🌼ሀላል ዘውጅ🌼

@halal_zewje


ለእናንተም ከነፍሶቻችሁ (ከጎሶቻችሁ) #ሚስቶችን ወደእነርሱ ትረኩ ዘንድ መፍጠሩ፣ በመካከላችሁም #ፍቅርንና እዝነትን ማድረጉ ከአስደናቂ ምልክቶቹ ነው፡፡ በዚህ ውስጥ ለሚያስተውሉ ሕዝቦች #ተዓምራቶች አልሉ፡፡
(አል ሩም) 21
for Comment @Hassen_l

ሀላል #ዘውጅ

🌼ሀላል ዘውጅ🌼

23 Oct, 08:43


ማንበብ የወንዶችን ወንድነት ይጨምራል፣ የሴትን ሴትነት ይጨምራል!
- ሰላም ለነዚያ ለአንባቢያን ይሁን! በዓለም ላይ በያሉበት ቦታ..

https://t.me/Halal_Zewje

🌼ሀላል ዘውጅ🌼

21 Oct, 03:31


ደስተኛው እስረኛ
~
ኢብኑ ተይሚያ ለቆሙለት አላማ ሲሉ ብዙ ተንገላተዋል፣ ተደብድበዋል፣ በተደጋጋሚ ታስረዋል። ሆኖም ግን ፈተናዎች ጭራሽ አላጠፏቸውም። በተደጋጋሚ ወህኒ ቢወረወሩም ከምንም አይቆጥሩትም ነበር። እንዲያውም ካይሮ ሳሉ ደማስቆ ወይም አሌክሳንድሪያ ውስጥ በገደብ ከመኖርና ከመታሰር ሲያስመርጧቸው መታሰርን መርጠዋል። መታሰራቸው ጠላቶቻቸው ከሚያስቡት በተቃራኒ ፍፁም ደስታን ነበር ያጎናፀፋቸው። ወደ እስር ቤቱ ግቢ በዘለቁ ጊዜ ይህቺን የቁርኣን አንቀፅ አነበቡ፦
فَضُرِبَ بَيۡنَهُم بِسُورٖ لَّهُۥ بَابُۢ بَاطِنُهُۥ فِيهِ ٱلرَّحۡمَةُ وَظَٰهِرُهُۥ مِن قِبَلِهِ ٱلۡعَذَابُ
“በውስጡ ችሮታ ያለበት፤ በውጪው በኩል ስቃይ ያለበት የሆነ (አጥር) በመካከላቸው ተደረገ።” [ሐዲድ፡ 13]
“ቅጣት የሚመስለው ለናንተ እንጂ ለኔ የእፎይታ አፀድ ነው” የሚል የሚደንቅ መልእክት እያስተላለፉ ነው።

እንዲያውም ጠላቶቻቸውን ለመታሰራቸው ሰበብ በመሆናቸው ባለትልቅ ውለታ እንደሆኑ ይገልጿቸው ነበር። ከወህኒ ቤት ሆነው እንዲህ ይሉ ነበር፦ “የዚህን እስር ቤት ሙሉ ወርቅ ብታደል እኔን በማሳሰር ለዋሉልኝ ውለታ ልከፍላቸው አልችልም።” ሱብሓነላህ!
እነሱ በማሰር ቅስማቸውን ሊሰብሩ ያልማሉ። እሳቸው ግን፡ “ጠላቶቼ ምን ያደርጉኛል?! እኔኮ ጀነቴ፣ የአትክልት ስፍራዬ ልቤ ውስጥ ነው ያለችው። የትም ብጓዝ ከኔው ጋር ነች፤ አትለየኝም። መታሰሬ ኸልዋ ነው። ብገደል ሸሃዳ ነው። ከሃገር መባረሬ (የአላህን ተአምራት የምመለከትበት) ጉብኝት ነው” ይሉ ነበር። ድንቅ ንግግር ከድንቅ ፍጡር!

