JIJIGA CUSTOMS COMMISSION BRANCH /በጉምሩክ ኮሚሽን የጅጅጋ ቅ/ጽ/ቤት @jijcustomsb Channel on Telegram

JIJIGA CUSTOMS COMMISSION BRANCH /በጉምሩክ ኮሚሽን የጅጅጋ ቅ/ጽ/ቤት

@jijcustomsb


ራዕይ፡- "በ2022 በአገራችን ደረጃዉን የጠበቀ ዘመናዊ የጉምሩክ አስተዳደር ተገንብቶ ማየት
ስ/ቁ-025-775-72-77

JIJIGA CUSTOMS COMMISSION BRANCH /በጉምሩክ ኮሚሽን የጅጅጋ ቅ/ጽ/ቤት (Amharic)

በጉምሩክ ኮሚሽን የጅጅጋ ቅ/ጽ/ቤት ተደራሽና እልሻለሁ! እባኮቴ የኤምባሲውን ቧሲት በቀናት በሳምንት ይዞ የመከራቸውን መጠን አግኝቼና ደካማ ከረሲትን እና እንዲሞላበት እንደማልቻቹ ለተመለጧቴ ቻኤት ያስተዳደራል። እባኮት በጉምሩክ ኮሚሽን የጅጅጋ ቅ/ጽ/ቤት ከማህበረሰብ አሸናፊ ለመስራት የሚከፈት እንቅስቃሴ እና ቅሬሌዎችን ከመዋቅር ባለው ክፍት የጅጅጋ ቅ/ጽ/ቤት እንዴት ላይ ማሳወቅ ይችላሉ እንጂ ከአንድ አሃዛን ሊያላግጥ የሚችሉት ባይቸጋም! የጅጅጋ ቅ/ጽ/ቤት እና የጤሌማርክ ፏውስ በሞባይል በጉምሩክ ኮሚሽን በቀናት መጠን ማህጸንና በመወቅት አፍቃራትን ሊሰማ ስለሚመጣው አግኝቼና ደካማ ማወቅ እናንተሰው እናመሰልናለን! በጉምሩክ ኮሚሽን የጅጅጋ ቅ/ጽ/ቤት በመፅሐፍ እና ለማገናኘት በቻኤቴ በሚያርቡት አገልግሎት እንሠራለን!

JIJIGA CUSTOMS COMMISSION BRANCH /በጉምሩክ ኮሚሽን የጅጅጋ ቅ/ጽ/ቤት

17 Feb, 07:12


ለተመረጡ ት/ቤቶች ስር ባሉ የታክስና ጉምሩክ ክበብ አባላት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ
*********************

👉የጅግጅጋ ጉምሩክ/ቅ/ጽ/ቤት እና የገቢዎች ሚነስቴር የድሬዳዋ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ከተመረጡ 08 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች ለተዉጣጡ የታክስና ጉምሩክ ክበብ አባላት በጉምሩክ ህጎች እና አሰራር እንዲሁም በአገር ዉስጥ ታክስ ዙሪያ በጋራ በመሆን የካቲት 08 ቀን 2017 ዓ.ም በጅግጅጋ ቅዱስ ዮሰፍ 2ኛ ደረጃ ት/ት ቤት የትምህርት ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጥቷል ።

👉የስልጠና መድረኩን የከፈቱት የጅግጅጋ ጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የደንበኞች ትምህርትና ድጋፍ የስራ ሂደት አቶ ሲሳይ ጥላሁን ለሰልጣኞች የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን የሰልጠናው ዓላማ አዲሱ ትዉልድ በቀረጥና ታክስ ላይ ያለዉን ግንዛቤ በማስፋት ታማኝ እና አገር ወዳድ ትዉልድ ለማፍራት የሚያግዝ መሆኑን እና በክላስተር 06 በጉምሩክ እና ታክስ ህጎች እና አሰራሮች ዙሪያ እየተሰጠ ያለዉ ስልጠና ቀጣይነት ያለዉ መሆኑን አመላክተዋል።

👉በ2016 ዓ.ም በሀገር አቀፍ ደረጃ 3ኛ የወጣችው ተማሪ ሲና አበራ ለተሳታፊ ተማራዎች የልምድ ልውውጥ እና መዘጋጀት ባለባቸው ጉዳዮች ላይ አሰተያየት በመሰጠት ለተወዳዳሪ ተማሪዎች መልዕክት አስተላልፋለች።

👉ስልጠናዉን በአገር ዉስጥ ታክስን በሚመለከት ከገቢዎች ሚኒስትር የድሬዳዋ ቅ/ጽ/ቤት የታክስ ክፋዮች ትምህርት ክፍል አቶ ሚሊዮን ኢያሱ እና በጉምሩክ ህጎች እና አሰራሮች ዙሪያ ደግሞ ከቅ/ጽ/ቤቱ በአቶ ሲሳይ ጥላሁን በጋራ በመሆን ስለታክስ ምንነት፣ የታክስ ዓይነቶች፣ ስለጉምሩክ ምንነት እና የጉምሩክ ሥነ-ስረዓት አፈፃፀም እንዲሁም ኮንትሮባንድና የታክስ ማጭበርበር ወንጀሎች በሀገር ላይ የሚያደርሱትን ጉዳት በተመለከተ ግንዛቤ በመፈጠር የሰልጠናው መድረክ ተጠናቋል።

************************
************************

በደንበኞች ትምህርት ቡድን የተዘጋጀ
የካቲት 10/ 2017 ዓ.ም
ጅግጅጋ, ኢትዮጵያ
**************

JIJIGA CUSTOMS COMMISSION BRANCH /በጉምሩክ ኮሚሽን የጅጅጋ ቅ/ጽ/ቤት

11 Feb, 06:02


የጉምሩክ ዝርዝር የዋጋ መረጃ ዲክላራሲዮን ጋር በአባሪነት ስለሚቀርቡ መረጃዎችና ሰነዶች
**********************************
በግብይት ዋጋ መሰረት ለማስተናገድ መቅረብ ያለባቸው መረጃዎችና ሰነዶች፡-
*****************
(👉1) ዲክላራሲዮን አቅራቢው በግብይት ዋጋ መሰረት ለመስተናገድ አስፈላጊ የሆኑ መረጃዎችንና ሰነዶች ከዲክላራሲዮን ጋር አባሪ በማድረግ ማቅረብ ይኖርበታል፡፡

(👉2) ዲክላራሲዮን አቅራቢው ግዢ ስለመከናወኑ ለማረጋገጥ የሚቀርቡ ሰነዶችና ማስረጃዎች፦
👍 የዋጋ ሰነድ (ኢንቮይስ) ፣
👍በግብይት ውስጥ ተሳታፊ የሆኑ አካላት እና ሚናቸውን የሚገልጽ ማስረጃ፣
👍ገቢ ዕቃዎቹ በጉምሩክ ቁጥጥር ሥር ከመግባታቸው በፊት ዕቃዎቹን ለመግዛት የተገቡ ውሎችና ሥምምነቶች፣
👍 ከዕቃው ግዢ ጋር የተያያዙ ሌሎች ሰነድና ደረሰኝ ማቅረብ ይጠበቅበታል፡፡

(👉3) ዲክላራሲዮን አቅራቢው ዕቃው የተከፈለ ወይም የሚከፈለው ዋጋ ትክክለኛነት ለማረጋገጥ የሚቀርቡ ሰነዶችና መረጃዎች፡-
👍ከዕቃው ጋር በተያያዘ በዲክላራሲዮን አቅራቢው በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ በገንዘብ ወይም በዓይነት የተከፈሉ ክፍያዎች የሚያሳይ ዝርዝር መረጃ ወይም ሰነድ
👍ከዕቃው በቀጥታ እና ከዕቃው ጋር ከተያያዙ መብቶች ጋር በተገናኘ የተከፈለ ወይም የሚከፈልን ክፍያን የሚያሳይ ዝርዝር መረጃ ወይም ሰነድ
👍 ዕቃውን ለመግዛት የወጡ ሌሎች ወጪዎች የሚያሳይ ዝርዝር መረጃ ወይም ሰነድ

(👉4) ዲክላራሲዮን አቅራቢው ዕቃው እስከ ተጫነበት ወደብ ድረስ የተከፈለ ትራንስፖርትና ኢንሹራንስ ወጪ ትክክለኛነት ለማረጋገጥ የሚቀርብ ሰነዶችና ማስረጃዎች፡-
👍ዕቃው የተላከበት (PLACE OF EXPORT) ሀገርና ዕቃው በኮንቴነር የታሸገበት ቦታ ማስረጃ፣
👍ዕቃው በተላከበት ሀገር ወደብ እስኪደርስ የወጣ የማጓጓዣ ወጪ ማስረጃ፣ በዕቃው ግብይት ወቅት ጥቅም ላይ የዋለ ዓለም አቀፍ የንግድ ሥያሜ (INCOTERMS) ማቅረብ ይጠበቅበታል፡፡

