Abdu Book Center

@abdubook


በመጻሕፍት መደብራችን ፡
የታሪክ መጻሕፍት
የትምህርት አጋዥ እና መማሪያ መጻሕፍት
የተለያዩ ልበ-ወለድ እና መንፈሳዊ መጻሕፍት
ቆየት ያሉና አዳዲስ መጻሕፍት ሌሎችም..
አድራሻችን=አዲስ አበባ ፒያሳ የምኒልክ ሀዉልት ፊቱ ባዞረበት በኩል ፊት ለፊቱ ባስ እስቴሽኑ 50ሜትር ገባ ብሎ
ለበለጠ መረጃ በ0929574133 ደዉልሉን
@Abduseller

Abdu Book Center

13 Oct, 12:56


ከ1-12 ክፍል ላሉ ተማሪዎች እንዲኾኑ ታስበዉ የተሰናዱ ማጣቀሻ(አጋዥ) መጽሐፍት በመደብራችን ከ20-30% ቅናሽ ይሸምቱ።
#Extreme_Book_series
#New_edition
#ለተጠቃሚዎች
#ለነጋዴዎች

ድርጅታችን ላለፉት 11 ዓመታት የExtreme Books ወኪል አከፋፋይ ሆኖ መቆየቱ ልብ ይለዋል።

አድራሻችን አዲስ አበባ ፒያሳ ጊዮርጊስ እሳት አደጋዉ ሻገር ብሎ "አባቢያ ራሕመት ታቦር" ሕንፃ ፊትለፊት

ለበለጠ መረጃ በ09-29-57-41-33 ይደዉሉልን።

በዚሁ ስልክ ቁጥር በቴሌ ግራም፣ በዋትሳፕ እና በኢሞ ያነጋግሩን!
ክፍለ አገር እና ባሕር ማዶ ላላችሁ የመጻሕፍት ወዳጆች በተመጣጣኝ ዋጋ እና በታማኝነት በያላችሁበት በፍጥነት እንልክላችኋለን።

በቴሌግራም👇👇👇
https://t.me/Abdubook

በtiktok፦👇??👇👇👇
https://vm.tiktok.com/ZMjLMx7X9

Abdu Book Center

08 Oct, 07:46


በሙስሊም ግዛቷ አንደሉስ(በአሁኗ ስፔን) የትምሕርት ተቋማት ዉስጥ ይማሩ የነበሩ አዉሮፓዊያን ተማሪዎች ስፊቅህና ስለሸሪዐ(ስለ እስልምና ሕግጋት) ተግባራዊ አፈፃፀም የሚያትቱ የሙስሊም ሥነ-ጽሑፎችን ተርጉመዋል።በዚህ ጊዜ አዉሮፓ የተረጋጋ የፖለቲካ ሥርዓትም ሆነ በእኩልነትና በፍትሕ ላይ የተመሰረተ ሕግ አልነበሩዋትም።ናፖሊዮን ግብፅን በወረራ በያዘበት ወቅት 1798-1801 በማሊኪይ ትምሕርት ቤት(መዝሀብ) የታወቁት የፊቅህ ህግጋት ወደ ፈረንሳይኛ ተተረጎሙ።ቀጥሎም ለፈረንሳይ ሕግ በእርሾነት ያገለገሉ "ኪታብ አል_ኸሊል"ተተረጎመ።በዚያን ጊዜ የነበረዉ የፈረንሳይ ሕግ በአብዛኛዉ ከማሊኪ ትምሕርት ቤት ፊቅህ ጋር ተመሳሳይ ሆኖ እናገኘዋለን።

አዉሮፓ ከግሪክ ፍልስፍና ጋር የተዋወቀችዉ በሙስሊሙ ኅትመቶችና የትርጉም ሥራዎች አማካኝነት ነበር።ለዚህም ነዉ የኢሥላሙ አለም ቢያንስ ለሦስት ክፍለ ዘመናት ያክል በሳይንስ ዘርፍም የአዉሮፓ መምህራን እንደነበረ በርካታ የአዉሮፓዊያን ጸሐፍት የሚመሰክሩት....

