መንገድ አለ !

@mengedale


መንገድ አለ !

04 Apr, 18:00


Live stream scheduled for

መንገድ አለ !

01 Apr, 05:29


ሰይጣን እንኳን ውሎ የሚያድረው በእግዚአብሔር ቸርነት ነው እንጂ እስካሁን ይጠፋ ነበር ። ለሰይጣንን የራራ አባት እኛን እንዴት ይተወናል። ምንም ነገር እንዳትፈሩ እግዚአብሔር አለልን እሺ 😊

መንገድ አለ !

29 Mar, 05:25


ምን እየሆንን ነው ?

መንገድ አለ !

28 Mar, 19:33


እንዴት ነበር የዛሬው Live stream ?

መንገድ አለ !

28 Mar, 19:31


https://telegra.ph/ሕይወትን-እንደ-አዲስ-መጀመር-03-13

መንገድ አለ !

28 Mar, 19:30


Live stream finished (1 hour)

መንገድ አለ !

28 Mar, 18:37


self-love / ራስን መውደድ

ሰው ራሱን አለመውደድ አይችልም። ራሱን አይወድም የሚያሰኙ ድርጊቶችን ቢፈጽም እንኳ ራሱን ስለሚወድ ነው። ይህን በአንድ ምሳሌ እንየው ፦ አንድ ሰው በጣም ከመጨነቁ የተነሳ ራሱን ቢያጠፋ ራሱን ያጠፋው ራሱን ስለሚጠላው ይመስላችኋል? አይደለም።ይልቁንም ከነበረበት ጭንቀት እና መረበሽ ለመላቀቅ ለራሱ ሰላምን፣ የተሻለ እረፍትን ለመስጠት ነው ይህን ያደረገው። ማንም ሰው በራሱ ላይ ክፉ ቢያደርግ እንኳ በኋላ (ክፉ ካደረገ በኋላ) የሚያገኘውን ጥቅም በማሰብ ነው። ምን አልባት አንድ ሰው ራሱን ሊያጠፋ ሲያስብ ከዚህ ኑሮ ሲኦል ይሻለኛል በሚል ስሜት ሊሆን ይችላል ነገር ግን ይህም ራሱን እንደሚወድ ያሳያል ምክንያቱም ሲኦል ይሻለኛል ያለው በራሱ ግምት ይቀላል ብሎ በማሰቡ ነው (ትክክል ባይሆንም)።ስለዚህ ሰው ራሱ ላይ ክፉ ቢያደርግ እንኳ ጭንቀቱን release ለማድረግ እና በኋላ የሚገኘውን የተሻለ እረፍት በማሰብ ነው እንጂ ራሱን በመጥላት አይደለም።

--> የቤተክርስቲያን አስተምህሮ
ቤተክርስቲያን ራስ ወዳድነትን(selfishness'ን) እንጂ ራስን መውድድን (self love'ን) አትቃወምም። ራስ ወዳድነት ፦ በሌሎች መጎዳት ላይ ፣ ከራስ ውጪ ሌላውን ባለመውደድ ላይ ፣ ሁሌም እኔ ብቻ በሚል ስሜት ላይ የተመሰረተ ራስን መውደድ ሲሆን ይህም ለጊዜው ራስን መውደድ ቢመስልም ነገር ግን አርቀው ቢያስቡት በኋላ ብዙ ችግሮችን የሚያስከትል ነው።
ቤተክርስቲያን ሰው ራሱን አለመውደድ እንደማይችል አስቀድማ የተረዳች በመሆኗ ትእዛዛቶቿ ራስን ከመውደድ የተነሳ እንዲፈጸሙ ሆነው ተሰርተዋል። የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅስ አንስተን በምሳሌ እንመልከት ፦ “በእናንተስ እንዲህ አይደለም፤ ነገር ግን ማንም ከእናንተ ታላቅ ሊሆን የሚወድ የእናንተ አገልጋይ ይሁን፥” ማርቆስ 10፥43 ። ይህን ኃይለ ቃል አስተውለን ብንመለከተው አንድ ሰው የሌሎች አገልጋይ የሚሆነው በኋላ ታላቅ የሆነችውን መንግሥተ ሰማያት ለመውረስ ሲል ነው። ራሱንም ዝቅ የሚያደርገው በኋላ ከፍ ያለ(ከኃጢአት የተለየ) ህይወት መኖር ስለሚፈልግ ነው። ከዚህ ሀሳብ ጋር የሚመሳሰሉ ጥቅሶች ፦ 1ኛ ቆሮንቶስ 3፥18 ፣ ሉቃስ 22፥26 ፣ ማርቆስ 9፥35 ፣ ማርቆስ 10፥44 .....።

