Walta Tv ዋልታ ቲቪ

@waltatv


Walta tv news Official Telegram Channel Join Us For more Update

Walta Tv ዋልታ ቲቪ

23 Oct, 07:05


ባለፉት ሶስት ወራት ለህዳሴ ግድብ ግንባታ ከ271 ሚሊዮን ብር በላይ ድጋፍ ተሰበሰበ

ጥቅምት 13/2017 (አዲስ ዋልታ) በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ከ271 ሚሊዮን ብር በላይ ድጋፍ መሰብሰቡን የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽህፈት ቤት አስታወቀ።

የፕሮጀክት ጽህፈት ቤቱ የፐብሊክ ዲፕሎማሲ ህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ስራ አስፈጻሚ ሰለሞን ዳንኤል በ2017 በጀት ዓመት ለህዳሴ ግድብ ግንባታ 1 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ ለመሰብሰብ መታቀዱን ገልጸዋል።

በመጀመሪያው ሩብ ዓመት በሀገር ውስጥና በውጭ ከሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን በቦንድ ሽያጭ፣ በ8100 አጭር የፅሑፍ መልዕክትና በስጦታ ከ271 ሚሊየን ብር በላይ ድጋፍ መሰብሰቡን ተናግረዋል።

በዓመቱ የታቀደውን ድጋፍ ለማሰባሰብ በትኩረት ይሰራል ያሉት ስራ አስፈጻሚው ህዝቡም እስከ ግንባታው ፍጻሜ ድጋፉን እንዲቀጥል ጥሪ ማቅረባቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

መገናኛ ብዙኃንና እውቅ የማህበራዊ ሚዲያ አንቂዎች የገቢ ማሰባሰቢያ አማራጮችን ለህብረተሰቡ በማሳወቅ ሚናቸውን እንዲወጡም ጠይቀዋል።

Walta Tv ዋልታ ቲቪ

23 Oct, 04:44


👉ላልጀመራችው እንዳያመልጣችሁ
http://t.me/hrummebot/game?startapp=ref652246848

Walta Tv ዋልታ ቲቪ

22 Oct, 09:07


አሜሪካ ዩክሬን ድሮን ለማምረት እንድትችል የ800 ሚሊዮን ዶላር እርዳታ ልትሰጥ ነው

ጥቅምት 12/2017 (አዲስ ዋልታ) አሜሪካ ዩክሬን ድሮን ማምረት እንድታቋቋም የሚያግዛት 800 ሚሊዮን ዶላር እርዳታ ለመስጠት መወሰኗን ፕሬዝዳንት ቮሎድሚር ዘለንስኪ ገለጹ።

ይህ ዕርዳታ በቅርቡ ኬየቭ ተጉዘው የነበሩት የአሜሪካ መከላከያ ሚኒስትሩ ሎይድ ኦስተን ቃል ከገቡት 400 ሚሊዮን ዶላር የጦር መሳሪያ እርዳታ በተጨማሪ መሆኑን ሮይተርስ ዘግቧል።

ፕሬዝዳንት ዘለንስኪ ዕርዳታውን አስመልክተው “ዩክሬን ስተደረገላት ዕርዳታ ታመሰግናለች፤ በዓለም ላይ የተጋረጠውን ማንኛውም ፖለቲካዊ አደጋ ዩክሬን ሉዓላዊነቷን እና ነጻነቷን ለማስከበር ቁርጠኛ መሆኗን ማረጋገጥ ያስፈልጋል” ብለዋል።

ዩክሬን ከሩሲያ ጋር ጦርነት ከገባች ጀምሮ  የጦር መሳሪያና ተተኳሽ በአገሯ ለማምረት ትኩረት ሰጥታ  እየሰራች መሆኗን መረጃዎች ያመለክታሉ።

ፕሬዝዳንት ዘለንስኪ ከጦር መሳሪያ አምራች ኩባንያ ባለስልጣናት ጋር በነበራቸው ውይይት አገራቸው በዓመት 4 ሚሊዮን ድሮን ለማምረት አቅም እንዳላት ገልጸዋል።

Walta Tv ዋልታ ቲቪ

21 Oct, 18:47


በመርካቶ ሸማ ተራ አከባቢ በተከሰተው የእሳት አደጋ በንብረት ላይ ለደረሰው ጉዳት እጅግ አዝነናል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

