Zebidar Media (ዘቢዳር ሚዲያ) @guragez Channel on Telegram

Zebidar Media (ዘቢዳር ሚዲያ)

Zebidar Media (ዘቢዳር ሚዲያ)
# ይህ የዘቢዳር ቻናል የሀገራችን ብሎም የጉራጌ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካ፣ ኪነ ጥበብ፣ ታሪክ፣ ርዕዮት እና ሁለንተናዊ መልክ የሚዳሰስበት የመገናኛ የመወያያ እና የመጦመርያ አውድ ነው!
4,354 Subscribers
4,395 Photos
73 Videos
Last Updated 02.03.2025 15:54

ዘቢዳር ሚዲያ: የጉራጌ ሀገር ወቅታዊነትና እድገት

ዘቢዳር ሚዲያ የጉራጌ ማህበራዊ ግንኙነት መረጃ እንደ የታሪክና የዕቅፍ ምንጭ ለእንደ ብዙ ቤተ-መዳይ የሚይዙበት ወር ነው። ይህ ቻናል ጉራጌ አካባቢ ተወላጅ የሆነ በፖለቲካ፣ ኢኮኖሚና ሐበሻ ታሪክ ዘዴ ያላቸው ገበሬዎችን የሚወቅድ ነው። ዘቢዳር ሚዲያ እንደ ማዕከል የህይወት ገጽታ ሲሆን ይህ የሚታወቀው የማህበሩን ውስነት ማስወሳሰብን እንደ የደረጃ ይሁን ዚና ትምህርት ይሳተፍ።

ዘቢዳር ሚዲያ ምን እንደሚያቀርባት ይወዳዳር?

ዘቢዳር ሚዲያ ጉራጌ ማህበራዊ እና ዕውቀት የሚቀርባች ታላቅ መገናኛ ይዘቷል። ይህ ቻናል በፖለቲካ ሂደት፣ የኢኮኖሚ ዝርዝር እና የታሪክ መረጃ ተስፋ ያከናውን ነው።

አብዛኛው የዘቢዳር የሚወዳድር ይህ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚ እንደ ገነዘባ እና በምዕመናዊ ዝክረት በድብር በፍርዳቸው ይገኛል።

ዘቢዳር ሚዲያ ለጉራጌ ማህበር ምን አስተሳሰብ እንደሚያፈራ?

ዘቢዳር ሚዲያ ለጉራጌ ማህበር የቅድሚያ ዝርዝር እንደሆነ ገለልተኛ የበለይ ዕድገት ይሰጣል። አስቀድሞ ይህ የሠላምና የድምፅ ወንድሞች ዘዴ ሲከናወን የሚወዳድር ነው።

ኢኮኖሚአዊ ሲሆን የሚያግዝ ዝርዝር የገበሬ ማህበር ሙስና ይውላል። በምርኮች ዘዴ የሚወዳድር ነው ያላቸው ህይወታቸው የንቁል ቪስንስ አሳይ የሆነ ዝርዝር ይወዳድር ነው።

የዘቢዳር ሚዲያ አካዳሚክ አቅድድ ምን እንደሚሰጥ?

ዘቢዳር ሚዲያ አንዳንድ የአካዳሚክ አቅድድ ይሠጣል ማለትም ዘርቃሻ ወዘ ሐበሻ አሳይ ከመርሀ የዳህይድ ያስቀድሞ ያደርጋል።

ይህ የሚታገይ ምን ይለዋል ዘግባ ያላቸው መንገድ የደረጃ ዕንዳ እንደማህበር ውርደው ለሚወዳድር አይደለም።

ዘቢዳር ሚዲያ ያደርገው የስራ ሂደት ምን ነው?

ዘቢዳር ሚዲያ ለአስታወስ የሚሰጥ አንዳች በመንግሥት በመያዙ ከባለሞያዎች ውህደት ይወቅ ብለው ማለፊያ ይገኛል።

ይህ ትኩረት የገጽታ የአሕዋላ ሂደት ይስተዋ ክትተፊይ ይቦታል አሉሀ እንደሚሠጣል።

ዘቢዳር ሚዲያ ለማህበራችን ምን ተሳታፊ እንደሚኖር?

