ደሴ- የካቲት 8/2017/ደሴ ፋና/ከላይ በተጠቀሰው አካባቢ ለግዜው ምክንያቱ ያልታወቀ የደን ቃጠሎ ከቀኑ 6.20 እስከ ቀኑ 7.40 ድረስ ተከስቶ የነበረ ሲሆን የእሳቱ ቃጠሎው በአካባቢው ማህበረሰብ፣ ወጣቶች በፓሊስ ፣በሚኒሻ፣ በመከላከያ ሐይል ርብርብ በቁጥጥር ስር ውሏል።
የቃጣሎውን ምክንያት ፖሊሰ እያጣራ መሆኑን የደሴ ከተማ አስተዳደር ፖሊሰ መምሪያ የ3ኛ ዋና ፖሊሰ ጣቢያ ሃላፊ ኢ/ር ከተማው ታደሰ ተናግረዋል።
በዚህ አጋጣሚ የተነሳው የእሳት ቃጠሎ በቁጥጥር ስር እንዲውል ትብብር ላደረጋችሁ የፀጥታ አካላትና የህብረተሰብ ክፍሎች የከተማው ፖሊስ መምሪያ ታላቅ ምስጋና ያቀርባል ብለዋል።
ደሴ ከተማ አስተዳደር ፖሊሰ መምሪያ ህዝብ ግንኙነት