Eritrean Press-Amharic @eritreanpressamharic Channel on Telegram

Eritrean Press-Amharic

@eritreanpressamharic


ኤርትራና ኢትዮጵያ ጎረቤት ብቻ ሳንሆን ከአንድ አብራክ የወጣን በደምና ስጋ የተዋሀድን ነን🇪🇷❤️🇪🇹

Eritrean Press-Amharic (Amharic)

ኤርትራና ኢትዮጵያ ጎረቤት ብቻ ሳንሆን ከአንድ አብራክ የወጣን በደምና ስጋ የተዋሀድን ነን! ይህ ታሪካዊ መረጃ የሚገኝበት የኤርትራና ኢትዮጵያ ጎረቤት ነው። በይህ ጎረቤት ለኤርትራና ኢትዮጵያ በነጻ ተገኝቷል። የሚያስችል መረጃም በነባሪው አፖቃን የሚገኙትን የኢትዮጵያውያን ታሪካዎችን ጎረቤታል። ብሏት መንግስት፣ ታሪካዎችና ታርክ ወይም አስተዳደር ተቃውሞ በወሬ በካሳ ሕብረተ ቁምተኛዎች፣ የሰው ልጅሽ መርከብ እና ሩብ ሇንሽን እንደ አከባቢክ እና አገላላዩ በመላክ ለኤርትራና ኢትዮጵያ ብሳጥም በከፍተኛ እና ልባችን ጎረቤታል።

Eritrean Press-Amharic

10 Nov, 19:05


የሶማሊያው ፕሬዝዳንት በወራት ውስጥ ለሁለተኛ ጊዜ ለጉብኝት አሥመራ ገቡ

ባለፈው ዓመት ግንቦት በተደረገው ምርጫ ወደ ሥልጣን የመጡት የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ሞሐሙድ ለአራት ቀናት ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ኤርትራ ገቡ።

ሐሰን ሼክ ሞሐሙድ ከልዑክ ቡድናቸው ጋር አሥመራ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርሱ በፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ አቀባበል እንደተደረገላቸው የኤርትራ ማስታወቂያ ሚኒስትር የማነ ገ/መስቀል በትዊተር ገጻቸው አስታውቀዋል።

ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ወደ ሥልጣን ከመጡ ወዲህ ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት በቀጠናው ወደሚገኙ አገራት የተጓዙ ሲሆን፤ ወደ ኤርትራ ሲያቀኑ ግን በጥቂት ወራት ውስጥ ለሁለተኛ ጊዜ መሆኑ ነው።

የኤርትራው የማስታወቂያ ሚኒስትር እንዳሉት፤ ፕሬዝዳንቱ ኤርትራ የተገኙት “ለሥራ ጉብኝት ነው” ከማለት ውጪ ሐሰን ሼክ መሐሙድ በአሥመራ ቆይታቸው ስለሚያከናውኗቸው ጉዳዮች ያሉት ነገር የለም።

ይሁን እንጂ በኤርትራ የሚገኙት የሶማሊያ ወታደሮች ጉዳይ የፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ የጉዞ አጀንዳ ሊሆን እንደሚችል ይገመታል።

ፕሬዝዳንቱ ሐምሌ 2014 ዓ.ም. ወደ አሥመራ ባቀኑበት ወቅት በኤርትራ ሥልጠና ላይ የነበሩ በሺዎች የሚቆጠሩ የሶማሊያ ወታደሮች የምረቃ ሥነ ሥርዓት ላይ መገኘታቸው ይታወሳል።

የኤርትራ መንግሥት ሐምሌ 03/2014 ዓ.ም. ለሦስት ዓመታት ወታደራዊ ሥልጠና ሲወስዱ የነበሩት የሶማሊያ ወታደሮች ፕሬዝዳንቱ በተገኙበት ተመርቀዋል ብሎ ነበር።

