..............................
ጥር 6/2017 /ምስ/አ/አ/አ/ግ/ከ/ቅ/ጽ/ቤት/
በገቢዎች ሚኒስቴር የምሥራቅ አዲስ አበባ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የበጀት ዓመቱ የጥር ወር የሞጁላር ስልጠና ተጀመረ ፡፡
የስልጠናውን መጀመር አስመልክተው አቶ እሸቱ ኢራጎ የታክስ ከፋዮች ትምህርትና መረጃ አቅርቦት የሥራ ሂደት አስተባባሪ ተወካይ ገለጻ ያደረጉ ሲሆን ታክስ ከፋዮች በቂ የታክስ ዕውቀት ኖሯቸው ግብራቸውን በሃላፊነት ፣ አዋጅ ፣ህግንና መመርያን ተከትለው መክፈል እንዲችሉ ታሰቦ ስልጠናው መዘጋጀቱን ገልጸዋል ።አያይዘዉም ከሰልጣኞች የሚጠበቀው በአግባቡ በመከታተል ያገኙትን ስልጠና ተገባር ላይ ማዋል መሆን እንዳለበት አሳስበዋል፡፡
ስልጠናው አጠናቀው የሚሰጠውን ፈተና ማለፊያ ውጤት ላስመዘገቡ ሰልጣኞች ሰርተፊኬት እንደሚዘጋጅና በሀገር አቀፍ ደረጃ እውቅና እንደሚሰጥ ጠቁመዋል ፡፡
ወ/ሮ እታፈራው ወርቁ የታክስ ከፋዮች ትምህርት መሪ ባለሙያ የእለቱን ስልጠና የሰጡ ሲሆኑ በመጀመሪያ ሴምስተር ከሚሰጠው ከመቀጠር የሚገኝ ገቢ የሚለውን ርእስ አንስተዋል ፡፡
በሌላ በኩልም የርቀት የሞጁላል ሰልጣኞችም በዛሬው እለት የክፍል አንድ ሞጁላር ገለጻ ተደርጎላቸዋል ስልጠናውንም ገለጻ ያደረጉት ወ/ሮ ይልፋሸዋ ይርጋ የታክስ ከፋዮች ትምህርት ከፍተኛ ባለሙያ ናቸው፡፡ ለድርጅት ስራ አስኪያጆችና ምክትል ስራ አስኪያጆች የተዘጋጀ ስልጠና ነው ፡፡
በታክስ ህጎች፣ ደንቦች እና መመሪያዎች ዙሪያ ለግብር ከፋዮች በተከታታይ የሚሰጠውን “ሞጁላር” የተሰኘ ስልጠና ተጠናክሮ ይቀጥላል ፡፡
……….