ህይወትን በጥበብ @lifeandwisdom Channel on Telegram

ህይወትን በጥበብ

@lifeandwisdom


CONTACT ADMIN👦 @Eftah12

GROUP :- https://t.me/big_dreamerss

ህይወትን በጥበብ (Amharic)

ህይወትን በጥበብ እየተሰበሩ የዚህ ተማሪ ቦታ ለምንድን እንደሆነ በትምህርት ፍላጎታዊ እና ምሳሌዎች ስክሪፊስት ተመልከቱ። የቴሌግራም ቻንኩን በሚከተለው መልእክት የሚያበረከተው ሲሆን፣ በትምህርት ለማወቅ እና በምርመራ ለማስተዋወቅ ይህ ቻንኩን ተደርጋለች። እዚህ ታሪኩን በማስረጃ ውስጥ በሚሰጠው ግሌ የሚሳቡበት ፍላጎታዊ ውይይት መላክና ምዘናና አስተያየታችሁን በማስፈለገ።

ህይወትን በጥበብ

06 Feb, 09:47


#ይሄኔ_የት_በደረስኩኝ_ነበር?!

• ሰዎች በእኔ ላይ ምን እንደሚያስቡ ለማወቅ የታገልኩትን ያህል ራሴን ለማወቅ ብሰራ ኖሮ . . . ይሄኔ የት በደረስኩኝ ነበር?!

• በፍጹም የማይፈልጉኝን ሰዎች ስለማመጥና ስከታተል ያሳለፍኩትን ጊዜ ለእኔ ዋጋ ላላቸው ሰዎች ሰጥቸው ቢሆን ኖሮ . . . ይሄኔ የት በደረስኩኝ ነበር?!

• በማያገባኝ የሰዎች ስራና ሃሳብ ላይ በማውራትና በመቃወም ያባከንኩትን ጊዜ የሚደገፍ ሰው ፍልጌ ደግፌ ቢሆን ኖሮ . . . ይሄኔ የት በደረስኩኝ ነበር?!

• በየጊዜው ካለእቅድ የማወጣቸውን የገንዘብ መጠኖች በጥንቃቄ ብቆጥባቸው ኖሮ . . . ይሄኔ የት በደረስኩኝ ነበር?!

• ምንም ያህል ብጨነቅ መለወጥ በማልችላቸው ነገሮች ላይ መጨነቄን ትቼ ለመለወጥ አቅም ያለኝ ነገሮች ላይ አተኩሬ ቢሆን ኖሮ . . . ይሄኔ የት በደረስኩኝ ነበር?!

• የሚወዱኝ ቤተሰቦቼና ጓደኞቼ ሲመክሩኝ የመስማትና ጥሩውን ምክር የመቀበል ልማድ ኖሮኝ ቢሆን ኖሮ . . . ይሄኔ የት በደረስኩኝ ነበር?!

• ለመጀመር ያሰብኳቸውን እነዛን ወሳኝ ነገሮች ጀምሬያቸው ቢሆን ኖሮ . . . ይሄኔ የት በደረስኩኝ ነበር?!

• የማይሆኑ የማሕበራዊ ጎጾች ሳስስ ያመሸሁባቸውን ምሽቶች የቀኑን ውሎየን ለመገምገምና ለነገ በማቀድ ባሳልፋቸው ኖሮ . . . ይሄኔ የት በደረስኩኝ ነበር?!

• ለየእለት ገጠመኞች ምላሽ እየሰጡ ከመሯሯጥ ይልቅ በራእይና በዓላማ ኖሬ ቢሆን ኖሮ . . . ይሄኔ የት በደረስኩኝ ነበር?!

ያም ሆነ ይህ ያለፈው አልፏል! ከጥቂት አመታት በኋላ እንደገና “ይሄኔ የት በደረስኩኝ ነበር?!” የሚል የግምገማ ስሜት እንደሚመለስብኝ ስለማውቅ አሁኑኑ ለውጥን አመጣለሁ።

@lifeandwisdom

ህይወትን በጥበብ

30 Jan, 13:37


#እስቲ_ለአላማ_ኑር!

ህይወትህን ለአላማ ኑር! ትኩረትህን ያለህ ነገር ላይ መባረክህ ላይ አድርግ። በሌለህ ነገር ከምትማረር ከምትሰላች ተስፋ ከምትቆርጥ ስላለህ ነገር አመስግን። ባለህበት ቦታ ጥቅምህን አስቀጥል። ማግኘትህን አካብት። የሌለህ ያ- ፍላጎትህ ራሱ ዳዴ ብሎ፣ ድክ ድክ እያለ፣ እየተረመደ ከዛም በፍጥነት እየሮጠ ወዳለህበት እንዲመጣ ያለህን ነገር ተጠቀምበት።

እድለቢስ ስለመሆንህ አትብሰልሰል። ጥንካሬ እና ብርታት አሻግሮ፣ አርቆ፣ አልሞ ማሰብ ከተቻለህ እድል ከፈጣሪ ዝቅ ሲል አንተ ለራስህ የምታመቸው ስራ ማለት ይሆናል።

ከድክመትህ ይልቅ ለጥንካሬህ ቦታ ስጥ። ከሚያልፈሰፈስህ ስንፍና የሚያበረታህን ጉብዝና ምን እንደሆነ ለይ።

ራስህን ሁን- ማንነትህን፣ አስተሳሰብህን ለሌሎች ለማረጋገጥ አትድከም፤ ከዛ ተሻልና ስለራስህ- ለራስህ ሃላፊነት ይሰማህ።

ከሁሉም በይበልጥ ደግሞ አዎንታዊ አመለካከት እና የተረጋጋ አእምሮ ይኑርህ።

ያለህበት አሁናዊ ሁኔታ ምንም ይሁን ምን፣ የሌለህን ሳይሆን ያለህን በረከትህን ቁጠር፤ ያንን ኮትኩት፣ አሳድግ፣ አበልጽግ የሌለህ ዳዴ፣ ድክድክ፣ ረመድመድ፣ እሎጥ እሮጥ እያለ ይቀርብሃል።

☑️ ህይወትህ ምን ያህል ውብ እንደሆነ እወቅ። አንተ ያለህ ሌሎች የሌላቸው ምን እንደሆነ ለይ- ተረዳ።

@lifeandwisdom

ህይወትን በጥበብ

23 Jan, 15:13


#ከዜሮ_መጀመር_አልፈራም

ሰው ሁኔታን መቀበል ስለማይችል ነው በሁኔታ የሚጎዳው፤ ዛሬ ካጣህ፣ የለመድከው ነገር ከቀረ፣ ከነገሮች ጋር ራስን ማዋሃድ ነው ያለብህ በቃ!

የሚቀሩብህ ነገሮች ይኖራሉ፤ ለዛሬ ይቅሩ፤ ነገ ይደርሳሉ።

እኔ አሁን ማጣትን አልፈራም፤ ከዜሮ መጀመር አልፈራም፤ ዜሮ ደግሞ ብሩ እይደለም። እኛ ብር አይደለም የሚከብደን- ሰው ነው የሚከብደን፤

አሁን እኔን «በየ ፖድካስቱ ለፍልፎ ይሀው ዜሮ ገብቶ. . . መክሮን ይኸው ዛሬ ዜሮ ገባ. . . .» ቢሉ አልፈራውም! እወጣዋለሁ! እንዲያውም ታሪኬን ያሳምርልኛል።

አንተ ውስጥህ ሰላም ከሆነ፣ ጤና ካለህ ምን ያስፈልጋል? ሁሉም ነገር ያለው አእምሮ ውስጥ ነው፤ ሁሉም ነገር ጨዋታው ያለው አእምሮ ውስጥ ነው!

@lifeandwisdom

ህይወትን በጥበብ

22 Jan, 13:30


መሉ በሙሉ በኢትዮጵያ ብር ተዋውለው ወዲያውኑ ቤትዎን ይረከቡ።

በመሀል ልደታ ላይ የሚገኝ ባለ 9 ወለል ዘመናዊ የመኖሪያ አፓርትመንት

100% የተጠናቀቀ እና fully furnished

ሁለት ቤት ብቻ ቀርተውታል!

3ኛ ወለል ላይ 173 ካሬ ባለ 3 መኝታ

8ኛ ወለል ላይ 151 ካሬ ባለ 3 መኝታ

አፓርትመንቱ የተማሉለት

-ሊፍት
-መጠባበቂያ ጀነሬተር
-ውሀ
-ፓርኪንግ
-ሰገነት

በካሬ ከ 95ሺ ብር ጀምሮ

እውነተኛ ገዢ ከሆኑ ቅናሽ ይደረግሎታል

ለበለጠ መረጃ ይደውሉ:
📞09 36 04 06 30

ህይወትን በጥበብ

15 Jan, 06:11


Invest in yourself



" ለሰው ልጅ ሁሉ እኩልና ያለስስት የተሰጠ ሀብት ቢኖር ጊዜ ነው ። ጊዜህን መጠቀም ስትችል እራስህን ትለውጥበታለህ...ራሥህን መለወጥ ሥትችል ሌሎችንም ትለውጣለህ ። ራስህን ለመለወጥ ጊዜን ካልወሰድህ ሌላን መለወጥ አትችልም ። ( Invest in your self )ራስህ ላይ ፈሰስ አድርግ መጀመርያ ራስህን ለውጥ ። አስተሳሰብህን ሞርድ ፣ እይታህን አጥራ ፣ ንግግርና እርምጃህን ገምግም ነገ የሚኖርህ ዛሬን ስትጠቀምበት ነው ። ከዛሬም ያለህ ጊዜ አሁን ነው...አሁን ደግሞ እያለፈ ነው! ጥያቄው እንዴት እያለፈ ነው የሚለው ነው ። ለዚህ ጥያቄ የምትመልሰው መልስ #ነገ በምትለው ምናባዊው ቀን ላይ ያለህን አንተነት ይወስነዋል ። "

ዛሬህን ተጠቀምበት...

