ኪነት በዮዳኒ @gbw_dan Channel on Telegram

ኪነት በዮዳኒ

@gbw_dan


በዚህ የጥበብ ቤት▼▼▼

🎨ስዕል

📔ወግ

📖የመጽሐፍ ጥቆማ

📚መጽሐፍት

🗒ግጥም

🗣ትረካ

🎭ኪነጥበባዊ መረጃና ትምህርት

📑ወቅታዊ ፅሁፍ ያገኛሉ።

ኪነት በዮዳኒ (Amharic)

ኪነት በዮዳኒ የተጠቃሚ ሥራዎችን እና መረጃዎችን የሚያስፈልጋቸው ቲማቲውን ነቀቅና ለማንበብ ዋጋ በመጠቀም የሚፈልጉ የመከላከያ ቀሚሶች፣ ትምህርቶች፣ መጽሐፍዎችና መረጃዎች መከላከያ እና ትምህርት ያለባቸውን ኪነጥበባዊ መረጃና ትምህርት ተመሳሳይ ለናካራቸው በዚህ ቲማቲት የተጠቃሚውን ብቻ ያምናሉ። ሥራዎችን ለማቀበልና ሥራዎችን ለማንበብ ቦታን የሚለዋወጥ በማህበረሰባቸው ቦታዎችን እና መከላከያዎችን መጠቀም በቀሚሶችና ትምህርቶች ላይ ነጥቀው እና ውስጣውን ካገኘብኩ መብላት እና አስፈላጊ መልሱን ትችላላችሁ። በመገመት፣ ይህ ቲማቲው በሚደርስበት ጊዜ ይህም የዚህ ቲማቲው ሰብሳቢዎችን ለመወሰን ወይም ላምጣናቸውን ለመስራት የተጠቃሚውን አንባቢዎች ወቅታዊ ፅሁፍ በትክክል ይከታተሉ።

ኪነት በዮዳኒ

18 Jan, 16:56


#ዋ ዮርዳኖስ

ለወንዙ ገደብ በሰጠ
ለውቅያኖሱ ማረፊያ የሰፈረለት
ማዕበል ወጀቡን በቃሉ  ገሳጭ
ባህሩን እንደመስታወት በስጋ ረጋጭ

መልኮትን ከስጋ ጋራ አንድ አድርጎ ያዋሃደ ፣
ጠፈር ሃኖስ ዋኖሱን ትቶ እንደምን ዮርዳኖስ ሄደ ?!
እንደምን ዮርዳኖስ ሄዴ?!

በእሳት አጥማቂ ተብለህ በወዳጅህ ተሰብኮልህ፣
የህይወት ሁሉ ወሃ ሆነህ?!
ዮርዳኖስ በምኑ ሳበህ?
እንዴት ወደ ወሃ ሄድህ አንተ ዮርዳኖስ ምን ምስጢር አለህ?።

ዋ ዮርዳኖስ !
አንቺ የወንዞች ሁሉ ንጉስ !
ዋ ዮርዳኖስ !
የቀላያት ሁሉ ዳኛ ፣
የማያት ሁሉ እረኛ !

የምድር የዳርቻዋ አድባር ፣
የፍጥረተ ወንዝ በኩር !
ዋ ዮርዳኖስ !

እንደምን ሸሸሽ ወደኋላ ፣
እንደምን ቆምክ ካለ ባላ፣

እንደው !
ስንቱ ጉድ ተሰማልን ፣
ስንት እንግዳ አስተናገድን ፣

በፍጥረቱ በውልደቱ ስንደመም ፣
ሌላ መንክር ተገለጠ በዮርዳኖስም ፣

ቤተልሔም ሲደመሙ ሰባ ሰገል፣
አሁን ደግሞ ምን ያቅርቡ ? ለፍቅሩ ቃል፣

አይ ዮርዳኖስ !
ምን ምስጢር አለ የቀበርኸው?
ታላቁ ጌታን  ና ግባ ያልኸው?!

አይ ዮርዳኖስ!
.....
እስኪ ኑ
#ዮርዳኖስ ሲያፈገፍግ እዩ
ዮሐንስ ሲያጠምቅ ክርስቶስን ሲያዩ!



...Solomon Adugna

January  ,2024

ኪነት በዮዳኒ

18 Jan, 10:50


ዛሬም ከእንግሊዝ አልወጣንም። አሁን ግን ከከተማዋ ጋር ሳይሆን ከገናናው ኦክስፎርድ ዩንቨርስቲ ጋር ነው ነገር አለማችን።

በዚህ ዩንቨርስቲ ለ180 አመታት የደውሉ ድምፅ ሳያቋርጥ የሚጠራ በባትሪ የሚሰራ ደውል አለ።

የሚገርመው ይህ አይደለም፤ ጉዱ የባትሪው ስሪት ሚስጥራዊ/ረቂቅ እንደሆነ እስካሁን ቆይቷል፤ ለ180 አመታት ሀይል ከየት እያገኘ ነው?።

ምናልባትም መሳሪያው እስካልተፈታታ ድረስ የደውሉ ጥሪ ሊያቆም አይችልም።

ኪነት በዮዳኒ

16 Jan, 05:01


እወድሃለሁ አልልህም ግን ...

የወደድኩትን ሙዚቃ እልክልሃለሁ።
እንደራበኝ እነግርሃለሁ።
የምፈራውን ነገር እነግርሃለሁ።
ቀኔ እንዴት እንዳለፈ እነግርሃለሁ።

እወድሃለሁ አልልህም ግን ...

በቢሮህ በኩል እንዳለፍኩና እንዳስታወስኩህ እነግርሃለሁ።
የሰጠኸኝ ትንንሽ ነገሮች እንዳልጠፉብኝ እነግርሃለሁ።
ስላናደደችኝ ጎረቤቴ እነግርሃለሁ።
እንደበረደኝ እነግርሃለሁ።

እወድሃለሁ አልልህም ግን ...

ፈተና ጥሩ እንደሰራሁ እነግርሃለሁ።
ደሞዜ እንዳልበቃኝ እነግርሃለሁ።
ጥቃቅን ነገሮችህን ሁሉ አስታውሳለሁ።
እጸልይልሃለሁ እልሃለሁ።
ያማረኝን እነግርሃለሁ።
እናቴ እንደናፈቀችኝ እነግርሃለሁ።
ያንተ ብቻ ስም አወጣልሃለሁ።

እወድሃለሁ አልልህም ግን

ስሜን ማን እንዳወጣልኝ እነግርሃለሁ።
ጠንካራነቴን ጥዬ አጠገብህ ማልቀስ እፈልጋለሁ።
አበባ እንደምወድ እነግርሃለሁ።
አመመኝ እልሃለሁ።

እወድሃለሁ አልልህም ግን እደገፍሃለሁ። በየ እጥፋቶቼ ሁሉ አስቀምጥሃለሁ። እወድሃለሁ አልልህም ፤ ስለምትወዳቸው ነገሮች እጠይቅሃለሁ። የምትወዳቸውን ሁሉ እወዳለሁ።

ቋንቋዬ ከገባህ ብዙ ነበር የነገርኩህ ...

Ruth H/mariam

ኪነት በዮዳኒ

15 Jan, 19:11


ለን____ደን

የታላቋ ብሪታንያ ከተማ የሆነችው ሎንዶን (ለንደንም ይሏታል🤷‍♂️ ፀሀይ አትጠልቅም ይሉም ነበር....ነበር ነው! አሁን መላው የአፍሪካ ጥቁር ህዝብ፣ ኤዢያው፣ አሜሪካኖች-ደቡብም፣ ሰሜንም ኢቭን አውስትራሊያ፣ አንታርቲካ ሳይቀር ነቄ ቶሎ ተቄ አሉባቸውና ጠቅለው ሀገራቸው ገብተው ጸሀይ ትጠልቅ ጀምሯል።

ለምን? የኢትዮጵያ ፒፕል አፍሪቃውያንን አስተባብሮ ፓን-ከፍሪካኒዝም በአንድ አቀነቀነ one love!። እንደገናም ደግሞ "ጥሊያንን በካልቾ እንዳልን እናንተንም ኦንዳንደግማችሁ" ሲሏቸው ነበር..አሉ። እናም ባርነት በቃኝ አለ። እንደገናም ደሞ እንደናንተው ሁሉ እኛም ጸሀይ እንዳትጠልቅብን እንፈልጋለን አሉ። ብለውም አልቀሩ የጥቁር፣ ጭቁን ህዝብ ነፃ ሆነ። ግን እንዳለመው ፀሀይ ለመሪዎቹ ብቻ ነው የማትጠልቀው። እስካሁን !!!!!! ፀሀይ ለመሞቅ እንደተመኘ አለ! )

ወደ ነገሬ ልመለስና በአለም ትልቁ፣ ሰፊው የከተማ ውስጥ ደን (urban forest) እስከ 21% የሚሆን የደን ሽፋን ያለው በለንደን ነው። (ይሄ ነበር አይደለም! አሁን ነው )
እንዲያውም በቅርቡ በከተማዋ ውስጥ ያለው የዛፍ ብዛት ለንደን ከተማዋ ውስጥ ካለው የህዝብ ቁጥር ጋር እኩል ሳይሆን አይቀርም።

ኪነት በዮዳኒ

14 Jan, 12:10


በ2017 G.c በአሜሪካዋ ኮሎራዶ ምን ሆነ መሰላችሁ?

አንዲት አጋዘን ወደ አንድ ስቶር ቀጥ ብላ ቀጭ ቋ...ቀጭ ቋ እያለች ትገባለች።
(በምስሉ ላይ እንደምትመለከቱትም ወገቧን ይዛ "ምን ታፈጣለህ አስተናግደኝ እንጂ" አይነት እይታ ታየዋለች 🤗 )

የሱፐርማርኬቱ አስተናጋጅም
በይ ይሄን ያዢና ሂጂ በሚል አይነት የለውዝ ቅቤ/ ፒኗት/ እጅ ከምን ይላታል። (ከፍቶ ይሰጣል ) አጋዘኗ በርግጥ ለቃ ትወጣለች፤ ክፍያም ሳትከፍል።

በሌላ ጊዜ ግን ስትመለስ ከነሙሉ ቤተሰቧ ከች አለች ከዛው ስቶር።

(የራት ግብዣ አለን ዛሬ ማታ ቤተሰብ ብላ 😂 እንደ ዘንድሮ አንዳንድ ሴቶቻችን ወንዱ ልጋብዝሽ ሲላት ሙሉ ጓደኞቿን አግተልትላ የትውውቅ መሰናዶ እንደማድረግ በሉት 🤗)

በዮዳA

ኪነት በዮዳኒ

12 Jan, 11:31


የምትመለከቱት ናትሮን ሀይቅ እንስሳትን ወደ አለትነት ይለውጣቸዋል።

ከፍተኛ አልካላይነት ባህሪ እና የሙቀት መጠን
ስላለው ወደ ሀይቁ ውስጥ ለዋናም ይሁን እንዲሁ ሞቋቸው አሊያም ፓርቲ አዘጋጅተው ለመፈታታት ቢገቡ immediately ይሞታሉ።
ቀጥሎም ደግሞ መገነዣ ምናምን ሳያስፈልግ ራሱ በሚንራል/ ማዕድናት ይገንዛቸዋል፣ አካላቸው ወደ አለትነት ይቀየራል።

ተፈጥሯዊ የሃውልት አሰራር ይሉሃል። እና አንድ ወደዚ ሀይቅ ገብቶ የሞተ አካል ቤተሰቦቹ ለለቅሶ ሳይሆን ለሐውልቱ ምርቃት ብቻ መምጣት ነው የሚጠበቅባቸው።

በዮዳኤ

ኪነት በዮዳኒ

11 Jan, 11:24


የአለማችን ረጅሙ፣ ቁመታም፣ ሎጋ ተራራ ማነው ብንባል ኤቨረስት አልያም ኪሊማንጃሮ ነው ምላሹ።

ነገርግን ውቅያኖስን ጠለቅ ብለን አልያም ውስጥ ለውስ ማሰስ ሳያሻን አይቀርም። ብሔራዊ የውቅያኖስ አገልግሎት(NOS) በሪፖርቱ እንዳሳወቀው ከሆነ 40,389 ማይሎች ርዝመት ያለው ተራራ የሚገኘው ከውቅያኖስ በታች 90%ቱ በውሃ ተውጦ ነው የሚገኘው።

(ልብ በሉ ኤቨረስት 8,500km ነው ርዝመቱ። ይሄ ከውሃ በታች የሚገኘው ተራራ ደግሞ 10 ወይም 20 እጥፍ እንደሚበልጠው ልብ ይሏል🤗)


በዮዳA

ኪነት በዮዳኒ

09 Jan, 12:22


ይቺ ሀገር ወዴት ሄደች 👀 ....ያያቹሃት።

ከዛሬ 9 አመት በፊት ስትወጣ የለበሰችው:-
ከወገቧ በላይ ጥጋብ
ከወገቧ በታች ሰላም
የተጫማችው :-
ደስታን ....


ነበረ !

ያያችሁ ጠቁሙን ስንል እንማጠን-ኣለን 🙏 ወረታውንም እንከፍ-ል-ኣለን።

የዚች ሀገር ነዋሪዎች አፋልጉኝ ማስታወቂያ

ኪነት በዮዳኒ

09 Jan, 07:57


ካርታ !

ለመዝናናት፣ ለቁማርና ለለቅሶ ማስተዛዘኛ የምንጫወትበት ካርታ ውስጥ ያሉ

አበባ
ጦር
ዳይመንድ
ልብ
(Spades, Clubs, Hearts &Diamonds )
እያንዳንዱ የቀድሞ ሃያል ነገስታትን ይወክላሉ።

📌 ይህም
ጦር-> ንጉሥ ዳዊትን
አበባ->ታላቁ እስክንድር
ልብ-> ቻርልማኝ
ዳይመንድ->ጁሊየስ ቄሳር

በዮዳA 🤗

ኪነት በዮዳኒ

08 Jan, 08:37


😂ጉዳጉድ 😲

አባይ ለግብጽ ምኗ? 🤔

እየውላቹማ እኒህ ምስሮች (ጥንታዊ ስማቸው ነው..)፤ እነዚ ጥንታዊያን ግብፆች የአባይን ውሃ መሙላት ይለኩት ነበር!

ለክተውት ምን ያደርጉት ካላችሁ ...ይሸቅሉበታል ስላቹህ ! (ሰከላን ይንሳኝ! ጣናን እምቦጭ ይውረስብኝ የምሬን ነው። ቁምነገር...ህእ!!! እኛ ነን እንጂ አራስ ሆነን መሰረተ-ድንጋይ ተጣለ፣ አሁንም መሠረቱን ሲሰሩ እንጂ ጠብ የሚል ነገርም ያላየን😒)

ከፍተኛ የውሃ ሙላት ወይም ጎርፍ ባለበት አከባቢ እየሄዱ እንደ ውሃው ብዛት ከበድ ያለ ታክስ ይጥሉበታል። ይህም ማለት ውሃው መጠኑ/ጎርፉ በዛ ካለ እዛ ስፍራ ያለ ነዋሪ  በዛ ያለ አዝመራ ይሰበስባል፤ ታክሱም እንደዚያው ከበድድድ፣ ወደድድድ ይላል ።

ጥንት ነው ይህ!

አሁን ደግሞ አስቡት የአስዋንን ግድብ ታክኮ ያለው ኤኮኖሚና ካይሮ !

እኛስ?

በዮዳA

ኪነት በዮዳኒ

06 Jan, 19:28


ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለብርሃነ ልደቱ በሰላም አደረሳችሁ ።

ኪነት በዮዳኒ

06 Jan, 19:24


አንድ ጥናት እንደሚያመላክተው ሁለት ሰዎች እየተነጋገሩ ሳለ፣ የአንደኛቸው አእምሮ የሌላኛቸውን የመምሰል አዝማሚያ አለው። ይህም ማለት ሚስትህ በቁጣ ስትናገርህ፣ ያንተም ምላሽ በቁጣ የተሞላ ይሆናል፤ ልጅህን በስክነት ውስጥ ሆነህ ስታናግረው፣ የእርሱም አእምሮ የሰከነ ይሆናል።

ወዳጅህ ሲስቅ አንተም ትስቃለህ፤ ወይም እርሱ ሲያዛጋ አንተም ማዛጋት ትጀምራለህ። ሁሉም ስሜቶች ተላላፊ ናቸው፤ ልክ እንደ ጉንፋን። ፍርሃት፣ ጭንቀት፣ ሃዘን ሁሉም ከሰው ወደ ሰው ይጋባሉ።

ስሜቶችህን ለመቆጣጠርና ወደ መንፈስ ከፍታ ለመድረስ የሚያስችሉህ መንገዶች:-

አንድ- በየዕለቱ፤ ጠዋትና ማታ ለአስር ደቂቃዎች ያህል ጽሞናን አካሂድ።

ሁለት- ከሰዎች ጋር መልካም የሆነ ግንኙነት እንዲኖርህ አድርግ፤ ሳቅህንና መልካም ሃሳቦችህን አጋባባቸው።

ሶስት- በሄድክበት ሁሉ ያንተን እርዳታ የሚሹ ሰዎችን ፈልግ፤ በተቻለህ አቅምም እርዳቸው። ይህም ሁላችንም አንድ ለመሆናችን እና የሌላው ደስታ ያንተም ደስታ እንደሆነ ማስታወሻ ይሆንሃል።

አራት- ያበሳጨህን፣ ያናደደህን ነገር በማስታወሻ ደብተርህ ላይ አስፍር፤ ይህን ስታደርግ ንዴትህ ይበርድልሃል፡፡

የአእምሮ ኢነርጂ መጽሐፍ

ኪነት በዮዳኒ

03 Jan, 19:31


😂ጉዳጉድ 😲

ታታሪዎቹ ንቦች/ተናዳፊዎቹም😁/ በምሽት መብረር እንደሚሳናቸው ያውቃሉ? ካወቁ ደግ፣ ካላወቁም እሰይ!

በዮዳA

ኪነት በዮዳኒ

02 Jan, 13:59


ባይሖን ልጣበቅሽ!

ከዐሮጌ ታክሢ,
ከተውተርታሪዋ ብልሽቴ ልቆ፣
ቆሜ ሥጠብቅሽ,
ነገዬ ቢታጠፍ በዛሬዬ ታንቆ።

ሠዉን ሠው ባልመሥለው,
ሥለዕኔ ለማውራት ዐንቺን ከሚናገር፣
ዕኔም ያንቺ ዐፍቃሪ,
ዕንዲሕ በቀላሉ ታምቼ ከምቀር።

ስሜም ዕንዲታደሥ፣
ዐንቺም ዕንዳይከብድሽ ቆሜ ስጠብቅሽ,
መገተር ዐቁሜ፣
መቆሙን ልርሣና ባይሖን ልጣበቅሽ! መታሠቢያነቱ ለዐፍቃሪዎች።

@eyadermoges1 @eyadermoges1 @eyadermoges1

እያጋራን 😁! @afengusbot ማጋራት የምትፈልጉትን ስራ፣ ያላችሁን ጥቆማ፣ ሃሳብ እና የግል ምልከታ ሊቀበላችሁ ዝግጁ ነው። እኛ ወደስራ እንገባበታለን ያጋሩን!

ኪነት በዮዳኒ

01 Jan, 23:28


https://t.me/chat_gpt_5_turbo_bot?start=_tgr_kKUvr084NTM0

ኪነት በዮዳኒ

01 Jan, 21:13


Bro, I'm desperate! This cat's been taunting me non-stop. I need backup!

ኪነት በዮዳኒ

01 Jan, 15:35


😂ጉዳጉድ 😲

ትውልደ አሜሪካዊው ከበርቴ ቢል ጌት በሰከንድ ውስጥ ብቻ 1,300$(አንድ ሺህ ሶስት መቶ የአሜሪካ ዶላር) ወደ ኪሱ ያስገባል። (አሁን ባለው የሀገራችን የዶላር ምንዛሬ 150 ሺህ የኢትዮጵያ ብር በሰከንድ !)

እንበልና ኪሱ እያፈሰሰበት መቶ ዶላር እየዘራ ቢሄድ ቆም ብሎ እሱን ለማንሳት አያስብም። ምክንያቱም ዝቅ ብሎ የሚያነሳበት ጊዜ ወይም 30ሴኮንዶች ከፍ ቢልም ስልሳ ሴኮንዶች 39 ወይም 78 ሺህ ዶላሮችን የሚያገኝበት ጊዜው ነውና።

አዘጋጅቶ በማቅረብ:-ዮዳA

ኪነት በዮዳኒ

28 Dec, 20:47


ኪነት በዮዳኒ pinned «መፅሐፍ መግዛት ስትፈልጉ @mexibooks ጎብኙ ። በኮሪደር ምክንያት ሱቁ ስለፈረሰ ፤ በዚህ ታገኙታላችሁ ። ሜክሲኮ አምደ መጻሕፍት | 0919370881 | 🙌 So the owner of the book store is called Eliyas, he is a vintage book collector of many years.…»

ኪነት በዮዳኒ

28 Dec, 20:46


መፅሐፍ መግዛት ስትፈልጉ @mexibooks ጎብኙ ። በኮሪደር ምክንያት ሱቁ ስለፈረሰ ፤ በዚህ ታገኙታላችሁ ። ሜክሲኮ አምደ መጻሕፍት | 0919370881 | 🙌 So the owner of the book store is called Eliyas, he is a vintage book collector of many years. He had a shop in Mexico but the corridor development has hindered his job. but he is active on calls and can sell old and classic books (including the first edition of the books and hard covers) starting from Amharic classic to English classic.

ኪነት በዮዳኒ

28 Dec, 11:48


ፈላስፋው ለ አስር አመት ያክል ከጠፋበት ድንገት አንድ ቀን አደባባይ መሃል ይከሰታል እናም ሌላ ፈላስፋ ጓደኛው አስር አመት ሙሉ የት እንደነበረ ይጠይቀዋል
"ቤቴን ዘግቼ ስለ ዓለም ምንነት እያብሰለሰልኩ ነበር እናም መጨረሻ የዓለምን ትርጉም አስረኛው አመት ላይ አገኘሁት"

"ኧረ ባክህ ይህማ ጥሩ ነው እና የአለም ትርጉም ምን ሆነ?"

"በቃ ዓለም ማለት ድልድይ ማለት ናት" ሲለው ጓደኝየው ፈገግ አለና
"ድልድይ ባትሆንስ?" አለው
"ኧ? "
" ድልድይ ባትሆንስ?"
ፈላስፋዉ በድንጋጤ አይኖቹ ፈጠጡ ወደ ሰማይ ቀና ብሎ አየና

"አንተ እዉነትክን እኮ ነዉ
ልክ ነህ ድልድይ ባትሆንስ?"
ይህን እያልጎመጎመ ከጓደኛው ተለይቶ ወደ ቤቱ...

ኪነት በዮዳኒ

27 Dec, 17:48


https://youtu.be/hsAng_NKbeQ?si=DnX8uSHe8KEld67h

ኪነት በዮዳኒ

26 Dec, 12:17


100% Real !

from @salkan_tube

ኪነት በዮዳኒ

20 Dec, 05:12


ሲያነቃቁን ለምን አንነቃም? ሙተን ይሆን እንዴ?
(አሌክስ አብርሃም)

ለመጀመሪያ ጊዜ self-help book የሚሏቸውን ሳነብ በጣም ነቅቸ ነበር! አስታውሳለሁ የ Rhonda Byrne ን The secret ሳነብ በጣም ከመንቃቴ የተነሳ ለስራ እጀን ከመጠቀም ይልቅ አዕምሮየን ለመጠቀም ወስኘ ነበር። ለምሳሌ መብራት አጥፍቸ ከመተኛት ተኝቸ መብራቱ ልክ እንቅልፍ ሲወስደኝ ይጠፋል ብየ ለራሴ እነግረዋለሁ፤ጧት ስነሳ እንደበራ ባገኘው አልደነቅም፣ ከእንቅልፌ ከመንቃቴ አንድ ደይቃ በፊት በራሱ ጊዜ እንደበራ አምናለሁ። የወሩ የመብራት ሂሳብ ግን የነገረኝ ሌላ ሆነ፤ ተው ወንድሜ በጣም አትንቃ አለኝ። እናም እያጠፋሁ መተኛት ጀመርኩ። ከ1890 ዓ/ም ጀምሮ መብራት ሀይል መብራት ያላጠፋበት ብቸኛ ወር ነበር። ስንነቃ አይወዱ😀

ኦሾን ያነበቡ የኔ ዘመን ወጣቶች ደግሞ "ሐይማኖት ባህል ገለመሌ ከጫነብን ፍዘት ወጣን" አሉና በየመንገዱ ፀጉራቸውን በመፍተል መቆዘም ጀመሩ፤ ይህንንም "ውስጣዊ ንቃት" አሉት። ከአመታት በኋላ ሁሉም ጠበል ገብተው እየጮሁ ከንቃታቸው በጣም ነቁ። በቀን አምስቴ ኡዱ የሚያደርጉ፣ ለጁመዓ የሽቷቸው መዓዛ ከሞያሌ የሚጣራ ፣ እንዴት ያሉ ንፁህ ሙስሊም ወዳጆቸ ሳይቀሩ ጀዝበው ገላቸውን መታጠብ አቁመው ነበርኮ! ስንት ተቀርቶባቸው ተመለሱ። የዛን ሰሞን ወጣቱ ሁሉ ውስጣችን በራልን እያለ ስንት ጨለማ ተከናነበ። ራሳቸውን ያጠፉም ነበሩ። ኦሾና አለቃ ገብርሃና ተረታቸው እንጅ ኑሯቸው አያምርም።

ይሄው በዚህኛው ዘመን ደግሞ አነቃቂወች እንደአሸን ፈሉና "ያሰብከውን ትሆናለህ፣ ነኝ በል፣ አለኝ በል፣ ደርሻለሁ በል፣ እችላለሁ በል፣ በሀሳብህ መኪና አስነሳ፣ አሉ፤ ወጣቱ የሀሳብ መኪና አስነሳ፤ በሀሳብ ሲጋልብ ራሱጋር ተጋጨ፣ ቤተሰቡ ጋር ተጋጨ፣ አገሩ ጋር ተጋጨ፣ፈጣሪው ጋር ተጋጨ ። ከሆነስ ሆነና ለምንድነው በዚህ ዘመን ይሄ ሀሁሉ አነቃቂ ንግግር ያላነቃን? የእውነት የሆነ ጊዜ ያነቃን ነበርኮ፣ እየቆየ ግን እንኳን ሊያነቃን ያስተኛን ጀመረ፤ እኮ ለምን?

