Muslim ሙስሊም @ethiomuslim_1 Channel on Telegram

Muslim ሙስሊም

@ethiomuslim_1


Muslim ሙስሊም (Amharic)

ማንኛውም ቀናት ከዚህ በፊት በተከታታይ ቦታ ያነሳናል - ከአዲስ አበባዎች እና በሌሎች አዋጅ ላይ ዳኛውን እንዴት ማገልገል ያልተምረው ከእነዚህ የተነሳ ተፅእኖ አሉ? ይህ አይነት የቴሌግራም ፕሮግራሞች የመሳሪያ ቡድን ነው። 'Muslim ሙስሊም' ከማንም ህዝብ እንደሚመረጥ ለሁሉም መልክ የሚጠቀሙበት እና በአጠቃላይ አስተያየቶች ላይ የተቀላቀሉበት ታሪኩ ነው። ለእኛ ነው የአካባቢዎችን እና የአባቶችን ለውጥ ስለሚያረጋግጡ፣ ነገሩን ለመጠበቅ፣ ለጣቢያዎች እና ለጇማዎች ለመቸረፈ እና ለስለስ ላልመናወጥ ጥናት ስንል ለምን እንደተሞክሩት ጊዜዎች ለእኛ ሁሉ በቅርቡ ደርሶ ለመገንዘብ የምትወዳትን ለአገልግሎት እና አስተማሪ ሥራዎችን ማዘጋጀት ከታመነ በኋላ ሊረሳን ያለው ባለሙያና ስለእኛ መረጃ እና አከባበል ይገኛል። ለተጨማሪ መረጃዎችን ፣ ሌሎች ቦታዎችን እና እናቶችን ለመጠበቅ እና ተጨማሪ ዝርዝርዎችን እንደምንጠቀሙ እና ለእኛ ላይ ለመታደግ በተመለከተ አስተዳደርን ማስፋፊያ አለበት።

Muslim ሙስሊም

12 Feb, 21:52


Muslim ሙስሊም pinned «#ጁለይቢብ__(ረ.ዐ) “ሰባት ጥሎ ወድቋል፤ እሱ ከኔ ነው እኔም ከርሱ ነኝ” (ነቢዩ ሙሐመድ ﷺ) ስሙ ያልተለመደና ያልተሟላ ነው። ጁለይቢብ “አጭር ፣ ትንሽ” ማለት ሲሆን የሚያመለክተውም ድንክዬ የነበረ መሆኑን ነው። ጁለይቢብ መልከ ጥፉ ሰውም ነበር። ሕብረተሰቡ ያገለለው ጁለይቢብ የዘር ሐረጉም አይታወቅም። ስለ አባቱ እናቱና ጎሣው በታሪክ የደረሰን የለም። ቤተሰብና ጎሣን በማምለክ ላይ…»

Muslim ሙስሊም

12 Feb, 08:05


#ጥልቅ_እምነት (#የቂን) #እና #በአላህ_መመካት (#ተወኩል)

#ክፍል_8

አላህ እንዲህ ብሏል፦
“አማኞቹም አሕዛብን ባዩ ጊዜ፡ ይህ አላህና መልዕክተኛው የቀጠሩን ነው፤ አላህና መልዕክተኛውም እውነትን ተናገሩ፡ (የተናገሩት እውነት መሆኑ ተገለጠ) አሉ። (ይህ) እምነትንና መታዘዝንም እንጂ ሌላን አልጨመረላቸውም።” (አል-አሕዛብ፡ 22)

#ሐዲሥ 7 / 81

አቡበክር አስ-ሲዲቅ (ረ.ዐ) -እርሳቸው፤ አባታቸውና እናታቸው የነቢዩ ባልደረቦች ነበሩ፣ እንዲህ ሲሉ አስተላልፈዋል፦ “(እኔና የአላህ መልዕክተኛ (ሶ.ዐ.ወ) ዋሻ ውስጥ እያለን አጋሪዎችን አየኋቸው። በላያችን ላይ ነበሩ። “የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! ከመካከላቸው አንዱ ወደ እግሮቹ አቅጣጫ ቢመለከት ሊያየን ይችላል” አልኳቸው። “አቡበክር ሆይ! አላህ አብሯቸው ባልለ ሁለት ሰዎች ላይ ምን ዓይነት ጥርጣሬና ስጋት ነው የሚያድርብህ?” አሉኝ። (ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል)

ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች

1/ ተገቢውን የጥንቃቄ እርምጃ ከወሰዱ በኋላ የአላህን ጥበቃና እንክብካቤ መማጸን ግዴታ ወይም (ዋጂብ) መሆኑ።
2 አቡበክር ለረሱል (ሶ.ዐ.ወ) የነበራቸው ከፍተኛ ፍቅርና በጠላት እጅ ወድቀው ተልዕኳቸው በእንጭጩ እንዳይቀጭ የነበራቸው ከፍተኛ ስጋት።
3/ አላህ ለነቢያትና ፈለጋቸውን ለተከተለ ሁሉ የሚያደርገው ጥበቃ፤ ለድልና ስኬት ማብቃቱ።
4/ የመልዕክተኛው (ሶ.ዐ.ወ) ጀግንነት።

Umma Life
https://ummalife.com/MuslimEthio

ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1

Muslim ሙስሊም

11 Feb, 07:03


#ጥልቅ_እምነት (#የቂን) #እና #በአላህ_መመካት (#ተወኩል)

#ክፍል_7

#ሐዲሥ 7 / 80

አቡ ዑማረህና በራእ ኢብኑ ዓዚብ እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ እንዲህ ሲሉ ተናግረዋል፦ "እገሌ ሆይ! ወደ መኝታህ በምትሄድበት ወቅት፦ "አላህ ሆይ! ነፍሴን ለአንተ አስረክቤያለሁ። ሁለ ነገሬን ወደ አንተ አስጠግቼያለሁ። ፊቴንም ወዳንተ አዙሪያለሁ። ጀርባዬን ወዳንተ መልሻለሁ። (ትሩፋትህን) በመከጀልና (ቁጣህን) በመፍራት። ከአንተ ቅጣት ነጻ መውጫና መመለሻ ከአንተ ውጭ ሌላ ኃይል የለም። ባወረድከው መጽሐፍ አምኛለሁ። በላክከው ነቢይም አምኛለሁ" በል። ይህንን ባልክበት ሌሊት ቢትሞት በተፈጥሮ ማንነትህ (ፊጥራህ) ላይ ሞትክ። በሕይወት ካነጋህም በመልካም ሁኔታ አነጋህ።" (ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል)