እነዚህ ላለፉት ዓመታት በሶማሊያ ፖለቲካ ውስጥ አወዛጋቢ ሆኖ የቆዩትና በኤርትራ የሚገኙ የሶማሊያ ወታደሮች ጉዳይ የፕሬዝዳንቱን ጉዞ ተከትሎ ተመርቀዋል ይባል እንጂ የት እና በምን ሁኔታ ኤርትራ ውስጥ እንደቆዩ ግልጽ ሳይሆን ቆይቷል።

ወታደሮቹ በቀድሞ የሶማሊያ ፕሬዝዳንት አብዱላሂ ፋርማጆ አስተዳደር ወቅት ወደ ኤርትራ እንደተላኩ የሚታመን ሲሆን፤ የፋርማጆ ተቀናቃኞች ፕሬዝዳንቱ ወታደሮቹን ወዳልታወቀ ስፍራ ልከው በጦርነት ውስጥ እንዲሳተፉ አድርገዋል ሲሉ ሲወቅሷቸው ነበር።

ወታደሮቹን በተመለከተ ከሚያወዛግቡ ጉዳዮች መካከል አንዱ፤ የጦሩ አባላት በሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት ከኤርትራ እና ከኢትዮጵያ ፌደራል መንግሥት ጋር ወግነው የትግራይ ኃይሎችን ወግተዋል የሚለው ይገኝበታል።

የሶማሊያ ወታደሮች በኤርትራ ስለመገኘትም ሆነ በሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት መሳተፋቸውን በተመለከተ የሞቃዲሾ መንግሥት አንዳንዴ ዝምታን ሲመርጥ ሌላ ጊዜ ደግሞ የሚቀርብበትን ክስ ሲያስተባብል ቆይቷል።

የወታደሮቹ ቤተሰብ አባላትም የልጆቻቸውን አድራሻ በመጠየቅ በሶማሊያ ጎዳናዎች ላይ ለተቃውሞ አደባባይ መውጣታቸው ይታወሳል።

ወታደሮቹን በተመለከተ ይፋዊ ምላሽ ከመግሥት ከተሰጠባቸው አጋጣሚዎቹ አንዱ ሞሐመድ አብዱላሂ ፋርማጆ በምርጫ መሸነፋቸውን ተከትሎ ሥልጣን ባስረከቡበት ወቅት የሰጡት ማረጋገጫ ይጠቀሳል።

ፋርማጆ በወቅቱ አምስት ሺህ የሶማሊያ መንግሥት ወታደሮች ኤርትራ ውስጥ ሥልጠና እየወሰዱ እንደሚገኙ ይፋ ያደረጉ ሲሆን፣ ምርጫው በተቃረበበት ጊዜ ፖለቲካዊ ተጽዕኖ እንዳይኖራቸው ባሉበት እንዲቆዩ መደረጉን አሳውቀው ነበር።

ከዚህ በኋላ አዲሱ ተመራጭ ፕሬዝዳንት ወደ ኤርትራ አቅንተው በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ በወታደሮቹ መካከል ሆነው ታይተዋል።

በወቅቱም ምን ያህል የሶማሊያ ወታደሮች ሥልጠናቸውን እንዳጠናቀቁ፣ ምን አይነት ሥልጠናዎችን እንደወሰዱ፣ ሶማሊያውያኑ ወደ ኤርትራ መቼ እንደገቡም ሆነ መቼ ወደ ትውልድ አገራቸው እንደሚመለሱ የተገለጸ ነገር አልነበረም።

ነገር ግን የሁለቱ አገራት መሪዎች ወታደሮቹ ወደ ሶማሊያ በሚመለሱበት ሁኔታ ላይ ተነጋግረው መስማማታቸው ተገልጾ ነበር።

Eritrean Press-Amharic

23 Oct, 16:45


ኤርትራ እና ኢትዮጵያ የእድገት መንገዳችን ላይ የተደቀኑትን እንቅፋቶችን አስወግደን ተያይዘን ፊታችን ወደ ልማት በማዞር በአፍሪካ ህዝባቸው የተሻለ ኑሮ የሚኖርባቸውን ሀገራት እንፈጥራለን | Eritrea 🇪🇷 | Ethiopia 🇪🇹

