Ethiopian Law™ ⚖ የኢትዮጵያ ሕግ™ @ethiopianlaw_s Channel on Telegram

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

@ethiopianlaw_s


Join us / ይቀላቀሉን👇
#የኢትዮጵያ_ህጎች_እንዲሁም_አዋጆች
#የሕግ_መማሪያ_መፅሀፍት
#የሕግ_ማብራሪያዎች
#በpoll_መልክ_የሚለቀቁ_የመውጫ_ፈተናወች_በብዛት_ይቀርቡበታል
#የታዋቂ_መምህራን_ትምህርቶችን_ያገኛሉ🤝
ለጥያቄ @Ethiopian_law_s_bot
For legal materials @Ethiopianlawlegalmaterialsbot

Ethiopian Law ⚖ የኢትዮጵያ ሕግ (English)

Are you interested in learning more about Ethiopian law and legal practices? Look no further than the 'Ethiopian Law ⚖ የኢትዮጵያ ሕግ' Telegram channel! This channel, with the username @ethiopianlaw_s, is dedicated to providing valuable insights, updates, and discussions on various legal topics relevant to Ethiopia. Whether you are a legal professional, student, or simply someone interested in understanding the legal system in Ethiopia, this channel is the perfect resource for you. Join us to access a wealth of knowledge on Ethiopian laws, legal principles, and case studies. Engage in meaningful conversations with fellow members and stay informed about the latest legal developments in the country. Don't miss out on the opportunity to expand your understanding of Ethiopian law and connect with like-minded individuals. To join the channel, simply click on the link provided and start exploring the world of Ethiopian law today! #የኢትዮጵያ_ህጎች_እንዲሁም_አዋጆች #የሕግ_መማሪያ_መፅሀፍት #የሕግ_ማብራሪያዎች #በpoll_መልክ_የሚለቀቁ_የመውጫ_ፈተናወች_በብዛት_ይቀርቡበታል #የታዋቂ_መምህራን_ትምህርቶችን_ያገኛሉ🤝 For personalized legal materials, don't forget to check out @Ethiopian_law_s_bot. Stay informed, stay engaged, and stay empowered with Ethiopian law!

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

19 Feb, 01:21


#Update

የቀድሞዉ የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ከቀረበባቸው ሁለት ክሶች ነፃ ቢሆኑም የሀዋሳ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቀሪ መዝገቦች አሉባቸው።

የቀድሞው የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ረ/ፕሮፈሰር ፀጋዬ ቱኬ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ከተመሰረተባቸው ሁለት ክሶች ነፃ መባላቸዉን መዘገባችን አይዘነጋም።

ነገርግን የቀድሞ ከንቲባ በሀዋሳ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቀሪ አራት ክሶች እንዳሉባቸዉና ፍርድ ቤቱ ለዉሳኔ ቀነ ቀጠሮ መስጠቱን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለጠበቆች አረጋግጧል።

በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የነበራቸዉን ሁለት የክስ መዝገቦች አስመልክቶ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃ ያደረሱት ጠበቃቸው አቶ ገብረመድህን ተክላይ " አንድ ዓመት ሙሉ ስንከታተል የነበረው የሙስና (ወይንም) ጉቦ የመቀበል ወንጀል እና በሕገወጥ መንገድ የተገኘን ገንዘብ ሕጋዊ አስመስሎ የመጠቀም  ወንጀል " በሚል ቀርቦባቸዉ ከነበረዉን ክስ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሀዋሳና አከባቢዋ ምድብ ችሎት ዛሬ ሙሉ በሙሉ በነፃ አሰናብቷቸዋል።

በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ ፍርድ ቤት ደግሞ ቀሪ የክስ መዝገቦች እንዳሏቸዉ የጠቀሱት ጠበቃቸው አቶ ገብረመድህን ተክላይ እሳቸዉ ግን ጥብቅናቸዉ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ለነበራቸው ሁለቱ መዝገቦች ብቻ መሆኑን ተናግረዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በጊዜ ቀጠሮ ላይ ባሉ መዝገቦች ዙሪያ ጉዳዩን ከያዙ ጠበቆች ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ያደረገዉ ሙከራ ለጊዜዉ አልተሳካም።

መረጃዎችን እንዳገኘን ተጨማሪ ዘገባ የምናደርስ ይሆናል።

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

18 Feb, 06:49


" የሞት ፍርድ ተፈርዶበታል ! "

የ17 አመት ታዳጊ በሆነችው አዶናይት ይሄይስ ላይ የአስገድዶ መድፈርና የግድያ ወንጀል የፈፀመው ተከሳሽ የሞት ፍርድ ተወሰነበት።

የወንጀል ድርጊቱ የተፈፀመው በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ክልል ልዩ ቦታው 15 ሜዳ ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ ነው።

የወንጀሉ ሰለባ የሆነችው የ17 አመት እድሜ ያላት አዶናይት ይሄይስ የተከሳሽ ሚካኤል ሽመልስ የፍቅረኛው ልጅ ነበረች።

መስከረም 19 ቀን 2015 ዓ/ም ከቀኑ 6:00 ሰአት ሲሆን ታዳጊ አዶናይት ይሄይስ መኖሪያ ቤቷ እያለች ተከሳሽ " ለምን አስገድዶ ደፈረኝ ብለሽ ለፖሊስ ክስ መሰረትሽ " በሚል ሰበብ  በቢላዋ የተለያየ የሰውነት ክፍሏን 16 ቦታ በመውጋት ምንም እንዳልተፈጠረ ወደ መኖሪያ ቤቱ በመሄድ ልብሱን በመቀየር ሊሰወር ሲሞክር በአካባቢው ማህበረሰብ እና በወንጀል መከላከል ስራ ላይ በነበሩ የፖሊስ አባላት ሊያዝ ችሏል።

ፖሊስም በተያዘው ተከሳሽ ላይ ባደረገው ምርመራ ከ2005  እስከ 2007 ዓ.ም ባልታወቀ ጊዜና ሰዓት  ታዳጊዋን " ነይ ሱቅ ልላክሽ " እና ሌሎች ማታለያዎችን እየተጠቀመ  በመኖሪያ ቤቱ በተደጋጋሚ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ሲፈፅምባት የቆየ መሆኑንና  በወቅቱ  እድሜዋ በግምት 10 አመቷ እንደነበረ የምርመራ መዝገቡ ያስረዳል፡፡ 

ግለሰቡ የእናቷ የፍቅር ጓደኛ የነበረ ሲሆን ይህንን አፀያፊ ድርጊት ለአንድ ሰው ብትናገሪ እናት እና አባትሽን እገላለሁ እያለ ሲያስፈራት የቆየ ስለመሆኑ የሚዘረዝረው የምርመራ መዝገቡ በተጨማሪም ሟችን " በሞባይል ካሜራ ቪዲዮ ቀርጬሻለሁ በሚዲያ እና በቴሌግራም እለቀዋለሁ " እያለ ለአመታት የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ሲፈፅምባት መቆየቱንና በዚህም ታዳጊዋ ከተከሳሽ በመፀነሷ ፅንሱን እንድታስወርድ ማድረጉን የተከሳሽ የምርመራ መዝገብ ያስረዳል።

ፖሊስ ባከናወነው  ተጨማሪ የምርመራ ስራ ተከሳሽ ሚካኤል ሽመልስ የወንጀል ድርጊቱን መፈፀሙን አምኖ ቦታው ድረስ በመሄድ መርቶ ያሳየ ሲሆን የምርመራ መዝገቡን በማደራጀትና በማጠናቀቅ ለዓቃቤ ህግ  በመላክ ክስ ተመስርቶበታል።

የወንጀል መዝገቡን ሲከታተል የቆየው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 2ኛ ወንጀል ችሎት ታህሳስ 25 ቀን 2017 ዓ/ም በዋለው ችሎት ተከሳሽ ሚካኤል ሽመልስ ጥፋተኛ ሆኖ በመገኘቱ #የሞት_ቅጣት እንዲቀጣ እና የዘወትር ህዝባዊ መብቶቹ እንዲሻሩ ውሳኔ አስተላልፎበታል፡፡

#AddisAbabaPolice

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

16 Feb, 15:14


የድህረ ምረቃ ፕሮግራምች (NGAT) ፈተና መቼ ይሰጣል?

አዲስ የቻናል ጥቆማ ሁለተኛ ደግሪ ለመማር ላሰባችሁ የድህረ ምረቃ ፕሮግራምች (NGAT) መለማመጃ ፈተናዎችን የሚያገኙበት ።@mockexxam


ለወቅታዊ መረጃ ይቀላቀሉን
👉ቴሌግራም ቻናላችን: @mockexxam

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

15 Feb, 12:25


አንጋፋው የህግ ባለሙያ አቶ አበበ ጉታ በህክምና ሲረዱ ቆይተው ከዚህ አለም በሞት ተለዩ::

***

አበበ ጉታ ላለፉት ለበርካታ አስርት አመታት በህግ ሙያ ላይ አገልግሎት የነበራቸው የፌደራል ጠበቆች ማህበር ጠንካራ አባል ነበሩ::
የህግ ባለሙያው አቶ አበበ ጉታ በፌደራል ጠበቆች ማህበር በበርካታ ጉዳዮች ጠንካራ ተሳትፎ የነበራቸው ፤ ሃሳባቸውን በነፃነት የሚገልፁ ፤ ሁለገብ እውቀት የነበራቸው አንጋፋ ባለሙያ ናቸው::

ባደረባቸው ህመም በአዲስ አበባ ከተማ ኮሪያ ሆስፒታል የህክምና ክትትል ስር ቆይተው ዛሬ የካቲት 08 ቀን 2017 ዓ.ም ከዚህ አለም በሞት ተለይተዋል።

የአንጋፋው የህግ ባለሙያ አቶ አበበ ጉታ የቀብር ሥነ-ስርአት ዝግጅት እየተደረገ ሲሆን የተጠናቀቀ መረጃ እንዳገኘን የምናሳውቅ ይሆናል::

#ELA

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

14 Feb, 20:53


የሞት ፍርድ ተፈረደበት!!

የባለቤቱን ህይወት በአሰቃቂ ሁኔታ ያጠፋው ተከሳሽ የሞት ፍርድ ተወሰነበት

ድርጊቱ የተፈፀመው በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 ክልል ልዩ ቦታው አርሴማ ፀበል እየተባለ ከሚጠራው አካባቢ ነው።

ነሀሴ 27 ቀን 2014 ዓ/ም ከቀኑ 5ሰአት ሲሆን ተከሳሽ ሟች አልማዝ እሸቱን ከሌላ ወንድ ጋር ትገናኛለሽ ስልክ ትደዋወያለሽ በሚል ጥርጣሬ ተነሳስቶ ሟች ለግል ጉዳይ ከቤት ለመውጣት ልብስ ለብሳ ጫማ ለማሰር ባጎነበሰችበት በሊጥ መዳመጫ እንጨት ማጅራቷን በመምታት ህይወቷ እንዲያልፍ አድርጓል።

በማስከተል የሟችን አስክሬን በመኖሪያ ቤቱ ውስጥ ባለው መጸዳጃ ቤት ውስጥ በማስገባት የግራ እግሯን ከዳሌዋ እስከ ባቷ ያለውን የሰውነት ክፍሏን በመቁረጥ፣ ስጋዋን በመመልመልና በመክተፍ የመጸዳጃ ሲንክ ውስጥ በመክተት ቀሪውን የሰውነት ክፍሏን ደግሞ መፀዳጃ ቤት ውስጥ ይደብቃል፤ የፖሊስ የምርመራ መዝገብ እንደሚያስረዳው ተከሳሽ ፀጋዬ የአልማዝ መጥፋት ላሳሰባቸው ለቤተሰቦቿና ለስራ ባልደረቦቿ ገዳም እንደሄደች ለማሳመን ሞክሯል።

ሆኖም በመኖሪያ አካባቢው የተለየ ሽታ መከሰቱ ያሳሰባቸው የአካባቢው ነዋሪዎች ለፖሊስ ያቀረቡትን አቤቱታ መነሻ በማድረግና ወደ አካባቢው በመሄድ የሟችን አስክሬን በማንሳት ወንጀል ፈፃሚውን በቁጥጥር ስር ያውለዋል፡፡

ተከሳሹ ላይ የሚቀሩ የምርመራዎችንና ተጨማሪ ማስረጃዎችን በማሟላት የወንጀል ድርጊቱን መፈፀሙን በሰጠው ቃል ከማረጋገጡም ባሻገር የወንጀል አፈፃፀሙን የሚመለከታቸው የሕግ ባለሙያዎችና ታዛቢዎች በተገኙበት መርቶ አሳይቷል።

ጉዳዩን ሲከታተል የቆየው የፌ/ከ/ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 2ኛ ወንጀል ችሎት ነሃሴ 28/2016 ዓ/ም በዋለው ችሎት ተከሳሽ ጥፋተኛ ሆኖ በማግኘቱ በእድሜ ልክ ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኗል።

ምንጭ:- አ.አ ፖሊስ

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

13 Feb, 17:08


#አዲስ_የሰበር_ውሳኔ የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለቤትነትን በሰው ምስክር ለማስረዳት የሚችሉበት የህግ መሠረት ባለመኖሩ ገዥ ቤቱን ገዝቼዋለሁ በማለት የሚያቀርቡት መከራከሪያ በሻጭ ሚስት ላይ ህጋዊ ውጤትን የሚያስከትል አይሆንም ሰ/መ/ቁ 224476 በቀን 05/02/2017ዓም የተወሰነ
==========================
የማይንቀሳቀስ ንብረት ካለዉ ልዩ ባህርይ አንፃር ንብረቱን ከአንድ ወደ ሌላ ሰዉ በሽያጭ ለማስተላለፍ የሚደረግ ዉል በሦስተኛ ወገን ላይ ህጋዊ ዉጤት ያስከትል ዘንድ ዉሉ በህግ አግባብ በሚመለከተዉ አካል ዘንድ ካልተመዘገበ ውሉ ፈራሽ እንደሚሆንና የፍ/ሕ/ቁ አንቀጽ 2878 ን ዋቢ በማድረግ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በሰ/መ/ቁ. 153664 ላይ አስገዳጅ የህግ ትርጉም የሰጠበት ሲሆን በተያዘው ጉዳይም ተጠሪው ይህ አከራካሪ ቤት ከአመልካችዋ ባለቤት ላይ በግዢ ያገኙት መሆናቸውን ከመግለጽ በቀር፤ ቤቱን በግዢ ስለማግኘታቸውና በህግ አግባብ ባለው አካል ዘንድ የግዢና የሽያጭ ውሉ የተመዘገበበት የሰነድ ማስረጃ ተጠሪው በሥር ፍርድ ቤት ያላቀረቡ በመሆኑና የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለቤትነትን በሰው ምስክር ለማስረዳት የሚችሉበት የህግ መሠረት ባለመኖሩ አመልካቹ ቤቱን ገዝቼዋለሁ በማለት የሚያቀርቡት መከራከሪያ በአመልካችዋ ላይ ህጋዊ ውጤትን የሚያስከትል አይሆንም.
https://t.me/Ethiopianlaw_s

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

09 Feb, 08:28


አባት አልባ ልጆችና የህፃናት መብት : የቤተሰብ ህግ አንቀፅ 107 (2) ላይ የተደረገ አጭር ምልከታ

አባትነትና እናትነት የሚታወቀው በመወለድ ሲሆን መወለድም ከጋብቻ እንዲሁም እንደ ባልና ሚስት አብሮ ከመኖር ግንኙነት እንዲሁም ከእነዚህ በህግ እውቅና ከተሰጣቸው ሁለት ግንኙነቶች ውጭ በተፈጠሩ ሌሎች ግንኙነቶች ሊፈጠር ይችላል፡፡ እናትነት ተፈጥሯዊ በሆነ የእርግዝና ሁኔታ የሚታወቅ በመሆኑ አብዛኛው ጊዜ ከመወለድ ጋር በተያያዘ ክርክር ሊያስነሳ የሚችለው የአባትነት ጉዳይ ነው፡፡ ለዛም ነው አባትነት እምነት እናትነት እውነት የሚባለው አባባል ተደጋግሞ የሚሰማው!

በፌዴራል የቤተሰብ ህጉ አንቀፅ 107 (1) ላይ በቤተሰብ ህጉ ስለጉዲፈቻ ልጅ ወይም ልጅነትን ስለመቀበል የተወሰኑት ድንጋጌዎች እንደተጠበቁ ሁነው ከእንደዚህ ያለ ግንኙነት የተወለዱ ልጆች ከእናታቸው በስተቀር ከሌላ ሰው ጋር ማናቸውም ኣይነት ህጋዊ ግንኙነት እንደማይኖራቸው ይደነግጋል፡፡ ይሄም ማለት በቤተሰብ ህጉ አንቀፅ 107 (1) መሰረት እውቅና ከተሰጣቸው ግንኙነቶች ውጭ ማለትም በጋብቻ ወይም ጋብቻ ሳይፈጸም እንደባልና ሚስት አብሮ ከመኖር (Irregular Union) ውጭ በአንድ ወንድና በአንዲት ሴት መካከል በሚደረጉ ሌሎች ግንኙነቶች የተወለዱ ልጆች ለአብነት ያህል ወንዱና ሴቷ ምንም አይነት የትዳር ግንኙነት ሳይኖራቸው በተፈጠረ የአንድ ቀን የግብረ ሥጋ ግንኙነት ምክንያት የተወለዱ ልጆች ወላጅ አባት (Biological Father) ቢኖራቸውም ህጋዊ አባት ግን ሊኖራቸው እንደማይችል የሚያመላክት ነው፡፡ የክልል የቤተሰብ ህጎችም ተመሳሳይ ድንጋጌን የያዙ በመሆናቸው ተመሳሳይ አቋም ያላቸው ናቸው፡፡

ይሄም ማለት አንድ ልጅ ወላጅ አባት ቢኖረውም ይሄ ተፈጥራዊ አባቱ (Biological Father) ግን በህግ ዓይን እንደአባት ስለማይቆጠር ወላጅ አባት ለልጁ ምንም አይነት ህጋዊ ግዴታዎች የሉበትም፤ ልጁም ከወላጅ አባቱ የሚጠይቀው ምንም አይነት መብት የለውም፡፡ ለምሳሌ ወላጅ አባት ልጁን ተከንከባክቦ የማሳደግና ቀለብ የመስጠት ግዴታ አይኖርበትም፡፡ ልጁም በወላጅ አባቱ ስም የመጠራት፣ ውርስ የመውረስ ፣ ቀለብ የመጠየቅ ወ.ዘ.ተ መብት አይኖረውም፡፡ ለወላጅ ኣባቱም ቀለብ የመስጠት ግዴታ አይኖርበትም፡፡ በቤተሰብ ሕጉ አንቀጽ 107/2/ ከጋብቻ እና ከባልና ሚስት አብሮ ከመኖር ውጭ ባለ ግንኙነት የተወለደ ልጅ ከእናቱ ጋር ካልሆነ በስተቀር ከሌላ ሰው ጋር ማናቸውም አይነት ግንኙነት አይኖረውም ተብሎ በመደንገጉ ይሄ ልጅ ጉዲፈቻ አድርጎ የሚቀበለው አባት ካላገኘ ወይም አባትነትን ማወቂያ መንገድ በሆነው ልጅነትን ስለመቀበል በተቀመጡት ድንጋጌዎች መሠረት ልጄ ነው ብሎ የሚቀበለው ሰው ካላገኘ በስተቀር ከሌላ ሰው ጋር ማናቸውም ዓይነት ሕጋዊ ግንኙነት እንዳይኖረው ስላደረገው ልጁ ፈፅሞ አባት ሊኖረው አይችልም፡፡ በሌላ አባባል ይሄን ልጅ በተመለከተ ህጋዊ አባት እንጂ ባዮሎጅካል አባት መሆን ልጁን ከአባቱ እንዲሁም አባትየውን ከልጁ ጋር በመብት እና በግዴታ ሊያስተሳስር የማይችል በሕግ ፊት ትርጉም የሌለው ግንኙነት ነው፡፡