ጥቅምት 11/2017 (አዲስ ዋልታ) በመርካቶ ሸማ ተራ አከባቢ በተከሰተው የእሳት አደጋ በንብረት ላይ በደረሰው ጉዳት ማዘናቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።

የተከሰተውን የእሳት አደጋ ለመቆጣጠር ከእሳት አደጋ እና ስጋት መከላከል እንዲሁም  ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር በመሆን ርብርብ እየተደረገ መሆኑንም ገልጸዋል።

አደጋውን ቶሎ ለመቆጣጠር እየተደረገ ያለዉን ጥረት አዳጋች ያደረገዉ የአካባቢው መንገድ የእሳት አደጋ መኪና በተሟላ ሁኔታ ለመንቀሳቀስ አስቸጋሪ በመሆኑ ምክንያት በሄሊኮፕተር ለመጠቀም እየጣርን  ነው ብለዋል። 

ይህንን አደጋ ለመቀነስ ርብርብ እያደረጋችሁ ያላችሁ አካላት ሁላ ጥረታችሁን አጠናክራችሁ እንድትቀጥሉ አሳስባለሁ ሲሉም በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው አስገንዝበዋል።

Walta Tv ዋልታ ቲቪ

21 Oct, 08:52


የባህር ዳር ከተማ ስማርት ሲቲ ፕሮጀክት ለመስራት የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ

ጥቅምት 11/2017 (አዲስ ዋልታ) የባህር ዳር ከተማ የስማርት ሲቲ ፕሮጀክት ለመስራት የሚያስችለውን ስምምነት የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር ተፈራረመ፡፡

በስምምነቱ ወቅት የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ ተፈጥሮ የቸረችንን ውበት ዘመኑ ባፈራው ቴክኖሎጂ በመታገዝና በመጠቀም ለሀገራዊ ኢኮኖሚና ለዜጎች ልንጠቀም ይገባል ብለዋል፡፡

ለዚህም በስማርቲ ሲቲ ፕሮጀክት እንደ ባህር ዳር ከተማ ያሉ ከተሞችን ለመገንባትና የቱሪዝም መዳረሻ ለማድረግ እየሰራን እንገኛለን ነው ያሉት፡፡

ባህር ዳርን በፕሮጀክቱ ለመገንባት የተሰራው ዲዛይን ለጎብኝዎችና ለነዋሪዎች ምቹ ከማደርግ ባለፈ የትራፊክ ፍሰትን የሚቀንስ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡

የባህር ዳር ከተማ ከንቲባ ጎሹ እንደላማው በበኩላቸው ባህር ዳር ከተማ የዘመናዊነት ከተማ ማሳያ እንድትሆን አዲስ ምዕራፍ ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር መጀመራቸውን ገልጸው ከተማዋን ለነዋሪዎቿ ምቹና ተስማሚ እንዲሁም በጎብኝዎች ተመራጭ የሆነች ከተማ ለመፍጠር እየተሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡

በከተማዋ ከዚህ በፊት በ22.5 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት እየተተገበረ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡

ከተማዋ የጎብኝዎች መዳራሻ እንደመሆኗ የቱሪስት ንብረቶች ሲጠፉ ትራክ አድርገው ንብረታቸውን ማግኘት የሚያስችል እንደሆነም ተጠቁሟል፡፡

ሰማኸኝ ንጋቱ (ከባህር ዳር)

Walta Tv ዋልታ ቲቪ

20 Oct, 19:22


የ5G ኔትዎርክ አገልግሎት በአማራ ክልል ተደራሽነቱን አስፍቶ ለተጠቃሚዎች ቀርቧል

ጥቅምት 10/2017(አዲስ ዋልታ) የ5G ኔትዎርክ አገልግሎት በአማራ ክልል ተደራሽነቱን አስፍቶ ለተጠቃሚዎች መቅረቡን የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ ገለጹ።

ኢትዮ ቴሌኮም በባህር ዳር ከተማ የአምስተኛውን ትውልድ (5G) ኔትወርክ በዛሬው እለት በይፋ አስጀምሯል፡፡

እንደ ሀገር ሀብትን በአግባቡ ለመጠቀም ቴክኖሎጂ ወሳኝ ነው ያሉት ሥራ አስፈፃሚዋ በቴክኖሎጂ ተግዳሮት ሲገቱ የነበሩ የብልፅግና እሳቤዎችን ለመፍታት የ5G ኔትዎርክ አስተፅኦው የጎላ መሆኑን ገልጸዋል።