የህክምና ባለሙያወች ከተሳሳትኩ አፉ ብለው ያርሙኝና በእነሱ ሙያ Drug tolerance የሚሉት ነገር አለ አሉ፤ በትክክል ከተረዳሁት ለሆነ ህመም የተሰጣችሁ መድሀኒት ከሆነ ጊዜ በኋላ በሽታችሁ ጋር ይግባቡና ፍሬንድ ይሆናሉ። በሽታው መድሃኒቱን ይላመደዋል።ጉቦ እንደበላ ደንብ አስከባሪ በሽታችሁ መንገድ ዳር ሲያሰጣችሁ መድሀኒቱ እንዳላየ ያልፈዋል። ለምሳሌ የእንቅልፍ ችግር ገጠማችሁና በሐኪማችሁ የእንቅልፍ ኪኒን ታዘዘላችሁ እንበል ፤ የመጀመሪያ ሰሞን ድብን ያለ እንቅልፍ ያስወስዳችኋል፤ እየቆየ ሰውነታችሁ ሲላመደው መድሀኒቱን ውጣችሁም ቁልጭ ቁልጭ ስትሉ ታነጋላችሁ። ወይ አይነቱን ወይ መጠኑን ባለሙያ ካልቀየረው በቃ ለውጥ የለም። አይ መጠኑን ራሴ እቀይረዋለሁ ብላችሁ ጨመር አድርጋችሁ ከወሰዳችሁ ደግሞ ትተኙ ይሆናል ግን እንደገና ላትነሱ ትችላላችሁ።

ወደህይወት ስናመጣው እኛ ኢትዮጵያዊያን በአሁኑ ሰዓት ማንኛውንም ማነቃቂያ ከመላመድ አልፈን እንደዘፈን ሸምድደነው አብረን እየደገምነው ነው። ገና ፊቱን ስታዮት አብራችሁ "ብሮሮሮሮሮ" አትሉም?! ለዛ ነው ከነዋሪ መካሪና ዘማሪ የበዛው። የፈለገ ብንመከር ብንዘከር ብንሰበክ ብንወገዝ ወይ ፍንክች። አሁን ሞራል፣ ሐይማኖት፣ የአገርም ይሁን የሰው ፍቅር፣ ይሉኝታ ፣መማር ፣ የራስ ክብር ወዘተ አእምሯችን ተላምዷቸው ተራ ነገር ሁነውብናል።

የሞራል ተቋሞቻችን በሞራል ድሽቀት ከተራው ህዝብ ቀድመው ባፍጢማቸው ተተክለዋል፤ የትዳር ሰባኪወቹ ማግባትና መፍታት መድረክ ላይ እንደመውጣትና መውረድ ቀሏቸዋል፤እንደውም የጓዳቸውን ውድቀት እንደባንዲራ በአደባባይ እየሰቀሉ እዮልን ባይ ሆኑ። አሁን እንደህዝብ ሁለት ነገሮች ብቻ ናቸው የሚያነቁን ወይ (((ብር ማጣት))) አልያም (((ብር ማግኘት))) ይሄ የመጨረሻው ዶዝ(መጠን) ነው! ሰው ክብሬ፣ ገመናየ ፣ማንነቴ የሚለውን ነገር ሁሉ ይዞ ገበያ ከወረደ ምን ይመልሰዋል?! ከዚህ በኋላስ? ምን ያነቃን ይሆን? ምክንያቱም በብር የሚመጣ ንቃት በአንዴ አይረካም፤ እንደአደንዛዢ ዕፅ በየቀኑ መጠኑን እየጨመሩ ካልወሰዱት መጨረሻ የለውም። መመለስም መቀጠልም የማንችልበት አውላላ ሜዳ ላይ የሚያስቀር መርገምት ነው!! ምን ላድርግ ቸገረኝ፣ የማደርገው አጣሁ ልሙት እንዴ ታዲያ በሚል ሰበብ ከሰውነት ድንበር ከምንርቅ በየግላችን "ይሄንኛው ነገሬ ለገበያ ከሚቀርብ ሞቴን እመርጣለሁ" የምንልለት የሆነ መስመር ልናሰምር ግድ ነው። ሰው ራሱ ወስኖ ያሰመረውን መስመር ከሞት በስተቀር ምን ያሻግረዋል?!

ኪነት በዮዳኒ

20 Dec, 03:59


አንዴ ብቻ ይድላኝ
አንዴ ብቻ ልረፍ
አንዴ ብቻ ልኑር
አንዴ ብቻ ልትረፍ
ፋታ ብቻ ላግኝ እንደምፈልገው
እንዴት እንደማለቅስ እኔ ነኝ የማውቀው ።

✍️ሀብታሙ ሀደራ

ኪነት በዮዳኒ

19 Dec, 05:05


እልልታ
ጭብጨባ
ከአውደ ምህረቱ ተነስቶ ይነፍሳል፤
የሰማእቷ ታ'ምር እንደ ጉድ ይወሳል።

"ሰምታኛለች እናቴ..."
"ታውቃለች አርሴማ..."
ክብሯን የሚመጥን
ይገባል ስለት - ጧፍ፣ ጥላ፣ ብር፣ ሻማ።

ሰው ይጸልያል
ሰው ይለምናል ክፍተቱን አይቶ፣
እኔ ከንቱ ግን
የጎደለኝን አላውቅም ከቶ፤
ብቻ እመጣለሁ
ብቻ አይሻለሁ፣
ደጅሽን ስረግጥ እታደሳለሁ።

እዪኣት ያቺን ሴት
ከአትሮንሱ ጀርባ የምትዘምረው
ስምሽን ደጋግማ የምታነሳው፤
እኔ እስከማውቃት
ፊደል የሚያንቃት
ኩልትፍ አንደበት - ነው የነበራት።

ምን ጸልያ ነው አፏ የተፈታ?
ምን ብላሽ ይሆን
ቃል አቅሙን አጥቶ ለእሷ የተረታ?
የእኔማ ምላስ አግድም ለፋፊ
ለ'ንቶ ፈንቶ እንጂ ለጸሎት ታጣፊ።

እይው ያንን ሰው
ኑሮ የደቆሰው
የደስታን እንባ ሞልቶ ሚያፈሰው፤
እኔ እስከማውቀው
ሞት 'ሚናፍቀው
ማጣት በዝቶበት ገዳይ ሚፈልግ
ተስፋን ተነጥቆ
አለመኖርን የሚያነበንብ።
ምን ሰጥተሽው ነው ፊቱ የፈካ?
ምን አግኝቶ ነው
የደስታው መጠን ጣሪያ የነካ?
እኔ ሳቅ አላውቅ እንባም አይገደኝ
መኖርም መሞት ትርጉም አይሰጠኝ፤
ብቻ እመጣለሁ
ብቻ አይሻለሁ፤
ደጅሽን ስረግጥ ነፍስ እገዛለሁ።

✍️ #ኤልዳን

ኪነት በዮዳኒ

17 Dec, 03:20


¹
ገና ወጣት ንፁህ ነበር .....
ያለ  ግብሩ  ወነጀሉት ፤
ይግባኝ  ቢልም አልገባቸው
ግራ ቀኝ ሳይሉ ገ ደ ሉት ።
ከመሬት አጋድመው
አፈ ሙዝ ደግነው እየፎከሩበት
እሳት ያዘለ እርሳስ አርከፈከፉበት ።
²
የእሱስ ይሁን አንዴ ሄደ
እንደ ንፋስ ....ነፍሶ (ደርሶ)
አተረፈው ከሕይወቱ
(ከስቃይ አዳነው ሞቱ !)
ይብላኝ ለኗሪ እናቱ ።
³
ያኔ ፊትለፊቷ....
ልጇን  በመስቀል ላይ የቸነከሩት ለት
ያሰረችበትን የወላድ አንጀቷን
አላቀበለቻት ማርያም መቀነቷን ።
ውስጥ ውስጡን ተከፍታ በሀዘን ዝላለች
ስዕሏ ፊት ቆማ እንዲህ ትላታለች

“ለደረሰበት ምኑ ሊነገር ?
ታውቂው የለም ወይ የልጅን ነገር !?
የልጅን ነገር ታውቂው የለም ወይ ?
አይተሽ የለም ወይ?
ወስደው ሲያዳፉት
አስረው ሲገርፉት
በምስማር ፊትሽ ሲቸነክሩት
አካል ገላውን በደም ሲነክሩት
አይተሽ የለም ወይ?
ታመሽ የለም ወይ?
.
.
.
«ያንቺስ ተነስቷል በሦስት ቀኑ
የኔ ግን ይሄው ስንት ዘመኑ
በአካል በስጋ መች ይገለጣል
ትዝታው ብቻ በሌት ይመጣል ።
እስኪ ንገሪኝ ?
እነዛ አይሁዶች አንቺን
እንደኔ በድለውሻል?
ልጅሽን ገድለው
አታልቅሽ ብለው
ከልክለውሻል?»

የታወቀ ነው.....
ደስታ ቢታሰር በሳቅ ያመልጣል
ሀዘን ፈንቅሎ በእንባ ይወጣል
(እሷ ትላለች ....)
«አልበቃ ብሎ ልጄን የነሱኝ
ባዋጅ በሕጉ እየመለሱኝ
እንደው በወጉ አላስለቀሱኝ »

ብዙ ቀን ሄዶ....ብዙ ቀን አልፎ
ከሕይወት ዛፍ ላይ ዘመን ረግፎ
ጎረቤቶቿ አብረው ሚኖሩ
በየሰርጉ ዳስ በየማ
በሩ
ድግስ ሲጠሩ
ትታደማለች ፤
እንደ ተፅናና ፈገግ ትላለች ።
ሀዘኗ ሳይሽር አውልቃው ማቋን ፤
ዕምባ ዕምባ ይላል ቢቀምሱት ሳቋን ።
እየዋሸች ነው እያስመሰለች
"እንደ ሚኖሩት ልኑር" እያለች ።
(አልተፅናናችም )

ተፅናናች እንዴ?
ፀኣዳ ቢሆን ከላይ ቀሚሷ
የሀዘን ማቋን ካልጣለች ነፍሷ
ውስጧ እንዳዘነ....
ልቧ ተከፍቶ ዘቅዝቆ ጥለት
‘ሞቶ መኖር’ ነው ....
“መፅናናት” ማለት ?
------
BekAlu ShuMye
ነሃሴ 23 — 2016 ዓም

ኪነት በዮዳኒ

13 Dec, 03:20


ጀርባ ይጠና ስትሉ ምን ትዝ አለኝ ...
(አሌክስ አብርሃም)

"ከእያንዳንዱ ስኬታማ ወንድ ጀርባ አንዲት ጠንካራ ሴት አለች" የምትሉት ተደጋጋሚ ጥቅስ አልበዛም? አልሰለቸም? ዝም ስንል እውነት መሰላችሁ? ብዙ ሀብታሞች ከጀርባየ የሊስትሮ ሳጥን እንጅ ሴት ነበረች ሲሉ ተሰምተው አያውቁም! የሆነ ሆኖ ግን እውነት ነው ቢባል እንኳን ከእያንዳንዱ ሰንደል ሰክቶ ከሚዞር ወንድ ጀርባም ፓኮ ሙሉ ሰንደል ይዛ ሲያልቅበት እየለኮሰች የምታቀብል ሴትም አለችኮ! ዋሸሁ? በየሰፈራችሁ ያሉ የአዕምሮ ህመምተኞችን በምን አበዱ ብላችሁ ጠይቁ!

አንዴ ጓደኛየ ጋር በጎፋ ስናልፍ ግንብ ተደግፎ ሲጋራ የሚያጨሰውን ሰውየ እያሳየኝ ሚሊየን ጊዜ የሰማሁትን የዛን "የማትመጣ ሴት ይጠብቃል" የሚባለውን ሰው ታሪክ ሊነግረኝ በመቋመጥ...."ስማ አብርሽ ከዚህ ሰውየ ጀርባ ምን እንዳለ ታውቃለህ?" አለኝ "አዎ! ለኮሪደር ልማት ያልፈረሰ ግንብ ይታየኛል" አልኩት፤ተቀየመኝ!

ለዚህ ሚስኪን ሰው ሁሉም ኢትዮጵያዊ ገጣሚ "ጥበቃ" የሚል ግጥም ፅፏል። ሰውየው በመቆም ብቻ ለኢትዮጵያ ስነፅሁፍ ባበረከተው አስተዋፅኦ አለመሸለሙ ይገርመኛል። በተለይ ሴት ገጣሚያን ሁሉም የሰውየውን ፅናት በግጥሞቻቸው ስላዳነቁ ከሰውየው ይልቅ ቁመው ያልጠበቋቸውን ወንዶች እንደሚያሸሙሩ ያልገባን ይመስላቸዋል። የሆነ ሆኖ ይሄ ሁሉ ግጥምና ዘፈን ሰውየውን ከቆመበት አላንቀሳቀሰውም። የሆነ ቀን ወደአእምሮው ቢመለስ እንኳን ሰንደሉ ሲያልቅበት እየለኮሱ የሚያቀብሉ የጥበብ ሰወች ከኋላው ተሰልፈው አይዞህ እያሉት በየት በኩል? ውድቀታችሁ የጥበበኞችን የመፃፍ ሙድ የሚያነሳሳ "ቪያግራ" ከመሆን ይጠብቃችሁ።

ይችን ጨምሬ ልጨርስ፤ አንድ ታዋቂ የአገራችን ባለሀብት ታሪክ ነው። የሆነች የገጠር ከተማ ገና ፎከታም የአስረኛ ክፍል ተማሪ እያለ አንዲት የሀብታም ልጅ አፈቀረ። ቤተሰቦቿ ያንን ችጋራም የስንቅ ተማሪ ልጃቸው ጋር ሲያዩ አነሰራቸው። "አሁን ይሄ ልጅ ቢያስረግዛት ደሃ የሚባል፣ ሁለት አፍ፣ አራት ሆድ፣ ሰባት ጆሮና ምንም እጅ የሌለው ፍጥረት ልትወልድብን አይደለምን?" አሉና ልጅቱን ወደአዲስ አበባ ላኳት። አዲስ አበባ ያኔ አሜሪካ በሉት። በቀጣዮ ቀን ሁልጊዜ የሚገናኙበት ቦታ ቁሞ ሲጠብቃት የለችም፣ በቀጣዮም ቀን የለችም ፤ በሶስተኛው ቀን ቤተሰቦቿ አዲስ አበባ እንደላኳት ከሰፈሯ ልጅ ሰማ! ልቡ ክፉኛ አዘነ ፣ ደማ ...እንባው በአይኑ ግጥም አለ ....ከተማ ሄዶ ጥንቢራው እስኪዞር መስከር ፈለገ።

ወዲያው ግን እዛው እንደቆመ የገጠር ሰወች እንቁላል ሊሸጡ በዘንቢል ሞልተው ወደከተማ ሲሄዱ ተመለከተ። ያችን ልጅ ለመጋበዝ አልበላም አልጠጣም ብሎ ያጠራቀማት ኪሱ ውስጥ የተቀመጠች አምስት ብር አስታወሰ ፣ ከተማ ባዶ እጀን ከምሄድ አለና ጊዜው ደህና ነበር ያኔ ዘንቢል ሙሉ እንቁላል ገዝቶ ከተማ ወስዶ አትርፎ ሸጠው። ትርፉን ሲያየው ደነገጠ፤ መጠጡን ትቶ አሪፍ ጥብስ በላ። ያ የተኮራመተ የተማሪ አንጀት ላይ ሲያርፍ ጥብሱ እንደድራግ አነቃቃው! ከዛች ቀን ጀምሮ ትምህርቱንም ልጅቱንም ትቶ ንግዱ ላይ አተኮረ ...ዛሬ ከቡና እስከሌጦ፣ ከሪል ስቴት እስከከተማው ሴት የግል ርስቱ ሆኗል። ማን ግጥም ፃፈለት? ማንም። ሊሞዚኑን ተደግፎ ለቆመ ሰው ማን ግጥም ይፅፋል። ገጣሚው ከቅናት የተረፈ ጊዜ አይኖረውም። እንደውም አስደግሞ ነው ይሉታል። ወንድሜ እመነኝ ጠንካራ ከሆንክ ሴቶች ብቻ ሳይሆኑ ወንዶችም አገሮችም መንግስቶችም ዕድሎችም ከኋላህ ናቸው። አያምጣውና እያለቃቀስክ ከቆምክ ግን የተደገፈከው ግምብ ይሸሽሀል።

ለዚህ ሐብታም ባለታሪካችን በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነ በፍቅር ላልወደቀ ሰው የተዘጋጀ ቅኔ እንደሚከተለው እዘርፋለሁ ፦

ደሀ ፍቅርን በቤተሰብ ተከለከለ
ደሀ ፍቅርን በቤተሰብ ተከለከከለ
ዓይኑን ከሴት እግሩን ከትምርት ነቀለ
ሐብታም እከሌ በቆመበት
ከንቁላል ተፈለፈለ
ከሌለህ ከኋላ ማንም የለ

ድገመው!😀

ኪነት በዮዳኒ

12 Dec, 08:51


Thank you🙏

ኪነት በዮዳኒ

12 Dec, 08:43


#የሥራ_ማስታወቂያ

የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት በ81 የሥራ መደቦች በዜሮ ዓመት የሥራ ልምድ ከ800 በላይ እንዲሁም የሥራ ልምድ በሚጠይቁ 41 የሥራ መደቦች ሰራተኞችን አወዳድሮ መቅጠር እንደሚፈልግ አስታውቋል።

አመልካቾች ከታህሳስ 9 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ቅዳሜን ጨምሮ ባሉት 15(አስራ አምስት) ተከታታይ የሥራ ቀናት አስፈላጊ የትምህርትና የሥራ ልምድ ማስረጃችሁን ዋናውንና የማይመለስ ፎቶ ኮፒ በመያዝ፦

📍 በአዲስ አበባ ከተማ ፒያሳ እናት ህንፃ አጠገብ በሚገኘው የተቋሙ ቢሮ፣

📍 በድሬደዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት፣

እንዲሁም በሁሉም ክልሎች የፕሬዝዳንት ጽ/ቤት በአካል ቀርባችሁ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን ተቋሙ ገልጿል።

ስራ ልምድ ለሚጠይቁ የሥራ መደቦች አመልካቾች አግባብነት ያለው የሥራ ልምድ ማቅረብ የሚጠበቅባቸው ሲሆን ዜሮ ዓመት ዲግሪ የትምህርት ደረጃ ለሚጠይቁ ስራ መደቦች ላይ ደግሞ የዩኒቨርስቲ መውጫ ፈተና (Exit Exam) ማስረጃ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።

እንዲሁም የዩኒቨርስቲ መመረቂያ ውጤት ለወንድ 2.5 እና ለሴት 2.00 መሆን አለበት። የትምህርት ደረጃ /Level/ ለሚጠይቁ ስራ መደቦች የCOC ማስረጃ ማቅረብ ይኖርባችኋልም ተብሏል።

ዜሮ ዓመት ለሚጠይቁ ስራ መደቦች ላይ የሚያመለክቱ ተወዳደሪዎች ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ የተመረቁ መሆን አለባቸው የተባለ ሲሆን መስፈርቱን አሟልተው ለሚመረጡ ተወዳዳሪዎች ተቋሙ የሚሰጠውን ስልጠና ለመውሰድ ፍቃደኛ መሆንና ተቋሙ በሚመድብበት ቦታ ለመስራት ፈቃደኛ መሆን ይጠበቅባቸዋል።

የተለያዩ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ሀገር ቋንቋ ክህሎት ያላቸው እንዲሁም መሠረታዊ የኮምፒዩተር ክህሎት (Basic computer skill) ያላቸው ተወዳዳሪዎች ይበረታታሉ ተብሏል።

❗️ተቋሙ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ማስታወቂያውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ ሊሰርዝው እንደሚችል ጠቁሟል።

ዝርዝሩን ይመልከቱ https://ics.gov.et/job/national-job-opening

#Share

@TikvahethMagazine

ኪነት በዮዳኒ

10 Dec, 15:35


#የመጨረሻ

ግን ይሄ ፋሺዝም፣ ልክ እንደ ናዚዝም (እና እንደ ኢምፔሪያሊዝምና እንደ ኮሙኒዝም ራሳቸው) አንዴ ከጀመረ ለከትን አያውቅም፡፡ ማቆሚያ የለውም፡፡ ይዞህ ገደል ካልከተተ፣ ደም ካላፈሰሰ፣ ረክቶ አይቆምም፡፡ ግብዓቱን ሳያይ አይቆምም፡፡ ይሄ ነገሩ ያስፈራኛል፡፡ ለሚያልፍ ቀን፣ የማይተካ ነፍሳቸውን የሚሰዉት የፋሺስት ጭፍሮች ያሳዝኑኛል፡፡ ከፋሺስቶች ጋር ሲተናነቅ የሚረግፈው ምስኪን ልቤን ይነካዋል፡፡

ደግሞ እንዲህ እያልኩም ደጋግሜ አስባለሁ፡- ፋሺስቶቹ - አቅላቸውን ባያጡኮ - ምስኪኖች ነበሩ፡፡ እያልኩ፡፡ የእውነትም ብዙዎቹ፡፡ ናቸው፡፡ ምስኪኖች፡፡ ኤዳም፡፡ ሙሶሊኒም፡፡ ጎብልስም፡፡ ሒትለርም፡፡ ሂምለርም፡፡ እና በየዘመኑ፣ በዘመናችን ጭምር ያሉ ሰው ‹‹በል፣ በል፣ በል›› ብሎ ያፈራቸው፣ የሰው ልጅ ፋሺስቶች፡፡ ፋሺስቶቻችን፡፡ ሁሉንም - ቀርበህ ካየሃቸው - ልባቸው የዋህና ምስኪን ይመስሉኛል፡፡

ብዙዎቹ መሬት ከያዘው ተጨባጭ ዓለም ፈር ለቀዋል፡፡ በምናብ ጦዘዋል፡፡ በራሳቸው ሀሳብ ተጀንጅነዋል፡፡ እያሉ የሉም፡፡ ሳይኖሩ እየኖሩ፣ ብዙ ያጠፋሉ፡፡ ትልቅ መስለው፣ ተነፍተው፣ ተነፋፍተው፣ በመጨረሻ ምስኪን ሆነው ይሞታሉ፡፡ ያሳዝኑኛል፡፡

ይሄ መጽሐፍ የኤዳ ታሪክ የሰፈረበት መጽሐፍ ብቻ አይደለም፡፡ አይመስለኝም፡፡ የሁላችንም ታሪክ ነው፡፡ የሰው ልጅ፣ የሰው ልጆች ታሪክ ነው፡፡ የጥጋብን ጅማሮና መጨረሻ የሚያሳይ ነው፡፡ ብዙ የሚነግረን የጓዳ ታሪክ አለው፡፡ ወደፊት ብዙ ብዙ ብዙ ልጽፍበት እነሳለሁ፡፡ ይቺን አመጸኛ ልብ የታጠቀች፣ ነጻ የኤዳ ነፍስ ግን፣ በግሌ፣ ወደድኩት፡፡ ኤዳ፡፡ የሙሶሊኒ ሴት ልጅ፡፡ ላና፡፡ የስታሊን ሴት ልጅ፡፡ ክብር የሚገባቸው፣ ሁለት ድንቅ መጽሐፎች፡፡

ደሞ ወደፊት ራሳችን የምንጽፈውንስ ማን ያውቃል? እኛስ ፋሺስት የለንም፣ ደራሲ የለንም ያለው ማነው?

ፈጣሪ ይጠብቀን፡፡

በነገራችን ላይ፡- የመጽሐፍን ምትሃቶች፣ የሰው ልጅን ታሪኮች፣ በትዕግሥት ራሳችሁን እየተመለከታችሁ የምታነቡ፣ አስተዋይ ወዳጆቼን፣ እንደ ሁልጊዜው፣ ከልቤ አመሰግናለሁ፡፡ (ደሞ፣ ጽሑፉ በዛ.. ምናለ ብታሳጥረው.. ያልከኝ ልጅ... ሰምቼሀለሁ! - እሺ አሳጥራለሁ!) ለጊዜው ግን.. እያረፍክ!🥰😄)

መልካም ጊዜ፡፡

ከአሰፋ ሀይሉ fb ገፅ የተወሰደ

ኪነት በዮዳኒ

06 Dec, 15:33


#ክፍል_3

የኢትዮጵያው የፋሺስት ዘመቻ ሲጠነሰስ ጀምሮ... ይቺ የሙሶሊኒ ሴት ልጅ - ኤዳ ነበረች፡፡ በእኔ ግምት የወረራውን ታክቲክ የነደፈችውና ለአባቷ ያቀረበችውም ይቺው ሴት ነች፡፡ የምናገረው ያለ ማስረጃ አይደለም፡፡ ኤዳ - ልክ እንደ ወንድሞቿና ባሏ - በአቢሲኒያ ላይ ዘምታ - የአድዋውን የአያቶቿን ሽንፈትና ውርደት ልትበቀል - ለምና ነበር፡፡ አባቷ ሙሶሊኒ - ፋሺዝም ሴቶች እንዳያርጉት የከለከለው ነገር ስለነበር - አውሮፕላን እንዳትለማመድ ከለከላት፡፡ እጅግ ተበሳጭታ አባቷን ጥላ ሄዳለች፡፡

የኤዳ ባል - ኢትዮጵያችን ላይ የመርዝ ቦምብና ጥይት አዝንቦ ሲመለስ 32 ሜዳሊያዎች፣ እና የንጉሡ ልዩ የክብር አርማ የተሸለመው ባሏ ቺያኖ - የኢጣልያ ባለሙሉ ሥልጣን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆኖ የሠራም ነው፡፡ ኤዳ በእንግሊዝ ሄዳ፣ የእንግሊዝ ልዑላንንና የመንግሥት ባለሥልጣናትን ድል ያለ ግብዣ ጠርታ፣ አስተያየታቸውን ትቀበላለች፡፡ ታግባባለች፡፡

በጨዋታ መሐል፣ በወቅቱ በእንግሊዝ እጅግ ተፅዕኖ ፈጣሪ የነበረውንና የአሶሺየትድ ፕሬስን ጨምሮ የበርካታ ፕሬሶች ባለቤት የነበረውን የእንግሊዙን ሎርድ ሮዘርሜርን ትጠይቀዋለች እንደዘበት፡- ‹‹ኢትዮጵያን ብንወር ትቃወሙናላችሁ?›› ብላ፡፡ ለአባቷ ሙሶሊኒ የህዝብ አስተያየት እየሰበሰበች ነው፡፡ ‹‹በፍጹም!›› ይላታል፡፡

በፍጹም ብሎ ቢያበቃ እሰየሁ፡፡ ‹‹እነዚያን የተረገሙ ጥቁሮች ሂዱና ያሻችሁን አድርጓቸው፣ ምንተዳችን!›› ይላታል፡፡ እያነበብኩ አረርኩ፡፡ ይሄ እርጉም ነጫጭባ!! እንዲህ እንዲህ እያለች ኢትዮጵያችንን አስገድዳ ለመድፈር የማትፈነቅለው ድንጋይ የለም! ገረመኝ! ገረሙኝ! ገረመችኝ! ልጂቱን ወድጃት፣ ግን የግፍ ሩጫዋን መጨረሻ ማየት ናፈቀኝ! መጨረሻቸውን ማየት፣ ማንበብ!!

እነ ኤዳ ሙሶሊኒ፣ ሁሉም፣ ያሰቡት ሁሉ ሆነላቸው፡፡ ምስኪኒቱ ኢትዮጵያችን ላይ ተረባረቡ፡፡ በዓለም ላይ በዓይነቱ ተወዳዳሪ ያልተገኘለትን ድራማ፣ ከአሜሪካ እስከ እንግሊዝ፣ ከኢጣልያ እስከ ጀርመን፣ ከጃፓን እስከ ቻይና፣ ከፈረንሣይ እስከ ስፔን ተጠራርተው ሠሩብን፡፡ ግፍን በላያች ዘሩ፡፡ ሞትን በምድራችን አነገሱ፡፡ የአባቶቻቸውን ደም ተወጡ፡፡ ሽንፈታቸውን ተበቀሉ፡፡ ገና ለወደፊቱ ዘመን ድረስ እንደ ሀገራችንን እንደ ካንሰር የሚጣቧትን መንጠቆ ዜጎች በአምሳላቸው ተብትበው በመካከላችን ተከሉብን፡፡..

