የእመቤታችን አንድምታ ወዳሴ ቅዳሴ @uraman4u12 Channel on Telegram

የእመቤታችን አንድምታ ወዳሴ ቅዳሴ

@uraman4u12


በዚሕ ቻናል የእመቤታችን ዉዳሴዋ ንባቡና ትርጓሜዉ በአንድምታ ይቀረባል። ከኛ የሚጠበቀዉ መማር ብቻ ነዉ። አምላክ ከኛ ጋ ይሑን የእመቤታችን አማላጅነት አይለየን።

ሐሳብ አስተያየት
👇👇👇👇👇👇
@woladite11

የእመቤታችን አንድምታ ወዳሴ ቅዳሴ (Amharic)

የእመቤታችን አንድምታ ወዳሴ ቅዳሴ ተለዋዋጭ ለብቻዎች እና አዳዲሆዎች የመንገድ አልባ እየተነሳ እያሰራ ይዘርበኛል። የነጻ ትክበትና የአዳዲስ ዘዴዎች በአሉላዩ ቢያበረው ዜናዊ ቤተ እርሃም ለሚዘን በዚህ ቡድን ተመሳሳይ ቤተ እርሃም እንዲሆን አስተማሪ እንዲሆኑ አሰራሉ። ከእናንተ ወጣቶች ጋር የእመቤታችን አንድምታ ወዳሴ ቅዳሴ የታዘዘን እርሃም የሙሉ ትኩብት በዚህ አንድምታ ቅዳሴ ተመራጭ ያደረጋችሁት የአቅም ቆይታ ነው።

የእመቤታችን አንድምታ ወዳሴ ቅዳሴ

29 Jan, 04:24


ተወዳጆች

ጥበበኛው ሰሎሞን

ተንሥኢ ወንዒ” የነፍሴ ደስታ የኾንሽ ውድ እናቴ ሆይ ተነሥተሽ ወደ እኔ ነዪ (መኃ ፪፥፲) ብሏታል።

ቅዱስ ያሬድም

«ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ ሞታ ለማርያም የዐጽብ ለኲሉ፤ ሞት ለማናቸውም ሰው ሁሉ የተገባ ነው የማርያም ሞት ግን ሁሉን ያስደንቃል» በማለት ገልጾታል።

አስተርእዮ ማለት መታየት፣ መገለጥ ማለት ነው። ቃሉ አስተርአየ ታየ፣ ተገለጠ ከሚለው የግዕዝ ግሥ የተገኘ ነው። ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በገባው ቃል ኪዳን መሠረት በሥጋ የተገለጠበት(የታየበት) ፣ አንድነት ሦስትነቱም የተገለጠበት ወቅት በመሆኑ ከልደት በዓል እስከ ጥር መጨረሻ በሙሉ ዘመነ አስተርእዮ በመባል ይታወቃል።


የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ሞትና ትንሣኤ በነገረ ማርያም አበው እንደሚያስረዱት ዕረፍቷ በጥር ፳፩ እሑድ ነው ። አባቶቻችን በጾመ ፍልሰታ ውዳሴ ማርያም ቅዳሴ ማርያም ሲተረጉሙ የእረፍቷን ነገር እንዲህ ብለው ይተርካሉ።

የእረፍቷስ ነገር እንደምን ነው ቢሉ ስድሳ አራት ዓመት በዚህ ዓለም ኖራ ጥር ፳፩ በእሑድ ቀን ጌታ እልፍ አዕላፋት መላእክቱን አስከትሎ መጥቶ እናቴ ሆይ ከዚህ ዓለም ድካም ላሳርፍሽ መጣሁ አላት። ልጄ ሰማይና ምድር የማይወስኑህ ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን በማህጸኔ ተሸክሜ በድንግልና ወልጄህ እሞታለሁን? አለችው። በሲዖል የሚሰቃዩ ነፍሳትን አሳይቶ እናቴ ሆይ ሞትሽ ለእነዚህ ቤዛ ይሆንላቸዋል አላት። እሊህን ከማርክልኝስ ይሁን አለችው። ቅድስት ሥጋዋን ከቅዱስ ነፍሷ ለይቶ በቃለ አቅርንት በዝማሬ መላእክት አሳረጋት። ደቀመዛሙርቱንም ከያሉበት በደመና ጠቅሶ ካለችበት አድርሶ እመቤታችሁን ስጋዋን በክብር አሳርፉ አላቸው። ሐዋርያት በአጎበር አድርገው ወደ ጌቴሰማኒ ይዘው ሲሄዱ አይሁድ ቀድሞ ልጇን ተነሳ ዐረገ እያሉ ሲያውኩን ይኖራሉ አሁን ደግሞ እሷን ተነሳች ዐረገች እያሉ ሊያውኩን አይደለምን በእሳት እናቃጥላታለን ብለው ተነሱ። ታውፋንያ የሚባል አይሁዳዊ ተራምዶ አጎበሩን ጨበጠው። መልአክ መጥቶ በሰይፍ ሁለት እጁን ቀጣው ከአጎበሩ ተንጠልጥሎ ቀረ። በድያለሁ ማሪኝ ብሎ ቢማጸናት እጁ ተመልሶለታል። ከዚህ በኋላ ዮሐንስን ጨምሮ በደመና ነጥቆ ከገነት አግብቶ ከዕፀ ሕይወት ሥር አኖራት።

ቅዱስ ዮሐንስን እንደምን ሆነች አሉት ከገነት ከዕፀ ሕይወት ሥር አለች አላቸው ቅዱስ ዮሐንስ አይቶ እኛ ሳናይ ብለው በነሐሴ መባቻ ጾም ጀመሩ ሁለት ሱባዔ ሲፈጸምም እሑድ አምጥቶ ሰጥቷቸው ቀብረዋታል በሶስተኛው ቀን ማክሰኞ “ከመ ትንሳኤ ወልዳ” እንደ ልጇ ተነሥታለች።

የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት አይለየን❣️

የእመቤታችን አንድምታ ወዳሴ ቅዳሴ

26 Jan, 17:25


ድንግል ሆይ

የኔ ምሕረት በልጅሽ ዘንድ ስላንቺ አይደነቅም 

ስለ ስምሽም

 የኔ ይቅር መባል በልጅሽ ዘንድ አይደነቅም 

ስለ ጸሎትሽም 

የኔን ኃጢአት ማቀለል በልጅሽ ዘንድ አይደነቅም፡፡

ስለ ልመናሽም

 የኔን ዕዳ በደል ማቅለል በልጅሽ ዘንድ አይደነቅም 

ባንቺ እታመናለሁ፡፡

 በዚህ ዓለም

ከፀብ ከክርክር ከሞት ታድኝኝ ዘንድ 
በሚመጣውም ዓለም
ማዕበል ሞገድ ከሚፈላው የእሳት ባሕር ታድኝኝ ዘንድ፡፡


የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት አይለየን❣️

የእመቤታችን አንድምታ ወዳሴ ቅዳሴ

26 Jan, 03:08


ድንግል ሆይ

ሐሰተኛ ከመሆን ሰውንም ከሰው ከማጣላት አድኝኝ፡፡
ዳዊት እንዲህ ብሏልና፡፡ ሐሰት የዓመፅ ሁሉ ራስ ነው፡፡

ድንግል ሆይ

ከመሰሰን ኃጢአት አድኝኝ በነገሥት መጽሐፍ እንዲህ የሚል ተጽፏልና፡፡ (መዝ ፳፯፣ ፲፪) (ዘፀአ ፳፣ ፲፮)ሴሰኝነት ታላቅ ኃጢአት ነውና፡፡