በመሆኑም ድንጋጌው “ስለጉድፈቻና ልጅነትን ስለመቀበል የተወሰኑ ድንጋጌዎች እንደተጠበቁ ሆነው” በሚለው አገላለጹ ምክንያት በቤተሰብ ህጉ አባትነትንና ልጅነትን ስለማረጋገጥ የተደነገጉ ሌሎች ድንጋጌዎች ተፈፃሚ ስለማይሆኑ የልጁ ምርጫ በጉዲፈቻ አባት ማግኘትና ልጄነህ ብሎ የሚቀበለው ሰው ማግኘት ወይም አባት አልባ ልጅ ሆኖ መኖር ነው፡፡ ይሄም ማለት ህጋዊ እውቅና ባልተሰጠው ግንኙነት የተወለደ ልጅ አባትነትን ስለማወቅና ልጅነትን ስለማረጋገጥ በቤተሰብ ሕጉ ከአንቀጽ 123 - 162 በተደነገጉት ድንጋጌዎች መሰረት የልጅነት ሁኔታ መኖሩን በማስረዳት፣ በምስክር ወይም በሌላ ማስረጃ ልጅነትን በማረጋገጥ እንዲሁም የአባትነት ማወቂያ መንገድ ከሆኑት አንዱ በሆነው በፍርድ ቤት ውሳኔ አባትነቱ እንዲታወቅለት በማድረግ አባት ማግኝት የሚችልበት መንገድ የለም፡፡

በተጨማሪም አንቀፅ 107 (2) “ከእናታቸው በስተቀር ከሌላ ሰው ጋር ማናቸውም ኣይነት ህጋዊ ግንኙነት አይኖራቸውም” የሚለው አባባል በዚህ ግንኙነት የተወለዱ ልጆች ካደጉም በኋላ ከሌሎች ሰዎች ጋር ማናቸውንም አይነት ህጋዊ ድርጊቶችን ለምሳሌ እንደ ውል መዋዋል፣ መውረስ፣ ቀለብ ማግኝነት የመሳሰሉ ሕጋዊ ግንኙነትን መፈጠር አይችሉም ወደሚል ወደተለጠጠ ትርጓሜ የሚወሰድን ነው፡፡ ይሁን እንጂ በድንጋጌው የተገለፀው ግንኙነት ማናቸውም ዓይነት የሕግ ግንኙነት ማለት ሳይሆን ከአባትነት እና ከልጅነት ግንኙነት አኳያ ያለን ግንኙነት የሚመለከት ብቻ ነው ብሎ በጠባቡ መተርጎሙ አሳማኝ ይመስላል ምክንያቱም ድንጋጌው ቤተሰብ በመመሥረት ሂደት ስላሉ ግንኙነቶች በሚገልፀው የሕጉ ክፍል የሚገኝ በመሆኑ ነው፡፡ ይሁን እንጂ አንቀጹን አጥብበን ብንተረጉመውም በህግ እውቅና ካልተሰጠው ግንኙነት የተወለዱ ልጆች አባታቸውን ማወቅ፣ ልጅነታቸውን ማረጋገጥ የሚባሉ ሕጋዊ ግንኙነቶች መፍጠርና በነዚህ ግንኙነቶችም የሚገኙ መብቶችን እና ግዴታዎችን ማቋቋም አይችሉም ወደሚል ድምዳሜ ያደርሰናል፡፡

በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገ መንግሥት ላይ ለህፃናት ከተደነገጉላቸው መሠረታዊ መብቶች አንዱ ህፃናት እናት አባታቸውን የማወቅና የእነሱንም ክትትልና እንክብካቤ ማግኘት ነው፡፡ ይሁን እንጂ በፌዴራሉም ሆነ በክልል የቤተሰብ ሕጎች ላይ ሁሉም ልጆች እናታቸውን እንጂ አባታቸውን ለማወቅ አልታደሉም፡፡ አባታቸውን የማወቅ መብት የተሰጣቸው በህግ ፊት እውቅና በተሰጠው ግንኙነት የተወለዱ ልጆች ብቻ ናቸው፡፡ በሕገ መንግሥቱ መሰረት ከጋብቻ ውጭ የተወለዱ ልጆች እና በጋብቻ በተወለዱ ልጆች እኩል መብት እንዳላቸው እንዲሁም ማንኛውም ህፃን ወላጆቹን የማወቅና የእነሱንም እንክብካቤ የማግኘት መብት ያለው መሆኑን በግልፅ ተደንግጎ ይገኛል (36(4) እና 36 (1) (ሐ) ይመለከቷል) ፡፡

በመሆኑም የቤተሰብ ሕጉ አንቀጽ 107/2/ ከጋብቻ እንዲሁም እንደ ባልና ሚስት አብሮ ከመኖር ግንኙነት ውጭ የተወለዱ ልጆች ከእናታቸው በስተቀር ወላጅ አባታቸውን (Biological Father) ጨምሮ ከሌሎች ሰዎች ጋር ምንም ዓይነት ሕጋዊ ግንኙነት የላቸውም በማለት መደንገጉ ከፍ ሲል በሕገ መንግሥቱ ከጋብቻም ሆነ ከጋብቻ ውጭ በሆነ መንገድ በተወለዱ ልጆች መካከል ልዩነት አይደረግም እንዲሁም ህፃናት ወላጆቻቸውን የማወቅና የእነሱን እንክብካቤ የማግኘት መብት አላቸው ከሚሉት ድንጋጌዎች ጋር የሚጣረስ በመሆኑ የቤተሰብ ሕጉ አንቀጽ 107/2/ ህጋዊ እውቅና ከተሰጣቸው ግንኙነት ውጭ የሚወለዱ ልጆችን በህግ ፊት አባት አልባ የሚያደርግና እነዚህ ልጆች በህገ-መንግስት የተሰጣቸውን የህፃናት መብት የሚጥስና በህግ አውጭው አስፈላጊው መሻሻል ሊደረግበት የሚገባ ድንጋጌ ስለመሆኑ የጸሀፊው እምነት ነው፡፡
#ByEthiolegaltech
Join🔥
@Ethiopianlaw_s

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

08 Feb, 10:51


ዶናልድ ትራምፕ የአፍሪካ መሪዎች ሰው መሆናቸውን እጠራጠራለሁ አሉ‼️

ከ50 ዓመታት የአህጉሪቷ የነጻነት ጉዞ በኋላ፣ ለህዝባችው አስፈላጊውን መሠረተ ልማት ካላሟላችው ሰው ነን ብላችው ታስባላችው?


በወርቅ፣ በአልማዝ፣ በነዳጅ፣ በዩራኒየም፣ በብረት፣ በማዕድን፣ በብር፣ በማግኒዥየም፣ በነሐስ፣ በጋዝ የተፈጥሮ ሃብቶቻችው ላይ ተቀምጣችው፣ ህዝባችው በረሃብ፣ በትምህርት አለመዳረስ፣ በጤና አገልግሎት እጦት፣ ቢሞት፣ ሰው ነን ብላችው ታምናላችው?

በስልጣን ላይ ቆይታችው፣የራሳችሁን  ዜጎች ለመግደል ከውጭ የጦር መሣሪያዎችን ስታስገቡ፣ ሰው ነን ብላችው ታስባላችው?

የገዛ ዜጎቻችሁን እንደውሻ ስታንገላቱና ስትገድሉ፣ ማን ዜጎቻችሁን እንዲያከብር  ትጠብቃላችው?

በራሳችው  አገር ላይ ቀማኛና ሌባ በመሆናችው ፣ የሃገራችሁን  ሀብቶች ሁሉ በመስረቅ፣ አብዛኞቹ ዜጋዎቻችው በስደትና በድህነት ውስጥ እንዲያልፉ ስታረጉ፣ የሰው ልጆ ነን ብላችው ታስባላችው?

ትራምፕ ይሄን የተናገሩት ሰሞኑን በዋሽንግተን ዋይት ሀውስ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ነው።
@Ethiopianlaw_s
@Ethiopianlaw_s

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

07 Feb, 19:23


#ሌሊት_በህግ_ቋንቋ!
በስንት ሰዓት ላይ ሲፈፀም ነው ወንጀል በሌሊት ተፈፀመ የሚባለው ?
🚥 🚥 🚥 🚥 🚥 🚥 🚥 🚥 🚥
እንደሚታወቀው በኢፌድሪ የወንጀል ህግ አንቀፅ 84(1) ስር ከተደነገጉት የወንጀል ቅጣትን ከሚያከብዱ ጠቅላላ ምክንያቶች መካከል በንዑስ ፈደል (ሐ) ላይ የተገለፀው ወንጀልን በሌሊት መፈፀም አንዱ ነው፡፡አንዲሁም አንድን የስርቆት ወንጀል ከባድ ስርቆት ከሚያሰኘው መካከል አንዱ በወንጅል ህጋችን አንቀፅ 669(3)(ለ) ላይ በሌሊት መፈፀሙ ሲሆን በሌሎችም የወንጀል ህግ ልዩ ክፍል በሌሊት ወንጀልን መፈፀም ወንጀሉን ከባድ እንደሚያደርጉት ተደንገጎ ይገኛል፡፡ታዲያ ይህ ሌሊት የሚባለው ስንት ሰዓት ሲሆን ነው? የሚለውን በምናይበት ጊዜ በእንግሊዝኛው ‹‹night›› የሚለው ብላክስ ሎው የህግ መዝገበ ቃላት the time from sunset to sunrise በግርድፉ ፀሀይ ከምትጠልቅበት እስከምትወጣበት ያለው ጊዜ ነው በማለት ይገልፀዋል፡፡በኢትዮጵያ ቋንቋዎች ጥናትና ምርምር ማዕከል የተዘጋጀው የአማርኛ መዝገባ ቃላትም ‹‹ሌሊት›› የሚለውን ቃል ከብላክስ ሎው መዝገባ ቃላት ጋር በተመሳሳይ መንገድ ይተረጉመዋል፡፡ይህም ማለት ከቀኑ 12፡00 ሰዓት እስከ ሌሊቱ 12፡00 ሰዓት ያለው ጊዜ ማለት ነው በመሆኑም አንድ ሰው ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ላይ ወንጀል ቢፈፅም ወንጀሉን በሌሊት ፈፅሞታል ተብሎ ቅጣቱ ሊከብድበት ይችላል ማለት ነው፡፡ነገር ግን የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በሰ/መ/ቁ 220926 ባልታተመ ውሳኔው የወንጀል ድርጊቱ ከምሽቱ 5፡00 ሰዓት ላይ የተፈፀመ ከሆነ በሌሊት ባለመሆኑ በወ/ህ/ቁ 84(1)(ሐ) መሰረት ቅጣት ማክበጃ ምክንያት ሊሆን አይገባም፡፡ሲል ትርጉም ሰጥቶበታል፡፡

ምንጭ : Ethiopian lawyers association Facebook group

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

07 Feb, 09:30


#USA

አሜሪካ በአስገድዶ መድፈር ወንጀል ጥፋተኛ የተባለ ዜጋዋን አፍና ገደለች።

አሜሪካዊው የ52 ዓመቱ ድሜትሪስ ፍሬዘር በአስገድዶ መድፈር እና ግድያ ወንጀሎች ጥፋተኛ ሆኖ ተገኝቷል።

ግለሰቡ በአላባማ በርሚንግሀም ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ፓውሊን ብራውን የተባለች የ2 ልጆች እናትን በመኖሪያ ቤቷ ገብቶ አስገድዶ ከደፈረ በኋላ #እንደገደላት ተገልጿል።

በሌላ ጊዜ የ14 ታዳጊ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል መፈጸሙ መረጋገጡን ተከትሎ በተደራራቢ ወንጀሎች ክስ ተመስርቶበት ነበር።

ይህንንም ተከትሎ ተከሳሽ ድሚትሪስ ፍሬዘር በሞት ፍርድ እንዲቀጣ የተላለፈበት ሲሆን የፍርድ ሂደቱ የተካሄደው የሞት ፍርድ የማይተላለፍበት ሚቺጋን ግዛት ውስጥ በመሆኑ ፍርዱ ወደ እድሜ ልክ እስራት ተቀይሮለት ነበር።

በአላባማ ወንጀል መፈጸሙ በፍርድ ቤት መረጋገጡን ተከትሎ ወደ አላባማ እስር ቤት ተላልፎ ሊሰጥ ችሏል።

አላባማ ግዛት የሞት ፍርድ የተላለፈባቸው ፍርደኞችን አየር አጥሯቸው እንዲሞቱ የሚያደርግ ህግ ስላላት ይህም ወንጀለኛ በናይትሮጅን ጋዝ ታፍኖ ህይወቱ እንዲያልፍ መደረጉን ሮይተርስን ዋቢ በማድረግ አል አይን ኒውስ ዘግቧል።

#tikvahethiopia

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

06 Feb, 18:35


በአጠቃላይ አቃቢ ህግ በእኔ ላይ መስርቶ ባቀረበው ክስ ላይ የተገለጸውን ወንጀል አልፈጸምኩም” - አቶ ክርስቲያን ታደለ

እነ አቶ ክርስቲያን ታደለ ዛሬ ችሎት ቀርበው የእምነት ክህደት ቃል መስጠታቸውን ጉዳዩን ከሚከታተሉ ሰዎችና ቃላቸውን ካቀረበበት ሰነድ መረዳት ትችሏል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተመለከተው አቶ ክርስቲያን የእምነት ክህደት ቃል የሰጡበት ሰነድ፣ “በአጠቃላይ አቃቢ ህግ በእኔ ላይ መስርቶ ባቀረበው ክስ ላይ የተገለጸውን ወንጀል አልፈጸምኩም። ጥፋተኛም አይደለሁም” ይላል።

አቶ ክርስቲያን በሰጡት የእምነት ክህደት ቃል ምን አሉ?

“ለ550 ቀናትም በግፍና ጭካኔ እገታ ውስጥ የምገኘው ለአንዲት ደቂቃ እንኳን በጥፋተኝነት የሚያስቀጣ አንዳችም የወንጀል ድርጊት የሚያቋቁም የህግ መተላለፍ ስለፈጸምኩ አይደለም። የአማራ ሕዝብ የሚያነሳቸውን የህልውና ጥያቄዎች በይፋ በማቅረቤ፣ በሕዝቤ የሚደርሰውን ግፍ፣ በደል በማስረጃ በመሞገቴ፣ የገዢውን ፓርቲ አፈናና የመንግስት አሰራሮችንና አመራሮችን ብልሹነትና ዘረፋ በመታገሌ ነው ” ብለዋል።

“ ተደጋጋሚ የአመራር ብልሹነት ባሳዩ አካላትም የወንጀልና የፍትሃብሔር ተጠያቂነት እንዲረጋገጥ ክስ እንዲመሰረት ፍትህ ሚኒስቴር አዝዥለው ” የሚሉና ሌሎች ድርጊቶችን በአደባባይ እንደታገሉ ገልጸዋል።

“ ጠቅላይ ሚኒስትሩን ጨምሮ ሌሎች የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች በአሰራራቸው የፋይናንስ ገልጸኝነትና ህጋዊነት እንዲከተሉና እንዲረጋገጡ እንዲሁም ኦዲት ለመደረግ ፈቃደኝነታቸውን እንዲያረጋግጡ ጠይቄከለሁ ” ነው ያሉት።

እነዚህን ጥያቄዎች እንዳልጠይቅ አንዳንድ አመራሮች ለማግባባት እንደሞከሩ ገልጸው፣ “ አንዳንዶቹም ሊገድሉኝ፣ ሊያስሩኝና አንዳች ነገር ሊያደርሱብኝ እንደሚችሉ ጭምር ነግረውኛል፤ መልዕክትም አድርሰውኛል ” ብለዋል።

“ አንዳች ወንጀል አልፈጸምኩም ” ያሉት ክርስቲያን፣ “ ይህን በተመለከተ ከክሱ ይዘት ብቻ ሳይሆን በራሴ መንገድ ይህን ክስ ተዘጋጅቶ እንዲቀርብብኝ ካደረገው አካል ዘንድም አረጋግጫለሁ ” ሲሉ አስረድተዋል።

“ እኔ አማራ የሆንኩት አማራ ሆኘ ስለተወለድኩ ነው። የከማራ ብሔርተኝነት አቀንቃኝ የሆንኩትም ፈቅጄ፣ መርጨና ወድጄ ነው። በየትኛውም ቦታና ሁኔታ ለአማራነቴ ጥብቅና መቆምም ተፈጥሯዊ ግዴታዬ ነው ” ብለዋል።

“ አማራዊ እሴቶታችን ለኛ ቅዱስ ነው ” ብለው፣ “ ይሁንና አቃቢ ህግ ባቀረበው የፓለቲካ ውንጀላ ሰነድ ላይ፣ ‘አማራ ርስቱን ተቀምቷል፤ አገሪቱ በአማራ እሴት መመራት አለባት’ የሚል የርዕዮተዓለማዊ አቋም መያዛችን ክስ ሆኖ ቀርቧል” ብለዋል።

ይህ የአቃቢ ህግ ክስ ግን መንግስት ከአማራና ከአማራነት የጸዳች ኢትዮጵያ ነው ወይ የሚፈልገው ? የሚል ሙግት ያስነሳል። ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት ከአማራና ከአማራነት በስተቀር እንዲሆኑ የሚደነግግ ህግስ አለ ወይ? ” ሲሉ ጠይቀዋል።

በሌላ በኩል “ በአቃቢ ህግ ክስ ላይ ‘ቋሪትና ደጋ ዳሞት ላሉ የሽብር ቡድን አስተባባዎች በስልክ ሐምሌ 25/2015 ዓ/ም በመደወል መከላከያን ማጥቃት ህገ መንግስታዊ መብት መሆኑን በማሳወቅ እንዲመቱ ትዕዛዝ ሰጥቷል’ ” ማለቱን ጠቅሰል።

“ አቃቢ ህግ ለዚህ ክስ አስረጅ የሆነ አንዳችም ማስረጃ አላቀረበም ” ብለዋል።

(ሙሉ የእምነት ቃላቸውን የሰጡበት ሰነድ ከታች ተያይዟል)

#TikvahEthiopia

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

05 Feb, 13:28


በእስር ላይ የሚገኘው ጆን ዳንኤል የሚባለው ድምጻዊና ቲክቶከር፣ በማረሚያ ቤት ውስጥ ከሌሎች እስረኞች ጋር በስልክ የተነሳቸው ፎቶ ግራፎች በማህበራዊ ሚዲያ መሠራጨቱን ተከትሎ፣ የማረሚያ ፖሊስ ፎቶውን የተነሱበትና የተለቀቀበትን ስልክ አግኝቻለሁ፣ በእስረኞቹ ላይም እርምጃ እወስዳለሁ ብሏል።

የፌዴራል ማረሚያ ቤት "ቅጣት የሚሰጠውን" መመሪያ ዛሬ እንደገና ለሕዝብ ይፋ አድርጓል። ለግንዛቤ እንዲረዳ ይኸው፦

በፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን የሕግ ታራሚዎችና የቀጠሮ እስረኞች በተሻሻለ የሥነ ስርዓት ጥፋት ቅጣት አፈፃፀም መመሪያ ቁጥር 5/2009 በክፍል 02 አንቀጽ 11 ቁጥር 35 የተከለከሉ ነገሮችን ማለትም (ጫት፣ ተቀጣጣይ ነገሮች፣ ስልክ፣ ሲም ካርድ ፣ ሲጃራ፣ ጋንጃ፣ ቡሪ፣ አንጋዳ፣ አልኮል መጠጥና …ወዘተ) ወደ ማረሚያ ቤትና ማረፊያ ማዕከል ለማስገባት መሞከር ወይም የገባውን መጠቀም የሚያስከትላቸው የቅጣት አይነት፡-
ለ4 ወር እንዳይጎበኝ መከልከል ወይም
ለ3 ወር ለብቻ ለይቶ ማሰር ወይም
ከ5 ወር ከ1 ቀን አስከ 6 ወር ለሚደርስ ጊዜ በማረሚያ ቤት ሆኖ ሥራ በመስራት ከሚያገኘው ገቢ 1/3ኛውን በመቀነስ ሥራ ማሰራት ወይም ማግኘት ከሚገባው የአመክሮ እስራት 3/4ኛውን መከልከል፡፡

🔴ቁጥር 36 የተከለከሉ ነገሮች (አደንዛዥ እጽ፣ ጦር መሳሪያ እና ተቀጣጣይ ነገሮች ወደ ማረሚያ ቤት እና ማረፊያ ማዕከል ለማስገባት መሞከር ወይም አስገብቶ መገኘት ወይም ሌሎች እንዲያስገቡ መተባበር፣ ወይም ጉዳት ማድረስ (በወንጀል ያለው ተጠያቂነት እንደተጠበቀ ሆኖ) የሚያስከትለው የቅጣት አይነት፡-
🔴 ለ4 ወር እንዳይጎበኝ መከልከል ወይም ፣
🔴 ለ3 ወር ለብቻ ተለይቶ መታሰር ወይም፣
🔴ከ5 ወር ከ1 ቀን እስከ 6 ወር ለሚደርስ ጊዜ ከሚያገኘው ገቢ 1/3ኛውን በመቀነስ ሥራ ማሰራት ወይም ማግኘት ከሚገባው የአመክሮ እስራት 3/4ኛውን መከልከል፡፡

🔵ቁጥር 37 የተከለከሉ ነገሮች (ሀሺሽ፣ ፈንጂ፣ እና ተቀጣጣይ ነገሮች…ወዘተ) ወደ ማረሚያ ቤት እና ማረፊያ ማዕከል ለማስገባት መሞከር ወይም ማስገባት ወይም የገባውን መጠቀም የወንጀል ተጠያቂነት እንደተጠበቀ ሆኖ የሚያስከትለው የቅጣት አይነት፡-

🔵ለ4 ወር እንዳይጎበኝ መከልከል ወይም ፣
🔵ለ3 ወር ለብቻ ለይቶ ማሰር ወይም፣
🔵ከ5 ወር ከ1 ቀን እስከ 6 ወር ለሚደርስ ጊዜ በማረሚያ ቤት ሆኖ ከሚሰራው እና ከሚያገኘው ገቢ 1/3ኛውን በመቀነስ ሥራ ማሰራት ወይም ማግኘት ከሚገባው የአመክሮ እስራት 3/4ኛውን መከልከል፣ የሚሉት ይገኙበታል፡፡(ዘ-ሐበሻ መረጃ)

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

03 Feb, 16:25


🏆Haramaya University College of Law has won the 2025 National Champion of the Philip C. Jessup International Law Moot Court Competition.