"የኢስላማዊዉ ሥልጣኔ አንፀባራቂ ገጽታዎች"
ዝግጅት፦ዶ/ር ሙስጠፋ አስ-ሲባዒ
ትርጉም፦ረ/ፕሮፌሰር ኢድሪስ ሙሀመድ(በአ አ ዩ የፊሎሎጂ ሙሁር)

አድራሻችን አዲስ አበባ ፒያሳ ጊዮርጊስ እሳት አደጋዉ ሻገር ብሎ "አባቢያ ራሕመት ታቦር" ሕንፃ ፊትለፊት

ለበለጠ መረጃ በ09-29-57-41-33 ይደዉሉልን።


በዚሁ ስልክ ቁጥር በቴሌ ግራም፣ በዋትሳፕ እና በኢሞ ያነጋግሩን!
ክፍለ አገር እና ባሕር ማዶ ላላችሁ የመጻሕፍት ወዳጆች በተመጣጣኝ ዋጋ እና በታማኝነት በያላችሁበት በፍጥነት እንልክላችኋለን።

በቴሌግራም👇👇👇
https://t.me/Abdubook

በtiktok፦👇??👇👇👇
https://vm.tiktok.com/ZMjLMx7X9

Abdu Book Center

28 Sep, 12:13


Renaissance

በአዲስ አቀራረብ

በአዲስ ቦታ ስራ ጀምረናል።

አድራሻችን አዲስ አበባ ፒያሳ ጊዮርጊስ እሳት አደጋዉ ሻገር ብሎ "አባቢያ ራሕመት ታቦር" ሕንፃ ፊትለፊት

ለበለጠ መረጃ በ09-29-57-41-33 ይደዉሉልን።

Abdu Book Center

06 Sep, 19:07


#በምሣሌነት_ማስተማር

የአላህ መልእክተኛ (ሰለሏሁ ዓለይሂ ወሠለም)ለማስተማር የሚፈልጉትን በአካላዊ እንቅስቃሴ ሠርተዉ ያሳዩ ነበር።ወደ አላህ እንዴት በፍጹም አክብሮትና ፍርሃት፣ራስን በማስተናነስ፣ጥልቅ በሆነ ስሜት ስግደትን፣በምሽት ወደ አላህ እየተለቀሰ መቃረብን፣እንዴት ማከናወን እንደሚገባ መጀመሪያ ራሳቸዉ ሠርተዉ ከዚያ ለተከታዮቻቸዉ አስተምረዋል።

በመሆኑም ያስተማሩት ሁሉ በመጀመሪያ ቤታቸዉ ባሉ አባላት፣ቀጥሎም በህብረተሰቡ፣ቃላቸዉን ከተግባራቸዉ በመጣጣሙ፣ወዲያዉ ልባቸዉን ነክቶ ተቀባይነት ለማግኘት ችለዋል።ከእርሳቸዉ ህልፈት በኋላም በእርሳቸዉ ት/ቤት በተኮተኮቱና ልቦናቸዉ በፍጹም ጸድቶ ለአላህ አገልግሎት ራሳቸዉን ባሠማሩት ብፁኣን አማካኝነት አስተምህሮቱ በዓለም ተሠራጭቶ፣የአላህ መልዕክተኛ ሰላትና ሰላም ይዝነብባቸዉና በዘረጉት ደረጃ ዲኑን የሚያገለግሉ ሙስሊሞችን ለማየት የሰዉ ልጆች በቅተዋል።

የመልእክተኛዉ ቤት በቋሚነት ለአላህ ራስን የማስተናነስና የመገዛት ስሜት ጎልቶ ይታይ ነበር።የገነት ምስራችና የገሃነም አስደንጋጭ ሁኔታም ይሰማ ነበር።መልዕክተኛዉ ገሀነምን በመፍራትና ገነትን በመመኘት ስሜት ዉስጥ ተዉጠዉ የሚያያቸዉ ሁሉ አላህን የሚያስታዉስበት ሁኔታ ዉስጥ ይገባ ነበር።ኢማም አል-ነሣኢ እንደ ዘገቡት "መልዕክተኛዉ ሰለሏሁ ዓለይሂ ወሠለም እየጸለዩ ባሉበት ወቅት የሚፈላ ዉሃ የሚያሰማዉ ድምጽ ዓይነት ይሰማ ነበር።“ ጸሎታቸዉ ሁሌም በሚቃጠልና በሚያለቅስ ልቦና ነበር የሚያደርሱት።አዒሻ ረዲየሏሁ ዓንሃ ሁልጊዜም ጌታቸዉ ፊት ሲሆኑ እየተንቀጠቀጡ ሲሰግዱ ነበር የምታገኛቸዉ።....

