Ministry of water and Energy የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር @mowieethiopia Channel on Telegram

Ministry of water and Energy የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር

Ministry of water and Energy የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር
ይህ ስለ ውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የተለያዩ ወቅታዊ መረጃዎችን የምታገኙበት የሚኒስቴሩ የቴሌግራም ቻናል ነው፡፡
5,691 Subscribers
4,536 Photos
23 Videos
Last Updated 05.03.2025 15:03

Ministry of Water and Energy of Ethiopia: A Comprehensive Overview

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በኢትዮጵያ ውስጥ የውሃ እና ኢነርጂ ለመረጃ እንደ መርገብ መስራት ይህ ወቅታዊ እና ተለይተው የሚያመለክት ተጠቃሚ ነው፡፡ ይህ ሚኒስቴር በውሃ በዝርዝር እና በኢነርጂ አካባቢ ትልቅ ተጽዕኖ አለው። የኢትዮጵያ ታላቅ በግለሰቦች የውሃ እና ኢነርጂ አዋጁነት የሚሰጡበት ይህ መለኪያ እና አመልካች አዋጁነት ይቀርባል፡፡ እነዚህ ከተመለከተው ዝርዝር እና መገለጫ ይገኛሉ። በዚህ መካከል የሚስተናገድ የታሪክ ዝርዝር ይህ ወቅታዊ መረጃዎች ለሚሰጡት የሚኒስቴሩ የቴሌግራም ቻናል ትሰጣለች።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ምን ዓይነት አቅም አለው?

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በመምሪያ ወቅት ውሃን ማህበራዊ ምርት እና ኢነርጂ በተወሰነ መሰረት ተሞክሮ ይሰጣል። ይህ የውሃ መስክ በመንግሥት የሚያስተናግድ አስፈላጊ ነው።

አንድ ዓለም በውሃ እንደ ትምህርት ማንኛውም ቢሆን ይህ ምርት በኢንዱስትሪ ይተወካላል። ከዚያ ውሃን የሚጠቀሙ የሚሄድ መስመር ይታይላል።

ሚኒስቴሩ የውሃ እና ኢነርጂ ስርዓት ምንድነው?

ሚኒስቴር ውሃን እና ኢነርጂ ላይ ታላቅ አስተዳደር ይወስዳል፡፡ ይህ የተለያዩ የውሃ ዘርፍ ይሆናል። ከሚኒስቴሪ የሚወጡ ውሃ አስተዳደር ይህ ተሞክሮ እንደ አምስት ዓለም ይህ ውሃ የእንቅስቃሴ ይወዳዳል።

ይህ የውሃ እና ኢነርጂ ሥርዓት በአሜሪካ ያለው ይህ የትስስይ ዝርዝር ይህ እንደ ዋንጫ ወንቅለኛ ይሆናል።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ምን እንደ ተሳታፊ ከሚሆን?

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር እንደ አነፃ ይናገር፡፡ ይህ የአዙም ዱቄት ይወዳዳል። የሚኒስቴር እንደ ወዱ ስለዚህ ከሚተንሻን ወይ በየዓለም መወጣት ይመለከታል።

ይህ የወዳዳል ነገር ከሚኒስቴሪ ይህ እንደ አነፃ ይህ ውሃን ይወዳዳል። የኢንዱስትሪ ዓይነት ይህ የማንኛውም እርዳታ ይተካለት።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ፕሮጀክቶች ምንድን ነበር?

የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር በመንግሥት በርኩም የምትመለከታ ፕሮጀክቶች ይቀርባሉ፡፡ ይህ የውሃ ታላቅ የሆኑ ፕሮጀክቶች ሙሉ ውሃ ያረጋግባሉ።

ይህ የውሃ ዘርግ እና የኢነርጂ ፕሮጀክቶች የወዳዳል ውሃን ይወዳዳል። ይህን የሚሚድ የኢንዱስትሪ ምን ዓይነት ኢትዮጵያ ይታወቃል።

በዚህ ሁሉ ውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር የማንኛውም ትርጉም ምንድን ነበር?