The team, comprising Abdurazak Nebi, Ayantu Adunga, Esayas Serbessa, and Mahder Berhanu, secured the championship through a cumulative assessment of their oral pleadings and written memorials.
This victory grants them the honor of representing Ethiopia at the 2025 Jessup International Rounds in Washington, D.C., USA.

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

03 Feb, 16:09


4 ወር ተፈረደባቸው‼️
በ3ቱ በአምቦ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች የተሰጠ ፍርድ
በጥምቀት ሰሞን በቅዱስ ሚካኤል ታቦት
እያሾፉ እና እየቀለዱ በቲክ ቶክ ቪዲዮ ለቀው የነበሩት እነዚህ ሶስት ተማሪዎች:
1ኛ. ተማሪ ገመቹ ምትኩ
2ኛ. ተማሪ ካሳን አድቬንቸር
3ኛ. ተማሪ ጋዲሳ ኢቲና
ዛሬ በአምቦ ዳዳቻ ወረዳ ፍርድ ቤት ቀርበው የነበረ ሲሆን እያንዳንዳቸው በ4 ወር እስር እንዲቀጡ ተወስኗል።
[አዩዘሀበሻ]

@Ethiopianlaw_s
@Ethiopianlaw_s

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

03 Feb, 15:45


Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ pinned «♨️Do you want to get ? 💥DIFFERENT UNIVERSITY SCHOOL OF LAW EXAM PAPERS FROM 2ND YEAR UP TO 5TH YEAR 💥ALMOST ALL LAW SCHOOL EXIT EXAMS Join👇👇👇 @Lawschoolexampaper @Lawschoolexampaper @Lawschoolexampaper»

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

03 Feb, 07:36


♨️Do you want to get ?

💥DIFFERENT UNIVERSITY SCHOOL OF LAW EXAM PAPERS FROM 2ND YEAR UP TO 5TH YEAR
💥ALMOST ALL LAW SCHOOL EXIT EXAMS

Join👇👇👇
@Lawschoolexampaper
@Lawschoolexampaper
@Lawschoolexampaper

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

31 Jan, 10:53


#ፀደቀ‼️
ከፍተኛ የትምህርት አቀባበል ያላቸው ተማሪዎች ወደ ቀጣይ ክፍል መሸጋገር የሚያሰችል አዋጅ ፀደቀ‼️
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 17ኛ መደበኛ ስብሰባው ከፍተኛ የትምህርት አቀባበል ያላቸው ተማሪዎች የሚገኙበትን የትምህርት ክፍል ሳያጠናቅቁ ወደ ቀጣዩ ክፍል መሸጋገር የሚያስችል የአጠቃላይ ትምህርት ረቂቅ አዋጅን አፅድቋል።

የአዋጁ መፅደቅ ብቁ የትምህርት ባለሙያ፣ አመራርና አደረጃጀት ለመፍጠር የሚያስችል ነው ተብሏል።

የሰው ሀብት ልማት፣ ሥራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር) ለምክርቤት ባቀረቡት ሪፖርት እንደገለፁት፣ የአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍን መሠረት አድርገው ከተቀረጹ መርሐግብሮችና ዕቅዶች አንጻር ትምህርትን ለመምራት የሚያስችል የሕግ ማዕቀፍ ባለመኖሩ ዘርፉን በሚፈለገው ደረጃ አላደገም።

ይህንን መሰረታዊ ችግር ለመፍታት አዲስ አዋጅ ማውጣት አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል ብለዋል። አዋጁ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥና በዘርፉ እያጋጠሙ ያሉ ተግዳሮቶችን ለመቅረፍ የሚደረገውን ሪፎርም ያግዛል።
በአዋጁ ከፍተኛ የትምህርት አቀባበል ያላቸው ተማሪዎች የሚገኙበትን የትምህርት ክፍል ሳያጠናቅቁ ወደ ቀጣይ ክፍል መሸጋገር እንዲችሉ ተደርጎ መዘጋጀቱንም ተናግረዋል።

አዋጁ ብቁ የትምህርት ባለሙያ፣ አመራርና አደረጃጀት ለመፍጠር ይረዳል ያሉት ሰብሳቢው፣ በመላው ሀገሪቱ ሁሉም የአጠቃላይ ትምህርት ተቋማት የሚከናወነው የመማር ማስተማር ሂደት የሀገሪቱን እሴት ጠብቆ እንዲካሄድ ግልጽ አቅጣጫ የሚሰጥ ስለመሆኑ አስረድተዋል።

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

31 Jan, 05:36


የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ውስጥ ከተደራጀ የክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በውክልና የማየት ስልጣን የሌለው ስለመሆኑ

ሰ/መ/ቁ፡ 204107

ጥቅምት 30/2014 ዓ/ም

ለሰበር የቀረበው ጉዳይ በአጭሩ ተጠሪ ከአመልካች ጋር ባደረኩት ውል ጠጠር ለማቅረብ ግዴታ ቢገባም በሚፈለገው ጥራትና መጠን ጠጠሩን ካለማቅረቡ በተጨማሪ ስራውን አቋርጦ የሄደ በመሆኑ ኪሳራ የደረሰብኝ በመሆኑ ይህንን ገንዘብ እንዲከፈልኝ ይወሰንልኝ በማለት በስር ፍርድ ቤት ክስ አቅርቧል፡፡ አመልካች በበኩሉ የጥራት ችግር ያለበት ጠጠር አላቀረብኩም፣ ጠጠሩም በገባነው ውል መሰረት ልክ የቀረበ ነው፣ ስራውን ያቆምነው በተጠሪ ጥፋት ነው፣ የአኙዋክ ብሄረሰብ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤትም ጉዳዩን የማየት ስልጣን የለውም በማለት ለስር ፍ/ቤት ምላሽ ሰጥቷል፡፡

የሠበር ችሎቱም የጋምቤላ ክልል የአኙዋክ ብሄረሰብ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት ጉዳዩን የማየት የስረ-ነገር ስልጣን አለው ወይንስ የለውም ? የሚለውን በጭብጥነት ይዞ ጉዳዩን መርምሯል፡፡

አመልካች (የስራ ተቋራጭ) ነዋሪነቱ አዲስ አበባ ከመሆኑም በላይ ተጠሪም በቻይና አገር የተቋቋመ ደንበር ተሻጋሪ የኮንስትራክሽን ድርጅት ነው፡፡ ይህ በመሆኑ የፌዴራል ፍርድ ቤቶችን ለመወሰን በወጣው አዋጅ ቁጥር 25/88 አንቀፅ 5(2 እና 4) መሰረት ጉዳዩን የማየት ስልጣን የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ያደርገዋል፡፡ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህገ-መንግስት አንቀፅ 80(2 እና 4) የክልል ከፍተኛ እና ጠቅላይ ፍርድ ቤቶች በቅደም ተከተል የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤትን እና የፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤትን ስልጣን በውክልና የማየት ስልጣን እንዳላቸው የሚደነግግ ሲሆን ይሄው ህገ-መንግስት በአንቀፅ 78(2) ላይ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አስፈላጊ ሁኖ ሲያገኘው የፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤትንም ሆነ የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤቶችን በሀገሪቱ በሙሉ ወይም በከፊል ማደራጀት እንደሚችል ይደነግጋል፡፡ በዚህም መሰረት የፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤትን በተወሰኑ ክልሎች ለማደራጀት አዋጅ ቁጥር 322/95 የወጣ ሲሆን በዚህ አዋጅ መሰረት የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ከተደራጀባቸው ክልሎች ውስጥ አንዱ የጋምቤላ ክልል ስለመሆኑ በአዋጁ አንቀፅ 2 ላይ ከተመለከተው ድንጋጌ መገንዘብ ይቻላል፡፡ ይህም የሚያሳየው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤትን ስልጣንን የጋምቤላ ክልል ጠቅላይ ፍ/ቤት በውክልና የማየት ስልጣን የሌለው መሆኑን ነው፡፡ በሌላ በኩል ምንም እንኳን የክልሉ ከፍተኛ ፍ/ቤት የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ስልጣንን በውክልና ለማየት ያለው ስልጣን ያልተነሳ ቢሆንም ለዚህ ክርክር መነሻ የሆነው ጉዳይ ከብር 500 ሺህ ብር በላይ በመሆኑ ክርክሩ በተጀመረበት ወቅት በስራ ላይ በነበረው አዋጅ ቁጥር 25/88 አንቀፅ 14 መሰረት ከፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ስልጣን በላይ በመሆኑ የክልሉ ከፍተኛ ፍ/ቤት ጉዳዩን በውክልና የማየት ስልጣን የለውም፡፡ አንድ ፍ/ቤት የቀረበውን ክስ ለማየት የተከራካሪ ወገኖችን ማንነት እና አድራሻ መሰረት በማድረግ የስረ-ነገር ስልጣን ያለው ስለመሆን አለመሆኑ በቅድሚያ ሊመረምር የሚገባው ስለመሆኑም የፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ 231(1/ለ) ያስገነዝባል፡፡ በመሆኑም ከፍተኛ ፍ/ቤቱ በሌለው ስልጣን ላይ የሰጠው ውሳኔ በመሆኑ መሰረታዊ የህግ ስህተት የተፈፀመበት ነው በማለት ሰበር ሰሚ ችሎቱ አስገዳጅ ውሳኔ ሰጥቷል፡፡
#Legaltech
Join👇
@Ethiopianlaw_s

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

30 Jan, 11:42


አቶ ብርሃኑ አዴሎ ለኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ኮሚሽነርነት  ዕጩ ሆነው ቀረቡ።

በቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ ዘመነ መንግስት የሚኒስትሮች ካቢኔ ሚኒስትር የነበሩት አቶ ብርሃኑ አዴሎ ገብረማርያም ለኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ኮሚሽነርነት ለመሰየም ዛሬ ጥር 22 ቀን 2017 ዓ/ም  ፓርላማ ቀርበዋል።

ሌሎች አራት ዕጩዎችም መቅረባቸውን ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል።

አቶ ብርሃኑ ከዚህ ቀደም በተለያዩ መንግሥታዊ ኃላፊነቶች ላይ የሠሩት ሲሆን የመጨረሻ መንግሥታዊ ኃላፊነታቸው የኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ጽህፈት ቤት ዋና ዳይሬክተርነት ነበር።

ከኃላፊነታቸው የተነሱት " በቀረበባቸው ቅሬታ " መሆኑን ሪፖርተር ጋዜጣ ከ10 ዓመታት በፊት ዘግቧል።

" ከሠራተኞች እና ከተቋሙ ደንበኞች ቅሬታዎች ይቀርቡባቸው እንደነበር " ጋዜጣው በወቅቱ ዘግቧል።

የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ አቶ ብርሃኑን ከዚህ ኃላፊነት ማንሳታቸውም የሪፖርተር ዘገባ ያሳያል።

አቶ ብርሃኑ የአዕምሯዊ ንብረት ጽህፈት ቤት ዋና ዳይሬከተር ሆነው ከመሾማቸው በፊት የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር ሆነው ከ1996 እስከ 2002 ዓ.ም. ለ6 ዓመታት አገልግለዋል።

በሪፖርተር ጋዜጣ ዘገባ መሠረት አቶ ብርሃኑ ከዚህ ኃላፊነታቸው የተነሱትም በቀረበባቸው ቅሬታ ምክንያት ነው።

ከተወለዱበት ካፋ ዞን ቦንጋ ከተማ ነዋሪዎች አዲስ አበባ ድረስ በመምጣት በአቶ ብርሃኑ ላይ የተፈራረሙትን ቅሬታ በጊዜው ጠቅላይ ሚኒስትር ለነበሩት አቶ መለስ ዜናዊ ማቅረባቸውን የሪፖርተር ዘገባ ያስታውሳል።

ይህን ተከትሎ " በቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር የተቋቋመ አጣሪ ኮሚቴ ባቀረበባቸው ሪፖርት ከካቢኔ ጉዳይ ሚኒስትርነታቸው እና ከኢሕአዴግ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልነታቸው እንዲነሱ " መደረጉን ሪፖርተር ከ10 ዓመታት በፊት በሠራው ዘገባ ጠቅሷል።

አቶ ብርሃኑ በመንግሥታዊ ተቋማት ከነበራቸው ኃላፊነት በተጨማሪ አወዛጋውን የ1997 ምርጫ ተከትሎ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል ነበሩ።

የትምህርት ሁኔታቸው ምን ይመስላል ?

ከሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በሕግ የመጀመሪያ ዲግሪ አላቸው። በዓለም አቀፍ ሰብዓዊ መብቶች ከሕንድ አገር የማስተርስ ዲግሪያቸውን ተቀብለዋል።

የስራ ህይወታቸው ምን ይመስላል ?

- ከመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት እስከ ዩኒቨርሲቲ አስተምረዋል።

- በዞን ፋይናንስ መምሪያ የህግ አማካሪ ሆነው አገልግለዋል።

- የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ባገኙበት የሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የህግ ፋካልቲ ለ3 ዓመታት አስተምረዋል።

- በቀድሞው ደቡብ ክልል የፍትህ ቢሮ ኃላፊነት ላይ ሰርተዋል። ከዛ በመቀጠልም በቀረበባቸው ቅሬታዎች ከስልጣን ወደተነሱባቸው የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር እና የኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ጽህፈት ቤት አቅንተዋል።

- ከመንግስታዊ የሥራ ኃላፊ ከተነሱ በኋላ ላለፉት 10 ዓመታት በጥብቅና እና በህግ ማማከር ስራ ላይ መሰማራታቸውን ለፓርላማ አባላት የቀረበው የስራ ልምድ ያሳያል።

Source - tikvahethiopia

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

29 Jan, 18:05


የሕግ ቻናሎችን ለማግኘት 
ከታች ባለው ሊንክ ይግቡ👇

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

28 Jan, 16:33


ከጋብቻ በፊት በባል ወይም በሚስት ተይዞ የቆየ የገጠር መሬት እንደ ግል ንብረት ሊቆጠር ይችላልን ?
በርእሱ በተገለጸው ጉዳይ ላይ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ሕገ መንግስታዊ ትርጉም ሰጥቶበታል። በዚህ ጉዳይ ላይ ለተሰጠው የሕገ መንግስት ትርጉም መነሻ የሆነው አመልካች እና ተጠሪ የነበራቸው ጋብቻ ሲፈርስ ተጠሪ አመልካች ከትዳር በፊት ይዛው የቆየችውን መሬት ከአባቴ በውርስ የተላለፈለኝ ነው በማለት ከህጻናት ልጆቿ ጋር ከመሬቱ እንዳስለቀቃት በመግለጽ ለፍርድ ቤት ያቀረበችው ክስ ነው።

ጉዳዩን በየደረጃው ያዩት ፍርድ ቤቶችም የተለያዩ ውሳኔዎች የሰጡ ሲሆን ጉዳዩን በሰበር ያየው የኦሮሚያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት "የገጠር መሬት እንደሌላ የግል ንብረት ከጋብቻ በፊት የተፈራ ንብረት ነው ሊባል አይችልም" በማለት ተጠሪ የይዞታ ክርክር ከተነሳበት መሬት ግማሽ የመካፈል መብት አለው በማለት ወሰኗል። አመልካች ይህንን ውሳኔ በመቃወም አቤቱታዋን ለፌዴራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ያቀረበች ብትሆንም ችሎቱ ቅሬታዋን ባለመቀበል መዝገቡን ዘግቶታል።

በመቀጠልም አመልካች የፍርድ ቤቶቹ ውሳኔ በጋብቻ ስም ከመሬት መንቀልንና ከፈረሰው ጋብቻ በፊት በነበረኝ ጋብቻ ከሟች የቀድሞ ባለቤቴ የወለድኳቸው ልጆቼ የመውረስ መብት የሚጥስ በመሆኑ ኢሕገ-መንግስታዊ ነው ተብሎ ውድቅ እንዲደረግላት በመጠየቅ አቤቱታዋን ለሕገ መንግስት ጉዳዮች አጣሪ ጉባኤ አቅርባለች። የሕገ መንግስት ጉዳዮች አጣሪ ጉባኤም ጉዳዩን በማጣራት የውሳኔ ሐሳቡም ለፌዴሬሽኑ ምክር ቤት አቅርቧል።