«እነሆ ተምሳሌት»ከገጽ 145-146

መጽሐፉ እዉቁ ቱርካዊ የእስልምና ኃይማኖት ሊቅ ፤የተለያዩ ከ40 በላይ መጽሐፍት አሰናኝ እና ከመቶ በላይ የሚቆጠሩ የተለያዩ ጥናታዊ ጽሁፎች አሳታሚ የኾኑት ሙሐመድ ፈትሁሏህ ጉለን «ሙሐመድ የአላህ መልእክተኛ» የሚል ርዕስ ሰጥተዉ ካሳተሙት ዳጎስ ያለ መጽሐፋቸዉ፤ ዋቢ በማድረግ አብዱልዋሲዕ ዩሱፍ ዓሊ መንዲዳ(ኤል ኤል ቢ ኤል ኤል ኤም) ሙክተሶር አድርገዉና የመልእክተኛዉ ስብእና እና ተምሳሌትነት የበለጠ ያጎላልኛል ያሉትን ፓርት ነቅሰዉ በማዉጣት «እነሆ ተምሳሌት» የሚል አርዕስት ሰጥተዉ በተባ ብዕራቸዉ 2009 ዓመተ ልደት ወደ አማርኛ ቋንቋ መልሰዉታል።

Abdu Book Center

04 Sep, 06:41


ማንኛዉንም መጽሐፍት ለማዘዝ ሲሹ በ👉@Abduseller
ይጠቀሙ።

Abdu Book Center

04 Sep, 06:35


#አላህ_ኃጢአተኞችን_በዚህ_ዓለም_የማይቀጣቸዉ_ረስቷቸዉ_አለመሆኑን_አስታዉስ

ሰዎች በዚህች ዓለም ላይ የዓመጽ ሕይወት ሲገፉ እያስተዋለ አላህ ዝም የሚላቸዉ ረስቷቸዉ አይደለም።የመረጡት የጥመት መንገድ መሆኑንና የማመዛዘን ችሎታቸዉን(ሕሊናቸዉን) ሊጠቀሙበት አለመፍቀዳቸዉን ስለሚያዉቅ ንቋቸዉ ነዉ።ይልቁንም በኃጢዓታቸዉ ላይ ዘዉታሪዎች ሆነዉ እያለ አንድ ቀን እንደሚይዛቸዉ ሲገልጽ እንዲህ ይላል፦

"አላህንም በደለኞች ከሚሠሩት ግፍ ዘንጊ አድርገህ አታስብ፤የሚያቆያቸዉ፥ዓይኖች በእርሱ እስከሚፈጡበት ቀን ድረስ ብቻ ነዉ።"(ኢብራሒም፡42)

ብዙ ሰዎች በአላህ እዝነት ስፋት ተዘናግተዉ በሃጢዓት ላይ በመዘዉተር እድሜያቸዉን ይገፋሉ።እንዲያዉም ከዚህም አልፈዉ አላህ በሚሰጣቸዉ ምድራዊ ጸጋ ተታልለዉ እንደሚወዳቸዉ ያስባሉ።ይህ ሁኔታም ብዙ የዓለም ሰዎችን ሲያዘናጋቸዉ ይታያል።አላህ እንዲህ ይላል፦

"ገንዘቦቻቸዉንና ልጆቻቸዉም አይድነቁህ፤አላህ የሚሻዉ በቅርቢቱ ሕይወት በነርሱ(በገንዘቦቻቸዉና በልጆቻቸዉ) ሊቀጣቸዉ፥ነፍሶቻቸዉም እነሱ ከሓ*ዲዎች ኾነዉ ሊወጡ ብቻ ነዉ።"(አት-ተዉባህ፡55)

«አስታዉስ»
በአህመድ ሑሰይን(አቡ-ቢላል)
2006 ዓመተ ልደት፥ገጽ 50

አድራሻችን፦
አዲስ አበባ ፒያሳ
ለበለጠ መረጃ በ 0929574133 ይደዉሉልን!

