Harari Government Communication Affairs Office

@hararigovernmentcommunication


Harari Government Communication Affairs Office

22 Oct, 15:15


በሐረሪ ክልል መኸር እርሻ እስካሁን 11 ሺህ 774 ሄክታር መሬት በዘር ተሸፍኗል

በሐረሪ ክልል የመኸር እርሻ ወቅት እስካሁን 11 ሺህ 774 ሄክታር መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ግብርና ልማት ቢሮ አስታወቀ።

የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ልማት ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሮዛ ኡመር እንደገለፁት በክልሉ በተለይም በአሁኑ ወቅት ፆም ሲያድር የቆየ መሬት ጥቅም ላይ እንዲውል በማድረግ ጭምር ምርታማነትን በማሳደግ ከተረጂነት ለመላቀቅ በቁርጠኝነት እየተሰራ ይገኛል።

ለዚህም የማዳበሪያ፣ የዘርና ሌሎች የግብርና ግብዓት አቅርቦት በማሟላት የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት የማሳደግ ስራ በተጠናከረ መልኩ መቀጠሉን ተናግረዋል።

በየደረጃው ያሉ የግብርና ባለሙያዎችም ለአርሶ አደሩ አስፈላጊውን ሙያዊ እገዛና ድጋፍ እያደረጉ መሆኑን ገልፀዋል።

በዚህም አርሶ አደሩን ከዝናብ ጠባቂነት ከማላቀቅና ተጠቃሚነትን ከማሳደግ አንፃር አበረታች ስራዎች ተከናውነዋል ብለዋል።

በክልሉ በተለይም ለስንዴ፣ ለማሽላ ፣ ለአትክልትና ፍራፍሬ ልዩ ትኩረት በመስጠት በክላስተር እየለማ መሆኑንም ጠቅሰዋል።

አርሶ አደሩ እያከናወናቸው ባሉ የተቀናጀ የግብርና ልማት ስራዎች ምርታማነትን በማሳደግ የከተማውን ህዝብ የኑሮ ውድነት ጫና ለመቀነስ ፋይዳው የላቀ ስለመሆኑ ጠቁመዋል።

በክልሉ መኸር እርሻ እስካሁን 11 ሺህ 774 ሄክታር መሬት በዘር መሸፈኑን ጠቅሰው በማሳያነትም 450 ሄክታር መሬት በስንዴ እንዲሁም 800 ሄክታር መሬት በአጭር ግዜ ምርት በሚሰጥ የማሽላ ኢንሼቲቭ መሸፈኑን ገልፀዋል።

በቀጣይም የተገኙ አበረታች ውጤቶችን በማስቀጠል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማጎልበትና ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ የላቀ ትኩረት እንደሚሰጥ አመላክተዋል።

Harari Government Communication Affairs Office

21 Oct, 10:42


"የታላቁ የህዳሴ ግድብ የብልፅግና ጉዟችንን የሚያፋጥን በሕዳሴ ምዕራፍ ውስጥ የሚደምቅ የሀገራችን ብርሃን ነው":- አቶ ሔኖክ ሙሉነህ

ሀረር ጥቅምት 11/2017(ሀኮመኮ):-በሐረሪ ክልል በተያዘው 2017 በጀት ዓመት ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ድጋፍ የሚውል 15 ሚሊዮን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን የክልሉ የታላቁ ህዳሴ ግድብ ህዝባዊ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት አስታወቀ።

የክልሉ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤትና በክልሉ የታላቁ ህዳሴ ግድብ ህዝባዊ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሔኖክ ሙሉነህ እንደገለጹት፤ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ በመላው ኢትዮጵያውያን ዕውቀት፣ ሀብትና ጉልበት እየተገነባ የሚገኝ ግዙፍ ፕሮጀክት ነው።

ፕሮጀክቱ የብልፅግና ጉዟችንን የሚያፋጥን በሕዳሴ ምዕራፍ ውስጥ የሚደምቅ የሀገራችን ብርሃን ነው ብለዋል።

የክልሉ ህዝብም ባለፉት ዓመታት በዕውቀት፣ በጉልበትና በገንዘብ ድጋፍ በማድረግ ለግድቡ ስኬታማነት የበኩሉን እየተወጣ ይገኛል ሲሉ ተናግረዋል።

በተያዘው በጀት ዓመትም በክልሉ የሚገኙ መላው ህብረተሰብን በማሳተፍ ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ 15 ሚሊዮን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አቶ ሄኖክ አስታውቀዋል።

በክልሉ ለግድቡ ግንባታ ድጋፍ እንዲውል የተያዘው እቅድ ስኬታማ እንዲሆን በክልሉ ሁሉም ወረዳዎች የውይይት እና የህዝብ ንቅናቄ የመፍጠር ስራዎች እንደሚከናወኑ ገልጸዋል።