በሌላ ቡኻሪና ሙስሊም በራእን ጠቅሰው ባሰፈሩት ዘገባ ላይ እንደተወሳው፥ የአላህ መልዕክተኛ እንዲህ ብለዋል፦ "ወደ መኝታህ በምትመጣበት ወቅት ለሶላት የምታደርገውን ዓይነት ዉዱእ አድርግ። ከዚያም በቀኝ ጎንህ ተጋደምና እንዲህ በል" በማለት ከላይ የተጠቀሰውን "ዱዓ" (ዚክር) አወሱ። ከዚያም፦ "እነኝህን ቃላት የንግግርህ መቋጫ አድርጋቸው" አሉ።

ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች

1/ በማንኛውም ጉዳይ ወደ አላህ የመመለስ አስፈላጊነት።
2/ በቀየኑ ከአላህ ጋር ያለን ቃልኪዳን ማደስና ከኢስላም ጋር የሚኖረን ግንኙነት በንግግም፥ በተግባርም ማጠናከር።
3/ እነኝህ ከላይ የተጠቀሱ አባባሎችን ሁልጊዜ ወደ መኝታ ሲሄዱ ማለትና የንግግርም መቋጫ ማድረግ። የኢማንንና የየቂንን ትርጓሜ ያካተቱ። ከአላህ ጋር ያለ ግንኙነት መልካም መሆኑን የሚያመለክቱ አባባሎች ናቸው።
4/ በምሉዕ ንጽሕና ለመተኛት ወደ መኝታ ሲሄድ ዉዱእ ማድረግ ተገቢ ነው።

mma Life
https://ummalife.com/MuslimEthio

ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1

Muslim ሙስሊም

10 Feb, 08:55


#ጥልቅ_እምነት (#የቂን) #እና #በአላህ_መመካት (#ተወኩል)

#ክፍል_6

አላህ እንዲህ ብሏል፦

“ፍጹም ምእምናን፡ እነዚያ አላህ በተወሳ ጊዜ ልቦቻቸው የሚፈሩት፤ በነሱም ላይ አንቀጾቻችን በተነበቡ ጊዜ እምነትን የሚጨምሩላቸው፡ በጌታቸውም ላይ ብቻ የሚመኩ ናቸው።” (አል-አንፋል፡ 2)

#ሐዲሥ 7 / 79

የአላህ መልዕክተኛ (ሶ.ዐ.ወ) ተከታዩን ሲናገሩ አድምጫለሁ በማለት ዑመር (ረ.ዐ) አስተላልፈዋል፦ “በአላህ ላይ እውነተኛ መመካትን ብትመኩ ኖሮ፡ በራሪ አዕዋፍን እንደሚመግብ እናንተንም ይመግብ ነበር። ማለዳ ላይ ባዶ ሆዷን ትወጣለች። ሆዷን ሞልታ ትመለሳለች።” (ቲርሚዚይ ዘግበውታል፤ “ሐሰን” ነውም ብለዋል)

ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች

1/ በእያንዳንዱ ጉዳይ ላይ በአላህ መመካት እንደሚገባ።
2/ “ሪዝቅ” ለማግኘት ሰበብ የሚሆኑ ነገሮችን አለመዘንጋት፤ በአላህ ከመመካት ጋር፤ እንደ በራሪ አዕዋፍ። እንዲሁ አይቀመጡም። ምግባቸውን ለማግኘት ይንቀሳቀሳሉ።

mma Life
https://ummalife.com/MuslimEthio

ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1

Muslim ሙስሊም

09 Feb, 06:40


#ጥልቅ_እምነት (#የቂን) #እና #በአላህ_መመካት (#ተወኩል)

#ክፍል_5

አላህ እንዲህ ብሏል፦

“እነዚያ ሰዎቹ ለእነርሱ፦ ሰዎች ለእናንተ (ጦርን) አከማችተዋልና ፍሩዋቸው፤ ይሉዋቸውና (ይህም) እምነትን የጨመረላቸው፤ በቂያችንም አላህ ነው፤ ምን ያምርም መጠጊያ! ያሉ ናቸው። ከአላህም በኾነ ጸጋና ችሮታ ክፉ ነገር ያልነካቸው ኾነው ተመለሱ፤ የአላህንም ውዲታ ተከትተሉ፤ አላህም የታላቅ ችሮታ ባለቤት ነው።” (አል-ዒምራን፡ 173-74)

#ሐዲሥ 7 / 78

ጃቢር እንዳስተላለፉት፦ እሳቸው (ጃቢር) ከአላህ መልዕክተኛ ጋር ወደ "ነጅድ" አቅጫ ዘመቱ። መልዕክተኛው ከዘመቻ ሲመለሱ እሾሃማ ከሆነ ሸለቆ አካባቢ ሲደርሱ የእኩለ ቀን የእረፍት ሰዓት (ቀይሉላህ) ደረሰባቸው። እዚሁ ሥፍራ ላይ ሰፈሩ። ሰዎች በየዛፎቹ ጥላ ሥር ተጠለሉ። የአላህ መልዕክተኛ ከአንድ እሾሃማ ዛፍ ሥር አረፉ፤ ጦራቸውን ከዛፉ ላይ አንጠልጥለው። እንቅልፍ አሸለበን። ብዙም ሳይቆይየአላህ መልዕክተኛ ጠሩን። አንድ "አዕረቢይ" (ገጠረ) ከጎናቸው አለ። "ይህ ሰው ተኝቼ እያለሁ በኔ ላይ ጎራዴ መዘዘ። ሾተን ከአፎቱ መዞ አየሁት። "ከኔ ማን ያድንሃል?" አለኝ። "አላህ አልኩት _ሦስት ጊዜ።" ካሉ በኋላ ተቀመጡ። አልተቆጡትም። (ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል)

