kuasmeda / ኳስሜዳ @kuasmeda1 Channel on Telegram

kuasmeda / ኳስሜዳ

@kuasmeda1


Ethio Sport News

kuasmeda / ኳስሜዳ (Amharic)

ኮሰመዳ - ክፍለ አምሳይ አድማሳዊ ምርጥ ዜና እና ስፖርት ይዘት፣ ወንጀል ልዩ በዚህ ሶስት ገንዘብ፡ ጥንታዊነት፣ ሚስጥሮች፣ ካሊፎርክሽን ፣ ፍቅሬ እና እንስሳነት፡ የወላጅነት እና የፖስት ረቂቅ ትምህርት፣ ሾው ማካተት እና ሀገር ትግል። ስፖርት፡ - @kuasmeda1 የሚለው ቁጥር ስር አንደኛ ድምፅ እና የሰነዳዊ ሀይቅ የተዘጋጀ አገልግሎት። አሁን ይህብስታችኋል, ስፖርት መዝገብን በድምፅ ለማወቅ ይቅርታ ያሉበት ቦታ።

kuasmeda / ኳስሜዳ

11 Feb, 11:39


#የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የመጀመሪያ ዙር የጥሎ ማለፍ ጨዋታዎች ዛሬ ምሽት የሚደረጉ ይሆናል። በተለይ ሪያል ማድሪድ ከ ማንቸስተር ሲቲ የሚያደርጉት ጨዋታ ተጠባቂ ነው።ሁሉም ጨዋታዎች በተመሳሳይ ሰዓት ምሽት 05:00 ይደረጋሉ።

kuasmeda / ኳስሜዳ

11 Feb, 11:29


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
አስር ተጫዋቾች የጨዋታ ቅጣት ተላለፈባቸው

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

1. ኬኔዲ ከበደ (ወላይታ ድቻ) : እሁድ የካቲት 2 2017 ዓ.ም. ክለቡ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር ባደረገው የ19ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ በ 27 ኛ ደቂቃ ላይ ሁለተኛ ቢጫ ካርድ የሚያስጥ ጥፋት በመፈፀሙ በቀይ ካርድ ከጨዋታ ሜዳ የተወገደ ስለመሆኑ ሪፖርት ቀርቦበታል ። ስለሆነም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 2 አንቀፅ 35(መ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።

2. ኢስማኤል አብዱል ጋኒዩ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም ከታች በተጠቀሱት 4 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ ካርድ ተመልክቷል ።

1. ድሬደዋ ከተማ – ወላይታ ድቻ
2. ባህርዳር ከተማ – ድሬደዋ ከተማ
3. ድሬደዋ ከተማ – ቅዱስ ጊዮርጊስ
4. ድሬደዋ ከተማ – ኢትዮጵያ መድን

በመሆኑም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ እ‥ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 2 አንቀፅ 35(መ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 1500 እንዲከፍል የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል ።

https://i0.wp.com/www.hatricksport.net/wp-content/uploads/2023/05/OMEGA_ADS.jpg?resize=1170%2C214&ssl=1

3. ካርሎስ ዳምጠው(ወላይታ ድቻ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም ከታች በተጠቀሱት 4 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ ካርድ ተመልክቷል ።

1. ድሬደዋ ከተማ – ወላይታ ድቻ
2. ኢትዮ ኤሌትሪክ – ወላይታ ድቻ
3. ባህርዳር ከተማ – ወላይታ ድቻ
4. ወላይታ ድቻ – ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ

በመሆኑም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 2 አንቀፅ 35(መ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 1500 እንዲከፍል የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል ።

4. አብነት ደምሴ(ወላይታ ድቻ) :  ከታች በተጠቀሱት 5 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ ካርድ ተመልክቷል ።

1. ወላይታ ድቻ – ኢትዮጵያ ቡና
2. ሀዲያ ሆሳዕና – ወላይታ ድቻ
3. ወላይታ ድቻ – ሃዋሳ ከተማ
4. መቐለ 70 እንደርታ- ወላይታ ድቻ
5. ወላይታ ድቻ – ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ

በመሆኑም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 2 አንቀፅ 35(መ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 1500 /አንድ ሺ አምስት መቶ እንዲከፍል የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል ።

5. መሳይ አገኘሁ(ባህርዳር ከተማ) : ከታች በተጠቀሱት 5 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ ካርድ ተመልክቷል ።

1. ባህርዳር ከተማ – አዳማ ከተማ
2. ባህርዳር ከተማ – ሀዲያ ሆሳዕና
3. መቐለ 70 እንደርታ-ባህርዳር ከተማ
4. ባህርዳር ከተማ – ቅዱስ ጊዮርጊስ
5. ባህርዳር ከተማ – ፋሲል ከነማ

በመሆኑም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ እ‥ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 2 አንቀፅ 35(መ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ በተጨማሪ የገንዘብ

ቅጣት ብር 1500 /አንድ ሺ አምስት መቶ/ እንዲከፍል የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል ።

6. እዮብ ማቲያስ (ፋሲል ከነማ) :  ከታች በተጠቀሱት 5 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ ካርድ ተመልክቷል ።

1. ፋሲል ከነማ – አርባምንጭ ከተማ
2. ፋሲል ከነማ – መቻል
3. ድሬደዋ ከተማ – ፋሲል ከነማ
4. ኢትዮጵያ መድን – ፋሲል ከነማ
5. ባህርዳር ከተማ – ፋሲል ከነማ

በመሆኑም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 2 አንቀፅ 35(መ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 1500 /አንድ ሺ አምስት መቶ እንዲከፍል የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል ።

7. ኪሩቤል ወንድሙ (ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ) : ከታች በተጠቀሱት 5 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ ካርድ ተመልክቷል ።

1. ቅዱስ ጊዮርጊስ – ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ
2. ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ-መቻል
3. አርባምንጭ ከተማ -ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ
4. ኢትዮጵያ ቡና – ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ
5. ስሁል ሽሬ – ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ

በመሆኑም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ እ ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 2 አንቀፅ 35(መ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 1500 /አንድ ሺ አምስት መቶ/ እንዲከፍል የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል ።

8. አሰጋኸኝ ጴጥሮስ (ስሁል ሽረ) : ከታች በተጠቀሱት 5 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ ካርድ ተመልክቷል ።

1. ስሁል ሽረ – ድሬደዋ ከተማ
2. ስሁል ሽረ- ባህርዳር ከተማ
3. ስሁል ሽረ – ሀዲያ ሆሳዕና
4. ስሁል ሽረ – መቻል
5. ስሁል ሽረ-ወልዋሎ አዲግራት ድጋፍ

በመሆኑም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 2 አንቀፅ 35(መ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 1500 /አንድ ሺ አምስት መቶ/ እንዲከፍል የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል ።

9. አዮብ ዓለማየሁ(ሀዲያ ሆሳዕና) : ከታች በተጠቀሱት 5 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ ካርድ ተመልክቷል ።

1. ሀዲያ ሆሳዕና – ሃዋሳ ከተማ
2. ኢትዮ ኤሌትሪክ – ሀዲያ ሆሳዕና
3. ድሬደዋ ከተማ – ሀዲያ ሆሳዕና
4. ሀዲያ ሆሳዕና – ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
5. ሀዲያ ሆሳዕና – ቅዱስ ጊዮርጊስ

በመሆኑም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ እ‥ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 2 አንቀፅ 35(መ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 1500 /አንድ ሺ አምስት መቶ/ እንዲከፍል የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል ።

10. ሙሴ ከበላ (አዳማ ከተማ) : ከታች በተጠቀሱት 5 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ ካርድ ተመልክቷል ።

1. ባህርዳር ከተማ – አዳማ ከተማ
2. ድሬደዋ ከተማ – አዳማ ከተማ
3. አዳማ ከተማ – ኢትዮጵያ መድን
4. አዳማ ከተማ – ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
5. አዳማ ከተማ – ሲዳማ ቡና

በመሆኑም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ እ∶ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 2 አንቀፅ 35(መ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ በተጨማሪ የገንዘብ

ቅጣት ብር 1500 /አንድ ሺ አምስት መቶ/ እንዲከፍል የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል ።

The post አስር ተጫዋቾች የጨዋታ ቅጣት ተላለፈባቸው first appeared on ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ.

The post አስር ተጫዋቾች የጨዋታ ቅጣት ተላለፈባቸው appeared first on ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ.

kuasmeda / ኳስሜዳ

09 Feb, 19:28


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
የኢትዮጵያ ቡና የውድድር ዘመኑ አጋማሽ ምርጥ ተጫዋች ዕጩዎች ይፋ ሆኑ

የ2017 ዓ.ም የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የመጀመሪያ ዙር ጨዋታዎቹን መቻልን 1 – 0 በመርታት ያጠናቀቀው ኢትዮጵያ ቡና የውድድር ዘመኑ አጋማሽ የምርጥ ተጫዋች ዕጩዎቹን ይፋ አድርጓል።

በዕጩዎቹ ዝርዝር የሊጉ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ እና የጥቅምት ወር የክለቡ የወሩ ምርጥ ተጫዋች አንተነህ ተፈራ እና የህዳር ወር የክለቡ የወሩ ኮከብ ተብሎ የተመረጠው ናይጄሪያዊው ዲቫይን ዋቹኩዋ መካተት ችለዋል።

ሁሉንም የመጀመሪያ ዙር ጨዋታዎች(17) ያደረገው እና በዘጠኝ ጨዋታዎች ግብ ያላስተናገደው ግብ ጠባቂው ዳንላንድ ኢብራሂም ፤ የቡድኑ አምበል ራምኬል ጀምሰ ፤ የቀኝ መስመር ተከላካዩ ረጂብ ሚፍታህ እና የመሀል ተከላካዩ ወልደአማኑኤል ጌቱ በዕጩዎቹ ዝርዝር የተካተቱ ሌሎች ተጫዋቾች ናቸው።

የኢትዮጵያ ቡና ደጋፊዎች የውድድር ዘመኑ አጋማሽ ምርጥ ተጫዋቻቸውን በክለቡ ይፋዊ የፌስቡክ ገፅ ላይ መምረጥ እንደሚችሉ ተገልጿል።

kuasmeda / ኳስሜዳ

09 Feb, 05:23


👉በትናንትናው እለት የአራተኛ ዙር የእንግሊዝ FA ዋንጫ ጨዋታ ውጤቶች ይህን ይመስላሉ። ጨዋታ ዎቹ ዛሬም ሲቀጥሉ

#ብላክበርን 🆚 ዎልቭስ

🏟 ኢዉድ ፓርክ

09:30 ቀን

#ፖሊይማውዝ 🆚 ሊቨርፑል

🏟 ሆም ፓርክ

12:00 አመሻሽ

#አስቶንቪላ 🆚 ቶተነሃም

🏟 ቪላ ፓርክ

08:35 ምሽት

"መልካም ጨዋታ"

kuasmeda / ኳስሜዳ

08 Feb, 19:28


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
የአንተነህ ተፈራ እና ሔኖክ አርፊጮ ግቦች ቡድኖቻቸውን አሸናፊ አድርገዋል

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 19ኛ ሳምንት የሁለተኛ ቀን ጨዋታዎች በዛሬው ዕለት ሲደረጉ ኢትዮጵያ ቡና እና ሀድያ ሆሳዕና ድል ቀንቷቸዋል።

በቀዳሚው ጨዋታ መቻልን የገጠመው ኢትዮጵያ ቡና አንተነህ ተፈራ በ49ኛው ደቂቃ ላይ ባስቆጠረው ብቸኛ ግብ 1 – 0 አሸንፏል።

የመቻል ተከላካዮች አለመረጋጋት ፤ የአማኑኤል እና ዲቫይን ጥረቶች ከአንተነህ ድንቅ አጨራረስ ጋር ተደምረው ግቡ እንዲቆጠር አስችሏል።

ባለፉት ተከታታይ ስምንት የሊግ ጨዋታዎች ሁለት ግቦችን ብቻ ያስተናገደው የቡናማዎቹ የተከላካይ ክፍል ብቸኛዋን ግብ አስጠብቆ ሶስቱን ነጥቦች ይዞ መውጣት ችሏል።

የአሰልጣኝ ገብረክርስቶስ ቢራራው ቡድን ሊጉ ወደ አዳማ ሲመጣ መሪ የነበረ ቢሆንም አዳማ ላይ ካደረጋቸው ሰባት የሊጉ ጨዋታዎች ማሸነፍ የቻለው በአንድ ብቻ ነው።

እንደ ሽመልስ በቀለ እና ምንይሉ ተሾመ አይነት ሁነኛ የማጥቃት ሂደቱ ተዋናዮችን በጉዳት ምክንያት በጨዋታው ያልተጠቀሙት አሰልጣኙ ፊት መስመር ላይ ያለው አለመረጋጋት እና የሚገኙ ዕድሎች አለመጠቀም ዋጋ እንዳስከፈላቸው ተናግረዋል።

ውጤቱንም ተከትሎ ኢትዮጵያ ቡና ነጥቡን 26 ያደረሰ ሲሆን መቻል በ27 ነጥቦች በነበረበት ለመቆየት ተገዷል።

በሁለተኛው ዙር ቀዳሚ ሳምንት ጨዋታዎች ኢትዮጵያ ቡና ከስሁል ሽረ እንዲሁም መቻል ከድሬዳዋ ከተማ ይጫወታሉ።

በዕለቱ ሁለተኛ መርሐግብር ከአመሻሽ 12:00 ጀምሮ በመሪነት ተርታ የሚገኙትን ሀድያ ሆሳዕና እና ቅዱስ ጊዮርጊስን ያገናኘው ጨዋታ በሀድያ ሆሳዕና አሸናፊነት ተጠናቋል።

በተመሳሳይ የ1 – 0 ውጤት በተጠናቀቀው ጨዋታ አምበሉ ሔኖክ አርፊጮ በ61ኛው ደቂቃ ላይ ከቅጣት ምት ያስቆጠረው ኳስ ቡድኑን አሸናፊ አድርጓል።

በተከታታይ ሁለተኛ ጨዋታ ላይ ከቆመ ኳስ ግብ ያስቆጠረው ሔኖክ በልምምድ ቦታ ላይ በሚገባ ሰርተን የመጣነው ነው ሲል ስለ ግቡ ተናግሯል።

ከሶስት ጨዋታዎች በኋላ ወደ ድል የተመለሰው ቡድኑ ነጥቡን 30 በማድረስም የሁለተኛ ደረጃን ከተጋጣሚው ቅዱስ ጊዮርጊስ ተረክቧል።

በውድድር ዓመቱ አዳማ ላይ የመጀመሪያ ሽንፈቱን ያስተናገደው ቅዱስ ጊዮርጊስ ከመሪው ኢትዮጵያ መድኅን ለመጠጋት የሚያስችለው ዕድል ዳግም ሳይጠቀምበት ቀርቷል።

ቡድኑ የሁለተኛ ደረጃውን ለሀድያ ሆሳዕና አስረክቦ በነበረበት 29 ነጥብ ላይ የሚቆይ ይሆናል።

በ20ኛው ሳምንት ጨዋታዎች ሀድያ ሆሳዕና ከሀዋሳ ከተማ እንዲሁም ቅዱስ ጊዮርጊስ ከባህርዳር ከተማ ይጫወታሉ።

kuasmeda / ኳስሜዳ

08 Feb, 11:27


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
አሰልጣኝ ሙሉጌታ ምህረት ወደ ቀድሞ ክለቡ ዳግም ተመልሷል

በዘንድሮው የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ባልተጠበቀ ጉዞ ላይ የሚገኘው ሀዋሳ ከተማ ከአሰልጣኝ ዘርዓይ ሙሉ ጋር ከተለያየ በኋላ በጊዜያዊ አሰልጣኝ ወንድማገኝ ተሾመ ሲመራ መቆየቱ ይታወቃል።

በጊዜያዊ አሰልጣኙ እየተመራም ከወራጅ ቀጠናው ለመላቀቅ የተቸገረው ሀዋሳ ከተማ አስቀድሞ በተጫዋችነት እና አሰልጣኝነት ክለቡን ያገለገለውን ሙሉጌታ ምህረትን በዋና አሰልጣኝነት መሾሙ ተረጋግጧል።

አሰልጣኝ ሙሉጌታ ቡድኑን እየመራ የመጀመሪያ ጨዋታውን በኢትዮጵያ ዋንጫ ከአራት ቀናት በኋላ በሀዋሳ ሰው ሰራሽ ሜዳ ላይ ከነገሌ አርሲ ጋር ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል።

kuasmeda / ኳስሜዳ

06 Feb, 11:27


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
አሸናፊ ፊዳ ፣ወንድማገኝ ማዕረግ፣ ይሁን እንዳሻው እና ነፃነት ገብረመድህን የጨዋታ እገዳ ሲጣልባቸው እንዲሁም በክለቦች ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ ፣ ወላይታ ድቻ እና አዳማ ከተማ ቅጣት ተላልፎባቸዋል

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

1. አሸናፊ ፊዳ (አርባምንጭ ከተማ) : ማከሰኞ ጥር 27 2017 ዓ.ም. ክለቡ ከሀዲያ ሆሳዕና ጋር ባደረገው የ18ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ በ 62 ኛ ደቂቃ ላይ የተጋጣሚን ተጫዋች በመማታት በቀይ ካርድ ከጨዋታ ሜዳ የተወገደ ስለመሆኑ ሪፖርት ቀርቦበታል ። ስለሆነም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 3 ምዕራፍ 3 አንቀፅ 63 በተቁ 1 (ሠ) እና በተቁ 2 መሰረት 4 ጨዋታ እንዲታገድ ና በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 3000 /ሶስት ሺ/ እንዲከፍል የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።

2. ወንድማገኝ ማዕረግ (ሃዋሳ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም ከታች በተጠቀሱት 4 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ ካርድ ተመልክቷል ።

* ሀዲያ ሆሳዕና – ሃዋሳ ከተማ
* ወላይታ ድቻ – ሃዋሳ ከተማ
* ሃዋሳ ከተማ – መቻል
* ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ – ሃዋሳ ከተማ

በመሆኑም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 1500 እንዲከፍል የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል ።

3. ይሁን እንዳሻው (አርባምንጭ ከተማ) : ከታች በተጠቀሱት 5 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ ካርድ ተመልክቷል ።

* ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ – አርባምንጭ ከተማ
* አርባምንጭ ከተማ – ድሬደዋ ከተማ
* ፋሲል ከነማ – አርባምንጭ ከተማ
* ኢትዮጵያ ቡና – አርባምንጭ ከተማ
* አርባምንጭ ከተማ – ሀዲያ ሆሳዕና

በመሆኑም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ እ‥ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 2 አንቀፅ 35(መ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 1500 /አንድ ሺ አምስት መቶ/ እንዲከፍል የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል ።

4. ነፃነት ገብረመድህን (ስሁል ሽረ) : ከታች በተጠቀሱት 5 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ ካርድ ተመልክቷል ።

* ወላይታ ድቻ – ስሁል ሽረ
* ኢትዮጵያ ቡና – ስሁል ሽረ
* ስሁል ሽረ-ባህርዳር ከተማ
* ስሁል ሽረ-መቻል
* ሲዳማ ቡና – ስሁል ሽረ

በመሆኑም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 2 አንቀፅ 35(መ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 1500 /አንድ ሺ አምስት መቶ/ እንዲከፍል የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል ።

1. ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ ክለቡ ከድሬደዋ ከተማ ጋር ባደረገው የ18 ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ የወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ ቡድን ተጫዋች የሆኑት

1. ናትናኤል ሰለሞን
2. ቡልቻ ሹራ
3. ጋዲሳ መብራቴ
4. ሳምሶን ጥላሁን
5. ሱልጣን በርሄ
6. በረከት አማረ

በተለያዩ ጥፋቶች ካርድ የተሰጣቸው በመሆኑ በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ መሰረት የገንዘብ ቅጣት ብር 5000 /አምስት ሺ/ እንዲከፍል የ ውድድር አመራርና ስነ- ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል፡፡

2. ወላይታ ድቻ ክለቡ ከመቐለ 70 እንደርታ ጋር ባደረገው የ18 ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ የወላይታ ድቻ ቡድን ተጫዋች የሆኑት

1. ፍጹም ግርማ
2. አብነት ደምሴ
3. ብዙአየሁ ሰይፉ
4. ውብሸት ክፍሌ
5. ቢኒያም ገነቱ

በተለያዩ ጥፋቶች ካርድ የተሰጣቸው በመሆኑ በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ መሰረት የገንዘብ ቅጣት ብር 5000 /አምስት ሺ እንዲከፍል የ ውድድር አመራርና ስነ- ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል፡፡

3. አዳማ ከተማ ክለቡ ከ ኢትዮ ኤሌትሪክ ጋር በነበረው የ18ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ ቅድመ ስብሰባ ወቅት የክለቡ ተወካይ ስላለመምጣቱ ሪፖርት ቀርቦበታል ። በመሆኑም በፕሪምየር ሊግ የውድድር ደንብ ክፍል 1 አንቀፅ 10 ተቁ 8 መሰረት ከለቡ ብር 5000/አምስት ሺህ/ እንዲከፍል የውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።

kuasmeda / ኳስሜዳ

06 Feb, 05:55


👉ሌላ ቀሪ የግማሽ ፍፃሜ የካራባኦ ካፕ ዋንጫ የመልስ ጨዋታ ዛሬ ምሽት የሚደረግ ይሆናል።

#ሊቨርፑል 🆚 ቶተነሃም

⌚️05:00 ምሽት

🏟 አንፊልድ

👉 በመጀመሪያው ጨዋታ ቶተነሃም ሆትስፐር በሜዳው አንድ ለባዶ ማሸነፉ የሚታወስ ነው ዛሬ ሊቨርፑል በሜዳው ምን ያሳየን ይሆን?

"መልካም ጨዋታ"

kuasmeda / ኳስሜዳ

06 Feb, 03:53


ኒውካስል 2:0 አርሰናል የጨዋታ ሃይላይት

kuasmeda / ኳስሜዳ

05 Feb, 19:26


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
አንዋር ሙራድ ለአሰልጣኙ ውድ የልደት ስጦታ ሲያበረክት ሻምፕየኑ ንግድ ባንክ ሀዋሳ ከተማን ረቷል

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 18ኛ ሳምንት የመጨረሻ ቀን ጨዋታዎች በዛሬው ዕለት ሲደረጉ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ፋሲል ከነማ ድል ቀንቷቸዋል።

በዕለቱ ቀዳሚ ጨዋታ የዓምናው ሻምፕዮን ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በውድድር ዓመቱ እየተቸገረ ያለውን ሀዋሳ ከተማን 2 – 0 አሸንፏል።

በጨዋታው አዲስ ግደይ በ26ኛው ደቂቃ ላይ በራሱ ላይ በተሰራ ጥፋት የተገኘውን የፍፁም ቅጣት ምት ከመረብ አሳርፏል።

የሁለተኛው አጋማሽ በተጀመረ ሁለተኛው ደቂቃ ላይ ደግሞ ሳይመን ፒተር የበፀሎት ልዑል ሰገዱን ቡድን መሪነት ወደ 2 – 0 አሳድጓል።

ውጤቱንም ተከትሎም ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ነጥቡን 21 በማድረስ ደረጃውን ወደ 13ኛ ከፍ አድርጓል።

በ15 ነጥብ ላይ ለመቆየት የተገደደው ሀዋሳ ከተማ የመጀመሪያውን ዙር በወራጅ ቀጠና ውስጥ ሆኖ ማጠናቀቁን አረጋግጧል።

በ19ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከወላይታ ድቻ ሲጫወት ሀዋሳ ከተማ የመጀመሪያ ዙር ጨዋታዎቹን አጠናቋል።

በዕለቱ ሁለተኛ እና በሳምንቱ የመጨረሻ መርሐግብር ደግሞ የሊጉ መሪ ኢትዮጵያ መድን በፋሲል ከነማ የ1 – 0 ሽንፈትን አስተናግዷል።

በጨዋታው አንዋር ሙራድ በ76ኛው ደቂቃ ላይ በግሩም ሁኔታ ያስቆጠረው ግብ ለአፄዎቹ ጣፋጭ ሶስት ነጥቦችን አስገኝቷል።

አንዋር ሙራድ በተከታታይ ሶስተኛ የሊግ ጨዋታ ያስቆጠረው ግብም ሆኖ ተመዝግቧል።

የውድድር ዓመቱን አራተኛ ድል ያስመዘገበው ፋሲል ከነማ ነጥቡን 23 በማድረስ ወደ 8ኛ ደረጃ ከፍ ማለት ችሏል።

ከ107 ቀናት በኋላ ሽንፈት ያስተናገደው ኢትዮጵያ መድን ከተከታዮቹ ያለውን የነጥብ ልዩነት ማስፋት የሚችልበትን ዕድል ባይጠቀምም በ32 ነጥቦች በመሪነቱ ቀጥሏል።

በመጀመሪያው ዙር የመጨረሻ ሳምንት ጨዋታዎች ፋሲል ከነማ ከባህርዳር ከተማ እንዲሁም ኢትዮጵያ መድን ከድሬዳዋ ከተማ ይጫወታሉ

kuasmeda / ኳስሜዳ

05 Feb, 07:32


👉የካራባኦ ካፕ ዋንጫ የመልስ ጨዋታ ዛሬ ምሽት የሚደረግ ይሆናል።

#ኒውካስል ዩናይትድ 🆚 አርሰናል

05:00 ምሽት

🏟 ሴንት ጄምስፓርክ

👉 በመጀመሪያው ጨዋታ ኒውካስል ዩናይትድ አርሰናልን በሜዳው ሁለት ለባዶ ማሸነፉ የሚታወስ ነው ዛሬ ምን ያሳየን ይሆን?

"መልካም ጨዋታ"

kuasmeda / ኳስሜዳ

04 Feb, 23:26


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
አዞዎቹ እና ነብሮቹ ከአስደናቂ ጨዋታ በኋላ ነጥብ ሲጋሩ የጦና ንቦቹ ወደ ድል ተመልሰዋል

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 18ኛ ሳምንት የሶስተኛ ቀን ጨዋታዎች በዛሬው ዕለት ሲደረጉ ከአመሻሽ 12:00 ጀምሮ የተደረገው የአርባምንጭ ከተማ እና ሀድያ ሆሳዕና ጨዋታ 3 – 3 ተጠናቋል።

በጨዋታው ሀድያ ሆሳዕናዎቹ ገና በጊዜ 2 – 0 መሪ መሆን ነበር።

በ4ኛው ደቂቃ ላይ ሄኖክ አርፊጮ ከቅጣት ምት በቀጥታ ወደ ግብ የመታው ኳስ በቀጥታ የሀድያ ሆሳዕና መረብ ላይ አርፏል።

በ14ኛው ደቂቃ ደግሞ ዳግም ንጉሴ ከማዕዘን የተሻገረለትን ኳስ በግንባሩ ገጭቶ በማስቆጠር የከቤራዎቹን መሪነት ወደ 2 – 0 ከፍ አድርጓል።


በ26ኛው ደቂቃ ላይ ዳግም ንጉሴ በአህብዋ ብሪያን ላይ በሳጥን ውስጥ የሰራውን ጥፋት ተከትሎ አዞዎቹ የፍፁም ቅጣት ምት ቢያገኙም ጥፋቱ የተሰራበት ብሪያን ሳይጠቀምበት ቀርቷል።

የመጀመሪያው አጋማሽ ሊጠናቀቅ በተቃረበበት ወቅት ግን አዞዎቹ ወደ ጨዋታው የመለሳቸውን ግብ ከመረብ አሳርፈዋል።

በ45+3 ደቂቃ ላይ ከአርባምንጭ የቀኝ አቅጣጫ ወደ ሳጥኑ የተሻገረውን ኳስ ቡታቃ ሸመና በደረቱ አረጋግቶ የሀድያ ሆሳዕናውን ግብ ጠባቂ ያሬድ በቀለ ስህተትም ታክሎበት ግቡን አስቆጥሯል።

በርካታ ክስተቶችን እያስመለከተ በቀጠለው ጨዋታ በሁለተኛው አጋማሽም ተጨማሪ ግቦችን አክሏል።

በ60ኛው ደቂቃ ላይ የፍፁም ቅጣት ምቱን መጠቀም ያልቻለው አህባዋ ብሪያን በረጅም የተላከለትን ኳስ የያሬድ በቀለን ሁለተኛ የጊዜ አጠባበቅ ስህተት ተጠቅሞ አርባምንጭ ከተማን አቻ አድርጓል።

ከግቡ መቆጠር ጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ግን አዞዎቹ አንድ ተጫዋች በቀይ ካርድ ማጣታቸውን ተከትሎ ቀሪውን ደቂቃ በ10 ተጫዋቾች ለመጨረስ ተገደዋል።

ተከላካዩ አሸናፊ ፊዳ ከኳስ ውጪ በሆነ እንቅስቃሴ እዮብ አለማየሁ ላይ የመታው ሲሆን በቅርበት ሆነው ሁነቱን የተመለከቱት የዕለቱ ዋና ዳኛ በቀጥታ የቀይ ካርድ ከሜዳ አስወግደውታል።

ጨዋታው 75ኛ ደቂቃ ላይ በደረሰበት ወቅት ግኑ አርባምንጭ ከተማዎች 2 – 0 ሲመሩበት የነበረውን የጨዋታ ውጤት ወደ 3 – 2 መቀየር የቻሉበትን ግብ አስቆጥረዋል።

ይሁን እንደሻው ከቆመ ኳስ ወደ ግብ ክልል ያሻገረውን ኳስ ቡታቃ ሸመና በጭንቅላት ገጭቶ በማስቆጠር የአዞዎቹን ደጋፊዎች አስፈንድቋል።

ጨዋታው በአርባምንጭ ከተማ አሸናፊነት የተጠናቀቀ በመሰለበት የመጨረሻ ደቂቃዎች ላይ ግን ጫና ፈጥረው የነበሩት ከቤራዎቹ 3 – 3 የሆኑበትን ግብ በብሩክ ማርቆስ አማካይነት አግኝተዋል።

በመጨረሻም ጥሩ ፉክክር እና በርካታ ክስተቶች የነበረው ጨዋታ በሶስት አቻ ውጤት የተጠናቀቀ ሲሆን ውጤቱንም ተከትሎ ሀድያ ሆሳዕና ነጥቡን 27 ሲያደርስ አርባምንጭ ከተማ በበኩሉ ነጥቡን 24 አድርሷል።

በ19ኛው ሳምንት ጨዋታዎች ሀድያ ሆሳዕና ከቅዱስ ጊዮርጊስ አርባምንጭ ከተማ ደግሞ ከኢትዮ ኤሌክትሪክ ይገናኛሉ።

በዕለቱ በቀዳሚነት በተደረገው ጨዋታ ወላይታ ድቻ መቀሌ 70 እንደርታን አሸንፏል።

እምብዛም ሳቢ ባልነበረው ጨዋታ ካርሎስ ዳምጠው በ73ኛው ደቂቃ ላይ ያስቆጠረው ግብ ለጦና ንቦቹ ሶስት ነጥብ ማሳካት በቂ ነበረ።

ካርሎስ ዛሬ ያስቆጠረውን ግብ ተከትሎም በውድድር ዓመቱ በሊጉ ያስቆጠራቸውን የግብ ብዛቶች 4 ማድረስ ችሏል።

ድሉ ለወላይታ ድቻ ከተከታታይ ሶስት ድል አልባ እና ሁለት ተከታታይ ሽንፈቶች በኋላ የተገኘ ሲሆን መቀሌ 70 እንደርታ በበኩሉ ሊጉ አዳማ ላይ መካሄድ ከጀመረ በኋላ የመጀመሪያ ሽንፈቱን አስተናግዷል።

በቀጣይ ሳምንት መርሐግብር ወላይታ ድቻ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሲጫወት መቀሌ 70 እንደርታ አራፊ ቡድን ነው።

kuasmeda / ኳስሜዳ

03 Feb, 15:48


ኖቲንግሃም ፎረስት 7 : 0 ብራይተን - የጨዋታ ሃይላይት

kuasmeda / ኳስሜዳ

03 Feb, 15:25


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
ቅዱስ ጊዮርጊስ የዳኝነት በደል ደርሶብኛል በማለት ቅሬታውን አቀረበ

በትናንትናው ዕለት በተደረገው እና ያለ ግብ በተጠናቀቀው የሸገር ደርቢ ጨዋታ ላይ ኢንተርናሽናል ዋና ዳኛ ቴዎድሮስ ምትኩ ያሳለፏቸው ጥቂት የማይባሉ ውሳኔዎች አነጋጋሪ ሆነው ቀጥለዋል።

በተለይም በተገኑ ተሾመ ፣ አብዱልሀፊዝ ቶፊቅ እና ፍፁም ጥላሁን ላይ በፍፁም ቅጣት ምት ሳጥን ውስጥ የተሰሩ ጥፋቶችን በዝምታ ማለፋቸው በተለይም በርካታ የቅዱስ ጊዮርጊስ ክለብ አባላት እና ደጋፊዎችን አስቆጥቷል።

ክለቡ ቅዱስ ጊዮርጊስም ከደቂቃዎች በፊት በይፋዊ የማህበራዊ ትስሰር ገፆቹ ይፋ ባደረገው መረጃ መሰረት በጨዋታው ላይ የዳኝነት በደል ደርሶብኛል በማለት ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን እና ለኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አክስዮን ማህበር አቤቱታውን አቅርቧል።

ክለቡ በአቤቱታውም ጉዳዩ ሊመረመር እና የማያዳግም እርምጃ ሊወሰድበት የሚገባ ነው ሲል ገልጿል።

ቅዱስ ጊዮርጊስ ያስገባው ሙሉ አቤቱታ እንደሚከተለው ቀርቧል።

“በየዘመኑ ተደጋጋሚ የሆኑ የዳኝነት በደሎች ቢፈፀሙብንም በሂደት ይስተካከላሉ በሚል እምነት በትዕግስት አሳልፈናል፡፡

ዳኛ ገለልተኛ ምስከርና የውድድር መሪ ነው፤ በዚህም የተነሳ የተለየ መብት አለው፡፡ ስህተት እንኳን ቢሠራም ውሳኔው የመጨረሻና የማይገሰስ ነው። ነገር ግን የእርሱ የተለዩ መብቶች ተጠያቂነትን ማምጣት አለባቸው:: አሁን አሁን በስታዲየም የሚፈፀሙ ግልጽና አድሏዊ የሆኑ የዳኝነት በደሎች ተጫዋቾችና የቡድን አባላት እንዲሁም ተመልካቹ ህዝብ የሥነ ምግባር ጥሰት ውስጥ እንዲገባ የሚገፋፉ ሆነው ታይተዋል፡፡

ጥር 25 ቀን 2017 ዓ.ም በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ሜዳ በእኛና በኢትዮጵያ ቡና መካከል የተደረገውን ጨዋታ በመሐል ዳኝነት የመሩት ኢንተርሽናል ዳኛ ቴዎድሮስ ምትኩ ሦስት የፍፁም ቅጣት ምቶችን የከለከሉበት ሁኔታ አግራሞት የፈጠረ ቢሆንም ጉዳዩ መመርመር የሚያስፈልገውና የማያዳግም እርምጃ ሊወሰድበት የሚገባ፣ ለእግር ኳሱ እድገት ፀር የሆነ አካሄድ ነው፡፡ ሦስቱንም የቪዲዮ ምስሎች በአጽንዖት እንድትመለከቱት እያይዘን አቅርበናል፡፡ ባለፈው ዓመት የውድድር ዘመን እኚሁ ዳኛ የፈፀሙበንን በደል በቪዲዮ አስደግፈን ማቅረባችን የማይዘነጋ ነው:: ሆኖም ከሚመለከተው አካል ለአቤቱታችን መልስም ሆነ ጉዳዩን አስመልከቶ የተወሰደ አንዳችም የእርምት ርምጃ ስለመወሰዱ የተገለፀ ነገር ባለመኖሩ ይኸው ዘንድሮም ጥፋቶቹ ተጠናከረውና ተበራከተው ቀጥለዋል።

በቀጣይም ትኩረት በሚሹ ወሳኝ ጨዋታዎች ላይ ጥንቃቄ ካልተደረገ በስተቀር የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር በዳኝነት በደሎች የተነሳ ከፍተኛ ውዝግብ ውስጥ ሊገባ እንደሚችል መገመት እያዳግትም። ስለሆነም የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንም ሆነ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አ.ማ. በብርቱ ሊያሰቡበት የሚገባና አስቸኳይ ትምህርት ሰጪ ርምጃዎችን በመውሰድ ሁኔታዎችን መቆጣጠር አስፈላጊ መሆኑን ማስገንዘብ እንወዳለን።”

kuasmeda / ኳስሜዳ

03 Feb, 04:14


አርሰናል ከማን ሲቲ ሃይላይት

kuasmeda / ኳስሜዳ

02 Feb, 19:25


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
ታላቁ ደርቢ ያለ ግብ ሲጠናቀቅ አሊቶዎቹ ከአራት ጨዋታዎች በኋላ ድል ቀንቷቸዋል

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 18ኛ ሳምንት ጨዋታዎች በዛሬው ዕለት መደረግ ሲጀምሩ የሸገር ደርቢ ያለ ግብ ሲጠናቀቅ ሲዳማ ቡና ስሁል ሽረን አሸንፏል።

በዕለቱ ቀዳሚ መርሐግብር ተጠባቂ በነበረው እና ኢንተርናሽናል ዋና ዳኛ ቴዎድሮስ ምትኩ በርካታ አወዛጋቢ ውሳኔዎችን ባሳለፉበት የሸገር ደርቢ ጨዋታ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ኢትዮጵያ ቡና ነጥብ ተጋርተዋል።

የሀገሪቱ ትልቁ ደርቢ በሆነው በዚህ መርሐግብር ምንም እንኳን እንደ ቀደሙት አመታት ባይሆንም በዘንድሮው የውድድር ዘመን ከተደረጉት ጨዋታዎች አንፃር በርካታ ቁጥር ያላቸው ደጋፊዎች ተገኝተዋል።

የጨዋታው የመጀመሪያው አጋማሽ እምብዛም በሙከራዎች ያልታጀበ ሲሆን በሁለቱም በኩል በተለይም በመስመር በኩል የሚደረጉ የማጥቃት ሂደቶች ውጤታማ አልነበሩም።

ወደ ግብ ክልል በመድረስ የተሻሉ የነበሩት ቅዱስ ጊዮርጊሶች በፍፁም ጥላሁን በኢትዮጵያ ቡና በኩል ደግሞ በበፍቃዱ አለማየሁ ያደረጓቸው ሙከራዎች በግብ ጠባቂዎቹ ተመልሰዋል።

በአጋማሹ ተገኑ ተሾመ በሳጥኑ የቀኝ አቅጣጫ ይዞት የገባውን ኳስ ይዞ ለማለፍ ሲሞክር በበፍቃዱ አለማየሁ ጥፋት ቢሰራበትም የጨዋታው ዋና ዳኛ ቴዎድሮስ ምትኩ በዝምታ ማለፋቸው አነጋጋሪ ሆኗል።

በጨዋታው የመጀመሪያ አጋማሽ ላይ ከነበሩት ክስተቶች መካከል የበረከት ወልዴ መጎዳት ሲሆን ተጫዋቹ ለተጨማሪ ህክምና ወድያውኑ ወደ ሆስፒታል ተወስዷል።

የሁለተኛው አጋማሽ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ የተሻለ ፉክክር ፣ የተሻሉ የግብ ሙከራዎች እንዲሁም በርካታ ካርዶችም የተመዘዙበት ነበር።

በጨዋታ ረገድ ቡናማዎቹ በአማካይ ክፍል ላይ አሜሪካዊውን ኪሩቤል ደሳለኝ እና ሚኪያስ ፀጋዬን ቀይረው በማስገባት ያደረጉት የተጫዋቾች ለውጥ በተለይም በመሀል ሜዳው ላይ ብልጫ እንዲወስዱ ያስቻላቸው ሲሆን ጠንካራ የግብ ሙከራዎችንም ማድረግ ችለው ነበር።

በአጋማሹ ዲቫይን ዋቹኩዋ ፣ ኪሩቤል ደሳለኝ ፣ አንተነህ ተፈራ እንዲሁም ሚኪያስ ፀጋዬ ለግብ የቀረቡ ጠንካራ የግብ ዕድሎችን መፍጠር ችለው ነበር።

በተለይም ሚኪያስ ፀጋዬ የግቡ ቋሚ የመለሰበት እንዲሁም አንተነህ ተፈራ ለጥቂት ከግቡ አግዳሚ በላይ የወጣበት የግንባር ኳስ ለቡናማዎቹ አስቆጪ የግብ ሙከራዎች ነበሩ።

በቅዱስ ጊዮርጊስ በኩል ደግሞ ፍፁም ጥላሁን እና አብዱ ሳሚዮ ቻታኮራ ከቅጣት ምት በቀጥታ ወደ ግብ ያደረጓቸው ጠንካራ ሙከራዎች በዳንላድ ኢብራሂም በግሩም ሁኔታ ግብ ከመሆን ድነዋል።

በሁለተኛው አጋማሽ በፍፁም ጥላሁን እና በቀድሞው የኢትዮጵያ ቡና ተጫዋች አብዱልሀፊዝ ቶፊቅ ላይ በፍፁም ቅጣት ምት ሳጥኖች ውስጥ ጥፋት ቢሰራባቸውም በጨዋታው አወዛጋቢ ውሳኔዎችን ሲወስኑ በነበሩት ኢንተርናሽናል ዋና ዳኛ ቴዎድሮስ ምትኩ በዝምታ ታልፈዋል።

ጨዋታው ያለ ግብ ከተጠናቀቀ በኋላ ቅዱስ ጊዮርጊስ ነጥቡን 29 ያደረሰ ሲሆን ኢትዮጵያ ቡና በበኩሉ ነጥቡን 23 አድርሷል።

በ19ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ቅዱስ ጊዮርጊስ ከሀድያ ሆሳዕና እንዲሁም ኢትዮጵያ ቡና ከመቻል በመጪው ቅዳሜ የካቲት 1 ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።

በዕለቱ ሁለተኛ መርሐግብር ደግሞ ሲዳማ ቡና ስሁል ሽረን 1 – 0 በማሸነፍ ከአራት ተከታታይ ጨዋታዎች በኋላ ወደ ድል ተመልሷል።

አመሻሽ 12:00 ጀምሮ በተደረገው የሲዳማ ቡና እና ስሁል ሽረ ጨዋታ ደግሞ የመስፍን ታፈሰ የ50ኛ ደቂቃ ግብ ለአሊቶዎቹ ሶስት ነጥቦችን ለማሳካት በቂ ነበር።

ውጤቱንም ተከትሎ ሲዳማ ቡና ነጥቡን 22 በማድረስ በጊዜያዊነት ከ12ኛ ወደ 9ኛ ደረጃ ከፍ ማለት ችሏል።

ስሁል ሽረ በበኩሉ የውድድር ዓመቱን ስምንተኛ ሽንፈት በማስተናገድ በወራጅ ቀጠና ውስጥ ለመቆየት ተገዷል።

በቀጣይ ሳምንት መርሐግብር ሲዳማ ቡና ከአዳማ ከተማ እንዲሁም ስሁል ሽረ ከወልዋሎ አዲግራት ይጫወታሉ።

kuasmeda / ኳስሜዳ

02 Feb, 11:44


kuasmeda / ኳስሜዳ pinned «የዛሬውን ተጠባቂ ጨዋታ ማን ያሸንፍ ይመስሎታል?»

kuasmeda / ኳስሜዳ

31 Jan, 19:24


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
መድኅን መሪነቱን ሲያጠናክር አፄዎቹ ከአራት ጨዋታዎች በኋላ ድል አድርገዋል

በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 17ኛ ሳምንት የመጨረሻ ቀን ጨዋታዎች በዛሬው ዕለት ሲደረጉ ኢትዮጵያ መድኅን እና ፋሲል ከነማ ሶስት ነጥቦችን አሳክተዋል።

በቀዳሚው ጨዋታ የሊጉ መሪ ኢትዮጵያ መድኅን በሶስት ርቆ ነጥቦች ከኋላው የሚከተለውን ሀድያ ሆሳዕናን ገጥሞ 1 – 0 አሸንፏል።

በጨዋታው የማሸነፊያውን ብቸኛ ግብ ዳዊት ተፈራ በ55ኛው ደቂቃ ላይ አስቆጥሯል። ዳዊት ይህን ግቡንም ተከትሎ በውድድር ዓመቱ ያስቆጠራቸውን የግብ ብዛቶች አራት አድርሷል።

በአሰልጣኝ ገብረመድህን ኃይሌ የሚመራው ኢትዮጵያ መድኅን ነጥቡን 32 በማድረስ በአራት ነጥቦች ልዩነት ሊጉን መምራት ቀጥሏል።

https://i0.wp.com/www.hatricksport.net/wp-content/uploads/2023/05/OMEGA_ADS.jpg?resize=1170%2C214&ssl=1

https://i0.wp.com/www.hatricksport.net/wp-content/uploads/2025/01/IMG_20250131_161825_259.jpg?resize=1170%2C780&ssl=1 ተከታታይ ሁለተኛ ሽንፈት ያስተናገደው ሀድያ ሆሳዕና በበኩሉ በ26 ነጥቦች 3ኛ ደረጃ ላይ ለመቆየት ተገዷል።

ኢትዮጵያ መድኅን በ18ኛ ሳምንት መርሐግብር ከፋሲል ከነማ ሲጫወት ሀድያ ሆሳዕና በበኩሉ ከአርባምንጭ ከተማ ይገናኛል።

በዕለቱ ሁለተኛ መርሐግብር ደግሞ ፋሲል ከነማ ድሬዳዋ ከተማን 2 – 1 አሸንፏል።

ለአፄዎቹ ሀብታሙ ተከስተ በ27ኛው ደቂቃ ላይ አንዋር ሙራድ ደግሞ በ46ኛው ደቂቃ ላይ ግቦቹን አስቆጥረዋል።

https://i0.wp.com/www.hatricksport.net/wp-content/uploads/2025/01/IMG_20250131_182709_853.jpg?resize=1170%2C780&ssl=1 ሙኽዲን ሙሳ በ53ኛው ደቂቃ ላይ ድሬዳዋ ከተማን ከሽንፈት ያልታደገች ግብ ማስቆጠር ችሏል።

ድሉ ለአፄዎቹ ከአራት ጨዋታዎች በኋላ የተገኘ ሲሆን ድሬዳዋ ከተማ ለተከታታይ ስድስተኛ የሊግ ጨዋታ ያለ ድል የተጓዘበትን ውጤት አስመዝግቧል።

ፋሲል ከነማ ነጥቡን 20 በማድረስ ወደ 9ኛ ደረጃ ከፍ ሲል ድሬዳዋ ከተማ በበኩሉ በ19 ነጥቦች 11 ደረጃ ላይ ለመቆየት ተገዷል።

በቀጣይ ሳምንት መርሐግብር ፋሲል ከነማ ከኢትዮጵያ መድኅን ድሬደዋ ከተማ ደግሞ ከወልዋሎ ኢዲግራት ይገናኛሉ።

The post መድኅን መሪነቱን ሲያጠናክር አፄዎቹ ከአራት ጨዋታዎች በኋላ ድል አድርገዋል first appeared on ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ.

