አድስ መረጃ Addis merja

@ethioaddiszena


እንኳን ደህና መጡ ወደ #አድስ_መረጃ ወቅታዊ እና አዳድስ ወሬዎችን እናደርሶታለን።

አድስ መረጃ Addis merja

03 Apr, 18:37


The account of the user that owns this channel has been inactive for the last 5 months. If it remains inactive in the next 7 days, that account will self-destruct and this channel may no longer have an owner.

አድስ መረጃ Addis merja

14 Mar, 07:24


The account of the user that owns this channel has been inactive for the last 5 months. If it remains inactive in the next 28 days, that account will self-destruct and this channel may no longer have an owner.

አድስ መረጃ Addis merja

08 Oct, 03:03


አድስ መረጃ Addis merja pinned «https://t.me/joinchat/8Ih2uEJ5kaFhZjU0»

አድስ መረጃ Addis merja

07 Oct, 19:45


#UPDATE

የቀድሞው የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ከአዲሱ የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ጋር የስራ ርክክብ አድርገዋል።

ዛሬ አዲሱ የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ከቀድሞ የሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዶ/ር ሳሙኤል ኦርቃቶ የስራ ርክክብ ማድረጋቸው ተገልጿል።

በርክክቡ ወቅት የከፍተኛ ትምህርት ንዑስ ዘርፍ ልማት ፣ የከፍተኛ ትምህርት ፖሊሲ እና ስትራቴጂ ፣ የ10 ዓመት ዕቅድ እና ሌሎች በሳይንስ ና እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር እየተከናወኑ ያሉ ሌሎች ሥራዎች ገለፃ ተደርጓል።

በተጨማሪም ከሳይንስ ንዑስ ዘርፍ ልማት የሳይንስ ፖሊሲ እና ስትራቴጂ ፣ የ10 ዓመት ፍኖተ ካርታ እና እንደ ብሔራዊ የምርምር ስትራቴጂ ፣ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ንዑስ ዘርፍ ልማት-የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ፖሊሲና ስትራቴጂ ፣ የ10 ዓመት ዕቅድ ፣ የምሥራቅ አፍሪካ 7 የልህቀት ማዕከል ግንባታ ዙሪያ ማብራሪያ ተሠጥቷል።

እንዲሁም የተቋማዊ የአቅም ግንባታ፣ የዩኒቨርሲቲዎች ልየታ፣ የከፍተኛ ትምህርት መረጃ ዲጂታል ሲስተም ፣ የአካዳሚክ አመራር ፣ የከፍተኛ ትምህርት እና የሥልጠና ዕውቅና ስትራቴጂ ዙሪያም የተሠሩ ስራዎች ማብራሪያ መሰጠቱን ለማወቅ ተችሏል።

Credit : MoSHE

አድስ መረጃ Addis merja

07 Oct, 19:37


ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ ጣልያን፤ ሮም ይገኛሉ።

በሚኒስትር ማዕረግ የድንበር ተሻጋሪ ወንዞችና የህዳሴ ግድብ ዋና ተደራዳሪና አማካሪ ሆነው የተሾሙት ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ ዛሬ በሮም ከኢጣሊያ የውጭ ጉዳይ ም/ሚ/ር ና የልማት ትብብር ሚ/ር Mrs Maria Sereni ጋር ተወያይተዋል።

ውይይቱ በወቅታዊ የኢትዮጵያ ጉዳዮች እና በህዳሴ ግድብ ግንባታና ድርድር ላይ ያተኮረ ሲሆን ቀጣይ የጋራ የትብብር ጉዳዮች ላይም ውይይት መካሄዱን ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በይፋዊ የትዊተር ገፃቸው አሳውቀዋል።

ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ ፥ ነገ "Encounters with Africa 2021” የኢነርጂ ኮንፈርስ ከአፍሪካ አገሮች፣ ጣሊያንና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ጋር በG20 የጣሊያን ፕሬዚዳንትነት ወቅት እንደሚካሄድ ጠቁመዋል።

@ethioaddiszena

አድስ መረጃ Addis merja

07 Oct, 11:51


https://t.me/joinchat/8Ih2uEJ5kaFhZjU0

አድስ መረጃ Addis merja

07 Oct, 10:02


ሹመት !

