ከስነ-ፅሁፍ ዓለም @ethiobooks Channel on Telegram

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

@ethiobooks


አዝናኝ፣ አስተማሪና ቁም ነገር የሚያስጨብጡ የብዕር ውጤቶች የሚቀርቡበት የናንተው ቻናል!
የቻናላችን https://t.me/Ethiobooks ቤተሰብ ሁኑ፣ ለወዳጅ ጓደኞቻችሁም 'share' አድርጉ።
ለአስተያየት፣ ስነ-ፅሁፋዊ ጥቆማና ማስታወቂያ
@firaolbm እና
@tekletsadikK ተጠቀሙ።

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም (Amharic)

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም የገና አዝናኝ ስነፆፋዊ ውጤቶች እና ከተሰብህ ሁኑ፣ በተጨባረለት ቋንቋ አሁኑን እናረጋግጠዋለን። እባኮትን የሚሠራውን ቻናላ እናመሰግናለን። ethiobooks በመተናሽ የናንተው ዋና ልዩ ቻናል ነው፣ ስንት ቦታዎችን በሁኑ፣ ፍላጎቻችሁንም ለማረጋጋት share መዝገብን አድርጉ። በመሆኑ፣ የማንነትህ ቻናላ በአጭሩ መሠረት ከፈለጉት ስነ-ፅሁፋዊውን እና ማስታወቂያውን በመጠበቅ አግዝተው። ለበኩላችሁ የምንፈልጉትን @firaolbm እና @tekletsadikK ሊያስተካክሉ ልትችሉ እንችላለን።

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

08 Feb, 09:00


ጆሞ ኬኒያታ - 2 የመጨረሻው!

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

08 Feb, 08:00


ጆሞ ኬኒያታ - 1

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

08 Feb, 07:55


ጆ ሞ ኬ ኒ ያ ታ
━━━━━━
«ባለ ጭራው ፕሬዝዳንት»
@ethiobooks

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

07 Feb, 07:00


💿 ገባኝ አሁን ገና 💿
   ══❁══
🎤 ጥበቡ ወርቅዬ 🎧
  @ethiobooks

🎼🎵🎶🎵🎶🎵
[ገባኝ አሁን ገና ገባኝ አሁን ገና
ከሰው ጋር ለመኖር አቋራጭ ጎዳና
ማስመሰል መሆኑን እያደረ ገና
ማስመሰል መሆኑን እያደረ ገና] 2×
🎵🎵
አንድን መጽሐፍ ውስጡን አይተው ሳያጠኑ
ቢፈርዱበት ያሳዝናል በሽፋኑ
ለማስመሰል አልችል ብዬ ስላቃተኝ
ሌላ አይደለም የኔው ጠላት ራሴው ነኝ
🎶🎶
ከሰው ጋር አብሬ ለመኖር
ለጊዜው ማስመሰል ባልችልም
እራሴን እስከማውቀው ድረስ
ያን ያህል ክፉም አይደለሁም
ግልፅነት እራሴን መሆኔ
ቢለየኝ ሀዘኔ ያበቃል
ብከፋም በሰው ቂም አልይዝም
የልቤን ፈጣሪ ግን ያውቃል
🎵
[ሁሉንም በሱ ላይ ትቻለሁ
ማስመሰል አልችልም አ'ቃለሁ
ብነጠል ግዴለም ልታገስ
እውነቱን እስከሚያውቁት ድረስ] 3×

🎵🎶🎵🎶🎵
[ገባኝ አሁን ገና ገባኝ አሁን ገና
ከሰው ጋር ለመኖር አቋራጭ ጎዳና
ማስመሰል መሆኑን እያደረ ገና
ማስመሰል መሆኑን እያደረ ገና] 2×
🎵🎵
ሰው ቀርቤ ሰው ሲርቀኝ ሳስበው
ብዙ ጊዜ ግልጽነቴን እረግማለሁ
የገባኝን ከመናገር ስለማላርፍ
ክፉ ሆኖ ስሜ ቀርቷል በሰዎች አፍ
🎶🎶
ብቻውን ይኖር ዘንድ በምድር
የሰው ልጅ እንዴት ይቻለዋል
ጓዳዬን ዘግቼ አልቀመጥ
ይህ ልቤ ሰው ይናፍቀዋል
ሰው ራቀኝ ተቀየመኝ ብዬ
በጸጸት ራሴን አልቀጣም
ግዴለም እምነቴ በሱ ነው
አንድ ቀን ብጤዬን አላጣም
🎵
[ሁሉንም በሱ ላይ ትቻለሁ
ማስመሰል አልችልም አ'ቃለሁ
ብነጠል ግዴለም ልታገስ
እውነቱን እስከሚያውቁት ድረስ] 2× ||

🎶🎵🎶
@ethiobooks

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

06 Feb, 13:00


ለ ፈ ገ ግ ታ
😁 😁 😁

አባትና ልጅ ጨዋታ ይዘዋል። በጨዋታቸው መሀል አባት ልጁን መጠየቅ ይጀምራል።

አባት፦ ከእኔና ከእናትህ የበለጠ የምትወደው ማንን ነው?

ልጅ፦ ሁለታችሁንም።

አባት፦ እሺ እኔ ወደ ማሌዥያ ብሄድና እናትህ ወደ ዱባይ ብትሄድ አንተ የት ትሄዳለህ?

ልጅ፦ ዱባይ!

አባት፦ ይህ የሚያሳየው እናትህን የበለጠ እንደምትወድ ነው።

ልጅ፦ አይ፣ ዱባይን ከማሌዢያ የበለጠ እንደምወደው ነው የሚያሳየው።

አባት፦ እሺ እኔ ወደ ዱባይ ብሄድ እና እናትህ ወደ ማሌዥያ ብትሄድ አንተ ወዴት ትሄዳለህ?

ልጅ፦ ማሌዢያ!

አባት፦ ለምን?

ልጅ፦ ምክንያቱም ዱባይ መጀመሪያ ከእናቴ ጋር ስለሄድኩ።


😂 😂 😂
━━━━━━━
📖 📖 📖 📖 📖
https://t.me/Ethiobooks

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

05 Feb, 07:00


«እዳ አለብሽ ካልከኝ እከፍልሃለሁ!»
━━━━━ ✦ ━━━━━
ዶ/ር ኢዮብ ማሞ
'
«ወሳኙና ትኩረታችንን ልንጥልበት የሚገባው ነገር እኛ ለሰዎች አደረግን ብለን የምናስበው ውለታ ላይ ብቻ ሳይሆን፤ ሌሎች ለእኛ ያደረጉልንንና አሁን የደረስንበት ደረጃ ለመድረስ ወሳኝ በሆኑት ነገሮችም ጭምር ላይ ሊሆን ይገባዋል።»

ለሰዎች «ይህንና ያንን ውለታ ሰርቻለሁ» በማለት ከመዘገባቸው ነጥቦች አጠገብ፣ ሌሎች ሰዎች ለእርሱ ያደረጉለትም ጭምር በመመዝገብ ሁኔታውን አመዛዝኖ የሚመለከት ሰው እጅግ ውብ የሆነ አእምሮ ያለው ሰው ነው። እንዲህ ዓይነቱ ሰው ከራሱ ይልቅ ሌሎችን ያስቀደመ ሰው ከመሆኑ ባሻገር የትኩረትን ምስጢር በሚገባ የተረዳ ሰው ነው።

የአስራ ሦስት አመት ልጅ ነው። በእናቱ ላይ ፊቱን ካኮማተረና ካኮረፈ ሰንበት ብሏል። ለምን ጸባዩ እንደተቀያየረ ለማወቅ ብዙ ብትጠይቀውም መልስ አልሰጥ ስላላት፣ «ጉርምስና ጀምሮታል» ብላ ተወት አድርጋዋለች። አንድ ቀን ወደ እናቱ መጣና አንድን ደብዳቤ ሰጣት። በእንደዚህ መልኩ ደብዳቤን ከልጇ ተቀብላ ስለማታውቅ ለማንበብ ቸኩላ ስትመለከተው እንዲህ የሚል ጽሑፍ አገኘች።

ይህንን ደብዳቤ ለመጻፍ የፈለኩት ያለብሽን እዳ ላስታውስሽና እንድትከፍዪኝ ለመጠየቅ ነው።

→ ግቢ ውስጥ ያደገውን ሳር የቆረጥኩበት = 5 ብር
→ ክፍሌን ያጸዳሁበት = 2 ብር
→ ወደ ሱቅ የተላላኩበት = 3 ብር
→ ሱቅ ስትሄጂ ወንድምህን ጠብቅ ብልሽኝ የጠበቅኩበት = 4 ብር
→ ቆሻሻ የደፋሁበት = 5 ብር
→ ትምህርት ቤት ጥሩ ውጤት ያመጣሁበት = 5 ብር

ያለብሽ እዳ ጠቅላላ ድምር = 24 ብር

ብዙ ውለታ ያደረገችለትና በጣም የምትወደው ልጇ ሁኔታውን በዚህ መልኩ ማየቱና ያደረገውን ሁሉ እንደ እዳ መቁጠሩ በጣም አስገረማት። ሁኔታውን በምን መልክ እንደምትይዘው ካሰበች በኋላ ወረቀቱን ገለበጠችና እንዲህ የሚል የምላሽ ደብዳቤ ጻፈችለት፡-

እዳዬን ስላስታወስከኝ አመሰግናለሁ። በመጀመሪያ አንተ ያለብህን እዳ ላስታውስህና አሁንም እዳ አለብሽ ካልከኝ እከፍልሃለሁ።

→ ዘጠኝ ወር ሙሉ ማህጸኔ ውስጥ የተሸከምኩበት = ከክፍያ ነጻ
→ በታመምክ ጊዜ ሁሉ ወደ ሐኪም ቤት ያመላለስኩበትና ገንዘብ ከፍዬ ያሳከምኩበት = ከክፍያ ነጻ
→ ሌሊት ስታለቅስ ቁጭ ብዬ በመንከባከብ ያደርኩበት = ከክፍያ ነጻ
→ ከልጅነትህ ጀምሮ ጡት ያጠባሁበትና በየቀኑ ምግብ ሰርቼ ያበላሁበት = ከክፍያ ነጻ
→ መጫወቻ፣ ልብስና ጫማ የገዛሁበት = ከክፍያ ነጻ
→ አንድ ነገር እንዳይደርስብህ ወደ ፈጣሪ ጸሎት በማድረግ ያሳለፍኳቸው ቀናትና ሰዓታት = ከክፍያ ነጻ

ያለብህ እዳ ጠቅላላ ድምር = 0

ይህንን የእናቱን ደብዳቤ ያነበበው ይህ የአስራ ሦስት አመት ልጅ ሳያስበው አይኖቹ በእንባ ተሞሉ። እስከዛሬ የታየው እሱ አደረኩኝ የሚለው እንጂ የተደረገለት ነገር አልነበረም። የእናቱ ምላሽ እድሜ ልኩን የማይረሳ ትዝታን ተወለት።

አንዳንድ ሰዎች እነሱ የከፈሉትን መስዋእትነት ብቻ የመቁጠር ዝንባሌ አላቸው። ካለፈው ሁኔታቸው አልፈው እዚህ ለመድረሳቸው ምክንያት የሆናቸው ሰውና ሁኔታ እንዳለ ለማሰብ ጊዜም የላቸው።
━━━━━━━
📖 📖 📖 📖 📖
https://t.me/Ethiobooks

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

01 Feb, 09:00


ንግሥት ሁ ቺ - 2 የመጨረሻው!