በዚሁ ስልክ ቁጥር በቴሌ ግራም፣ በዋትሳፕ እና በኢሞ ያነጋግሩን!
ክፍለ አገር እና ባሕር ማዶ ላላችሁ የመጻሕፍት ወዳጆች በተመጣጣኝ ዋጋ እና በታማኝነት በያላችሁበት በፍጥነት እንልክላችኋለን።

በቴሌግራም👇👇👇
https://t.me/Abdubook

በtiktok፦👇??👇👇👇
https://vm.tiktok.com/ZMjLMx7X9

Abdu Book Center

02 Sep, 10:25


በሐላልና በሐራም አጀንዳ ላይ የኢስላም መሠረታዊ መርሆዎች

- የነገሮችን መሠረታዊ ባሕሪ ሐላልነት ነዉ፣

- ነገሮችን ሐላል ወይም ሐራም በማለት የመወሰን መብት የአላህ ብቻ ነዉ፣

- ሐላሉን ሐራም፥ሐራሙን ሐላል ማለት የሺርክ አካል ነዉ፣

- ሐራምነት ከመጥፎነት እና ከጉዳት ጋር የተያያዘ ነዉ፣

-ፍላጎትን ሊያሟሉ የሚችሉ ነገሮች፥ወደ ሐራም መሄድ ሳያስፈልግ፥ሐላል ዉስጥ ይገኛሉ፣

-ለሐራም የሚያበቃ ነገር ሁሉ ሐራም ነዉ፣

-ለሐራም መዘየድ ሐራም ነዉ፣

- ቅን ሐሳብና መልካም "ኒያ" ሐራምን ሐላል አያደርጉም፣

- አሻሚ ነገሮችን መጠንቀቅ፣

-በሐራም ነገሮች ላይ በሰዎች መካከል ልዩነት የለም፣

-አስገዳጅ ሁኔታዎች ሐራምን(ለጊዜዉ) ለመጠቀም መነሻ ይሆናሉ።

ዝግጅት፦ፕ/ር ኢማም ዩሱፍ አልቀረዳዊ(ራሕመቱላሂ ዓለይህ)

ትርጉም፦አምባሳደር ዑስታዝ ሐሰን ታጁ

Abdu Book Center

02 Sep, 05:42


የሐረር ከተማ
አቦከርን አልፈን ከበታቻችን የሐረርን ከተማ ባየሁ ጊዜ አእምሮዬ በጣም ተቀስቅሶ፣በሸዋ በር ገብተን፣በግምብ ቤቶች መካከል ስናልፍ ያገሩ ሰዎች፣ወንዶቹም ሴቶቹም፣በየግንቡ ላይ እየተንጠለጠሉ ቁልቁል ያስተዉሉናል።ባጠገባቸዉ ስናልፍ ሴቶቹ በእልልታ ተቀበሉን።

የግንብ ከተማ በቤት ላይ ቤት የተሠራበት አይቼ አላዉቅም።ሱቆች እና መደብሮች በዉስጣቸዉ ስንትና ስንት ዐይነት ዕቃዎች የተደረደሩባቸዉ እና የተሞሉባቸዉ ናቸዉ።ይህን ሁሉ ባንድ ጊዜ ማየት በባላገር ዉስጥ ላደገ ልጅ እንዴት ያስደንቃል?ራስ ያዞራል፤ልብ ያማልላል።.....

በጥቂት ቀኖች ዉስጥ ከተማዉን አዳረስኩት፤በአምስቱም በሮች እየወጣሁ እየገባሁ፣እየተመላለስኩ የከተማዉን ዙሪያ፣በዉስጡም የሚገኘዉን ሁሉ ማተርኩት።ሙዝ፣ሸንኮራ አገዳ፣ትርንጎ፣ወይን፣ሎሚ፣ሮማን...ሞልተዋል።ባንድ መሐለቅ(ትሙን) አንድ አበዛ ሙዝ መግዛት ይቻላል፤ሱካር፣ወረቀት፣ቀለም፣እርሳስ፣ክብሪት፣ሴንጢ፣አቡጀዲ፣ዲንቲ፣ሻሽ፣ሱቲ፣ጃንጥላ...ስንቱ ይነገራል፤...ሞልተዋል።ሁሉም ያስደንቃል።...