"አፍቅር ቢጸከ ከመ ነፍስከ" " ወንድምህን እንደራስህ ውደድ"
“ነገር ግን ባልንጀራህን እንደ ራስህ ውደድ፤ እኔ እግዚአብሔር ነኝ።”ዘሌዋውያን 19፥18 ፣ ማቴዎስ 22፥39 ፣ ገላትያ 5፥14
የሰው ልጅ ምንም ነገር ለመሞከር ቢፈልግ እና እርግጠኛ የሆነ ውጤት ሊያገኝ ቢወድ ከራሱ የተሻለ ሌላ የለም። የአንድን ምግብ መጣፈጥ እና አለመጣፈጥ ለመለየት ከአንተ የተሻለ ሰው የለም(ምግቡ ለራስህ ከሆነ)። ስለዚህ ይህም እንዲህ ነው ቀምሰህ የጣፈጠህን ምግብ ለወንድምህ ስጠው ነው ሀሳቡ። ምናልባት ይህ ሰው ራሱን የማይወድ ቢሆን የሚመርጠውም ምግብ የማይጣፍጥ ይሆናል ለወንድሙም የሚጣፍጠውን ለመስጠት አይቻለውም ስለዚህ ራስን መውደድ ለኛ ለወጣኒዎቹ የሚጣፍጠውን የምንለይበት መንገዳችን ነው። ምናልባት የፍፁማኑን ነገር ስላልደረስኩበት ራሳቸውን ይወዳሉ ብዬ ከመናገር ይልቅ በክርስቶስ ፍቅር ከመስከራቸው የተነሳ ራሳቸውን ይተዋሉ ማለትን እመርጣለሁ። ወደዚህ ደረጃ ከመድረሳቸው በፊት ግን አስቀድመው ፍቅርን በራሳቸው እንደተለማመዱት ከቀድሞ ህይወታቸው እንረዳለን።

--> self-esteem / ለራስ ያለ አዎንታዊ ግምት
ሰው ለራሱ ያለው ምልከታ/ግምት አዎንታዊ(positive) ካልሆነ ሌሎችን በአዎንታዊ ዕይታ ለመመልከት ይቸገራል አንድ ሰው ቀይ መነጽር ቢያደርግ አከባቢው ሁሉ ቀይ ሆኖ እንደሚታየው ሁሉ ሰው ሌላውን የሚገምተው ለራሱ ካለው ግምት በመነሳት ነው።

ስለራሳችን ጥሩ እና ትክክለኛ አረዳድ ሲኖረን ለራሳችን ጥሩ ነገር መመኘት እንችላለን።ምሳሌ፦ የሰው ልጅ ከቅዱስ ቁርባን ከሚርቅበት ትክክል ያልሆኑ ምክንያቶች አንዱም ለራሱ ያለው አረዳድ ትክክል ባለመሆኑ ቅዱስ ቁርባንንም የተረዳበት መንገድ ትክክል ስለማይሆን ነው። ሰው ኃጢአተኛ ቢሆንም ከኃጢአቱ መንጻትን የሚመኘው ለራሱ ጥሩ ግምት ሲኖረው ነው።
“አጥብቀህ ልብህን ጠብቅ፥ የሕይወት መውጫ ከእርሱ ነውና።” ምሳሌ 4፥23

ዲ/ን ኤፍሬም ሲሳይ
መጋቢት 19/2016ዓ.ም

መንገድ አለ !

28 Mar, 18:00


Live stream started

መንገድ አለ !

28 Mar, 08:40


ከረጅም ጊዜ በኋላ ዛሬ ማታ live stream እናካሂዳለን የጠፋንበትንም ምክንያት እናስረዳለን 😊

ስለዚህ ሁላችንም ማታ 3 :00 ላይ " ምን እየሆንን ነው ? " በሚል ርዕስ እናወራለን ። እናንተም ለሌሎች ሰዎች share በማድረግ እንድታግብዙ እንጠይቃለን ።

ሰላም አስመሾቶ በሰላም ያገናኘን

መንገድ አለ !

28 Mar, 18:00


Live stream scheduled for

መንገድ አለ !

26 Mar, 05:03


“መኃልየ መኃልይ ዘመንገድ”
.
.
.