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ለከፍተኛ የመንግስት ሃላፊነት ቦታዎች ሹመቶች ሠጡ::

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) በዛሬው እለት አቶ ተፈሪ ፍቅሬን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ሃላፊ እና የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር አድርገው በድጋሚ የሾሙ ሲሆን ለ4 ከፍተኛ የሃላፊነት መደቦችም በሚኒስቴር ማእረግ የሚከተሉትን ሹመቶች ሰጥተዋል፡-

1. አቶ አደም ፋራህ - በሚኒስትር ማዕረግ የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ዋና አስተባባሪ

2. አቶ ተስፋዬ ቤልጅጌ - በሚኒስትር ማዕረግ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ተጠሪ

3. ዶ/ር ስለሺ በቀለ - በሚኒስትር ማዕረግ የድንበር ተሻጋሪ ወንዞችና የህዳሴ ግድብ ዋና ተደራዳሪና አማካሪ

4. ዶ/ር ለገሰ ቱሉ - በሚኒስትር ማዕረግ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ኃላፊ

በተጨማሪም ፦
- ዶ/ር ምህረት ደበበ - የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዚዳንት፤

- አቶ ፍሰሃ ይታገሱ - የኢትዮጵያ ብሮድካስት ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈፃሚ፤

- እንዲሁም አቶ አብዱራህማን ሩቤ - የኢትዮጵያ ብሮድካስት ኮርፖሬሽን ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሆነው ተሹመዋል፡፡

#PMOfficeEthiopia

@ethioaddiszena

አድስ መረጃ Addis merja

07 Oct, 10:00


#UNSC

ትላንት በተመድ የፀጥታው ምክር ቤት ኢትዮጵያ በተመድ ሰራተኞች ላይ ስለወሰደውች እርምጃ ማብራሪያ የሰጡት አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ ፥ በዓለም አቀፍ ህግ ሀገራት መብቶቻቸውን መጠቀም ይችላሉ፤ የኢትዮጵያ መንግስት ለውሳኔውም ምንም አይነት ማብራሪያ የማቅረብ ግዴታ የለበትም ብለዋል።

ሀገራት የተለያዩ የተመድ ሰራተኞችን እና የሀገራት ዲፕሎማቶችን ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ከሀገራቸው ማስወጣታቸውን እናውቃለን፤ ሆኖም ግን ተመድ በእነሱ ላይ ስብሰባ አድርጎ ያውቅ ይሆን ? ሲሉ ጠይቀዋል።

የኢትዮጵያ መንግስት እርምጃውን ስለ መውሰዱ ለማንኛውም አካል ማብራሪያ የመስጠት ግዴታ የለበትም ሲሉ ተናግረዋል።

የተመድ ሰራተኞች የገለልተኝነት መርሆችን በጣሰ መልኩ ለህወሓት የሚወግኑ መሆናቸውን ገልፀዋል። 

የተመድ ሰራተኞች ያልሞቱ ሰዎችን በረሃብ ሞተዋል በሚል የሀሰት መረጃዎችን ማሰራጨት፤ የመገናኛ መሣሪያዎችን ለህወሓት ወገን ማድረስ፤ ህወሃት መቐለ ሲገባ ከቡድኑ ጋር ደስታቸውን መግለጽ ፤ ከሳዑዲ የትግራይ ተወላጆችን ወደ ሶስተኛ ሀገር በማምጣት ለቡድኑ እንዲዋጉ ስልጠና የሚያገኙበትን ሁኔታ ማመቻቸትና ህወሓትን የሚደግፉ ጹሑፎችን ማዘገጀት ላይ ተጠምደው ነበር ብለዋል።

ማን ይገባል፤ ማን ይወጣል ፣ ማን ይቆያል የሚለውን የሀገር መሰረታዊ ሉዓላዊ መብት ነው ብለዋል።

የመረጃ ግብአ አልዓይን ፣ ቪኦኤ፣ የUN ገፅ።

@ethioaddiszena

አድስ መረጃ Addis merja

07 Oct, 09:58


የተመድ የፀጥታው ም/ቤት በኢትዮጵያ ጉዳይ ምን አለ ?