(👉5) ዲክላራሲዮን አቅራቢው ዕቃው ከተጫነበት ወደብ እስከ መጀመሪያ የኢትዮጵያ መግቢያ በር ድረስ የተከፈለ የማጓጓዣ የኢንሹራንስ ወጪ ትክክለኛነት ለማረጋገጥ የሚቀርቡ ሰነዶችና ማስረጃዎች፡-
👍የማጓጓዣ እና የኢንሹራንስ ሥምምነት ሁኔታን የሚያሳይ መግለጫ፤
👍ዕቃውን እስከ ኢትዮጵያ የጉምሩክ ክልል የመጀመሪያ መግቢያ በር ለማድረስ የወጣ የማጓጓዣ፣ የመጫኛ የማራገፊያ፣ የመንከባከቢያና የኢንሹራንስ ወጪዎች ማስረጃ ማቅረብ ይጠበቅበታል፡፡

(👉6) ዲክላራሲዮን አቅራቢው የኮሚሽኑ ክፍያዎች ስለመኖራቸው ለማረጋገጥ የሚቀርቡ ሰነዶችና ማስረጃዎች፡-
👍የውክልና ስምምነት ሰነድ፣ የኮሚሽን ክፍያ ዓይነት የሚገልጽ ሰነድ፣
👍 የኮሚሽን ክፍያ ኢንቮይስ ማቅረብ ይጠበቅበታል፡፡

(👉7) ዲክላራሲዮን አቅራቢው የማሸጊያ እና የመያዣ ወጪ ክፍያዎች ስለመኖራቸው እና ትክክለኛነታቸውን ለማረጋገጥ የሚቀርቡ ሰነድና ማስረጃዎች፡-
👍ዕቃውን ለማሸግ የወጣ የማቴሪያል ዓይነትና የጉልበት ወጪ፣ ዕቃውን የማሸግ ሥራው የተከናወነበት ቦታ ወይም አገር፣
👍 ዕቃውን የማሸግ ሥራ  ያከናወነው አካል፣
👍 ከዕቃው ተነጥለው የማይታዩ የዕቃ መያዣ ወጪ ማቅረብ ይጠበቅበታል፡፡

(👉8) ዲክላራሲዮን አቅራቢው ለላኪው ያቀረባቸውን ግባቶችና አገልግሎቶች ስለመኖራቸው ትክክለኛነታቸውን ለማረጋገጥ የሚቀርቡ ሰነድና ማስረጃዎች፡-
👍ዕቃውን ለማግኘት ወይም ለማምረት በገዢው በቀጥታ ወይም በገዢው ስም በሦስተኛ ወገን በኩል ለአምራቹም ሆነ ለላኪው የቀረቡ ዕቃዎችና አገልግሎቶች ዝርዝር፣
👍ከላይ የተጠቀሱት ዕቃዎችና አገልግሎቶች የማምረቻ ወጪ ወይም የገዢ ዋጋ እና የማድረስ ወጪ የሚያሳይ ማስረጃ ማቅረብ ይጠበቅበታል፡፡

(👉9) ዲክላራሲዮን አቅራቢው የሮያሊቲ ፍቃድ ክፍያዎች ስለመኖራቸውና ትክክለኛነታቸውን ለማረጋገጥ የሚቀረቡ ሰነድና ማስረጃዎች፡-
👍በዕቃው ግብይት ውስጥ ተሳታፊ የሆኑትን አካላት ሚናና ግንኙነት የሚያስረዳ መግለጫ፣ የሮያሊትና ፍቃድ ሥምምነት ሰነድ፣
👍የሽያጭ ስምምነት ሰነድ ፣
👍ከዕቃው ገዢ ጋር የተያያዙ ሌሎች ሰነዶች ማቅርብ ይጠበቅበታል፡፡

(👉10) ዲክላራሲዮን አቅራቢው ዕቃዎችን መልሶ በመሸጥ ከሚገኘው ገቢ ላይ የሚከፈሉ ክፍያዎች ለመኖራቸውና ትክክለኛነታቸውን ለማረጋገጥ የሚቀርቡ ሰነድና ማስረጃዎች፡-
👍የሽያጭ ስምምነት ሰነድ፣
👍 ገዢው ዕቃውን መልሶ በመሸጥ ለሌላ በማስተላለፍ ወይም በመጠቀም ከሚገኝ  ገቢ ላይ ለሻጩ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የሚከፈሉ ክፍያዎች የሚያሳይ ዝርዝር ማስረጃ፣
👍ከዕቃው ገዢ ጋር የተያያዙ ሌሎች ሰነዶች ማቅረብ ይጠበቅበታል፡፡

(👉11) ዲክላራሲዮን አቅራቢው ዕቃው ሀገር ውስጥ ከገባ በኋላ የተሸጠ ወይም የሚሸጥ የቴክኒክ ድጋፍ መኖሩና ትክክለኛነታቸውን ለማረጋገጥ የሚቀርቡ ሰነድና ማስረጃዎች፡-
👍 የዕቃዎች ወይም የአገልግሎቶች ግዢ ውል ሰነድ ፣
👍ክፍያዎቹ ዕቃዎቹ ሀገር ውስጥ ከገቡ በኋላ ለወጡ ወጪዎች የተከፈሉ መሆናቸውን የሚያሳይ መግለጫ፤
👍 የሚደረገውን ድጋፍ ዓይነት ወጪ መጠን ማስረጃ፣
👍 ወጪዎቹ ለዕቃው በተከፈለው ወይም በሚከፈለው ዋጋ ውስጥ መካተታቸውን የሚያሳይ ማስረጃ ማቅረብ ይጠበቅበታል፡፡

(👉12) ዲክላራሲዮን አቅራቢው ዕቃው ሀገር ውስጥ ከገባ በኋላ የተከፈሉ የማጓጓዣ እና አስተዳደራዊ ወጪዎች መኖራቸውን ለማረጋገጥ የሚቀርቡ ሰነድና ማስረጃዎች፡-
👍ዕቃው ሀገር ውስጥ ከገባ በኋላ  የወጣ የማጓጓዣ እና አስተዳደራዊ ወጪ መኖሩን የሚያሳይ መግለጫ፣
👍 የማጓጓዣ እና አስተዳደራዊ ወጪውን መጠን የሚያሳይ ማስረጃ፣ የአገልግሎቱን ባህሪና ሁኔታ የሚያሳይ ማስረጃ፣ ወጪው ለዕቃው በተከፈለው ወይም በሚከፈለው ዋጋ ውስጥ መካተቱን ወይም አለመካተቱን የሚያሳይ ማስረጃ ማቅረብ ይጠበቅበታል፡፡

(👉13) ዲክላራሲዮን አቅራቢው ተቀናሽ የፋይናስ ወጪዎች መኖራቸውንና ትክክለኛነታቸውን ለማረጋገጥ የሚቀርቡ ሰነድና ማስረጃዎች፡-
👍ወደ ሀገር ውስጥ ከገቡት ዕቃዎች ግዥ ጋር በተያያዘ በገዢው የተከፈለውን የብድር ወይም የፋይናንስ ወለድ ክፍያና የክፍያ ስምምነት ሁኔታ የሚያሳይ ማስረጃ፣
👍ክፍያውን ዘግይቶ እንዲፈጽም የሚያስችሉ ስምምነቶች የሚያስረዳ ሰነድ ማቅረብ ይጠበቅበታል፡፡

(👉14) ዲክላራሲዮን አቅራቢው ከሻጩ ጋር ግንኙነት ወይም ዝምድና ያለው መሆኑንና አለመሆኑን ለማረጋገጥ የሚቀርቡ ሰነድና ማስረጃዎች፡-
👍 በገዢና ሻጭ መካከል ያለውን ግኑኝነት ሁኔታና ዓይነት፣
👍በገዢና ሻጭ መካከል ያለውን ግኑኝነት በዕቃው ግብይት ዋጋ ላይ ያለውን ተጽዕኖ የሚያስረዳ የሰነድ ማስረጃ፣
👍 የኮርፖሬቱ (ድርጅት) ዝርዝር ፕሮፋይል የዋጋ ፖሊሲ የሚያሳይ ሰነድ፣ የገዢውን የማካፈል ወይም የኤጀንት (ብቸኛ ወኪል) መብት ስምምነት የሚያሳይ ሰነድ፣
👍የዕቃው የሽያጭ የውል ሰነድ እና የሻጩ ኢንቮይስ፣ በተመሳሳይ ወቅት ግንኑነት በሌላቸው ገዢና ሻጭ መካከል የተከናወነ ሽያጭ (ወደ ኢትዮጵያ የተላኩ) አንድ ዓይነት ወይም ተመሳሳይ ዕቃዎች የግብይት ዋጋ የሚያሳይ ዝርዝር ማስረጃ እና ሌሎች አስፈላጊ መረጃዎችና ሰነዶች ማቅረብ ይጠበቅበታል፡፡