ኢጣልያ ኢምፓየር ሆነች! ዱቼ ሙሶሊኒ ሁሌም ትክክል ነው ተባለ፡፡ አምላክ መሆን ቃጣው፡፡ ኤዳ አውሮፓ ጠበበቻት፡፡ ሮማ አልበቃት አለች፡፡ ሻንጋይን ጨፍራ አልጨርስ አለቻት፡፡ ዓለም ሁሉ በሽበሽ፣ ህይወት ሁሉ ሙሉ፣ ሜዳው ሁሉ የድልና የሙላት እሸት መላበት፡፡ ግን ይሄ ሁሉ - በእኛ ደም ላይ የበቀለ የፋሺስት እሸት ነበር፡፡

መጨረሻቸው ይገርማል፡፡ ሁሉም ኃይለሥላሴ እንደተነበዩት ነበር፡፡ እኛ ላይ የወረደው መርዝ፣ እናንተን ሣያገኝ የሚቀር ከመሰላችሁ ተሳስታችኋል፡፡ የኛን ሞትና ለቅሶ ስንነግራችሁ ስለራሳችሁ አልቅሱ፡፡ ነበር ያሏቸው፡፡ ፋሺዝም ሞት ነው፡፡ መኪና ያለ ነዳጅ እንደማይንቀሳቀሰው፣ ይላል ሙሶሊኒ፣ የፋሺዝም ታሪክም፣ ያለ ደም አይንቀሳቀስም፡፡ የደም ታሪክ ነው፡፡ ግን ያ በደም ላይ የበቀለ የስኬት ታሪክ መልሶ በደም እንደሚጠናቀቅ የገባቸው ጥቂቶች ነበሩ፡፡

እኛን ኢትዮጵያውያንን በመርዝ ጋዝና በታንኮች በባለሞተር አውቶማቲክ ጠመንጃዎች ጨርሰው ሀገራችንን ወሰዱ፡፡ አልባኒያም ወረዱ፡፡ ስፔንም አልቀራቸው፡፡ ግሪክም ገብተዋል፡፡ ራሺያም ዘመቱ፡፡ በአንድ የስኬታቸው ጫፍ ላይ - የኢትዮጵያ ወረራቸውን የሚያሳይ ‹‹አቡነ ማሲያስ›› የሚል ፊልም ሲሠሩ፣ የበጀቱት ባጀት በወቅቱ ሆሊውዶችን ራሱ ያስደነገጠ፣ በሚሊዮኖች የሚቆጠር ሊሬ ነበር፡፡ ገንዘቡን ዘሩት፡፡ እና ፊልሙ ሲቀረጽ፣ 11 ሺህ ሻሞላ የታጠቁ ተዋጊዎች፣ እና 4ሺ500 ፈረሶችን ጭነው አምጥተው፣ ቀለብ እየሰፈሩ፣ አበል እየቆረጡ፣ ፊልሙን ቀርጸው መርቀዋል፡፡

የሮማ ሙዝየሞች፣ በተወረሱና በተዘረፉ ወርቆች፣ ቅርሶችና ጽላቶች ተሞልተው ነበር፡፡ ለህዝብ እይታ ክፍት የሆኑ የዱር እንስሳት ማቆያዎች፣ የአሣ አኳሪየሞች በግዙፍነታቸውና በዝርያቸው ብዛት ከዓለም ተወዳዳሪ ጠፍቶላቸው ነበር፡፡ ለሙሶሊኒ በግሉ ከየዓለሙ የሚላኩለት ከአንበሳ እስከ ካንጋሩ፣ ከነብር እስከ ጥንቸል፣ ከኮብራ እስከ በቀቀን፣ የመኖሪያ ቅጽሩን መካነ አራዊት አስመስሎት ተቸግሮ ነበር፡፡

የጥንት የሮማ ነገሥታት፣ የእነ አውጉስተስ ቄሳርና የእነ ማርከስ ኦርሌየስ እጅግ ግዙፍ ኃውልቶች፣ ከተቀበሩበት፣ ካረጁበት እየወጡ ሮማን አልብሰዋት ነበር፡፡ የፈረስ እሽቅድምድም ሽልማቱ ሚሊየን ሊሬዎች ናቸው፡፡ ከዓለም ፈረሰኞች ይጎርፋሉ፡፡ የኦስካርን ሽልማት የሚያስንቅ ‹‹የኮፓ ሙሶሊኒ›› የጥበብ ሥራዎች ሽልማት ሁሉ ተፈጠረ፡፡ ሁሉም በሽበሽ ሆነ፡፡ የጦር አውሮፕላኖች ብዛት በብዙ ሺህዎች የሚቆጠር ነበር፡፡

በመጨረሻስ? ያሸተው ሁሉ ነገር በዓይናቸው ፊት ረገፈ፡፡ ብዙዎቹ በሞት ተነጠቁ፡፡ ብዙዎቹ ጀግኖች ተዋረዱ፡፡ የድል ዜናዎቻቸው ሁሉ በሽንፈትና በውርደት ታሪክ ተተኩ፡፡ ሙሶሊኒ ከስልጣን ተባሮ ታሰረ፡፡ ተፈቶ ነግሶ፣ ተዋርዶ ከነፍቅረኛው ተገድሎ፣ ተሰቅሎ ሞተ፡፡

ከኢትዮጵያ ሜዳሊያ ጭነው የሄዱ ልጆቹ ቪቶሪዮ - ወደ ብራዚል ኮበለለ፡፡ ብሩኖ - በአውሮፕላን ሙከራ በረራ ተከስክሶ ሞተ፡፡ የኤዳ ባል ቺያኖ - በራሱ በፋሺስት አባቷ ችሎት ተፈርዶበት፣ በጥይት ተደብድቦ ተገደለ፡፡ ኤዳ - ከስንት ሞትና መከራ ተርፋ፣ ከበቀል ሸሽታ፣ ከነ ሶስት ልጆቿ በውርደትና በቁም እስር ወደ ስዊስ ተሰደደች፡፡

የኢትዮጵያ ወረራ በታወጀ ማግሥት - ሙሶሊኒ የሮማን ህዝብ - ሊግኦፍ ኔሽንስ ማዕቀብ ጥሎብናልና የሮማ ህዝብ ያለህን የወርቅና የብር የሠርግ ቀለበትና ጌጥ እያወጣህ ስጠን፣ በጋራ ተነስተን ኢትዮጵያን አይቀጡ ቅጣት እንቅጣት የሚል ‹‹ብሔራዊ ጥሪ›› ሲደረግለት፣ የጣልያን ህዝብ በአንድ ቀን፣ በአንድ ጀምበር ያዋጣውን የሰርግ ቀለበት ክምር - በተራሮች የሚገለጽ ነበር፡፡ 37 ቶን የወርቅ፣ እና 115 ቶን የብር ቀለበቶች በኢጣልያ የጌጣጌጥ ተራራን ሠርተው ነበር ለሙሶሊኒ ያገቡት፡፡

የሮማ ህዝብ ኋላ ታሪኮቹ ሁሉ በውርደት ሲጠናቀቁ፣ የሚበላው አጥቶ፣ ወደ ዱር አራዊት መጠበቂያ እየሄደ፣ ሽኮኮዎችንና ኤሊዎችን፣ አጋዘኖችንና ፒኮኮችን ሳይቀር መብላት ጀመረ፡፡ በመጨረሻ ስጋ ተከለከለ፡፡ ጥቂት ሥጋ የተያዘባቸው ፋሺስቶች ይረሸኑ ጀመር፡፡ ኋለ ጀርመኖች መጥተው፣ የእነ አውጉስተስንና ማርከስ ኦርሊየስን ትልልቅ ሀውልቶች፣ የተኩስ ዒላማ መለማመጃ አደረጓቸው፡፡ ከመቶ ሺኅ ዘማቾች - ራሺያዎች 90ሺህውን ማረኳቸው፡፡ ኋላ ከምርኮኞቹ በህይወት ተርፎ ከራሺያ ምድር የወጣው 4ሺህ አይሞላም፡፡

ፋሺዝም - በኤዳ ህይወት በኩል ሲተረክ - ብዙው ነገሩ ደስስ ይላል፡፡ የፋሺዝም ታሪክ የራሳችንም ታሪክ ነው፡፡ የኤዳ ህይወት፣ የእኔም ህይወት ነው፡፡ ይቺ ተሸላሚ ደራሲት - ካሮላይን ሙርሄድ - ብዙውን ፋሺዝምን እንድወደው አድርጋኛለች፡፡ ፋሺሺም ምትሃቱ ደስ ይላል፡፡ ሰዎችን ለትልቅ ነገር ሲያነሳሳ፡፡ እንደ ሃሺሽ ለልብ የሚሰጠው የበላይነት ስሜትም ደስ ይላል፡፡.. በዜጎች ላይ የሚፈጥረው አርበኝነትም ያስቀናል፡፡

ኪነት በዮዳኒ

06 Dec, 10:11


"ህሊና" አለቺኝ
'ወዬ ' አልኳት....

' ታውቃለህ በሞተ ሰው አቀናለሁ። ባለው ሰላም፣ በሌለው ንብረት፣ በምንምነቱ አቀናለሁ። ማንም መጥቶ አይረብሸውም፣ ምንም አያስጨንቀውም---አያስቀናም?'

"እ....."


#me_yami

ኪነት በዮዳኒ

03 Dec, 15:31


#ክፍል_2

አንዲት ሴት ናት፡፡ አባቴ ተዘቅዝቆ ተሰቅሏል፡፡ ሥጋው ተተልትሏል፡፡ ልብሶቹ በላዩ ተቦጫጭቀዋል፡፡ ደሙ አካሉን ሁሉ በክሎታል፡፡ እና ከዚያ ፎቶ መካከል አንዲት ሴት አለች፡፡ ያቺ ሴት አባቴ አጠገብ ቆማ፣ የተተለተለና የተዋረደ አካሉን በኩራት ዘና ብላ፣ በደስታ ተሞልታ፣ ፈገግ ብላ ጥርሶቿን ገልጣ እየሣቀች ነው የምትመለከተው፡፡ ሁሉን ነገር እሺ ይሁን ብያለሁ፡፡ ሁሉንም እሺ ተቀብያለሁ፡፡ ይሄን የልጅቷን ሳቅ ግን...፡፡ እንዴት ሣቅ?

በፍጹም ልረዳው አልቻልኩም፡፡ በፍጹም አልኖርኩበትም፡፡ ያንን የልጅቷን ሣቅ ሳስብ ውስጤን ይረብሸዋል፡፡ በዚያ መልክ፣ በዚያ ቦታ ሣቅ? እንዴት ይመጣልሃል? በእውነት አንድ ያልተረዳሁት፣ ያልኖርኩት፣ የሆነ ዓይነት ልብ መኖር አለበት እላለሁ፡፡ ያንን አልኖርኩትም፡፡

በህይወቴ የተድላና የክብር ከፍታ ጫፍ ላይ በደረስኩበት ጊዜ እንኳ፣ የሌሎች መከራ፣ በጣም የምጠላቸው ሰዎች መከራ ራሱ፣ ውስጤ ዘልቆ የሚሰማኝ ሰው ነበርኩ፣ ነኝ፡፡ በሰዎች መከራ ስቄ አላውቅም፡፡ ያ ሳቅ የሰው አይመስለኝም፡፡ የሰው ልጅ እስከዚያ ርቀት ድረስ መሄድ ያለበት አይመስለኝም፡፡ ብንለያይም፣ ብንጠላላም፣ ግን ሰው መሆናችንን ማመን አለብን፡፡ ሰው ነን፡፡ ሰውነታችንን መርሳት የለብንም፡፡

አባቴን ጨምሮ፣ በአንድ ወቅት የሚሊዮኖችን ውዳሴ ተከትለው፣ በውስጣቸው አምላክነት የተሰማቸውም ሞተዋል፡፡ በዓለም ሁሉ ዓይን ውስጥ ገባህ፣ ከዓለም ሁሉ ዓይኖች ተሸሽገህ አዘገምክ፣ የሁላችንም ጉዞ መጠናቀቁ አይቀርልንም፡፡ በመጨረሻ ሁላችንም ሰው ነን፡፡ መዋቲ ነን፡፡ በሰዎች ሞት መርካት እሺ፡፡ ቂምን መወጣት እሺ፡፡ ግን ያ ሣቅ፡፡ የሆነ ከሰውነት የተነጠቀ ሆነብኝ፡፡ እስካሁን ይገርመኛል፡፡
በኢትዮጵያችን ሠማይ ላይ፡፡ የሞት መልዕክተኞችን መርቃ የላከችው፡፡ ለሚሊየኖች ነፍስ የማትሳሳው፡፡ ኤዳ ሙሶሊኒን፡፡ አንዲት የማትቋቋማት ሣቅ ጨርሳ ድል ነሣቻት፡፡

ይህ የኤዳ ሙሶሊኒ የህይወት ታሪክ፣ ከነግርጌ ማስታወሻዎቹ ከ400 የለጠቁ ገጾች አሉት፡፡ በህይወቴ፣ በሙሉ ቀልቤ፣ በሙሉ ልቤ፣ በሙሉ አንጎሌ፣ በሙሉ ሀሳቤ፣ በሙሉው እኔ በ24 ሰዓት አንብቤ (ብቻ ሳይሆን መጥጬ!) የጨረስኩት፡፡ ስለ ጣልያን ብቻ ሳይሆን፣ ስለ ሀገሬ ኢትዮጵያ፣ እጅግ ብዙ፣ ብዙ አዳዲስ ነገሮችን ከራሱ ከፈረሱ አንደበት ተጠግቼ እያነፈነፍኩ እንድቀስም፣ እንድማር፣ እና እንድመረምር ያደረገኝ እጅግ ሲበዛ ድንቅና ውብ መጽሐፍ ነው፡፡

ገና የመጽሐፉን 50 ገጾች ሳላገባድድ፣ አጻጻፉ፣ እና አተራረኩ፣ ዘዬው፣ ገለጻው፣ ሁሉነገሩ፣ አንድ በጣም የማውቀው ደራሲ የጻፈው ሆነብኝ፡፡ እና ድንገት ደግሜ የሽፋን ገጹን ገልበጥ አድርጌ ተመለከትኩት፡፡ የደራሲው ስም፡- ‹‹ካሮላይን ሙርሄድ›› ይላል፡፡ ሙርሄድ የሚለው ስም ጭንቅላቴ ውስጥ አቃጨለ፡፡ ከነተባ ውብ አተራረክ ዘዬው፡፡ ማነበር ሙርሄድ? ማንነበር?... ድንገት እንደ ምሽት መብረቅ፣ ድንገት... ትዝዝዝዝ.... አለኝ!! ብልጭ አለልኝ ስሙ! አለን ሙርሄድ!! አለን ሙርሄድ ማነበር?

አምስት ዓመታት ወደኋላ፡፡ የብሉናይል (የእኛን አባይ ወንዝን) እና የዋይት ናይልን ታሪኮች በሁለት መጽሐፎች ውብ አድርጎ የጻፈው፣ የአጼ ቴዎድሮስን አነሳስና ውድቀት፣ እስከመጨረሻዋ የወደቁባት መሬትና የለበሷትን ሀገርልብስ፣ ሳትቀር ተጠግቶ የጻፈልን፡፡ ያ ድንቅ የታሪክ ጸሐፊ ነው፡፡ ሙርሄድ፡፡ የዚህች ደራሲ ስም የእርሱን ስም አስከትሏል፡፡ ተንደርድሬ ኢንተርኔቴን ከፈትኩ፡፡ የህይወት ታሪኩን ገና ከፈት ሳደርግ፡- አንዲት ብቸኛ ልጅ ነበረችው ይላል ደራሲው፡፡ ስሟ? ካሮላይን ሙርሄድ፡፡

ተደመምኩ! እንደ አባቷ፣ በአባቷ ልሳን፣ በአባቷ ልክ በተሠፋ ጥልቅ ዕውቀትና የሰው ልጅ ቱባ የህይወት ተሞክሮ የምትጽፍ ድንቅ ደራሲት፡፡ ካሮላይን ሙርሄድ፡፡ በአጻጻፏ አወቅኳት፡፡ የደራሲውን አባቷን መንታ መጽሐፍት ወዲያው ፈልጌ አገኘኋቸው፣ እጅግ ደስ እያለኝ ማንበቤን ቀጠልኩ፡፡

ከሙሶሊኒ ሴት ልጅ - ከኤዳ ሙሶሊኒ ህይወት ላይ - ዓይኔን መንቀል አልቻልኩም፡፡ ከዘመኑ ላይ፡፡ ከዘመኑ ፋሺስቶች፡፡ ከዘመኑ ኢትዮጵያውያን፡፡ ከዘመኑ እንግሊዞች፡፡ ከዘመኑ ናዚዎች፡፡ ከዘመኑ አሜሪካኖች፡፡ ከዘመኑ የሰው ልጅ፡፡ ከዘመኑ ኤዳ ላይ፡፡ መጽሐፉን ሳላገባድድ ዓይኖቼን መንቀል አልቻልኩም፡፡ ድህረ-ታሪኩ አልቀረኝም፡፡ ምስጋናው ሁሉ አልቀረኝም፡፡ ስጨርስ እፎይ አልኩ፡፡

አንዳንድ ብዕሮች አሉ፡፡ አንዳንድ ተራኪዎች አሉ፡፡ እና አንዳንድ ታሪኮች ደሞ አሉ፡፡ ለነፍስህ፣ ለማንነትህ፣ ለሥሪትህ - እጅግ ቅርብ የሆኑ፡፡ እና በአጋጣሚ የምታገኛቸው፡፡ ይሄ አስደናቂ የሙሶሊኒ ሴት ልጅ የህይወት ታሪክ መጽሐፍ እንደዚያ ነው፡፡ ሙሉው፡፡ ሙሉው ጉድ ነው፡፡

በአንዲት ሴትና በአባቷ፣ እና አባቷ ከተደባዳቢነት ህይወት ተነስቶ በሁሉንቻይነት በተመለከበት፣ እና ተዘቅዝቆ በተሰቀለበት ምድር በኩል እያጠነጠነ፣ የወቅቱን የዓለም ታሪክ በአንድ መጽሐፍ ገበታ ላይ ቁጭ አድርጋዋለች ይቺ ድንቅ ደራሲ፡፡ የአባቷ ልጅ፡፡ ግን ከየት ጀምሬ የት ልጨርሰው? ስለ የትኛው የኤዳ ታሪክ ላንሳ? ስለ ስንቶቹ?

ለመሆኑ.. ኢትዮጵያ በኢጣልያ እንድትወረር፣ አውሮፓዎችን፣ አሜሪካኖችን፣ ጀርመኖችን፣ ጃፓኖችን፣ ቻይናዎችን፣ ፈረንሳዮችን፣ እየዞረች ያግባባችው፣ የለመነችው፣ ያሳካችው ይቺ ኤዳ የተባለች የሙሶሊኒ ልጅ ናት ቢባል ማን ያምናል? ፋሺስት ኢጣልያ ኢትዮጵያን ስትወርር፣ በወረራው በአዛዥነት የተሰለፉትን ባሏንና ሁለት ታናናሽ ወንድሞቿን (የሙሶሊኒን ልጆች ማለት ነው)፣ እዚህ ግብጽ ድረስ መጥታ ስቃ፣ አጨብጭባ፣ መርቃ ሸኝታ ተመልሳለች ቢባል ማን ያምናል ይቺን ሴት?

የኤዳ ባል (ጋሊያኖ ቺያኖ) እና ታናሽ ወንድሟ (ቤኒቶ ቪቶሪዮ ሙሶሊኒ) የመጀመሪያውን ተከዜ ወንዝ ላይ የተገነባውን ድልድይ አውሮፕላን እያበረሩ ሄደው፣ በቦምብ እንዲያፈርሱ ትዕዛዝ የተሰጣቸውና ያፈረሱት እነሱ ናቸው ቢባል ማን ያምን ይሆን? ማርሻል ባዶግሊዮ በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ 316 ቶን ክብደት ያለው የመርዝ ጋዝ እንዲያዘንብ በአባቷ ተመርቆ ሲሸኝ አብራ ቁጭ ብላ ሻይ እያስተናገደች የሸኘችው ይቺ ሴት ናት ቢባል ማን ያምናል?

የኤዳ ባል ቺያኖ ከኢትዮጵያ ወረራ ወደጣልያን በድል ሲመለስ፣ 32 ሜዳሊያዎችን፣ ተከታይ ወንድሟ ቪቶሪዮ ሙሶሊኒ 36 ሜዳሊያዎችን፣ የእርሱ ታናሽ የሆነው ወንድሟ ብሩኖ ሙሶሊኒ ደሞ 34 ሜዳሊያዎችን ተሸክመው ሲመለሱ፣ በደስታ እላያቸው ላይ እየተጠመጠመች የተቀበለቻቸው ይቺ ኤዳ ነች ሲባል... እውን አንደ ኢትዮጵያዊ አንባቢ ምን ይሰማዋል?

የኤዳ ታናሽ ወንድም - ቪቶሪዮ - ከኢትዮጵያው የፋሺስት ዘመቻ መልስ - ‹‹ቮሊ ሱሌ አሜቤ›› በሚል ርዕስ ያሳተመው፣ የኢትዮጵያው ዘመቻ ሙሉ ታሪክ የተካተተበት በወቅቱ እጅግ ተነባቢ የሆነ የህይወት ታሪክ መጽሐፍ ሁሉ አለው፡፡ በዚያ መጽሐፍ ላይ - ቪቶሪዮ - እንዴት ከሠማይ ሆነው - በአውሮፕላን - የኢትዮጵያን ሴቶችና ህጻናት፣ ምስኪን ገበሬዎች ሳይቀር ዒላማ አድርገው እንደ ገብስ ክምር በጥይት ዝናብ እያጨዱ ይከምሩ እንደነበር መጻፉን - ይቺ ደራሲት ካሮላይን ሙርሄድ - በትዝብት አንደበት ትገልጽና - ኋላ ላይ ይቅርታ ጠይቆበታል ብላ ግፉን ታስተባብልለታለች፡፡

ኪነት በዮዳኒ

29 Nov, 15:27


ክፍል 1

የሙሶሊኒ (እንዲሁም የስታሊን) ሴት ልጅ!

‹‹በራሷ የምትመራ፣ ሁሉንም የሆነች፣ በሁላችን ውስጥ ያለች፣ ዘመንንም ድንበርንም የምትሻገር፣ በዓለም እጅግ አደገኛዋ ሴት››

በቅርብ ጊዜ እየተጻፉ ያሉ መጽሐፎች ጉድ ናቸው፡፡ ብዙው የዘመናችን ነገር ወደ ቪዲዮና ኢንተርኔቱ ዓለም ተቀይሮ የመጻፍና የማንበብ ነገር አለቀለት፣ አበቃለት ሲባል፣ ጭራሽ ከቀድሞው ዘመን ብሶ ቁጭ ብሏል፡፡ ስነጽሑፍ እጅግ ረቋል፡፡ የሰው ልጅን ህይወት የምናይበት የህይወት መነፅር እጅግ በዝቷል፡፡ እጅግ መጥቋል፡፡

በተለይ የሰዎች እውነተኛ ታሪክ፡፡ በአስደማሚ ብዕረኞች ለጉድ እየተተረከ፣ ያለፈውን ዘመን የሚገለጡ ገጾች ባሉት አንድ የተጠረዘ መጽሐፍ በኩል፣ ሥጋና ነፍስ አላብሰው፣ ወደዚህ ዘመን ትውልድ ልብና የፍርድ ሚዛን እያቀረቡት ነው፡፡ መጽሐፍት አሰልቺነታቸው ቀርቷል፡፡ ስነጽሑፍ የተጠጋውን ሁሉ ቀልብ የሚገዛ ምትሃት ሆኗል፡፡ የሰው ልጅ የግል ታሪክ፣ ዘመንን ተሻግሮ ያነበበውን ልብ ሙሉ በሙሉ የሚቆጣጠር ዘመን ተሻጋሪ መስተፋቅር ሆኗል፡፡

ባለፈው ሮዝሜሪ ሱሊቫን የተባለች ደራሲ - የአንዲትን እንስት ታሪክ ህይወት በመጽሐፏ ከትባ፣ የዓለምን አንባቢ ቀልብ ገዛች፡፡ ደራሲዋ የወጣላት የስነጽሑፍ ኤሜሪተስ ፕሮፌሰርም ነች፡፡ የዛሬ 5 ዓመት የጻፈችው ይህ ጉደኛ መጽሐፍ ‹‹የስታሊን ሴት ልጅ›› የተሰኘ ነበር፡፡ መጽሐፉ፣ ብቸኛዋን የጆሴፍ ስታሊን ሴት ልጅ - ስቬትላናን ህይወት ይተርካል፡፡

ላና - ከሚገመትና ከሚታወቅ የቅምጥል ህይወቷ ባሻገር - ከዓለም ዓይኖች ተከልላ ያለፈችባቸውን ቀጫጭን መሪርም ጣፋጭም በአደጋና በብቸኝነት የተዋጡ ህይወት ፈለጎች ልብ በሚነካ አኳኋን የሚያስቃኝ መጽሐፍ ነው፡፡ መጽሐፉ የራሺያንና የምዕራቡን ዓለም እንደ ሀር የተፈተለ የጋራ ፍቅርና ጥላቻ ታሪክ፣ ከአንዲት ምስኪን መለመላ እንስት ነፍስ ጋር በአስደማሚ ዕውቀትና ምናብ እያሰናሰለ ይተርካል፡፡

ያ የሮዝሜሪ መጽሐፍ ስለተነካ ልብ እየጻፈ ልብን እጅግ ይነካል፡፡ የስታሊን ሴት ልጅ ህይወት በመጽሐፍ በኩል ወደየሰዉ ልብ ገብቶ፣ የገለጠውን ሁሉ አስደመመ፡፡ ከመቼው በየቋንቋው ተተርጉሞ ዓለምን አዳረሰ፡፡ አነጋገረ፡፡ በቴክኖሎጂ ብዛት የማይነጥፈው ይሄ ስነጽሑፍ የሚሉት ኃያል መንፈስ፣ እንዴት ያለ ድንቅ ጥበብ ነው? ድንቅ ጸሐፊ፣ ድንቅ አዋቂ፣ ድንቅ የሰው ልጆችን የልብ ውስጥ ጠልቆ የተረዳ፣ ድንቅ የዚችን ዓለም ነገር በየስርቻው አስሶ የደረሰበት፣ ድንቅ ደራሲ፣ የድንቅ አዋቂ እጆች.. ያለፈውን ዘመን ከነታደሉና ከነፈረደባቸው ነዋሪዎቹ በምናብ ነፍስ ዘርቶ እያመጣ፣ እንደ አዲስ ያነጋግራል፡፡ በአንድ ዘመን እየኖርን፣ ሁለት ሶስት ዘመኖችን ይሸልመናል፡፡ ለመጽሐፉ ተጨበጨበ፡፡

ያ የስታሊን ሴት ልጅ ታሪክ ገና ወረቱ አላከተመም፡፡ ደሞ ካሮላይን ሙርሄድ የተባለች ሌላ እንስት ደራሲ፣ የዛሬ አስር ወር ደሞ መጣች፡፡ ‹‹የሙሶሊኒ ሴት ልጅ›› የሚል ሌላ አስማተኛ መጽሐፍ ይዛ፡፡ ይኸው ይቺ ካሮላይን የተባለች ምትሃተኛ ጸሐፊ፣ አርጅተው የማይሞቱ፣ በጊዜ የማይነጥፉ፣ ከሰው ልጅ ጋር ዘለዓለም ነዋሪ የሆኑ የሰው ልጅ የውስጥ፣ የልብ፣ የተኖሩ፣ የተወጡ፣ የተወረዱ ህይወቶችን በመጽሐፏ ሞልታ፣ ወደመጽሐፏ ደፍረው የተጠጉትን አንባቢዎች ሁሉ ልብ ነካች፡፡ በሰው ህይወት አዘኔታና ፍቅር አጥለቀለቀች፡፡

ኤዳ - በመልክ ቁርጥ ራሱን ዱቼውን አባቷን ሙሶሊኒን የመሰለች - እንደ ዓይኑ ብሌን የሚሳሳላት፣ እና በአምሳሉ የቀረጻት፣ ቀዳሚት ልጁ ነች፡፡ ሁሉነገሩ ነች፡፡ ብዙውን ነገሩን አውርሷታል፡፡ አውሮፓን በተረከዞቿ ሥር ያዋለች፣ የዓለም ሠራዊት ቢንጋጋ ከሃሳቧ የማይቀለብሳት፣ በአንበሳ ደቦሎች ስትጫወት ያደገች፣ ዓለም የሚንቀጠቀጥለትን ሒትለርን በፊቱ በፉከራ እያቅራራች ልክ ልኩን የነገረች፣ ማንንም ምንንም የማትፈራ፣ በማንም የማትገራ፣ እና በመጨረሻም ብዙዎቹን መከራና ስብራቶቿንም ብቻዋን በፀጥታ ያወራረደች፣ የታደለችም፣ ደግሞ ያልታደለችና የፈረደባትም የፋሺስት ኢጣልያ እንቡጥ ነች!