የተመድ የፀጥታው ም/ቤት በኢትዮጵያ ጉዳይ ስብሰባ ሲቀመጥ ሁለት (2) ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ይኸኛው ለአራተኛ (4) ጊዜ (በዝግና በክፍት) ነው።

ይኸኛው ስብሰባው ለምን ተጠራ ?

- ኢትዮጵያ 7 የተመድ ሰራተኞችን ከሀገር በማስወጣቷ።
- የሰሜን ኢትዮጵያ ሰብዓዊ ሁኔታ ላይ ለመወያየት።

ስብሰባው እንዲካሄድ የጠየቁት፦ አሜሪካ ፣ ዩኬ (UK)፣ ኖርዌይ ፣ ኢስቶኒያ ፣ ፈረንሳይ እና አየርላንድ ናቸው።

በስብሰባው ላይ የኢትዮጵያ ተወካይ አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

የተመድ ዋና ፀሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ንግግር አድርገዋል።

የምክር ቤቱ አባል ሀገራት የተለያዩ ሀሳቦችን ሰንዝረዋል።

ሙሉ ውይይቱን (ክፍት ውይይት ስለሆነ) በተመድ የYouTube ቻናል ማግኘት እንደምትችሉ እየጠቆምን የተነሱ ዋና ሃሳቦችን ግን በአጭሩ እንዳስሳለን።

ይህን ተጭነው ያንብቡ (Instant View)👇
https://telegra.ph/UNSC-10-07

አድስ መረጃ Addis merja

06 Oct, 22:36


#Update

የተመድ ፀጥታው ምክር ቤት ስብሰባ በመካሄድ ላይ ሲሆን በተመድ የኢትዮጵያ አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ ለምክር ቤቱ ማብራሪያ በመስጠት ላይ ይገኛሉ።

የዛሬው የፀጥታው ምክር ቤት ስብሰባ ክፍት ሲሆን በተመድ (UN) ይፋዊ የ #YouTube ቻናል መከታተል ይቻላል : https://youtu.be/cX2tXnUL-cY

@ethioaddiszena

አድስ መረጃ Addis merja

06 Oct, 22:31


የኢትዮጵያው ከፍተኛ ባለስልጣን #ፌስቡክ መረጃዬን አሳልፎ ሰጠብኝ አሉ።

ዛሬ ምሽት የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ ዋ/ዳሬክተር ዶ/ር ሹመቴ ግዛው በፌስቡክ ገጻቸው ላይ ''ሀክ ተደረጉ'' ከሚል ጹሑፍ ጋር ተንቀሳቃሽ ምስሎች ተለጥፈው ነበር።

ይህ ከሆነ ከደቂቃዎች በኃላ ዳሬክተሩ፥ ''ለግንዛቤያችሁ'' ብለው ባሰፈሩት መልዕከት ይፋዊ የፌስቡክ አካውንታቸው ''በውጭ አካላት ሃክ አልተደረገም'' ብለዋል።

የተለቀቀው ቪዲዮም ከ1 ዓመት በፊት ፌስቡክ የመልዕክት መላኪያ መተግበሪያ (Messenger) አማካኝነት ከጓደኞቻቸው ጋር ያወሩት እንደሆነ ገልጸዋል።

ዶ/ር ሹመቴ ግዛው ''ፌስቡክ መዝግቦ ያስቀመጠውን መረጃ (Password, Username) እንዴት አሳልፎ እንደሰጠና በዚህም ግለሰብንና ሀገርን ለማሳጣት የተደረገውን የቴክኖሎጂ ውንብድና በህግ አግባብ እንሄድበታለን'' ሲሉ በጹሑፋቸው ገልጸዋል።

በገጻቸው ላይ ለተለጠፈው ተንቀሳቃሽ ምስልም ፌስቡክን መረጃዬን አሳልፎ በመስጠቱ ነው ሲሉም አስረድተዋል።

''የኛ Username እና password እነርሱ ጋር ስለሚገኝ ይህንን ማድረግ ተገቢ አይደለም። ጠላትነታችን እዚህ የደረሰ አልመሠለኝም ነበር'' ይላል አጭር ያሰፈሩት ጹሑፍ።