@lifeandwisdom

ህይወትን በጥበብ

07 Jan, 06:02


እንኳን ለብርሃነ ልደቱ በሰላም አደረሳችሁ
በዓሉ የደስታ፣ የፍቅር እና የጤና እንዲሆንልላችሁ እመኛለሁ


🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄

ህይወትን በጥበብ

24 Dec, 05:49


#አታስመስል_የሆንከውን_ሁን!

በትክክል የሆንከውን ሆነህ መታየት ስትጀምር ሕይወትህን በከፍተኛ ደረጃ መለወጥ ትጀምራለህ።

የሆንከውን ሆነህ መታየት ስትጀምር፣ አላስፈላጊ መረጃዎችን እንዲቆሙ ታደርጋለህ።

በዚህም ራስህን እንደምትወድ ብቻ ሳይሆን፣ ዋጋ ያለህ መሆንህንም ለዓለም ታውጃለህ።

ከዚያ እሴቶች ብቻ ሳይሆን ሊያስፈልግህ የሚችል ሁሉም ነገር ይኖርሃል።

የምትፈልገው ቦታ ስትደርስም ባለመርህ ብቻ አትሆንም።

የሆነ ሰው ሲያፈቅርህም ደስተኛ ብቻ አትሆንም። እንደሆንከው ሆነህ ስትመጣ ይህንን አካሄድ ታፋልሳለህ።

ከዚህ በኋላ የሕይወት መልካምነት ምናልባት ላትሆን ለምትችለው ለተሻለው አንተነትህ የተያዘ አይደለም።

እንዴት መታየትና ስሜትህን ማሳየት መፍቀድ መጀመር እንዳለብህ ከማወቅህ በፊት፣ በተፈጥሮ ጥሩ ስሜት የማይሰማህ ለምን እንደሆነ ለራስህ ማብራራት ለአንተ ሁልጊዜ ጨዋታ ነበር። አሁንም በጨለማ ውስጥ የምትኖር ከሆነ፣ ያንን ማፈንና በሌሎች ጉዳዮች ላይ ማሳየት ነበረብህ።

ዛሬ የሆንከውን ሆነህ እየታየህ፣ ለምናባዊው አንተነትህ የሚገባውን ሳይሆን፣ የአንተ የሆነውን ትወስዳለህ። ዓለም የሚሰጥህ ያስብልኛል ብለህ የምታስበውን ሳይሆን፣ አንተ፣ እዚህ፣ አሁን የምታስበውን ነው።

#እውነተኛ_ፈውስ_ያ_ነው።

ልክ ልክህን እየነገረ ምርጥ ጓደኛ የሚሆንህን #ተራራው_አንተ_ነህ_መጽሐፍ ደግሞ እንድታነበው ትጋበዛለህ

@lifeandwisdom

ህይወትን በጥበብ

10 Dec, 05:29


#5ቱ_የእርጋታ_በረከቶች

ብዙ ሰዎች ይህን ለማወቅ አመታት ፈጅቶባቸዋል። አንተ ግን እኒህ እውነታዎች በማንበብ ብቻ፤ አሁን ልታውቃቸው እና ልትተገብራቸው ይቻላል።

#አንደኛ እስኪ… ቀስ ብለህ ተራመድ። እስኪ...ቀስ ብለህ ተናገር። ምክንያቱም ብዙ ሰዎች ቸኩሎ የመሄድና ፈጥኖ የመናገርን ስሜት ሊቆጣጠሩት አይችሉም። አንተ ልዩ ለመሆን እድሉ አለሁ።

ወዳጄ '' የረጋ ወተት ቅቤ ይወጣዋል።''

#ሁለተኛ ሰዎችን ስታገለግል የበለጠ ሃይል እንደሚኖርህ ተረዳ። መኮፈስ የሚባለውን አላዋቂነት በጊዜ ብትተወው ሰው ለመሆን ትበቃለህ።

#ሶስተኛ የበዛ ራስ ወዳድነትህን ዜሮ እስኪደርስ ገሸሽ አድርገው።

#አራተኛ ሁሌም በየቀኑ ለሰዎች አንድ ነገር ማድረግን ልመድ። ምንም አጸፋ፤ ምትክ ባለመጠበቅ በለጋስነት የመቆም ብቃት ይኑርህ።

#አምስተኛ። ሰዎች ንቀት ባሳዩህ ጊዜ ዝምታህ ይብለጥ። ክብርህ አንተው ጋር እንደሆነ እስኪገባቸው ድረስ፤ አይኖቻቸውን አትኩረህ ተመልከት።

☑️ እስኪ ባንተው አቅም ለሰዎች ምን ማድረግ ትችል ይሆን? ሀሳብህን አካፍለን፡፡

@lifeandwisdom

ህይወትን በጥበብ

30 Nov, 11:38


እውነት...?
(በፍልስፍና...!)

፨፨፨

ሱፊስቶች ስለ እውነት ይህንን እይታ ያስቀምጣሉ
<< እውነት የሚመጣው ከስሜት ነው። ስለዚህም የእውነት ጥያቄ ምላሹ ስሜትህ ነው።...ስለዚህም እውነት ማለት የምትቀምሰው፣ የምታሸተው፣ የምትነካው፣ የምትሰማውና የምታየው ነገር ነው። >> ይላሉ
ይህንን እይታ ካልተቀበሉት ፈላስፎች ግንባር ቀደሙ ፕሌቶ ነበር እሱም እንዲህ አለ...
<< እውነት ማለት ሱፊስቶች እንደሚሉት ስሜትህ ከሆነ እውነት የለም ማለት ነው። ምክንያቱም እያንዳንዱ ሰው አንድን ነገር የሚያሸተው፣ የሚነካው፣ የሚቀምሰው፣ ወዘተ...በተለያየ መንገድ ነውና። >>

፨ አንድን ነገር ሁለት ሰዎች በሁለት መንገድ ከሰማው ወይም ካየው ነገሩ አንድ መሆኑ አብቅቷል፤ ስለዚህ ነገሩ በራሱ እውነት አይደለም! እያለን ነው እንግዲህ ፕሎቶ...!

<< ስለሆነም የእውነት ጥያቄ የሚመለሰው በምክንያታዊ ማሰብ(Reasoning) እንጂ በስሜት አይደለም።...አንድን ነገር ለማየት ማሰብ ያስፈልጋል። አስቀድመህ የምታስበው ነገር ወደ አይንህ መልእክት አስተላልፎ የምታየውን ማየት ቻልክ፤ በሌላ አባባል የምታየው እውነት መሆኑን በማሰብህ ነው፤ ስለዚህ እውነት ማለት 'ማሰብ' ነው ። >> ይላል ፕሉቶ



የጠርጣሪነት ፍልስፍና መስራች የሆነው #ፊሮ ደግሞ የሱፊንም ሆነ የፕሌቶን አስተሳሰብ አይቀበልም ያንንም አስመልክቶ ይህንን ይለናል...
ስለ ሱፊዎች እምነት...
<< የምታየውን እንዴት ማመን ትችላለህ?...ፀሐይ ከመሬት እጅግ ብዙ እጥፍ ግዙፍ እንደሆነች እናውቃለን። ነገር ግን መሬት ላይ ቆመን ፀሐይን ስናያት ትንሽዬ ነች። ስለዚህ የምናየው ነገር ሁሉ እውነት አይደለም ማለት ነው። >>
ስለ ፕሎቶ እና አርስቶትል እይታ...
<< እንግዲህ አንድን ነገር እውነት የሚያደርገው ማሰብ ስለቻልን ከሆነ፦ ሰው የሚያስብ ፍጡር ነው፤ ሶቅራጥስ ደግሞ ሰው ነው፤ ስለዚህም ሶቅራጥስ ሰው ስለሆነ ማሰብ ይችላል ማለት ነው። ይኽ ደግሞ ሁልጊዜ አይሠራም ምክንያቱም ሰው ሁሉ ማሰብ ይችላል ማለት ሞኝነት ነውና። >> ይለናል ፊሮ



