ ዛሬ ላይ የምትሰራውን ሥራ ውደድ ማለት እንጂ!


እግዚአብሔር አምላክ ይርዳን !

ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ

09 Dec, 05:05


የተሻለው መንገድ ከመጀመሪያውኑም ከኃጢአት መራቅ ነው፡፡ አድርገነው ከኾነ ደግሞ መበደላችንን መገንዘብና በጥንቃቄ ራሳችንን መለወጥ ነው፡፡ እንደ በደልን ካልታወቀን ግን እንዴት ወደ እግዚአብሔር መጸለይ ይቻለናል? ኃጢአት እንደ ሠራን ካልተገነዘብንስ እንዴት ይቅርታን መለመን ይቻለናል? ኃጢአት የሠራኸው አንተው ራስህ መበደልህን ለማወቅ ፈቃደኛ ካልኾንህ፥ እግዚአብሔርን የምትለምነው ለየትኛው ኃጢአት ይቅር እንዲልህ ነው? አንተ ለማታውቀው ኃጢአትህ ነውን? የበደልህን መጠን ሳታውቅስ እንዴት የይቅርታውን ታላቅነት ማወቅ ይቻልሃል? ስለዚህ ስለ ሠራኸው ኃጢአት አንድ በአንድ ተናገር (ተናዘዝ)፡፡
ይህን ጊዜም ለየትኛው ኃጢአትህ ይቅርታን እንዳገኘህ ዐውቀህ ለቸሩ አምላክህ ምስጋናን ማቅረብ ይቻልሃል፡፡

የማቴዎስ ወንጌል፣ ድርሳን 14፥5  — ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንደተረጎመው

ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ

08 Dec, 17:24


ዐባታችን ቅዱስ ዐግናጥዮሥ ምጥው ለዐንበሣ ዕንዲኽ ዐለ፦ "ለሚበላሽ ምግብም ኾነ ለዚኽ ሕይወት ተድላ ምንም ሥሜት የለኝም፤ ይልቁኑ የእግዚአብሔርን ዕንጀራ ይኽም ከዳዊት ዘር የተገኘውን የኢየሱስ ክርስቶስን ሥጋ፣ ለመጠጥም ደሙን ዕመኛለኹ ይኽም የተወደደና ፈፅሞ የማይበላሽ ነው"

📜[መልዕክት ወደ ሮሜ ሠዎች 7:3]

ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ

07 Dec, 19:34


💕ከዘማሪያን የማንን መዝሙር ማዳመጥ ይ ፈ ል ጋ ሉ ? 🔔 💕

[┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ 💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
[┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ሊቀ መዘምራን ኪነጥበብ 💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ዘማሪ አቤል መክብብ 💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕ዘማሪት ሲስተር ህይወት ተፈራ💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕ዘማሪ ዲያቆን ሙሉቀን ከበደ💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ 💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ዘማሪት ፋሲካ ድንቁ 💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛

🌷👥 የሁሉንም ዘማሪያን መዝሙር ለማግኘት 🔔 👇
🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧

ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ

04 Dec, 19:14


ጭንቀት ውስጥ ላላችሁ

ጌታ ቅርብ ነው። በነገር ሁሉ በጸሎትና በምልጃ ከምስጋና ጋር በእግዚአብሔር ዘንድ ልመናችሁን አስታውቁ እንጂ በአንዳች አትጨነቁ።  ፊል 4:6

ቅዱስ ጳውሎስ ለሰብአ ፊልጵስዩስ መልእክቱን በላከላቸው ጊዜ ይሄንን ቃል ብሏቸው ነበር:: ወእንዘ ተአኵቱ ክሥቱ ስእለተክሙ ኀበ እግዚአብሔር (ስትለምኑ ለእግዚአብሔር አንድ ነገር ገልጣችሁ ንገሩት)

የእኛ ችግራችን የሚያስጨንቀንን ነገር ለእግዚአብሔር መናገር አለመቻላችን ነው:: ሐዋርያው ሲናገር በግልጥ ችግራችሁን ንገሩት አለ:: እንዴት አድርገን ነው ችግራችንን ለእግዚአብሔር የምንነግረው?

ጸሎት
ጸሎት ብሂል ተናግሮ ምስለ እግዚአብሔር (ጸሎት ማለት ከእግዚአብሔር ጋር መነጋገር ማለት ነው) አንድ ቅዱስ እንዲህ ይላል:-
ስትጸልይ አንተ እግዚአብሔርን ታወራዋለህ ቅዱሳት መጻህፍትን ስታነብ ደግሞ እግዚአብሔር አንተን ያናግርሃል:: እኛ በጸሎታችን ውስጥ የምናስበውን ሃሳብ ሁሉ ለእግዚአብሔር የምንነግርበት መንገድ ነው ከዚህ በተጨማሪ አንባቢው ማስተዋል ያለበት ነገር እግዚአብሔር የጸለይነውን ጸሎት ሁሉ የሚሰማን እንዳይመስላችሁ እንዲሁ አባት ለልጁ የሚሰጠውን ያውቃልና እግዚአብሔርም የሚያስፈልገንን ነው እንጂ የሚሰጠን እኛ የፈለግነውን አይደለም በዚህም መጽሐፍ እንዲህ ይላል:- የሰው ልጅ ተጨንቆ ተጠቦ ካሰበው (ካቀደው) እቅድ ይልቅ እግዚአብሔር ተሞኝቶ ያሰበው ይበልጣል እንዳለ (አስተውል ተሞኝቶ ሲል በሰውኛ ዘይቤ ሲነገር ነው እንጂ እግዚአብሔር የሚሞኝ አምላክ ሆኖ አይደለም)
ስለዚህ በጸሎት ችግሮቻችንን ለእግዚአብሔር የምናቀርብበት ዋነኛው መንገድ ነው::

አስተውል
እግዚአብሔር ጸሎትን ሁሉ ይሰማል በተበታተነ አዕምሮ ውስጥ ሆነን እንኳን ብንጸልይ እግዚአብሔር ይሰማል በዚህ ውስጥ ሆነን ግን እኛ በተበታተነ አዕምሮ ውስጥ ሆነን ስንጸልይ ጽድቅ አድርጎ የሚወስድልን አይምሮአችንን ለመሰብሰብ የምናደርገውን ጥረት ተመልክቶ ለዚህ ዋጋ ይሰጣል:: ሶስት ነገሮችን እናስተውል እኛ እግዚአብሔርን ስንለምነው ቶሎ ከሰጠን እምነታችንን ሊያጠነክርልን ነው:: ከዘገየ ደግሞ ትዕግስትን እያለማመደን ነው:: ጭራሹኑ ካልሰጠን ደግሞ የለመነው ነገር ለእኛ አይጠቅመንም ማለት ነው ከዛ የተሻለ ነገር እግዚአብሔር አስቀምጦልናል ማለት ነው እኛ ግን በዚህ ውስጥ ሳንታክን ሳንሰለች ሳንሳቀቅ ሁልጊዜ እግዚአብሔርን በጸሎት መለመን ነው:: ልክ ሊቁ እንዳለው ሰይጣን አንተን ኃጢአት ቢያሰራህ ቢያሰራህ አይረካም ነገር ግን ሰይጣን የሚረካው ተስፋ ስንቆርጥለት ነው:: ስለዚህ አንድ ነሳሂ ኃጥዕ እኔ ሌባ ነኝ እኔ ዘማዊ ነኝ እኔ…… ነኝ እግዚአብሔር መቼም ይቅር አይለኝም ብሎ ማሰብ ነውር ነው:: በምውጽሐፍም እንዲህ ይላል:- ስለዚህ እንዲህ በላቸው፦ የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ወደ እኔ ተመለሱ፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር፥ እኔም ወደ እናንተ እመለሳለሁ፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር። ዘካ 1:3 ስለዚህ በፍጹም ልብ ወደ እግዚአብሔር መመለስ ነው::

ዲያቆን አክሊሉ ደርበው
25/03/2017 ዓ.ም
ደብረ ማርቆስ

ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ

02 Dec, 08:09


ልጄ ሆይ በክርስትናህ መጎልመስ ከፈለክ ከቅዱሳት መጻሕፍት ጋር ራስህን አዛምድ።

          —  ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ

01 Dec, 18:24


“የጋለ ብረትን ለመቀጥቀጥ የሚነሣ ሰው አስቀድሞ በብረቱ ምን ለመሥራት እንዳሰበ መወሰን አለበት፤ መጥረቢያ፥ ሰይፍ፥ ወይስ ማጭድ? እኛም በምን ዓይነት የሕይወት መስመር ፍሬ ለማፍራት እንዳሰብን አስቀድመን ልቡናችንን ማዘጋጀት አለብን፡፡”

አባ እንጦንስ

ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ

01 Dec, 10:41


የክርስቲያኖች ሀይል🙏

✍️ አሁን ባለንበት ዘመን ትልቅ ኃይል አላቸው የምንላቸው ብዙ ነገሮች አሉ። እንዲሁም በጦርነት ዓለም በዋነኝነት ከሚጠቀሱት ትልቅ ኃይል መካከል Nuclear Bomb ነው።

መጽሐፍ  ቅዱስ ሲነግረን፦
ያዕቆብ 5
¹⁷ ኤልያስ እንደ እኛ የሆነ ሰው ነበረ፥ ዝናብም እንዳይዘንብ አጥብቆ ጸለየ፥ በምድርም ላይ ሦስት ዓመት ከስድስት ወር አልዘነበም፤ ሁለተኛም ጸለየ፥
¹⁸ ሰማዩም ዝናብን ሰጠ ምድሪቱም ፍሬዋን አበቀለች።


ከጸሎት ውጪ ሰማይ የሚከፍት ሰማይ የሚዘጋ ምንም ኃይል አላየንም።

ስለዚህ ከNuclear Bomb እና ከሌሎች ኃይሎች የጠነከረ ታላቅ ኃይል አለ እርሱም ጸሎት ነው!

“ወደ ፈተና እንዳትገቡ ትጉና ጸልዩ፤።”
  — ማቴዎስ 26፥41
ለምኑ፥ ይሰጣችሁማል፤ ፈልጉ፥ ታገኙማላችሁ፤ መዝጊያን አንኳኩ፥ ይከፈትላችሁማል።”
  — ማቴዎስ 7፥7
አምናችሁም በጸሎት የምትለምኑትን ሁሉ ትቀበላላችሁ ።”
  — ማቴዎስ 21፥22
“ማናቸውንም ነገር በስሜ ብትለምኑ እኔ አደርገዋለሁ።”
  — ዮሐንስ 14፥14

                

ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ

26 Nov, 16:17


ንስሐ


ወንድሞቼ ሆይ! ጊዜ ሳለልን #ንስሐ እንግባና ለንስሐ የሚገባ ፍሬ እናፍራ፡፡ ጌታችን ምን እንዳለ እስኪ አድምጡ፡- “ንስሐ
ከማያስፈልጋቸው ከዘጠና ዘጠኝ ጻድቃን ይልቅ ንስሐ በሚገባ በአንድ ኃጢአተኛ በሰማይ ደስታ ይኾናል” /ሉቃ.15፡7/፡፡

ወንድሞቼ ሆይ! ስለምን ታድያ በኃጢአት፣ በስንፍና፣ በንዝህላል እንደተያዘዝን እንቆያለን? ስለምንድነው ተስፋ ቆርጠን የምንቆዝመው? በእኛ ንስሐ መግባት ምክንያት በሰማያት ታላቅ ደስታ የሚሆን ከሆነ ምንድነው የሚያስፈራን? ቅዱሳን መላዕክት ስለ እኛ ንስሐ እጅግ ደስ የሚላቸው ከሆነ ስለምንድነው እኛ ልል ዘሊል፣ ደንታ ቢስና ፈዛዛ የምንሆነው? የመላዕክት ጌታ ንስሐ ግቡ እያለ አስተምሮን ሳለ ምንድነው የምንፈራው? የማይከፈሉ ሦስት፣ የማይጠቀለሉ አንድ የሚሆኑ ሥላሴ ንስሐ እንገባ ዘንድ እየጠሩን ሳለ እኛ ያለምንም የንስሐ ፍሬ እንቆይ ዘንድ አግባብ ነውን?

ተወዳጆች ሆይ! በዚህ ጊዜአዊ ዓለም ርኵሰት ጣዕም አንታለል፡፡ እንዲህ ካልሆነ ግን እሳቱ የማይጠፋ ትሉ የማያንቀላፋ ምረረ ገሃነም ይጠብቀናል፡፡ ስለዚህ ከዘለዓለማዊው እሳት እንድን ዘንድ አሁን ጥቂት ብናለቅስ ይሻለናል፡፡

ተወዳጆች ሆይ! እስኪ እናስተውል፡፡ ስለምንናገረው ነገርም ችላ የሚለው ሰው ከቶ አይገኝ፡፡ ክርስቶስ ድንገት እንደ ብርሃን ብልጭታ ይመጣልና፡፡ ክርስቶስ ድንገት በመጣ ጊዜ በዙፋኑ ላይ ተቀምጦም ለሁሉም እንደየሥራው ሲከፍለው ማየት አያስፈራምን? የዚያን ጊዜ ሁሉም የየራሱን ሸክም ይሸከማል፡፡እያንዳንዱ ሰው በዚህ ምድር የዘራውን ያጭዳል፡፡ ሁሉም ዕራቆቱ ይቆማል፡፡ ሁሉም ወደ ክርስቶስ የፍርድ ዙፋን ይቀርባል፡፡ የዚያን ጊዜ ማንም ማንንም መርዳት አይችልም፡፡ ወንድም ወንድሙን ወይም ጓደኛ ጓደኛውን መርዳት አይችልም፡፡ ወላጆች ልጆቻቸውን መርዳት አይችሉም፡፡ ልጆች ወላጆቻቸውን መርዳት አይችሉም፡፡ ባሎች ሚስቶቻቸውን መርዳት አይችሉም፡፡ ሁሉም በፍርሐትና በረዐድ በመንቀጥቀጥም የእግዚአብሔርን ፍርድ ይጠብቃል እንጂ ማንም ማንንም መርዳት አይችልም፡፡