የፌዴሬሽን ምክር ቤትም የኦሮሚያ ክልል እና የፌዴራሉ ሰበር ሰሚ ችሎቶች ውሳኔ በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገ መንግሥት አንቀጽ 35 ንኡስ ቁጥሮች 2 እና 7 መሰረት ሴቶች መሬትን በመጠቀም፤ በማስተላለፍ፤ በማስተዳደርና በመቆጣጠር ረገድ ከወንዶች ጋር እኩል መብት እንዳላቸው፡ በአንቀጽ 36 /2/ መሰረትም ህጻናትን የሚመለከቱ እርምጃዎች በሚወሰዱበት ጊዜ በፍርድ ቤቶች ጨምሮ በሁሉም የመንግስት አካላት የሕጻናት ደህንነት ቀዳሚነት ሊሰጠው እንደሚገባና የኢትዮጵያ አርሶ አደሮች መሬት በነጻ የማግኘት እና ከመሬታቸው ያለመነቀል መብትን ከሚደነግገው አንቀጽ 40 /4/ አንጻር ሲታይም አመልካች እና ከሟች የመጀመሪያ ባለቤትዋ የወለደቻቸው ሕጻናት ልጆቿ በገጠር መሬት ይዞታቸው የመጠቀምና ያለመነቀል እንዲሁም የመውረስ መብታቸውን የሚጥስ በመሆኑ ውሳኔው ኢሕገ-መንግስታዊና በሕገ መንግስቱ አንቀጽ 9/1/ መሰረት ተፈጻሚነት የለውም በማለት ምክር ቤቱ በሙሉ ድምጽ ወስኗል።

ከዚሁ ሕገ መንግስታዊ ትርጉም ለመረዳት የሚቻለውም የገጠር መሬት የህዝብና የመንግስት መሆኑ በሕገ መንግስቱ የየደነገገ ቢሆንም ይህ ድንጋጌ አርሶ አደሮች እንደ ግለሰብ በህጋዊ መንገድ የያዙት መሬት ሕጋዊ ጥበቃ የሚደረግለትና በተለይም የግል ይዞታ የሆነ መሬት በጋብቻ ምክንያት ብቻ የጋራ ይዞታ ወደመሆን የማይለወጥ መሆኑን ነው።
#Legaltech
Join👇
@Ethiopianlaw_s

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

27 Jan, 16:00


በችሎት ስልክን ማስጮህ የችሎት መድፈር ተግባር ነውን ?
የወንጀል ህግ አንቀፅ 449(1)(ሀ)እና(ለ)እንደሚነግረን ማንም ሰው በፍርድ ቤት ምርመራ በሚደረግበት ወይም የፍርድ ስራ በሚከናወንበት ጊዜ
ሀ) ፍርድ ቤቱን ወይም የዳኝነት ስራ በማከናውን ላይ ያለውን ዳኛ በማናቸውም መንገድ የሰደበ፣ያወከ ወይም በእነዚሁ ላይ ያፌዘ ወይም የዛተ እንደሆነ ወይም
ለ) የፍርድ ቤቱን ሥራ በማናቸውም ሌላ መንገድ ያወከ እንደሆነ ከ1 ዓመት በማይበልጥ ቀላል እስራት ወይም ከ3000 ብር በማይበልጥ መቀጮ እንደሚቀጣ ይደነግጋል፡፡

ይህም የመድፈር ተግባር የተከናወነው በፍትሐብሔር መዝገብ ላይ ቢሆን እንኳን ቅጣቱ ተፈፃሚነት እንዳለው የፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ 481 ይደነግጋል፡፡በመሆኑም በችሎት ውስጥ ስልክ ማስጮህ እና ሌላ ያልተገባ ባህሪ ማሳየት የችሎት መድፈር ተግባር ነውን? የፌደራልጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ቅፅ 15 የሰ/መ/ቁ 92459 ላይ የሰበር አመልካቹ በችሎት ውስጥ ስልክ በማስጮህ ከተቃራኒው ተከራካሪ ጋር ያልተገባ ክርክር መፍጠር፣ፍ/ቤቱ ስነ-ሥርዓት እንዲይዙ ቢያሳውቃቸውም ፈቃደኛ ሳይሆኑ በመቅረታቸው እንዲሁም ፍ/ቤቱ በስነ-ሥርዓት ያናግረን በሚል ያልተገባ በህሪይ በማሳየታቸው በስር ፍ/ቤቶች በ5 ወራት መቀጣታቸውን ያየው ሰበር ሰሚው ችሎት የፍርድ ስራ በሚከናውንበት ጊዜ ፍርድ ቤቱን ማወካቸውን የሚያሳይ እና በፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ 481 አግባብ በወንጀል ህጉ አንቀፅ 449(1)(ሀ) ድንጋጌ ስር ተጠያቂነት የሚያስከትል ተግባር ነው ከሚባል በስተቀር ሌላ ትርጉም የሚሰጠው አይደለም፡፡ሲል የስር ፍ/ቤት የሰጠውን የእስራት ቅጣት አፅንቶታል፡፡
#Ethiolegaltech
@Ethiopianlaw_s
@Ethiopianlaw_s

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

26 Jan, 19:55


የሕግ ቻናሎችን ለማግኘት 
ከታች ባለው ሊንክ ይግቡ👇

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

26 Jan, 17:45


ከዚህ በመነሳት በመጀመሪያ ህጻናት ላይ የዘረ መል (DNA) ምርመራ ማድረግ በራሱ ህጻናት ወላጆቻቸውን ለማወቅ ያላቸውን መብት ወይም የህጻናትን ጥቅም የቃረናልን? የሚለውን ጥያቄ ያነሳን እንደሆነ ይኸው ምርመራ የሕክምና ቴክኖሎጂ ውጤት ሆኖ አንድ ልጅ ልጄ አይደለም ብሎ ከከሰሰው ወንድ መወለዱ ወይም አለመወለዱን ለመለየት የሚረዳ ከመሆኑ አንጻር ልጁ ትክክለኛ አባቱን ለማወቅ ይረዳው እንደሆነ እንጂ የሚከለክለው አይደለም። ስለዚህም ምክር ቤቱ በዚህ ረገድ ያስቀመጠው ትችት አሳማኝ ሆኖ አይታይም።

የህጻናትን መብትና ጥቅም በቀዳሚነትና በተሻለ አኳኋን ከማስጠበቅ አንጻር ሲታይም ምክር ቤቱ የዘረ መል (DNA) ምርመራ በሕጻኑ ላይ የሚያደርሰው አካላዊ ወይም ስነ ልቦናዊ ጉዳት መኖሩን አስመልክቶ የጠቀሰው ሳይንሳዊ ግኝት የለም።ወይ ደግሞ ህጻናት የዚሁ ዓይነት ምርመራ እንዳይደረግባቸው መከልከሉ ምን የተለዬ ጥቅም እንደሚያስገኝላቸውም የቀረበ አሳማኝ ሳይንሳዊ ትንታኔ የለም።

በበኩሌ ምክር ቤቱ የፍርድ ቤቶቹ ውሳኔ ተፈጻሚነት የለበትም በማለት በጉዳዩ ላይ በተለይ የሰጠው ውሳኔ በውጤት ደረጃ እስማማበታለሁ። ለዚህም ምክንያቱ 1ኛ ከላይ እንደተገለጸው ክሱ እንደማንኛውም መደበኛ ክስ የሚቀርብ ሳይሆን በፍርድ ቤት ፈቃድ በልዩ ሁኔታ የሚቀርብ ሲሆን ምክር ቤቱ ውሳኔ በሰጠበት ጉዳይ ላይ ግን ተጠሪ ልጁ ከአመልካች ጋር ከተጋባን በሶስት ወር ውስጥ የተወለደ በመሆኑ በDNA ይመርመርልኝ የሚል ይዘት ያለው መሆኑ ስነ ስርዓቱን ያልጠበቀ ክስ ሆኖ ስለሚታይ ነው። ሁለተኛው ምክንያት ደግሞ ከላይ እንደተገለጸው የመካድ ክስ የቀረበበት ህጻን ልጅ በልዩ ሞግዚት ሳይወከል መከራከሩም የህጻኑን መብትና ጥቅም ሊጎዳ የሚችል በመሆኑ የህገ መንግስታዊነት ጥያቄ ስለሚያስነሳ ነው።

ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ ግን ለህጻኑ ልጅ ጥቅምና መብት እንዲቆም በፍርድ ቤት የተመደበ ልዩ ሞግዚት በልጁ ላይ የDNA ምርመራ አይደረግም ያለ እንደሆነ ልጁ የመካድ ክስ ካቀረበበት ወንድ መወለዱን የሚያመላክቱ ሌሎች ተቃራኒ ማስረጃዎች እስከሌሉ ድረስ ፍርድ ቤት በፍትሐብሔር ሕጉ ቁጥር 22 መሰረት ህጻኑ የመካድ ክስ ያቀረበው ሰው ልጅ አይደለም በሚል ሕጋዊ ግምት ውሳኔ መስጠቱ ልጁ አባቱን ለማወቅ ያለው መብት ሆነ ሌላ ጥቅሙን የሚጎዳ ኢሕገ መንግስታዊ ውሳኔ ማለቱ አሳማኝ አይደለም።

በመሰረቱም ከሳሽ በትዳር ውስጥ የተወለደው ህጻን ልጄ አይደለም ሲል፥ ህጻኑም በልዩ ሞግዚቱ በኩል ልጅነቱን ለመለየት የሚረዳና የተተጋገጠ የጎንዮሽ ጉዳይ የሌለበት ምርመራ ለማድረግ ፈቃደኛ አለመሆኑን ከገለጸ ልጁ ከከሳሹ ለመወለዱ የሚጠራጠርበት ምክንያት አለው ወደሚል ምክንያታዊ ድምዳሜ ነው የሚወስደው።

ስለዚህም ሌላ ተቃራኒ ማስረጃ እስከሌለ ድረስ የDNA ምርመራ ለማድረግ ፈቃደኛ አለመሆኑን ፍርድ ቤት በመደበለት ልዩ ሞግዚት አማካኝነት የገለጸ ህጻን የመካድ ክስ ያቀረበበት ሰው ልጅ አይደለም ብሎ መወሰን የህጻኑን ህገ መንግስታዊ መብት ይቃረናል የሚባልበት ምክንያት ግልጽና አሳማኝ ባለመሆኑ ተገቢ መሻሻል ሊደረግለት ይገባል።
#Ethiolegatech
Join us 👇
@Ethiopianlaw_s
@Ethiopianlaw_s
@Ethiopianlaw_

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

26 Jan, 17:45


አባትነትን ለመወሰን የሚደረግ የDNA ምርመራና የሕጻናት መብት

ስለአባትነት በአጠቃላይ የሚደነግገው የተሻሻለው የቤተሰብ ሕግ ዓንቀጽ 125 አባትነት በሶስት መንገድ የሚታወቅ መሆኑና እነሱም፥

1. ልጅ በሚፀነስበት ወይም በሚወለድበት ጊዜ በእናትየዋና በአንድ ወንድ መካከል በሕግ የታወቀ ግንኙነት መኖሩ ሲረጋገጥ ወንዱ የልጁ አባት እንደሆነ ይገመታል።

2. ከእናተየዋ የተወለደው ልጅ ልጄ ነው ብሎ የተቀበለው ወንድ የልጁ አባት እንደሆነ ይገመታል።

3. በፍርድ ቤት በሚሰጥ ውሳኔ አንድ ወንድ የልጁ አባት መሆኑ ሲታወቅ ነው።


በዚህም መሰረት አባትነት የሚታወቅበት አንደኛውን መንገድ ነጥለን ስንመለከት ልጅ በሚፀነስበት ወይም በሚወለድበት ጊዜ በእናትየዋና በአንድ ወንድ መካከል በሕግ የታወቀ ግንኙነት መኖሩ ሲረጋገጥ ያወንድ የልጁ አባት እንደሆነ ሕጋዊ ግምት እንደሚወሰድ ለመረዳት ይቻላል።

"በሕግ የታወቀ ግንኙነት" የሚል አገላለጽ በመደበኛ ሕብረት (ጋብቻ) እና ኢመደበኛ ሕብረት የሚፈጠሩትን ዝምድናዎች የሚያጠቃልል ነው። ለዚህም የቤተሰብ ሕጉን አናቅጽ 126 እና 130 ማየቱ በቂ ነው።

አንቀጽ 126 "በጋብቻ ውስጥ የተፀነሰ ወይም የተወለደ ልጅ አባቱ ነው የሚባለው ባልየው ነው" በማለት ይደነግጋል። በተመሳሳይ አንቀፅ 130 /1/ "ጋብቻ ሳይፈፀም እንደባልና ሚስት አብረው በሚኖሩበት ጊዜ የተፀነሰ ወይም የተወለደ ልጅ አባት በዚሁ ግንኙነት ከእናትየዋ ጋር አብሮ የሚኖረው ሰው ነው" ይላል።

በዚህ መልኩ የሚታወቅ አባትነት በጠንካራ የሕግ ግምት ላይ የተመሰረተ ቢሆንም በልዩ ሁኔታ ግን ግምቱ ሊስተባበልና ልጁ በሚፀነስበት ወይም በሚወለድበት ጊዜ ከእናቲቱ ጋር በሕግ የሚታወቅ ግንኙነት የነበረው ሰው የልጁ አባት አይደለም ተብሎ ሊወሰን ይችላል። ይህ የሚሆነውም በሕጉ አባት ነው ተብሎ የሚገመተው ሰው፥ እርሱ በህየወት ከሌለም ወራሾቹ የመካድ ክስ ሲያቀርቡ ብቻ ነው (አንቀጽ 167 እና 177)።

ሆኖም ክሱን ማቀረብ የሚቻለው በፍርድ ቤት ፈቃድ ብቻ ሆኖ ፍርድ ቤትም ፈቃዱን የሚሰጠው ክሱን እንዲቀበል የሚያደርገው በቂና አስተማማኝ ከሆነ መረጃ የሚመነጭ የህሊና ግምት ወይም ከባድ ምልክት ሲኖር ብቻ ነው (አንቀጽ 171)። ታድያ "የህሊና ግምት" ወይም "ከባድ ምልክት" ምን ማለት ይሆን? አንቀጽ 172 እንደሚከተለው ይደነግጋል፥

1) "የህሊና ግምቶችና ከባድ ምልክቶች የሚባሉት ልጅህ ነው ከተባለው ሰው አባትነት ጋር የማይስማሙ ለመሆናቸው በሳይንስ እውቀት ተለይተው የሚታዩ ተጨባጭ መረጃዎች ሊሆኑ ይችላሉ።"

2) "እንዱሁም እነዚህ ነገሮች ሴቲቱ በሰውየው አባትነት ላይ ጥርጣሬ በሚያሳድር አኳኋን የልጁን መወለድ ወይም እርግዝናዋን ከሰውየው ከደበቀችበት ድርጊት ሊመነጩ ይችላሉ።"

በንኡስ አንቀጽ 1 የተደነገገው "በሳይንስ እውቀት ተለይተው የሚታዩ ተጨባጭ መረጃዎች" የዘረ መል (DNA) ምርመራንም እንደሚያካትት ለመረዳት ይቻላል። ይህም ማለት በአባት በኩል ያለን መወለድ በመቃወም ከቀረበው ክስ ጋር በማስረጃነት ተያይዞ የቀረበው የDNA ምርመራ ውጤት "ልጅህ ነው ከተባለው ሰው አባትነት ጋር የማይስማሙ ለመሆናቸው" የሚያሳይ ሆኖ ከተገኘ ፍርድ ቤቱ ክሱን መቀበል ይኖርበታል።

ወደ ንኡስ አንቀጽ 2 ስናልፍ ሴቲቱ በሰውየው አባትነት ላይ ጥርጣሬ በሚያሳድር አኳኋን የልጁን መወለድ ወይም እርግዝናዋን ከሰውየው የደበቀችበት መሆኑ የሚያመለክት በቂ መረጃ የቀረበለት እንደሆነም ፍርድ ቤቱ ክሱን መቀበል ይኖርበታል። ልጁ የDNA ምርመራ እንዲደረግለት ፍርድ ቤቱ ትእዛዝ እንዲሰጥ ከሳሽ ሊጠይቅ የሚችለውም በዋነኝነት በዚህ ሁኔታ ነው። ታድያ የልጁ ሞግዚት በፍርድ ቤት ትእዛዝ መሰረት ልጁን ለማስመርመር ፈቃደኛ ባይሆን ውጤቱ ምን ይሆናል? በቅርቡ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ይህንን ጉዳይ አስመልክቶ ሕገ መንግስታዊ ትርጉም ሰጥቷል።

የፌዴሬሽኑ ምክር ቤት በሰጠው ትርጓሜ ሕጻናት በፍርድ ቤት ለማስረጃነት የሚውል የዘረ መል (DNA) ምርመራ ለማድረግ እንደማይገደዱ ምርመራውን ለማድረግ ፈቃደኛ አለመሆናቸው ብቻውንም እንደ በቂ ማስረጃ ተቆጥሮ "ሕፃኑን DNA ለማስመርመር ፈቃደኛ ያልተሆነው ልጁ የባልየው ባይሆን ነው" በሚለው ሕጋዊ ግምት ላይ በመመስረት ባልዬው የልጁ አባት አይደለም ብሎ መወሰን ሕገ መንግሥቱን የሚቃረን መሆኑ ትርጉም ሰጥቶበታል (ፌዴሬሽን ም/ቤት መ/ቁ 94/13 ግንቦት 30/2013 ዓ.ም)።

በዚህ ውሳኔ ልጁን ለማስመርመር ፈቃደኛ ያልሆነችው አመልካች የልጁ እናት መሆንዋ ከመዝገቡ ለመረዳት ይቻላል። ከዚህ አንጻር አስቀድሞ መታየት ያለበት በዚሁ ዓይነት ክስ ስለ ልጁ ሆኖ መልስ መስጠትና መከራከር የሚችለው ማነው? የሚል ነው። በዚህ ረገድ የተሻሻለው የቤተሰብ ሕግና ለምክር ቤቱ ውሳኔ መነሻ የሆነው የአማራ ክልል የቤተሰብ ሕግ ተመሳሳይ ድንጋጌ አላቸው። በአማራ የቤተሰብ ሕግ አንቀጽ 190/3/ እና በተሻሻለው የቤተሰብ ሕግ አንቀጽ 179 /3/ መሰረት የመካድ ክስ የቀረበበት ልጅ አካለመጠን ያልደረሰ ከሆነ ፍርድ ቤት በተለይ ለዚህ ጉዳይ የመረጠው ሞግዚት ወኪል የሆነዋል። ይህም ህጻናትን የሚመለከት ማናቸውም ጉዳይ የህጻናት ጥቅም በተሻለ መንገድ በሚጠብቅ መልኩ መፈጸም እንዳለበት ከሚደነግገው የሕጻናት መብቶች ስምምነት አንቀጽ 3 /1/ እና የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ሕገ መንግስት አንቀጽ 36 /2/ አንጻር ሲታይ ፍርድ ቤቱ በተቻለ መጠን የሕጻኑን መብትና ጥቅም ለማረጋገጥ የተሻለ ብቃት ያለው ሰው እንዲመድብ የሚያስገድደው ነው።

ከዚህ አኳያ ጉዳዩን በቅድሚያ የተመለከቱት ፍርድ ቤቶች ሕጉ በሚደነግገው መሰረት ለልጁ ልዩ ሞግዚት ሊያቆሙለት ሲገባቸው የልጁ እናት የሆነችውን አመልካች በክርክሩ እንደ ልጁ ወኪል በመቁጠርና በልጁ ላይ የዘረ መል (DNA) ምርመራ ለማድረግ ፈቃደኛ ባለመሆኗ ልጁ የተጠሪ

አይደለም በማለት የሰጡት ውሳኔ የሕገ መንግስታዊነት ጥያቄን የሚያስነሳ ነው።

ሁለተኛው መታየት ያለበት ነጥብ ፍርድ ቤቱ በህጉ መሰረት የመካድ ክስ የቀረበበትን ህጻን ልጅ በመወከል መልስ እንዲሰጥና እንዲከራከር ያቆመው ልዩ ሞግዚት በልጁ ላይ የዘረ መል (DNA) ምርመርስ ሊደረግ አይገባም የሚል ተቃውሞ ቢያቀርብስ ውጤቱ ምን ይሆናል? የሚል ነው። ለዚሁ ጥያቄ ከቤተሰብ ህግጋቱ ቀጥተኛ ምላሽ ማግኘት አይቻልም። ስለዚህም ጉዳዩን ያዩት ፍርድ ቤቶች እንዳደረጉት የፍትሐብሔር ሕጉን ማየት ግድ ይላል። በዚህም መሰረት ቁጥር 22 እንደሚከተለው ይደነግጋል፥

"አንድ ሰው በሰውነት ላይ አንዳችም እርግጠኛ አደጋ ሊያስከትል በማይችል በሐኪም ምርመራ ለመመርመር እንቢ ያለ እንደሆነ ዳኞች ተመርምሮ ሊገኝበት ይችላል ተብሎ የተገመተው ነገር እንዳለበት ያህል ሊቆጠሩት ይችላሉ።"

እንግዲህ ጉዳዩን ያዩት ፍርድ ቤቶች ልጁ የተጠሪ አይደለም በማለት የወሰኑት በዚሁ ድንጋጌ መሰረት ነው። በሌላ በኩል የፌዴሬሽን ምክር ቤት ይህ ድንጋጌ በህጻናት ልጆች ላይ ተፈጻሚ መሆኑ ህጻናት ወላጆቻቸውን ለማወቅ ያላቸው ህገ መንግስታዊ መብት የሚጥስና "ማናቸውም እርምጃ ሲወሰድ የህጻናት መብትና ጥቅም ቀዳሚነት ሊሰጠው ይገባዋል" የሚለው ህገ መንግስታዊ መርህን የሚጻረር በመሆኑ ተፈጻሚነት የለውም በማለት ወስኗል።👇👇👇

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

26 Jan, 15:48


ነፃ የህግ ድጋፍ 0961103179
⚖️ Law vs practice ⚖️.
ነፃ የህግ የማማከር አገልግሎት፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጆች፣ ደንቦች፣ መመሪያዎች፣ የውል ፎርሞች፤ መፅሐፍቶች : አጫጭር ኖቶች እዚሁ ያገኛሉ። Here on our channel, we provide Free legal Aid.