ማራቶን የገቢያ ማዕከል ሳይደርስ የቆመው ታክሲ ተሳፋሪዎቹን እያወረደ ነው። ተሳፋሪዎቹ ከታክሲው እንደወረዱ አከባቢው ላይ ወዳሉ ህንጻዎች ለመጠለል ተፈተለኩ፤ ምክንያቱም በረዶ ከቀላቀለው ዝናብ ማምለጥ ግድ ስለሚያስብል። ዘላለም ግን ከታክሲ እንደወረደ በዛ ዶፍ ማራቶንን የገቢያ ማዕከል አልፎ ወደ መተባበር በሚወስደውን ቁልቁለት በችኮላ መራመድ ጀመር።

ሰማይ የተቀደደ ይመሰል ከላይ የሚወርድበት ዝናብ የተሰማው እስከማይመስል እየበሰበሰ ይጣደፋል። መተባበር ጋር ደርሶ ወደ ቤቴል ፕላዛ ለመሻግር የመኪማውን መንገድ ግራ ቀኝ ገረመመና መራመዱን ቀጥሎ አስፓልቱ መሃል ላይ ካለው አበባ መትከያ ደረሰ። በቀልቡ አይደለምና ግራ ቀኙን አስተውሎ ሳይመለከት የመኪናውን መንገድ ለመሻገር ሶስት እርምጃ እንደተራመደ.....ሲ....ጥ......ጥ.....የሚል ፍሬን የያዘ መኪና ድምጽ ተሰማ። አከባቢው ላይ ያሉ ሰዎች ጩኸት ተከተለ። ዘላለም ደንግጦ ወደ ቀኙ ዞረ፤ ነጣ ያለ ቪትዝ ከእርሱ ጥቂት ሳንቲ ሜትሮችን ብቻ ሲቀሩት ቁሟለች። አሽከርካሪው አንገቱን በመስኮት አውጥቶ፤ "እያየህ አትሄድም አይንህ አያይም....."ሹፌሩ ስድቡን ቀጠለ። ዞላ ከድንጋጤው ለመረጋጋት ሞከረ። እያሮጠው ያለውን ጉዳይ ሲያስታውስ ድንገት ተፈትልኮ ወደ ቤትል ፕላዛ አቀና።

ከህንጻው ስር ካለ ካራቫን ኮፊ ሲደርስ በውሃ ተነክሮ እንደወጣ ብርድ ልብስ ውሃ ከመላ ሰውነቱ አየተንጠባጠበ ነው። ስልኩን አውጥቶ ሲመለከት በዝናብ ውሃ በስብሶ ጭልም ብሏል። እየተበሳጨ ወደ ውስጥ ገባ። ተስተናጋጁ በግርምት ገረመመው እርሱ ግን በአይኑ እያማተረ ሰው መፈለግ ጀመረ። የሚፈልገውን ሰው ሲያጣ ወደ አንደኛው ፎቅ ደረጃን ከሩጫ ባልተናነሰ ፍጥነት ተረማመደ። በዝናብ መበስበሱና ጥድፊያው በጥምረት የተስተናጋጁንም የአስተናጋጆቹንም ትኩረት ስቧል።

አንድኛ ፎቅ ላይ ካለው መስተናገጃ ደርሶ አሁንም አይኑን እያንከራተተ ቆይቶ ተስፋ በቆረጠ ድምጽ "oh shit" አለ። ከበሰበሰው ልብስ አሁንም ውሃ እየተንጠባጠበ ነው። ተስፋ በቆረጠ አኳሃን ወደ ታች ለመውረድ አለና ባልኮኒው ላይ ያለውን መስተናገጃ አስታወሰ። ትንሽ ተስፋ በውስጡ ተጫረ፤ ወደ ባልኮኒው እንደወጣ ጥግ ላይ ተቀምጠው የሚስተናገዱ ጥንዶችን ሲመለከት "እፎይ" አለ ለራሱ ብቻ በሚሰማ ድምጽ።

ከእነርሱ ጥቂት ፈንጠር ብሎ ከወንዱ ጋር ፊትለፊት በሚተያዩበት አቅጣጫ ዙሮ ተቀመጠ። አስተናጋጇ ስትመጣ ማኪያቶ አዘዘና ስልኩን አውጥቶ መጠራረግ ጀመረ። ስልኩ ሲከፍትለት ፊቱ በአንዴ ፈካ ተዝናንቶ ተቀመጠ። አስተናጋጇ ማኪያቶውን ስታመጣለት በስልኩ መልዕክት መላኪያ ላይ የሆነ ነገር እየጻፈ ነበር። አስተናጋጇን የሆነ ነገር ነገራት። ተመልሳ ስትመጣ ሁለት የሂሳብ ደረሰኝ ጠረጴዛው ላይ አስቀመጠች።