ወንድሞቼ ሆይ!ታድያ ለምንድነው ጊዜ ሳለልን የምንሰንፈው? ለምንድነው ልል ዘሊል የምንሆነው? ለምንድነው በምግባር በሃይማኖት የማንዘጋጀው? ለምንድነው ጊዜ ሳለልን የማናስተውለው? ለምንድነው ቃለ ሕይወትን ለመስማት የማንቻኰለው? ስለምንድነው ቃለ እግዚአብሔርን የማንሰማው? ስለምንድነው ቃለ ክርስቶስን ችላ የምንለው? ቃሉ በዚያ ሰዓት እንደሚፈርድብን አትገነዘቡምን? ቃለ ነቢያት ቃለ ሐዋርያት በዚያ ሰዓት እንደሚፈርድብን አታውቁምን? ካላወቃችኁ ጌታችን ለደቀ መዛሙርቱ ያላቸውን አድምጡ፡- “የሚሰማችሁ እኔን ይሰማል፤ እናንተንም የጣለ እኔን ይጥላል፤ እኔንም የጣለ የላከኝን ይጥላል” /ሉቃ.10፡16/፡፡ ዳግመኛም በሌላ አንቀጽ እንዲህ ብሏል፡- “የሚጥለኝ ቃሌንም የማይቀበለው ርሱ የሚፈርድበት አለው፤ እኔ የተናገርኩት ቃል ርሱ በመጨረሻው ቀን ይፈርድበታል” /ዮሐ.12፡48/፡፡ በመጨረሻው ቀን የሚፈርድብን ቃሉስ የትኛው ነው? በወንጌሉ እንዲሁም በሐዋርያትና በነቢያት አድሮ የተናገረው ቃሉ፡፡ እንኪያስ ወንድሞቼ ሆይ! ቃሉን ችላ የምንለው አንኹን፡፡ “ሰማይና ምድር ያልፋሉ፤ ቃሌ ግን አያልፍም” ያለውን አንርሳው /ማቴ.24፡35/፡፡

እንኪያስ እጅግ የምወዳችሁ ሆይ! ኑ! አስፈሪው ቀን ሳይመጣ ቃሉን ሰምተን ንስሐ እንግባ፡፡ የእግዚአብሔርን ምሕረት እንቀበል፡፡ እግዚአብሔር ዛሬ ምሕረቱን እንድንቀበል እንዲህ እያለ ያበረታታናልና፡- “እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ ወደ እኔ ኑ፤ እኔም አሳርፋችኋለሁ” ማቴ.11፡28፡፡ በዚህ ቃሉ ትዕግሥተኛው፣ አፍቃሪውና ሰው ወዳጁ ጌታ ሁላችንም እንድን ዘንድ ይጠራናል፡፡ የጠራው የተወሰኑ ሰዎችን ብቻ አይደለም፤.“ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ” ብሎ ሁላችንም እንጂ፡፡ “ባለጸጋም ቢሆን ድኻም ቢሆን ሁሉም ወደ እኔ ይምጣ፡፡ ወደ እኔም የሚመጣውን ከቶ ወደ ውጭ አላወጣውም፡፡ ወደ እኔ የሚመጣውስ ማን ነው ትዕዛዛቴን የሚጠብቀው፤ ቃሌን የሚሰማው፤ በላከኝም የሚያምነው፡፡” የክርስቶስን ቃል ሰምቶ ንስሐ የሚገባው ንስሐም ገብቶ የንስሐን ፍሬ የሚያፈራ ሰው ንዑድ ክቡር ነው፡፡ የማይሰማው ግን እጅግ ጐስቋላ ሰው ነው፡፡ እንዲህ ተብሎ እንደተጻፈ፡- “በሕያው እግዚአብሔር እጅ መውደቅ የሚያስፈራ ነው” /ዕብ.10፡31/፡፡

#ቅዱስ_ኤፍሬም

ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ

24 Nov, 18:09


ከመብል ከመጠጥ ታቅቦ የሚጾም አንድ ሰው በሐሜት የሰዎችን ሥጋ መብላትን ከቀጠለ ይህ ጾም ግብዝነት ነው፡፡

ማር ይስሐቅ

እንኳን አደረሳችሁ ለጾመ ነቢያት

ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ

19 Nov, 19:38


"በሰው ላይ የምንመለከተው የእግዚአብሔር መልክ ነው። የእኛ ሰዓሊ ሲስለን እርሱን እንድንመስል አድርጎ ነው፡፡ የእርሱን ውበት በእኛ ውስጥ ይሰራዋል፡፡

በቀለም ፋንታ በተለያየ መንፈሳዊ በጎነት ያሳምረናል፤ የእግዚአብሔር ምስልና መልክም ከምንም ነገር ጋር ስለማይነጻጸር ሰውም ይህ እውነተኛ መልኩ በመሆኑ ከሌሎች ምድራዊ ነገሮች ጋር አይቀላቀልም፣... ተፈጥሯችንን ያስዋበ እግዚአብሔር ከተጠቀመበት ብሩሽ አንዱ #ፍቅር ነው።

#ቅዱስ_ጎርጎርዮስ_ዘኑሲስ

ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ

18 Nov, 19:05


‹‹በጒብዝናህ ወራት ፈጣሪህን አስብ›› (መክብብ ፲፪፥፩)
መምህር ቢትወደድ ወርቁ

በቅዱሳት መጻሕፍት ወጣትነት ጉብዝና አንዳንዴም ጉልምስና እየተባለ ይጠራል፡፡  የወጣትነት ዕድሜ ብያኔ እንደ የማኅበረሰቡና እንደ የሀገሩ ቢለያይም ሰው ሠርቶ ማግኘት፣ ወድቆ መነሣት፣  የሚችልበት ዕድሜው የጉብዝናው ዕድሜ ነው፡፡ ወጣትነት  /ጉብዝና/  ከመነሻው አያሌ ባሕርያዊ አካላዊና ሥነ ልቡናዊ ለውጦች የሚከሠቱበት የዕድሜ ክልል ነው፡፡
በመሆኑም የሚመለከታቸውን አካላት የቤተ ክርስቲያን መምህራን፣  ወላጆች፣  የቀለም ትምህርት ቤት መምህራን፣  እንዲሁም ወጣቶችን ማዕከል አድርገው የተቋቋሙ የመንግሥት ተቋማት ወጣቶችን ከሥሩ በተገቢው መልኩ ካላስተማሩ የሚከሠተው ሰብአዊና ሀገራዊ ቀውስ ከፍተኛ ይሆናል፡፡  የሀገር ህልውናዋ የሚወሰነው ወጣቶች ላይ በሚሠራው ሥራ ነውና፡፡  የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮችም ፍሬያቸው በዋናነት የሚመዘነው ምን ያህል ወጣቶችን በአገልግሎት ምርታማና ውጤታማ እንደሚሆኑና በነፍሳቸውም ለእግዚአብሔር የሚገዙ እንዲሆኑ አድርገዋል? በሚለው ሚዛን ነው፡፡  ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ  ሲገልጽ ቅዱስ ጴጥሮስን በግልገል የተመሰሉ ሕፃናትንና በበጎች የተመሰሉ አረጋውያንን አሠማራ ሲለው በጠቦት የተመሰሉ ወጣቶችን ግን ጠብቅ ብሎታል፡፡  (ዮሐ. ፳፩፥፲፮)
ወጣቶች መንገዳቸው ከአምላካቸው  ከልዑል እግዚአብሔር ጋር የተስማማ ይሆን ዘንድ በማስተዋል ሊጓዙ ይገባቸዋል፡፡ በማስተዋል መጓዛችን ከሚገለጥባቸው መንገዶች መካከል አንዱና ዋነኛው ደግሞ ፈጣሪያችን ልዑል እግዚአብሔርን በኑሯችን ሁሉ ማሰብ ነው፡፡

እግዚአብሔርን ማሰብ – ከእግዚአብሔር ጋር መኖር

ጠቢቡ ሰለሞን ‹‹በጉብዝናህ ወራት ፈጣህን አስብ›› ብሎ የተናገረው ቃል በወጣትነት ወራት ከአምላካችን ከእግዚአብሔር ጋር እንድንኖር የሚያሳስብ ነው፡፡ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለድኅነተ ዓለም በመስቀል ላይ በተሰቀለ ጊዜ በቀኙ የተሰቀለው ወንበዴ ‹‹ጌታ ሆይ፥ በመንግሥትህ በመጣህ ጊዜ አስበኝ›› ብሎ እንደተማጸነው እናስተውል፡፡  ለዚህ የወንበዴው ጸሎት ጌታችን ‹‹እውነት እልሃለው፥ ዛሬ ከእኔ ጋር በገነት ትኖራለህ›› በማለት ‹‹አስበኝ›› ለሚለው ጸሎት ‹‹ከእኔ ጋር ትኖራለህ›› በማለት ከመለሰለት መልስ እግዚአብሔርን ማሰብ ማለት ከእግዚአብሔር ጋር መኖር ማለት መሆኑን እንረዳለን፡፡  (ሉቃ. ፳፫፥፵፪)
ከእግዚአብሔር ጋር እንኖር ዘንድ የታዘዝን ክርስቲያን ወጣቶች ዛሬ ከማን ጋር እየኖርን ነው? ሐሳባችን፣  ንግግራችንና ተግባራችን የሚገልጸው ከእግዚአብሔር ጋር መኖራችንን ነው? እግዚአብሔርን የሚያስብ ወጣት አኗኗሩ እንደ ቅዱስ ዮሴፍ እግዚአብሔርን በመፍራትና በኑሮው ውጣ ውረድ ሁሉ እግዚአብሔርን አለመዘንጋት ነው፡፡  እግዚአብሔርን መፍራት የጥበብ ሁሉ መጀመሪያ የመልካምነትም ሁሉ መሠረት ነው፡፡ እግዚአብሔርን የሚፈራ ወጣት ዘወትር በማንኛውም ቦታና ሁኔታ አምላኩ ከእርሱ ጋር እንዳለ ስለሚያስብ ሰው አየኝ አላየኝ ብሎ ብቻ ሳይሆን እንደ ዮሴፍ እግዚአብሔርን በማሰብ ከኃጢአት ይሸሻል፡፡  ወጣቱ ቅዱስ ዮሴፍ እግዚአብሔርን በማሰብ ፈጣሪውን ከእርሱ ጋር እንዲሆን አድርጎታልና ትጉህና ውጤታማ ሠራተኛ ሆነ፡፡  ዋዛ ፈዛዛ ሳቅ ስላቅ ከበዛበት፣  ፌዝና ተረብ ከነገሠበት ነገር ራሱን በማራቅ ከዋዛ ፈዛዛ ይልቅ በሥራ መትጋትና ኃላፊነትን በአግባቡ መወጣት ለታላቅነት እንደሚያበቃ በመረዳት ትኩረቱን ሥራው ላይ ያደርግ ነበር፡፡  በዚህም በደረሰበት ሥፍራ ሁሉ እግዚአብሔር ከፍ ከፍ ያደርገው ነበር፡፡  ፍጻሜው የሚያምር ስኬት ላይ ለመድረስ መሠረቱ እግዚአብሔርን መፍራት እንደሆነ የተነገረው ለዚህ ነው፡፡  ዮሴፍ በተደላደለው መንገዱ ከጲጥፋራ ሚስት እግዚአብሔርንም እንዲያሳዝን ለመገፋፋት በዝሙት እንደተፈተነ ሊቀ ነቢያት ሙሴ በዘፍጥረት መጽሐፍ ጽፎልናል፡፡ (ዘፍ. ፴፱፥፰-፱)
እግዚአብሔርን በጉብዝናው በማሰብ ከእግዚአብሔር ጋር ይኖር ስለነበረ ዮሴፍ እንቢ ለኃጢአት አለ፤ ‹‹እነሆ ጌታዬ (አለቃዬ)  በቤቱ ያለውን ምንም ምን የሚያውቀው የለም፡፡  ያለውንም ሁሉ ለእኔ አስረክቦኛል፤  ለዚህ ቤት ከእኔ የሚበልጥ ሰው የለም፤  ሚስቱ ስለሆንሽ ከአንቺም በቀር ያልሰጠኝ ነገር የለም፤  እንዴት ይህን ትልቅ ክፉ ነገር አደርጋለሁ? በእግዚአብሔር ፊት እንዴት ኃጢአትን እሠራለሁ?›› እንዲል፤ (ዘፍ. ፴፱፥፰-፱)
ዛሬ የሰውን ሚስት የሚያባልጉ በሐሰትና በሚያሳስት ንግግር ወደ ዝሙት የሚወስዱ ይህንንም እኩይ ግብራቸውን እንደ ጀብድና ጀግንነት የሚቆጥሩ ወጣቶች መብዛታቸውን ስንመለከት የቅዱስ ዮሴፍ ታላቅነትና እግዚአብሔርን መፍራት እንደሚጎድላቸው እንረዳለን፡፡ ዮሴፍ ሕግ ባልተሰጠበትና ሰዎች በሕገ ልቡና በሚመሩበት በዚያ ዘመን የዝሙትን አስከፊነት መጽሐፍ ሳይጠቀስለት በትውፊት ከአባቶቹ ተምሮ ከዝሙት ሸሸ፡፡  ለራሱም፣ ለአለቃውም፣ ለፈጣሪውም የታመነ መሆኑን በተግባር አስመሠከረ፡፡ የዛሬ ወጣቶች ለምንሠራበት ተቋም፣ ለአለቃችን፣  ለጓደኛችን ታማኞች ነን? የአደራ ጥብቅነት ከሰማይ ርቀት ጋር ተነጻጽሮ በሚነገርበት ማኅበረሰብ መካከል አድገን ታማኞች መሆን አለመቻላችን ምክንያቱ ምን ይሆን? ዮሴፍ ዓለም በኃጢአት ስትፈትነው በወጥመዷ ላለመያዝ እግዚአብሔርን አስቧልና በሐሰት ወንጅለውና ወደ ወህኒ እንዲጣል አድርገው ለመከራ በዳረጉት ጊዜ እግዚአብሔርም እርሱን አሰበው፡፡  በወጣትነት ዘመን እግዚአብሔርን ማሰብ የጉልምስናና የሽምግልና ብሎም ከሞት በኋላ ለሚኖረውም ሕይወት ዋስትና በመሆኑ ጠቢቡ ሰሎሞን ‹‹አፈርም ወደ ነበረበት ምድር ሳይመለስ፥ ነፍስም ወደ ሰጠው ወደ እግዚአብሔር ሳይመለስ ፈጣሪህን አስብ›› ብሎ አስተማረ፡፡ (መክ.፲፪፥፩)
በዓለም ላይ ያሉ ማናቸውንም ነገሮች ያለማቋረጥ ማሰብ አንዱ የሥነ ልቡና ሕመም መነሻ መሆኑን ባለሙያዎቹ ይናገራሉ፡፡  ስለ ባለጠግነት ብቻ የሚያስብ ሰው ሐሳቡ ሳይሳካለት ቀርቶ በድኅነት ቢኖር ወይም ደግሞ ማግኘቱ ተሳክቶለት ዳግም ቢቸገር በሁለቱም ይጎዳል፡፡ የጤናን ነገር ሁሌ በማሰብ የሚኖር ሰው ሕመም በጎበኘው ጊዜ ይፍገመገማል፡፡  ደስታን ብቻ የሚያስብ ሰው ኃዘን በገጠመው ጊዜ ቆሞ መራመድ ያዳግተዋል፡፡ ማግኘትን ብቻ የሚያስብም ማጣትን አይቋቋምም፡፡ እግዚአብሔርን ያለማቋረጥ ሲሔዱም ሲቀመጡም፣ሲበሉም ሲጠጡም፣ ሲሠሩም ሲያርፉም ማሰብ ግን ሕይወትም፣ ጤናም፣ የደስታም ምንጭ ነው፡፡