ደራሲት ሮዝሜሪ ታሪኳን የጻፈችላት ስቬትላና ስታሊን - በ85 ዓመቷ ነው ከዚህ ዓለም የተለየችው፡፡ ደራሲት ካሮላይን የምትተርካት ኤዳ ሙሶሊኒ ደሞ በ84 ዓመቷ፡፡ የላናን ፍቅረኛ ስታሊን ነጥቆ፣ ልቧን ሰብሮታል፣ በሳይቤሪያ የጉልበት ማጎሪያ ፍዳውን አብልቶታል፡፡ የኤዳን የልጅነት ፍቅረኛና ባል፣ እና የሶስት ልጆቿን አባት ደሞ፣ ሙሶሊኒ ነጥቆ፣ በእስር አማቅቆ፣ በጥይት አስደብድቦ አስገድሎ፣ ልቧን አድምቶታል፡፡...

ላና በህንድ በኩል አድርጋ፣ የሩሲያን ድንበር ተሻግራ፣ ከኮሙኒስቶች መዳፍ አምልጣለች፡፡ ኤዳ ደሞ በበኩሏ፣ በስዊዘርላንድ ድንበር ተሻግራ፣ ከፋሺስቶችም ከጸረ-ፋሺስቶችም፣ ከጀርመኖችም፣ ከእንግሊዞችም፣ ከሁሉም እጅ አፈትልካ ነፍሷን አትርፋለች፡፡ ላና ስሟን ቀይራለች፡፡ ኤዳም እንደዚያው፡፡..

እነዚህ ሁለቱ ዓለም በትክክል የልባቸውን ገመና ገልጦ ያላየላቸው የሁለት አይምሬ ኃያላን አምባገነን ሴቶች ሎጆች፣ ላና እና ኤዳ፣ ብዙ ተመሳሳይ ህይወት፣ ብዙ ተመሳሳይ ቁስል፣ ብዙ ተመሣሣይ ዕጣፈንታ አላቸው፡፡ የላና ህይወት በሮዝሜሪ ብዕር በተተከረ በ5 ዓመቱ፣ ደሞ የኤዳ ህይወት በካሮላይን ብዕር ይተረክልን ገባ፡፡

መንዶቻችን ይለያያሉ፡፡ ታሪካችንና የምናውቃቸው ስሞች ይለያያሉ፡፡ ዘመናችን ይለያያል፡፡ ግን ከርታታዋ፣ እምቢ ባይዋ ነፍሳችን አንድ ታደርገናለች፡፡ ገጻችን ሲለይ፣ ልባችን አንድ ያደርገናል፡፡ የምንሸሸው ስቃይና፣ የደበቅነው ቁስል፣ ከውስጣችን የምንሻው ምኞት፣ ሰብዓዊ ሥሪታችን... ከሚለያየው ስማችንና መልካችን ባሻገር - ቁርጥ አንድ ነው፡፡ ይሄ ይሄ ነገር እጅግ ግርም ብሎኝ አላባራ ያለ ጉድ ሆኖብኛል፡፡..

ራሺያና ኢጣልያ፣ ብሪታንያና ኢትዮጵያ፡፡ ታሪካችን ይሰናሰላል፡፡ ይገናኛል፡፡ ዓለም ጠባብ ነች፡፡ ተዋናዮቿ በተለያዩ ገቢሮች ብቅ እያልን፣ የተገመደልንን ተመሳሳይ ድርሰት እንመደርካለን፡፡ ይቺ ትያትር ዓለም፡፡ ይህ ሁሉ ትያትረኛ ቢልዮን የዓለም ፍጥረት፡፡ እና ሁላችንም በአንድ ትልቅ መድረክ ላይ፣ አንድ ትልቅ የህይወትን ዕጣፈንታ፣ በተለያዩ ገጸባህርያት የምንወጣ፣ ቁርጥ አንድ ፍጥረቶች መሆናችንን የሚያረዳን ምትሃተኛ የደራስያን ብዕር፡፡... ሁሉም ነገር ጉድ ይሆንብኛል፡፡ መጽሐፎች ምትሃት ሆነዋል፡፡ የሰው ልጅ በደራስያን እጅ ወደ አንድ ልብ፣ ወደ አንድ እስትንፋስ፡፡ ወደ አንድ እንባና ወደተለያየ ፍንጥቅጥቅታ ሳቅ እየተቀየረ ነው፡፡

ኤዳ ሙሶሊኒ - ብዙ ዓመታትን አንገቷን ደፍታ፣ አንደበቷን ለጉማ ኖራ ስታበቃ፣ በስተመጨረሻ ለአንድ ደራሲ እንዲህ ስትል የልቧን አካፈለችው፡፡ በህይወቴ ብዙ አይቼያለሁ፡፡ ብዙ ፍቅርንም፣ ብዙ ጥላቻንም፣ ብዙ ውርደትንም፣ ብዙ ክብርንም፣ ሁሉንም አይቼያለሁ፡፡ ያላየሁትን ደሞ እረዳዋለሁ፡፡

ሰዎች ቢጠሉ፡፡ በቀል ቢሰማቸው፡፡ ልባቸው ቢነድድ፡፡ ነፍሳቸው በቁጣ ብትንተከተክ፡፡ ሁሉም ላይ ነበርኩ፡፡ ሁሉንም እረዳለሁ፡፡ ሁሉንም እቀበላለሁ፡፡ የአባቴንም ነገር ተቀብያለሁ፡፡ አባቴን ዘቅዝቀው ሲሰቅሉት ተመልክቼ ተቀብያለሁ፡፡ ገድለው አልበቃቸው ሲል ስሜታቸውን ተረድቼዋለሁ፡፡ አባቴን ገድለው በአስከሬኑ ላይ ሲሸኑበት፣ ሲተፉበት - ያም ምንጩ ገብቶኛል፡፡ ብዙ ነገሮች ገብተውኛል፡፡ ግን አንድ ብቻ ፈጽሞ የማላውቀውም፣ ያልገባኝም፣ አንድ ነገር ብቻ አለ፡፡

ኪነት በዮዳኒ

25 Nov, 14:51


🕊️

Bodhidarma የ Zen Buddhism መስራች እንደሆነ ይነገርለታል። በርካታ አስተምሮቶቹን ያስተላለፈልን በደቀ መዝሙሩ Hiuke ለኩል ነው።
አንድ ቀን Hiuke መምህሩን ይጠይቀዋል።
'' አዕምሮዬ ከቀን ወደ ቀን በጭንቀት እየተሞላ ነው። አሁንስ ላብድ ነው። እባክህን መምህር ወይ ጭንቅላቴን ፀጥ አሰኘው ዘንድ እርዳኝ። " ይለዋል።
Bodhidarmaም
'' ችግር የለውም ጭንቀቶችንህን በሙሉ ፀጥ አሰኝልሀለሁ። ነገር ግን በመጀመሪያ 'ውጥረት ውስጥ የከተቱኝ ጭንቀቶች እኒህ ናቸው ' ብለህ ጭንቀቶቹን አሳየኝ ።ከዛ በሰኮንዶች መሀል ፀጥ አሰኛቸዋለዉ። " ይለዋል።
ይህን ሲሳማ Hiuke ለመጀመሪያ ጊዜ አንድ እዉነት ተገለፀለት። ጭንቀት የአዕምሮ ፍጡር እንጂ በእውነታው የሌለ ብዥታ መሆኑ።
ፍርሀታችን፣ ስጋታችን ፣ ጭንቀታችን ፣ በሙሉ ቅዠት መሆናቸውን Bodhidarma ያስረዳል።
ጋሽ ስብሀት '' ከሩቅ ያየኸው ሰማያዊ ተራራ ቀረብ ስትል አረንጓዴ ነው። '' ይላል። ከውጭ ሆነን ያየናቸው ሀሳቦቻችን ወደ ውስጥ ጠልቀን ስናያቸው ሌላ ናቸው። ምንም ናቸው። የተለየ ልንጨነቅለት የሚገባ ነገር የለም እያልኩ አይደለም። ' መጨነቅ ' በራሱ የለም እንጂ። "ማንም ሰዉ ተጨንቆ በቁመቱ ላይ አንድ ክንድ መጨመር አይችልም። " ለምን ? ምክንያቱም ጭንቀት የሰዉ እንጂ የእግዚአብሄር ፍጡር ስላልሆነ።
....
በሉ ደግሞ እንዴት ከጭንቀት ልውጣ የሚል ጭንቀት ውስጥ እንዳትገቡ። ብቸኛ መፍትሄው ወደ ውስጥ መመልከት ብቻ ነው። መመልከት ብቻ - ሌላ ምንም ማድረግ አያስፈልግም። ካልተመለከታችሁት ግን መኖሩን ይቀጥላል ይህን ነው Bodhidarma " Because you never look at it, it goes on
existing. It is in your not looking for it, in your unawareness, that it exists. '' ሲል የሚነግረን ።
....
አንዴ ነው አሉ... አንድ ጀማሪ ቡድሂስት የተመስጦ አቀማመጥ ተቀምጦ ያስባል። ጓደኛው ይመጣና '' ምን እያረግህ ነው ? ሲል ይጠይቀዋል።
ከዛ አጅሬ

" እንዴት አለማሰብ እንደሚቻል እያሰብኩ ነው። "

(ከ'ንዲህ ያለ ከንቱነት ይሰውረን !)

............... . .......... .........
15 / 03/17

ኪነት በዮዳኒ

25 Nov, 03:12


ለሰኞ ንቃት

12 የዕውቀት ጠብታዎች ከኖህ መርከብ!

    ⚓️-⚓️-⚓️_

1️⃣ ወደ መልካም ነገር የምትወስድህ ጀልባ ስትመጣ ፈጥነህ ተሣፈር፣ የመዳንህ መርከብ ስትቀርብ በቶሎ በእርሷ ላይ ውጣ፤ በሕይወት ዘመንህ አንዴ ካልሆነ ያቺን መርከብ ደግመህ ላታገኛት ትችላለህና – በፍፁም መርከብህን አታስመልጥ!

2️⃣ ሁልጊዜ ይህን ነገር አስታውስ፡- ሁላችንም ያለነው በአንዲቱ ጀልባ ውስጥ ነው፤ ጀልባይቱ ብትሰበር ሁላችንም እናልቃለን፤ ጀልባይቱ በሠላም ብትጓዝ ሁላችን እንተርፋለን! ይሄን አትርሳ – ሁላችንም ያንዲት ጀልባ ተጓዦች መሆናችንን!

3️⃣ በህይወትህ ልታደርጋቸው የምትመኛቸውን ነገሮች አስቀድመህ ዐቅዳቸው! ልብ በል፤ ኖህ መርከቡን መገንባት የጀመረው ዝናቡ መዝነብ ከጀመረ በኋላ አልነበረም! ደመናም በሠማይ ሣይዞር፤ የዝናብ ጉርምርምታም ሣይሰማ – አስቀድሞ ነው መርከቢቱን ማነፅ የጀመረው!

4️⃣ የአካል ጥንካሬህን ሁልጊዜም ጠብቀህ ተገኝ፤ ሁልጊዜም ብቁ ሁን! ማን ያውቃል? ምናልባት በ600 ዓመትህ፤ የሆነ ሰው ድንገት መጥቶ፤ አንድን እጅግ ታላቅ ነገር እንድታከናውን ሊጠይቅህ ይችላልና!

5️⃣ መናቆርን ብቻ ሥራዬ ብለው በያዙ ነቃፊዎች ትችት በፍፁም አትበገር! መሥራት ያለብህ ትክክለኛ ነገር ካለ፤ ዝም ብለህ ሥራህን ቀጥል! ለወሬኛ መድኃኒቱ ያ ነው – ትክክለኛ ሥራህ በስተመጨረሻ ይገለጣል!

6️⃣ ወደፊት ልትደርስበት አጥብቀህ የምትፈልገውን የህይወት ራዕይ፤ በታላቅ ሥፍራ ላይ አኑረው! ታላቅን ሕልም አልም! ለከበበህ ቁጥቋጦ ሣትበገር፤ ከፍ ባለ ሥፍራ ላይ የሕይወትህን ዋርካ ቀልስ! በታላቅ ሥፍራ ላይ የራዕይህን ማደሪያ መቅደስ ለመገንባት – አልመህ፤ ቆርጠህ ተነስ!

7️⃣ ጥንድ ጥንድ ሆነህ መጓዝ፤ ለክፉም ለደጉም ይበጃልና፤ ጉዞህ የተቃና እንዲሆን፤ ከጥንድህ ጋር መጓዝን አስብበት!

8️⃣ ከፈጣኖች እንደ አንዱ ነኝ ብለህ፤ በፍጥነትህ አትመካ፤ ፍጥነት ሁልጊዜም ላያድንህ ይችላልና! በደንብ አስተውል፤ በመርከቡ ውስጥ እኮ፤ ቀርፋፋዎቹ ቀንዳውጣዎችም፤ ፈጣኖቹ አቦሸማኔዎችም – ሁለቱም እኩል ፍጥነት ባለው ቀሰስተኛ መርከብ ተጉዘው ነው፤ በህይወት የተረፉት!

9️⃣ ጭንቀት ሲይዝህ፤ ካለህበት ነገር ወጣ በል፤ ትንሽ ዘወር በል፤ ለተወሰነ ጊዜ ቅዘፍ! ከችግርህ በላይ ሆነህ ስትንሣፈፍ – ያስጨነቀህ ነገር እልፍ ማለቱ አይቀርም!

🔟 ይህን ነገር ሁሌም አስታውስ፤ የኖህ መርከብ የታነፀችው ልምድ በሌላቸው በአማተሮች እጅ ነው! እንዲያም ሆኖ፤ ታላቅን ማዕበል ተቋቁማ፤ የተጓዦቿን ህይወት አተረፈች! ታይታኒክስ? 

ታይታኒክ የተገነባችው፤ አሉ በሚባሉ ዕውቅ ባለሙያዎች ነው! ግን የአንድ ቀንን ማዕበል መቋቋም ተስኗት፤ ተሣፋሪዎቿን ውሃ አስበላቻቸው! አየህ አይደል?

በሙያ ልቀት ብቻ አትመካ፤ ከሌሎችም ዘንድ ከአንተ የበለጠ ጠቃሚ መፍትሄ ሊገኝ እንደሚችል ዕወቅ! የታናናሾችህ የእጅ ሥራ፤ ህይወትህን የመታደግ አቅም ሊኖረው እንደሚችል – በዘመንህ ሁሉ አስብ!  

1️⃣1️⃣ ማዕበሉ የቱንም ያህል ቢናወፅ፤ አምላክህ ከአንተ ጋር ካለ፤ ማዕበሉ ፀጥ እንደሚል፤ ቀስተደመናም በሠማይህ ላይ ሊወጣ እየጠበቀህ እንደሆነ፤ በፍፁም ልብህ እመን!

የማዕበሉ ወጀብ በመንገድህ ላይ በርትቶ ሲፀናብህ፤ የአንፀባራቂው ቀስተደመናህ መውጣት እውን ሊሆን መቃረቡን የሚያበሥር፤ አንዳች የተስፋ ምልክት እንደሆነ ዕወቅ!!

1️⃣2️⃣ በጉዞዎችህ ሁሉ ከላይ የተነገሩት ጥንቃቄዎች አይለዩህ! የቱንም ያህል ማዕበሉ በመንገድህ ቢፀና፤ በስተመጨረሻ ጉዞህ እንደ ኖህ የተቃና ይሆንልሃል!

ይህ የሚሆነው ግን፤ ጉዞህን ከራስህ አልፎ - የሌሎችንም ሕይወት የሚታደግ እንዲሆንልህ አድርገህ ስታቅደው ነው! እንደ ኖህ፤ ያሰብከው ይሰምርልህ ዘንድ፤ ሥራዎችህን፤ ጥረቶችህን፤ በረከቶችህን ሁሉ ለሌሎች የሚተርፉ አድርጋቸው!

መልካም ጉዞ!

ቦን ቮያዥ!

⚓️♥️

_____

የእንግሊዝኛ መልዕክቱ (ከከበረ ምስጋና ጋር):-

«Everything I need to know about life, I learned from Noah’s Ark». ውርስ ትርጉም የራሴ። Aug 14, 2018. Via Assaf Hailu.

ኪነት በዮዳኒ

23 Nov, 04:41


በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሰረቱ መዚቃዎች እንደሆኑ ከሰማሁት ውስጥ
-------------------------
መጥቻለሁ - የሃይልዬ ሙዚቃ ሲሆን ግጥሙን የፃፈው አለማየሁ ደመቀ ነው። የሃይልዬ እናት ካረፈች በሆላ የወጣ ሙዚቃ ነው።

ልረሳሽ አልቻልኩም - የኤርሚያስ አስፋው ሙዚቃ ሲሆን የሌላ ሰው እውነተኛ ታሪክ ነው።

እኔ ልኮራመት - የአለማየሁ እሸቴ ሙዚቃ ሲሆን ለታላቅ ለእህቱ የዘፈነው ሙዚቃ ነው።

ባይተዋር - የአለማየሁ ሂርጾ ሙዚቃ ሲሆን ግጥሙን የፃፈው አለማየሁ ደመቀ ነው። ይሄ ሙዚቃ የአለማየሁ ሂርጾ ባለቤት ስታርፍ የወጣ ሲሆን በተጨማሪም አለማየሁ ደመቀ የእርሱን እናት ማረፍን በማሰብ የፃፈው ግጥም እንደሆነ ሲናገር የሰማሁ ይመስለኛል።

ትመጭ እንደሁ - የሚካኤል በላይነህ ሙዚቃ ሲሆን ግጥሙን የፃፈው ቴዎድሮስ ፀጋዬ ነው።

ሳታመኻኝ ብላ - የጎሳዬ ሙዚቃ ሲሆን ግጥሙንም የፃፈው አማኑኤል ይልማ ነው።

ግልግል ነው - የብስራት ጋረደው ሙዚቃ ሲሆን የፍቅረኛ ጎደኞቹ እውነተኛ ታሪክ ነው።

I can't make u love me - ግጥሙን የፃፉት Mike Reid Allen እና shamblin ሲሆን Bonnie Raitt ዘፍናዎለች። Adeleም ተጫውታዋለች።
_______________________
ሌሎችም የምታቋቸው ካሉ አስታውሱን። ብዙጊዜ የአርት ስራ ከእውነተኛ መነካት ሲሆን የተዋጠለት ስራ ነው የሚሆነው።

ኪነት በዮዳኒ

22 Nov, 19:23


Thursday ,2:00 AM November 21, 2024


<የሀዘን እራፊ >

      (በሰሎሞን አዱኛ )


ከልብ በታሼ በተሰናሰለ
በነፍሳዊ ዳና በተወለወለ
ብሶት ከትዝታ ከመብሰልሰል ጋራ
መከፋት ከህመም ከጸጸት አዝመራ
በእዝነት  አንጎራጎርጉ
ነፍስ ዘራች ነፍሴ
ለየቅል ሆኖባት መኖሩ ከራሴ፣

ደግሞ ከበሰለ ከተብሰለሰለ
በደሳሳ ጎጆ ለሞት በታበለ

ከባጥ ባመለጠች በጥቂት ጨለጨይ
አንጎራጎርኩልሽ ፣
ሽተሌዋን ነፍሴን በመርገም ማልኩልሽ

የችግር ቀን መጽናኛዬ የህይወት ሶማዬን
አረሰረስኩ በእንጉርጉሮ ገለጽኩት ሽተሌዬን
ሞቴን ለእኔ አሳበብኩት ለመከፋት ምርኳዝ ሰጠሁ
ላለመኖር ምስካብ አኖርኩ ከሀዘኔ ተቆራኜሁ

ንውዝ ካይኔ ተነጠቀ ጎኔም ለሱ ማሪፊያ አጣ
አንደበቴ ቃሉን ሳተ ኩናቴዬ ከ'ንቱን ቃጣ
ያለሁባት ጉሮኖዬ የመከፋቴ ግርግም
ጨለጨዩ ተደፈነ ያፈሰሰው የህይወት ደም

ሰውስ ብሆን ስሞት አይደል ከወዳጄ መራራቱ የተቸረ፣
ጸጸት ግሪፊያ የገረፈው ሰውነትስ የከረረ

ለእንግድነት መሽቶብኛል ከሰማይ አድባር ጸሃይ ጠልቋል!
ነተስፋ ዛፍ ተዘንጥፎ (ተገንብቶ) የአልቦ ጫፉ አቆጥቁጧል።

ኪነት በዮዳኒ

20 Nov, 00:47


ፍቅር እንዳማረበት እንዲዘልቅ የሚያደርጉ 10 መንገዶች
#Share (ላገባም ላላገባም የሚሰራ ነው።)
__
የፍቅር ተፈጥሮአዊ አካሄድ አልጋ በአልጋ እ
ንዳልሆነ ይታወቃል፡፡ የፍቅር ግንኙነቱ ሲጀመር የነበረው ፍቅር በሂደት እየቀነሰ የነበረው እንዳልነበረ ሊሆን ሁሉ ይችላል፡፡ በመሰረቱ ካልታረመ፣ ካልተኮተኮተ፣ በጥቅሉ አስፈላጊው እንክብካቤ ካልተደረገለት ዝም ብሎ ማበቡን እና መልካም ፍሬ ማፍራቱን የሚቀጥል ምንም ነገር የለም፡፡ ያልተሰራበት ግንኙነት እጣ ፈንታው ደስታ አልባ መሆን ነው፡፡ ሌላው ቀርቶ እጅግ በጣም ጥሩ የሚባሉ፣ ለብዙዎች ምሳሌ ሆነው የሚቀርቡ የፍቅር ግንኙነቶች እንኳን ፍፃሜያቸው የማታ ማታ መራራቅ አልፎ ተርፎም መለያየት ሊሆን ይችላል፡፡ ትልቁ የፍቅር ሕይወት ፈተና ሲጀመር የነበረው ፍቅር እንዳማረበት እንዲዘልቅ ማድረግ ነው፡፡

ምንም እንኳን ፍቅርን ለመመስረት ሁለት ሰዎች አስፈላጊ ቢሆኑም እንዲፀና እና ይበልጥ አስደሳች እንዲሆን ለማድረግ ግን አንድ ሰውም በቂ ሊሆን ይችላል፡፡ ኃላፊነቱን ግን አስቀድሞ መውሰድ ይጠይቃል፡፡ የፉክክር ቤት ሳይዘጋ ነው የሚያድረው፡፡ ክፍቱን የተተወ ቤት ውስጥ ብዙ ነገር ገብቶ ይወጣል፤ ብዙ ነገር እንዳልነበረ ይሆናል፡፡ ያለመጠባበቅ የቻልነውን ያህል ለማድረግ ጥረት ማድረግ አስፈላጊ የሚሆነው በዚህ ምክንያት ነው፡፡ ውጤቱ ላይ ትኩረት ማድረግ ጥሩ ነው፡፡ ዋናው ነገር ከእሷ ወይንም ደግሞ ከእሱ መምጣቱ ሳይሆን ዞሮ ዘሮ የሁለቱ የፍቅር ግንኙነት ጣፋጭ እና ፅኑ መሆኑ ነው፡፡ ፍቅራችሁ የሚፀናበት ይበልጥ የፈካ እና የደመቀ፣ ዘመናትን የተሻገረ መሆን የሚችለው ያለመጠባበቅ ኃላፊነት ወስዳችሁ መስራት ያለባችሁን መስራት ስትችሉ ነው፡፡ ምንም ተባለ ምንም አንድ ሰው ሁልጊዜም ኃላፊነቱን መወጣት መጀመር አለበት፡፡ በራሱ ሊንቀሳቀስ እና ሊለወጥ የሚችል ምንም ነገር የለም፡፡ የትዳር ግንኙነት ሲሆን ደግሞ ለማደስ ጥረት ካልተደረገ ወደ መፍረሱም ሊያቀና ይችላል፡፡

ቀጥሎ የትዳር ህጎች ከሚል መጽሐፍ ውስጥ ያገኘናቸውን 10 ፍቅር እንዳማረበት እንዲዘልቅ ያደርጋሉ የሚባሉ ህጎችን አለፍ አለፍ ብለን እናስቃኛችሁ፡፡ እነዚህ ተግባራት ላገቡ ብቻ ሳይሆን ላላገቡና በፍቅር ግንኙነት ላሉም የሚጠቅሙ ተግባራት ናቸው ፡፡

1ስሜትን የሚያነቃቁ ነገሮችን ማድረግ

መቼም አብሮ ሲኖር የሚያጋጭ፣ የሚያቀያይም፣ ቅሬታ የሚፈጥር ወዘተ ብዙ ነገር ይኖራል፡፡ ስሜት ይህንን ተከትሎ ይቀዘቅዛል፡፡ ፍቅር ስሜትም ነው በአንድ ጎኑ፡፡ በመሆኑም ስሜትን የሚያነቃቃ ደስታ የሚፈጥር ነገር ማድረግ የአድናቆት አስተያየት መስጠት ለአብነት ያህል አስፈላጊ ነው፡፡ ስራዬ ብላችሁ ማድነቅን ተለማመዱ፡፡ “ትላንት ማታ ጓደኛዬ ቤት በጣም ተጫዋች ሆነህ ነበር ያመሸኸው፤ ደስ ብሎኛል”፣ “አምሮብሻል” ወዘተ ዓይነት አድናቆት ሊሆን ይችላል፡፡ ከትችታችን ይልቅ አድናቆታችን በጣም መብለጥ ይኖርበታል፡፡