የቴሌግራም ቻናላችኝ t.me/eritreanpressamharic

Eritrean Press-Amharic

22 Sep, 17:24


በትግራይ ክልል የእርዳታ እህል በህወሓት ሃይሎች በመዘረፉ ሁሉም በሚባል መልኩ የእህል መጋዘኖች ባዶ መሆናቸው አንድ የእርዳታ ድርጅት ተናግረዋል። ህወሃት አሁንም በፌዴራል መንግስት ላይ ጦርነት በመክፈት መንገዶችን በመዝጋት ለትግራይ ህዝብ የሚሄደው የሰብዓዊ እርዳታ እንዲቋረጥ አድርጓል።

Eritrean Press-Amharic

21 Sep, 15:35


ፕሬዝደንት ኢሳያስ ለ Eri Tv  መግለጫ ሰጥተዋል በመግለጫቸው ምን አሉ?

ክፍል-1

1- ምስራቅ አፍሪካን በተመለከተ

ፕ/ኢሳያስ እንዳሉት " የኢትዮዽያ ሰላም እና አንድነት ለመላው አፍሪካ በተለይም ለምስራቅ አፍሪካ ቀጠና ወሳኝ ነው። የቀጠናው ስጋት የሆኑት የህወሃት፣ የኦነግ እና የአልሸባብ የሽብር ቡድኖች አንድነት እንዲፈጥሩ ያስገደዳቸው የጋራ አጀንዳ ኢትዮዽያን ማፍረስ የሆነበት ምክንያትም ኢትዮዽያ የቀጠናው ዋልታ ስለሆነች ነው።"

2- ምዕራባውያንን እና ሕወሃትን በተመለከተ

"አሜሪካና አውሮፓ ሁልጊዜም ቢሆን አጀንዳቸው የራሳቸው ብሄራዊ ጥቅም ነው። የእነርሱን ብሄራዊ ጥቅም የሚያስጠብቅ አጎብዳጅ ቡድን ከሆነ እንኳንስ ህወሃት በእነርሱ ም/ቤት #አሸባሪ ብለው የፈረጁት  አልሻባብም ሆነ አልቃዒዳ የእነርሱ ወዳጅ ነው።

አሜሪካና አውሮፓ በየትኛውም የአለም ሃገር አጎብዳጅ መንግስት በመመስረት እየጋለቡት እነርሱ ጥቅም ላይ እንዲያደርሳቸው የማይፈነቅሉት ዲንጋይ አይኖርም። በተመሳሳይ ለእነርሱ የማያጎበድድ መንግስት ያለውን ማንኛውንም የአለም ሀገር በማእቀብ በማሽመድመድ፣ ሰብአዊ እርዳታ ሳይቀር ማንኛውንም እርዳታ በመከልከል...ወዘተ እኩይ ተግባራት ላይ ይጠመዳሉ።

አሁን የምንመለከተው ኢትዮዽያ ላይ እየፈፀሙት ያለው ተጽእኖም ለእኩይ ተግባራቸው ዋና ምሳሌ ነው። በኢትዮዽያ ህዝብ ጫንቃ ላይ ለ27 አመታት ተኮፍሶ የምእራባውያንን እኩይ ተልእኮ ሲያስፈጽም የነበረው የትህነግ ሽብር ቡድን ተገርስሶ አሁን ያለው የዶ/ር አብይ መንግስት ወደ ስልጣን ሲመጣና በህወሃት የለመዱትና ጠብቀውት የነበረው አጎብዳጅነት ህልም ሆኖ ሲቀርባቸው፣ ትናንት የህወሃትን መውደቅ ውጤታማ እንዳላደረጉት ሁሉ በውሳኔያቸው ተፀፅተው ከሽብር ቡድኑ ፊት ቀድመው በመሰለፍ የዶ/ር አብይን መንግስት በኢትዮዽያ ህዝብ ውሳኔ ወደ ስልጣን ከነመምጣቱ ረሱት።