እግዚአብሔርን ማሰብ – መልካም ነገርን መናገር

ማሰብ ከመናገር ጋር የአንድ ሳንቲም ገጽታ ነው፤ ሰው የሚናገረው ያሰበውን ነውና፡፡  ማሰብና መናገር ያላቸውን አንድነት ልበ አምላክ ነቢዩ ዳዊት ከተናገረው ኃይለ ቃል መረዳት ይቻላል፡፡  ‹‹አቤቱ በድንኳንህ ውስጥ ማን ያድራል? በተቀደሰውም ተራራህ ማን ይኖራል? በቅንነት የሚሄድ ጽድቅንም የሚያደርግ፣ በልቡም እውነትን የሚናገር›› በማለት የተናገረውን ቃል እናስተውል፡፡ ሰው በልቡናው ያስባል እንጂ አይናገርም፤ ሆኖም ግን በአንደበት የሚነገረው በልቡና የታሰበ ነውና በልቡም እውነትን የሚናገር ብሎ ተናገረ፡፡ (መዝ. ፲፬፥፩-፪)

ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ

18 Nov, 19:05


በጉብዝናችን ወራት ፈጣሪያችንን እንድናስብ የሚረዳን አንደበታችን ከክፉ ከልክለን ሽንገላንም ከእኛ አርቀን ሰዎችን የሚያጽናና የሚያረጋጋ መልካም ነገርንም ብቻ ስንናገር ነው፡፡  እግዚአብሔርን የማሰብ አንዱ መገለጫ መልካም ነገር መናገር ነው፡፡  መጽሐፍ ‹‹እግዚአብሔር መልካም ነው›› ብሎ እንደተናገረ ስለ እግዚአብሔር ቸርነት፣ ታላቅነትና መጋቢነት የሚናገር መልካም ነገር ተናገረ፡፡ (ናሆ. ፩፥፯)
እግዚአብሔር ስለሚወደውና ስለሚፈቅደው ነገር ብቻ መናገር እግዚአብሔርን ማሰብ ነው፡፡  ዛሬ ላይ ብዙዎቻችን እግዚአብሔርን ማሰብ ስላቆምን ከአንደበታችን የሚወጣው ቃል ሁሉ ስድብ፣  ትችት፣  ነቀፋ፣ ሐሜት፣ ሽንገላ፣ ተረብና የመሳሰሉት ሆነዋል፡፡  ነቢዩ ዳዊት ‹‹ጉሮሮአቸው የተከፈተ መቃብር ነው፤ በምላሳቸው ሸነገሉ፤ ከከንፈራቸው በታች የእባብ መርዝ አለ፤  አፋቸው መርገምንና መራራን ተሞልቶዋል  …. እግዚአብሔርን መፍራት በዓይናቸው የለም›› ብሎ እንደተናገረው የእኛም ነገር እንዲሁ ሆኗል፡፡ (መዝ. ፲፫፥፬-፮)
እግዚአብሔርን የሚያስብ ወጣት የሚናገረውን ያውቃል፡፡ አንደበቱም የተገራና በመልካም ነገር የተቀመመ ነው፡፡ ሰውን የሚያስደነግጥ፣ የከፋውን የሚያባብስ፣  በወገኖች መካከል ልዩነትን የሚያሰፋና ጠብ የሚጭር ነገር ከአንደበቱ አይወጣም፡፡ እየጮኸ፣ ጎረቤት እያወከ፣ ሰዎችን እያሳቀቀ፣ የሰዎችን ክብር እየነካ፣ በሌላው የአካል መጉደል እያሾፈ አይናገርም፡፡ ‹‹በአፍ ይጠፉ በለፈለፉ›› እንደሚባለውም በአንደበቱ ምክንያት የማይገባውን እየተናገረ በራሱና በማኅበረሰቡም ሆነ በሀገሩ ላይ ጥፋትና መጠፋፋትን አያመጣም፡፡ የምንናገረውን ለማወቅ ፈጣሪያችን ልዑል እግዚአብሔርን እናስብ፡፡  እግዚአብሔርን ማሰብ ስላቆምን ስለተውነውም ሰዎች በድለውንም ይሁን ሳይበድሉን የስድብ ናዳ እናወርድባቸዋለን፡፡  በአንድ ሰው ስሕተት አባቱ፣ እናቱ፣ ወንድሞቹ በመጣበት ነገድ፣ የተወለደበት መንደር ሳይቀረን በስድብ እናጥረገርጋቸዋለን፡፡  እግዚአብሔርን ማሰብ ስላቆምን የምንናገረው እያንዳንዱ ነገር ሰዎች ላይ ምን ዓይነት አሉታዊ ተጽዕኖ እንደሚያሳድር በሀገርም ላይ ምን ዓይነት ጥፋት ይዞ እንደሚመጣ ማስተዋል ተስኖናል፡፡  ጥቂት የማንባል ወጣቶች እግዚአብሔርን ማሰብ እንደሞት ስለምንቆጥረው የሞት ምክንያት የሆኑ አያሌ ነገሮች ከአጠገባችን ቆመዋል፡፡  ሽማግሎዎችን እንሳደባለን፤ አካል በጎደላቸው እንሳለቃለን፤ ችሎታ የጎደለውን እናሸማቅቃለን፤  ከደረስንበት ያልደረሰውን እናቃልላለን፡፡

እግዚአብሔርን  ማሰብ- ከመከራ ሁሉ መዳኛ መንገድ ነው፡፡

ጠቢቡ ሰሎሞን ‹‹በጉብዝናህ ወራት ፈጣሪህን አስብ›› ብሎ የተናገረበትን ምክንያት ሲገልጥ የመጀመሪያ ምክንያት አድርጎ ያቀረበው ‹‹የጭንቀት ቀን ሳይመጣ›› የሚል ነው፡፡ በወጣትነት በልዩ ልዩ ምክንያቶች የሚገጥሙንን የጭንቀት ፈተናዎች የምንወጣው በተለያዩ አደንዛዥ ዕፅ ሱሶች ውስጥ በመደበቅ፣ አልኮል መጠጦችን በማብዛት፣ መፍትሔ ብለን የምንወስዳቸው ሌሎች ችግር አምጪ አማራጮች ውስጥ በመግባትና ሌሎች መሰል ድርጊቶችን በመከወን መሆን የለበትም፡፡ የጭንቀት መድኃኒቱ እግዚአብሔርን ማሰብና እንደ ፈቃዱም መመላለስ ነው፡፡ የወጣትነት ዕድሜ ካለፈ በኋላም ለሚገጥመን የሽምግልና ጭንቀት መድኃኒቱ የወጣትነት ዕድሜን አካሄድ ማስተካከል እንደሆነ የሥነ ልቡና ባለሙያዎችም ሳይቀሩ ይመክራሉ፡፡ ነቢዩ ዳዊት ‹‹ጎልማሳ መንገዱን በምን ያነጻል? ቃልህን በመጠበቅ ነው›› ብሎ እንዳስተማረውም በኋለኛው ዘመን የሚኖረንን መዳረሻ የሠመረና ትርጉም ያለው የሚያደርገው በወጣትነት ዘመናችን ከእግዚአብሔር ጋር እንዲኖረን የምናደርገው መልካም አኗኗር ነው፡፡ በወጣትነት ያልዘሩትን በሽምግልና አያጭዱትም፡፡ በጉብዝና ያላረሙትን በዕርግና አያስተካክሉትም፡፡ (መዝ. ፻፲፰፥፱)
ጠቢቡ ሰሎሞን በጉብዝና ወራት ፈጣሪን የማሰብ ምክንያት አድርጎ ያቀረበው ሌላኛው ምክንያት ‹‹ደስ አያሰኙኝም የምትላቸው ዓመታት ሳይደርሱ፤ ፀሐይና ብርሃን ጨረቃና ከዋክብትም ሳይጨልሙ፥ ደመናትም ከዝናብ በኋላ ሳይመለሱ፤……….አፈርም ወደነበረበት ምድር ሳይመለስ÷ ነፍስም ወደሰጠው ወደ እግዚአብሔር ሳይመለስ ፈጣሪህን አስብ›› የሚል ነው፡፡ በፀሐይ በጨረቃና በከዋክብት የተመሰለ ማግኘት፣ ማሸነፍ፣ ነግዶ ማትረፍ፣ ሮጦ ማምለጥ፣ ወድቆ መነሣት የሚቻልበት የወጣትነት ጊዜ በእርጅና በድካም በደዌና ከፍ ሲልም በሞት ይደመደማል፡፡ በብርሃን ጀምረን በብርሃን፤ በድል ጀምረን በድል እንድንፈጽም ታናሽ የሆነ ጅማሬያችን እጅግ የበዛ እንዲሆን በጉብዝናችን ወራት ፈጣሪያችን ልዑል እግዚአብሔርን በመንገዳችንና በተግባራችን ሁሉ እናስብ፤ ከእርሱ ጋር እንኑር፤ ስለ እርሱም እንናገር!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር

ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ

14 Nov, 06:18


ከኦርቶዶክሳዊ ወጣት ምን እንጠብቅ?
ዲ/ን ታደለ ፈንታው(ዶ/ር)

ክፍል አንድ

ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖታችን የደም ዋጋ ተከፍሎበት፤ ተፈትኖ፣ ነጥሮ፣ ከትውልድ ወደ ትውልድ ተሸጋግሮ በቅብብሎሽ የመጣ እውነተኛ ሃይማኖት ነው፡፡ የዓለማውያን ፍልስፍና፣ ተረት ተረት፣ ድርሰትም፣ የታዋቂ ሰዎች ድንገተኛ ፈጠራም አይደለም፡፡

ቤተ ክርስቲያን በክርስቶስ ደም ላይ ተመሥርታለች እና ተጠብቃ ከትውልድ ወደ ትውልድ እንድትሸጋገርም ወጣቶች የከፈሉት ዋጋ ደማቅ በሆነ በደም ቀለም በቤተ ክርስቲያናችን ቅዱሳት መጻሕፍት የተመዘገበ ነወ፡፡ እንደ ምሳሌም ሊቀ ዲያቆናት ቅዱስ እስጢፋኖስን ማንሣት እንችላለን፡፡ ራሱን ለእግዚአብሔር አሳልፎ በመስጠቱ አይሁድ በድንጋይ ሲወግሩት ሰማያት ተከፍተው የእግዚአብሔርን ዙፋን እስከ ማየት አድርሶታል፤ ምሥጢርም ተገልጦለታልና አቤቱ ይህን ኃጢአት አትቁጠርባቸው” እስከ ማለት አደረሰው፡፡ የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንም ወጣቶች አርአያ ሊያደርጉት ይገባል፡፡ (ሐዋ. ፯፥፶፬-፷)

ከአባቶቻችን፣ ከእናቶቻችን የተቀበልነውን ይህንን የደም ዋጋ የተከፈለበትን እውነተኛ ሃይማኖት እንደ ወጣት በምንኖርበት ዘመን የመጠበቅ፣ የመከላከል፣ የብዙዎች መዳንን የሚሹ፣ በእውነተኛው መንገድ ለመጓዝ የፈቀዱ ሰዎችን እንዲያውቁት፣ እንዲገነዘቡት፣ በሥጋቸውም በነፍሳቸውም እንዲጠቀሙበት ማድረግ የአንድ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ተከታይ ወጣት የሃይማኖት ግዴታ ነው፡፡ እምነታችንም የሚገለጠው ዕለት ዕለት በማኅበረሰቡ መካከል ስንመላለስ በምናሳየው የማይለዋወጥ ባህርይጥሩ ሥነ ምግባር አማካኝነት ነው፡፡ የእኛ ጽናት፣ አቋም፣ ጥንካሬ፣ መንፈሳዊ ሕይወት የሃይማኖታችንን እውነተኛነት ይገልጣል፡፡ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ተከታይ የክርስቶስ መልክ የሚታይበት ሰው ነው፡፡ በክርስቶስም የእግዚአብሔር መልክ በእርሱ ላይ ታትሟልና፡፡

በምንኖርበት ሉላዊ ምድር በዓለም ላይ እንደሚኖር ሰው ተግዳሮቶች አሉብን፡፡ እኒህ ተግዳሮቶች ታስበው ታቅደው እንደሚሠሩ ሁሉ ሰው በመሆናችን፣ ሉላዊውን ዓለም በመጋራታችን ጭምር የሚመጡ እንጂ ክርስቲያን በመሆናችን ምክንያት ብቻ ተለይተው የሚመጡ አይደሉም፡፡ ክርስትናን ለመቃወም ታስበውም ሆነ ሳይታሰቡ የሚወጡ አፋኝ ሕጎች፤ የሉላዊነት ተጽእኖ፣ ኤችአይቪ ኤድስና ሌሎች ተላላፊ በሽታዎች፤ ድህነት፣ የደኅንነት ስጋት፣ ዘረኝነት፣ ያልተስተካከለ እና ሕይወትን የማያሻሽል መሠረቱን አገር በቀል እውቀትን ያላደረገ የተኮረጀ ትምህርት እና የመሳሰሉት ተግዳሮቶች ለአብነት ይጠቀሳሉ፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ በገላትያ መልእክቱ ሲያስተምር እንዲህ ብሏል፡- “እናንተ ለአርነት ተጠርታችኋልና ፤ ብቻ አርነታችሁ ለሥጋ ምክንያትን አይስጥ፤ ነገር ግን በፍቅር እርስ በርሳችሁ እንደ ባሪያዎች ሁኑ፤ ሕግ ሁሉ በአንድ ቃል ይፈጸማልና እርሱም ባልንጀራህን እንደራስህ አድርገህ ውደድ የሚል ነው፡፡ ነገር ግን እርስ በርሳችሁ ብትነካከሱና ብትበላሉ እርስ በርሳችሁ እንዳትጠፋፉ ተጠንቀቁ፡፡” እንዲል(ገላ 5፡13)