(👉ምንጭ)፡- የጉምሩክ ዋጋ አተማመን መመሪያ ቁጥር 158/2011 እና የጉምሩክ አዋጅ 859/2006
*************************************

በደንበኞች ትምህርት ቡድን የተዘጋጀ
የካቲት 04/ 2017 ዓ.ም
ጅግጅጋ, ኢትዮጵያ
***************
      

JIJIGA CUSTOMS COMMISSION BRANCH /በጉምሩክ ኮሚሽን የጅጅጋ ቅ/ጽ/ቤት

10 Feb, 07:50


👑👑 እንኳን ደስ አላችሁ👑👑
*************************************


👑ለክቡራን አስመጭዎቻችን፤ ለላኪዎች፤ ለጉምሩክ አስተላላፊዎች እና ለቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ሰራተኞች በሙሉ የጅግጅጋ ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት በ2017 በጀት ዓመት በጥር ወር 245,928,009.36( ሁለት መቶ አርባ አምስት ሚሊዮን ዘጠኝ መቶ ሃያ ስምንት ሺህ ዘጠኝ  ብር) ለመሰብሰብ አቅዶ በጥር ወር 395,449,933.88 (ሶስት መቶ ዘጠና አምሰት ሚሊዮን አራት መቶ አርባ ዘጠኝ ሺህ ዘጠኝ መቶ ስላሳ ሶሰት ብር ) ለመሰብሰብ የተቻለ ሲሆን የጥር ወር የዕቅድ አፈጻጸም የዕቅዱን 161% በማሳካት ያጠናቀቀ ሲሆን ለዚህ ዕቅድ መሳካት እና አፈጻጸም ክቡራን አሰመጭዎቻችን፤ላኪዎች፤ የጉምሩክ አስተላላፊዎች፤ የባለደርሻ አካላት እና የቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሰራተኞች ላበረከታቹት አሰተዋጽኦ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ልባዊ ምስጋናውን እያቀረበ ቀረዎቹን የበጀት ዓመቱ ወራቶችን በስኬት ለማጠናቀቅ ቀልጣፋ እና ፈጣን አገልግሎት ለመሰጠት ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ዝግጁ መሆኑን እያሳወቅን ላደረጋችሁት አሰተዋጽኦ ልባዊ ምስጋናውን ያቀርባል።
🙏🙏🙏🙏      🙏🙏🙏🙏    🙏🙏🙏🙏

"''ማገልገል ክብር ነው መዳረሻውን ብልፀገና አድርጋ በፍጥነት በመጓዝ ላይ ያለችን ሀገር እና ዜጎቿን ማገልገል ድርብ ክብር ነው''"

*****///***********/////************//////********

JIJIGA CUSTOMS COMMISSION BRANCH /በጉምሩክ ኮሚሽን የጅጅጋ ቅ/ጽ/ቤት

24 Jan, 07:04


የጅግጅጋ ጉ/ቅ/ጽ/ቤት የ6 ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ አካሄደ
*********************************
*********************************

👉የጅግጅጋ ጉ/ቅ/ጽ/ቤት በቀን 15/2017 ዓ.ም የ 6 ወር የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ በቶጎወጫሌ መቆጣጠሪያ ጣቢያ መሰብሰቢያ አዳራሽ የተደረገ ሲሆን
በፕሮግራሙ የቅ/ጽ/ቤት ሰራ/አስኪያጅ የመክፈቻ ንግግር በማድረግ ፕሮግራሙን አስጀምረዋል።

👉በዕለቱም በዕቅድና ለውጥ ስራዎች ቡድን ተወካይ በአቶ አብዱረሂም አምረዲን የዕቅድ አፈጻጸም ሰነድ የቀረበ ሲሆን  በቀረበውም ሰነድ በ2017 በጀት ዓመት በ6 ወር  2,071,782,738.56 ቢሊዮን ለመሰብሰብ ታቅዶ 1,565,332,722.39 ቢሊዮን ብር ወይም 75.55% ለመሰብሰብ ተችሏል ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ጊዜ ጋር ስነጻጸር 677,163,257.87 ሚሊዮን ብር ወይም 76.24% ብልጫ አሳይቷል ፡፡

👉በኮንትሮባንድ መከላከልና ቁጥጥር በበጀት ዓመቱ 6 ወር ውስጥ ገቢ ኮንትሮባንድ 766,351,412 ሚሊዮን ብር ግምታዊ ዋጋ ያላቸው እና ወጪ ኮንትሮባንድ 581,127,840 ሚሊዮን ብር ግምታዊ ዋጋ ያላቸው በአጠቃላይ 1,347,479,252 ቢሊዮን ብር  ያላቸውን የተለያዩ ዕቃዎች በመያዝ ገቢ ለማድረግ የተቻለ ሲሆን ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ጊዜ ጋር ስነጻጸር 411,508,856 ሚሊዮን ብር ወይም 43.97% ብልጫ አሳይቷል።  በተጨማሪም በንግድ ማጭበርበር ማለትም በኢንተለጀንስ ስራዎች 8,817,078.92 ሚሊዮን ብር ፣ በድንገተኛ ፍተሻ 26 ሚሊዮን ብር ግኝት መገኘቱን ተጠቁመዋል።

👉እንዲሁም በኮንትሮባንድ ዝውውር የተጠረጠሩ 33 ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር በመዋል አስፈላጊው ህጋዊ እርምጃ እንዲወሰድባቸው እየተደረገ ነውም ተብለዋል።

👉በመጨረሻም በዘርፉና በስራ ሂደቶች በነበሩት የአፈጻጸም ክፍተቶች ላይ በሰፊው ውይይት የተደረገ ሲሆን የቅ/ጽ/ቤት ስራ አስኪያጅ አቶ ዝናው ደርበ እንዳሉት በቀጣይ ስድስት ወራቶች ላይ ለገቢ አሰባሰብ አስተዋጽኦ የሚያበረክቱትን ጉዳዮች የዕዳ ክትትል፤ የጉምሩክ አቤቱታ፤ የመረጃ ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን ማዘመንና እና አገልግሎት አሰጣጡን ለአስመጪዎች፤ ላኪዎች ፤ለተመረጡ የኢኮኖሚ አንቀሳቃሾች የተሟላ አገልግሎት መሰጠት እንዳለብን አሳስበው በተገኘው ውጤትም ባለድረሻ አካላትና የቅ/ጽ/ቤት ሰራተኞችን አመሰግነው ምቹ የስራ አከባቢን በመፈጠር ቀሪውን ጊዜ የገቢ አቅማችን አሟጠን መጠቀም እንዳለብን አቅጣጫ ተሰጥቶበት የግምገማ ፕሮግራም ተጠናቋል፡፡

************************************
************************************

በደንበኞች ትምህርት ቡድን የተዘጋጀ
ጥር 16/2017 ዓ.ም
ጅግጅጋ, ኢትዮጵያ
*******************************

JIJIGA CUSTOMS COMMISSION BRANCH /በጉምሩክ ኮሚሽን የጅጅጋ ቅ/ጽ/ቤት

14 Jan, 07:58


ጨረታ የወጡ ተሽከርካሪዎች በምስል
******************************
******************************

JIJIGA CUSTOMS COMMISSION BRANCH /በጉምሩክ ኮሚሽን የጅጅጋ ቅ/ጽ/ቤት

06 Jan, 10:35


💒✝️ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ብርሃነ  ልደት በሠላምና በጤና አደረሳችሁ።

✝️በአሉ በጋራ አንድነት ፈጥረን ለጋራ ሰላም እና ለልማት የምንተጋበት፣ ቂምና በቀልን አስወግደን ይቅር የምንባባልበት፣ የሁሉም መሠረት የሆነውን ሰላም አብዝተን የምንጠብቅበት፣ በዓሉ እርስ በእርስ የምንተሳሰብበት፤ ያለው ለሌለው የምናካፍልበት፣ ከልዩነት ይልቅ አንድነታችን ጎልቶ የሚታይበት በዓል እንዲሆን እየተመኘ በዓሉ የሠላም፣ የፍቅር፣ የአብሮነትና የብልፅግና በዓል እንዲሆን ከልቡ ይመኛል።