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

26 Jan, 09:10


Durov airdrop የቴሌግራም መስራቹ የራሱ ነው ቶሎ ጀምሩት

ለስምንት ቀናቶች ብቻ ነው የሚቆየው ምንም መረጃ አልተነገረም የዱሮቭ መሆኑ ብቻ ነው የታወቀው። ከስምንት ቀናቶች ቡሃላ ይጠናቀቃል ነውም የተባለው።  countdown ጀምሯል
እንዳያመልጣቹህ
👇👇

https://t.me/DurovCapsBot/caps?startapp=1131913592
Yo!
y

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

25 Jan, 11:05


አንድ የአስተዳደር ውሳኔ ህጋዊ ነው የሚባለው ምን ሲያሟላ ነው?

የአስተዳደር ውሳኔ መስጠት እና መፈፀም የአስተዳደር ተቋሞች ከተፈጥሮ ባህሪያቸው የሚመነጭ የእለተ ዕለት ዋነኛ ተግባር ነው፡፡ እነዚህ ውሳኔዎች በሰዎች መብትና ጥቅም ላይ አዎንታዊም ሆነ አሉታዊ ውጤት ማስከተላቸው የሚጠበቅ ነው፡፡ ስለሆነም አንድ የአስተዳደር ውሳኔ ህጋዊ ነው የሚባለው ምን ሲያሟላ ነው? የሚለውን በተመለከተ የፌዴራል አስተዳደር ስነ-ስርዓት ህግ አዋጅ ቁጥር 1183/2012 በክፍል ሶስት የህግ መስፈርቶችን አዘጋጅቷል፡፡


1. ውሳኔውን የሚሰጠው ህጋዊ ስልጣን የተሰጠው ሰው መሆን አለበት (አንቀፅ 23)

አስተዳደራዊ ውሳኔ የመወሰን ስልጣን ከህግ እና ከተሰጠ ውክልና ይመነጫል፡፡ የአስተዳደር ተቋም የበላይ ሃላፊዎች ውሳኔ የመወሰን ስልጣን የሚያገኙት ከህግ ሲሆን ሰራተኞች ደግሞ ከህግ አልያም ከበላይ ሀላፊዎች በተሰጠ ውክልና ነው፡፡

2. በህግ የተሰጠ ስልጣን ወሰንን አለማለፍ (አንቀፅ 24)

ይሄ የተሰጠ ስልጣን ገደብ ላይ ተመርኮዞ ውሳኔን መወሰን መቻል ነው፡፡

3. የግልና የህዝብ ጥቅምን ማመዛን (አንቀፅ 25)

የአስተዳደር ውሳኔ የግል ጥቅምና የህዝብ ጥቅም በሚጋጩበት ጊዜ ቅድሚያ ለህዝብ ጥቅም መስጠት ይኖርበታል፡፡ ይሁን እንጂ አንድ ጥቅም የህዝብ ጥቅም ነው ተብሎ በምን አይነት መስፈርት ሊፈረጅ እንደሚችል ግልፅ መለኪያዎችን አላስቀመጠም፡፡

4. አግባብነት በሌለው ጉዳይ ወይም ፍላጎት አለመመራት (አንቀጽ 26)

አግባብነት የሌለው ጉዳይ ወይም ፍላጎት ማለት ተገልጋዩ ለተቋሙ ካቀረበው የውሳኔ ይሰጥልኝ ጥያቄ እና ተቋሙ ከቆመለት ዓላማ ወይም ስልጣንና ተግባር ጋር ያልተያያዘ ማናቸውም አላግባብ የሆነ ድርጊት ነው፡፡

5. ሙያዊ ውሳኔ (አንቀፅ 27)

በአዋጁ መሰረት ሙያዊ ውሳኔ ተሰጠ የሚባለው ውሳኔውን የሰጠው አካል ሙያው የሚጠይቀውን ስነ-ምግባር፣ ትጋት እና ክህሎት ሲኖረው ነው፡፡

6. ማዳመጥ/መስማት (አንቀፅ 28)

ማንም ሰው በጥቅሙ ወይም በመብቱ ላይ ውሳኔ ሲሰጥ የመደመጥ መብት አለው፡፡ ስለሆነም ቅሬታ ያቀረበው ሰው ሀሳብ ውሳኔ ከመሰጠቱ በፊት ሊሰማ ይገባል፡፡ ይሁን እንጂ አዋጁ ባለጉዳዩን ማደማጥ ሳያስፈልግ ውሳኔ ሊሰጥባቸው የሚችሉ 3 ልዩ ሁኔታዎችን አንቀፅ 36 (2) ላይ አስቀምጧል፡፡ እነዚህም የፍሬ ነገር ክርክር ከሌለ፣ ተቋሙ ባለጉዳዩቹን ሳይሰማ የመወሰን መብት በህግ ከተሰጠው እንዲሁም አስቸኳይ ውሳኔ መስጠት የሚፈልግ ድርጊት ሁኖ ሲገኝ ብቻ ነው፡፡

7. በቅን ልቦና መወሰን (አንቀፅ 29)

ውሳኔ የሚሰጠው ሰው ሆነ ብሎ ቅሬታ አቅራቢውን ለመጉዳት ወይም ለመጥቀም ውሳኔ መስጠት የለበትም፡፡ ይሁን እንጂ ቅን ልቦና ህሊናዊ ጉዳይ በመሆኑ በክፉ ልቡና የተሰጠ ውሳኔ ነው ብሎ አንድን አስተዳደራዊ ውሳኔን ለመቃወም ቀላል አይሆንም፡፡

8. በቂ ምክንያት መስጠት (አንቀፅ 30)

ይሄ በሀገራችን ላይ የበርካታ አስተዳደራዊ ውሳኔዎች ችግር ነው፡፡ አብዛኛዎቹ በአስተዳደራዊ ተቋማት የሚሰጡ አስተዳደራዊ ውሳኔዎችን በጥሞና ከመረመርን ለውሳኔያቸው መደምደሚያ መሰረት የሆነውን የህግ ምክንያት የሚጠቅሱ አይደሉም፡፡ በመሰረቱ አንድ ውሳኔ በህግ አይን እንደ ውሳኔ ሊቆጠር የሚችለው የህግ መሰረት በግልፅ ከተጠቀሰበት ነው፡፡ የህግ መሰረት የሌለው ውሳኔ ከድርሰት የሚለይ አይደለም፡፡

9. የጥቅም ግጭት ማስቀረት (አንቀፅ 31)

የአስተዳደር ውሳኔ የሚሰጠው ሰው ከባለጉዳዩ ጋር የስጋም ሆነ የጋብቻ ዝምድና ወይም የጠበቀ ጓደኝነት/ትውውቅ ወይም የጥቅም ግንኙነት ካለው ራሱን ጉዳዩን ከማየት ማግለል ይኖርበታል፡፡

10. የተገልጋዮችን እኩልነት ማክበር (አንቀፅ 32)

ሁሉም ሰዎች በህግ ፊት እኩል በመሆናቸው ውሳኔ የሚሰጠው አካል በሰዎች መካከል በብሄር፣ በዘር፣ በቀለም፣ በሀይማኖት፣ በፖለቲካ አመለካከት፣ በማህበራዊ አመጣጥ፣ በሀብት መጠን፣ በትውልድ ሁኔታ ወይም በሌላ ምክንያት ልዩነት ሳያደርግ መወሰን አለበት፡፡

11. በተገቢው ጊዜ መወሰን (አንቀፅ 33)

ይሄም በሀገራችን ላይ በመሰረታዊነት የሚታይ ጉልህ ችግር ነው፡፡ ህጉ ውሳኔ ለመስጠት ባስቀመጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ መስጠት ህጋዊ ግዴታ ነው፡፡ በአዋጁ በአንቀፅ 33(2) ላይ አንድ የአስተዳደር ተቋም አንድ ውሳኔን በተገቢው ጊዜ ሳይሰጥ ከቀረ ጥያቄውን ውድቅ በማድረግ እንደተሰጠ ውሳኔ ይቆጠራል በማለት ይደነግጋል፡፡

12. ተገማች መሆን (አንቀፅ 34)

በፍሬ ነገር ተመሳሳይ በሆኑ ጉዳዮች ላይ በየትኛውም ጊዜ ቢሆን አንድ አይነት ውሳኔ ሊሰጣቸው ይገባል፡፡

13. ግልፅ መሆን (አንቀፅ 35)

በአዋጁ መሰረት ግልፅ መሆን ማለት ባለጉዳዩ ውሳኔ ሲሰጥ ውሳኔው የሚሰጥበትን ሂደት የማወቅ መብት እንዳለው የሚያመላክት ነው፡፡ የውሳኔ ፍትሃዊነት የሚለካው በሚሰጠው የመጨረሻ ውሳኔ ላይ ብቻ ሳይሆን በሂደቱም ጭምር ነው፡፡

14. በፅኁፍ መስጠት (አንቀጽ 40)

አብዛኛውን ጊዜ በሀገራችን የተለመደው ውሳኔን በፅኁፍ ከማድረግ ይልቅ በቃል መናገር ነው፡፡ ይሁን እንጂ በአዋጁ መሰረት የትኛውም ውሳኔ በፅኁፍ መሆን እንዳለበት በግልፅ አስቀምጧል፡፡

በአጠቃላይ አንድ የመጨረሻ ውሳኔ ከላይ ከተጠቀሱት ውስጥ አንዱን ያጓደለ ከሆነ በአዋጁ አንቀፅ 48 (2) እና 49 (1) መሰረት ውሳኔው ላይ የዳኝነት ክለሳ እንዲረግለት ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የማቅረብ መብት አለው፡፡
#Ethiolegatech
Join us 👇
@Ethiopianlaw_s
@Ethiopianlaw_s
@Ethiopianlaw_s

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

25 Jan, 07:46


ያላቸው በመሆኑ በቀድሞ ውሳኔ ላይ ከተሰጠው ድምፅ በሚያንስ የድምፅ ብዛት የቀድሞውን ውሳኔ መሻር በችሎቶቹ መካከል ህጋዊ ያልሆነ የስልጣን ልዩነት የሚፈጥር ነው፡፡

በአጠቃላይ የሰበር ሰሚ ችሎቶች ላይ የሥልጣን ተዋረድ ልዩነት የሌለ በመሆኑና ያላቸው ብቸኛ ልዩነት የድምፅ ልዩነት ብቻ በመሆኑ የቀድሞ የሰበር ውሳኔ በሌላ ጊዜ በሚሻርበት ጊዜ የቀድሞው ሰበር ሰሚ ችሎት ከሰጠው የድምፅ ብዛት የበለጠ ድምፅ ካልተገኘ በስተቀር የቀድሞው የሰበር ውሳኔ ሊሻር እንደማይገባው የጸሀፊው እምነት ነው፡፡
#Ethiolegatech
Join us 👇
@Ethiopianlaw_s
@Ethiopianlaw_s
@Ethiopianlaw_s

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

25 Jan, 07:46


የፌዴራል ሰበር ሰሚ ችሎት በአምስት ዳኞች ሙሉ ድምፅ የሰጠውን ውሳኔ በሰባት ዳኞች በቀላል አብላጫ ድምፅ (Simple Majority) መሻሩ ተገቢ ነውን ?

ሰበር (Cassation) የሚለው ቃል Casser ከሚል የፈረንሳይኛ ቋንቋ ግስ የመጣ ቃል ሁኖ ቀጥተኛ ትርጉሙ መሻር (To Invalidate) ወይም መሰረዝ (To Quash) የሚል ሲሆን ከህግ አኳያ የቃሉ ጥሬ ትርጉም አንድን ውሳኔ ህጋዊ ውጤት እንዳይኖረው ማድረግ ወይም መሻር ወይም ውሳኔው ተግባራዊ እንዳይሆን በማድረግ ተፈፃሚነቱን ማስቀረት መሆኑን በ Black's Law መዝገበ ቃላት ላይ ተገልጿል፡፡ የሰበር ፅንሰ ሀሳብ የመጣው ከሲቪል ህግ ስርዓት ሲሆን የህግ በላይነት መርሆዎች ከሆኑት የህግ ተገማችነት እና ወጥነት ላይ የተመሰረተ ፅንሰ ሀሳብ ነው፡፡

ፈረንሳይ በ1790 እ.ኤ.አ የሰበር ሰሚ ችሎት (French Court de Cassation) በማቋቋም ግንባር ቀደም በመሆን የሰበር ፅንሰ ሀሳብን ለዓለም አስተዋውቃለች፡፡ በሀገራችንም በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህገ-መንግስት አንቀፅ 80 (3) (ሀ) መሰረት የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት መሰረታዊ በሆነ የህግ ስህተት ያለበትን ማናቸውንም የመጨረሻ ውሳኔ በሰበር ችሎት ለማረም የሚችል መሆኑ ተደንግጓል፡፡ በፌዴራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013 አንቀፅ 25(2) መሰረት በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ከአምስት ያላነሱ ዳኞች እንደሚያስችሉ ይደነግጋል፡፡

በአዋጅ ቁጥር 1234/2013 አንቀፅ 26(1) መሰረት በሰበር ሰሚ ችሎት አስቀድሞ የተሰጠ አስገዳጅ ውሳኔ ከሰባት ያላነሱ ዳኞች በሚሰየሙበት ሰበር ሰሚ ችሎት እንደገና እንዲታይ ለፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ማመልከት እንደሚቻል ይገልፃል፡፡ ይህም ሊሆን የሚችለው አምስት ዳኞች የተሰየሙበት የሰበር ችሎት በራሱ አነሳሽነት ወይም የሰበር ባለጉዳዮች የቀድሞው የሰበር ውሳኔ በሰባት ባላነሱ ዳኞች እንዲታይ ለፕሬዝዳንቱ ሲያመለክቱ ነው፡፡

እዚህ ላይ ሊነሳ የሚገባው ጥያቄ የቀድሞው የሰበር ውሳኔ በአምስቱ ዳኞች በሙሉ ድምፅ (Unanimously) ቢፀድቅ ከሰባት ያላነሱ ዳኞች በሌላ ጊዜ በሚታይበት ጊዜ በቀላል አብላጭ ድምፅ (Simple Majority) መፅደቁ ተገቢ ነውን ? እንደሚታወቀው ሁለት አይነት አብላጭ ድምጾች አሉ፡፡ እነዚህም ቀላል አብላጭ ድምፅ (Simple Majority) እና ፍፁማዊ አብላጭ ድምፅ (Absolute Majority) ናቸው፡፡

ቀላል አብላጭ ድምፅ (Simple Majority) ማለት ምልዕተ ጉባኤው ላይ ከተገኙ ዳኞች መካከል አብላጭ ድምጭ ማለት ነው፡፡ ለምሳሌ ሰባት ዳኞች በተሰየሙበት ሰበር ሰሚ ችሎት ቢያንስ 4 ዳኞችና ከደገፉት ማለት ነው፡፡ ይሄም ማለት 4 ለ 3 ወይም 5 ለ 2 ወይም 6 ለ 1 በሆነ ድምፅ ውሳኔው ድጋፍ ሲያገኝ ማለት ነው፡፡

ፍፁማዊ አብላጭ ድምፅ (Absolute Majority) ማለት ደግሞ ሊሰየሙ ከሚገባቸው ጠቅላላ ዳኞች መካከል ከግማሽ በላይ (50 +1) በውሳኔው ሲስማሙ ማለት ነው፡፡ ፍጹማዊ አብላጭ ድምፅ ለማስላት በችሎቱ ላይ በዛ ቢባል ሊሰየሙ የሚችሉ የዳኞች ቁጥር (Maximum number of judges) መታወቅ አለበት፡፡ ይሄም ማለት ከሰባት ባላነሱ ዳኞች የሚሰየመው የሰበር ችሎት ላይ በዛ ቢባል ሊሰየሙ የሚችሉት የመጨረሻው ዳኞች ቁጥር 13 ዳኞች ቢሆኑ ፍፁማዊ አብላጭ ድምፅ ሊኖር የሚችለው ከግማሽ በላይ ማለትም ቢያንስ በሰባት ዳኞች ውሳኔው ተቀባይነት ሲያገኝ ነው፡፡

ይሁን እንጂ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013 ላይ ከሰባት ባላነሱ ዳኞች በሚሰየም ችሎት የቀድሞው ውሳኔ ሊታይ እንደሚገባው ያስቀምጣል እንጂ በችሎቱ ላይ በዛ ቢባል ሊሰየሙ የሚችሉትን የመጨረሻ የዳኞች ቁጥር/ብዛት አያስቀምጥም፡፡ በሌላ አባል አዋጁ የሰበር ሰሚ ችሎቱን ምልዕተ ጉባኤ ቢያንስ ሰባት ናቸው ብሎ ከማስቀመጥ ውጭ በችሎቱ ላይ በዛ ቢባል ሊሰየሙ የሚችሉ የዳኞች ብዛት በአዋጁ ላይ አልተቀመጠም፡፡ ስለሆነም የህግ አውጭው ዓላማ ከፍጹማዊ አብላጫ ድምፅ ይልቅ በቀላል አብላጭ ድምፅ ውሳኔ እንዲሰጥ ማድረግ ነው፡፡ በተግባርም ደረጃ እየተሰራበት የሚገኘው በቀላል አብላጭ ድምፅ ነው፡፡