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በግድያ ወዲውት ሁሉ የዉሃ እና የኢነርጂ ምን ዓይነት ትርጉም ይታወቃል፡፡ ይህ በሂሬ ወይ ዘርዝር ግንኙነት ይታወቃል።

ይህ የሚያስተዳድሩ የውሃ ሞንድ ይወዳዳል፡፡ እንዲሆን የኢነርጂ ስርዓት ይታወቃል።

Ministry of water and Energy የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር Telegram Channel

ምን አካሄደች እና አስቀምጠዋችሁ? ለውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ቴሌግራም ቻናል ማኅበረሰብ ላይ ያነሱት ሰዎችን ህዝብ ለማስወጣት ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት ስለመገኘት ሲሞሉ። በቴሌግራም አፕሊኬሽን ወይም በቴሌግራም ስትሰጥም እና ሌሎቹን የቴሌግራም ዕቅድና መረጃዎች በሌላ ቤት የምንገኝ ሰዎች አሉ፡፡ ውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የምንጠይቁትን የሚኒስቴራ መረጃዎችን እንዴት እንደሚከብድ እና ለማስፈሻል እንነጋገር የሚኒስቴራ የበለጠሩበት ነጋዴን እንስጥር፡፡ እና በመሆን። ውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴሩ የምንጠይቁትን መረጃ ለመገኘት ካሉ መረጃ ውጤቱ እንዴት እናመለከታለን? ከላይ ሲጠቀሙ ፓስፊሮ ሚኒስቴርዎችን ለመቀላቀሉ ውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴሩ አዉርድ ይችላሉ።

Ministry of water and Energy የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር Latest Posts

Post image

ከ348 ሚሊየን ብር በላይ ወጭ የተገነባው የዲላ ከተማ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ጀመረ፡፡

የካቲት 25/2017ዓ.ም (ው.ኢ.ሚ) በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በዋን ዋሽ ብሔራዊ ፕሮግራም ከ348 ሚሊየን ብር በላይ ወጭ የተገነባው የዲላ ከተማ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ጀመረ፡፡

የምረቃ መርሀ ግብሩ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የደቡብ ኢትዮጵያ ርእሰ መስተዳደር ክቡር አቶ ጥላሁን ከበደ ፕሮጀክቱ ከተማችንን አንድ ደረጃ ከፍ የሚያደርግና ከተማችን የብልጽግና ተምሳሌት፣ ለነዋሪዎቿ ምቹ፣ ለኢንቨስትመንት ሳቢ፣ የሚያደርግ ፕሮጀክት እንድናስመርቅ ከጎናችን ለነበሩ ፈተናዎችን ላሻገሩን ክቡርዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋን አመሠግናለሁ ብለዋል።

ክቡር ርእሰ መስተዳድሩ በማከል ህብረተሰቡ ውሃን በመጠቀም ሁሉን አቀፍ ስራ በመስራት፣ ከጽዳት ጋር በማቀናጀት፣ የተበላሹ መስመሮችን በማስተካከል በቀጣይ ሌሎችም ፕሮጀክቶችን በመስራት ገቢ ማግኘት እንዲያስችል ጥገና ፣ ጥበቃ እና እንክብካቤ በማድረግ ህይወት ያለው ለማድረግ የዲላ ከተማ ውሀና ፍሳሽ አገልግሎት ሀላፊነቱን እንዲወጣ አደራ በማለት መልእክት አስተላልፈዋል።

ፕሮጀክቱን በቦታው ተገኝተው ያስመረቁት የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል 1.6 ሚሊየን የህብረተሰብ ክፍሎችን የንጹህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ለማድረግ እየሰራን ነው ስንል በአንድ ዞን ሁለት ከተሞች ማስመረቃችን የስኬታችን ማሳያ ነው ብለዋል። ክቡር ሚኒስትሩ በማከል የዲላ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ከተማዋ የነበረባትን ችግር ሙሉ በሙሉ ከመቅረፍ ባሻገር መሠረታዊ ለውጥ ያመጣል ለዚህም ውሃ ላይ ብቻ ሳይሆን ሳንቴሽን ላይ ህብረተሰቡ እና አመራሩ በመተባበር መስራት ይጠበቅበታል ብለዋል።