ከሁሉም በተለየ መልኩ የሱፊ እምነት ተከታይ የነበረው ጎርጂያስ ደግሞ እውነትን በተናጋሪው የንግግር እና የማሳመን ችሎታ ይመነዋል ያንንም አስመልክቶ ይህንን ይለናል...
<< እውነት የሚባል ነገር የለም፤ ቢኖር እንኳን ነገሩን ነገሩን እውነት የሚያደርገው የአንተ ተናግሮ የማሳመን ችሎታ እንጂ የነገሩ እውነትነት አይደለም >> ይላል ሲያብራራው ደግሞ ይህንን ያክልበታል...
<< ምንም ነገር የለም፤ አንድ ነገር ቢኖር እንኳን መኖሩን ማወቅ አንችልም፤ ማወቅ ብንችል እንኳን ስለዚያ ነገር ማስረዳት አንችልም፤ ምክንያቱም አለ ብለን የምናስበው ነገር የለምና፤ ስለዚህም አለ ብለን ነገሩን ስላሰብን ብቻ እንዴት በድፍረት አለ ብለን እንፈርዳለን>> ይለናል...
በምሳሌ ሲያብራራው ደግሞ ይህንን ያክላል...
<< ለምሳሌ አንድን ነገር ሁለት ሰዎች እንዴት እንደሚያዩት ብትጠይቅ በጣም የተለያየ መልስ ታገኛለህ፤ ስለነገሩ አስረዱኝ ብትላቸው ደግሞ ከሁለቱ ሰዎች የአንዱ ንግግር ስለነገሩ የበለጠ ሊያሳምንህ ይችላል። ለዚህም ነው ነገሮች እውነት ናቸው ብለን እንድናምን የተሻለ ተናጋሪ ሰው መፍጠር አለብን የምንለው...>>



ምንጭ ፦ ጥበብ ከጲላጦስ ቅጽ ፩ ( 4 በ 1)
፨ መቼም በፍልስፍናው ዓለም እውነትን በተመለከተ ዛሬም ድረስ የሚያስማማ እይታ ማግኘት አልተቻለም...በርግጥም የፍልስፍና አላማው መስማማት አይደለምና...ዛሬ ላይ #እውነትን በተመለከተ ያሉት እይታዎችም በዚህ ዙርያ የሚሽከረከሩ ይመስለኛል...
፩, እውነት አለ #ፍጹማዊም ነው
፪, እውነት አለ ግን #አንፃራዊ ነው
፫, እውነት ብሎ ነገር #የለም...!!


@lifeandwisdom

ህይወትን በጥበብ

17 Nov, 14:39


#በመሬት_ልብ_ውስጥ_ያለው_ወርቅ

በአንተ አእምሮ ውስጥም አለ!

ሀሳብ የመፍጠር ኃይል ነው ወይም የፈጠራ ኃይል እንዲንቀሳቀስ ማድረግ የሚችል ተጽዕኖ ፈጣሪ ኃይል ነው፡፡

በተወሰነ መንገድ ማሰብ ሀብትን ወደ እናንተ ያመጣል፡፡ ነገር ግን ለተግባራችሁ ትኩረት ሳትሰጡ በሀሳባችሁ ላይ ብቻ መተማመን የለባችሁም፡፡

ብዙ ሳይንሳዊ ሜታፊዚክስ አሳቢዎች የሚሰናከሉበት አለት ይህ ነው፡፡ ሀሳብን ከግለሰባዊ ተግባር ጋር ማገናኘት አለመቻል፡፡

ካለ ተፈጥሯዊ ሂደቶች ወይም ካለ ሰው ልጅ ጣልቃ ገብነት ነገሮችን ከቅርጽ አልባው ንጥረ ነገር መፍጠር ይቻላል ብለን ብንል እንኳን የሰው ልጅ እንደዚህ አይነቱ የእድገት ደረጃ ላይ አልደረሰም፡፡

#ሰው_ማሰብ_ብቻ_ሳይሆን_ያለበት፣ የግል ተግባሩም ሀሳቡን የሚያሟላ መሆን አለበት፡፡

በመሬት ልብ ውስጥ ያለውን ወርቅ በሀሳባችሁ ኃይል ወደ እናንተ እንዲመጣ ማድረግ ትችላላችሁ፡፡ ነገር ግን ወርቁ እራሱን ከመሬት አውጥቶ፣ አጣርቶ፣ ቅርጽ ያለው ሳንቲም አድርጎ በጎዳናዎች ላይ እየተሽከረከረ ወደ ኪሳችሁ አይገባም፡፡


@lifeandwisdom

ህይወትን በጥበብ

24 Oct, 08:44


#በምንም_ሁኔታ_የማይበገር_ሁን!


#1_አይበገሬነትህን_ተቀበለው!

ውስጥህ የተደበቀ አይበገሬነት አለ፤ ሁሉም ሰው ይህ ተፈጥሮ አለው። ይህ አይበገሬ ማንነት የማይፈራ፣ የሚተማመንና የትኛውንም ነገር ማሳካት የሚችል ነው። በዚህ መጽሐፍ የምትማረውም ድጋሚ ይህን ተፈጥሯዊ ማንነት ስለመቀበልና ስለማግኘት ነው።

#2_ከምቾት_ቀጠናህ_ውጣ

እድገትህ ያለው ከምቾት ቀጠናህ ማዶ ነው። ከግቦችህ እና ይገባኛል ከምትለው የተሟላ ሕይወት የሚያደርስህን ቁልፍ የምታገኘውም ምቾት ማጣትንና አደጋን መቀበል ስትጀምር ነው።

#3_ራስህን_ማነጻጸር_አቁም

ስለራስህ ያለህን ዋጋ ለማሳነስ ፈጣኑ መንገድ ራስን ከሌሎች ማነጻጸር ነው። የራስህ መንገድና ጉዞ ላይ ብቻ አተኩር፤ ያንተ በሆኑ ጥንካሬዎችህና ስኬቶችህ ተደሰት።

#4_በራስህ_እመን

መድረስ ከሚገባህ ታላቅነት እንዳትደርስ ገድቦ የያዘህ ብቸኛው ነገር የራስህ ጥርጣሬ ነው። ራስህ ላይ ያለህን መተማመን በማጎልበት እውነተኛ አቅምህን የማውጣት እና እስከ ጥግ የመጠቀም አቅም አለህ።

#5_ገዳቢ_እምነቶችህን_ጣል

እነዚህ ገዳቢ እምነቶች ለራስህ ይህን እችላለሁ፣ ይህን ደግሞ አልችልም እያልክ የምትነግረው የተሳሳቱ አመለካከቶች ናቸው። እነዚህን አመለካከቶች ለይ እና ሞግታቸው፣ አስወግዳቸው። በቦታቸው የሚያበረቱ፣ የሚያነቃቁ ግቦችን ተካ።

#6_ሐብት_ይገባሃል!

የምትፈልጋቸውን ነገሮች ለማሟላት ገንዘብ ያስፈልግሃል። ገንዘብ መስራት፣ ሐብት ማካበት እንደምትችልና እንደሚገባህ እመን። አቅሙ አለህ። ዋናው ነገር ጥበቡን ማወቅ ነው!

#7_ገንዘብ_ኃይል_ነው!

ገንዘብ ያንተን እምነትና ድርጊት መሰረት አድርጎ ከአንተ የሚወጣ እና ወደ አንተ የሚመጣ ኃይል ነው። ስለዚህ ስለ ገንዘብ የሚኖርህ አመለካከትና ድርጊት ገንዘብን ወደ አንተ እንዲፈስ እንጂ ከአንተ እንዲወጣ የሚያደርግ እንዳይሆን ተጠንቀቅ!

@lifeandwisdom

ህይወትን በጥበብ

13 Oct, 12:36


#ስሜትህን_ቀይር!

አንድ ማወቅ ያለብህ ነገር ስሜትህን መቀየር እንደምትችል ነው።

ነገር ግን እንዴት የገባህበትን ከባድ ስሜት ወደተሻለ ስሜት መቀየር ትችላለህ? ከባድ ጥያቄ ይመስላል።

በትክክል ቀላል አይደለም። ልምምድ ያስፈልገዋል።

ህምምም... እንበልና የሆነ ሰው አበሳጨህ፣ ዝቅ አድርጎሃል! ጉዳት ተሰምቶሃል እና? በመጀመሪያ ስሜቱን አትካደው ነገር ግን ለምን እንደዛ ሊሰማህ እንደቻለ ራስህን ጠይቅ... ምናልባት ያ ሰው እንደዛ እንዲሰማህ አልፈለገም... ምናልባት ያ የራስህ የአረዳድ ችግር ይሆናል... ምናልባት ያለብህ የበታችነት ስሜት... ምናልባትም ለዛ ሰው ያለህ ድብቅ ጥላቻ... ወይም በትክክል ያበሳጨህ ሰው ሆን ብሎም ሊሆን ይችላል።
የፈለገ ይሁን የሚረብሽ ስሜት ለምን ውስጥህ ቀረ? ይሄን ጥያቄ ምትመልሰው አንተ ሁነህ ሳለ እኔም የምጠቁምህ ነገር ይኖራል።