ፍቅር የእምነታችን እና ጽናታችን መሠረት

እንደ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አማኝ ተከታይ የእምነታችን ታላቅነት የሚገለጠው ለሌሎች በሚኖረን ፍቅር እና አክብሮት ላይ ነው፡፡ ሕግ ሁሉ በሁለት ምሰሶዎች ላይ የቆመ ነው፡፡ እነርሱም ፍቅረ እግዚአብሔር እና ፍቅረ ቢጽ(የወንድም ፍቅር) ናቸው፡፡ ሰው የሚመለከተውን ወንድሙን፣ የሚመለከታትን እኅቱን የማይወድ ከሆነ የማይመለከተውንና ያላየውን እግዚአብሔርን መውደድ እንደምን ይቻለዋል? ስለዚህ ፍቅራችን በሰው እና በእግዚአብሔር መካከል የቆመች እውነተኛ የሃይማኖታችን መገለጫ ምልክት ናት፡፡ እኛም እውነተኛ የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ እንደመሆናችን፤ በቅዱሳት መጻሕፍትም መሠረትነት ላይ ልንጓዝ ግድ ይለናል፡፡

የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ መገለጫው ፍቅር ደስታ፣ ሰላም፣ ቸርነት በጎነት የዋህት፣ ራስን መግዛት(ገላ. ፭፥፳፪) እንጂ ዝሙት ርኩሰት ፣ መዳራት፣፣ ጣዖትን ማምለክ ምዋርት፣ ጥል፣ ክርክር፣ ቅንዓት፣ ቁጣ አድመኛነት፣ መለያየት፣ መናፍቅነት፣ ምቀኝነት መግደል ስካር ዘፋኝነት (ገላ. ፭፥፳) አይደለምና በቀደሙ በአባቶቻችን የፍቅር መንገድ እንጓዝ፡፡

መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ “መልካሙን ሥራችሁን ተመልክተው በሰማያት ያለውን አባታችሁን ያመሰግኑ ዘንድ ብርሃናችሁ በሰው ሁሉ እንዲሁ ይብራ” እንዳለ(ማቴ ፭፥፲፫) ከውኃና ከመንፈስ ዳግም ስንወለድ ሀብተ ጸጋ ሀብተ ልጅነት ሆነው የተሰጡን መንፈሳውያን ሀብቶቻችን ይገለጡ ዘንድ ብርሃናችን በዓለሙ ሁሉ ይብራ፡፡ እነዚህም አስቀድመን የገለጥናቸው ናቸው፡፡ ፍቅር የእግዚአብሔር ገንዘብ ነው፡፡ ፍቅር እግዚአብሔርን የምናውቅበት ፍኖት ነው፡፡

ፍቅር እግዚአብሔር የፈጠረውን ፍጥረት፣ ሰው፣ እንስሳ ሳንል የምንወድበት መሳሪያ ነው፡፡ ፍቅር ተፈጥሮአችንን የምናድስበት ነው፡፡ ፍቅር ጉድለታችንን የምንሞላበት መዝገብ ነው፡፡ ፍቅር የተጣመመን ሰብእና የምናርቅበት መዶሻ ነው፡፡ ፍቅርን ተከትለው የሚመጡ ሌሎች ሀብታት አሉ እንጂ ፍቅር ብቻውን የሚመጣ አይደለም፡፡ ፍቅር፡– ሰላምን፣ ደስታን ያስከትላል፡፡ ርኅራኄ እና ለጋስነት ያጅቡታል፡፡ ፍቅር ማደሪያውን ትሕትናን እና ራስን መግዛትን ያደርጋል፡፡

እንደ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት አማኝ የሚጠበቅብን ብዙ ነገር አለ፡- አስቀድመን በገለጽናቸው መንፈሳዊ ሀብታት መኖር እና ማደግ ዕድገታችንም ዕለት በዕለት ያለ ድካም፣ ያለ ፍርሃት፣ የሚጨምር ሊሆን ይገባዋል፡፡ እነዚህን ሀብታት ሳንታክት ገንዘብ ልናደርጋቸው የሚገቡ ጠቃሚ ሀብታት ናቸው፡፡ በእነዚህ ሀብታት ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ እንደተናገረ ክርስቶስን እንለብሰዋለን፡፡ የእግዚአብሔር ቤተ መቅደሶችም ተብለን በእውነት ልንጠራ የተገባን እንሆናለን፡፡

ሌሎች ሊኖሩን የሚገቡ ዕሤተ ምግባራት

እንደ ክርስቲያን በሕዝብ እና በአሕዛብ መካከል የምንመላስ የክርስቶስን እውነት የምንመሰክር ደምቀን የምንታይ አጥቢያ ኮከቦች ነን፡፡ አጥቢያ ኮከብ ደምቆ፣ ፈክቶ እና አብርቶ ስለሚኖር ለሁሉ እንደሚታይ እውነተኛ ክርስቲያንም በሰው ሁሉ ፊት የተገለጠ ነው፡፡ የበለጠ ደምቀን እንድንታይ የሚያደርጉን ኦርቶዶክሳዊ ዕሤተ ምግባራት አሉ፡ እነርሱም፡- አርምሞ፣ ሥርዓት፣ ሰላማዊ ኑሮ፣ ዕውቀት፣ ማስተዋል፤ በሕዝብ ተገብቶ ራስን አሳልፎ መስጠት፣ ከግለኝነት መጽዳት፣ በሰዎች ጉዳይ ጣልቃ አለመግባት፣ እና እኒህን የመሳሰሉ ናቸው፡፡ ልንታገሳቸው የማይገቡንም ነገሮች አሉ፡፡ እነርሱም፡- ሞራል ማጣት፣ የነፍስን ቅድስና ገንዘብ አለማድረግ፤ ጣዖትን ማምለክ፣ ጥንቆላ እና ተያያዥ ተግባራትን መውደድ፣ ምቀኝነትን አለመጥላት፣ ጠብንና አምባጓሮን መውደድ፣ ከቁጣ ነጻ አለመሆን፣ በተሰጠን ነገር አለመርካት፣ ራሳችንን ከሌሎች ጋር ማነጻጸር እና የመሳሰሉት ናቸው፡፡ አስቀድመን የዘረዘርናቸውን ነገሮች የምንጠላቸው በሥጋችን ሥቃይን የሚጨምሩብን በነፍሳችንም የሚያስጎዱን እንጂ የሚጠቅሙን ባለመሆናቸው ነው፡፡

በእውነት መንገድ የሚኖር ኦርቶዶክሳዊ ወጣት፡-

ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ

14 Nov, 06:18


በምንመራው ኦርቶዶክሳዊ እውነተኛ ኑሮ ሕይወትን በተወሳሰበ እና ለዓለም በሚመች መልኩ ማድረግ ጣጣው ብዙ ነው፡፡ እኛ እንድንኖር የተፈቀደልን ሕይወት ጸሎት ያጀበው ሕይወት፣ የፍቅር ሕይወት፣ ለጎረቤቶቻችን ለወንድሞቻችንና እኅቶቻችን መልካም ነገርን የማድረግ ሕይወት ከምንም በላይ ለነፍሳችን ድኅነት የሚጠቅመንን ሥራ የመሥራት ሕይወት ነው፡፡ ንቁ ሆነን፣ አለባሰሳችን እንደ ሃይማታችን ሥርዓት ሆኖ፣ ለጸሎት የነቃን፣ የታጠቅን መሆን ይኖርብናል፡፡ እግዚአብሔር አምላክን በቃልም ቢሆን በተግባርም ቢሆን በኀልዮም ቢሆን የሠራነውን ኃጢአት ይቅር ይለን ዘንድ መትጋት ይጠበቅብናል፡፡ እግዚአብሔር ዘወትር በሥራው ከእኛ ጋር ይሆን ዘንድ ይህ የአንድ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ተከታይ የዘወትር ጸሎት ነው፡፡ መሻቱም፣ ፈቃዱም ፣ ውዱም ሁሉም ተጠቅሎ ያለው በዚያ ውስጥ ነው፡፡ መነሻውም መድረሻውም የጸሎት እና የምስጋና ሕይወት ነው፡፡

በዚህ መንገድ የሚኖር ኦርቶዶክሳዊ ወጣት፡- ሕይወቱ ለአንድ የተስተካከለ እና ጤናማ ሕብረተሰብ መኖር ምሰሶ ነው፡፡ የማኅበረሰብ ፍትኅ፣ ደስታ እና ሰላም የሚጠበቀውም በእንዲህ ዓይነት መንገድ አልፈው ማኅበረሰቡን በሚያገለግሉ ወጣቶች እንጂ አፈ ጮሌዎች ፣ ስግብግቦች እና ነገር አዋቂዎች አይደለም፡፡ እንዲህ ዓይነት እዩኝ እዩኝ የሚሉ ከንቱ ሰዎች ማኅበረሰብን መርተው ወደሚፈልገው ዕድገት አያሻግሩም፡፡

ሀብት አስፈላጊ ቢሆንም ኦርቶዶክስ ክርስቲያን የሚኖረው ሀብት ለማግበስበስ፣ ሌሎችን ለመቀማት ወይም ለማስቀናት አይደለም፡፡ ሀብትን ከፈለግነው በአባቶቻችን በእናቶቻችን መንገድ በርግጥ በእውነት እና በቅንነት ብንመላለስ የሚመጣ እንጂ የሚርቅ ነገር አይደለም፡፡ ቅዱስ መጽሐፍ በመጀመሪያ ጽድቁን እና መንግሥቱን ሹ፤ ሥጋን ለሥጋ ነገር ማለማመድ ለአሁኑ ጊዜ ይጠቅማል፤ ሥጋን ለመንፈሳዊ ነገር ማለማመድ ለአሁኑ ጊዜ ለሚመጣውም ጊዜ ይጠቅማል ይላል፡፡

የሚገጥመን ተግዳሮት

በመንፈሳዊ ልምምድ ሳለን የሚገጥመን ተግዳሮት ቀላል አይደለም፡፡ ጠላታችን ዙሪያችንን ይዞራል፡፡ ወጥመዱን ይዘረጋል፡፡ የአጋንንትን ትምህርት በሚያስተምሩ ሰዎች ልባችንን ለመክፈል እንዲሠሩ ያደርጋል፡፡ ነገሮች ለእነርሱ አልጋ በአልጋ ሲሆኑ ለጊዜው ሁሉም ነገረ የተሳካላቸው አስመስሎ፤ የሌለ ነገር እንዳለ አድርጎ ማሣየት የአጋንንት ተግባር ነው፡፡ ከእውነተኛው ሃይማኖታችን ለማስወጣት የማይፈነቅለው ድንጋይ የለም፡፡ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ተከታይ በመሆናችን ሃይማኖታችንን የድኅነት ምንጭ፣ ስብከታችንንም ከንቱ አድርጎ ሊስል ይዳዳዋል፡፡ በእምነት የቀደሙንን ቅዱሳን፤ አሠረ ፍኖት ትተውልን የሄዱ ዋኖቻችንን ድካም ከንቱ ድካም አድርጎ ለመሳል የማይሄድበት ርቀት የለም፡፡ ረብህ የሌላቸውም ምናምንቴ ሰዎች በገበያ እና በፕሮሞሽን ወደፊት አውጥቶ ሰዎች እንዲከተሏቸው ያደርጋል፡፡ የዲያብሎስ ወጥመዱ ብዙ ነው፡፡

የቅዱስ ጳውሎስ ምክር “በቃልና በኑሮ በፍቅርም በእምነትም በንጽሕናም ለሚያምኑት ምሳሌ ሁን እንጂ ማንም ታናሽነትህን አይናቀው፤ እስክመጣ ድረስ ለማንበብና ለመምከር ለማስተማርም ተጠንቀቅ፡፤( ፩ኛ ጢሞ. ፬፥፲፪) የሚል ነው፡፡ ፍቅራችን፣ ራስን መግዛታችን በቃልም በኑሮም ከተገለጠ የወጣትነት ሕይወታችን እጅግ ጣፋጭ፣ ተወዳጅ እና ፍሬ የሚያፈራ ይሆናል፡፡ በእንዲህ ዓይነት የተቀደሰ ሕይወት ስንመላለስ ፈተና ቢገጥመን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ እኛ ሲል የተቀበላቸው በርከት ያሉ መከራዎችን እናስብ፡፡ እርሱን በመልበሳችን ምክንያት ወደ እኛ የመጡ መከራዎች መሆናቸውን በማሰብ ዕለት ዕለት በፈተና እንጸና ዘንድ ሳናቋርጥ እንጸልይ፡፡ ጸሎታችንም መንፈሳዊ ድፍረትን፣ ጥበብን ፣ ማስተዋልን፣ ሰላምን፣ ትዕግሥትን፣ ፍቅርን፣ ትሕትናን በጎ ጤንነትን፣ ሀብትን፣ ረጅም የአገልግሎት ዕድሜን ይሰጠን ዘንድ ነው፡፡ ይቆየን፡፡

ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ

12 Nov, 16:49


መልስ
የሰንበት ቂጣ ሃይማኖታዊና
ትውፊታዊ አንድምታ ምንድን ነው???
በቤተ ክርስቲያን የሚፈጸሙና የሚከናወኑ መንፈሳዊ ተግባራት ሃይማኖታዊ ሥርዓታዊና ትውፊታዊ መነሻ ያላቸው ሰዎችን ወደ ድኅነት የሚያደርሱና የሚያሸጋግሩ ናቸው።