ምዕራባውያን ለዚያ ነው እንግዲህ በኢትዮጵያ ህዝብ ተወካዮች ም/ቤት #አሸባሪ ተብለው የተፈረጁትን የሕወሃት እና የኦነግ ሽብር ቡድኖችን አጥብቀው በመደገፍ አሁን ያለውን ጠንካራ እና የአጎብዳጅነት መንፈስ የሌለውን ቆራጡን የኢትዮዽያ መንግስት እጁን ጠምዝዘው ፈረሳቸው ለማድረግ ወይም የሽብር ቡድኑን በመደገፍ ዳግም ወደ ስልጣን ለማምጣት አሊያ ደግሞ የዶ/ር አብይን መንግስት ጥለው እንደፈለጉት የሚጋልቡትን አዲስ መንግስት ወደ ስልጣን ለማምጣት እየደከሙ የሚገኙት።

...........ይቀጥላል

Eritrean Press-Amharic

20 Sep, 18:06


ፕሬዝደንት ኢሳያስ አሜሪካን እና አሸባሪውን ህወሃት የተመለከተ ዛሬ ለEri Tv መግለጫ ሰጥተዋል።

እኛም ሙሉ መግለጫውን በነገው እለት በቴሌግራም ቻናላችን እናቀርበዋለን።

Telegram ቻናላችንን #Subscribe በማድረግ ይጠብቁን

👉ቴሌግራም t.me/eritreanpressamharic

Eritrean Press-Amharic

20 Sep, 16:31


ለ ጀግኖቹ | 💚❤️💙
ለኤርትራ ብስክሌት ተወዳዳሪ ቡድናችን ላይክና ሼር በማድረግ ፍቅር አሳዩልን።

Eritrean Press-Amharic

17 Sep, 13:04


የኤርትራ መከላከያ ሰራዊት አዛዥ ጄ/ፊሊፖስ ወ/ዮሐንስ አዲስ የተገነባውን የምጽዋ ድሮን ስቴሽን መርቀው ከፍተዋል!

ኤርትራ ከሩስያ መንግስት የተደረገላትን 12 ድሮኖችን ( የውጊያ እና የቅኝት ሰው አልባ በራሪ ኤሮ-ፕሌኖች) በመቀበል በምስራቅ አፍሪካ የተሟላ ጦር ኃይል እንድትገነባ አስችሏታል።

ይህንን ተከትሎ ኤርትራ ከተባበሩት አረብ ኢሜሬትስ በተደረገላት የገንዘብ ድጋፍ የድሮን ስቴሽን (የድሮን ማረፊያ እና ማዘዣ ጣቢያ) በምጽዋ ገንብታ ሙሉ አገልግሎት እንዲሰጥ ዛሬ በኤርትራ ጦር ጠቅላይ አዛዥ በጄኔራል ፊሊፖስ ወ/ዮሐንስ ተመርቆ ተከፍቷል።

የተባበሩት አረብ ኢሜሬትስ ከዚህ በተጨማሪም 32(ሰላሳ ሁለት) ኤርትራውያንን ሙሉ ልጫቸውን በመሸፈን በድሮን ቴክኖሎጂ የ9 ወራት ስልጠና በውጭ ሐገር እንዲከታተሉ በማድረግ ድጋፍ ማድረጓም ተገልጿል።

ስቴሽኑን መርቀው የከፈቱት ጄኔራል ፊሊፖስ እንደተናገሩት "ኤርትራ በምስራቅ አፍሪካ ቁጥር አንድ የሆነ የተሟላ የመከላከያ ኃይል ገንብታለች" ብለዋል።

ከፌስቡክ በተጨማሪ
በቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/eritreanpressamharic

Eritrean Press-Amharic

15 Sep, 15:23


የህወሃት ጄኔራሎች ስሙ ሲነሳ የሚርበተበቱለት ቆፍጣናው ብ/ጄ ሓዲሽ ኤፍሬም #3

በጨረፍታ ያየነው ሰውዬ በሚያውቁት ሰዎች ትረካው ቀጥሏል፡፡ እንደውም  ሰለ ጀግኖቻችን ውሎ  የምናወሳበት በፌስ ቡክ ''የጀግኖች ወግ'' እንክፈት እየተባለ ነው፡፡በኢትዮጵያ ቴሌቭዥን ስብሃት ጦጢት  ሲያዝ  በጨረፍታ ካየነው ግዜ ጀምሮ ማነው? ምንድነው? ወዴት ነው? የሚሉ ጥያቄዎችን ለመመለስ ከታተሩት ሰዎች መሃል ማርታ ሰለሞን፡ አንዱን ቀን፡''ንሽቴ ይህን ሰው የምታውቁት እስቲ ንገሩን ብላ የአፋልጉኝ አይነት ማስታወቂያ ከፎቶው ጋር አያይዛ ለጠፈች፡፡ ሞቅ ያለ ክርክር ተከተለ፡፡