እዚህ ጋር- ህይወት ሁሌም ደስታ፣ መፈለግ፣ ማግኘት፣ እኩል መሆን፣ ስኬት እንዳልሆነች ተገንዘብ። ብስጭት ወይም የስሜት መረበሽ ሲያጋጥምህ ዝም ያለ ቦታ ሂድ፤ ከራስህ ጋር በፍቅር ተነጋገር። የመጥፎ ገጠመኞችን ጥሩ ጎን ለማየት ራስህን በአዎንታዊነት እንዲመራ አስገድድ።

የበደለህን ይቅር በለው ጤና ይሰጥሃል። የተበላሸብህ ነገር ደግመህ ሞክረው- ጥንካሬን ስለምታገኝ። ደስተኛ ለመሆን ቻል መከፋት ሲረዝም በብዙ ስለሚያሳጣ። ፈጣሪህን አመስግን- የተሻለ ስለምታገኝ። ካንተ የባሰበትን ተመልከት መጽጽናናት ስለሚሆንልህ። ካንተ የተሻለውን አስተውል- ተስፋ ስለሚጎበኝህ። ስለገጠመኝህ ሰዎችን አማክር- መፍትሄ ስለሚሰጡህ። ጸልይ፣ ለብቻህ ተደብቀህ አልቅስ- ለእፎይታህ።

@lifeandwisdom

ህይወትን በጥበብ

09 Sep, 13:26


መሳጭ ከሆኑ የፈላስፋው #ኮንፊሽየስ ንግግሮች በጥቂቱ...

<< የታላቅ ሰው ታላቅነት የሚገለጸው #በተግባሩ እንጂ #በንግግሩ አይደለም። የተግባር መሰረቱ ደግሞ #ጽኑ_ፍላጎት ነው።....የአንድን ተራ ሰው ጽኑ ፍላ ፍላጎት ከውስጡ ከመውሰድ፣ የአንድን ታላቅ ሃገርን የጦር አዛዥ መማረክ ይቀላል። >>



<< ሰዎች እያወሳሰቧት እንጂ ሕይወት ቀላል ናት...ሰዎች በጨለማው ላይ ከሚያፈጡና ከሚያለቅሱ ይልቅ አንዲት ሻማ ቢለኩሱ ለጨለማው ችግራቸው በቀላሉ መፍትሄ ያገኛሉ። >>



<< ታላቅ ሰው ችሎታውን ለማሳየት አይሽቀዳደምም...የአላዋቂን ሰው ስንፍና ልኩን የሚያውቅ አዋቂ ሰው ብቻ ነው። እናም በሌሎች ዘንድ ለመታወቅ ከመድከም ይልቅ ልታወቅ የሚገባኝ ነኝ በሚለው እምነት ውስጥ ሞልተህ ተቀመጥ። የእውቀቱ አንዱ ጥቅሙ በራስ መተማመንን ማምጣቱ ነውና።...ታላቅ ሆኖ ሳለ ነገር ግን ታላቅነቱ ባለመታወቁ የማይናደድ ሰው እሱ በእርግጥ ታላቅ ነው። >>



<< አንድን ነገር መቼም ላውቀው አልችልም በሚል ስሜት ተማረው፤ ስታውቀው ደግሞ ላጣው እችላለሁ በሚል ስሜት አጥብቀህ ያዘው። >>

@lifeandwisdom

ህይወትን በጥበብ

02 Sep, 17:12


#ይሄኔ_የት_በደረስኩኝ_ነበር?!

• ሰዎች በእኔ ላይ ምን እንደሚያስቡ ለማወቅ የታገልኩትን ያህል ራሴን ለማወቅ ብሰራ ኖሮ . . . ይሄኔ የት በደረስኩኝ ነበር?!

• በፍጹም የማይፈልጉኝን ሰዎች ስለማመጥና ስከታተል ያሳለፍኩትን ጊዜ ለእኔ ዋጋ ላላቸው ሰዎች ሰጥቸው ቢሆን ኖሮ . . . ይሄኔ የት በደረስኩኝ ነበር?!

• በማያገባኝ የሰዎች ስራና ሃሳብ ላይ በማውራትና በመቃወም ያባከንኩትን ጊዜ የሚደገፍ ሰው ፍልጌ ደግፌ ቢሆን ኖሮ . . . ይሄኔ የት በደረስኩኝ ነበር?!

• በየጊዜው ካለእቅድ የማወጣቸውን የገንዘብ መጠኖች በጥንቃቄ ብቆጥባቸው ኖሮ . . . ይሄኔ የት በደረስኩኝ ነበር?!

• ምንም ያህል ብጨነቅ መለወጥ በማልችላቸው ነገሮች ላይ መጨነቄን ትቼ ለመለወጥ አቅም ያለኝ ነገሮች ላይ አተኩሬ ቢሆን ኖሮ . . . ይሄኔ የት በደረስኩኝ ነበር?!

• የሚወዱኝ ቤተሰቦቼና ጓደኞቼ ሲመክሩኝ የመስማትና ጥሩውን ምክር የመቀበል ልማድ ኖሮኝ ቢሆን ኖሮ . . . ይሄኔ የት በደረስኩኝ ነበር?!

• ለመጀመር ያሰብኳቸውን እነዛን ወሳኝ ነገሮች ጀምሬያቸው ቢሆን ኖሮ . . . ይሄኔ የት በደረስኩኝ ነበር?!

• የማይሆኑ የማሕበራዊ ጎጾች ሳስስ ያመሸሁባቸውን ምሽቶች የቀኑን ውሎየን ለመገምገምና ለነገ በማቀድ ባሳልፋቸው ኖሮ . . . ይሄኔ የት በደረስኩኝ ነበር?!

• ለየእለት ገጠመኞች ምላሽ እየሰጡ ከመሯሯጥ ይልቅ በራእይና በዓላማ ኖሬ ቢሆን ኖሮ . . . ይሄኔ የት በደረስኩኝ ነበር?!

ያም ሆነ ይህ ያለፈው አልፏል! ከጥቂት አመታት በኋላ እንደገና “ይሄኔ የት በደረስኩኝ ነበር?!” የሚል የግምገማ ስሜት እንደሚመለስብኝ ስለማውቅ አሁኑኑ ለውጥን አመጣለሁ።

@lifeandwisdom

ህይወትን በጥበብ

15 Aug, 07:03


#4ቱ_ሰዎች_የሚለወጡባቸው_ጊዜያት

#1_በከባድ_ህመም_ውስጥ_ሲሆኑ

በህይወት ውስጥ የሰው ልጅ ከባድ ጊዜያቶችን ሲያሳልፍ ህይወቱን ለመቀየር ግድ ይሆንበታል። የመለወጥ ፍላጎት ባይኖረው እንኳን ህመሙን ላለመሸከም ነገሮችን ሳይፈልግ እንዲቀይር ይገደዳል።

#2_ሰዎችን_አይተው_ሲነሳሱ

አድርገው የሚያሳዩ መልካም ምሳሌዎችን መመልከት እኔም እችላለሁ የሚል ስሜት በውስጣቸው ያጭራል። የእነሱንም ፈለግ በመከተል ብዙዎች ራሳቸውን ይቀይራሉ።

#3_በቂ_ሲያውቁ

እውቀት ብርሀን ነው። በብርሀን አይናችን ዙሪያውን እንዲያይ እንደሚረዳው እውቀትም አእምሯችን ችሎታውን እንዲያይ ይረዳዋል። የመለወጥ አቅሙ እንዳላቸው ሲያውቁ "ለምን አልለወጥም?" የሚል የመለወጥ ፍላጎት ይፈጠርባቸዋል።

#4_ውጫዊ_ለውጦች

በህይወት የሚከሰቱ ለውጦች ሰውዬውንም የመለወጥ አቅም አላቸው።
የጊዜ መለወጥ፣
የአካባቢ ለውጥ፣
የኑሮ ደረጃ መሻሻል፣
ታዋቂነት፣
በህይወት የሚመጡ መልካም እድሎች ሰውን ይቀይራሉ።

እስቲ በህይወታችሁ የለወጣችሁን አጋጣሚ ኮሜንት ላይ አጋሩን!

መልካም የለውጥ ጊዜ!!!

@lifeandwisdom

ህይወትን በጥበብ

23 Jul, 13:13


" ስሞት ዘቅዝቃችሁ ቅበሩኝ ራሱን ዝቅ ያደረገ አንድ ቀን ከፍ ማለቱ አይቀርምና "

/ ዲዮጋን /

ተአምረኛው ዲዮጋን እቺን የተናገራት በጊዜው የነበሩት ባላባቶች ሥለ አቀባበራቸው ይጨነቁ እንደነበር ባስተዋለ ጊዜ ነው ። ሕይወትን እንዴት እንደሚኖራት ያላወቀ ሰው ስለሞት እና በክብር ሥለመሞት ሲያስብ እና ሲጨነቅ ማየት አሁን አሁን በእኛም አገር የተለመደ እውነታ ነው ። በውድ የሬሳ ሳጥን መቀበር እና በአበባ መሽቆጥቆጥ በህይወት እያለ አንድ አበባ እንኳን ተክሎ የማያውቅ ሁሉ ሲሞት በአበባ ይከበባል የኛ ሰው በቁሞ ሳይሆን ሞቶ ውድ ነው መሰል...!