     ✝️መልካም የገና በአል💒⛪️✝️

    የጅግጅጋ ጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት
✝️⛪️⛪️⛪️⛪️💒💒💒⛪️⛪️⛪️
✝️

JIJIGA CUSTOMS COMMISSION BRANCH /በጉምሩክ ኮሚሽን የጅጅጋ ቅ/ጽ/ቤት

01 Jan, 11:24


የጅግጅጋ ጉምሩክ ቅርንጫፍ  ጽ/ቤት ከባለድርሻ አካላት ጋር የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሄድ ***********************************
***********************************

👉የጅግጅጋ ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት ታህሳስ 22 ቀን 2017 ዓ/ም የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ አመራሮች፤ የፋፈን ዞን አስተዳደሮች፤ የወረዳ አመራሮች፤ የፀጥታ ዘረፍ ኃላፊዎች፤ የሀገር ሽማግሌዎች፤የቦንባስ መቆጣጠር ጣቢያ አሰተባባሪዎች፤ የፌዴራል ፖሊስ አመራሮች እና በየደረጃው ያሉ የሚመለከታቸው አካላት በተገኙበት በፋፈን ከተማ  የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አደረገ።

👉የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ የደንበኞች ትምህርትና ድጋፍ የስራ ሂደት አቶ ሲሳይ ጥላሁን በኮንትሮባንድ ምንነት፤ በህግ ተግዥነት ዙሪያ፤ በቅሬታ አቅራርብ፤ በወሮታ አከፋፈል፤ በጉምሩክ አዋጆችና መመሪያዎች ዙሪያ የተዘጋጅውን አሰተማሪ የሆነ ስነድ ገለፃ አደርጓል።

👉የህግ-ተግዥነት ዘርፍ ወክሎ የተገኑት አቶ አብዱልፈታህ መሐመድ በበኩላችሁ የመድረኩ አላማ የኮንትሮባንድና ህገ ወጥ ንግድ የሚያደርሰዉን ዘርፈ ብዙ ፖለቲካዊ፣ማህበራዊ ፣ ኢኮኖሚያዊ ጉዳቶች ለመከላከልና የህብረተሰቡ ተሳትፎ ለማጠናከር የተዘጋጅ መድረክ መሆኑን ገልፆዋል።

👉ለተነሱ ጥያቄዎችም የደንበኞች ትምህርትና ድጋፍ የስራ ሂደት ፤ የመቆጣጠሪያ ጣቢያ አሰተባባሪ እና የፌዴራል ፖሊስ አመራር ምላሽ ከሰጡ በኋላ ቀጣይነት ባለው መልኩ የኮንትሮባንድና የህግ ወጥ ንግድ ቁጥጥር ተጠናክረው መቀጠል እንዳለበት እና ክፍተቶችን በማረም ቀጣይነት ያለውን የኮንትሮባንድ መከላከል ስራ ከህብረተሰቡ ጋር እጅና ጓንት በመሆን ስራ እንደሚሰራ ሀሳብ በመስጠት የዉይይት መድረኩ ተጠናቀዋል።


በደንበኞች ትምህርት ቡድን የተዘጋጀ
23/04/2017 ዓ.ም
ጅግጅጋ,ኢትዮጵያ
*****************************

JIJIGA CUSTOMS COMMISSION BRANCH /በጉምሩክ ኮሚሽን የጅጅጋ ቅ/ጽ/ቤት

30 Nov, 08:11


5. በወጪ ስሌት ላይ የተመሰረተ የዋጋ አተማመን ዘዴ አፈጻጸም*************************************
*********

👉ከላይ በተገለጹት የዋጋ መተመኛ ዘዴዎች ዋጋ ሊወሰን በማይቻልበት ጊዜ ከአምራቹ ድርጅት በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ በሚገኙት መረጃዎች እና ደጋፊ ማስረጃዎች ዕቃውን ለማምረትና ለመሸጥ የወጡ የሚከተሉትን ወጪዎች በሚያካትት ስሌት ላይ ተመሥርቶ ይወሰናል፡፡
  👍የዕቃዎቹን የማምረቻ ወይም የማዘጋጃ ወጪዎች፣
  👍ዕቃዎቹ በተላኩበት አገር በአምራቾች ሲሸጡ አብዛኛውን ጊዜ የሚያስከትሉትን ጠቅላላ ወጪና የሚያስገኙትን የትርፍ መጠን፣ እና
  👍ዕቃዎቹን እስከ ጉምሩክ ክልል መግቢያ በር ለማድረስ የሚያስወጣውን የማጓጓዣ፣ የመጫኛ፣ የማራገፊያ፣ የመንከባከቢያና የኢንሹራንስ ወጪ በሚያካትት ስሌት ላይ ተመሥርቶ ይወሰናል፡፡
  👍ከላይ እንደተገለጸው የግብይት ዋጋን ለመወሰን በአምራቹ ፍቃድ የሚገኘውን መረጃ ለማረጋገጥ፣ የሚመለከተው የአምራቹ አገር መንግስታዊ አካል ጉዳዩን በቅድሚያ እንዲያውቀው በማድረግ የማይቃወመው መሆኑ መረጋገጥ አለበት፡፡

6.ሚዛናዊ የዋጋ አተማመን ዘዴ አፈጻጸም
************************************
👉ከላይ በተገለጹት አምስት የዋጋ መተመኛ ዘዴዎች ዋጋ ለመወሰን ካልተቻለ በአገር ውስጥ ያለውን ወቅታዊ መረጃ በመጠቀምና ከጉምሩክ አዋጅ ድንጋጌዎች አጠቃላይ መርህ ጋር የተጣጣመ ሚዛናዊ ዘዴን በመጠቀም ይወሰናል፡፡ ይህም ከላይ የተጠቀሱትን የዋጋ አተማመን ዘዴዎች በቅደም ተከተላቸዉ መሰረት አተረጓጎማቸዉን በማስፋት ዋጋ የመወሰን ስራ ይፈጸማል፡፡
👉የአንድ አይነት ወይም የተመሳሳይ ዕቃ ሚዛናዊ ዘዴ በ90 ቀናት ውስጥ የገባ የአንድ አይነት ወይም የተመሳሳይ ዕቃ ዋጋ በማይገኝበት ወቅት በ180 ቀናት ውስጥ ወደ ሀገር የገባ የአንድ አይነት ወይም የተመሳሳይ ዕቃ ዋጋ እንደ ቀረጥና ታክስ ማስከፈያ ዋጋ ሊያገለግል ይችላል፡፡ ሆኖም አስመጭው ሲጠይቅ የተተመነው ዋጋና የአተማመን ዘዴው በጽሁፍ ይገለጽለታል፡፡

👉የዕቃዎች ማነጻጸሪያ ዋጋ በመረጃ ቋት ውስጥ ሁለትና ከዚያ በላይ በሚገኝበት ወቅት የጉምሩክ ዋጋ ማነጻጸሪያ ተደርጎ የሚወሰደው የንግድ ዕቃ ባህሪ ያላቸውና ተቀባይነት ያገኙ ዋጋ በሙሉ ተቀራራቢ አማካኝ (Weighted Average) ተጠቅሞ በማስላት ይሆናል፡፡

👉ከላይ እንደተገለጸው (Weighted Average) አማካይ ሲሰላ የማነጻጸሪያ ዋጋ ከ30 በመቶ በላይ የተጋነ ወይም ያነሰ ዋጋ በስሌቱ ውስጥ እንዳይካት ይደረጋል፡፡ 
👉ወደ አገር የገባ ዕቃ በተመረተበት አገር የተመረተ የአንድ አይነት  ወይም የተመሳሳይ ዕቃ ዋጋ በማይገኝበት ጊዜ በተመሳሳይ የዕድገት ደረጃ በሚገኝ አገር የተመረተ የአንድ አይነት ወይም የተመሳሳይ ዕቃ አድርጎ መውሰድ ይቻላል፡፡

👉ወደኋላ በማስላት እና በውጪ ስሌት ላይ በተመሰረተ የዋጋ አተማመን ዘዴ መሰረት የተወሰኑ የአንድ አይነት ዕቃ ወይም የተመሳሳይ ዕቃ ዋጋ የቀረጥና ታክስ ማስከፈያ ዋጋ ሆኖ ሊያገለግል ይችላል፡፡

👉በ180 ቀናት ውስጥ ወደ ሀገር የገባ የአንድ አይነት ወይም የተመሳሳይ ዕቃዎች ዋጋ ካልተገኙ 180 ቀናት በላይ በየስድስት ተጨማሪ ወራት ጊዜ ውስጥ ያለ መረጃ በቅደም ተከተል በመውሰድ ዋጋ መወሰን ይቻላል፡፡