"ይህን መሳይ ጀ ግ ና  እንዲህ ፌስ ቡክ ላይ የምታሰጡት ለምንድ ነው? ብለው የተቆጡም ነበሩ፡፡፡ እንዴ! ጎረቤት አገር በቲቪ መስኮት አየነዋ! ማንነቱን ብናውቅ ምን ችግር አለው?  አለማወቅ እንጂ መጥፎ የዘመኑን የምስራቅ አፍሪካን አሸባሪ ወገብ ዛላውን የሰበረውንማ እንወቀው እንጂ!  ይልቁንስ የምታውቁት ካላችሁ ወጋችሁን ቀጥሉ እየተባለ አስተያየትና ክርክር  ጎረፈ፡፡ ሌላው ይነሳና ደሞ፡
''እናንተ! ምን ልሁን ብላችሁ ነው በባህላችን የሌለ ነገር የምትዘባርቁት! እኔስ ለምንድነው አስሬ የሚያነሱት ብዬ ገርሞኝ ነበር ስራ ፈቶች!''  ያለም አይጠፋ!

ለነገሩ አንዳንድ ቦታ ''ጁንታን ያደቀቃት ጀ ግ ና'' እየተባለ በደፈናው ብቅ  ያደርጉት ነበር፡፡ ለካንስ በሆዱ የያዘውን ይዞ በዝምታ የሚታዘብ  ነበርና የማርታን ቤት በዚህ ጀግና ውሎ ያላቸውን አካፈሉን፡፡ ማርታ ሰለሞን ለከፈትሽው በርና አስተያየት የሰጣችሁ በሙሉ ከወዲሁ ምስጋና ይድረሳችሁ፡፡ ወደፊትም ''የጀግኖች ወግ'' እንድንቀጥል ብዙዎች ተስማምተዋልና ሁላችሁም ተሳትፏችሁ አይለየን እንላለን፡፡ ወጉ ሲቀጥል፡

ብ/ጄ ሓዲሽ ኤፍሬም፡ በራሱ እንደ ተራራ የቆመ ገድል ነው፡፡ ለምንም ነገር ቁብ የማይሰጠው፡ በሃገሩ ፍቅር ብቻ የነደደ የህዝባዊ ግንባር አባል ነው፡፡ የሚፈጥረው የውግያ ቅድ፡ ከበሳል አይምሮው የሚቀዳ፡ ትልቋ ሳህል ካፈራቻቸው ልጆች መሃል ቀዳሚውን የሚይዝ የአምበሶች አምበሳ ነው፡፡ በ1997 ከወያኔ ጋር በዋለው ጦርነት፡ ለዘር እንኳ ሳያስተርፍ በሙሉ ሲደመስ ሳቸው፡ በሌላ ግዜ ደሞ 2000 ከሚሆኑት ላይ 3 አስቀርቷል፡፡ የሱ ሰራዊት በቁጥር 100 ሲሆኑ 5 ተሰውተዋል፡፡ የውግያ ቅዱ" አንድ ሳላስተርፍ ልላስ" ሲሆን የፈረደባት ወያኔ በአዲሱ ስሟ ጁንታ ከተባለች በኋላ 2020 ላይ እንደገና አግኝቶ አልማራትም፡፡ እንደጨው አሟሟት፡፡ከኢፌዲሪ ሰራዊት ጎን ሆኖ በሚዋጋበት ሜዳ ''ሰው ይሁን አቦሸማኔ ያልታውቀ ጉዳይ ነው፡፡'' ሲሉት፡፡ ሰራዊቱ እየተወረወረ እንደ እባብ እየተጠመጠመባቸው ሲያዩ፡ እነዚህ ፍጥረታት የሰው ይሁኑ የሌላ አለየም፡፡ ብለው አግራሞታቸውን ገልጸዋል፡፡
ከህዝባዊ ግንባር መድህን ሃገር፡ የተገኘ