የክልሉ ህዝብ ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ስኬታማነት እያከናወኑ የሚገኘውን የድጋፍ ስራዎችን አጠናክረው እንዲቀጥሉም አቶ ሄኖክ ጥሪ አቅርበዋል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

👉 ድረ ገጽ፦ https://hararigovcommunication.et/
👉 ቴሌግራም :-https://t.me/HarariGovernmentCommunication
👉 ፌስቡክhttps://www.facebook.com/profile.php?id=100064845514191&mibextid=ZbWKwL
👉ቲውተር :- https://twitter.com
👉 ዩትዩብ፦https://youtube.com
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን

Harari Government Communication Affairs Office

20 Oct, 16:53


ለኮሪደር ልማቱ ውጤታማነት ድጋፋቸውን እንደሚያጠናክሩ በሀረሪ ክልል የተለያዩ የገጠር ወረዳዎች የሚገኙ ነዋሪዎች ተናገሩ

በሀረሪ ክልል የተጀመረው የገጠር ኮሪደር ልማት ውጤታማ እንዲሆን ድጋፋቸውን እንደሚያጠናክሩ የአካባቢው ነዋሪዎች ተናግረዋል።

ነዋሪዎቹ በሰጡት አስተያየት የኮሪደር ልማት ስራው ዜጎች የተሻለ አካባቢን በመፍጠር ረገድ አስተዋጽኦ የላቀ ነው ብለዋል።

በተለይም በገጠሩ አካባቢ የሚከናወኑ የኮሪደር ልማት ስራዎች አርሶ አደሩን የአኗኗር ዘዬ እንዲቀየር ሚናው የላቀ መሆኑን ጠቁመዋል።

የኮሪደር ልማቱ በተለይም በገጠሩ አካባቢ የመንገድ መሰረተ ልማት እንዲሟላ በማስቻል አርሶ አደሩ ምርቱን ከእንግልት ነፃ በሆነ መልኩ ወደ ገበያ እንዲያቀርብ ያግዛል ሲሉ ተናግረዋል።

ከዚህ በተጨማሪም ሰፋፊ የእግረኛ መንገድ እንዲኖር በማድረግ የትራፊቅ አደጋ እንዲቀንስ እገዛ ያደርጋልም ብለዋል።

ለኮሪደር ልማቱ አስፈላጊውን ድጋፍ እያደረጉ መሆኑን ጠቁመው በቀጣይም ለስኬታማነቱ ድጋፋቸውን እንደሚያጠናክሩ ገልፀዋል።

በክልሉ በሚገኙ ሦስት የገጠር ወረዳዎች አዳዲስ የገጠር ኮሪደር ልማት ስራዎች በመከናወን ላይ እንደሚገኙ ይታወሳል።

Harari Government Communication Affairs Office

20 Oct, 16:52


ኮሪደር ኔሮት ነቲጃምነትሌ ተዓወኖት ሞሸቤ ዚገረብዚዩ  አታጮቱ ያሽዛሉነቱ ደርጋ ወረዳ ነባሪያች አሴነኑ

ሀረሪ ሁስኒቤ ዚትኤገላ ኮሪደር ኔሮት ነቲጃምነትሌ ተዓወኖት ሞሸቤ ዚገረብዚዩ አታጮቱ ያሽዛሉነቱ ደርጋ ወረዳ ነባሪያች አሴነኑ

ነባሪያችዞ ዚሰጦ ራእዪቤ ኮሪደር ኔሮት ዲላጋ መደኒያችሌ ዚጦኛ ሺርቲው መኽለቅቤ አታጮትዞ ላቂ መኽነዞው አሴነኑ።

ሉይቤም ደርጋ ሺርቲቤ ዪትሜሀርዛል ኮሪደር ኔሮት  ዲላጋ ሀራሺዞ ኒብሪ ሀለቱ መናወጥቤ ላቂ ፋይዳ ዛላነቱ አቀነኡ።

ዩቤ ዲባያም ደርጋ ሺርቲያችቤ ኡጋ አሳሲያ ኔሮት ዪትማለዒኩት ሞኘቤ ሀራሺዞ ኦሚሽዞው ተዓብ ቢላይ መጋላ የቀርቢኩታ ጊርጋራ ያሻል ባይቲቤም ገለጡ።

ዲባየቤም ዘጋህ ዋ ሙች ኢጊር ኡጋች ዪነብሪኩት ሞሸቤ ትራፊክ ቂፊኝኛው መናቀስሌ ያትፊርኪዛል ኢንታም ባዩ።

ኮሪደር ኔሮትዞሌ አትኼሽ ተአወኖት ሞሸቤ ዛሉነቱ መቄቀልቤ ኪል ኤቀዱም ኮሪደር ኔሮትዞ ዪነጅሂኩታ ተአወኖትዚዩው ዚቅቲቤ ያሊጥቦዛልነቱ አትቴወቁ።

ሁስኒዞቤ ዪትረኸብዛሉ 3 ደርጋ ወረዳችቤ ሀጂስ ኮሪደር ኔሮት ዲላጋች መትሜሀርቤ ዪትረኸባሉ።

Harari Government Communication Affairs Office

20 Oct, 16:51


Bu'a qabeessummaa misooma koridariif deeggarsa isaanii cimsinii akka itti fufan jiraattoonni aanoolee baadiyaa Naannoo Hararii ibsan.