ድንግል ሆይ

ከነገረ ዘርቅ ዋዛ ፈዛዛውን ከንቱውንም ነገር ሁሉ ከመናገር ሠውሪኝ በወንጌል እንዲህ ይላልና ዋዛ ፈዛዛውን ከንቱውንም ነገር የሚናገር ሁሉ ኃጥእ ተብሎ ይፈረድበታል፡፡ ከነገርህም የተነሣ ትጸድቃለህና ከነገርህም የተነሣ ትኮነናለህ፡፡ (ዘፀአ ፳፣ ፲፬) (ማቴ ፲፪፣ ፴፯)

ድንግል ሆይ

ከሐዋርያት ትምህርት ከመውጣት ከማፋለስ አድኝኝ ልጅሽ እንዲህ ብሏቸዋልና እናንተን የሰማ እኔን የሰማ ነው፡፡ እናንተን እምቢ ያለ እኔን እምቢ ያለ ነው፡፡ የላከኝንም እምቢ አለ፡፡ (ማቴ ፲፣ ፵ ም ፲፰፣ ፭ ሉቃ ፲፣ ፲፮)

ጳውሎስ ደግሞ

እንዲህ አለ እናንተስ የኛን መንገድ ተከተሉ እኛም ካስተማርናቸሁ ትምህርት ሌላ ያስተማራችሁ ቢኖር የሰማይ መላክ ቢሆን ውጉዝ ይሁን፡፡ (ገላ ፩፣ ፰) ፲. ደግሞ እንዲህ አለ እኛ ካስተማርናችሁ ሌላ ትምህርት ብትማሩ የተወገዛችሁ ሁኑ፡፡ (ገላትያ ፩፣ ፱)

የቅድስት ድንግል ማርያም❣️ አማላጅነት አይለየን

የእመቤታችን አንድምታ ወዳሴ ቅዳሴ

23 Jan, 15:50


ጸጋ ክብርን የተመላሽ ድንግል ሆይ 

ከመግፋት ከመገፋት አድኝኝ፡፡

ቅድስና የተመላሽ ድንግል ሆይ 

ከመበደል ሌላውንም ከመበደል አድኝኝ፡፡ ከደም አፍሳሽ አድኝኝ፡፡ እኔም ደግሞ የሌላውን ደም ከማፍሰስ ሠውሪኝ፡፡

 የተድላ መፍሰሻ ድንግል ሆይ

 ከሽንገላ አድኝኝ፡፡ 
ከሸንጋይም ደግሞ ሠውሪኝ፡፡

የምስጋና መፍሰሻ ድንግል ሆይ

 ከሽሙጥ ከስድብ ከሚያስሽሟጥጥና 
ከሚሰድብ ደግሞ ሠውሪኝ፡፡

የባለጸግነትና የክብር መፍሰሻ ድንግል ሆይ

 ሰውን ከሰው ከማጣላት አድኝኝ፡፡ ሰውን ከሰው ከሚያጣላ ሐሰተኛ ደግሞ ሰውሪኝ 

የሕይወት የመድኃኒት ምንጭ ሆይ 

ከቂምና ከቅናት አድኝኝ 
ከቂመኛ ከቀናተኛ ደግሞ አድኝኝ፡፡

 የፈውስ መቅጃ የበረከት አዘቅት ድንግል ሆይ 

ከፀብ ከክርክር አድኝኝ፡፡
 ከሚጣላና ከሚከራከር አድኝኝ፡፡ እሳት የሚለብሱ ኪሩቤልና ሱራፌል
 በመብረቅ ክንፍ የሚጋርዱሽ 

የንጉሠ ነገሥት ማደሪያ የምትሆን የብርሃን ድንኳን ሆይ፡፡ በሕይወት በመድኃኒት ጋሻ ጋርጅኝ 
ከአጋንንት ፍላፃ እንድድን፡፡

የእመቤታችን አንድምታ ወዳሴ ቅዳሴ

08 Jan, 11:31


🛐 ጸሎት 📖
"""""""'''''''''""""""""''


☑️ ዘር ነውና መከር አለው
☑️ እንባ ነውና ሳቅ አለው
☑️ ትግል ነውና ድል አለው
☑️ ጩከት ነውና መልስ አለው
☑️ መተንፈስ ነውና ሕይወት አለው
☑️ መራቆት ነውና ፀጋ አለው
☑️ ንግግር ነውና ማስተዋል አለው
☑️ መንበርከአ ነውና ማሸነፍ አለው



                👇👇
         ◤◢◤◢◤◢◣◥◣◥◣◥
        █   𝐉𝐎𝐈𝐍 𝐔𝐒 ➲      █ 
        ◣◥◣◥◣◥◤◢◤◢◤◢

የእመቤታችን አንድምታ ወዳሴ ቅዳሴ

08 Jan, 09:03


▶️ Open የሚለውን ንኩ የፈለጋቹትን 📕ኦርቶዶክስሳዊ 📕ቁም ነገር ታገኙበታላችሁ።

1.ጉዞ ወደ እግዚአብሔር.....Open

2.ሕማማት......................Open

3.ቅዱስ አትናቲዎስ...........Open

4.አባቶችህን እወቅ...........Open

5.ሃይማኖተ አበው............Open

7.ትንሿ ቤተክርስቲያን.......Open

8.የብርሃን እናት...............Open

9.ማህሌተ ፅጌ................Open

10.የኤፍራጥስ ወንዝ.........Open

11.ተግባራዊ ክርስትና........Open

የእመቤታችን አንድምታ ወዳሴ ቅዳሴ

07 Jan, 01:36


እንኳን ለብርሃነ ልደቱ አደረሳችሁ…!

"…ልዩ ከሆነች ድንግል ማርያም ይህ የአምላክ መወለድ ምን ይደንቅ? ቃልን ወሰነችው። ልደቱንም ዘር አልቀደመውም። በመወለዱም ድንግልናዋን አልለወጠም። ቃል ከአብ ያለ ድካም ወጣ። ከድንግልም ያለ ህማም ተወለደ። ሰብአሰገል ሰገዱለት። አምላክ ነውና ዕጣን አመጡለት። ንጉሥም ነውና ወርቅ አመጡለት። ስለኛ በፈቃዱ ለተቀበለው መዳኛችን ለሆነው ሞቱም ከርቤ አመጡለት። እርሱ ቸርና ሰውን ወዳጅ የሆነ አንድ እርሱ ብቻ ነው። ቅድስት ሆይ ለምኚልን።

"…ቤዛ ይስሐቅ በግዕ ከኅቱም ዕፀ ሳቤቅ እንደተገኘ፤ ለእስራኤልም በበረሀ ውስጥ ከኅቱም አለት ውኃ እንደ ፈለቀ፤ የተደነቀች የአሮን በትርም እንደለመለመችና እንደ አፈራች፤ በሶምሶንም እጅ ውስጥ ከአህያ መንጋጋ አጥንት ውኃ እንደ ፈሰሰ፤ እንዲሁ የጌታችን ልደት በኅቱም ድንግልና ሆነ። በዕፀ ጳጦስ ውስጥ እሳት እንደ ነደደች ዕፂቱም እንዳልተቃጠለች እንዲሁ የመለኮቱ እሳት ድንግልን አላቃጠላትም። ለእርሱም ከቸር አባቱ ከማሕየዊ መንፈስ ቅዱስ ጋር ጌትነት ክብር ምስጋና ሰጊድ ከርሱ ጋር በትክክልነት ይገባል ለዘላለሙ አሜን።

"…በዓለ ጌናን ስናከብር በኀዘን በመከራ፣ በጭንቅ፣ በራብና በጥም፣ በሰቀቀን፣ በስደት፣ በወኅኒ ቤት፣ በአልጋ ቁራኛ በደዌ ደኛ፣ በፅኑ ህመም ተይዘው፣ በየቤቱ፣ በየጎዳናው፣ በየሆስፒታሉና በፀበል ስፍራዎች ሁሉ ያሉትን፣ ከሞቀ ቤትና ንብረታቸው ተፈናቅለው በየጥሻው የወደቁትን በማሰብ፣ በመንከባከብ፣ በመጠየቅ፣ በመጎብኘትና ማዕድ በማጋራት ይሁን። ሀገራችን ኢትዮጵያንና ጎረቤቶቿን፣ መላውንም ዓለም ሁሉ ሰላማዊው ኢየሱስ ክርስቶስ ሰላም ያድርግልን። አሜን።