በዝናብ የረሰረሰው ልብሱ ጠፈፍ ሲልለት፤ ሂሳብ ከፍሎ ከጥንዶቹ መካከል ለወንዱ በእጁ አንድ ምልክት አሳይቶት ጀብዱ እንደፈጸመ ሰው እየተጎማለለ ካፍቴሪያውን ለቆ ወጣ። ከአፍታ ቆይታ በሇላ ጥንዶቹ አስተናጋጇን ጠርተዋት ስትመጣ።
"ቢል አመጪልን" አለ ወንዱ
"ሂሳብ ተከፍሏል" አለች አስተናጋጇ
" ማን ነው የከፈለው አለ" ግራ በተጋባ አኳሃን
"እዚህ ጋር የነበረው ልጅ" ብላ ዘላለም የተቀመጠበትን ወንበር አመለከተች። አስተናጋጇ እንደተመለሰች ማን ሊሆን ይችላል የሚለውን እየተጠያየቁ ካራቫንን ለቀው ወጡ።

⏱️ከምሽቱ 3:00⏱️

የዘላለም ስልክ ጮኸ፤ ተመለከተውና በፈገግታ አንስቶ
"አንተ የስራህን ይስጠህ እሺ" አለ
"እንደዛ በዝናብ በስብሰህ ሳይህ ሳቄን ሊያመልጠኝ ምንም አልቀረኝም ነበር" አለው ካሌብ እየተከተከተ
"አንተ ሳቅ ምን አለብህ፤ በመኪና ሁሉ አስበልተኸኝ ነበር" ሲለው ካሌብ ሳቁን ቀጥ አድርጎ
"እውነት? እንዴት? ዬት" እያለ ጥያቄውን አክተለተለ
" መገናኛ፤ ዝናብ ውስጥ ወደ አንተ እየሮጥኩ ከዬት መጣች ያላልኳት ቪትዝ ለትንሽ ድጣኝ ነበር" አለ ዘላለም ኩነቱን እያስታወሰ ስቅጥጥ ብሎት።
"ውይ ወንድሜ እንኳን አተረፈህ" ከማለቱ ዘላለም አቋረጠውና
"እኔ ያልገባኝ ግን ገንዘብ ሳትይዝ ሂደህ ነው ቺኳን አስቀምጠህ ብር እንዳመጣልህ ቴክስ የላከው?" አለ በግርምት
" ባክህ ታክሲ ለመያዝ ስጋፋ ነው መሰል ኪሴን አጥበውታል፤ ደግነቱ ሞባይሌን በእጄ መያዜ ጠቀመኝ" ከማለቱ ዘላለም በሳቅ ተንከትክቶ ሲያበቃ።
"አንተ ሞዛዛ አንተንም አለመስረቃቸው ደግ ሁነው ነው" ብሎ ሳቁን ቀጠለ።
"እኔ ያስደነገጠኝ ከልጅቷ ጋር ቁጭ ብለን እያወራን አጋጣሚ እጄን ወደ ኪሴ ስሰደው ነው። የቀነስኩትን ኪሎ አትጠይቀኝ። ከዛ ሳላስፎግር ስልኬን አውጥቼ ቴክስት ላኩልህ። አንተም አላሳፈርከኝም ከች ብለህ ከጉድ ታደከኝ። በጣም ነው የማመሰግነው ዞላ" አለ ከጉድ ያተረፈውን ወዳጁን ውለታ እያሰበ።
"ኧረ አካበድከው፤ አንተ ብትሆን የማታደርገው አስመሰልከው እኮ።" አለ ዘላለም። ጥቂት እየተተራረቡና እየተቀላለዱ ካወሩ በሇላ ተሰነባብተው ስልኩን ተዘጋ።

ስልኩን እንደዘጋ የየዕለቱን ውሎ የሚያሰፍርበትን ማስታወሻ ከፍቶ ጓደኛውን ዘላለምን እያሰበ የሚከተለውን አሰፈረ።

"ጓደኝነት መዋደድ ነው፣ ጓደኝነት መፈለግ ማስፈለግ መፈላለግ ነው፣ ከውስጥ የመነጨ መሰጠት ነው፣ መሰዋትነትም ነው፣ ለሌላው መኖር፣ ለሌላው መዘርጋት ነው ግና ይሄ ሁሉ ጥቅምን ሳያስተምን ነው፤ በጓደኝነት ለመቀበል መስጠት ሳይሆን ከፍቅር የፈለቀ መካፈል ነው።

አዎን ጓደኝነት በብዙ አስቸጋሪ ፈተናዎችና ተግዳሮቶች ውስጥ አብሮ መዝለቅ ነው። አለመግባባት ተደምሮ ንዴትን ንዴት ተደጋግፎ ጥልን ቢያስከትልም ቅያማት ሳይሰነብት የሚፋቅበት ውድ ህብረት ነው ጓደኝነት። ጓደኝነት የጾታን፣ የዘርን፣ የዜግነትን፣ የሐይማኖትን እና የመሰል መደቦችን የገደብ አጥርን እየጣሰ በልብ ትስስር የሚመሰረት ወዳጅነት ነው።"

መንገድ አለ !