2ትችትን መቀነስና አድናቆት መጨመር

በአንፃሩ ትችት ትዳር ሲመሰረት አካባቢ አስፈላጊ ነው ይላሉ ብዙ ሰዎች፡፡ ጊዜ በነጎደ ቁጥር ግን ሰዎች ለትችት አለርጂክ መሆን ይጀምራሉ፡፡ ስለዚህ በተቻለ መጠን ትችትን መቀነስ አንድ አንድ ነገሮችን አይቶ እንዳላዩ ማለፍም ያስፈልጋል፡፡ መነገር አለበት የምንለው ነገር ካለም ከሁለት እና ሶስት አረፍተ ነገር ባልበለጠ እርዝማኔ መገልፅ ይመከራል፡፡ እርግጥ ነው ለትዳርና ፍቅር መጽናት አስፈላጊ የሆኑ መስተካከል ያለባቸው ነገሮች ከሆኑ፤ ግንኝነቱን በማይጎዳ መልኩ መነጋገሩ አስፈላጊ ነው፤ ምክኒያቱም አለባብሰው ቢያርሱ በአፈር ይመለሱ እንዳይሆን፡፡ ስለዚህ ትችቱ ለፍቅር ግንኝነቱ ሲባል እንጂ እጸጽን ነቅሶ ለማውጣትና የእራስን ትክክለኝነት ለማጉላት መሆን የለበትም፡፡ ትችት በምንሰጥበት ጊዜ ከጥሩ ጀምረን መሀል ላይ ትችታችንን ገልጸን ከዛም በአድናቆት ወይም በበጎ ነገር መደምደም ይመከራል (ሳንድዊች እስታይል እንደሚባለው)፡፡

3አዳማጭ ሁኑ

ማደመጥ ለፍቅረኛችን ወይንም ለትዳር አጋራችን የምንሰጠው ትልቁ ስጦታ ነው፡፡ ትርጉም መስጠታችሁን፣ ተሳሳተ የምትሉትን መረጃ ማስተካከላችሁን ጥላችሁ በሙሉ ልባችሁ ማዳመጥ ጠቃሚ ነው፡፡

4ራሳችሁ ላይ ትኩረት አድርጉ

ለራሳችሁ፣ ጓደኞቻችሁ፣ ቤተሰባችሁ ወዘተ ከትዳራችሁ በተጨማሪ ጊዜ መስጠት ጥሩ ነው፡፡ የግላችሁ ጊዜ ማሳለፊያ ልምድ ይኑራችሁ፡፡ በራሳችሁ እና በራሳችሁ ጉዳይ ላይ ምንም ትኩረት የማታደርጉ ይልቁንም ሙሉ ትኩረታችሁ የትዳር አጋራችሁ ላይ ከሆነ ተቺዎች ወይንም ደግሞ ጭንቀታሞች ትሆናላችሁ፡፡ እያንዳንዷን እዚህ ግባም የማትባል ጉዳይ እያነሳችሁ ስትጥሉ አሰልቺ እና አፋኝ ዓይነት ግንኙነት እንዲኖራችሁ ታደርጋላችሁ፡፡

5ይቅርታ ጠይቁ

ምንም እንኳን ለተፈጠረው ችግር የእናንተ እጅ ድርሻ ትንሽ እንደሆነ ብታስቡም “እኔ ይኼ ችግር እንዲፈጠር ለተጫወትኩት ሚና ይቅርታ ይደረግልኝ” ማለትን ተለማመዱ፡፡

6ይቅርታ ካልተጠየኩኝ ሞቼ እገኛለሁ አትበሉ

አንድ አንድ ጊዜ ይቅርታ ሳይጠይቁ ሰዎች መተዋቸውን፣ ለውጥ ለማድረግ ፍላጎት እንዳላቸው በተለያየ መንገድ ሊገልፁ ይችላሉ፡፡ይቅርታ ካልተጠየኩ ሞቼ እገኛለሁ ማለት ግን አላስፈላጊ ተደራራቢ ችግር ይፈጥራል፡፡ ዋናው ቁም ነገር ተፈላጊው ለውጥ መምጣቱ ነው፡፡

7ዘወትር ፈላጊዎች አትሁኑ

በስሜት የራቀ የሚመስል ሰው ጫና ሲደረግበት ይበልጥ ይርቃል፡፡ መተንፈሻ አየር መስጠት፣ ራስ ላይ ትኩረት ማድረግ በአንፃሩ የራቀንም ያቀርባል፡፡ የት ወጣች የት ገባች ውጤታማ አይደለም፡፡

8ሀሳባችሁን አጭር እና ለስላስ በሆነ መንገድ ግለፁ

ደጅ ደጁን የሚል ሰው አንድ አንድ ጊዜ ህመም የሚፍጥረበትን የቃላት ልውውጥ ሽሽት ውስጥ ይሆናል፡፡ ስለዚህ ሀሳብን አጠር አድርጎ፣ በተለሳለሰ መንገድ መግለፅ ጥሩ ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ድምፅንም ጭምር ዝቅ አድርጎ መናገር ተገቢ ነው፡፡ ከጣራ በላይ ድምፅን ከፍ አድርጎ መናገር ቁጣ ይመስላል፤ ከሆነም በዛ መልኩ መግለፁ አስፈላጊ አይደለም፤ ከመፍትሄነት ይልቅ የባሰ ችግር ፈጣሪነቱ ይጎላል፡፡

9ሁሉን መስዋዕት አታድርጉ

ተለዋወጭ ሰው መሆን አስፈላጊ ባይሆንም ሁሉንም ነገር ለእርስ በእርስ ግንኙነቱ ሲባል መስዋዕት ማድረግ ግን አይመከርም፡፡ ጫና እየተደረገባችሁ ሁሉንም እምነታችሁን፣ ምርጫችሁን እና መንገዳችሁን ገደል አትክተቱ፡፡

10በመጠኑም ቢሆን ሁለታችሁም የግልጊዜ ይኑራችሁ

ሰዎች በባህሪያቸው የሚሳቡት ከእርስ በእርስ ግንኙነቱ ውጪ ሌሎች ተጨማሪ የሚወዳቸው የራሱ ነገሮች ወዳሉት ሰው ነው፡፡ የመጽሐፍት ክበብ፣ በጎ ፍቃድ፣ ዋና ወዘተ ሊሆን ይችላል ባላችሁ ትርፍ ጊዜያችሁ መሞከሩ ይመከራል፡፡ ለብቻችሁ የሚኖራችሁ ጊዜ በጋራ ለሚኖራችሁ ጥሩ ቆይታ አስተዋፅዖ ያደርጋል፡፡ሁሌ አብሮ መሆን መዛዛግና መሰለቻቸት ሊፈጥር ይችላል ፡፡

በነጋሽ አበበ

© የስብዕና ልህቀት

ኪነት በዮዳኒ

18 Nov, 11:20


ማን?...ልቤን ተጫነኝ.
"እንጃ"
መቻል ደከመኝ።
የሞት ሀሳቤ እንዲጠፋብኝ
አለሁኝ በለኝ፣ነፍሴ ነሽ በለኝ?
እስኪ ታቀፈኝ፣ መኖር ይልመደኝ
✍️ዳጊ አሰፍ

ኪነት በዮዳኒ

17 Nov, 08:40


አለ አይደል?

የማያውቁት ሃገር፣
ያልተነገረለት፣
ያልተሰማ ዜማ፣
የሸፈኑት ውበት፤
ሲሸሸግ እያለ፣
ሳይገለጥ ፊቱ፣
መተማመን ይዞት፣
ከመድረክ መቅረቱ፤
ለራሱ እየቀረ፣
ወቶ እንደመታየት፣
ከሠው ስምን ያጣል ያልተነገረለት።

ባለው አመስግኖ እንደሚያድር ደሃ፣
ኖሮት ተሸክሞ፣
ገብቶ ከበረሃ፤
ለራሱ መንኖ፣
ራሱን ማሞካሸት፣
መታየት ሲጠላ፣
መደበቅ ሸፍኖት፤
ይቀራል አንድ አንዴ፣
ይመጣል አርፍዶ፣
መታየት በዝቶበት ሊመለስ እርዶ።  (የሞገሤ ልጅ)

@eyadermoges1

እያጋራን 😁! @afengusbot ማጋራት የምትፈልጉትን ስራ፣ ያላችሁን ጥቆማ፣ ሃሳብ እና የግል ምልከታ ሊቀበላችሁ ዝግጁ ነው። እኛ ወደስራ እንገባበታለን ያጋሩን!

ኪነት በዮዳኒ

17 Nov, 07:09


አያ ሙሌና እግዜር

"...ሙሉጌታ ግን ከቅዳሴ እስከ ቅኔ ከዛም ተሻግሮ ቁርአን ፣ ሀዲስንና መንዙማን የሚያውቅ ምሁር ነው። ይህም ባንዳንድ ግጥሞቹ ውስጥ ይታያል። እግዜርም ሸይጣንንም በእኩል ንቀት እየገረመመ ሲያናግራቸው እንደ ዳኛ ነው። ምንም ምክንያት ሳላገኝለት እውስጤ የሰረፀ ጥርጣሬ አለኝ። በሞተበት ቦታና ሰዓት ከሰይጣን ጋር እየተፈጠጠ እየተናነቀ ነበር ይሆን?....''

:- ጋሽ ስብሀት ለአብ
( ለባለቅኔ ሙሉጌታ ተስፋዬ የግጥም መድብል " የባለቅኔ ምህላ"..." የተረገመው ባለቅኔ " በሚል ርዕስ እንደ መግቢያ ከፃፈው....)

ሙሉጌታ ስብሀት እንዳለው በግዜርም በሰይጣንም ላይ እንደ ዳኛ ነው። ባለሙሉ ስልጣን። የሰይጣኑ ይቆይና በእግዜር ላይ ስለሚሰጠው ሁለት ጎን ፍርድ እናንሳ :: አያ ሙሌ እግዜርን ሲያምግስም ሲወቅስም በሙሉ ልብና በሙሉ እርግጠኝነት ነው ። በሁለቱም ጊዜ (በፍቅሩና በጥሉ) ስሜቱን አይሰስትም። ፍርሀት ሚባል ነገር ጋር ሲኖር ባንድ መንገድ እንኳን አልተተላለፉም።


[ ስለ አያ ሙሌ ድፍረት ሳስብ አንድ ቃለ መጠይቅ ላይ : " ከኔና ከይልማ ሀብተየስ ሌላ ኢትዮጵያ ውስጥ የዘፈን ግጥም ፀሐፊ የለም። " ያለውና
" አሁን እኔና ነጋሶ ጊዳዳ አንድ ላይ ብንቆም፣ ህዝቡ ከፕሬዝዳንቱ ይልቅ እኔ ባለቅኔውን ነው የሚሰማ። " ያለው ሁሌም ትዝ ይለኛል። ]

ወደ እግዜር ስንመለስ። አያ ሙሌ እግዜርን....

1. ሲያመሰግን

በገናዬን ልቃኝ
ከናፍቅኩህ በቃኝ...
ፍቅርህ እየጠራኝ
መስቀሉ እየመራኝ
ጀምሬአለሁ ጉዞ,...
ሰንሰል ተጎዝጉዞ....


2. ሲመካበት

...ባልቀድስም ባልቀስ
በሥላሴ ፊት ነው የኔ መመላለስ
አንድ እሱን አምኜ ሰርዶ የምነቅል
ላገር ማገር ስሆን.. ለድምበር ለጎበር
ሞፈር በመስቀሌ እንቅፋት ቢመታኝ
ብወድቅ የሚያነሳኝ...
እኔን የሚል አምባ አለ የማይረሳኝ...

3. ሲለምነው

ምንም ቢፈጠር ምንም
ካንተ መስቀል በስተቀር ሌላው አይታመንም
ቃልህን ተከተልኩት ድምፅህ ደሞ ናፈቀኝ
የልቦናዬን መስኮት ክፈትልኝ...
ምንም ባለጌ ብሆን... ማረኝና...
ከጨዋ ልጅ ጋር ልቀኝ....
ካይኔ አትራቀኝ
ያልበላሁት እያነቀኝ
ያለጠፋሁት አንዳንዴ...
ከሳሽ መንፈስ እየላከ... ያለ ነቃሽ እያሳቀቀኝ
አደቀቀኝ
ጌታ ሆይ ነፍሴን ባርከኝ
ጌታ ሆይ ልቤን ማርከኝ...

4. ሲወቅሰው ( ሲከሰው)

.... አቀርቅረን ስናቋርር
ቅሪታችንን ስናንቃርር
እንደቀላጤ አከንባሎ....
ቁልቁል ባፍጢም ተተከለን
በእርኩስ አመዳይ ተበክለን
እንዲህ የትም ስንቀር እያየህ ዝም ካልክማ
እዉነት.... እዉነት ከመንበርህ የለህማ!
ጀምበር ትንታጓን ረጭታ ሰብ ዓለሙን ስትፈጀው
አብ ወልድ ቃልህ ካልባጀን
ድርሳነ ትንቢትህ ካልዋጀን...
አንተስ ምንህ መለኮት - እኔስ ለምን ያንተ ባርያ
ሆዴን ሁዳዴን ላምልክ እንጂ...
ትንሳኤ እንደሌለው እርያ
ያንተን ጉድማ አየሁት
ያንተን ገድልማ ለየሁት
ማረኝ ሲሉት የሚመር የማይታደግ አላመልክም
(በሰበራ ገል አልላክክም )
ወትሮም የተማረ ቄስ እንጂ የሰው ልጅ መላክ አይልክም።

[ ምርቃት ]

ስብሀት አያ ሙሌ ቁርዓኑን ፣ ሀዲሱን መንዙማውን ያውቀዋል ሲል እንዲሁ ወሎዬ ስለሆነ አይደለም። ምሁር ስለሆነ እንጂ ።
እንደምርቃት
" የጎራው ወይራ ዝየራ! " የሚለውን ግጥም (ሙሉውን ) ላስፍር።
.....
ቢስሚላሂ ብዬ ልጀምር መደዱን
የሐርሽን ቀንዳማ ቢያሳየኝ መንገዱን....
ካላጣው ወሪዳ
ኢልም እንደ ፍሪዳ...
በልቶ ያሳየኝ... የሩሄን ቐሪባ...
ግለጥልኝ እንጂ ፥ ሞጥልልኝ አንተው
ደግሞ መሳቱ አይቀር ፥ ቀድሞ የቶበተው
አስረዱኝ ሸሆቼ ፥ የቁርዓኑን ተፍሲር
የኢማኑን ተውሂድ ፥ የሙሃባውን ሲር
የከዳም በረካ ፥ የኢልምን ጥፍጥና
አስተሳሰሩኝ ኒካ ፥ በዲን ታጥባ ታጥና
ዱአዬ እንዲሰማ ፥ በዓለመል ዘራ
ያውጣኝ ከመናደፍ ፥ እንደጉም ናዜራ
ወለደል ኋሊሓ አይንሳኝ አውገረድ
የባጢኑ ዓይኔ ፥ ከሽፎ እንዳይጋረድ
ዚክርና ተስቢህን ፥ ጥንዱን ባንድ ገምዶ
ያግራልኝ ሐለቴን ፥ ነብስያን አጥምዶ !

( ሮመዳን ዋዜማ / 96 ተፃፈ)


...... እንግዲህ ያብዛኛዎቹ ቃላት ትርጉም ባይገባኝም፤ ለውበቱ ስል የወደድኩት ግጥም ነው።
....
በጋሽ ስብሃት ምስክርነት ጽሁፉን ስንዘጋ


"( አያ ሙሌ)... በገጣሚነቱ ብቸኛ አቻው ዊልያም ሸክስፒር ( ነው።) "


.........................
08 /03/17

ኪነት በዮዳኒ

14 Nov, 11:12


መፅሐፍ ከማሳተማችሁ በፊት🚫
ለማሳተም ሐሳብ ላላችሁ
(አሌክስ አብርሃም)

ብዙ ወዳጆቸ መፅሐፍ ለማሳተም እንደምትፈልጉና ከህትመት ጋር በተያያዘ አስተያየት እንድሰጣችሁ በየጊዜው ትጠይቁኛላችሁ። ምክንያቱ ባይገባኝም በተለይ ሰሞኑን ደግሞ
ጥያቄው በዛ ብሏል። አንዳንዶቻችሁ መልስ አለመስጠቴ ትንሽ እንዳሳዘናችሁ ፅፋችሁልኛል። ኩራት አልያም ንቄት ነው ያላችሁኝም አላችሁ። እውነታው በዚህ ጉዳይ ምክርም አስተያየትም መስጠት አስቸጋሪ ሆኖብኝ ነው። የግድ አስተያየቴን መስጠት ካለብኝ ግን ቀጣዮቹን 10 ነጥቦች ላካፍል። የተለየ ሐሳብ ካለም በደስታ እቀበላለሁ።

1ኛ. እንኳን ፃፋችሁ፣ መፃፋችሁን ቀጥሉ! ከእናንተ የሚጠበቀው ከባዱ ሀላፊነት ይሄው ነው። የፀሐፊ ስራው ሳይታክት መፃፍ፣መፃፍ አሁንም መፃፍ ነው። ይህ ፅሁፍ ግን ስለመፃፍ ብቻ ሳይሆን ((ስለማሳተም)) ነው።

2.መፅሐፍ ስታሳትሙ ለህትመት ያወጣችሁትን ገንዘብ እንደጠፋ፣ እንደተሰረቀ ወይም ፈፅሞ ከዚህ በኋላ እንደማታገኙት ሐብት ቁጠሩት። ከተመለሰ እሰየው! ካልተመለሰም በሞራልም በገንዘብም ህይወታችሁን እንዳያመሳቅል ብዙ ተስፋ አታድርጉ።

3.🚫በጣም እንዳትሞክሩት የምመክረው ...ንብረት በመሸጥ፣ በማስያዝ፣ ወይም በብዙ ድካም ለሌላ ጉዳይ ያጠራቀማችሁትን ገንዘብ በማውጣት መፅሐፍ አታሳትሙ። እባካችሁ አታሳትሙ። ስፖንሰር ከተገኘ፣ ለማሳተም ብዙም የገንዘብ ችግር ከሌለባችሁና ለስሜታችሁ ስትሉ ማሳተም ከቻላችሁ ችግር የለውም።

4. የግጥም መፅሐፍ ማሳተም አሁን ባለው የመፅሐፍ ገበያ የሚመከር አይደለም።

5. ጥሩ ፅፋችሁ በአመታት ድካምና መስዋዕትነት ያሳተማችሁት መፅሐፍ በቀናት ውስጥ በዮ ቲዮብ፣ በሬዲዮ ጣቢያዎች ፣ በቲክቶክና በቴሌግራም አየር ላይ ተበትኖ የሽያጩ ነገር ከአፈር ሲደባለቅ ማየት የዚህ ዘመን የደራሲያን የልብ ስብራት ነው።

6. እነእንትና እንኳ ፅፈው ተነቦላቸው የለ የሚል ሞኝ ንፅፅር ውስጥ ራሳችሁን አታስገቡ። ሰወች ምንጊዜም እንደባህር አለት ጫፋቸው ብቻ የሚታይ ፍጥረቶች ናቸው ውሀው ውስጥ ያላቸውን መሠረት አናውቅም።

7. ሁልጊዜም ሽፋን ላይ የምታዮት ዋጋ ለደራሲው በቀጥታ የሚደርስ አይደለም። እውነታው ግማሹ እንኳን አይደርሰውም። ስለዚህ ማሳተም ስታስቡ ይሄን ያህል ኮፒ በዚህ ዋጋ ቢሸጥ ከሚል የዋህ "ቀቢፀ ሒሳብ" ውጡ።

8. እንዲህም ሆኖ ብዙ መፅሐፍት ይታተማሉ የሚል ግርታ ውስጥ ከሆናችሁ ከብዙወቹ እንደአንዱ ከመሆናችሁ በፊት በእነዚህ ነጥቦች ላይ የራሳችሁን ጥናት ደግሞ አድርጉ። በማይገባኝ ምክንያት ደራሲያን ትክክለኛውን መረጃ እርስ በእርስ አይለዋወጡም።

9. መሠረታዊ ችግሩ በሁሉም ዘርፍ ያለው የዋጋ መናር ካለን ደካማ የንባብ ባህል ጋር መዳመሩ ሲሆን በተጨማሪም አንባቢው በተደጋጋሚ በሚታተሙ መፅሐፍት ያሰበውን ያህል እርካታ ማግኘት አለመቻሉ ያሳደረው ተፅዕኖም ቀላል የሚባል አይደለም።

10. መፅሐፋችሁ መሸጡ ወይም አለመሸጡ የእናተን ደካማ ደራሲነት ወይም ጥሩ ፀሐፊነት ማረጋገጫ ላይሆን ይችላል። ሊሆን የሚችልበትም አጋጣሚም ይኖራል። የመፅሐፍ ገበያ እብድ ነው። ታዋቂ ሁናችሁ ያጨበጨበው ሁሉ ድራሹ ሊጠፋ በተቃራኒው ድንገት ብቅ ብላችሁ ህዝብ ሊሻማ ጥሩ ሊሸጥና ሊነበብም ይችላል። ግን ከመቶ ሁለትና ሶስት እንኳን ይሄ እድል አይገጥመውም። በበኩሌ ህይወትን ለዕድል መተው ለማንም የምመክረው ነገር አይደለም። ዕድልን በህይወት ውስጥ መጠቀምን እመርጣለሁ። ምክንያቱ ብዙና ውስብስብ ነው። የሆነ ሆኖ የተሻለ ተስፋ ብሰጣችሁ ደስ ይለኝ ነበር፤ ግን እውነታው ቢታደጋችሁ ይሻላል። አውቃችሁ ተጋፈጡት!!

ኪነት በዮዳኒ

13 Nov, 11:00


https://vm.tiktok.com/ZMhp44ekL/ This post is shared via TikTok Lite. Download TikTok Lite to enjoy more posts: https://www.tiktok.com/tiktoklite

ኪነት በዮዳኒ

10 Nov, 20:37


© Yiftusera Meteku

(fb page)

ኪነት በዮዳኒ

10 Nov, 20:35


ስለድብርት

ብዙ ጊዜ 'ደብሮኛል' ያሉ ሰዎች ከዛ ስሜት ለመውጣት ሲራወጡ ማየት ለምደናል:: በርግጥ ወዳጆቻችንም 'ደብሮናል' ሲሉን እንዴት በፍጥነት ከድብርት እንደምናስወጣቸው እናስባለን:: ደግ ሃሳብ ነው ይሄኮ::
እኔ ግን በግሌ ከድብርት ጋር የተያያዘ ተሞክሮዬን ላካፍላችሁ::

አይኖሩ ህይወትን ኖሬያለሁና ተደጋጋሚ የድብርት ጊዜያት አሳልፌያለሁ::
እንዴት እንዴት ይሰማኛል?

ድብርት ሲሰማኝ ሰውነቴን ማዘዝ አልችልም:: ከተቀመጥኩበት መነሳት: ከተኛሁበት ቀና ማለት ያቅተኛል:: ሰው አጠገቤ ባይኖር እመርጣለሁ:: አጠገቤ ሰው ካለም ማውራት አልችልም::
ውስጤ ባዶ ይሆናል:: 'የእስከዛሬው ቀን እንዴት አለፈ? ነገስ?' ይለኛል ውስጤ:: ማሰብ ብፈልግም ምንም ምሰብ አልችልም::

እንዲህ ሲሰማኝ ምን አደርጋለሁ?

ከባዱን ያንድ ወቅት ተሞክሮዬን ልንገራችሁ::

ከዩኒቨርሲቲ ወጥቼ ብዙ ብዙ ነገር አልፌ የሞከርኩት ሁሉ አልሆን ብሎኝ እናቴ ቤት ሄጄ ነበር:: እቤት ቁጭ ብዬ ለከባድ ድብርት ተጋለጥኩ::
ምን አደረኩ? ተኛሁ:: (በርግጥ ከላይ እንዳልኩት ሰውነቴም አይታዘዘኝም)
ተኛሁ ለሁለት ወራት:: ሁለት ወር መተኛት ሲባል እንዲህ እያረፍኩ እየተነሳሁ እንዳይመስላችሁ:: አልጋው ላይ ስር እስክሰድ ድረስ:: የወጣ የገባ 'አሁንም ተኝታለች?' እያለ: 'አሁንስ አበዛሽው' እየተባልኩ: ተኛሁ::

እንዴት ነበሩ እኒያ ሁለት ወራት? ለምን ለመነሳት አልታገልኩም?
ያለሁበት ጊዜ ከባድ እንደሆነ ባውቅም እንደሚያልፍ ይሰማኝ ነበር:: ወይም በድፍረት 'ያልፋል' እላለሁ ለራሴ:: እንዴት እንደሚያልፍ አላውቅም:: የምንም ነገር ውል አልነበረኝም::
'ያልፋል' እላለሁ ግን:: 'ያልፋል' ስል ግን በጎ በጎው እየታየኝ እንዳይመስላችሁ:: 'ብሞትም ማለፍ አይደል?' እላለሁ:: እንዲህ እያልኩ ድፍን ሚያዝያንና ግንቦት ተኛሁ::
ከዛስ?
ሰኔ ገባ:: አንድ ሐሙስ ጠዋት ስነቃ ከትናንቱ የተለየ ጤንነት አለው ሰውነቴ:: አሃ አልኩ:: ንቅት አልኩ:: ንቅት!
ከመኝታዬ ተፈናጥሬ ተነሳሁ:: ወደሳሎን ሄድኩ:: እህቶቼ ወደስራ ለመሄድ ይዘገጃጃሉ:: ልጄ ወደትምህርት ቤት ለመሄድ ዩኒፎርም ለብሳለች:: 'አደርሳታለሁ' አልኩ:: የለበስኩትን ልቀይር ወደልብሶቼ ስሄድ...ታምናላችሁ የለበስኩት ልብስ ያለፉትን ሁለት ወራት ከላዬ አልተነሳም:: ልብሱን ለማውለቅ ስሞክር ሙሉ ሰውነቴን በላኝ:: ልጄን መሸኘቴን ተውኩት:: አንደኛዋን እህቴን 'የሳሙና መግዣ ስጪኝ' አልኩ::
ቀኑን ሙሉ ልብስ ሳጥብ ዋልኩ:: የኔን ብቻ ሳይሆን የቤተሰቡን ሁሉ አጠብኩ::
ወደአስር ሰዓት ገደማ ልብስ አጥቤ ጨርሼ ሰውነቴን ልታጠብ ገባሁ:: አይወራም መቼም የሰውነቴ:: ጠጉሬን ልታጠብ ፈታሁት:: ሌላ ጉድ ደሞ:: ጠጉሬ በዛላው ልክ ቅማል አፍርቷል:: ማለት እንዴት አብራራዋለሁ? እጄን እንዲህ ሰደድ አድርጌ ስመልሰው እፍኝ ሙሉ ቅማል:: ይዘገንናል አይደል? የሆነው ግን እንደዛ ነው:: ሁለት ወር ሙሉ እንደነገሩ ወደሁዋላ በተያዘበት የተተወ ጠጉሬ ለብቻው ህይወት ይመግባል::
ብታጠበው ባበጥረው ሊወጣ ነው ተባዩ? ያችን ሰዓት አለቀስኩ:: ማርያምን:: ሁለት ወር ሙሉ አላለቀስኩም ብያችሁ ነበር? ከመተኛት ሌላ ያደረኩት የለም ብያችሁ ነበር አይደል? በዛች ጠጉሬን እያበጠርኩ በሆነው ሰዓት ግን አለቀስኩ:: ስቅስቅ ብዬ:: ጠጉሬ ላይ ያለው ርጥበት ፊቴን መከለል እስካይችል ድረስ:: ከልቤ ውስጥ ውስጥ...ከአንጀቴ!