👉ከድብልቅ ማቴሪያሎች የተሰሩ ዕቃዎች ዋጋ አወሳሰን
**********************************************
👍ወደ አገር ውስጥ  የሚገባ ዕቃ ከድብልቅ ማቴሪያል የተሰራ ዕቃ ሆነው ቅ/ጽ/ቤቱ የጉምሩክ ባለሙያ ወይም የስራ ኃላፊ በሁሉም የዋጋ አተማመን ዘዴዎች በመጠቀም ውሳኔ መስጠት በማይቻልበት ጊዜ የዕቃውን የጉምሩክ ዋጋ ለመወሰን ዕቃው የተሰራበት የድብልቅ ንጥረ ነገር  ዋጋ ተወስዶ አማካኝ ሬሾ ላይ  በመመስረት ይሆናል፡፡

👉ምንጭ፡- የጉምሩክ ዋጋ አተማመን መመሪያ ቁጥር 158/2011 እና የጉምሩክ አዋጅ 859/2006


በደንበኞች ትምህርት ቡድን የተዘጋጀ
21/03/2017 ዓ.ም
ጅግጅጋ,ኢትዮጵያ
***************

JIJIGA CUSTOMS COMMISSION BRANCH /በጉምሩክ ኮሚሽን የጅጅጋ ቅ/ጽ/ቤት

30 Nov, 05:23


4. ወደኋላ የማስላት ዘዴ አፈጻጸም
*******************************
👉የዕቃው ዋጋ ከላይ በተገለጹት ሶስት የዋጋ አተማመን ዘዴዎች መወሰን ያልተቻለ እንደሆነ ግንኙነት በሌላቸው ገዢና ሻጭ መካከል በተደረገ ግብይት በዲክላራሲዮን አቅራቢው ወይም በሌሎች ዲክላራሲዮን አቅራቢዎች ዕቃው ከተጫነበት አገር በቀጥታ ወይም ከሌላ አገር ወደ ሀገር ውስጥ የገባ ዕቃ ወይም ወደ ሀገር ውስጥ ከገባ 90 ቀናት ያልበለጠ አንድ አይነት ወይም ተመሳሳይ ዕቃ በከፍተኛ ብዛት በሀገር ውስጥ በተሸጠበት ነጠላ ዋጋ ላይ በመመሥረት እና የሚከተሉትን ከዋጋው ላይ በመቀነስ ይወሰናል፡፡

👉እነርሱም፡-
*************
👍ለዕቃዎቹ አብዛኛውን ጊዜ የሚከፈለውን ኮሚሽን ወይም የሚደመረውን የጠቅላላ ወጪና የትርፍ መጠን፤
👍ለዕቃዎቹ በኢትዮጵያ ውስጥ አብዛኛውን ጊዜ የሚከፈሉትን የማጓጓዣ፣ የኢንሹራንስና ሌሎች ተዛማጅ ወጪዎች፤
👍ለዕቃዎቹ  ወደ አገር ውስጥ ሲገቡ የሚከፈለው ቀረጥ፣ ታክስና ሌሎች ክፍያዎች ናቸው፡፡
👍ዕቃ ሀገር ውስጥ ከገባ በኋላ ከመሸጡ በፊት የተከናወነ በምርት ሂደት የታከለ ተጨማሪ እሴት መጠን  የተሸጠ ከሆነ ተቀናሽ ይደረጋል፡፡

👉ሻጭ ማለት ዲክላራሲዮን አቅራቢው ሲሆን ገዥ ማለት ዕቃውን ከዲክላራሲዮን አቅራቢው የገዛ ሲሆን እንደ ሁኔታው አከፋፋይ፣ ቸርቻሪ ወይም የመጨረሻ ተጠቃሚ ሊሆን ይችላል፡፡

👉ወደኋላ በማስላት ዘዴ የጉምሩክ ዋጋ ሊተመን የሚችለው፡-
***************************************
👍በዲክላራሲዮን አቅራቢው (ሻጭ) እና በገዢው መካከል ግንኙነት ከሌለው ወይም ግንኙነቱ በመሸጫ ዋጋው ላይ ተጽዕኖ እንዳላሳደረ ዲክላራሲዮን አቅራቢው ማስረጃ ማቅረብ ከቻለ፣
👍በገዥ በኩል ለሻጩ ከዕቃው ጋር በተያያዘ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ በነጻ ወይም በቅናሽ ዋጋ የተከፈለ ክፍያ ወይም የተሰጠ ስጦታ ከሌለ፣
👍ዕቃው በከፍተኛ ብዛት በአገር ውስጥ የተሸጠበት ነጠላ ዋጋ መሆኑን በማስረጃ ማስረዳት የተቻለ እንደሆነ ነው፡፡
የደንበኞች ትምህርት ቡድን

👉ምንጭ፡- የጉምሩክ ዋጋ አተማመን መመሪያ ቁጥር 158/2011 እና የጉምሩክ አዋጅ 859/2006

በደንበኞች ትምህርት ቡድን የተዘጋጀ
21/03/2017 ዓ.ም
ጅግጅጋ,ኢትዮጵያ

*******************************
*******************************

5. በወጪ ስሌት ላይ የተመሰረተ አተማመን ዘዴ....ይቀጥላል ...........

JIJIGA CUSTOMS COMMISSION BRANCH /በጉምሩክ ኮሚሽን የጅጅጋ ቅ/ጽ/ቤት

29 Nov, 13:06


የፌዴራል የስራተኞች አዋጅ አስመልክቶ ስልጠና ተሰጠ
************************
                                   ************************


✍️በጅግጅጋ ጉ/ቅ/ጽ/ቤት በቅ/ጽ/ቤቱ የስልጠና አዳራሽ የፌዴራል የሰራተኞች አዋጅ ቁጥር 1064/2010 ዙሪያ ላይ ያተኮረ ስልጠና ህዳር 20/2017 ዓ.ም ለቅ/ጽ/ቤቱ አመራሮችና ሰራተኞች ተሰጠ፡፡

✍️ሰልጠናዉን የሰጡት የቅ/ጽ/ቤቱ የስው ሀብት ስራ አመራር የስራ ሂደት አሰተባባሪ አቶ ሰለሞን አስፋ በበኩላቸዉ  ስልጠናው የሰራተኞች አቅም ለመገንባትና ስራተኞችም መብትና ግዴታቸውን አውቀው የመንግስት ስራ በአግባቡ እንዲፈጸሙ ለማድረግና መብትና ግዴታቸውን በአዋጁ መሰረት እንዲያውቁ ለማድረግ የተሰጠ ስልጠና መሆኑን ገልጸዋል፡፡

✍️የስልጠናው ተሳታፊዎች በበኩላቸው ስልጠናው የሰራተኞች መብትና ግዴታዎችን በደንብ እንድናውቅ ያደረገ መሆኑን አሳውቀው ስልጠናው በሌሎች በተቋሙ አዋጆች፣ መመሪያዎች እና ደንቦች ዙሪያ ቀጣይነት ባለው መልኩ ቢሰጥ የተሻለ ግንዛቤ ሰራተኞች ላይ የሚፈጠር መሆኑን አሳውቀዋል።

**********************************
**********************************


በደንበኞች ትምህርት ቡድን የተዘጋጀ
ህዳር 20/2017 ዓ.ም
ጅግጅጋ, ኢትዮጵያ
**********************************

JIJIGA CUSTOMS COMMISSION BRANCH /በጉምሩክ ኮሚሽን የጅጅጋ ቅ/ጽ/ቤት

29 Nov, 12:40


ማስታወቂያ
**********


👉ዝቅተኛ የህግ ተገዥነት ደረጃ ያስመዘገቡና ከዚህ በላይ ከተዘረዘሩ አስመጪዎች እና የጉምሩክ አስተላላፊዎች ጋር የጉምሩክ ኮሚሽን ህዳር 23 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ በካፒታል ሆቴል ጧት ከ2፡30 ጀምሮ ለግማሽ ቀን የውይይት መድረክ ስላዘጋጀ በዝርዝሩ ውስጥ የተካተታችሁ አስመጪዎችና የጉምሩክ አስተላላፊዎች በዕለቱ በውይይት መድረኩ ላይ እንድትሳተፉ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።

JIJIGA CUSTOMS COMMISSION BRANCH /በጉምሩክ ኮሚሽን የጅጅጋ ቅ/ጽ/ቤት

29 Nov, 05:38


2. የአንድ አይነት ዕቃዎች ዋጋ አወሳሰን ዘዴ አፈጻጸም
********************************************

✍️አንድ አይነት ዕቃ ማለት፡- በአካላዊ ባህሪያቸው፣ በጥራታቸውና በተፈላጊነታቸው አንድ የሆኑና በአንድ አገር የተመረቱ ናቸው፡፡