The post መድኅን መሪነቱን ሲያጠናክር አፄዎቹ ከአራት ጨዋታዎች በኋላ ድል አድርገዋል appeared first on ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ.

kuasmeda / ኳስሜዳ

31 Jan, 18:22


#ኬይላን ምባፔ የማድሪድ ህይወቱ እየተረጋጋ እየመጣ ይመስላል የላሊጋውን የወሩ ምርጥ ተጫዋች ማሸነፍ ችሏል።

kuasmeda / ኳስሜዳ

31 Jan, 12:19


#የአዲሱ የሻምፒዮንስ ሊግ ፎርማት የጥሎ ማለፍ ድልድል የወጣ ሲሆን ከወዲሁ ማንችስተር ሲቲ ከ ሪያል ማድሪድ የሚያደርጉት የጥሎ ማለፍ ጨዋታ ተጠባቂ ሆኗል።

👉 የመጀመሪያ ዙር ጨዋታዎች የካቲት 4 እና 5 ሲደረጉ የመልስ ጨዋታዎች የካቲት 11 እና 12 የሚደረጉ ይሆናል።

👉 ሙሉ መረጃውን የያዘው ሰንጠረዥ ይህን ይመስላል።

kuasmeda / ኳስሜዳ

30 Jan, 19:21


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
ሀዋሳ ከተማ ወደ አሸናፊነት ሲመለስ ወልዋሎ አዲግራት ነጥቡን ከፍ ያደረገበትን ውጤት አስመዝግቧል

በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 17ኛ ሳምንት የሶስተኛ ቀን ጨዋታዎች በዛሬው ዕለት ሲደረጉ ሀዋሳ ከተማ ከ103 ቀናት በኋላ ሶስት ነጥቦችን አሳክቷል።

አመሻሽ 12:00 ጀምሮ በተደረገው ጨዋታ የሊጉ የሁለት ጊዜ ሻምፒዮን ሀዋሳ ከተማ ከመሪዎቹ ተርታ የሚገኘው መቻልን 1 – 0 አሸንፏል።

በጨዋታው ኤርትራዊው ዓሊ ሱሌማን በ54ኛው ደቂቃ ላይ ያስቆጠረው ግብ ለሀይቆቹ አሸናፊነት በቂ ሆኗል።

ለበርካታ ቀናት እና ሳምንታት ከድል የራቀው ሀዋሳ ከተማ የመጨረሻ ድሉን ጥቅምት ዘጠኝ ቀን ሀድያ ሆሳዕናን 2 – 1 በረታበት ጨዋታ ላይ ማስመዝገቡ ይታወሳል።

ውጤቱን ተከትሎ ሀዋሳ ከተማ ነጥቡን 15 በማድረስ ደረጃውን ወደ 16ኛ ከፍ ማድረግ ችሏል።

ድል አድርጎ የሊጉን መሪነት ዳግም መረከብ የሚችልበትን ዕድል ያመከነው መቻል በ27 ነጥብ 3ኛ ደረጃ ላይ ለመቆየት ተገዷል።

ቡድኑ የዛሬውን ጨምሮ ካለፉት ተከታታይ አራት ጨዋታዎች ማግኘት ከሚገባው 12 ነጥቦች ማግኘት የቻለው ሶስቱን ብቻ ነው።

በ18ኛ ሳምንት መርሐግብር ሀዋሳ ከተማ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሲጫወት መቻል በበኩሉ አራፊ ቡድን ነው።

በዕለቱ በቀዳሚነት ከቀን 9:00 ጀምሮ በተደረገው ጨዋታ ወልዋሎ አዲግራት ለተከታታይ ሶስተኛ ጨዋታ ከሽንፈት የራቀበትን ውጤት አስመዝግቧል።

ቡድኑ በ55ኛው ደቂቃ ላይ በዳዋ ሆጤሳ አማካይነት በፍፁም ቅጣት ምት በተቆጠረ ግብ ለ13 ያህል ደቂቃዎች መሪ መሆን ችሎ ነበር።

በ68ኛው ደቂቃ ላይ ግን ፍቃዱ አለሙ ኤልፓን አቻ ያደረገ ግብ ከመረብ አሳርፏል።

ዳዋ ሆጤሳ ከ259 ቀናት እንዲሁም ፍቃዱ አለሙ ከ225 ቀናት በኋላ በሊጉ ግብ ያስቆጠሩበት ጨዋታ ሆኗል።

ውጤቱን ተከትሎ ወልዋሎ አዲግራት ነጥቡን 6 ሲያደርስ ኢትዮ ኤሌክትሪክ በበኩሉ 19 አድርሷል።

በ18ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ወልዋሎ አዲግራት ከድሬዳዋ ከተማ እንዲሁም ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከአዳማ ከተማ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።

kuasmeda / ኳስሜዳ

30 Jan, 11:21


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
አህመድ ሁሴን ለአንድ ወር ከሜዳ ይርቃል

የአርባምንጭ ከተማው የፊት አጥቂ አህመድ ሁሴን ቡድኑ ከመቀሌ 70 እንደርታ ባደረገው ጨዋታ ላይ ጉዳት ማስተናገዱ ይታወሳል።

በ89ኛው ደቂቃ ላይ ከቀኝ መስመር የተሻገረለትን ኳስ ለማስቆጠር በሚያደርገው ጥረት ጉዳቱን ያስተናገደው አጥቂው ጨዋታውን ለመጨረስ ሳይችል ቀርቷል።

በጨዋታው ላይ የቡድኑን ቀዳሚ ግብ አስቆጥሮ የነበረም ሲሆን በአዲስ አበባ ተጨማሪ ምርምራ ካደረገ በኋላ በጉልበቱ የውጪኛው ክፍል ላይ የአጥንት ጉዳት ማስተናገዱ ተረጋግጧል።

ይህንንም ተከትሎ የአዞዎቹ እጅግ ወሳኝ ተጫዋች የሆነው አህመድ ለሁለት ወራት ያህል ከሜዳ እንደሚርቅ እርግጥ ሆኗል።

አህመድ ሁሴን በውድድር ዘመኑ 14 የሊግ ጨዋታዎች ላይ ለ1,191 ደቂቃዎችን የተጫወተ ሲሆን 7 ግቦችን በማስቆጠርም የሊጉን ኮከብ ግብ አግቢነት ከአንተነህ ተፈራ እና ያሬድ ብርሀኑ ጋር በጥምር እየመራ ይገኛል።

ይህንንም ተከትሎ የአዞዎቹ እጅግ ወሳኝ ተጫዋች የሆነው አህመድ ለአንድ ወር ያህል ከሜዳ እንደሚርቅ እርግጥ ሆኗል።

kuasmeda / ኳስሜዳ

29 Jan, 19:21


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
የመዲናዋ ክለቦች ከደርቢው ጨዋታ በፊት ወሳኝ ድሎችን አስመዝግበዋል

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 17ኛ ሳምንት የሁለተኛ ቀን መርሐግብሮች በዛሬው ዕለት ሲደረጉ የአዲስ አበባዎቹ ክለቦች ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ኢትዮጵያ ቡና ድል ቀንቷቸዋል።

ከ9:00 ጀምሮ በተደረገው ቀዳሚው ጨዋታ ፈረሰኞቹ የጦና ንቦቹን 2 – 0 አሸንፈዋል።

እስከ 76ኛው ደቂቃ ድረስ ያለ ግብ በተጓዘው ጨዋታ አብዱ ሳሚዮ ቻታኮራ ቅዱስ ጊዮርጊስን መሪ ያደረገ ግብ በ77ኛው ደቂቃ ላይ አስቆጥሯል።

ከስምንት ደቂቃዎች በኋላ ደግሞ አማኑኤል ኤርቦ ሁለተኛ ግብ አክሎ ጨዋታው በቅዱስ ጊዮርጊስ የ2 – 0 አሸናፊነት እንዲጠናቀቅ አድርጓል።

አማኑኤል ኤርቦ በጨዋታው ያስቆጠረውን ግብ ተከትሎ በውድድር ዓመቱ ያስቆጠራቸውን የግብ ብዛቶችንም 6 ማደረስ ችሏል።

ፈረሰኞቹ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ስታድየም ያላቸውን መልካም ውጤት ያስቀጠሉበት ውጤት ሆኖ ተመዘግቧል።

ቡድኑ ነጥቡን 28 በማድረስም በመጪው አርብ ጨዋታውን ከሚያደርገው የሊጉ መሪ ኢትዮጵያ መድኅን ያለውን የነጥብ ልዩነት አንድ ብቻ አድርጓል።

በ18ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ቅዱስ ጊዮርጊስ ከኢትዮጵያ ቡና ሲጫወት ወላይታ ድቻ በበኩሉ ከመቀሌ 70 እንደርታ ይጫወታል።

በዕለቱ ሁለተኛ መርሐግብር ደግሞ ኢትዮጵያ ቡና ባህርዳር ከተማን ከስድስት ዓመታት በኋላ ያሸነፈበትን ድል አስመዝግቧል።

ቡናማዎቹ 3 – 1 ባሸነፉበት ጨዋታ ኮንኮኒ ሀፍዝ በ6ኛ እና 36ኛ ደቂቃዎች ላይ እንዲሁም አንተነህ ተፈራ በ89ኛው ደቂቃ ላይ ግቦቹን አስቆጥረዋል።

አንተነህ ተፈራ ከያሬድ ብርሀኑ እና አህመድ ሁሴን በመቀጠል በውድድር ዓመቱ 7ኛ የሊግ ግብ ያስቆጠረ ተጫዋች ሆኗል።

በጨዋታው ሙጂብ ቃሲም ባህርዳር ከተማን ከሽንፈት ያልታደገች ግብ በ15ኛው ደቂቃ ላይ ማስቆጠር ችሎ ነበር።

ኢትዮጵያ ቡና ድሉን ተከትሎ ነጥቡን 22 በማድረስ ወደ ሰባተኛ ደረጃ ከፍ ማለት ችሏል።

ባህርዳር ከተማ በበኩሉ ወደ ሊጉ መሪዎች ከፍ ማለት የሚችልበትን ዕድል ሳይጠቀም በመቅረቱ በ23 ነጥቦች 5ኛ ደረጃ ላይ ለመቆየት ተገዷል።

በቀጣይ ሳምንት ጨዋታዎች ኢትዮጵያ ቡና ከቅዱስ ጊዮርጊስ ሲጫወት ባህርዳር ከተማ አራፊ ቡድን ነው።

kuasmeda / ኳስሜዳ

29 Jan, 15:20


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
ፍሬው ኃይለገብርኤል የወሩ ኮከብ አሰልጣኝ በመሆን ተመረጠ

የኡጋንዳው ካምፓላ ኩዊንስ አሰልጣኝ የሆነው ፍሬው ኃይለ ገብርኤል የኡጋንዳ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የታህሳስ ወር ኮከብ አሰልጣኝ በመሆን ተመርጧል።

የቀድሞው የሉሲዎቹ አሰልጣኝ በወሩ ቡድኑን እየመራ ባደረጋቸው አራት ጨዋታዎች በሶስቱ ሲያሸንፍ በአንዱ ነጥብ ተጋርቷል።

ቡድኑ በታህሳስ ወር ላይ ቱሮ ኩዊንስን 2 – 1 ፤ ኦሊላ ኤች ኤስን 3 – 0 ፣ ካዌምፔ ሙስሊም ሌዲስን 4 – 1 ሲረታ ከሺ ማሩንስ 0 – 0 ተለያይቷል።

አሰልጣኝ ፍሬው የወሩ ኮከብ ሆኖ መመረጡን ተከትሎም የ500 ሺህ የኡጋንዳ ሽልንግ እና የዋንጫ ሽልማት ተበርክቶለታል።

በአሰልጣኝ ፍሬው ኃይለገብርኤል የሚመራው ካምፓላ ኩዊንስ በሊጉ ካዳረጋቸው 11 ጨዋታዎች በ7 አሸንፎ በ4 አቻ በመለያየት በ25 ነጥቦች ሊጉን በመምራት ላይ ይገኛል።

kuasmeda / ኳስሜዳ

28 Jan, 19:21


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ወደ ድል ሲመለስ መቀሌ 70 እንደርታ እና አርባምንጭ ከተማ ነጥብ ተጋርተዋል

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት ጨዋታዎች በዛሬው ዕለት በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ስታድየም መደረግ ጀምረዋል።

በቀዳሚው ጨዋታ የተገናኘቱ መቀሌ 70 እንደርታ እና አርባምንጭ ከተማ በ2 – 2 ውጤት ጨዋታቸውን አጠናቀዋል።

ያሬድ ብርሀኑ በሰባተኛው ደቂቃ ላይ በፍፁም ቅጣት ምት ያስቆጠረው ግብ ምዓም አናብስቱን በጊዜ መሪ ማድረግ ችሎ ነበር።

ነገር ግን የመቀሌ 70 እንደርታዎች የ1 – 0 መሪነት ለ11 ደቂቃዎች ብቻ ነበር መቆየት የቻለው።

በ16ኛው ደቂቃ ላይ አህመድ ሁሴን ከግብ ጠባቂው ፋሪስ አለዊ ከረጅም ርቀት የደረሰውን ኳስ በግንባር በመግጨት አስቆጥሯል።

ያሬድ ብርሀኑ እና አህመድ ሁሴን ያስቆጠሯቸውን ግቦች ተከትሎ በውድድር ዘመኑ ያስቆጠሯቸውን የግብ ብዛቶች 7 በማድረስ የኮከብ ግብ አግቢነቱን በጋራ መምራት ጀምረዋል።

በ32ኛው ደቂቃ ላይ ደግሞ ቦና አሊ ያስቆጠረው ግብ መቀሌ 70 እንደርታን ዳግም መሪ አድርጓል።

ጨዋታው በሁለተኛው አጋማሽ 60ኛ ደቂቃ ላይ ሲደርስ ፍቃዱ መኮንን ግሩም የግንባር ኳስ አስቆጥሮ የጨዋታውን ውጤት 2 – 2 አድርጓል።

የዘጠኝ ሰዓቱ ጨዋታ ተጨማሪ ግብ ሳያስተናግድ በሁለት አቻ ውጤት ተጠናቋል።

ውጤቱን ተከትሎ አርባምንጭ ከተማ ነጥቡን 23 በማድረስ በግብ ክፍያ በልጦ 5ኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ መቀሌ 70 እንደርታ በበኩሉ በ22 ነጥቦች በነበረበት የ7ኛ ደረጃ ለመቆየት ተገዷል።

በቀጣይ ሳምንት መርሐግብር መቀሌ 70 እንደርታ ከወላይታ ድቻ እንዲሁም አርባምንጭ ከተማ ከሀድያ ሆሳዕና ይጫወታሉ።

በዕለቱ ሁለተኛ መርሐግብር ደግሞ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አዳማ ከተማን በመጨረሻ ደቂቃ ግቦች 2 – 0 ረቷል።

ኤፍሬም ታምራት በ88ኛው ኪቲካ ጀማ ደግሞ በ90+5 ደቂቃዎች ላይ የዓምናውን ሻምፒዮን አሸናፊ ያደረጉ ግቦችን አስቆጥረዋል።

ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከሁለት ጨዋታዎች በኋላ ወደ ድል የተመለሰበት ሲሆን አዳማ ከተማ በበኩሉ ተከታታይ አራተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደበት ጨዋታ ሆኗል።

ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ነጥቡን 18 በማድረስ ወደ 13ኛ ደረጃ ከፍ ሲል አዳማ ከተማ በበኩሉ በ15 ነጥቦች በነበረበት 15ኛ ደረጃ ላይ ለመቆየት ተገዷል።

በ18ኛው ሳምንት ጨዋታዎች ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከሀዋሳ ከተማ እንዲሁም አዳማ ከተማ ከኢትዮ ኤሌክትሪክ ይጫወታሉ።

kuasmeda / ኳስሜዳ

28 Jan, 07:19


ግር ኳስ ያለው አመለካከት እንዲቀየር በክልሎች ያሉ ተጫዋቾችም እንዲነቃቁ እና እንዲጫወቱ እድል ይፈጠራል እና እነዚህ ናቸው ቢስተካከሉ ብዬ የማስበው።

ሀትሪክ – በአውሮፓ የመጫወት ዕድል ብታገኚ መጫወት የምትፈልጊበት ክለብ ?

ማህሌት – አውሮፓ ውስጥ ዕድል ባገኝ መጫወት የምፈልገው ማድሪድ ነው። የማድሪድ ደጋፊ ስለሆንኩ ማድሪድ ብጫወት በጣም ደስ ይለኛል። ከእንግሊዝ ደግሞ ማንችስተር ዩናይትድ ብጫወት በጣም ደስ ይለኛል።

ሀትሪክ – በሊጉ ላይ ካሉ ተጫዋቾች አብሬያት ብጫወት የምትያት ተጫዋች ማናት ?

ማህሌት – ወደ ፊት ሰናይት ቦጋለን ባገኛት ሊጉ ላይ ተፎካካሪ ግብ አግቢ ብቻ ሳይሆን አንደኛ ኮከብ ግብ አግቢ ሆኜ እንደምጨርስ አምናለሁ። በጣም ደስ የምትል አጥቂዎችን ብቻ እየመገበች የምትጫወት የምመኛት አይነት አማካይ ተጫዋች ናት።በጣም ትመቸኛለች።

ሀትሪክ – መልበስ የምትወጂው ቁጥር ? ለምን ?

ማህሌት – መልበስ የምወደው ቁጥር 13 ነው። የተወለድኩበትም ወር 13ኛ ወር ውስጥ ሲሆን እናም የሩፋኤል ቤተክርስትያን ውስጥ ስላደግኩኝ ነው። የሆነ ጊዜ ላይ ታምሜ ሩፋኤል ቤተክርስቲያን ሄጄ ፀሎት ተደርጎልኝ ነው የዳነኩት። መንትያ እህት ነበረችኝ እና መንትያዬ ስታርፍ እኔ ደግሞ እየተጣጣርኩኝ ነበር። ከዛ እናቴ ተሳለች ሩፋኤል ቤተክርስቲያን በዛን ወቅት ዳንኩኝ ማለት ነው ለዛም ነው 13 ቁጥርን የምለብስበት ምክንያት።

ሀትሪክ – ሜሲ ወይስ ሮናልዶ ?

ማህሌት – ምንም ጥርጥር የለውም። ክርስቲያኖን ነው በጣም የምወደው ለኔ ልዩ ነው። ሜሲም ይችላል ግን ክርስቲያኖ ሮናልዶ ለኔ በጣም ልዩ ነው።

ሀትሪክ – የምትወጂው ምግብ ?

ማህሌት – ሁሉንም ምግብ እወዳለሁ። በይበልጥ የምወደው ቤተሰብም ያሳደገኝ ክትፎ ነው። ክትፎ በጣም እወዳለሁ። ክትፎ ስፖርተኛ ብዙም አይወድም ግን አሁን ላይ እግር ኳሱ ላይ ከገባሁ በኋላ ማዘውተር ትቻለሁ ግን በጣም የምወደው እሱን ነው። ቅንጬም በጣም እወዳለሁ።

ሀትሪክ – ጠዋት ስትነሺ መጀመሪያ የምታደርጊው ነገር ?

ማህሌት – ጠዋት ስነሳ መጀመሪያ የማደርገው ፀሎት ነው። ከዛ በኋላ ልምምድ ካለ ከፀሎት በኋላ ወደ ልምምድ እሄዳለሁ ልምምድ ከሌለ ደግሞ ቤተክርስቲያን ሄደን እንመጣለን።

ሀትሪክ – ቅፅል ስምሽ ?

ማህሌት – ቅፅል ስም የለኝም ግን ትንሿ ሎዛ ይሉኛል ፣ ሀላንድ ይሉኛል ብዙ አለ CR7ም የሚለኝ አለ። ቅፅል ስም ይሄ አለ የምለው የለም ሁሉም በሚፈልገው ነው የሚጠራኝ።

ሀትሪክ – ከኢትዮጵያውያን ሴት ተጫዋቾች በተለየ የምታደንቂያቸው ?

ማህሌት – ቅድም እንዳልኩህ ሰናይተ ቦጋለ በጣም ትመቸኛለች። በጣም ምርጥ አማካይ ናት።ከአጥቂ ከተባለ ሎዛ አበራ ፣ ሴናፍ ዋቁማ እና ሀና ቶርጋ የምትባል ተጫዋች ነበረች። ሲጫወቱ በጣም ደስ ይሉኛል።

ሀትሪክ -እግር ኳስ ተጫዋች ባትሆኚ ኖሮ ምን ትሆኚ ነበር ?

ማህሌት – ነጋዴ የምሆን ይመስለኛል። በቤተሰብም ስራ እንሰራ ነበረ። ማለት እኛ ቤታችን ብዙ አይነት ስራዎችን እየሰራን ነው ያደግነው። ይሄ ይሄ ነው ብዬ ማብራራት አልችልም። ታዳጊ እያለሁ እንኳን ሳምቡሳ እየሸጥኩ በቆሎ እየሸጥኩ ነበር ያደግኩት እና ነጋዴ የምሆን ይመስለኛል።

ሀትሪክ – በመጨረሻም ማመስገን የምትፈልጊያቸው ካሉ …

ማህሌት – እዚህ ለመድረሴ እዚህ ለመቆሜ ምስጋና ለመድኃኒዓለም እናት ለቅድስተ ድንግል ማርያም ይሁንልኝ። ፈጣሪዬን አመሰግናለሁ። በመቀጠል ቤተሰቤን ፤ ቤተሰቤ ከጎኔ ሆኖ ምን በላሽ ምን ጠጣሽ እያሉ አካዳሚ ሆኜ እንኳን ምግብ በምሳ ዕቃ ቋጥረው ይልኩልኝ ነበር። ቤተሰቤን በጣም ማመስገን እፈልጋለሁ። ወንድሞቼን እህቶቼን ታናናሾቼ ሳይቀር ተነሺ ሂጂ ልምምድ ሂጂ እያሉ ያበረታታቱኛል።

የደብረዘይት አሰልጣኞቼን ቅድም የጠቀስኳቸው እነ ቶማስ ፣ መንጌ ፣ ሰናይት ፣ መሐመድ ፣ ፍሬው ፣ ኤርሚያ(ነብሶ) በጣም ነው የማመሰገንናችሁ ክበሩልኝ።

አካዳሚ በነበርኩበት ሰዓት ላይ ደግሞ እነ አስናቀ ፣ ኩመራ በቀለ ፣ አብዮት በጣም ነው የማመሰግነው እና እዛ ያሉ ሙሉ የአካዳሚ ተጫዋቾች እና ሰራተኞች በጣም ነው የማመሰግነው።

አሁን ላይም በውስጥ መስመርም ስማችሁን ያልተጠቀስኩም ሰዎች በጣም ነው የማመሰግናችሁ ክበሩልኝ።

ሀትሪክ – አመሰግናለሁ ።

ማህሌት – አመሰግናለሁ።

kuasmeda / ኳስሜዳ

28 Jan, 07:19


ይሄን ያህል ግፊት አልነበረም። ታላቅ ወንድም እና እህቴ ደብረዘይትን ወክለው ተጫውተዋል። ግን እንደ ማንኛውም ማህበረሰብ ስራ እየሰራን ስለነበረ የተወሰነ ጫና ነበረው። አካዳሚ ራሱ ስንሄድ እኔ እና እህቴ ነበርን የተመለመልነው እና ሁለታችሁ እንኳን ቢደርሳችሁ በዕጣ ነበር ትሄዳላችሁ የተባልነው ፤ እና እንደ አጋጣሚ እኔ ተመርጬ እኔ ሄድኩኝ እንጂ ከቤተሰብ ጋር ይሄን ያህል ቁጣ የሚያስነሳ ነገር አልነበረም ። እንደውም አንዳንዴ ቀምጣ ምናምን ይገዛልን ነበር።

እዚህ ለመድረስ ያበቁኝ ቤተሰቦቼ በመሆናቸውም በጣም ደስ ይለኛል። ይረዱኛል። አባቴም ስለ ኳስ ስለሚያውቅ ለእናቴም ያስረዳታል። በጣም ደስ ይል ነበር በቤተሰብ ዘንድ ያገኘሁት አቀባበል።

ሀትሪክ -በእግር ኳስ ሕይወትሽ ትልቅ አስተዋጽኦ ያበረከተልሽ ማነው ?

ማህሌት – ይሄ ይሄ ለማለት ይከብደኛል። ደብረዘይት ላይ አራት ሰው ጋር ተጫውቻለሁ ። ነብሶ ፣ ቶማስ ፣ መንጌ እና ሰናይት የምትባል አሰልጣኝ አለች እነሱጋር ስራዬ ብዬ በሚገባ ሰርቻለሁ።

ክረምት ላይ ስመጣ የደብረዘይት ህዝብ ሁሉ ለኔ አስተዋጽኦ አድርጎልኛል። ወደ ፕሮፌሽናሊዝም ደግሞ መጓዝ ስጀምር ኩመራ በቀለ አለ በአካዳሚ ደረጃ አብዮት እንዲሁም አስናቀ አለ። አካዳሚ እያለሁ ዶክተሮቹ ሳይቀሩ አስተዋጽኦ አበርክተውልኛል።

ብቻ እግር ኳሱ ላይ እግርህን ካስገባህ የሚደግፍህ አይዞህ የሚልህ ሰው አይጠፋም ። በዛው ልክ ደግሞ ቅስምህንም የሚሰብር አትሆንም አንቺ እንዲ ነሽ አንቺ እንዲ ነሽ የሚል አለ እና በእግር ኳሱ ላይ እነዚህን ሰዎች ለኔ ተፅዕኖ ፈጥረውልኛል ብዬ አምናለሁ። አመሰግናለሁ።

ሀትሪክ -እስካሁን ካስቆጠርሻቸው ግቦች በተለየ የምታስታውሺው ወይም ምርጡ ግብሽ ?

ማህሌት – አካዳሚ እያለሁ 2015 ላይ ባህርዳር ላይ ከ16.50 ውጪ ያስቆጠርኩት ግብ አይኔ ላይ ነው። አሁንም ድረስ ማግባት የምፈልገው አይነት ጎል ነበር። ከርቀት ማግባት ደስ ይለኛል እና ተመችቶኛል ለራሴ እና አዳማ ላይም ዘንድሮ በቺፕ ያገባሁት ጎል የማልረሳቸው ጎሎቼ መካከል ናቸው።

https://i0.wp.com/www.hatricksport.net/wp-content/uploads/2025/01/photo_2025-01-27_22-16-24.jpg?resize=1170%2C780&ssl=1 ሀትሪክ – ብዙዎች በቀጣይ አመታት ላይ በኢትዮጵያ እግር ኳስ እንደምትደመቂ እና በሉሲዎቹ ማልያ ታሪክ እንደምትሰሪ ይናገራሉ። ስለነዚህ አስተያየቶች ምን ትያለሽ ?

ማህሌት – እንኳን እነሱ ይቅሩና እኔ ራሱ የማስበው ተፅዕኖ እፈጥራለሁ ብዬ የማምን እና ቆርጬ የተነሳሁ ስለሆንኩኝ እንደዚህ በማሰባቸው እና እኔ ላይ ተስፋ በመጣላቸው ደስተኛ ነኝ። ደግሞ ድጋሚ አንተ ያሰብከው እና አዕምሮክ ላይ ያቀድከው ሌላ ሰው እንደዚህ ባንተ ዕምነት ሲጥል ነገ አንተ ትተካለክ ፤ እንዲህ መንገድ ላይ ስሄድ አንቺ ማህሌት ነገ በብሔራዊ ቡድን ትትኪያለሽ ሲሉኝ በጣም ደስ ይለኛል በቃ።

ፍላጎትህ ይበልጣል በቃ ትልቅ ደረጃ እንደምትድረስ ታስባለህ እና እንደዚህ በማሰባቸው እንደዚህ ደግሞ ሞራል ሲሰጡኝ በጣም ነው ደስ የሚለኝ።

አባቴ ራሱ ደውሎ ዘንድሮ መበርታት ነው ብሔራዊ ቡድን ምናምን ሲል በጣም ደስ ይላል። እንደዚህ ተስፋ የተጣለባት ሴት ልጅ በመሆኔ በጣም ደስ ብሎኛል። እኔ ራሴን እዚህ ላይ በማግኘቴ በጣም ደስ ብሎኛል እና ተስፋቸውን እና ዕምነታቸውን ከፈጣሪ ጋር እንዲረዳኝ እና እንዳሳካ ፀሎት በማድረግ ይተባበሩኝ እኔም ደግሞ እዚህ ስራዬን በመስራት ትልቅ ደረጃ ለመድረስ እጥራለሁ።

ሀትሪክ – ኢትዮጵያውያን ሴት ተጫዋቾች ሎዛ በአሜሪካ ፥ አርያት እና አረጋሽ በታንዛኒያ ብቃታቸው በደንብ እያስመሰከሩ ነው ? የነሱ በዚህ ደረጃ መገኘት ላንቺም ሆነ ለሌሎች ሴት ተጫዋቾች የሰጣችሁ መነሳሳት እንዴት ትገልጪዋለሽ ?

ማህሌት – ገና ብሔራዊ ቡድን ተመርጬ ወደ ውጪ ወጥቼ ስጫወት እኔማ እዚህ መጥቼ መጫወት አያቅተኝም የሚል ራሴ ላይ የገነባሁት ሀሳብ ነበረኝ። እነሱ ወጥተው ሲጫወቱ እነሱ ጎል ሲያገቡ በጎሎች ላይ ሲሳተፉ በጣም ደስ ይለኛል።

በክለብ ራሱ ምግብ ልንበላ ቁጭ ስንል ኧረ እኛማ የመጫወት ዕድል አለን። እንወጣለን። እነሱ መንገዱን ከፍተውልናል እና እንጫወታለን። እነሱ አንዴ ካስጀመሩት እንጫወታለን። ብቻ ብሔራዊ ቡድናችን ውጤት ይኑረው እንጂ ወጥተን የመጫወት አቅም አለን። እየተባባልን እንመካከራለን እና የነሱ መውጣት ለኛ ጥሩ ነገር ነው የፈጠረልን።

ከመነሳሳትም ባሻገር የአፍሪካ ሀገራትም የአውሮፓ ሀገራትም ወደ እኛ እግር ኳስ ዞረው እንዲመለከቱ አድርገውታል እና በጣም ጥሩ ነው።የነሱ መውጣት ለኛ ጥሩ ሆኖልናል።

ሀትሪክ – በእግር ኳስ ትልቁ ግብሽ ምንድነው ?

https://i0.wp.com/www.hatricksport.net/wp-content/uploads/2025/01/photo_2025-01-27_22-16-03.jpg?resize=1060%2C1059&ssl=1 ማህሌት – በእግር ኳስ ትልቁ ግቤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ማልያን ለብሼ ዋንጫ ማሳካት ነው። በቃ ትልቁ አላማዬ በምንም ይሁን በምንም በትንሹም ይሁን በትልቁ የኢትዮጵያን የየሴቶች ብሔራዊ ቡድንን ወክዬ ዋንጫ ማንሳት ነው።

ከዛ ባሻገር ደግሞ ሀገር ውስጥ ብቻ አይደለም ዕቅዴ ከሀገር ወጥቼ የመጫወት ዕቅድ አለኝ። ይህንንም ደግሞ ከፈጣሪ ጋር አሳካዋለሁ ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ።

ሀትሪክ -ከእግር ኳስ ውጪ ያለሽን ጊዜ በምን ታሳልፊያለሽ ?

ማህሌት – በውድድር ጊዜ ሲሆን መፅሐፍቶችን በማንበብ ፤ በመተኛት ፤ ለኔ የሚጠቅሙኝን ማህበራዊ ድህረ ገፆች(Social Media) በመጠቀም አሳልፋለሁ።

ከውድድር ውጪ ሆነን ደግሞ ከውድድር ውጪ በምንሆንበት ጊዜ ዋና በመዋኘት ፣ ፕሌይ ስቴሽን በመጫወት ፣ ፑል በመጫወት እና ከጓደኞቼ ጋር አብሬ አሳልፋለሁ።

የበዓላት ወቅት ላይ ደግሞ ገጠር ያሉ ቤተሰቦቼ ጋር በመሄድ እዝናናለሁ አልፎ አልፎ ደግሞ የተራራኳቸውን ጓደኞቼን አገኛለሁ።

ሀትሪክ – በሴቶች እግር ኳስ ላይ መስተካከል አለባቸው የምትያቸው ነገሮች ምንምንመ ምንድናቸው ?

ማህሌት – በሴቶች እግር ኳስ ላይ ትኩረት መሰጠት አለበት። አሁን እየተሰጠ አይደለም እያልኩ ሳይሆን ሙሉ ለሙሉ ለወንዶቹ የሚሰጠውን ያህል ትኩረት ቢሰጥ በእርግጠኝነት እግር ኳሱ እስካሁን ለውጥ ይመጣ ነበረ። አሁንም ለውጥ እየመጣ ነው ግን አሁንም ተጨማሪ ለውጥ ይመጣል።

ሁለተኛው ደግሞ ለሴት የሚሰጠው ቦታ ልክ አይደለም። በአመራር ዘንድም በብዙዎች ዘንድም የሚሰጠው ትኩረት ልክ አይደለም።

አንዳንድ ክለቦች ላይ ለሴት ተጫዋቾች የሚሰጠው በደመወዝም ሆነ በትጥቅ ጉዳይ ምናምን ልክ አይደለም። ለወንዱ የደረሰው ሁሉ ለሴት መድረስ አለበት አሁን ኤልፓ እንደዚህ አይነት ነገር የለም። ማለት ሙሉ ለሙሉ ይሰጥሀል እኩል ነው የምትካፈለው ግን አንዳንድ ክለቦች ላይ ደግሞ እየተቸገሩ ይስተዋላል።

በእግር ኳሱ ላይ ትኩረት መስጠት በቃ በአጭሩ ለሴቶች ትኩረት ቢሰጥ የበለጠ ውጤት ይመጣል። የምንወዳደርባቸው ከተሞች ደግሞ ቢቀያየሩ ጥሩ ነው ብዬ ነው የማምነው። የአየር ሁኔታውን ለመልመድም የሴት እግር ኳስም እንዲህ አለ እንዴ እንዲባልም ያደርጋል።

ለምሳሌ ዘንድሮ አዲስ አበባ ተቀላቀለ ከአዳማ እና ከሀዋሳ ውጪ ደግሞ ሌሎች ከተሞች ላይ ቢሆን ሰዉም ለሴት እ[...]

kuasmeda / ኳስሜዳ

28 Jan, 07:19


ሀትሪክ – የዘንድሮው የውድድር ዘመን የመጀመሪያው አጋማሽ እንዴት ነበር ላንቺ ?

ማህሌት – ብዙም አይደለም። እንደጠበኩት አይደለም። ቡድኔን አገኘዋለሁ ብዬ የሄድኩበት አጋጣሚ ከቤቴ ተነስቼ የወጣሁበት ግብ ላይ ስላላደረስኩኝ ዘንድሮ የመጀመሪያ አጋማሽ ደስ አይልም። ቀጣይ ሁለተኛ ዙር ላይ እንደ ቡድንም አስተካክላለሁ ብዬ አስባለሁ። ያው ብዙዎቻችን አዳዲስ ተጫዋችም ስለሆንን ጊዜ ይፈልጋል ።

ሀትሪክ – በዘንድሮው የውድድር ዘመን በጨዋታ ሂደት ቦታ እየቀያየርሽ ስትጫወቺ ነበር። ይበልጥ ምቾች የሚሰጥሽ የትኛው ቦታ ላይ ስትጫወቺ ነው ?

ማህሌት – በፊት መጫወት የምፈልገው የፊት አጥቂ ቦታ ላይ ነበር ከጊዜ ሂደት በኋላ ደግሞ ወደ መስመር ስወጣ መስመርን ምርጫዬ አደረግኩት እና የመስመር ተጫዋች መሆን ይበልጥ ምቾት የሚሰማኝ ቦታ ነው።

ሀትሪክ – በሁለተኛው ዙር ምን አቅደሻል ? በግልም በክለብም ?

ማህሌት – ሁለተኛ ዙር ላይ እንደ ግል የመስመር አጥቂ ከመሆኔ አንፃር የጎል ዕድሎችን መፍጠር እና ያገኘሁትን የጎል አጋጣሚዎች በመጠቀም አሁን ላይ ካለን የደረጃ ሰንጠረዥ እና ውጤት ቡድኔን ጥሩ ደረጃ ለማድረስ ነው። እንደ ቡድን የሁላችንም አላማ እንደዚህ ነው ዕቅዳችን። ሁለተኛው ዙር ላይ ጥሩ ውጤት ይዘን ለማጠናቀቅ ነው።

ሀትሪክ – ወደ ብሔራዊ ቡድን እንምጣ እስኪ ? ለዕድሜ እርከን እና በዋናው ብሔራዊ ቡድንም መጫወት ችላሻል። ስለ እርሱ ንገሪኝ እስኪ ?

ማህሌት – የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን መጀመሪያ የተጫወትኩት በ17 አመት በታች ብሔራዊ ቡድን ነው። አሰልጣኝ እንዳልክ ይዞት በነበረው እና ታንዛኒያ ላይ በተዘጋጀው ውድድር የተሳተፈው ቡድን ላይ ተጫውቻለሁ።

ከዛ በኋላ ደግሞ አሰልጣኝ ፍሬው በዋናው ብሔራዊ ቡድን ከነ ሎዛ ጋር ጠራኝ ከዛ በኋላ ደግሞ ከ20 አመት በታች እስከ ሞሮኮ ባለው ድረስ ተጫወትኩኝ።

ቀጥሎ ከ17 አመት በታች ደግሞ አሰልጣኝ ራውዳ በያዘችው ቡድን የዓለም ዋንጫ ለማለፍ ተጫወትኩኝ ማለት ነው እና በብሔራዊ ቡድን በተሰጠኝ ዕድል ተጠቅሜያለሁ።

ሀትሪክ – ለመጀመሪያ ጊዜ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ጥሪ ሲደረገልሽ ምን አይነት ስሜት ፈጠረብሽ ?

ማህሌት – ለመጀመሪያ ጊዜ ብሔራዊ ቡድን ጥሪ የተደረገልኝ ከ17 አመት በታች ነው።ራሴን ብቃቴን ስለማውቀው ምንም አልመሰለኝም ነበር። እንኳን የፊት ተጫዋች ተከላካይ እያለው ራሱ ተጫዋቾች ሲጠሩ ሙሉ የራስ መተማመን ነበረኝ እንደምጠራ ፤ የዛኑ አመት ደግሞ በ19 ግቦች ክብረወሰን ሰብሬ የከፍተኛ ሊጉ ኮከብ ግብ አግቢ ስለነበርኩ እንደምጠራ እርግጠኛ ሆኜ ራሴን አዘጋጅቼ ነበር። እንደ አዲስ አልሆነብኝም ነበር እና በጣም ቀሎኝ እና ደስ ብሎኝ ስጫወት ነበር በብሔራዊ ቡድን።

ሀትሪክ – ተከላካይ ነበርሽ ማለት ነው ? እንዴት ወደ አጥቂነት ተቀየርሽ ?

ማህሌት – አካዳሚ ልክ እንደገባሁ ኩመራ በቀለ በተከላካይነት ነበረ ያሰለፈኝ። ሶስት አመት ከግማሽ አካባቢ በተከላካይ ቦታ ተጫወትኩ እና በአንድ ጨዋታ በእልህ ተናድጄ ከተከላካይ ተነስቼ የአጥቂ ቦታ ሄድኩና ግብ አስቆጥሬ ባገባሁት ጎል ቡድናችን አሸነፈ። በዛ ሰዓት ነበር መልሼ ወደ በፊት ቦታዬ የተመለስኩት ፤ አካዳሚ ከመግባቴ በፊት ግን አጥቂ ነበርኩ።

ሀትሪክ – በሉሲዎቹ ማልያ ምን ማሳካት ታልሚያለሽ ?

ማህሌት – በብሔራዊ ቡድን ማሳካት የምፈልገው ትልቅ ነገር ነው። የብሔራዊ ቡድን ጥሩ አገልጋይ ሆኜ ሀገሬን ከፍታ ላይ አድርሻት ማለት ጥሩ ደረጃ ላይ ማድረስ ፍላጎት አለኝ።

ሀትሪክ -በእግር ኳስ ሕይወትሽ በጣም የተደሰትሽበት እና ያዘንሽበት አጋጣሚ ?