ወደ ጥያቄ ስመጣ የሰንበት ቂጣ ሃይማኖታዊና ትውፊታዊ አንድምታው እንዴት ነው ስንል! በብሉይ ኪዳን ጀምሮ ቤተ እግዚአብሔር (ምኩራብ) ይመጡ የነበሩ ኦሪታውያን (እስራኤል) ያከናውኑት የነበረ ሃይማኖታዊ ትርጉም ያለው ተግባር ነው።
በኋላም በሐዲስ ኪዳን ዘመን
ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሚያስተምርበት ጊዜ ሲማር የዋለው ሕዝብ ትምህርቱን ሰምቶ ወደ ቤቱ ለመሄድ ከመሰናበቱ በፊት ደቀ መዛሙርቱ ቀርበው ያለንበት ቦታ ምድረ በዳ ነውና ሰዓቱም አልፏልና በጊዜ ወደ ከተማ ሂደው ምግባቸውን ገዝተው ይመገቡ ባሉት ጊዜ ጌታ ደቀ መዛሙርቱን እንዲህ አላቸው። “አኮ መፍትው ርኁባኒሆሙ ይሑሩ አላ ሀብዎሙ አንትሙ ዘይበልዑ፦ (በመሸም ጊዜ ደቀ መዛሙርቱ ወደ እርሱ ቀርበው፦ ቦታው ምድረ በዳ ነው አሁንም ሰዓቱ አልፎአል፤ ወደ መንደሮች ሄደው ለራሳቸው ምግብ እንዲገዙ ሕዝቡን አሰናብት፡ አሉት። ኢየሱስም፦ እናንተ የሚበሉትን ስጡአቸው እንጂ ሊሄዱ አያስፈልግም፡ አላቸው። (ማቴ.፲፬፡፲፭) ይላል።

ያንን መነሻና ምክንያት በማድረግ ዛሬም ሥጋውን ደሙን የተቀበሉ ምእመናን ከቅዳሴ በኋላ በቤተ ክርስቲያን እንዲመገቡት የሚዘጋጅ መክፈልት ነው።

የሰንበት ቂጣ የአዘገጃጀት ሥርዓት?
የሚያዘጋጁትና ማዘጋጀት ያለባቸው በእድሜ ገፋ ያሉ መነኮሳይያት እናቶች ሙቀት ልምላሜ የተለያቸው፤ ደም ያደረቁ፤ ጭምቶች የሆኑ ለሌላው አርአያና ምሳሌ መሆን የሚችሉ ነውር ነቀፋ የሌለባቸው መነኮሳይያት ናቸው።

ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ለሚወደውና በመንፈስ ለሚልደው ለደቀ መዝሙሩ ለጢሞቴዎስ ምን ዓይነት ዲያቆናይትን መሾም እንዳለበት ጽፎ በላከለት መልእክቱ ላይ እንዲህ ብሎታል፦ “ባልቴት በመዝገብ ብትጻፍ ዕድሜዋ ከስድሳ ዓመት እንዳያንስ፥ የአንድም ባል ሚስት የነበረች እንድትሆን ያስፈልጋል።
ልጆችን በማሳደግ እንግዶችንም በመቀበል፥ የቅዱሳንንም እግሮች በማጠብ፥ የተጨነቁትንም በመርዳት በጎንም ሥራ ሁሉ በመከተል፥ ይህን መልካም ሥራ በማድረግ የተመሰከረላት ልትሆን ይገባል”። (፩ጢሞ.፭፡፱) ብሎ የሚመርጥበትን መስፈርት አስቀምጦለታል፤ በዚህ መንገድ እንደነዚህ ያሉ እናቶች እንዲያዘጋጁ ይደረጋል።
ነገር ግን በዚህ የዕድሜ ደረጃና መዓርግ የደረሱ ቢታጡና ቢጠፉ ግን ክብረ ንጽሕናቸውን የጠበቁ፣ በድንግልናቸው የታወቁ፣ ጥሩ ስነ ምግባር ያላቸው ደናግል ሴቶች ሊመረጡና የሰንበት ቂጣውን ሊጋግሩ ይችላሉ።
ከመ/ር ፍሬስብሐት ካሳ

ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ

10 Nov, 19:19


የምስራች

እነሆ በTikTok በYoutube እናበተለያዩ ሶሻል ሚዲያዎች የምናውቀው ወንድማችን ልጃችን መምህራችን ዲያቆን ዘላለም ታየ በቴሌግራም መጥቷል ትምህርቶችን እንዲሁም እርሱ የሚጽፋቸውን ጦማሮች እንከታል ለህይወት ስንቅ ናቸውና::

Link👉https://t.me/dn_zelalem_taye

ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ

10 Nov, 18:15


ጭንቀት ~ምን ያህል ከአምላክ መንፈስ እንደራቅን የሚጠቁም ስሜት ነው::

ሰላም ~ ምን ያህል ወደ አምላክ መንፈስ እንደቀረብን የሚናገር ስሜት ነው::

ከፈጠረን አምላክ አስበልጠን ሌላ ነገር ስንፈልግ በውስጣችን ጭንቀት ይፈጠራል::በልባችን ፍርሃት እና ውጥረት ያድራል::

ከሁሉም ነገር አብልጠን የአምላክን መንፈስ ስንፈልግ ሰላም በውስጣችን ይወለዳል::ልባችን በፍቅር እና በደስታ ይሞላል::

ዓለም እና ነገሮቿን ሁሌም ከእኛ ጋር ማድረግ አንችልም::ሰው ..ገንዘብ …ስልጣን ….ዝና እና ወ.ዘ.ተ ምንም ጊዚያዊ ደስታን ቢሰጡም ቶሎቶሎ የመቀያየር ጠባይ አላቸው::ያዝናቸው ስንል ይሄዳሉ::

የማይሄደው እና ምንጊዜም በልባችን የሚኖረው እኛንም እስከመጨረሻ የሚወደን ቅዱሱ የእግዚአብሄር መንፈስ ብቻ ነው::

ገንዘብ ብናገኝ ብናጣ ~ሰው ቢፈልገን ባይፈልገን ~
ጤና ቢኖረን ባይኖረን በቅፅበት በሚለዋወጠው አለም ሁሌም የማይቀያየር አምላካችን ብቻ ነው::

ይህንን አምላክ ከዓለም ያስቀደሙ አለምን ያሸንፋሉ::ለከንቱ ምኞት ውድ ነፍሳቸውን አይሰጡም::በጊዜያዊ ደስታ ዘለዓለማዊውን አምላክ አይለውጡም::
በሚለዋወጠው ዓለም የማይለዋወጥ ግንኙነት ከአምላክ ጋር አድርገዋል::ከጊዚያዊው አብልጠው ዘለዓለማዊውን መርጠዋል::

እርሱ የእውነት መታመን የሚቻልበት ወዳጃቸው ነው::ጥበብ ~ፍቅር ~ሀይል ~ስልጣን ~በረከት ~ሀብት እና ሁሉም ነገር አለው::

ወደዚህ መልካም አምላክ ስንቀርብ እርሱም ወደ እኛ ይቀርባል::ሰላሙንም በልባችን ያኖራል::ጭንቀት እና ፍርሃታችን ይወገዳል::

ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ

08 Nov, 05:01


አህያና ግርዛት

አሁን ሐዲስ ኪዳን ነው:: መገረዝ ግዴታ አይደለም:: ዋናው ጥምቀት ነው:: ባንገረዝ ምንም አይጎድልብንም::  በዚህ ጉዳይ በመጀመሪያዋ ቤተ ክርስቲያን ውዝግብ ተነሣ:: አሕዛብ ሳይገረዙ ኖረዋልና ጸረ ግዝረት ሆኑ:: አይሁድ ደግሞ እንዴት ግዝረት እንተዋለን አሉ::

ወደ ክርስትና የተጠሩት እነዚህ ሁለት ወገኖች ሁለቱም ከራሳቸው አመጣጥ አንጻር እውነት አላቸው:: አሕዛብ የማያውቁትን ነገር መቀበል ሊገደዱ አይችሉም:: ክርስትናም አላስገደዳቸውም:: አይሁድ ደግሞ የኖሩበትን መተው አይችሉም:: ክርስትናም ግዝረትን ባይጠይቅም አልከለከለም::

በመጨረሻ በብዙ ምክር የሐዋርያት ቤተ ክርስቲያን አሕዛብንም ያላገለለ እስራኤልንም ያላቃለለ ውሳኔ ወሰነች:: ውሳኔውን በጥሩ ቃል በመልእክቱ ቅዱስ ጳውሎስ እንዲህ ሲል ገልጾታል::

"ማንም ተገርዞ ሳለ ተጠርቶ እንደ ሆነ፥ ወደ አለመገረዝ አይመለስ፤ ማንም ሳይገረዝ ተጠርቶ እንደ ሆነ አይገረዝ። ... እያንዳንዱ በተጠራበት መጠራት እንደዚሁ ይኑር" 1 ቆሮንቶስ 7:18፣ 20

በዚህ መሠረት ኦሪትን ተቀብለው ተገርዘው ወደ ክርስትና የተጠሩት እስራኤል በመገረዛቸው ይቀጥሉ እንጂ ወደ አለመገረዝ አይመለሱ ተባለላቸው:: ሳይገረዙ የተጠሩት አሕዛብ ግን መገረዝ የእነርሱ ልማድ አልነበረምና አይገረዙ ተባለ:: ይህ ለእስራኤል የተወሰነ ውሳኔም እንደ ኢትዮጵያ ኦሪትን ተቀብላ ለኖረችና ተገርዛ ሳለ የተጠራች (ሐውልቶችዋ ሳይቀር የተገረዘ ወንድን የሚያሳዩባት) ሀገርም ላይ ይጸናል::

ይህ ውሳኔ ለሁሉም እንደ ግዝረት ያሉ ሕግጋት ይሠራል::

"ማንም ተገርዞ ሳለ ተጠርቶ እንደ ሆነ፥ ወደ አለመገረዝ አይመለስ፤ ማንም ሳይገረዝ ተጠርቶ እንደ ሆነ አይገረዝ"

"ማንም አህያ እየበላ ተጠርቶ እንደ ሆነ አህያ ወዳለመብላት አይመለስ ፤ ማንም አህያ ሳይበላ ተጠርቶ እንደሆነም አህያ አይብላ"
(የአህያን ስም በአሳማ በአይጥ በውሻ ወዘተ እየቀየሩ ዐረፍተ ነገር ይሥሩ:: ሃሳቡ ያው ነው) ግዝረትም የማይበሉ ምግቦችም ከ613 የአይሁድ ሕግጋት (The 613 Mitzvot) ውስጥ ናቸው::

እስራኤል በግዝረት ቀጥሉ ሲባሉ ደስ አላቸው አሕዛብም አትገረዙ ሲባል ደስ አላቸው:: ለእስራኤል ሔደህ የአሕዛብን ዜና ብትነግራቸው ምንም እንኩዋን ግዝረት ግድ ባይሆንም ቅር ይላቸዋል:: የአህያ መበላት ዜናም የሚያስደስተው አህያን እንዴት ልንተው እንችላለን ብለው ለተጨነቁ አሕዛብ ብቻ እንጂ ለእኛ ሆድ የሚበጠብጥ ዜና ነው::

ከዚያ ውጪ እንደ ክርስቲያን ብሉ ብለን ልንሰብከው የሚገባን የሕይወት እንጀራ ሥጋ ወደሙ ብቻ ነው::

እያንዳንዱ በተጠራበት መጠራት ይኑር!

ዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ
2017 ዓ.ም.
አዲስ አበባ  ቄራ (የበሬ)

"ለሚሰሙት ጸጋን ይሰጥ ዘንድ፥ እንደሚያስፈልግ ለማነጽ የሚጠቅም ማናቸውም በጎ ቃል እንጂ ክፉ ቃል ከአፋችሁ ከቶ አይውጣ" ኤፌሶን 4:29

ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ

07 Nov, 16:59


👆👆👆 ጠቃሚ ምክር!

ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ "ለደካሞች ትጉላቸው " ብሎ በተናገረው መሠረት ምንጊዜም የሰዎችን ሞራልና መንፈስ ለመጠበቅ እንሞክር። [1ኛ ተሰ 5*14]  አንድን ሰው ሲቆጡት፤ ሲወቅሱትና ፤ትህትናን ሲነፍጉት ብትመለከቱት እርሱን ከጎናችሁ አድርጋችሁ የሚገባውን በእርሱ ስም ተናገሩለት። በእርግጥም ይህ ሰው ይህንን ታላቅ ሥራችሁን በእድሜው ዘመን ሙሉ አይረሳውም። ይህ ማለት ደግሞ በፍቅርና በቸርነት በተሞሉ ታታላላቅ ልቦናዎች መንፈሳቸው ለደከመ ሰዎች የተደረገ ታላቅ ሥራ ነው። በኃጢአት የተተበተበ አንድ ሰው ብታገኙ ከዚህ ነፃ አውጡት እንጂ አትገስጹት።

  በአንድ ወቅት አንድ ወጣት ልጅ የገባበት ውኃ ሊያሰጥመው ሲል ራሱን ለማዳን በመፍጨርጨር ላይ ሳለ በዚያ የሚያልፍ አንድ ሰው "ልጄ ሆይ ዋና ሳትችል እንዴት እዚህ ባሕር ውስጥ ልትገባ ቻልክ! ?" እያለ ሲቆጣው ልጁ "በእርግጥ ተሳስቻለሁ ወደዚህ ባሕር የገባሁበትን ምክንያት እንድነግርህ ግን በመጀመሪያ ከሞት አድነኝ " ብሎ መልሶለታል። እናንተም ልክ እንደዚህ ሰውዬ መሆን የለባችሁም። ማንንም ሰው ሲወድቅ ብትመለከቱት አትገስጹት ይልቁንም። ተስፋ ስጡት። " እኔ ብዙ ጠቃሚ ምክሮች መክሬሃለሁ አንተ ግን አልተጠቀምክባቸውም ስለዚህ ከባድ መከራ ቢደርስብህ አይቆጨኝም " ብለን አንናገር።