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

01 Feb, 08:00


ንግሥት ሁ ቺ - 1

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

01 Feb, 07:55


          ንግሥት ሁ ቺ
               ━━━━━
«ከቁባትነት ወደ
ንግሥተ ነገሥታትነት»
              @ethiobooks

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

29 Jan, 12:00


ዋ  ስ
🤝 🤝

🤝
ዋስ ካለህ ዱቄትህን ለነፋስ አበድረው።

🤝
ዋስ ያለው አይታሰርም፣ ቀለብ ያለው ጦም አያድርም።

🤝
ያገኘ በራሱ፣ ያጣ በዋሱ።

🤝
ለዋስ አፍ የለው፣ ለጉንዳን ደም የለው።

🤝
ዋስ አይሞግት፣ ቆማጣ አይፈተፍት።

🤝
ነገር በዋስ፣ እህል በነፋስ።

🤝
ዋስ ጠርቼ ሹልክ ብዬ ወጣሁ።

🤝
ላትከፍል አትዋስ፣ ላትደርስ አትገስግስ፣

🤝
የዋስ ወንድም አይታገት፣ የአባያ ወንድም አይጎተት።

🤝
ዋሱን የሚያወጣ፣ ጢም እያወጣ።

🤝
በዋስ ያ'ለ ከብት፣ በጣት ያ'ለ ቀለበት።

🤝
ዋስ ለማቅረብ፣ ስንዴ ለመቁረብ።

🤝
ዋስ ያለው ያመልጣል፣ ዋስ የሌለው ይሰምጣል።

🤝
የዋስ ተሟጋች፣ የድውይ ፈትፋች።

🤝
የበረታ ከራሱ፣ የሰነፈ ከዋሱ።

🤝
ዋስ አይወሳወስ፣ በግ አይናከስ።

🤝
አይዋስ ቢዋሰኝ፣ ከባለ ዕዳው ጣለኝ።

     🤝   🤝
   ነገር በምሳሌ

@ethiobooks

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

28 Jan, 13:00


ዶ ል ፊ ን
🐬

🐬
ከእንስሳት ሁሉ በጣም ድንቅ ሥነ-ምግባር ያላቸው ፍጥረታት ዶልፊን እና ዝሆን ናቸው።
🐬
ዶልፊን የሰው ልጆችን በማዝናናት ፍቅሩን ይገልፃል። በመርከብ ጉዞ ወቅት ዶልፊኖች መርከቡን በማጀብና የተለያዩ ትርኢቶችን በማሳየት መርከበኞችንና ተጓዦችን ያዝናናሉ።
🐬
በመርከብ ጉዞ ላይ የዶልፊኖች መታየት የባሕር ማዕበል፣ ወጀብ፣ አውሎ ንፋስ እና የመሳሰሉ የተፈጥሮ አደጋዎች እንደማይከሰቱ ጠቋሚዎች ናቸው። በመሆኑም መርከበኞች ዶልፊንን የሰላም ምልክት አድርገው ያያሉ።
🐬
ከጎሬላ ቀጥሎ ከፍተኛ የማስተዋል ችሎታ ያለው እንስሳ ዶልፊን ነው።
🐬
አንዲት ዶልፊን ልትወልድ በምጥ ላይ እያለች ሌሎች በአካባቢው ያሉት ዶልፊኖች በሙሉ ተሰብስበው ይከቧትና እስክትወልድ ድረስ በራሳቸው ቋንቋ ያበረታቷታል።
🐬
ከአጥቢ እንስሳት እጅግ በጣም ፈጣን ዋናተኛ ዶልፊን ነው።
🐬
ዶልፊን የሚያዳምጠው በራስ ቅሉ ሲሆን፤ የሚያንቀላፋው ደግሞ አንድ ዓይኑን ብቻ በመጨፈን ነው።
🐬
ዶልፊኖች ስልጠና ተሰጥቷቸው ፀረ-መርከብ ፈንጂዎችን ከባሕር ውስጥ በመልቀም አገልግሎት ላይ ተሰማርተው የሰውን ልጅ ከአደጋ መታደግ እንደሚችሉ በተግባር ተመስክሯል።
🐬
የድምፅ ማስተጋባትን ባህርይ (Echolocation) ወይም የተፈጥሮ ራዳር በመጠቀም ምግብ አድኖ መያዝ የሚችሉ እንስሳት ዶልፊን እና የሌሊት ወፍ ናቸው።
🐬
ዶልፊኖች የሚኖሩት ውቅያኖስ እና ባሕር ውስጥ ሲሆን በዓለም ላይ ዶልፊን የሚገኝበት ወንዝ በደቡብ አሜሪካ የሚገኝ አንድ ወንዝ ብቻ ነው። በወንዝ ውስጥ የሚኖሩ እነዚህ ዶልፊኖች ዓይን የላቸውም።
🐬 🐬 🐬 🐬

━━━━━━━
📖 📖 📖 📖 📖
https://t.me/Ethiobooks

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

27 Jan, 06:45


━━━  ማላል ዮሳፍዛይ  ━━━
        @ethiobooks

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

27 Jan, 06:07


╔══💚💛♥️══╗
      ከስነ-ፅሁፍ ዓለም
    📖 📖 📖 📖 📖
አዝናኝ፣ አስተማሪና ቁም ነገር የሚያስጨብጡ ስነ-ጽሑፎችና የብዕር ውጤቶች የሚቀርቡበት የናንተው ቻናል!

የቻናላችን
👇👇👇
https://t.me/Ethiobooks  ቤተሰብ ሁኑ፣ ለወዳጅ ጓደኞቻችሁም 'share' አድርጉ።

📖 📖 📖 📖 📖

አስተያየት፣ ስነ-ፅሁፋዊ ጥቆማና ማስታወቂያ ካላችሁ

👇👇👇
@firaolbm እና
@tekletsadikK ን በመጠቀም ልታገኙን ትችላላችሁ። በአክብሮት ተቀብለን እናስተናግዳችኋለን።

🙏   አብረን እንዝለቅ።  🙏

      
@ethiobooks
╚══💚💛♥️══╝

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

25 Jan, 09:00


ማርዋን ባርጎቲ - 2 የመጨረሻው!

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

25 Jan, 08:00


ማርዋን ባርጎቲ - 1

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

25 Jan, 07:55


ማ ር ዋ ን ባ ር ጎ ቲ
━━━━━━━
«ፍልስጤማዊው ኔልሰን ማንዴላ»
@ethiobooks

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

24 Jan, 09:00


ጋብቻ ትርጉሙ
══✦══
ታገል ሰይፉ
'
አራት ግድግዳ ዝግ
የነፃነት ምሽግ
ወይም አጉል ወጥመድ
* * *
ሶስት ጉልቻ እሳት
የፍቅር ትኩሳት
አሊያም ክምር አመድ
* * *
ሁለት ባዳ ጣት ላይ
የመዛመድ ሜዳይ
አሊያም እጀ ሙቅ
* * *
አንድ ልብ ይባላል
ሲቀርቡት ደስ ያላል
ወይ ይቀፋል ከሩቅ።
════════
📔 የሰዶም ፍፃሜ
📖 📖 📖 📖 📖
https://t.me/Ethiobooks

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

23 Jan, 04:00


💬
❝የመጀመሪያው ነገር ለራስህ ሐቀኛ መሆን ነው። ራስህን ካልቀየርክ በኅብረተሰቡ ላይ ተጽዕኖ ማሳደር አትችልም።❞
ኔልሰን ማንዴላ

💬
❝በሮችህን በዘጋጋህ፣ ክፍልህንም ባጨለምክ ጊዜ ከቶም ብቻዬን ነኝ ብለህ አታስብ። እግዚአብሔርና ታላቅነትህ አብረውህ ናቸውና ብቻህን አይደለህም። እነርሱ አንተ የምትሠራውን ነገር ለማየት ምን ብርሃን ያስፈልጋቸዋል?❞
ኤፒክቲተስ

💬
❝ትዕግስት የውጤታማነት አስኳል ነው። ረዘም ላለ ጊዜ ጫን እያደረገ በር የሚያንኳኳ እንግዳ ከቤተኛው አንዱን መቀስቀሱ አይቀርም።❞
ሄንሪ ዎድስዎርዝ ሎንግፌሎ

💬
❝ሌሎችን ድል የሚያደርግ በእርግጥ ጎበዝ ነው። በራሱ ላይ ድልን የሚቀዳጅ ግን በኃያልነቱ ከማንም ይልቃል።❞
ላኦ ትዙ

💬
❝በሕይወትህ ንጋት ሥራበት፤ በተሲዓቱ ምክር ስጥበት፤ ባመሻሹ ደግሞ ጸልይበት።❞
ሔዞይድ

💬
❝ራሱን ነፃ ማውጣት የጀመረ ማንኛውም ሕዝብ ለኢኮኖሚ ባርነት ለመዳረግ አንገቱን አያስገባም።❞
ክዋሜ ንክሩማህ

💬
❝ደህና አድርጎ ለሚኖር ሰው፣ ማንኛውም የሕይወት ዓይነት ተስማሚው ነው።❞
ሳሙኤል ጆንሰን

💬 💬
ጥቅሶች
@ethiobooks

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

21 Jan, 07:15


«የማልረሳት ያች ወጣት»
━━━━✦━━━━
አሌክስ አብርሃም
'

ለመጀመሪያ ጊዜ ከደሴ ወደ አዲስ አበባ ስጓዝ ከጎኔ አንዲት ከዚያም በፊት ከዚያም በኋላ ያላየሁት ቁንጅና የነበራት ልጅ ተቀምጣ ነበር። በጧት አውቶብሱ ውስጥ  ከተከፈተው መዝሙር ጋር ተዳምሮ  በመላእክ ታጅቤ ወደገነት የምሄድ እስኪመስለኝ ውብ ነበረች። 

እናቷ አንድ ወንበር አልፈው ከኋላችን መቀመጣቸውንም በኋላ ነው ያወኩት። ገና በደንብ ሳንተዋወቅ "እናቴን ትቻት ነው አንተ ጋር የመጣሁት" ስትለኝ "ሰው እናትና አባቱን ይተዋል ..." አልኩ በውስጤ!

ያች ልጅ ከምንም በላይ ውብ የእጆቿ ጣቶች ይታወሱኛል። የፊት ለፊቱን መደገፊያ ይዛ ስለነበር መጀመሪያ በደንብ ያየሁት እጇን ነው። ወሬያችንን የጀመረችው ራሷ ነበረች "ማነው ስምህ" ነገርኳት። የእርሷንም ነገረችኝ። ተደፋፈርኩ ሲበዛ ግልፅና ፈፅሞ አይቼው የማላውቀው ዓይነት ድፍረት ነበራት።

ሳልጠይቃት የራሷንም የቤታቸውንም ስልክ ቁጥር ሰጠችኝና "በሁለቱም ካጣኸኝ ይሄ የማሚ ስልክ ነው ይሄንኛው ደግሞ የእህቴ" እያለች በአጠቃላይ የአምስት ሰው ስልክ ሰጠችኝ። በተትረፈረፈ ግልፅነቷ ትንሽ ግራ ብጋባም ደስ አለኝ! "በፈለከው ጊዜ ደውልልኝ ጧት፣ ምሳ ሰዓት፣ ከሰዓት፣ ማታ፣ ሌሊት..." አለች! ሳቄ ቀደመኝ። አልሳቀችም! እንዴት እንዴት ነው ይሄ አዲስ አበባ አልኩ።

በየመሀሉ ደግሞ ታንጎራጉራለች በሚያምር ድምፅ

ሸጋ ልጅ ጉብል ባይኔ ተመላለሰው...
ልቤ አንተን ናፍቋል አይተህ እንድታግዘው....ኧረረረረረረረ!

ዕድሜዋ 19 እንደሆነ ካነሳነው ርዕስ ጋር በማይገናኝ መንገድ ድንገት ነገረችኝ። ከዛም በፊት ከዛም በኋላ ትክክለኛ ዕድሜዋን የነገረችኝን ሴት አላስታውስም። አንዲት ሴት ትክክለኛ ዕድሜዋን ከተናገረች ነገሩ ከግልፅነትም ሊያልፍ ይችላል ብዬ መጠርጠር የጀመርኩት ከዚያ በኋላ ነው።

መጀመሪያ የምናልፋቸውን ትናንሽ ከተሞችና መንደሮችን በስም እየጠቀሰች ስትነግረኝ አዲስ እንደመሆኔና ቆንጆ እንደመሆኗ አምኛት ነበር። ይሄን ሁሉ እንዴት አወቀችው ብዬም ተገርሜያለሁ። እንደውም ማስታወሻ ሳልይዝ እቀራለሁ?! በኋላ ሁሉም የነገረችኝ ከተሞች ልክ እንዳልነበሩ ተረዳሁ። ከሚሴ የሚል ጽሑፍ አይቼ ይሄኮ ከሚሴ ነው የሚለው ብላት "ቢሆን ባይሆን ዙሮ ዙሮ እዚህ አንወርድ" አለችኝና ማንጎራጎሯን ቀጠለች።

ሸጋ ልጅ ጉብል ባይኔ ተመላለሰው...

እስከ ዛሬ ከደሴ እስከ አዲስ አበባ ያሉ ከተሞች ስም እንደተምታታብኝ አለሁ። የትኛው ከየትኛው ቀጥሎ እንደሚመጣ አይገባኝም! በተለይ ሸለብ አድርጎኝ ከነቃሁማ ሸዋሮቢት ናይሮቢ ሆና ነው የምትታየኝ። እንደ ልጅቱ አባባል ከሆነ ለምሳ የወረድነው ቡታጅራ ነው። በደሴና አዲስ አበባ መካከል ቡታጅራ የሚባል ከተማ የለም።

በኋላ ለምሳ ወርደን እናቷ መረቁኝ "ተባረክ የኔ ልጅ አስቸገረችህ ይሆን? አሉኝ! ጥያቄያቸው ግራ ገብቶኝ "አይይይ" ከማለቴ "እንዲህም አርፋ ተቀምጣ አታውቅምኮ፣ ትንሽ አሞብኝ  ጠበል ይዣት ከርሜ መመለሴ ነው። ምናምን አዙረውባት እንዲህ ሆነችብኝ" አሉ ከእኛ ራቅ ብላ ቆሎ ስትገዛ በዓይናቸው እየተከታተሏት። ቆሎና ፍራፍሬ የሚሸጡት ልጆች ከበዋት ሲንጫጩ፣ በውብና ዘለግ ባለ ሰውነቷ፣ ከነሚዘናፈል ጥቁር ፀጉሯ ላያት በደንገጡሮቿ የተከበበች ልዕልት ትመስል ነበር።

"ሁኔታችሁን አይቼ ስትጫወቱ ትንሽ ጎኔን አሳረፍኩ ተባረክ ከተኛሁ ስንት ቀኔ ካስቀየመችህም ይቅር በላት" አሉ። ልጅቱ ትንሽ የአእምሮ ህመም ነበረባት። ስትመለስ ስድስት ኪሎ ቆሎ ተሸክማ መጣችና "እስከ አዲስ አበባ ይበቃናል?" አለችኝ። "አዎ ይበቃናል" ብዬ አገዝኳትና ወደ አውቶብሳችን ገባን።

አውቶብሱ ጉዞ ሲጀምር ያለፍናትን ደብረሲና የምትባል ከተማ ናዝሬት መሆኗን ነገረችኝ። ፊቷን ሳየው ፈገግ አለች! ውበቷ የሚገርም ነበር። ንፁህና ገራገር! ህዝቡ አብዶ ነው እንጅ ደብረሲና የሚለው እርሷ ልክ ናት ደብረሲና ናዝሬት ነች። "የናዝሬት ቆሎ አሪፍ ነው" አልኳት! ትንሽ እንደተጓዝን ራሷን ከነዘንፋላ ፀጉሯ ትከሻዬ ላይ ጣል አድርጋ እንቅልፍ ወሰዳት።

አንገቴን ወደኋላዬ በቀስታ አዞርኩ ድካም ያዛላቸው እናቷ በትህትናና ሀዘን ባረበበበት ፊት ፈገግ አሉልኝ። የሆነ ለስላሳ ሀዘን ልቤ ላይ በእርጋታ ሲነፍስ ተሰማኝ።
━━━━━━━
📖 📖 📖 📖 📖
https://t.me/Ethiobooks

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

19 Jan, 11:21


ከስነ-ፅሁፍ ዓለም pinned «የ ጥ ም ቀ ት በ ዓ ል ═══ ❁ ═══ ➢ የጥምቀት በዓል አከባበር በኢትዮጵያ የተጀመረው የክርስትና እምነት እንደገባ መሆኑ ይታመናል። እስከ ስድስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ድረስ ግን የጥምቀት በዓል የሚከበረው አሁን በሚከበርበት ሁኔታ አልነበረም። ➢ በዓለ ጥምቀትን በሜዳና በውኃ አካላት ዳር ማክበር የተጀመረው በዓፄ ገብረ መስቀል ዘመነ መንግስት (530 - 544 ዓ.ም.) እንደሆነ ይነገራል።…»

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

18 Jan, 09:00


ቅድስት አርሴማ - 2 የመጨረሻው!