ለአብነትም ባህር ዳር ከተማን ስማርት ሲቲ ከማድረግ ጀምሮ የግብርናውን፣ የጤናውን ዘርፍና ሌሎችን አገልግሎቶችን በማሳለጥ የዜጎችን ኑሮ የሚያዘምን ነው ሲሉ ጠቁመዋል።

በዚህም ዛሬ ይፋ የተደረገው የአምስተኛውን ትውልድ (5G) ኔትወርክ በባህር ዳር ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን፣ በባህር ዳር መናኸሪያ፣ በባህር ዳር ዩኒቨርስቲ ፖሊ ካምፓስና በተለያዩ የከተማዋ አካባቢዎች እንደሚሰራ ገልጸዋል።

79 ሚሊዮን ደምበኞች ያሉት ኩባንያው በየጊዜው በተለያዩ የቴክኖሎጂ አማራጮች አገልግሎቱን ቀልጣፋና ምቹ በማድረግ ኢትዮጵያውንን ተጠቃሚ ለማድርግ እየሠራ ይገኛልም ነው ያሉት።

ለዚህም ኢትዮ ቴሌኮም የወደፊቷን ዲጂታል ኢትዮጵያን በመገንባት ረገድ በትጋት የበኩሉን ሚና እየተወጣ ያለ ተቋም ነው ሲሉ ተናግረዋል።

በሰማኸኝ ንጋቱ (ከባሕር ዳር)

Walta Tv ዋልታ ቲቪ

15 Oct, 08:24


የአውሮፓ ህብረት በኢራን ላይ አዲስ ማዕቀብ ጣለ

ጥቅምት 5/2017 (አዲስ ዋልታ) የአውሮፓ ህብረት ለሩሲያ ሚሳኤል እና ድሮን ሰጥታለች በሚል በኢራን ላይ አዲስ ማዕቀብ ጣለ።

አዲሱ ማዕቀብ ሚሳኤሎቹንና ድሮኖቹን ወደ ሩሲያ በማስተላለፍ ተሳትፈዋል በተባሉ ተቋማትና ግለሰቦች ላይ ያነጣጠረ ሲሆን ንብረታቸው መታገዱንና የጉዞ ዕቀባ እንደተደረገባቸው ተጠቅሷል።

የኢራን ምክትል መከላከያ ሚኒስቴር፣ የአብዮታዊ ጥበቃ ኃይል (ቃድ) ከፍተኛ አባላት እና ሶስት የአገሪቱ አየር መንገዶች ጨምሮ ከ12 በላይ የሚሆኑ ግለሰቦችና ተቋማት የአዲሱ ማዕቀብ ሰለባ መሆናቸውን አልጃዚራ ዘግቧል።

የአውሮፓ ህብረት ኮሚሽን ፕሬዝዳንት በኤክስ ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት “የኢራን መንግስት በዩክሬን ላይ ጦርነት ላወጀችው ሩሲያ የሚያደርገው ድጋፍ ተቀባይነት የለውም፤ መቆም አለበት” ብለዋል።

በኢራን ላይ የተጣለውን ማዕቀብ አስመልክቶ የዩክሬን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጸብ አጫሪነትን የሚደግፉ ሁሉ ኃላፊነት ይወስዳሉ፤ ዋጋም ያስከፍላቸዋል ብለዋል።

የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ በበኩላቸው አገራቸው ድርጊቱን አለመፈጸሟን ገልጾ የህብረቱ እርምጃ ዓለም አቀፍ ህግን የጣሰ ነው ሲልም ኮንኗል።

የኢራን ፕሬዝዳንትም አገራቸው በጉዳዩ እጇ እንደሌለባት ገልጸዋል።

Walta Tv ዋልታ ቲቪ

07 Oct, 16:16


"ዛሬ የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ሆነው ለተሾሙት አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ  እንኳን ደስ አለዎት ለማለት እፈልጋለሁ።

በዚህ ትልቅ የኃላፊነት ቦታ ሀገራችንን በቅንነት፣ በጥበብ እና በጥልቅ የዓላማ ስሜት እንደሚያገለግሉ ሙሉ ዕምነት አለኝ። በአገልግሎት ዘመንዎ የላቀ ስኬት እንዲኖርዎት እመኛለሁ።