"…እንኳን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለአምላካችንና ለፈጣሪያችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል አደረሰን

የእመቤታችን አንድምታ ወዳሴ ቅዳሴ

18 Dec, 08:58


አማላጂቱ ሆይ

በጭንቅ፣ በኃጢያትና በበደል ውስጥ ላለን እኛ
ምልጃሽን እንፈልጋለንና ይቅር ባይ ተወዳጅ ከሆነው ልጅሽ
ከኢየሱስ ክርስቶስ ሰላሙን፣ ይቅርታውንና ምህረቱን
ይልክልን ዘንድ ለምኝልን አሜን 👏

የእመቤታችን አንድምታ ወዳሴ ቅዳሴ

17 Dec, 20:24


ለሰው ልጆች ሁሉ ታላቅ ስጦታ የሆነውን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን እንድትወልድ ከሴቶች ሁሉ በላይ ተመረጠች።
ቅድስተ ቅዱሳን እናታችን፣ በአክብሮት ቴዎቶኮስ ተብላ ትጠራለች፣ አምላክ የተሸከመች፣ እንዲሁም ከፍ ያለ ክብር ያለው ፓናጊያ የሚል ስያሜ አግኝታለች።
"ፓናጊያ" የግሪክ ቃል ሲሆን ትርጉሙም "ሁሉ-ቅዱስ" ወይም "እጅግ ቅዱስ" ማለት ነው። የሰው ልጆች አዳኝ ኢየሱስ ክርስቶስን የወለደች ቅድስተ ቅዱሳን እናታችን የአምላክ እናት በመሆን ወደር የለሽ ንጽህና እና ቅድስናን የሚያመለክት በመሆኑ የተሰጠ ስያሜ ነው። ቃሉ በእምነት ያላትን ከፍ ያለ ቦታ፣ ከቅዱሳን ሁሉ በላይ ያጎላል፣ እና በድነት ታሪክ ውስጥ ያላትን ልዩ ሚና ያጎላል። ቅድስተ ቅዱሳን እናታችንን በጥልቅ አክብሮት እናከብራታለን፣ እርሷን እንደ እምነት፣ ትህትና እና ታማኝነት የመጨረሻ አርአያ አድርገን እንገነዘባለን። "ፓናጊያ" በኦርቶዶክስ ውስጥ ማእከላዊ ቦታዋን ያንፀባርቃል, ከሁሉም ሴቶች መካከል በጣም የተባረከች እንደሆነች ያከብራታል.


የእመቤታችን አንድምታ ወዳሴ ቅዳሴ

15 Dec, 05:50


ድንግል ሆይ

አንቺ የተባረክሽ ዕፅ ነሽ የሕይወትና የደህነት ዕፅ ነሽ፤



በገነት ውስጥ ባለው ዕፅ ሕይወት ፈንታ
በዚህ ዓለም የሕይወት ዕፅ ሆነሽ፤
ፍሬሽም የሕይወት ፍሬ ነው::
በሚወዱት (በሚያውቁት) በዓለም ሰዎች ዘንድ የሚሽት
መልካም መዓዛ ያለው አበባ ካንቺ ታየ፡፡

ይኸውም ከርቤ፣ሚዓ፤ ስሊክ የተባሉ ሽቶች በልብሶችሽ ላይ አሉ፡፡ ብሎ በበገና ነቢዩ ዳዊት ትንቢት የተናገረልሽ ነው::


ቅድስት ሆይ ልጅሽ ይቅርታውን ያድለን ዘንድ ለምኝልን🙏

የእመቤታችን አንድምታ ወዳሴ ቅዳሴ

12 Dec, 10:41


"ድንግል ሆይ

አንገታቸውን እንደሚያገዝፉ እንደ ዕብራውያን ሴቶች ልጆች በዋዛ ያደግሽ አይደለም፤ በንጽሕና በቅድስና በቤተ መቅደስ ኖርሽ እንጂ፤

ድንግል ሆይ

ምድራዊ ኅብስትን የተመገብሽ አይደለም፤ ከሰማየ ሰማያት የበሰለ ሰማያዊ ኅብስትን ነው እንጂ፤

ድንግል ሆይ

ምድራዊ መጠጥን የጠጣሽ አይደለም፤ ከሰማየ ሰማያት የተቀዳ ሰማያዊ መጠጥን ነው እንጂ፤

ድንግል ሆይ

ከአንቺ አስቀድሞ ከአንቺም በኋላ እንዳሉ ሴቶች መተዳደፍን የምታውቂ አይደለም፤ በንጽሕና በቅድስና ያጌጥሽ ነሽ እንጂ፤

ድንግል ሆይ

የሚያታልሉ ጐልማሶች ያረጋጉሽ አይደለም የሰማይ መላእክት ጐበኙሽ እንጂ እንደተነገረ ካህናትና የካህናት አለቆች አመሰገኑሽ እንጂ....."

(አባ ሕርያቆስ - ቅዳሴ ማርያም)

የእመቤታችን አንድምታ ወዳሴ ቅዳሴ

11 Dec, 16:36


የዓለም ሁሉ መመኪያ

ድንግል እናት ሆይ


ከሚያሰጥመው ካመፀኛ አፍ በደምም ከሰከረች ምላስ አድኝኝ፡፡

መንፈሳዊት መርከብ ሆይ ድንግልናዊት መፆር ሆይ

ከክፉ ዘመን መከራ አድኝኝ፡፡

የሁላችን መመኪያ የመድኃኒት ሽቱ ብልቃጥ ያለ ርኩሰት ሙሽራ ሆይ

ከቀን ወራሪ ከሌሊት ሰባሪ አድኝኝ፡፡

የእመብርሃን አማላጅነት አይለየን🙏

የእመቤታችን አንድምታ ወዳሴ ቅዳሴ

10 Dec, 16:31


እመብርሃን ሆይ

ደስ ብሰኝ ባንቺ ደስ እሰኛለሁ፡፡ ባዝንም ባአንቺ እጽናናለሁ፡፡ መከራና ችግርም ቢያገኘኝ ወዳንቺ እጮሃለሁ፡፡ያመፀኛም ምላስ ቢያስከፋኝ ወዳንቺ ፊት እማለላለሁ፡፡
ሰወነቴም የወደደችው ነገር ቢኖር አንቺን እለምናለሁ፡፡ በመታመን የሻትሁትንና የተመኘሁትንም ባንቺ አገኛለሁ ።
መታመን ያድናል ሃይማኖትም ያስቀናል መታመን ያነጻል፡፡ ሃይማኖትም ያራቅቃል መታመን ተስፋ ያደርጋል ሃይማኖትም ይሰጣል፡፡ መታመን ይጀምራል ሃይማኖት ይፈጽማል፡፡

የ ቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት አይለየን🙏

የእመቤታችን አንድምታ ወዳሴ ቅዳሴ

10 Dec, 03:04


ተወዳጆች

አለም ሁሉ ተደምሮ
የአንዷን የፀጉሯን ዘላላ ያህል ክብር የለውም 
የአንዷን የፀጉሯን ዘላላ
አሁን ስለ እመቤታችን ስለምኗ ትናገራላችሁ ?
ሰው ስለምኗ ይናገራል ?
ስለ እናትነቷ ቢናገር  ድንግል ትሆንበታለች
ስለ ድንግልናዋ ቢናገር እናት ትሆንበታለች
እናትነቷን ብቻ ልናገር ቢል   አይሆንለትም
አምላክን መውለድ እንደምን ያለ ነገር ነው
ይሄ እስከዛሬ ድረስ አይገባንም
ከገባንማ ነገሩም ቀላል ነው ማለት ነው ።

