ጥር 19/2017 ዓ.ም (የገቢዎች ሚኒስቴር)
የገቢዎች ሚኒስቴር ከክልል እና ከተማ አስተዳደር የገቢ ተቋማት ጋር በጋራ በመቀናጀት ወደ ስራ ያስገባው በQR ኮድ (በሚስጥራዊ መለያ) የተደገፈ የማንዋል ደረሰኝ ህትመት ከየካቲት 3/2017 ዓ.ም ጀምሮ ሙሉ ለሙሉ ተግባራዊ ይደረጋል፡፡
ስለሆነም በየደረጃው የምትገኙ ግብር ከፋዮች ግብር ለምትከፍሉበት ቅ/ፅ/ቤት ወይም ታክስ ማዕከል ተገቢውን የደረሰኝ ህትመት ጥያቄ በማቅረብ በQR ኮድ የተደገፈ ደረሰኝ ከብርሃን እና ሰላም ማተሚያ ድርጅት ብቻ የጊዜ ገደቡ ከመጠናቀቁ በፊት እንድታሳትሙ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡
ከዚህ በፊት ባለው አሰራር አሳትማችሁ ነገር ግን ያልተጠቀማችሁበት የማንዋል ደረሰኝ ካለ ቁጥሩን በመግልፅ ለቅ/ፅ/ቤታችሁ እንድትመልሱ እናሳስባለን፡፡
ሙሉ መልዕክቱ፥ የገቢዎች ሚኒስቴር ነው
#Ethiopiatax #ግብር #ታክስ