✍️የዕቃውን ዋጋ በግብይት ዋጋ አተማመን ዘዴ መወሰን ካልተቻለ ዕቃው ከመግባቱ በፊት በነበሩት 90 ቀናት ውስጥ በተመሳሳይ የንግድ ደረጃ እና በተቀራራቢ ብዛት ወደ ሀገር ገብተው በነበሩ ግንኙነት ለሌላቸው ገዢዎች የተሸጡ አንድ አይነት ዕቃዎችን አስመልክቶ ዲክላራሲዮን አቅራቢው በሚያቀርበው የዋጋ መረጃ በመነሳት የዋጋ ውሳኔ ይተላለፋል፡፡

✍️በአንድ አይነት ዕቃ መሠረት ለመስተናገድ መቅረብ ያለባቸው መረጃዎችና ሰነዶች
👍1.  በዚህ የዋጋ አተማመን ዘዴ መሰረት ዋጋው ትክክል የሚሆንበትን ምክንያት የሚያስረዳ መግለጫ፤
👍2.  ከዕቃው በፊት ወደ ሀገር ውስጥ የገቡ አንድ ዓይነት ዕቃዎችን በተመሳሳይ የንግድ ደረጃና በተቀራራቢ ብዛት በተሸጡ ነጠላ ዋጋ የሚያሳይ ማስረጃ፤
👍3.  በተመሳሳይ ወይም በተቀራራቢ ወቅት ወደ ኢትዮጵያ የገቡ አንድ ዓይነት ዕቃዎች ማስረጃ፤
👍4.  የአንድ አይነት ዕቃዎች የአምራች የመሸጫ ዋጋ ዝርዝር መረጃ (PRICE LIST)
የሚያሳይ የሰነድ ማስረጃ መቅረብ አለበት፡፡


3. የተመሳሳይ ዕቃዎች ዋጋ አወሳሰን ዘዴ አፈጻጸም
*******************************************
✍️ተመሳሳይ ዕቃ ማለት፡- በሁሉም አንጻር ባይመሳሰሉም ተመሳሳይ ባህሪ ያላቸው፣ ከተመሳሳይ ማቴሪያል የተመረቱ፣ ተመሳሳይ ተግባር ማከናወን የሚችሉና ተመሳሳይ  የገበያ ተፈላጊነት ያላቸው ሲሆኑ ጥራታቸው፣ በአንድ አገር የተመረቱ መሆናቸውን፣ ተፈላጊነታቸውንና  የንግድ ምልክታቸው ስለተመሳሳይነታቸው ከግምት ውስጥ ይገባል፡፡

✍️የዕቃውን ዋጋ ከላይ በተገለጹት ሁለት የዋጋ አተማመን ዘዴዎች መወሰን ካልተቻለ በ90 ቀናት ውስጥ በተመሳሳይ የንግድ ደረጃ እና በተቀራራቢ ብዛት ወደ ሀገር ገብተው በነበሩ ግንኙነት ለሌላቸው ገዢዎች የተሸጡ ተመሣሣይ ዕቃዎችን አስመልክቶ ዲክላራሲዮን አቅራቢው በሚያቀርበው የዋጋ መረጃ መሰረት የዋጋ ውሳኔ ይተላለፋል፡፡

👉ምንጭ፡- የጉምሩክ ዋጋ አተማመን መመሪያ ቁጥር 158/2011 እና የጉምሩክ አዋጅ 859/2006


በደንበኞች ትምህርት ቡድን የተዘጋጀ
20/03/2017 ዓ.ም
ጅግጅጋ, ኢትዮጵያ
*********************************

4. ወደኋላ የማስላት አተማመን ዘዴ.....ይቀጥላል .....

JIJIGA CUSTOMS COMMISSION BRANCH /በጉምሩክ ኮሚሽን የጅጅጋ ቅ/ጽ/ቤት

28 Nov, 07:44


የጉምሩክ  ዋጋ አተማመን ዘዴዎች
*****************************

✍️የጉምሩክ ዋጋ ማለት የጉምሩክ ቀረጥና ታክስን ማስከፈያ  ዋጋ ሲሆን በዋጋ አተማመን ዜዴዎች አማካኝነት የሚሰላ እስከ ኢትዮጵያ የጉምሩክ ክልል የመጀመሪያ መግቢያ ወይም መውጫ ድረስ በትክክል ለዕቃው የተከፈለ ወይም ሊከፈል የሚገባው የሲ.አይ.ኤፍ ዋጋና ሌሎች ወጪዎችና ክፍያዎች ጠቅላላ ድምር ነው፡፡

✍️የቀረጥና ታክስ ማስከፈያ ዋጋ የሚወሰነው በቅደም ተከተላቸው መሰረት በሚከተሉት ስድስት ዘዴዎች አማካኝነት ነው:: እነዚህም፡-

1.  የግብይት ዋጋ አተማመን ዘዴ፣
2.  የአንድ አይነት ዕቃዎች ዋጋ አተማመን ዘዴ፣
3.  የተመሳሳይ ዕቃዎች ዋጋ አተማመን ዘዴ፣
4.  ወደ ኋላ የማስላት አተማመን ዘዴ፣
5.  በወጪ ስሌት ላይ የተመሰረተ አተማመን ዘዴ፣
6.  ሚዛናዊ የዋጋ አተማመን ዘዴን በቅደም ተከተል  በመጠቀም ይሆናል፡፡

1.  የግብይት ዋጋ አተማመን ዘዴ፣
*****************************
✍️የግብይት ዋጋ ተደርጎ የሚወሰደው ወደ ኢትዮጵያ እንዲላክ ለተሸጠው ዕቃ በትክክል የተከፈለው ወይም  የሚከፈለው የግብይት ዋጋ ሲሆን ተጨማሪ ክፍያዎችን ያካትታል፡፡ 
  
      በግብይት ዋጋ ውስጥ የማይካተቱ ክፍያዎች
******************************************
👍የፋብሪካ መሳሪያዎች፣ ማሽነሪዎች ወይም መሳሪያዎች ወደ አገር ዉስጥ ከገቡ በኋላ  ለተከናወነ ወይም ለሚከናወን የግንባታ፣ የማሻሻያ፣ የተከላ ወይም  የጥገና ሥራ ወይም ለቴክኒክ ድጋፍ የሚከፈል ክፍያ፤
👍ዕቃዎች ወደ ጉምሩክ ክልል ከገቡ በኋላ የሚከፈል የትራንስፖርት ክፍያ፤
👍ወደ አገር ውስጥ ከገቡት ዕቃዎች ግዢ ጋር በተያያዘ ገዢው ለገባው የብድር ወይም የፋይናንስ ስምምነት የሚከፈል የወለድ ክፍያ፤
👍የግዢ ኮሚሽን                
👍ወደ አገር ውስጥ ከገቡ ዕቃዎች ጋር በተያያዘ ኢትዮጵያ ውስጥ የተከፈለ ቀረጥና ታክስ ሌሎች ክፍያዎች
👍ወደ አገር ውስጥ የገቡትን ዕቃዎች በአገር ውስጥ እንደገና ለማምረት የሚከፈሉ ክፍያዎች፣
👍ዕቃዎቹን ለመላክ በቅድመ ሁኔታነት የተቀመጡ ካልሆነ በስተቀር ወደ አገር ውስጥ የገቡ ዕቃዎችን ለማከፋፈል ወይም እንደገና ለመሸጥ በገዢው የሚከፈሉ ክፍያዎች ናቸው፡፡

ምንጭ፡- የጉምሩክ ዋጋ አተማመን መመሪያ ቁጥር 158/2011 እና የጉምሩክ አዋጅ 859/2006
***********************************

በደንበኞች ትምህርት ቡድን የተዘጋጀ
19/03/2017 ዓ.ም
ጅግጅጋ, ኢትዮጵያ
  ****************************

2. የአንድ ዓይነት ዕቃዎች ዋጋ አተማመን ዘዴ........ይቀጥላል .......................