አልቅሼ አልቅሼ ሲወጣልኝ ይሄ ጠጉር ከዚህ ወዲያ መዋቢያ አይሆነኝ' የሚል ሃሳብ መጣብኝ:: ደሞ ምንስ ባደርግ ያንን ሁሉ ተባይ ከላዬ ማራገፍ ይቻለኛል?
ወጥቼ መቀስ ገዛሁ:: እዛው ባለበት መደመድኩት:: እየቆረጥኩትም አልቅሻለሁ ምን ያደርጋል ውሸት:: ብዙ ብዙ አድናቆትና ፍቅር ሸምቼበት ኖሬያለሁ በጠጉሬ:: ከሰው ጠጉርም ተወዳድሮ 'ሌላ ነውኮ ያንቺው' ተብዬበታለሁ:: 'ጠጉሬ እንዳንቺው በሆነልኝ' ተብዬም ኩራት ኩራት ብሎኝ ያውቃል:: አያያዙን አላውቅበት ስልም 'ስንት የሚፈልገው እያለ ላንቺ ይስጥ ይሄን የመሰለ ጠጉር?' ተብያለሁ:: ብዙ ተወድጄበታለሁ:: አናቴን በመቀስ ጅብ የሄደበት ጥሻ እያስመሰልኩት አለቀስኩ:: ማምሻውን እህቶቼ ከስራ ሲመለሱ ደነገጡ:: ድንጋጤያቸው መለስ ሲል ተሳሳቅን:: አቆራረጤ ልክ አልነበረምና 'እንዴት ይስተካከል' ሲባል በምላጭ ይነሳ አልኩ:: ተላጨሁት::

የዛን ዕለት ዳግም መወለዴ ነበር:: በበነጋው የሰፈር ሰው ሁሉ መላጣዬን ለማየት ቤት ሲመጣ ሲስቅብኝ ስስቅ ዋልኩ:: ስውል ሳድር መነቃቃቴ እየጨመረ መጣ:: ያሉኝን ወዳጆች አስታወስኩ:: ማንን ምን መጠየቅ እንዳልብኝ በተራ በተራ ይመጣልኝ ጀመር:: ስልኬን ከጣልኩበት አነሳሁ:: ደዋወልኩ:: ስራ ፈልጉልኝ: ነይ በሉኝ አልኩ::
እህህ ከዛማ ምኑ ይጠየቃል?

አለፈ እያልኩዋችሁ ነውኮ::

መላጣዬም ሌላ ፋሽኔ ሆኖ አለፈ::

Cc :💪Yiftusera Meteku

ኪነት በዮዳኒ

10 Nov, 07:26


ማህደሬን ሳገላብጥ ከ 2 አመት በፊት የጻፍኩት ግጥም ታየኝ። እስኪ ልጋብዛችሁ 😀

ፌሚኒሥቷ ፍቅሬ

ሠሚ ያሠለቸው የኖርሽለት ቃልሽ፣
ድንገት ወዴት ገባ የቱ ጅብ በላብሽ?
ትዳር የሚሉት ጉድ ባል የሚሉት ጣጣ፣
ኣልየው ኣይየኝ ባፍንጫዬ ይውጣ።

ላልሽበት ኣንደበት ኣመኔታ ችሬ፣
ላለማፍቀር ብዬ ፍቅሬ ኣንቺን ኣፍቅሬ፤
ተጥመልምሎ ዞሮ ዙሩን እያጉነ፣
እቃቃችን ድንገት እንዴት የምር ሖነ?

እኮ በየት በኩል፣
በየት ኣርጎ መቶ፣
መንገዴን ቀይሮ ያንቺንም ኣስትቶ፤
ከኣፍቃሪ ኣፎት ከፍቅር ማህደር፣
ከትዳር ሠንሠለት ከህይወት ቁምነገር፤
ቀድመን ሣንረዳ ሣናውቀው ሣይገባን፣
ሢከተን ሣናየው እንዴት ከቶን ኣየን?

እኔ ግን ያን ግዜ፣
ብቻሽን ሥትኖሪ ብቻዬን ለመኖር፣
ኣንቺን ያፈቀርኩሽ ላለማፍቀር ነበር።

እያደር ሞገሥ (የሞገሤ ልጅ)

@eyadermoges1 @eyadermoges1 @eyadermoges1

የቻናሉን link ማጋራት እና ድጋፍዎን ማጠናከር አይዘንጉ! ሃሳብ ካለዎት ወይም በቻናላችን እንዲጋራ የሚፈልጉት ስራ ካለዎት @afengusbot ላይ ይላኩልን! አዲስ ነገር ይገባችኋል።

ኪነት በዮዳኒ

10 Nov, 04:12


በዚህ ዓመት ትምህርት ከጀመርን ጀምሮ እስከዛሬ ለሳምንት ሚያህል ጊዜ ሲያሳስበኝ የቆዬ ጉዳይ 🤔....

ከምንም መማር የአዋቂ ሰዉ ባህሪ ነው። በምንም ነገር ውስጥ እውነትና እውቀትን ማቆየት መቻል ደግሞ የጠቢብ ።
አንዳንዴ የትም ቦታ ብንሆን ሊያስተምሩን የተዘጋጁ 'ነገሮች ' አይጠፋም። ሁሌም ቁጭ ባልን ቁጥር አይምሯችን ስራ እንዳይፈታ እንፈትላቸው ዘንድ የተዘጋጁ የሀሳብ ድሮች በዙሪያችን አሉ። ልዩነቱ የማስተዋልና የአለማስተዋል ነው።
...
ፋታ ከሚያጣጡኝ ና ሰዉ ስለመሆን ሳስብ ከሚመጡልኝ የሀሳብ ጉንጉኖች አንዱ '' ራስን መሆን '' የሚለው ሀሳብ ነው። socrates "be Yourself" ካስተማራቸው ትምህርቶች በሙሉ የሚልቀው ነው። በዛ 'የሰው እጣ ፈንታ፣ ዛሬ ና ነገው በአማልክት እጅ ላይ ነው ያለ ' ብሎ በሚያምን ማህበረሰብ ውስጥ ፤ ነገሮች ሁሉ ፣ ቀስቶች ሁሉ ወደ አማልከቱ በሚጠቁሙበት ዘመን፣ በአጠቃላይ እያንዳንዱ የተፈጥሮ ክስተት የራሱ ገዢና ኃላፊ ተሹሞለት ለእንያንዳንዷ የእግር ዱካ ፈቃድ ለማግኘት ቀና በማለት ግድ በሆነባት ግዜ... ሰውን የፍጥረት ሁሉ ማዕከል አርጎ መነሳት በእርግጥም የሆነ አይነት " ራስህን መሆን " ውስጡ ቢኖር ነው ያስብላል። እንዴት ወቅትና ዘመን የጫኑትን የሀሳብ ቀንበር አውርዶ ብቻን መቆም እንዲያ ቀለለ ? መርዝን እንደ መጠጥ በኵራት የሚያስጠጣ "ራስን መሆን " እንደምን አርጎ ልቡን ቤቱ አረገ ? በውነት ሶቅራጥስ ሶቅራጥስ ነበር።
...
John Stuart Mill ስለ ማሰብ “It is better to be a human being dissatisfied than a pig satisfied; better to be Socrates dissatisfied than a fool satisfied.” ይላል ::(የተመቸው አሳማ ከመሆን ያልተመቸው ሰዉ መሆን ይሻላል፤ የተመቸው ሞኝ ከመሆን ያልተመቸው ሶቅራጥስ መሆን ይሻላል)
አንዳንዴ ልክ ነው... ሰዉ ያረገን ማሰባችን ነው። ማሰብ ነው ሰውን ከአሳማ የሚለየው። ወይም ደግሞ አንዳንድ ጊዜ እንግሊዛዊው ፈላስፋ Russle እንደሚለን " ማሰብ ሰውን ከእንስሳት ሳይሆን ሰውን ከሰው ነው የለያየው። በተራው ሰውና በእንሰሳት መካከከል ካለው ልዩነት ይልቅ በተራው ሰውና በሶቅራጥስ ወይም በፍሬድሪክ ኒቼ መካከል ያለው ልዩነት ይስፋል። '' ራስን መሆን ማለትም ይህ ነው። እንደሰው ልንሰራ ፣ እንደሰው ልንበላ ፣ እንደሰው ልንኖር ፣ እንደ ሰዉ ልንስቃይ እንችላለን። ይህ ሁሉ የሰውኛ ባህሪ ነው። እንደ እኛ ሳይሆን እንደ ሰዉ ማሰብ ስንጀምር ግን እንደኛ መሞት እንጀምራለን።
ፕሌቶ ሶቅራጥስ ዘንድ ሄደው የሚማሩ ሰዎች "ማሰብ ባይችሉ እንኳን ማሰብ እንዳሚችሉ አውቀው ይመለሳሉ። "ይለናል። የራስን መሆን እንደራስ ማሰብ ነው...ያ ባይሆን እንኳን እንደራስ ማሰብ እንደሚቻል አውቆ ለዛ መትጋት ነው::
...
ደራሲ ዓለማየሁ ገላጋይ መጽሐፍቱን ያነበቡ ሰዎች በተላይ ደግሞ ሐሰተኛው (በእምነት ስም) የወጣ ሰሞን፤ ስለ ፈጣሪ የሚያነሳቸውን ሀሳቦች ፣ ስለ እዉነት የሚነግረን አስደንጋጭ እዉነት፣ በፍቅር ስም ስላለ ጥቅም ፈላጊነትና ፀረ- ፍቅር አቋም፣ እምነት ብለን የያዝናቸውን ነገሮች አንድ በአንድ በመፅሀፍቱ ሲያፈራርሳቸው ስለሱ የሰጉ ሰዎች ይመክሩታል
'' አረ ተዉ አሌክስ እንዲህ እያሰብክ እንዳታብድ ... " ብለው
ታዲያ የዓለማየሁ መልስ
" ካለማሰብ ማበድ ይሻላል !." ነበር።
ይህን ነው በትንሹም ከላይ ልለው የፈለግሁት።
...
ይህንን 'ሁሉ 'እንድል ያረገኝ ግን ከታች የምታዩት የወንዶች ዶርም 2ኛ ፍሎር በበተቀኝ በኩል ካለው ሽንት ቤት የመጨረሻው ዳር ላይ ካለው ፣ የበሩ የውስጥ ክፍል ተፅፎ ያገኘሁት ፅሁፍ ነው:: ( የቀድሞ የዩንቨርሲቲው ተማሪዎች የፃፉት መሰለኝ። ደግሞ እንኳንም ፃፋት..... የሆዴን ሸክም ላቃልል ገብቼ የአዕምሮ ሸክም ይዤ ወጣሁ እንጂ 😁)

ኪነት በዮዳኒ

08 Nov, 18:33


https://vm.tiktok.com/ZMhqbQcef/ This post is shared via TikTok Lite. Download TikTok Lite to enjoy more posts: https://www.tiktok.com/tiktoklite

ኪነት በዮዳኒ

08 Nov, 16:27


ጉዞውን አስደሳች ያደረገው መንገዱ ነው። ብታይ ለአቅመ ጥርጊያ በደምብ ያልበቃው መንገድ ስትተነፍሺ እንኳን ንፋስ ነፈሰ ብሎ አዋራውን ወደላይ ያምዘገዝገዋል። ምራቅ ከተፋሽ ዘነበ ብሎ አጨቀያየት ትጠያለሽ። በቃ አያልቅም እንጂ ቤት እድለኛ ሆነሽ ከደረስሽ እራሱን ተሸክመሽ የገባሽ እስክትመስዪ አዋራ ትጠግቢያለሽ። ደጋፊ ካለሽ በቃ በዱላ ሲያራግፉልሽ አንዴ መተውሽ ሶስቴ እያስነጠሱ፣ አንድኛው አይኑ የገባን አዋራ ንፋስ እስኪወስድለት ተጠባባቂው እየወቃሽ ነው። ደብዳቢዎችሽ ካስነጠሱ አንቺስ የሚለውን ማሰብ ነው ታድያ! ግን ያ ሆኖ ሳታምኚ ሠው ትሆኛለሽ። እድለኛ ከሆንሽ ደግሞ አዋራ ለብሶ የሚመጣ መንገደኛ የምታገኚ እንደሆነ አዋራን አራጋፊ የምትሆኚ እና ለምስክረነት የምትጠሪ የተጓዦች አመራር ትሆኛለሽ። አሁን ቤት ገብቼ እየደበደቡልኝ ነው።

@eyadermoges1

ኪነት በዮዳኒ

08 Nov, 09:51


በቃ እንዲሁ ልንቀጥል ነው?
(አሌክስ አብርሃም)

"የዛሬ አምስት ዓመት የምሰራበት የህክምና ተቋም ህንፃ ላይ የተፃፈውን ስምና፣ ዋንጫ ላይ የተጠመጠመ እባብ ከነምላሱ ከዚህ ጋ ሆኘ ቁልጭ አድርጌ ማየት እችል ነበር...አሁን ግን በጣም ካልተጠጋሁ በስተቀር ቀለሙ እንጅ ፊደሎቹም እባቡም አይታየኝም። ብዢዢዢ ይልብኛል። ይህን የታዘብኩት ከወር በፊት ነው በአጋጣሚ" አለኝ። ከሩቅ የሚታየውን ህንፃ እያሳየኝ። እናም " አይኔን ያደከመው ቀን ሌሊት ሳልል የምጎረጉረው ስልክ ነው። መነፀር ያስፈልገሀል ተብያለሁ። ፀሐይ ላይ ስሆን እንባየ ያስቸግረኛል። ካየሁት ሁሉ ምን ተጠቀምኩ? ተዝናናሁ እንበል ለመዝናናት የዓይን ጤናን መክፈል ያዋጣል? እንቅልፍ ያጣሁባቸው ምሽቶች ቁጥር ስፍር የላቸውም፤ ምን አገኘሁ? ምንም። መረጃ እንበል ፣ እንቅልፍ የሚከፈልለት መረጃ የትኛው ነበር ? የት እንዳይሄድ? የቱ ህይወት የሚቀይር መረጃ? " አለም አንድ ሆነች ብለው ከራሳችን ለዮን።

እያወራኝ አሰብኩ ...በብዙ ሺ የሚቆጠሩ የማይመለከቷችሁን ቪዲዮዎች አያችሁ፣ እንቅልፍ እንደበፊቱ እየተኛችሁ አይደለም በጣም እየተጎዳችሁ ነው፣ ከምትወዷቸው ጋር የምታሳልፉት ጊዜ ተወስዷል፣ ( ልጆቻችሁ ጭምር) ብዙወቻችሁ አይናችሁን ቸክ ተደረጉ እስኪ ወይም ራሳችሁ አድርጉት እይታችሁ እንደበፊቱ ነው? ... ሌላም ውሎ አድሮ የሚከሰት አካላዊም ይሁን አዕምሯዊ ችግር አይቀሬ ነው። ያውም የኢንተርኔት ክፍያው፣ የስነልቦና ጫናው፣ ጥላቻው፣ ስጋቱ፣ ባልተገባ ውድድር የሚፈጠርባችሁ የበታችነት ስሜት፣ ከእምነትና ማንነታችሁ ጋር የሚጋጭ ትእይንትና ነውር ወዘተ ሳይቆጠር። ምንድነው ሳናቋርጥ ስልካችን ላይ የምንፈልገው? ምን? የሆነስ ሆነና ሶሻል ሚዲያው ላይ "ዘና ለማለት" በሚል ይሄን ሁሉ መክፈላችን ያዋጣል? እንደቀልድ ቁጭ ብለን ሰዓቱ እንዴት እንደሚፈተለክ አስባችሁታል? ዕድሜ የሚከፈልለት ምን? በቃ እንደዚህ እየኖርን ልናረጅ ነው? በቃ ህይወታችን ይሄ ሊሆን ነው ?እስከመቸ?

ኪነት በዮዳኒ

03 Nov, 15:00


https://vm.tiktok.com/ZMhXyWr5x/ This post is shared via TikTok Lite. Download TikTok Lite to enjoy more posts: https://www.tiktok.com/tiktoklite

ኪነት በዮዳኒ

02 Nov, 10:13


⨳ ሥነ — ግጥምና የማኅበራዊ ሚዲያ መተግበሪያዎች

በኢንተርኔት ላይ መሠረታቸውን የጣሉ የማኅበራዊ ሚዲያ መተግበሪያዎች (applications and platforms) መዳበር የዓለምን ገጽታና የሰው ልጆችን ዕጣታ ፈንታ ሙሉ ለሙሉ ቀይሮታል። በሁሉም የሕይወት እና የሙያ መስክ ነገሮች እንደ ድሮ አይደሉም። ይህ ለውጥ እጅግ ወግ አጥባቂ (conservative) የሚባሉ ክፍለ ዓለማትን ሳይቀር የተወደረ ክንዳቸውን እንዲያጥፉ፣ በባሕል ጦርነት እየተሸነፉ እንዲሄዱ እያደረገ ይገኛል። ኢንተርኔት የዓለምን አንድ መንደርነት ወይም ግሎባላይዜሽንን እውን የሚያደርግ፣ አይቀሬነቱን ያስረገጠ እጅግ ኃይለኛ መሣሪያ ሆኗል። ደጅን ዘግቶ፣ ተገልሎና ለሌላው ዓለም ባይተዋር ሆኖ መቀመጥ እምብዛም የሚቻል አይደለም።

🦅

በሀገራችንም ያሉ ፖለቲካዊ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች በማኅበራዊ ሚዲያ መተግበሪያዎች ተጽዕኖ ሲዘወር የምናየው ነው። በኪነ ጥበቡ ዘርፍ ያሉ ወቅታዊ (contemporary) ከያኒያንም ከዚህ የቴክኖሎጂ በረከትና መርገም ተካፋዮች ናቸው። የትኛውም የሥነ — ጽሑፍ ሰው በዘመኑ ካለ ክስተት ራሱን ለማግለል ቢጣጣርም፣ ፈጽሞ ግን ማምለጥ አይችልም። ለብቻው ሌላ ዓለምና መሸሸጊያ ደሴት የለውም። በአንድም ሆነ በሌላ መንገድ የከባቢው ሰለባ ነው። በሀገራችን ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ለሚታየው የሥነ — ግጥም ጥበብ እና ሕትመት መነቃቃት በግልጽ በሚታይ መልኩ የፌስቡክ መተግበሪያ ጉልህ አስተዋጽዖ አለው። አሁን አሁን ደግሞ ቲክቶክ ያፈራቸው ገጣሚያንም አሉ።

🦅

ቀስ በቀስ እየከሰሙ እስከሚሄዱ ድረስ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ የሥነ — ግጥም አብዮትና መድረኮች ተፋፍመው ነበር። ሥነ — ግጥም ከፒያሳና ከብሔራዊ የጥበብ ገዳም ወጥቶ በተለያዩ የአዲስ አበባና የክልል ከተሞች ተሰይሟል። ከዚያም ግዛቱን በማስፋት በመንፈሳዊ ተቋማት ሳይቀር ጉባኤ እስከማዘርጋት ደርሷል። ሆኖም ባለንበት ዘመን ሥነ — ግጥም ከመልካም ዕድል እና ከአስጊ ተግዳሮት ጋር የተጋፈጠ ይመስላል። ሥነ — ግጥም እንደ አንድ የጥበብ ዘርፍ እያበበ ነው ወይስ እየሞተ? ብለን እንድንጠይቅ እንገደዳለን።

🦅

ከላይ በተጠቀሰው በአዝመራው መስፋት፣ በገበያው መድራት የመዘነው እንደሆነ ህልውናው አይካድም። በየጊዜው ከአዳዲስ ገጣሚያንና የሥነ — ግጥም መጻሕፍት ጋር እየተዋወቅን ነው። ማኅበራዊ ሚዲያ የአንድ ነገርን እሴት የምንለካበትን መለኪያ ቀይሮታል። የሥነ — ግጥም ይዘቶችን (content) ዋጋ የምንለካው ባገኙት እይታ (view)፣ በተወደዱበት (like)፣ በተጋሩበት (share)፣ ደግመው በተለጠፉበት (repost) መጠን ነው። ከዚህ አንጻር ካየነው በተለያዩ የማኅበራዊ ሚዲያ መተግበሪያዎች ላይ ከፍተኛ የዕይታ መጠን ያስመዘገቡ የሥነ — ግጥም ከያኒያንና ይዘቶችን እንታዘባለን። ታዳሚያን በነጻና ገንዘብ እየከፈሉ የሚገቡባቸው የሥነ — ግጥም ዓለማዊ (secular) እና መንፈሳዊ ጉባኤያትም ወምበራቸው ጦሙን አድሮ አያውቅም። በማኅበራዊ ሚዲያና በተለያዩ መድረኮች ዝና በማትረፍ የተሸጡ፣ ከአንድ ዙር በላይ የታተሙ በጣት የሚቆጠሩ የሥነ — ግጥም ሥራዎችም ያጋጥሙናል።

🦅

ነገር ግን እነዚህ ውጤቶች በሙሉ ልብ የሚወሰዱ የሥነ — ግጥም እሴት እውነተኛ መለኪያዎች ናቸው ወይ? ተደማጭነትን በማሳደድ የተጻፉ አይደሉም? ማኅበራዊ ሚዲያ ቅኝት (Algorithm) ካልነቁበትና ተጠንቅቀው ካልያዙት ጠልፎ ጣይ ነው። ከያኒው ከሕዝቡ በፊት የሚቀድም ሳይሆን የተከታዮቹን ትርታ እያየ ገበያው ወደነፈሰበት እንዲነፍስ የማድረግ ጠባይ አለው። በእንዲህ ዓይነት ወጥመድ ለሚወድቁ ገጣሚያን ጸጋዬ ገብረ መድኅን በእሳት ወይ አበባ መግቢያው ብሮኖውስኪን አስታክኮ “በኪነ ጥበብ የተሰጥዖ ግዳጁ ተዳክሞ ተጭለምልሞ ነፍሱን ሲያሳድፍና የስሙን ጩኸት በምጥ በማስተጋባቱ ብቻ ዕለታዊ ተደማጭነትን እንደ ጥቅም ሲቃርምና ሲዘርፍ ግን ‘ያማ የኪነቱን የእውነታ አቅጣጫ ስቶ ብዕሩንም አሳተ ማለት ነው” ይላል።

🦅

ሌላኛው ከዚህ ጋር ተያይዞ የሚነሣው ተግዳሮት ወደተነሣንበት የሥነ — ግጥም መፍቻ ይመልሰናል። የሰው ልጅ ከሥጋዊ ሥሪቱ በተጨማሪ መንፈሳዊ የኾነ ፍጡር ነው ብለናል። ግጥም ተፈጥሯዊ ሥሪቱ መንፈሳዊ ሲሆን ሥጋን ለማገልገል ሲውል ግን ጥንቃቄ ይፈልጋል። ምክንያቱም የግጥም ውበት የሚጓደለው ለሥጋ ሲባል ይህንን መንፈሳዊ ጥበብ አመቻምቾ ማቅረብና መሸቃቀጥ ሲጀመር ነው። በቀደሙት ዘመናት “court poets” የሚባሉ ለሕይወት ዘመን በገዢዎች የሚቀጠሩ ገጣሚያን ነበሩ፤ የእነዚህ ገጣሚያን ሥራም እግር በእግር እየተከታተሉ ገዢዎቹን ማሞገስና እንጀራ መብላት ነው። እንጀራ አጉራሻቸውን፤ ድርጎ ቆራሻቸውን ላለማስቀየም ሲሉ ከግጥም መንፈሳዊ ጠባይ በተቃራኒው በመሄድ በአድርባይነት ያገኙትን ሲቃርሙ ይኖራሉ። ቅኔያቸው “ካለው ተወለድ ወይ ካለው ተጠጋ” ይሆንና ረብ ያለው ሥራ ከማበርከት ይልቅ የጊዜን ፈተና የማይቋቋም ወገቡ የተመታ ጎታታ የቃላት ድሪቶን ሲያጭቁ መኖር ይሆናል። በዚህ መልኩ ያጣናቸው ብዙ ባለተሰጥዖዎች የሚያስቆጩ ናቸው። እዚህ ጋር ሮበርት ፍሮስትን መጥቀስ ያዋጣል፦ “poetry is a condition not a profession”

🦅

ሥነ — ግጥም ንዑድ ክቡር ቤተ መቅደስ ቢሆን ገጣሚ ደግሞ ካህን ወይም ነቢይ ነው። “ባለቤቱ ያቀለለውን አሞሌ ባለእዳ” አይቀበለውም” ነውና ገጣሚያንም የግጥምን መልክ ወደቀድሞ ቁመናውና ሀቀኝነቱ ለመመለስ ትልቅ ሥራ ይጠበቅባቸዋል። እነዚህንና በዚህ ጽሑፍ ያልተዳሰሱ ተግዳሮቶችን ከግምት አስገብተን ሥነ — ግጥም ባለንበት ዘመን እያበበ ነው ወይስ እየሞተ? ብለን ስንጠይቅ የምናገኘው አንድም በተስፋ ያበበ፣ ሁለትም በድርቀት የተመታ መንታ መንገድ ይሆናል።

Cc ፡ Yohanes Molla, Theodros Atlaw

ኪነት በዮዳኒ

01 Nov, 10:21


የእመቤቴ እለት

ማደጌን አውቄ፣
ሔዋኔን ፍለጋ ልቤ እግር አብቅሎ፣
በእመቤቴ ቀን፣
እቅዱን ለማግኘት ማመንታቱን ጥሎ።

መንገድ ጀመረ እና፣
ብዙ በመፈለግ በማጣራት ማስኖ፣
በእመቤቴ እለት፣
ድካሙ አበበ መሰልቸቱ በኖ።

የመቤቴን እለት፣
ደጋግሞ ኖረ እና ወደድኩህ ካለችው፣
አንዱን ሰሞን ጠፍታ፣
ሳታገኘው ስትቆይ መስሎት የጠላችው።

ያገኘውን ማጣት፣
ከብዶ ታየው እና ደጇ ስለት ገብቶ፣
አምኗት ተረጋጋ፣
ጭንቀቱን አጋርቷት መጨነቁን ትቶ።

ብዙ ቆየች እና፣
ሳትደውል ሳያያት በአንዱ የማርያም ቀን፣
ናፈከኝ አለችው፣
በሚጣፍጥ ቃና በለሆሳስ ዘፈን።

ደሥታውን አምቆ፣
ስለቱን ሊያስገባ ሊሰናበታት ሲል፣
ዛሬን አብሯት ውሎ፣
እንዲያድር አዘዘችው በመፈቀሯ ኃይል።

አይሆንም አለና፣
ክልከላዋን ጥሶ መጓዙን ሲጀምር፣
ድጋሜ እንዳይመጣ፣
አበክራ ነግራው ዘጋች የልቧን በር።

አማኝ ምስኪን ልቤ፣
የእመቤቴ ቀን በእናቴ እለት፣
ያገኛትን ወዳጅ፣
በእመቤቴ ቀን ለእምነቱ ሊያጣት፤
ስለቱን ሸምቶ፣
ለሰማችው እናት ወስዶ እያስረከበ፣
አትምጣ ካለችው፣
እሷን አስበልጦ ከመሄድ ታቀበ።

✍️ እያደር ሞገሥ (የሞገሤ ልጅ)
👇👇👇https://t.me/eyadermoges1 https://t.me/eyadermoges1 https://t.me/eyadermoges1

ኪነት በዮዳኒ

01 Nov, 10:11


አንዳንድ ጊዜ የሚጻፉም ሆኑ በመድረክ የሚቀርቡ ሥነ — ግጥሞች “ተመልካች ምን ዓይነት ርእሰ ጉዳይ ላይ ያተኮረ ሥነ ግጥም ቢቀርብለት ይወዳል?” በሚለው ላይ ሊመረኮዙ ይችላሉ። በብዛት ርእሰ ጉዳያቸው ምን ላይ ያመዝናል? የገጣሚያኑ አቀራረባቸው፣ ድምፅ አጠቃቀማቸውና ተክለ ቁመናዊ እንቅስቃሴያቸው ማንን ይመስላል? ይህን መንገድ ለምን መረጡ? የጥበብ ቅኝቱ ገበያ ተኮር ሲሆን ገጣሚውም ሆነ ሥነ — ግጥሙ ይከሽፋል። ኀያሲና ገጣሚው ሰሎሞን ዴሬሳም በዘበት እልፊቱ መስከንተሪያው “ግጥምን የሚያረክሰው ያንዳንድ መስመሮች መበላሸት ሳይሆን፣ የሀሳብ ወይንም የስሜት ሀቅ ማጣት ወይንም ለገጣሚው ባይተዋር መሆን ነው።” በማለት ያጸናል። በዕውቀቱ ስዩምም «ገጣሚ ያላረገዘውን የማያምጥ፣ ያላማጠውን የማይወልድ፣ ያልወለደውን የእኔ ብሎ የማይጠራ እንደሆነ እናምናለን» ሲል ከሰሎሞን ጋር ይተባበራል።

🦅

ሥነ — ግጥም እንደ ሃይማኖት አንድ ወጥ ድንጋጌና ብያኔ የለውም። ስያሜው አቃፊ ቃል (umbrella term) ነው። ነገር ግን በባሕሪው የክዋኔ ጥበብ (performative art) እንደመሆኑ መጠን ራሱን በተለያየ መደብ፣ ቅርጽና አቀራረብ ሊገልጥ ይችላል። በዚህ ላይ የድኅረ ዘመናዊነት ጣጣ ሲጨመርበት ቀኖናዎች ፈርሰው ይበልጥ ለብያኔና ለዳኝነት ያዳግታል። ሆኖም ከያኒው ምን በአጉል ፈሊጥ ቢራቀቅ፣ በጄ ብሎ ቅጽር ቢነቀንቅ፣ ከፍ ሲልም ቢያፈርስ በሥነ — ግጥም ምንነት ዙሪያ መግባቢያዎች አሉ። ያን ልብ ማለት ያስፈልጋል።

🦅

በሀገራችን እንደ ጃዝ ካሉ ሙዚቃዎች ጋር ተቀናብረው የምንመለከታቸውና የምናደምጣቸው አብዛኛዎቹ የመድረክ ሥነ — ግጥሞች፤ በባሕላዊ የመሰንቆ፣ የክራር፣ የበገና ዜማ መሣሪያዎች ሲዜሙ ካደመጥናቸው ዘመን አይሽሬ ሥነ — ግጥሞች ጋር ለማነጻጸር ያለ አጃቢ ሙዚቃ ብናደምጣቸው ለጆሮ ይሰንፋሉ፣ ለልብ አይመቱም። ከዚያ በመለስ ይህ ልምምድ በራሱ ምጣኔ ያለውን፣ ቤት የሚመታውን (rhyme)፣ ሥልተ ምት (rhythm)፣ ቅርጽ (form)፣ እና መሰል ባሕርያት ኖረውት ምልዑ የሆነው ሥነ ግጥም፣ ካለሙዚቃ መሣሪያ አጀብ ለዓይን፣ ለጆሮና ለልብ የማይሞላ ተደርጎ እንዲሣል እያደረገ ስላለመምጣቱ መጠናት ይኖርበታል። እንዲሁ በአስደሳች ጥራት (quality) ታትመው የተሸጡ የሥነ — ግጥም መጻሕፍት፣ ቢያንስ በአንድ ዘለላ ሥነ — ግጥማቸው እንደ ዝርዉ ሥነ — ጽሑፍ፣ እንደ ወግ (essay) ላሉ ለሌላ የሥነ — ጥበብ ዘርፍ መቆስቆሻ ሆነው ሲጠቀሱ የማንሰማው ለምንድነው?