የእመቤታችን አንድምታ ወዳሴ ቅዳሴ

08 Dec, 11:39


ተወዳጆች

የድንግል ማርያም እራስ ግን እግዚአብሔር ነው
ህሊናዋ ውስጥ ከእግዚአብሔር ውጭ አስባ አታውቅም
ስለዚህ ምን ትባላለች ? የእግዚአብሔር ከተማ ትባላለች

የእመቤታችን አንድምታ ወዳሴ ቅዳሴ

08 Dec, 09:29


አውቀዋለሁ ደጅሽን የእረፍት ቦታየን
ፅኑ ሰላም ፀጥታ ማግኛየን
የት እሄዳለሁ አላልም ሲከፋኝ
ኪዳነ ምህረት አንቺ እያለሽልኝ

የእመቤታችን አንድምታ ወዳሴ ቅዳሴ

07 Dec, 08:41


📍የመስቀል ምልክቱን ንኩት እና መንፈሳዊ እና ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶችን ምክሮችን የያዘ የቴሌግራም ቻናል ይቀላቀሉ ።
👇👇
እግዚአብሔር በአንድም በሌላም መንገድ ያስተምራል። ኑ አብረን እንማር።👇👇

🌑🌑███🌑🌑
🌑🌑███🌑🌑
█████████
█████████
🌑🌑███🌑🌑
🌑🌑███🌑🌑
🌑🌑███🌑🌑
🌑🌑███🌑🌑
🌑🌑███🌑🌑

የእመቤታችን አንድምታ ወዳሴ ቅዳሴ

05 Dec, 10:03


በዚህ አለም ላይ

ተወዳጆች ሆይ

የእመቤታችን ፍቅር❣️

እንደውሃ የፈሰሰለት ሰው የታደለ ነው።

አባ ጊዮርጊስ ለዚህ ነው

ፍቅርሽ እንደ ወይን እና እንደ ውሃ በልቤ ውስጥ ተቀላቅሏል
ወይን እና ውሃ ከተቀላቀለ በኋላ
ይሄ ወይን ነው ይሄ ውሃ ነው ማለት አይቻልም
እኔን ከማርያም ፍቅር ለይቶ ማሳየት የሚችል የለም
እንዴት አድርጎ ቢወዳት ነው እናንተ
እንዴት አድርጌ ላመስግንሽ ይሆን አለ

ምን ላድርግ ?

ፀጉሬ እንኳን አፍ አውጥቶ ቢዘምርልሽ አይበቃሽም ይላል
ስለዚህ ዝም ብየ ቡርክት ቡርክት ቡርክት እልሻለሁ ይላል።

አምላክ እናቴ ያላትን እኔ እናቴ ላልላት ነው እንዴ
ፈጣሪ እናቴ ካላት እኔማ ሎሌሽ ነኝ ብላት
ኧረ! እናትም የሆነችን በቸርነቷ ነው

አንደኛ

የእግዚአብሔር ቸርነት ይገርማል
የእሱን እናት እኛም እናታችን ስንል
ለነገሩ ፈጣሪ ቅናት የለበት አይደል
እንጂማ የአምላክን እናት
እናቴ ማለትኮ እራሱ ትዕቢት እኮ ነው
ትዕቢት ነው አዛኘን

ሁለተኛ ደግሞ

የሷም ደግነት

እኔ አንተን ልጄ ባልኩበት
ዘማያውያንን ሁሉ ልጄ አልልም አለማለቷ
የረከሱት ሁሉ እናቴ ማርያም አይሉኝም
እንዳይሉኝ ከልክላቸው አለማለቷ

የምድር ንግስት ብትሆን እኮ
ዞርበል ያንተ እናት አይደለሁም ትለን ነበር።

እሷ ግን

ቸር እናት ስለሆነች

የመሀሪው እናት ፣ እርህርሂት ማርያም
የውሻ ያዘነች ስለሆነች እናታችን ስንላት አናፍርም

እናትነቷ ሲበዛብን እንጂ

የፈጣሪን እናት እናት እንድትሆነን የፈቀደልን እግዚአብሔር
ስሙ የተመሰገነ ይሁን አሜን አሜን አሜን 🙏


ርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን❣️

የእመቤታችን አንድምታ ወዳሴ ቅዳሴ

29 Nov, 17:36


ድንግል ሆይ

የሚበላውን ያፈራሽልን የሚጠጣውን ያስገኘ ሽልን ።

ወዮ ከአንቺ የተገኘ ኅብስት

በማመን ከርሱ ለሚቀበሉ
ሕይወትንና ደኅንነትን የሚሰጥ ነው ።


ወዮ ከአንቺ የተገኘ ኅብስት

በማመን ከርሱ ለማይቀበሉ ሰዎች

የማይላመጥ ጽኑ ነው
ይኸውም ኃያል የሚሆን የአድማስ ደንጊያ ነው ።


ወዮ ከአንቺ የተገኘ ጽዋ በማመን

ከርሱ ለሚጠጡ ሰዎች
ጥበብን የሚገልጽ ሕይወትንም የሚሰጥ ነው ።


ወዮ ከአንቺ የተገኘ ጽዋ በማመን

ከርሱ ለማይጠጡ ሰዎች
የሚያሰክርና የሚያፍገመግም
የሚጥልና ኃጢአትን ስለሚያስተው ፈንታ
ኃጢአትን የሚጨምር ነው ።


አሁንም ላንተ ምስጋና ይገባሃል ።

ለመንግሥትህም ምስጋና ይገባል እያልን እናመስግነው
ከንጹሕ ዕጣን ጋራ ምስጋናን እናቀርብልሃለን ።

ቅዳሴ ማርያም❣️

የእመቤታችን አንድምታ ወዳሴ ቅዳሴ

24 Nov, 09:56


ተወዳጆች ሆይ

ሹመትም አይኑራችሁ እውቀትም አይኑራችሁ
ጤናም አይኑራችሁ ሀብትም አይኑራችሁ
ማርያም ስላለችልን ብቻ ደስ ሊለን ይገባል።
እሷ ስላለችን ይበቃናል ።

የ አክል ሐይማኖት ዘአልቦ ጥልቀት
ወእምነት
በ ቅድስት ድንግል ከመ
ይዕቲ ወላዲተ አምላክ

ዘአልቦ ጥልቀት አለ

ጥርጥር የሌለበት ሐይማኖት ለምንም ነገር ይበቃል።
ማርያም ወላዲተ አምላክ ናት ብሎ ማመን ለሁሉም ይበቃል

ለልብስ ይበቃል ክርስቶስን እንለብሳለን
ለምግብ ይበቃል የህይወት እንጀራ ልጇን እንበላለን።
ለጥበቃ ይበቃል መልካም እረኛ ልጅ አላትና በእሷ ይጠብቀናል ።
ስለዚህ ምንም የሚጎልብን ነገር የለም
ሰው ማርያምን ከወደደ የሚያጣው ነገር የለም ።

መለመን ያለብን

የእናትህን ፍቅር ጨምርልን ብለን ነው
መፀለይ ካለብን እሷን ነው
በኃጢአት የመረረው ህይወታችን ሊጣፍጥ የሚችለው
ጥዕምተ ስም ማርያም በልቡናችን ያደረች እንደሆነ ነው

እሷ ስታድርብን

መራራው ንቅል ንቅል ንቅል እያለ ይጠፋል

መራራውን ህይወታችን
መራራውን ኃጢአታችን
በእናቱ በጣፈጠው ሥሟ ነቅሎ ይጣልልን 🙏


ርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን❣️

Share
👇👇👇👇
https://t.me/uraman4u12
https://t.me/uraman4u12
https://t.me/uraman4u12

የእመቤታችን አንድምታ ወዳሴ ቅዳሴ

21 Nov, 12:16


በእንተፍቅረ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ኬንያ
ንስእለኪ ማርያም በሀሌ ሉያ
ኃዘና ስምዒ ወብካያ ለሀገሪትነ ኢትዮጵያ

የእመቤታችን አንድምታ ወዳሴ ቅዳሴ

19 Nov, 05:40


ከ60 second በኋላ ይጠፋል! 🎬 ምን አይነት የኦርቶዶክስ መንፈሳዊ ፊልም መመልከት ይፈልጋሉ?