ዘቢዳር ሚዲያ የማህበራችን ባለቤት ዝርዝር ይነሱዋ። አምደለኛነት እንደሚይኖሩ እና ማብራሪያ ወቀነት ይረዳዋ።

ይህ የመስክ በምዕመናዊ ዝርዝር በዕመን ይወዳድር እንደገንዝዎ ይገኝበረወ ይወዳዳል።

Zebidar Media (ዘቢዳር ሚዲያ) Telegram Channel

ዘቢዳር ሚዲያ (Zebidar Media) የጉራጌ ሀገርን ኢኮኖሚንን ስኬትን እና ታሪኩን እና እርጉሞን እና ሁለንተናዊ እና መልክ ያሉ የመገናኛ መወያያ እና መጦመርያ አውድ ነው። ይህ ቻናል በገጠማችን ምንም አልተደጋገመማለት፣ ဌራካፍኛማና ኢኮኖሚያ፣ ፖለቲካ፣ ኪነ ጥበብ፣ ታሪክ፣ ርዕዮት እና ሁለንተናዊ መልክኛን ማውረድ እና መስራት ይችላሉ። የእኛውን ምርጫ በTelegram መለዋወጥ ይችላሉ።

Zebidar Media (ዘቢዳር ሚዲያ) Latest Posts

Post image

ሃገር የራሷን ዜጋ ወደ ሃገርህ አትመለስም ብላ መከልከል ትችላለች?
***
በዳንኤል ፍቃዱ / ጠበቃና የህግ አማካሪ/

•የኢትዮጵያ ዜጎች ወደ ሀገራቸው የመመለስ መብት በሕገ መንግሥት እና በአለም አቀፍ ሕግ የተጠበቀ ነው።
•የኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት፣ አንቀጽ 32(1 እና 2)
•ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ወይም በሕጋዊ መንገድ ሀገሪቱ ውስጥ የሚገኝ የውጭ ዜጋ በመረጠው የሀገሪቱ አካባቢ የመዘዋወርና የመኖሪያ ቦታ የመመሥረት፣ እንዲሁም በፈለገው ጊዜ ከሀገር የመውጣት ነጻነት አለው።
•ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ወደ ሀገሩ የመመለስ መብት አለው።
•የሰብአዊ መብቶች ሁለንተናዊ አዋጅ (UDHR, አንቀጽ 13) እና የሲቪል እና ፖለቲካዊ መብቶች ዓለም አቀፍ ቃል ኪዳን (ICCPR, አንቀጽ 12(4)) ዜጎች ወደ ሀገራቸው የመመለስ መብትን ያረጋግጣሉ ።
  •ይህ መብት ለግለሰቦች ብቻ ሳይሆን ለቡድኖችም (ለምሳሌ ስደተኞች) የሚተገበር የሆነበት ሁኔታ በሕግ ባለሙያዎች መካከል ውይይት ያለበት ነው ።
•የሲቪል እና ፖለቲካ መብቶች ዓለም አቀፍ ቃልኪዳን፣ አንቀጽ 12(3)
• ብሔራዊ ደኅንነትን፣ የኅብረተሰብ ሰላም፣ የሕዝብን ጤና ወይም ሞራል ወይም የሌሎችን መብቶችና ነጻነቶች ለመጠበቅ ሲባል በዚህ ቃል ኪዳን ከሰፈሩት ድንጋጌዎች ጋር በሚስማማ አኳኋን በሚወጣ ሕግ መሠረት ካልሆነ በስተቀር ከላይ በተጠቀሰው መብት ላይ ምንም ዐይነት ገደብ አይደረግም፡፡
•የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ስምምነት:-  ስደተኞች በፀጥታ ምክንያት ወደ ሀገራቸው ለመመለስ ካለመቻላቸው ጋር በተያያዘ ጊዜያዊ ጥበቃ ይሰጣቸዋል።

•የመመለስ ሂደትን የሚገድቡ ሁኔታዎች

"የአንድ ሀገር ዜጋ በመሆን ብቻ ከተረጋገጡ ዓለም አቀፋዊ የሰብዓዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶች ድንጋጌ ውስጥ ዜጋው ወደ ትውልድ ሀገሩ በፈለገ ጊዜ የመመለስ መብትን መከለከል/መገደብ ከመሠረቱ ሕገወጥ ተግባር ስለመሆኑ"


•የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብቶች የቃልኪዳን ሰነድ

•አንቀጽ 13/2/ ‘‘ማንኛውም ሰው የራሱን ሀገር ጨምሮ በማንኛውም ሀገር የመግባትና የመውጣት መብት አለው ’’ ይላል
• ዓለም አቀፍ የሲቭልና ፖለቲካዊ መብቶች የስምምነት ሰነድ
•  አንቀጽ 12/2/ ‘‘ማንኛውም ሰው የራሱን ሀገር ጨምሮ በማናቸውም ጊዜ ለቆ የመውጣት መብት አለው፡፡’’
• አንቀጽ 12/3/ ከላይ የተጠቀሱት መብቶች በማናቸውም መንገድ ወይም ሁኔታዎች ሊገደቡ የማይችሉ ቢሆንም በተለየ ሁኔታ ለሕዝብ ሰላምና ደህንነት ሲባል፤ ለብሔራዊ ደህንነት ሲባል፤ ለሕዝብ ጤናና ሥነ ልቡና ሲባል፤ ወይንም ለሌሎች ሰዎች መብቶችንና ነፃነቶችን ለመጠበቅ አስፈላጊ መሆኑ ካልታመነ በቀር መብቶቹ ሊገደቡ የማይችሉ መሆናቸው ተደንግጓል፡፡
•አንቀጽ 12/4/ ከላይ የተገለጹት ልዩ የገደብ ምክንያቶች ቢኖሩም ‘‘ማናቸውም ዜጎች በዘፈቀደ እና በኃይል ተግባር ወደ ሀገራቸው እንዳይገቡ ሊከለከሉ አይገባም’’ በሚል ያትታል፡፡

አንድ ሃገር የራሷን ዜጋ ወደ ሃገርህ አትመለስም ብላ መከልከል ትችላለች ። ይህ ይሆን ዘንድ የሚደርግ ውሳኔ የሚወሰደው በዚያ ሃገር አዋጆች እና የስርዓተ ፍትሕ ሂደቶች መሰረት ነው። በተለይ የሚከተሉት ሁኔታዎች ክልከላን ሊያስከትሉ ይችላሉ፦
1. የዜጎች መብቶች፦ ዜጎች የራሳቸውን ሃገር  የመግባት እና የመውጣት መብት እንዳላቸው ይታወቃል።  የሃገር መንግስት ይህን መብት የሚገድብ  ውሳኔ  ለማወጅ የሚያስፈልገው በሕግ የተደነገገ ምክንያት ሊኖረው ይገባል።
2. የስርዓተ ፍትሕ ሂደቶች፦ የሃገር መንግስት የራሱን ዜጋ ወደ ሃገርህ አትመለስም ብሎ ለማከልከል የሚወስደው  ውሳኔ  በሕግ የተደነገገ ሂደት ይኖረዋል። ይህ ዜጋ የሚያቀርበውን የሕግ አቤቱታ የመስጠት እድል ይኖረዋል።
3. የሃገር ደህንነት፦ የሃገር መንግስት የራሱን ዜጋ ወደ ሃገርህ አትመለስም ብሎ ይከልከል የሚችለው የሃገር  ደህንነት ይጠበቅ ወይም የሕዝብ ጤና የሚያሳስበው ይሆን ይችላል።

በቅርቡ የወጣው የኢሚግሬሽን እና ዜግነት ጉዳዮች አዋጅ፦ በአዋጁ ላይ እንደተመላከተው ወደ ኢትዮጵያ የሚበሩ ማናቸውም አየር መንገዶች የተጓዦችን ስም ዝርዝር ከ3 ቀን በፊት ለኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት የማሳወቅ ግዴታ አለበት ይላል።
ሲጠቃለል የዜጎች ወደ ሃገር መመለስ መርህ / principle/ በመሆኑ በሰፊው ተተርጉሞ ክልከላው ልዩነት / exception/ በመሆኑ በጠባቡ ሊተረጎምና ሊተገበር ይገባል።