በተጨማሪም ላለፉት ስድስት ዓመታት ኢትዮጵያን በፕሬዝዳንትነት ላገለገሉት ክብርት ሣሕለ ወርቅ ዘውዴ ላበረከቱት የላቀ ለአገልግሎት ምስጋናዬን ለማቅረብ እወዳለሁ፡፡" - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ

Walta Tv ዋልታ ቲቪ

06 Oct, 20:20


"ማምሻዉን በመዲናዋ የተለያዩ አከባቢዎች የተሰማው የመሬት ንዝረት ፈንታሌ ላይ በደረሰው የመሬት መንቀጥቀጥ ምክነያት የተከሰተ መሆኑ ተገለፀ።

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂኦ ፊዚክስ እና ስፔስ ሳይንስ ዳይሬክተር ዶ/ር ኤሊያስ ሌዊ እንዳገለጹት ዛሬ ማምሻውን በከተማችን አዲስ አበባ የተከሰተው የመሬት ንዝረት በስምጥ ሸለቆ በተለይም ፈንታሌ አካባቢ ዛሬ ብቻ ሳይሆን ላለፉት 10 ቀናት ዉስጥም እየተከሰተ የነበረ የመሬት መንቀጥቀጥ ምክንያት መሆኑን እና በአዲስ አበባም እየተከሰተዉ የነበረው የመሬት ንዝረት በዚሁ ምክንያት መሆኑን ገልጸዋል ።
የከተማችን ነዋሪዎች ሳይደናገጡ በባለሙያው የተገለጹ መደረግ የሚገባቸው ጥንቃቄዎችን እንዲያደርጉ ይህን መረጃ አጋርቻለሁ።"

ከንቲባ አዳነች አቤቤ

Walta Tv ዋልታ ቲቪ

03 Oct, 19:19


ሰሞኑን በጅቡቲ የባህር ዳርቻ በደረሰው አደጋ የሞቱት ዜጎች ኢትዮጵያዊያን መሆናቸው ተረጋገጠ

መስከረም 23/2017 (አዲስ ዋልታ) ሰሞኑን በጅቡቲ የባህር ዳርቻ በደረሰው የጀልባ መስጠም አደጋ የሞቱት ዜጎች በሙሉ ኢትዮጵያዊያን መሆናቸው መረጋገጡን በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስታወቀ፡፡

መስከረም 21 ቀን 2017 ዓ.ም ማምሻውን ከየመን ወደ ጅቡቲ 320 መደበኛ ያልሆኑ ፍልሰተኞች ይዘው የተነሱት ሁለት የስደተኞች ጀልባዎች በጅቡቲ ባህር ዳርቻ አከባቢ ሲደርሱ በደረሰው አደጋ የዜጎች ህይወት ማለፉ ይታወሳል።

አደጋውን ተከትሎ 48 ፍልሰተኞች ህይወታቸው ሲያልፍ፣ 197 ፍልሰተኞች ከአደጋው ተርፈው ኦቦክ የሚገኘው ዓለም አቀፉ የስደተኞች ካምፕ መድረሳቸው ተጠቅሷል።

የተቀሩት 75 ፍልሰተኞችን አካል የማፈላለጉ ስራ በነፍስ አድን ሠራተኞች መቀጠሉም ተገልጿል።
 
እስከአሁን በስፍራው በተደረገው የዜጎች ማጣራት ሂደት ሁሉም ፍልሰተኞች ኢትዮጵያዊያን መሆናቸውን ከሚመለከተው አካላት በተገኘው መረጃ ማወቅ መቻሉን በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አመልክቷል።

ኤምባሲው በዚህ ከባድ አደጋ ምክንያት ህይወታቸውን ባጡ ዜጎች የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን በመግለጽ በህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ምክንያት በየጊዜው እየደረሰ ያለውን ሞት ለመቀነስ ሁሉም ተቋማት በርብርብ ሊሰራ እንደሚገባ አሳስቧል፡፡

ህገ-ወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎች ከዚህ ድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ያሳሰበው ኤምባሲ በቀጣይ መንግስት እነዚህ ግለሰቦች ላይ ጠንካራ እርምጃ የሚወስድ መሆኑን መግለጹን ከኤምባሲው የተገኘ መረጃ ያመላክታል።