የእመቤታችን አንድምታ ወዳሴ ቅዳሴ

19 Nov, 04:15


💬 ጥያቄ
=======



💠 አባታችን ያዕቆብ ከእግዚአብሔር ጋር ሲታገል ያደረበት ስፍራ

የእመቤታችን አንድምታ ወዳሴ ቅዳሴ

17 Nov, 06:36


ተወዳጆች

ድንግል ማርያምን የያዘ ሰው የክርስቶስ በግ ነው ።
ምልክት የሌለው የላባ ነው ማለት
ምልክቲቱ ድንግል ማርያም ናትና
ድንግል ማርያም የሌለቻቸው ሰዎች የዲያብሎስ ናቸው ።
የክርስቶስ በጎች አይደሉም አንዱ ምልክታችን መስቀል ነው።
መስቀል የላቸውም አያምኑትም ይክዱታል።

ቅዱስ ጳውሎስ እንዲህ ይላል ።

እኔ ከክርስቶስ መስቀል በቀር በምንም ባንዳች አልመካም

የእመቤታችን አንድምታ ወዳሴ ቅዳሴ

15 Nov, 17:45


የዓለም ሁሉ መድኃኒት የምትሆን ብላቴና እግሯ የተመላለሰበቱን ምድር እስም ዘንድ ማን በከፈለኝ
ይቅርታን የምታሰጥ ብላቴና ጥላዋ ይነካኝ ዘንድ ማን በከፈለኝ የብርሃን ልጅ ወደሄደችበት እከተላት ዘንድ ማን በከፈለኝ የእግሯንም ጫማ እሸከም ዘንድ ማን በከፈለኝ።
                          
  አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ   

የእመቤታችን አንድምታ ወዳሴ ቅዳሴ

10 Nov, 19:44


ሰው ፍለጋ እግሩን የሚያደክም ሰው
ልቡ ይወልቃል እንጂ ሰው አያገኝም
የራስን ልብ እራስን ማስተካከል ነው
ሰውን ከማስተካከል እራስን ማስተካከል
ሰውን ለማስተካከል መድከም በፍፁም አይቻልም
እሚቻለው እራስን ማስተካከል ነው
ተስፋ የቆረጡ ሰዎች ይሄን ሁሉ አልፈው
ከተስፋ መድረስ እንደሚቻል የምታሳይ
ብቸኛዋ የቤተክርስቲያን ተስፋ ምልክት
እመብርሃን ቅድስት ድንግል ማርያም ነች።

እግዚአብሔርን ለያዘ ብቸኝነት የለበትም።


ርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ❤️

የእመቤታችን አንድምታ ወዳሴ ቅዳሴ

10 Nov, 10:32


እመቤታችን በጣም በጣም ችግሮቻችንን ትመለከታለች
ድካም ትረዳለች እናታችን ናት
እመቤታችን ጥቃቅን የሰው ችግር አይሰወራትም
ሁሉን ማየት ትችላለች ለዚህ ነው እርግበየ መደምደሚያየ የምንላት
ለሁሉም የምትበቃ እናት እመቤታቸን ናት
እኔ እናቴ ልታበላኝ ትችላለች ልታድነኝ ግን አትችልም
በነፍሴ ብታሰር ግን ልታስፈታኝ አትችልም
እመቤታችን ለሁሉም ምትብቃ ናት


ርዕሰ ሊቀውንት አባ ገብረ ኪዳን❤️

የእመቤታችን አንድምታ ወዳሴ ቅዳሴ

09 Nov, 14:23


ናሁ ተፈጸመ ተፈጸመ ናሁ ማኀሌተ ጽጌ ሥሙር ተፈጸመ ናሁ/፪/
አስምኪ ቦቱ አስምኪ ቦቱ ንግሥተ ሰማያት/፪/

ተፈጸመ ናሁ #ማኅሌተ_ጽጌ_ሥሙር፥ አስምኪ ቦቱ ንግሥተ ሰማያት ወምድር፥ ከመ በሕጽንኪ ያሰምክ ፍቁር፡፡” — “ንጹሕ የተዓምርሽ ቀስት (5 ቀስተ ደመና የማርያም መቀነት) እንደ ብር ገንቦ ጌጥ፥ በአረንጓዴ ቢጫና ቀይ ዐይነት በወርቅ አምሳል የተሠራ ነው፥ የሰማይና የምድር #ንግሥት ኾይ! የተወደደ የጽጌ ምስጋና ተፈጽሟልና፥ የቀጣዩን ዓመት ምስጋና በሰላም አቅርቢልን።”


እንኳን አደረሰን አደረሳችሁ🙏

የእመቤታችን አንድምታ ወዳሴ ቅዳሴ

08 Nov, 01:28


መላእክት ሁሉ ይዘምሩላታል

በሰማያት ኵሎሙ መላእክት ይኬልልዋ… ወበምድርኒ ኵሎሙ ቅዱሳን ይቄድስዋ... እስመ ወለደት ወልደ ዘበኵራ ያፈቅርዋ እንዘ ንጽሕት በድንግልና… አልባቲ ሙስና ፤ ❞

ትርጉም ፦ በሰማያት መላእክት ሁሉ ይዘምሩላታል ፣ … በምድርም ቅዱሳን ሁሉ ያመሰግኗታል ፣ … በድንግልናዋ ንጽሕት ስትሆን የበኵር ልጇን ወልድን ስለወለደች ይወዷታልና ፣ … እሷ ርኵሰት የሌለባት ናት"



[   ቅዱስ ያሬድ   ]

የእመቤታችን አንድምታ ወዳሴ ቅዳሴ

31 Oct, 08:20


የጅማ ዩኒቨርሲቲ ተማሪ ወይም ልጆች ወይም የምትሰሩ አዋሩኝ ፕሊስ እባካችሁ.

የዩኒቨርሲቲ ተማሪ ቢሆን ይመረጣል

በማርያም

👇👇👇👇👇

@mogesinewokibrene

የእመቤታችን አንድምታ ወዳሴ ቅዳሴ

30 Oct, 14:19


የጅማ ዩኒቨርሲቲ ተማሪ ወይም ልጆች ወይም የምትሰሩ አዋሩኝ ፕሊስ እባካችሁ

በማርያም

👇👇👇👇👇


@mogesinewokibrene

የእመቤታችን አንድምታ ወዳሴ ቅዳሴ

30 Oct, 10:10


🎧 የበገናና የንሰሃ መዝሙሮች ስብስብ ❤️
============================



♡ ስምሽ ጉልበት ሆኖኝ ♡

✞ በጾም ትትፌውስ ቁስለ ነፍስ ✞

✞ የመርከቧ ተጓዦች ነን ✞

᯽ ላሐ ማርያም ᯽

✧ ስለ ድንግል ብሎ ✧

♡ የእኛ ጌታ ♡

✰ እረ ስማኝ ፈጣሪ ✰

✥ ይሁዳ የሸጠው ✥

✥ በእምባዬ የማመልክህ ✥

✟ የማደርገውን አላውቅም ✟



✝️ ይቀላቀሉ ✝️

የእመቤታችን አንድምታ ወዳሴ ቅዳሴ

30 Oct, 09:05


⁉️ የማንን መንፈሳዊ ትምህርት ማግኘት ይፈልጋሉ?👇


┏━━━━━━━━━━━━━━┓
1⃣ የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
┗━━━━━━━━━━━━━━┛
┏━━━━━━━━━━━━━━┓
2⃣ የአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
┗━━━━━━━━━━━━━━┛
┏━━━━━━━━━━━━━━┓
3⃣ የብጹህ አቡነ ሽኖዳ ሳልሳዊ
┗━━━━━━━━━━━━━━┛
┏━━━━━━━━━━━━━━┓
4⃣ የቅዱስ እንጦስ ትምህርቶች
┗━━━━━━━━━━━━━━┛
┏━━━━━━━━━━━━━━┓
5⃣ የቅዱስ ኤፍሬም ትምህርቶች
┗━━━━━━━━━━━━━━┛
┏━━━━━━━━━━━━━━┓
6⃣ የአባ ሕርያቆስ ትምህርቶች
┗━━━━━━━━━━━━━━┛


🎯የሁሉንም አባቶች ትምህርት ይፈልጋሉ❓️
-----------------------------------------------------

የእመቤታችን አንድምታ ወዳሴ ቅዳሴ

29 Oct, 05:31


ድንግል ሆይ

ቤተ ክርስቲያን ታመሰግንሻለች!!!