ኦቶባዮግራፊ(የሕይወት ታሪክ)
ፊታዉራሪ/በጅሮንድ ፊታዉራሪ ተክለ ሐዋሪያት ተክለ ማርያም

ገፅ 26
የመጀመሪያ ሕትመት ፲፱፻፺፷

አድራሻችን፦
አዲስ አበባ ፒያሳ
ለበለጠ መረጃ በ 0929574133 ይደዉሉልን!

በዚሁ ስልክ ቁጥር በቴሌ ግራም፣ በዋትሳፕ እና በኢሞ ያነጋግሩን!
ክፍለ አገር እና ባሕር ማዶ ላላችሁ የመጻሕፍት ወዳጆች በተመጣጣኝ ዋጋ እና በታማኝነት በያላችሁበት በፍጥነት እንልክላችኋለን።

በቴሌግራም👇👇👇
https://t.me/Abdubook

በtiktok፦👇??👇👇👇
https://vm.tiktok.com/ZMjLMx7X9

Abdu Book Center

03 Aug, 14:12


አዲስ መጽሐፍ በገበያ ላይ
በእንዳለጌታ ከበደ(ዶ/ር)
ሐምሌ 2016 ዓ.ል

«ሲጥል» እንደ ከዚህ ቀደም የእንዳለጌታ መጻሕፍት ከራሳችን ጋር የሚያጨዋዉቱ፣ለሙግትም የሚጋብዙ ሃሳቦች የተስተናገዱበት ኪናዊ ማዕድ ነዉ።የድኀረ ዘመናዊ ደራሲያንን የአጻጻፍ መንገድ በከፊል ተከትሎ፣የትረካ ስልቱን ደግሞ እንደ ጃዝ ሙዚቃ አድርጎታል።በጃዝ ሙዚቃ እያንዳንዱ ተሳታፊ ሙዚቀኛ በተናጠል ስሜቱንና ሃሳቡን ለዕድምተኛዉ የሚያጋባበት፣ችሎታዉን የሚያስፈትሽበት ጥቂት "ዕድል"እንዳለዉ ሁሉ፣የ"ሲጥል" ገጸባህሪያትም አንዳንዴ ለየብቻ-ከዐዉዱ ሳይነጠሉ፣ድባቡንም ሳያዉኩ-ኑረታቸዉን ይተርኩልናል፤እነዚህ ለየብቻ ሲጫወቱልን የቆዩ ተራኪዎች ተመልሰዉ ደግሞ በኅብር ይከይኑልናል....ፍቅርና ጥላቻን...ሣቅና ሲቃን....ፍርሃትና ድፍረትን...«መሆን ወይም አለመሆን»ን!

Abdu Book Center

03 Aug, 13:58


«ለእርቃን ሩብ ጉዳይ»

በሕይወት እምሻዉ

ሐምሌ 2016

የመጽሐፉ የገጽ ብዛት፦208
የሽፋን ዋጋ፦300

የደራሲዋ ቀደምት ስራዎች፦

*ባርቾ(ቀዳማይ የድርሰት ስራዋ፥2007)
*ፍቅፋቂ እና ማታ ማታ

መጽሐፍቱ በ Abdu Book Delivery ይገኛሉ።

Abdu Book Center

02 Aug, 12:37


የተጓዡ ጋዜጠኛ ሄኖክ ስዩም አዲሱ መጽሐፍ አስገብተናል።

Abdu Book Center

25 Jul, 18:01


ሩሕ(መንፈስ)

ሩሕ በዐይን ከማይታዩ ረቂቅና አስገራሚ የአላህ ፍጥረታት መሀከል ዉስጥ ነዉ፤የሩሕን ትክክለኛ ምንነት ከአላህ ዉጭ ማንም አያዉቀዉም፤ሩሕ ከምድራዊዉ የሰዉ ልጅ አካል ጋር ሲቆራኝ የሰዉነት ክፍሎች ህያዉ ሆነዉ መንቀሳቀስ ይጀምራሉ።

የሩሕን(የመንፈስ) ኑረት ማፅደቅ ስነ-እምነታዊ ግዴታ ነዉ፤አላህ(ሱብሃነሁ ወተዓላ)እንዲህ ይላል፦

ከሩሕም ይጠይቁሀል።«ሩሕ ከጌታዬ ነገር ነዉ ከእዉቀትም ጥቂትን እንጂ አልተሰጣችሁም»በላቸዉ።

በዚህ አንቀጽ ላይ እንደምናስተዉለዉ የሰዉ ልጅ እዉቀት የተገደበና ዉስን እንደሆነ ነዉ፤ብሎም በከባቢዉ ያለዉን ፍጡር እንኳን አስረግጦ ከመገንዘብ ደካማ የሆነ ፍጡር ስለ ኃያሉ ፈጣሪዉ ትክክለኛ እዉንነት ከማወቅ ምን ያህል ደካማ ሊሆን እንደሚችል ማሰብ ቀላል ነዉ።....