Zebidar Media/ ዘቢዳር ሚዲያ

12 Feb, 12:10
1,512
Post image

አስራ አምስት ወራትን የተሻገረው ችሎት ለመጋቢት 01 ተቀጠረ።

#ዘቢዳር ሚዲያ:- ጥር 27/2017

በዛሬው ዕለት በፌደራል ተዘዋዋሪ ችሎት በእነ ጀምበር አብዶ መዝገብ አቃቤ ህግ ክስ የመሰረተባቸው ተጠርጣሪዎች መዝገብ ለተጨማሪ ጊዜ ለመጋቢት 01, 2017 ተቀጠረ።

አቃቤ ህግ 30 የሰው ምስክሮች አሉኝ ብሎ አስመዝግቦ የነበረ ቢሆንም ከ10 የሰው ምስክሮች በላይ የምስክርነት ቃል ማሰማት ሳይችል ቀርቷል።

ፍርድ ቤቱ ችሎቱን ለመጋቢት 01 የቀጠረው አቃቤ ህግ ክሱን ያስረዱልኛል ብሎ ባቀረባቸው የሰነድና የተንቀሳቃሽ ምስሎች ላይ የተከሳሽ ጠበቆች ምላሽ ለመስማት መሆኑን የተከሳሾች ጠበቃ የሆኑት አቶ ጌዲኦን ቦጋለ ለዘቢዳር ሚዲያ አሳውቀዋል።

ትላንት በዋለው ችሎት አቃቤ ህግ ማስረጃ አላገኘሁባቸውም በማለቱ ፍርድ ቤቱ በአቶ ጃፈር ተማም በድሩ እና በአቶ ትጉነህ ትዛዙ ላይ የተመሰረተው ክስ እንዲቋረጥ ወስኗል። በቅርቡ አቶ Jafer Temam Bedru እየደረሰባቸው የነበረውን ተደጋጋሚ እስር፣ ዛቻና ማስፈራራት ሽሽት ከሃገር መሰደዳቸው ይታወቃል።

በተመሳሳይ አቶ ጀምበር አብዶ ላይ በተናጠል ተመስርቶ የነበረው ተደራቢ ክስ አቃቤ ህግ ማስረጃ አላገኘሁም በማለቱ ፍርድ ቤቱ በዛሬው እለት ክሱ እንዲቋረጥ ወስኗል።

Zebidar Media/ ዘቢዳር ሚዲያ

04 Feb, 16:59
2,411
Post image

እኛን ሚመለከቱ መረጃዎች የት ነው የተከማቹት?

AI ወይም ሰው ሠራሽ አስተውሎት በሰው ልጆች ልክ መገንዘብ ወይም መማር የሚችልበት የዘመናችን ድንቅ የቴክኖሎጂ ፈጠራ ሆኖ ተከስቷል፡፡ በዚህ ምክንያት ከአሁን በኃላ እንደ ግለሰብ ሆነ ማህበረሰብ ከፍ ሲልም አንደ ሀገር በሁሉም ማህበራዊ ሚድያዎች የምናሰፍራቸው እያንዳንዱ ቃላትና ፎቶ ወይም የትኛውንም አይነት መረጃ በማንነታችን ብየና ውስጥ ወሳኝ ሚና አለው።

የሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) ለጥያቄዎች ምላሽ እንዲሰጡ ከማስቻሉ በተጨማሪ ውስብስብ የሒሳብ ቀመር እንዲፈቱ ያስችላል፤ በጤና፣ በግብርና፣ በትምህርት እና በሌሎችም ዘርፎች ጥቅም ላይ የሚውሉ አገልግሎቶችን ይሰጣል፡፡ የእነዚህ ነገር ሁሉ መገኛው ከእያዳችን የሚወሰዱ መረጃዎች ድምር ውጤት ነው፡፡ ለዚህም ነው ዳታ ወይም መረጃ አስፈላጊነት የነዳጅ ወይም የከበሩ ማእድናት ያክልነው የሚባለው፡፡

ለዚህ ጥሩ አብነት ስሞኑን በአለም ላይ መነጋገርያ የሆነው "ዲፕሲክ" "DeepSeek" የተሰኘው AI መተግበርያ አለምን በመረጃ ስርአት ውስጥ ቻይና ያላትን አቅምማሳየቷ ነው፡፡
ይህ ቴክኖሎጂ በርካታ የቋንቋ ሞዴሎችን በመያዝ የሚቀርብ በመሆኑ ለቋንቋ፣ ለታሪክ፣ ለባህል፣ ለኪነ ጥበብ እና የኢኮኖሚ እድገትም አስተዋጽኦው ከፍተኛ ነው፡፡ ከዚህ ቀደም በተሸለ መልኩም በአማርኛ፣ በአፋን ኦሮሞ እና በትግርኛ ከሌሎች መሰል ቻትቦቶች በተሻለ አገልግሎት እየሰጠም ነው፡፡