"ያዘነች ስትሆን በልጅሽ በወዳጅሽ ትንሣኤ የተጽናናችው፡፡

የተዋረደች ስትሆን በድንግልናሽ ቡቃያ መውጣት ከፍ ከፍ ያለችው ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ታመሰግንሻለች፡፡

በዕለተ ዓርብ ከልጅሽ ቀኝ በፈሰሰው ውሀ ተጠምቃ የውግታቱን ደም ተቀብታ ቅድስት ቤተክርስቲያን ታመሰግንሻለች።

የልዑል እግዚአብሔር በግ የተባለ ልጅሽ ዐማኑኤልየተሞሸረባት መርዓዊ ሰማያዊ የተባለባት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ታመሰግንሻለች"

አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ❤️

የእመቤታችን አንድምታ ወዳሴ ቅዳሴ

28 Oct, 17:43


ውድ  ቤተሰቦቼ እንደምን አላችሁልኝ በጣም ነው ሁለችሁንም የምወዳችሁ ፈጣሪ በመልካም ምግባር ያኑርልኝ 💖💖❤️❤️

የእመቤታችን አንድምታ ወዳሴ ቅዳሴ

26 Oct, 09:36


የእመቤታችን የቅድስት ድንግል
ማርያም አማላጅነት አይለየን

የእመቤታችን አንድምታ ወዳሴ ቅዳሴ

25 Oct, 12:27


ተወዳጆች

መኝታውን በወርቅ ያጌጠ ማድረግ ሲችል
በግርግም ውስጥ ማድረግን መረጠ
እናቱንም ከንግሥታት አንዲቱን ማድረግ ሲችል
አላደረገም ብሏል፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
❤️

ድንግል ማርያም እንዲህ ናት::
ታላላቅ ሀብታትን ሳትጠይቅ የተቀበለች ፣
ሳትለምን የተመረጠች ፣ ሳታገባ የፀነሰች ፣
ሳታምጥ የወለደች ፣ ድንግልናዋን ሳታጣ እናት የሆነች ፣
አንዳች ሳትሻ ሁሉን ያገኘች
የእግዚአብሔር ድንቅ ሥራ እርስዋ ናት፡፡

የእመቤታችን አንድምታ ወዳሴ ቅዳሴ

25 Oct, 12:22


ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ

ደናግል ሆይ

የሰማያዊ ሕይወት አርኣያና አምሳል የሆነችው
የድንግል ማርያም ሕይወት ይኑራችሁ፡፡
እርስዋ ለክርስቶስ እናት ለመሆን
በምንም የምታንስ አልነበረችም'

የእመቤታችን አንድምታ ወዳሴ ቅዳሴ

22 Oct, 09:14


እንደ ውሃ አለሙን በሞቱ ያድን ዘንድ
ሁነሻል ምክንያት ለፍጥረት መዛመድ
የአለም መክበሪያ ንፅህት ጽዋ ነሽ
የማትጠፊሺ ፋና ማትፈርሽ መቅደስ ነሽ

የትኛው ልቡና የቱ አንደበት ነው
ይህን ልዩ ምስጢር ማወቅ የሚቻለው

የእመቤታችን አንድምታ ወዳሴ ቅዳሴ

19 Oct, 23:52


ቅዱስ አግናጥዮስ፣ መልእክት ኀበ ሰብአ ጥራልያን፣ ምዕ. 10

👉የማምነውና ተስፋ የማደርገው በምትሐት ወይም በማስመሰል ሳይሆን ስለ እኔ በእውነት ሰው በሆነውና በሞተው በኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡

👉ሐሰት የሆነ ነገር ለእውነት አስጸያፊ ነውና፡፡ ስለሆነም የማምነው ድንግል ማርያም የፀነሰችውና የወለደችው እግዚአብሔር ቃል የተዋሐደውን ሥግው ቃልን ነው፡፡

👉 የእግዚአብሔር ቃልም የእኛን ባሕርይ ገንዘቡ አድርጎ በእውነት ከድንግል ማርያም ተወልዷል፡፡

👉ሰዎችን ሁሉ በማኅፀን የሚፈጥረውና የሚቀርጸው እርሱ ራሱ ከድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነሥቶ በድንግልና በማኀፀኗ ተፀንሶ ኖሯልና፡፡

የእመቤታችን አንድምታ ወዳሴ ቅዳሴ

18 Oct, 06:24


ተወዳጆች

(ቅዱስ አግናጥዮስ፣ መልእክት ኀበ ፊልጵስዮስ፣ ምዕ. 4)

እንዳለው

“ሰይጣን በአንዳንዶች መስቀሉን ይክዱ ዘንድ በእነርሱ ላይ ሥራውን ይሠራል

የጌታችንን ሕማማቱንና ሞቱን እንዲያፍሩበትና ምትሐት ነው እንዲሉ በውስጣቸው ይሠራባቸዋል

ከድንግል መወለዱንና ሥጋ መልበሱን፣ እንዲሁም የእኛን ባሕርይ ርኩስ እንደ ሆነ አድርጎ ይነቅፋል፡፡

ከአይሁድ ጋር ደግሞ ሰዎች መስቀሉን እንዲክዱ ቤተ ክርስቲያንን ይዋጋታል፤ ከአሕዛብ ጋር ደግሞ ድንግል ማርያምን ይነቅፋሉ፣ ያክፋፋሉ፡ ክርስቶስ ከእርሷ ባሕርይዋን ገንዘቡ አድርጎ እንዳልተወለደ አድርገው ይናገራሉ፡፡

የክፋት ሁሉ መሪና ፍታውራሪ የሆነው ዲያብሎስ አሠራሩ ብዙ ዓይነት ነውና፣ እርሱ የሰዎች ፈታኝና አታላይ እንደ መሆኑ ሰዎችን በተለያዩ መንገዶች ከእውነት ይለያቸው ዘንድ ይፈትናቸዋል፡፡”

የእመቤታችን አንድምታ ወዳሴ ቅዳሴ

18 Oct, 06:05


ተወዳጆች

ቅዱስ አትናቴዎስ

ሐዋርያዊ ይህን መሠረታዊ ጉዳይ በአርዮሳውያን ላይ በጻፈው ጥልቅና ሰፊ ትምህርቱ ላይ እንዲህ ሲል ያብራራዋል-

ቃል ፍጡር ቢሆን ኖሮ ይህ [የእኛ መዳን] ተፈጻሚ ሊሆን አይችልም ነበር፤ ፍጡር ቢሆን ኖሮ ዲያብሎስም ራሱ ፍጡር ስለሆነ ትግሉን ይቀጥልበት ነበር፤ ሰውም በሁለቱ መካከል ሆኖ ከእግዚአብሔር ጋር የሚዋሐድበትና ከፍርሃት ነጻ የሚወጣበት መንገድ አጥቶ ሕይወቱ ሁል ጊዜ በአደጋ ውስጥና በጥፋት ላይ እንደ ሆነ ይቀጥል ነበር፡፡