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

18 Jan, 08:00


ቅድስት አርሴማ - 1

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

18 Jan, 07:55


ቅ ድ ስ ት አ ር ሴ ማ
━━━━━━━
«ውበቷ ያስገደላት ሰማዕት»
@ethiobooks

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

17 Jan, 06:00


ምንድነው ምስጢሩ?
═══✦═══
ተስፋዬ ማሞ
'
እንስሳቱ ሁሉ፣ አራዊቱ ሁሉ፤
አለተፈጥሯቸው ተዋደው ሲኖሩ፣
ተቃቅፈው ሲያወሩ።
ባለ አእምሮዎቹ የእንስሳቱ ገዢ
የአራዊቱ አዳኞች
በአንድ አምሳል ተፈጥረው
ሲጋደሉ ውለው ሲጋደሉ አደሩ።

ከቶ ለምን ይሆን?
የተገላቢጦሽ የሆነው ነገሩ።
በምን ስሌት ሄደው በምን ተቃቃሩ
አልገባኝም እኔ ምንድነው ምስጢሩ
ተሳስቶ ይሆን የእግዜር 'ሶፍትዌሩ'
የእንስሳና የሰው ቦታው መቀየሩ?
═════════
🗓 ሚያዝያ 19 , 2016 ዓ.ም.
📖 📖 📖 📖 📖
https://t.me/Ethiobooks

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

15 Jan, 07:04


ም ን
🙁🙁

🙁
ምን ይዞ፣ ጉዞ።

🙁
ምን ቢፋቀሩ፣ አብረው አይቀበሩ።

🙁
ምን ይበሏል ነጭ፣ ምን ይጠጧል ጠጅ።

🙁
ምን ይሰማ ጆሮ፣ ምን ይውጥ ጉሮሮ።

🙁
በምን በላህ በሳማ፣ ባይፈጅህማ።

🙁
ምን እበላ ሲሉ እንግዳ፣ ምን እለብስ ሲሉ ዕዳ።

🙁
ምን ያመጣ ድሃ፣ ምን ያገሳ ውሃ።

🙁
ምን ቢለፈልፉ፣ ድካም ነው ትርፉ።

🙁
ምን ያህል የተባለው ዝናብ በሰማይ ደረቀ።

🙁
ምን ቢያርሱ፣ እንደ ጎመን አይጎርሱ።

🙁
ምን በእግሩ ቢመጣ፣ በእጁ እንዳይመጣ።

🙁
በምን የተነሳ፣ ይህ ሁሉ ጠባሳ።

🙁
ምን ቢዋደዱ፣ ለየቅል ነው መንገዱ።

🙁
ምን ቢወቅሱ፣ በእጅ አይካሱ።

🙁
ምን ቢፈሩ፣ ከሞት አይቀሩ።

🙁
ምን ያመጣል ሰኔ፣ ምን ይሰራል ቦዘኔ።

🙁 🙁
ነገር በምሳሌ
@ethiobooks

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

13 Jan, 07:00


📔 ምን ሆኛለሁ?

>>>
አንዳንድ ግቢዎች በቆርቆሮ ይታጠራሉ። ወደ ገጠር ከሄድክ በአጋምና በኮሽም ይታጠራሉ። በግንቡ ላይ ደግሞ «አደገኛ አጥር» የሚል እሾሀማ ሽቦ ይደረግበታል። ኃይለኛ ተናካሽ ውሻ ግቢው ውስጥ ይኖራል።

እንደየአስፈላጊነቱ ደግሞ የጦር መሳሪያ የሚሰጠው የሰለጠነ ጥበቃ ሠራተኛ ሊኖርም ይችላል። ግቢውና ቤት ውስጥ የሚገጣጠም የደህንነት ካሜራ አለ። ይህ ሁሉ አጥር ግቢው ውስጥ ያሉትን ሰዎች ከሌሎች አደጋ መከላከያ ነው። ቤት ውስጥ ገብተንም በሩ በጥሩ ቁልፍ ይቆለፋል።

ሁላችንም እንዲህ የሚታይና የማይታይ ራሳችንን ከአደጋ የምንከላከልበት አጥር አለን። እንደየአስተዳደጋችን ችግር አጥሩ እየረዘመና እየጠነከረ ይሄዳል።

ራሳችንን ከጥቃት የምንከላከልባቸው የተለያዩ ዓይነት አጥሮች ይኖሩናል። በልጅነታችን ባሳለፍነው ክፉ ትውስታ ልክ የማንፈልገውን ኮተት አልጋ ስር አድርገን ከእይታ እንደምንከላከለው ራሳችንን የምንከልልበት የራሳችን አጥርም አለን።

ችግሩ ሲመጣ አጥሩ ሳያስፈልግ እንጋፈጠው ብንል የልጅነት ትውስታችን እየመጣ ስለሚረብሸን አራቱን ዓይነት አጥሮች እንጠቀምባቸዋለን። «አንተ ተወዳጅ አይደለህም። ብቁ አይደለህም። ከሌሎች ታንሳለህ» የሚል ረብሻ ውስጥ እንዳትገባ ከቻልክ ትጋፈጠዋለህ። አሊያም ንዴትህን ዋጥ አድርገህ ጤነኛ መስለህ ለመታየት ትሞክራለህ።

ጭምብል አጥልቀህ የሆንከውና የመሰልከውን አለያይተህ ታሳያለህ። ወይም በትንሽ በትልቁ እየጮኽክ ሰዎች በጩኸትህ ስር እንዲገቡ ትሞክራለህ ካልገቡልህ ትሸሻለህ። እነዚህ ሁሉ ራስህን ከሌሎች አደጋና ጥቃት የምትከላከልባቸው አጥሮች ናቸው። እነዚህ አጥሮች የተሰሩት በልጅነታችን ነው።

ከላይ የተዘረዘሩት ሀሳቦች በልጅነታችን በህይወት እንድንቆይ ያደረጉን ናቸው። በጣምም ጠቃሚ ነበሩ። እነርሱ ባይኖሩ ምናልባት የዛሬዋን ቀን ላናይ እንችላለን፤ አስፈላጊም ነበሩ።

አዋቂነት እድሜ ላይ የሚያስፈልገን ከችግሮቻችን መሸሽ፤ ጭምብል ማጥለቅ ወይም መደንዘዝ ሳይሆን ነገሮችን በተቻለ መጠን በተረጋጋ መንፈስ ማየት እና አቅም በፈቀደው መጠን ለችግሮች መፍትሄ መፈለግ ነው።
━━━━━━━━
ትዕግስት ዋልተንጉሥ
      ቴዎድሮስ ተ/አረጋይ
📄 198 - 199
🗓 ሐምሌ 2016 ዓ.ም.

📖 📖 📖 📖 📖
https://t.me/Ethiobooks

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

11 Jan, 09:00


ኤድጋር ሁቨር - 2 የመጨረሻው!

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

11 Jan, 08:00


ኤድጋር ሁቨር - 1

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

11 Jan, 07:55


ኤ ድ ጋ ር ሁ ቨ ር
━━━━━━━
«በፕሬዝዳንቶች ጭምር የሚፈ'ሩት... »
@ethiobooks

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

09 Jan, 07:00


💿 ከፍቶኝ 💿
  ════
🎤 ለምለም ኃ/ሚካኤል 🎧
     @ethiobooks
🎼🎵🎶🎵
[ከፍቶኝ የቆየ አይመስለኝ
ባይኖር አለሁ የሚለኝ
ምክንያት ሆነልኝ ከላይ
ዘመን ራሴን እንዳይ] 2×
🎵
ጊዜ - ጊዜማ ጊዜ
ሲሆን - የባለጊዜ
ወትሮም - በዓለም የጸና
የታል - ሰው ሆኖ ጀግና
እንዴት - እንዴት ነው እንዴት
መኖር - መቻሉስ እንዴት
ወዴት - ወዴት ነው ስፍራው
ፍቅር - ሰጥቶ መኖሪያው
🎶🎵🎶
ሀቀኛው ተንቆ አፈኛው ሲፈራ
መዋል ብርቅ ሆኖበት አንዱ ባንዱ ስፍራ
ክብር ከብር ውሎ በሰው ላይመዘን
ያጣስ እንቅልፍ አለው ላገኘ ነው ማዘን
ሀ ሁ... ላይ ተክኖ ፊደል ከቆጠረው
ያውቀዋል እንደኔ ሕይወት ያስተማረው
ዓለም ለውለታ ግድም ባይሰጣት
ዐይኔን ገልጦልኛል አግኝቶ ማጣት
🎶
እህ - ለንቧ ነው እንጂ ለማር ለሰፈፏ
ማን ቀለሰ ጎጆ ማደሪያ ለወፏ
እንደ ወፍ እንደ ወፍ ያኑረኝ እንደ ወፍ
በሰው ልብ እንደ ሰው ካልታደልኩኝ ማረፍ

🎵🎶🎵
ከፍቶኝ የቆየ አይመስለኝ
ባይኖር አለሁ የሚለኝ
ምክንያት ሆነልኝ ከላይ
ዘመን ራሴን እንዳይ
🎵
ጊዜ - ጊዜማ ጊዜ
ሲሆን - የባለጊዜ
ወትሮም - በዓለም የጸና
የታል - ሰው ሆኖ ጀግና
እንዴት - እንዴት ነው እንዴት
መኖር - መቻሉስ እንዴት
ወዴት - ወዴት ነው ስፍራው
ፍቅር - ሰጥቶ መኖሪያው
🎶🎵🎶
ተቸግሮ እስኪያየው የማግኘት መዘዙን
ማን ይቆጥረው ነበር የስሙ አበዛዙን
ለካስ ዘመም ሲል መስጠት እያባራ
ከቀንም ቀን አለው በስም የሚያስጠራ
መርጠው ለክፉ ቀን ሲቸግር እንዲደርስ
የክት አይቀመጥ መቼም ሰው እንደ ልብስ
እስኪለየው ድረስ ፍሬን ከገለባ
ሰው ከእሾህ ይውላል ወይ ደግሞ ከአበባ
🎶
እህ - በርሬ በርሬ ደርሼ ከቦታው
አገኘው እንደሆን ፍቅርን ከከፍታው
እንደ ወፍ እንደ ወፍ ያኑረኝ እንደ ወፍ
በሰው ልብ እንደ ሰው ካልታደልኩኝ ማረፍ
🎵
[ጊዜ - ጊዜማ ጊዜ
ሲሆን - የባለጊዜ
ወትሮም - በዓለም የጸና
የታል - ሰው ሆኖ ጀግና
እንዴት - እንዴት ነው እንዴት
መኖር - መቻሉስ እንዴት
ወዴት - ወዴት ነው ስፍራው
ፍቅር - ሰጥቶ መኖሪያው] 2×||

     🎶🎵🎶
@ethiobooks

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

07 Jan, 13:12


ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ፳፻፲፯ ዓ.ም. የጌታችን፣ የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ።
በዓሉ የሰላም፣ የደስታና የጤና እንዲሆንላችሁ ከስነ-ፅሁፍ ዓለም ልባዊ ምኞቱን ይገልፃል።

━━━━━━━━━━━
መልካም ዐውደ ዓመት!!!
     📖  📖  📖  📖  📖
https://t.me/Ethiobooks

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

06 Jan, 07:00


ቅ ዱ ስ   ላ ሊ በ ላ
━━━ ❖ ━━━

መራ ተክለሃይማኖትና ልዕልት መሶበ ወርቅ ከወለዷቸው ልጆች አንዱ ዣንስዩም የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ኾነ።

ቅዱስ ላሊበላ ከንጉሠ ነገሥቱ ከዣንስዩምና ከእናቱ ኬረዎርና ከተባለችው ከአገው ሴት ታህሣሥ 29 ቀን 1120 ዓ.ም. ተወለደ።

ኬረዎርና ከላስታ አገው መጥታ በንጉሡ ቤት በአገልጋይነት የተቀመጠች ነበረች። ኬረዎርና ማለት ቤተክርስትያን ማለት ነው። ንጉሡ ዣንስዩም ውበቷ ስለማረከው ደረሰባት ልጅም ፀነሰች። በሌሊት በራእይ 'በዚህች ሌሊት በማሕፀንሽ የተቀመጠው ሕፃን ፈጣሪውን ለማገልገል የተመረጠ ነው።' የሚል ድምፅ ቅዱስ ሚካኤል አበሰራት። ጥቂት ቀኖችም እንዳለፉ ፅንሱ እየገፋ ኼደ።