የዲላ ክላስተር አስተባባሪና የውሃ፣ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊ ኢ/ር አክሊሉ አዳኝ ውሃ የህብረተሰቡ መሠረታዊ ችግር ላይ የሚሰራው ስራ ሌሎች ልማቶችን በማሳለጥ በጤና ፣ በትምህርት፣ በኢኮኖሚና በአጠቃላይ በልማቱ ዘርፍ የሚያሳድረው ተጽእኖ ከፍተኛ መሆኑን ጠቅሰው ይህን ታሳቢ በማድረግ እንደ ክልል በ14 ከተሞች በተለያዩ ፕሮግራሞች 1.2 ሚሊየን ህዝብ ተጠቃሚ የሚያደርጉ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች እየተገነቡ መሆኑን ገልጸው ዛሬ የሚመረቁት ፕሮጀክቶች የዚሁ አካል ናቸው ብለዋል።

ኢ/ር አክሊሉ በማያያዝ የዲላ ከተማ መጠጥ ውሀ ፕሮጀክት ነባር የሆነውን ስምና ችግሮች ር ስለሚፈታ በአግባቡ ከብክነት በጸዳ በመጠቀም ገቢ እንዲያስገኝ ልናደርግ ይገባል ብለዋል።

በዋን ዋሽ ብሔራዊ ፕሮግራም የገንዘብ ድጋፍና በውሀ ልማት ፈንድ አስተባባሪነት የተተገበረው የዲላ ከተማ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት 192ሺ የህብረተሰብ ክፍሎች የንጹህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ በማድረግ የከተማውን የመጠጥ ውሃ ችግር እንደሚፈታ ተገልጿል፡፡

ፕሮጀክቱ ዘላቂነት ያለው አገልግሎት እንዲሰጥም ህብረተሰቡም አስፈላጊውን ጥበቃና እንክብካቤ ማድረግ እንዳለበትም በምርቃቱ ላይ ተገልጿል ፡፡

በፕሮግራሙ ላይ የውሀና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች ፣የክልሉ ባለስልጣናት እና የሚመለከታቸው አካላት ተገኝተዋል።

ስለተቋማችን ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት

ፌስቡክ
https://www.facebook.com/share/127Jeg3ch6p/
ቴሌግራም
http://t.me/mowieethiopia
ዌብሳይት
http://mowe.gov.et
X/ትዊተር
https://x.com/mowe_ethiopia
ዩቱዩብ
https://youtube.com/@ministryofwaterandenergy-e8842?s
ቲክቶክ
tiktok.com/@mowetikto

04 Mar, 19:54
440
Post image

ለውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴርና ለተጠሪ ተቋማት አመራሮች የአቅም ግንባታ ስልጠና እየተሰጠ ነው።

የካቲት 24/2017 ዓ/ም በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የተዘጋጀ በተቋሟዊ ተግባቦት /organizational communication/ ላይ ያተኮረ የአቅም ግንባታ ስልጠና ለተቋሙና ለተጠሪ ተቋማት አመራሮች እየተሰጠ ነው።

የስልጠናውን መርሃ ግብር ያስጀመሩት በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የኢነርጂ ዘርፍ ሚንስትር ድኤታ ክቡር ዶ/ር ሡልጣን ወሊ ውድ ጊዜና ገንዘብ ተመድቦ የአቅም ግንባታ ስልጠና የተዘጋጀው በተቋማችን ውጤታማ ስራ ለመስራት፣ ትክክለኛ ተግባቦትና ጤናማ ግንኙነት ወሳኝ በመሆኑ ነው ብለዋል።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በውሃና ኢነርጂ ዘርፍ በርካታ ውጤታማ ስራዎችን እየሰራ ይገኛል ያሉት ሚንስትር ድኤታው በቀጣይ በየስራ ክፍላችን የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ የስራ ክህሎታችንን ከፍ ለማድረግ፣ ጤናማ ግንኙነትና ትክክለኛ ተግባቦት መሰረታዊ ጉዳይ ነው ብለዋል።