   የሐዋርያው ቃል በንቃት አድምጡ። "...... ለደካሞች ትጉላቸው ሰውን ሁሉ ታገሱ" [1ኛ ተሰ 5*14] ። ሥሩን የሰደደ ኃጢአትን ነቅሎ ለመጣል ጊዜና ትዕግስት ስለሚጠይቅ እግዚአብሔር እንደነዚህ ያሉትን ደካሞች በጸጋው እስኪጎበኛቸው ነጻ እስኪያወጣቸው ድረስ ትዕግስት አድርጉላቸው። አንተም ተፈጥሮህ ከእነርሱ ጋር ተመሳሳይ ስለሆነ ከዚህ የሚከተለውን የሐዋርያውን ቃል ዘወትር ከፊትህ አስቀድም። " ከእነርሱ ጋር እንደ ታሰረ ሆናችሁ እስሮችን አስቡ የተጨነቁትን ደግሞ ራሳችሁ ደግሞ በሥጋ እንዳለ ሆናችሁ አስቡ ።[ዕብ 12*3] ።
  #የእግዚአብሔርን_ሕዝብ_ተስፋ_ለማስቆረጥ_የተጉትን_ሰዎች_እግዚአብሔር_ወደ_ተስፋይቱ_ምድር_እንዲገቡ_አልፈቀደላቸውም።
እግዚአብሔር ሕዝቡን ".....በኃይል ከእኛ ይበረታሉና በዚህ ሕዝብ ላይ መውጣት አንችልም...... ያየናቸው ሰዎች ሁሉ ረጃጅም ሰዎች ናቸው. .... እኛም በዓይናችን ግምት እንደ አንበጣዎች ነበርን " በማለት ሊያዳክሙት የነበሩትን ሰዎች ገድቧቸዋል ። [ዘኁ13*31-33]።
  እናንተ ግን አንድ ሰው ኃጢአተኛ ወይም ደካማ ቢሆንም እንኳ በሕይወቱ ውስጥ መልካም ጎኑን በመፈለግ አውጥታችሁ እነዚያ ባሕርያቱን አሞግሱለት። ኢየሱስ ክርስቶስ ለሳምራዊቷ ሴት ያደረገው እንደዚህ ነው። " ባል የለኝም በማለትሽ መልካም ተናገርሽ. ..."በዚህ እውነት ተናገርሽ "[ዮሐ 4*17እና 18] ።ይህ ውዳሴ ሴቲቱ ኃጢአቷን እንድትናዘዝ ስላደረጋት ለንስሓ ትበቃ ዘንድ ጌታ አሸንፏታል። አንዱ ሰው ሌላው ሸክሙን በሚያቀሉለት በቅዱሳት መጻሕፍት ታሪኮች ሲበረታታ ሌላው ደግሞ ስለ እግዚአብሔር ጸጋና ሥራ ሲነገረው ይበረታታል። ከዚህ ሌላ ስህተቶቹን ሁሉ በመርሳት የሚበረታታ ሰው ይኖራል። ለተፈጸመ ስህተት ሁሉ ቁጣን ማቅረብ ግን ወደ ተስፋ መቁረጥ ያደርሳል።
  አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ እንዳስተማሩት! !

ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ

07 Nov, 15:21


የክርስትና ሃይማኖት፦

፩.ከባለቤቱ ለቅዱሳን የተገለጠ
፪.የተቀበልነው
፫.የምንጠብቀው
፬.የምናቀብለው ነው።
በዚህ መንገድ ከሐዋርያት እስከ ዛሬ ደርሰናል። ነገር ግን በክፉ ሥርዓት እና በስንፍናችን ምክንያት ጠባቂም ተቀባይም እያጣ ነው።
በዕቅበተ እምነት ሁኖ በሥጋ መሞት ተፈጥሯዊ ርሥት ነው።በሃይማኖት ደክሞ በነፍስ መሞት ግን ዘለዓለማዊ ደይን ነው።
ቤተ ክርስቲያን ከብዙዎቻችን ጀምሮ ተናጋሪ እንጂ ሠሪ እያጣች ነው።
በተለይም ፍርሀት እና ማስመሰል በጢሟ ሊደፏት ተቃርበዋል።

ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ

06 Nov, 01:10


እራቁቴን አይደለሁም
የለበስኩት ልጅሽን ነው
ሐዘን ደስታ ቢፈራረቅ
የማርያም ልጅ
የማርያም ነው።

ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ

04 Nov, 04:07


      እርዱኝ እረዳችኋለሁ     
አንድ ትልቅ አረጋዊ በረጅም የሽምግልና ዘመናቸው ጆሯቸው ሳይደነግዝ ሁሉን ይሰማሉ፣ዓይናቸው ሳይፈዝ ሁሉን ያያሉ።አንድ ሰው ይጠይቃቸዋል እንዲህ ብሎ፦"አባ እግዚአብሔር ረድቶዎት ነው እንጂ በእርስዎ እድሜ ውስጥ ያሉት እኮ ዓይናቸው ዓያይም ጆሯቸው አይሰማም?" ይላቸዋል።
እሳቸውም፦"ምን እግዚአብሔር ብቻ ይረዳኛል እኔም እግዚአብሔርን ረድቸው ነው እንጂ ወራት እየለየሁ ቅቤ እቀባለሁ፣በፀሐይ አላነብም፣ጨረር አላይም እና እኔስ እየረዳሁት አይደለምን? እግዚአብሔር የሚረዳን ስንረዳው ነው"ይሉታል።
ታዲያ በሀገራችን ብሂልም "እርዱኝ እረዳችኋለሁ ብሏል" እየተባለ ይነገራል።
ይሄንን ሀሳብ ወድጀዋለሁ እግዚአብሔር የነጻነት አምላክ ነው ወደን ፈቅደን የምናደርገውን መልካም ነገር ሁሉ ይባርክልናል።የድርሻችንን ሳንወጣ ግን እርዳን ማለት ትልቅ ስንፍና ነው።
እግዚአብሔር አስገድዶ ምንም ነገር አድርጉ አይለንም። የሚጠቅመንን የሚያጸድቀንን እንድናደርግ ግን ይወዳል።
ቁጭ ብለን እግዚአብሔር ይርዳን ብንል ግን ስንፍናን በሰማይ ሰሌዳ ላይ እንደመጻፍ ነው።
"የተነቃነቀ ጥርስ ቢስቁበት አያደምቅ ቢበሉበት አያደምቅምና"ጠንክረን እንሥራ።
በሆነ ባልሆነው ነገር፦ብእል እንደበላው አቡጄዴ፣ዋግ እንደ መታው ስንዴ መሟሸሽ የወንድ ልጅ ተግባር አይደለም።

ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ

03 Nov, 08:00


የምስራች

እነሆ በTikTok በYoutube እናበተለያዩ ሶሻል ሚዲያዎች የምናውቀው ወንድማችን ልጃችን መምህራችን ዲያቆን ዘላለም ታየ በቴሌግራም መጥቷል ትምህርቶችን እንዲሁም እርሱ የሚጽፋቸውን ጦማሮች እንከታል ለህይወት ስንቅ ናቸውና::

Link👉https://t.me/dn_zelalem_taye

ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ

01 Nov, 17:55


"በጎ ነገር አግኝተህ እንደ ሆነ እግዚአብሔርን አመስግን፤ ያም በጎ ነገር ከአንተ ጋር ጸንቶ ይኖራል፡፡ በጎ ያልሆነ ነገር ደርሶብህ እንደሆነም እግዚአብሔርን አመስግን፤ ያም በጎ ያልሆነ ነገር ወደ በጎ ነገር ይቀየራል፡፡"

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ

29 Oct, 10:00


የምስራች

እነሆ በTikTok በYoutube እናበተለያዩ ሶሻል ሚዲያዎች የምናውቀው ወንድማችን ልጃችን መምህራችን ዲያቆን ዘላለም ታየ በቴሌግራም መጥቷል ትምህርቶችን እንዲሁም እርሱ የሚጽፋቸውን ጦማሮች እንከታል ለህይወት ስንቅ ናቸውና::

Link👉https://t.me/dn_zelalem_taye

ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ

29 Oct, 08:53


ሮሜ 14
¹⁰ አንተም በወንድምህ ላይ ስለ ምን ትፈርዳለህ? ወይስ አንተ ደግሞ ወንድምህን ስለ ምን ትንቃለህ? ሁላችን በክርስቶስ ፍርድ ወንበር ፊት እንቆማለንና።
¹¹ እኔ ሕያው ነኝ፥ ይላል ጌታ፥ ጉልበት ሁሉ ለእኔ ይንበረከካል መላስም ሁሉ እግዚአብሔርን ያመሰግናል ተብሎ ተጽፎአልና።
¹² እንግዲያስ እያንዳንዳችን ስለ ራሳችን ለእግዚአብሔር መልስ እንሰጣለን።
¹³ እንግዲህ ከዛሬ ጀምሮ እርስ በርሳችን አንፈራረድ፤ ይልቁን ግን ለወንድም እንቅፋትን ወይም ማሰናከያን ማንም እንዳያኖርበት !

    ቅዱስ ጳውሎስ

ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ

27 Oct, 16:28


ዘፈን ኃጢዓት ነው::

ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ

25 Oct, 16:34


በከበረች ጸሎቱ ይቅር ይበለንና ራሱን በትሕትና "ከጌቶች ልጆች የሚወድቀውን ፍርፋሪ የሚለምን ውሻ" ብሎ የሚጠራው ሶርያዊው ኮከብ ቅዱስ ኤፍሬም በየድርሰቶቹ መካከል እንዲህ እንዲህ አለ:-

"ጌታችን ከሣምራዊትዋ ሴት ጋር በተነጋገረ ጊዜ በንግግራቸው መጀመሪያ ማንነቱን አልገለጠላትም። መጀመሪያ ያየችው ውኃ የጠማውን ሰው ነበር ፣ ከዚያ አይሁዳዊ ፣ ከዚያ መምህር (ረቢ) ፣ ቀጥሎ ነቢይ ከሁሉም መጨረሻ መሲህ መሆኑን አየች።
ውኃ የተጠማውን ሰው በንግግር ልትረታ ስትሞክር በአይሁዳዊ ላይ ያላትን ጥላቻ አሳየች። ከመምህሩ ጋርም ተከራከረች ፣ ከነቢዩ እግር ስር ተንበረከከች ፣ መሲሁንም ወደደችው"       
ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ (ስለ ሣምራዊቷ ሴት ዮሐ 4:1)

★ ★ ★

"ጌታ ሆይ ለእኛ ፊት ክብርን የሠጠ እንደ አንተ ያለ ማን አለ?
የዕውሩን ዓይን ባበራህለት ጊዜ ላድነው ነህ ብለህ በፊቱ ላይ አልተፋህበትም።
ነገር ግን አርኣያችንን አክብረህ በመሬት ላይ እንትፍ ብለው ፈወስከው።
ጌታዬ ሆይ በእኔ ላይ ግን በፊቴ ላይ እንትፍ በልብኝ ፣ በፈቃዴ ያጠፋሁትን ዓይኔን በፈቃድህ አብራልኝ"
                      
ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ
(ዕውር ሆኖ ስለተወለደው ዮሐ 9:30)

★ ★ ★
"ጌታ ሆይ ዕውሩን ሂድ ብለህ ወደላክህበት ወደ ሰሊሆም መጠመቂያ አሁን ልንሔድ አንችልም።  ነገር ግን ሕይወትንና ብርሃንን የተሞላው የከበረ ደምህ ያለበት ጽዋ በእኛ ዘንድ አለ። ከእርሱ በተቀበልን ቁጥር እንነጻለን"  ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ

★ ★ ★

"ጌታዬ ሆይ በሔድኩበት ውጣውረድ የተሞላ መንገድ እምነቴ ደከመ ፣ መንገዱ የሚወስደኝም በግራ ወደሚቆሙት ፣ በደጅ ቆመው ክፈትልን ሲሉህ "አላውቃችሁም" ከምትላቸው ወገን ልሆን ነው።
ጌታዬ ሆይ እኔ አውቅሃለሁ ፣ አንተ ግን አላውቅህም ትለኝ ይሆን? አቤቱ በአንተ ለማምን ለእኔ ለኃጢአተኛው ራራልኝ።  ብበድልህም እንኳን አሁንም በርህን እያንኳኳሁ ነው። እየተጎተትኩም ቢሆን አሁንም የምጓዘው ወደ አንተ ለመምጣት ነው"
                                      
ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ (ማቴ 7:7)
★ ★ ★

"ጌታ ሆይ እነዚህን በዕድሜ ሕፃናት የሆኑ የመንፈስ ልጆቼን ይቅር በላቸው። ሕፃን የነበርከው ሆይ የሕፃንነትህን ጊዜ አስብ። ልጅነታቸው ያንተን ልጅነት እንዲመስል አድርግላቸውና በቸርነትህ አድናቸው"
                                        ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ

ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ

24 Oct, 05:16


+ ከሁሉ በኋላ ጭንጋፍ ለምሆን ለእኔ ታየኝ +

ቅዱስ ጳውሎስ ለቆሮንቶስ ምእመናን ስለ ጌታ ትንሣኤ ማስረጃ እያቀረበ ነው:: በዚያን ዘመን ለጌታ ትንሣኤ ማስረጃ ስትጠቅስ በማቴዎስ ወንጌል እንዲህ ይላል ብለህ እንዳትጠቅስ ገና ወንጌላት አልተጻፉም:: ቢጻፉም ማቴዎስ በሕይወት እያለ በቃሉ መመስከር ሲችል ጽሑፉን ማስረጃ ማድረግ አያስፈልግህም:: ስለዚህ ለመነሣቱ ማስረጃዎች ከተነሣ በኋላ ያዩት ሰዎች ነበሩ:: በሕይወት ያሉትን የዓይን ምስክሮችን መጥቀስ ይቻላል:: የዓይን እማኞች ምስክርነት ከጽሑፍ በላይ የታሪክ ማስረጃ ነው:: ስለዚህ ጳውሎስ ስለ ጌታ ትንሣኤ "እነ እገሌ አይተውታል" እያለ መዘርዘርን መረጠ::

ጌታ ከተነሣ በኋላ እንደ ቀድሞው ለሁሉ አልታየም:: እርሱን ለማየት የተገባቸው ጥቂት ወደ ሺህ የሚጠጉ ሰዎች ነበሩ:: በማኅበር ያዩት አሉ:: በግል ያዩት አሉ::
ያዩት ነገር ወንጌል የሆነላቸው ብፁዓን ዓይኖች ያሏቸው እንዴት የታደሉ ናቸው? የተሰቀለውን ተነሥቶ ያዩት! ዳግም በሚመጣበት አካል የተገለጠላቸው ምንኛ የታደሉ ናቸው? ከመድኃኔ ዓለም አፍ ተቀብለው ኪዳን ያደረሱ! የጌታን ቅዳሴ ተቀብለው ያስቀደሱ! የትንሣኤው ማግስት ምስክሮች እንዴት ዕድለኞች ናቸው? ቢሞቱም እንኳን መነሣታቸውን በጌታ ትንሣኤ አይተው ደስ ብሎአቸው ያንቀላፉ እነርሱ ምንኛ የታደሉ ናቸው?