ሩሕ ከሰዉ ልጅ አካል ዉስጥ የሚገባዉ ፅንስ በአፈጣጠር እርከኑ 4 ወር ሲሞላዉ እንደሆነ ጠቢበል በሸር የኾኑት የአላህ መልእክተኛ (ሰለሏሁ ዓለይሂ ወሠለም) እንዲህ በማለት ገልፀዉልናል፦

«አንዳችሁ ፍጥረቱ በእናቱ ሆድ ዉስጥ ለ40 ቀናት የፍትወት ጠብታ ሆኖ ይሰበሰባል፣ከዛም ልክ እንደዛዉ(ለ40 ቀናት) የረጋ ደም ይሆናል፣ከዛም ልክ እንደዛዉ ቁራጭ ስጋ ይሆናል፣ከዛ መላአኩ ወደሱ ይላካል፣መንፈስም(ሩሕ) ይነፋበታል፣ሲሳዩን፣እድሜዉን፣ስራዉን፣እድለኝነቱን አልያም እድለ ቢስነቱን (እጣ ፈንታዉ) እንዲጽፍ በአራት ቃላቶች ይታዘዛል፣....

ህያዉ ብርሐን
ዑስታዝ አብዱልሐሚድ አማን( አቡ ሱሀይል)
2014 ዓመተ-ልደት

Abdu Book Center

22 Jul, 17:41


ቴዎድሮስ ተ/አረጋይ ዳጎስ ባለ የሕይወትና ስራ ልምዱ ብዙ እንድንማርበት የበቃ ጋዜጠኛ ነዉ።ትዕግስት ዋልተ ንጉስ በስነ-ልቦና አማካሪነቷ ጉልህ ዉጤት ያላት ሙያተኛ ናት።ሁለቱም በማሰብ ጥሞናቸዉ ይመሳሰላሉ።ሁለቱም ስለሀገርና ስለትዉልድ ብርቱ ኃላፊነት እንደሚሰማቸዉ አብረንም ስለምናሳልፍ አዉቃለሁ።እነዚህ ሁለቱ ባለሙያዎች «ምን ሆኛለሁ?» በሚል ርዕስ ለምን ሆነናልነት መልስ የሚሰጥ፣እንደ ሀገር ፈር ቀዳጅ የሆነ መጽሐፍ ሰንደዉልናል።
ሙሐመድ ዓሊ(ቡርሀን አዲስ)
(የ40 የፍልስፍናና የታሪክ መጻሕፍት፣የ"ዉሀ እና ወርቅ"እና "ዓለም በቃኝ" ፊልሞች ደራሲ)

አድራሻችን፦
አዲስ አበባ  ፒያሳ
ለበለጠ መረጃ በ 0929574133 ይደዉሉልን!

በዚሁ ስልክ ቁጥር በቴሌ ግራም፣ በዋትሳፕ እና በኢሞ ያነጋግሩን!
ክፍለ አገር እና ባሕር ማዶ ላላችሁ የመጻሕፍት ወዳጆች በተመጣጣኝ ዋጋ እና በታማኝነት በያላችሁበት በፍጥነት እንልክላችኋለን።

በቴሌግራም👇👇👇
https://t.me/Abdubook

በtiktok፦👇??👇👇👇
https://vm.tiktok.com/ZMjLMx7X9

Abdu Book Center

22 Jul, 17:38


ነገ(ማክሰኞ) መነሻችን ፒያሳ ፤መዳረሻችን አለም ባንክ ነዉ ሚኾነዉ።

free delivery

እስከ ረፋድ የምትፈልጓቸዉን መጽሐፍት ማዘዝ ትችላላችሁ

ለማዘዝ፦inbox

ለማዘዝ፦@Abduseller