ማህሌት – እስካሁን ባለው በዘንድሮው የውድድር ዘመን ድሬዳዋ ላይ በመጨረሻ ደቂቃዎች ግብ ያስቆጠርኩበትን አጋጣሚ ነው። በቃ በጣም ደስ ብሎኝ ነበር።

መቼም የማልረሳው ደግሞ አይሻለኝም ብዬ ተስፋ ቆርጬ ማለት ሲዳማ ቡና እያለሁ ሁለተኛ ዙር ላይ ከመቻል በነበረን ጨዋታ አዳማ ላይ ተጎድቼ ነበር።የዛን ስሜት አረሳውም መቼም።

ከዛን በኋላ ደግሞ በኔ ምክንያት ሁለት ተጫዋቾችን ጎድቼ ነበረ። ቅድስት ንግድ ባንክ እና ደማ ድሬዳዋ የነበረችው ማለት ያው እግር ኳስ ላይ ያጋጥማል። እና በነዚህ ሶስት ጨዋታዎች ላይ የማልረሳቸው አጋጣሚዎች ተፈጥረው አልፈዋል።

ሀትሪክ – ጉዳቱ ምን ያህል ከባድ ነበር ?

ማህሌት – አካዳሚ ሶስተኛ አመት ላይ እያለሁ ነው። ከፍተኛ ሊግ የገባን ሰዓት ላይ የጡንቻ መሰንጠቅ ጉዳት አጋጠመኝ እና አንድ ወር ከምናምን ቁጭ አልኩ። በዛን ወቅት ደግሞ ከኳስ አይደለም አንድ ወር አንድ ቀን መራቅ ራሱ በዛ ሰዓት ላይ ያለው ስሜት ከባድ ነው።

ሁለተኛው ደግሞ የሊጉ ውድድር አዳማ ላይ ሲደረግ ከመቻል ሁለተኛ ዙር ላይ ስንጫወት የብሽሽት ጉዳት አስተናገድኩ። እና ለረጅም ጊዜያቶች እስከ ክረምት ድረስ አልዳንኩም ነበረ። ተቀይሬ በመግባት 5 ወይም 10 ደቂቃ ምናምን እያልኩ እያገገምኩ ነበር ዓመቱን ያጠናቀኩት።

ሀትሪክ – ሴትነት እና እግር ኳስ ምን ያህል ከባድ ነው?

ማህሌት – ሴትነት እና እግር ኳስ በጣም ከባድ ነው። ማለት በኛ ሀገር ነው እንዲከብድ የሆነው የሰዉ አመላካከት ፣ የቤተሰብ አመለካከት ፣ የጎረቤት አመለካከት በጣም ከባድ ነው።እሱ ብቻ ሳይሆን በእግር ኳሱ ላይ ራሱ እኔ እስካሁን አላጋጠመኝም ግን ብዙዎቹ በክልልም ብትሔድ ፣ በፕሪሚየር ሊጉም ብትሄድ ፣ በከፍተኛ ሊጉም ብትሔድ ሴትነትን የሚፈትኑ አመራሮች አሉ። ብዙ አይነት አሰራር አለ በቃ ኳስን ወደኸው እንዳትጫወት የሚያደርጉ ሰዎች አሉ።

በኔ ላይ አልደረሰም ግን በብዙ ጓደኞቼ ታዳጊ እዚ ደብረዘይት ላይ በሚባሉ ነገሮች ላይ እንደዚህ አይነት ነገሮች ይፈጠራሉ እና ሴትነት እና እግር ኳስ ከባድ ነው።

የሴት ወጉን ትትው ነው አንዳንዶቹ ፤ አሁን እግር ኳስ ሲባል የወንድ ብቻ ስለሚመስላቸው የሴትነት ባህሪዋን ትታ ወደ እግር ኳሱ አለም የምትገባ ሴት አለች።

ሁለት ደግሞ ሴት ምን ብዙ አይነት ፈተና አለባት። ሴት ልጅ ምን ስትሆን ነው የወደፊት መንገዷን የምትመራው የሚሉት ነገሮች ሁሉ ስታ እግር ኳስን ወዳ ብዙ ነገሮችን ትታ ትገባበታለች እና አንዳንዴ በኛ ሀገር ሲሆን ደግሞ በጣም ከባድ ነው። ማህበረሰቡ ካልተቀበለ እንደውም አሁን አሁን እየተስተካከለ ስለሆነ በጣም ደስ ይላል። ግን በመስተካከል ውስጥ ደግሞ ብዙ የተሸፈኑ ገበናዎች አሉ። ሴትነታቸውን ተፈትነው ከእግር ኳሱ የወጡ ሴቶች ብዙ ሴቶች አሉ እና ሴትነት እና እግር ኳስ በጣም ከባድ ነው።

ሀትሪክ – በእግር ኳስ ሕይወትሽ የቤተሰብሽ ድጋፍ ምን ያህል ነው ?

ማህሌት – ቀደም ብዬ እንደነገርኩህ በቤተሰባችን እግር ኳስ ተጫዋቾች ስለነበሩ[...]

kuasmeda / ኳስሜዳ

28 Jan, 07:19


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
“ትልቁ ግቤ በኢትዮጵያን ብሔራዊ ቡድን ማልያ ዋንጫ ማሳካት ነው” ማህሌት ምትኩ (ኢትዮ ኤሌክትሪክ)

“ለሴቶች ትኩረት ቢሰጥ የበለጠ ውጤት ይመጣል”

“አውሮፓ ውስጥ ዕድል ባገኝ መጫወት የምፈልገው ማድሪድ ነው”

“ሰናይት ቦጋለን ባገኛት ሊጉ ላይ ኮከብ ግብ አግቢ ሆኜ እንደምጨርስ አምናለሁ”
https://i0.wp.com/www.hatricksport.net/wp-content/uploads/2023/05/OMEGA_ADS.jpg?resize=1170%2C214&ssl=1 በኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ላይ ደምቀው በመታየት ላይ ካሉ እና ለነገ ተስፋ ተጥሎባቸው ዛሬን ስማቸውን እየተከሉ ካሉት መካከል ቀዳሚዋ ናት።

ትውልዷ ከአዲስ አበባ በቅርብ ርቀት ከምትገኘው ደብረዘይት ቢሾፍቱ የሆነው ፤ የኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ የ2015 ምሩቅ የሆነቸው ፤ በኢትዮጵያ ከ17 እና ከ20 ዓመት በታች እንዲሁም በዋናው ብሔራዊ ቡድን የተጫወተች ፤ አምና በሲዳማ ቡና ዘንድሮ በኢትዮ ኤሌክትሪክ የደመቀችው ፤ በሁለቱም እግሮቿ በምቾት የምትጫወተው ማህሌት ምትኩ የሳምንቱ የሀትሪክ ስፖርት ድህረገፅ እንግዳችን ናት።

የታላላቆቿን መንገድ ተከትላ ሩቅ በመጓዝ ላይ ያለች በድንቅ ብቃቷ ከሀገር ወጥቶ ከመጫወት ባለፈ በብሔራዊ ቡድን ማልያ ዋንጫ ማሳካት አለብኝ ብላ በቆራጥነት በራሷ ላይ እየሰራች ያለች ናት።

ብዙ ተማርኩበት ስለምትለው የኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ ቆይታዋ ፤ የሲዳማ ቡና ቆይታዋ ፤ በኢትዮ ኤሌክትሪክ እያሳለፈችው ስላለው ጊዜ ፤ በዕድሜ እርከን እና ዋናው ብሔራዊ ቡድን የነበራት ቆይታ ፤ ሰለ ሩቅ ሕልሟ ፤ ከአጥቂ ወደ ተከላካይ ከተከላካይ ደግሞ ወደ አጥቂ ስለተመለሰችበት አጋጣሚ እና በሴቶች እግር ኳስ መስተካከል ስላለበት ነገርም የበሰለ አስተያየቷን ተናግራለች።

13 ቁጠር ማልያን የምትለብስበት ከቁጥርነት የዘለለ ትልቅ ምክንያት ፤ በሊጉ አብሬያት ብጫወት የሊጉ ኮከብ ግብ አግቢ እሆናለሁ ስላለቻት ተጫዋች ፤ ከሜሲ እና ከሮናልዶም ያለ ጥርጥር ብላ በቀዳሚነት የጠቀሰችውንም ተጫዋች በቃለ ምልልሱ ገልፃልናለች።

ልዩ ብቃት ፣ የላቀ የራስ መተማመን ፣ ትልቅ ህልም ፣ ለህልም መሳካት ዛሬ መልፋት ፣ ትሁትነት ፣ ከህፃንነት የጀመረ ጠንካራ ሰራተኝነት መገለጫዋ ነው።

ማህሌት ምትኩ አዲስ አበባ አበበ ቢቂላ ስታድየም ላይ በተደረገው የሴቶች ፕሪምየር ሊግ የመጀመሪያ ዙር ውድድር አምስት ግቦችን አስቆጥራለች።

ውድ የሀትሪክ ስፖርት ድህረ ገፅ ተከታታዮች ከኢትዮ ኤሌክትሪክ እና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የመስመር አጥቂዋ ማህሌት ምትኩ ጋር ሰፋ ያለ ቆይታ አድርገናል። እንደታነቡት ተጋብዛችኋል።

https://i0.wp.com/www.hatricksport.net/wp-content/uploads/2025/01/photo_2025-01-27_22-16-28-2.jpg?resize=1170%2C780&ssl=1 ሀትሪክ – እግር ኳስ የጀመረሽበት መንገድ ምን ይመስላል ?

ማህሌት – ወደ ኳስ የገባሁት ታላቅ ወንድም እና እህቴ እግር ኳስ ተጫዋች ነበሩ እና እነሱን በማየት በትምህርት ቤት ተጫወትኩኝ ከዛን በኋላም ቢሾፍቱን በመወከል በተለያዩ የኦሮሚያ ክልል ከተሞች በመሄድ ብዙ ቡድኖች ነበሩ እየሄድኩኝ በመጫወት እግር ኳስን ወደ ራሴ ህይወቴ አስገባሁኝ። እና ደስ ይላል እግር ኳስን በዚህ ሁኔታ በመጀመሬ ደስተኛ ነኝ።

ሀትሪክ – በኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ የነበረሽ ቆይታ እና ከወጣሽ በኋላ ላለው የእግር ኳስ ሕይወትሽ ምን ያህል ጠቅሞሻል ?

ማህሌት – የአካዳሚ ቆይታዬ በጣም ደስ ይል ነበር። አራት አመታትን ነው የቆየሁት ስገባ በጣም በልጅ ዕድሜዬ ነበር። ምንም የማውቀው ነገር አልነበረም። ቢሆንም ግን ከሰው ጋር ስለምግባባ እና ስለምቀላለድ እዛ ደስ ይል ነበር በጣም። ያለው ሁሉ ነገር ደስ ይል ነበር።

በአካዳሚው የተማርኩት ትምህርት ደግሞ ሴት ልጅ ነኝ ብዙ ነገሮች ሊኖሩ ይችላሉ ፤ እነሱን ሁሉ ተጋፍጬ እንዴት ማለፍ እንዳለብኝ ፤ ሁለት ደግሞ አዕምሮዬ ላይ እንዴት ራሴን መገንባት እንዳለብኝ ብዙ አይነት ፈተናዎች ቢያጋጥሙኝ እንዴት ማለፍ እንዳለብኝ የተረዳሁበት ነው።

እንደውም የሆነ ጊዜ የገባን ሰዓት ላይ ከፍተኛ ሊግ ገብተን ነበር እና ሙሉ መሸነፍ ነበር። በመሸነፍ ውስጥ አዕምሮአችን ጠንካራ እንዲሆን እንደዚህ አይነት ፈተናዎች እንደሚያጋጥሙን እየተመከርን እና አዕምሮአችንን እያሳደግን ቀጣይ አመት በዛ ልክ አስተካክለን። እና በጣም ደስ የሚል የአካዳሚ ቆይታ ነበር።

ከአሰልጣኞቹ እስከ ተጫዋቾቹ ድረስ በምግብ ቤት ባለው ዙሪያ ድረስ በጣም ደስ የሚል ነው ማለት ትህትናቸው የተለየ ነበር። ስርዓት ላለው ልጅ በጣም ደስ የሚል እና ጥሩ ቦታ ነው ስርዓት ለሌለውም ልጅ የሚማርበት እና የሚስተካከልበት ነው። እና በጣም ደስ የሚል የአካዳሚ ቆይታ ነው የነበረኝ።

https://i0.wp.com/www.hatricksport.net/wp-content/uploads/2025/01/photo_2025-01-27_22-16-28.jpg?resize=1024%2C1280&ssl=1 ሀትሪክ – ከኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ በኋላ ሲዳማ ቡና የተቀላቀልሽበት አጋጣሚ ?

ማህሌት – ሲዳማ ቡና የገባሁበት አጋጣሚ ሀዋሳ ላይ ውድድር ሲደረግ በአሰልጣኜ በኩል ይጠይቁኝ ነበር። ክረምት ላይ አካዳሚ ከተመረቅኩ በኋላ ብዙ ክለቦች ጠይቀውኛል። ከብዙ ክለቦች መካከል ሲዳማ ቡናን ምርጫዬ አድርጌ ክለቡን ተቀላቀልኩ።

ሲዳማ ቡና በቆየሁበት ደግሞ አስተማሪ የሆኑ ነገሮችን ፣ ፈተናዎችን ፣ የመጀመሪያ ክለቤም ስለሆነ እንዴት ማለፍ እንዳለብኝ ብዙ ብዙ አይነት ትምህርቶችን ፣ ስነ ምግባር እና እንዴት ክለብ ላይ ደግሞ ራሴን እንዴት ማስተዳደር እንዳለብኝ እረፍት እንዴት መውሰድ እንዳለብኝ ጨምሮ ብዙ ብዙ ነገሮችን ተምሬ ወጥቻለሁ።

በአጠቃላይ ሲዳማ ቡና ቤት በጣም ደስ የሚል ቆይታ ነበረኝ ያው ከሁለተኛ ዙር በኋላ ውጤቱ አሪፍ ባይሆንም ማለት መሸነፍ እና የአቻ ውጤት ብናስከተልም በጣም ደስ የሚል ቆይታ ነበር ያሳለፍኩት በሲዳማ ቤት።

https://i0.wp.com/www.hatricksport.net/wp-content/uploads/2025/01/photo_2025-01-27_22-16-25.jpg?resize=1024%2C1280&ssl=1 ሀትሪክ – በሲዳማ ቡና የአንድ አመት ቆይታ ካደረገሽ በኋላ ወደ ኢትዮ ኤሌክትሪክ አመራሽ። ከሌሎች ክለቦች በተለየ ኤሌክትሪክን የመረጥሽበት ምክንያት ምን ነበር ?

ማህሌት – ወደ ኢትዮ ኤሌክትሪክ የገባሁት አካዳሚ እያለን ከኛ ባች ፊት ለፊት የነበሩት እዛ ይገቡ ነበር። በቢጫ ቴሴራ ምናምን ብቻ እዛ ቤት ያለው ነገር ሁሉ አሰልጣኟ ሴት በመሆኗ ብቻ ራሱ በጣም የመግባት ፍላጎቴ ራሱ እዛ ነበረ። ያለው ነገር በሚሰጡት ትኩረት በብዙ በብዙ ነገሮች የመግባት ፍላጎት ነበረኝ ወድያው ጥያቄ እንደቀረበልኝ(ከዛ በፊት መቻል አቅርቦልኝ ነበረ) እሱን ውድቅ አድርጌ ወደ ኢትዮ ኤሌክትሪክ አቀናሁኝ እና በጣም ደስ የሚል እና አሪፍ ቡድን ነው የገባሁት በጣም ደስ ብሎኛል።

ክለቡም እኔን የመረጠኝ ከአካዳሚ ጀምሮ በሲዳማ ቡና እንዲሁም በብሔራዊ ቡድን ባሳየሁት ብቃት እና ፀባይ ነው ብዬ ነው እኔ የማስበው።

ht[...]

kuasmeda / ኳስሜዳ

27 Jan, 15:19


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
ኤፍሬም ኃይለማርያም፣ ግሩም ሃጎስ፣ ብርሃኑ አዳሙ እና ብሩክ እንዳለ የጨዋታ እገዳ ተጣለባቸው

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

1. ኤፍሬም ኃይለማርያም (ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ)  እሁድ ጥር 18 2017 ዓ.ም. ክለቡ ከሀዲያ ሆሳዕና ጋር ባደረገው የ16ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ በ 90+1 ኛ ደቂቃ ላይ የተጋጣሚን ተጫዋች በመማታት በቀይ ካርድ ከጨዋታ ሜዳ የተወገደ ስለመሆኑ ሪፖርት ቀርቦበታል ። ስለሆነም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ እ‥ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 3 ምዕራፍ 3 አንቀፅ 63 በተቁ 1 (ሠ) እና በተቁ 2 መሰረት 4 ጨዋታ እንዲታገድ ና በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 4000 /አራት ሺ/ እንዲከፍል የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።

2. ግሩም ሃጎስ (መቻል) በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም ከታች በተጠቀሱት 4 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ ካርድ ተመልክቷል ።

1. ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ – መቻል
2. መቻል – አዳማ ከተማ
3. መቻል – ቅዱስ ጊዮርጊስ
4. መቻል -ባህርዳር ከተማ

በመሆኑም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 1500 እንዲከፍል የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል ።

https://i0.wp.com/www.hatricksport.net/wp-content/uploads/2023/05/OMEGA_ADS.jpg?resize=1170%2C214&ssl=1 3. ብርሃኑ አዳሙ(ስሁል ሽረ) የ ከታች በተጠቀሱት 5 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ ካርድ ተመልክቷል ።

1. ስሁል ሽረ – ድሬደዋ ከተማ
2. ኢትዮጵያ ቡና – ስሁል ሽረ
3. ቅዱስ ጊዮርጊስ – ስሁል ሽረ
4. ስሁል ሽረ – አርባምንጭ ከተማ
5. ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ – ስሁል ሽረ

በመሆኑም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ እ‥ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 2 አንቀፅ 35(መ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 1500 /አንድ ሺ አምስት መቶ/ እንዲከፍል የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል ።

4. ብሩክ እንዳለ (ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ) ከታች በተጠቀሱት 5 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ ካርድ ተመልክቷል ።

1. መቻል – ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
2. ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ – ኢትዮጵያ መድን
3. ሲዳማ ቡና – ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
4. ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ – ኢትዮ ኤሌትሪክ
5. ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ – ስሁል ሽረ

በመሆኑም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ እ‥ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 2 አንቀፅ 35(መ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 1500 /አንድ ሺ አምስት መቶ/ እንዲከፍል የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል ።

kuasmeda / ኳስሜዳ

27 Jan, 04:04


ሊቨርፑል ከ ኢፕስዊች ታውን ሃይላይት

kuasmeda / ኳስሜዳ

26 Jan, 19:18


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
ወልዋሎ አዲግራት ከድል ጋር ሲታረቅ ኤልፓ ከተከታታይ ሽንፈቶች በኋላ ወደ አሸናፊነት ተመልሷል

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 16ኛ ሳምንት የመጨረሻ ቀን ጨዋታዎች በዛሬው ዕለት ሲደረጉ ከድል የራቁ ቡድኖች ወደ ድል የተመለሱበትን ውጤት አስመዝግበዋል።

በቀዳሚው የዕለቱ ጨዋታ በሻምፒዮንነት ፉክክሩ ላይ ያለው ሀድያ ሆሳዕናን የገጠመው ወልዋሎ አዲግራት ድል ቀንቶታል።

የውድድር ዘመኑን ቀዳሚ ድል ከ14 ጨዋታዎች በኋላ ያገኘው ወልዋሎ አዲግራት የማሸነፊያ ግቡን በቡልቻ ሹራ አማካኝነት አግኝቷል።

ክለቡ ለመጨረሻ ጊዜ በሊጉ ያሸነፈው ከአምስት አመታት በፊት ታህሳስ 29 2012 ዓ.ም ድሬዳዋ ከተማን ነበር።

የሊጉን ግርጌ የያዘው ቡድኑ ነጥቡን ወደ አምስት ማሳደግም ችሏል።

ሀድያ ሆሳዕና በበኩሉ ድል አድርጎ ከመሪው ኢትዮጵያ መድኅን በነጥብ እኩል የሚሆንበትን ዕድል ሳይጠቀምበት ቀርቷል።

ቡድኑ ሽንፈት ያስተናገደውም ከስምንት(7 ድል እና 1 አቻ)ተከታታይ ጨዋታዎች በኋላ ነው።

በቀጣይ ሳምንት መርሐግብር ወልዋሎ አዲግራት ከኢትዮ ኤሌክትሪክ ሲጫወት ሀድያ ሆሳዕና በበኩሉ ከሊጉ መሪ ኢትዮጵያ መድኅን ጋር ይጫወታል።

በሳምንቱ የመጨረሻ መርሐግብር ደግሞ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ስታዲየም ላይ አሸንፎ የማያውቀው ኢትዮ ኤሌክትሪክ ድል ቀንቶታል።

ሲዳማ ቡናን የገጠመው ኢትዮ ኤሌክትሪክ 2 – 0 በሆነ ውጤት ሲያሸንፍ ሁለቱንም ግቦች ናትናኤል ገ/ጊዮርጊስ በ21ኛ እና 24ኛ ደቂቃዎች ላይ አስቆጥሯል።

የዘሪሁን ሸንገታው ቡድን ፋሲል ከነማን ከረታበት የሰባተኛ ሳምንት ጨዋታ በኋላ ያሳካው የመጀመሪያ ሶስት ነጥብ ነው። ውጤቱን ተከትሎ ነጥቡን 18 ማድረስም ችሏል።

ሲዳማ ቡና በበኩሉ ከሶስት ተከታታይ የአቻ ውጤቶች በኋላ ሽንፈትን ያስተናገደበት ጨዋታ ሆኗል። ቡድኑ በነበረው 19 ነጥብም ለመቆየት ተገዷል።

በቀጣይ ሳምንት ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከወልዋሎ አዲግራት ሲጫወት ሲዳማ ቡና በበኩሉ አራፊ ቡድን ነው።

kuasmeda / ኳስሜዳ

25 Jan, 19:18


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
መቻል እና ቅዱስ ጊዮርጊስ ወደ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጉበትን ዕድል ሳይጠቀሙበት ቀርተዋል

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 16ኛ ሳምንት የሶስተኛ ቀን ጨዋታዎች በዛሬው ዕለት ተደርገው ሁለቱም ጨዋታዎች በአቻ ውጤት ተጠናቀዋል።

በዕለቱ ቀዳሚ መርሐግብር ከቀን 9:00 ጀምሮ በተደረገው ጨዋታ በደረጃ ሰንጠረዡ 2ኛ እና 5ኛ ላይ የነበሩት መቻል እና ባህርዳር ከተማ ነጥብ ተጋርተዋል።

1 – 1 በተጠናቀቀው ጨዋታ አቤል ነጋሽ በ16ኛው ደቂቃ ላይ ከሳጥን ውጪ በግራ እግሩ አክሮ በመምታት ያስቆጠረው ድንቅ ግብ ጦሩን ለ23 ደቂቃዎች መሪ አድርጓል።

በ39ኛው ደቂቃ ላይ ግን ቸርነት ጉግሳ በግሩም ሁኔታ የመቻልን ተጫዋቾች ሸውዶ ከሳጥን ውጪ የመታው ኳስ ከመረቡ አርፎ የጣና ሞገዶቹን አቻ አድርጓል።

በቀሪ የመጀመሪያ አጋማሽም ሆነ በሁለተኛው አጋማሽ ተጨማሪ ግብ ያላስተናገደው ጨዋታ ለሁለቱም አንድ አንድ ነጥብ አጋርቶ ተጠናቋል።

መቻል ከሊጉ መሪ ኢትዮጵያ መድኅን ጋር በነጥብ መስተካከል የሚችልበትን ዕድል ሳይጠቀምበት ቀርቷል። በተመሳሳይ ባህርዳር ከተማም በጨዋታው ድል ማድረግ ቢችል ከሊጉ መሪ ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ አራት ማጥበብ ይችል ነበር።

በቀጣይ ሳምንት መርሐግብር መቻል ከሀዋሳ ከተማ ባህርዳር ከተማ ደግሞ ከኢትዮጵያ ቡና ይጫወታሉ።

በዕለቱ ሁለተኛ መርሐግብር የተገናኙት ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሀዋሳ ከተማም በተመሳሳይ 1 – 1 ተለያይተዋል።

በጨዋታው 41ኛ ደቂቃ ላይ ፍፁም ጥላሁን ከበረከት ወልዴ የደረሰውን ኳስ ለቢንያም ፍቅሩ አቀብሎት ቢንያም ፍቅሩ ኳስና መረብን በማዋሀድ ቡድኑን መሪ አድርጓል።

የመጀመሪያው አጋማሽ መጠናቀቂያ በተቃረበበት ወቅት ግን አቤኔዘር ዮሐንስ ከርቀት አክርሮ የመታውን ኳስ በአስደናቂ ሁኔታ አስቆጥሮ ሐይቆቹን አቻ አድርጓል።

ውጤቱን ተከትሎ ቅዱስ ጊዮርጊስ ነጥቡን 25 ሲያደርስ ሀዋሳ ከተማ በበኩሉ 12 ነጥብ ላይ መድረሽ ችሏል።

በ17ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ቅዱስ ጊዮርጊስ ከወላይታ ድቻ እንዲሁም ሀዋሳ ከተማ ከመቻል ይጫወታሉ።

kuasmeda / ኳስሜዳ

23 Jan, 23:18


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
አህመድ ሁሴን አዞዎቹን ባለ ድል ሲያደርግ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከስሁል ሽረ ነጥብ ተጋርቷል

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 16ኛ ሳምንት ጨዋታዎች በዛሬው ዕለት በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ስታድየም መደረግ ጀምረዋል።

በቀዳሚው ጨዋታ አርባምንጭ ከተማ ከመመራት ተነስቶ ወላይታ ድቻን አሸንፏል።

2 – 1 በተጠናቀቀው ጨዋታ አዞዎቹ በያሬድ ዳርዛ የ16ኛ ደቂቃ ግብ እስከ 60ኛው ደቂቃ ድረስ መሪ መሆን ችለዋል።

በረጅም ወደ አርባምንጭ ከተማ የሳጥን ክልል የተላከውን ኳስ የቡድኑ ተከላካዮች በተገቢው መልኩ ለማራቅ በተቸገሩበት አጋጣሚ ያገኘው ያሬድ ዳርዛ በግብ ጠባቂው ላይ ከፍ አድርጎ ከመረብ አሳርፎታል።

ጨዋታው 60ኛ ደቂቃ ላይ ሲደርስ አህመድ ሁሴን ከቡድን አጋሩ የተላከለትን ኳስ የግብ ክልሉን ለቆ በወጣው አብነት ሀብቴ አናት ላይ ከፍ በማድረግ ቡድኑን አቻ አድርጓል።

መደበኛው ዘጠና ደቂቃ ሊጠናቀቅ አንድ ደቂቃ ብቻ በቀረው ጊዜ አህመድ ሁሴን በድጋሚ ግብ አስቆጥሮ አዞዎቹን አሸናፊ አድርጓል።

አጥቂው ከመስመር የተሻገረለትን ኳስ በግሩም ሁኔታ በቀኝ እግሩ ተቆጣጥሮ በግራ እግሩ በመምታት ከመረቡ አዋህዶታል።

ውጤቱን ተከትሎ አርባምንጭ ከተማ ነጥቡን 21 በማድረስ ደረጃውን ወደ 6ኛ ከፍ ሲያደርግ ወላይታ ድቻ በበኩሉ ወደ 7ኛ ደረጃ ተንሸራቷል።

በ17ኛ ሳምንት ጨዋታዎች አርባምንጭ ከተማ መቀሌ 70 እንደርታ እንዲሁም ወላይታ ድቻ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ይጫወታሉ።

በዕለቱ ሁለተኛ መርሐግብር ደግሞ በወራጅ ቀጠና ውስጥ የሚገኙት የዓምናው ሻምፒዮን ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከስሁል ሽረ 1 – 1 ተለያይተዋል።

በጨዋታው 60ኛ ደቂቃ ላይ ኪቲካ ጀማ ከባሲሩ ዑመር የተሻገረለትን ኳስ በግንባር በመግጨት ቡድኑን መሪ ማድረግ ችሎ ነበር።

ነገር ግን የንግድ ባንክ መሪነት ከአምስት ደቂቃዎች መሻገር አልቻለም።

በ65ኛው ደቂቃ ላይ ከማዕዘን የተሻገረን ኳስ መሀመድ ሱሌማን በግንባሩ በመግጨት ስሁል ሽረን አቻ ያደረገ ሲሆን ጨዋታውም በ1 – 1 ውጤት ፍፃሜውን አግኝቷል።

ሁለቱም ቡድኖች ነጥባቸውን በአንድ ከፍ ቢያደርጉም በደረጃቸው ላይ ግን ለውጥ ማድረግ ሳይችሉ በነበሩበት ለመቆየት ተገደዋል።

በ17ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከአዳማ ከተማ ሲጫወት ስሁል ሽረ አራፊ ቡድን ነው።

kuasmeda / ኳስሜዳ

22 Jan, 11:16


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
በረከት ሳሙኤል፣አላዛር ማረነ፣ያሬድ ከበደ፣ ዋልታ አንደይ የጨዋታ እገዳ ሲጣለባቸው በክለብ ደግሞ ድሬደዋ ከተማ ቅጣት ተላልፎበታል

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

1. በረከት ሳሙኤል (ሃዋሳ ከተማ) ማከሰኞ ጥር 13 2017 ዓ.ም. ክለቡ ከወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ ጋር ባደረገው የ15ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ በ 45+2 ኛ ደቂቃ ላይ ሁለተኛ ቢጫ ካርድ የሚያስጥ ጥፋት በመፈፀሙ በቀይ ካርድ ከጨዋታ ሜዳ የተወገደ ስለመሆኑ ሪፖርት ቀርቦበታል ። ስለሆነም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 2 አንቀፅ 35(መ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።

2. አላዛር ማረነ (ድሬደዋ ከተማ) ቅዳሜ ጥር 10 2017 ዓ.ም. ክለቡ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር ባደረገው የ15ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ በ 53 ኛ ደቂቃ ላይ የተጋጣሚን ቡድን ግልፅ ግብ የማግባት ዕድል በማበላሸት በቀይ ካርድ ከጨዋታ ሜዳ የተወገደ ስለመሆኑ ሪፖርት ቀርቦበታል ። ስለሆነም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ እ‥ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 3 ምዕራፍ 3 አንቀፅ 63 በተቁ 1 (ሐ) እና በተቁ 2 መሰረት 3 ጨዋታ እንዲታገድ ና በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 3000 /ሶስት ሺ/ እንዲከፍል የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።

3. ያሬድ ከበደ(መቐለ 70 እንደርታ) ከታች በተጠቀሱት 5 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ ካርድ ተመልክቷል ።

ፋሲል ከነማ – መቀሌ 70 እንደርታ

መቐለ 70 እንደርታ – መቻል

ኢትዮጵያ ቡና – መቀሌ 70 እንደርታ

መቀሌ 70 እንደርታ – ባህርዳር ከተማ

ኢትዮ ኤሌክትሪክ – መቀሌ 70 እንደርታ

በመሆኑም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 2 አንቀፅ 35 (መ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 1500 /አንድ ሺ አምስት መቶ/ እንዲከፍል የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል ።

4. ድሬደዋ ከተማ ክለቡ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር ባደረገው የ15 ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ የድሬደዋ ከተማ ቡድን ተጫዋች የሆኑት

1 ኢስማኤል አብዱል ጋኒዩ

2 ሄኖክ ሀሰን

3 ዘርዓይ ገብረስላሴ

4 አላዛር ማረነ

በተለያዩ ጥፋቶች ካርድ የተሰጣቸው በመሆኑ በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ መሰረት የገንዘብ ቅጣት ብር 5000 /አምስት ሺ/ እንዲከፍል የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል፡፡

5. ዋልታ አንደይ /ስሁል ሽረ – ለዕለቱ ጨዋታ ያልተመዘገበ ተጫዋች ክለቡ ከአርባ ምንጭ ከተማ ጋር በነበረው የ15ኛ ሳምንት ግጥሚያ ከተቀያሪ ውጪ የሆኑ ተጫዋቾች በሚቀመጡበት ቦታ ላይ ሆኖ ዳኞችን በተደጋጋሚ አስፀያፊ ስድብ ስለመሳደቡ እና በዚህም ምክኒያት በፀጥታ ኃይሎች ስታድየሙን ለቆ እንዲወጣ ሲደረግ ያልተገባ ባህሪ ስለማሳየቱ ሪፖርት ቀርቦበታል ። ስለሆነም ተጫዋቹ ለፈጸመው ጥፋት በኢ እ‥ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 3 ምዕራፍ 3 አንቀፅ 66 በተቁ 1 መሠረት 3/ሶስት/ ጨዋታ እንዲታገድና ብር 3000 /ሶስት ሺህ / እንዲከፍል የውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።

kuasmeda / ኳስሜዳ

21 Jan, 23:16


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
አረጋሽ ካልሳ በመጀመሪያ ጨዋታዋ ግብ አስቆጠረች

የታንዛኒያው ያንጋ ፕሪንሰስ ክለብን በትናንትናው ዕለት በይፋ የተቀላቀለችው አረጋሽ ካልሳ ዛሬ ቡድኗ ቡንዳ ኩዊንስን 4 – 1 ባሸነፈበት ጨዋታ አንድ ግብ አስቆጥራለች።

አረጋሽ የቡድኑን ሁለተኛ ለራሷ ደግሞ የመጀመሪያውን ግብ በ24ኛው ደቂቃ ላይ እጅግ በአስደናቂ ሁኔታ ከመረብ አሳርፋለች።

ካስቆጠረችው ግብ በተጨማሪም የቡድኑ አንደኛ እና ሶስተኛ ግቦች ሲቆጠሩ አመቻችታ ማቀበል ችላለች።

kuasmeda / ኳስሜዳ

21 Jan, 19:16


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
መቻል የሊጉን መሪነት መረከብ የሚችልበትን ዕድል ሲያመክን የሊጉን ግርጌ የያዙት ክለቦች ነጥብ ተጋርተዋል

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ15ኛ ሳምንት መርሐግብር ዛሬ በተደረጉ ጨዋታዎች ፍፃሜውን አግኝቷል።

በዕለቱ በቀዳሚነት ከቀን 9:00 ጀምሮ በተደረገው ጨዋታ የተገናኘቱ በሊጉ የደረጃ ሰንጠረዥ ግርጌ የሚገኙት ሀዋሳ ከተማ እና ወልዋሎ አዲግራት ነጥብ ተጋርተዋል።

በጨዋታው ናትናኤል ዘለቀ በ25ኛው ደቂቃ ላይ ከቆመ ኳስ መነሻውን ባደረገ ኳስ ባስቆጠረው ግብ ወልዋሎ አዲግራትን መሪ ማድረግ ችሏል።

ወልዋሎ አዲግራት በመሪነት የመጀመሪያውን አጋማሽ ቢያጠናቅቅም የሁለተኛው አጋማሽ በተጀመረ 48ኛው ሰከንድ ላይ ግብ አስተናግዷል።

ግቡን ያስቆጠረው እስራኤል እሸቱ ሲሆን የውድድር ዓመቱ ቀዳሚ ግቡ ሆኖም ተመዝግቧል።

ውጤቱን ተከትሎ ሀዋሳ ከተማ አሸንፎ ደረጃውን ማሻሻል የሚችልበትን ዕድል ባለመጠቀሙ በ11 ነጥቦች በነበረት የ17ኛ ደረጃ ለመቆየት ሲገደድ ወልዋሎ አዲግራትም ነጥቡን 2 አድርሶ የ18ኛ ደረጃውን ይዞ ቀጥሏል።

በ16ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ሀዋሳ ከተማ ከቅዱስ ጊዮርጊስ እንዲሁም ወልዋሎ አዲግራት ከሀድያ ሆሳዕና ጋር ይጫወታሉ።

የሳምንቱ የመጨረሻ መርሐግብር ፋሲል ከነማን ከመቻል አገናኝቶ በተመሳሳይ 1 – 1 ተጠናቋል።

በረከት ደስታ በ38ኛው ደቂቃ ላይ ያስቆጠረው ግብ ጦሩን መሪ ሲያደርግ እስከ 70ኛው ደቂቃ ድረስም ጨዋታው በ1 – 0 ውጤት ቆይቷል።

በ70ኛው ደቂቃ ላይ የፋሲል ከነማው አንዋር ሙራድ ከግራ መስመር የተሻገረውን ኳስ አየር እንዳለ በመቀስ ምት በመምታት በድንቅ ሁኔታ ከመረብ አሳርፏል።

ውጤቱንም ተከትሎ መቻል ዳግም ወደ መሪነት የሚመለስበትን ዕድል ሳይጠቀምበት ቀርቷል።

መቻል በጨዋታው ባገኘው አንድ ነጥብ አማካይነት ነጥቡን 26 በማድረስ የሁለተኛ ደረጃን የያዘ ሲሆን ፋሲል ከነማ በበኩሉ ነጥቡን 17 በማድረስ ወደ 12ኛ ከፍ ብሏል።

በቀጣይ ሳምንት በሚደረጉ ጨዋታዎች መቻል ከባህርዳር ከተማ ሲገናኝ ፋሲል ከነማ አራፊ ቡድን ነው።

ሊጉን ኢትዮጵያ መድኅን ፣ መቻል እና ሀድያ ሆሳዕና ተመሳሳይ 26 ነጥቦችን ይዘው በግብ ክፍያ በመበላለጥ ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ያለውን ደረጃ ይዘዋል።

ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፣ ስሁል ሽረ ፣ ሀዋሳ ከተማ እና ወልዋሎ አዲግራት በወራጅ ቀጠና ውስጥ የሚገኙ ክለቦች ናቸው።

kuasmeda / ኳስሜዳ

21 Jan, 11:16


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
አቡበከር ናስር ለአሰልጣኙ ንግግር መልስ ሰጥቷል

ከቀናት በፊት የሱፐርሰፖርት ዩናይትዱ አሰልጣኝ ጋቪን ኸንተ ስለ አቡበከር ናስር የተናገሩት ንግግር አነጋጋሪ መሆኑ የሚታወቅ ነው።

አሰልጣኙ በንግግራቸው አበቡከር ናስር የት እንደሚገኝ እንደማያውቁ እና ለሁለት ሳምንታት ያህል ከቡድኑ ጋር አለመሆኑን ገልፀው ነበር።

ይህንንም በተመለከተ አቡበከር ናስር ከደቂቃዎች በፊት በይፋዊ የፌስቡክ ገፁ ምላሽ ሰጥቷል።

የአቡበከር ናስር ሙሉ ምላሽ “በሱፐርስፖርት ዩናይትድ እግር ኳስ ክለብ አሁን ያለሁበትን ሁኔታ በተመለከተ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ እየተሰራጩ ያሉ መረጃዎችን ተመልክቻለሁ፡፡ እውነት ለመናገር ከክለቡ ጋር የመረጃ ክፍተት ተፈጥሮ ነው እንጅ ጉዳዩ ይሄን ያክል የሚወራ አልነበረም፡፡”

“በቅርቡ ማለትም በታህሳስ 27/2017 ባደረግነው የወዳጅነት ጨዋታ ላይ ባጋጠመኝ መጠነኛ ጉዳት ምክንያት በክለቡ የህክምና ቡድን ረፍት እንዳደርግ ተነግሮኝ በዛው መሰረት ረፍት አድርጌያለሁ፡፡”

“በኋላም የመቅረቴን ጉዳይ በተመለከተ ከወኪሌ መልእክት ተላከልኝ፡፡ ከዛም ለክለቤ ሁኔታውን አስረድቼ ለተፈጠረው የመረጃ ክፍተትም ይቅርታ ጠይቄያለሁ፡፡”

kuasmeda / ኳስሜዳ

19 Jan, 15:15


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
የኢትዮጵያ ሴቶች ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን ቀጣይ ተጋጣሚውን አውቋል

በሞሮኮ አስተናጋጅነት ለሚደረገው የሴቶች ከ17 ዓመት በታች የዓለም ዋንጫ የማጣሪያ ጨዋታዎች መደረግ ጀምረዋል።

በመጀመሪያው ዙር ማጣሪያ ከዚምባቡዌ አቻው ተድልድሎ የነበረው የኢትዮጵያ ሴቶች ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን ተጋጣሚው ራሱን ከማጣሪያው በማግለሉ ወደ 2ኛው ዙር ማለፉም የሚታወስ ነው።

በአሰልጣኝ ራውዳ ዓሊ የሚመራው ቡድኑ በ2ኛው ዙር የማጣሪያ የደርሶ መልስ ጨዋታ ከካሜሩን አቻው እንደሚጫወትም ተረጋግጧል።

የካሜሩን የሴቶች ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን የግብፅ አቻውን ትናንት ምሽት አስተናግዶ 1 ለ 0 ያሸነፈ ሲሆን በድምር የ6 ለ 0 ውጤት ወደ ቀጣዩ ዙር ማለፉን አረጋግጧል።

የኢትዮጵያ እና የካሜሩን የሴቶች ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድኖች የመጀመሪያ ጨዋታቸውን ካሜሩን ላይ ከየካቲት 28 – 30 የመልሱን ደግሞ ከመጋቢት 5 – 7 ባሉት ቀናት መካከል በኢትዮጵያ ያደርጋሉ።

የዚህ ጨዋታ አሸናፊ በመጨረሻው ዙር የማጣሪያ ጨዋታ የናሚቢያ እና የዩጋንዳ አሸናፊን ይገጥማል።

kuasmeda / ኳስሜዳ

19 Jan, 03:15


አርሰናል ከ አስቶንቪላ ሃይላይት

kuasmeda / ኳስሜዳ

18 Jan, 19:15


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
ቅዱስ ጊዮርጊስ ድሉን ሲያስቀጥል አርባምንጭ ከተማም አሸንፏል

በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ15ኛ ሳምንት ጨዋታዎች በጥምቀት ዋዜማ በዕለተ ከተራ መደረግ ጀምረዋል።

በሳምንቱ ቀዳሚ ጨዋታ የፋሲል ተካልኙ ቅዱስ ጊዮርጊስ በአ.ሳ.ቴ.ዩ ስታድየም ያለውን የማሸነፍ ግስጋሴ ያስቀጠለበትን ድል በድሬዳዋ ከተማ ላይ ተቀዳጅቷል።

2 – 0 በሆነ ውጤት በተጠናቀቀው ጨዋታ የድሬዳዋ ከተማው አብዱል ጋንዩ በራሱ መረብ ላይ እንዲሁም ፍፁም ጥላሁን ከዕረፍት መልስ የፈረሰኞቹን ግብ ከመረብ አሳርፈዋል።

የቅዱስ ጊዮርጊስ ድል በሁለቱ ክለቦች የእርስ በርስ ግንኙነት ከሶስት ጨዋታዎች በኋላ የተመዘገበ ነው።

ፍፁም ጥላሁን የውድድር ዓመቱን 6ኛ የሊግ ግብ በማስቆጠር የከፍተኛ ግብ አስቀጣሪነቱን በጥምር የሚመሩትን ተጫዋቾች መቀላቀል ችሏል።

ባለፉት ሁለት አመታት በባህርዳር ከተማ ቆይታ የነበረው ፍፁም በሁለቱ የውድድር ዘመናት በድምር ያስቆጠራቸውን የግብ ብዛቶች ለመስተካከል ሁለት ግብ ብቻ ቀርቶታል።

ተከታታይ አራተኛ ጨዋታውን በአ.ሳ.ቴ.ዩ ስታድየም ያሸነፈው ቅዱስ ጊዮርጊስ ከመሪው መቻል ጋር በአንድ ነጥብ ርቀት ብቻ ተቀምጧል።

በዚህ ስታድየም ምንም ሽንፈት ያላስተናገደው የሊጉ የ16 ጊዜ ሻምፒዮን በ33ኛ ጨዋታው ያስተናገደው 24ኛ ድሉ ሆኗል።

የይታገሱ እንዳለው ድሬዳዋ ከተማ በበኩሉ ተከታታይ አምስተኛ ድል አልባ ጉዞው የቀጠለበትን ሽንፈት አስተናግዷል።

ቡድኑ ባለፉት አራት ተከታታይ የሊጉ ጨዋታዎች ላይ የአቻ ውጤት ያስመዘገበ ሲሆን ሽንፈቱም ከ73 ቀናት በኋላ የተመዘገበ ነው።

በተለይም መሐመድኑር ናስርን ካጣ በኋላ በፊት መስመር እየተቸገረ ያለው ድሬዳዋ ከተማ አጥቂውን በጉዳት ካጣ በኋላ ባደረጋቸው አምስት ጨዋታዎች አንድ ግብ ብቻ አስቆጥሯል።