እስር ላይ በነበሩ ጊዜ ሱጁድ ላይ ሆነው “አላሁመ አዒኒ ዐላ ዚክሪከ ወሹክሪከ ወሑስኒ ዒባደቲክ። ይሉ ነበር። ደስታ! እርካታ! እንዲያውም ራሳቸውን እንደ እስረኛም አይቆጥሩም ነበር። በተደጋጋሚ አብረዋቸው የታሰሩት ተማሪያቸው ኢብኑል ቀይም በአንድ ወቅት፡ “ 'እስረኛ ማለት ልቡ ከጌታው የታሰረ ነው። ምርኮኛ ማለት ደግሞ ስሜቱ የማረከው ነው' አሉኝ” ይላሉ። ኢብኑል ቀይም አሁንም ስለ ሸይኻቸው እንዲህ ሲሉ ይቀጥላሉ፦
“ኑሮው የተጣበበና ከምቾት የራቀ ከመሆኑ ጋር፤ እንዲሁም ከነበረበት እስር፣ ዛቻና ማጨናነቅ ጋር እንደሱ ደስተኛ ህይወት የሚኖር፣ ፈታ ያለና ልቡ የፀና እንዳላየሁ አላህ ያውቃል። ይህ ሁሉ ከመሆኑ ጋር በህይወቱ ደስተኛ፣ ዘና ያለ እና ልቡ የፀና፣ ነፍሱ የረጋ ነው። የድሎት ፀዳል ከፊቱ ያንፀባርቃል። እንዲያውም ስጋት ሲበረታብን፣ ክፉ ጥርጣሬ ሲያጠቃን፣ ምድር ሲጠበን ቀጥታ ወደሱ ነበር የምንሄደው። ከዚያም ስናየውና ንግግሩን ስንሰማ ያ ሁሉ ይወገድልናል። ልባችን ይሰፋል። ብርታታችንም፣ የቂናችንም፣ መረጋጋታችንም ይጨምራል። አላህ ከሱ ጋር ሳይገናኙ በፊት ለልዩ ባሮቹ ጀነቱን ስላሳያቸው፣ በስራ አለም በሮቿን ስለከፈተላቸው ጥራት ይገባው። እሷን በመፈለግና ወደሷ በመሽቀዳደም የደከሙትን ያክል ከድሎቷ፣ ከለዛዋ አቀመሳቸው።”
እናት ወልዳለች የተይሚያ ልጅ! ድንቅ የአላህ ተአምር! “ዱንያ ውስጥ ጀነት አለች። እሷን ያልገባት የኣኺራዋን ጀነት አይገባትም” ይሉ ነበር። [አልዋቢሉ ሶይብ፡ 48] አላህ ከላይኛው ፊርደውስ ያቀማጥላቸው።

https://t.me/Halal_Zewje

🌼ሀላል ዘውጅ🌼

19 Oct, 12:52


አስመሳይነት በኢስላም የተጣላ ባህሪ ነው!

ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦

﴿إِنَّ مِنْ شَرِّ النَّاسِ ذَا الْوَجْهَيْنِ ؛ الَّذِي يَأْتِي هَؤُلَاءِ بِوَجْهٍ، وَهَؤُلَاءِ بِوَجْهٍ﴾

“ከሰዎች መጥፎ ማለት ባለ ሁለት ፊት ነው። አንዱን በሌላ ፊት ሌላኛውን በሌላ ፊት የሚቀርብ።”

📚 ሙስሊም ዘግበውታል: 2526

||
https://t.me/Halal_Zewje

🌼ሀላል ዘውጅ🌼

16 Oct, 04:36


ያለምንም ችግር ሰዎችን ገንዘብ መለመን ያለው አደጋ!

ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦

﴿ما يَزالُ الرَّجُلُ يَسْأَلُ النّاسَ، حتّى يَأْتِيَ يَومَ القِيامَةِ وليسَ في وجْهِهِ مُزْعَةُ لَحْمٍ﴾

“ሰውዬው (ገንዘብ ለማብዛት ብሎ) ሰዎችን ከመጠየቅ አይወገድም። በቂያማ እለት ሲቀሰቀስ በፊቱ ላይ እንኳ  ቁራጭ ስጋ አይኖረውም።”

📚 ቡኻሪ (1474) ሙስሊም (1040) ዘግበውታል

||
https://t.me/Halal_Zewje

🌼ሀላል ዘውጅ🌼

13 Oct, 03:14


አላህ ዘንድ ተወዳጅ ስራ!

ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦

﴿أحبُّ الأعمالِ إلى اللهِ ﷻ  سُرُورٌ يدْخِلُهُ على مسلمٍ، أوْ يكْشِفُ عنهُ كُرْبَةً، أوْ يقْضِي عنهُ دَيْنًا، أوْ تَطْرُدُ عنهُ جُوعًا﴾

“አላህ ዘንድ ተወዳጅ ስራ ማለት በሙስሊም ወንድምህ ልብ ውስጥ ደስታን ማስገባት፣ ወይንም ከርሱ ያለበትን ጭንቅ ማስወገድ፣ ወይንም ብድሩን መክፈል፣ ወይንም ረሀቡን ማባረር (ማስወገድ) ናቸው።”

📚 ሲልሲለቱ አሶሂሃ: 906


https://t.me/Halal_Zewje

🌼ሀላል ዘውጅ🌼

12 Oct, 10:13


በቂያማ የአላህ ጎረቤቶች እነማን ናቸው?

ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦

﴿اللهَ لَيُنادِي يومَ القيامةِ: أين جِيرانِي، أين جِيرانِي؟ قال: فَتقولُ الملائكةُ: رَبَّنا ! ومَنْ يَنبغي أنْ يُجاوِرَكَ؟ فيقولُ: أين عُمّارُ المَساجِدِ؟﴾

“አላህ በትንሳዔ ዕለት ጎረቤቶቼ የታሉ፣ ጎረቤቶቼ የታሉ? በማለት ይጣራል። መላእክቶች ይላሉ፦ ጌታችን ሆይ! ላንተ ጎረቤት ሊኖርህ የተገባ አይደለም። አላህም መስጂድ አሳማሪዎች የታሉ? ይላል።”

  ሲልሲለቱ አሶሂሃ፡ 2728

https://t.me/Halal_Zewje

🌼ሀላል ዘውጅ🌼

08 Oct, 17:30


ብስራት ለበሽተኛ!

ከአቡ ሁረይራ (رضي ﷲ عنه) ተይዞ:  ነቢዩ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦

﴿ إنَّ اللهَ تعالى يَبتلِي عبدَهُ المؤمن بالسَّقَمِ؛ حتى يُكفِّرَ عنهُ كلَّ ذنْبٍ﴾

“አላህ አማኝ ባሪያውን ሁሉም ወንጀሎቹ እስኪታበሱለት ድረስ በበሽታ ይፈትነዋል።”

📚 ሶሂህ አልጃሚዕ: 1870

https://t.me/Halal_Zewje

🌼ሀላል ዘውጅ🌼

07 Oct, 17:55


ለሴቶች አደራችሁን!

قال رسول الله صلى الله عليه وسلم:

ነብዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦

"አደራችሁን፣ ለሴቶች በጎ ሁኑ። ከታጠፈ የጎን አጥንት የተፈጠሩ ናቸውና።  ከጎን አጥንት መካከል ይበልጥ የታጠፈው የላይኛው ነው። ቀጥ ልታደርገው ብትሞክር ትሰብረዋለህ። ከተውከው ደግሞ የታጠፈ እንደሆነ ይኖራል። ለሴቶች በጎ ሁኑ፣ አደራ።
(ቡኻሪና ሙስሊም)
||
https://t.me/Halal_Zewje

🌼ሀላል ዘውጅ🌼

07 Oct, 14:21


የወለድ አደገኘነት!

ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦

﴿من أكل الرِّبا بُعِثَ يومَ القيامةِ مجنونًا يتخبَّطُ﴾

“ወለድን የሚበላ በቂያማ እለት ሸይጧን የሚጥለው እብድ ሆኖ ነው የሚቀሰቀሰው።”

📚 ሲልሲለቱ አሶሂሃ: 3313

https://t.me/Halal_Zewje

🌼ሀላል ዘውጅ🌼

06 Oct, 16:06


መጥፎ ተግባር ወዳጅ ያሳጣል!

ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦

﴿إنّ شرَّ الناسِ منزلةً عند اللهِ يومَ القيامةِ من تركه الناسُ اتِّقاءَ فُحشِه﴾

“ከሰዎች መጥፎ ሆኖ በትንሳዔ ዕለት አላህ ዘንድ የሚመጣው፤ ከመጥፎ ስራው ለመጠንቀቅ ሲሉ ሰዎች የተዉት ሰው ነው።”

📚 ቡኻሪ (6032) ሙስሊም (2591) ዘግበውታል

https://t.me/Halal_Zewje

🌼ሀላል ዘውጅ🌼

05 Oct, 03:27


ከተዘነጉ ሱናዎች በልጆች አጠገብ ሲያልፉ ሰላምታ ማቅረብ

ከአነስ (رضي ﷲ عنه) ተይዞ፡ እንዲህ ይላል፦

﴿أنَّ رَسولَ الله (ﷺ) مَرَّ على غِلْمانٍ فَسَلَّمَ عليهم﴾

“የአላህ መልዕክተኛ (ﷺ) በልጆች አጠገብ ሲያልፉ ለነሱ ሰላምታ ያቅርቡ ነበር።”

📚 ሙስሊም ዘግበውታል፡ 2168

https://t.me/Halal_Zewje

🌼ሀላል ዘውጅ🌼

04 Oct, 16:17


ሰደቃ ያለ ገንዘብ!

ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦

﴿وَتُمِيطُ  الْأَذَى عَنِ الطَّرِيقِ صَدَقَةٌ﴾

“ከመንገድ ላይ አስቸጋሪ ነገር ማሰወገድ ሰደቃ ነው።”

📚 ቡኻሪ (2959) ሙስሊም (1009) ዘግበውታል

||
https://t.me/Halal_Zewje

🌼ሀላል ዘውጅ🌼

02 Oct, 17:51


አራት ነገሮች ሪዝቅን ያመጣሉ ፡-

«ለሊት በዒባዳ ማሳለፍ( መስገድ)፣
ሱሑር ወቅት ኢስቲግፋር ማብዛት፣
ሰደቃን በተቻለ መጠን መመፅወት
በቀኑ መጀመሪያ እና መጨረሻ ላይ ዚክር ማድረግ።»

ኢብኑል ቀዪም/ ዛዱል ሚዓድ (4/378)

https://t.me/Halal_Zewje

🌼ሀላል ዘውጅ🌼

01 Oct, 06:31


በማይመለከትህ ጉዳይ አትግባ!

ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦

﴿من حُسنِ إسلامِ المرءِ تركُه ما لا يَعْنيه.﴾

“የአንድ ሰው ከእስልምናው ማማር የማይመለከተውን ነገር መተዉ ነው።”

📚 ቲርሚዚ ሀሰን ብለውታል: 2317

https://t.me/Halal_Zewje

🌼ሀላል ዘውጅ🌼

30 Sep, 08:31


ከአቅም በላይ በሆነ ነገር አትጠየቅም!

ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦

 ﴿إنَّ اللَّهَ وضَعَ عن أمَّتي الخطَأَ والنِّسيانَ وما استُكرِهوا عليهِ﴾

“አላህ ከህዝቦቼ ላይ ስህተትን፣ መርሳትን እና የተገደዱበትን ነገር አንስቶላቸዋል።”

📚 ኢብኑ ማጃህ ሶሂህ ብለውታል: 1677

@Halal_Zewje
@Halal_Zewje

🌼ሀላል ዘውጅ🌼

29 Sep, 09:38


#ለሴት ልጅ ትልቁ ክብሯ እንቁነቷ በሁሉም ነገር ላይ ቁጥብነቷ ነው!  ቁጥብ ሴት ሁሌም እንቁ (ውድ) ናት !
           ውድና የተከበረ እንጂ አያገኛትም❗️
\\____
        ..............
_\\___
ሀላል ዘውጅ 👇

@Halal_Zewje
@Halal_Zewje
@Halal_Zewje

🌼ሀላል ዘውጅ🌼

28 Sep, 08:10


💜 ሴት ልጅ ሀያእ ስታደርግ
የወንድ ልጅ አፍንጫን የማይስት
ግሩም የሆነ መአዛ ትበትናለች ።

ሀላል ዘውጅ
@Halal_Zewje 🌹
@Halal_Zewje 🌹
@Halal_Zewje 🌹

🌼ሀላል ዘውጅ🌼

27 Sep, 13:50


. ☞ ስጦታ እና ትዳር በኢስላም ውስጥ፡-

ስጦታ ለትዳር ማጣፈጫ ቅመም ሲሆን ሚስቶች ደግሞ ስጦታን የመውደድ ልዩ ተፈጥሮአዊ ባህሪ አላቸው፡፡

ባል ለሚስቱ ስጦታ ሲሰጣት ኢስላማዊ በሆነ መልኩና አላህን የሚያስደስት
ሲሆን ይበልጥ ለትዳር ማማር ትልቁን ሚና ይጫወታል፡፡

#ሀላል ዘውጅ

ጆይን
https://t.me/Halal_Zewje 🌹

🌼ሀላል ዘውጅ🌼

26 Sep, 06:01


🥀ለፈገግታ ፈገግ በሉ እስቲ🥀

#ባልና ሚስት ነበሩ ሚስት ትንሽ ቀበጥ አለችና

#ባል ሚስቱን ሊቀጣ በር ላይ አወጣና ብትር ፈልጎ ሚስቱን እየመታት አንድ መንገደኛ  በበራቸው ሲያልፍ ያያቸዋል እና ለምድነው የምትመታት ይለዋል