በግብፃውያን ዘንድም ፈርኦኖች ሲሞቱ በዛኛው አለም እንዳይፈሩ ተብሎ ሎሌያቸው ከነሕይወቱ በፍቃዱ አብሯቸው ይቀበር እንደነበር የታሪክ ድርሳናት ይናገራሉ...ዛሬም ከነመኪናቸው የተቀበሩ ዜጎች እንዳሉ መረጃዎችን በየሚዲያው እንሰማለን...የጆሮ ስብአቱ አለመሙላቱ ... ነውና መቻል ነው እንግዲህ

" እንዴት እንደምትኖር ካላወቅህ ሥለሞትህ ልትጨነቅ አይገባም ። "
/ ኮንፊሺየስ /


@lifeandwisdom

ህይወትን በጥበብ

17 Jul, 08:41


#ራሳችሁን_አትሰሩ!

ሰዎች ምን ይሉኛል እያላቹ ብቻ የምትኖሩ ከሆነ፣ ጥረታቹ ሁሉ ሰዎችን impress ለማድረግ ከሆነ፣ ጥሩ ስሜት የሚሰማቹ ሰዎች ሲያደንቋችሁና ሲፈልጓቹ ከሆነ፣ ሁሌም ተቀባይነት ለማግኘት ብቻ የምትኖሩ ከሆነ፣ በሰዎች ጥፋት ራሳችሁን የምትወቅሱ ከሆነ፣ እመኑኝ እስር ቤት ውስጥ ናችሁ።

ሰዎች ሁለንተናችንን እንዲቆጣጠሩት አንፍቀድ። ሰዎች ምን ይላሉ ከሚለው በላይ ምን መሆን አለበት ብለን እንጠይቅ። ዋጋችን ራሳችን ውስጥ እንጂ ሰዎች ውስጥ እንደሌለ አንርሳ። ሰዎችን ብቻ ስንከተል ራሳችንን እንዳናጣ እንጠንቀቅ።


@lifeandwisdom

ህይወትን በጥበብ

01 Jul, 06:33


ፍላጎትን ለፍርሃት የማስበለጥ ስኬት

“እንዲሳካልህ ከፈለክ፣ ካለብህ የመውደቅ ፍርሃት ይልቅ ለስኬት ያለህ ፍላጎት ሊልቅ ይገባዋል” – Bill Cosby

ከልባችን ያልተጸየፍነውን ነገር አንሸሸውም፤ በጽኑ ያልፈለግነውንና ያልተከታተልነውን ነገር ደግሞ በፍጹም ልንደርስበት አንችልም፡፡ የአንድ አንድ ሰው ሕልም በትምህርት አንድ ደረጃ መድረስ ነው፡፡ የሌሎች ሕልም ደግሞ ቤተሰባቸው አሁን ካለበት ችግር ማላቀቅ ነው፡፡ ከዚህም ባለፈ ሁኔታ፣ በስራ፣ በግል ጤንነት፣ እና በሌሎች ሁኔታዎች አንጻር ሰዎች ግብን አውጥተው እዚያ ለመድረስ ይጣጣራሉ፡፡ የእነዚህ ሁኔታዎች መሳካት የአጠቃላይ ሕይወት መሳካት ባይሆንም የስእሉ አካል ስለሆኑ አስፈላጊ ጉዳዮች ናቸው፡፡

በዚህ ሰው ሁሉ በሚጋራው አንድ ደረጃ የመድረስ ጉዞ ውስጥ ማንንም የማይምር አንድ ችግር አለ፤ እርሱም የፍርሃት ችግር ነው፡፡ ሁላችንም ቢሆን በአንድም ሆነ በሌላ መንገድ የምንፈራቸው ነገሮች አሉን፡ የመውደቅ ፍርሃት፣ ስኬት የማጣት ፍርሃት፣ ተቀባይነት የማጣት ፍርሃት፣ ጀምሮ የማቋረጥ ፍርሃት …፡፡ በአጭሩ፣ ከፍርሃት ነጻ የሆነ ሰው የለም፡፡ ይህንን ሰው ሁሉ የሚጋራውን ፍርሃት የተሰኘውን ተራራ አልፎ ወደ አላማ ለመዝለቅና ወደግባችን ለመድረስ ያለን የውስጥ ፍላጎት ካለብን ስጋትና ፍርሃት በብዙ እጥፍ ሊጠነክር ይገባዋል፡፡

ለመራመድ ያሰብከውን እርምጃ አስበውና ያንን ነገር ለማድረግ ያለህን ፍላጎትና በውስጥ የምትፈራውን ነገር በሚዛን ላይ አስቀምጣቸው፡፡ የትኛው ያመዝናል? ፍርሃቱ ካየለ ወደኋላ ያስቀርሃል፣ ፍላጎቱ ካየለ ግን ፍርሃትህን አሸንፈህ እንድትዘልቅ ብርታት ይሆንሃል፡፡ ፍላጎትህን ከፍርሃትህ ለማስበለጥ ከፈለክ ደግሞ ክምትወስደው እርምጃ የተነሳ የምታገኛቸውን ወሳኝ ለውጦችና ጥቅሞች ማሰብ፣ ማወቅና ማሰላሰል ያስፈልጋል፡፡

@lifeandwisdom

ህይወትን በጥበብ

13 Jun, 18:23


#15ቱ_የታላላቅ_ሰዎች_ታላላቅ_አባባሎች

#አንድ
ከሰዎች ጋር ሮጠህ ያልደረስክበት ነገር ካለ ወደ ተነሳህበት ተመልሰህ ከፈጣሪህ ጋር መሮጥ ጀምር፣ ያኔ ካሰብክበት ሳይሆን ካሰበልህ ቦታ ትደርሳለህ፡፡

#ሁለት
በአብዛኛው ጊዜ ሴቶች የፍቅርን ትርጉም የሚጠፋባቸው
በውበታቸው ማምለክ ሲጀምሩ ሲሆን ወንዶች ደግሞ በገንዘባቸው ማምለክ ሲጀምሩ ነው፡፡

#ሶስት
መጀመሪያ ለራስህ ራስህ መሆን ስትጀምር ለማን ምን መሆን
እንዳለብህ ትገነዘባለህ፡፡

#አራት
የሰው ልጅ የማሰብ ችሎታው ሲጨምር የጓደኞቹን ብዛት ይቀንሳል፡፡

#አምስት
ዝቅተኛ እውቀት ባለህ ቁጥር የምትተኛው እንቅልፍ ከፍተኛ
ይሆናል፡፡

#ስድስት
ጓደኛን አለማመን ከመካድ የከፋ ነው፡፡

#ሰባት
የራስህን ትኩስ እንጀራ ለመጋገር ስትል የሌላውን ቂጣ አትርገጥ፡፡

#ስምንት
አንዳንድ ሰዎች የሚወድቁት ሌሎችን በሁለት እግሮቻቸው ለመርገጥ ሲጣጣሩ ነው፡፡

#ዘጠኝ
ሰው ከጊዜ እና ከማጣት ብዙ ይማራል፡፡

#አስር
አንዳንዴ ሽንፈትም ከድል የበለጠ ዋጋ አለው/ ከማሸነፍ ይልቅ በመሸነፍ ውስጥ ብዙ እውቀት አለ፡፡

#አስራአንድ
ሠው የበለጠ እያገኘ በሄደ ቁጥር የበለጠ ስግብግብ እየሆነ ይሄዳል፡፡

#አስራሁለት
ሠዎች ትርጉም ያለው ሥራ መስራት ካልቻሉ የመኖር ትርጉምም ይጠፋባቸዋል፡፡

#አስራሶስት
የሰው ልጅ ከደስታው ይልቅ የሀዘኑን ጊዜያት መቁጠር ይወዳል፡፡

#አስራአራት
ባንኮች ዝናብ ሳይኖር ዣንጥላ ያበድሩህና መዝነብ ሲጀምር ግን ዣንጥላውን ይነጥቁሃል፡፡

#አስራአምስት
አዋቂ ሆኖ ለመታየት የምናደርገው ጥረትና ከንቱ ድካም አላዋቂ አድርጎ ያስቀረናል፡፡

@lifeandwisdom

ህይወትን በጥበብ

08 Jun, 17:17


#ራስህን_እንደ_አሸናፊ_ተመልከት!