በ16ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ቅዱስ ጊዮርጊስ ሀዋሳ ከተማን ሲገጥም ድሬዳዋ ከተማ አራፊ ቡድን ነው።

በዕለቱ ሁለተኛ መርሐግብር ስሁል ሽረ ከአርባምንጭ ከተማ ተገናኝተው አዞዎቹ 1 – 0 ረተዋል።

ለበረከት ደሙው ቡድን ቡታቃ ሸመና በ73ኛ ደቂቃ ላይ ብቸኛውን ግብ ከመረብ አሳርፏል። ቡድኑ ባሳለፍነው ሳምንትም አዳማ ከተማን 2 – 0 አሸንፎ እንደነበር አይዘነጋም።

ስሁል ሽረ በበኩሉ ድሬዳዋ ላይ መቀሌ 70 እንደርታን ከረታበት ጨዋታ በኋላ በአ.ሳ.ቴ.ዩ ስታድየም ተከታታይ አራተኛ ሽንፈቱን አስተናግዷል።

በቀጣይ ሳምንት መርሐግብር አርባምንጭ ከተማ ከወላይታ ድቻ እንዲሁም ስሁል ሽረ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ይጫወታሉ።

kuasmeda / ኳስሜዳ

17 Jan, 19:14


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
የሉሲዎቹ አዲሱ ዋና አሰልጣኝ ታውቋል

አሰልጣኝ ዮሴፍ ገብረወልድ አዲሱ የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ በመሆን መሾሙን የእግር ኳስ ፌዴሬሽኑ ይፋ አድርጓል።

አሰልጣኙ በውድድር ዘመኑ የአርባምንጭ ከተማ የሴቶች ቡድንን በዋና አሰልጣኝነት በመምራት ላይ የነበሩ ናቸው።

ሉሲዎቹንም ለቀጣይ ሁለት ዓመታት በዋና አሰልጣኝነት ለመምራት ፊርማቸውን አኑረዋል።

አሰልጣኝ ዮሴፍ ቀዳሚ ጨዋታቸውን በ2026 የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ከዩጋንዳ ብሔራዊ ቡድን ጋር ያደርጋሉ።

kuasmeda / ኳስሜዳ

17 Jan, 11:14


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
አሰልጣኝ ፀጋዬ ኪዳነ ማሪያም ፣ ዮናስ ለገስ ፣ አማኑኤል ኤርቦ ፣ ሄኖክ ተወልደ እና አሮን አንተር የጨዋታ እገዳ ተጣለባቸው

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

1. ፀጋዬ ኪዳነ ማሪያም(ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ) ረቡዕ ጥር 7 2017 ዓ.ም. ክለባቸው ከወላይታ ድቻ ጋር ባደረገው የ14ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ በ 90+2 ኛ ደቂቃ ላይ ዳኛን አፀያፊ ስድብ በመሳድብ በቀይ ካርድ ከጨዋታ ሜዳ የተወገዱ ስለመሆኑ ሪፖርት ቀርቦባቸዋል ። ስለሆነም የቡድን አመራሩ ለፈፀሙት ጥፋት በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የውድድር ደንብ ክፍል 1 አንቀፅ 13 ንዑስ አንቀፅ 13.3 ተ.ቁ 18 መሰረት 3 ጨዋታ እንዲታገዱ ና በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 10000 /አስር ሺ/ እንዲከፍሉ የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።

2. ዮናስ ለገስ(ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ)  ማከሰኞ ጥር 6 2017 ዓ.ም. ክለቡ ከኢትዮ ኤሌትሪክ ጋር ባደረገው የ14ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ በ 89 ኛ ደቂቃ ላይ ከስፖርታዊ አድራጎት ውጭ በመሆን/በመጫወት በቀይ ካርድ ከጨዋታ ሜዳ የተወገደ ስለመሆኑ ሪፖርት ቀርቦበታል ።

ስለሆነም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ እ‥ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 2 አንቀፅ 35(መ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።

3. አማኑኤል ኤርቦ (ቅዱስ ጊዮርጊስ) ከታች በተጠቀሱት 5 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ ካርድ ተመልክቷል ።

ቅዱስ ጊዮርጊስ-ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ

ቅዱስ ጊዮርጊስ – አርባምንጭ ከተማ

መቻል – ቅዱስ ጊዮርጊስ

ቅዱስ ጊዮርጊስ – ኢትዮ ኤሌትሪክ

ቅዱስ ጊዮርጊስ – ስሁል ሽረ

በመሆኑም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 2 አንቀፅ 35(መ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 1500 /አንድ ሺ አምስት መቶ/ እንዲከፍል የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል ።

4. ሄኖክ ተወልደ (ስሁል ሽረ)  ክለቡ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር በነበረው የ14ኛ ሳምንት ግጥሚያ ጨዋታው ተጠናቆ ወደመልበሻ ክፍል በመሄድ ላይ እያለ የተጋጣሚ ቡድንደጋፊዎችንና ከተጠባባቂ ውጪ (over bench)ተጨዋቾችን በምልክትና በድምፅ አፀያፊ ስድብ ስለመሳደቡ ሪፖርት ቀርቦበታል ። ስለሆነም ተጫዋቹ በፈጸመው ጥፋት በኢ እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 3 ምዕራፍ 3 አንቀፅ 66 በተቁ 1 መሠረት 3/ሶስት ጨዋታ እንዲታገድና ብር 3 000 / ሶስት ሺህ / እንዲከፍል የውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።

5. አሮን አንተር (ቅዱስ ጊዮርጊስ) (ለ2017 የውድድር ዘመን ያልተመዘገበ)/ ክለቡ ከስሁል ሽረ ጋር በነበረው የ14ኛ ሳምንት ግጥሚያ ጨዋታው ተጠናቆ ክለቦቹ ወደመልበሻ ክፍል በመሄድ ላይ እያሉ ከተጠባባቂ ውጪ (over bench)ተጨዋቾች ከሚቀመጡበት ቦታ ላይ ሆኖ የተጋጣሚ ቡድንን ተጫዋች ለመደባደብ እንደተጋበዘና በፀጥታ ኃይሎች ተይዞ የተገላገለ ስለመሆኑን ሪፖርት ቀርቦበታል ። ስለሆነም ተጫዋቹ በፈጸመው ጥፋት በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የውድድር ደንብ ክፍል 10 አንቀፅ 35 በተቁ 2 መሠረት ከ15ኛ ሳምንት ጀምሮ ቅዱስ ጊዮርጊስ የሚያደርጋቸውን 5/አምስት/ ተከታታይ ጨዋታዎች ስታድየም ገብቶ እንዳይመለከት የውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ወስኗል

kuasmeda / ኳስሜዳ

16 Jan, 19:14


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
ቡናማዎቹ አፄዎቹን ሲረቱ ሐይቆቹ በመጥፎ ጉዟቸው ቀጥለዋል

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 14ኛ ሳምንት የመጨረሻ ቀን ጨዋታዎች በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ስታድየም በዛሬው ዕለት ተደርገዋል።

በዕለቱ ቀዳሚ ጨዋታ ኢትዮጵያ ቡናን ከፋሲል ከነማ አገንኛቶ በቡናማዎቹ የ1 – 0 አሸናፊነት ተጠናቋል።

ለአሰልጣኝ ነፃነት ክብሬው ቡድን የማሸነፊያውን ግብ ዲቫይን ዋችኩዋ በ66ኛው ደቂቃ ላይ አስቆጥሯል።

አንተነህ ተፈራ ከበፍቃዱ አለማየሁ የተቀበለውን ኳስ በሳጥኑ የግራ አቅጣጫ ይዞ ገብቶ ወደ ግብ ሞክሮት በግብ ጠባቂው ዮሐንስ ደርሶ ቢመለስም በቅርብ የነበረው ዲቫይን ዋቹኩዋ ከመረብ አሳርፎታል።

ግቡም ለናይጄሪያዊው ተጫዋች በቡናማዎቹ ማልያ ያስቆጠረው ሁለተኛ ግቡ ሆኖ ተመዝግቧል።

ውጤቱንም ተከትሎ ኢትዮጵያ ቡና ነጥቡን 17 በማድረስ ወደ 7ኛ ከፍ ማለት ችሏል።

ጨዋታውን ግብ ሳይቆጠርባቸው ያጠናቀቁት ቡናማዎቹ ባለፉት አምስት ተከታታይ ጨዋታዎች ምንም ግብ ሳያስተናግዱ መቀጠል ችለዋል። ይህም በውድድር ዘመኑ በአምስት ተከታታይ ጨዋታዎች ግብ ባለማስናገድ ብቸኛ ቡድን አድርጓቸዋል።

በተጨማሪም በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ስታድየም ተከታታይ ያለመሸነፍ ጉዟቸውን 10ኛ ጨዋታ ላይ አድርሰዋል።

በአሰልጣኝ ውበቱ አባተ የሚመራው ፋሲል ከነማ በበኩሉ ሌላ መጥፎ ሽንፈትን ያስተናገደበት ዕለት ሆኖ አልፏል።

ኢትዮጵያ ቡናን በ2003 ዓ.ም የሊግ ዋንጫ አሸናፊ ማድረግ የቻሉት ውበቱ አባተ ፋሲልን እየመሩም ለመጀመሪያ ጊዜ በቀድሞ ክለባቸው ተረተዋል።

በውድድር ዘመኑ በሶስት ጨዋታዎች ብቻ ድል የቀናው የጎንደር ከተማው ተወካይ ከአምስት ሽንፈት አልባ ጨዋታዎች በኋላ ሽንፈትን ቀምሷል።

ቡድኑ በቀጣይ ከሚያደርጋቸው ተከታታይ አራት ጨዋታዎች መካከል በሶስቱ በደረጃ ሰንጠረዡ እስከ አራተኛ(መቻል ፣ ኢትዮጵያ መድኅን እና ባህር ዳር ከተማ) ከሚገኙ ክለቦች ጋር ማድረጉ ደግሞ ሁኔታዎችን ሊያከብድበት እንደሚችል እንዲገመት አድርጓል።

አፄዎቹ አሁን ላይ ከወራጅ ቀጠናው በሁለት ነጥቦች ብቻ ርቀት ላይም ይገኛሉ።

በ15ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ፋሲል ከነማ የሊጉን መሪ መቻልን ሲገጥም ኢትዮጵያ ቡና በበኩሉ በሳምንቱ አራፊ ቡድን ነው።

በዕለቱ ሁለተኛ እና በሳምንቱ የመጨረሻ መርሐግብር ኢትዮጵያ መድኅን ሀዋሳ ከተማን 2 – 0 ረቷል።

በጨዋታው መሐመድ አበራ እና ዳዊት ተፈራ የኢትዮጵያ መድኅንን ግቦች ያስቆጠሩ ተጫዋቾች ናቸው።

በአሰልጣኝ ገብረመድህን ኃይሌ የሚመራው መድኅን በተከታታይ እያስመዘገባቸው ባለው ውጤቶች ከመሪው መቻል በሁለት ነጥቦች ርቀት ብቻ ለመቀመጥ ችሏል።

ቡድኑ የውድድር ዓመቱ ብቸኛውን ሽንፈት በሶስተኛው ሳምንት በሲዳማ ቡና ካስተናገደ በኋላ ባለፉት ተከታታይ ዘጠኝ ጨዋታዎች አልያም 88 ቀናት ያለ ሽንፈት መጓዝ ችሏል። ቡድኑ በዚህ ጉዞው በስድስቱ ጨዋታዎች ሶስት ነጥቦችን ይዞ ወጥቷል።

በተጨማሪም በመከላከል ረገድ ጠንካራ ሆኖ የቀጠለው ቡድኑ ከ12 ጨዋታዎች ለሰባተኛ ጊዜ ግብ ሳያስተናግድ ያጠናቀቀበት ጨዋታ ሆኗል።

እጅግ መጥፎ የውድድር ዘመን እያሳለፈ ያለው ሀዋሳ ከተማ በበኩሉ በሊጉ ከድል ከተራራቀ ሶስተኛ ወሩን ደፍኗል።

ክለቡ አሰልጣኝ ዘርዓይ ሙሉን አሰናብቶ በጊዜያዊ አሰልጣኞች ቢመራም በኢትዮጵያ ዋንጫ ቅዱስ ጊዮርጊስን ከረታበት ጨዋታ ውጪ በሊጉ ደጋፊዎቹን ማስደሰት አልቻለም።

ባሳለፍነው የውድድር ዘመን በተለይም በኤርትራዊው አሊ ሱሌይማን የሚመራው የፊት መስመሩ በርካታ ግቦችን ማስቆጠር ቢችልም ዘንድሮ እስካሁን ባለው ቁጥር የሊጉ ሁለተኛ ዝቅተኛ ግብ አስቆጣሪ ቡድን ሆኗል።

ባለፉት አምስት ተከታታይ ጨዋታዎችም ሐይቆቹ ኳስና መረብን አንድም ጊዜ ማገናኘት አልቻሉም።

ቡድኑ አሁንም ከ13 ጨዋታዎች 10 ነጥቦችን ብቻ በመያዝ ወልዋሎ አዲግራትን ብቻ በልጦ 17ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።

በቀጣይ ሳምንት ጨዋታዎች ሀዋሳ ከተማ ከተከታዩ ወልዋሎ አዲግራት ሲገናኝ ኢትዮጵያ መድኅንም ተከታዩን ባህርዳር ከተማ ይገጥማል።

kuasmeda / ኳስሜዳ

14 Jan, 19:12


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
የሊጉ መሪ ነጥብ ሲጥል የዓምናው ሻምፒዮን ወደ ድል ተመልሷል

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ14ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬም ቀጥለው ሲደረጉ የዓምናው ሻምፒዮን ከሳምንታት በኋላ ወደ ድል ሲመለስ የሊጉ መሪ መቻል ከድሬዳዋ ከተማ ነጥብ ተጋርቷል።

በቀዳሚው መርሐግብር ኢትዮ ኤሌክትሪክን የገጠመው ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በአዲስ ግደይ ድንቅ የቅጣት ምት ግብ 1 – 0 አሸንፏል።

ባለፉት ስድስት ተከታታይ ጨዋታዎችን ሳያሸንፍ ለተጓዘው ቡድኑ ድሉ እፎይታን እንደሚሰጥ ይጠበቃል። በተጨማሪም ውጤቱ በጊዜያዊነት ከወራጅ ቀጠናው ለመላቀቅ አሰችሎታል።

በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዓምናው የሻምፒዮንነት ጉዞ ትልቅ ሚናን ከተወጡ ተጫዋቾች አንዱ የሆነው አዲስ ግደይም በውድድር ዓመቱ ያስቆጠራቸውን የግብ ብዛቶች 5 ማድረስ ችሏል።

ኢትዮ ኤሌክትሪክ በበኩሉ ሊጉ በዚህ ፎርማት መደረግ ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ በአዳማ ሳይንሰና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ስታዲየም አሁንም ድል ማድረግ አልቻለም።

በቅዱስ ጊዮርጊስ እስከተረታበት ጨዋታ ድረስ በዘጠኝ ተከታታይ ጨዋታዎች ያልተሸነፈው ቡድኑ በውድድር ዘመኑ ለመጀመሪያ ጊዜ ተከታታይ ሽንፈትን አስተናግዷል።

ሁለቱ ቡድኖች ከቀናት በፊት በኢትዮጵያ ዋንጫ ተገናኝተው የአሰልጣኝ በፀሎት ልዑልሰገዱ ቡድን አሸናፊ እንደነበረም ይታወሳል።

በቀጣይ ሳምንት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከሀድያ ሆሳዕና እንዲሁም ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከመቀሌ 70 እንደርታ ይጫወታሉ።

በዕለቱ ሁለተኛ መርሐግብር ደግሞ መሪው መቻል ከተከታዮቹ ያለውን የነጥብ ልዩነት ማጥበብ የሚችልበትን ዕድል ሳይጠቀም ቀርቷል።

ድሬዳዋ ከተማን የገጠመው ቡድኑ ግብ ሳያስቆጥርም ሳያስተናግድም በአቻ ውጤት ተለያይቷል።

ጦሩ ባለፉት አራት ተከታታይ የሊግ ጨዋታችም በአንዱ ብቻ ሙሉ ሶስት ነጥቦችን አሳክቷል።

የመቻል ነጥብ መጣል ለተከታዮቹ መልካም ዜና ይመስላል።

በተለይም ሀድያ ሆሳዕና በ15ኛው ሳምንት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክን ማሸነፍ ከቻለ የሊጉን መሪነት ዳግም መልሶ ያገኛል።

የአሰልጣኝ ይታገሱ እንዳለው ድሬዳዋ ከተማ በበኩሉ በሊጉ አራተኛ ተከታታይ የአቻ ውጤትን ያስመዘገበበት ጨዋታ ሆኗል።

ቡድኑ ከዚህ ጨዋታ ቀደም ብሎ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፣ ባህርዳር ከተማ እና ኢትዮጵያ ቡና ነጥብ ተጋርቷል።

በመከላከሉ ረገድ ባለፉት ሰባት ጨዋታዎች ሁለት ግብ ብቻ ያስተናገደው ቡድኑ በአራቱ ጨዋታዎች ግን በተጋጣሚዎቹ ላይ ግብ ማስቆጠር አልቻለም።

ቡድኑ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪውን መሐመድኑር ናስርን በጉዳት ካጣ በኋላ ባደረጋቸው አራት ጨዋታዎች አንድ ግብ ብቻ አስቆጥሯል።

በቀጣይ ሳምንት መቻል ከፋሲል ከነማ ድሬዳዋ ከተማ ደግሞ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ይጫወታሉ።

kuasmeda / ኳስሜዳ

13 Jan, 19:12


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
ፈረሰኞቹ ተከታታይ ድላቸውን ሲያስቀጥሉ አዞዎቹ ወደ ድል ተመልሰዋል

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ14ኛ ሳምንት መርሐግብር በዛሬው ዕለት በተደረጉ ሁለት ጨዋታዎች ጅማሮውን አድርጓል።

9:00 ላይ በጀመረው ቀዳሚው ጨዋታ ቅዱስ ጊዮርጊስ ስሁል ሽረን ገጥሞ በፍፁም ጥላሁን ብቸኛ ግብ 1 – 0 አሸንፏል።

ያለፉትን ሁለት ዓመታት በባህርዳር ከተማ ያሳለፈው ፍፁም ጥላሁን በቡድኑ ቆይታው 50 የሊግ ጨዋታዎች አድርጎ 8 ግቦችን አስቆጥሯል።

በዚህ የውድድር ዘመን ግን በቅዱስ ጊዮርጊስ ማልያ ገና በ12ኛ ጨዋታው 5ኛ ግቡ ላይ ደርሷል።

በተጨማሪም የውድድር ዘመን የቡድኑን ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነትን ከአማኑኤል ኤርቦ ጋር መጋራት ችሏል።

ቅዱስ ጊዮርጊስ በውድድር ዘመኑ ካስቆጠራቸው 15 ግቦች 10 ወይም 66.7% በሁለቱ ተጫዋቾች የተገኙ ናቸው።

የዓመቱን ስድስተኛ ድል ያስመዘገበው ቅዱስ ጊዮርጊስ ነጥቡን 21 በማድረስ ከመሪው መቻል ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሶስት አጥብቧል።

ተሸናፊው ስሁል ሽረ ለአራተኛ ጊዜ ቅዱስ ጊዮርጊስን በገጠመበት ጨዋታ አሁንም ግብ የሚያስቆጥርለት ተጫዋች ማግኘት አልቻለም።

ከተከታታይ 12 ጨዋታዎች በአንዱ ብቻ ድል የቀናው ቡድኑ በ11 ነጥብ የ16ኛ ደረጃን ይዟል።

በቀጣይ ሳምንት በሚደረጉ ጨዋታዎች ቅዱስ ጊዮርጊስ ከድሬዳዋ ከተማ እንዲሁም ስሁል ሽረ ደግሞ ከአርባምንጭ ከተማ ይገናኛሉ።

በዕለቱ ሁለተኛ መርሐግብር አርባምንጭ ከተማ አዳማ ከተማን 2 – 0 ረቷል።

አህመድ ሁሴን በ13ኛው እንዲሁም በፍቅር ግዛው በ40ኛው ደቂቃ ላይ አዞዎቹን ባለ ድል ያደረጉ ግቦችን አስቆጥረዋል።

አርባምንጭ ከተማ በውድድር ዓመቱ አምስተኛ ድሉን ያስመዘገበም ሲሆን በአምስቱም ድል ባደረገባቸው ጨዋታዎች ላይ ግብ አላስተናገደም።

የአሸናፊነት ግቦቹ ለአህመድ ሁሴን የውድድር ዘመኑ ሶስተኛ ለበፍቅር ግዛው ደግሞ ሁለተኛ ግባቸው ነው።

በቀጣይ ሳምንት ጨዋታዎች አርባምንጭ ከተማ ከስሁል ሽረ ሲጫወት አዳማ ከተማ አራፊ ቡድን ነው።

kuasmeda / ኳስሜዳ

13 Jan, 04:08


አርሰናል ከ ማን ዩናይትድ ሃይላይት

kuasmeda / ኳስሜዳ

12 Jan, 11:11


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
ስሁል ሽረ፣ ሲዳማ ቡና፣ ሀዲያ ሆሳዕና እና ፋሲል ከነማ ቅጣት ተላለፈባቸው

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

በረከት ወልዴ (ቅዱስ ጊዮርጊስ) በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም ከታች በተጠቀሱት 4 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ ካርድ ተመልክቷል ።

ቅዱስ ጊዮርጊስ – ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ

ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ – ቅዱስ ጊዮርጊስ

ቅዱስ ጊዮርጊስ – ኢትዮ ኤሌትሪክ

https://i0.wp.com/www.hatricksport.net/wp-content/uploads/2023/05/OMEGA_ADS.jpg?resize=1170%2C214&ssl=1

አዳማ ከተማ – ቅዱስ ጊዮርጊስ

በመሆኑም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 1500 እንዲከፍል የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል ።

ስሁል ሽረ ክለቡ ከመቻል ጋር ባደረገው የ13 ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ የስሁል ሽረ ቡድን ተጫዋች የሆኑት

* ነፃነት ገብረመድህን
* ጎይቶም ነጋ
* ዊሊያም ሰለሞን
* አሰጋኸኝ ጴጥሮስ
* ክፍሎም ገ/ሂወት

በተለያዩ ጥፋቶች ካርድ የተሰጣቸው በመሆኑ በኢ እፌ ዲሲፕሊን መመሪያ መሰረት የገንዘብ ቅጣት ብር 5000 /አምስት ሺ/ እንዲከፍል የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል፡፡

ሲዳማ ቡና ክለቡ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር ባደረገው የ13 ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ የሲዳማ ቡና ቡድን ተጫዋች የሆኑት

* ፍራወል መንግስቱ
* ያሬድ ባየህ
* ሐብታሙ ታደሰ
* ደስታ ደሙ
* ኢማኑኤል ሳባን ላሪዬ

በተለያዩ ጥፋቶች ካርድ የተሰጣቸው በመሆኑ በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ መሰረት የገንዘብ ቅጣት ብር 5000 /አምስት ሺ/ እንዲከፍል የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል፡፡

ሀዲያ ሆሳዕና ክለቡ ከፋሲል ከነማ ጋር ባደረገው የ13 ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ የሀዲያ ሆሳዕና ቡድን ተጫዋች የሆኑት

* ሰመረ ሀፍተይ
* ደስታ ዋሚሾ
* በረከት ወልደዮሐንስ
* ብሩክ ማርቆስ
* ሄኖክ አርፊጮ

በተለያዩ ጥፋቶች ካርድ የተሰጣቸው በመሆኑ በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ መሰረት የገንዘብ ቅጣት ብር 5000 /አምስት ሺ/ እንዲከፍል የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል፡፡

ፋሲል ከነማ ክለቡ ከሀዲያ ሆሳዕና ጋር ባደረገው የ13 ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ የፋሲል ከነማ ቡድን ተጫዋች የሆኑት

* ተመስገን ካስትሮ
* ሐብታሙ ተከስተ
* ማርቲን ኪዛ
* ብሩክ አማኑአል
* መንገሻ አየሩ

በተለያዩ ጥፋቶች ካርድ የተሰጣቸው በመሆኑ በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ መሰረት የገንዘብ ቅጣት ብር 5000 /አምስት ሺ/ እንዲከፍል የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል፡፡

አቶ መንግስቱ ታደሰ /ኢትዮጵያ ቡና የክለብ-አመራር/ ኢትዮጵያ ቡና ከድሬዳዋ ከተማ ጋር በነበረው የ12ኛ ሳምንት ግጥሚያ ጨዋታው ከተጠናቀቀ በኋላ

የእለቱ ዳኞችን አጸያፊ ስድብ ስለመሳደባቸው ሪፖርት ቀርቦባቸዋል ። ስለሆነም አመራሩ ለፈጸሙት ጥፋት በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 3 ምዕራፍ 3 አንቀፅ 66 በተቁ 1 መሠረት ከ14ኛ ሳምንት ጀምሮ ኢትዮጵያ ቡና የሚያደርጋቸውን 6/ስድስት/ ተከታታይ የፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎችን ወደ ስታድየም ገብተው እንዳይመለከቱ እንዲታገዱ/ በተጨማሪም ብር 5 000 /አምስት ሺህ / እንዲከፍሉ የውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ወስኗል

kuasmeda / ኳስሜዳ

11 Jan, 23:11


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
ሱራፌል ዳኛቸው በክለቡ የሚለበሰው የማልያ ቁጥር ታውቋል

ባለ ድንቅ ብቃቱ ተጫዋች ሱራፌል ዳኛቸው ወደ ሎደን ዩናይትድ ካመራ በኋላ ከልምምድ ውጪ በጨዋታ ላይ ሲሰለፍ አልታየም።

ሎደን ዩናይትድ ሳምንታት በኋላ በሚጀምረው የ”USL CHAMPIONSHIP” የሚጫዋቱ የክለቡን ተጫዋቾች የማልያ ቁጥር ይፋ ሲያደርግ ሱራፌል ዳኛቸውም ተካቷል።

ክለቡ ይፋ እንዳደረገው ከሆነም ሱራፌል ዳኛቸው በቡድኑ 19 ቁጥር ማልያን የሚለብስ ይሆናል።

ይህም ከ11 ሳምንታት በኋላ በሚጀምረው የ”USL CHAMPIONSHIP” ላይ ተጫዋቹ ወደ ጨዋታ እንደሚመለስ ፍንጭ የሰጠ ሆኗል።

እስከ 2026 ድረስ ከክለቡ ጋር ውል ያሰረው ሱራፌል በወረቀት ጉዳዮች አለመጠናቀቅ ምክንያት እ.አ.አ በ2024 የውድድር ዘመን ለክለቡ ጨዋታ አለማድረጉ ይታወቃል።

kuasmeda / ኳስሜዳ

11 Jan, 07:11


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
ጋቶች ፓኖም የኢራቁን ክለብ በአንድ ዓመት ውል ተቀላቀለ

የውድድር ዓመቱን በኢትዮጵያ መድኅን በማሳለፍ ላይ የነበረው ጋቶች ፓኖም ወደ ኢራቅ ማምራቱ እርግጥ ሆኗል።

ግዙፉ ተጫዋች ኒውሮዝ ስፖርት ክለብን የተቀላቀለ ሲሆን በክለቡም የአንድ አመት ውል ተፈራርሟል።

1.90 ሜ የሚረዝመው ጋቶች ከዚህ ቀደም ከሀገር ውጪ በሩስያ ፣ በግብፅ እና በሳዑዲ አረቢያ ክለቦች ማሳለፉ ይታወቃል።

ከተመሰረተ የ31 ዓመት ዕድሜ ያለው ኒውሮዝ ስፖርት ክለብ በውድድር ዘመኑ ካደረጋቸው 13 ጨዋታዎች በ4 አሸንፎ ፣ በ2 አቻ ሲለያይ በቀሪ 7 ሽንፈት አስተናግዷል።

20 ክለቦች ባሉበት ሊግም በ14 ነጥቦች 16ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።

kuasmeda / ኳስሜዳ

10 Jan, 11:11


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ ሁለተኛ ዙር የሚደረግበት ከተማ ይፋ ሆነ

የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የሁለተኛ ዙር ውድድር በሀዋሳ ከተማ እንደሚደረግ የውድድር ዳይሬክቶሬት አሳውቋል።

አንደኛውን ዙር በአዲስ አበባ ከተማ አበበ ቢቂላ ስታድየም ላይ ሲያደርግ የቆየው ሊጉ ሁለተኛውን ዙር የካቲት 29 እንደሚጀምርም ተያይዞ ተገልጿል።

የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግን ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሶስት ቀሪ ጨዋታዎች እያሉት በ28 ነጥቦች በመምራት ላይ ይገኛል።

kuasmeda / ኳስሜዳ

07 Jan, 10:08


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
ሃዋሳ ከተማ፣ድሬደዋ ከተማ፣ቅዱስ ጊዮርጊስ እና መቐለ 70 እንደርታ ቅጣት ተላልፎባቸዋል

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
ሐብታሙ ሽዋለም (ኢትዮ ኤሌትሪክ ) ቅዳሜ ታህሳስ 26 2017 ዓ.ም. ክለቡ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር ባደረገው የ12ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ በ 87 ኛ ደቂቃ ላይ ሁለተኛ ቢጫ ካርድ የሚያስጥ ጥፋት በመፈፀሙ በቀይ ካርድ ከጨዋታ ሜዳ የተወገደ ስለመሆኑ ሪፖርት ቀርቦበታል ። ስለሆነም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ እ ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 2 አንቀፅ 35(መ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።
አብዩ ካሣዬ (ድሬደዋ ከተማ) ቅዳሜ ታህሳስ 26 2017 ዓ.ም. ክለቡ ከባህርዳር ከተማ ጋር ባደረገው የ12ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ በ 5 ኛ ደቂቃ ላይ የተጋጣሚን ቡድን ግልፅ ግብ የማግባት ዕድል በማበላሸት በቀይ ካርድ ከጨዋታ ሜዳ የተወገደ ስለመሆኑ ሪፖርት ቀርቦበታል ። ስለሆነም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ እፌ ዲሲፕሊን መመሪያ መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ ና በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 3000 /ሶስት ሺ/ እንዲከፍል የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።
እንየው ካሳሁን (ሃዋሳ ከተማ) አርብ ታህሳስ 25 2017 ዓ.ም. ክለቡ ከፋሲል ከነማ ጋር ባደረገው የ12ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ በ 45 ኛ ደቂቃ ላይ ሁለተኛ ቢጫ ካርድ የሚያስጥ ጥፋት በመፈፀሙ በቀይ ካርድ ከጨዋታ ሜዳ የተወገደ ስለመሆኑ ሪፖርት ቀርቦበታል ። ስለሆነም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 2 አንቀፅ 35(መ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።
ፍፁም ጥላሁን (ቅዱስ ጊዮርጊስ) በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም ከታች በተጠቀሱት 4 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ ካርድ ተመልክቷል ።

1. ቅዱስ ጊዮርጊስ – ፋሲል ከነማ
2. ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ – ቅዱስ ጊዮርጊስ
3. መቻል – ቅዱስ ጊዮርጊስ
4. ቅዱስ ጊዮርጊስ – ኢትዮ ኤሌትሪክ

በመሆኑም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 10,000 /ኣስር ሺ/ እንዲከፍል የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል ።
ሃዋሳ ከተማ ክለቡ ከፋሲል ከነማ ጋር ባደረገው የ12 ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ የሃዋሳ ከተማ ቡድን ተጫዋች የሆኑት
1. እንየው ካሳሁን
2. በረከት ሳሙኤል
3. ሰለሞን ወዴሳ
4. አሊ ሱሌማን
5. ወንድማገኝ ተሾመ
6. እንየው ካሳሁን
7. ቢንያም በላይ
8. ዳዊት ታደሰ

በተለያዩ ጥፋቶች ካርድ የተሰጣቸው በመሆኑ በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ መሰረት የገንዘብ ቅጣት ብር 5000 /አምስት ሺ/ እንዲከፍል የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል፡፡
ድሬደዋ ከተማ ክለቡ ከባህርዳር ከተማ ጋር ባደረገው የ12 ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ የድሬደዋ ከተማ ቡድን ተጫዋች የሆኑት

1. አብዩ ካሣዬ
2. አህመድ ረሺድ
3. ኢስማኤል አብዱል ጋኒዩ
4. አቡበከር ሻሚል
5. አላዛር ማረነ
በተለያዩ ጥፋቶች ካርድ የተሰጣቸው በመሆኑ በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ መሰረት የገንዘብ ቅጣት ብር 5000 /አምስት ሺ/ እንዲከፍል የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል፡፡
ቅዱስ ጊዮርጊስ ክለቡ ከኢትዮ ኤሌትሪክ ጋር ባደረገው የ12 ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ የቅዱስ ጊዮርጊስ ቡድን ተጫዋች የሆኑት
1. አማኑኤል አረቦ
2. ፍፁም ጥላሁን
3. ቢንያም ፍቅሩ
4. በረከት ወልዴ
5. ሄኖክ ዮሀንስ
6. አዳነ ግርማ
7. ተመስገን ዮሃንስ

በተለያዩ ጥፋቶች ካርድ የተሰጣቸው በመሆኑ በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ መሰረት የገንዘብ ቅጣት ብር 5000 /አምስት ሺ/ እንዲከፍል የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል፡፡
መቐለ 70 እንደርታ ክለቡ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር ባደረገው የ12 ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ የመቐለ 70 እንደርታ ቡድን ተጫዋች የሆኑት

1. መድሃኔ ብርሀኔ
2. ሔኖክ አንጃው
3. ሙሉጌታ ወ/ጊዮርጊስ
4. ሸሪፍ መሀመድ
5. ዘረሰናይ ብርሃነ
በተለያዩ ጥፋቶች ካርድ የተሰጣቸው በመሆኑ በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ መሰረት የገንዘብ ቅጣት ብር 5000 /አምስት ሺ/ እንዲከፍል የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል፡፡

kuasmeda / ኳስሜዳ

06 Jan, 06:08


ፉክክር የሚያሳየን ፈታኝ ዓመትም ይመስለኛል ።

ሀትሪክ :- ቀጣይ ዕቅድክ ምንድነው ?

ብሩክ ማርቆስ :- ሀገሬን በአህጉራዊና በዓለም አቀፋዊ ውድድሮች ላይ ከመወከል ባለፈ ውጤታማ እንድትሆን ከቡድን ጓደኞቼ ጋር በመሆን የበኩሌን አስተዋጽዖ ማድረግ እና አለፍ ሲልም ከሀገር ውጭ ባሉ ክለቦች የመጫወት እቅድ አለኝ ። ለዛም በእየለቱ ጠንክሬ እየሰራሁ እገኛለሁ ።

ሀትሪክ :- ብሔራዊ ቡድኑ ውጤታማ እንዲሆን ምን መደረግ አለበት ትላለህ ?

ብሩክ ማርቆስ :- የብሔራዊ ቡድናችን ውጤት ማጣት ችግር ዛሬ የመጣ ነው ብዬ አላስብም ። ባለፉት ዓመታትም የነበረ ነው። ድንገት ብልጭ ብሎ የሚጠፉ ስኬቶች አልፎ አልፎ ቢኖሩም በተከታታይ በአህጉራዊና አለም አቀፍ ውድድር ላይ የሚፎካከር ጠንካራ ብሔራዊ ቡድን ግን አልነበረንም ።

ይህንን ችግር ለመቅረፍ የተጠናከረ ሀገራዊ ስራ መሰራት አለበት ብዬ አስባለሁ ። ለአብነት ሁሉም ክለቦች ወጣት ቡድኖቻቸው ላይ በደንብ ትኩረት ሰጥተው መስራት አለባቸው ። ጠንካራ ወጣት ቡድን ያለው ክለብ ጠንካራ ዋና ቡድን ይኖረዋል ። የጠንካራ ዋና ቡድኖች ውጤት ጠንካራና ተፎካካሪ ብሔራዊ ቡድን ይፈጥራል የሚል እይታ ነው ያለኝ ።

ሀትሪክ :- ከሀድያ ሆሳዕና ጋር አሁን ላይ ያለህ ኮንትራት እስከ መቼ የሚቆይ ነው ?

ብሩክ ማርቆስ :- አሁን ላይ ከሀዲያ ሆሳዕና ጋር ያለኝ ኮንትራት በዚህ ዓመት መጨረሻ ይጠናቀቃል ።

ሀትሪክ :- በሊጉ ከመሪው በሁለት ነጥብ ብቻ ርቀት ላይ ነው የምትገኙት ፤ በኢትዮጵያ ዋንጫም የመጨረሻ አስራ ስድስቱን ተቀላቅላቸኋል። በዓመቱ መጨረሻ ምን ለማሳካት አቅዳችሁ እየሰራችሁ ነው ?

ብሩክ ማርቆስ :- በኢትዮጵያ ዋንጫም በሊጉም ከዓምናው የተሻለ ውጤት ለማምጣት እንደ ክለብ እቅድ አለን። እቅዳችንን ለማሳካትም ጠንካራ ስራ እየሰራን እንገኛለን ።

ሀትሪክ :- ከሀገር ውስጥ ተጫዋቾች አርዓያዬ የምትለው ማነው ?

ብሩክ ማርቆስ :- በጣም በዙ ናቸው ። ለምሳሌ አስራት መገርሳ ፣ አዲስ ህንፃ ፣ ጋቶች ፓኖም… በእኔ ቦታ ከተጫወቱ እና እየተጫወቱ ያሉ እንደ አርዓያ የምወስዳቸው ኢትዮጵያዊያን ተጫዋቾች ናቸው ።

ሀትሪክ :- ኳስ ተጫዋች ባትሆን ኖሮ በምን ሙያ ትሰማራ ነበር ?

ብሩክ ማርቆስ :- ከልጅነቴ ጀምሮ ራሴን ከኳስ ተጫዋች ውጭ አይቼው አላውቅም። ኳስ ተጫዋች ባልሆን ኖሮ ብዬ አስቤ ሰለማላውቅ ፈጣሪ ይመስገን ህልሜን እየኖርኩ ነው ።

ሀትሪክ :- ዛሬ አመሻሽ 12:00 ጀምሮ ከሊጉ መሪ መቻል ተጠባቂ ጨዋታ ታደርጋላችሁ። ካሸነፋችሁ የሊጉን መሪ ትሆናላችሁ። ለጨዋታው ያደረጃችሁት ዝግጅት ምን ይመስላል ? የተለየ ዝግጅት አድርጋችኋል ?

ብሩክ ማርቆስ :- ለዛሬው ጨዋታ ብለን የተለየ የምንለው ዝግጅት አላደረግንም ። ለሁሉም ክለቦችና ለሁሉም ጨዋታዎች ተመሳሳይ የሆነ ዝግጅት ነው የምናደርገው ።

ሀትሪክ :- በጨዋታው አሸንፋችሁ ወደ መሪነት ለመምጣት ያለው የቡድኑ መንፈስ ምን ይመስላል ?

ብሩክ ማርቆስ :- ቡድናችን ጥሩ መነቃቃት ላይ ነው ያለው ። 90 ደቂቃውን ለመፋለም ዝግጁ ነን።

ሀትሪክ :- ምስጋና

ብሩክ ማርቆስ :- በመጀመሪያ ዕድሜና ጤና ሰጥቶ ለዚህ ያደረሰኝ ፈጣሪ ይመስገን ። በመቀጠል ከልጅነቴ ጀምሮ ከእኔና ከእኔ ህልም ጋር የቆሙትን ቤተሰቦቼን ከልብ አመሰግናለሁ ። ስቀጥል ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ሀዲያ ሆሳዕና እንድገባ አምኖኝ ከዛም በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደ ሜዳ እንድገባ እድሉን የሰጠኝን አሰልጣኝ ያሬድ ገመቹን ከልብ አመሰግናለሁ ፤ በየቀኑ እንድሻሻል የሚያግዘኝ አሰልጣኝ ግርማ ታደሰ(መንቾ) እና የአሰልጣኝ ቡድን አባላት ፣ አጠቃላይ የቡድን ጓደኞቼን ፣ የሀዲያ ሆሳዕና እግር ኳስ ክለብ ፅ/ቤት እና የክለቡ ስራ አመራር ቦርድ እንዲሁም የሀዲያ ሆሳዕና ደጋፊዎችን ሁሌም ከጎኔ ሰለሆናችሁ ከልብ አመሰግናለሁ ።

ሀትሪክ ስፖርት ድህረገፅም እንግዳችሁ ስላደረጋቹኝ ከልብ አመሰግናለሁ ።

kuasmeda / ኳስሜዳ

06 Jan, 06:08


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
“ህልሜን እየኖርኩ ነው” “ቡድናችን በጥሩ መነቃቃት ላይ ነው” “ለእግር ኳስ የተለየ ፍቅር ካለው ማህብረሰብ ውስጥ በመፈጠሬ ዕድለኛም ደስተኛም ነኝ” “የውጤታማነታችን ሚስጥር አንድነታችን ነው” “ክለቦች ወጣት ቡድኖቻቸው ላይ በደንብ ትኩረት ሰጥተው መስራት አለባቸው” ብሩክ ማርቆስ (ሀዲያ ሆሳዕና)

በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ በቅርብ ዓመታት ላዬ አስደናቂ የሜዳ ላይ እንቅስቃሴ በማሳየት ላይ ካሉ ተጫዋቾች አንዱ ነው።

በክለብ ያሳየው ብቃትም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን ማልያ ለብሶ እንዲጫወትም አድርጎታል። በቀጣይ ዓመታት በሊጉ ከሚነግሱ ፤ በሌሎች ሊጎች ከሚታዩ እና ለዋልያዉ በተስፋ ከሚጠበቁ ተጫዋቾች መካከል ከፊት የሚገኘው ነው።

ለትውልድ ከተማው ክለብ በመጫወት ላይ የሚገኘው ብሩክ ማርቆስ………ውድ የሀትሪክ ስፖርት ድህረገጽ ተከታታዮች ከተስፈኛው ብሩክ ማርቆስ ጋር ቆይታ አድርገናል።

የሀድያ ብሔረሰብ የዘመን መለወጫ በዓል “ያሆዴ”ን አስታኮ የሚደረገው “ያሆዴ ካፕ” የእግርኳስ ውድድር ዛሬ ለደረሰበት ትልቁን ድርሻ አበርክቶለታል።

ከ2015 የውድድር ዘመን ጀምሮ በከቤራዎቹ ማልያ በመድመቅ ላይ ያለው ብሩክ የዘንድሮ ሁሉም አስሩንም የሊግ ጨዋታዎች ጨምሮ በአጠቃላይ 66 የሊግ ጨዋታዎችን በክለቡ ማልያ ለብሶ በሊጉ ተጫውቷል።

ከእግርኳስ አጀማመሩ እስከ ወደ ፊት ህልሙ ፤ ስለ ሀድያ ሆሳዕና የዘንድሮው ድንቅ ግስጋሴ ፤ ስለ ኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን እንዲሁም ዛሬ ከመቻል ጋር ስለሚያደርጉት ተጠባቂ ጨዋታ ሀሳቡን አጋርቶናል።

ሀትሪክ :- የእግር ኳስ አጀማመርክ ምን አይነት ገፅታ ነበረው ?