 #ባል ኧረ ባየሀት ቅብጥ ብላብኛለች አለው

#መንገደኛውም ስትቀብጥብህ በብትር
ሳይሆን በሴት ቅጣት አለው ሴትን በሴት ነው መቅጣት አለው



#እሱ ሴትን በሴት እደት ይቀጣል ብሎ ግራ ገብቶት ምን ለማለት ፈልገህ ነው ብሎ ሲጠይቀው

#እሷ ገብቷታል በደንብ ምን ለማለት እደፈለገ ኧረ ዝምበለው ሰውየው እብድ ነው እኮ አተ የእብድ ወሬ አትስማ

ዝምብለህ መማታትህን ቀጥል አለችው ይባላል

#አቤት ሴቶችዬ እኛና ሁለት ፣ሶስት  መቼ ነው የምንግባባው

منقول
https://t.me/Halal_Zewje

🌼ሀላል ዘውጅ🌼

24 Sep, 07:47


#እህቶች_የወንዶችን_ሚስጥር_አሳልፌ ልስጣቹህ
____
ወንድ በባህሪው  #በሱ___ፍቅር ከምታለቅስ እንስት ( ሴት ) ይልቅ
እሱን በፍቅሯ #የምታስለቅሰውን ቁጥብና ጥንቁቅ ሴትን እጅግ አድርጎ ይወዳል !
____
ስለዚህም ሆሌ ቁጥብነትና ጥንቁቅነት መለያችሁ ይሁን !
___
እናም
እህቴ!
#ጥንቁቅ ሁኝ በነገሮች ላይ
ትዕግስት(ሶብር) ይኑርህሽ አትቸኩይ!

ወንድን ልጂ የሚወዳቸው  ጥንቁቅነትሽን ጥብቁነትሽን  ጥንካሬሽን እንጂ ወደሽው
አፍቅረሽው በሱ ፍቅር ብትጎጂ  ብትንከራተች ሊወድሽ / ሊረዳሽ አይችልም!

እንዳውም ጀግንነት ይሰማዋል!
#ያልፍስፍስ የነበረ  ወንድ በቃ ፉላኒት ትወድሀለች በተባለ ጊዜ   አላህን ፈሪ ነው ቂርአት ቀርቷል የተባለ ቢሆንኳ ሴት ልጂ እንደወደደችው ካወቀ የጀግና ጀግና ይልቅ!
   ምርጫው የሚያረገው እሱ የወደዳትን ያበደላትን አልቅሶ ተንበርክኮ የጠየቃትን ነው!

  የምትወጂውን ወንድ አላህ ብሎ አግብተሽ እንኳ ብትኖሪ  መቸም ደስታን አታገኝም!

ምክንያቱም አንች ነሻ የምትወጅው እንዳውም #በህልሙ እንኳ #ያላየውን በአንች ጫንቃ  ትካሻ መወጣጫ ነው የሚያደርግሽ!!

እሱ ግን ወዶሽ አንች ባትወጂውም እንኳ ከትዳር ቡኃላ በሚሰጥሽ ደስታ ፍቅር እንድትወጂው ያደርግሻል!

እናም እህቴ ብስል ጠንቃቃ ጠንካራ ሁኝ! ያኔ እሱ እየዳከ ይመጣል!
#ተግባባን አይደል!

ህይወት በብቸኝነት ቢከብድሽም በአላህ ላይ ተስፋ አድርጊ በሶብር / በትዕግስት ጠብቂ!

  ጥሩ ነገሮች ሁሉ ምን ጊዜም ግዜ ይወስዳሉ!
#ትዕግስተኛና በአላህ ላይ እርግጠኛ ሆነሽ ብቻ ጠብቂ !
ሁሉም ነገሮች በአላህ ፈቃድ አንድ ላይ ይመጣሉ ይሳካሉ ተስፋ አትቁረጪ!!!
      
Join
||
@Halal_Zewje 🌹
@Halal_Zewje 🌹
@Halal_Zewje 🌹