እቴጌ ዕፅፍት የተባለችው የንጉሡ የሕግ ባለቤት መኻን ስለነበረች አልወደደቻትም፤ ኬረዎርናን ከባድ ሥራ ታሠራት ጀመር። የመውለጃዋ ጊዜ ሲደርስ እንጨት ለመልቀም እኼደችበት ጫካ ውስጥ ወለደችው። ኬረዎርና እቴጌ ዕፅፍት በተንኮል እንደተነሳችባት ስለምታውቅ ሕፃኑን ይዛ ወደ ቤተመንግሥት ለመመለስ የሚያሰጋ እንደሆነ አሰበች።

ሮሃ ከተባለው ቦታ ላይ ከአንድ ዋሻ ውስጥ አስተኛችው። 'እንድትወለድ የፈቀደ ፈጣሪህ ነው፤ ወደቤት ወስጄ ዓይኔ እያየ ከማስገድልህ ሳላይህ ከዚህ ብትሞት ይሻላል' ብላ ከዋሻው ውስጥ ትታው ኼደች።

ወደ ቤተመንግሥቱም በደረሰች ጊዜ ኬረዎርና ተዳክማ ስለነበር ወደቀች። ይኽንን የሰማ የንጉሥ አገልጋይ እየሮጠ ኼዶ የኾነውን ሁሉ ለንጉሡ ነገረው። ወዲያው ለድካሟ ማስታገሻ የሚረዳትን ነገር እንዲያደርጉላት አዘዘና ስለ ልጁ ሁኔታ ጠየቃት። እርሷም የተፈፀመውን ሁሉ ገለፀችለት።

ንጉሡም አዛዡንና አገልጋዮቹን ጠርቶ ትታው ወደ መጣችበት በቶሎ ይዘዋት እንዲኼዱና በሕይወቱ ቢገኝ መልካም፣ በሕይወቱም ባይገኝ ሬሳውን በፍጥነት እንድታመጡልኝ ብሎ ላካቸው። እነርሱም እንደታዘዙት ሁሉ እየተፋጠኑ ኼደው ሕፃኑ ወደ አለበት ደረሱ።

በዚያን ጊዜ ንቦች ከላዩ ላይ ሰፍረው አገኙት። የንቦቹ በህፃኑ ላይ መስፈር ያስደነቃቸው 'ላልይበላ' አሉት። በአገው ቋንቋ 'ላል' ማለት ማር ማለት ስለሆነ 'ማር ይበላል' ማለት ነው።

ፈላጊዎች ንብ ሰፍሮበት በመገኘቱ ሊመግቡት ይሆናል በማለት ላሊበላ ቢሉትም፤ እሱ ግን አድጎ በንጉሥነት፣ በመሪነት በመቀጠሉ ሕዝብና ንብን በማመሳሰል የተነገረለት ምስጢራዊ ትንቢት ተፈፃሚነትን አገኘለት። ስሙም ላሊበላ ተብሎ በመሪነት ኖረ።

መንፈሳዊው ንጉስ ላሊበላ  ከሚታወቅባቸው ነገሮች አንዱና ዋንኛው  በዘመኑ ከአንድ ወጥ ድንጋይ ያስፈለፈላቸው አስራ አንድ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት ናቸው፡፡ ፍልፍል አብያተ ክርስቲያናቱ በሶስት መደብ የተከፋፈሉ ሲሆኑ፤ ሁሉም የመሬት ውስጥ ለውስጥ መተላለፊያ ያላቸው ናቸው፡፡

በመጀመሪያው መደብ ውስጥ ቤተ መድኃኒዓለም፣ ቤተ-ማርያም፣ ቤተ-መስቀል፣ ቤተ-ደናግል፣ ቤተ-ጎለጎታ እና ቤተ-ሚካኤል ሲገኙ፤ በሁለተኛው መደብ ውስጥ ደግሞ፣ ቤተ-አማኑኤል፣ ቤተ-መርቆሪዮስ፣ ቤተ-ሊባኖስ እና ቤተ-ገብርኤል ይገኛሉ። በሶስተኛው መደብ ውስጥ የሚገኘው ቤተ-ጊዮርጊስ ነው፡፡

ቤተ-ጊዮርጊስ ከሁሉም አብያተ ክርስቲያናት በስተመጨረሻ የተሠራና እጅግ ያማረ፣ በኪነ ህንፃ ውበቱም ከሁሉም የላቀ ነው፡፡ ይህም የአብያተ ክርስቲያናቱ ሠሪዎች በሥራቸው ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተራቀቁ የመምጣታቸው ምስክር ነው፡፡ አብዛኛውን ጊዜም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናት ሲወሱ የሚታየው ምስል የዚሁ የቤተ-ጊዮርጊስ ምስል ነው፡፡

ገድለ ላሊበላ እንደሚያስረዳው የፍልፍል አብያተ ክርስቲያናቱ ሥራ የተጀመረው  በላሊበላ አስረኛ ንግሥ ዘመኑ ነው፡፡ ሥራውን ለማጠናቀቅም 23 ዓመታት ፈጅቷል ይላል - ገድለ ላሊበላ።

የቅዱስ ላሊበላ የልደት ቀን ታህሳስ 29 የገና ዕለት በስሙ በተሰየመችው በቀድሞዋ ሮሐ ባሁኗ ላሊበላ በታላቅ ድምቀት ይከበራል።
━━━━━━━━
📖 📖 📖 📖 📖
https://t.me/Ethiobooks

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

06 Jan, 05:16


╔══💚💛♥️══╗
      ከስነ-ፅሁፍ ዓለም
     📖 📖 📖
'
የቻናላችን
👇👇👇
https://t.me/Ethiobooks  ቤተሰብ ይሁኑ፣ ለወዳጅ ጓደኞችዎም 'share' ያድርጉ።
📖  📖  📖  📖  📖

ለማንኛውም አስተያየት፣ ስነ-ፅሁፋዊ ጥቆማና ማስታወቂያ ፦
@firaolbm እና
@tekletsadikK ን ተጠቀሙ።
በአክብሮት እንቀበላለን።

🙏   አብረን እንዝለቅ።  🙏
       @ethiobooks
╚══💚💛♥️══╝

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

04 Jan, 09:00


አሊ ቡቶ - 2 የመጨረሻው!

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

04 Jan, 08:00


አሊ ቡቶ - 1

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

04 Jan, 07:55


ዙልፊካር አሊ ቡቶ
━━━━━━━
«እህል ላበደረ አፈር፣
ወርቅ ላበደረ ጠጠር»
@ethiobooks

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

03 Jan, 09:00


ከራስነት እስከ ትራስነት
═══ ✦ ═══
ካሳሁን ከበደ
'
ተነሣ ተራመድ ... ክንድህን አበርታ
ለሀገር ብልጽግና
ለወገን መከታ (1966)

አበርትቶ አሳየኝ
እሷ ትቅደም ብሎ
የማይጣለውን ከሚጣል ነጥሎ።

የኔን ግን ማን አየው?
ፈርጣማ ጡንቻዬን
ስራስራም ክንዴን
ከነ 'ብራስሌቱ'

እሷ ትቅደም ብሎ 'ልክ እሱ እንዳረገው'
በ'ሎሽን' ለስልሶ
በትራስነት 'ለክብር' ሲያውለው
የእኔንስ ማን አየው?
የሚለይ ይለየው።
═════════
📔 ከጃርት ወደ ዳርት
🗓 2ለት ሺህ ዓ.ም.
📖 📖 📖 📖 📖
https://t.me/Ethiobooks

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

02 Jan, 13:00


>>>
ሕይወት እንደ ፈጠራ ድርሳን ወጥ ምስልን አትሰጥም። በሰመረ ምክንያትና በተዋጣለት ድርጊት አትሰናከልም።

በትርጉም መፋለስ የተላለፉና የተጣጡ ሰዎች በእውነተኛው ዓለም በስተመጨረሻ አይገናኙም። ወደ አንድ መሥመር አይመጡም። አይገነዛዘቡም። አስተያየት የሚያደርግላቸው ሁሉን አወቅ ደራሲ አያገኙም።

ማንንም ለማስደሰትና ለማሳዘን አይደለም። ሕይወት ገለልተኛ መድረክ ናት። የባለወንጭፉ ዳዊትን ገድል ለማሳመር ብላ የባለ ስል ሰይፉ ጎልያድን ገድል አታበለሻሽም።

ትዕይንቱ በተዋናዮቹ 'ኢምፕሮቫይዜሽን' ይወሰናል። እስኪ የሕይወት መድረክ ላይ ወጣ ብለህ ስንት ዳዊቶች በአንድ የጎልያድ ሰይፍ እንደተገደሉ ቁጠር?

>>>
━━━━━━━━
📄 24
🗓 ሐምሌ 2012 ዓ.ም.

📖 📖 📖 📖 📖
https://t.me/Ethiobooks

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

31 Dec, 11:00


ጥ ጃ
🐮 🐮

🐮
ጥጃ ቢፈነጭ በሜዳ፣ ውሃ ቢሄድ በጎድጓዳ።

🐮
ያሳደግኋት ጥጃ፣ አለችኝ በእርግጫ።

🐮
ጥጃ ሣር ይበላል፣ ቤቱ ዕዳ ይሞላል።

🐮
የሚጠባ ጥጃ አይጮኽም።

🐮
ጥጃ ቢሳሳት ከእናቱ፣ ነገር ቢሳሳት ከጠዋቱ።

🐮
ለላም ጥጃዋ፣ ለአህያ ውርንጭላዋ።

🐮
ስድ የለመደ ጥጃ፣ ሲይዙት ያጓራል።

🐮
ጥጃ ጠባ፣ ከሆድ ገባ።

🐮
ያሞሌ ጥጃ፣ በወንዟ ትፋፋ።

🐮
ከበሬ ፊት የምትገኝ ጥጃ፣ የሣር በሽታ ይገድላታል።

🐮
የሚያድግ ጥጃ ከገመዱ፣ የሚያጠግብ ቂጣ ከምጣዱ።

🐮
ከርሞ ጥጃ፣ አድሮ ቃሪያ።

🐮
በሬ ሲያረጅ ከጥጃ ጋር ይውላል።

🐮
ፍቅርህን የፈለገ ልጅህን፣ ጠብህን የፈለገ ጥጃህን።

🐮
ጥጃዬም አይከሳ፣ ወተቷንም አለቅ።

🐮
ሲጠባ ያደገ ጥጃ፣ ቢይዙት ያጓራል።

🐮 🐮
ነገር በምሳሌ

@ethiobooks

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

30 Dec, 08:02


አ ል ቅ ት
━✦━

ያ ደግ ሰው፣ ጎድኑ የገጠጠ ጥጃ በመንገዱ ላይ ሲኼድ አገኘው። አንዳንድ ጊዜ ጥጃ ይሰማ የለ! ትንሽ የማንቂያ ቃል እንዲህ ሲል ነገረው።

«ሰው በእናትህ ጡት ላይ የተለጠፈ አልቅት ነው። ላንተ ግን ወተቱን ትተህ፣ ከድርሻህ ርቀህ፣ ጎሽ በሚኖርበት አካባቢ ለምለም ሣር መጋጥ ይሻልሃል»

ጥጃውም ያን ደግ ሰው እየተመለከተ፡ «ዳቦ የሚበላ ሰው ወተት ይጠጣል? ደሞ ሰው ከላም ሳይወለድ የእናቴን ጋት መንካቱ ልክ አይደለም» አለው።

ያ ደግ ሰው፡ «እንግዲያስ እውነቱን ካልከኝ፣ አሳዳሪህ "አሳዳሪህ" አይደለም። መኖሪያህም በረት አይደለም። እውነት ይመስልሃል? አንገትህ ላይ ያለው ገመድ "እንዳትጠፋ ነው" ሲሉህ ታምናቸዋለህ? ከመሬት ላይ ወዴት ነው የሚጠፋው?

ለማንኛውም ብዙ የሚያባብልህ ብዙ የሚጎዳህ ነው። ሣር አጭዶ የሚያቀርብልህ ኋላ አንተን ያጭድሃል። አኹን ደግ ሰው "ክፉ ነው" ብልህ መች ይገባሃል?

ለእርድ የሚውል በሬ በመንገድ ላይ፣ የሚቆረጠም ቆሎ በምጣድ ላይ ይታመሳሉ። እንግዲህ የመብሰል መልኩ ብዙ ነው። መኼድም እየታመሱ ነው» አለው።

ጥጃው የደጉ ሰው ንግግር አልገባውም ነበር። ቢኾንም፣ ደስ የሚለውን ጨዋታ እየተጫወተ፣ እግሩን ወደ ላይ እያጎነ ኼደ።
━━━━━━━━━
📔 ግርባብ - ያ ደግ ሰው
ፍቃዱ አየልኝ
📄 17 - 18

📖 📖 📖 📖 📖 
https://t.me/Ethiobooks

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

28 Dec, 10:25


ጆን ጋራንግ - 2 የመጨረሻው!

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

28 Dec, 08:01


ጆን ጋራንግ - 1

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

28 Dec, 08:01


         ጆ ን   ጋ ራ ን ግ
             ━━━━━━
       «የጦርነትና የሰላም ሰው»
             @ethiobooks

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

27 Dec, 09:00


📔 ዮቶር ፪ ፡ ቶ

ያልተጀመረ መች ያልቃል?