ቅዱስ ጳውሎስ በወንጌል ከተጠቀሱት ከነ ኬፋ በተጨማሪ ለይቶ ጌታ ለማን ለማን እንደታየ ገለጸ:: ለያዕቆብ ታየ ብሎ የእልፍዮስን ልጅ ለይቶ ጠቀሰው:: የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ጸሐፍት እንደሚሉት ይህ ሐዋርያ ከሌሎች በተለየ የጌታን ትንሣኤ ሳላይ እህል አልቀምስም ብሎ የተሳለና አክፍሎትን የጀመረ ነበርና ጌታ ለይቶ ክብሩን አሳይቶታል:: ከዚያም ለዐሥራ ሁለቱ ታየ ብሎ የጌታን ድኅረ ትንሣኤ አስተርእዮ ዘረዘረ::  እኔ ማለትን የማይወደው ትሑት ቅዱስ ጳውሎስ "ከሁሉ በኋላ እንደ ጭንጋፍ ለምሆን ለእኔ ደግሞ ታየኝ አለ::

ጭንጋፍ ምንድር ነው? ጭንጋፍ  (ጸዕጻዕ/ ተውራድ) ለፅንስ የሚነገር ቃል ነው:: መወለድ ያለበትን ጊዜ ያልጠበቀ ያለ ጊዜው የተወለደ ፅንስ ነው:: በመጠኑ ከሌላው ጊዜውን ከጠበቀ ፅንስ የሚያንስ ሲሆን ዕድገቱን በተገቢው ጊዜ ከሚወለድ ልጅ ጋር ለማስተካከል ሲባል በሙቀት ማቆያ ክፍል እንዲቆይ ይደረጋል:: ይህ ፅንስ ሲወለድ በሕመም ውስጥ ሆኖ ተሰቃይቶ ተጨንቆ ነው::

ቅዱስ ጳውሎስ ራሱን ለመግለጽ የተጠቀመበት ይህ አንድ ቃል የሕይወት ታሪኩን ጠቅልሎ የያዘ ድንቅ ቃል ነበር::
ቅዱስ ጳውሎስ ምንም እንኳን የቤተ ክርስቲያን ብርሃን የሆነ ሐዋርያ ቢሆንም እንደ ዓሥራ ሁለቱ ሐዋርያት በጊዜው የተጠራ አልነበረም:: እርሱ ከሐዋርያት ጋር አብሮ በዳግም ልደት የተወለደ ሳይሆን ያለ ጊዜው ክርስቶስ ባረገ በስምንተኛው ዓመት የተጠራ ነበረና ራሱን ካለ ጊዜው ከተወለደው ፅንስ ጋር አመሳስሎ እንደ ጭንጋፍ የምሆን ብሎ ጠራ::

ጭንጋፍ ሲወለድ በመጠኑ ከሌላው ፅንስ ያነሰ ይሆናል::
ቅዱስ ጳውሎስም ራሱን ጭንጋፍ ካለ በኋላ "እኔ ከሐዋርያት ሁሉ የማንስ ነኝና፥ የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ስላሳደድሁ ሐዋርያ ተብዬ ልጠራ የማይገባኝ" ብሎ አብራርቶታል:: (1ቆሮ 15:9)

ልጅ ጭንጋፍ ሆኖ ሲወለድ በሥቃይ ነው:: ጤና ያጣል ይታመማል:: እናቲቱም ትታወካለች በድብታ በጭንቀት ትቸገራለች:: ባለሙያዎቹ እንደሚሉት  እናት ያለ ጊዜው ከተወለደ ልጅዋ ጋር እናታዊ ትስስር ለመፍጠርና የእናትነት ፍቅርዋን ለመሥጠት  ባልጠበቀችው ጊዜ የመጣ በመሆኑ ምክንያት ለጥቂት ጊዜ ትቸገራለች:: በአጭሩ ጭንጋፍ ሆኖ ሲወለድ እሱም ይሰቃያል እናቱንም ያስጨንቃል:: ወዲያው እንደሌላ ሕፃን በሰው እጅ አይታቀፍም:: ከተፈጥሮአዊ እስከ ሰው ሠራሽ እንደየጊዜው እየዘመነ በሔደው የልጅ ሙቀት መስጫ መንገድ እየታገዘ የሰውነት አካሎቹ በአግባቡ መሥራት እስከሚችሉና በሽታ መቋቋም እስከሚችል ይቆያል::

ቅዱስ ጳውሎስ እንደ ጭንጋፍ ነበርኩ ያለው ለዚህ ነው:: በዳግም ልደት የተወለደው በደማስቆ መንገድ ወድቆ ሊቋቋመው ባልቻለው ብርሃን ተመትቶ ነበር:: "ሳውል ሳውል ስለምን ታሳድደኛለህ?" የሚል ድምፅ ሲሰማ ፅንስ ነውና ዓይኑን እንኳን መግለጥ አልቻለም ነበር::
ከተወለደ በኋላም ወዲያው ወደ ቤተ ክርስቲያን እቅፍ ወደ ሐዋርያት ማኅበር አልገባም:: እንደ ጭንጋፍ የምሆን እንዳለ ሙቀት ያስፈልገው ነበርና የሰው እጅ ሳያቅፈው ሦስት ዓመት በሱባኤ ቆይቶ በመንፈስ ቅዱስ ተማወቀ::

"ነገር ግን በእናቴ ማኅፀን ሳለሁ የለየኝ በጸጋውም የጠራኝ እግዚአብሔር በአሕዛብ መካከል ስለ እርሱ ወንጌልን እሰብክ ዘንድ ልጁን በእኔ ሁኔታ ሊገልጥ በወደደ ጊዜ፥ ወዲያው ከሥጋና ከደም ጋር አልተማከርሁም፥ ከእኔም በፊት ሐዋርያት ወደ ነበሩት ወደ ኢየሩሳሌም አልወጣሁም፥ ነገር ግን ወደ ዓረብ አገር ሄድሁ እንደ ገናም ወደ ደማስቆ ተመለስሁ። ከሦስት ዓመት በኁዋላ ወደ ኢየሩሳሌም ወጣሁ" ብሎ ስለ መንፈሳዊ ኃይል መልበሱ ይናገራል:: (ገላ 1:15-18)

ጭንጋፍ ሆኖ የተወለደ ልጅ የሚገጥመው ችግር ከወላጆቹ ጋር በሥነ ልቡና ለመተሳሰር መቸገሩ ነው::
ቅዱስ ጳውሎስን ለማመንና እንደ ልጅ ለመቀበል የቤተ ክርስቲያን ማኅበርም ተቸግራ ነበር::
"ሳውልም ወደ ኢየሩሳሌም በደረሰ ጊዜ ከደቀ መዛሙርት ጋር ይተባበር ዘንድ ሞከረ፤ ሁሉም ደቀ መዝሙር እንደ ሆነ ስላላመኑ ፈሩት" ሐዋ 9:26 ስለዚህ ሐዋርያው እንደ ጭንጋፍ ነኝ አለ::

ቅዱስ ጳውሎስ ስለ ጌታ መነሣት ምስክሮች ብሎ ሌሎችን ከዘረዘረ በኋላ  "ከሁሉ በኋላ ጭንጋፍ ለምሆን ለእኔ ታየኝ" ብሎ ተናገረ:: ክርስቶስ ተነሥቶአል ወይ ብለው ሲጠይቁህ አዎ ተነሥቶአል እነ እገሌ አይተውታል ብለህ ዘርዝረህ
"ከሁሉ በኁዋላ ለእኔም ታየኝ" ብለህ መናገር መቻል እንዴት መታደል ነው!?

ወዳጄ ክርስቶስ መነሣቱን ታምናለህ:: ልክ ነህ ለብዙዎች ታይቶአል:: አንተስ ከሁሉ በኁዋላ ለእኔም ታየኝ ማለት ትችል ይሆን? ጌታ ከተነሣ በኁዋላ ላለፉት ሁለት ሺህ ዓመታት ለብዙዎች ታይቶአል:: ብዙዎቹ ቅዱሳን አይተውታል:: ቅዱስ እስጢፋኖስ አይቶታል : ቅድስት አርሴማ አይታዋለች : አቡነ ተክለ ሃይማኖት አይተውታል : አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ተመልክተውታል:: አባ ጳኩሚስ በዕንባ ተመልክቶታል : ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ አይታዋለች::

ሁሉም ቅዱሳን ብዕር ቢሠጣቸው ከዕንባ ጋር
"ከሁሉ በኁዋላ ለእኔም ታየኝ" ብለው የትንሣኤውን ማስረጃ ዝርዝር ይቀጥላሉ:: ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ በበረሃ ሲጸልይ አይቶት ነበርና ሰው ባገኘ ቁጥር
ወቅቱ የፋሲካ ሰሞን ባይሆንም እንኳን በፈገግታ ተሞልቶ
"ክርስቶስ ተነሥቶአል!" ብሎ ያበሥርና ሰላምታ ይሠጥ ነበር::

ጌታ ሆይ ለእኔ ለኃጢአተኛው የምትታየኝ መቼ ይሆን? ቸርነትህን አይቻለሁ! ፍቅርህን አይቻለሁ! ብሩሕ ገጽህን የማየው መቼ ይሆን? መች እደርሳለሁ የአምላኬንስ ፊት መቼ አየዋለሁ? እኔም እንደ ቅዱሳንህ "ከሁሉ በኁዋላ ለእኔ ታየኝ" ብዬ የተቀመጠውን ብዕር አንሥቼ የምጽፈው መቼ ይሆን? አቤቱ ፊትህን እሻለሁ! አቤቱ ፊትህን ከእኔ አትመልስ! አቤቱ ፊትህን እሻለሁ!

"ኢየሱስ ክርስቶስ በግዕ ዘቀራንዮ
ለላሕይከ ንትሜነይ ከመ ንርአዮ"
"የቀራንዮው በግ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ
ውበትህን ልናየው እንመኛለን"

ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ

23 Oct, 04:50


የምስራች

እነሆ በTikTok በYoutube እናበተለያዩ ሶሻል ሚዲያዎች የምናውቀው ወንድማችን ልጃችን መምህራችን ዲያቆን ዘላለም ታየ በቴሌግራም መጥቷል ትምህርቶችን እንዲሁም እርሱ የሚጽፋቸውን ጦማሮች እንከታል ለህይወት ስንቅ ናቸውና::

Link👉https://t.me/dn_zelalem_taye

ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ

22 Oct, 18:44


+ ትሞታለህና ቤትህን አስተካክል +

ንጉሥ ሕዝቅያስ በጠና ታምሞ ተኝቶአል::  ነቢዩ ኢሳይያስ ሊጠይቀው መጣ:: ሆኖም እንደ ልማዱ እግዚአብሔር ይማርህ አላለውም:: ለጆሮ የሚከብድ  ቃል ጥሎበት ወጣ:: "ትሞታለህና ቤትህን አስተካክል!"

ነቢዩ ይህንን ብሎት ከወጣ በኁላ ሕዝቅያስ ወደ ግድግዳው ዞሮ ስቅስቅ ብሎ አለቀሰ:: አምላኩ በንግግር ብዛት የሚሰማ አምላክ አይደለምና ፊቱን ወደ መቅደሱ አቅጣጫ አዙሮ አለቀሰ:: 

ከጥቂት ደቂቃ በኁዋላ ነቢዩ ኢሳይያስ ሌላ መልእክት ይዞ ተመለሰ:: እግዚአብሔር እንዲህ ይላል :- ጸሎትህን ሰምቻለሁ ዕንባህን አይቻለሁ በዕድሜህ ላይ ዐሥራ አምስት ዓመት እጨምራለሁ" (ኢሳ 38:5)

ሕዝቅያስ ቤትህን አስተካክል ከተባለ በኁዋላ ፊቱን አዙሮ ከማልቀስ በቀር ምንም አላደረገም:: ሕዝቅያስ ሆይ ከአልጋህ ሳትወርድ ያስተካከልከው ቤት ምን ዓይነት ቤት ነው? ለባሪያዎችህ መመሪያ ሳትሠጥ የምታስተካክለው ቤትስ እንዴት ያለ ነው? በደቂቃዎች ውስጥ ትሞታለህ ከተባልክ በኁዋላ ዐሥራ አምስት ዓመት ያስጨመረልህ ምን ዓይነት ማስተካከያ አድርገህ ነው? ለእኛም ንገረንና ዕድሜ እናስጨምር::

ሕዝቅያስ ከአልጋው ሳይነሣ ያስተካከለው ቤቱ ልቡ ነበር::
ልብህን ካስተካከልህ ቤትህ ይስተካከላል:: እግዚአብሔር እንደሆን ትሞታለህ ቢልህም መሞትህን አይፈልግም:: እርሱ ካንተ ጋር ጸብ የለውም::

"በውኑ ኃጢአተኛ ይሞት ዘንድ እፈቅዳለሁን? ይላል ጌታ እግዚአብሔር፤ ከመንገዱስ ይመለስና በሕይወት ይኖር ዘንድ አይደለምን?" ይላል መሐሪው (ሕዝ 18:23)

እርሱ ትሞታለህ የሚልህ መኖርህን ፈልጎ ነው:: አንዴ ብያለሁ ብሎ አይጨክንብህም:: በንስሓ ተመለስ እንጂ ምሬሃለሁ ለማለት ይቸኩላል:: አሁን ትሞታለህ ብዬው አሁን ትድናለህ ብለው ይንቀኛል ሳይል ተመልሶ ይምርሃል:: ኃጢአትህንም ወደ ጥልቁ ይጥለዋል:: በጎ እንድትሠራም ዕድሜ ይጨምርልሃል:: አንተ ብቻ ተመለስና አሁኑኑ ንስሓ ግባ::
ከበደል አልጋ ጋር ያጣበቀህን ፈተናም ድል መንሻው ጊዜ አሁን ነው:: ሕዝቅያስ በደቂቃ ዕንባ ምሕረት አግኝቶ ዕድሜ ካስጨመረ በዐቢይ ጾም ሙሉ የሚያለቅስ ምን ያህል ዕድሜ ያገኝ ይሆን?
ወዳጄ አንተም ተነሣና በዚህ ወር ቤትህን አስተካክል::
እንደ ሕዝቅያስ ፈጣሪህ ይጠብቅሃል:: የተቀየምከውን ይቅር በል  የበደልከውን ካስ የሚበቀልህን የማይተኛ ጠላትህን ዲያቢሎስ ተበቀለው::