ተንቀሳቃሽ ምስሉ ዳይሬክተሩ ለጓደኞቻቸው በፊት ለፊት ካሜራ ቀርጸው የላኩት ''አታስቀኑኝ በርሬ መጣለው'' የሚል መልዕክት የያዘ ሲሆን በገጻቸው ላይ በተደጋጋሚ ''ሹመቴ ግዛው ሀክ ተደረገ'' የሚል የሥላቅ መልዕክት ታክሎበት በገጹ ለደቂቃዎች ተለጥፎ ነበር።

አሁን ተንቀሳቃሽ ምስሎቹ ከገጹ የጠፉ ሲሆን ሂደቱን በህግ እንደሚከታተሉም ዶ/ር ሹመቴ አስታውቀዋል።

ዶ/ር ሹመቴ ከ2012 ጀምሮ የኢመደኤ ዋና ዳይሬክተር ሆነው በማገልገል ላይ ይገኛሉ።

@ethioaddiszena

አድስ መረጃ Addis merja

06 Oct, 21:53


#ነእፓ

ነፃነት እና እኩልነት ፓርቲ (ነእፓ) ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በፓርላማ የተናገሩትን ንግግር አስመልክቶ መግለጫ አውጥቷል።

ዛሬ በተካሄደው 6ኛው የህዝብ ተወካዮች ም/ ቤት 1ኛ አመት የስራ ዘመን 1ኛ ልዩ ስብሰባ ላይ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የነጻነትና እኩልነት ፓርቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር አብዱልቃድርን ለአዲስ አበባ ም/ቤት የካቢኔ አባልነት ተጠይቀው ፓርቲያቸው እንዳልፈቀደ ተናግረው ነበር።

ይህን ተከትሎ ፓርቲው ባወጣው መግለጫ ብልፅግና ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር በጋራ ለመስራት ያለውን ፍላጎት አድንቆ ለሀገሪቱ ፖለቲካ ጠቃሚ በመሆኑ ደግፋለሁኝ ብሏል።

ፓርቲው በአዲስ አበባ ካቢኔ ውስጥ ለመሳተፍ ስምምነቱን የገለፀ ሲሆን ከአፈፃፀም ጋር በተያያዙ ጉዳዮች ከብልፅግና ጋር ውይይት ማድረጉን አሳውቋል።

በተደረገው ውይይትም በአ/አ ካቢኔ ውስጥ እንዲሳተፉ የተጠየቁት የፓርቲው ሊቀመንበር ምትክ ሌላ የፓርቲው ከፍተኛ አመራር እንዲሳተፉ ከብልፅግና ጋር ስምምነት መደረሱን አስታውሶ ፓርቲውን ወክለው በአ/አ ካቢኔ አባል እንዲሆኑ የተመረጡት የነእፓ አመራር ለብልፅግና እንዳሳወቀ በመገለጫው ጠቅሷል።

ይሁን እንጂ ነእፓ መርጦ የላካቸው የፓርቲው ተወካይ በካቢኔው ሳይካተቱ መቅረታቸውን ገልጿል፤ይህንንም በተመለከተ ከብልፅግና የተሰጠው ማብራሪያ እንደሌለም አሳውቋል።

ፓርቲው ሀገርን በጋራ ለማገልገል ተፎካካሪዎች በመንግስት ስልጣን እንዲሳተፉ በብልፅግና የተሰጠው እድልን አድንቆ በሀገሪቱ የመንግስት ታሪክ አዲስ አሰራር በመሆኑ ከገዢው ፓርቲ ጋር አብሮ ለመስራት ያለውን ዝግጁነት አረጋግጧል።

ነገር ይህ አዲስ አሰራር ተግባራዊ ሲደረግ ተፎካካሪ ፓርቲዎች በሂደቱ በግልፅ እንዲሳተፉ ማድረግ በሀገር ደረጃ ለታሰበው አዲስ የፖለቲካ ባህል ውጤታማነት አስፈላጊ ነው ብሏል።

@ethioaddiszena

አድስ መረጃ Addis merja

06 Oct, 21:49


ሽብርተኛው ትህነግ ሰብዓዊ ድጋፍ ለማቅረብ እንቅፋት እንደሆነበት የእንግሊዝ መንግሥት አስታወቀ!