እንደ አመራር መረጃ ልውውጣችንና የተግባቦት ደረጃችን የት፣ መቼ፣ ከማን ጋርና እንዴት የሚሉ ጥያቄዎችን በአግባቡ የሚመልስና ስራችንን ውጤታማ በሚያደርግ መልኩ መሆኑንም በጥንቃቄ ማየት አለብንም ብለዋል።

ክቡር ሚንስትር ድኤታው አክለው የተቋማችንና የተጠሪ ተቋማት አመራሮች የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን ከፍ በማድረግ ዘመኑን የዋጀ ስራ ለመስራት፣ ጥራት ያለው አገልግሎት ለማቅረብና በቡድን የመስራትን መንፈስ ለማጠናከር የአቅም ግንባታ ስልጠናው ከፍተኛ ጠቀሜታ ስላለው ትኩረት ሰጥተን መከታተል አለብን ብለዋል።

ከአዲስ አባባ ዩኒቨርሲቲ የመጡ የዘርፉ ምሁራን በተቋማዊ ተግባቦት፣ የተግባቦት ዋና ዋና ጉዳዮችና ሀይድሮፖለቲክስና ዲፕሎማሲ በሚሉ ርዕሶች ላይ ሰፊ ማብራሪያ በመስጠትና የቡድን ስራ በማሰራት ጠለቅ ያለ ግንዛቤ አስጨብጠዋል።

ሰልጣኞችም በቡድን ስራ በመሳተፍና በመወያየት፣ ጥያቄዎችን በመጠየቅ የነቃ ተሳትፎ አድረገዋል ፣ ስልጠናው ለስራቸው ውጤታማነት ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳለውም ገልፀዋል።

ስልጠናው ለሁለት ቀናት እንደሚቀጥልም ተገልጿል።

ስለተቋማችን ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት

ፌስቡክ
https://www.facebook.com/share/127Jeg3ch6p/
ቴሌግራም
http://t.me/mowieethiopia
ዌብሳይት
http://mowe.gov.et
X/ትዊተር
https://x.com/mowe_ethiopia
ዩቱዩብ
https://youtube.com/@ministryofwaterandenergy-e8842?s
ቲክቶክ
tiktok.com/@mowetikto

04 Mar, 19:48
373
Post image

“የዓባይ ግድብ እና ዓድዋ የአንድነታችን ማሰሪያ የቁጭታችንም ማሳያ ስኬቶቻችን ናቸው” –

ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር

ዓባይ ግድብ እና ዓድዋ ድል የአንድነታችን ማሰሪያ፤ የቁጭታችንም ማሳያ ስኬቶቻችን ናቸው ሲሉ የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) ገለጹ:: ሁለቱም ስኬቶች በሕዝቡ እና በመሪዎች ቅብብሎሽ የተገኙ ድሎች መሆናቸውን አስታወቁ::

የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ኢንጂነር ሀብታሙ (ዶ/ር) ከአዲስ ዘመን ጋር ባደረጉት ቆይታ እንዳስታወቁት፤ የዓባይ ግድብም ሆነ ዓድዋ የኢትዮጵያውያን አንድነት የተረጋገጠባቸው ስኬቶች ናቸው:: ኢትዮጵያውያውን በሁለቱም ላይ አንድነታቸውን አሳይተዋል፤ በቁጭት በሠሩት ሥራ የማይደፈር ማንነት እንዳላቸው አረጋግጠዋል::

ሁለቱም ታላላቅ ስኬቶች ኢትዮጵያውያን በብቃት የተጫወትንባቸው ሜዳዎች ናቸው ያሉት ሚኒስትሩ፤ ጠላትን በዝረራ ከጨዋታ ወጪ ያደረግንበትን ድልም አስመዝግበንበታል ብለዋል:: ዓባይ ግድብ ሆነ ዓድዋ ድል ኢትዮጵያ ይደርስባት የነበረውን የውጭውን ጫና በብቃት የመከተችበት ሲሆን፤ ያንን የተሳሳተ አስተሳሰብ ያኮላሸችበት ስኬቷ እንደሆኑም ገልጸዋል::