የዐቢይ ጾም የወንጌል ምንባብ ስለ ዲያቢሎስ ፈተና ሦስቱ ወንጌላት የተናገሩትን ስናስተውል ሦስት ዓይነት ጥቅሶች እናገኛለን::

አርባ ቀን ከዲያብሎስ ተፈተነ። (ሉቃ 4:2)

በምድረ በዳም ከሰይጣን እየተፈተነ አርባ ቀን ሰነበተ (ማር 1:13)
የሚሉት ቃላት ጌታችን ዐርባውንም ቀን መፈተኑን ያሳያሉ::

አርባ ቀንና አርባ ሌሊትም ከጦመ በኋላ ተራበ። ፈታኝም ቀርቦ እንዲህ አለው (ማቴ 4:2)

የሚለው ደግሞ ከጾሙ በኁዋላ የቀረቡለትን ሦስት ፈተናዎች የሚያሳይ ነው::
ሦስተኛው ጥቅስ ደግሞ ከተፈተነ በኁዋላ ያለው ሲሆን

ዲያቢሎስም ፈተናውን ሁሉ ከጨረሰ በኋላ እስከ ጊዜው ከእርሱ ተለየ። (ሉቃ 4:13) ይላል:: ዲያቢሎስ ፈተናውን ቢጨርስም የሚተወው ለጊዜው እንጂ መፈተኑን አያቆምም::  የዲያቢሎስ ፈተና ስልቱ ይቀያየራል እንጂ ይቀጥላል::

ዐቢይ ጾም ዲያቢሎስ ድል የተደረገበት የጦር ዐውድማ ነው:: በዚህ ወራት ድል ያላደረግነውን ፈተና በሌላ ጊዜ አናደርገውም:: ሰነፍ ገበሬ በሰኔ ይሞታል እንደሚባለው በዐቢይ ጾም የተኛ ክርስቲያን መቼም አይነቃም:: ከነስሙ ሁዳዴ (ሰፊ እርሻዬ) የምንለው ይህ ጾም ለነፍሳችን ብዙ ዘር የምንዘራበት አጋንንት መድረሻ የሚያጡበት ጾም ነው:: በዐቢይ ጾም ያልተገራ አንደበት መቼም አይገራም:: በዐቢይ ጾም ያልተፈወሰ ቂም መቼም አይፈወስም::

ጌታችን በወንጌል አንዴ ወደ እሳት አንዴ ወደ ውኃ የሚጥል ጋኔን ያለበትን ልጅ ሲፈውስ "ይህ ዓይነቱ ጋኔን ያለ ጾምና ጸሎት አይወጣም" ብሎ ነበር:: ሀገራችንን አንዴ ወደ እሳት አንዴ ወደ ውኃ የሚጥላት የጥላቻ ጋኔንም ያለ ጾምና ጸሎት አይወጣም::

ወዳጄ ከቁስልህ የምትፈወስበት ወር እንደደረሰ ዕወቅ:: አንተስ ብትሆን ልትላቀቀው እየፈለግህ ያቃተህ ክፉ ልማድ የለብህም:: እንደ ቅዱስ ጳውሎስ "የምፈልገውን መልካም ነገር አላደርግም የማልፈልገውን ክፉ ነገር ግን አደርጋለሁ:: ምንኛ ጎስቋላ ለዚህ ለሞት ከተሠጠ ሰውነት ማን ያድነኛል?" ብለህ ምርር እንድትል ያደረገህ ኃጢአት የለም? እንግዲያውስ እወቀው:: ይህ ዓይነቱ ወገን ያለ ጾምና ጸሎት አይወጣም:: ይህ ጾም ቁስል የሚሽርበት ጾም ነው:: ይህ ጾም ሸክም ማራገፊያ ጾም ነው:: እንደ ሕዝቅያስ በዚህ ወር ቤትህን በንስሓ አስተካክል::

ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ

21 Oct, 07:31


"እግሮቻችሁ በብረት ችንካር እንደተተከሉ እንደ ፅኑ አምዶች ፀንታችሁ በቤተክርስትያን ትኖሩ ዘንድ እነግራችኋለሁ።"

ቅዱስ አትናቴዎስ

ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ

21 Oct, 06:14


የምስራች

እነሆ በTikTok በYoutube እናበተለያዩ ሶሻል ሚዲያዎች የምናውቀው ወንድማችን ልጃችን መምህራችን ዲያቆን ዘላለም ታየ በቴሌግራም መጥቷል ትምህርቶችን እንዲሁም እርሱ የሚጽፋቸውን ጦማሮች እንከታል ለህይወት ስንቅ ናቸውና::

Link👉https://t.me/dn_zelalem_taye

ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ

20 Oct, 20:44


ጸሎት

ሕማማት ዲ/ን ሔኖክ ኃይሌ

20 Oct, 08:20


ቅምሻ - ፩

አሐቲ ድንግል - አንዲት ድንግል 

ድንግል ማርያም ለምን አንዲት ድንግል ትባላለች?

እመቤታችን ድንግል ማርያም በምድርም በሰማይም አቻ የማይገኝላት አንዲት ድንግል ናት። ከኪሩቤል የምትበልጥ ከሱራፌልም የምትልቅ በራሷ ላይ ትእምርተ መስቀል ያለው አክሊልን የተቀዳጀች በወንጌል የተፃፈች አንዲት ድንግል አለች። ይላል ቅዱስ ያሬድ።

ከዚህም ተነስቶ አንድ ሰው ተነስቶ በወንጌል ሌሎች ደናግል የሉምን? ስለምን በወንጌል የተጻፈች አንዲት ድንግል ትላለህ? ብሎ ቢጠይቀው ከኪሩቤል የምትበልጥ ከሱራፌል የምትበልጥበት የድንግልና ዘውድ ያላት አንዲት ድንግል አልኩህ እንጂ ደናግላንማ ብዙ ደናግል አሉ ብሎ ይመልስለታል።

ቀጥሎም በመላዕክት ክንፍ የምትጋረድ በክብሩ መንበር በፊት ምህረት የምትለምን በራሷ ላይ ትእምርተ መስቀል ያለው አክሊል የተቀዳጀች አማኑኤል የመረጣት አንዲት ድንግል አለች።

አሁንም ቅዱስ ያሬድን ስለምን አማኑኤል የመረጣት አንዲት ድንግል ትላለህ አርሱ የመረጣቸው ብዙ ደናግላን የሉምን? ብሎ የሚጠይቀው ቢኖር፥ አማኑኤል ሥጋን ይለብስ ዘንድ የመረጣት፤ ከእርስዋም ሥጋን ለብሶ አማኑኤል የተባለባት፥ በመላእክት ክንፍ የምትጋረድ፥ እግዚአብሔር በክብሩ ዙፋን በፊቱ ለመቆም የመረጣት፥ በእናትነት የሰለጠነ የባለሟልነት ዘውድን የተቀዳጀች አንዲት ድንግል አልኩ እንጂ እርሱ የመረጣቸው ደናግላንማ ስንቱ! ብሎ ይመልስለታል።

ደግሞም ፀጉሯ እንደ ሐር ፈትል ያማረ፥ የአንደበቷ መዓዛ እንደ እንኮይ የጣፈጠ ትእምርተ መስቀል ያለው አክሊልን የተቀዳጀች የልዑል ንጽሕት አዳራሽ የሆነች አንዲት ድንግል አለች።

የእግዚአብሔር ማደሪያ የሆኑ ሌሎች ደናግላን የሉምን ስለምን ለይቶ እርሷን አንዲት ድንግል አለ ቢሉ? ከእርሷ ስጋ ይነሳ ዘንድ እግዚአብሔርን በማህፀኗ ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን የወሰነች እውነተኛ የእርሱ ማደሪያ ሌላ ድንግል ከማርያም በቀር ወዴት አለ ይለዋል! ብቻዋን የእግዚአብሔር መቅደስ ለመሆን የበቃች እንደሆነች ሁሉ ከቅዱሳን ሁሉ ተለይታ በእግዚአብሔር ተቀባይነት ያለው እንደ እንኮይ የጣፈጠ አማላጅነት ያላት አንዲት ድንግል እርሷ ብቻ ናት! ስለዚህ እንደ ቅዱስ ያሬድ እመቤታችን ብቻዋን አንዲት ድንግል የተሰኘችበት  ወላዲተ አምላክነቷ፤ ንፅሕናዋ ፤ማኅደረ መለኮትነቷ አማላጅነቷ እና ዘለዓለማዊ ድንግልናዋ ናቸው ማለት ነው።

፩.በድንጋሌ ሥጋ ዘለዓለማዊ
በተፈትሆ የማይመረመር ድንግልናዋ ነው። ይህም ሥስት የማይመረመሩ ግብራት አሉት። ድንግል እንደሆነች መፀነስ፥ ድንግል ሆና ሳለ መውለዷ፥ ከወለደች በኋላ ድንግል ሆና መኖሯ ናቸው። እነዚህ በህገ ተፈጥሮ የማይታሰቡ ረቂቅ ግብራት ናቸው። ሰው ድንግል ሆኖ ያለ ወንድ ዘር መፀነስ አይቻለውም፥ በድንግልና እያለ የፀነሰ መሆን አይችልም፥ ሰው በድንግልና መውለድ አይቻለውም፥ ከወለደ በኋላ ደግሞ ድንግል መሆን እንዴት ይችላል? ድንግል የሆነች ሌላ ሰው እናት አይደለችም፥ እናትም ከሆነች ድንግል አይደለችም። ይህ ለአንዲቱ ለድንግል ማርያም ብቻ የተቻለ ነው።

፪. ድንግል በቃሏ - በቃሏም ድንግል
የቃል ድንግልና በሦስት ወገን ነው። እኒህም ክፉ አለመናገር፥ ምስጋና አለመብላትና በጎውን መናገር ናቸው። ሰው በንግግሩ ብዙ ኃጢአቶች ይሰራል። ሐሜት፣ ማጉረምረም፥ ቁጣ፥ ብስጭት፥ መዋሸት፥ መርገም፥ መሳደብ፥ ዋዛ ፈዛዛ፥ ያለጊዜው መሳቅ መሳለቅ፥ ዘፈን፥ ተውኔት፥ ድንፋታ፥ መንፈግ ነገር ማመላለስ፥ ቃል መለዋወጥ፥ አደራ መብላት፥ በሀሰት መማል፥ ሰጥቶ መንሳት፥ ክህደት፥ ማታለል፥ ማስነወር፥ አድልዎ፥ መጠራጠር፥ ማሽሟጠጥ፥ አሽሙር፥ ኃጢአትን ማመስገንና ማስፈራራት እነዚህን የመሳሰሉ ሁሉ ናቸው።

እመቤታችን በማንም ክፋትን ተናግራ አታውቅም አንደበቷ የለዘበ የለመለመ ነው። ቅዱስ ገብርኤል ዓይን ያላየውን ጆሮ ያልሰማውን በሰው ልቡና የማይታሰብ ዕፁብ ድንቅ የመውለዷን ዜና ሲነግራትም እኔ ወንድ ሳላውቅ እንዴት ይሆንልኛል ብላ ነገሩን ወደ መረዳት ተሻገረች እንጂ ይህ የማይሆን ነገር ነው ብላ ወደ መጠራጠር ወይም መልአኩን ወደ መንቀፍ አልቃጣችም። የአንደበት ድንግልና ማለት የማይቻል ጭንቅ ፍጹም ከተፈጥሮ ህግ በላይ የሆነን ነገር በመስማት ጊዜም ቢሆን ያለመጠራጠር በሃይማኖት መጠየቅና ፍፃሜውን በትዕግሥት መጠበቅ ነው።

መከራ በደረሰ ጊዜ ብዙ የቃል ድንግልና ያላቸው ቅዱሳን ችግሩን የፈጠሩትን ከመንቀፍ ይልቅ በእኔ ችግር የተከሰተ ነው ብለው ራሳቸውን ይወቅሳሉ። ነገር ግን እነርሱ ቀድሞ መበደላቸውን እያስታወሱ ነው። የድንግል ማርያም ግን የሚደንቀው ምንም ነውር የሌለባት ስትሆን በቃሏ ድንግል ስለሆነች እኔ ኃጢተኛ ነኝ ትል ነበር። በብስራተ መልአክ አምላክን የፀነስኩ እናት ነኝ ስትል ገናንነቷን አትናገርም። መልካም በመናገር ንግግሯ ሁሉ ሃይማኖት ተስፋና ፍቅር ናቸው።

፫. ድንግል በኅሊናሃ - በኅሊና ድንግልና የፀናች አንዲት ድንግል፦
ሰው በተግባር ቢነጻ በንግግር አይነጻም፥ በንግግር ቢነጻ በኅሊናው መንፃት አይቻለውም። ጻድቃንም ቢሆኑ ወድቀው ተነስተው በተጋድሎ ለክብር ይበቃሉ እንጂ ከጅማሬ እስከ ፍፃሜው አለመበደል ከቶ የተቻለው የለም። እመቤታችን ድንግል ማርያም ግን በኅሊናዋ እንኳን ያልበደለች ፍጽምት  አንዲት ድንግል ነች። ጽድቅን ሁሉ የተሞላች ድንግል ማርያም ንጽሕት በመሆኗ በኅሊናዋን ድንግልና፤ የቃሏን ድንግልና፤ የስጋዋን  ድንግልና በአንድ ላይ "እንዘ ኢይአምር ብእሴ" "ወንድ ስለማላውቅ" በሚል የንፅህና ሸማ ጠቅልላ ተናገረች (ሉቃ.፩፥፴፬) በዚህ ድንግልናዋም አምላክን ለመፀነስ በቃች።.....(ቀጣዩን መጽሐፉን ገዝተው ያንብቡ)

(ከርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ አሐቲ ድንግል መጽሐፍ ገፅ 241-251 የተቀነጨበ)

9,136

subscribers

154

photos

12

videos