ቃል ሥጋ እንደኾነው -
ሥጋ ይኾናል እንጂ ቃል፤
የረቀቀም እንደ ገዘፈ -
የገዘፈም ይረቅቃል፤
ታላቁ ውቅያኖስም -
ካ'ንዲት ዛፍ ስር ይፈልቃል፤
ባሕር ኾኖ ለመወለድ -
ምንጩም ከወንዝ ይጠልቃል፤
እንጂ -
መች ጉዞ ያበቃል?
═══════
ዓለምአየሁ ደመቀ
🗓 ግንቦት 2016 ዓ.ም.
📖 📖 📖 📖 📖
https://t.me/Ethiobooks

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

26 Dec, 07:02


አንዳንድ እውነታዎች ስለ ካንሰር
━━━━━✦━━━━━

→ ሁሉም ሰው በካንሰር ሊጠቃ ይችላል።

→ ከ100 በላይ የካንሰር ዓይነቶች ያሉ ሲሆን ከግማሽ በላይ የሚሆኑ የካንሰር ዓይነቶችን መከላከል ይቻላል።

→ 90 በመቶ የካንሰር መንስኤ አካባቢያዊ ሲሆን 10 በመቶ ደግሞ ዘረ-መላዊ (ከወላጆች በዘር የሚወረስ) ነው።

→ በዓለማችን በካንሰር ምክንያት ከሚፈጠረው አጠቃላይ ሞት ውስጥ ትምባሆ ማጨስ 25 በመቶ የሚሆነውን ድርሻ ይይዛል። 90 በመቶ የሳምባ ካንሰር መንስኤም ሲጋራ ማጨስ ነው።

→ አንዲት ሲጋራ ውስጥ ከ7 ሺህ በላይ ኬሚካሎች አሉ፡፡ ከእነዚህ ውስጥ ከ70 በመቶ የሚበልጡት ካንሰር አምጪ ናቸው።

→ በዓለማችን በካንሰር ምክንያት ከሚፈጠረው አጠቃላይ ሞት ውስጥ አልኮል መጠጣት ከ3 እስከ 5 በመቶ ድርሻ ይይዛል።

→ ዓለም ላይ ሴቶችን በብዛት የሚያጠቃው የካንሰር ዓይነት የጡት ካንሰር ነው።

→ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማድረግ በጡት ካንሰር የመያዝ እድልን ከ25 - 30 በመቶ ይቀንሳል።

→ ወንዶችን በብዛት ከሚገድሉ የካንሰር ዓይነቶች ውስጥ የሳምባ ካንሰር፣  የጉበት ካንሰር፣  የጨጓራ ካንሰር፣ የአንጀት ካንሰር እና የፕሮስቴት እጢ ካንሰር ይጠቀሳሉ።

→ ሴቶችን በብዛት ከሚገድሉ የካንሰር ዓይነቶች ውስጥ የጡት ካንሰር፣ የሳንባ ካንሰር፣ የአንጀት ካንሰር፣ የማህፀን በር ካንሰር እና የጨጓራ ካንሰር ይጠቀሳሉ፡፡

→ ካንሰር የዓለም ኢኮኖሚን ክፉኛ እየጎዳ ይገኛል። የዓለም ሀገራት በዓመት ከ1 ትሪሊዮን ዶላር በላይ ለካንሰር ሕክምና ያወጣሉ።

→ ትምባሆ ባለማጨስ፣ አልኮል ባለመጠጣት፣ ጤናማ አመጋገብ በመከተል እና የአካል ብቃት እንቅስቃሴ በማድረግ ብቻ የካንሰር ተጋላጭነትን እስከ 30 በመቶ መቀነስ ይቻላል። 
━━━━━━━
📖 📖 📖 📖 📖
https://t.me/Ethiobooks

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

24 Dec, 13:00


💬
❝ሥራ ከሦስት ታላላቅ ሰይጣናዊ ድርጊቶች ይጠብቀናል። እነሱም ስንፍና፣ ክፉ ተግባር እና ድህነት ናቸው።❞
ቮልቴር

💬
❝99% የሚሆኑ ሰዎች ሀሳብህን ከተጠራጠሩህ፣ እጅጉን ስተሀል አልያም ታሪክ ልትሰራ ነው።❞
ስኮት ቤልስካይ

💬
❝ሰውን ሰው ያደረገው ልብስ ነው። እርቃናቸውን የሆኑ ሰዎች በማኅበረሰቡ ምንም ተሰሚነት የላቸውም።❞
ማርክ ትዌን

💬
❝ተፈጥሮ ንጹህና ምርጥ ጓደኛ ናት።❞
ዊልያም ወርድስወርዝ

💬
❝ታላቅ ስልጣኔ የሚመጣው በሰው አእምሮ ውስጥ በሚገኝ ነፃነት ነው።❞
ፍሬድሪክ ኒቼ

💬
❝ቴክኖሎጂን ያለጥበብ እና ጥንቃቄ መፍጠር ከቀጠልን፣ እንዲያገለግሉን የምንፈጥራቸው ማሽኖች አጥፊዎቻችን ሊሆኑ ይችላሉ።❞
ጄኔራል ኦማር ብራድሊ

💬
❝የግንባራችንን መሸብሸብ ልባችን አይወቀው።❞
ጀምስ ጋርፊልድ

💬 💬
ጥቅሶች
@ethiobooks

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

30 Nov, 09:00


የቶራጃዎች ባህል
"Manene tradition" - 2 የመጨረሻው!

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

30 Nov, 08:00


የቶራጃዎች ባህል
"Manene tradition" - 1

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

30 Nov, 07:50


▶️ የቶራጃዎች ባህል
"Manene tradition"
━━━━━━━
«ከመዋቲዎች ጋር መኖር»
@ethiobooks

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

29 Nov, 06:00


ጅማሬ ሰበብ
══ • ══
የሰው ልጅ፦
ጥፋቱን በሰው ላይ
ሊያሳብብ ሲሞክር
በውሸት ማጭበርበር
ማታለል ሲጀምር
የቆመውን ድንጋይ
በካልቾ ነርቶ
"እንቅፋት መ'ቶኝ ነው"
ይላል አፉን ሞልቶ።
═══════
📖 📖 📖 📖 📖

የዕንቅልፍ ዋጋ
══ • ══
የ'ስፖንጅ ፍራሹ
ቤቴ ቢዘረጋ
ብርድ ልብስ አንሶላው
ቢነጠፉ ባልጋ
ከቶ ምን ሊረቡ
ሲመሽ ቢሰናዱ
መኝታው ቢኖርም
ዕንቅልፉ ነው ውዱ።
═══════
አንዱዓለም ኪዳኔ
📔 በዝናብ ቅጠሪኝ
📖 📖 📖 📖 📖
https://t.me/Ethiobooks

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

27 Nov, 13:00


ቀ ጭ ኔ
🦒  🦒

🦒
ከእንስሳት ሁሉ በርዝመት ቀጭኔን የሚወዳደር የለም። የአንድ ጎልማሳ ወንድ ቀጭኔ ቁመት እስከ 5.5 ሜትር ይረዝማል።
🦒
ቀጭኔ ራሷን ከጥቃት ለመከላከል በዋነኝነት የምትጠቀመው እግሮቿን ነው። ረዣዥም እግሮቿ እንደ አንበሳና ጅብ ከመሳሰሉት አጥቂዎቿ ለመከላከል ይጠቅሟታል። ቢሆንም በምድር ላይ ቀጭኔን የሚያሰጋት አዳኝ እንስሳ አንበሳ ነው።
🦒
ቀጭኔዎች በቀን እስከ 45 ኪ.ግ. የሚደርስ ቅጠሎችና ቀንበጦችን የሚመገቡ ቢሆንም ብዙ ውሃ ግን አይጠጡም። ምክንያቱም አብዛኛውን ውሃ የሚያገኙት ከቅጠላ ቅጠል ምግባቸው ነው።
🦒
የቀጭኔ ምላስ ቀለም ሰማያዊ ነው። ጆሮዎቿን የምታጸዳውም ግማሽ ሜትር በሚረዝመው ምላሷ ነው።
🦒
በቀጭኔ አንገት ውስጥ ያለው የአከርካሪ አጥንት ብዛት በሰው አንገት ውስጥ ካለው የአጥንት ብዛት እኩል 7 ነው።
🦒
ከእንስሳት ሁሉ ከፍተኛ የደም ግፊት ያላት ቀጭኔ ናት። ይህም ግፊት ደም ከልቧ ተነስቶ ረዥም ጉዞ በመዘዋወር በርቀት ወዳለው ጭንቅላቷ በቀላሉ እንዲደርስ ይረዳታል።
🦒
የቀጭኔ ልብ ከግማሽ ሜትር በላይ ርዝመት አለው።
🦒
ቀጭኔ የምትወልደው ቆማ ሲሆን፤ ግልገሉ በ2 ሜትር ከፍታ ላይ ከሚገኘው ማህፀን ተገፍትሮ መሬት ላይ ቢፈጠፈጥ ምንም ዓይነት ጉዳት አይደርስበትም። እንዲያውም በ30 ደቂቃዎች ውስጥ መቆም እና ከሰዓታት በኋላ ደግሞ መሮጥ ይችላል።
🦒
ቀንድ መሰል አካል ያላትና ከነቀንዷ የምትወለድ ብቸኛ እንስሳ ቀጭኔ ናት።
🦒
ቀጭኔ በተፈጥሮ ሀብለ ድምፅ (vocal chord) የላትም። በዚህም ምክንያት የዓለማችን ዝምተኛዋ ወይም ድምፅ አልባዋ እንስሳ በመባል ትታወቃለች።
🦒
የቀጭኔዎች አማካይ ዕድሜ 25 ዓመት ቢሆንም እስከ 40 ዓመት ድረስ በሕይወት ሊኖሩ ይችላሉ።
━━━━━━━
📖 📖 📖 📖 📖
https://t.me/Ethiobooks

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

26 Nov, 07:00


📔 አለመኖር 

>>>
የሰው ልጆች በመጀመሪያ በውልደት ወደዚህ ዓለም ስንመጣ፤ የመጀመሪያው ትግላችን ከአመኖር ጋር መታገል ነው። እርግጠኛ ነኝ ስለ ልጅ አወላለድ ያስተማሯችሁ መምህሮቻችሁ፤ የመጀመሪያው አንድ ደቂቃ ከሚቀጥሉት  አርባ ዓመታት በላይ የበለጠ ፋይዳ አለው ብለዋችኋል።

እውነት ነው። ምክንያቱም የመጀመሪያው አንድ ደቂቃ ከመሞት በፊት ያለው ትልቁ የሕይወት ለውጥ ነው። በእርግጥ መምህሮቻችሁ ይህን ያስተማሯችሁ ህፃን ልጅ ሲወለድ በአግባቡ አለመተንፈሱ በአንጎሉ ዕድገት ላይ የሚያደርሰውን ተጽዕኖ ትኩረት በመስጠት ነው። ለኔ ግን ከዚያም በላይ ፋይዳ አለው። ማለትም ሰው ሲወለድ የለመደው በጎ ነገር በጠቅላላ ይቀየራል።

በእናት ሆድ ውስጥ ጥጋብ ነው፤ ረሃብ የለም። በእናት ሆድ ውስጥ ሙቀት ነው፤ ብርድ የለም። ከሁሉ በላይ ግን በእናት ሆድ ውስጥ ጣዕር የለም። መሥራት የለም። በምቾት መንፈላሰስ እና በለስላሳ ውሃ ውስጥ መንሳፈፍ ነው።

ይህ ሁሉ ድሎት በተወለድንበት ቅጽበት ይለወጣል። መተንፈስ ግድ ይላል። ረሃብን ለማስታገስ መጥባት እንጀምራለን። ይበርደናል፤ ሙቀት ለማግኘት ከሌላው እንጠጋለን። ለመኖር። አለበለዚያ መኖር የለም። መታፈን፣ በረሃብ አለንጋ መቆላትና በብርድ ቆርፍዶ መሞት የፍርሃታችን መነሻ ይሆናሉ።

በእናታችን ማህፀን ውስጥ የምናውቀው መኖርን ብቻ ነው። መወለድ ግን አለመኖርን አመላካች ነው። ይህ ስጋት ታዲያ በሕይወታችን ሙሉ የሚዘልቅ ነው። በየደረጃው፣ በየዕድሜያችን  ለአለመኖር ስጋት እንደተጋለጥን እንዘልቃለን።

የምንኖርበት ዓለም ደግሞ የሰው ልጅ የዘመናት የአለመኖር ስጋቱን ለማስወገድ በመመኘት የገነባው የአኗኗር ስርዓት አለው። ይህም ስርዓት ከመወለዳችን ይረከበናል።

ወላጆች፣ ዘመድ፣ ጎረቤት፣ ሰፈር፣ ብሄር፣ ሀገር፣ ቋንቋ፣ ባህል፣ ሃይማኖትና ልምድ ያሉበት ዓለም ከእኛ ቀድሞ ይጠብቀናል። ይህ ሁሉ ባለበት ዓለም ተወልደን፣ በእኚህ ቀድመው በተዘጋጁ ስርዓቶች ውስጥ አለመኖርን ሸሽተን ለመኖር ስንል እንታሰራለን።
>>>
━━━━━━━━━
ዳዊት ወንድማገኝ (ዶ.ር)
📄 5 - 6
🗓 ፳፻፱
ዓ.ም.
📖 📖 📖 📖 📖
https://t.me/Ethiobooks

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

25 Nov, 07:00


💬
❝በሰው ዘር ታሪክ ውስጥ አለማወቅ ከአዋቂነት ተሽሎ የተገኘበት ጊዜ ተፈልጎ አይገኝም።❞
          ኔይል ዳ'ግራሴ ታይሰን

💬
❝በድህነት ውስጥ ለረዥም ጊዜ ስትኖር ሕይወት ከዚያ ውጭ ያለ አይመስልህም።❞
ኦፕራ ዊንፍሬ

💬
❝የተደበቀን ዕውቀት የሚያከብርና፣ የተደበቀን ውበት የሚያደንቅ ጥቂት ነው።❞
ኤራስመስ

💬
❝በዚህ ዓለም ላይ ጥሩ ወይም መጥፎ ነገር የለም። ያንን የሚፈጥረው ግን ሃሳባችን ነው።❞
ሼክስፒር

💬
❝የተሳካለት ፖለቲከኛ ማለት አጥር ላይ ቆሞ መድረክ ላይ እንደሆነ ሰዎችን የሚያሳምን ነው።❞
ዲዝራኤሊ

💬
❝አርበኝነት ማለት፣ ዕድሜው አጭር የሆነ የስሜት ድንፋታ ሳይሆን ሕይወት እስካለ ድረስ የሚደከምበት የረጋና የማያወላውል ቅን አገልግሎት ነው።❞
አድሌይ ስቴቨንሰን

💬
❝በሰዎች ተፈጥሮ ከፍተኛው ግፊት ትልቅ የመሆን ፍላጎት ነው።❞
ዶክተር ጆን ዴዊ

💬 💬
ጥቅሶች
@ethiobooks

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

23 Nov, 09:00


ዴቪድ ፍሮስት - 2 የመጨረሻው!