Walta Tv ዋልታ ቲቪ

01 Oct, 17:07


ኢትዮጵያ በካርቱም የተባበሩት አረብ ኤሜሬቶች አምባሳደር መኖሪያ ቤት ላይ የደረሰውን ጥቃት አወገዘች

መስከረም 21/2017 (አዲስ ዋልታ) ኢትዮጵያ በሱዳን ካርቱም በሚገኘው የተባበሩት አረብ ኤሜሬቶች አምባሳደር መኖሪያ ቤት ላይ የተፈፀመውን ጥቃት እንደምታወግዝ አስታወቀች፡፡

ኢትዮጵያ በሱዳን ያሉ ሁሉም ወገኖች ዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲያዊ ደንቦችን እንዲያከብሩና የዲፕሎማቲክ ሰራተኞችን እና ተቋማትን አደጋ ላይ ከሚጥል ድርጊት እንዲቆጠቡ ጥሪ አቅርባለች፡፡

Walta Tv ዋልታ ቲቪ

01 Oct, 09:08


የሚኒስትሮች ምክር ቤት ባካሄደው 39ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ

መስከረም 21/2017 (አዲስ ዋልታ) የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 39ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ፡፡

በ39ኛ መደበኛ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባ ላይ የተላለፉ ውሳኔዎች የሚከተሉት ናቸው፡-

1. በቅድሚያ ምክር ቤቱ የተወያየው ብሔራዊ የመካከለኛ ዘመን 2017-2020 የገቢ ስትራቴጂ ላይ ነው፡፡ ስትራቴጂው የታክስ ሥርዓቱን ለማዘመን እና ለግል ኢንቨስትመንቱ ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር የታለመ ሲሆን አጠቃላይ የታክስ ፖሊሲዎችን እና አስተዳደራዊ ሪፎርሞችን እንዲሁም ማሻሻያዎችን ለመተግበር የሚያስችል ነው፡፡ ሰትራቴጂው ከ10 ዓመቱ የልማት ዕቅድ ጋር የተጣጣመ እንዲሆን ተደርጎ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በስትራቴጂው ላይ በዝርዝር ከተወያየበት በኋላ በምክር ቤቱ ውሳኔ ካገኘበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡

Walta Tv ዋልታ ቲቪ

26 Sep, 09:35


ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለመስቀል በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

መስከረም 16/2013(አዲስ ዋልታ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለመስቀል በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

የጠቅላይ ሚኒስትሩ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት እንደሚከተለው ቀርቧል።

ለ2017 ዓመት የመስቀል በዓል እንኳን አደረሳችሁ

የመስቀል በዓል የሕልም ጉልበት የታየበት በዓል ነው፡፡

ንግሥት ዕሌኒ መስቀሉን ለማውጣት ያለመችው ምንም አመቺ ነገር ባልነበረበት ጊዜ ነው፡፡ ዙሪያዋ ጨለማ ነበር፡፡ መንገዶች ሁሉ ዝግ ነበሩ፡፡ ነገሮች ሁሉ አስቸጋሪ ነበሩ፡፡ ማንም በማያስበው ጊዜ፤ አይቻልም አይሞከርም በሚባልበት ወቅት፤ አንድ ቀን፤ ፈጣሪዋ ሲፈቅድ፤ መስቀሉን ከተቀበረበት ሥፍራ ለማውጣት ሕልም ነበራት፡፡

ሕልሟ እንዲሳካ ሠራች፤ ታገለች፡፡ ጨለማውን እየገፈፈች፤ አስቸጋሪውን ጎዳና እየጠረገች፤ ከውስብስብ ችግሮች ጋር እየተጋፈጠች ወደ ፊት ተጓዘች፡፡ በመጨረሻም ኢየሩሳሌም ተሻግራ፣ መስቀሉን ከተቀበረበት ሥፍራ ለማውጣት በቃች፡፡ ሕልሟ እውን ሆነ፡፡ ታሪክን ቀየረች፡፡ ልዕልናን ዐወጀች፡፡ ደመራ ለሚታገል፤ ተስፋ ለማይቆርጥና እስከ መጨረሻው ለሚጸና ሰው ሕልሙ አንድ ቀን እውን እንደሚሆን የሚያሳይ ትእምርት ነው፡፡