እንደ ኢንጂነር ሀብታሙ (ዶ/ር) ገለጻ፤ ዓድዋ ድል እና ዓባይ ግድብ የኢትዮጵያውያን አንድነት የተረጋገጠባቸው ናቸው:: ዓድዋ ላይ እንደ አሁኑ ጊዜ ቴክኖሎጂ አልነበረም::

ተንቀሳቃሽ ስልኩ፣ ኢንተርኔቱ እና ሌላ ሌላው አልነበረም::

እንዲያም ሆኖ ለኢትዮጵያ አንድነት ሲባል ከጥግ ጥግ ድረስ በአራቱም ማዕዘን ንቅናቄ በመፍጠር ኢትዮጵያ የእኔ ናት ብሎ ስለሚያምን ለኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ሕዝቡ መንቀሳቀስ ችሏል:: በወቅቱ የራሱ የሆነና እንዲፈታለት የሚፈለገው ችግር ሊኖርበት ይችል ይሆናል:: ነገር ግን በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ ድርድር አያውቁም:: የዓባይ ግድብም በተመሳሳይ የሚጠቀስ ነው::

የዓባይ ግድብ በየትኛውም ክልል ሆኖ የትኛውም ቀበሌ ውስጥ ያለ ሰው ዓባይ ሲባል አንዳች የአንድነት እና የመተባበር መንፈስ ውስጡ እንዳለ ይታወቀዋል:: የእኔነት ስሜቱ የጎላ ነው:: ምክንያቱም ከሌለው ነገር ላይ ለዓባይ ግድብ አቋድሷል::

በዓድዋ በኩል ወይ ራሱ አሊያም ልጆቹን ወደ ግንባር እንዳላከ ሁሉ ለዓባይ ግድብም እንዲሁ በጉልበቱ፣ በገንዘቡና በሀብቱ ተሳትፏል:: ከዚህ መነሻነትም ዓድዋ ድልና ዓባይ ግድብ የአንድነት ማሳያ ናቸው:: ሁለቱም የኢትዮጵያውያን ምልክት ናቸው::

ሚኒስትሩ፣ ሁለቱም የውጭ ጫና የፈተናቸው ታላላቅ ስኬቶች ናቸው:: ኢትዮጵያ በዓድዋ ጦርነት ጊዜ የተዋጋችው አንድን ሀገር ብቻ አይደለም:: በወቅቱ ከጣሊያን ጋር ኅብረት ከፈጠሩትና የቅኝ ግዛትን ማስፋፋት ከሚፈልጉት ሀገራት ጋር ሁሉ ነበር ማለት ይቻላል:: ኢትዮጵያ በወቅቱ ያሸነፈችው የተነሱባትን ኃይሎች ሁሉ ነው:: ይህ ትልቅ ስኬት ነው ብለዋል::

የዓባይ ግድብን በተመለከተ ደግሞ እኛን ስትገዳደረን የነበረችው ግብጽ ብቻ አይደለችም ያሉት ኢንጂነር ሀብታሙ (ዶ/ር)፤ ኢትዮጵያ ማሸነፍ የቻለችው በድህነቷ እንድትዘልቅ የሚፈልጉ ኃይሎችን ጭምር እንደሆነ አስረድተዋል::

ኢትዮጵያ በዓባይ ግድብ ምክንያት በጸጥታው ምክር ቤት ስትወሰድ ዓላማው ኢትዮጵያን በዚያ ደረጃ ማብጠልጠል ነው:: በመሆኑም በኢትዮጵያ ጥንካሬ እሱን ወደ አፍሪካ ኅብረት መመለስ መቻል ትልቅ ስኬት ተደርጎ የሚወሰድ መሆኑን አመልክተዋል::

በዓድዋ ጊዜ በውጊያ የነበረው የቅኝ መግዛት ሕልም ኢትዮጵያ እንዳጨናገፈች ሁሉ አሁን ደግሞ በኢኮኖሚው በኩል በቅኝ ለመግዛት የተቋመጠውን አካሔድ ኢትዮጵያ ያሸመደመደችው መሆኑ ሁለቱን የሚያመሳስላቸው ጉዳይ ነው ብለዋል::

