አዲስ አበባ፤ ጥር 24 ቀን 2017 ዓ.ም
ዋና ኮሚሽነር አቶ ባዮ ሽጉጤ አርሶ አደሮችን መልሶ ማቋቋምና ማልማት፣ ከተማ ግብርናን ማስፋፋትና ማጠናከር፣ ጤንነቱና ደህንነቱ የተረጋገጠ የግብርና ምርትና አገልግሎት ለከተማዋ ነዋሪ እዲቀርብ ማድረግ ላይ ሥራዎች መሰራታቸውን ገልፀዋል።
አያይዘውም አስተዳደራዊ የሆኑ በርካታ ሥራዎች የተሰሩ መሆኑን ተናግረዋል።
ይሁንና በቁልፍ ተግባርም ሆነ በዐብይ ተግባር የአፈፃፀም ክፍተቶች መኖራቸውን ዋና ኮሚሽነሩ አንስተው የሥራ መመሪያ ሰጥተዋል።
የአርሶ አደር ማቋቋምና ሬጉላቶሪ ዘርፍ ም/ኮማሽነር ወ/ሮ ሎኮ ዳለቻ አርሶ አደሩን መልሶ ከማቋቋምና ከማልማት ጋር በተያያዘ ሰፊ ሥራ ተሰርቷል፤ ይሁንና መረጃ አደራጅቶ ከመያዝ አንፃር፣ መብት ፈጠራ እና የሥራ ዕድል ፈጠራ ልዮ ትኩረት ስለሚፈልግ ተቀናጅተን መሥራት ይገባል ብለዋል።
የከተማ ግብርና ዘርፍ ም/ኮሚሽነር አቶ ፋሩቅ ጀማል የሌማት ትሩፋትእና ዕቅድን ማሳካት ላይ እውቅና መስጠት ይገባል፤ ሌላው በርካታ ሥራዎች በግማሽ ዓመቱ የተሰሩ መሆኑን ገልፀው ነገር ግን ነባርና አዲስ የከተማ ግብርና ተጠቃሚዎችን መረጃ ጥርት ባለ መንገድ በማደራጀት ዕቅድና ሪፖርታችንን ከላይ እስከታች በተናበበ መንገድ መያዝ አለብን ብለዋል።
ተሳታፊዎችም የ6 ወራት ሥራ አፈፃፀም ሪፖርቱን መነሻ በማድረግ በጥንካሬና በክፍተት አለ ያሉትን ሃሳብ አንስተዋል።
ዋና ኮሚሽነር አቶ ባዮ ሽጉጤ መደበኛ እና የሌማት ቱርፋት ሥራዎችን አቀናጅቶ መምራት፣ ዕቅድን ከሪፖርት ጋር አናቦ መሬት ላይ ሕይወት እንዲኖረው ማድረግ፣ መረጃን በጥራት ማደራጀት፣ ቁልፍና ዐበይት ተግባራትን አጣጥሞ መሥራ፣ ቅንጅታዊ ሥራዎችን ከሚመለከታቸው ተቋማት ጋር በመናበብ ተግባራዊ ማድረግ ይገባል ብለዋል።