JIJIGA CUSTOMS COMMISSION BRANCH /በጉምሩክ ኮሚሽን የጅጅጋ ቅ/ጽ/ቤት

19 Nov, 06:14


😭😭የሀዘን መግለጫ😭😭
😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭


😭የቅ/ጽ/ቤታችን ባልደረባ የሆኑት ም/ኢንስፔክተር ፍስሀ ሀንኮሳ ባገጠማቸው ህመም ምክንያት በህክምና ሲረዱ ቆይቶ ህዳር 9/2017 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡😭😭

😭ም/ኢንስፔክተር ፍስሀ ሀንኮሳ ከመጋቢት 12 ቀን/2010 ዓ.ም ጀምሮ ህይወታቸው እስካለፈበት ህዳር 9/2017 ዓ.ም በጅግጅጋ ጉምሩክ/ቅ/ጽ/ቤት በመቆጣጠሪያ ጣቢያ መሪ ባለሙያነት ስራ በቅንነት አገልግለዋል፡፡  ም/ኢንስፔክተር ፍስሀ ስራ ወዳድ እና መልካም ሰው ነበሩ!😭😭

😭መላው የቅ/ጽ/ቤታችን አመራርና ሠራተኞች በስራ ባልደረባችን ም/ኢንስፔክተር ፍስሀ ድንገተኛ ህልፈት የተሰማንን መሪር ሀዘን እየገለፅን ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጆቻቸውና ለስራ ባልደረቦቻቸው መፅናናትን እየተመኘን ፈጣሪ ነፍሳቸውን ይምር ዘንድ ምኞታችንን እንገልፃለን!😭😭😭ነፍስ ይማር! 😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭
                                                                                                                                                                                         የጅግጅጋ ጉምሩክ /ቅ/ጽ/ቤት
     😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭

JIJIGA CUSTOMS COMMISSION BRANCH /በጉምሩክ ኮሚሽን የጅጅጋ ቅ/ጽ/ቤት

08 Nov, 13:37


ለጨረታ የወጡ የተለያዩ ስማርት ስልኮች ምስል በፎቶ
**********************//////////////

JIJIGA CUSTOMS COMMISSION BRANCH /በጉምሩክ ኮሚሽን የጅጅጋ ቅ/ጽ/ቤት

31 Oct, 06:01


ጨረታ የወጡ ተሸከርካሪዎች

JIJIGA CUSTOMS COMMISSION BRANCH /በጉምሩክ ኮሚሽን የጅጅጋ ቅ/ጽ/ቤት

30 Oct, 06:33


ዕቃዎች ከመንግስት/ውርስ/ የጉምሩክ መጋዘን ስለሚወጡበት ሁኔታ፣
***************************************

(👉1) ከመንግስት የጉምሩክ መጋዘን የሚወጣ ማንኛውም ዕቃ በጉምሩክ መጋዘን በቡድን አስተባባሪው ወይም በተወካዩ መረጋገጥ አለበት፣

(👉2) ከዚህ በታች በተገለፁት ምክንያቶች  ዕቃዎች ከመንግስት የጉምሩክ መጋዘን እንዲወጡ ሊፈቀድ ይችላል፡-

👍እንዲወገዱ ውሳኔ የተሰጠባቸው ዕቃዎች፣
👍በፍትህ አካላት በእግዚቢትነት እንዲቀርቡ የተጠየቁ ዕቃዎች፣
👍በክርክር ላይ የነበሩና ለባለንብረቱ እንዲመለሱ ውሳኔ የተሰጠባቸው ዕቃዎች፣
👍ለመንግስት መስሪያ ቤቶች እንዲተላለፉ ውሳኔ የተሰጠባቸው ዕቃዎች፣
👍ለሰብአዊ እርዳታ እንዲተላለፉ ውሳኔ የተሰጠባቸው ዕቃዎች ናቸው፡፡


(የመረጃ ምንጭ) :-የጉምሩክ መጋዘን አስተዳደር መመሪያ  ቁጥር 154/2011)
**************************************

በደንበኞች ትምህርት ቡድን የተዘጋጀ
ጥቅምት 20/2017  ዓ.ም
ጅግጅጋ, ኢትዮጵያ
*************************************
ለበለጠ መረጃ ፤ አሰተያየት እና ቅሬታ በታች ባለው ቁጥር ያሳወቁን፤ ይጠይቁን።

                           
📞
+251257757299
*********************************

JIJIGA CUSTOMS COMMISSION BRANCH /በጉምሩክ ኮሚሽን የጅጅጋ ቅ/ጽ/ቤት

29 Oct, 06:41


ወደ  ተፈቀደ የጉምሩክ መጋዘን የገቡ ዕቃዎችን  የማቆያ የጊዜ ገዳብ፦
***************
***             **************************
     
(👉1)በኮሚሽኑ ወይም ስልጣን በተሰጠው አካል ውሳኔ መሠረት ወደ ቦንድድ  መጋዘን ፣ቦንድድ ኤክስፖርት ፋብሪካ፣ የቦንድድ ኤክስፖርት ማምረቻ መጋዘን  እና  የቦንድድ ግብአት አቅርቦት መጋዘን የገቡ ዕቃዎችን በሚከተሉት ምክንያቶች የጊዜ  ገደቡን ለተጨማሪ  ጊዜ  ሊራዘም ይችላል፡-
********     *******        ******
(👍ሀ) ከኢንዱስትሪው የሚገለገልበት ማሽን በመሰበሩ ወይም በሰራተኞች የሥራ ማቆም አድማ እና ሌሎች አሳማኝ ምክንያት ድርጅቱ ከአንድ ወር ላላነሰ ጊዜ  ሥራ ማቆሙን የሚያረጋግጥ  መረጃ  ሲቀርብ፣

(👍ለ) ጥሬ ዕቃው በዓለም ገበያ ላይ እጥረት ያለበት በመሆኑ ወይም ከፍተኛ የግዢ ትዕዛዝ በመኖሩ ምክንያት የተያዘ ስቶክ ሲኖር፣

(👍ሐ) ምርቱን የሚገዛው የውጭ ድርጅት ውሉን ማፍረሱ ሲረጋገጥ ወይም ሌላ ገበያ ለማግኘት  ተጨማሪ ጊዜ የሚያስፈልግ ሆኖ ሲገኝ፣

(👍መ) በሌሎች ከአቅም በላይ በሆኑ ምክንያቶች፣

(👍ሠ) በዚህ ንዑስ አንቀጽ  /ሀ/ ፣/ለ/፣ /ሐ/ እና /መ/  ከተመለከተው በተጨማሪ ስልጣን ከተሰጠው  አካል የድጋፍ ደብዳቤ መቅረብ ይኖርበታል፡፡

(👉2) ባለፈቃዱ በአንድ በጀት ዓመት ከሁለት ጊዜ በላይ የማራዘሚያ ጥያቄ ማቅረብ አይችልም፡፡

(👉3) የጊዜ ገደብ  ማራዘሚያ  ጥያቄ  የሚቀርበው የጊዜ ገደቡ ከማለፉ በፊት መሆን አለበት።

(👉4) የማራዘሚያው ጥያቄ በኮሚሽነሩ ወይም ኮሚሽነሩ በሚወክለው አካል  ሲፈቅድ ብቻ  ተፈጻሚ ይሆናል፡፡

( የመረጃ ምንጭ) :-የጉምሩክ መጋዘን አስተዳደር መመሪያ  ቁጥር 154/2011)
*************************************


በደንበኞች ትምህርት ቡድን የተዘጋጀ
ጥቅምት 19/2017 ዓ.ም
ጅግጅጋ, ኢትዮጵያ
*************************************

ለበለጠ መረጃ ፤ አሰተያየት እና ቅሬታ በታች ባለው ቁጥር ያሳወቁን፤ ይጠይቁን።
ቁጥር:
+251257757299
***********************

JIJIGA CUSTOMS COMMISSION BRANCH /በጉምሩክ ኮሚሽን የጅጅጋ ቅ/ጽ/ቤት

28 Oct, 07:57


ቀረጥና  ታክስ  ሳይከፈልበት  ወደ  አገር  ስለገባ  ዕቃ
***************
                            ***********************

(👉1) ከቀረጥና  ታክስ  ነፃ  ሆኖ  ወደ  አገር  የገባን  ዕቃ  ቀረጥና  ታክሱ  ሳይከፈልበት  ተመሳሳይ  የቀረጥ  ነፃ  መብት ለሌለው  ማንኛውም  ሰው  ማስተላለፍ  ወይም  የቀረጥ  ነፃ  መብት  ከተሰጠበት  ዓላማ  ውጪ  መገልገል ወይም  በሌሎች  ሰዎች  ይዞታና  አገልግሎት  እንዲውል  ማድረግ  የተከለከለ  ነው፡፡

(👉2) ከቀረጥና  ታክስ  ነፃ  ሆኖ  ወደ  አገር  የገባ  ዕቃ  ቀረጥና  ታክስ  ሳይከፈልበት  ተመልሶ  ከአገር  ሊወጣ  ወይም ተመሳሳይ  የቀረጥና  ታክስ  ነፃ  መብት  ላለው  ሰው  ሊተላለፍ  ወይም  ቀረጥና  ታክሱ  ተከፍሎበት  ለሌላ  ሰው ሊተላለፍ  ይችላል፡፡  ቀረጥና  ታክሱም  የሚሰላው  ዕቃው  በተላለፈበት  ጊዜ  በሚያወጣው  ዋጋና  ፀንቶ  ባለው የታሪፍ  ልክ  መሠረት  ይሆናል፡፡