እርሳቸው እንዳሉት፤ በጣም ወሳኙ ጉዳይ በኢትዮጵያ የውሃ ልማት ታሪክ ዛሬ ያመጣነው ስኬት በአንድ ጀምበር የመጣ ሳይሆን በትውልድ ቅብብሎሽ የተገኘ ስኬት ነው:: በዚህ ስኬት ውስጥ የመሪዎች ቅብብሎሽ አለ:: ንጉሱ አጼ ኃይለስላሴ የአሜሪካ ኩባንያ ቀጥረው ኢትዮጵያ ውስጥ ለግድብ የሚሆን ብዙ ቦታ ካስጠኑ በኋላ ብድር ጠይቀው ተከልክለዋል:: ይሁንና አንድ ቀን ኢትዮጵያውያኑ እንደሚገነቡት ተስፋ አድርገው አልፈዋል::

ሙሉውን ለማንበብ
https://press.et/?p=146503

ስለተቋማችን ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት

ፌስቡክ
https://www.facebook.com/share/127Jeg3ch6p/
ቴሌግራም
http://t.me/mowieethiopia
ዌብሳይት
http://mowe.gov.et
X/ትዊተር
https://x.com/mowe_ethiopia
ዩቱዩብ
https://youtube.com/@ministryofwaterandenergy-e8842?s
ቲክቶክ
tiktok.com/@mowetikt

04 Mar, 19:43
353
Post image

ሁለተኛው አድዋችን የሆነው ህዳሴያችን የጋራ ማንነታችን መገለጫ ነው።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ

የካቲት 21/2017 ዓ.ም (ው.ኢ.ሚ) 129ኛው የዓድዋ ድል በዓል “አድዋ የጥቁር ሕዝቦች ድል!” በሚል መሪ ቃል በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር አመራሮችና ሰራተኞች ተከበረ።

በአሉን አስመልክቶ ንግግር ያደረጉት የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ ሁለተኛው አድዋችን የሆነው ህዳሴያችን የጋራ ማንነታችን መገለጫ ነው፤ አድዋ የትም ቦታ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ የሚዘክረው በመሆኑ ማንነታችንን ያበሰርንበት ነው ብለዋል።

ኢትዮጵያውያን ከዳር እስከ ዳር በዘመቱበት ወቅት ሁሉም ዜጋ በተሰማራበት ዘርፍ የድርሻቸውን በመወጣት አሻራቸውን ያኖሩበትና ትልቅ ስኬት የተመዘገበበት በመሆኑ ልንዘክረው ይገባል ያሉት ክቡር ሚኒስትሩ ጀግኖች አባቶቻችን በሀገር ጉዳይ በጋራ ሲቆሙ ብሔር ሳይለዩ የጀግንነት ድርሻቸውን ተወጥተዋል ብለዋል።

ክቡር ሚኒስትሩ አክለውም ሁለተኛው አድዋችን የምንኮራበትና የአንድነታችን የጋራ መገለጫችን በመሆኑ በወቅቱ የነበሩ መሪዎች ዋጋ ከፍለው እዚ አድርሰውልናልና ልናስቀጥለው ይገባል፤ በተጨማሪም የይቻላል መንፈስ ያዳበርንበት በመሆኑ የጋራ ሀገር ለሁሉም ኢትዮጵያዊ የምትሆን ኢትዮጵያን እንገምባ ብለዋል።

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ስራ አስፈፃሚ አቶ ጌትነት ጌጡ በዓሉን አስመልክቶ የተዘጋጀውን የመወያያ ሰነድ አቅርበው እንደተቋም ሁለተኛውን አድዋችንን ለማስቀጠል ሁሉም በተሰማራበት ዘርፍ ኃላፊነታችንን በመወጣት የራሳችንን አሻራ ማስቀመጥ እንዳለብን ጠቁመዋል።

መድረኩ በኢትዮጵያ ህዝብ መዝሙር የተጀመረ ሲሆን በቀረበው የመወያያ ሰነድ ዙሪያ ከሰራተኞች በተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ክቡር ሚኒስትሩ ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።

28 Feb, 17:29
945