Walta Tv ዋልታ ቲቪ

26 Sep, 06:30


በ አንድ ሳምንት ብቻ ከ 12M በላይ ሰው የጀመረው Airdrop_Moonbix

ለመጀመር👉https://t.me/Binance_Moonbix_bot/start?startapp=ref_652246848&startApp=ref_652246848

Walta Tv ዋልታ ቲቪ

23 Sep, 08:21


የከፈቾ ብሔር ዘመን መለወጫ በዓል "ማሽቃሮ" በድምቀት እየተከበረ ነው

መስከረም 13/2017(አዲስ ዋልታ) የከፈቾ ብሔር ዘመን መለወጫ በዓል "ማሽቃሮ" በተለያዩ ዝግጅቶች በቦንጋ ከተማ እየተከበረ ይገኛል።

“ማሽቃሮ” በካፈቾ ብሔር ዘንድ በታላላቅ ኩነቶች ታጅቦ በድምቀት የሚከበር ከአሮጌው ዓመት ወደ አዲስ ዓመት የሚሸጋገሩበት በዓል ነው።

Walta Tv ዋልታ ቲቪ

23 Sep, 05:39


በ አንድ ሳምንት ብቻ ከ 12M በላይ ሰው የጀመረው Airdrop_Moonbix

ለመጀመር👉https://t.me/Binance_Moonbix_bot/start?startapp=ref_652246848&startApp=ref_652246848

Walta Tv ዋልታ ቲቪ

19 Sep, 14:11


ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢጋድ የቱሪዝም ሻምፒዮን ሆኑ

መስከረም 9/2017(አዲስ ዋልታ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለሚቀጥሉት ሦስት ዓመታት የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) የቱሪዝም ሻምፒዮን ሆነው ተመርጠዋል።

“ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አዲሱ የኢጋድ የቱሪዝም ሻምፒዮን መሆናቸውን ስንገልፅ ኩራት ይሰማናል” ሲል የኢጋድ ጽሕፈት ቤት በኤክስ ገጹ አስፍሯል።

ጽሕፈት ቤቱ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ባለራዕይ መሪነት በቀጠናው ቱሪዝምን ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው በመግለጽ አመራራቸውም በኢጋድ አባል ሀገራት የኢኮኖሚ ዕድገትን ለማምጣት፣ ቅርሶችን እና አካባቢን ለመጠበቅ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያደርጋል ብሏል።

Walta Tv ዋልታ ቲቪ

18 Sep, 17:31


አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከ500 በላይ ውጤት ላመጡ ተማሪዎች ነጻ የትምህርት ዕድል ሰጠ

መስከረም 8/2017 (አዲስ ዋልታ) የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ፈተና ከ500 በላይ ላመጡ 200 ተማሪዎች ነጻ የትምህርት ዕድል መስጠቱን አስታወቀ፡፡

ዩኒቨርሲቲው ራስ ገዝ መሆኑን ተከትሎ ተማሪዎችን በራሱ የቅበላ ሥርዓት ተቀብሎ ለማስተማር ምዝገባ እያከናወነ መሆኑንም ገልጿል፡፡

በቅርቡም ያዘጋጀውን የተማሪዎች መግቢያ ፈተና እንደሚሰጥና ብቃትን፣ ብዝኃነትንና ፍትሐዊነትን ማዕከል አድርጎ እንደሚቀበል አስታውቋል፡፡

ከዚሁ ጋር በተያያዘ በ2016 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ወስደው 500 እና ከዚያ በላይ ያዝመዘገቡ 200 ተማሪዎችን በውድድር ነፃ የትምህርት እድል ከመኝታና የካፌ አገልግሎት ጋር እንደሚሰጥ አመልክቷል፡፡

ይህም ዩኒቨርሲቲው ብቃትና ተሰጥዖ ያላቸው ተማሪዎች መዳረሻ ለመሆን ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይ ከዩኒቨርሲቲው ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

Walta Tv ዋልታ ቲቪ

18 Sep, 12:04


🗼Binance ያስጀመረው አድስ Airdrop
ሳይዘገይ ቶሎ ጀምሩት
👎👎👎👎👎👎👎
https://t.me/Binance_Moonbix_bot/start?startapp=ref_652246848&startApp=ref_652246848