አሸናፊዎች ሽንፈትን እንደ ተሸናፊዎች አያዩትም።

በመንገዳቻው ሽንፈት ሲገጥማቸው የታሪካቸው ማብቂያ አድርገው አይወስዱትም። ይልቁንም ሽንፈትን በሌላ መልኩ ነው የሚያዩት።

ሽንፈት ለአሸናፊዎች እንደ መማሪያ እድል፣ እንደ መሻሻያ አጋጣሚ፣ አንደ ማደጊያ ክፍተት ጠቋሚ ነው የሚመለከቱት።

ከሸንፈታቸው ስለሚማሩ ሽንፈትን አይፈሩትም። ሽንፈት ይልቁንም ያሳድጋቸዋል።

ወዳጄ አንተም ሽንፈትን እንደ ህይወትህ ፍጻሜ አትመልከት። እራስህን እንደምታሻሽልበት የክፍተት ጠቋሚ ተመልከተው። ያኔ እራስህን ለማሻሻል የምትሰራበትን ብዙ ክፍተት ታገኛለህ። ያኔ ራስህን በማሻሻል የበለጠ ከፍታ ላይ ታገኛለህ፤ አሁን ለደረጃህ የሚመጥን ፈተና ይገጥምሀል፤ በእሱም በድጋሚ እራስህን ታሳድጋለህ።

ፈተና አያልቅም ሌላ ይመጣል፤ ያንተም እድገት አያቆምም፤ ይቀጥላል።

@lifeandwisdom

ህይወትን በጥበብ

01 Jun, 12:31


ጣሪያህን ንቀለው

“ውስንነትህን ለይተህ እወቅ፣ ነገር ግን በፍጹም አትቀበለው” – Unknown Source

ጣሪያህ ምንድን ነው? ጣሪያህ ሁኔታዎች የወሰኑልህና እንዳንተ አይነት ሰው የትም አይደርስም ብለው የደመደሙብህ እይታ ነው፡፡ ጣሪያህ ምንድን ነው? በአንተ ሁኔታ የተወለደና ያደገ ሰው በፍጹም ከዚህ ከፍታ በላይ ሊሄድ አይችልም ብሎ ሕብረተሰቡ የደመደመው ገደብ ነው፡፡ ጣሪያህ ምንድን ነው? ሰዎች የገቢህን ሁኔታ፣ የትውልድህን አመጣጥና የትምርት ደረጃህን ከደመሩና ከቀነሱ በኋላ የራሳቸው ድምዳሜ ላይ በመድረስና መስመርን በማስመር በላይህ ላይ የከደኑት ክዳን ነው፡፡

አየህ፣ ሕብረተሰቡ ይህንን የማድረግና “ከዚህ አታልፍም” ብሎ መስመር የማስመር መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡ አንተም በበኩልህ ያንን መስመር አልፈህ የመሄድ ሙሉ መብት አለህ፡፡ ያለፈው ትውልድ ያቆመበት ላይ ማቆም የለብህም፣ አዲስ ፈር ልትቀድና ወደ አዲስ አቅጣጫ ልትዘልቅ ይገባሃል፡፡ ይህ እንዲሆን ግን “ባለሁበትና ሰዎች ነህ ብለው በወሰኑልኝ ሁኔታ አልወሰንም” የሚል ቁርጥ ውሳኔ ከአንተ ይጠበቃል፡፡

😊

@lifeandwisdom

ህይወትን በጥበብ

28 May, 16:37


#6ቱ_የእኔ_ራስን_የመምሪያ_ጥበቦች

በጠብታ ማር መጽሐፉ የምናውቀው የዴል ካርኒጌ ሌላ ማር፣ ማር የሚል

6ቱ የእኔ ራስን የመምሪያ ጥበቦች

እኔ የምከተለውንና ውጤታማ እየሆንኩ ያለሁበትን "እራስን የመምራት ጥበብ" ላካፍላችሁ፦

• በመጀመሪያ እራሴን በአግባቡ ማወቅና ከእኔ በላይ ለእኔ ኃላፊነትን ሊወስድ የሚችል አንድም አካል እንደሌለ ማወቅ፣

• እራሴን ለመምራት ከሌሎች ሹመትን መጠበቅ እንደሌለብኝ፤ ይልቁንም መልካም የሆነ የህይወት መንገድን መከተል እንዳለብኝ በቅጡ ማመን፣

• በህይወት እያለሁ ለመኖር የምፈልገውን ኑሮ ለመኖር ለማሳካት ግብና አላማ ማስቀመጥ፥ ለስኬታማነታቸውም ዲሲፕሊን ወይም መልካም የሆነ ስነምግባርን መከተል፤ በመሆኑም በሰከነ አዕምሮ የታሰበን ጉዳይ ስሜት ቢፈቅድም ባይፈቅድም መልካም የሆነ ነገርን ከማድረግ ወደኋላ አለማለት፡ ለዚህም ይረዳ ዘንድ፦

1. ከምንም በፊት የምንፈልገውን ማወቅ

2. የምንፈልገውን ነገር ለማግኘት ደግሞ የሚመጥነውን ልማድና ባህሪ አንደሁኔታው ለይቶ መገንዘብ፣

3. ከዚያም ውጥንን ለማሳካት ፈጥኖ ከመጀመር በፊት ድጋሜ ማሰብ፥ ከጀምሩ ደግሞ ባለማቋረጥ እስከፍፃሜው ድረስ መጓዝ፣

4. በማይሳካልኝ መንገድ ብዙ በመጓዝ ከመብከንከን ይልቅ ሊሳኩልኝ ለሚችሉ ነገሮች ትኩረት መስጠትና ውጤታማ የሆንኩባቸውን ጉዳዮች የበለጠ ለማሻሻልና ለማሳደግ ጥረት ማድረግ፣

5. እራስን በዕውቀት ብሎም በገቢ ማሻሻል፣

6. እራስን ለእርምት ማዘጋጀትና ከስህተት መንገድ ለመመለስና እራስን ለማነፅ ልቦናን መክፈት፣

@lifeandwisdom

ህይወትን በጥበብ

16 May, 18:22


#የራስህ_ስኬት_ሰለባ_ነህ!

ጆርጅ ኦርዌል፣ “አንድ ሰው አፍንጫው ስር ያለውን ነገር ለማየት የማያቋርጥ ትግል ይጠይቃል፡፡” ይላል።

እውነት ነው።

እኛም የጭንቀቶቻችን እና የውጥረቶቻችን መፍትሄ ያለው አፍንጫችን ስር ሆኖ እኛ ግን መፍትሄ የማይሆኑ ማሽኖቻችን ላይ እንጣዳለን።

ከዚያ የራቁት ምስሎችንና ማስታወቂያዎችን በማየት ተጠምደን፣ በስፖርት የተገነባ ሰውነት ኖሮን በጣም ከምታምር አማላይ ሴት ጋር ተያይዘን መዞር የማንችለው ለምን እንደሆነ እናስባለን፡፡

ስለ “የመጀመሪያው ዓለም ችግሮች” እንቀልዳለን፣ ነገር ግን የራሳችን ስኬት ሰለባ ሆነናል።

ባለፉት ሰላሳ አመታት ውስጥ ከውጥረት ጋር የተያያዙ የጤና ጉዳዮች፣ የጭንቀት፣ የድብርት ችግሮች ጨምረዋል።

ምንም እንኳን ሁሉም ሰው ፍላት ስክሪን ቲቪ ያለው እና የገዛውን ዕቃ ቤቱ ድረስ እንዲመጣለት ማዘዝ የሚችል ቢሆንም፣ ባለፉት ሰላሳ አመታት ውስጥ ከውጥረት ጋር የተያያዙ የጤና ችግሮች ቁጥር በሚገርም ፍጥነት አሻቅቧል።

በዚህም ምክንያት ችግራችን ቁሳዊ ሳይሆን፣ ህልውና ነው፤ መንፈሳዊ ነው። ከአሁን በኋላ ስለ ምን ግድ ሊኖረን እንደሚገባን እንኳን እስከማናውቀው ድረስ በጣም ብዙ አስጨናቂ ነገሮች እና በጣም ብዙ እድሎች ያሉን ሆነናል።

እኛ ግን በብዛት ከብዙ እድሎች ይልቅ ብዙ አስጨናቂ ነገሮችን እንመርጣለን፡፡ በዚያ ፈንታ እንዴት ብዙ እድሎችን እንምረጥ?