Bu'a qabeessummaa hojii misooma kooridarii naannoo Harariitti eegalameef deeggarsa  isaanii cimsinii akka itti fufan jiraattonni naannichaa ibsan.

Jiraattoonni kunneen akka jedhanitti, misoomni kooridarii haala jireenya lammiilee fooyyaa'aa uumuu keessatti gumaacha guddaa akka qabu ibsaniiru.

Haala jireenya qonnaan bultootaa jijjiiruuf gaheen misooma kooridarii baadiyaa qabu olaanaa ta’uu hubachiisaniiru.

Keessattuu baadiyaatti misoomni kooridarii  qonnaan bultoonni oomisha isaanii rakkoo tokko malee gabaaf dhiyeessuuf kan gargaaru ta’uu ibsaniiru.

Kanaan alatti daandii imaltootaa mijjachuu fi  balaa tiraafikaa hir’isuuf ni gargaara jedhaniiru.

Misooma kooridarii kanaaf deeggarsa barbaachisu gochaa akka jiran eeruun milkaa’ina isaaf deeggarsa taasisaa jiran cimsanii akka itti fufan ibsaniiru.

Naannichatti aanaalee baadiyaa sadeen keessattuu hojiiwwan misooma kooridarii haaraan hojjetamaa jira.

Harari Government Communication Affairs Office

20 Oct, 12:49


የማህበረሰቡ ትብብር ለኮሪደር ልማቱ ምቹ ሁኔታን ፈጥሯል-አቶ ሙክታር ሳሊህ

ሀረር ጥቅምት 10/2017(ሀኮመኮ):-ማህበረሰቡ እያደረገው ያለው ትብብር ለኮርደር ልማቱ ምቹ ሁኔታን መፍጠሩን በምክትል ርዕሰ መስተዳድር መዓረግ የሀረሪ ክልል ከተማ ልማት እና ኮንስትራክሽን ቢሮ ሀላፊ አቶ ሙክታር ሳሊህ ገለፁ።

በሀረሪ ክልል በሚገኙ ወረዳዎች ገቢራዊ እየሆነ የሚገኘው የኮሪደር ልማት አፈፃፀም በዛሬው ዕለት ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።

በምክትል ርዕሰ መስተዳድር መዓረግ የሀረሪ ክልል ከተማ ልማት እና ኮንስትራክሽን ቢሮ ሀላፊ አቶ ሙክታር ሳሊህ በውይይቱ ላይ እንደገለፁት በሁሉም ወረዳዎች የኮሪደር ልማቱ የወሰን ማስከበር ስራ በጥሩ ደረጃ ላይ ይገኛል።

ማህበረሰቡ የኮሪደር ልማቱ የሚያስገኛቸውን ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ፋይዳዎች መገንዘቡን ተከትሎ ለልማቱ አስፈላጊውን ትብብር እያደረገ እንደሚገኝም ገልፀዋል።

በተለይ ማህበረሰቡ የኮሪደር ልማቱ የሚነካቸውን አጥር እና ቤቶች በገዛ ፈቃዱ በራሱ ማንሳት መቻሉ ለስራው ምቹ ሁኔታን መፍጠሩን ገልፀዋል።

አክለውም የወሰን ማስከበር ስራ በተሰራባቸው አካባቢዎች ወደ ስራ መግባት እንደሚገባ እና የተቀሩ የወሰን ማስከበር ስራዎች በቀጣዩ ሳምንት እንዲጠናቀቁ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።

የኮሪደር ልማት ስራውን በ 3 ወራት ለማከናወን ዕቅድ ተይዞ ወደ ስራ መገባቱን በማስታወስ ስራውን በምሽት ጭምር በማከናወን ከተያዘለት ጊዜ ቀደም ብሎ እንዲጠናቀቅ በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ አቶ ሙክታር ሳሊህ ገልፀዋል።

Harari Government Communication Affairs Office

19 Oct, 18:06


https://vm.tiktok.com/ZMh593Ytg/ This post is shared via TikTok Lite. Download TikTok Lite to enjoy more posts: https://www.tiktok.com/tiktoklite

1,135

subscribers

19,137

photos

406

videos