⨳ ሕትመትና ሥነ — ግጥም

እዚህ ጋር ደግሞ ወረድ ያልን እንደሆን ሌላ ተቃርኖ ያጋጥመናል። ወደ ወቅታዊ የሕትመት ገበያው እና የመጻሕፍት ግብይት ያመራን እንደሆነ ሥነ —ግጥም በአሳታሚያንም ሆነ፣ በአንባቢያን ዘንድ እየተገፋ እንዳለ እናስተውላለን። እጃችን ላይ በተከታታይ የገቡ መጻሕፍት በገጣሚያኑ አሳታሚነት የሕትመትን ብርሃን ያዩ ናቸው። ገጣሚያኑ የደከሙበትን ያህል እንደማይነበቡና እንደማይሸጡ ቢያውቁም የነፍስ ጥሪያቸውንና መቃተታቸውን ለማስታገስ ሲሉ የጻፉትን በግላቸው ተበድረውም ቢሆን የሥነ — ግጥም ሥራቸውን ያሳትማሉ። ዶ/ር ፈቃደ አዘዘ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ላሳተመው የኮሌጅ ቀን ግጥሞች ስብስብ በጻፉት መግቢያ ላይ ሥነ — ግጥም የጻፍ ጻፍ ግፊት፣ በተለያዩ ምክንያቶች እውስጣቸው ሰርፆ ፋታ በነፈጋቸው፣ ለዚህ ግፊት መልስ ለመስጠት ሲሉ በሚያሰናኙ ገጣሚያን እንደሚጻፍ ይጠቁማሉ።

🦅

ከሕትመት ገበያው እና ካለመነበብ አንጻር ካየነው ሥነ — ግጥም ለጊዜው እየሞተ ያለ ይመስላል። ለአንድ ጸሐፊ ካለመነበብ በላይ ሞት የለም። ሆርሄ ሉዊስ ቦርሄስ “This craft of verse” በተሰኘ መጽሐፉ ኤመርሰን ዋልዶ ጠቅሶ ከመጻሕፍት ንባብ ጋር በተያያዘ እንዲህ ጽፏል፦ “a library is a kind of magic cavern which is full of dead men. And those dead men can be reborn, can be brought to life when you open their pages.” የሥነ — ግጥምም ሆነ ሌሎች መጻሕፍት በፊደልነታቸው ደረቅ ሲምቦሎች ናቸው፣ ትርጉምና እስትንፋስ የሚዘራባቸው መነበብ ነው።

🦅

የግጥም ንባብ ቢዳከምም፣ አድማጭና ተመልካች ግን አለ። በአንጻሩ ይህ ከመጻሕፍት ንባብ ጋር በተያያዘ እንደ ሕዝብ ጆሯችን ለማድመጥ እንጂ ዓይናችን ለማንበብ እንዳልሠለጠነ በከፊል ሊነግረን ይችላል። የሀዲስ ዓለማየሁ ፍቅር እስከ መቃብር ይበልጥ ዝነኛ ያደረገው መነበቡ ሳይሆን በወጋየሁ ንጋቱ እየተተረከ በራዲዮ መደመጡ ነው። ሀዲስ ዓለማየሁ በራሳቸው አንደበት “ወጋየሁ ከመተረኩ በፊት ቆይቷል ፍቅር እስከ መቃብር በገበያ ላይ። ግን እርሱ ካስተዋወቀው በኋላ ነው ያን ያህል ተወዳጅነትን ያገኘው።” በማለት ይመሰክራሉ። በሌላ አንጻር ቀደም ባሉ ዓመታት ለሥነ — ግጥም የነበረውን ወርቃማ ጊዜ በዓይነ ኀሊናችን ብንቃኝ፣ “ታዲያ የግጥም አፍቃሪያኑ አሁን ላይ እንዲቀዛቀዙ ያደረጋቸው ምክንያት ምንድር ነው? በተለያዩ የማኅበራዊ ሚዲያ መተግበሪያዎችና መድረኮች ሥነ — ግጥም ሲታደም የምናየው ምዕመን ለምን የሥነ — ግጥም መጻሕፍት ለገበያ ሲበቁ ጠብቆና ተሻምቶ ሲገዛ አናገኘውም?” ብለን መሠረታዊ ጥያቄ እንድንጠይቅ ያነሣሣናል።

⨳ ሥነ — ግጥምን ወንዝ ማሻገር

በዚህ መሃል እጅግ የነጠሩ፣ እንኳን ለእኛ ለቀሪውም ዓለም በተለያየ ቋንቋ ቢተረጎሙ የሚተርፉ ሥራዎች በደጋፊ በማጣትና በማስታወቂያ እጥረት እስከጊዜው ድረስ ተደብቀዋል። አሁን አሁን በተለያዩ ክፍትና የኦንላይን መድረኮች ላይ በእንግሊዘኛ የሚቀርቡ የሀገር ልጆች የሥነ — ግጥም ሥራ ቢኖርም፣ ይህም በግል ጥረት የሚደረግ እንቅስቃሴ እንጂ ከጀርባ ድጋፍ አቅራቢ አካል ያለው አይደለም። እነዚህን ሥራዎች ገልጦ በማንበብና በማስተዋወቅ፣ ብሎም ሥነ — ግጥም ላይ የተጋረጡ ተግዳሮቶች ላይ እየተወያየ መፍትሔ የሚሰጥ የገጣሚያን ኅብረት የለንም። በራሳችን ቋንቋም በዓለም አቀፍ የሥነ — ግጥም መድረኮች ላይ እንድንወዳደር እና እንድንሳተፍ ጥሪ ለማቅረብ የሚሻ አካል ቢኖር ይሄን ጥሪ የሚሰማ ጆሮ ያለው አንድ ተቋም አለመኖሩ ያስቆጫል።

ኪነት በዮዳኒ

01 Nov, 10:11


Part #1

🦅 የሥነ — ግጥም ዘመነኛ መልኮች| overview
ባለንበት ዘመን ሥነ — ግጥም እያበበ ነው ወይስ እየሞተ?
🎈 Full Version | እሱባለው አበራ ንጉሤ

⨳ ሥነ — ግጥም ምንድነው?

የሰው ልጅ ከሥጋዊ ሥሪቱ በተጨማሪ መንፈሳዊ የኾነ ፍጡር ነው። ከሌሎች እንስሳት የሚለየውም በእዚሁ የመንፈሳዊ ሥሪት፣ አሳብና ስሜቱ ጭምር ነው። ስለዚህም የሰው ልጅ ፍላጎት በመብላት፣ በመጠጣት፣ በመዳራት ከሚገኙ ሥጋዊ እርካታዎች ይረቅቃል። ይህ ረቂቅ መሻት ደግሞ እርሱ ካለፈ በኋላ ለሚመጣው ቀጣይ ትውልድ ራስን በመግለጽና የኖረበትን የዘመን መንፈስ በመመርመር ለመተረክ በመትጋት ይገለጻል። ቃላት ተፈጥረው ለአፍአዊ ትርክት፣ ፊደላት ደግሞ ተፈጥረው ለሕትመትና ንድፍ ግልጋሎት ሲውሉ ይህንን የሰው ልጅ ነባር ፍላጎት ለሟሟላት ነበር። “ከሰው መርጦ ለሹመት፤ ከእንጨት መርጦ ለታቦት” እንደሚባለው ከቃላትም ደግሞ መርጠው ለሥነ-ግጥም ያውላሉ። ሥነ — ግጥም በአጭሩ የኖርንበትን የዘመን መንፈስ ለመግለጽ ያጨናቸው፣ ረቂቅ ስሜት የሚያጋቡ፣ ትርጉምና ውበትን አስተባብረው የያዙ የንዑድ ቃላት ስብስብ ነው ማለት ይቻላል።

⨳ ሥነ — ግጥም ለምን ይጻፋል?

አሜሪካዊው ገጣሚና ኀያሲ ዳና ጊኦያ ሥነ — ግጥም ከጥንታዊ የሰው ልጅ ኑባሬ፣ ዕድገትና ውስጣዊ ጉዞ ጋር ተያያዥነት ያለው የጥበብ ዘርፍ መሆኑን ያነሣል። ሥነ — ግጥም ሕልውናውም ከቅድመ ታሪክ (pre-history) ጊዜ አንሥቶ የነበረ ነው። የሰው ልጆች ታሪካቸውንና ጥበባቸውን በጽሑፍ መሰነድ ከመጀመራቸው በፊት የነበረ ኪነት እንደመሆኑ መጠን ሥነ — ግጥም ለሰው ልጆች የህልውና ጉዳይ ነበር ማለትም ይቻላል። ነገሮችን ባሉበት ወይም በተከሰቱበት ሐተታዊ ኹኔታ እንደ ወረደ ለማስታወስ መሞከር ከባድ ፈተና ነው። የማስታወስ ክሂሎት እጅግ ተለዋዋጭና የማያስተማምን ነው። ስለዚህም ሰዎች ታሪካቸው፣ ባሕላቸው፣ እምነታቸው፣ ፍልስፍናቸው፣ ግላዊ ተመስጥዖና ኀሠሣቸው እንዳይጠፋና እንዳይረሳ ወደ ሥነ — ግጥምነት ያረቁታል፣ ያሻግሩታል። ሕይወታቸው በቃላዊ ሥነ — ግጥም እየተነበነበ፣ እየተመደረከ መታወስ ይጠበቅበታል።

🦅

ጥንታውያኑ ሥነ — ግጥምን እንደ «Memory technology» ተገልግለውበታል። አሜሪካዊው ገጣሚ ሮበርት ፍሮስት «Poetry is a way of remembering what it would impoverish us to forget» ወይም «ሥነ — ግጥም እንድንረሳ የሚያደርገንን የምናስታውስበት መንገድ ነው» በማለት ይናገራል። ስለዚህም ሥነ — ግጥም ለሰው ልጆች ከትውስታ ዝንጋኤ ጋር ትግል የሚገጥሙበት፣ ራሳቸውን ለመግለጽ የሚጣጣሩበት፣ ጀብዱን የሚተርኩበት፣ አማልክቱን የሚያመልኩበት፣ መንፈሳቸውን የሚያድሱበት መንፈሳዊ ጸጋና መሣሪያቸው ነው። የሆሜር Iliad፣ Odyssey፣ የህንዶችን Mahabharata፣ የዳንቴን Divine Comedy፣ የጆን ሚልቶን Paradise Lost መሰል ጥንታዊ የገድል (Epic) ሥነ — ግጥም ድርሳናትን፣ እንዲሁም ከብሉያት ቅዱሳት መጻሕፍት እንደ ትንቢተ ዕዝራ፣ ትንቢተ ሕዝቅኤል፣ መዝሙረ ዳዊት፣ መጽሐፈ መክብብ፣ መጽሐፈ ኢዮብ ያሉትን በአብነት ማቅረብ እንችላለን።

🦅

ባሕልን ከዝንጋኤ ከመከላከል ባለፈ ሥነ — ግጥም የቃላትን ኃይል ለማጠንከርና ጉልበት ለመስጠት ይውላል። ገብረክርስቶስ ደስታ በመንገድ ስጡኝ ሰፊ ያላለቀ መግቢያው “አብዛኛውን ጊዜ ቃላት በግጥም ተቀርጸው በሚገቡበት ጊዜ ከትርጉማቸው በላይ አልፈው ተርፈው ይሄዳሉ” ይላል። ግጥም ከዝርው ይልቅ ለሰው ስሜትና ውስጣዊ ጆሮ ቅርብ ነው። በፕሮፖጋንዳ ያልዘመተው በሽለላና ቀረርቶ ይነሣል፤ በምክር ያልተገሰጸው በጥበባዊ ሥራ “እሺ” ይላል። እንዲሁም ግጥም ሀገራዊ ብልሽቶችን ለመታገል፤ ማኅበራዊ መበስበሶችን ለማረቅና የእኩልነትና የፍትሕ ድምፆችን ለማስተጋባት ጥቅም ላይ ውሏል።

🦅

በዓለም ላይ የነበሩ ትላልቅ አብዮቶችና ንቅናቄዎችን ከፊት ሆነው የመሩት ጠመንጃ ካነገቱ ተዋጊዎች ባልተናነሰ መልኩ ገጣሚያን ነበሩ። የጥቁሮችን የሰብዓዊ መብት መገፈፍ ወይም “Civil right movement” እንደ Maya Angelou, Nikki Giovanni, Margaret Walker, June Jordan ያሉ እንዲሁም፣ በተለያዩ የዓለም ጥግጋቶች የሕዳጣንን መበደል ይፋ አውጥተው ድምፅ የሆኑት ገጣሚያን ናቸው። ከእዚህም ባለፈ ብዙኅን ተስፋ ባጡበት፣ ማኅበራዊና ፖለቲካዊ አስተዳደሮች በተንኮታኮቱበት ወቅት ተስፋ እንዳለ በመንገር፣ ገብተው የወጡበትን ጨለማ በማመላከት ተስፋ የሰጡ፣ ኑሮን ያስቀጠሉ፣ የሕይወትን ሽታ ያሳዩ ባለቅኔዎች ናቸው።

🦅

በእኛም ሀገር “አዝማሪው ምን አለ?” ይባል ነበር። ነገሥታቱ የሕዝቡን ትርታ በአዝማሪዎች በኩል ያደምጡ እንደነበር ታሪክ ያስረዳል። በ1960ዎቹ የአብዮቱ ትውልድ የተማሪዎች እንቅስቃሴ ውስጥም በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴና በመኳንንቱ ፊት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በድፍረት ይቀርቡ የነበሩ የኮሌጅ ቀን ሥነ — ግጥሞች የትግል እንቅስቃሴው አንድ መልክ ናቸው። ከዚያ ባሻገር በተለያዩ የደስታ፣ የችግርና የመከራ ጊዜያት በቃል የተሰናኙ ጥንታዊ ግጥሞችን ለትውስታ ብንከልስ ሥነ — ግጥም የህልውና ወይም የ«Necessity» ጉዳይ እንደሆነ እንረዳለን።

🦅

ባለመሰንቆ የገዘገዘው፣ ባለበገና የደረደረው፣ አባ ውዴዎች በአራራይ ያንጎራጎሩት ሥነ — ግጥም ልባች ድረስ ዘልቆ መንፈሳችንን ያነቃቃዋል። ያስተክዘናል፣ ያሳስበናል። ዘመን ያሳልፋሉ እንጂ፣ ጊዜ አያልፍባቸውም። የባለቀረርቶና የሸላይ የስንኝ ጉልበትና ዘራፋቸው በሰላም ሀገር ያዘምታል። ፍርሃትን አባርሮ ወኔን ያስታጥቃል። በአጠቃላይ የ “Dead poet society” ገጸ ባሕርይ የሆነው “John Keating” እንደሚለው “We read and write poetry because we are members of the human race” ግጥም የምንጽፈው የሰው ልጅ በመሆናችንና ከዚህ ተላላፊ እዳ ነጻ ልንሆን ባለመቻላችን ነው።

⨳ ዘመነኛ የሥነ — ግጥም ተግዳሮቶች

ባለቅኔ በዕውቀቱ ስዩም በኗሪ አልባ ጎጆዎች መክፈቻው «ግጥም የህያው ስሜቶች ምስክርነት እንደሆነ እናምናለን፤ ምናባዊ መገለጥ እንደሆነ እናምናለን፤ ለአባቶቻችን የአብዮትን ሰይፍ የሚስል ሞረድ፣ ለእኛ ፍለጋ /ኀሰሳ/ መሆኑን እናምናለን፤ ያልተንዛዛ ለቅሶ፣ ያልቆረፈደ ተረብ፣ ያልተዝረከረከ ፍልስፍና መሆኑን እናምናለን» ሲል ያውጃል። ከዚህ አንጻር ተነሥተን ከቅርብ ዓመታት ወዲህ እየተገጠሙ በማኅበራዊ ሚዲያ ሰሌዳና በመጻሕፍት ሰፍረው ያነበብናቸው፣ የሰማናቸውና የተመለከትናቸው አብዛኛዎቹ ሥነ — ግጥሞች ከውስጣዊ መቃተት የመነጩ፣ መረሳት ስለሌለባቸው የተጻፉ፣ በጊዜ የማይደበዝዙ፣ ውበትና እውነትነታቸው እያደር እየገዘፈ የሚሄዱ ግጥሞች ናቸው ወይ? የሚለውን ጥያቄ የመመለስ የቤት ሥራ ይጠበቅብናል። ኀያሲ አብደላ እዝራ ለኤፍሬም ስዩም ኑ ግድግዳ እናፍርስ ለተሰኘ መጽሐፉ ባሰፈረው ድኀረ ቃል ላይ «ግጥም ስሜትን ለማፍካት፣ በሆነ ጉዳይ ለመብሰክሰክ፣ በውበት ለመደመም፣ ቢቀር ቢቀር በቋንቋው ንዝረት ለማገገም ይነበባል። አንብበነው እውስጣችን የሚፈነዳ፣ ለንዴት አሳልፎ የሚሰጠን፣ ለባይተዋር ነፍስ ሆነ ለሌላው ጉዳይ እንድንቆረቆር፣ ከህሊናችን እሚላወሰው በጣም ጥቂት ነው» በማለት ያጸናል።

🦅

ኪነት በዮዳኒ

30 Oct, 19:43


https://youtu.be/mlYHsMFeBYo

ኪነት በዮዳኒ

30 Oct, 09:02


Share 'አልተዘዋወረችም ✍️አሌክስ አብረሃም @gbw_dan.pdf'

ኪነት በዮዳኒ

30 Oct, 08:54


ኪነት በዮዳኒ pinned «ከደቂቃዎች በኋላ የአሌክስ አብረሃም #አልተዘዋወረችም መጽሐፍ ለናንተ ይደርሳል! Share ..... አዘጋጅ:-@gbw_dan #me_yami»

ኪነት በዮዳኒ

30 Oct, 08:53


ከደቂቃዎች በኋላ የአሌክስ አብረሃም #አልተዘዋወረችም መጽሐፍ ለናንተ ይደርሳል!

Share .....


አዘጋጅ:-@gbw_dan
#me_yami

ኪነት በዮዳኒ

27 Oct, 11:00


#ትዝታ
በሠንበት ወግ
(የ ሞገሤ ልጅ)

እንደኃገራችን በእድሜ ወደፊት በኑሮ ወደኋላ መጓዝ እኔ እና መሰሎቼ እጣችን እንደሆነ ማሰብ ለመጀመር የተገደድኩት እኔን ጨምሮ አንድ አንድ የማውቃቸው፣
“ድሮ እኮ ጥሩ ነበር”
ማለት እንደምናበዛ በማወቄ ነው።
ምክንያቱም ጥሩ የነበረው ድሮ በእኔ አልተሰራም። በእኔ የተሰራው ዛሬ ግን ጥሩ አይደለም ማለት ነው። ስለዚህ ጥሩ የሰራውን ግለሠብም ሆነ ኅብረተሠብ መሻማት የምንኖርበት ዛሬ ትዝብት ለመሆን ተገዷል።
*ማኅበረሠብ ወታደራዊ እና ዘመናዊ ተብሎ መከፈል ይችላል።
በወታደራዊው የማኅበረሠብ አይነት ውስጥ በእራስህ መንገድ መኖር የማይታሰብ ነው። የሠራሐው ነገር ተቀባይነት የማያገኘው ልክ ስላልሆነ ሳይሆን ባህል ስላልሆነ ሊሆን ይችላል።
በአንጻሩ ግን ዘመናዊ የማኅበረሠብ ክፍል ውስጥ ምርጫህን ከመረጠህ ጋር ወይም ብቻህን ትኖራለህ።
እንደልብ እራስን ማጨማለቅም ማርቀቅም የተፈቀደ ነው።
እራሱን መምራት ላልቻለ ታዲያ ዘመናዊነቱን አልደግፍለትም።
“ሠው ማኅበራዊ እንስሳ ነው” የሚለውን ሳይንሳዊ ትንተና ተቀብሎ ሳያላምጥ በመዋጥ አንተ በምታልፍበት ጎዳና ሲወስብ ታገኘዋለህ። በፈሪሃአምላክ አትንኩ የተባለን ሳይነካ ኗሪ፣
“አምላክ መኖሩን ማስረጃ” ብሎ ይጠይቀው እና ማስረጃዎቹን ከአፈር ከቀላቀለ ብኋላ፣
“አምላክ ሊኖር እንደሚችል ማስረጃው አምላክ እንደሌለ ማረጋገጥ አለመቻሉነው” ይልህ እና አምላክ ሊኖርም ላይኖርም ይችላል ወደብሎ ማመን ያሸጋግርሃል። ከዛ ብስልም ጥሬም ባለመሆን በአምላክህ ትተፋለህ።
እኔ ታዲያ ዘመናዊዉን የማኅበረሠብ አኗኗር በጥቅሉ አልደግፍም፣ የወታደራዊው አይነት ግን በከፊል ውስጤ ነው። እንግዲህ ወደራሴ ትዝታ ግን በሌሎች ወደተሰራ ትላንት መመለሴ ነው።
• ሠፊ በሚባል ቤተሠብ ውስጥ መኖሬ መቻቻልን፣ አንድነትን፣ መተሳሰብን፣ መተባበርን እና መከባበርን እንድረዳ እንዳገዘኝ አምናለሁ። ብዙ ያልቆየ መቀራረብ፣ ረጅም ዘመን ያልተቆጠረበት ኅብረት፣ ያልተጠገበ አብሮ መኖር፣ የተገደበ መቻቻል፣ የሰፋ መነፋፈቅ፣ የተራራቀ መገናኘት፣ የተለካ አብሮ መሆን፣ የተወሰነ መጨዋወት የሰፈነበት ትልቅ ቤተሠብ።
• * 12 ሆነን በምንኖርበት የአባታችን እና እናታችን ቤት ውስጥ ብዙ ጸባያት ነበሩ። ብስጭት፣ የዋህነት፣ ሞኚነት፣ ብልጥነት፣ ሞልቃቅነት፣ ዝምተኝነት፣ እና ሌሎች በውል ምድባቸው ያልተገለጹልኝ በሃሪያት።
• ***
• ወንድማችን ነው። ከሚያጠልቀው ቦት ጫማ በቁመት ኮርቶ ሳይበልጥ እራሱን ማስተዳደር የወሰነ ጀግና። ከላይ ሲረዳን እንደየዋህ የሚያደርገው ደፋር።
እህል የተወቃበትን አውድማ ለሊት ጠርጎ በቁጥር በጣም ትንሽ በኃይል ጠንካራ በሆነች ሳንቲም ዶሮ ገዝቶ ማርባት ጀምሮ እንቁላል ማምረት ይዞ ነበር። ታድያ እኛ ለመንካት አይፈቀድልንም።
የተባበሩት ወንድሞች ዘዴ ታድያ በግዜው ከማስተዋሉ የበለጠ ሆነ እና በጭራሽ ለመንካት የማይፈቀድልን እንቁላል ወደያልተገደበ የምግብ ዝርዝር ተሸጋግሯል። ሃሳቡን ከመናገሬ በፊት ግን ያ በጥብቅ የሚጠበቀው እንቁላል እኔን በደረሠብኝ ግዜአዊ ህመም ጥቅም ላይ በቸርነት ውሏል። ታድያ የዛሬው ትረካዬ ካልሆነችው ተወዳጅ እህቴ ያልታወሰኝ የኃብት ምንጭም ተጨማሪ እንቁላል ታክሎበት ነበር። አሁን ወደታሪኩ ልመለስ።
• የተከማቸው እንቁላል የሚያጓጓን ልጆች መብዛታችን እና በአይምሮ የተሻለ የበሰሉ ጓጊዎች መኖራቸው የዛን ንብረት ክልከላ እንዳይመለስ አድርጎ ማጥፋቱ እሙን ነው። ወደ ማሳመኛው ሃሳብ ቶሎ ወስጄ ላሳያችሁ። የወንድሜን ስም ግን ባምላክ ብዬ ለዚህ ጽሁፍ እጠራዋለሑ። ስለዚህም በታሪኩ ባምላክ እየተባለ የሚገለጸው ወንድሜ ንብረቱን ያስረከበ፣ ወንድሞቼ እያልኩ የምገልጻቸው ወንድሞቼ ደግሞ የሃሳቡ አመንጪ እና የንብረቱ ተጋሪ መሆናቸው ልብ ይባልልኝ።
• *ወንድሞቼ፣
• “ባምላክዬ እንቁላል እንብላ ዛሬ?”
• *ባምላክ፣
• “ማርያምን አንድ ሠው ይነካ እና!”
“ወንድሞቼ፣
“ለምን እንዴ!”
ባምላክ፣
“ዶሮዎቹ የራሴ ናቸዋ አያገባችሁም።”
ወንድሞቼ፣
“እኮ ዶሮዎቹ ናቸዋ ያንተ!”
ባምላክ፣
“እና?”
ወንድሞቼ፣
“እንቁላሉ ደግሞ የኛ ነው!”
ባምላክ፣
“ኧረ እ!”
ወንድሞቼ፣
“እውነት! ስለዚህ ዶሮዎችህን አንነካም፣ እንቁላል ግን እንበላለን።”