በሌላ ዘገባ ደግሞ ጃቢር እንዲህ ሲሉ ማስተላለፋቸው ተወስቷል፦

"ዛተ አር_ሪቃዕ" በተባለ ዘመቻ ወቅት ከአላህ መልዕክተኛ ጋር ነበርን። ጥላማ ከሆነ ዛፍ ደረስን። ለአላህ መልዕክተኛ ተውንላቸው። አንድ አጋሪ ሰውዬ መጣ። የአላህ መልዕክተኛ ጎራዴ ከዛፉ ላይ ተንጠልጥሏል። ጎራዴውን በመልዕክተኛው ላይ አነጣጠረና፦ "ትፈራኛለህ?" አላቸው። "አልፈራህም" ሲሉ መለሱለት። "ከእኔ ማን ያድንሃል?" አላቸው። "አላህ" አሉ።

አቡበክር ኢስማዒል ባስተላለፉት ሶሒሕ ዘገባ ደግሞ፦

"ከኔ ማን ያድንሃል?" አላቸው። "አላህ" አሉት። ጎራዴው ከእጁ ወደቀ። የአላህ መልዕክተኛ ጎራዴውን ያዙና፦ "ከኔ ማን ያድንሃል?" አሉ። "ክፉን በክፉ የማይመልስ ደግ ወዳጅ ሁን" አላቸው። "ከአላህ ሌላ አምላክ አለመኖሩንና እኔ የአላህ መልዕክተኛ መሆኔን ትመሰክራለህን?" አሉት። "ይህንን አልፈጽምም። ግና ካንተ ጋር ላልዋጋና አንተን ከሚወጉህ ሰዎች ጋር ላላብር ቃል እገባልሃለሁ" አላቸው። ከባልደረቦቹ ዘንድ ሄደና፦ "ከሰው ሁሉ ይበልጥ ደግ ከሆነ ሰው ዘንድ ነበርኩ" አላቸው።

"ዛተ አርሪቃእ የተባለው ዘመቻ የተካሄደው እንደ ሂጅሪያ አቆጣጠር በወርሃ ሸዕባን አራተኛ ዓመት ላይ ነበር። (አርታኢው)

ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች

1/ ነቢዩ በአደጋ ወቅት የነበራቸው ጀግንነትና ጽናት፥ በአላህ ላይ የነበራቸው እምነትና እውነተኛ ተውኩላቸው (ትምክህታቸው)፤ ወደ አላህ የመመለስ ችሎታቸውም።
2/ በአደጋ ወቅት በአላህ መመካት የሚያስገኘው መልካም ውጤት።
3/ የነቢዩ ይቅር ባይነትና መልካም ባሕሪያቸው፥ ከብቀላ የራቄ አስተዋይ መሆናቸው። እንዲሁም የሰዎችን ልቦና ከሐቅ ጋር ለማስተዋወቅ ይፈጽሙት የነበረ ብስለት የተሞላበት ክንውን።

Umma Life
https://ummalife.com/MuslimEthio

ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1

Muslim ሙስሊም

06 Feb, 11:20


#ጥልቅ_እምነት (#የቂን) #እና #በአላህ_መመካት (#ተወኩል)

#ክፍል_4

አላህ እንዲህ ብሏል፦

“ፍጹም ምእምናን፡ እነዚያ አላህ በተወሳ ጊዜ ልቦቻቸው የሚፈሩት፤ በነሱም ላይ አንቀጾቻችን በተነበቡ ጊዜ እምነትን የሚጨምሩላቸው፡ በጌታቸውም ላይ ብቻ የሚመኩ ናቸው።” (አል-አንፋል፡ 2)

#ሐዲሥ 7/ 77

አቡ ሁረይራ (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ (ሶ.ዐ.ወ)፦ “ልቦናዎቻቸው እንደ በራሪ አዕዋፍ ልቦና የሆኑ አያሌ ሰዎች ጀንነትን ይገባሉ” ብለዋል። (ሙስሊም ዘግበውታል)
“በአላህ ላይ የሚመኩ” ሰዎችን ለማመልከት እንደሆነ ተወስቷል። “ልቦናቻቸው በአላህ ፍርሃት የለሰለሰ” የሚል ትርጓሜም ተሰጥቶታል።

ከሐዲሡ የምንማረው ቁምነገር

፨ በአላህ የመመካትና የልቦና ልስላሴ ጠቀሜታ ጀንነትን ለመጎናጸፍ ከሚያስችሉ ምክንያቶች መካከል ናቸው።

Umma Life
https://ummalife.com/MuslimEthio

ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1

Muslim ሙስሊም

05 Feb, 11:22


#ጥልቅ_እምነት (#የቂን) #እና #በአላህ_መመካት (#ተወኩል)

#ክፍል_3

አላህ እንዲህ ብሏል፦

“ቁርጥ ሐሳብም ባደረግህ ጊዜ በአላህ ላይ ተመካ።” (አል-ዒምራን፡ 159)


#ሐዲሥ 7 / 76

ኢብኑ ዐብባስ (ረ.ዐ) እንዲህ ሲሉ አስተላልፈዋል፦ “ሐስቡነላህ ወኒዕመል ወኪል” (አላህ በቂያችን ነው! በርሱ መመካት ምን አማረ) የሚለውን ቃል ነቢዩ ኢብራሂም (ሶ.ዐ.ወ) እሳት ውስጥ የተጣሉ ዕለት ብለውታል። ነቢዩ ሙሀመድ (ሶ.ዐ.ወ) “ሰዎች ጦር አካማችተውላችኋልና ፍሯቸው” ባሏቸው ጊዜ ሁኔታው ኢማናቸውን ጨመረላቸው፤ “ሐስቡነሏህ ወኒዕመል ወኪል” አሉም። (ቡኻሪ ዘግበውታል)
ኢብኑ ዐብባስን (ረ.ዐ) ጠቅሰው ቡኻሪ ባሰፈሩት ሌላ ዘገባ ላይ ደግሞ፦
“ኢብራሂም ወደ እሳት በተወረወሩበት ዕለት የተናገሩት የመጨረሻ ቃል “ሐስቡነሏህ ወኒዕመል ወኪል” ነበር” የሚል ተወስቷል።

ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች

1/ በአላህ መመካት ያለው ትሩፋትና በጭንቀት ሰዓት አስፈላጊነቱ።
2/ በአላህ ላይ በመመካት የነቢያትንና የአላህ ወዳጆች አርአያነት መከተል።