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

23 Nov, 08:04


ዴቪድ ፍሮስት - 1

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

23 Nov, 07:57


▶️ ዴ ቪ ድ ፍ ሮ ስ ት
━━━━━━━
«ሰይፈኛው ጋዜጠኛ»
@ethiobooks

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

22 Nov, 05:00


አያሻም መደነቅ
══✦══
ፀሐይ መልአኩ
'
ማንኛውም ነገር -
ያለው በዚች ዓለም፣
ጊዜያዊ ነው እንጂ -
ቋሚ ነገር የለም፤
ተደንቆ ይናቃል፣
ተነስቶ ይወድቃል፤
ተናፍቆ ይረሳል፣
ከብሮ ይገሰሳል።

መከላት መተካት -
ደንቡን ስለማይለቅ፣
ለመጣ ለሄደው -
አያሻም መደነቅ።
ሰው እስካለ ድረስ
እንዳይጎዳው ሃሳብ
እንዳይጎዳው ጭንቀት፣
ቢያጤን ይጠቅመዋል -
ሂደትን በጥልቀት፤
ስለሚገኝ ዕውቀት -
ከትውፊት ከተግባር፣
ከንዝህላል ውድቀት -
ብልጥነት ነው መማር። ════════
📔 የስሜት ትኩሳት
📖 📖 📖 📖 📖
https://t.me/Ethiobooks

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

20 Nov, 07:00


ዐዋቂ / አላዋቂ
   🤔    🤔

🤔
ዐዋቂ ይርዳኝ፣ ሸንጎ ይፍረደኝ።

🤔
ያላዋቂ ቆራሽ፣ ማዕድ አበላሽ።

🤔
ዐውቆ መተው፣ ነገሬን ከተተው።

🤔
ላዋቂ ምክር፣ ላላዋቂ በትር።

🤔
ዐዋቂ ሲበዛ፣ አስታራቂ ይሞታል።

🤔
ከዐዋቂ ጠያቂ፣ ከጠያቂ አጥባቂ።

🤔
ባላወቀው ፈርዶ፣ አደረገው ባዶ።

🤔
ዐወቅሽ ዐወቅሽ ሲሏት መጽሐፍ አጠበች።

🤔
ያወቁ ሲታጠቁ፣ ያላወቁ ተሳሳቁ።

🤔
ዐውቆ የተኛን ቢጠሩት አይሰማም።

🤔
ለዐዋቂ አትወቅበት፣ ለረዥም አትከንዳበት።

🤔
ዐውቆ የሚያጠፋ፣ ኑሮው ምን ይከፋ።

🤔
ባላዋቂ ቤት፣ እንግዳ ናኘበት።

🤔
ዐውቀው በድፍረት፣ ሳያውቁ በስህተት።

🤔
ያላዋቂ ሳሚ፣ ንፍጥ ይለቀልቃል።

🤔
ዐዋቂ፣ አስታራቂ።

🤔
ዕወቅ ያለው ባርባ ቀኑ፣ አትወቅ ያለው ባርባ ዘመኑ።

     🤔   🤔
   ነገር በምሳሌ

@ethiobooks

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

18 Nov, 06:48


━ ደራሲና ተርጓሚ ባሴ ሀብቴ ━
          (1942 - 1988)
          @ethiobooks

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

15 Nov, 08:00


እንዳንተ ማን አለ ?
═══❖═══
አበራ ለማ
'
እንዳንተ ማን አለ -
     የወደቀ ፍሬ እሚያነሳ
የሰው ልጅ ሲጨቀይ -
     እድፉን አጥቦ እሚያነጻ?
ማን አለ? እኮ ማን አለ?
     ካንተ ሌላ - ለኔ ብጤው የዋለ
ማን አለ? እምዬ ናት አልል
     ከእምባ ግብር ሌላ አትከፍል፤

ስደቴን ሳስታምመው -
     መከራዬ ሲበረታ
ዋስ ስጠራህ የቆምክልኝ -
     የክፉ ቀናቴ ጎልጎታ፣
አሁን እንዳንተ ማን ደግ አለ
ለለመነው፣ ለተማጸነው -
በተጠራበት የዋለ?

እንደ ሰው ልብ ያልሻከርክ
ጥንትም የነበርክ
ዘለዓለማዊ አርኬ
አንተው ብቻ ነህ! ... አምላኬ።
══════════
📔 አውጫጭኝ - ግጥሞች
🗓 1994 / 2002

📖 📖 📖 📖 📖
https://t.me/Ethiobooks

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

14 Nov, 06:01


ስርቅታ ምንድነው?
━━━✦━━━

ስርቅታ ለመተንፈሻነት የሚያገለግለው ጡንቻ (ዲያፍራም) እና የአየር ቧንቧ እየደጋገመ ሲኮማተር የሚፈጠር፣ ጉሮሮን እንቅ እያደረገ የሚወጣ ድምፅ ወይም ህቅታ ነው።

በአገራችን ልማድ በሩቅ ያለ ዘመድ ወይም የቅርብ ሰው ስምን በሚያነሳ ጊዜ (በሀሜት ምክንያት) ስሙ የተነሳው ሰው ስርቅታ ይመጣበታል የሚል አባባል አለ። እንዲያውም ስርቅታ ሲጀምር "ማን አነሳኝ?" ይባላል። ነገር ግን ይህ ሳይንሳዊ መሰረት የለውም።

በጣም በመጥገብ፣ ማለትም ሆድ በምግብ ሲወጠር፣ የጨጓራ የሙቀት መጠን ሲቀየር፣ አልኮል መጠጥና ሲጋራ አብዝቶ ሲወሰድ፣ ከመጠን በላይ መዳከም ሲኖር ወይም ከባድ የፍራቻ ስሜት ውስጥ ሲገባ ለመቆጣጠር በማይቻል ሁኔታ ስርቅታ ይፈጠራል።

ስርቅታ በሚመጣ ጊዜ በቀላሉ ማስቆም ከሚቻልባቸው መንገዶች ጥቂቱን እነሆ፦

• የወረቀት ቦርሳ (የካኪ ፖስታ) ውስጥ መተንፈስ፤ ማለትም አፍና አፍንጫን በከረጢቱ ውስጥ አድርጎ መተንፈስ አንዱ መፍትሄ ነው።

• በተለምዶ ትንፋሽን ይዞ ከመቆየት ባሻገር ሎሚን መምጠጥም ሌላኛው መፍትሄ ነው።

• ከምላስ ስር አንድ ማንኪያ ስኳር ወይም ማር ማድረግና መምጠጥም ስርቅታን ሊያስቆም ይችላል።

• ጆሮን ማሻሸት ሌላኛው መፍትሄ ነው። ይህን በማድረግና የነርቭ ስርአትን በማነቃቃት ሆድ ላይ የሚፈጠር ጫናን መቀነስ ይቻላል።

• ጉሮሮ አካባቢ ላይ አነስ ያለ በረዶን ለተወሰኑ ጊዜያት ማሸትም ስርቅታን ለማስቆም ይረዳል።

• አንድ ብርጭቆ ቀዝቃዛ ውሃን ጠረጴዛ ላይ በማስቀመጥ አጎንብሶ መጠጣት።

• በመምጠጫ ወይም በስትሮው ውሃን መጠጣት፤ ውሃው በሚጠጣበት ጊዜም ጆሮዎችን በጣት ደፍኖ መያዝ ስርቅታን ለማስቆም የሚረዱ መፍትሄዎች ናቸው።

እስቲ ይሞክሯቸውና ውጤቱን ያረጋግጡ!!!
━━━━━━━
📖 📖 📖 📖 📖
https://t.me/Ethiobooks

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

12 Nov, 12:00


ቫ ቲ ካ ን
🇻🇦

➥  አንዲት ሀገር እንዳለች ሙሉ በሙሉ በዩኔስኮ በዓለም ቅርስነት ተመዝግባለች። ይህች ሙሉ ይዘቷ በዩኑስኮ ቅርስነት የተመዘገበው ሉዓላዊት ሀገር ቫቲካን ናት።

➥  ቫቲካን የዓለማችን ትንሿ ሀገር ስትሆን የቆዳ ስፋቷ 44 ሔክታር ነው። በቆዳ ስፋት ትንሽ ሀገር ብትመስልም በዓለማችን ላይ ቁጥር አንድ ተፅዕኖ ፈጣሪ ሀገር ናት።

➥  የህዝቧ ብዛት 932 ብቻ ሲሆን ያላት የባቡር ሀዲድ ርዝመት 890 ሜትር ብቻ ነው።

➥  ምንም ዓይነት ደን እና የእርሻ ምርት፣ መሥሪያ ቤት እንዲሁም ምንም የፖለቲካ ፓርቲ የሌላት ብቸኛ ሉዓላዊት ሀገር ቫቲካን ናት።

➥  ቫቲካን ከካርበን የአየር ብክለት ፍፁም የጸዳች ሀገርም ነች።

➥  የቫቲካን ሙዚየም 14.5 ኪ.ሜ. ርዝመት ያለው ሲሆን በሙዚየሙ ውስጥ ያለውን እያንዳንዱን ቅርስ ለአንድ ደቂቃ እያየን ብናልፍ በአጠቃላይ ሙዚየሙን አይቶ ለመጨረስ የሚፈጀው ጊዜ 4 ዓመት ነው! ሙዚየሙ ከቫቲካን ድንበር አልፎ እስከ ሮማ ይዘረጋል።

➥  ቫቲካን በሮማ መሀል የምትገኝ የጣልያን ምድር ብትሆንም ለየት ባለ ሁኔታ ራሷን የቻለች ሉዓላዊት ሀገር ናት። የሮማ ካቶሊክ ሊቀ-ጳጳስ መቀመጫ የሆነችው ቫቲካን ራሷን ችላ እንድትተዳደር የተወሰነው በ1929 ዓ.ም. ነው።

➥  ጣልያናዊ ዜግነት ያላቸው ሁሉ ከገቢያቸው ላይ 8% ለቫቲካን መንግሥት ይለግሳሉ።

➥  ቫቲካን የኢኮኖሚ መሰረቷ ከመላው ዓለም የካቶሊክ እምነት ተከታዮች በሚሰጠው አስራት፣ መባ እና ስጦታ ሲሆን ከዚህ በተጨማሪ ሌሎች የገቢ ምንጮቿ ህትመት፣ ፖስታ፣ ቴምብር፣ የጥንታዊ ሳንቲሞች ሽያጭ እና ቱሪዝም ናቸው።

➥  ቫቲካን የምትተዳደረው በንጉሠ ነገሥታዊ ሥርዓት-መንግሥት ነው። ንግሥናው ግን በዘር የሚወረስ አይደለም። የንግሥናው ምንጭ የሮማ ሊቀ-ጳጳስ መሆን ነው። የካቶሊክ ቤተ-ክርስትያን ሊቀ-ጳጳስ የቫቲካን ንጉሥ ናቸው።

➥  በቫቲካን የሊቀ-ጳጳሱ ጠባቂ ለመሆን የስዊዘርላንድ ዜጋ መሆን ያስፈልጋል።

➥  100% ወይም ሙሉ ለሙሉ ከተማ የሆነች ሉዓላዊት ሀገር ቫቲካን ብቻ ናት።

➥  ከቫቲካን ሲቲ በመቀጠል የዓለማችን ትንንሽ ሉዓላዊ ሀገራት ሞናኮ፣ ናሁሩ፣ ቱቫሉ፣ ሳንማሪኖ፣ ሊቸንስቴን፣ ሴንትኪትስ፣ ማልዳይቭ፣ ማልታ እና ግሪናዳ ናቸው።