ማርቲ! እስኪ ከሚያውቁት ሰዎች የሰማሁትን ላካፍልሽ! ብ/ጄ ሓዲሽ ኤፍሬም፡ከነጻነት ትግል ጀምሮ የተዋጋና ያዋጋ ከፍተኛ ዲሲፕሊን ያለው ወታደር ነው፡፡ጓዶቹኑና ሰራዊቱን በጣም የሚሳሳላቸውና የሚያፈቅራቸው ከመሆኑ የተነሳ፡ ወደኋላ ትቷቸው ቤተሰብ ጥየቃ እንኳ አይወጣም፡፡ ሚስትም ልጆችም ሃገር ስትኖር ነው ይላል፡፡ የራሴ የሚለው ነገር የለውም፡፡ ከራሱ ፍላጎት በፊት የአገሩንና የሰራዊቱ ፍላጎት ቢያሟላ ይመርጣል፡፡ በደረጃው ልክ የመንግስት ንብረት አይጠቀምም፡፡ በሃገር ፍቅር የነደደ ወደር የማይገኝለት ንቁ ዜጋ ነው፡፡ከነጻነት በኋላም ቢሆን፡ አገሩን፤ መንግስቱን፤ ሃገሩን በታላቅ ዲሲፕሊን ይህ ቀረው የማይባልለት አገልግሎት ሲሰጥ ነው የነበረው፡፡ በቀዝቃዛው ጦርነት ግዜ ሰራዊቱን አስተባብሮ የውሃ ግድብ በመስራት ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይል ላቡን ያንጠፈጠፈ ስራ ወዳድ ነው፡፡

ከ22 አመታት በፊት የወያኔ ሰራዊት በአእላፍ  ተዘጋጅተው ሳለ፡ የተኩስ አቁም ስምምነት ተደርጓልና ከምሽግ ወጥታችሁ ወደኋላ አፈግፍጉ የሚል ትእአዝ ሲመጣ፡፡ ሬሳዬንና የሰራዊቴን ሬሳ አልፋችሁ ትሄዳላችሁ እንጂ አለቅም ብሎ አሻፈረኝ ስላለ እውነትም አታላ መግባት የፈለገችውን ወያኔ የአሞራ ሲሳይ አድርጎ  የቡሬን ግንባር ድል ከሞት አፋፍ አውጥቶ ወደብና መሬታችንን ያዳነ ቃላት የማይገልጹት ጀግና ነው፡፡ እድሜና ጤና ይሰጠው፡፡
መሓሪ ጸጋይ

የተረካችሁልን ሁሉ ድጋሚ ምስጋና ይድረሳችሁ፡፡ የብ/ጄ ሓዲሽ ''የጀግኖች ወግ'' በዚህ ይደመደማል፡፡ ማርታ ትብብሯን ትቀጥልና የሚቀጥለውን ጀግና መርጠን  እናውጋ!

ክብር የኤሪትርያ ዲፌንስ ፎርስ! ዓወት ንሓፋሽ!

Eritrean Press-Amharic

15 Sep, 14:46


🇪🇷የኤርትራ ጥንካሬ የኢትዮጵያ🇪🇹

🇪🇹የኢትዮጵያ ጥንካሬ የኤርትራ 🇪🇷

የሁለቱ ወንድማማች ሀገር ጥንካሬ ከኢትዮ ኤርትራ ሉዓላዊነት በላይ ለምስራቅ አፍሪካ ሰላም ትልቅ ሚና ይጫወታል የምዕራቡን አለም ተልዕኮ እየቀበለ ለማበጣበጥ የሚንቀሳቀሱ ሃይሎች ከየትኛውም እንቅስቃሴ ሊታቀብ የሚችለው እኛ ስንጠነክር ነው።