Umma Life
https://ummalife.com/MuslimEthio

ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1

Muslim ሙስሊም

05 Feb, 06:27


አቡ ሙሀመድ ሐሰን ኢብኑ ዐሊይ ኢብኑ አቢ ጧሊብ (ረ.ዐ) እንዲህ ሲሉ አስተላልፈዋል፦ ከአላህ መልዕክተኛ (ሶ.ዐ.ወ) ጠቃሚ ምክር ይዣለሁ፦ “የሚያጠራጥርህን ነገር በመተው የማያጠራጥርህን ያዝ። እውነት ውስጣዊ ሰላምና መረጋጋት ሲሆን፤ ሐሰት ደግሞ ጥርጣሬና የልቦና አለመረጋጋት ነው።”
(ቲርሚዚይ ዘግበውታል፡ ሐዲሱን “ሐሰን” ነውም ብለዋል)
ከሐዲሡ የምንማረው ቁምነገር
=› አሻሚ ነገሮችን በመተው ሐላል ወደሆኑ ነገሮች መዘንበል እጅግ ጠቃሚ ነው። ከአሻሚ ነገሮች የራቄ ዲኑንም፤ ክብሩንም ጠብቋልና።

Muslim ሙስሊም

02 Feb, 08:03


#ጥልቅ_እምነት (#የቂን) #እና #በአላህ_መመካት (#ተወኩል)

#ክፍል_2

አላህ እንዲህ ብሏል፦

“በአላህም ላይ ብቻ ምእምናን ይመኩ።” (አል-ዒምራን፡ 160)

#ሐዲሥ 7 / 75

ኢብኑ ዐብባስ (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ (ሶ.ዐ.ወ) ተከታዩን ይሉ ነበር፦ “አላህ ሆይ! ለአንተ እጅ ሰጥቻለሁ፤ ባንተ አምኛለሁ፤ በአንተ ላይ ተመክቻለሁ፤ ወዳንተው ተመልሻለሁ። (ጠላቶችህን) ስለ አንተው ተሟግቻለሁ። አላህ ሆይ! ከአንተ ሌላ አምላክ የለም፤ እንዳታጠመኝ በኃይልህና በሥልጣንህ እጠበቃለሁ። አንተ የማትሞት ሕያው አምላክ ነህ። ሰዎችና አጋንንቶች ግን ይሞታሉ።” (ቡኻሪና ሙስሊም)
ይህ ከሙስሊም ዘገባ ላይ የተወሰደ ነው። ቡኻሪ አሳጥረው አስፍረውታል።

ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች

1/ በአላህ መመካትና ጥበቃን ከርሱ ብቻ መሻት ግዴታ ነው። አላህ የምሉዕ ባሕሪያት ባለሃብት በመሆኑ እርሱ ብቻ ነው ሊመኩበት የሚገባ። ፍጡራን ሁሉ አቅመ-ቢስና ደካማ፡ ሟቾችም እንደመሆናቸው መመኪያ ሊሆኑ አይችሉም።
2/ በእነኝህ የእምነት ጽናትና ጥልቀት የሚገልጹ አጠቃላይ ማራኪ ቃላት ዱዓ በማድረግ የነቢዩን (ሶ.ዐ.ወ) አርአያነት ልንከተል ይገባል።

Umma Life
https://ummalife.com/MuslimEthio

ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1

Muslim ሙስሊም

31 Jan, 09:20


#ጥልቅ_እምነት (#የቂን) #እና #በአላህ_መመካት (#ተወኩል)

#ክፍል_1

አላህ እንዲህ ብሏል፦
“በዚያም በማይሞተው ሕያው አምላክ ላይ ተመካ፤” (አል-ፉርቃን፡ 58)

#ሐዲሥ 7/ 74

ኢብኑ ዐብባስ እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ እንዲህ ብለዋል፦ "ሕዝቦች ተገለጹልኝ፤ አንድን ነቢይ ከጥቂት ተከታዮች ጋር፣ ሌላውን ነቢይ ከአንድ ወይም ሁለት ሰዎች ጋር፣ ሌላኛውን ነቢይ ደግሞ ምንም ተከታይ የሌለው ሆኖ ብቻውን ተመለከትኩ። የኔ ተከታዮች እንደሆነ ገመትኩ። "ይህ ሙሳና ተከታዮቹ ናቸው። ነገር ግን ወደ ሌላኛው አድማስ ተመልከት" ተባልኩ። በርካታ አባላትን ያቀፈ የሰዎች ስብስብ ተመለከትኩ። "እነኝህ ተከታዮችህ ናቸው። ከነርሱ መሐከል ያለምንም ጥያቄና ቅጣት ጀንነት የሚገቡ ሰዎች አሉ" ተባልኩ።" ነቢዩ ይህን እንደተናገሩ ተነስተው ወደ ቤታቸው ገቡ። ስለነዚያ ያለ ምንም ጥያቄና ቅጣት ጀነት ስለሚገቡ ሰዎች ታዳሚው ይነጋገር ጀመር። ከፊሎቹ፦ "የነቢዩ ባልደረቦች ሊሆኑ ይችላሉ" የሚል አስተያየት ሰጡ። ከፊሎቹ ደግሞ፦ "ምናልባትም በዘመነ ኢስላም የተወለዱና በአላህ አንዳችም ነገር ያላጋሩ" ሊሆኑ እንደሚችሉ ገመቱ። ሌሎች ግምቶችም ተሰነዘሩ። በዚህ ወቅት የአላህ መልዕክተኛ ከነበሩበት ክፍል በመውጣት፦ "ስለምን እየተነጋገራችሁ ነው?" ሲሉ ታዳሚዎችን ጠየቁ። የሚነጋገሩበትን ጉዳይ ነገሯቸው። "እነዚያ (ያለምንም ጥያቄና ቅጣት ጀነት የሚገቡ ሰባ ሺህ ሰዎች) የማይደግሙና የማያስደግሙ፣ በገድ የማያምኑና በአላህ ብቻ የሚመኩ ናቸው" አሉ። ዑካሻህ ኢብኑ ሚሕሶን፦ "ከነርሱ ያደርገኝ ዘንድ አላህን ይማጸኑልኝ" አላቸው። "አንተ ከነርሱ ነህ" አሉት። ሌላ ሰው ቆመና፦ "እኔንም ከነርሱ ያደርገኝ ዘንድ አላህን ይማጸኑልኝ" አላቸው። "ዑካሻህ ቀድሞሃል" አሉት። (ቡኻሪና ሙስሊም)

ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች

1/ ይህ መገለጽ የነቢዩን ልቅና ያመለክታል። በሕልማቸው ሊሆን ይችላል የተገለጸላቸው። የነቢያት ሕልም እውነት ነው። ወይም የኢስራእ ጉዞ ባደረጉበት ሌሊት በእውን አለያም በሌላ መልኩ ሊሆን ይችላል። አላህ ለነቢያት ከሌሎች ሰዎች የተለዩ ነገሮችን አድርጎላቸዋል።
2/ አላህ ነቢዩን ከሌሎች ነቢያት ማላቁ እዚህ ዘገባ ላይ ተመልክቷል። ተከታዮቻቸው ከየትኛውም ነቢይ ተከታይ ይበልጥ በርካታ ናቸው።
3/ በአላህ መመካት (ተወኩል) ያለው ጠቀሜታና አላህ በርሱ ለሚመኩ ሰዎች ያዘጋጀውን የላቀ ምንዳ ከዚህ ሐዲሥ ዘገባ ላይ ተወስቷል።
4/ የደረሰን ክፉ ነገር ለማስወገድ ወይም ይደርሳል ተብሎ የሚታሰበውን እንዳይደርስ ለመከላከል ከነቢዩ የተገኘውን ስልትና የቁርኣን አንቀጾችን መጠቀም በኢስላም ሕጋዊ (መሽሩዕ) ነው። ግና የኢማንን ጥራትና የተወክሉን ምሉዕነት የሚከውን የጃሂሊያ አጉል ልማድና ድግምት ግን ኢስላም ፈጽሞ አይፈቅድም።
5/ በገድ ማመን የተከለከለ ነው።

Umma Life
https://ummalife.com/MuslimEthio

ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1

Muslim ሙስሊም

30 Jan, 07:57


#ጥንቁቅነት (#ተቅዋ)

#ክፍል_5

አላህ እንዲህ ብሏል፦

“እናንተ ያመናችሁ ሆይ! አላህን ፍሩ። ትክክለኛንም ንግግር ተናገሩ፤” (አል-አሕዛብ፡ 70)

#ሐዲሥ 6 / 73

አቡ ኡማመህ ሱደይ ኢብኑ ዐጅላን አል-ባሂሊይ (ረ.ዐ) የአላህ መልዕክተኛ (ሶ.ዐ.ወ) የመሰናበቻ ሐጅ ዕለት ተከታዩን ንግግር ሲያሰሙ አድምጫለሁ በማለት አስተላልፈዋል፦ “አላህን ፍሩ፤ አምስት ወቅት ሶላቶችን ስገዱ፤ የረመዷንን ወር ጹሙ፤ ከገንዘባችሁ ዘካን ስጡ። መሪዎቻችሁን ታዘዙ፤ ጌታችሁ ያዘጋጀላችሁን ጀነት ትገባላችሁ።” (ቲርሚዚይ ዘግበውታል። “ሐሰኑን ሶሒሕ” ነው ብለውታል)

ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች

1/ እነኝህን ተግባራት ማከናወን አላህን የመፍራት ምልክት ነው። “ተቅዋ” ጀነትን ለመጎናጸፍ ዓይነተኛ መሣሪያ ነው። በዚህች ዓለም ውስጥ ለአላህ መንበርከክና ለፍላጎቱ ማደር በመጭው ዓለም ለስኬት ያበቃል።
2/ በኢስላማዊ ሥርዓት የሚያስተዳድሩ የኢስላማዊ መንግሥት መሪዎችን በወንጀል እስካላዘዙ ድረስ መታዘዝ ግዴታ ነው።

Umma Life
https://ummalife.com/MuslimEthio

ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1

Muslim ሙስሊም

29 Jan, 07:49


#ጥንቁቅነት (#ተቅዋ)

#ክፍል_4

አላህ እንዲህ ብሏል፦

“እላንተ ያመናችሁ ሆይ! አላህን ቢትፈሩ የእውነት መለያን ብርሃን ያደርግላችኋል፤ ክፉ ሥራዎቻችሁንም ከእናንተ ላይ ያብስላችኋል፤ ለእናንተም ይምራችኋል፤ አላህም የታላቅ ችሮታ ባለቤት ነው።” (አል-አንፋል፡ 29)

#ሐዲሥ 6 / 72


አቡ ወሪፍ ዐዲይ ኢብኑ ሓቲም አጥ-ጧኢው (ረ.ዐ) የአላህ መልዕክተኛ (ሶ.ዐ.ወ) ተከታዩን ሲናገሩ አድምጫለሁ፡ በማለት አስተላልፈዋል፦ “መሐላን የፈጸመና መሐላውን ከመሙላት መቆጠቡ አላህን ይበልጥ ያረካዋል የሚል እምነት ካደረበት የማለበትን ነገር ከመፈጸም ይቆጠብ።” (ሙስሊም ዘግበውታል)

ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች

1/ “ተቅዋ” ግዴታ ነው።
2/ አንድን ኃጢአት ለመሥራት የቆረጠ -ቢምል ቢገዘት እንኳ- ቅጣት (ካፍፋራህ) በመክፈል መሐላውን ያብስ እንጂ በጭራሽ ወንጀሉን መፈጸም የለበትም።

Umma Life
https://ummalife.com/MuslimEthio

ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1

Muslim ሙስሊም

28 Jan, 08:35


#ጥንቁቅነት (#ተቅዋ)

#ክፍል_3

አላህ እንዲህ ብሏል፦

“አላህንም የሚፈራ ሰው ለእርሱ መውጫን ያደርግለታል። ከማያስበውም በኩል ሲሳይን ይሰጠዋል፤” (አጥ-ጦላቅ፡ 2-3)

#ሐዲሥ 6 / 71

ኢብኑ መዑድ (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ (ሶ.ዐ.ወ)፦ “አላህ ሆይ! ምሪትን፣ ተቅዋን፣ ከሐራም መቆጠብንና ክብረትን እጠይቀሃለሁ” ይሉ ነበር። (ሙስሊም ዘግበውታል)

ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች

1/ በማንኛውም ሁኔታ ወደ አላህ መመለስና እርሱን ብቻ መለመን ይገባል።
2/ አላህን ከማንም በላይ የሚያውቁትና የሚፈሩት ነቢይ (ሶ.ዐ.ወ) ከአላህ የጠየቋቸው እነኝህ ማራኪ በሕሪያት እጅግ ጠቃሚ እንደሆኑ ዘገባው ያስረዳል።

Umma Life
https://ummalife.com/MuslimEthio

ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1

Muslim ሙስሊም

26 Jan, 19:05


ራስን ማሸነፍ.mp3

Muslim ሙስሊም

26 Jan, 19:05


አንድ ሙስሊም ለምን በዱንያ ይፈተናል.mp3

Muslim ሙስሊም

26 Jan, 09:45


#ጥንቁቅነት (#ተቅዋ)

#ክፍል_2

አላህ እንዲህ ብሏል፦

“አላህንም የቻላችሁትን ያክል ፍሩት፤” (አት-ተጋቡን፡ 16)

#ሐዲሥ 6 / 70


አቡ ሰዒድ አል-ኹድሪይ (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ (ሶ.ዐ.ወ) እንዲህ ሲሉ ተናግሯል፦ “ይህች ዓለም (ዱንያ) ጣፋጭና አረንጓዴ ናት። አላህ በዚህች ዓለም ውስጥ ወኪሉ አድርጓችኋል። ይህንን ተግባራችሁን (ኃላፊነታችሁን እንደት እንደምትወጡ) ይመለከታል። ዱንያንና ሴትን ልጅ ተጠንቀቁ። የበኒ ኢስራኤል የመጀመሪያ ፈተና ሴት ልጅ ነበረች።” (ሙስሊም ዘግበውታል)

ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች

1/ ባዕድ ከሆኑ የወሲብ ስሜትን ሊያጭር ከሚችል ልቅ የሆነ የሁለቱ ፆታዎች ግንኙነትና ወሲብን ልቀሰቅስ የምችልን የሰውነት ክፍል ከማየት፡ ሚስት ከሆነች ደግሞ ከርሷ ጋር የሚደረገው ግንኙነት ከኃላፊነት እንዳይዘናጋ መጠንቀቅ። በሴቶች ከመፈተን ራስን መጠበቅ ያስፈልጋል።
2/ ካለፉት ሕዝቦች መማር ያስፈልጋል። በኒ ኢስራኤሎች ላይ የደረሰው ውድቀት ሁኔታዎች ከተሟሉ በሌሎች ሕዝቦች ላይም የማይከሰትበት ምክንያት አይኖርም።

Umma Life
https://ummalife.com/MuslimEthio

ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1

Muslim ሙስሊም

25 Jan, 21:31


https://youtu.be/rzYHUrtM8QU?si=0JHSW_hp4o2jWiGk

Muslim ሙስሊም

20 Jan, 07:39


#የአላህን_የበላይ_ተቆጣጣሪነት #ምንጊዜም_አለመዘንጋት (#ሙራቀበህ)

#ክፍል_5

#ሐዲሥ 5 / 64

አቡ ሁረይራ (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ (ሶ.ዐ.ወ) እንዲህ ሲሉ ተናግረዋል፦ “ልዑል የሆነው አላህ ይቀናል። የአላህ ቅናት አንድ ሰው (አላህ) ውጉዝ (ሐራም) ያደረገውን ነገር ሲፈጽም ነው።” (ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል)

ከሐዲሡ የምንማረው ቁምነገር

=› ሐራም የሆኑ ተግባራትን ከመፈጸም መቆጠብ ግዴታ ነው። ምክንያቱም ሐራም የሆኑ ተግባራት የአላህን ቁጣ ያስከታላሉ።

Umma Life
https://ummalife.com/MuslimEthio

ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1

Muslim ሙስሊም

19 Jan, 08:06


#የአላህን_የበላይ_ተቆጣጣሪነት #ምንጊዜም_አለመዘንጋት (#ሙራቀበህ)

#ክፍል_4

#ሐዲሥ 5 / 63

አነስ እንዲህ ሲሉ አስተላልፈዋል፦ "በእናንተ ዓይን ከፀጉር የቀጠኑ ኢምንት፥ ነገር ግን በአላህ መልዕክተኛ ዘመን ከአጥፊ የወንጀል ክንውኖች እንቆጥራቸው የነበሩ ሥራዎችን ትሠራላችሁ።" (ቡኻሪ እንደዘገቡት)

ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች

1/ ወንጀልን አቅልሎ መመልከት "ተቅዋ" (አላህን መፍራት፣) ጥንቃቄ አለመኖሩን ያመለክታል። እያንዳንዱ ጥቃቅን ወንጀል እንደ ትልቅ ጥፋት መመልከት ደግሞ የላቀ "ተቅዋ"ና "ሙራቀባ" እንዳለ ይጠቁማል።
2/ ከነቢያት ቀጥሎ አላህን ከምንም ይበልጥ የሚያውቁትና የሚፈሩት የነቢዩ ባልደረቦች ናቸው። ጥቃቅን ጥፋቶችን ሁሉ እንደ አጥፊ ወንጀሎች ይመለከቱ ነበር፤ የአላህን ታላቅነት፣ ልዕልናና ግዝፈት በጥልቅ ስለሚረዱ።

Umma Life
https://ummalife.com/MuslimEthio

ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1

Muslim ሙስሊም

18 Jan, 15:29


#የአላህን_የበላይ_ተቆጣጣሪነት #ምንጊዜም_አለመዘንጋት (#ሙራቀበህ)

#ክፍል_3

አላህ እንዲህ ብለዋል፦
“ጌታህ በመጠባበቂያ ላይ ነውና።” (አል-ፈጅር፡ 14)