(👉3) ቀረጥና  ታክስ  ሳይከፈልበት  ወደ  አገር  ውስጥ  የገባ  ዕቃ  የጠፋ  ወይም  ጉዳት  የደረሰበት  እንደሆነ አስመጪው  ለባለሥልጣኑ  ይህንኑ  ማሳወቅ  አለበት፡፡

(👉4) ለኢንቨስትመንት  ሥራ  የቀረጥና  ታክስ  ነፃ  መብት  የተሰጠው  ሰው  ከቀረጥና  ታክስ  ነፃ  ሆነው  የገቡ ዕቃዎችን  ለሌላ  ሰው  ሲያስተላልፍ  ወይም  የኢንቨስትመንት  ፈቃዱን  ሲመልስ  በቅድሚያ  ከኮሚሽኑ የተሰጠውን  የክሊራንስ  ሰነድ  የማቅረብ  ግዴታ  ይኖርበታል፡፡

(👉5) የሚመለከተው  ፈቃድ  ሰጪ  ወይም  መዝጋቢ  አካልም  ከላይ  በተራ  ቁጥር 4  ላይ  የተደነገገው  ሁኔታ መሟላቱን  የማረጋገጥ  እና  ክትትል  የሚያስፈልጋቸው  ሁኔታዎች  መኖራቸውን  እንዳወቀ  ለባለሥልጣኑ የማሳወቅ  ግዴታ  አለበት፡፡

(👉6) ቀረጥና  ታክስ  ሳይከፈልበት  ወደ  አገር  የገባን  ዕቃ  በዋስትና  ማስያዝ  የሚቻለው ከኮሚሽኑ  ጋር  በቀረጥና ታክሱ  አከፋፈል  ረገድ  ስምምነት  ላይ  ሲደረስ  ይሆናል፡፡

(👉7) የባለቤትነት  ስም  ዝውውር  የሚመዘግብ  ማናቸውም  አካል  ቀረጥና  ታክስ ያልተከፈለበትን ዕቃ  ሲመዘግብ ይህንኑ  በባለቤትነት  የምስክር  ወረቀት  ላይ  መግለጽ  ያለበት ሊሆን  ዕቃው  ለሦስተኛ  ወገን  በሚተላለፍበት  ጊዜ ቀረጥና ታክሱ  መከፈሉን  የማረጋገጥ  ግዴታ  አለበት፡፡ 

(የመረጃ ምንጭ) ፡- የጉምሩክ አዋጅ 859/2006
***************************************

በደንበኞች ትምህርት ቡድን የተዘጋጀ
ጥቅምት 18/2017 ዓ.ም
ጅግጅጋ, ኢትዮጵያ
***************************************

ለበለጠ መረጃ ፤ አሰተያየት እና ቅሬታ በታች ባለው ቁጥር ያሳወቁን፤ ይጠይቁን።


ቁጥር: +251257757299
***********************

JIJIGA CUSTOMS COMMISSION BRANCH /በጉምሩክ ኮሚሽን የጅጅጋ ቅ/ጽ/ቤት

22 Oct, 08:17


የጉምሩክ ሥነ-ሥርዓት የኤሌክትሮኒክስ መረጃ ልውውጥ አጠቃቀም ምንነትና የሚያሰፈልጉ መስፈርቶች
*************************
*************************

✍️በኤሌክትሮኒክስ ዘዴ የጉምሩክ መረጃ ልውውጥ ሥርዓት ማለት*******************************************
******
👉በጉምሩክ ሥነ-ሥርዓት አፈጻጸም መረጃዎች እና ሰነዶች በኤሌክትሮኒክስ ዘዴ የሚመዘገቡበትና የሚተላለፉበት ሥርዓት ነው።

👉ፈቃድ ማግኘት የሚችሉ ስዎች፦
***************************

(1) በኤሌክትሮኒክስ ዘዴ መረጃ ለማቅረብ ፈቃድ ማግኘት የሚችሉት የሚከተሉት ብቻ ናቸው፦
👍ሀ) አስመጪዎች/ላኪዎች
👍ለ) የጉምሩክ አስተላላፊዎች
👍ሐ) የዕቃ አስተላላፊዎች
👍መ) አጓጓዦች

(2) ከላይ የተደነገገው ቢኖርም ዓለም አቀፍ መንገደኞች ያለምንም ፈቃድ ኮሚሽኑ በሚያወጣው የአጠቃቀም መግለጫ መሰረት በድህረ-ገፅ አማካኝነት የግል መገልገያዎችን በተመለከተ የጉምሩክ ሥነ-ሥርዓት ለመፈጸም መረጃ ማቅረብ ይችላሉ።

👉ለአስመጪዎች እና ላኪዎች የሚሰጥ ፈቃድ መስፈርት፦
*********************************************

👉አንድ አስመጪ/ ላኪ በኤሌክትሮኒክስ ዘዴ የዕቃዎችን መረጃ እንዲያቀርብ ፈቃድ የሚሰጠው የሚከተሉትን መስፈርቶች አሟልቶ ሲገኝ ነው ፤
👍(1) የአስመጪነት/ የላኪነት የንግድ ፈቃድ፤
👍(2) በጉምሩክ አስተላላፊነት ሙያ የሰለጠነ እና የሙያ ማረጋገጫ ሰረቴፊኬት ያለው፤
👍(3) ኮሚሽኑ ተዘጋጅቶ የሚቀርብለትን አጠቃቀም ሥርዓት እና የደህንነት ውል ስምምነት ሲፈፅም፤
👍(4) ተጠቃሚው በሥርዓቱ ላይ ሥልጠና መውሰዱ ሲረጋገጥ

👉ለጉምሩክ አስተላላፊዎች የሚሰጥ ፈቃድ መስፈርት፦
*******************************************
👍(ሀ) የጉምሩክ አስተላላፊነት ፈቃድ ሲያሟላ፤
👍(ለ) በኮሚሽኑ ተዘጋጅቶ የሚቀርብለትን የአጠቃቀም ሥርዓት እና የድህንነት ውል ስምምነት ሲፈፅም፤
👍(ሐ) ተጠቃሚው በሥርዓቱ ላይ ሥልጠና መውሰዱ ሲረጋገጥ
👍(መ) የንግድ ፈቃድ ያለው ሲሆን ነው።

👉የዕቃ አስተላላፊዎች የሚሰጥ ፈቃድ መስፈርት፦
****************************************
👍(ሀ) የዕቃ አስተላላፊነት ፈቃድ ሲያሟላ፤
👍(ለ) የጉምሩክ አስተላላፊነት ፈቃድ ያለው፤
👍(ሐ) በኮሚሽኑ ተዘጋጅቶ የሚቀርብለትን የአጠቃቀም ሥርዓት እና የድህንነት ውል ስምምነት ሲፈፅም፤
👍(መ) ተጠቃሚው በሥርዓቱ ላይ ሥልጠና መውሰዱ ሲረጋገጥ፤
👍(ሠ) የንግድ ፈቃድ ያለው ሲሆን ነው።

👉ፈቃድ የሚሰጠውን ክፍል ሰለመወሰን፦
**********************************
(👍1) ማንኛውም ፈቃድ ጠያቂ በመመሪያው የተደነገገውን መስፈርት በማሟላት ጥያቄውን ለኮሚሽኑ የደንበኞች ትምህርትና ድጋፍ ዳይሬክቶሬት ያቀርባል፤
(👍2) ዳይሬክቶሬቱ የሚቀርብለትን ጥያቄ በመቀበል መስፈርቶቹ መሟላታቸውን አረጋግጦ ፈቃድ እንዲሰጥ ለመረጃ ቴክኖሎጂ ሰራ አመራር ዳይሬክቶሬት ያስተላልፋል፤
(👍3) የመረጃ ቴክኖሎጂ ሰራ አመራር ዳይሬክቶሬት የሚቀርብለትን ጥያቄ መሰረት በማድረግ ተጠቃሚው የመረጃ ቴክኖሎጂውን ለመጠቀም የሚያስችል የውል ግዴታ አስገብቶ ፈቃድ ይሰጣል።


**************************************
ምንጭ፦ የጉምሩክ ሥነ-ሥርዓት የኤሌክትሮኒክስ መረጃ ልውውጥ አጠቃቀም መመሪያ ቁጥር 155/2011
**************************************


በደንበኞች ትምህርት ቡድን የተዘጋጀ
ጥቅምት 12/2017 ዓ.ም
ጅግጅጋ, ኢትዮጵያ