ነገር ግን እንደጸሀፊው እምነት በአምስት ዳኞች በሙሉ ድምፅ የተወሰነን የቀድሞ የሰበር ውሳኔ በሰባት ዳኞች እንደገና ሲታይ 4 ለ 3 ወይም 5 ለ 2 በሆነ ድምፅ መሻር አግባብነት የለውም፡፡ ምክንያቱም የቀድሞውን ውሳኔ የሰጠው ከ 5 ዳኞች የተውጣጣው ችሎት እና አዲሱን ውሳኔ የሰጠው ከሰባት ዳኞች የተውጣጣው ችሎት በስልጣን የማይበላለጡ አቻ የሰበር ሰሚ ችሎቶች ናቸው፡፡ በአምስቱ ዳኞች ችሎት እና በሰባቱ ዳኞች ችሎት መካከል ምንም አይነት የስልጣን ተዋረድ (Hierarchy) ልዩነት የለም ያለው የድምፅ ልዩነት ብቻ ነው፡፡ ስለሆነም አምስት ዳኞች በሙሉ ድምፅ ተስማምተው ያጸደቁትን ውሳኔ በሰባቱ ዳኞች ሊሻር የሚገባው ከአምስት በላይ በሆነ ድምፅ ነው፡፡ ለምሳሌ ከሰባቱ ዳኞች መካከል አራቱ በሙሉ ድምፅ የፀደቀውን የቀድሞው የሰበር ውሳኔ እንዲሻር ቢደግፉና 3ቱ ደግሞ እንዳይሻር ቢደግፉ 4 ለ 3 በሆነ ውጤት በ 5 ዳኞች ሙሉ ድምፅ የፀደቀው የቀደመው ውሳኔ ይሻራል፡፡ ያ ማለት በ 5 ዳኞች በሙሉ ድምፅ የፀደቀው የቀድሞው የሰበር ውሳኔ 4 ዳኞች በሰጡት ድምፅ እየተሻረ ነው፡፡ ባለ 5ቱም ሆነ ባለ 7ቱ የሰበር ሰሚ ችሎቶች እኩል ስልጣን ያላቸው የሰበር ሰሚ ችሎቶች ሁነው በ5 ድምፅ የፀደቀው የቀድሞው ውሳኔ ከአምስት ባነሰ ድምፅ እንዲሻር የምንፈቅድበት አሳማኝ የህግ የምክንያት የለም፡፡

በሌላ በኩል ከሰባት ዳኞች የተውጣጣው የሰበር ሰሚ ችሎት 5 ለ 2 በሆነ ድምፅ በ 5 ዳኞች በሙሉ ድምፅ የፀደቀውን የሰበር ውሳኔንም ሊሽረው አይገባም፡፡ እዚህ ላይ ከሰባቱ ዳኞች መካከል አምስቱ የቀድሞው የሰበር ውሳኔ ሊሻር ይገባዋል ቢሉም የቀድሞው የሰበር ውሳኔ በአምስት ዳኞች በሙሉ ድምፅ እስከፀደቀ ድረስ የሁለቱም ችሎቶች ድምፅ ባልተበላለጠበት ሁኔታ ከሰባት ዳኞች የተውጣጣው ችሎት በ5 ዳኞች በሙሉ ድምፅ የተሰጠውን ውሳኔ በእኩል ድምፅ የሚሽርበት የህግ ምክንያት የለም፡፡ ምክንያቱም በሁለቱ ችሎቶች መካከል ያለው ልዩነት የዳኞች ብዛትና ድምፅ ነው እንጂ የስልጣን ተዋረድ ልዩነት በሁለቱ ችሎቶች መካከል የለም፡፡ ካለበለዚያ ከሰባት ዳኞች የሚሰየመው የሰበር ችሎት ከአምስት ዳኞች ከሚሰየመው ሰበር ችሎት በስልጣን ይበልጣል ወደሚል የተሳሳተ ድምዳሜ ሊያስኬደን የሚችል ነው፡፡

በሌላ በኩል እነዚህ ከሰባት ያላነሱ የሰበር ዳኞች የሚሰጡት ውሳኔም በሌላ ጊዜ ከሰባት ባላነሱ ዳኞች በተሰየሙበት የሰበር ችሎት በተመሳሳይ ጭብጥ እንደገና ታይቶ ሌላ የህግ ትርጉም ሊሰጥበት እንደሚችልም በአዋጁ አንቀፅ 26(4) ላይ ተገልጿል፡፡ እዚህ ላይ ሊነሳ የሚገባው ጥያቄ ሰባት ዳኞች በሙሉ ድምፅ የሰጡት ውሳኔ በተመሳሳጭ ጭብጥ በሌላ ጊዜ በሰባት ዳኞች በሚታይበት ጊዜ በቀላል አብላጭ ድምፅ (Simple Majority) ሊፀድቅ ይገባዋልን? የሚለው ነው፡፡ ይሄም ከላይ እንዳየነው ተመሳሳይ የሆነ የመከራከሪያ ነጥብ ሊነሳበት የሚችል ሲሆን በሰባት ዳኞች ታምኖበት የፀደቀን ውሳኔ በሌላ ጊዜ በተመሳሳይ ጭብጥ 4 ለ 3 ወይም 5 ለ 2 ወይም 6 ለ 1 በሆነ ድምፅ ማፅደቅ ተገቢነት የለውም፡፡ በሰባት ዳኞች የፀደቀው የቀድሞው ውሳኔ ሊሻሻል ወይም ሊሻር የሚገባው ከሰባት በላይ በሆነ ድምፅ ነው፡፡ ምክንያቱም ችሎቶቹ እኩል ስልጣን

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

24 Jan, 12:24


የሰው ስጋን የከተፈው ተከሳሽ በሞት እንዲቀጣ ተወሰነበት
*
ፀሃዬ ቦጋለ በየነ የተባለ ተከሳሽ ከነሐሴ 27 ቀን 2014 ዓ.ም በግምት ከቀኑ 5፡00 እስከ ነሐሴ 28 ቀን 2014 ዓ.ም ከምሽቱ 12፡30 ድረስ ባለው ጊዜ በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 04 አርሴማ ፀበል አከባቢ ባለቤቱ የነበረችውን ሟች ወንበር ላይ ተቀምጣ እያለ ሳታየው ከኋላዋ በመምጣት በሊጥ ማዳመጫ ዱላ ማጅራትዋን በመምታት እራሷን እንድትስት ካደረገ በኋላ እዛው ትቷት ከቤት ወጥቶ በመሄድና ከተወሰነ ሰዓታት በኋላ ተመልሶ በመምጣት ሟች እራሷን ስታ ከወደቀችበት መሬት ለመሬት በመጎተት እቤት ውስጥ ወደሚገኘው መታጠቢያ ቤት በማስገባት አንድ እግሯን ከዳሌዋ ጀምሮ በመቁረጥና ሙሉ የእግሯን ስጋ አጥንቷ ባዶ እስኪሆን ድረስ መልምሎ በማውጣት ስጋዋን አድቅቆ በመክተፍና በመቆራረጥ ሽንት ቤት ውስጥ በመጨመር የቆረጠውን እግሯ ለሁለት በመስበርና በፌስታል በመቋጠር ፀጉሯን በመቀስ በመቁረጥ ቀሪ አስከሬንዋ ላይ ጨርቅና የተለያየ መዘፍዘፊያ በመጫን እዛው መታጠቢያ ቤት ውስጥ በማስቀመጥ እስከ 30/12/2014 ዓ.ም ድረስ ምንም እንዳልተፈጠረ እቤት ውስጥ እያደረ ከቆየ በኋላ ከ1/13/2014 ዓ.ም ጀምሮ እስከ 16/1/2015 ዓ.ም ድረስ ቤቱን ዘግቶ በመሰወሩ ምክንያት በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ምርመራ ተጣርቶ በፍትህ ሚኒስቴር የጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ዘርፍ በሴቶችና ህጻናት ላይ ሚፈፀሙ ወንጀሎች ዐቃቤ ሕግ ዳይሬክቶሬት በወ/ሕ/አ539/1/ሀ/ መሰረት በፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 2ኛ የሰው ግድያና ከባድ ውንብድና ወንጀል ችሎት ክስ ቀርቦበት ክርክር ሲደረግ ቆይቷል፡፡

በክርክሩ ሒደትም የዐቃቤ ሕግ ማስረጃ ከተሰማ በኋላ ተከሳሽ እንዲከላከል ብይን ቢሰጥም የመከላከያ ማስረጃ አቅርቦ የቀረበበትን ክስ ሊከላከል ባለመቻሉ ፍ/ቤቱ በተከሳሽ ላይ የጥፋተኛነት ፍርድ በመስጠት በዕድሜ ልክ ፅኑ እስራት እንዲቀጣ የወሰነ የነበረ ቢሆንም ዐቃቤ ሕግ ባቀረበው ይግባኝ መሰረት የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት የወሰነውን የእድሜ ልክ ጽኑ እስራት ውሳኔ በመሻር ተከሳሹ በሞት እንዲቀጣ ወስኖበታል፡፡

የፍትህ ሚኒስቴር

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

24 Jan, 09:21


Exciting Opportunity for Students!
ELSA is thrilled to announce the Second National Essay Competition! This year’s theme is: "Assessing the Impact of Technological Advancement on Legal Education in Ethiopia.”
Don’t miss the chance to showcase your ideas and win exciting prizes!
Check out the poster and guidelines for more details .
@Ethiopianlaw_s
@Ethiopianlaw_s
@Ethiopianlaw_s

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

23 Jan, 19:33


If you want to get different university school of law exam papers from 2nd year up to 5th year
Join👇
👇👇
@Lawschoolexampaper
@Lawschoolexampaper
@Lawschoolexampaper

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

23 Jan, 16:25


የፍ/ቤት ፕሬዝዳንት በእስራት ተቀጣ
---------------------------------------------
ስልጣንን ያለ አግባብ በመጠቀም እና የማይገባውን ጥቅም ለማግኘት ወንጀል በፈጸመ የፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ላይ የ6 ዓመት ጽኑ እስራትና በገንዘብ መቀጮ ቅጣት ማስተላለፉን የቤንች ሸኮ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ገለጸ።

በወንጀሉ ተባባሪ የነበረች ሌላ ግለሰብም የእስራትና የገንዘብ መቀጮ ቅጣት ማስተላለፉን ከፍተኛ ፍርድ ቤቱ ገልጿል።

የቤንች ሸኮ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት አቶ ቢኒያም ባቡ እንደተናገሩት አንደኛ ተከሳሽ አቶ ሙሉጌታ መሰረት እና 2ኛ ተከሳሽ ወይዘሮ ፈጠነች በዛብህ በፈጸሙት የሙስና ወንጀል የቅጣት ውሳኔ መተላለፉን ገልጸዋል።

አንደኛ ተከሳሽ አቶ ሙሉጌታ መሰረት የደቡብ ቤንች ወረዳ ፍርድ ቤት ዳኛና ፕሬዝዳንት ሆነው እየሰሩ በነበሩበት ወቅት ከሁለተኛ ተከሳሽ በፍርድ ቤቱ የግዥና ንብረት አስተዳደር ቡድን መሪና ቼክ ፈራሚ ሆና ከምትሰራው ከወይዘሮ ፈጠነች በዛብህ ጋር ለራሳቸውና ለሌሎች ሰዎች ጥቅም ለማስገኘት በማሰብ ለፍርድ ቤቱ ከተመደበው በጀት ውስጥ ከተቋሙ ስራ ጋር ለማይገናኝ አላማ የተቋሙ ሰራተኛ ላልሆኑ ነጋዴዎች በ2013 ዓ.ም 163ሺ ብር አበል ክፍያ ፈጽመዋል ብለዋል።

በዚሁ መዝገብ ግለሰቧ በ2014 ዓ.ም ለሌላ ነጋዴ 197ሺ 706 እንዲሁም በ2015 ዓ.ም 721ሺ 442 ብር ፣ በ2016 ዓ.ም 309ሺ 822 ብር ክፍያ እንዲፈጸም በማድረግ በድምሩ 1 ሚሊየን 361ሺ 768 ብር በአበል ክፍያ እንዲፈጸም አድርገዋል ብለዋል።

በዚህም ያለአግባብ ስልጠናቸውን በመጠቀም ወንጀሉ በሚሰጠው ሙሉ ፍሬ ተካፋይ ለተቆሙ የተመደበውን በጀት ለታለመለት አላማ እንዳይውል ማድረጋቸው በሰውና በሰነድ ማስረጃ ተረጋግጧል ብለዋል።

በዚህም የቤንች ሸኮ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ከዐቃቤ ህግ በቀረበለት መዝገብ ላይ ግራ ቀኙን ሲያከራክር ቆይቶ በትላንትናው ዕለት የቅጣት ውሳኔና ፍርድ ሰጥቷል ብለዋል። በዚህም አንደኛ ተከሳሽ እጃቸው ከተያዘበት ከቀን 27/05/2016 ዓ.ም ጀምሮ በሚታሰብ የ6 ዓመት ጽኑ እስራትና የ7ሺ 500 ብር መቀጮ እንዲቀጡ ወስኗል ብለዋል።

2ኛ ተከሳሽ እጃቸው ከተያዘበት ከቀን 27/05/2016 ዓ.ም ጀምሮ የሚቆጠር በ5 ዓመት ከ6 ወር ጽኑ እስራትና በ5ሺ 500 ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ ፍርድ የተሰጠ ሲሆን አንደኛና ሁለተኛ ተከሳሽ በጋራ ያጎደሉትን 1ሚሊየን 345ሺ 320 ብር በጋራ እንዲከፍሉ የተወሰነ ሲሆን 2ኛ ተከሳሽ በግል በኦዲት የተገኘባቸውን ተጨማሪ 16ሺ ብር 448 ብር እንድትመልስ ውሳኔ መሰጠቱን ገልጸዋል።

አቶ ቢኒያም በመጨረሻም በዞኑ የተለያዩ አካባቢዎች የሙስና ወንጀሎች አይነትና የመፈጸሚያ ስልቶቹ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተበራከቱ መምጣታቸውን ገልጸው ህዝቡ ሙስናን በመፀየፍና ተፈጽሞ ሲገኝ ጥቆማ በምስጠት የዜግነት ግዴታውን ሊወጣ ይገባል ብለዋል።

Join us 👇
@Ethiopianlaw_s
@Ethiopianlaw_s

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

22 Jan, 17:18


ለህግ ባለሙያው የፍቅር ደብዳቤ የተሰጠ መልስ(Statement of defense )

ውድ የህግ ባለሙያው፡የፃፍክልኝን የፍቅር ደብዳቤ ከሽብር አዋጁ ባልተናነሰ ደም ፍላትውስጥ ሆኜ አነበብኩት፡፡ በእውነቱ በወስላታነትና በስግብግብነት
ተነሳስተህ ደብዳቤውን በመፃፍህ ልቤን እንዳከብድብህና የፍቅር ጥያቄህንም በብይን እንድዘጋው አስገድዶኛል፡፡ ደግሞም ባለፈው
ቅዳሜ ይህንን ውሳኔዬን አሳውቄሃለሁ፡፡ አሁን ድጋሜ ዳኝነት የጠየቅክበት ምክንያት አልገባኝም፡፡ የቅን ልቦና አፍቃሪ (lover in good faith) አይደለህም፡፡ በኔ ውሳኔ ተነስተህ ሴቶችን በሙሉ አጠቃለህ መዝለፍህ hasty generalization ሆነብህ፡፡ ድሮም ንግግር ከማያውቅ ወንድ የሚጠበቅ ነው፡፡ ቢሆንም ንግግርን አለማወቅ ይቅርታ አያሰጥም (ignorance of speech is no pardon)፡፡ ሲጀመር አለባበስህ ተማሪ እንደገነጣጠለው የጀስቲስ ማቴሪያል የተዝረከረከ ነው፡፡ እንደ 'ፍርድ' ዓ/ነገር የረዘመ ቁመና ቢኖርህም ልብህ ግን እንደ 'ትዕዛዝ' ያጠረ ነው፡፡ እንደ ግራቨን ፅሁፍ የቀጨጩ ልም አይኖችህን ሳያቸው ያቅለሸልሹኛል፡፡ ካንተም ብሶ እንደ ዙፋን ችሎት ታካብዳለህ!? አመለካከትህ ጭብጥ እንደሌለው መዝገብ የተምታታ ነው፡፡ ወሬህ አይጨበጥም፡፡ እንደ ዳብል ራንቯ ዶክትሪን (double renvoi doctrine) አንዴ እዚያ አንዴ እዚህ ትረግጣለህ፡፡ ልብህና አንደበትህ እንደ አማርኛውና እንግሊዝኛው የህግ ቅጅ (version) የተለያዩ ናቸው፡፡ ሀሣብህ እንደ ቀሽም ዐቃቤ-ህግ ጥያቄ እርባና ቢስ ነው፡፡ "በቸልተኝነት የሚፈፀም አስገድዶ መድፈር ልፈፅምብሽ ነበር" ያልከውን ፅሁፍህን ሳነበው ክርክሩን እንዳሸነፈ ጠበቃ ብቻየን እንባዬ እስኪወርድ ሳቅሁ፡፡ ሞክረኸኝ በሆነ! ታስቦ በሚፈፀም ከባድ የአካል ጉዳት ጥርስህን አርግፌህ አንድ ጥርስህ በኤግዚቢትነት ተተክሎ ታዬው ነበር፡፡ ደግሞ የገረምከኝ "ላንቺ ያለኝን ፍቅር ከምክንያታዊ ጥርጣሬ በላይ (beyond reasonable doubt) ላስረዳሽ ሞክሬአለሁ ማለትህ ነው፡፡ፅድቁ ቀርቶ በወጉ በኮነነኝ አሉ! 'ከምክንያታዊ ጥርጣሬ በላይ' የሚል ከንቱ ቅዠትህ ቀርቶ 'በበቂ ሁኔታ' (sufficient evidence) ብታቀርብልኝ እንኳ አልገፋህም ነበር፡፡ ዳሩ ምን ዋጋ አለው:: ፍቅርህን የማስረዳት ሸክሙ (burden of proof) ያንተ ቢሆንም የምታቀርበው መከራከሪያ ሁሉ ባዶ የድምፅ ብክለት (noise pollution) ሆነብኝ፡፡ በእርግጥ በፍቅርሽ ተማረክሁ ያለኝን (prisoner of war (POW)) እንዲጎሳቆል የምወድ አረመኔ አይደለሁም፡፡ ብታበሳጨኝም ታሳዝነኛለህ፡፡ ነገር ግን እንደ
ህገመንግስቱ አንቀፅ 39 ባዶ ተስፋ ልሰጥህም አልፈልግም፡፡አንተና እኔ እንደ አገራችን ህግ (the law) እና አሰራር (the practice) ፍፁም የተለያየን ሰዎች ነን፡፡ የምፈልገውን ልትሰጠኝ አትችልም፡፡ ፍቅር ደግሞ ሰጥቶ መቀበል (quid pro quo relationship) እንጅ የበጎ አድራጎት ስራ (pro bono service) አይደለም፡፡ አንደ አስጠቂ ምስክር አልከኝ? ህ! አንተማ እንደ መሀይም መርማሪ ፖሊስ ያንተን ሀሳብ መልሼ እንዳስተጋባልህ ነበር የፈለከው፡፡ አያያዝህ እንደ crime control model ያስጨንቃል፡፡ እያደረስክብኝ ያለው ስነ-ልቦናዊ ጫና (undue influence) ምስኪኑን ሚራንዳ የሆንኩ ያህል እንዲሰማኝ አድርጎኛል፡፡ ወዳጄ! እንኳን ፍቅር ውልም በነፃነት ሲሆን ነው የሚፀናው፡፡ ግግም ብሎ ማፍቀር aquisitive prescription የሚሰጥህ መስሎህ ከሆነ ተሳስተሃል፡፡ ሽህ አመት ብታፈቅረኝም እኔ ያንተ ልሆን አልችልም፡፡ በጊዜ ዘወር ብትል ይሻልሃል፡፡ካለበለዚያ በነጭ ድሀ ላይ እንዳስፈረደ የፍርድ ባለገንዘብ (judgment creditor) አይን አይን ስታይ መኖርህ ነው፡፡ ወደድኩ ብለህ ስትንቀዋለል ባለቤት አልባ (res nullies) ሆነህ እንዳትቀር ተጠንቀቅ፡፡ አካሄድህ ሁሉ ለዩኒቨርስቲ ሴት አይመጥንም፡፡ ልብህን ወደ ሀይስኩል ችኮች ሪማንድ (remand)ብታደርገው የተሻለ ነው፡፡ ለኔ የምትቀባጥረውን ፍቅር ግን void
abinitio ብየዋለሁ፡፡ ወዳጄ! አንድ ነገር ልንገርህ! እንደ intrinsic element በቂጥ በቂጤ አትከተለኝ፡፡ በቃ አታናግረኝ፡፡ከኔ ጋር ለመነጋገር locus standi እንደሌለህ ልታውቅ ይገባሃል፡፡ አድብቶ መንከስ (wait and bite) አልወድም፡፡ቀድሜ ማስጠንቀቂያ (notice) ልስጥህ፡፡ ከዛሬ ጀምሮ ባጠገቤ ብትደርስ እንደ አገራችን ፌደራሊዝም (centrifugal federalism) እንደምበታትንህ እወቅ፡፡ ላንተ እበቃሃለሁ፡፡የሶስተኛ ወገን ጣልቃገብነት (third party intervention) አያስፈልገኝም፡፡ ዋ!!! ይሄ ውሳኔ የመጨረሻ ነው፡፡ ይግባኝ የለውም፡፡ መዝገቡ ተዘግቷል ወደ መዝገብ ቤት ይመለስ!የማይነበብ ፊርማ አለበት፡፡
Just for fun😁
Join us 👇
@Ethiopianlaw_s
@Ethiopianlaw_s

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

21 Jan, 13:13


አዲሱ የፌደራል መንግስት ሰራተኞች አዋጅ ቁጥር 1335/2017

Federal Civil Servants Proclamation Number 1335-2025

https://t.me/Ethiopianlaw_s

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

19 Jan, 04:36


እንኳን ለጌታችን ለመድሀኒታችን
ለኢየሱስ ክርስቶስ
የጥምቀት በዓል
በሰላም አደረሳችሁ!!