24 Mar, 02:57


ተስፋ ባጣችሁበት ነገር ላይ እግዚአብሔር አለሁ ይበላችሁ !

መንገድ አለ !

22 Mar, 04:00


ከደረሱብን ችግሮች ይልቅ የሚደርስልን እግዚአብሔር ይበልጣል !

መንገድ አለ !

21 Mar, 17:02


ስድስት ወይስ ዘጠኝ?
ከሁለቱ ትክክል ማን ነው? አንዳንዶች ሁለቱም ነገሩን ያዩበት ማዕዘን (perspective) የተለያየ በመሆኑ እንጂ ሁለቱም አልተሳሳቱም ይላሉ። ሁኖም ከተለያየ አቅጣጫ መመልከት ለተለየ እይታ መንስኤነት እንጂ የትክክለኛነት ማረጋገጫ ሊሆን አይችልም። ነገሮችን ከተለያየ ማዕዘን ሁነን መመልከታችን ለነገሮች የተለያየ ትርጉም እንድንሰጥ የማድረጉ እውነታ ለትክክለኝነት ማረጋገጫ አይሆነንም።

ከላይ ባለው ምስል ላይ ያለው ቁጥር ስደስትም ዘጠኝም ሊሆን አይችልም፤ ሰዎቹ በዛ መንገድ ተረዱት ማለት ነገሩ በእርግጥም እንደዛ ነው ማለት አያስችልም። የነገሩን ምንነት የሚወስነው ራሱ ነገሩ እንጂ የእኛ እይታ አይደለም። ከላይ ያለው ቁጥር ሲጻፍ ከዬት እንዲነበብ ታስቦ ነው? የጻፈው ሰው ዬትኛውን ቁጥር ለመጻፍ አስቦ ነው? እውነታው እርሱ ጋር ነው ያለው። የተጻፈው ቁጥር ስድስት ከሆነ ዘጠኝ አድርጎ የተመለከተው የተመለከተበት ማዕዘን ልክ አልነበረም ማለት ነው። የተጻፈው ዘጠኝ ከሆነም ስድስት ያለው ከተሳሳተ ማዕዘን ላይ ቁሞ ነው። እውነት እኛ ቁምን እንደምናይበት ማዕዘን (perspective) የሚወሰን ሳይሆን በራሱ በእውነታ ላይ የሚመሰረት ነው።

እናም "እኔን የሚታየኝ "ይሄ" ነው ብሎ ችንክር ከማለት ነገሩን የተመለከትኩበት ማዕዘን (perspective) ትክክለኛ ነው ወይ?" የሚለውን መመለስ የተሻለ ወደ እውነታ ይመራል።
ደህና እደሩ!

መንገድ አለ !

19 Mar, 05:03


ይህችን ዛሬን እኮ ከዚህ በፊት አይተናት አናውቅም ። የዛሬን አዲስነት እያሰቡ መደሰትን ይስጠን ።

መንገድ አለ !

17 Mar, 04:12


ልክ ላይመስል ይችላል ግን እግዚአብሔር በሕይወታችን ላይ ምን እያደረገ እንዳለ ያውቃል ብቻ እናንተ እመኑት ። እሺ ?

መንገድ አለ !

16 Mar, 11:43


ይህ የብዙዎቻችንን ጥያቄ ይመልሳል ብለን ተስፋ እናደርጋለን ። ከልብ አንብባቹ ሕይወትን እንደ አዲስ ለመጀመር ጉዞ እንደምትጀምሩ ተስፋ አለን ። አስተያየታችሁን አካፍሉን 🙏

መንገድ አለ !

16 Mar, 11:41


https://telegra.ph/ሕይወትን-እንደ-አዲስ-መጀመር-03-13

መንገድ አለ !

15 Mar, 04:13


❝ሰው ዝም ብሎ የእግዚአብሔርን ማዳን ተስፋ ቢያደርግ መልካም ነው።❞
  —ሰቆ. 3: 26