ብሩክ ማርቆስ :- ያው እግር ኳስን (ይህ ምላሽ በበርካታ ኢትዮጵያውያን ተጨዋቾች ዘንድ የተለመደ ምላሽ ቢመስልም በወቅቱ ሌሎች አማራጮች ሰላልነበሩ) እንደ አብዛኛው ኢትዮጵያዊ በሰፈር ውስጥ ጨርቅ ኳስ በመጫወት ነበር የጀመርኩት ። ከልጅነቴ ጀምሮ የእግር ኳስ ፍቅር በውስጤ ነበረ እና ፍቅሬን ለማስታገስም በሰፈር እና በትምህርት ቤቶች ውድድሮች ላይ በመሳተፍ ነው የጀመርኩት ፤ ከዛም በፕሮጀክት ደረጃ በሆሳዕና ከተማ “ሴች ዱና” በሚባል የፕሮጀክት ቡድን ውስጥ በሰይፈዲን(ሰይፎ) አማካይነት ከእድሜ እኩዮቼ ጋር እንሰራ ነበር።

ሀትሪክ :- ክለብ የገባህበትን አጋጣሚ አስታውሰኝ እስኪ ?

ብሩክ ማርቆስ :- ለመጀመሪያ ጊዜ ክለብ የገባሁት በ2014 ዓ.ም ላይ ነበር ። በወቅቱ በብሔራዊ ሊግ የሚሳተፈው “ሀዲያ ሌሞ” ክለብ የሙከራ ጊዜ አዘጋጅቶ ነበር እና ያን የሙከራ ጊዜዬን በተሳካ ሁኔታ አጠናቅቄ ቡድኑን መቀላቀል ችያለሁ ። ሀዲያ ሌሞ ቤት የነበረኝ የአንድ ዓመት ቆይታ ለእኔ በጣም ጥሩና ብዙ ነገሮችን የተማርኩበትም ነበር ማለት እችላለሁ ።

ከዛም በመቀጠል በየዓመቱ መስከርም ወር መጀመሪያ ላይ የሀዲያ ብሔር ዘመን መለወጫ “ያሆዴ” በዓል በደማቅ ሁኔታ ይከበራል ። የበዓሉ ማድመቂያ ከሆነ ነገሮች አንዱ በክረምት ወራት የሚካሄድ “ያሆዴ ካፕ” ውድድር ሲሆን ይህ ውድድር የሚካሄደውም በዓሉ ከመድረሱ በፊት ቀደም ብሎ ባለው ክረምት ላይ ነው ።

በዛ ዓመት በነበረው “ያሆዴ ካፕ” ውድድር ላይ “ወየዳ” ቡድንን ወክዬ በመጫወት ከቡድን ጓደኞቼ ጋር የውድድሩ ሻምፒዮን መሆን ችለናል ። በፍፃሜው ጨዋታ ቀን በወቅቱ የሀዲያ ሆሳዕና ዋና አሰልጣኝ በመሆን የተሾሙት አሰልጣኝ ያሬድ ገመቹ ሆሳዕና አቢዬ ኤርሳሞ መታሰቢያ ስታዲየም ተገኝተው የፍፃሜውን ጨዋታ ከተመለከቱ በኃላ የሙከራ እድል ሰጡኝ ።

በሙከራው ወቅት በነበረኝ ተስፋ ሰጪ እንቅስቃሴ ምከንያት ቀጥታ ወደ ሀዲያ ሆሳዕና ዋናው ቡድን በአሰልጣኝ ያሬድ ገመቹ አማካይነት በ2015 ዓ.ም መቀላቀል ችያለሁ ። በዚህ አጋጣሚ አሰልጣኝ ያሬድ ገመቹ አምኖብኝ ዕድል ስለሰጠኝ ከልብ አመሰግናለሁ ማለት እፈልጋለሁ ።

ሀትሪክ :- ሀድያ አካባቢ ያለው የእግርኳስ ፍቅር ምን ይመስላል ?

ብሩክ ማርቆስ :- ሀዲያ ዞን ውስጥ ሴቱም ወንዱም ለእግር ኳስ ስፖርት ያለው ፍቅር የተለየ ነው ። የሚገርምህ ሀዲያ ሆሳዕና ጨዋታ ሲኖረው በከተማው የተለያዩ ቦታዎች ላይ የክለቡ ባንዲራ ተሰቅሎ ትመለከታለህ ፣ የሊጉ የውድድር ቅርፅ በሜዳ እና ከሜዳው ውጪ በነበረ ወቅት ሀዲያ ሆሳዕና ጨዋታ ሲኖረው ስታዲየም ውስጥ እና ስታዲየም ዙሪያ የተገኘውን ሰው አይተህ ቤት ውስጥ ማን ቀረህ? ብለህ እራስህን ልትጠይቅ ትችላለህ።

ዲኤስቲቪ ከመጣ በኋላም ሀዲያ ሆሳዕና ጨዋታ ካለው ዲኤስቲቪ ቤቶች ተጨናንቀው ማየት የተለመደ ነው ።

ሆሳዕና አቢዬ ኤርሳሞ መታሰቢያ ስታዲየም ብትሄድ የክረምት ውድድሮችን ለማየት የሚሄደውን የሰው ብዛት ይገርምሀል ። የሀዲያ ህዝብ ለእግር ኳስ አልፎም ለሀዲያ ሆሳዕና እግር ኳስ ክለብ ምን ያህል ፍቅር እንዳለው ክለቡ ጨዋታ ባለበት ቦታ ሁሉ በየከተማው እየዞረ የሚደግፈውን የደጋፊ ብዛት ማየት ነው ።

ባለፈው ክረምት ደቡብ አፍሪካ በሄድንበት አጋጣሚ ስታዲየም ውስጥ የነበረው የተመልካች ቁጥር ብዛት አይተሀል መቼም ። ያን ሁሉ ተመልካች ያየ ሰው ኢትዮጵያ ውስጥ ለዛውም ሆሳዕና እንጂ ደቡብ አፍሪካ ነበር ብትለው ላያምን ይችላል ። በአጠቃላይ ለእግር ኳስ የተለየ ፍቅር ካለው ማህብረሰብ ውስጥ በመፈጠሬ እድለኛም ደስተኛም ነኝ ።

ሀትሪክ :- በፕሮጀክትም ሆነ ወደ ክለብ ስትቀላቀል የቤተሰብክ ድጋፍ ምን ያህል ነበር ?

ብሩክ ማርቆስ :- ያለ ፈጣሪና ቤተሰብ እገዛማ እዚህ ጋር መገኘት ፈፅሞ የሚታሰብ አይደለም ። ቤተሰብ ህልሜን እንድኖር ባያግዘኝ ፈጣሪም ባይረዳኝ እዚህ እገኛለሁ ማለት ለእኔ ድፍረት ነው ። በዚህ አጋጣሚ ከፈጣሪ በመቀጠል ቤተሰቦቼን ላመሰግናቸው እወዳለሁ ።

ሀትሪክ :- በእግር ኳስ ምርጡ ጓደኛክ ማነው ?

ብሩክ ማርቆስ :- ሀዲያ ሆሳዕና ውስጥ ካሉ ከታዳጊ እስከ ሲነየር ተጨዋቾች ድረስ ጥሩ ግንኙነት አለኝ ። ለእኔ ሁሉም ምርጥ ጓደኞቼ ናቸው ።

ሀትሪክ :- የሀድያ ሆሳዕና የዘንድሮው የውድድር ዘመን ውጤታማነት ሚስጥር ምንድነው ማለት ይቻላል ?

ብሩክ ማርቆስ :- የውጤታማነታችን ሚስጥር አንድነታችን ነው ። እግር ኳስ የህብረት ስራ ነው ። ሜዳ ውስጥም ከሜዳ ውጭም ከተባበርክና ለአንድ ዓላማ ከቆምክ ስኬታማ መሆን ትችላለህ ።

ሀትሪክ :- የዘንድሮው ፉክክር ካለፉት አመታት ጋር ሲነፃፀር ከባድ ወይስ ….

ብሩክ ማርቆስ :- ዘንድሮ የጨዋታዎች ቁጥር ከፍ ብሏል ። ስለዚህ ጫና አለው ። አራት ቡድኖች ወደ ታችኛው ሊግ ስለሚወርዱ ሁሉም ቡድኖች ሁሉንም ጨዋታዎች በጥንቃቄ ነው የሚጫወቱት ።2

ሌላው ዳግም ወደ ሊጉ ያደጉት አርባምንጭ ከተማና ኢትዮ ኤሌክትሪክም ጠንካራ ተፎካካሪ ሆነው ነው የተመለሱት ። ከአራት ዓመታት በኃላ ዳግም ወደ ሊጉ የተመለሱት ሶስቱ የትግራይ ቡድኖችም ብንመለከት በጣም ጠንካራ ናቸው ። ሰለዚህ ሊጉ ጥሩ [...]

kuasmeda / ኳስሜዳ

03 Jan, 18:06


ዚህ ሰዓት ላይ ላይ ይሄ ይሄ ነው አልልህም ለምን ? አብዛኞቹ ወጣቶች ናቸው ፤ ቡድኑ እንደ እቅድ ሀ ብዬ የተቀበልኩት ነው እና ወጣቶች ናቸው ብዙዎቹ ልምድ ያላቸው ተጫዋቾች አይደለም ያሉኝ። ነገር ግን ይህን ስል የተሻለ ነገር የመስራት አቅም ያላቸው ተጫዋቾች አሉ። በሒደት ቡድኑን ከፍ ማድረግ እና ኢትዮ ኤሌክትሪክ የሚታወቅበትን ወደ ጥሩ ቦታው ላይ ለመመለስ ነው ትልቁ ዓላማዬ።”

በቀድሞው ስሙ መብራት ኃይል በአሁኑ መጠሪያው ኢትዮ ኤሌክትሪክ ፕሪሚየር ሊጉ በአዲስ ቅርፅ ከ1990 ጀምር ሲደረግ ቀዳሚውን ዋንጫ የወሰደ ክለብ ነው።በ1993ም ሁለተኛውን ደግሟል።

ቀስ በቀስ ከነበረው የታላቅነት መድረክ ተንሸራቶ ከሊጉ እስከ መሰናበት ደርሶ ዳግም በዘንድሮው የውድድር ዘመን ቤተኛ እንግዳ ሆኖ ወደ ለመደው ሊግ ተመልሷል።

ክለቡ ከስም ለውጡ በኋላ ዳግም የቀደመ ስሙን ለመመለስ ስኬታማ ስራዎችን እየሰራ ይገኛል።

ይህ ይሳካ ዘንድም የአመራሩ ድጋፍ እንዳልተለየው አሰልጣኝ ዘሪሁን ገልጿል። “ይህ ክለብ ትልቅ ነው ከነ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቀጥሎ ታሪካዊ ክለብ ነው ኢትዮ ኤሌክትሪክ ። እነሱ ሲሰጡኝም ሆነ ስንወያይ የተሻለ ነገር ለመስራት ጥሩ ነገር ለማድረግ ነው እየሰራን ያለነው። ቀስ በቀስ የተሻለ ቡድን እንደምንሰራ ያውቁታል እነሱም ፤ ብዙ ድጋፍ እያደረጉልኝ ነው እና ጥሩ ነገር ለማድረግ እነሱንም አመሰግናቸዋለሁ።”

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አሁን እየተካሄደ ባለበት ቅርፅ በተመረጡ ከተሞች መደረግ ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ወደ አዳማ ከተማ ተጉዞ አሸንፎ አያውቅም። ዘጠኝ ጨዋታዎች አድርጎ በሶስቱ አቻ ሲለያይ በስድስቱ ተሸንፏል።

የአሁኑ የቡድኑ ዋና አሰልጣኝ ዘሪሁን ሸንገታ ደግሞ ቅዱስ ጊዮርጊስን እየመራ ከመዲናዋ በ85 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በምትገኘው ከተማ ካደረጋቸው 29 ጨዋታዎች በ18 አሸንፏል። ይህም ቀዳሚው አሰልጣኝ ያደርገዋል።

አሰልጣኝ ዘሪሁን ከዚህ ጋር በተያያዘም የኔ ትኩረት በአዳማ በሚኖረን ቆይታ የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ስራዬን መስራት እና መስራት ብቻ ነው ብሏል።

በቡድን ዜና አኳያ ተከላካዩ አብዱላሂ አሊ በጉዳት ምክንያት ከጨዋታዉ ውጪ የሆነ ብቸኛው የቡድኑ ተጫዋቾች መሆኑን የአሰልጣኝ ዘሪሁን ሸንገታ ገልጿል።

የ12ኛ ሳምንት መርሐግብሩን ዛሬ ማድረግ የጀመረው ፕሪሚየር ሊጉ ነገ ከአመሻሽ 12:00 ጀምሮ በአሰልጣኝ ፋሲል ተካልኝ የሚመራው ቅዱስ ጊዮርጊስን በአሰልጣኝ ዘሪሁን ሸንገታ ከሚመራው ኢትዮ ኤሌክትሪክ ያገናኛል።

ሁለቱ ክለቦች ከዚህ ቀደም ተገናኝተው በሊጉ በ40 ጨዋታዎች ተገናኝተው ቅዱስ ጊዮርጊስ በ28 ሲያሸንፍ ኢትዮ ኤሌክትሪክ በበኩሉ በ3 አሸንፎ ፤ በቀሪ 9 ነጥብ ተጋርተዋል።

kuasmeda / ኳስሜዳ

03 Jan, 18:06


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
“ካደክበት ፣ ብዙ ዓመታት ካሰለጠንክበት እና ከተጫወትክበት ክለብ ጋር መጫወት ከባድ ነው” “ኢትዮ ኤሌክትሪክን ወደ ሚታወቅበት ጥሩ ቦታው ላይ ለመመለስ ነው ትልቁ ዓላማዬ” “ቅዱስ ጊዮርጊስ ኢትዮጵያ ውስጥ ካሉት መካከል ትልቁ ክለብ ነው ፤ ይሄን ማንም የማይክደው ነው።” “የቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊዎቼ 12ኛ ተጫዋቾቼ ነበሩ።”

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ12ኛ ሳምንት ጨዋታ በነገው ዕለትም ቀጥሎ ሲደረግ አመሻሽ 12:00 ጀምሮ ቅዱስ ጊዮርጊስን ከኢትዮ ኤሌክትሪክ የሚያገናኘው ጨዋታ ይጠበቃል።

በተለይም ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር ከታዳጊነቱ ጀምሮ ከ20 ዓመታት በላይ እጅግ ስኬታማ ጊዜያትን ያሳለፈው ፤ በ2014 እና በ2015 ቅዱስ ጊዮርጊስን በዋና አሰልጣኝነት እየመራ ሻምፒዮን የሆነው አሰልጣኝ ዘሪሁን ሸንገታ ለመጀመሪያ ጊዜ የቀድሞ ክለቡን መግጠሙ ጨዋታውን ተጠባቂ አድርጎታል።

በተጨማሪም ቅዱስ ጊዮርጊስን ከሚመራው አሰልጣኝ ፋሲል ተካልኝ ጋር በተጫዋችነትም ሆነ በአሰልጣኝነት በፈረሰኞቹ ቤት ታላላቅ ስኬቶችን በጋራ አስመዝግቧል።

አሰልጣኝ ዘሪሁን ከጨዋታው ጋር በተያያዘ ከሀትሪክ ስፖርት ድህረ ገፅ ጋር አጠር ያለ ቆይታን አድርጓል።

የውድድር ዓመቱ ጅማሮ መልካም ነው የሚለው አሰልጣኝ ዘሪሁን በርከት ያሉ ወጣት ተጫዋቾች መያዙን በመጥቀስ የእስካሁኑ ጉዞ መጥፎ የሚባል አይደለም ጥሩ ነው ሲል ገልፆታል።

ከፕሪሚየር ሊጉ በጣት የሚቆጠሩ ተጫዋቾችን ብቻ ናቸው ያስፈረምኩት አብዛኞቹ ከከፍተኛ ሊግ የመጡ ናቸው ፤ ቢሆንም ግን እጅግ ጥሩ አቅም እና ተስፋ ያላቸውም ናቸው ብሏል።

“አቅም አላቸው ፤ መስራት የሚችሉ እና ወደ ፊት ትልቅ ተስፋ ያላቸው ናቸው። እነሱን ማቀናጀት እና ወደ ጥሩ ነገር ለመሄድ ጊዜ ይፈልጋል። አሁንም በዚህ ሂደት ላይ ነው የምንገኘው።ተዋህደው ከዚህ በላይ የማድረግ አቅም አላቸው።”

አሰልጣኝ ዘሪሁን በቅዱስ ጊዮርጊስ ክለብ ከታዳጊ ቡድን ጀምሮ ሌላ ማልያን ሳይለብስ ለቢጫ እና ቀዩ ማልያ ታምኖ በተጫዋችነቱ በርካታ ዋንጫዎችን አሸንፏል።

ጫማውን ከሰቀለ በኋላም የፈረሰኛው እና የዘሪሁን ሸንገታ ቁርኝት በምክትል እና ዋና አሰልጣኝነት ታላላቅ ስኬቶቹን አስቀጥሎ ተጉዟል።

ሜዳ ላይ በሚያሳየው ብቃት የክለቡ ደጋፊዎች ደግመው ደጋግመው አዚመውለታል። በተጫዋችነት ያስፈነደቃቸውን የክለቡን ደጋፊዎች በምክትል አሰልጣኝነትም ዳግም ደስታቸውን ሲያስቀጥል በዋና አሰልጣኝነት ደግሞ ለአራት አመታት ከዋንጫ ርቆ የቆየውን ክለብ ባለ ድል አድርጓል። በተከታታይ ለሁለት ዓመታት ፤ ካደረጋቸው 60 ጨዋታዎች በሶስቱ ብቻ ተሸንፎ።

በአወዛጋቢ ሁኔታ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር ከተለያየ በኋላ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ የቀድሞ ክለቡን በነገዋ ዕለት በተቃራኒ ሆኖ ይገጥማል።

አሰልጣኝ ዘሪሁን ስለዚህ ቀዳሚ ጨዋታ ሲናገርም ያሳደገኝን ክለብ መግጠም ከባድ ነው ሲል ተናግሯል።

“ከባድ ነው ፤ ካደክበት ብዙ ዓመት ካሰለጠንክበት እና ከተጫወትክበት ክለብ ጋር መጫወት ከባድ ነው ለኔ። ግን እንደማንኛውም ጨዋታ ያው እግር ኳስ ነው እንደ አሰልጣኝነቴ ከማንኛውም ቡድን ጋር እንደምጫወተው ጥሩ ዝግጅት እያደረኩ ነው ያለሁት።”

“ቅዱስ ጊዮርጊስ ኢትዮጵያ ውስጥ ካሉት ትልቁ ክለብ ነው። ይሄን ማንም የማይክደው ነው።ከእርሱ ጋር ነው የምጫወተው አዎ ፤ ትልቅ ቡድን ነው ጠንካራ ጨዋታ ይገጥመኛል።”

አሰልጣኝ ዘሪሁን ነገ የሚገጥመው 89ኛ ዓመቱን የደፈነውን የልጅነት ክለቡን ቅዱስ ጊዮርጊስን ብቻ ሳይሆን አብሮት በተጫዋችነት እና በአሰልጣኝነት ስኬትን ካጣጣመው አሰልጣኝ ፋሲል ተካልኝ ጋር ነው።

“ይሄ ከባድ ጨዋታ ይሄ ቀላል ጨዋታ ነው የሚባል ነገር የለም ሁሉም ጨዋታ ትኩረት እና ትኩረት የሚፈልግ ነው። ወንድሜ ነው(አሰልጣኝ ፋሲል ተካልኝ)ከወንድሜ ጋር ነው የምጫወተው በወንድምነት ሁለታችንም አብረን ያሳደገን እና ያደግንበት ክለብ ውስጥ ነው ያደግነው። ስንወለድ አንድ አካባቢ ያደግን ነን በወንድምነት። ከአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ጀምሮ አንድ ላይ ነው የተማርነው እና ስራችን እና ስራችን ላይ አተኩረን እሱም እኔም ጥሩ ነገር እንሰራለን ብዬ አስባለሁ።”

ከላይ እንደተጠቀሰው የአሰልጣኝ ዘሪሁን ሸንገታ እና የቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊዎች ቁርኝት እጅግ የተለየ ነው። እርሱ ሰለ ቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊዎች አንስቶ አይጠግብም። እነርሱም ለብዙ የደስታ ቀኖቻቸው ምክንያት ለሆነው ውድ ልጃቸው መውደዳቸውን ለመግለፅ ቃላት ለመምረጥ ይቸገራሉ።

እንግዲህ ነገም ያሳደገኝ ነው ከሚለው ክለብ ፣ ወንድሜ ከሚለው አሰልጣኝ ፋሲል ተካልኝ ጋር ብቻ ሳይሆን ከነዚህ ደጋፊዎች ጋርም ነው በተቃራኒ ሆኖ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታድየም የሚሰየመው።

ስለ እርሱ እና ስለ ቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊዎች ትስስር አሰልጣኝ ዘሪሁን ሲያነሳ በነገው ጨዋታ ከባዱ እና ትልቁ ነገር ደጋፊዎች ናቸው ይላል።

“ለነሱ ትልቅ ክብር ነው ያለኝ መቼም የማልረሳው የማልጥለው ትልቅ ክብር አለኝ ለነሱ። በቅዱስ ጊዮርጊስ ትልቅ ደጋፊዎቼ ፤ 12ኛ ተጫዋቾቼ ነበሩ። ለቅዱስ ጊዮርጊስ የሚደክሙትን የሚለፉትን ነገር ስለማውቅ ከምንም በላይ እነሱን ነው ቀና ብዬ ማየት የማልችለው ለምን ? በጣም በጣም በጣም ትልቅ ነገር አድርገውልኛል። ውጤት እንዳመጣ አግዘውኛል። ቅዱስ ጊዮርጊስ በሄደበት ሁላ ቅዱስ ጊዮርጊስን የሚደግፉ ተስፋ ሳይቆርጡ ለጥሩ ውጤት ያበቁ ትልቅ ደረጃ እንዲደርስ ትልቁን ሚና የተወጡ ናቸው። ከምነግርህ በላይ ትልቅ ክብር አለኝ ለነሱ።”

ከዚህ መልሱ በመቀጠል ያነሳንለት ጥያቄ ስለወቅቱ የቅዱስ ጊዮርጊስ ሁኔታ ነበር። ቅዱስ ጊዮርጊስ በዘንድሮው የውድድር ዘመን ከወትሮው ቡድኑ ቀዝቀዝ ብሎ ስለመቅረቡ ብዙዎች ይስማማሉ።

አሁን ላይ በውስጡ ስለሌለው ይህ ነው የምለው ነገር የለም የሚለው አሰልጣኝ ዘሪሁን ግን ዳግም ወደ ቀደመ ብቃቱ እንደሚመለስ ዕምነቱ መሆኑን ጠቁሞ አልፏል።

“ማንኛውም ቡድን ጠንክሮ መስራት እና የተሻለ ደረጃ መድረስ ይችላል። ጊዮርጊስ ደግሞ ትልቅ ቡድን ነው። ከየትኛውም ቡድን በላይ ትልቅ ቡድን ነው እና ወደ ጥሩ ነገር ይመለሳል ብዬ አስባለሁ ግን እዛ ውስጥ ስለሌለው ይሄ ይሄ ነው ብዬ መናገር ይከብደኛል።”

በዋና አሰልጣኝነት የሁለት ጊዜ ሻምፒዮን የሆነው አሰልጣኝ ዘሪሁን በውድድር ዓመቱ የሊጉን የሁለት ጊዜ ሻምፒዮን እየመራ ባደረጋቸው 10 የሊግ ጨዋታዎች በሶስት አሸንፎ ፣ በስድስት አቻ ሲለያይ በአንድ ብቻ ተሸንፏል።

በሊጉም ባለፉት ዘጠኝ ተከታታይ ጨዋታዎች ምንም ሽንፈት ባለማስተናገድ ከሊጉ መሪ መቻል ጋር ተመሳሳይ ቁጥር ይዟል።

እግር ኳስ ሂደት ነው የሚለው አሰልጣኙ በዚህ ላይ የአብዛኞቹ ተጫዋቾቹ በፕሪሚየር ሊጉ ልምድ አልባ ስለመሆናቸው በማንሳት ካሉት ልምድ ያላቸው ተጫዋቾች ጋር በማጣመር የተሻለውን ኢትዮ ኤሌክትሪክ ለማሳየት ነው የምፈልገው ይላል።

አሰልጣኝ ዘሪሁን በቅዱስ ጊዮርጊስ ዋና አሰልጣኝነት ኃላፊነት ላይ ሳለ በሰጠው አንድ ቃለ ምልልሱ ላይ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ውጪ ከሌላ ክለብ ጋር ዋንጫ የማሳካት አቅሙ እንዳለው ተናግሮ ነበር።በኢትዮ ኤሌክትሪክ ክለብም ትልቁ ዓላማው ክለቡን ወደ ቀደመ ክብሩ መመለስ ስለመሆኑ ጠቅሷል።

“በ[...]

kuasmeda / ኳስሜዳ

29 Dec, 09:36


👉ተወዳጁ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የበአል ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬም የሚቀጥሉ ይሆናል። በዛሬው መርሃግብር:

#ሌሲስተር ሲቲ 🆚 ማንችስተር ሲቲ

11:30 ቀን

🏟 ኪንግ ፓወር


#ቶተነሃም ሆትስፐርስ 🆚 ዎልቭስ

12:00 አመሻሽ

🏟 ኋይኸርትሌይ

👉 በተመሳሳይ ሰዓት ሌሎች መረሃግብሮችም የሚደረጉ ይሆናል።

#ዌስትሃም 🆚 ሊቨርፑል

02:15 ምሽት

🏟 ለንደን

"መልካም ጨዋታ"

kuasmeda / ኳስሜዳ

27 Dec, 16:38


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
የ2009 የውድድሩ አሸናፊ ቀጣዩን ዙር ሲቀላቀል ሸገር እና ሱሉልታም ተጋጣሚዎቻቸውን ረተዋል

የ2017 ዓ.ም የኢትዮጵያ ዋንጫ የሁለተኛ ዙር ጨዋታዎች በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ አበበ ቢቂላ ስታድየም መደረግ ጀምረዋል።

በቀዳሚነት ከረፋድ 4:00 ጀምሮ በተደረገው ጨዋታ የአንደኛ ሊግ ተሳታፊ የሆነው ሱሉልታ ክፍለ ከተማ የፕሪሚየር ሊጉን ተሳታፊ ወልዋሎ አዲግራትን አሸንፏል።

በጨዋታው ሁለተኛ ደቂቃ ላይ ኪያ ወርቁ ያስቆጠረው ግብ ሱሉልታ ክፍለ ከተማን ለዘጠኝ ያህል ደቂቃዎች መሪ ማድረግ ችሎ ነበር።

ጨዋታው 11ኛ ደቂቃ ላይ ሲደርስ ግን ኤፍሬም ኃይለማርያም ወልዋሎ አዲግራትን አቻ አድርጓል።

መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ተጨማሪ ግብ ባለማስተናገዱ ወደ መለያ ምት አምርቶ ሱሉልታ ክፍለ ከተማ 3 – 0 በማሸነፍ የመጨረሻ አስራ ስድሰቱን ተቀላቅሏል።

ሱሉልታ ከተማ በሶስተኛው ዙር ከመቻል እና አዲስ አበባ ከተማ አሸናፊ ጋር ጨዋታውን ያደርጋል።

ቀትር 7:00 ጀምሮ በተደረገው ጨዋታ የከፍተኛ ሊጉ የምድብ ሀ መሪ ሸገር ከተማ ቦሌ ክፍለ ከተማን በመርታት ቀጣዩን ዙር ተቀላቅሏል።

በጨዋታው 18ኛ ደቂቃ ላይ ሰይፈ ዛኪር ሸገርን መሪ ያደረገ ግብ ሲያስቆጥር ቦሌ ክፍለ ከተማዎች ከ20 ደቂቃዎች በኋላ ዑመድ ኦፒቲ ባስቆጠረው ግብ ወደ ጨዋታው ተመልሰዋል።

የመጀመሪያውን አጋማሽ በ1 – 1 ውጤት የፈፀመው የቀትሩ ጨዋታ 53ኛው ደቂቃ ላይ ሌላ ግብ አግኝቷል።

ምስጋናው ሚልኪያሰ የሁለተኛው አጋማሽ ከተጀመረ 8 ደቂቃዎች በኋላ ሸገር ከተማን ዳግም መሪ ሲያደርግ በ81ኛው ደቂቃ ላይ ደግሞ ያሬድ መኮንን 3ኛው ግብ ከመረብ አሳርፏል።

ከያሬድ መኮንን ግብ መቆጠር ሁለት ደቂቃዎች በኋላ ቦሌ ክፍለ ከተማዎች በጁንዲ ሀጂ አማካይነት ግብ አስቆጥረው በቀሩት ደቂቃዎች ዳግም አቻ ለመሆን ቢጥሩም ሳይሳካላቸው ቀርቷል።

ሸገር ከተማ በቀጣይ ዙር የኢትዮ ኤሌክትሪክ እና ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጨዋታ አሸናፊ ጋር ይጫወታል።

9:30 ጀምሮ ሁለቱን የፕሪሚየር ሊግ ክለቦች ወላይታ ድቻ እና መቀሌ 70 እንደርታ ያገናኘው ጨዋታ በ2009 የውድድሩ ሻምፒዮን አሸናፊነት ተጠናቋል።

ሙሉ ዘጠና ደቂቃው ግብ ሳያስተናግድ በተጠናቀቀው ጨዋታ አላፊውን ለመለየት ወደ መለያ ምት አምርቶ ወላይታ ድቻ 3 – 1 በማሸነፍ ወደ ቀጣዩ ዙር መቀላቀሉን አረጋግጧል።

የዓምና የፍፃሜ ተፋላሚ የሆኑት የጦና ንቦቹ በቀጣይ ዙር የአዳማ ከተማ እና ቦዲቲ ከተማን አሸናፊ ይገጥማሉ።

የኢትዮጵያ ዋንጫ የመጀመሪያ ዙር ጨዋታዎች በነገው ዕለትም ቀጥለው ሶስት ጨዋታዎች በአዲስ አበባ አበበ ቢቂላ ስታድየም ላይ ይደረጋሉ።

ረፋድ 4:00 ላይ ድሬደዋ ከተማ ከአርባምንጭ ከተማ ፤ ቀትር 7:00 ላይ ኢትዮጵያ መድኅን ከአርባምንጭ ከተማ እንዲሁም 9:30 ላይ ሀዋሳ ከተማ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።

kuasmeda / ኳስሜዳ

27 Dec, 12:38


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
ሀብታሙ ተከስተ ወደ ክለቡ ተመልሷል

ለረጅም ወራት በጉዳት ምክያንት ከሜዳ ርቆ የሰነበተው ሀብታሙ ተከስተ(ጎላ) ዳግም ወደ ሜዳ መመለሱ እርግጥ ሆኗል።

ተጫዋቹ ያለፉትን ሳምንታት ከፋሲል ከነማ ዋናው ቡድን ጋር አብሮ ልምምድ ሲሰራ ከቆየ በኀላ በይፋ እስከ ቀጣዩ ዓመት መጨረሻ የሚያቆየውን ውል ፈርሟል።

ሀብታሙ በተለይም በፋሲል ከነማ እንዲሁም በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን መለያ በአማካይ ተከላካይ ቦታ ላይ አስደናቂ እንቅሰቃሴ ሲያሳይ እንደነበር የሚታወስ ነው።

kuasmeda / ኳስሜዳ

27 Dec, 12:32


👉በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የቦክሲንግ ዴይ ጨዋታዎች ዛሬም ሲቀጥል አርሰናል በሜዳውና በደጋፊው ፊት ኢፕስዊች ታውንን የሚያስተናግድ ይሆናል። አርሰናሎች የዛሬን ጨዋታ ጨምሮ በትንሹ ለስምንት ሳምንታት ያክል የኮከብ ተጨዋቻቸው ቡካዮ ሳካ ግልጋሎትን በጡንቻ መሳሳብ ጉዳት ምክንያት የማያገኙ ይሆናል።

#አርሰናል 🆚 ኢፕስዊች

ምሽት 05:00

🏟 ኤምሬትስ

"መልካም ጨዋታ"

kuasmeda / ኳስሜዳ

27 Dec, 04:38


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
በኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ላይ ክስ የመሰረቱት እነ ሻለቃ ሃይሌ ገ/ስላሴ ለዕርቅ ዝግጁ ነን አሉ….

*… የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ግን ፕሬዝዳንቱ ከውጪ ይምጡና አቋማችንን እናሳውቃለን ብሏል….
በኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ላይ ክስ የመሰረቱት እነ ሻለቃ ሃይሌ ገ/ስላሴ የተፈጠረውን አለመግባባት በዕርቅ ለመጨረስ ከፍርድቤት የቀረበላቸውን ጥያቄ መቀበላቸው ተሰማ።

ትላንት ጉዳኑን የያዘው ችሎት ፊት የቀረቡት ሁለቱ ወገኖች ፍርደ ቤቱ የተፈጠረውን አለመግባባት በዕርቅ እንዲፈቱ ጥያቄ ያቀረበላቸው ሲሆን ከሳሾችና ጠበቆቻቸው በዕርቅ ለመስማማት ፍቃደኛ መሆናቸውን ለችሎቱ ገልጸዋል።

የተከሳሹ የኢትየጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ጠበቆች በበኩላቸው ዕርቁን እንደሚደግፉት ነገር ግን የኦሎምፒክ ኮሚቴው ፕሬዝዳንት ዶ/ር አሸብር
ወ/ጊዮርጊስ ሀገር ውስጥ ስለሌሉ ወደ ሀገር ሲመለሱ ከተወያዩበት በኋላ ውሳኔያቸውን እንደሚያሳውቁ የመደበኛ ፍርድቤቱ የህጋዊ ክርክሩ ሂደት ግን እንዲቀጥል ለችሎቱ መጠየቃቸው ታውቋል።

የኢትዮጵያ ቴኒስና ቦክስ ፌዴሬሽኖች ከሻለቃ ሃይሌ
ገ/ስላሴና አትሌት ገዛኧኝ አበራ ጋር በመሆን በኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ላይ ባቀረቡት ክስ ተላልፎ የነበረው የአመራሮች የጉዞ ዕግድና የኦሎምፒክ ኮሚቴው የአካውንት ዕገዳ ተነስቶ የኦሎምፒክ ኮሚቴው የዕለት ተዕለት ስራ መቀጠሉንም ከታማኝ ምንጭ የተገኘው መረጃ ያስረዳል።

kuasmeda / ኳስሜዳ

26 Dec, 09:35


👉ተወዳጁ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የቦክሲንግ ዴይ ጨዋታዎች ዛሬ የሚጀምሩ ይሆናል። በዛሬው መርሃግብር:

#ማንቸስተር ሲቲ 🆚 ኤቨርተን

09:30 ቀን

🏟 ኤቲሃድ

#ቼልሲ 🆚 ፉልሃም

12:00 አመሻሽ

👉 በተመሳሳይ ሰዓት ሌሎች መረሃግብሮችም የሚደረጉ ይሆናል።

#ዎልቭስ 🆚 ማንቸስተር ዩናይትድ

02:30 ምሽት

#ሊቨርፑል 🆚 ሌሲስተር ሲቲ

05:00 ምሽት

🏟 አንፊልድ

"መልካም ጨዋታ"

kuasmeda / ኳስሜዳ

22 Dec, 09:21


#ታላቁ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ተጠባቂ እና ታላቁን ጨዋታ ይዞ ይቀጥላል። ቀሪ ጨዋታዎች እያሉት ሊጉን በምርጥ አቋም በመምራት ላይ የሚገኘው ሊቨርፑል በሳምንቱ አጋማሽ በካራባኦ ዋንጫ ጨዋታ ማንችስተር ዩናይትድን በሜዳው ገጥሞ አዝናኝ በሆነ ጨዋታ ማሸነፍ የቻለውን ቶተነሃምን ከሜዳው ውጪ ተጉዞ የሚገጥም ይሆናል።

#ቶተነሃም 🆚 ሊቨርፑል

ምሽት 01:30

🏟 ኋይትኸርትሌይን

👉ከዚህ ተጠባቂ ጨዋታ ቀደም ብሎ ሳይጠበቅ በምርጥ አቋም እየገሰገሰ ያለው ቼልሲ ወደ መርሲሳይድ ተጉዞ ኤቨርተንን ይገጥማል በተጨማሪም ሌሎች ጨዋታዎችም በተመሳሳይ ሰዓት በዛሬው መረሃ ግብር ይደረጋሉ።

#ኤቨርተን 🆚 ቼልሲ

🏟 ጉዲሰንፓርክ

#ማንችስተር ዩናይትድ 🆚 ቦርንማውዝ

🏟ኦልድትራፎርድ

#ፉልሃም 🆚 ሳውዝአምፕተን

🏟ክራቨንኮቴጄ

#ሌስተር 🆚 ዎልቭስ

🏟ኪንግፓወር

ከላይ ያሉት ጨዋታዎች ሁሉም በተመሳሳይ ሰዓት 11:00

"መልካም ጨዋታ"

kuasmeda / ኳስሜዳ

22 Dec, 06:00


አርሰናል ከ ክሪስታል ፓላስ ሃይላይት

kuasmeda / ኳስሜዳ

21 Dec, 19:32


👉Arsenal record their biggest win of the season!

kuasmeda / ኳስሜዳ

21 Dec, 15:13


#ማንችስተር ሲቲ ዳግም ሽንፈት አስተናግዷል ጊዜው የሲቲ እና የጋርዲዮላ አይደለም።

kuasmeda / ኳስሜዳ

21 Dec, 11:28


#17ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች ዛሬ ሲደረጉ የሳምንቱን ተጠባቂ ጨዋታ የሚያስመለክተን ይሆናል

👉 በውጤት ቀውስ ውስጥ የሚገኘው የአምናው ሻምፒዮን ማንችስተር ሲቲ ሌላኛውን ከባድ ጨዋታ ዛሬ ከሜዳው ውጪ የሚያደርግ ይሆናል።

#አስቶንቪላ 🆚 ማንቸስተር ሲቲ

09:30 ቀን

🏟 ቪላፓርክ

👉 በሌላ ጨዋታ አርሰናል በካራባኦ ካፕ ጨዋታ በሜዳው ያሸነፈውን ክሪስታል ፓላስን ከሜዳው ውጪ ተጉዞ የሚገጥም ይሆናል።

#ክሪስታልፓላስ 🆚 አርሰናል

02:30 ምሽት

🏟 ሴልሁረስት ፓርክ

👉 በዛሬው 17ኛ ሳምን መረሃግብር ሌሎች ጨዋታዎችም በተሠሳሳይ አመሻሽ 12:00 ሰዓት ላይ የሚደረጉ ይሆናል።

#ብሬንትፎርድ 🆚 ኖቲንግሃም ፎረስት

#ኢፕስዊች 🆚 ኒውካስል

#ዌስትሃም 🆚 ብራይተን


"መልካም ጨዋታ"

kuasmeda / ኳስሜዳ

20 Dec, 12:33


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
“ብዙ ሙከራዎች አድርገን ነው ይሄ ውሳኔ የተወሰነው” “መንግስት ዕገዛ ሊያደርግ ይገባል” አቶ ባህሩ ጥላሁን ፦ የኢ.እ.ፌ ዋና ስራ አስፈፃሚ

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከጥቂት ወራት በፊት ባደረገው ጠቅላላ ጉባዔ ላይ የፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራ ተቋማቸው ካለበት የገንዘብ ዕጥረት አንፃር ውድድሮችን ሊሰርዝ እንደሚችል መናገራቸው ይታወሳል።

በኡጋንዳ አስተናጋጅነት እየተደረገ በሚገኘው የአፍሪካ ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ላይም የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን በገንዝብ ዕጥረት ከውድድሩ ራሱን አግሏል።

ከዚህ ጋር በተያያዘም የፌዴሬሽኑ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ባህሩ ጥላሁን ተከታዩን ብለዋል።

“እንደሚታወቀው የ17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድናችን መሳተፍ አልቻለም። ባለመሳተፋችን እኛም የምንቆጭበት ነው። ምክንያቱም የታዳጊዎች ልማት ላይ ሰራን ካልን እንደዚህ አይነት ውድድሮችን መሰረዝ ከጠቀሜታው ጉዳቱ ያመዝናል የሚል ዕምነት አለን።”

“ቀጣዩም ብሔራዊ ቡድን ውጤታማ ብሔራዊ ቡድን የምንፈልገው እንደዚህ ከታች ጀምሮ በሚደረጉ ውድድሮች እና የልማተ ስራዎች በሚመጣ ውጤት እንደሆነ ይታወቃል።

አቶ ባህሩ ጥላሁን አክለውም በርካታ አማራጮችን ፈልገን ነው በመጨረሻም ለመሰረዝ የተገደድነው ሲሉ በቁጭት ተናግረዋል።

“በነገራችን ላይ የተለያዩ አማራጮችን ፈልገን ነው የ17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድኑን ወድድር የሰረዝነው ፤ ብዙ አማራጮችን ተመልክተናል። የተለያዩ አካላቶችን የመጠየቅ ዕድሉ እና ሌሎች የፋይናንስ አማራጮችን እንደ ፌዴሬሽን ተመልክተን ባለቀ ሰዓት ነው ያንን ውሳኔ የወሰነው ማለት ይቻላል።”

በጣም ብዙ ሙከራዎች አድርገን ነው ይሄ ውሳኔ የተወሰነው ያሉት አቶ ባህሩ ውሳኔውን በጣም የሚያስቆጭ ነው ሲሉ ገልፀውታል።

በተያያዘም በቻን ውድድር ላይ ብሔራዊ ቡድኑ ሱዳንን ረቶ ማለፍ ከቻለ በተመሳሳይ ጉዳይ ያለመሳተፍ ነገር ሊኖር ይችል ይሆን ተብሎ ለተነሳላቸው ጥያቄም ነገሮች የተመቻቹ ባይሆኑም እንኳን ቡድኑ ተሳታፊ እንደሚሆን ማረጋገጫ ሰጥተዋል።

“ይሄን ውድድር ማለፍ በራሱ የሚያመጣቸው ተጨማሪ ጥቅሞች ይኖሩታል። በመንግሥት በኩል ከዚህ በፊት ያለው አቋም እናንተ ለዋና ውድድሮች እለፉ እንጂ መንግስት ድጋፍ ያደርጋል የሚለው ነገር በፊትም ሲሰራበት የነበረ ነው።”

ከዚህ ቀደም በነበሩ የዋና ውድድሮች ተሳትፎ የመንግሥት ዕገዛ እንደነበር በማስታወስም በቀጣይ ቡድኑ ወደ ቻን ስናልፍ የመንግሥትን ድጋፍ እንጠብቃለን ሲሉ ተናግረዋል።

ብሔራዊ ቡድኑን ከመደገፍ አንፃር ከባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ጋር እየተነጋገርን ያለንባቸው ሒደቶች አሉ እነዚህ ነገሮች ወደ መልካም አጋጣሚ የሚቀየሩበት ጊዜ ይመጣሉ የሚል ዕምነት አለን ሲሉም አቶ ባህሩ ጥላሁን ገልፀዋል።

kuasmeda / ኳስሜዳ

19 Dec, 20:33


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
ዋሊያዎቹ ቤንጋዚ ሊቢያ ላይ ከሱዳን ጋር ባለባቸው ጨዋታ የመጀመሪያ ግጥሚያውን በዝግ እንዲካሄድ ጥረት እየተደረገ መሆኑ ተነገረ

ዋሊያዎቹ ቤንጋዚ ሊቢያ ላይ ከሱዳን ጋር ባለባቸው ጨዋታ የመጀመሪያ ግጥሚያውን በዝግ እንዲካሄድ ጥረት እየተደረገ መሆኑ ተነገረ።

ዋሊያዎቹ ከሱዳን ጋር ላለባቸው ጨዋታ ወደ ሊቢያ ቤንጋዚ ከማቅናታቸው በፊት ዛሬ በፌዴሬሽኑ ጽ/ቤት በተሰጠ መግለጫ ላይ ቡድኑ ቤንጋዚ ላይ ባለሜዳ በሚሆንበት ጨዋታ ላይ ሀገሪቱ ሊቢያ በመሆኗኗ በርካታ ሱዳናዊያን በመኖራቸው የሜዳ አድቫንቴጅ እንዳይወሰድ ሲባል ጨዋታው በዝግ እንዲሆን ለካፍ ጠይቀናል ሲሉ ዋና ስራ አስፈጻሚው አቶ ባህሩ ጥላሁን ገልጸዋል።