#የኢትዮጵያ_ሕግ❤️‍🔥

@Ethiopianlaw_s
     

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

17 Jan, 17:08


ነፃ የህግ ድጋፍ 0961103179
⚖️ Law vs practice ⚖️.
ነፃ የህግ የማማከር አገልግሎት፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጆች፣ ደንቦች፣ መመሪያዎች፣ የውል ፎርሞች፤ መፅሐፍቶች : አጫጭር ኖቶች እዚሁ ያገኛሉ። Here on our channel, we provide Free legal Aid.

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

17 Jan, 16:54


የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የጣሪያ ግድግዳ/የንብረት ግብር ብሎ ከከተማዋ ነዋሪ እየሰበበሰበ ያለው ግብር ሕገ ወጥ ነው በሚል የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ወሰነ!!!

***

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የጣሪያ ግድግዳ/የንብረት ግብር ብሎ ከከተማዋ ነዋሪ እየሰበበሰበ ያለው ግብር "ሕገ ወጥ መኾኑን" በመግለጽ እናት ፓርቲ ክስ መመሥረቱን አስታዉሶ ክሱን የተመለከተው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ አስተዳደር ችሎት ዛሬ ጥር 9ቀን  2017 ዓ.ም.ባስቻለው ችሎት የንብረት ግብር ማሻሻያ ጥናት ተብሎ ሚያዝያ 3ቀን 2015 ዓ.ም. የወጣውና "ለግብሩ መሰብሰብ መሠረት የሆነው መመሪያ ተፈጻሚነት ሊኖረው አይገባም" ተብሎ መመሪያው እንዲሻር በሙሉ ድምጽ ወስኖልኛል ሲል በማህበራዊ ገፁ አስታውቋል::

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

17 Jan, 10:26


Vacancy Alert!

Human Rights Officer, Monitoring and Investigation
Samara, Ethiopia

Human Rights Officer, Human Rights Education
Addis Ababa, Ethiopia

Project Development & Resource Mobilization Officer
Addis Ababa, Ethiopia



Apply via - https://ehrc.org/jobs/

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

15 Jan, 18:10


የህግ ባለሙያው የፍቅር ደብዳቤ
ይድረስ የልቤ ሉአላዊ ስልጣን ባለቤት ለሆንሽው ለምወድሽና ለማፈቅርሽ!
ባንቺ ይሁንታ ብቻ የምኖረው የህግ ባለሙያው አፍቃሪሽ ነኝ፡፡ ደጋግሜ ልገልፅልሽ እንደሞከርኩት ልቤን በsingular title ከወረስሽው ይሄው ግንቦት ሀያ ሲመጣ አመት ሊሞላኝ ነው፡፡ መጀመሪያ ልተዋወቅሽ ስሞክር ግልምጫ በምትይው የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ (preliminary objection) የትውውቅ ሙከራየን ውድቅ ልታደርጊብኝ ከሞከርሽበት ቀን ጀምሮ ፍቅርሽ በልቤ ንውፅውፅታ ፈጥሮብኛል፡፡ እንደ civil procedure code ሸንቀጥ ያለው ቁመናሽ፣ እንደ employment proclamation አንቀፆች በጥንቃቄ የተሞላው ሰበር ሰካ አረማመድሽ፣ እንደ civil code የነጡ በረዶ ጥርሶችሽ፣ ቀዩን ህገ-መንግሥት የመሠለው ሮማን ከንፈርሽ፣ የዳኞችን ጥቁር ጋዎን የመሠለው ሀር ፀጉርሽ፣ እንደመዶሻ እጀታ የተመዘዘው መቃ አንገትሽ ተባብረው እንደ አልሸባብ ሰላሜን አሣጡኝ፡፡ የመበርበርያ ትዕዛዝ (search warrant) ሳይኖርሽ የልቤን በር ከፍተሽ ገባሽ (ያውም 12:00 ካለፈ በሗላ)፡፡ ባንቺ ምክንያት እንደ land proclamation ክፍተቴ በዝቶ በቀላሉ ሆድ ይብሰኛል፡፡ በየቀኑ እየከሳሁና እየኮሰመንኩ የcriminal procedure code መስየልሻለሁ፡፡ ለፍቅርሽ ስል የት ልሂድ? የትም ብሄድ ፍቅርሽ extradite አድርጎ እንደሚመልሰኝ አልጠራጠርም፡፡ ውዴ! ባለፈው ቅዳሜ ባደረግነው oral litigation ላንቺ ያለኝን ልባዊ ፍቅር ከምክንያታዊ ጥርጣሬ በላይ (beyond reasonable doubt) ላስረዳሽ ሞክሬአለሁ፡፡ አንቺ ግን እንደ አስጠቂ ምስክር ያወቅሽውን ሁሉ ካድሽኝ፡፡ በዚህም በጣም ስለተበሳጨሁ በቸልተኝነት የሚፈፀም የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ልፈፅምብሽ ነበር፡፡ ያ ነገር በቸልተኝነት እንደማይፈፀም ትዝ ሲለኝ ተውኩት፡፡ the right to be heard የሚለው ህገ-መንግሥታዊ መርህ ባንቺ ዘንድ ቦታ እንደሌለው አስተውያለሁ፡፡ እንደ 1931ዱ ህገ-መንግስት ራስሽን የመካብ አባዜ ተጠናውቶሻል፡፡ የሆድ የሆዴን ሳወራሽ appeal to pitty fallacy ነው እያልሽ ታሸማቅቂኛለሽ፡፡ ነገር ግን ሴቶችን ስሜታቸውን በሚቀሰቅሰው appeal to pitty እና appeal to people (ad hominium fallacy) ካልሆነ በስተቀር በinductive እና deductive reasoning ማሳመን የማይሞከር እንደሆነ አልተሰወረብኝም፡፡ ውዴ! ምነው እንደ ፍትሐ-ብሄር ሕጉ አቋምሽን ማሻሻል ተሳነሽ? ከሕገ-መንግስቱ የማሻሻያ አንቀፆች (አንቀፅ 104 እና 105) የበለጠ ግትር ሆንሽብኝ፡፡ አንዳንዴ ሕገ-መንግስቱን መቀበልሽ እንኳ ያጠራጥረኛል፡፡ ምነው እንደ ሰበር ችሎት (cassation bench) ገደብሽን አለፍሽ?? ሴቶች እኔንና ፖለቲካን ለምን እንደምትጠሉን አይገባኝም፡፡ ተስፋ የጣልኩብሽ አንቺ እንኳን ለፍቅር አቤቱታዬ የሰጠሽኝ መልስ ሁከት ይወገድልኝ ብቻ ሆነ፡፡ የኔ ቆንጆ! ጥያቄየ እንደ ስልጤ ህዝበሸ ጥያቄ ውስብስብ አይመስለኝም፡፡ ታዲያ ምነው እንደወ/ሮ ከዲጃ በሽር አንዴ እምቢ አንዴ እሺ እያልሽ አስቸገርሽኝ? በነገራችን ላይ ውዴ....... ሴቶች ግን እንደ tax proclam ወሬያችሁ ሁሉ ስለገንዘብ የሆነው ለምንድነው? ሁልጊዜ ገቢ መሰብሰብ ብቻ? አንዳንዴማ ከinsurance እነ ጡረታ አዋጆችም ስለመስጠት ትንሽ ተማሩ እንጅ፡፡ ኤጭ! አንዳንዶቻችሁማ እንደወንጀል ሕጉ አሸማቃቂ፣ እንደ tax authority ሆዳሞች፣ እንደ civil code ወሬኞችና ነገር አራዛሚዎች፣ እንደ ፀረ-ሽብር ሕጉ ቁጡና ግልፍተኞች ናችሁ፡፡ በዚያ ላይ እንደ ሊዝ አዋጁ የከፈለ ሁሉ የሚከራያቸው ብዙ አሉ፡፡ አንዳንዶቹ ደግሞ  ፀባያቸው እንደ commercial code ይደብራል፡፡ በእርግጥ አንቺ በፍቅር ላይ እንደ immoviable property ሽያጭ ጥብቅና የተለየ መርህ እንደምትከተይ አውቃለሁ፡፡ የሆነ ሆኖ ህይዎቴን እንደ united nations charter አንቀፆች በምትፈልጊው መንገድ እያጣመምሽ እየመራሻት ነው፡፡ ከአፍሪካ human rights charter ጋር ያላቹህን ግንኙነት ባላውቅም አንድ ነገር ግን ያመሣሥላቹሃል፡፡ ሁለታችሁም አሳይቶ መንሳት (claw back) ታበዛላችሁ፡፡ መጀመሪያ ላይ ጥሩ ተስፋ ትሰጡና ቀጥላችሁ ደግሞ ሆኖም ግን፡ ቢሆንም እንኳ፡ ነገር ግን፡ ምናምን እያላችሁ የሰጣችሁትን ተስፋ መልሳችሁ አፈር ታስግጡታላችሁ፡፡ ውዴ........ ፍቅሬን renounce ካደረግሽው ሌላ ወራሽ ስለሌለኝ በ escheat መርህ መሠረት ፍቅሬ ለመንግሥት ገቢ ይሆናል፡፡ ማለትም ላንቺ የነበረኝን ፍቅር ወደ ሀገር ፍቅር እቀይረዋለሁ፡፡ ይሄ ከመሆኑ በፊት ግን ፍቅራችን እነደ evidence ህጋችን በ draft እንዳይቀር ወይም እንደ ደርግ ህገ-መንግስት እድሜው እንዳያጥር የበኩልሽን አድርጊ፡፡ እኔ እንደሆንኩ እነደ gap filling provision ሳይሆን እንደ mandatory rule አክብሬ እይዝሻለሁ፡፡ ከሃሳብሽ intentionallyም ይሁን neglligently አላፈነግጥም፡፡ pacta sunt servanda!
ልዩነታችን እንደ common law እና civil law legal system የሰፋ ቢሆንም በ convergence እንደሚጠብ ተስፋ አለኝ፡፡ እስከዚያው የሲቪል ኮዱን ዝና፡ የክሪሚናል ኮዱን ግርማ ሞገስ፡ የህገመንግስቱን የበላይነት፡ የፋሚሊ ኮዱን ቁንጅና እመኝልሻለሁ፡፡
የፍቅር መዝገቡም ለጊዜው ተዘግቷል!
(የማይነበብ የአፍቃሪው ፊርማ አለበት)
©Uploaded by J.S.O
Join💫
@Ethiopianlaw_s
@Ethiopianlaw_s

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

14 Jan, 15:05


ምክር ቤቱ የሁለት የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኞችን የስንብት ውሳኔን አጸደቀ
--------------------
( ዜና ፓርላማ ) ጥር 06 ፣ 2017 ዓ.ም.፤ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 15ኛ መደበኛ ጉባዔው የሁለት የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኞች የስንብት ውሳኔን አጽድቋል፡፡

የስንብት ውሳኔውን ሪፖርት እና የውሳኔ ሃሳብ የሕግና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የተከበሩ ወ/ሮ እጸ-ገነት መንግስቱ አቅርበዋል፡፡

ዳኛ አዱኛ ነጋሳ እና ዳኛ አክሊሉ ዘሪሁን የተጣለባቸውን ሕዝባዊ ኃላፊነት ባለመወጣት ከባድ የዲሲፕሊን ጥፋት መፈጸማቸውን ወ/ሮ እጸ-ገነት አብራርተዋል፡፡

የተሰጣቸውን ሹመት አላግባብ በመጠቀም፣ ዳኛ አዱኛ ነጋሳ ገንዘብ እና ቼክ በመቀበል ፤ ዳኛ አክሊሉ ዘሪሁን የአስር ሚሊዮን ብር ቼክ በመቀበል ከባድ የዲሲፕሊን ቅጣት መፈጸማቸውን ሰብሳቢዋ ጠቅሰዋል፡፡

ጉዳዩን አስመልክቶ ቋሚ ኮሚቴው ከፌዴራል ዳኞች አስተዳደር ጉባኤ ጋር በጥልቀት እንደመከረበት ወ/ሮ እጸ-ገነት ተናግረው ፣ ውሳኔውን ምክር ቤቱ እንዲያጸድቅላቸው ጠይቀዋል፡፡

ውሳኔውን በተመለከተ የምክር ቤት አባላት አስተያየቶችን የሰነዘሩ ሲሆን፣ “ቅጣቱ አስተማሪ አይደለም፤ አስተማሪ የሕግ ተጠያቂነት ሊረጋገጥ ይገባል ፤ ወደ መረጠን ሕዝብ ስንሄድ አገልግሎት እና ፍትህ የምናገኘው በገንዘብ ነው ስለሚሉን ውሳኔው ተገቢ ነው” ብለዋል፡፡

በአንጻሩ፣ “ቋሚ ኮሚቴው ዳኞቹ ከመሰናበታቸው አስቀድሞ የፌዴራሉን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ውሳኔ ማዳመጥ ይገበዋል፤ የፌዴራል ዳኞች አስተዳደር ጉባኤን ውሳኔ እንደ ምስክር ተጠቅሞ ዳኞችን ከስራ ማሰናበት የዳኞቹን መብት ይጋፋል” የሚሉ አስተያየቶች ቀርበዋል፡፡

በተነሱት ጥያቄዎች እና አስተያየቶች ምላሽ እና ማብራሪያ ከቀረበ በኋላ ውሳኔው ውሳኔው ውሳኔ ሃሳብ ቁጥር 5/2017 ሆኖ በሁለት ድምጸ-ተኣቅቦ እና በአብላጫ ድምጽ ጸድቋል፡፡

በመጨረሻም፣ ምክር ቤቱ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሀን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር  ሹመትን አጽድቋል፡፡

ምክር ቤቱ፣ ሳምሶን መኮንንን (ዶ/ር) የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሀን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አድርጎ  በአንድ ድምጸ-ተአቅቦ እና በአብላጭ ድምጽ አጽድቋል፡፡

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

13 Jan, 09:15


VACANCY POSTS

For Fresh & Exp🎴Enat Bank SC


▪️Job Position 1 - Human Capital Management Officer
▪️Job Position 2 - Junior Attorney
▪️Job Position 3 - Administrative Assistant
▪️Find More Details here
          💧💧💧💧
https://kebenajobs.com/job/enat-bank-sc-jan-13-25/

➭Deadline: January 17,2025

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

10 Nov, 17:58


በሌላ ሰው ገንዘብ በራስ ስም ቤት ስለመግዛት
--------------------
ከሳሽ ተከሳሽ በኃይል የያዘብኝን ቤትና ቦታ ለቆ እንዲወጣ ይወሰንልኝ የሚል ክስ ሲያቀርብ ሊለቅልኝ ይገባል የሚልበት ምክንያት በተከሳሽ ስም ቢገዛም የከሳሽ ነዉ በሚል ከገለጸ ከሳሽ ከቤቱ ጋር በተያያዘ መብትና ጥቅም ያለዉ መሆኑን በግልጽ በሚያሳይ ሁኔታ የቀረበ መሆኑን የሚያሳይ ነዉ። ተከሳሽ ከሳሽ ምንም ዓይነት የባለሀብትነትም ሆነ የባለይዞታነት መብት ባይኖራቸዉ ያቀረበዉ ክስ ነዉ በሚል ያሚያቀርበዉ መቃወሚያ ከሳሽ በእርግጥ በቤቱ ላይ መብት ያለዉ መሆን ያለመሆኑ በክርክር ሂደት ተጣርቶ እልባት ሊሰጥበት የሚገባ ጉዳይ ነዉ ከሚባል በስተቀር ከሳሽ ክሱን ለማቅረብ መብትና ጥቅም የለዉም ወደሚል ድምዳሜ የሚያደርስ ባለመሆኑ ከመነሻዉም በመጀመሪያ መቃወሚያነት ሊቀርብ የሚገባዉ አይደለም።
ሰ/መ/ቁ 216702 ሚያዚያ 26 ቀን 2014 ዓም የተወሰነ
source:- Minda Girma Law Office

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

10 Nov, 16:07


ለብድር ውል ዋስትና ይሆን ዘንድ የማይንቀሳቀስ ንብረት በመያዣነት ሲሰጥ: የመያዣ ውሉ ከተፃፈበት ቀን አንስቶ የማይንቀሳቀሰው ንብረት በሚገኝበት አድራሻ ባለው በማይንቀሳቀስ ንብረት መዝገብ ካልተፃፈ በቀር ምንም አይነት ውጤት የማያስገኝ ስለመሆኑ የፍ/ብ/ህ/ቁ. 3052, 3053, በመጥቀስ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመዝገብ ቁጥር 33295 ቅጽ (7) ላይ አስገዳጅ ውሳኔ ሰጥቷል፡፡

ስለሆነም ይህን የማይንቀሳቀስ ንብረት መያዣ ውል ለመገልገል ብሎም በሕግ ፊት ውጤት እንዲኖረው ተጠቃሚው በሚመለከተው የመሬት አስተዳደር አካል ውሉን ማስመዝገብ ይጠበቅበታል::
Join 👇
@Ethiopianlaw_s
@Ethiopianlaw_s

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

10 Nov, 06:56


የቀጠለ👇👆
ይህ ብቻ ሳይሆን የአንዳንድ ሁነቶች መፈጠር ኑዛዜ ፈራሽ እንዲሆን ሊያደርግ ይችላል፡፡ ይኸውም፡-
የልጅ መወለድ
ኑዛዜ ያደረገ ሰው ከኑዛዜው በኋላ ሌላ ልጅ ቢወልድ እና ልጁ ውርስ ለመቀበል ፈቃደኛ ከሆነ ተቃራኒ ቃል ቢኖር እንኳን ኑዛዜው ፈራሽ ይሆናል፡፡ ሆኖም ተናዛዡ ልጅ መወለዱን ቢያውቅም ኖሮ ስጦታውን አያስቀርም ተብሎ የሚገመት ከሆነ ዳኞች በኑዛዜ የተሰጡት ስጦታዎች በከፊል ወይም በሙሉ እንዲፀኑ ማድረግ የሚችሉ ቢሆንም ልጁ የሚያገኘው ግን በማናቸውም ምክንያት እጅግ ቢያንስ ከሀብቱ ሶስት ሩብ ማነስ የለበትም የፍትሐ ብሔር ሕግ አንቀጽ 904&905፡፡
ሶስት ሩብ ማለት ምን ማለት ነው?
ከኑዛዜ በኋላ የተወለደ ልጅ የሚያገኘውን የውርስ ድርሻ በተመለከተ የፍትሐብሔር ህጉ በአማርኛ ቅጂው ግልፅነት ይጎድለዋል፡፡ አማርኛው ከውርሱ ሀብት ሶስት ሩብ በሚል ሲያስቀምጥ እንግሊዝኛው “three fourths of the share which he would receive in the intestate succession” ማለትም ውርሱ ያለኑዛዜ ቢሆን ያገኝ ከነበረው ሶስት አራተኛ ማነስ እንደሌለበት ይደነግጋል፡፡ ስለዚህ ሶስት አራተኛ ከጠቅላላ ውርሱ መሆኑን መረዳት ያሻል፡፡
➢ የጋብቻ መፍረስ የፍትሐ ብሔር ሕግ አንቀጽ 906
ለባል ወይም ለሚስት ጥቅም ተብሎ በኑዛዜ ተካቶ ከሆነ ጋብቻው በሞት ሳይሆን በሌላ ምክንያት ከፈረሰ ኑዛዜው ውድቅ ይሆናል፡፡👇ምሳሌ
አቶ አባተ እና ወ/ሮ ይመኙሻል ለ10 አመታት በጋብቻ ኖረዋል፡፡ በተጋቡ በ8ኛ አመት አቶ አባተ ኑዛዜ ሲያደርጉ ከጋራ ንብረታቸው ላይ ከእርሳቸው ድርሻ ግማሹ ለባለቤታቸው እንዲሆን ይናዘዛሉ፡፡ ሆኖም በ10ኛ አመት አቶ አባተ እና ወ/ሮ ይመኙሻል በመሀላቸው በተፈጠረ አለመግባባት በፍቺ ይለያያሉ፡፡ የተለያዩት በፍቺ በመሆኑ ለወ/ሮ ይመኙሻል የተደረገው የኑዛዜ ስጦታ ውድቅ ሆኗል ማለት ነው፡
Join us👇
@Ethiopianlaw_s

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

09 Nov, 11:10


የመንደር ውሎች በሕግ ፊት ተቀባይነታቸው ምን ያህል ነው? ውል የሚጸናው ምን ሲሟላ ነው ?