#ሐዲሥ 5 / 62

ኢብኑ ዐብባስ እንዲህ ሲሉ አስተላልፈዋል፦ ከዕለታት አንድ ቀን ከነቢዩ ኋላ ነበርኩ። እንዲህ አሉኝ፦ "አንተ ልጅ ሆይ! ጥቂት ቃላቶችን አስተምርሃለሁ። የአላህን ትእዛዝ ጠብቅ፣ እርሱም ይጠብቅሃል። አላህን ጠብቅ፤ ከፊት ለፊት ታገኘዋለህ። ስትጠይቅ አላህን ብቻ ጠይቅ። እርዳታ ስትፈልግ በአላህ ብቻ ተረዳ። ሕዝቦች ሁሉ ሊጠቅሙህ ቢሰበሰቡ በእርግጥ አይጠቅሙህም _አላህ በእርግጥ የወሰነልህ ነገር ሲቀር። ሊጎዱህ ቢሰበሰቡም ሊጎዱህ አይችሉም _አላህ በእርግጥ የወሰነብህ ነገር ቢሆን እንጅ። ብዕሮች ተነስቷል፤ ገጾችም ደርቋል።" (ቲርሚዝይ ዘግበውታል፤ "ሐዲሡን ሰሒሕ" ብለውታል)

ከቲርሚዚይ ውጭ ካሉ ሌሎች ዘገባዎች ላይ ደግሞ፦

"አላህን ጠብቀው፤ ከፊት ለፊትህ ታገኘዋለህ። ከአላህ በሰላም ጊዜ ተዋወቅ፤ በችግር ጊዜ ዕውቅና ይሰጥሃልና። ያላጋጣመህ ነገር ሊደርስብህ፥ ያልነበረና የደረሰብህም ነገር የሚያልፍህ እንዳልነበር ተረዳ። ድል ከትዕግስት ጋር፤ እርዳታ ከጭንቅ ጋር፥ ችግርም ከምቾት ጋር መኖሩን እወቅ" የሚል ተወስቷል።

ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች

1/ ከአላህ ውጭ ማንም ማድረግ የማይችላውን ነገሮች ከአላህ ውጭ ያለን ፍጡርን መጠየቅ ሐራም ነው። ሰዎች በሚችሉት ጉዳይ ላይ እርዳታቸውን መሻት ግን የተከለከለ አይደለም።
2/ በኣላህ እውቀት ሥር ያለ ማናቸውንም ነገር የጸደቀ ነው። አይዘገይም። አይሻርም። ያለፉትም ይሁን ወደፊት የሚከሰቱ ነገሮች ሁሉ በአላህ እውቀት ሥር ናቸው። ከአላህ እውቀት ውጭ የሚከሠት አንድም ነገር የለም።
3/ እርካታ ከጭንቀት፤ ምቾት ከችግር ጋር የመቆራኘት ምስጢር አንድ ሰው ችግር በሚበረታበት ወቅት ከአላህ ውጭ ባለ ማንኛውም ኃይል ላይ ያለው ተስፋ ይሟጠጣል። ልቦናው ከአላህ ጋር ብቻ የተቆራኘ ይሆናል። እውነተኛ "ተወኩል" ይህ ነው።
4/ ይህ ሐዲሥ ስለ "ሙራበቃህ" የአላህን መብት ስለመጠበቅ፣ ለትእዛዙ ስለ ማደር፣ በርሱ ስለመመካት ብቸኛ አምላክነቱን ስለመናዘዝና ፍጡራን አንዳችም ነገር ለመሥራት ችሎታው የሌላቸውና የአላህን እርዳታ እንደሚሹ የሚያሳይ መሠረታዊ ዘገባ ነው።

Umma Life
https://ummalife.com/MuslimEthio

ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1

Muslim ሙስሊም

15 Jan, 08:56


#የአላህን_የበላይ_ተቆጣጣሪነት #ምንጊዜም_አለመዘንጋት (#ሙራቀበህ)

#ክፍል_2

አላህ እንዲህ ብለዋል፦
“(አላህ) የዓይኖችን ክዳት ልቦችም የሚደብቁትን ሁሉ ያውቃል።” (አል-ሙዕሚን፡ 19)

#ሐዲሥ 5 / 61

አቡ ዘር ጁንደብ ኢብኑ ጁናዳህ እና አቡ ዐብዱረሕማን ሙዓዝ ኢብኑ ጀበል (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ (ሶ.ዐ.ወ) እንዲህ ሲሉ ተናግሯል፦ “ምንጊዜም ቢሆን አላህን ፍራ። ኃጢአትን በመልካም ተግባር አስከትል፤ ኃጢአትን ታብሳለችና። ሰዎችን በመልካም ሥነ-ምግባር ተጉዳኝ።” (ቲርሚዚይ ዘግበውታል። ሐዲሱን “ሐሰን” ነውም ብለዋል)

ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች

1/ መልካም ተግባር ኃጢአትን ያብሳል። ይህ ትናንሽ ወንጀሎችን ብቻ እንደሚመለከት ተወስቷል። ታላላቅ ወንጀሎች የግድ ሸርጡን ደንቡን (መስፈርቱን) ያሟላ ተውበት ያስፈልጋቸዋል። ወንጀሉ ከሰዎች ሐቅ ጋር ተያያዥነት ያለው መሆን እንደሌለበትም ተመልክቷል።
2/ ብሩህ ገጽታ፣ እንቅፋትን ማስወገድ፣ መልካም ነገርን ለመፈጸም በጎ ፈቃደኝነት፣ ከሰዎች ጋር የሚኖረን ግንኙነት መልካም ማድረግ ከጥሩ ሥነ-ምግባር የሚካተቱ ናቸው።

Umma Life
https://ummalife.com/MuslimEthio

ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1

Muslim ሙስሊም

14 Jan, 14:46


#የአላህን_የበላይ_ተቆጣጣሪነት #ምንጊዜም_አለመዘንጋት (#ሙራቀበህ)

#ክፍል_1

አላህ እንዲህ ብለዋል፦
"አላህ በምድርም በሰማይም ምንም ነገር በርሱ ላይ አይሰወርም።” (አል-ዒምራን፡ 5)