*አሁን ላይ በታሪኩ ሁላችንም እንስቃለን። እውቀት ሲደረስበት ይናቃል እንጂ በግዜው የቤቱ ድንቅ ተንኮል ነበር ሃሳቡ። በልጅ አእምሮ የታሰበ ድንቅ ማታለያ።
ሕይወት ጥሩ ሆና ልትዘልቅ ትችል ይሆናል፣ መጨረሻዋ የሚበሠረው በሞት ስለሆነ ግን ደሥ አይልም። በጥሩ ቤታችን እንደነበረ እንዳይቀጥል መጠነኛ እርማት ያደረገ ችግር ግን ነበር፣ እንመጣበታለን። እስከዛው ለሌሎች እያዳረስን! አበቃሁ።
https://t.me/eyadermoges1 https://t.me/eyadermoges1 https://t.me/eyadermoges1

የቻናሉን link ማጋራት እና ድጋፍዎን ማጠናከር አይዘንጉ! ሃሳብ ካለዎት ወይም በቻናላችን እንዲጋራ የሚፈልጉት ስራ ካለዎት @afengusbot ላይ ይላኩልን! አዲስ ነገር ይገባችኋል።

ኪነት በዮዳኒ

27 Oct, 09:26


ትዝ ይልሻል!
ነሃሴ ወር
ስንተዋወቅ
በምሽት ቁር
በርዶሽ ነበር
በርዶኝ ነበር።

ታዲያ ምን አሰብን?
ጨረቃን እናንድድ ተባባልን!
ለኮስናት
ሞቅናት።

#me-yami

ኪነት በዮዳኒ

26 Oct, 06:23


ደርሷል ደርሷል ደርሷል!
የሞገሤ ልጅ አዲስ ግጥሙን ከደቂቃዎች ብኋላ ለቤተሠቦቹ ያስመለክታል!
አሁኑኑ ይቀላቀሉ፡ https://t.me/eyadermoges1 https://t.me/eyadermoges1

የቻናሉን link ማጋራት እና ድጋፍዎን ማጠናከር አይዘንጉ! ሃሳብ ካለዎት ወይም በቻናላችን እንዲጋራ የሚፈልጉት ስራ ካለዎት @afengusbot ላይ ይላኩልን! አዲስ ነገር ይገባችኋል።

ኪነት በዮዳኒ

25 Oct, 19:08


🖤💧⚰️💀

አስር ሞት ቁሟል ከ'ደጄ ~
አይኔ ላይ ያንዣብባሉ ~ በርካታ ውል አልባ ቅርፆች
በቀየው ህይወት የለችም ~
ሚሰማው...
በሬሳ ያጥንት ትፍግፍግ ~ ሚወጡ የሙታን ድምፆች።

ላሽወይና ያሟሟቀ አፍ ~ ያወርዳል የዘመን ሙሾ
ሰዉ ከሰው ቂም ተቆጣጥሯል ~ አፍርቷል የበቀል እርሾ
ለሰርግ የጣሉት ዳስ ላይ ~ ሞት ወረደበት እስክስታ
አባት በልጁ ሞት አለቀሰ ~ እናት ወደቀች ራሷን ስታ።
ተስፋ መቁረጥ ንጉስ ሆነ ~ ተስፋ ራሱ ተስፋን አጣ
ደህና ውሎ ቤቱ አይገባም ~' ደህና አውለኝ ' ሲል የወጣ።
ቄስና ሼኩም አንድ ላይ ~ ፈጣሪ ላይ አኮረፉ
" ወይ ፍረድ፤ ወይ ዉረድ "~ ሲሉ ጌታቸውን ወረፉ።

ይሄውልሽ እኔ ቤት ነኝ ~ ሰፈሩ በሞት ሲታጠብ
የሟቹ ቁጥር አይሎ ~ የቀብር ቦታ ሲጣበብ
አካሌን ቀቢፀ ተስፋ ~ የስጋት ደረመን ሲያጥር
በነፍሴ ትርትር እላለሁ ~ ዙሪያዬ ኮሽ ሲል ቁጥር።

ቆይማ...
( ምንድነው እዚህ ሚሰማኝ?)

መባርቅት ያጀቡት ክላሽ ~ የመሞት አዋጅ ለፈፈ
ይሄውልሽ...
በጎኔ ጥይት አለፈ።
(ደንገጥኩ )
መስኮቴን ከፍቼ ወጣሁ ~ መንገዱን በትኩረት ማተርኩ
ወዲያው ግን (አንድ ቀን የነገርሽኝን )
'' በሬ ሳላይ መጣሁ ከዛ'ስከዚ ድረስ "
ምትል ቅኔ አስታወስኩ።

ሰፈሩ እንዳለ ወድሟል ~ አንድ ቤት የለም
የቀረ (አንድ ሰዉ የለም የቀረ)
ያ ዋርካ (አድባራችንም )...
አንገቱን ደፍቶ ለሚያየው ~ ይመስላል ያቀረቀረ።

[ ወዳንቺ ልመጣ ወሰንኩ ]

መሬት ላይ መንፏቀቅ ጀመርኩ ~ በቁሜ መራመድ ፈራሁ
ከፊቴ ያለን ሬሳ ~ ቀስ ብዬ ወደ ጎን ገፋሁ
ታውቂያለሽ....
ቢበዛ ሰባት ዓመት ልጅ ~ ሰባቴ ጥይት መቶታል
[ መንግስት ላይ ተስፋ ብንቆርጥም ~ ነገር ግን እግዚሩስ የታል?]
ከኢየሱስ ስቃይ በማያንስ - ብዙ ሰዉ እዚህ ተሰቅሏል
ያውልሽ እዛ ጋ ደግሞ
የኢዮብን ቁስል በሚያስንቅ ~አንድ ሰዉ አካሉ ቆስሏል።

ይህንን 'የሞት ደብዳቤ ' ቢቀናኝ (በህይወት ብተርፍ)
ራሴው እነግርሻለሁ
አሊያ ግን ሞት ከቀደመኝ...
ራስሽ እንድተነቢው ~ ኪሴ ውስጥ አኖረዋለሁ።
ከደረት ኪሴ ስላለ - ስትቀብሩኝ መሬት ይወድቃል
ያን ጊዜ በፍጥነት አንሺው
{ አደራ እንዳትረሺው }

፦ ግዑዝኤል

ኪነት በዮዳኒ

20 Oct, 13:10


ታናሽ እህቴ ናት በአስራ ሶስት አመት እበልጣታለሁ ። እሷ ላይ ያለኝ ስልጣን የአለቃ ነው ። 'exercise' የማደረገው ስልጣን ብዙ ነው የአፍሪካ መሪዎች  ዜጎቻቸው ላይ ካላቸው  ስልጣን አያንስም ። እሷም ስልጣኔ ነው ብዬ 'exercise' የማደርገውን በፀጋ ተቀብላለች ።

ልጄ ትመስለኛለች ምግብ በጋራ ስንበላ ቀድሜ ነው በቃኝ የምለው ። ከሷ ጋር እንዳልሻማ ፍቅሬ እና ሃላፊነቴ ይገታኛል ።

ሁኔታዋን  አየዋለሁ ሲዶክካት፣ ስትደሰት እንቅስቃሴዋን  አስተውላለሁ  ። ከጓደኛዋ እንዳታንሳ  'Invest' አደርግባታለሁ ።

የሆነ ፊልም እያየን  መጥፎ ገፀባህሪ  ስታይ "ኤፍሬም ፊልም ስለሆነ ነው እንጂ:  እንደዚህ አይነት ሰው በትክክለኛ ህይወት የለም አይደል? " ትላለች

ሰው የማርያምን ስም ጠርቶ የሚዋሽ አይመስላትም ፣ ለገንዘብ ብሎ ሰው ጓደኛውን የሚክድ አይመስላትም ፣ የውሸት ለቅሶ ያለ አይመስላትም ። ንፁህነቷ ያስደነግጠኛል ። ብስለት የሚባለውን እውቀት ማጥመቅ ፈልጌ አጠማመቁ ግራ ይገባኛል ።

ስለዓለም ክፋት መንገር እጀምር ና አለምን የምታይበት መነፅር እንዳይንሸዋረር እሰጋለሁ ።

'Feminist ' አደረገችኝ። ትሁቴን እያሰብኩ መደፈር፣ ድብደባ፣ ጭቆና እቃወማለሁ ። ትሁቴን  ስለማስብ ሴት አታልሎ ወደ አልጋ መውሰድ አልችልም ። ትሁትን እያሰብኩ  ገራገር  እንስቶች ላይ 'Advantage ' ለመውሰድ አልሞክርም ።

ትሁቴ የመጀመርያ ልጄ ነች ። በሷ ጉዳይ አልራቀቅም  ፣ በሷ ምክንያት ሴቶች ላይ በደል አልሰራም ።

ትሁቴ እንዳትኮርጀኝ ሰክሬ አልንገላወጅም ፣ የማይረባ ጓደኛዬን እቤታችን አላመጣም ፣ ትልቅ ለመሆን እባትላለሁ ።

የአንዳንድ ታናሽ አሻራ እንደ መምህር አይነት ነው !!
   © Adhanom Mitiku

ኪነት በዮዳኒ

18 Oct, 09:57


#ጥቆማ: 4ኛው የኢሰመኮ ዓመታዊ የሰብአዊ መብቶች ፊልም ፌስቲቫል የጥበብ ሥራዎች ውድድር ተጀምሯል።

ውድድሩ በሕይወት የመኖር መብት በተለይም በሴቶች ሕይወት ላይ፣ በኢኮኖሚያዊ እና ማኅበራዊ መብቶች ዘርፍ ደግሞ በበቂ ምግብና ውሃ በማግኘት መብት ላይ የሚያተከኩር ሲሆን እስከ ጥቅምት 30 ቀን 2017 ዓ.ም ለተወዳዳሪዎች ክፍት ሆኖ ይቆያል።

- የሥዕልና የፎቶግራፍ ውድድሩ ትኩረቱን በቂ ምግብና ውሃ በማግኘት መብቶች ላይ ያደርጋል።

- የሥነ ጽሑፍ ሥራዎች ውድድር ደግሞ በሕይወት የመኖር መብት በተለይም በሴቶች ሕይወት ላይ የሚያተኩር ነው፡፡

በአጫጭር የሥነ ጽሑፍ ሥራዎች ዘርፍ ለውድድር የሚቀርብ ሥራ ከ 3 ገጽ ያልበለጠ (ከ600 ቃላት ያላነሰ፣ ከ1200 ቃላት ያልበለጠ) ሊሆን ይገባል።

በሁለቱም ዘርፎች የሚቀርቡ የጥበብ ሥራዎች ዘጋቢ፣ ምናባዊ ወይም እውነተኛ ታሪክ ላይ መሠረት ያደረጉ ሊሆኑ ይችላሉ ተብሏል።

ለውድድሩ የኪነጥበብ ሥራዎችን የመላክ ሂደት ምን ይመስላል ?

ለውድድሩ እስከ ጥቅምት 30 ቀን 2017 ዓ.ም. እኩለ ለሊት ወይም ድረስ ለውድድር የሚቀርበውን የኪነጥበብ ሥራ እንዲሁም የተሞላ እና የተፈረመበት የተሳትፎ ቅጽ በማያያዝ፤

በኢሜል [email protected]
በቴሌግራም @EthioHRC መላክ ይቻላል።

በተጨማሪም በኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ቢሮዎች በአካል በመገኘት መላክ ይችላሉ ተብሏል።

#ተጨማሪ: ውድድሩ የሚካሄድባቸውን ከተሞችንና የውድድሩን ዘርፎች ከምስሉ ላይ ይመልከቱ።

@tikvahethmagazine 💬@tikvahmagbot

ኪነት በዮዳኒ

18 Oct, 07:51


መልካም ዜና 12ኛ ክፍል ላጠናቀቃችሁ በሙሉ፦

🚴‍♀️ ብስክሌት
🏍 ሞተር
🛵 E-bike ካልዎት ምን ይጠብቃሉ? ከቢዩ ዴሊቨሪይ ጋር መስራት ይችላሉ!

💰 ቢዩ ዴሊቨሪይ የምግብ አድራሽ ድርጅት ሲሆን፤ ብስክሌት፣ ሞተር እና E-bike ካለው ግለሰብ ጋር አብሮ መስራት ይፈልጋል፡፡

💰 በተጨማሪም 🚲ብስክሌት🚲 ለሌላቸውና ይሄን ሥራ መስራት ለሚፈልጉ ሰዎች በቅናሽ ዋጋ አመቻችቶ ብስክሌት በመስጠት ኑ አብረን እንስራ ይላችኋል።

የትምህርት ደረጃ፦ 12ኛ ክፍል ያጠናቀቀ
የሥራ አድራሻ፦ አዲስ አበባ

ለመመዝገብ፦

- በ Telegram Bot 👉 https://t.me/DriversRegistration_bot በመጠቀም የቀረባልችሁን ጥያቄ በመሙላት

- በስልክ ቁጥር 0923344444 ላይ በመደወል መመዝገብ ይችላሉ።

ኪነት በዮዳኒ

17 Oct, 18:44


🏆 ሁለተኛ ዙር የበጨዋደምብ የግጥም ውድድር እየደረሰ ነው!
በሁለት ሳምንት አንዴ የሚደረገው የግጥም ውድድር እንሆ በፊታችን እሁድ ምሽት ይደረጋል!
አሁኑኑ ይዘጋጁ እና በተሰጠው መወዳደርያ ስራን ማስገቢያ ሰአት ያስገቡ!
ስለህግጋቶቹ እና ተጨማሪ መረጃዎችን በዚህ ሊንክ፡ https://t.me/eyadermoges1/1361 ላይ ማገኘት ይቻላል! እግረመንገድዎን ቻናሉን ጆይን ማድረጎ አይረሳ! ደርሷል 🏃🏃!

ኪነት በዮዳኒ

16 Oct, 05:36



እግሬ ወደ ጉድጓድ ፥ ነፍሴ ወደ አምላኳ ፥ ልቤ ወደ ሞቱ፥ ለመሄድ ሲቻኮል
እንደ እንቅፋት ሆኖ፥ መንገዴ ላይ አለ፥ መኖር ይሉት ተንኮል
ሞቴን እንዳልጨብጥ ፥ ለሙሉ እኔነቴ ነፍሴን እንዳልወክል
መኖር እግሬ ስር ፥ እንደ ታኮ አለ ፥ እንደ መስናክል

(ከመኖርም እሷ : ከህይወትም ፍቅሯ
እሷ እያለች ላልሞት የገባሁላት ቃል : እንዲሁም መኖሯ )

ልቤን ያደረገው...
ለሞት እንዳይጨክን ፥ እንዳይርቅ ከነፍሱ
ከቤቱ ግድግዳ ፥ ከልቡ አፀድና፥ ከፃፈው ደብዳቤ፥ በጉልህ አድምቆ ያስቀመጠው ጥቅሱ

(እንዲህ ይላል ጥቀሱ...)

''አንቺ ኖረሽ እንጂ ~ መኖር የጣፈጠ
አንቺን አይቶ እንጂ ~ ይህ ቀድሞ ሟች ልቤ ~ ህይወት የቋመጠ
መኖርማ እንደሆን !
የሟቾች እዳ ነው ~በለት ዕለት መቅለጥ ~ በጊዜ ሚከፈል
መኖርማ እንደሆን !
ልክ እንደ ጫጩት ነው ~ በትዕግስት የሚገኝ መሞት ሲፈልፈል ''

ይል ነበረ ጥቅሱ
(እውነቴን እኮ ነው...)
እሷ ኑራ እንጂ፥ ለነፍሴማ እንደሆን...
ይሻላት ነበረ፥ ሁሌ ከመታመም ፥ ያንድ ቀን ሙት መሆን ።

፦ ግዑዝኤል

ኪነት በዮዳኒ

14 Oct, 03:33


🫦

እስቲ ሳሚኝ
ሳሚኝማ
በያ ሳሚኝ...

{ እሺ ስሚኝ... }

መሳምሽ መሳም አይደለም እኔጋ ፥ ማሳለም ነው ውብ ከንፈርሽን
ለኔም መሳም መሳለም ነው፥ ውስጥሽ ያለ ታቦትሽን።
ታቦትን ጣውላ ነው ለሚል ፥ ለዚህ ትውልድ ባይገባውም
እግዜርን ካንችነትሽ
ታቦትን ከከንፈርሽ ፥ አስበልጬ አላየውም።

ከንፈርሽ...
ያ' ስቴር ልሳኗን
የ'ናቴ ቃሏን
(ይመስለኛል)
ተኝቼ ሳለሁ በህልሜ
አካል አልባ ፤ ፊት አልባ
ከንፈር ብቻ
( ይታየኛል)።

አትሳቂልኝ ግድ የለሽም ፥ ጭንሽም ይቆይ ይከደን
እኔኮ ቤትሽ የመጣሁ ፥ ማር - ዘነብ ከንፈር ለማደን።

ሳሚኝ ቅድም
ሳሚኝ ነገ
ሳሚኝ አሁን...
ከዛ ግን ስትፈልጊ
'ጎረምሳ' ድምፅሽን ልሁን
....
ፀጉርሽ ለፍሬዝ ያንሳል ፥ ሲቀጥል ምላጭ ይሰብራል
ግንባርሽ ሰፊ ሜዳ ነው ፥ አስራ ስንት ሰፈር ያሰራል

አፍንጫሽ ድንበር ይጥሳል
ምላስሽ እግር ይልሳል
አንገትሽ ከቀጭኔ ፊት
እልፍ አ'ላፍ ቅናት ያተርፋል
ቁመትሽ ሲሄዱት ቢያድሩ
ማራቶን ያህል ይተርፋል

የጥርስሽ አደንደሩ
የጥያ ትክል ድንጋይን
ለቅፅበት ያሳውሰኛል
እንዳንቺ ያለን ሴት ታዲያ
ጤነኛ እንዴት ይመኛል ?

ምክንያቱ:-
የማርያም ድንግልናዋን
የክርስቶስ ሰምራ ቅድስናዋን
የአርሴማ ልግስናዋን
በውበት የሚስተካከል፤
እግዜሩ ከንፈር ሰጦሻል
በውርደቶችሽ መካከል።

እኔም ...
" እሷ ትቅር ይቅር
ጌታ ሆይ አደራ ከንፈሯን አትንሳኝ
በዚ አለም ባይሆንም
ኋላ ስትመጣ ከንፈሯ ጋር አንሳኝ ''
እያልኩኝ እፀልያለሁ
ፀሎቴን ከ'ግዜር ደብቄ
አንቺኑ ስሚኝ እላለሁ
(አንቺኑ ሳሚኝ እላለሁ፡፡)

ሳሚኝ እስቲ በ'ናትሽ

:- ግዑዝኤል

ኪነት በዮዳኒ

11 Oct, 20:57


✏️🖤

አድባር ጠራኝ
ጌታ መራኝ
ለግጥም ብዕሬን አተባ
በሬን ከፍቼ ባባርረው ፥ በጓሮ በር ዞሮ ገባ።

ቃላትን በቃላት ላይ ደራረበ
መንፈሱ በላዬ ላይ አረበበ
ስሜት ሰጠኝ
ሀሳብ ሰጠኝ...
በጩኸት መሀል ሰማሁት፥በዝምታ መሀል ዋጠኝ
ረበሸኝ በጠበጠኝ...
ሁለመናዬን የራሱ አረገ
መንፈሴም ከኔ ጋር ሆኖ፥ጥሎኝ ሰማያት አረገ።

እኔን ለኔ ተወልኝ
ነፍሴን በፍቅሩ አሻፈዳት
አይኔ እያየ ከጉያዬ ፥ ከጎኔ ስቦ ወሰዳት
እኔን ግን ለኔ ተወልኝ
ነፍሴን ግን በፍቅሩ ሰዋት።

ከኔ ቀጥሎ
ከሰው ነጥሎ
እንደ ባዕታዊ ባዕት ውስጥ ፥ ዘጋባት ብርሃን ከልክሎ
መንፈሷን ላበራች ውብ ነፍስ ፥ ሌሊት ነው ሚሻላት ብሎ።

አድባር ጠራኝ
ጌታ መራኝ
ቀረብ ስል ሶስት አረገኝ
( እኔ ~ ነፍሴ ~ የነፍሴ መንፈስ )
ከወንጌሉ አጣቅሼ
ምዕራፍ እንተን ቁጥር እንትን ስል ጠቅሼ
እንዳልችል እንኳ
"እኔና ነፍሴ አንድ ነን
እኔ በነፍሴ እኖራለሁ
ነፍሴም በኔ ዘንድ አለች "
ብሎ ማለት
እኔነቴ ያለ ነፍሴ፥ እድፍ ጉድፍ በዛበት።

ንግድ አረኩት ሁሉን ነገር፥ያዋጣል አያዋጣም ጥናት
ለወለድኳቸው ግጥሞች፥አልችል አልኩኝ መሆን እናት።

ስሜት ሰጦኝ
ብዕር ሰጦኝ
ልብ ሰጦኝ....
ከሰዎች መሀል ነጥሎ
ቅፅበታትን ከውብ ቃላት፥አንድ አድርጎ ሰጦኝ መርጦ
አያያዙን አልችል አልኩኝ ፥ አዕምሮዬ ከልቤ በልጦ።

ክፋቴ የሞት እኩያ ፥ ምቀኝነት የ 'ለት ግብሬ
ግጥም ብዬ የምፅፈው ፥ ስሜት አልባ ተራ ወሬ
ለጥበብ ባደላደለው
ልብ በሚባል እርሻ ፥የበቀልኩኝ ያሳብ አረም
ዙሪያዬን በሾህ አጥሬ ፥ ካመት ዓመት ማልታረም።
ከዛ ግን ጌታ መጥቶ
እኔን ጠርቶ
ነፍሴን ነፃ ሊያወጣት ከራሴው ፥ ቀራኒዮ ላይ ሰቀለኝ
ያን ጊዜ ነፍሴ አመለጠች ፥ አንዳችም ሸክም ቀለለኝ።

ከጌታ ስር ሄጄ ተደፋሁ ፥ በፅኑ እንባ ተላመንኩት
" ነፍሴን ከኔ እንደነጠልክ
እኔን ከኔ ነጥልና
እኔን በነፍሴ አኑረኝ''
....................................አልኩት።

፦ ግዑዝኤል

ኪነት በዮዳኒ

11 Oct, 18:56


መአዛ:- "ያለንባብ ሕይወት ምንድነው?
ዓለማየሁ:- "ያው መብላት፣ መጠጣት፣ መዋሰብ ሊሆን ነው እንግዲ…"
መአዛ:- "ይሄንንማ እንሰሳትም ያደርጉታልኮ"
---
የትግራይ አቡነ ዮሐንስ ናቸው አሉ። አንዱ ወጣት ሊሳለም ይመጣል። ሲመለከቱት አይማርም።

አቡኑ:- "አትማርም?"

ወጣቱ:- "አልማርም"

አቡኑ:- "ለምን አትማርም?"

ወጣቱ:- "ምን በልቼ ልማር…?"

አቡኑ:- "ምን በልተኸ ደደብክ" አሉት ይባላል።

"ዓለማየሁ ገላጋይ ሸገር ካፌ ላይ ስለንባብ ከተናገረው"

ኪነት በዮዳኒ

10 Oct, 15:27


የሜሪ ፈለቀ "ጠበኛ እውነቶች" አምስተኛ ዕትም መጽሐፍ ለንባብ በቃ

ለመጀመሪያ ጊዜ በ2012 ዓ.ም ታትሞ ለንባብ የበቃውና ተወዳጅነትን አትርፎ  በዚያው ዓመት  ብቻ አራት ጊዜ ታትሞ ዝናን ያተረፈው  የደራሲ ሜሪ ፈለቀ "ጠበኛ እውነቶች" መጽሐፍ፤ ከሦስት ዓመት ቆይታ በኋላ አምስተኛ ዕትም መጽሐፍ ለአንባቢያን ቀርቧል። 

"ጠበኛ እውነቶች"  በ4 ክፍሎች የተከፈለ ልብወለድ ሲሆን፤ የተለያየ ማህበራዊና ግላዊ ሕይወትን የሚዳስስ መፅሐፍ ነው።

መጽሐፉ በ252 ገጾች የተቀነበበ ሲሆን፤ በውስጡ የተካተቱ አራቱ ታሪኮች፡-  “ቅዳሴና ቀረርቶ፣ ቀላውጦ ማስመለስ፣ እናቴን ተመኘኋት፣ ምርጫ አልባ ምርጫ” ይሰኛሉ ::

"ጠበኛ እውነቶች"፤ በሁሉም መጻሕፍት መደብሮች እንደሚገኝ ለማወቅ ተችሏል፡፡

ምንጭ አዲስ አድማስ

ኪነት በዮዳኒ

07 Oct, 15:08


ንዝረቱ ያመጣብኝ መርዶ!


የትናንትናው የመሬት መንቀጥቀጥ ነገር ፈጣሪ አተረፈን እንጂ በጣም አስፈሪ ነበረ።

ይህ ባለሞያዎቹ "አዋሽ ፈንታሌ የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ የፈጠረው ሞገድ በመሬት ውስጥ እዚህ ደርሶ ነው" ያሉት አስፈሪ እና ድንገተኛ የመሬት ንዝረት ሲከሰት እኔ ከሚስቴ ጋ ሀያት በሚገኘው የጋራ መኖሪያ ሶስተኛው ወለል ላይ ያለው መኝታቤታችን ውስጥ አልጋችንን በስሜት እያንቀጠቀጥን ነበረ። በድንገት በከባድ ድምፅ ያለንበት ህንፃ ሲናወጥ እና ህዝቤ ወደመሬት ለመውረድ ሲተራመስ የማትተርፍና በፍርስራሽ የምትቀበር የመሰላት ሚስቴ የበለጠ ጥብቅ ብላብኝ በፍርሀት ተውጣ እያየችኝ ኑዛዜ በሚመስል ሁኔታ "እኔ ላንተ ምገባ ሴት አይደለሁም፤ ፍቅራችንን ረግጬ ፍፁም በማይደረግ መልኩ ከ"........ እያለች ሳለ በቅፅበት ሁሉም ነገር  ወደነበረበት ሰላማዊ ሁኔታ ተመለሰ፤ ሚስቴም ምንም እንዳላወራች በሚመስል ወደ ጋለው ጭኗ እያስጠጋችኝ  "ውዴ ፍርሀቱ አቃዠኝ እኮ" ብላኝ ይኸው የመሬቱን ንዝረት ተክቼ እኔ እስካሁን እየተንቀጠቀጥኩ እገኛለሁ ምን ተሻለኝ ጎበዝ

ጫላ