የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ለተለያዩ የትምህርት ተቋማት የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ።
******************************************
የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 ትምህርት ፅህፈት ቤት ስር ለሚገኙት አዲስ ራዕይ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤትና በቦሌ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በመገኘት የትምህርት መርጃ መሳሪያዎች ድጋፍ አድርጓል።
ድጋፉን የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሳምሶን ቢራቱ ያስረከቡ ሲሆን የወረዳ 5 ትምህርት ፅህፈት ቤት ሀላፊ አቶ እሸቱ ኢፋ እና የየትምህርት ተቋማቱ ተወካዮች ተቀብለዋል።
የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፉ ከ212,784 ብር በላይ ወጪ የተደረገበት ሲሆን የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፉ ለችግር ተጋላጭ ለሆኑ ተማሪዎች የተደረገ ድጋፍ ነው።