አራት ነገር ካልተሟላ ውል አይጸናም ።

1ኛ• ፈቃድ (Consent) ነው። ተዋዋዩ ፈቃዱን የሰጠው ወዶና ፈቅዶ በማያሻማ ሁኔታ መሆን ይኖርበታል። ምን ማለት ነው ይሄ፣ በመታለል/በማታለል የተፈጸመ ውል ዋጋ አይሰጠውም።

2ኛ• ተዋዋዮቹ በሕግ 'ችሎታ ያላቸው' መሆን አለባቸው። 'ችሎታ' የሕግ ትርጉሙ ሁለት ነው። የተዋዋዮች ዕድሜ ከ18 ዓመት በላይ መሆን እና የአእምሮ ጤና ነው።

3ኛ• የውሉ ዋና ጉዳይ በሕግ የሚፈጸም መሆን አለበት። ለምሳሌ ባዶ መሬት መሸጥ አይቻልም። ስለዚህ የባዶ መሬት ሽያጭ ውል ቢደረግም በፍርድ ቤት ውድቅ ነው።

4ኛ• የውል አቀራረጽ ወይም ፎርም ነው። ይህም ማለት ለምሳሌ ለማይንቀሳቀስ ንብረት ሲሸጥ 2 ምስክሮች መኖራቸው፣ በውል አዋዋይ ፊት መረጋገጥ፣ ሕጉ ያስቀመጣቸው ዝርዝሮች ሟሟላት።

◼️ የመንደር ውል ሕጋዊ ነው ?

የማይንቀሳቀሱ ንብረቶች፣ ማለትም ቤትና መሬት በርካታ ሰዎች በመንደር ውል የሚሻሻጡ ቢሆንም በርካታ ሰዎች ተግባሩን ስላደረጉት ግን ሕጋዊ አያሰኘውም። ይህ የመንደር ውል በሕግ ተቀባይነት የማይኖረው የሰነድ ማረጋገጥ ዋና ዓላማን የሚጥስ መሆኑ ነው ።

◾️ሰነድ ለምን ይረጋገጣል? ባይረጋገጥስ ምን ችግር አለው ?

አንደኛ በተዋዋዮቹ መካከል ያለውን ግንኙነት ለመግዛት ነው። ሁለተኛው ምክንያት ደግሞ ሦስተኛ ወገን ለሚያነሳው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ነው። ሦስተኛ ወገን የሚባሉት እነማን ናቸው ያልን እንደሁ፣ ከገዥና ሻጭ ውጪ ያሉ የትኛውንም ወገኖችን ያካትታል። ለምሳሌ የመንግሥት አካል፣ የክፍለ ከተማ መሬት አስተዳደር፣ ባንክ፣ ለምሳሌ ሽያጩ ይፍረስልኝ የምትል/የሚል ሚስት/ባል . . . ወዘተ እነዚህ ሁሉ 3ኛ ወገን ይባላሉ።

ከእነዚህ አካላት አንዱ፣ እንበልና በመንደር ውል በተፈጸመ ንብረት ላይ ጥያቄ ቢያነሱ ሙግቱን ያለምንም እሰጥ አገባ አሸነፉ ማለት ነው። በመንደር ውል ቤት የገዛ ሰው ቀለጠ ማለት ነው። በአጭሩ ውል የሚረጋገጥበት ዋንኛ ዓላማ ሦስተኛ ወገኖች ለሚያነሱት ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ነው። "የመንደር ውል ችግሩም ይሄ ነው።

እርግጥ ውል በሰነዶች ሲረጋገጥ መንግሥት ቴምብር ያሳርፍበታል። ገቢ ያገኛል። ገዥና ሻጭ ሰነዱን ይዘው ክፍለ ከተማ ሲሄዱ የመንግሥት አካል ቀረጥ ይጥላል። ከዚያም ገቢ ይገኛል። ተዋዋዮች ሕጋዊ ሰነድ ይዘው ስለቀረቡ፣ ሕጋዊ አገልግሎት አግኝተው የስም ማዞርያ አሹራ ይከፍላሉ። ይህም ሌላ ገቢ ነው። ለዚህም ነው ውሉ በሕጉ ላይ የተቀመጠውን ፎርም ስላሟላ እንደ ሕጋዊ ውል ተቆጥሮ ተፈጻሚነት የሚኖረው።

◼️ተፈጻሚነት ይኖረዋል ማለት ግን ምን ማለት ነው ?

በአጭሩ ለምሳሌ ሻጭ ለገዢ ስም አላዞርልህም ቢል ፍርድ ቤት ከሶ በግዴታ ስም እንዲያዞር፣ ገዥ ላይ ለደረሰው ኪሳራም ካሳ እንዲያገኝ ይሆናል ማለት ነው። ይህን ዕድል ግን በመንደር ውሎች ላይ ለማሳካት አስቸጋሪ ይሆናል።

◼️በመንደር ውል የተሸጠ ንብረት እጣ ፈንታው ምንድነው ?

በፍርድ ቤት ቀርቦ ያልተመዘገበ ውል፣ ወይም በውል አዋዋዮች ፊት ያልተረጋገጠ የመንደር ውል እንደ ሕጋዊ ተቆጥሮ አፈጻጸም ሊቀርብበት አይችልም። በዚህ ላይ ምንም ብዥታ መኖር የለበትም። የማይንቀሳቀስ ንብረት ሽያጭ ውል በጽሑፍ መሆን አለበት፣ በሁለት ምስክሮች ፊት መሆን አለበት። በአዋዋይ ፊት መሆን አለበት።

ውሉ በመንደር ቢደረግ እጣ ፈንታው ምንድነው የሚሆነው ?

እውነት ለመናገር በዚህ ረገድ ሕጉ የተረጋጋ አይደለም :: የአገሪቱ የመጨረሻ ፍርድ ቤት የሆነው ሰበርም ቢሆን ከውል አዋዋይ (ውልና ማስረጃ) ውጪ የተደረጉ የመንደር ውሎች ይፀናሉ ወይስ አይፀኑም በሚለው ላይ በተለያየ ጊዜ የተለያየ ውሳኔ ሰጥቷል።

በአንድ በኩል፣ ሰዎች በመንደር ከተዋዋሉና ነገር ግን ፊርማቸውን ካልተካካዱ ውሉ በተዋዋዮቹ መካከል ብቻ ይጸናል ብሎ የወሰነበት ፍርድ አለ። (ሰበር መዝገብ ቍ 21448)

በሌላ በኩል ደግሞ የመንደር ውል በውል አዋዋይ ፊት እስካልተመዘገበ ድረስ ሕግ ተቀባይነት አይኖረውም የሚል ፍርድ አለ። (ሰበር መዝገብ ቁ 83674)

ይህ ማለት ውሉ የሚጸናው በእነሱ ላይ ብቻ ነው። ሌሎች ሦስተኛ ወገኖች ላይ መቃወሚያ ሆኖ ሊቀርብ ግን አይችልም። ምን ማለት ነው፣ አንድ ሰው ቤቱን በመንደር ውል ቢሸጥና ውል ለማፍረስ ፍርድ ቤት ቢሄድ ገዥ ገንዘቡን ለመክፈል ይገደዳል። ሻጭም ቤቱን ለመስጠት ይገደዳል። ሆኖም ግን፣ ለምሳሌ ባንክ በቤቱ ላይ ጥያቄ ቢኖረው የመንደር ውሉ አይጸናበትም። ወይም ደግሞ ሻጭ ላይ ባለ ዕዳ የሆነ ሰው ዕዳዬ ቤቱ ተሸጦ ይከፈለኝ ቢል ቤቱ ተሸጧልና አይከፈልህም ሊባል አይችልም። ምክንያቱም በመንደር ውል ስለተሸጠ። አደጋውም እዚህ ላይ ነው። ገዢው የመንደር ውሉን ይዞ "እኔ እኮ ይሄን ቤት ገዝቼዋለሁ" ብሎ ጥያቄ ያነሱ ሦስተኛ ወገኖችን ዝም ሊያሰኛቸው አይችልም። ስለዚህ ገዢ በመንደር ውል መፈራረሙ ወዶና ፈቅዶ በራሱ ላይ አደገኛ አደጋን ጋብዟል::

🟢 ተዋዋዮች የመንደር ውልን ለምን ተመራጭ ያደርጋሉ?

አሁን አሁን የተለመደው አሰራር ገዥና ሻጭ ውል የሚፈጽሙት በሁለት ዙር ነው። መጀመሪያ በመንደር ውል ይፈጣጠሙና ነው ወደ ሁለተኛ ውል አዋዋይ ዘንድ የሚመጡት። ብዙውን ጊዜ አንድ ቤት ስንት እንደተሸጠ በትክክል የሚታወቀውም በመንደር ውል ላይ እንጂ በትክክለኛው ውል ላይ አይደለም።

ተዋዋዮች ወደ መንግሥት ተቋማት ሄደው የሚዋውሉት በ2ኛ ደረጃ ነው። ይህን ሲያደርጉም ብዙውን ጊዜ ዋጋ ቀንሰው ነው። ጥቂት ሰዎች ብቻ ናቸው ትክክለኛ ዋጋ ተናግረው የሚዋዋሉት። መንግሥት ቢቸግረው ተመን አውጥቶ ያስክፍላል። 6 በመቶ አሹራ ትከፍላለህ። የተዋዋልከው ከተመኑ ከፍ ካለ በተዋዋልከው ያስከፍላል። ዝቅ ካለ ደግሞ በተመኑ ያስከፍላል።

በሁለት ዓይነት ዋጋ መፈራረም የሚያመጣው አደጋ ስምምነት ሲፈርስ ነው። አንድ ሰው ለምሳሌ ውል ይፍረስልኝ ብሎ ፍርድ ቤት ሲሄድ ውል ይፈርሳል። ውል ሲፈርስ ደግሞ ወደነበረበት ነው የሚመለሰው። ሻጭ ገንዘብ ይመልሳል፣ ገዥ ንብረቱን ይመልሳል።

በአሥር ሚሊዮን ብር የተሸጠ ቤት ውልና ማስረጃ ባረጋገጠው ውል፣ ፍርድ ቤት ተሂዶ ውል ቢፈርስ ተዋዋዮቹ ዋጋ ዝቅ አድርገው ስለሚዋዋሉ [ለምሳሌ 6ሚሊዮን ብር] ሻጭ ገንዘብ መልስ ይባላል። ይህን ጊዜ እንዲመልስ የሚገደደው በውልና ማስረጃ በገዛበትን ገንዘብ ነው። ይህ ማለት ገዥ 4 ሚሊዮን ብር ከሰረ ማለት አይደል?

በመሆኑም የማይንቀሳቀስ ንብረትን በሚመለከት የሚደረጉ የሽያጭ ውሎች በጽሑፍ ብቻ ሳይሆን  በአዋዋይ ወይም ፍርድ ቤት ፊት መከናወን ይገባቸዋል፡፡ ከላይ እንደተጠቀሰው ; የማረጋገጥ መስፈርት ውሉ በሦስተኛ ወገኖች ላይ ውጤት እንዲኖረው ብቻ መከናወን ያለበት ሳይሆን ውሉ በተዋዋይ ወገኖች መካከል ውጤት እንዲኖረውም ጭምር መከናወን ያለበት ነው፡፡
#tebekasamuel 
#ጠበቃ_ሳሙኤል_ግርማ

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

09 Nov, 07:14


ኑዛዜ ፈራሽ ወይም ውድቅ የሚሆንባቸው ምክንያቶች

ኑዛዜ ህግን ተከትሎ ባለመደረጉ ወይም በሌሎች ምክንቶች ፈራሽ ሊሆን ይችላል፡፡ ለአብነት፡-አንድ
ኑዛዜ ተጠቃሚውንና ጉዳዩን ካላመላከተ ወይም አፈፃፀሙን የማይቻል ከሆነ ፈራሽ ነው (የፍትሐ ብሔር ሕግ አንቀጽ 865)፡፡ለምሳሌ፡👇
አቶ ጫላ አምስት ልጆች አሏቸው፡፡ አድሜአቸው እየገፋ በመምጣቱም እሳቸው ካለፉ በኋላ በውርስ የተነሳ ግጭት እንዳይፈጠር በማሰብ ኑዛዜ አዘጋጁ ፡፡ ነገር ግን በኑዛዜአቸው ላይ እያንዳንዳቸው 20% ይውሰዱ ከማለታቸው ውጪ የኑዛዜተጠቃሚዎቹን አልገልፁም፡፡ ይህን መሰል ኑዛዜ ፈራሽ ነው፡፡
ብዙ ሰዎች በአንድ ፅሁፍ ላይ ቢናዘዙ ፈራሽ ይሆናል የፍትሐ ብሔር ሕግ አንቀጽ 858
የኑዛዜው ቃል ለህግ ወይም ለመልካም ጠባይ ተቃራኒ ከሆነ ፈራሽ ይሆናል የፍትሐ ብሔር ሕግ አንቀጽ 866
👉ምሳሌ
ወ/ሮ አለምነሽ ልጃቸው አቤል የሸክላ ሥራ የተሰማራ መሆኑ ደስተኛ አላደረጋቸውም፡፡ በዚህም ባደረጉት ኑዛዜ ወንድማቸው አቶ ብርሀኑ ልጃቸው ይህን ሥራ እንዳይሰራ የሚያደርገው ከሆነ ብር 300,000 እንዲሰጠው ቢናዘዙ ይህ ኑዛዜ ልጃቸው በፈለገው የሥራ ዘርፍ የመሰማራት መብቱን የሚነፍግ በመሆኑ ፈራሽ ይሆናል ማለት ነው፡፡
አንድ ሰው ኑዛዜ ያደረገው በሀይል ከሆነ ወይም ተገዶ ከሆነ ፈራሽ ይሆናል የፍትሐ ብሔር ሕግ አንቀጽ 867
👉 ምሳሌ
ወ/ሮ ብርሀን ስድስት ልጆች አሏቸው፡፡ ሁሉም ልጆቻቸው በውጪ ሀገር የሚኖሩ ሲሆኑ እሳቸው ከሀገር መውጣት ስለማይፈልጉ በአዲስ አበባ ከተማ ይኖራሉ፡፡ በእርጅና እና በጤና ችግር ምክንያት የሰው እርዳታ እያስፈለጋቸው ሲመጣ የእህታቸው ልጅ ወደ ሆነች ሄልን ጋር ሄደው መኖር ይጀምራሉ፡፡
ይህን እንደጥሩ አጋጣሚ የወሰደችው ሄለን ኑዛዜ አድርገው የውርስ ተጠቃሚ እንዲያደርጓት በተዳጋጋሚ እንደምትገላቸው ታስፈራራቸዋለች፡፡ በዚህም ምክንያት ኑዛዜ አድረገው የኑዛዜ ተጠቃሚ አደረጓት፡፡በዚህ የሀይል ድርጊት የተደረገ ኑዛዜ ፈራሽ ነው፡፡
ይቀጥላል .....
Join us 👇
@Ethiopianlaw_s
@Ethiopianlaw_s

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

07 Nov, 19:03


ክፍት የስራ መደብ ለህግ ተመራቂዎች
ሸር ላይክ በማድረግ ለሌሎች ያጋሩ
https://t.me/Ethiopianlaw_s

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

07 Nov, 16:32


Bahir Dar university school of law students are participating on The All Africa International Humanitarian Law Competition by representing Bahir dar university and our country, Ethiopia. Surprisingly they passed to the semi final.
Wish you the best!
Join 👇
@Ethiopianlaw_s
@Ethiopianlaw_s

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

06 Nov, 18:17


Join 👇
@Ethiopianlaw_s
@Ethiopianlaw_s

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

06 Nov, 18:17


International humanitarian law ppt
Join 👇
@Ethiopianlaw_s
@Ethiopianlaw_s

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

06 Nov, 18:17


Join 👇
@Ethiopianlaw_s
@Ethiopianlaw_s

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

06 Nov, 18:17


የፌደራል የቤተሰብ ህግ ይዘት እና አተገባበሩ.pdf
Join 👇
@Ethiopianlaw_s
@Ethiopianlaw_s

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

06 Nov, 18:17


Join 👇
@Ethiopianlaw_s
@Ethiopianlaw_s

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

06 Nov, 18:17


Criminal code Hateta ze Mikniat
Join 👇
@Ethiopianlaw_s
@Ethiopianlaw_s

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

06 Nov, 18:17


Principles of Ethiopian criminal law
By_ Elias N. Stebk
JOIN US FOR MORE BOOKS
Join 👇
@Ethiopianlaw_s
@Ethiopianlaw_s

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

06 Nov, 18:17


Join 👇
@Ethiopianlaw_s
@Ethiopianlaw_s

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

05 Nov, 11:13


Join us👇
@Ethiopianlaw_s
@Ethiopianlaw_s
@Ethiopianlaw_s

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

05 Nov, 11:13


Join us👇
@Ethiopianlaw_s
@Ethiopianlaw_s
@Ethiopianlaw_s

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

05 Nov, 11:13


Join us👇
@Ethiopianlaw_s
@Ethiopianlaw_s
@Ethiopianlaw_s

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

05 Nov, 11:13


Join us👇
@Ethiopianlaw_s
@Ethiopianlaw_s
@Ethiopianlaw_s

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

05 Nov, 11:13


Join us👇
@Ethiopianlaw_s
@Ethiopianlaw_s
@Ethiopianlaw_s

Ethiopian Law የኢትዮጵያ ሕግ

05 Nov, 11:13


Join us👇
@Ethiopianlaw_s
@Ethiopianlaw_s
@Ethiopianlaw_s