ቡድኑ ከታህሳስ 3/2017 ጀምሮ ጠንካራ ዝግጅት እያደረገ መቆየቱን የገልጹት የዋሊያዎቹ አሰልጣኝ የወዳጅነት ጨዋታ ባለመኖሩ. ከ20 አመት በታች ቡድን ጋር ተጫውቶ 4ለ1 ያሸነፈ መሆኑና ከአጨዋወት አንንጻር ጥሩ ዝግጅት ማድረጋቸውን ገልጸዋል።

ዋና ስራ አስፈጻሚው እንደተናገሩት የቻን ውድድር ይቀጥል ይቁም የሚል ውይይት ኬንያ ላይ ተደርጎ እንዲቀጥል በመወሰኑና፡ውሳኔው ዘግይቶ የደረሰን በመሆኑ ከዚያ በተጨማሪ የወዳጅነት ጨዋታ ለማድረግ ያልተቻለው በፊፋ ካላንዳር መሰረት የሚካሄድ ውድድር ባለመሆኑ ነው ሲሉ ገልጸዋል።

kuasmeda / ኳስሜዳ

17 Dec, 12:32


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
ያሬድ ከበደ እና ብርሀኑ በቀለ ቅጣት ተላለፈባቸው

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የውድድርና ስነ ስርዓት ኮሚቴ በ12ኛ ሳምንት እና በአንደኛ ሳምንት ተስተካካይ ጨዋታዎች ላይ የቀረቡትን ሪፖርቶች ተመልክቶ የቅጣት ውሳኔዎችን አስተላልፏል።

የሲዳማ ቡናው ብርሀኑ በቀለ ቡድኑ ከሀድያ ሆሳዕና ጋር ባደረገው ጨዋታ የተጋጣሚን ተጫዋች በመማታቱ ምክንያት በቀይ ካርድ ከሜዳ መሰናበቱ ይታወቃል።

በዚህም ተጫዋቹ የአራት ጨዋታዎች እና የሶስት ሺህ ብር የገንዘብ ቅጣት ተጥቶለበታል።

የመቀሌ 70 እንደርታው አጥቂ ያሬድ ብርሀኑ በበኩሉ ቡድኑ በስሁል ሽረ በተረታበት መርሐግብር ከጨዋታው መጠናቀቅ በኋላ የጨዋታውን ዳኛ አፀያፊ ስድብ ሰለመሳደቡ ሪፖርት ቀርቦበታል።

ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋትም ሶስት ጨዋታዎች እንዲታገድ እና ሶስት ሺህ ብር እንዲቀጣ ተወስኖበታል።

በተጨማሪም መቀሌ 70 እንደርታ ስሁል ሽረን በገጠመበት ጨዋታ ላይ የቡድኑ አምስት ተጫዋቾች የቢጫ ካርድ በመመልከታቸው ክለቡ አምስት ሺህ ብር ተቀጥቷል።

በተያያዘም የኢትዮጵያ ቡናው ስራ አስኪያጅ አቶ ገዛኸኝ ወልዴ እና የመቀሌ 70 እንደርታው ዋና አሰልጣኝ ዳንኤል ፀሐዬ ኮሚቴው ሊያነጋግራቸው ጥሪ አድርጎላቸዋል።

kuasmeda / ኳስሜዳ

16 Dec, 04:44


ዩናይትድ ከሲቲ ሃይላይት

kuasmeda / ኳስሜዳ

15 Dec, 18:37


#ተጠባቂው ጨዋታ በዩናይትድ አሸናፊነት ተጠናቀቀ ሲቲ በሜዳው ሽንፈትን በማስተናገድ ይህ ዓመት ዳግም እንደከበደው ታይቷል።

kuasmeda / ኳስሜዳ

01 Dec, 08:34


አርሰናል ከዌስትሃም ሃይላይት

kuasmeda / ኳስሜዳ

01 Dec, 05:06


በ13ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ አርሰናል ከሜዳው ወጪ ተጉዞ በለንደን ደርቢ ጨዋታ በሰፊ ግብ ድል አስመዝግቦ ተመልሷል።

👉 ዛሬ ተጠባቂውን የሊግ ጨዋታ ይዞ ይቀጥላል የወቅቱ ሃያል ክለብ ሊቨርፑል ከፍተኛ የውጤት መዋዠቅ የገጠመውን ማንችስተር ሲቲን በሜዳው የሚያስተናግድ ይሆናል።

#ሊቨርፑል 🆚 ማንቸስተር ሲቲ

🏟 አንፊልድ

ምሽት 01:00

👉 በተጨማሪ ሌሎች ተጠባቂ ጨዋታዎችም በተመሳሳይ ሰዓት ቀደም ብለው ይደረጋሉ።

#ቼልሲ 🆚 አስቶንቪላ

#ማንችስተር ዩናይትድ 🆚 ኤቨርተን

#ቶተነሃም 🆚 ፉልሃም

ቀን 10:30

"መልካም ጨዋታ"

kuasmeda / ኳስሜዳ

27 Nov, 12:13


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
የስምንተኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

1. አለሙ አዛናው (ፋሲል ከነማ-ወጌሻ) ማከሰኞ ህዳር 17 2017 ዓ.ም. ክለባቸው ከወላይታ ድቻ ጋር ባደረገው የ8ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ በ 89 ኛ ደቂቃ ላይ ዳኛን አፀያፊ ስድብ በመሳድብ በቀይ ካርድ ከጨዋታ ሜዳ የተወገዱ ስለመሆኑ ሪፖርት ቀርቦባቸዋል ። ስለሆነም የቡድን አመራሩ ለፈፀሙት ጥፋት በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የውድድር ደንብ ክፍል 1 አንቀፅ 13 ንዑስ አንቀፅ 13.3 ተ.ቁ 18 መሰረት 4 ጨዋታ እንዲታገዱ ና በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 10000 /አስር ሺ/ እንዲከፍሉ የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።

2. ፍቅሩ አለማየሁ (አዳማ ከተማ) እሁድ ህዳር 15 2017 ዓ.ም. ክለቡ ከኢትዮጵያ መድን ጋር ባደረገው የ8ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ በ 22 ኛ ደቂቃ ላይ የተጋጣሚን ተጫዋች በመማታት በቀይ ካርድ ከጨዋታ ሜዳ የተወገደ ስለመሆኑ ሪፖርት ቀርቦበታል ። ስለሆነም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ እ‥ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 3 ምዕራፍ 3 አንቀፅ 63 በተቁ 1 (ሠ) እና በተቁ 2 መሰረት 3 ጨዋታ እንዲታገድ ና በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 3000 /ሶስት ሺ/ እንዲከፍል የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።

3. ዋንጫ ቱት (ኢትዮጵያ መድን ) እሁድ ህዳር 15 2017 ዓ.ም. ክለቡ ከአዳማ ከተማ ጋር ባደረገው የ8ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ በ 22 ኛ ደቂቃ ላይ የተጋጣሚን ተጫዋች በመማታት በቀይ ካርድ ከጨዋታ ሜዳ የተወገደ ስለመሆኑ ሪፖርት ቀርቦበታል ። ስለሆነም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ እፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 3 ምዕራፍ 3 አንቀፅ 63 በተቁ 1 (ሠ) እና በተቁ 2 መሰረት 3 ጨዋታ እንዲታገድ ና በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 3000 /ሶስት ሺ/ እንዲከፍል የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።

ሚሊዮን ሰለሞን (ኢትዮጵያ መድን ) እሁድ ህዳር 15 2017 ዓ.ም. ክለቡ ከአዳማ ከተማ ጋር ባደረገው የ8ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ በ 90+2 ኛ ደቂቃ ላይ ሁለተኛ ቢጫ ካርድ የሚያስጥ ጥፋት በመፈፀሙ በቀይ ካርድ ከጨዋታ ሜዳ የተወገደ ስለመሆኑ ሪፖርት ቀርቦበታል # ስለሆነም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 2 እንቀፅ 35(መ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።

5. ኢትዮጵያ መድን ክለቡ ከአዳማ ከተማ ጋር ባደረገው የ8 ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ የኢትዮጵያ መድን ቡድን ተጫዋች

1. ዋንጫ ቱት በ22ኛው ደቂቃ
2. ሚሊዮን ሰለሞን በ54ኛው ደቂቃ
3. ያሬድ ካሳዬ በ76ኛው ደቂቃ
4. መሃመድ አበራ በ85ኛው ደቂቃ
5. ሚሊዮን ሰለሞን በ90+2ኛው ደቂቃ

በተለያዩ ጥፋቶች ካርድ የተሰጣቸው በመሆኑ በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ መሰረት የገንዘብ ቅጣት ብር 5000 /አምስት ሺ/ እንዲከፍል የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል፡፡

6. ናትናኤል ገ/ጊዮርጊስ (ኢትዮ ኤሌትሪክ) ክለቡ ከመቻል ጋር በነበረው የ8ኛ ሳምንት ግጥሚያ ጨዋታው ተጠናቆ ወደመልበሻ ክፍል በመሄድ ላይ እያለ በኮሪደር ላይ የጨዋታ እና የውድድር አመራሮችን አጸያፊ ስድብ ስለመሳደቡ ሪፖርት ቀርቦበታል ። ስለሆነም ተጫዋቹ በፈጸመው ጥፋት በኢ እፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 3 ምዕራፍ 3 አንቀፅ 66 በተቁ 1 መሠረት 3/ሶስት ጨዋታ እንዲታገድና ብር 3000 /ሶስት ሺህ / እንዲከፍል የውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።

7. አለሙ አዛናው (ፋሲል ከነማ-ወጌሻ) ክለቡ ከወላይታ ድቻ ጋር በነበረው የ8ኛ ሳምንት ግጥሚያ ባጠፉት ጥፋት ቀይ ካርድ በማየት እንዲወጡ ከተደረገ በኋላ ወደመልበሻ ክፍል በመሄድ ላይ እያሉ የጨዋታ አመራሮችን አጸያፊ ስድብ ስለመሳደባቸው ሪፖርት ቀርቦባቸዋል ። ስለሆነም የቡድን አመራሩ ከላይ በተራ ቁጥር 1 ላይ ከተላለፈባቸው ቅጣት በተጨማሪ ለፈጸሙት ሁለተኛው ጥፋት በኢ እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 3 ምዕራፍ 3 አንቀፅ 66 በተቁ 1 መሠረት 3/ ሶስት ጨዋታ እንዲታገዱና ብር 3000 /ሶስት ሺህ / እንዲከፍሉ የውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።

ጥሪ

ለኢትዮ-ኤሌትሪክ የቡድን መሪ የፕሪምየር ሊግ ውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ሊያነጋግሮት ስለሚፈልግ ረቡዕ ህዳር 18 2017 10:30 ስዓት በድሬዳዋ ስታድዮም (ቅድመ ስብሰባ በሚደረግት ቦታ) እንዲገኙ ጥሪውን ያስተላልፋል።

ለአሰልጣኝ በረከት ገብረመድኅን (ስሁል ሽረ – ረዳት አሰልጣኝ) የፕሪምየር ሊግ ውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ሊያነጋግሮት ስለሚፈልግ ረቡዕ ህዳር 18 2017 በ 10፡00 ስዓት በድሬዳዋ ስታድዮም (ቅድመ ስብሰባ በሚደረግት ቦታ) እንዲገኙ ጥሪውን ያስተላልፋል።

kuasmeda / ኳስሜዳ

27 Nov, 12:13


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
ሊግ ኩባንያው በፈረሰኞቹ ክስ ዙሪያ ዛሬ ውሳኔ ይሰጣል….

*….. የኮሚሽነሯ ሪፖርት ይጠበቃል….

አወዛጋቢ የዳኝነት  ውሳኔዎች የታዩበት  የሲዳማ ቡናና የቅዱስ ጊዮርጊስ  የዳኝነት ውሳኔ ዛሬ ይጠበቃል።

በፕሪሚየር ሊጉ  8ኛ ሳምንት  መርሃግብር ባለፈው ሰኞ የሲዳማ ቡናና የቅዱስ ጊዮርጊስ ጨዋታ ተካሂዶ 0 ለ 0 በሆነ አቻ ውጤት  መጠናቀቁ ይታወቃል። በጨዋታው  ሂደት   በ44ኛው  ደቂቃ ላይ  በተገኑ ተሾመ.ላይ  የተሰራው ፋውል ከፍጹም ቅጣት ምት ክልል ውጪ ነው  በማለት   የዕለቱ የመሃል ዳኛ  ኢንተርያሽናል አርቢትር ኤፍሬም ደበሌና  ረዳቱ ፌዴራል ረዳት ዳኛ  ሚፍታ ሁሴን  ውሳኔያቸው ቅጣት ምት መሆኑ አነጋጋሪ ሆኗል።

የቪዲዮ ምስሎች እንደታየው ጥፋቱ የተሰራው የፍጹም ቅጣት ክልል ውስጥ በመሆኑ ተበድለናል በማለት ቅዱስ ጊዮርጊሶች  ለውድድርና ስነርርዓት ኮሚቴ ክስ መስርተዋል።  በእስካሁኑ ሂደት የዳኞቹ ሪፖርት የተላከ ሲሆን የኮሚሽነሯ  ፍቅረ ገነት አስማማው ሪፖርትም ከቆይታ በኋላና ለዎድድና ስነስርዓት ኮሚቴው በመግባቱ ዛሬ የሚደረገው ስብሰባ ላይ ውሳኔ የሚያገኝ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል።

ኮሚሽነሯ ፍቅረገነት የዛሬ አመት ተመሳሳይ ክስተት ገጥሟት በትክክለኛ ሪፖርቷ ፌዴራል አርቢትር ባህሩ ተካ መቀጣቱ ይታወሳል። አሁን ግን በእውነተኛ ሪፖርቷ እውነቱን እንዳይጻፍ ሙከራ ተደርጓል የሚል መረጃ በመውጣቱ ውሳኔው እሰኪታወቅ ጉዳዩ ትኩረት አግኝቷል።

ኮሚሽነሯ እውነተኛ ራፖርት ካቀረበች ከፈረሰኞቹ ክስ ጋር ተያይዞ አርቢትሩና ረዳቱ ሊቀጡ እንደሚችሉ የኮሚሽነሩ ሪፖርት ግን በተቃራኒው ከሆነ አርቢትሮቹ ሳይቀጡ ሊግ ኩባንያውው ኮሚሽነሯ ላይ ርምጃ ይወስዳል ተብሎ ይገመታል።

kuasmeda / ኳስሜዳ

24 Nov, 13:05


ማን ሲቲ ከቶትነሃም ሃይላይት

kuasmeda / ኳስሜዳ

24 Nov, 12:33


#በትናንትናው የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ያልተጠበቀ ውጤትን ያስመለከተን ሊጉ ዛሬም የሚቀጥል ሲሆን።

👉 የሊጉ መሪ ሊቨርፑል ከሜዳው ውጪ ተጉዞ ሳውዛምፕተንን የሚገጥም ይሆናል። ሊቨርፑል ዛሬ ድል ከቀና ሊጉን በ8 ነጥብ ልዩነት የመምራት እድል ይኖረዋል።

ቀን 11:00

👉 ማንችስተር ዩናይትድ በአዲስ አሰልጣኙ እየተመራ የመጀመሪያ የሊግ ጨዋታውን ከሜዳው ውጪ ያደርጋል።

ምሽት 01:30

"መልካም ጨዋታ"

kuasmeda / ኳስሜዳ

23 Nov, 10:01


#የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች ከሃገራት ጨዋታ መልስ ዛሬ የሚመለስ ይሆናል

👉 12ኛ ሳምንት ጨዋታዎች የሚደረጉ ይሆናል
ከሳምንቱ ታላቅ ጨዋታ መካከል አንዱ የሆነው ዛሬ የሚካሄድ ይሆናል

አሰልጣኙ ፔፕ ጋርዲዮላን ለተጨማሪ አንድ አመት ውሉን ያራዘመለት ማንችስተር ሲቲ 🆚 ቶተነሃም የሚጫወት ይሆናል። ከሃገራት ጨዋታ በፊት ለመጀመሪያ ጊዜ በአራት ተከታታይ  ጨዋታዎች ነጥብ የጣለው ማንቸስተር ሲቲ ከባድ ተጋጣሚውን ቶተነሃምን በሜዳውና በደጋፊው ፊት የሚያስተናግድ ይሆናል። በእስከዛሬው የሁለቱ ክለቦች ግጥሚያ ብርቱ ፉክክር የሚታይበት ከመሆኑ አንፃር የዛሬው ጨዋታ ተጠባቂ ያደርገዋል።

ምሽት 02:30

🏟 ኤቲሃድ

👉 በሌላ ጨዋታ የሚኬል አርቴታ አርሰናል 🆚 ኖቲንግሃም ፎረስት ጨዋታውን የሚያደርግ  ይሆናል።

አመሻሽ 12:00

🏟 ኤምሬትስ

#በተመሳሳይ ሰዓት ሌሎች ጨዋታዎችን ፕሪሚየር ሊጉ የሚያስመለክተን ይሆናል።

👉 በቀን መረሃ ግብር ቀደም ብሎ

#ሌስተር ሲቲ 🆚 ቼልሲ

ከቀኑ 09:30

"መልካም ጨዋታ"

kuasmeda / ኳስሜዳ

23 Nov, 00:09


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
በአፍሪካ ደረጃ ሁለተኛ የሆነው የፋስት ትራክ ስልጠና ተጀመረ….

“መንግስትና ህዝቡ ድጋፍ ሳያደርጉ ውጤት ይጠብቃሉ ነገር ግን አዳነ ግርማና ሳላህዲን ሰይድን በድጋሚ መፍጠር አልቻልንም””
ዶ/ር ዳኛቸው ንግሩ
/ የኢት. እግርኳስ ፌዴሬሽን ም/ል ፕሬዝዳንት/

” ኢትዮጵያ በ2029 የአፍሪካ ዋኝጫ ስታዘጋጅ ብሄራዊ ቡድኑን ከሚመሩት አሰልጣኞች መሀል እንድትገኙ እመኝላችኋለሁ”
ኢንስትራክተር አብርሃም መብራቱ

” የፋስት ትራክ ስልጠና ለብዙዎች ጥያቄ ምላሽ የሰጠ በመሆኑ ሁላችሁንም እንኳን ደስ አላችሁ”
አቶ ባህሩ ጥላሁን
/የፌዴሬሽኑ ዋና ስራ አስፈጻሚ/

” ስልጠናውን የምትወስዱት ሰላሳዎቹ አሰልጣኞች እያንዳንዳችሁ የዛሬ አምስት አመት አንድ ተጨዋች ካወጣችሁ እንደ ደሀገር ለውጥ ይመጣል” ሲሉ የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ም/ል ፕሬዝዳንት ተናገሩ።

ዛሬ ጠዋት የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ለ30 አሰልጣኞች ያዘጋጀው ፋስት ትራክ የቢ ላይሰንስ ስልጠና ሲጀመር የፌዴሬሽኑ ምክትል ፕሬዝዳንትና የቴክኒክ ሃላፊ የሆኑት ዶ/ር ዳኛቸው ንግሩ እንደገለጹት ” ይሄ ስልጠና ትልቅ እድል ነው ፌዴሬሽናችን እናንተን ለማገዝ ዝግጁ ነው ይሄ ፋስት ትራክ በትግል የተገኘ እድል በመሆኑና በመሳካቱ ደስ ብሎኛል በርቱ ከተጨዋችነት ወደ አሰልጣኝነት ስትቀየሩ ማንበብና ጽናት ይጠይቃል” ሲሉ መክረዋል።

ዶክተሮ ዳኛቸው እንደተናገሩት ” የዛሬ አምስት አመት ስልጠና የምትወስዱት ሰላሳዎቹ አሰልጣኞች እያንዳንዳችሁ አንድ ተጨዋች ካወጣችሁ እንደ ሀገር ለውጥ ይመጣል ባለፉት አምስት አመታት አንድ አሰልጣኝ አንድ ተጨዋች ማፍራት አልቻልንም ይህን ማድረግ አቅቶን ነው የተቸገርነው ሲሉ ገልጸዋል።

እንደ ምክትል ፕሬዝዳንቱ “መንግስትና ህዝቡ ድጋፍ ሳያደርጉ ውጤት ይጠብቃሉ ነገር ግን አዳነ ግርማና ሳላህዲን ሰይድን በድጋሚ መፍጠር አልቻልንም ለዚህ ነው እናንተ ላይ ትልቅ አደራ ያለው” ሲሉ ሰልጣኞቹን አበረታተዋል።

የፌዴሬሽኑ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ባህሩ ጥላሁን እንደተናገሩት የፋስት ትራክ ስልጠና ለብዙዎች ጥያቄ ምላሽ የሰጠ በመሆኑ ሰላሳችሁንም እንኳን ደስ አላችሁ ማለት እፈልጋለሁ ስልጠናው የግድ በማስፈለጉና ላይሰንስ መያዝ ስላለባችሁ እንጂ የናንተ ልምድ በራሱ በጣም አስፈላጊ ነው ካፍ የፈቀደው ለ25 ሰልጣኞች ቢሆንም ፕሬዝዳንታችን ከካፍ ሰዎች ጋር ተነጋግረው አምስት ኮታ ተጨምሮ ለ30 አሰልጣኞች መፈቀዱ አስደስቶኛል ስኬታማ የስልጠና ጊዜ እኔዲሆን እመኛለሁ” ሲሉ ተናግረዋል።

ስልጠናውን የሚሰጠው የካፍ ኤሊት ኢንስትራክተርነት አብርሃም መብራቱ በበኩሉ ” እናንተን በማሰልጠኔ ደስተኛ ነኝ ወደዚህ ትራክ በመግባታችሁ ደስ ብሎኛል ኢትዮጵያ በ2029 የአፍሪካ ዋኝጫ ስታዘጋጅ ብሄራዊ ቡድኑን ከሚመሩት አሰልጣኞች መሠል እንድትገኙ እመኝላችኋለሁ” ሲል ተናግሯል።

ለስልጠናው ስ ኬት ትልቅ አስተዋጼኦ ያደረጉትን ባለሙያዎች ያመሰገነው ኢንስትራክተር አብርሃም መብራቱ ” ጉልህ ሚና የነነበራቸውን ፕሬዝዳንቱ ኢሳያስ ጅራን አመሰግናለሁ የካፍ የቴክኒክ ዳይሬክተር ከጉዞና ከግል ጥቅም በዘለለ ለልማትና ለስልጠና የሚጥሩ የሁለት ሀገራት ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንቶች የሆኑት የኛው ኢሳያስ ጅራና የላይቤሪያ አቻቸው ሙስጠፋ ራጂ ብቻ ናቸው ብሎ አድንቋል” ሲል ሁለቱን ፕሬዝዳንቶች አሞግሷል።

በስልጠናው ከካሳዬ አራጌ እስከ ኤፍሬም ወንደሰን፣
ከአዳነ ግርማ እስከ ሳላህዲን ሰይድ ፣ ከደጉ ደበበ እስከ ሳምሶን ሙሉጌታ፣ ከዳዊት እስጢፋኖስ እስከ ፍጹም ገ/ማሪያም ፣ ከአስራት መገርሳ እስከ አበባው ቡጣቆ ፣ ከራውዳ አሊ እስከ ኤልመዲን መሃመድ ድረስ በስልጠናው ተሳታፊ ናቸው።

ይሄ ስልጠና በአፍሪካ ደረጃ ከሞሮኮ ቀጥሎ የሚሰጥ መሆኑ ታውቋል።

kuasmeda / ኳስሜዳ

21 Nov, 12:08


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
ፋሲል ተከላካይ አስፈርሟል

የፋሲል ከነማ ስፖርት ክለብ ቦርድ ፕሬዚዳንት እና የጎንደር ከተማ ከንቲባ አቶ ቻላቸው ዳኛው ከቦርድ አባሎች እንዲሁም ከአሰልጣኝ አባላቶች ጋር ጎንደር ላይ ባደረጉት ስብሰባ ላይ ጠንካራ እና ደካማ ጉኖችን የገመገሙ ሲሆን የአፄዎቹን ቡድን ለማጠናከር እና ወደ ተፎካካሪነት ከፍ ለማደረግ ስራዎችን በትኩረት እየሰሩ የሚገኙ ሲሆን ቡድናችን ክፍተት ባሉበት ቦታዎች ሁሉ ማስተካከያ ለማድረግ አሰልጣኝ ውበቱ አባተ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከ20 አመት በታች በቋሚነት ጥሩ እንቅስቃሴ በማድረግ ያሳለፈውን ወጣት ተስፈኛ ተጫዋች ኪሩቤል ዳኘን ከ ኢትዮ ንግድ ባንክ ታዳጊ ቡድን ለሶስት አመት በሚቆይ ውል አስፈርመዋል።

kuasmeda / ኳስሜዳ

19 Nov, 20:07


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
የአትሌቲክሱ አውራ ለመሆን 6 ዕጩዎች ተፋጠዋል…..

*…. የክልልሎችን ውክልናና ድጋፍ ይጠበቃል….
*…. ከበርካታ አመታት በኋላ የተደረገ ምርጫ
ይሆናል….ብቸኛ ዕጩ የለም…..
*….. ከዕጩዎቹ ጀርባ ድጋፍ ሰጪ ሃይል ይጠበቃል..
*….. ለፍልሚያው ስካይ ላይት ተመርጧል…..
በመጪው ታህሳስ ወር የሚካሄደው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ጠቅላላ ጉባኤና ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ገና ከአሁኑ ትኩረት ስቧል።

ከታማኝ ምንጮች በተገኘ መረጃ በእግርኳሱ ምርጫ ላይ ይታይ የነበረውን የምረጡኝ ዘመቻን ለመጀመሪያ ጊዜ በአትሌቲክሱ ላይ ለመከሰት አትሌት ስለሺ ስህን ፣ አትሌት ገ/እግዚአብሄር ገ/ማሪያም ፣ አትሌት መሰረት ደፋር ፣ አትሌት አሰፋ መዝገቡ፣ አቶ ጌታ ዘሩና አቶ ቢኒያም ምሩጽ የረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉ የስልጣን በትርን ለመረከብና የኢትዮጵያ ኩራት የሆነውን አትሌቲክስን ለመምራት ትልቅ ፍጥጫ ላይ መሆናቸው ተሰምቷል።

ባለፉት አራት አመታት ፌዴሬሽኑን የመራችው ረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ያሸነፈችውን ምርጫ ጨምሮ ወደ ኋላ የተካሄዱት ምርጫዎች ውድድር ያልነበረባቸውና ከጀርባ ባሉ አካሄዶች የሚጠናቀቁ ምርጫዎች እንደነበሩ ይታወቃል። የዘንድሮ ግን የምረጡኝ ግብግቦች የሚታዩበት ከመጋረጃ ጀርባ ምክክሮች የሚኖሩባቸው ፖለቲካዊ አመራሮች፣ ባለሀብቶች ፣ ታዋቂ ሰዎች ተጽዕኖ ፈጠሪዎች በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ እጃቸውን የሚያስገቡበት እንደሚሆን ይጠበቃል።

የቶኪዮው የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ሊካሄድ ወራቶች በቀሩበት በአሁኑ ወቅት የሚመረጠው ፕሬዝዳንት ስፖርቱን የማረጋጋት የአትሌቶችን ስነልቦና የሚደግፍ ስራ መስራት ፣ ብሄራዊ ቡድኑን ዳግም መመስረትና የማናጀሮችን እጅ መመለስ ከምንም በላይ በየትኛውም አቅጣጫ የማይጎተት ለአንድ አላማ የቆየ የስራ አስወጻሚ ኮሚቴ ውህደት መፍጠር አትሌቲክሱን ከዘርና ከሃይማኖት ልዩነት ማጽዳት የሚጠበቅበት ሆኗል።

በፓሪስ ኦሎምፒክ የተገኘውን ደካማ ውጤት ተከትሎ እንደ ዋና ችግር ከታዩት ምክንያቶች መሃል ዋናው የብሄራዊ ቡድን መፍረስ ሲሆን ይህን የማስተካከልና ቡድኑን ዳግም የመመለስ የማናጀሮች አሰልጣኞችና የአትሌቶች ባሎች ከፍተኛ ጫና የሚወገድበት ሁኔታን የመፍጠርና አትሌቲክሱን የማዳን ትልቅ ሃይል የሚይዝ ፕሬዝዳንትና ስራ አስፈጻሚ የሚመረጥበት እንዲሆን የመምረጫ ካርዱን የያዙ ተወካዮች ትልቅ ሀገራዊ ሃላፊነት እንደሚሆን የብዙዎችም እምነት ሆኗል።

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ጠቅላላ ጉባኤ በመጪው ታህሳስ ወር በስካይላይት ሆቴል ይካሄዳል ተብሎ ይጠበቃል።

kuasmeda / ኳስሜዳ

13 Nov, 20:04


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ከፍተኛ አመራሮች ላይ ተጥሎ የነበረው የውጪ ጉዞ ዕገዳ ተነሳ

የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ አምስት ከፍተኛ አመራሮች
ላይ ተጥሎ የነበረው የውጪ ጉዞ ዕገዳ በይፋ ተነስቷል።

ጉዳዩን ከያዙት ጠበቆች በተገኘ መረጃ የፌዴሬል ከፍተኛ ፍ/ቤት ከፌዴራል ፖሊስ የቀረበለትን ጥያቄ ተመልክቶ ፕሬዝዳንቱ ዶክተር አሸብር ወ/ጊዮርጊስ ፣ ዋና ጸሃፊው አቶ ዳዊት አስፋውና ምክትላቸው አቶ ገዛኧኝ ወልዴ፣ ሀቃቤ ነዋይዋ ኤደን አሸናፊ እንዲሁም የፓሪስ ኦሎምፒክ የቴክኒክና የህዝብ ግንኙነት ኮሚቴ ሃላፊ አቶ ቢልልኝ መቆያ ላይ የጉዞ ዕገዳ ሲጥል የተከሳሽ ጠበቆች ቅሬታ ያቀርባሉ።

ፍርድ ቤቱ ዶክተር አሸብር የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል በመሆናቸው ያለመከሰስ መብት ያላቸው በመሆኑ እንዲሁም የአፍሪካ ፓርላማ ም/ል አፈጉባኤ መህናቸውን ከግምት አስገብቶ እገዳውን በማንሳት የአራቱን አመራሮች ዕገዳ ማጽናቱ ጉዳዩን የያዙት ጠበቆችን ለፌዴራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ይግባኝ እንዲጠይቁ አድርጓል። ይግባኙ ውሳኔ ሳያገኝ በመሀል ወደ ውጪ ጉዞ ሊያደርጉ ቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ የደረሱ አንድ የኦሎምፒክ ኮሚቴው ከፍተኛ አመራር እንዲመለሱ የተደረጉ መሆኑ ይታወሳል።

ዛሬ የቀረበለትን ይግባኝ የተመለከተው የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በሰጠው ውሳኔ የአምስቱን የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ከፍተኛ አመራሮችን የውጪ ጉዞ እገዳ ሙሉ በሙሉ በማንሳት የከፍተኛ ፍርድ ቤቱን ውሳኔ መሻሩን እስታውቋል።

kuasmeda / ኳስሜዳ

10 Nov, 05:05


#11ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች ዛሬም ሲቀጥሉ የሳምንቱን ተጠባቂ ጨዋታ የሚያስመለክተን ይሆናል

👉 በምርጥ አቋም ላይ የሚገኘው ቼልሲ በሜዳው የውጤት መዋዠቅ የገጠመውን አርሰናልን የሚያስተናግድ ይሆናል። አርቴታ ይህንን ጨዋታ የማሸነፍ ግዴታ ውስጥ ገብቶ የሚያደርገው ጨዋታ ይሆናል ።

ምሽት 1:30

🏟 ስታምፎርድ ብሪጅ

👉 በሌላ ጨዋታ አሰልጣኙ ኤሪክ ቴንሃግ ያሰናበተው ማንቸስተር ዩናይትድ በሜዳው ሌሲስተር ሲቲን የሚያስተናግድ ይሆናል።

አመሻሽ 11:00

🏟 ኦልድትራፎርድ

👉 በተመሳሳይ ሰዓት ሌሎች ቀሪ ጨዋታዎች የሚደረጉ ይሆናል የወሩ ኮከብ ተጨዋችና አሰልጣኝን ያስመረጠው ኖቲንግሃም ከ ኒውካስል እና ቶተነሃም ከ ኤፕስዊች።

"መልካም ጨዋታ"

kuasmeda / ኳስሜዳ

10 Nov, 03:16


👉 ፔፕ ጋርዲዮላ በአሰልጣኝነት ህይወቱ ለመጀመሪያ ጊዜ በሁሉም ውድድሮች 4 ጨዋታዎችን በተከታታይ ሲሸነፍ ክለቡ ማንቸስተር ሲቲ ደግሞ ከነሐሴ 2006 በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በአራት ተከታታይ ጨዋታዎች ሽንፈት አስተናግዷል።

👉 ሊቨርፑል በበኩሉ አስቶንቪላን 2 ለ 0 በመርታት ሊጉን በ5 ነጥብ ልዩነት መምራት የቻለበትን ውጤት ማስመዝገብ ችሏል።

kuasmeda / ኳስሜዳ

09 Nov, 10:04


#11ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች ዛሬ ሲደረጉ በዛሬው እለት ከሚደረጉት ውስጥ ሁለቱም ጨዋታዎች ምሽት የሚደረጉ ይሆናል።

👉 ብራይተን 🆚 ማንቸስተር ሲቲ

ማንችስተር ሲቲ በተላያዩ ውድድሮች ከሶስት ተከታታይ ሽንፈት በኋላ የሚያደርገው ጨዋታ ሲሆን ብራይተን ወቅታዊ አቋሙ እና በሜዳው የሚያደርገው ጨዋታ ከመሆኑ አንፃር ጨዋታው ከወዲሁ ተጠባቂ ያደርገዋል።

ምሽት 02:30

👉 ሊቨርፑል 🆚 አስቶንቪላ

👉 የሊጉ መሪ ሊቨርፑል የቀድሞ አሰልጣኙን ካጣ በኋላ መንገራገጭ ይገጥመዋል ተብሎ ቢታሰብም በተቃራኒው በጥሩ አቋም ሊጉን እየመራ ይገኛል።

አስቶንቪላ ምንም እንኳ የውጤት መዋዠቅ እየገጠመው ያለ ቢሆንም ለሊቨርፑል ቀላል ተጋጣሚ እንደማይሆን ይጠበቃል።

ምሽት 05:00

👉 ሌሎች ጨዋታዎች አመሻሽ 12:00 ላይ ቀደም ብለው የሚደዠረጉ ይሆናል።

"መልካም ጨዋታ"

kuasmeda / ኳስሜዳ

09 Nov, 10:01


#11ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች ዛሬ ሲደረጉ በዛሬው እለት ከሚደረጉት ውስጥ ሁለቱም ጨዋታዎች ምሽት የሚደረጉ ይሆናል።

👉 ብራይተን 🆚 ማንችስተር ሲቲ

ማንችስተር ሲቲ በተላያዩ ውድድሮች ከሶስት ተከታታይ ሽንፈት በኋላ የሚያደርገው ጨዋታ ሲሆን ብራይተን ወቅታዊ አቋም አንፃር እና በሜዳው የሚያደርገው ጨዋታው ከመሆኑ አንፃር ከወዲሁ ተጠባቂ ያደርገዋል።

ምሽት 02:30

👉 ሊቨርፑል 🆚 አስቶንቪላ

👉 የሊጉ መሪ ሊቨርፑል የቀድሞ አሰልጣኙን ካጣ በኋላ መንገራገጭ ይገጥመዋል ተብሎ ቢታሰብም በተቃራኒው በጥሩዠ አቋም ሊጉን እየመራ ይገኛል።

አስቶንቪላ ምንም እንኳ የውጤት መዋዠቅ እየገጠመው ያለ ቢሆንም ለሊቨርፑል ቀላል ተጋጣሚ እንደማይሆን ይጠበቃል።

ምሽት 05:00

👉 ሌሎች ጨዋታዎች አመሻሽ 12:00 ላይ ቀደም ብለው የሚደረጉ ይሆናል።

"መልካም ጨዋታ"

kuasmeda / ኳስሜዳ

09 Nov, 09:10


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
የአ/አ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ :- በከተማው እግርኳስ ፌዴሬሽን ጠቅላላ ጉባኤ ላይ የፍትህና የኦዲት ኮሚቴዎች አያስፈልጉም ማለቱ ከፍተኛ ቁጣ ቀሰቀሰ።

*…. ዋነኞቹ ባለድርሻ የሆኑት ክለቦች ዕጩ ፕሬዝዳንት እንዳያቀርቡ ታግደው ክለብ አልባ ለሆኑት የክፍለ ከተሞች መፈቀዱ ቅሬታ ፈጥሯል…

*…. የጽ/ቤት ሃላፊው ማስጠንቀቂያ ተሰጠው….

የአዲስ አበባ ከተማ እግርኳስ ፌዴሬሽን ጠቅላላ ጉባኤ ስልጣን በሰጠው የደንብ ሰነድ አዘጋጅ ኮሚቴ የስራ ድርሻ ላይ ጣልቃ እየገባ ነው በሚል የአ/አ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ላይ ቅሬታ ቀረበ።

የጠቅላላ ጉባኤው የከተማውን እግርኳስ ዕድገት ላይ ማነቆ በሆኑና በደንቡ ላይ መካተት ያለባቸውን ህጎች አካቶ ለማጸደቅ ጥናት አድርጎ እንዲያቀርብ ስልጣን በሰጠው አካል ላይ ቢሮው ጣልቃ እየገባ አላሰራ ብሏል የሚል ቅሬታ ከተወከለው ኮሚቴ መቅረቡ ተሰምቷል።

ፌዴሬሽኑ ደንብና የምርጫ ሰኘድ ላይ ካልነበሩትና አጠቃላይ እግር ኳስን በሚመሩ አካላት የማይጠፉ የፍትህ አካላት ፣ የኦዲት ኮሚቴና የይግባኝና ግልግል ኮሚቴ የሌለው መሆኑ እግርኳሱ ላይ ከፍተኛ ሚና ያላቸው የተጨዋቾች ፣ የአሰልጣኞች የዳኞችና ኮሚሽነሮች ማህበራት ድምጽ የሌላቸው መሆኑ ሲያነጋግር የነበረ ክፍተት መሆኑ ይታወቃል። የሰነድና አዘጋጅ ኮሚቴው እነኚህንና የጠቅላላ ጉባኤው የተፈጻሚነት ወሰን የሚለውን በሰነዱ ላይ አካቷል።

ነባሩና በ2013 የጸደቀው ደንብ ከዚህም ውጪ በእግርኳስ ፌዴሬሽኑ ውስጥ በሚካሄዱ የትኞቹም ውድድሮች ላይ የማይወዳደሩት ክፍለ ከተሞች ብቻ ለፕሬዝዳንትነት እጩ እንዲያቀርቡ ዋነኛ ባለድርሻ የሆኑትና ክለቦች ግን ስራ አስፈጻሚ እንጂ ዕጩ ፕሬዝዳንትን እንዳይልኩ የከለከለ ሲሆን በአዲሱ ደንብ ላይ ግን ክለቦች ዕጩ ስራ አስፈጻሚም ሆነ ፕሬዝዳንት እንዲልኩ ተደርጎ የተስተካከለ ቢሆንም ከላይ የተጠቀሱትን አዲሶቹ ደንቦችን ቢሮው በማህበራት ማደራጃ ዳይሬክቶሬት በኩል ከደንቡና መመሪያው ሰርዞ የሰነድ አዘጋጁን ልፋት ገደል ከትቷል በሚል ወቀሳ ቀርቦበታል።

የፍትህና የኦዲት ኮሚቴዎች በጠቅላላ ጉባኤው የሚመረጡና ቀጥተኛ ተጠሪነታቸው ለጠቅላላ ጉባኤው ብቻ እንጂ በፌዴሬሽኑ አመራሮች የማይጠየቁና የማይታዘዙ ዋነኛ ኮሚቴ መሆናቸው እየታወቀ ቢሮው አይሆንም ማለቱ እግር ኳሳዊ አመራር ላይ ያሐውን ክፍተት ያሳያል ተብሏል።

ጉዳዩን የሚከታተሉ ባለሙያዎች ግን የቢሮው ጣልቃ ገብነት ህገወጥ መሆኑን በመግለጽ ጠቅላላ ጉባኤ የወከለውን አካልና የግድ በሰነዱ ሊካተቱ ይገባል የተባሉ አንቀጾችን ሰርዞ መላኩ ከብሄራዊ ፌዴሬሽኑ ጋር እንዳያጋጨውና የስፖርቱን ዘርፍ የሚመራው አካልና ማህበራት ማደራጃው የእውቀት ማነስ የሚታይበት መሆኑ ቢሮውን ለትዝብት ይዳርጋል እያሉ ስጋታየውን እየገለጹ ነው። የየክፍለ ከተሞቹ ስራ አስፈጻሚውች ይህን ሴራ ያውቁ ይሆን ..? የሚሉት ባለሙያዎቹ በትውውቅና በውስጥ ለውስጥ አሰራር በየክፍለ ከተማዎቹ የሚወከሉ ሰዎች በትክክል አቅም ያላቸው መሆናቸው መረጃው አላቸው ወይ ..? እንዲልኩ የማይፈቀድላቸው ክፍለ ከተሞችስ ለምን ብለው ይጠይቃሉ..? የአሁኑ ምርጫ ላይ ተወካይ የላኩት ከ3 የማይበልጡ መሆናቸውንስ ይረዱት ይሆን ..? ብለው ጠይቀው በየክፍለ ከተማዎቹ ያሉትን ወጣቶችን ለቅሬታ የሚዳርገውን ሂደት እንዲያስቀለብሱ ዋና ስራ አስፈጻሚዎቹን ጠይቀዋል።

ከወራቶች በፊት ከትውልደ ኢትዮጵያዊያን ጋር ተያይዞ ከከተማው አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ጋር ውዝግብ ውስጥ የነበሩት ቢሮውና የማህበራት ማደራጃው አሁን ከእግርኳስ ፌዴሬሽኑ ጋር አለመግባባት መፍጠራቸው ልዩነቱ ሌላ አቅጣጫ እንዳይይዝ የብዙዎች ስጋት ሆኗል።

በሌላ በኩል ያለ ፌዴሬሽኑ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ዕውቅናና ስልጣን ውጪ በራሱ የግል ውሳኔ የፌዴሬሽኑን ጠቅላላ ጉባኤ ግዮን ሆቴል እንዲደረግ ከሆቴሉ ጋር የተነጋገረው የጽ/ቤት ሃላፊው አቶ አበበ ድረስ ማስጠንቀቂያ ተሰጠው።

የቢሮው ውክልና ያለው የጽ/ቤት ሃላፊው በተደጋጋሚ ጊዜያት የፌዴሬሽኑ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ በማያውቀው ሁኔታ በግሉ እየወሰነ ከስራ አስፈጻሚው የቃል ማስጠንቀቂያ ሲደርሰው እንደነበር ታውቋል። ከሰሞኑ ይህን ድርጊት ቀጥሎበት ጠቅላላ ጉባኤው ህዳር 21 ይደረጋል በማለት ከግዮን ሆቴል ጋር በደብዳቤ ምልልስ ማድረጉ ስራ አስፈጻሚውን ያስቆጣ ሲሆን የጽ/ቤት ሃላፊው ከድርጊቱ እንዲቆጠብ የጀመረውን ግንኙነት እንዲያቆም ያ የማይሆን ከሆነ ለሚደርሰው የህግ ተጠያቂነት ሃላፊነቱ የርሱ መሆኑን በመግለጽ ማስጠንቀቂያ እንደተሰጠው ከታማኝ ምንጭ የተገኘው መረጃ ያስረዳል።

kuasmeda / ኳስሜዳ

08 Nov, 13:09


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
ቢንያም ፍቅሬ የ31 ጊዜ ሻምፒዮኖቹን ተቀላቅሏል

በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ በተለይም ባለፉት ሁለት አመታት በወላይታ ድቻ አስደናቂ እንቅስቃሴን ማሳየት የቻለው ቢንያም ፍቅሬ ቅዱስ ጊዮርጊስን መቀላቀሉ ተረጋግጧል።

ተጫዋቹ በአሰልጣኝ ፋሲል ተካልኝ ለሚሰለጥነው ቅዱስ ጊዮርጊስ ለሁለት ዓመታት ለመጫወት መስማማቱን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

ቢንያም በግብፅ ፕሪሚየር ሊግ ለሚሳተፈው እስማኤልያ ለመፈረም ከቡድኑ ጋር የሙከራ ጊዜ አሳልፎ የነበረ ቢሆንም መዳረሻው የ31 ጊዜ ሻምፒዮኑ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሆኗል።

ተጫዋቹ ባሳለፍነው የውድድር ዘመን ለወላይታ ድቻ በ22 የሊጉ ጨዋታዎች ላይ ተሰልፎ 8 ግቦችን ያስቆጠረ ሲሆን ባሳየው ጥሩ እንቅስቃሴም ለብሔራዊ ቡድን የመጫወት ዕድል ማግኘቱ ይታወቃል።

ተስፈኛው ተጫዋች በውድድር ዓመቱ በአማካይ በጨዋታ 1.17 ግቦችን እያስቆጠረ ለሚገኘው ቅዱስ ጊዮርጊስ የአጥቂ አማራጩን እንደሚያሰፋ ይጠበቃል።

ቅዱስ ጊዮርጊስ በክረምቱ የዝውውር መስኮት በአጥቂ ቦታ ላይ አብዱ ሳሚዮ እና መሀመድ ኮኔን ማስፈረሙም የሚታወስ ነው።

kuasmeda / ኳስሜዳ

07 Nov, 21:08


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
አብዛኞቹ የፕሪሚየር ሊግ ክለቦች አሁንም ደመወዝ እየከፈሉ አይደለም” አቶ ክፍሌ ሰይፈ / የፕሪሚየር ሊግ አክሲዮን ማህበር ዋና ስራ አስኪያጅ”/

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አብዛኞቹ ክለቦች አሁንም ደመወዝ እየከፈሉ አለመሆኑ የክለቦቹ ወርሃዊ ሪፖርት አመለከተ።

የሊግ ኩባንያው ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ክፍሌ ሰይፈ እንደተናገሩት እየቀረበልን ካለው የክለቦቹ ሪፖርት አሁንም አብዛኞቹ ክለቦች ደመወዝ እየከፈሉ አይደለም ሲሉ ተናግረዋል።

አት ክፍሌ ሲያብራሩ ከክለቦቹ የሚጠበቀው ወርሃዊ ሪፖርት ነው ከፍለውም ከሆነ ከፍለናል ካልከፈሉም አልከፈልንም ብለው ሪፖርት ማድረግ የግድ አለባቸው ያንን እያደረጉ ባሉት ክለቦች እንዳየነው አብዛኞቹ ደመወዝ አልከፈሉም ይሄ ለሊጉ ስጋት ነው ሲሉ ገልጸዋል።

እንደ አቶ ክፍሌ ትዝብት በኛ ሀገር እግርኳስ ዋንጫ በወሰደና በወረደው ክለብ መሃል ያለው ልዩነት ገንዘቡ እንጂ እንደ ሀገር ለውጥ የለውም ውጤት በሌለው እግርኳስ ላይ ብዙ ማውራት ያሳፍራል” ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

እየቀረበላቸው ስላለው ጥቆማ የተነገሩት አቶ ክፍሌ
” ወጣት ነን እኛን አይፈልጉም የሚያቋቸውን ብቻ ነው የሚጠቀሙት ኳስ እንችላለን አቅም አለን ለፍተናል ቦታ ግን አጣን ለምን ይሄ አይስተካከልም የሚል ቅሬታ እየመጣልን ነው ወጣቶቹ ቦታ ያጡት ባለው በጥቅም ትስስር ነው ይሄ ደግሞ በገንዘብ በክፍያ የመጣ በመሆኑ መበጠስ አለበት ሲሉ ተናግረዋል።

አቶ ክፍሌ የምስረታ ዘመናቸውን ስናይ በ1940
በ1950 የሆኑ ክለቦች አሉ ያኔ ተመስርተው ተቋማዊ መልክ የሌላቸው ብዙ ክለቦች አይተናል አሁን ድረስ ዘመናዊነት ያልተላበሱ መሆናቸው ያሳዝናል በዚህ ዘመነ
የክለብ ላይሰንሲንግ መጠየቁ ያሳፍራል ሲሉ ተናግረዋል።

ከዲ ኤስ ቲቪ ጋር በተያያዘ እንደገለጹት
ከዲ.ኤስ. ቲቪ ጋር የነበረን ውል ዘንድሮ ይጠናቀቃል ከተስማማን ውል እናድሳለን ካልሆነ ጨረታ እናወጣለን ያም ሆኖ በ2018 ውድድሩ የቴሌቪዥን ስርጭት ያጣል ብለን አንሰጋም ስጋታችን ዲ ኤስ ቲቪ የሚከፈለንን ገንዘብ ያህል ላናገኝ እንችላለን የሚለው ነው ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

kuasmeda / ኳስሜዳ

07 Nov, 13:08


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
የሰባተኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

1. ደስታ ዋሚሾ(ሀዲያ ሆሳዕና) የመታወቂያ ቁጥር EFF-17-0021 ረቡዕ ጥቅምት 27 2017 ዓ.ም. ክለቡ ከድሬደዋ ከተማ ጋር ባደረገው የ7ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ በ 90+9 ኛ ደቂቃ ላይ ሁለተኛ ቢጫ ካርድ የሚያስጥ ጥፋት በመፈፀሙ በቀይ ካርድ ከጨዋታ ሜዳ የተወገደ ስለመሆኑ ሪፖርት ቀርቦበታል ። ስለሆነም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 2 አንቀፅ 35(መ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ የውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።
2. ሀዲያ ሆሳዕና ክለቡ ከድሬደዋ ከተማ ጋር ባደረገው የ7 ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ የሀዲያ ሆሳዕና ቡድን ተጫዋች የሆኑት
1 ሰመረ ሀፍተይ
2 ደስታ ዋሚሾ
3 እዮብ ዓለማየሁ
4 ቃለአብ ውብሸት
5 ካሊድ መሀመድ
6 ዳግም ንጉሴ
7 ኢያሱ ደስታ
8 በረከት ወልደዮሐንስ
9 ደስታ ዋሚሾበተለያዩ ጥፋቶች ካርድ የተሰጣቸው በመሆኑ በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ መሰረት የገንዘብ ቅጣት ብር 5000 /አምስት ሺ/ እንዲከፍል የ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ወስኗል፡፡

kuasmeda / ኳስሜዳ

07 Nov, 11:58


📊ከ4ኛ ዙር የUEFA ቻምፒየንስ ሊግ ጨዋታዎች በኋላ የደረጃ ሰንጠረዡ ይህን ይመስላል።

kuasmeda / ኳስሜዳ

06 Nov, 13:07


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
ኢትዮጵያ ቡና የአጥቂ ስፍራ ተጫዋች አስፈረመ

ኢትዮጵያ ቡና የሞሪታንያ ዜግነት ያለውን ሲዲ ማታላን በአንድ ዓመት ውል ማስፈረሙን ከደቂቃዎች በፊት ይፋ አድርጓል።

በአጥቂ ቦታ ላይ የሚጫወተው ሲዲ ማታላ በሞሪታንያ ፕሪሚየር ሊግ ፤ በሳዑዲ አረቢያ አንደኛ ዲቪዝዮን እና በሊብያ ሊግ ላይ ተጫውቶ አሳልፏል።

በተጨማሪም ለሀገሩ ብሔራዊ ቡድን በአራት ጨዋታዎች ላይ ተሰልፎ አንድ ግብ ማስቆጠሩን የክለቡ መረጃ ያመላክታል።

kuasmeda / ኳስሜዳ

06 Nov, 13:07


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
ሀምበርቾ ዱራሜ ከከፍተኛ ሊግ ውድድር ተሰረዘ

በ23/2/2017ዓ/ም ሀምበርቾ እግር ኳስ ቡድን ከ ወልቂጤ ከተማ እግር ኳስ ቡድን ጋር በነበረዉ _ጨዋታ የሀምበርቾ ኳስ እግር ቡድን በሜዳ ላይ ያለመገኝታቸውን የጨዋታና የውድድር አመራሮች ሪፓርት ቀርቧል፡፡ በዚህም መሠረት፥

ሀ. የጨዋታ ፕሮግራም ወጥቶለት በሰዓቱ ቀርቦ ውድድሩን ያላከናወነው ሀምበርቾ እግር ኳስ ቡድን በ2017 ዓ/ም ለውድድሩ ማስፈጸሚያ በወጣው ደንብ አንቀጽ 5 ተራ ቁጥር 3 እና 5 መሰረት ብር 60,000 (ስልሳሽህ ብር) ቅጣት 26/02/17 ዓ/ም እስከ 03/03/17 ዓ/ም ድረስ ባሉት 7 ቀናት ዉስጥ በቅጣት ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ገቢ እንዲያደርጉ በተሰጠዉ 7ቀን የጊዜ ገደብ ውስጥ ገንዘቡን ገቢ የማያደርጉ ከሆነ በየቀኑ 2% ሁለት በመቶ ቅጣት ተጨምሮ እንዲከፍሉ ተወስኗል፡፡

ለ. ሀምበርቾ እግር ኳስ ቡድን 17/02/2017 እና 23/02/2017 ዓ/ም እንጅባራ እግር ኳስ ቡድን እና ወልቂጤ ከተማ እግር ኳስ ቡድን ጋር በነበረዉ ጨዋታ የሀምበርቾ እግር ኳስ ቡድን 2 (ሁለት) ጊዜ በተከታታይ ወይም በዚያው የውድድር ዓመት በተለያየ ጊዜ በጨዋታ ሜዳ ባለመገኝቱ ፎርፌ በመስጠታቸው በተሻሻለው የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የዲሲፕሊን መመሪያ ምዕራፍ 3 አንቀጽ 69 ተራ ቁጥር 14 መሰረት ከኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ውድድር መሰረዛቸዉን ኮሚቴው ወስኗል፡፡

kuasmeda / ኳስሜዳ

06 Nov, 11:43


#የአውሮፓ ዋንጫ ጨዋታዎች ዛሬም ሲቀጥሉ የእንግሊዙ ክለብ አርሰናል ወደ ጣሊያን ተጉዞ በሳንሴሮ ኢንተርሚላንን የሚገጥም ይሆናል።

ምሽት 05:00

👉 ሌሎች ተጠባቂ ጨዋታዎችም በተመሳሳይ ስዓት የሚደረጉ ይሆናል።

"መልካም ጨዋታ"

kuasmeda / ኳስሜዳ

06 Nov, 08:31


#የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ጨዋታዎች ውጤት ይህን የመስላል በተለይ ማንችስተር ሲቲ ስቶንስ ባስቆጠራት ግብ ሲመራ ቆይቶ በስፖርቲን ሊዝበን የደረሰበት ሽንፈት መነጋገሪያ ሆኗል።

kuasmeda / ኳስሜዳ

05 Nov, 09:14


#የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ጨዋታዎች ዛሬ የሚቀጥሉ ሲሆን ዣቪ አሎንሶ የጀርመኑ ክለብ ሌቨርኩሰንን ይዞ የቀድሞ ክለቡ ሊቨርፑልን የሚገጥም ይሆናል ምሽት 04:00 ሰዓት በአንፊልድ ስታዲየም። ሌሎች ጨዋታዎችም በተመሳሳይ ሰዓት የሚደረጉ ሲሆን የእንግሊዙ ሻምፒዮን ሲቲም ወደ ፖርቹጋል ተጉዞ በሊዝበን ስፖርቲንግ ሊዝበንን የሚገጥም ይሆናል።

"መልካም ጨዋታ"

kuasmeda / ኳስሜዳ

03 Nov, 21:06


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
አማኑኤል ኤርቦ ፈረሰኞቹን ባለ ድል ሲያደርግ የጣና ሞገዶቹ ከጦና ንቦቹ ነጥብ ተጋርተዋል

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የሰባተኛ ሳምንት ጨዋታዎች በዛሬው ዕለት መደረግ ሲጀምሩ ባህርዳር ከተማ እና ወላይታ ድቻ ያለ ግብ ሲለያዩ ቅዱስ ጊዮርጊስ አርባምንጭ ከተማን አሸንፏል።

በዕለቱ ቀዳሚ ጨዋታ ከቀን 10:00 ጀምሮ የተገናኙት ባህርዳር ከተማ እና ወላይታ ድቻ ጨዋታቸውን ያለ ግብ አጠናቀዋል።

ከአሸናፊነት መልስ ወደ እዚህ ጨዋታ የመጡት ሁለቱ ቡድኖች ተከታታይ ድል ለማስመዝገብ ያደረጉት ጥረት ሳይሳካ ቀርቷል።

በጨዋታው የጣና ሞገዶቹ በይበልጥ በኳስ ቁጥጥሩ ተሽለው ዕድሎችን ለመፍጠር ሲጥሩ የጦና ንቦቹ በበኩላቸው በአጭር ቅብብሎች እና ረጃጅም ኳሶች ወደ ፊት ለመድረስ ሞክረዋል።

ውጤቱን ተከትሎም ወላይታ ድቻ ከሶስት አመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ተከታታይ አራት የሊጉ ጨዋታዎችን ሳይሸነፍ መጓዝ ችሏል።

በስምንተኛ ሳምንት ጨዋታዎች ባህርዳር ከተማ ከስሁል ሽረ እንዲሁም ወላይታ ድቻ ከፋሲል ከነማ ይጫወታሉ።

በዕለቱ ሁለተኛ ጨዋታ ቅዱስ ጊዮርጊስ በአማኑኤል ኤርቦ የ83ኛ ደቂቃ ብቸኛ ግብ አርባምንጭ ከተማን 1 – 0 አሸንፏል።

በጨዋታው ፈረሰኞቹ የግብ ዕድሎችን በመፍጠር የተሻሉ የነበሩ ቢሆንም ግብ ለማስቆጠር ግን እስከ 83ኛው ደቂቃ ለመጠበቅ ተገደዋል።

ውጤቱን ተከትሎ ቅዱስ ጊዮርጊስ ነጥቡን 10 ሲያደርስ አርባምንጭ ከተማ በበኩሉ በነበረው 7 ነጥብ ለመቆየት ተገዷል።

በስምንተኛው ሳምንት ጨዋታዎች ቅዱስ ጊዮርጊስ ከሲዳማ ቡና እንዲሁም አርባምንጭ ከተማ ከወልዋሎ አዲግራት ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።

kuasmeda / ኳስሜዳ

03 Nov, 12:01


#በትናንትናው አስረኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ያልተጠበቁ ውጤቶችን ያስመለከተን በዛሬው እለት ሁለት ተጠባቂ ጨዋታዎችን ይዞ ይቀጥላል በተለይ አሰልኙን ኤሪክ ቴንሃግን ያሰናበተው ዩናይትድ በሜዳው ጥሩ አቋም ላይ የሚገኘውን ቼልሲን ምሽት 1:30 ላይ ይገጥማል።

"መልካም ጨዋታ"

kuasmeda / ኳስሜዳ

02 Nov, 13:06


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
በረከት አማረ እና እንየው ካሳሁን የጨዋታዎች ቅጣት ተላለፈባቸው

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የስድስተኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች ይፋ ሲሆኑ ሁለት ተጫዋቾች የጨዋታዎች ዕገዳ ተላልፎባቸዋል።

የወልዋሎ አዲግራቱ አምበል እና ግብ ጠባቂ በረከት አማረ ክለቡ ከኢትዮጵያ መድኅን ጋር ከነበረው ጨዋታ በኋላ የጨዋታውን ዳኛ አፀያፊ ስድብ በመሳደቡ የቀይ ካርድ ተመልክቷል።

በተጨማሪም የሀዋሳ ከተማው እንየው ካሳሁን ክለቡ ከኢትዮ ኤሌክትሪክ ከነበረው ጨዋታ በኋላ የተጋጣሚ ቡድን አባላትን በምልክት አፀያፊ ስድብ ስለመሳደቡ ሪፖርት ቀርቦበታል።

በዚህም ሁለቱም ተጫዋቾች እያንዳንዳቸው የሶስት ጨዋታ እና የሶስት ጨዋታዎች እገዳ ተላልፎባቸዋል።

በረከት አማረ ክለቡ ወልዋሎ አዲግራት ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፣ ከአርባምንጭ ከተማ እና ከፋሲል ከነማ ጋር የሚያደርጋቸው ጨዋታዎች እንዲሁም እንየው ካሳሁን ክለቡ ሀዋሳ ከተማ ከድሬዳዋ ከተማ ፣ ከወላይታ ድቻ እና መቀሌ 70 እንደርታ የሚያደርጋቸው ጨዋታዎች የሚያልፏቸው ይሆናል።

በተያያዘም ባህርዳር ከተማ ፣ ሀድያ ሆሳዕና እና አዳማ ከተማ በሳምንቱ ጨዋታዎቻቸው ላይ አምስት አምስት ተጫዋቾቻው የማስጠንቀቂያ የቢጫ ካርድ በመመልከታቸው እያንዳንዳቸው የ5 ሺህ ብር የገንዘብ ቅጣት ተላልፎባቸዋል።

kuasmeda / ኳስሜዳ

02 Nov, 13:06


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
የወላይታ ድቻ እና ሀድያ ሆሳዕና ደጋፊዎች በ170 የስታድየም ወንበሮች ላይ ጉዳት ማድረሳቸው ተገለጸ

በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የስድስተኛ ሳምንት አራተኛ መርሀግብር ሀድያ ሆሳዕና ከወላይታ ድቻ ተገናኝተው ጨዋታው በወላይታ ድቻ የ1 – 0 አሸናፊነት መጠናቀቁ ይታወቃል።

ከጨዋታው በኋላም የሁለቱም ክለብ ደጋፊዎች በተቀመጡባቸው የስታድየሙ ክፍሎች አካባቢ ያሉ ወንበሮች ላይ ጉዳት ማድረሳቸው ተገልጿል። የወላይታ ድቻ ደጋፊዎች በነበሩት አካባቢ 105 ወንበሮች እንዲሁም የሀድያ ሆሳዕና ደጋፊዎች በነበሩበት ደግሞ 65 ወንበሮችን ስለመነቃቀላቸው ሪፖርት ቀርቧል።

ይህንን ጉዳይ የተመለከተው የሊጉ የዲሲፕሊን ኮሚቴ በሁለቱም ክለቦች ላይ የቅጣት ውሳኔ ያሳለፈ ሲሆን የተነቃቀሉትን ወንበሮች እንዲያሰሩ ወይም የስታድየሙ ባለቤት አሰርቶ የሚያቀርበውን ዋጋ እንዲከፍሉ ተወስኖባቸዋል።

The post የወላይታ ድቻ እና ሀድያ ሆሳዕና ደጋፊዎች በ170 የስታድየም ወንበሮች ላይ ጉዳት ማድረሳቸው ተገለጸ first appeared on ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ.

The post የወላይታ ድቻ እና ሀድያ ሆሳዕና ደጋፊዎች በ170 የስታድየም ወንበሮች ላይ ጉዳት ማድረሳቸው ተገለጸ appeared first on ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ.

kuasmeda / ኳስሜዳ

02 Nov, 08:34


👉 አስረኛ ሳምንተ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የሳምንቱ ታላቅ ጨዋታ ጨምሮ ይዞልን ይቀጥላል።

# በቀን የምሳ ሰዓት ፕሮግራም የሳምንቱ ተጠባቂ ጨዋታ ኒውካስል 🆚 አርሰናል

👉 ይህ ጨዋታ ለሁለቱም ክለቦች እጅግ በጣም ወሳኝ ጨዋታ ሲሆን። አርሰናል ከሊግ መሪዎቹ ለመራቅ ኒውካስል በበኩ ከገባበት የውጤት መዋዠቅ ለመውጣት ሲል የሚያደረገው ጨዋታ በመሆኑ እንዲሁም ከዚህ ቀደም ሁለቱ ክለቦች ባላቸው የእርስ በእርስ ግንኙነት ባላቸው ግንኙነት እና ፉክክር አንፃር እጅ በጣም ተጠባቂ ጨዋታ ነው።


09:30 ቀን

🏟 ሴንትጄምስፓርክ

👉 አርሰናል ከጉዳት ያላገገሙትን የክለቡ እድል ፈጣሪ እና አምሉን ኦዴጋርድን እንዲሁም የአዲስ ፈራሚው ካላፊዮሪን ግልጋሎትን በዛሬው ጨዋታ የማያገኝ ይሆናል።

👉 በሌላ ጨዋታ በዛሬው መረሃግብር አመሻሽ 11:00 ሰዓት የአምናው ሻምፒዮን ማንቸስተር ሲቲ ከሜዳው ውጪ ተጉዞ ቦርንማውዝን ሲገጥም በተመሳሳይ ሰዓት ሌሎች ጨዋታዎች የሚደረጉ ይሆናል።

👉 በዛሬው ቀሪ መረሃግብር ምሽት 01:30 ዎልቭስ 🆚 ክሪስታል ፖላስ የሚጫወቱ ይሆናል።


"መልካም ጨዋታ"

kuasmeda / ኳስሜዳ

27 Oct, 08:29


👉 ዘጠነኛ ሳምንተ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የሳምንቱ ታላቅ ጨዋታ የወቅቱ ሃያል ክለቦችን ሊቨርፑል ከ አርሰናል የሚያገናኝ ይሆናል።

ምሽት 01:30 ሰዓት

🏟 ኤምሬትስ

👉 አርሰናል በጉዳት እና በቅጣት ወሳኝ ተጨዋቾችን በዛሬው ጨዋታ የሚያጣ ሲሆን። በአርነስ ስሎት የሚመራው ሊቨርፑል በወጥ አቋሙ ለመጓዝ የዛሬውን ጨዋታ ለማሸነፍ ወደ ኤምሬትስ የሚያቀና ይሆናል። ከወዲሁ ጨዋታው በብዙ ምክንያቶች ተጠባቂ እንዲሆን ያደርገዋል።

👉 በሌላ ጨዋታ ማንችስተር ዩናይትድ ከሜዳው ውጪ ተጉዞ ዌስትሃምን የሚገጥም ይሆናል

ቀን 11:00 ሰዓት

በተመሳሳይ ሰዓት ቼልሲ በሜዳው ከ ኒውካስል ሲጫወት እንዲሁ ቶተነሃም ከሜዳው ውጪ ክሪስታል ፓላስን የሚገጥም ይሆናል።

"መልካም ጨዋታ"

kuasmeda / ኳስሜዳ

26 Oct, 09:40


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
የክለቦች ክፍያ አስተዳደር ስርዓት መመሪያን ባለመተግበር በአራት ክለቦች ላይ የቅጣት ውሳኔ ተላለፈ።

በክለቦች የክፍያ ስርዓት አስተዳደር መመሪያ መሰረት ክለቦች የየወሩን ጥቅል የደመወዝ ሪፖርት ወር በገባ እስከ 10 ቀን ማሳወቅ እንዳለባቸው ተጠቅሷል።     መመሪያው ከሚያዘው ውጪ የፕሪሚየር ሊጉ አራት ክለቦች ሪፖርት ማድረግ ከነበረባቸው ከ12 እስከ 27 ቀናት በላይ በመቆየት ሪፖርት አድርገዋል።

የፋይናንስ አሰራር ተቆጣጣሪ ኮሚቴ በክለቦች የክፍያ ስርዓት አስተዳደር መመሪያ ቁጥር 01/2016 አንቀፅ 9 መሰረት በአራት ክለቦች ላይ የቅጣት ውሳኔዎችን አስተላልፏል።

በዚህ መሰረትም :-

ሀዋሳ ከተማ ሪፖርት ማድረግ ከነበረበት ከ12 ቀናት በላይ በመዘግየቱ ብር 70,000(ሰባ ሺህ ብር)

አዳማ ከተማ ሪፖርት ማድረግ ከነበረበት ከ23 ቀናት በላይ በመዘግየቱ ብር 180,000(አንድ መቶ ሰማኒያ ሺህ ብር)

አርባምንጭ ከተማ ሪፖርት ማድረግ ከነበረበት ከ24 ቀናት በላይ በመዘግየቱ ብር 190,000(አንድ መቶ ዘጠና ሺህ ብር) እንዲሁም

ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ሪፖርት ማድረግ ከነበረበት ከ27 ቀናት በላይ በመዘግየቱ ብር 220,000(ሁለት መቶ ሃያ ሺህ ብር) ተቀጥተዋል።

kuasmeda / ኳስሜዳ

26 Oct, 09:23


#የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዘጠነኛው ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ የሚደረጉ ይሆናል። 👇


👉 በባለፈው ሳምንት በባከነ ሰዓት ስቶንስ ባስቆጠረው አጨቃጫቂ ግብ ዎልቭስን 2 ለ 1 ያሸነፈው ማንችስተር ሲቲ በሜዳ ሰውዛምፕተንን ሲያስተናግድ። በተመሳሳይ ሰዓት ሌሎች መረሃግሮችም ይኖራሉ።

11:00 ሰዓት

👉 በሌላ ጨዋታ ምሽት 1:30 ኤቨርተን በሜዳው ፉልሃምን ያስተናግዳል።


"መልካም ጨዋታ"

kuasmeda / ኳስሜዳ

24 Oct, 13:39


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በአምስት አመታት ውስጥ ዝቅተኛው የፊፋ ወርሐዊ ደረጃ ተሰጠው

የዓለም አቀፉ የእግርኳስ የበላይ አካል ፊፋ ወርሀዊ የብሔራዊ ቡድኖች የደረጃ ሰንጠረዥን ከደቂቃዎች በፊት ይፋ አድርጓል።

በዚህም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ባለፈው ወር ከነበረበት 145ኛ ደረጃ ሶስት ደረጃዎችን በመቀነስ 148ኛ ላይ ተቀምጧል። ይህም በ2012 ዓመተ ምህረት ተመሳሳይ ወቅት ከነበረበት የ151ኛ ደረጃ በኋላ ዝቅተኛው ሆኖ ተመዝግቧል።

ቡድኑ ከአፍሪካ አስቀድሞ በነበረበት የ43ኛ ደረጃ ቀጥሏል።

ባለፈው ወር 1063 ነጥቦች ተሰጥቶት የነበረው ቡድኑ በዚህ ወር ግን ወደ 1049.28 ዝቅ ብሏል።

በዚህ ወር ከጊኒ ብሔራዊ ቡድን ጋር ባደረጋቸው ሁለት የ2025 አፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታዎች 3 – 0 እና 4 – 1 መሸነፉ የሚታወስ ነው።

kuasmeda / ኳስሜዳ

24 Oct, 13:39


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
መቀሌ 70 እንደርታ ከ ድሬዳዋ ከተማ ቁጥራዊ መረጃዎች

መቀሌ 70 እንደርታ ከድሬዳዋ ከተማ

መቀሌ 70 እንደርታ

አራተኛ የአመት የፕሪሚየር ሊግ ተሳትፎውን በማድረግ ላይ ያለው ቡድኑ ከአራት ጨዋታዎች በኋላ ያስመዘገበው አምስት ነጥብ ከሶስቱ አመታት ዝቅተኛው ነው

በፕሪሚየር ሊጉ አስቀድሞ ግብ ባስቆጠረባቸው ጨዋታዎች ሽንፈት ያስተናገደው አንድ ጊዜ ብቻ ነው(በ2010 የውድድር ዘመን 28ኛ ሳምንት በሲዳማ ቡና 2 – 1)

በሊግ ታሪኩ በ1 – 1 ውጤት ከተለያየባቸው ስድስት ጨዋታዎች ቀጥሎ ባደረጋቸው ጨዋታዎች ሽንፈት ያስተናገደው አንድ ጊዜ ብቻ ነው

በውድድር አመቱ አራት ጨዋታዎችን ካደረጉ ክለቦች መካከል ከኢትዮ ኤሌክትሪክ እና ባህርዳር ከተማ ጋር ዝቅተኛ ግብ ያስቆጠረው ቡድን ነው(3 ግቦች)

በሊጉ ባደረጋቸው የአምስተኛ ሳምንት ሶስት ጨዋታዎች በአንድ አሸንፎ ፣ በአንድ አቻ ሲለያይ በአንዱ ተሸንፏል

በፕሪሚየር ሊጉ ያስቆጠራቸውን የግብ ብዛቶች 100 ለማድረስ 5 ግቦች ይቀሩታል (95 ግቦች)

ድሬዳዋ ከተማ
በፕሪሚየር ሊግ ታሪኩ በመጀመሪያ ሶስት ጨዋታዎች ከፍተኛውን ነጥብ አስመዝግቧል (7 ነጥቦች)

በፕሪሚየር ሊጉ በመጀመሪያ ሶስት ጨዋታዎች ሽንፈት ያላስተናገደው ለመጀመሪያ ጊዜ ነው

የዛሬው ጨዋታ 360ኛ የፕሪሚየር ሊግ ጨዋታው ነው

ባለፉት ስድስት ተከታታይ ጨዋታዎች ላይ ግብ ያስተናገደ ሲሆን ይህም በ2015 የውድድር ዘመን የመጀመሪያ 15 ተከታታይ ጨዋታዎች ላይ ግብ ካስተናገደበት በኋላ ከፍተኛው ነው

ባለፉት ሰባት የውድድር አመታት የዓመቱ አራተኛ ጨዋታዎች በሁለቱ ብቻ ሲያሸንፍ ሁለቱም ጅማ አባጅፋርን ነው

ቻርለስ ሙሴጌ ለድሬደዋ ከተማ በሊጉ 60ኛ ጨዋታውን ያደርጋል

እርስ በርስ
በሊጉ ከዚህ ቀደም በአምስት ጨዋታዎች ተገናኝዋል
መቀሌ 70 እንደርታ በሶስቱ ሲያሸንፍ በሁለቱ ድሬዳዋ ከተማ አሸንፏል
በነዚህ ጨዋታዎች መቀሌ 70 እንደርታ ስድስት ግቦችን ሲያስቆጥር ድሬዳዋ ከተማ አራት ግቦችን አስቆጥሯል
በመጨረሻው የእርስ በርስ ግንኙነተቻው ድሬዳዋ ከተማ 1 – 0 አሸንፏል

kuasmeda / ኳስሜዳ

24 Oct, 09:39


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
አቡበከር ናስር ሱፐር ስፖርት ዩናይትድን በይፋ ተቀላቀለ

አቡበከር ናስር ሱፐር ስፖርት ዩናይትድን በአንድ አመት በሚቆይ ውል መቀላቀሉን ክለቡ ይፋ አድርጓል።

ተጫዋቹ ወደ ማሚሎዲ ሰንዳውንስ ካመራ በኋላ በጉዳት ምክንያት የተጠበቀውን ያህል እንቅስቃሴ ለማድረግ ተቸግሮ ቆይቷል።

ማሚሎዲ ሰንዳውንስም የውጭ ሀገራት ተጫዋቾች ኮታን ከአቡበከር ናስር ውጪ ሙሉ ማድረጉን ተከትሎም የተጫዋቹ ማረፊያው ሌላኛው የደቡብ አፍሪካ ክለብ ሱፐር ስፖርት ዩናይትድ ሆኗል።

አቡበከር በማሚሎዲ ሰንዳውንስ ቆይታው በ18 ጨዋታዎች ላይ ተሰልፎ አራት ግቦችን ማስቆጠሩ ይታወቃል።

የቀድሞው የፊት አጥቂ ተጫዋች ፍቅሩ ተፈራ እ.አ.አ በ2010/11 የውድድር ዘመን በሱፐርስፖርት ዩናይትድ ተጫውቶ አሳልፏል።

የሶስት ጊዜያት የደቡብ አፍሪካ ሊግ ሻምፒዮን የሆነው ሱፐርስፖርት ዩናይትድ በዚህ የውድድር ዘመን ካደረጋቸው አምስት ጨዋታዎች አራት ነጥቦችን ብቻ በመሰብሰብ ከ16 ክለቦች የ13ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።

kuasmeda / ኳስሜዳ

23 Oct, 13:39


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
የዲሲፕሊን ኮሚቴው ለበፀሎት ልዑልሰገድ ፣ አዳነ ግርማ እና ሳምሶን ሙሉጌታ ጥሪ አደረገ

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አራተኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች ከደቂቃዎች በፊት ይፋ ሲደረጉ በፀሎት ልዑልሰገድ ፣ አዳነ ግርማ እና ሳምሶን ሙሉጌታ በዲሲፕሊን ኮሚቴው እንዲቀረቡ ጥሪ ተላልፎላቸዋል።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንኩ ዋና አሰልጣኝ በፀሎት ልዑል ሰገድ ዛሬ 10:00 ላይ በድሬዳዋ ስታድየም እንዲገኝ ሲል የዲሲፕሊን ኮሚቴው አሳውቋል።

እንዲሁም የቅዱስ ጊዮርጊስ ምክትል አሰልጣኝ ሳምሶን ሙሉጌታ እና የቡድን መሪው አዳነ ግርማ ደግሞ በመጪው ቅዳሜ 6:15 ላይ በድሬዳዋ ስታድየም እንዲገኙ ጥሪ ተላልፎላቸዋል።

በተጨማሪም የመቀሌ 70 እንደርታው መድኃኔ ብርሀኔም ዛሬ 10:30 ላይ በተመሳሳይ በድሬዳዋ ስታድየም እንዲገኝ ጥሪ ቀርቦለታል።

በተያያዘም ሀዋሳ ከተማ ፣ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ ወላይታ ድቻ በሳምንቱ ጨዋታዎቻቸው አራት እና ከዛ በላይ የሆኑ ተጫዋቾቻቸው ካርዶችን በመመልከታቸው እያንዳንዳቸው ክለቦች የ5 ሺህ ብር የገንዘብ ቅጣት ተወስኖባቸዋል።

kuasmeda / ኳስሜዳ

23 Oct, 13:39


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
ሽመልስ በቀለ ፣ በረከት ወልዴ እና ኤፍሬም ታምራት የጨዋታ ቅጣት ተላለፈባቸው

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የአራተኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች ይፋ ሲደረጉ በርከት ያሉ የቅጣት ውሳኔዎች ተላልፈዋል።

በተጫዋቾች ባሳለፍነው ዕሁድ ምሽት በተደረገው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ቅዱስ ጊዮርጊስ ጨዋታ ከጨዋታው በኋላ ተጫዋች በመማታት በሚል ኤፍሬም ታምራት እና በረከት ወልዴ የአራት ጨዋታዎች ቅጣት ተበይኖባቸዋል።

ተጫዋቾቹ ከጨዋታ ቅጣቱ በተጨማሪም እያንዳንዳቸው የሶስት ሺህ ብር የገንዘብ ቅጣት ተላልፎባቸዋል።

በዚህም ኤፍሬም ታምራት ክለቡ ከፋሲል ከነማ ፣ ከመቻል ፣ ከወልዋሎ አዲግራት እና ከኢትዮጵያ መድኅን የሚያደጋቸው ጨዋታዎች የሚያልፉት ሲሆን ፤ በረከት ወልዴ በበኩሉ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከኢትዮጵያ መድኅን ፣ ከአርባምንጭ ከተማ ፣ ከሲዳማ ቡና እንዲሁም ከመቻል የሚያደርጋቸው ጨዋታዎች ያልፉታል።

አንጋፋው የመቻል ተጫዋች ሽመልስ በቀለም ቡድኑ ከመቀሌ 70 እንደርታ ነጥብ በተጋራበት ጨዋታ ላይ የጨዋታውን ዳኞች አፀያፊ ስድብ ተሳድበሀል በሚል የሶስት ጨዋታዎች እና የሶስት ሺህ ብር ቅጣት ተበይኖበታል።

በዚህም መቻል ከወልዋሎ አዲግራት ፣ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ከአዳማ ከተማ ጋር የሚያደርጋቸው ጨዋታዎች ላይ የማይሰለፍ ይሆናል።

በተጨማሪም የኢትዮጵያ ቡናው ራምኬል ጀምስ እና የአዳማ ከተማ አድናን ረሻድ በሳምንቱ ጨዋታዎች ላይ የቀይ ካርድ መመልከታቸውን ተከትሎ ከአምስተኛ ሳምንት ጨዋታዎች ታግደዋል።

kuasmeda / ኳስሜዳ

21 Oct, 21:34


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
የጦና ንቦቹ ወደ ድል ሲመለሱ አዳማ ከተማ እና ፋሲል ከነማ አቻ ተለያይተዋል

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የአራተኛ ሳምንት የሶስተኛ ቀን ጨዋታዎች በዛሬው ዕለት ሲደረጉ ወላይታ ድቻ ኢትዮጵያ ቡናን ከመመራት ተነስቶ አሸንፏል።

ከቀን 10:00 ጀምሮ በተደረገው ጨዋታ በግብ ቀዳሚ የነበሩት ቡናማዎቹ ነበሩ። ጨዋታው በተጀመረ 4ኛው ደቂቃ ላይ አንተነህ ተፈራ በኮንኮኒ ሀፍዛ የተሞከረው ኳስ ሲመለስ አግኝቶ ግቡን አስቆጥሯል።

አስቀድመው መሪ የሆኑት ቡናማዎቹ የመጀመሪያውን አጋማሽ በመሪነት ቢያጠናቅቁም ሁለተኛው አጋማሽ ግን ከነርሱ በተቃራኒ ነበር።

በ48ኛው ደቂቃ ላይ ያሬድ ዳሬዛ ከቡድን አጋሩ የተቀበለውን ኳስ በሳጥኑ የግራ አቅጣጫ ይዞ በመግባት ኳስ እና መረብን አገናኝቷል።

ይህ ግብ ከተቆጠረ 18 ደቂቃዎች በኋላ ያሬድ ዳርዛ የጦና ንቦቹን ከመመራት ወደ መሪነት የቀየረ ግብ አስቆጥሯል።

በመጨረሻም በወላይታ ድቻ የ2 – 1 አሸናፊነት ጨዋታው ተጠናቋል።

በአምስተኛው ሳምንት ጨዋታዎች በመጪው ቅዳሜ ጥቅምት 16 ኢትዮጵያ ቡና ከሲዳማ ቡና ሲጫወቱ በተከታዩ ቀን ጥቅምት 17 ወላይታ ድቻ ከስሁል ሽረ ጨዋታቸው ያደርጋሉ።

ምሽት 1:00 ጀምሮ የተደረገው የአዳማ ከተማ እና የፋሲል ከነማ ጨዋታ በ1 – 1 ውጤት ፍፃሜውን አግኝቷል።

በጨዋታው 63ኛ ደቂቃ ላይ ቢንያም አይተን አዳማ ከተማን ቀዳሚ ያደረገ ግብ ከመረብ አሳርፏል። ቢንያም ረጅም ሜትሮችን እየገፋ በመሄድ ግቡን አስቆጥሯል።

መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ሊጠናቀቅ ሶስት ያህል ደቂቃዎች በቀሩበት ጊዜ በረከት ግዛው ኳስ እና መረብን አገናኝቷል።

በመጨረሻም ውጤቱ በ1 – 1 ተጠናቋል። በአምስተኛው ሳምንት ጨዋታዎች በመጪው ሀሙስ ጥቅምት 14 ፋሲል ከነማ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እንዲሁም ጥቅምት 15 አዳማ ከተማ ከሀዋሳ ከተማ ይገናኛሉ።

የሊጉ መርሐግብሮች በነገው ዕለትም ሲቀጥሉ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከባህርዳር ከተማ እንዲሁም ሲዳማ ቡና ከኢትዮጵያ መድኅን ይጫወታሉ።

kuasmeda / ኳስሜዳ

21 Oct, 13:34


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
ካፍ ለአባል ሀገራት እግር ኳስ ፌዴሬሽኖች የሚያከፋፍለውን ዓመታዊ የገንዘብ ድጋፍ አሳደገ

46ኛው የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን ጠቅላላ ጉባዔ በአዲስ አበባ ስካይላይት ሆቴል ከትናንት ጀምሮ በተለያዩ መድረኮች በመካሄድ ላይ ይገኛል።

በትናንትናው ዕለት ስድስቱም የክፍለ አህጉር የዞን ፌዴሬሽኖች ፕሬዚዳንት ዶ/ር ፓትሪስ ሞትሴፔ በተገኙበት ውይይት አድርገዋል።

በውይይቱም ካፍ ለአባል ሀገራት ፌዴሬሽኖች የሚያከፋፍለውን ዓመታዊ የገንዘብ ድጋፍ ከዚህ ቀደም ከነበረው በ150 ሺህ ዶላር ከፍ ማድረጉ ታውቋል።

ከዚህ ቀደም ይሰጥ የነበረው 250 ሺህ ዶላር ሲሆን በአዲሱ ማሻሻያ የአባል ሀገራት እግርኳስ ፌዴሬሽኖች በዓመት 400 ሺህ ዶላር ይከፋፈላሉ።

በተጨማሪም የየክፍለ አህጉሩ የዞን ፌዴሬሽኖችም ከዚህ ቀደም ያገኙት ከነበረው 450 ሺህ ዶላር የ300 ሺህ ዶላር ጭማሪ በማድረግ 750 ሺህ ዶላር እንደሚሰጥ ይፋ አድርጓል።

ካፍ በተለይም በቀጣይ በትኩረት የሚሰራባቸውን ስምንት የሚደርሱ የትኩረት አቅጣጫዎች አያይዞ ይፋ አድርጓል።

ከፌዴሬሽኖች ፣ መንግስታት እና የግል ሴክተር ጋር ያለውን ግንኙነት ማጠናከር ፤ የተሻለ የአስተዳደር ስርዓት እና ተጠያቂነት ፤ ቀጣይነት ያለው ስርዓት መዘርጋት እንዲሁም የቫር አካዳሚዎችን መገንባት ተጠቅሰዋል።

በተጨማሪም በትምህርት እና ስልጠና የአቅም ግንባታ ስራዎችን መስራት ፤ በትምህርት ቤቶች ውድድር ላይ መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ ፤ የእግርኳስ ልማት ስራዎች በገንዘብ መደገፍ እና በሴት አሰልጣኞች ላይ በንቃት ለመስራት ማቀዱን ገልጿል።

kuasmeda / ኳስሜዳ

20 Oct, 21:34


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
ፈረሰኞቹ ንግድ ባንክን ሲረቱ ድሬዳዋ ከተማ እና ስሁል ሽረ ያለመሸነፍ ጉዟቸውን አስቀጥለዋል

በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አራተኛ ሳምንት የሁለተኛ ቀን ጨዋታዎች መካከል ተጠባቂ የነበረው የቅዱስ ጊዮርጊስ እና ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጨዋታ በቅዱስ ጊዮርጊስ የ3 – 2 አሸናፊነት ተጠናቋል።

ምሽት 1:00 ጀምሮ በተደረገው እና በከፍተኛ ትኩረት የተጠበቀው የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ በርካታ ክስተቶችን አስተናግዶ እና 5 ግቦች ተቆጥርውበት ተጠናቋል።

በጨዋታው አስቀድመው በግብ መሪ የሆኑት ፈረሰኞቹ ሲሆኑ ተገኑ ተሾመ በ25ኛው ደቂቃ ላይ ከግራ መስመር የተነሳውን ኳስ ተጠቅሞ ቡድኑን መሪ አድርጓል።

የመጀመሪያው አጋማሽ ሊጠናቀቅ ተቃርቦ በተጨማሪ ደቂቃዎች ላይ ሳለ ግን የአምና ሻምፒዮኖቹ በፍፁም ቅጣት ምት ግብ አስቆጥረዋል። ግቡን ያስቆጠረው የቀድሞው የቅዱስ ጊዮርጊስ ተጫዋች አዲስ ግደይ ነው።

በሁለተኛው አጋማሽ የአሰልጣኝ በፀሎት ልዑልሰገድ ቡድን ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ወደ መሪነት የመጣበትን ግብ በ54ኛ ደቂቃ ላይ አግኝቷል።

ንግድ ባንኮች የቅዱስ ጊዮርጊስ የጨዋታ እንቅስቃሴ በማቋረጥ ያገኙትን ኳስ በፈጣን ቅብብል ያገኘው ኪቲካ በሳጥን ውስጥ ሆኖ ኳስ እና መረብን አገናኝቷል።

የንግድ ባንክ መሪነት ግን ከሶስት ደቂቃዎች በላይ መዝለቅ የቻለ አልነበረም። በ57ኛው ደቂቃ ላይ አማኑኤል ኤርቦ ከፍፁም ጥላሁን የደረሰውን ኳስ ግብ ጠባቂው ፍሬው ጌታሁን በማለፍ ጭምር ኳስ እና መረብን አገናኝቷል።

መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ሊጠናቀቅ ስምንት ያህል ደቂቃዎች በቀሩበት ጊዜ ፈረሰኞቹ ዳግም መሪ እንዲሁም አሸናፊ የሆኑበትን ግብ አስቆጥረዋል። በፈጣን መልሶ ማጥቃት ከራሳቸው የሜዳ ክፍል ተነስተው በተጋጣሚ የሜዳ ክፍል የገቡት ቅዱስ ጊዮርጊሶች በፍፁም ጥላሁን አማካኝነት የጨዋታውን 3ኛ ግብ ከመረብ አሳርፈዋል።

በርካታ ጉሽሚያዎች ከታዩበት የመጨረሻ ደቂቃዎች በኋላም ቅዱስ ጊዮርጊስ በ3 – 2 ውጤት ሶስት ነጥቡን ወስዷል።

በቀጣይ ሳምንት መርሐግብር በመጪው ጥቅምት 14 ሀሙስ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከፋሲል ከነማ እንዲሁም ጥቅምት 16 ቅዳሜ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከኢትዮጵያ መድኅን ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።

ከዚህ ጨዋታ አስቀድሞ ከቀን 10:00 ጀምሮ የተደረገው የስሁል ሽረ እና ድሬዳዋ ከተማ ጨዋታ ባለመሸናነፍ ተጠናቋል።

በ1 – 1 ውጤት ፍፃሜውን ባገኘው ጨዋታ ቻርለስ ሙሴጌ በ21ኛው ደቂቃ ላይ የይታገሱ እንዳለውን ቡድን መሪ አድርጓል።

ቻርለስ ሙሴጌ ግቡንም ተከትሎ በውድድር ዓመቱ ያስቆጠራቸውን የግብ ብዛቶች አራት ማድረስ ችሏል።

በሁለተኛው አጋማሸ 54ኛ ደቂቃ ላይ ደግሞ የስሁል ሽረው ብርሀኑ አዳሙ ግብ አስቆጥሮ ቡድኑን ከጨዋታው አንድ ነጥብ እንዲያሳካ አስችሏል።

በአምስተኛው ሳምንት ጨዋታዎች በመጪው ጥቅምት 14 ሀሙስ ድሬዳዋ ከተማ ከመቀሌ 70 እንደርታ እንዲሁም ጥቅምት 17 እሁድ ስሁል ሽረ ከወላይታ ድቻ ያገናኛሉ።

የሊጉ መርሐግብር በነገው ዕለትም ሲቀጥል 10:00 ላይ ወላይታ ድቻ ከኢትዮጵያ ቡና እንዲሁም ምሽት 1:00 ላይ አዳማ ከተማ ከፋሲል ከነማ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።

kuasmeda / ኳስሜዳ

20 Oct, 21:34


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
አማኑኤል ገብረሚካኤል ወደ ጨዋታ ለመመለስ ተቃርቧል

የፋሲል ከነማው የፊት መስመር ተጫዋች አማኑኤል ገብረሚካኤል ለረጅም ጊዜ ከሜዳ ካራቀው ጉዳት አገግሞ ወደ ጨዋታ ለመመለስ መቃረቡ ተዘግቧል።

ክለቡ በማህበራዊ ትስስር ገፁ ይፋ እንዳደረገው መረጃ ከሆነ ተጫዋቹ በነገው ዕለት ከቡድኑ ጋር ልምምድ ማድረግ ይጀምራል። በ2015 ዓ.ም የዝውውር መስኮት ከቅዱስ ጊዮርጊስ ፋሲል ከነማን የተቀላቀለው አማኑኤል በግሉ ልምምዶችን ሲሰራ ቆይቷል።

አማኑኤል ባሳለፍነው ዓመት የውድድር ዘመን 19ኛ ሳምንት ፤ ፋሲል ከነማ ከኢትዮጵያ ቡና ነጥብ በተጋሩበት ጨዋታ ላይ ጉዳቱን ማስተናገዱ የሚታወስ ነው።

በመቀሌ 70 እንደርታ እና ቅዱስ ጊዮርጊስ የሊጉን ዋንጫ ያሸነፈው አማኑኤል ፋሲል ከነማን ከተቀላቀለ በኋላ በ14 ጨዋታዎች ላይ ተሰልፎ 962 ደቂቃዎች በመጫወት 4 ግቦችን ከመረብ አሳርፏል።

https://i0.wp.com/www.hatricksport.net/wp-content/uploads/2023/05/OMEGA_ADS.jpg?resize=1170%2C214&ssl=1 አማኑኤል ምናልባት በ5ኛው ሳምንት ፋሲል ከነማ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክን በሚገጥምበት አልያም በ6ኛው ሳምንት አርባምንጭ ከተማን በሚገጥምበት ጨዋታ ዳግም በሜዳ ላይ እንደምናየው ይጠበቃል።

The post አማኑኤል ገብረሚካኤል ወደ ጨዋታ ለመመለስ ተቃርቧል first appeared on ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ.