━━━━━━━━
ምንጭ ➢ የዕውቀት ማኅደር
📖 📖 📖 📖 📖
https://t.me/Ethiobooks

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

11 Nov, 07:00


💿 ሀ ገ ሬ 💿
🇪🇹
🎤 ሚካያ በኃይሉ 🎧
@ethiobooks
🎼🎵🎶🎵🎶🎵

ነይ ፍቅር እንውለድ ነይ ፍቅር እንዝራ
ነይ ትውልድ እንውለድ ነይ ትውልድ እናፍራ
ጊዜን የቀደመ ጊዜን የሚመራ
ህሊናው የነቃ ምግባሩ የጠራ
አሸናፊ ትውልድ ፊታውራሪ አውራ
ምርጥ ዘር ይብዛልሽ እንደ ዕንቁ 'ሚያበራ
🎵
በልጆችሽ ብርታት ይሙላብሽ የደስደስ
ቁንጅናሽ ይመለስ ውበትሽ ይታደስ
ስምሽ በዓለም ዙሪያ ይመስገን ይወደስ
ፍሬሽ ለዓለም ይሁን ይባረክ ይቀደስ
🎵🎶🎵
[ኢትዮጵያ ሀገሬ - ትዳሬ
ቃልኪዳኔ ፍቅሬ] 2×
ታላቅ ሁኝ ክበጂ - አሜን
ኃያል ሁኝ ፍረጂ - አሜን
እልልታሽ ከፍ ይበል - አሜን
ድልሽን አውጂ
[ሀገሬ ..... ትዳሬ] 2×
[በልጆችሽ ጥበብ ተዋቢ አጊጪ
ከሰማይሽ በላይ ከራስሽ ብለጪ] 2×
አሜን ..... አሜን .....
🎵🎶🎵🎶🎵
ነይ ፍቅር እንውለድ ነይ ፍቅር እንዝራ
ነይ ትውልድ እንውለድ ነይ ትውልድ እናፍራ
ዘመንን እንርታ ጊዜን እንብለጠው
ልኩን እናሳየው በእፍኝ እንጨብጠው
በብርሃን ተጉዘን ጊዜን እንለፈው
ዘመንን ተርጉመን በመልካም እንጻፈው
🎵
በልጆችሽ ብርታት ይሙላብሽ የደስደስ
ቁንጅናሽ ይመለስ ውበትሽ ይታደስ
ስምሽ በዓለም ዙሪያ ይመስገን ይወደስ
ፍሬሽ ለዓለም ይሁን ይባረክ ይቀደስ
🎵🎶🎵
[ኢትዮጵያ ሀገሬ - ትዳሬ
ቃልኪዳኔ ፍቅሬ] 2×
ታላቅ ሁኝ ክበጂ - አሜን
ኃያል ሁኝ ፍረጂ - አሜን
እልልታሽ ከፍ ይበል - አሜን
ድልሽን አውጂ
[ሀገሬ ..... ትዳሬ] 2×
[በልጆችሽ ጥበብ ተዋቢ አጊጪ
ከሰማይሽ በላይ ከራስሽ ብለጪ] 2× ||

🎶🎵🎶
@ethiobooks

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

11 Nov, 04:16


╔══ 💚💛♥️ ══╗
     ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

👉 የደራሲያን፣ ገጣሚያን፣ ከያኒያን እና የተለያዩ ግለሰቦች የሕይወት ታሪክና ሥራዎች፤
👉 ወጎች፣
👉 ግጥሞች፣
👉 ልብ ወለዶች፣
👉 የፍልስፍናና የስነ-ልቡና ፅሁፎች፣
👉 ተረትና ምሳሌዎች
      «ነገር በምሳሌ»
👉 ተረኮች
      "የቅዳሜ ተረክ"
👉 የዘፈን ግጥሞች
      (ከሙዚቃ ጋር)
👉 ጥቅሶች
      (ከታዋቂ ሰዎች እንደበት)
እና ልዩ ልዩ የብዕር ውጤቶች  የሚቀርቡበት የናንተው ቻናል
  ❤️ ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

ቻናላችንን
👇👇👇
https://t.me/Ethiobooks
ለወዳጅ ጓደኞችዎ 'share' ያድርጉ።

📖 📖 📖 📖 📖
ለማንኛውም አስተያየት፣ ስነ-ፅሁፋዊ ጥቆማና ማስታወቂያ
@firaolbm እና
@tekletsadikK ን ተጠቀሙ።
በአክብሮት እንቀበላለን።

🙏   አብረን እንዝለቅ።  🙏
       @ethiobooks
╚═══💚💛♥️═══╝

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

09 Nov, 09:00


ማርክ ፌልት - 2 የመጨረሻው!

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

09 Nov, 08:00


ማርክ ፌልት - 1

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

09 Nov, 07:59


▶️ ማ ር ክ ፌ ል ት
━━━━━━
«የሰላዩ የ30 ዓመታት ምስጢር»
@ethiobooks

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

08 Nov, 09:01


የኑሮ ዓይነት
══•══
ፈቃደ አዘዘ
'
ባለፈው ትናንት ተኩራርቶ ...
ኮራ! ኮራ! ኮራ!
ባሉበት ዛሬ ቸልቶ ...
ችላ! ችላ! ችላ!
ለማያውቁት ነገ ተግቶ ...
ተጋ! ተጋ! ተጋ!

ኮራ - ችላ- ተጋ!
ተጋ - ችላ - ተጋ!
የአሁኑ ግን ባሰ
ችላ -- ችላ -- ችላ!
═══════
📔 እየሄድኩ አልሄድም
🗓 ፲፱፻፹፱ ዓ.ም. - አዲስ አበባ
📖 📖 📖 📖 📖
https://t.me/Ethiobooks

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

07 Nov, 11:00


>>>
«ሕይወት ትርጉም የሚኖራት ሁሌም ንቁና ጠንካራ ስንሆን፣ ግብ ስናዘጋጅ እና በየጊዜው ዓላማችንን ከግብ ለማድረስ የሚያስፈልገውን መስዋዕት በዘላቂነትና በቁርጠኝነት ስንከፍል ነው።

ብዙ ጊዜ ደስታ ማጣት በሕይወት ግልጽ የሆነ ትርጉምና ዓላማ ከማጣት ይመጣል። እያንዳንዱ የሚገጥሙን ፈተናዎች ሕይወትን ተወዳጅ የሚያደርጓት ማጣፈጫ ቅመሞች ናቸው።

ሕይወትን ትርጉም ያላት የምናደርጋት ደግሞ የሚሰነዘሩብንን ፈተናዎች በብቃትና በስሌት መቋቋም ስንችል ነው። ለመለወጥ ካሰብን ግልጽ የሆነ ግብና በራስ የመተማመን መንፈስም ሊኖረን ይገባል።

የስኬታማነት አንዱ አስፈላጊ ምስጢር በራስ መተማመን ነው። በራስ ለመተማመን አስፈላጊ መሣሪያው ደግሞ የማያቋርጥ ዝግጁነት ነው። በራስ ላይ እምነት ማጣት ከሌሎች ውጫዊ እንቅፋቶች ይልቅ የአንድን ሰው አቅምና ችሎታ ሽባ ያደርጋል።»

>>>
━━━━━━━━

📖 📖 📖 📖 📖
https://t.me/Ethiobooks

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

02 Nov, 09:01


አድሚራል ያማሞቶ - 2 የመጨረሻው!

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

02 Nov, 08:01


አድሚራል ያማሞቶ - 1

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

02 Nov, 07:56


▶️   አድሚራል ያማሞቶ
          ━━━━━━━
         «ጦርነትን የሚሠራ ግን
  ጦርነትን የማይወደው የጦር መሪ»
               @ethiobooks

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

31 Oct, 13:00


ተ ስ ፋ
═✦═
ታገል ሰይፉ
'
መኖር ጣር ነውና -
     ሁልጊዜ አለማረፍ
ካንዱ ሞት አምልጦ -
     ለሌላ ሞት መትረፍ
እጅ አልሰጥም ብሎ -
     ሰው በፅናት ሲከንፍ
አንድ ቀን... አንድ ቀን...
     ዝሎ እንደሚሸነፍ
የሚያስታውስበት -
     ምንም ጊዜ አይትረፍ ...
═══════
📔 የሰዶም ፍፃሜ
📖 📖 📖 📖 📖
https://t.me/Ethiobooks

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

30 Oct, 11:00


>>>
«ልጅነት የነገ ታሪክ ተቀርጾ የሚቀመጥበት የትንቢት መዝገብ ነው፤ እኛ ወላጆች ነጋችንን ለማወቅ ዛሬ እዚያ ልጅነት መዝገብ ላይ የከተብነውን ማንበብ ነው የሚጠበቅብን። ነጋ'ችንን ለማድመቅ ዛሬ እዚኽ መዝገብ ላይ የምናሰፍረውን ነው ማንጠር ያለብን። ...

«እኛ ዛሬ ላይ እየኖርን ያለነው ወላጆቻችን በማወቅም ይኹን ባለማወቅ በልጅነታችን መዝገብ ላይ ያሰፈሩብንን፣ በልጅነታችን ማሳ ላይ የዘሩትን አይደል?

«በልጅነት መዝገብ ላይ በዘፈቀደ የተሳለ ኹሉ የኋላ ኋላ ጅራቱን እና አናቱን የማይለዩት ቅዠት ያስታቅፋል፤ ግብ ያለው፣ የተዋጣለት እና እያረሰረሰ የሚፈስ አስተሳሰብ፣ ባህል፣ ትውልድ እና አገር ይኖር ዘንድ መልካም ገበሬ ኾኖ የልጆቻችን የልጅነት ማሳ ላይ ምርጡን ዘር መዝራት የግድ ነው፤ ከዚያም ከስር ከስር መኮትኮት፣ ማረም ...»

>>>
━━━━━━━━
🗓 ግንቦት 2016 ዓ.ም.
📄 96

📖 📖 📖 📖 📖
https://t.me/Ethiobooks

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

29 Oct, 07:00


ሁ ለ ት  ዓ ለ ም
━━❁━━
ከሕይወት እምሻው
'

ጌታሁን ለሁለት ልጆቹ፣

«የሚቀጥለውን ክፍያዬን ስቀበል ባለ ሰማኒያ አምስቱን ኢንች እገዛላችኋለሁ» ብሎ ቃል በገባው መሰረት "ትንሽ ነው" ብለው ያጣጣሉትን ባለ ሃምሳ አምስት ኢንች ቴሌቪዥናቸውን አስወጥቶ አዲሱን ግድግዳው ላይ አሰቀለ።

     ከሁለቱ ትልልቅ ሳሎኖቻቸው በቤታቸው አንደኛ ፎቅ ላይ የሚገኘው "ኢንተርቴንመንት ሩም" ብለው የሰየሙት ሳሎናቸው ውስጥ በኩራት እየተንጎራደደ ሲጠብቃቸው በደስታ ይጠመጠሙብኛል ብሎ ጠብቆ ነበር።

ልጆቹ ግን በተቃራኒው፣

«ባባ… ይሄም እኮ ብዙ ትልቅ አይደለም። በሚቀጥለው መቶ ኢንች ግዛልን» ብለው እየተነጫነጩ ወደየመኝታ ክፍሎቻቸው ለመግባት ደረጃውን በፍጥነት ወጡ።

     የእነ ጌታሁንን ቤት በሳምንት ሁለቴ እየመጣች ከላይ እስከ ታች የምታፀዳው ሻሼ፣ አቶ ጌታሁንን አስፈቅዳ የወሰደችውን የሰማንያ አምስት ኢንቹ ቴሌቪዥን የመጣበትን ካርቶን ይዛ ቤቷ ስትገባ ግን ሁለቱ ልጆቿ ጮቤ ረገጡ።

«እማምዬ፣ ከእንግዲህ ስንተኛ ከሚያስቸግረን ቅዝቃዜ ልንገላገል ነው፡፡ ቆይ ፍራሻችንን ከመሬቱ እናንሳውና ካርቶኑን ከስር እናንጥፈው» እያሉ።
━━━━━━━━
📖  📖  📖  📖  📖
https://t.me/Ethiobooks

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

28 Oct, 07:00


💬
❝ደግነት ማለት መስማት የማይችል ሊያዳምጠውና፣ ዓይነ ስውር ሊያነበው የሚችል ቋንቋ ነው።❞
ኮልሪጅ

💬
❝በሕይወት የሚያጋጥም እውነተኛ ድክመት አንድ ብቻ ነው፤ ያም ልብ የሚያውቀውን እንደማያውቁ መምሰል ይሆናል።❞
ካነን ፍሬድሪክ ፋራር

💬
❝ከጊዜ የተሻለና የላቀ ሌላ ስጦታ ተፈልጎ አይገኝም።❞
ጆናታን ሳፍራን ፎዬር

💬
❝በሕይወት አኗኗሬ ውስጥ እኔ ተዋናይ ነኝ፤ የትወና ሥራዬም፣ የራሴ ሕይወት ነው።❞
ሱ ዙ ኪ

💬
❝ባለስልጣን ማለት የራሱን ፍላጎት መቆጣጠር የማይችል፤ ነገር ግን የሕዝቡን ፍላጎት መቆጣጠር የሚፈልግ ሰው ማለት ነው።❞
ሶቅራጥስ

💬
❝ሕይወት ትርጉም ሊኖረው የቻለው ማብቂያ ስላለው ነው።❞
ፍራንክ ካፍካ

💬
❝እንዴት መኖር እንዳለብኝ እየተማርኩ እንደሆነ ሳስብ፣ እንዴት መሞት እንዳለብኝ እየተማርኩ ነበር።❞
ሊዮናርዶ ዳቪንቺ

💬 💬
ጥቅሶች
@ethiobooks

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

26 Oct, 09:00


ስቴፈን ሀውኪንግ - 2 የመጨረሻው!