እኛ_ግን_የት_ ነን?_ ይህ ቴክኖሎጂ የእኛስ ቋንቋ ጉራግኛ እንዲጠቅም ምን እናድርግ? ብሎ መቆዘም የግድ አስፈላጊ ነው! በተለይ የአፋን ኦሮሞ እና የትግርኛ ቋንቋዎች ዛሬ ላይ የሚድያና የስራ ቋንቋ ከመሆን ተሸግረው የዲጂታል ቋንቋ የሆኑት የብሔረሰቦቹ ተወላጆች በዘመናት መካከል ለጉዳዩ በሰጡት ትኩረት ነው፡፡

መተገበርያዎቹ ጥሩ አገልግሎት የሚሰጡት የተከማቸ እና ጥራት ያለው መረጃ ሲገኝባቸው በመሆኑ ለዲጂታሉ አለም ስለ ጉራጌ የምንጽፈው፣ የምንናገረው፣ የምናጋራው ምስል ምን አይነት ነው? ስለ ጉራጌ በዲጂታሉ አለም በቂ መረጃ ማግኘት ይቻላል ወይ? አሉ የምንላቸው መረጃዎች ጥራታቸውና ብዛታቸው እንደው ምን ያክል ነው ብለን ብንጠይቅ መልሱ በጣም ቀላል ነው፡፡

በአጠቃላይ ስለ ጉራጌ አለም በቅጡ እንዲረዳና ሆነ እኛም እንድንገለገልበት በዘመኑ ቴክኖሎጂዎች ላይ ንቁ ተሳታፊ መሆን በቂ እና ጥራት ያላቸው መረጃዎችን በስፋትና ማሰራጨት በማህበራዊና እንደ ታሪክ እና ፖለቲካ ባሉ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ የተሻለ ግንዛቤ ያላቸው አካላት በጉዳዩ ላይ መሪ ተዋንያ እንዲሆኑ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡
ይህ ካሆነ ግን ዲጂታል አለሙ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ እርግጠኛ እና ሙሉ መረጃ የሚመግቡ አካላት የበዙበት በመሆኑ ከሀገርም ሆነ ከአለም ስርአት ውስጥ እየተገለልን መምጣታችን አይቀርም፡፡

Zebidar Media/ ዘቢዳር ሚዲያ

31 Jan, 12:07
3,105
Post image

ማረዳ ፊት አውራሪ ሳፎ ጀጀነ!

ኔሁ እንዴ! ዘንድረ ታረፋም ተመስቀር ውጤ ገኔንየ ንዥነ።

ቶቶት የዘርማ ማመረንዳ በህርም ህርም አት ግዝየ ያስራጅን "የገናኸ ሀርም፤አትኸር" ማረዳ ዘድር የ6ተነ ግዝየ በሰባት ቤት በጟታ አፈር ዛራ ይውሪ ንቃር ቀልብ ይሽን ድብርንየ ይወርድቴ። በህሜማንዳ የገነንዳ ይሽሮ ጀፎረም ናዠነቴ ተህም ገነንዳ ምር ትመስር ኸማ ተጨራ ንኽነም ናትኸነቴ።

ማረዳሁታ ንቃር ገነሁና ይረምዶ ንቅ ኮረምቶ/ሶሬሳ ሰብ ተዘርማ እማቴ ያሮ የኸሬ ንቃር የኽን ያሰራ ቃር አስራጀት ያነወ የኽሬ እናመንጠናሁ።

☑️መቸው? በባሁ:-
እንተጎጎት (የካቲት 8&9)
📣ያርም ይትዠቦርቤ የመኪና ዋጋ፣ሸረትም፣ካናቴራ ደበረምታ=2800ብር

የትመዝገቦት:
📲0913155230
📲0936261036
📲0923576123
"ቶቶት፤ ይፈዝ ከረ"

29 Jan, 07:24
2,017