The post አማኑኤል ገብረሚካኤል ወደ ጨዋታ ለመመለስ ተቃርቧል appeared first on ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ.

kuasmeda / ኳስሜዳ

19 Oct, 21:34


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
የጨዋታ ዘገባ | ሀዋሳ ከተማ ድል ሲቀናው መቀሌ 70 እንደርታ ከመቻል ነጥብ ተጋርተዋል

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ከብሔራዊ ቡድን ጨዋታዎች በኋላ በዛሬው ዕለት በአራተኛ ሳምንት ጨዋታዎች ሲመለስ ፤ ሀዋሳ ከተማ ሀድያ ሆሳዕናን 2 – 1 የረታ ሲሆን መቀሌ 70 እንደርታ ከመቻል ነጥብ ተጋርተዋል።

ከቀን 10:00 ጀምሮ በተደረገው የዕለቱ ቀዳሚ ጨዋታ የዘርዓይ ሙሉው ሀዋሳ ከተማ ሀድያ ሆሳዕናን 2 – 1 አሸንፏል።

በጨዋታው ሀዋሳ ከተማ ገና በ8ኛው ደቂቃ ላይ በአቤኔዘር ዮሐንስ በተቆጠረ ግብ መሪ ሆኗል። አቤኔዘር ዮሐንስ ከሳጥኑ የቅርብ ርቀት የተገኘውን የቅጣት ምት በአስገራሚ ሁኔታ በቀጥታ ግብ አድርጎታል።

ሀይቆቹ መሪነታቸውን ከፍ ለማድረግ አራት ደቂቃዎች ብቻ ነበር የፈጁባቸው። ኤርትራዊው አጥቂ ዓሊ ሱሌማን በ12ኛው ደቂቃ ላይ የሀዋሳ ከተማን መሪነት ወደ 2 – 0 አሳድጓል።

አጥቂው ከታፈሰ ሰለሞን በግሩም እይታ የደረሰውን ኳስ በተፈጥሯዊ ጠንካራ እግሩ በቀጥታ ወደ ግብ በመምታት ኳስ እና መረብን አገናኝቷል።

በሁለተኛው አጋማሽ 51ኛው ደቂቃ ላይ ፀጋአብ ግዛው ሀድያ ሆሳዕና ወደ ጨዋታው መመለስ የምትችል ግብ አስቆጥሯል። ከቅጣት ምት ወደ ግብ የተሻገረውን ኳስ የሀዋሳ ከተማ ተጫዋቾች በአግባቡ ለማራቅ በተቸገሩበት ወቅት ፀጋአብ ኳስና መረብን አገናኝቷል።

በመጨረሻም ሀዋሳ ከተማ 2 – 1 በማሸነፍ የውድድር ዓመቱን ሁለተኛ ድል ሲያሰመዘግብ ሀድያ ሆሳዕና ተከታታይ ሽንፈት ያስተናገደበት ሆኗል።

በአራተኛ ሳምንት ጨዋታዎች በመጪው አርብ ጥቅምት 15 ሀዋሳ ከተማ አዳማ ከተማን ሲገጥም ፤ ሀድያ ሆሳዕና በበኩሉ ከሁለት ቀናት በኀላ ጥቅምት 17 ከኢትዮ ኤሌክትሪክ ይጫወታል።

በዕለቱ ሁለተኛ መርሐግብር ከምሽት 1:00 ጀምሮ ጨዋታቸውን ያደረጉት መቀሌ 70 እንደርታና መቻል 1 – 1 በሆነ ውጤት ጨዋታቸውን አጠናቀዋል።

በጨዋታው 37ኛ ደቂቃ ላይ የመቀሌ 70 እንደርታው ያሬድ ብርሀኑ ቡድኑን ቀዳሚ ያደረገ ግብ አስመዝግቧል።

ከማዕዘን የተሻገረውን ኳስ በሌላኛው የቡድን አጋሩ ተገጭቶ ያገኘው ያሬድ ብርሀኑ በግንባር በመግጨት ግቡን አስቆጥሯል።

በሁለተኛው አጋማሽ 51ኛ ደቂቃ ላይ መቻል አቻ የሆነበት ግብ ተመዝግቧል። የመቀሌ 70 እንደርታው ዘረሰናይ ብርሀኑ ከመቻል ተጫዋች በረጅሙ ወደ መቀሌ 70 እንደርታ የግብ ክልል የተሻገረውን ኳስ ለማውጣት ሲጥር ተጨርፎበት በራሱ መረብ ላይ አሳርፎታል።

በመጨረሻም ጨዋታው በ1 – 1 ውጤት ፍፃሜውን አግኝቷል።

በአራተኛ ሳምንት ጨዋታዎች በመጪው ሀሙስ ጥቅምት 14 መቀሌ 70 እንደርታ ከድሬዳዋ ከተማ ሲጫወት ፤ በተከታዩ ቀን ጥቅምት 15 መቻል ከወልዋሎ አዲግራት ጋር ይገናኛል።

የሊጉ መርሐግብር በነገው ዕለትም ሲቀጥል ቀን 10:00 ጀምሮ ስሁል ሽረ ከድሬዳዋ ከተማ እንዲሁም ከምሽት 1:00 ጀምሮ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።

kuasmeda / ኳስሜዳ

19 Oct, 09:33


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
ሀድያ ሆሳዕና ከ ሀዋሳ ከተማ – ቅድመ ጨዋታ ቁጥራዊ መረጃዎች

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ከብሔራዊ ቡድን ጨዋታዎች መልስ በዛሬው ዕለት በአራተኛ ሳምንት ቀዳሚ ጨዋታዎች ወደ ውድድር ይመለሳል።

በድሬዳዋ ስታዲየም በሚቀጥለው የሊጉ ውድድር የግርማ ታደሰው ሀድያ ሆሳዕና ከዘርዓይ ሙሉው ሀዋሳ ከተማ ጋር ጨዋታውን ያደርጋል።

በውድድር ዓመቱ የመጀመሪያ ጨዋታ መቀሌ 70 እንደርታን በማሸነፍ የጀመረው ሀድያ ሆሳዕና በሁለተኛው ሳምንት አራፊ የነበረ ሲሆን ፤ በሶስተኛው ሳምንት በባህርዳር ከተማ የ2 – 0 ሽንፈት አስተናግዷል።

ሀዋሳ ከተማ በበኩሉ በቀዳሚው ጨዋታ በሮዱዋ ደርቢ ሲዳማ ቡናን አሸንፎ ፤ በሁለተኛ ሳምንት ከስሁል ሽረ ጋር በተጨማሪ ደቂቃ በተቆጠረ ግብ ነጥብ ተጋርቷል። ቡድኑ በሶስተኛው ሳምንት የዓመቱን የመጀመሪያ ሽንፈቱን በኢትዮጵያ ቡና በ3 – 1 ውጤት አስተናግዷል።

https://i0.wp.com/www.hatricksport.net/wp-content/uploads/2023/05/OMEGA_ADS.jpg?resize=1170%2C214&ssl=1 ሀድያ ሆሳዕና
ባለፉት ሶስት ተከታታይ ዓመታት የአራተኛ ሳምንት ጨዋታዎች 0 – 0 በሆነ ውጤት ጨዋታዎቹን አጠናቋል

አምና በተመሳሳይ በመጀመሪያው ዙር ባህርዳር ከተማን ከገጠመ በኋላ ነበር ሀዋሳ ከተማ የገጠመው

አሰልጣኝ ግርማ ታደሰ ሀድያ ሆሳዕናን አምና ከዮሐንስ ሳህሌ ከተረከቁ በኋላ በሁሉም ውድድሮች 30ኛ ጨዋታቸው ነው

በጨዋታው የሚያስቆጥሩት ቀዳሚ ግብ በአሰልጣኝ ግርማ ታደሰ ስር የተቆጠረ 30ኛ የክለቡ የሊግ ግብ ይሆናል

ባሳለፍነው ዓመት የአራተኛ ሳምንት ጨዋታ ከሀምበሪቾ ዱራሜ ጋር ያለ ግብ ተለያይተዋል

ካለፉት አስር የሊጉ ጨዋታዎች በአንዱ ጨዋታ ብቻ ነው ግብ ያልተቆጠረባቸው

ቡድኑ ከአንድ የግብ ልዩነት በላይ የተሸነፈው(በባህርዳር ከተማ 2 – 0) ከ2015 የ29ኛ ሳምንት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው

ካለፉት ሁለት የ2 – 0 ሽንፈቶቻቸው በኋላ ባደረጓቸው ጨዋታዎች አሸንፈዋል

ባሳለፍነው የውድድር ዘመን በቅዳሜ ቀን ባደረጋቸው ጨዋታዎች በአንዱም አላሸነፈም

ሀዋሳ ከተማ
በሶስቱም ጨዋታዎች የተለያየ ውጤት ያስመዘገበው ሁለተኛው የሊጉ ቡድን ነው(ሌላኛው መቀሌ 70 እንደርታ)

በአሰልጣኝ ዘርዓይ ሙሉ ስር ያለፉት ሶስት የውድድር ዘመናት እና የዘንድሮው ከሶስት ጨዋታዎች በኋላ የተመዘገቡ ነጥቦች
2014 – 6
2015 – 3
2016 – 5
2017 – 4

ካለፉት ስድስት የውድድር ዘመናት የአራተኛ ሳምንት ጨዋታዎች ማሸነፍ የቻለው በአንዱ ብቻ ነው(በ2015 ወልቂጤ ከተማን 4 – 3)

ቡድኑ ባሳለፍነው የውድድር ዘመን ካደረጋቸው ሰባት የቅዳሜ ቀን ጨዋታዎች ያነሸነፈው በአንድ ብቻ ነው

ባሳለፍነው የውድድር ዘመን በአራተኛ ሳምንት ከኢትዮጵያ መድኅን ነጥብ ተጋርቷል

ካለፉት 25 የሊግ ጨዋታዎች በአንዱ ብቻ ነው ግብ ያላስቆጠረው

ከኢትዮጵያ ቡናው የ3 – 1 ሽንፈት በፊት ለመጨረሻ ጊዜ በተመሳሳይ ውጤት የተሸነፈው በ2014 25ኛ ሳምንት በተመሳሳይ በኢትዮጵያ ቡና ነበር

ቡድኑ አዳማ ከተማን ከመግጠሙ በፊት ባደረጋቸው ጨዋታዎች ለመጨረሻ ጊዜ የተሸነፈው በ2007 የውድድር ዘመን ነበር

አዳማ ከተማን ከመግጠሙ በፊት ባደረጋቸው ያለፉት 16 ጨዋታዎች በ9 አሸንፎ በ7 አቻ ተለያይቷል

እርስ በርስ
ሁለቱ ቡድኖች በሊጉ ለ12ኛ ጊዜ የሚያደጉት ጨዋታ ነው

ሀዋሳ ከተማ በሶስቱ ሲያሸንፍ በሰባት አቻ ተለያይተዋል በአንዱ ብቻ ሀድያ ሆሳዕና አሸንፏል

በነዚህ ጨዋታዎች ሀዋሳ ከተማ 16 ግቦችን ሀድያ ሆሳዕና ደግሞ 13 ግቦችን አስቆጥረዋል

የሀድያ ሆሳዕና ብቸኛ ድል በ2014 የውድድር ዘመን ሁለተኛ ዙር ላይ ነበር(ሀድያ ሆሳዕና 3 – 1 ሀዋሳ ከተማ)

በመጨረሻው ግንኙነታቸው ሀዋሳ ከተማ 2 – 1 ሲያሸንፍ እስራኤል እሸቱ እና ዓሊ ሱሌማን ለሀዋሳ ከተማ እንዲሁም ዳዋ ሆቴሳ ለሀድያ ሆሳዕና ኳስ እና መረብን አገናኝቷል

kuasmeda / ኳስሜዳ

17 Oct, 17:30


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
የዋሊያዎቹ አለቃ ገብረመድህን ሃይሌ በጠንካራ ቃላት የታጀቀ መግለጫ ሰጡ…..

” ብዙ አልናገርም በሁለቱም ጨዋታዎች ተሸንፈናል በጨዋታዎቹ ዙሪያ ጥያቄ ካላችሁ ጠይቁኝ ”

” ለማጋነን ተብሎ 7ለ1 መባል የለበትም ክሬዲት ለማሳጣት እንዳይሆንባችሁ እሰጋለሁ 8 ለ 0 ተሸንፈንም እናውቃለን”

ሽንፈቱን የአለም ፍጻሜ አታድርጉት ጊኒን የገጠምነው ትልቅ ቡድን ይዘን አይደለም የኡትዮጵያ ብሄራዊ ቡድንን ይዘን ነው ” ሲል አሰልጣኝ ገብረመድህን ሃይሌ ተናገረ።

ከጊኒ የደርሶመልስ የ7ለ1 ሽንፈት መልስ ዛሬ መግለጫ የሰጡት አሰልጣኙ ተጠባቂውን መግለጫ የጀመሩት ሁለቱን ጨዋታዎች አይታችኋል ብዬ ስለማመን ብዙ አልናገርም በሁለቱም ጨዋታዎች ተሸንፈናል በጨዋታዎቹ ዙሪያ ጥያቄ ካላችሁ ጠይቁኝ በማለት ለማብራራትም ፍላጎቱ ሳይኖራቸው የተጀመረ መግለጫ ሆየኗል።

የፊታችን ጥቅምት 23/2017 ስለሚጠናቀቀው
ውላተው የተጠየቁት አሰልጣኙ “ውሌ በ23 ይጠናቀቃል ያኔ እለቅላችኋለው ምን እንደሚያስጨንቃችሁ አላውቅም በ2 ጨዋታ 4ለ1 እና 3ለ0 ተሸነፍን እንጂ ለማጋነን ተብሎ 7ለ1 መባል የለበትም ክሬዲት ለማሳጣት እንዳይህንባችሁ እሰጋለሁ 8 ለ0 ተሸንፈንም እናውቃለን ሽንፈት ሲገጥም ከማንም በላይ ነው የምጎዳው ነገር ግን ተጨባጭ አቅማችንን ማወቅ አለብን ጊኒዎች ከ300 በላይ ፕሮፌሽናል ተጨዋቾች አሏቸው ሲገጥሙን የአቅማችን ልዩነት ታይቷል” ሲል ምላሽ ሰጥቷል።

“በአሰልጣኝነት ህይወቴ ረጅም ጊዜ አልቆይም እስካለሁ ድረስ ግን አጨዋወቴን አልለውጥም
እንደ ቡድን ከጠየቃችሁኝ ተጨዋቾቻችን የተለያየ አቋም እያሳዩ መሆኑ ችግር ፈጥሮብናል ብዙዎቹ በአንድ ነገር ላይ መርካት ውስጥ ይገባሉ ሁለት ሶስት ጨዋታ ላይ በነበራቸው ጥሩ አቋም ላይ አይታዩም የፍሬዘርና የያሬድ አቋምም የሚያሳየው ይህንን ነው ከዲሞክራቲክ ኮንጎ ጋር በነበረን ጨዋታ ብዙ ስህተት የሰሩት እነሱ ናቸው” ያሉት አሰልጣኙ ባለሙያ አያስፈልገንም የሚል አቋም የለኝም ግን የስፒድ አሰልጣኝ ብናመጣም የተጫዋቾቻችን ፍጥነት በዚህ እድሜ አይሻሻልም” ሲል አስረድቷል።

” ዲሞክራቲክ ኮንጎን ሴራሊዮንና ጊኒንም የገጠምነው አዲስ አበባ ቢሆን ኖሮ በርግጠኝነነት እናሸንፍ ነበር ብሄራዊ ቡድኑ በሜዳው እንዲጫወት ጥረት ማድረግ አለባችሁ በአየራችንና በደጋፊዎቻችን እንዳንታገዝ አድርጎናል ይሄ ካልተለወጠ ችግር ነው” ሲል የመከረው አሰልጣኝ ገብረመድህን ሃይሌ በርካታ ተጨዋቾችን ቀይሬያለሁ ምክንያቱ ደግሞ ተጨዋቾቼ ወጥ አቋም ስለማያሳዩ ነው በዚያ ላይ ኳስ ሲያገኙ ብቻ ነው የሚጫወቱት ይሄ ልክ አይደለም የኛ ስነልቦና ችግር እንዳለ ሆኖ አንድ ጎል ሲገባ ተጨማሪ ግብ ይገባብናል ይሄ በቀጣይ መታረም ያለበት ይሄ ትልቁ ችግራችን ነው” ብሏል።

kuasmeda / ኳስሜዳ

17 Oct, 13:30


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
“እሱ አያስጨንቅህም አሁን ከአምስት ቀን በኋላ እለቅልሀለሁ” ገብረመድህን ኃይሌ ፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ

“እሱ አያስጨንቅህም አሁን ከአምስት ቀን በኋላ እለቅልሀለሁ”

“ትልቅ ቡድን ይዘን አይደለም ጊኒን የገጠምነው”

“ዲሞክራቲክ ኮንጎ እዚህ ቢመጣ በእርግጠኝነት ነው የምላችሁ ኢትዮጵያ ያሸንፋል”

“የተጋነነ ነገር ያለ አድርጋችሁ አትውሰዱት የአለም መጨረሻ አልያም ፍፃሜ አይደለም”

ገብረመድህን ኃይሌ ፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ

https://i0.wp.com/www.hatricksport.net/wp-content/uploads/2023/05/OMEGA_ADS.jpg?resize=1170%2C214&ssl=1

አሰልጣኝ ገብረመድህን በሰጡት የዛሬው ጋዜጣዊ መግለጫ አስቀድመን ካጋራናችሁ ባለፈም ሌሎች ሀሳቦችን በጥያቄ እና መልስ አብራርተዋል።

የጊኒ ብሔራዊ ቡድን ከባድ ተጋጣሚ ነበር ልዩነታችን በጣም ግልፅ ነው ያሉት አሰልጣኝ ገብረመድህን የተጋነነ ነገር ያለ አድርጋችሁ አትውሰዱት የአለም መጨረሻ አልያም ፍፃሜ አይደለም። የጊኒን ቡድን የገጠምነው ሌላ ትልቅ ቡድን ይዘን አይደለም ብለዋል።

ቡድኑ በርሳቸው ስር ያደረጋቸውን ጨዋታዎች በሙሉ ከሜዳው ውጪ መጫወቱን በማንሳትም የጊኒ ሁለቱም ጨዋታዎች ጊኒ በሜዳው የተጫወተ ነው የሚመስለው በርካታ ደጋፊዎቹን ይዞ ነበር ብለዋል። በቀጣይም ብሄራዊ ቡድኑ ወደ ሀገሩ ተመልሶ ካልተጫወተ ከባድ ይሆናል ያሉት አሰልጣኙ ብሔራዊ ቡድኑ ወደ ሀገሩ ተመልሶ እንዲጫወት ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣም ጠይቀዋል።

በሜዳችን የምናደርጋቸው ጨዋታዎች መኖር በቀጣይም ወጥተን ለምንጫወታቸው ጨዋታዎች ተፅእኖ አላቸው ሲሉም ተናግረዋል።

በምድቡ የሚገኘውን እና በሁለተኛው የምድብ ማጣሪያ ጨዋታ 2 – 0 በሆነ ውጤት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን ያሸነፈው የዲሞክራቲክ ኮንጎ ቡድንን ሀገራችን ላይ ብንገጥመው እናሸንፈው ነበር የሚል ሀሳብ አሰልጣኙ ተናግረዋል።

“እዚህ ቢመጣ ዲሞክራቲክ ኮንጎ በእርግጠኝነት ነው የምላችሁ ኢትዮጵያ ያሸንፋል። ምንም ጥርጥር የለውም በብዙ ነገር ማለት ነው።ሴራ ሊዮንን ብታዩ እዚህ ቢመጣ ምን ያህል ተከናንቦ እንደሚሄድ ግልፅ ነው። ስለዚህ ጊኒም ቢመጣ እዚሁ ይሸነፋል። እዛ ሊያሸንፈን ይችላል ግን ይሸነፋል።”

ከቆይታቸው ጋር በተያያዘ ለቀረበላቸው ጥያቄም ተከታዩን መልሰ ሰጥተዋል። “እሱ አያስጨንቅም አሁን ከአምስት ቀን በኋላ እለቅልሀለሁ ፤ ችግር የለውም ውሉ ሲያልቅ ይጠናቀቃል። ውሉ በ23 ነው የሚያልቀው ለምን እንደሚያስጨንቃችሁ አይገባኝም እኔ” ሲሉ መልስ ሰጥተዋል።

ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ተጫዋቾችን አምጥተን ለብሄራዊ ቡድን ማጫወት አለብን ያሉት አሰልጣኙ የኮሞሮስ ብሔራዊ ቡድንን እንደ ምሳሌ በማንሳት እነዚህ ተጫዋቾች ማጫወት ከቻልን ሀገር ውስጥ ላሉ ተጫዋቾችም ብዙ ነገር ያስተምራሉ ሲሉ ሀሳባቸውን ሰጥተዋል።

The post “እሱ አያስጨንቅህም አሁን ከአምስት ቀን በኋላ እለቅልሀለሁ” ገብረመድህን ኃይሌ ፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ first appeared on ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ.

The post “እሱ አያስጨንቅህም አሁን ከአምስት ቀን በኋላ እለቅልሀለሁ” ገብረመድህን ኃይሌ ፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ appeared first on ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ.

kuasmeda / ኳስሜዳ

17 Oct, 13:30


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
“አጨዋዋታችን ስህተት ስለነበረ አይደለም የተሸነፍነው” ገብረመድህን ኃይሌ ፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ

“አጨዋዋታችን ስህተት ስለነበረ አይደለም የተሸነፍነው”

“የኛ ተጫዋቾች ኳስ ሲያገኙ ነው የሚጫወቱት ሲያጡ አይጫወቱም”

“የአቅማችን ልዩነት ጎልቶ ታይቷል”

“አቋሜን አልቀይርም አሁንም ወደ ፊትም ቀጥተኛ አጨዋወት ነው የምጫወተው”

“ረጅም ጊዜ አልቆይም በስልጠናው ላይ”

ገብረመድህን ኃይሌ ፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ገብረመድህን ሀይሌ ሁለቱን የጊኒ ጨዋታዎች አስመልክቶ የድህረ ጨዋታ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።

አሰልጣኙ የጊኒ ብሔራዊ ቡድን በቀዳሚ ሁለት ጨዋታዎች(ከታንዛኒያ እና ዲሞክራቲክ ኮንጎ) ከነበረው ተቀይሮ መምጣቱን የገለፁ ሲሆን በጉዳትና በተለያዩ ምክንያቶች ያልነበሩ ተጫዋቾችን መልሰው ማግኘተቻው ተናግረዋል። በዚህም ልዩነት ፈጣሪ ተጫዋቾችን በማግኘተቻው ተጠቃሚ እንዳደረጋቸው አንስተዋል።

ቡድናቸው የስነ ልቦና ችግር እንዳለበት ያነሱት አሰልጣኙ አንድ ጎል ሲገባ ሌላ ጎል በቀላሉ የማስተናገድ ችግሮች ነበሩ ብለዋል።

በተለይም በሁለተኛው ጨዋታ ጋር ተያይዞ ባነሱት ሀሳብ በመጀመሪያው አጋማሽ 3 – 0 ተመርተው አጋማሹን ቢፈፅሙም በሁለተኛው አጋማሽ ግን በተሻለ ለማጥቃት መጣራቸውን እና የጊኒ ቡድን ጥቅጥቅ ብሎ በመጫወቱ አስከፍተው ዕድል ለመፍጠር መቸገራቸውን ጠቁመዋል።

ስለ ቡድኑ ውጤት በተመለከተ ከማንም በላይ የማዝነው እኔ ነኝ ሲሉ ተናግረዋል። “ኢትዮጵያ ስትሸነፍ ከማንም በላይ ነው የምቆረቆረው ፤ ተዋናይ ስለሆንኩን ማለት ነው። ከማንም በላይ እጎዳለሁ ፤ ስሜቱም በጣም ከፍተኛ ነው የሚሆነው።”

ያለን ወቅታዊ እና ተጨባጭ ሁኔታ መገንዘብ ያስፈልጋል ያሉት አሰልጣኝ ገብረመድህን ከቅርበት እና ርቀት ሲታይ አንድ አይደለም ግልፅ የአቅም ልዩነት አለ ብለዋል።

ለአብነት ያህልም የፍጥነት እና የጨዋታ ግንዛቤን በማንሳት ቡድኑ ከተጋጣሚያቸው ያነሰ መሆኑን በመግለፅ በተለይም ከኳስ ውጪ በሚደረግ እንቅስቃሴ ያለብን ችግር በጣም ከፍተኛ ነው ሲሉ ተናግረዋል።

በቀጣይም በደንብ ሊሰራበት ይገባል ባሉት ከኳስ ውጪ ያለ እንቅስቃሴ ደጋግሜ ለተጫዋቾቹ ነግሬያቸዋለሁ የኛ ተጫዋቾች ኳስ ሲያገኙ ነው የሚጫወቱት ሲያጡ አይጫወቱም ብለዋል።

አሰልጣኝ ባለፉት ሶስት ተከታታይ ጨዋታዎች ላይ የተጠቀሙትን እና በአራተኛው ጨዋታ ስለቀየሩት የፍሬዘር ካሳ እና የያሬድ ባየህ የመሀል ተከላካይ ጥምረት ተከታዩን ብለዋል።

“ፍሬዘር እና ያሬድ አንድ ላይ ተጣምረው በአንድ ተጣምረው የተጫወተለበት በአንድ ጨዋታ ላይ በጣም ጥሩ ነበሩ።በጣም ደስተኛ ነበርን። ከዛ በሁለተኛ ቀን ደግሞ ሙሉ ለሙሉ ሁለቱም ጥሩ አልነበሩም። ተጫዋቾቻችን በየጨዋታው የተለያየ አቋም ማሳየት ትንሽ ችግር ፈጥሮብናል። በዚህ ላይ የስነ ልቦና ድጋፍ ያስፈልጋቸዋል በአንድ ነገር ቶሎ የመርካት ነገር ይታይባቸዋል። ብዙዎቹ ማለት ነው።”

“የፍሬዘር እና ያሬድ የመጀመሪያ ጨዋታ በጣም ጥሩ ነበር። በሁለተኛው ጨዋታም ሁለቱም እነሱ ነበሩ የመጡት ፤ ግን ደግሞ ብዙ ስህተት የሰሩት እነሱ ናቸው።”

ከአጨዋወት ጋር በተያያዘ ለተነሳላቸው ጥያቄም “አቋሜን አልቀይርም አሁንም ወደ ፊትም ቀጥተኛ አጨዋወት ነው የምጫወተው ፤ ከዚህ በኋላ ምን ያህል ጊዜ ሊኖረኝ ይችላል ? ባለኝ አጭር ጊዜም ቢሆን ማለት ነው ፤ ረጅም ጊዜ አልቆይም በስልጠናው ላይ ማለት ነው ፤ እኔ ባመንኩበት ነው የምቀጥለው።”

አጨዋወታችን ስህተት ስለነበረ አይደለም በግልጽ ልዩነት ስላለን ነው የተሸነፍነው ሲሉ አሰልጣኝ ገብረመድህን ሀይሌ ተናግረዋል።

kuasmeda / ኳስሜዳ

16 Oct, 21:30


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
“ከመቀሌ ጋር ስንጫወት የፊፋን እና የሊግ አክስዮን ማህበሩን ህግ የሚጋጭ ነው” “ጊፍት ፍሬድ የጡንቻ ጉዳት አጋጥሞታል” ፋሲል ተካልኝ ፦ የቅዱስ ጊዮርጊስ ክለብ ዋና አሰልጣኝ

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ በብሔራዊ ቡድን ጨዋታዎች ምክንያት ከተቋረጠ በኋላ በመጪው ቅዳሜ በአራተኛ ሳምንት ጨዋታዎች ይመለሳል።

በሳምንቱ ከሚደረጉት ጨዋታዎች መካከል ዕሁድ የሚደረገው የቅዱስ ጊዮርጊስ እና ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጨዋታ ተጠባቂ ነው።

ቢሾፍቱ በሚገኘው የይድነቃቸው ተሰማ አካዳሚ ልምምዱን በማድረግ ላይ የሚገኘው የቅዱስ ጊዮርጊስ ክለብ ዋና አሰልጣኝ የሆኑት አሰልጣኝ ፋሲል ተካልኝ ከክለቡ የሬድዮ ፕሮግራም ጋር ስለነበራቸው የዝግጅት ጊዜ እና ተያያዥ ጉዳዮች ሀሳባቸውን ሰጥተዋል።

“የተወሰነ እረፍት ከወሰድን በኋላ አዳዲስ ተጫዋቾች ከቡድኑ ጋር የማዋሀድ እና ባለፉት ጨዋታዎች ላይ የታዩ ደካማ ጎኖች የማሻሻል ፤ በአካልም በአዕምሮ ተጫዋቾች የማዘጋጀት ስራዎች ሰርተናል” ሲሉ አሰልጣኝ ፋሲል ተካልኝ ተናግረዋል።

አሰልጣኙ የቡድናቸውን አቅም ከፍ ያደርጋሉ ብለው ስለሚያስቧቸው እና ከውጪ ሀገራት ስለፈረሙት ተጫዋቾች መረጃ ሲሰጡም ፤ የኮትዲቯራዊው አጥቂ መሀመድ ኮኔ የወረቀት ስራዎች አለመጠናቀቁን ገልፀዋል።

“አንደኛው አጥቂያችን ኮኔ ዘግይቶ ቢሆንም የገባው ሶስቱም ተጫዋቾች በነበረው የእረፍት ጊዜ ከኛ ጋር ዝግጅታቸውን አድርገዋል።ከቡድኑ ጋር ለማዋሀድ እየሞከርን ነው። ኮኔ ከመኖሪያ ፈቃድ ጋር በተያያዘ አስተዳደራዊ ጉዳዩ አላለቀም። ምናልባት በዚህ ሁለት ቀናት ውስጥ ተጠናቆ ከኛ ጋር ወደ ድሬዳዋ እንደሚያመራ እጠብቃለሁ።”

ቅዱስ ጊዮርጊስ በሊጉ ካደረጋቸው ሶስት ጨዋታዎች ወልዋሎ አዲግራትን ሲያሸንፍ በፋሲል ከነማ እና መቀሌ 70 እንደርታ ሽንፈቶችን አስተናግዷል። አሰልጣኝ ፋሲል የተጫዋቾቻቸው ስነ ልቦና ላይ ክፍተቶች መኖራቸውን በማንሳት ይህንን ለማስተካከልም ጠንካራ ስራዎች በመስራት ላይ እንደሚገኙም ጠቁመዋል።

“ተጫዋቾችን በየጊዜው በአካል ብቃትም በአዕምሮም ለማዘጋጀት እንጥራለን። ወጣቶች ከመሆናቸው ጋር ተያይዞ የሚገጥሙንን ችግሮች በንግግር እና በስራ ለመፍታት እየሞከርን ነው።”

“አንዳንድ ጊዜ በሜዳ ላይ ያሰብነው ነገር ሳይሳካ ሲቀር በቀላሉ የመሰበር የመደንገጥ ነገር በተጫዋቾቻችን ላይ አለ። ይሄ እንግዲህ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ታላቅነት እና ካለው ሀላፊነት ጋር ተያይዞ እሱን የመሸከም አቅም ነው።እንግዲህ በሂደት ይቀረፋል ብለን እናስባለን። ከዚህ ውጪ ተጫዋቾቹ ለመስራት ለማሸነፍ የሚጠበቅባቸውን ለማድረግ ያላቸው ጉጉት ከፍተኛ ነው።”

ቡድኑ በሶስተኛው ሳምንት ከመቀሌ 70 እንደርታ ጨዋታ ያደረጉበት ሰዓት ላይ ቅሬታ እንዳላቸው ያነሱት አሰልጣኙ ጉዳዩን አስቀደምውም ለሚመለከተው አካል በማሳወቅ መጠየቃቸውን ገልፀዋል።

“ከመቀሌ ጋር ስንጫወት የፊፋን እና የሊግ አክስዮን ማህበሩን ህግ የሚጋጭ ነው። አንድ ቡድን ከ72 ሰአታት በኋላ ነው መጫወት ያለበት ይላል ህጉ እኛ ደግሞ ስንጫወት 69 ሰዓት ነው።”

ከጨዋታዉ አስቀድሞ ቀርበው መጠየቃቸውን እና ማስረዳታቸውን ያነሱት አሰልጣኝ ፋሲል በነበረው ጠባብ ጊዜ ጨዋታውን ማድረጋቸው ለሽንፈቱ ዋነኛ ምክንያት እሱ ነው ባይባልም ተፅዕኖ ግን አልነበረውም ማለት አይቻልም ብለዋል።

ከመቼውም ጊዜ የበለጠ የክለቡ አባላቶች ደጋፊውን ይፈልጋሉ ያሉት አሰልጣኝ ፋሲል ደጋፊው በቀጣይ ጨዋታዎች ላይ ቡድኑን እንዲያበረታታ ጥሪ አቅርበዋል።

በቀጣይ ሶስት ጨዋታዎች ላይ ከአራት እስከ አምስት ቀናት ልዩነቶች አሉ ስለዚህ እነዚህን ሶስት ጨዋታዎች እየተመላለስን ነው የምንጫወተው።

አርብ ልምምዳችንን ከሰራን በኋላ ቅዳሜ ወደ ድሬዳዋ በማቅናት በጨዋታው ማግስት ሰኞ እንመለሳለንም ብለዋል።

ቅዱስ ጊዮርጊስ በሊጉ አራተኛ ሳምንት መርሐግብር በመጪው ዕሁድ ምሽት 1:00 ጀምሮ በድሬዳዋ ስታድየም ጨዋታውን ያደርጋል።

kuasmeda / ኳስሜዳ

16 Oct, 17:29


ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
አሰልጣኝ ስዩም ከበደ ይቅርታ ጠየቀ…..

“እንኳን ቡድኔ ውስጥ ከ20 አመት ሊግ ውስጥ ከ20 አመት በታች ተጨዋቾች የሉም”

“ከሀገሪቱ ምርጥ ሶስት አሰልጣኞች መሃል አንዱ እኔ ነኝ ሁለቱን ብትጠሩም አለሁበት ”

“በእድሜ ትልቅነት የሚገመቱና የሚጠረጠሩ ተጨዋቾች በሙሉ ፓስፖርታቸው ያጫውታቸዋል”

ከ20 አመት በታች ውድድር ሳይሆን የቻን ውድድር በሚመስለው ሻምፒዮና ላይ ለተመዘገበው ደካማ ውጤት ሰፊውን የኢትዮጵያ ህዝብን ይቅርታ እጠይቃለሁ” ሲሉ አሰልጣኝ ስዩም ከበደ ተናገሩ።

በታንዛኒያ ሲካሄድ በነበረው የሴካፋ ከ20 አመት በታች ሻምፒዮና ላይ ደካማ ውጤት ያስመዘገበው ቡድን ዙሪያ ዛሬ መግለጫ የሰጡት አሰልጣኙ” ውድድሩን ካየነው የ20 አመት በታች ሳይሆን የቻን የአፍሪካ ዋንጫ ይመስል ነበር ሁሉም ሀገራት በሚያስብል ደረጃ 20 አመት ተብሎ በትክክለኛ መንገድ የመጡ አይደለም” ሲሉ ቡድናቸውን ተከለክለዋል።

አሰልጣኝ ስዩም “ድክመት ቢኖርም አንገት የሚያስደፋ እንቅስቃቃሴ አላሳየንም
ቦክስ ላይ ተወዳዳሪው ሲቀጠቀጥጥ ፎጣ እንደሚያስወረውር ሁሉ ቡድኔ ደካማ አልነበረም
የተልከሰከሰ የዘቀጠ የወረደ ቡድን አልነበረኝም .. ውጤቱ ደካማ በመሆኑ ግን ቅር ብሎኛል
የሚዲያ አካላትን አስተያየት እሰማለሁ ለሀገር የነገ እድገት ለነገ ብሄራዊ ቁድን ማሰብ አለብን በቅንንነት ካያችሁት ሌሎቹ በእድሜ ይበልጡናል ከአሰልጣኞች ጋር ሳወራ ለብሄራዊ ቡድኖቻቸው የቀረበውን ቡድን ይዘው እንደመጡ ነግረውኛል” ብሏል።

በኢትዮጵያ ከ20 አመት በታች ሻምፒዮና ላይ አሸናፊ የሆነው ምክትል አሰልጣኙ ከራሱ ቡድን አንድም ተጨዋች ሳያካትት ስለመሄዱ የተጠየቀው አሰልጣኝ ስዩም ” እንኳን ቡድኔ ውስጥ ከ20 አመት ሊግ ውስጥ ውስጥ ከ20 አመት በታች ተጨዋቾች የሉም ይሄ መታረም አለበት በእድሜ ትልቅነት የሚገመቱና የሚጠረጠሩ ተጨዋቾች በሙሉ ፓስፖርታቸው ያጫውታቸዋል” ሲሉ ያልተጠበቀ ምላሽ ሰጥተዋል።

ዋሊያዎቹን በቀጣይ ልትረከብ እንደሆነ መረጃዎች እየወጡ ነው መረጃው እውነት ነው ወይ ..? የተባለው አሰልጣኝ ስዩም ” ከሀገሪቱ ምርጥ ሶስት አሰልጣኞች መሃል አንዱ እኔ ነኝ ሁለቱን ብትጠሩም አለሁበት ያለሁበት የትምህርት ዝግጅትም ጥሩ የሚባል ነው” ሲል ቀጣዩ የዋሊያዎቹ አሰልጣኝ ሊሆን እንደሚችል ፍንጭ ሰጥቷል።

ለቡድኑ አቀባበል ስላለመደረጉ የተጠየቀው አሰልጣኝ ስዩም ” እውነት ነው አቀባበል አልተደረገልንም እግርኳስ በውጤት ስኬትና በመሸነፍ ውስጥ ያለ ነው ይህ ግን መለመድ አለበት ለምን አቀባበል እንዳልተደረገም አልገባኝም ” ሲል ተናግሯል።

አሰልጣኝ ስዩም ” እድሜና ጤና ይስጠኝ እንጂ ለሀገሬ እየለፋሁ እቀጥላለሁ በእስካሁኑ የሰልጣኝነት ህይወቴ ለብሄራዊ ቡድን የበቁ ተጨዋቾችና በአሁኑ ወቅት አሰልጣኝ የሆኑ ባለሙያዎች በማፍራቴ እኮራለሁ” ሲል አስተያየቱን ሰጥቷል።