ስለዚህም በእውነት የእኛ የሆነውን ሰውነትና ባሕርይ ነሣ (ገንዘብ አደረገ)፡ ይህም ባሕርያችንን እርሱ ፈጣሪውና አስገኚው እንደ መሆኑ በእርሱ በራሱ ያከብረው ዘንድ፣ በዚህም በእርሱ መሪነትና አርአያነት ወደ መንግሥተ ሰማያት ያገባን ዘንድ ነው::' የሰው ባሕርይ (ትስብእት) የተዋሐደው ከፍጡር ጋር ቢሆን ኖሮ፣ ወይም ወልደ እግዚአብሔር እውነተኛ እግዚአብሔር ባይሆን ኖሮ የእኛ ባሕርይ የጸጋ አምላክነትን አያገኝም ነበር፤ የእኛን ሥጋ የለበሰው የእርሱ (የእግዚአብሔር] እውነተኛና የባሕርይ ልጁ ባይሆን ኖሮ ሰው ወደ እግዚአብሔር ዘንድ ከፍ ከፍ ሊልና ሊቀርብ አይችልም ነበር፡፡ (ትምህርት በእንተ አርዮሳውያን፣ ትምህርት 2፣ ቁ. 43)

የእመቤታችን አንድምታ ወዳሴ ቅዳሴ

15 Oct, 10:21


የእመቤታችን በረከት አይለየን

የእመቤታችን አንድምታ ወዳሴ ቅዳሴ

13 Oct, 06:16


ቆሜ ስራመድ ጤነኛ እመስላለሁ
የውስጤን ጎደሎ እኔ አውቃለሁ
ድንግል ሆይ ቅረቢኝ አይዞህ ልጄ በይኝ
የጭንቀቴን ካባ አውጥተሽ ጣይልኝ

የእመቤታችን አንድምታ ወዳሴ ቅዳሴ

12 Oct, 17:57


ከሴቶች ሁሉ ልዩ እንደሆነች በቅዱስ ገብርኤል እና በቅድስት ኤልሳቤጥ የተመሰከረላት እናታችን ንጽሕት ቅድስት ድንግል ማርያም በሰው ልጅ ድኅነት ታሪክ ውስጥ ብቻ ሳይሆን በሥርዓተ አምልኮታችን ሁሉ ልዩ ቦታ እንዳላት የታወቀ ነው። እውነቱን ለመናገር ከሉተር መነሣት በኋላ ባሉ የክርስትና ዲኖሚኔሽኖች ካልሆነ በቀር ከጥንታውያን አብያተ ክርስቲያን መካከል እመቤታችን በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ያላትን ልዩ ቦታ የማይቀበል ልዩ ምስጋና የማያመስግናት እና ልዩ አክብሮት የማይሰጣት የለም። ከዚህም የተነሣ ከዚያው ከሐዋርያት ዘመን ጀምሮ ስለእመቤታችን ንጽሕት ድንግል ማርያም ብዙ ተብሏል፣ ተጽፏል፣ ተተርኳል። በተለይ ደግሞ መናፍቃን መነሣት ከጀመሩበት ከሦስተኛው እና ከዐራተኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ የተነሡ ሊቃውንት ስለእመቤታችን ንጽሕት ድንግል ማርያም ብዙ አስተምረዋል፣ ብዙም ጽፈዋል። ሆኖም ጠላት ዲያብሎስም ኑፋቄን አሾልኮ ከአስገባበት ጊዜ ጀምሮ በእመቤታችን ላይ ብዙ አመለካከቶችን ለማምጣት ሳይሰለች እና ሳይደክም ሠርቷል። በአንጻሩ ደግሞ ሊቃውንትም ብዙ መልሶችን ሰጥተዋል፣ ቅዱሳንም ስለእመቤታችን ብዙ የምስጋና እና የተመስጦ ድርሰቶችን ደርሰዋል። ከዚህ የተነሣ አሁንም እመቤታችን ከሰው ሁሉ ከፍጥረትም ሁሉ የተለየች እንደመሆኗ ባለ ብዙ መልኮች በርካታ መጻሕፍት ተደርሰውላታል፣ ተጽፈውላታል።

እመቤታችን ልዩ መሆኗን ከሚያረጋግጡልን ነገሮች አንዱ ደግሞ ሰይጣንና መናፍቃን ሳያቋርጡ እንደሚዘልፏት ሊቃውንት እና ቅዱሳን ደግሞ ሳያቋርጡ የሚያመስግኗት መሆኗ ነው። ይህ መጽሐፍም የዚህ ተግባር እንዱ ማሳያ ነው ማለት ይቻላል። ከጥንት ዘመን ሰይጣን በመናፍቃን አድሮ ያናገራቸው ትችቶች አሁንም ድረስ እንደ አዲስ እየተነገሩ እየተጻፉ ቢቀጥሉም በአንጻሩ ደግሞ እንደ ጥንቱ መንፈስ ቅዱስ ያናገራቸው ሊቃውንት ትምህርቶች በልዩ ልዩ ሊቃውንት አሁንም ይመሠጠራሉ፣ ይሰበካሉ፣ እመቤታችንም ትመሰገናለች፣ እጂጉን ትከበራለች ። "አሐቲ ድንግል” የተባለው ይህ የርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን መጽሐፍም ለዚህ ጥሩ ማሳያ ነው። መጽሐፉ የብዙ ሊቃውንትን ድርሰቶች ሰብሰቦ በአንድ ላይ በማቅረብ ቅድሚያውን ሊወስድ የሚችል መጽሐፍ እንደሆነ ይሰማኛል። በዚህም ቤተ ክርስቲያናችን ስለእመቤታችን ያላትን አስተምህሮ በሥርዓተ አምልኮዋ ውስጥ እመቤታችን ያላትን ቦታ እና ቅዱሳን ስለእርሷ እንዴትእንዳስተማሩ እና እንዴት እንዳመሰገኗት ማወቅ የሚፈልግ ሁሉ ይህ መጽሐፍ በእጂጉ ያስፈልገዋል።

ዲያቆን ብርሃኑ አድማስ

የእመቤታችን አንድምታ ወዳሴ ቅዳሴ

12 Oct, 17:34


የፀሓይ ብርሃን በጠቢባን ጥበብ ይሰፈራል፤ የጨረቃም ውበት ይመጠናል፤ ሰማይና ምድር በአድማስ፣ ባሕርም በናጌብ ይወሰናል።

የእመቤታችንን ክብር ግን መመጠንና መወሰን ይቅርና ማን ሊመረምረው ይቻለዋል? 'ሊቁ መኑ ዘይክል ነቢበ ዕበይኪ” እንዳለ ገናንነትሽን ማን ይናገራል እያልን ስለ እሷ የተነገረውን ሁሉ በመደነቅ እናነባለን።

ሊቃውንቱ ለእመቤታችን ውዳሴ በመጽሐፍ የሚያኖሩት ለኀሊና ማቅኛ እንዲሆን ነው እንጅ ከዚያ በኋላስ ኅሊና አስቦ ወደማይደርስበት ጥልቅ ባሕረ ውዳሴ መግባት ነው።

የአበቦችን ውበት በምድረ በዳ፣ ከዋክብትን በሰማይ ላይ በጥበቡ የገለጠ አምላክ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምንም በሊቃውንት እንደበት ይገልጣታል።

ቅዱስ ኤፍሬምን አፈ በረከት ቅዱስ ዮሐንስን አፈ ወርቅ ያሰኛቸው የድንግል እመቤታችን ውዳሴ ነው።

እስከ ዕለተ ምጽእት የሚነሣው ትውልድ እንዲያመሰግናት በትንቢት የተነገረላት ሉቃ 1:48 ይፈጸም ዘንድ ዛሬ ባሉ የቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት እንደበትም በጉባኤ፣ በማኅሌት፣ በቤተ መቅደስ ትመሰገናለች።

ርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን እመቤታችን "ያስተበፅዑኒ ኩሉ ትውልድ” ብላ ከተናገረችላቸው አንዱ ናቸው። ለዚህም ምስክሬ ትምህርታቸው ነው።

በዐውደ ምሕረት "የምድር ጌጥ ይሏታል። በጉባኤ ቤት “ብርሃንኪ የዐቢ እምብርሃነ ፀሐይ” ይሏታል።

በበዐታቸው "ሰአሊ ለነ ቅድስት'' ይሏታል። ዛሬ ደግሞ ተነቦ የማይጠገብ ውዳሴዋን በመጽሐፍ አቅርበውልናል።

ይሄ መጽሐፍ በትውፊት የምናወርሰው፥ ነገር ግን እያየነው የተደረሰ አዲሱ አርጋኖን ነው።

ቅድመ ዓለም በአምላክ ኅሊና ከታሰበው ድኅረ ዓለም በነቢያት እስከተነገረው፣ በመላእክት ከተዘመረው በሐዋርያት እስከተሰበከው ሊጠቀስ የሚገባው ተጠቅሷል።

የእመቤታችን ነገር ሐረግ ነው፤ በነካነው ጊዜ ሁሉ ብሉያትን ሐዲሳትን ሊቃውንትን ያንቀሳቅሳል።

ርእሰ ሊቃውንት እንደ ሐረግ ሳቢ አንድ ጥቅስ በመዘዙ ጊዜ የመጻሕፍት ሁለንተናቸው ይንቀሳቀሳል።

ከብሉይ ኪዳን ጀምሮ በእግዚአብሔር መንፈስ የተጻፈ መጽሐፍ ሁሉ እመቤታችን የሌለችበት መጽሐፍ አይገኝም።

ይህን መጽሐፍ ባነበባችሁ ጊዜ ይህንን እውነት ትረዱታላችሁ። "አሐቲ ድንግል" አንድ መጽሐፍ ብቻ አደለም።

ትርጓሜ፤ ድርሳን፤ ምዕላድ፤ ውዳሴም ነው።

ሁልጊዜ የርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳንን ስብከት ስሰማ የምመኘው ይህንን መጽሐፍ ነበር።

አንዳንዴ ስብከት መሆኑን ረስቼ መጽሐፍ የሚያነቡልኝ ይመስለኝ ነበርና። እነሆ የተመኘሁት መጽሐፍ በብራና ተጠቅሎ በቤተ መጻሕፍት ተጥሎ አገኘነው። ከእኔ ጋራ የተወለደውን የመጻሕፍት ንጉሥ ታዩ ዘንድ ኑ!

ሊቀ ሊቃውንት ስምዐ ኮነ መልአክ የ፬ቱ ጉባኤያተ መጻሕፍት ምስክር መምህር

የእመቤታችን አንድምታ ወዳሴ ቅዳሴ

11 Oct, 17:41


ተወዳጆች

↘️መኃልየ መኃልየ ዘሰሎሞን

መኃ 4፥12፦ <<እህቴ ሙሽራ
የተቆለፈ ገነት
የተዘጋ ምንጭ
የታተመም ፈሳሽ ናት

↘️አንድምታ

እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዘላለማዊ ድንግል ነች ሲል ነው ፣ ቅድመ ዓለም በእግዚአብሔር ታስባ የነበረች ኋላም በሃሳብና በሥራ ንጽህት ድንግል የሆነች ስለሆነ የተቆለፈ ገነት የተዘጋ ምንጭ የታተመም ፈሳሽ ናት ሲል ምሥጢር ነግሮናል

ረድኤቷ በረከቷ አይለየን

የእመቤታችን አንድምታ ወዳሴ ቅዳሴ

04 Oct, 07:44


ተወዳጆች

እኔ

እመቤታችንን እንኳን በገሀድ አይተናት
እንደው በህልማችንም አይተን በሞትን
እንዴት ያለች ውብ ናት ፈጣሪ እንዴት አድርጎ ወደዳት
እንዴት ያለች መልከኛ ናት
መላእክት እኮ ሳስተውላታል

ለቅዱስ ሚካኤል እና ለቅዱስ ገብርኤል


ተመልከቱ አዳምን ፈጥሬ ማድነው በዚች ነው ብሎ
ከክንፋቸው ላይ ሳለላት
ስሎ ቢያሳያት ኧረ ቶሎ ፍጠርልን ኧረ ቶሎ ፍጠራት
ናፍቃናለች ለኛም እህት እንድትሆነን
በንፅህና እንድትመስል ቶሎ ፍጠርልን


ሚካኤል መልአክ በክንፉ ፆራ የተባለች ለዚህ ነው


በክነፉ ፁሮ ክንፋቸው ላይ ስሎ አሳይቷቸዋል
እና ገና ሳያገኟት ሳትወለድ ነበር ሚወዷት
በዚህ ዓለም ላይ የእመቤታችን ፍቅር
እንደ ውሃ የፈሰሰለት ሰው የታደለ ነው

አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ለዚህ ነው

ፍቅርሽ እንደ ወይን እና ውሃ በልቤ ውስጥ ተቀላቅሏል
ወይን እና ውሃ ከተቀላቀለ በኋላ
ይሔ ወይን ነው ይሔ ውሃ ነው አይባልም


እኔን ከማርያም ፍቅር ለይቶ ማሳየት የሚችል የለም

እንዴት አድርጎ ቢወዳት ነው እናንተ
እንዴት አድርጌ ላመስግንሽ ይሆን ? አለ
ምን ላድርግ ? ፀጉሬ እንኳን
አፍ አውጥቶ በዚምርልሽ አይበቃሽ ይላታል
ዝም ብዬ ቡርክት ቡርክት ቡርክት እልሻለሁ ይላል።

ስሟ እግዚአብሔር እንዳመሰገነው የከበረ ይሁን ።

ርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን❤️

የእመቤታችን አንድምታ ወዳሴ ቅዳሴ

03 Oct, 17:48


ተወዳጆች ሆይ

ሁሉ ቢተወን እመቤታችን ግን ታየናለች
እመቤታችን ማንንም ነው ምትሰማው ማትንቀው
የሰውን ችግር ታውቃለች እመቤታችን
ከልቤ ነው የምነግራችሁ

አሁን እናንተ የሚመሰላችሁ
አላውቅም ምን እንደሚመስላችሁ
ይሄ ትዕቢት ስለሆነ ማለት ነው

ብቻ ብዙዎቻችን ግን ሚመሰለን
እመቤታችን የሆኑ ሰዎችን ምትረዳቸው
እኛን ደሞ ማትረዳን ነው የሚመስለን

እንደው ለኛ ለኛ ማናሳዝናት
ይመስላችኋል አይደለም
የማንም ችግር ያሳዝናትል
የማንም ችግር እውነት ከልቤ ነው

ማንም ሰው ሳያይላችሁ
ቀድማ የምታይላችሁ እመቤታችን ናት

ይሔው ቃና ዘገሊላ ላይ
ሁሉም ሰው ከዚህ ቅዳ
ስጥ ለእንግዳ እያለ ይቆርጣል እንጂ

ማን ጠጅ ማለቁን አይቷል
እሷ እኳ ናት ጓዳቸውን ያየችላቸው

ማንም አልተረዳም ነበር
እርሱ ግን እያወቀ ትቶት ለምን
የእመቤታችን ክብር እንዲገለጥ

አምላክ ነው እሱ ያውቃል

ር ዕሰ ሊቃውንት አባገብረ ኪዳን❤️

5,164

subscribers

151

photos

5

videos