የእንግሊዝ መንግሥት የሰብዓዊ ድጋፍ ልዩ አማካሪ ሽብርተኛው ትህነግ ወርሯቸው የነበሩ የአማራ ክልል አካባቢዎችን የጎበኙ ሲሆን ጦርነቱ ንፁሃንን ለሞት፣ ለእንግልት እና ለስደት መዳረጉን ገልጸዋል። አሸባሪው ትህነግ በወረራቸው የአማራ እና የአፋር ክልሎች የተለያዩ አካባቢዎች ንፁሃን ዜጎችና ምንም የማያውቁት እንስሳትም ጭምር ተገድለዋል፤ በርካታ ወገኖች ለአካል ጉዳት እና ለስደትም ተዳርገዋል፤ መሠረተ ልማቶችም ወድመዋል።

“ይህን ሰብዓዊ እና ቁሳዊ ውድመት በአካል ሄደን በዓይናችን አይተናል፤ አዝነናልም” ብለዋል ከአሚኮ ጋር ቆይታ ያደረጉት የእንግሊዝ መንግሥት የሰብዓዊ ደጋፍ ልዩ መልዕክተኛ የሆኑት ሚስተር ኒክድል። ሚስተር ኒክድል ሕጻናት ጭምር ለሞት እና ለጉዳት መዳረጋቸውን አንስተዋል፡፡ የእንግሊዝ መንግሥት ለማንም የማድላት ፍላጎት የለውም ያሉት ልዩ መልዕክተኛው ተቀዳሚና መሠረታዊ ትኩረቱ ሰብዓዊ ድጋፍ ማድረግ ነው ብለዋል፡፡

ልዩ መልዕክተኛው ባለፈው ዓመት ለትግራይ ክልል በተፈጥሮ እና ሰው ሰራሽ ምክንያቶች ለተለያዩ ችግሮች የተጋለጡ ወገኖችን ለመደገፍ መንግሥታቸው 136 ሚሊዮን ዶላር ወጭ ማድረጉንም አንስተዋል። አፋጣኝ ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ዜጎች ለመድረስ ሽብርተኛው ትህነግ የጦርነት ትንኮሳውን ማቆም አለበት ብለዋል፡፡ ሽብርተኛው ትህነግ በአማራ ክልል ላይ እያደረገ ያለውን ወረራ እና ጥቃት ሊያቆም ይገባል ነው ያሉት፡፡ ይህ ካልሆነ ሰብዓዊ ድጋፍ ለማድረግ እንቸገራለን፤ ሰብዓዊ ድጋፍ ለማቅረብ ዓለም አቀፍ ሕጎች ሊከበሩ እንደሚገባ ልዩ መልዕክተኛው አሳስበዋል።

@ethioaddiszena
@ethioaddiszena

አድስ መረጃ Addis merja

06 Oct, 21:47


EBC ሀክ ተደረገ።

የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ይፋዊ ፌስቡክ ገፅ #ሀክ መደረጉ /መጠለፉ/ ተገልጿል።

በገፁ ላይ የሚሰራጩት መረጃዎችም የተቋሙ አይደሉም ተብሏል።

@ethioaddiszena

አድስ መረጃ Addis merja

04 Oct, 08:51


#Update

የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች እና የፌዴሬሽን ምክር ቤቶች የመክፈቻ ስነ ስርዓት ተጠናቋል።

ኘሬዝዳንት ስህለ ወርቅ ዘውዴ ለሁለቱም ምክር ቤቱቶች የመክፈቻ ንግግር አድርገዋል።

ከሰዓታት በኃላ ደግሞ በአዲስ አበባ " መስቀል አደባባይ " የበዓለ ሲመት ስነስርዓት ይካሄዳል።