@lifeandwisdom

ህይወትን በጥበብ

12 May, 18:21


#መርዛማ_ሰዎችን_አስወግድ


#አንድ
#መርዛማ_ሰዎችን_አስወግድ

ከመርዛማ ሰዎች ጋር አብዝተን የምንገናኝ ከሆነ በአካልም ሆነ በአእምሮ ሊጎዱን ይችላሉ ይለናል። እነዚህ ከልክ ያለፈ ትችት የሚሰጡ፣ ምቀኛ፣ ትዕቢተኛ፣ ጠበኛ ወይም ራስ ወዳድ የሆኑ ሰዎችን ያጠቃልላል። እነዚህን ባህሪያት በራሳችን እና በሌሎች እንዴት መለየት እንዳለብን እና ራሳችንን ከእነሱ እንዴት ማራቅ እንዳለብን ያስተምረናል።

#ሁለት
#ስሜታዊነትህን_ተቆጣጠር

ስሜታችን ምን ያህል በጥልቅ እንደሚገዛን እና ውሳኔዎቻችንን እና ድርጊቶቻችንን እንዴት እንደሚነካ አናውቅም። ምክንያታዊነትን በማዳበር እነዚህን ስሜታዊ ተፅእኖዎች እንዴት መቋቋም እንደምንችል ማወቅ የግድ ይለናል። እራሳችንን ጠንቅቆ ማወቅ፣ ስሜቶቻችንን ከሥሮቻቸው መፈተሽ፣ የምላሽ ጊዜያችንን ማዘግየት፣ የአስተሳሰብ እና የስሜታዊነት ሚዛንን ማግኘትን የመሳሰሉ ስልቶችንም ሮበርት ግሪን በመጽሐፉ ይጠቁመናል።

#ሶስት
#ከጓደኞችህ_ጋር_አብረህ_ወደ_ገደል_አትግባ

ከሌሎች ጋር ለመስማማትና ብቻችንን ላለመሆን ብለን የሌሎችን አስተያየት ወይም ግምት ከልክ በላይ እንዳንቀበል ያስጠነቅቀናል። ይህ ግለሰባዊ አቅማችንን እንድናጣ እና ለቡድን አስተሳሰብ እንድንጋለጥ ሊያደርገን ይችላል።

#አራት
#ሳታቋርጥ_የተሻለ_ነገርን_ፈልግ

ባለን ነገር እንዳንረካ እና ሌላ ቦታ ያለን የበለጠ ደስታን የሚሰጥ ነገር እንድንፈልግ ይገፋናል። ከመጠን በላይ የሆነ ምሬትም ወደ ብስጭት፣ ጭንቀት፣ መሰላቸት ወይም ሱስ እንደሚመራን፣ ከዚህ ይልቅም እስካሁን ያገኘነውን በምስጋና ተቀብለን፣ ራሳችንን በማሻሻል ላይ ማተኮር እንዳለብን ያሳየናል።

#አምስት
#በሰዎች_ጭምብል_ስር_ምን_እንዳለ_ተመልከት

ሮበርት ግሪን፣ ሰዎች ብዙውን ጊዜ እውነተኛ ሀሳባቸውን እና ስሜታቸውን ከራስ መተማመናቸውና ከአካላዊ ውበታቸው ስር እንዴት እንደሚደብቁ ያሳየናል። በሌሎች ቃላት እና ድርጊቶች ውስጥ ያሉ የማታለል ምልክቶችን እንዴት መለየት እንደሚቻል ያብራራልናል። እንዲሁም በሰዎች ፊት ሀቀኝነታችንን እና ታማኝነታችንን ሳናጣ እንዴት መጫወት እንዳለብንም ያስረዳናል።

#ሰውና_ተፈጥሮው_መጽሐፍ

@lifeandwisdom

ህይወትን በጥበብ

30 Apr, 16:12


#ወደ_ተሳሳተ_ምንጭ_አትሂድ

በአንድ መንደር ውስጥ የሚኖር ገበሬ አንዲት ላም ነበረችው። ላሟን እጂግ ከመውደዱ የተነሳ አብዝቶ ይንከባከባታል። ጥሩ ሳር ባለበት ቦታ እየወሰደ ይመግባታል። በአካባቢው ወዳለ ንጹህ ምንጭ እየወሰደም ውኃ ያጠጣታል።

ነገር ግን ላሟ ሁልጊዜ ትከሳለች። ከቀን ወደ ቀን የበለጠ ቀጭን ትሆናለች።

ሰውዬውም እጅግ እየተገረመና ግራ እየገባው

"ላሜ እንዲህ እየተንከባከብኳት ለምንድን ነው የምትከሳው?" ይል ነበር።

መልሱን ለማግኘትም ብዙ ጊዜ አልወሰደበትም። አንድ ቀን፥ ድንገት ውኃ ጠምቶት ከምንጩ ለመጠጣት ዝቅ ሲል አንድ ነገር አስተዋለ። ውኃው ውስጥ የሆኑ አስፈሪ ነፍሳት ነበሩ። አዎ ምንጩ በአለቅት ተወሩ ነበር።

ስለዚህም ላሟ በየቀኑ ከምንጩ በጠጣች ቁጥር ከውኃው ጋር አለቅቶች ወደ ሆዷ ይገቡ ነበር። ገብተውም ደሟን እየመጠጡ ያዳክሟታል።

የዚህ ዘመን ሰው መንፈሳዊ ሕይወትም እንደዚህ ዓይነት ነገር ነው ያጋጠመው። ጥሙን ለማርካት ውኃ የሚጠጣው ወደ ተሳሳተ ምንጭ በመሄድ ነው።

ወዳጄ አንተም ጥምህን ለማርካት ወደ ተሳሳተ ምንጭ አትሂድ!

@lifeandwisdom

ህይወትን በጥበብ

27 Apr, 11:30


#ስሜትህን_ቀይር!

አንድ ማወቅ ያለብህ ነገር ስሜትህን መቀየር እንደምትችል ነው።

ነገር ግን እንዴት የገባህበትን ከባድ ስሜት ወደተሻለ ስሜት መቀየር ትችላለህ? ከባድ ጥያቄ ይመስላል።

በትክክል ቀላል አይደለም። ልምምድ ያስፈልገዋል።

ህምምም... እንበልና የሆነ ሰው አበሳጨህ፣ ዝቅ አድርጎሃል! ጉዳት ተሰምቶሃል እና? በመጀመሪያ ስሜቱን አትካደው ነገር ግን ለምን እንደዛ ሊሰማህ እንደቻለ ራስህን ጠይቅ... ምናልባት ያ ሰው እንደዛ እንዲሰማህ አልፈለገም... ምናልባት ያ የራስህ የአረዳድ ችግር ይሆናል... ምናልባት ያለብህ የበታችነት ስሜት... ምናልባትም ለዛ ሰው ያለህ ድብቅ ጥላቻ... ወይም በትክክል ያበሳጨህ ሰው ሆን ብሎም ሊሆን ይችላል።
የፈለገ ይሁን የሚረብሽ ስሜት ለምን ውስጥህ ቀረ? ይሄን ጥያቄ ምትመልሰው አንተ ሁነህ ሳለ እኔም የምጠቁምህ ነገር ይኖራል።

እዚህ ጋር- ህይወት ሁሌም ደስታ፣ መፈለግ፣ ማግኘት፣ እኩል መሆን፣ ስኬት እንዳልሆነች ተገንዘብ። ብስጭት ወይም የስሜት መረበሽ ሲያጋጥምህ ዝም ያለ ቦታ ሂድ፤ ከራስህ ጋር በፍቅር ተነጋገር። የመጥፎ ገጠመኞችን ጥሩ ጎን ለማየት ራስህን በአዎንታዊነት እንዲመራ አስገድድ።

የበደለህን ይቅር በለው ጤና ይሰጥሃል። የተበላሸብህ ነገር ደግመህ ሞክረው- ጥንካሬን ስለምታገኝ። ደስተኛ ለመሆን ቻል መከፋት ሲረዝም በብዙ ስለሚያሳጣ። ፈጣሪህን አመስግን- የተሻለ ስለምታገኝ። ካንተ የባሰበትን ተመልከት መጽጽናናት ስለሚሆንልህ። ካንተ የተሻለውን አስተውል- ተስፋ ስለሚጎበኝህ። ስለገጠመኝህ ሰዎችን አማክር- መፍትሄ ስለሚሰጡህ። ጸልይ፣ ለብቻህ ተደብቀህ አልቅስ- ለእፎይታህ።

@lifeandwisdom

ህይወትን በጥበብ

22 Apr, 11:17


#የታገሰ_ከምርጡ_ፍሬ_ይበላል!

አንድ ጊዜ አንዲት ድኃ ሴት የወይን ተክል ባለበት ማሳ በኩል እያለፈች ነበር። ማሳው በሚያማምሩና በበሰሉ የወይን ዘለላዎች የተሞላ ነበር። ሴቷ ጠምቷት ስለነበር የወይኑን ማሳ እያየች

"ከእነዚህ የበሰሉ ፍሬዎች አንዱን ወለላ የሚሰጠኝ ባገኝ..." ብላ ተመኘች

የወይን ማሳው ባለቤት በመንገዱ በኩል እያለፈ ስለነበር አያት፤ እንዳያትም ሰላም ካላት በኋላ

"ምን እያየሽ ነው የኔ ውድ? የወይን ዘለላ ትፈልጊያለሽ?" ብሎ ጠየቃት።

"አዎ እፈልጋለሁ" አለችው "ግን መውሰድ አልችልም"

ባለቤቱ ወደ ማሳው ገብቶ፣ በማሳው መሐል ጠፋ።
ጠበቀችው፣በጣም እንደዘገዬ ሲታወቃት ግን ምን አልባት ረስቶታል ማለት ነው ብላ መንቀሳቀስ ጀመረች። ከጥቂት ጊዜ በኋላ የማሳው ባለቤት ሲመጣ ሴቷ ሄዳለች። ነገር ግን ከርቀት ስላያት ጠራት።

እንደተመለሰችም
"ስለዘገየሁ ይቅርታ። ግን ለምን ሄድሽ? የዘገየሁት እኮ እጅግ ምርጡን ዘለላ እየፈለግኩልሽ ስለነበር ነው። ይሄው ሙሉ ቅርጫት አመጣሁልሽ!" አላት

ቅርጫቱንም ሰጣት። ሴቷ ትንሽ አፈረች፣ አንገቷን ደፍታም ቅርጫቱን አነሳች። የማሳውን ባለቤት አመስግናም ሄደች።

ይህ ታሪክ ለሁሉም ሰው የሚሆን አንድ ትልቅ ትምህርት አለው። ብዙ ጊዜ በጸሎት አንድ ነገር እንጠይቅና ወዲያው ግን ምላሽ አናገኝም። ከዚያም እግዚአብሔር ለእኛ አይጨነቅም ብለን እናስባለን። ከሆነ ጊዜ በኋላ ሲመጣ ግን የዘገየው ለካ ለእኛ ጥቅም ነው። ምላሹም እጅግ የተባረከና ከጠበቅነውና ከጠየቅነው በላይ ይሆናል።

@lifeandwisdom

ህይወትን በጥበብ

18 Apr, 16:27


#አታስመስል_የሆንከውን_ሁን!