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

26 Oct, 08:00


ስቴፈን ሀውኪንግ - 1

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

26 Oct, 07:55


▶️ ስቴፈን ሀውኪንግ
━━━━━━
«ሳይንስ የደገፈው ሳይንቲስት»
@ethiobooks

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

25 Oct, 06:00


☆ ☆ ☆
መርዝም መድኃኒት ነው
ሲሆን በጠብታ፣
እንዲሁም ለተንኮል
አለው ቦታ ቦታ።
ምን ቢሠለጥኑ
ቢራቀቁ በጣም፣
ሁልጊዜ ደጋግሞ
ብልጠት አያዋጣም።
በእጅ የተበተቡት
ተንኮል ዞሮ ዞሮ፣
ማጋለጡ አይቀርም
እጅና እግር አስሮ።
መጽሐፉም ይለናል
ሲያስተምረን ጥበብ፣
ብልጥ ሁን እንደ እባብ
የዋህ እንደ ርግብ።
ስለዚህ በብልጠት
ተንኮል ስትሠሩ፣
በዝቶ እንዳይገድላችሁ
ገርነት ጨምሩ።
═══════
ከበደ ሚካኤል
📔 የዕውቀት ብልጭታ
📖 📖 📖 📖 📖
https://t.me/Ethiobooks

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

23 Oct, 12:00


እ ር ጉ ዝ
🫄   🫄

🫄
እርጉዝ ያቅፉ፣ ይደግፉ።

🫄
እርጉዝ ላም ያለው፣ ደረቅ አያንቀው።

🫄
የተረገዘ በሆድ፣ የታዘለ በለምድ።

🫄
የአራሷን በእርጉዟ።

🫄
ስትወልድ የምትበላውን፣ በእርጉዝነቷ ጨረሰችው።

🫄
ባረገዘች፣ ክታቡን ያዘች።

🫄
እርጉዝ ሲያርዱ፣ በወዳጅ ሲፈርዱ፣ ሆድ መርበድበዱ።

🫄
ለፍቅር ብተኛት፣ ለፀብ አረገዘች።

🫄
በተረገዘ በዓመት፣ በተወለደ በዕለት።

🫄
የአራሷን ገንፎ እርጉዟ ውጣ ሞተች።

🫄
ያረገዘች ታስታውቅ፣ ከደረቷ ትታጠቅ።

🫄
ልጅ ይወለዳል ከእርጉዝ፣ ላም ይገዛል ከወንዝ።

🫄
የተኛችው ሳለች፣ የተሳመችው አረገዘች።

🫄
'ሚስትህ አረገዘች ወይ?' ቢለው፣ 'ማንን ወንድ ብላ' አለው።

      🫄  🫄
   ነገር በምሳሌ

@ethiobooks

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

22 Oct, 12:00


እርጉዝ እንቁላል
━━ 🥚 ━━

ያ ደግ ሰው፣ እንቁላል በመሸጥ ወደሚተዳደሩ አንድ አዛውንት ዘንድ ኼደ።

"ሰላም ለርስዎ ይኹን! እነዚህን ፍሬ የሚመስሉ እንቁላሎች ግሩም አድርገው ይዘዋቸዋል። ዐቅፋ የተቀመጠች ዶሮን ራቅ ብለው ሲያዩአት እኮ የጥቅል ጎመን አትክልት ነው የምትመስለው። እና ጥሩ የሚሏትን እንቁላል ቢሰጡኝ ዘርቼ የማበቅላት ይመስልዎታልን?" አላቸው።

እኚያ እንቁላል ነጋዴም እየሣቁ፡ "ምኑ ቀልደኛ ነህ! "እንቁላል ዘርቼ ዶሮ ላብቅል" ትላለህ! በል ንሳ ዐደራህን፤ እንቁላሉን በእርሻ ላይ ጥለህ እንደ ድንች ጒንፍ ጒንፍ አድርገህ ክበበው፤ ጫጩቶች እንደ ድርጭት ወፍ ከማሳ ላይ ብድግ እያሉ እንዲበሩልህ" አሉት።

ያ ደግ ሰው፡ "እንዲያው ዶሮ ግን የሆዷ ማሽካካት የወፍጮ ውቅራት ስለመሰላት፣ "እንቁላሌ ውጪ ይቀመጥ፣ ሆዴ ውስጥ አለ መናወጥ" ብላ ብትጥለው፣ እንኳን የተጣለን ያልተነገረን የሆድ ድብቅ ምስጢር ለመስማት የሚያሰፈስፈው ሰው እየተከተለ ይለቅመዋል። የሆድ ከሆድ ከወጣ በኋላ አስኳሉ ከምኑ ጋር እየተበጠበጠ ይቀራል እንጂ መቼ ለፍጥረት ማስቀጠያ እንዲኾን ይውላል? እስኪ ሌላ ከሆድ ውስጥ የወጣ የሚወዱትን ነገር ይንገሩኝ?" አላቸው።

እኚያ እንቁላል ነጋዴ፡ "እኔ ወተት እወዳለሁ። አንተስ ማር ትወድ ይኾን?" አሉት።

ያ ደግ ሰው እየሣቀ፡ "ነገሬን ራቅ አድርጌ ጀምሬው ነው እንጂ ለካ ኹላችንም የሆድ ንብረት ነን" አላቸው።

እንቁላል ነጋዴው አንድ ዓይናቸውን ጨፍነው፣ አንድ ዐይናቸው ላይ እንቁላል እያሽከረከሩ ይመለከታሉ።

ያ ደግ ሰው፡ "ለምንድር ነው ወደ ፀሓይ አድርገው እንቁላሉን የሚፈትሹት?" አላቸው።

እኚያ እንቁላል ነጋዴ፡ "እርጒዝ እንቁላል እንዳንበላ ብዬ ነው" አሉት።
━━━━━━━
📄 223 - 224
📖 📖 📖 📖 📖
https://t.me/Ethiobooks

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

21 Oct, 07:00


“አምሮት” /-phagia/
  ━━━✦━━━

የምግብነት ጠቀሜታ የሌላቸውን ልዩ ልዩ ነገሮች የሚያስበላ ወይም ለመብላት የሚያነሳሳ የስነ ልቡና ወይም የጤና ችግር ፒካ ይባላል። በርካታ የፒካ ዓይነቶች ያሉ ሲሆን ስማቸው ሁሉ "ፋጂያ" በሚለው ቃል የሚያልቅ ነው።

ከእነዚህም ውስጥ ፦
ጂኦፋጂያ ➢ አፈር፣ አሸዋ እና ሸክላ መብላት
አሚሎፋጂያ ➢ እንጨትና ቅጠል መብላት
ዛይሎፋጂያ ➢ ወረቀት መብላት
ሐይሎፋጂያ ➢ መስታወት ቆርጥሞ መዋጥ
ኑዶዋፋጂያ ➢ ለስላሳ ድንጋይ መብላት
ፓጎፋጂያ ➢ በረዶ መብላት
ትራይኮፋጂያ ➢ ፀጉር መብላት
ጋርቤጆፋጂያ ➢ ቆሻሻ መብላት ይጠቀሳሉ።

ለእንደዚህ ዓይነት የስነ ልቦና ችግር የሚያጋልጡ አጋጣሚዎች፦
➥ ️ረሃብ፣ ጉስቁልናና መረን የለቀቀ ድህነት
➥ የአእምሮ ዝግመት
➥ ከባድ ሀዘንና አደገኛ ትካዜ
➥ የኑሮ መመሰቃቀል
➥ የቅርብ ዘመድ ሞት እና
➥ እርግዝና ሊሆኑ ይችላሉ።

እርግዝና በርካታ ነገሮችን ለመብላት ያነሳሳል፣ ለምሳሌ የተራረፈ ምግብ፣ የግድግዳ አፈር ... ወዘተ። እርጉዝ ሴቶች ለእንደዚህ ዓይነት ችግር የሚጋለጡት በሰውነታቸው ውስጥ ከእርግዝናው ጋር ተያይዞ የሚመነጩት ኬሚካሎች በአእምሯቸው ላይ በሚያሳድሩት ተፅእኖ እና ነፍሰ ጡርነትን ተከትሎ በሚከሰት  የደም ማነስ ችግር ነው።

የደም ማነስ በህፃናትና በነፍሰ ጡሮች ላይ በከፍተኛ ሁኔታ ሲከሰት አፈር እና ሸክላ ፈርፍሮ የመብላትን ስነ ልቦናዊ ፍላጎት ይፈጥራል። በተለይ "Iron Deficiency Annemia" የተባለው የደም ማነስ ዓይነት፣ በሰውነት ውስጥ ያለው የብረት ንጥረ ነገር ሲያንስ እና 'ሔሞግሎቢን' የተባለው ከብረት ኬሚካል የሚሠራው ኦክሲጂን ተሸካሚ ፕሮቲን ሲያንስ ነው።

ይህንን ንጥረ ነገር ለመተካት ሲባል አፈር ለመብላት የሚያጓጓ አስገራሚ የስነ ልቦና ተነሳሺነትን በአእምሮ ውስጥ ይፈጥራል።

ስለ 'ጂኦፋጂያ' ለመጀመሪያ ጊዜ የጻፈው ፈላስፋ 'የሕክምና አባት' ተብሎ የሚጠራው ሂፖክራተስ ነው። ሂፖክራተስ በጥንቱ ጽሑፍ ውስጥ ሲያስረዳ "አንዲት ነፍሰ ጡር ሴት አፈርና የግድግዳ ጭቃ የመብላት አባዜ ካደረባትና እንደጓጓችውም ካደረገችው ልጁ ከተወለደ በኋላ አደግ ሲል እሱም እንደ እናቱ አፈር ቆንጥሮ የመብላት ስሜት ያድርበታል" ይላል።

ሂፖክራተስ ይህንን የጻፈው ከ2500 ዓመታት በፊት ሲሆን፣ ጥንት በነበረው የስልጣኔ ደረጃ ይህንን ያህል ግንዛቤ መውሰዱ የሚደነቅ ነው። ሳይንሳዊ ትንታኔው ግን ከእርግዝና ጋር ተከትሎ የሚመጣው "Iron Deficiency Annemia" የተባለው ከላይ የተጠቀሰው የደም ማነስ ዓይነት ነው።
>>>

━━━━━━━━
📖 📖 📖 📖 📖
https://t.me/Ethiobooks

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

19 Oct, 09:00


ዳሊ ላማ - 2 የመጨረሻው!

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

19 Oct, 08:02


ዳሊ ላማ - 1

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

19 Oct, 08:00


▶️         ዳ ሊ   ላ ማ
               ━━━━
       «የርህራሄ፣ የትዕግስትና
              የፍቅር ሰባኪ»
            @ethiobooks

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

18 Oct, 05:00


በተረት ላሰላስል
══ ✦ ══
ደበበ ሰይፉ
'
መሬትና ጥንቸል ማኅበር ገቡና
          ጽዋ ተጣጡና፤ ...
(ያው እንደዚያው ማለት)
ያጋጣሚ አይደል፤
የተፈጥሮ ባህል፤ የታሪክ ዘይቤ አለው አንድ ቋንቋ
     አለው አንድ መላ
     አንተና ልደትህን፣ አንተና ሀገርህን -
በማይረግብ ገመድ፣ ባንድ ላይ የቋጨ፤
     ከዐፀደ ዘመን፤ ከቦታ ከለላ
በደም ቃልኪዳኑ ባንድ ያስተሳሰረ
በማይታዩ እጆች ባልተሰማ መሀላ።

እና፤

መሬትና ጥንቸል ማኅበር ገቡና
          ጽዋ ተጣጡና፤
መሬት የፈንታዋን ስትከፍል በጽሞና፤
(ያው እንደዚያው ማለት)
የሀገርህ ህይወት - የብዙኃን ሕይወት - ወዝ ደምና ቅስሙ
ብርታቱ ድካሙ - ተስፋውና ሕልሙ
ከእንቡጥ ወደ አበባ - ከአበባ እስከ ፍሬ - ለምልመህ ለማየት
በክንዶችህ ብርታት - በአዕምሮህ ንቃት -
በኅሊናህ ጥራት - ፀንተህ ለመመልከት
ዘንሟል በዘመናት - ወርዷል እንደዠማ - ፈሷል እንደ ጅረት።

እና፤

መሬትና ጥንቸል ማኅበር ገቡና
          ጽዋ ተጣጡና፤
መሬት የፈንታዋን ስትከፍል በጽሞና
እብስ አለች ጥንቸል፣ መክፈል ጠላችና፤...
(ያው እንደዚያው ማለት)
በስንት ትላንት ነውና ዘንቦ ወይ ፀሕይቶ
በቁር ተኮራምቶ በዋዕይ ገርጥቶ
     የበቀለ ዛሬ፤
ትውልድም ነውና፣ ያያት የቅድመ አያት
     የእንዝላት የእንጅላት
     የመሠረት ፍሬ፤
በሺ እግሮች ተራምዶ ዛሬን የደረሰ ለእሱ እሱነቱ
     በወቅቱ ለወቅቱ
ይኖር ወይ ደካማ የትውልድ እንክርዳድ 
     አደገኛ አዝመራ ከዚህ ከወጣቱ?
ማነው ይህ መጢቃ የፀደይ ቀን ዘመድ
ወጪቱን እሚሰብር፣ ዕዳውን እሚክድ
ከወገኑ እማይቆይ ከወገኑ እማይነድ?
የጫጨ መንፈሱ፤ የሸፈተ ሀሣቡ የከነፈ ልቡ
ራሱ መነሻው ደሞ ራሱ ግቡ?

እና፤

መሬትና ጥንቸል ማኅበር ገቡና
          ጽዋ ተጣጡና፤
መሬት የበኩሏን ስተከፍል በጽሞና
እብስ አለች ጥንቸል፤ መክፈል ጠላችና፤....
ግና ምን ይሆናል?
ብትሮጠው ብትሮጠው ጋራውን ተሻግራ፣
     ሜዳውን አቋርጣ
አልቻለችም ከቶ፣ ከዕዳዋ ልትድን
     ከመሬት አምልጣ።
═════════  
📔 የብርሃን ፍቅር
(ለራስ የተጻፈ ደብዳቤ)
📖 📖 📖 📖 📖
https://t.me/Ethiobooks