በትክክል የሆንከውን ሆነህ መታየት ስትጀምር ሕይወትህን በከፍተኛ ደረጃ መለወጥ ትጀምራለህ።

የሆንከውን ሆነህ መታየት ስትጀምር፣ አላስፈላጊ መረጃዎችን እንዲቆሙ ታደርጋለህ።

በዚህም ራስህን እንደምትወድ ብቻ ሳይሆን፣ ዋጋ ያለህ መሆንህንም ለዓለም ታውጃለህ።

ከዚያ እሴቶች ብቻ ሳይሆን ሊያስፈልግህ የሚችል ሁሉም ነገር ይኖርሃል።

የምትፈልገው ቦታ ስትደርስም ባለመርህ ብቻ አትሆንም።

የሆነ ሰው ሲያፈቅርህም ደስተኛ ብቻ አትሆንም። እንደሆንከው ሆነህ ስትመጣ ይህንን አካሄድ ታፋልሳለህ።

ከዚህ በኋላ የሕይወት መልካምነት ምናልባት ላትሆን ለምትችለው ለተሻለው አንተነትህ የተያዘ አይደለም።

እንዴት መታየትና ስሜትህን ማሳየት መፍቀድ መጀመር እንዳለብህ ከማወቅህ በፊት፣ በተፈጥሮ ጥሩ ስሜት የማይሰማህ ለምን እንደሆነ ለራስህ ማብራራት ለአንተ ሁልጊዜ ጨዋታ ነበር። አሁንም በጨለማ ውስጥ የምትኖር ከሆነ፣ ያንን ማፈንና በሌሎች ጉዳዮች ላይ ማሳየት ነበረብህ።

ዛሬ የሆንከውን ሆነህ እየታየህ፣ ለምናባዊው አንተነትህ የሚገባውን ሳይሆን፣ የአንተ የሆነውን ትወስዳለህ። ዓለም የሚሰጥህ ያስብልኛል ብለህ የምታስበውን ሳይሆን፣ አንተ፣ እዚህ፣ አሁን የምታስበውን ነው።

#እውነተኛ_ፈውስ_ያ_ነው።

ልክ ልክህን እየነገረ ምርጥ ጓደኛ የሚሆንህን #ተራራው_አንተ_ነህ_መጽሐፍ ደግሞ እንድታነበው ትጋበዛለህ

@lifeandwisdom

ህይወትን በጥበብ

11 Apr, 07:31


ስኬትን ፍለጋ

“ስኬትን ከፈለክ ስኬትን ዓላማህ አድርገህ አትያዝ፡፡ የምታምንበትንና የምትወደውን ነገር ከልብህ ስታደርግ ስኬት ራሱ ይመጣል” - David Frost

ለትክክለኛ አላማ መቆም ስኬትን ይቀድማል እንጂ ስኬት አላማን አይቀድምም፡፡ አንዳንድ ሰዎች፣ “ቢሳካልኝ ኖሮ ይህንና ያንን አደርግ ነበር” በማለት በገንዘብና በተለያዩ አቅጣጫዎች “ቢሳካላቸው” ሊያደርጉ ስለሚፈልጉት የወደፊት አላማ ሲናገሩ ይደመጣሉ፡፡ አንድ ማስታወስ ያለባቸው እውነታ ግን አንድን አላማ ይዘው መስራታቸው ወደ ስኬት እንደሚወስዳቸው ነው፡፡ በሌላ አባባል፣ ተሳካላቸው በመባል የሚታወቁ ሰዎች ለስኬት የኖሩ ሰዎች ሳይሆኑ ለአንድ አላማ በጽንአት የኖሩ ናቸው፤ ያንን ሲያደርጉ ስኬት ተከተላቸው፡፡

ለስኬት የሚኖር ሰው ስኬት ያጣ ሲመስለው ያቆማል፡፡ ለአላማ የሚኖር ሰው ግን ስኬት ያላገኘ ቢመስለውም እንኳ ጉዞውን ይቀጥላል፣ ምክንያቱም አላማ የተሰኘውን የስኬቶችን ሁሉ ስኬት በእጁ ጨብጧልና ነው፡፡ “የምትወደውንና መልካም የሆነውን ነገር አድርግ፣ ያንን የምታደርገውን ነገር ደግሞ ውደደው” የሚለው አባባል እውነት ነው፡፡ ስኬትን ፍለጋ ከአላማህ ውጪ የሆነን “ታላቅ” ነገር ከማድረግ፣ አላማን በመከተል አስቸጋሪ ጎዳና መጓዝ ይመረጣል፡፡

@lifeandwisdom

ህይወትን በጥበብ

08 Apr, 17:19


የተቃውሞ ውበት

“ስኬታማ ሰው ማለት ሰዎች የሚወረውሩበትን የተቃውሞ ድንጋይ መሰረት ለመጣል የሚጠቀምበት ሰው ነው” - David Brinkley

የማይንቀሳቀስንና የማይሰራን ሰው ብዙም ተቃውሞ ሲገጥመው አይታይም፡፡ የሚያልምን፣ የሚሰራን፣ ለውጥን ለማምጣት የሚነሳሳንና ውጤትን የሚያስመዘግብን ሰው ግን ለመቃወም ሃሳብ ሰጪው ብዙ ነው፡፡ በሕይወትህ የመጀመሪያውን የስኬት ጣእም አጣጥመህ ሳትጨርስ የመጀመሪያውን የተቃውሞ ድንጋይ ወደ አንተ ሲወረወር ማየትህ የማይቀር ነው፡፡ ሆኖም፣ አንድ እውነታ መዘንጋት የለብህም፣ ለስኬታማነትህ መዋጮ የሚያደርጉት የሚደግፉህና የሚያደንቁህ ሰዎች ብቻ አይደሉም፤ የሚቃወሙህና የማይቀበሉህም ሰዎች ጭምር እንጂ፡፡ የሚጋፉህና የሚቃወሙህም ሰዎች በሕይወትህ ትልቅ ስፍራ እንዳላቸው መዘንጋት የለብህም፡፡

ሰው በተቀባይነት ውስጥ ይነሳሳል፣ በተቃውሞ ውስጥ ደግሞ ይጠነክራል፡፡

ተቃውሞ ራስህን ካለማቋረጥ እንድትመለከትና እንድትፈትሽ ያስታውስሃል፡፡ ተቃውሞ ነገ የተሻለ ስኬት በእጅህ ሲገባ ከተከፈለበት መስዋትነት አንጻር ለስኬቱ እንድትጠነቀቅ ይረዳሃል፡፡ ተቃውሞ ነገ የስኬት ከፍታ ላይ ስትደርስ ስኬቱን በጨዋነት እንድትይዘው የሚስችልህን ባህሪይ ይገነባልሃል፡፡ መለስ ብለህ ታሪክን አንብብና ለአለምም ሆነ ለሕብረተሰባችን መልካም ፈርን ቀድደው ያለፉ ሰዎችን ጎዳና አጢን፣ ምናልባት ለማመን የሚያስቸግርህን ውጣ ውረድና ተቃውሞ አሸንፈው እንዳለፉ ትደርስበታለህ ብዬ እጠረጥራለሁ፡፡

አየህ፣ ብዙ ሰዎች የሚቃወሙትን እንጂ የሚደግፉትን አያውቁም … የሚያፈርሱትን እንጂ የሚገነቡትን አያውቁም … የሚጠሉትን እንጂ የመወዱትን አያውቁትም፡፡ እንደዚህ አይነት ሰዎች ከላይ የተዘረዘሩትን አሉታዊ እርምጃዎች ከወሰዱና የተመኙትን አሉታዊ ውጤት ካገኙ በኋላ አዎንታዊ እቅድ ስለሌላቸው ሌላ የሚቃወሙትን፣ የሚያፈርሱትንና የሚጠሉትን ፍለጋ ይቅበዘበዛሉ፡፡ አንተ ግን ዝም ብለህ ዓላማህ ላይ አተኩር፡፡

@lifeandwisdom

1,443

subscribers

257

photos

6

videos