#ሐዲሥ 5 / 60

ዑመር ኢብኑ አል ኸጧብ እንዲህ ሲሉ አስተላልፈዋል፦ ከዕለታት አንድ ቀን ከአላህ መልዕክተኛ ዘንድ ተቀምጠን እያለ አንድ በጣም ነጭ የሆነ ልብስ የለበሰ፥ ፀጉሩ በጣም ጥቁር የሆነ፥ የጉዞ ምልክት የማይታይበት፥ ከመካከላችንም ማንም የማያውቀው አንድ ሰው ብቅ አለ። ጉልበቱን ከነቢዩ ጉልበት ጋር አሳክቶ ተቀመጠ። መዳፎቹን ደግሞ ታፋዎቹ ላይ አደረገ። "ሙሐመድ ሆይ! ስለ ኢስላም ንገሩኝ" ሲልም ጠየቀ። "ኢስላም ከአላህ ሌላ አምላክ የሌለ መሆኑን እና ሙሐመድ የአላህ መልዕክተኛ መሆናቸውን መመስከርህ፥ ሶላትን አስተካክለህ መስገድህ፥ ዘካን መስጠትህ፥ የረመዷንን ፆም መፆምህና ወደ ሐጅ ለመጓዝ ችሎታው ያለህ ከሆነ ሐጅ ማድረግህ ነው" ሲሉ የአላህ መልዕክተኛ መለሱለት። "እውነት ብለዋል" አላቸው። ገረመን። ይጠይቃቸዋል፥ እውነት መናገራቸውንም ይናዘዛል። "ስለ ኢማን (እምነት) ይንገሩኝ" አላቸው። "በአላህ፣ በመላእክት፣ በመጻሕፍት፣ በመልዕክተኞች፣ በዕለተ ትንሳኤና ክፉም ሆነ በጎ በአላህ ዕቅድና ሕግ ማመንህ ነው" አሉት። "እውነት ብለዋል" አላቸው። "ስለ ኢሕሳን ይንገሩኝ" አላቸው። "አላህን እንደምታየው አድርገህ ማምለክህ ነው፣ አንተ ባታየው እርሱ ያይሃል" አሉት። "ስለ ፍርዱ ቀን ንገሩኝ" አላቸው። "የሚጠየቀው ሰው ከጠያቂው የበለጠ ዕውቀት የለውም" ሲሉ መለሱት። "እሺ ስለ ምልክቶቿ ንገሩኝ" አለ። "የሴት ባሪያ እመቤቷን ትወልዳለች። ጫማ የሌላቸው፣ የታረዙ፣ ድሆችና የፍየል እረኞች (የነበሩ ሰዎች) ታላላቅ ሕንጻዎችን በመንገባት ሲፎካከሩ ትመለከታለህ" አሉት። ከዚያ ወጥቶ ሄደ። ትንሽ ቆየሁ። "ዑመር ሆይ! ጠያቂው ማን እንደሆነ አወቅከውን ?" አሉኝ መልዕክተኛው። "አላህና መልዕክተኛው ያውቃሉ" አልኩ። "ጂብሪል ነው። ሃይማኖታችሁን ሊያስተምራችሁ ከናንተ ዘንድ መጥቶ ነው" አሉ። (ሙስሊም ዘግበውታል።

ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች

1/ አላህ ሙእሚኖችን እርስ በርሳቸው በሚጠራሩት ዓይነት ነቢዩንም እንዳይጠሩ በቁርኣን (24፥ 62) ቢከልክልም መላእኩ ጂብሪል ነቢዩን ስማቸውን መጥራቱ ማንነቱን ለመደበቅ ወይንም መልአክቶች ይህ ቁርኣናዊ ትእዛዝ የማይመለከታቸው በመሆኑ።
2/ ኢማን ማለት፥ የዲኑን መሠረቶች አምኖ መበቀል ሲሆን፥ ኢስላም ደግሞ ሸሪዓዊ ትእዛዝን መተግበር ነው። ሁለቱም ተያያዥነት ያላቸው ጽንስ ሐሳቦች ናቸው። ኢማን ያለ ኢስላም፥ ኢስላም ደግሞ ያለ ኢማን ተቀባይነት የላቸውም። በተወራራሽነት የሚሠሩበትም ቦታ ይስተዋላል።
3/ አንድ ሰው ሙስሊም ለመባል ቃለ ተውሒድን በምላሱ መናገር _ችሎታው ካለው_ ግዴታ ይሆንበታል።
4/ በነቢዩ እና በጂብሪል መካከል፥ በተደረገው ቃለ ምልልስ የውውይትና የቃለ ምልልስ ሥነ ሥርዓት፥ እንዲሁም የማስተማር ስልት ተንጸባርቋል።
5/ ጂብሪል ከነቢዩ ፊት ለፊት መቀመጡ ዒልም (ዕውቀት) የሚሰጥበትን ቦታ ማክበርና ከዒልም ቦታ ላይ መጠበቅ የሚገባቸውን ሥነ ሥርዓቶች ይመለከታል።
6/ የ"ፍርዱ ቀን" መቼ እንደሚሆን ትክክለኛ ወቅቱን አላህ ለማንም አልገለጸም። ግና የ"ፍርዱን ቀን" መድረሱን የሚጠቁሙ አያሌ ምልክቶች አሉ። ከነኝህም መሐከል ከዚህ ሐዲሥ ውጭ በቃል ሐዲሥ የተጠቀሱት ይገኙበታል። ለምሳሌ፦ የዒሳና የደጃል መምጣት። ፀሐይ በመግቢያዋ የመውጣቷ ክስተት፣ ወዘተ።
7/ ሰዎች ምንጊዜም ቢሆን የአላህን የበላይ ተቆጣጣሪነት መዘንጋት የለባቸውም።
8/ ይህ ሐዲሥ እንደሚጠቁመው የኃላፊነት ቦታዎች አግባብነት ለሌላቸው ሰዎች መያዛቸውንና በወላጆች ላይ የሚፈጸም ግፍ መበራከቱ የፍርዱ ቀን መቃረቡን ይጠቁማሉ።
9/ ሙስሊም የዲኑን መሠረቶች ሊጠብቅና ከአላህ የተጠያቂነት ስሜት አድሮበት እያንዳንዱን ተግባር አላህን በመፍራት ስሜት ሊያከናውን ይገባል።

Umma Life
https://ummalife.com/MuslimEthio

ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1

Muslim ሙስሊም

12 Jan, 10:39


#እውነተኝነት

#ክፍል_5

#ሐዲሥ 4 / 58

አቡ ሁረይራ እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ እንዲህ ሲሉ ተናግረዋል፦ "ከአላህ ነቢያት አንዱ ለዘመቻ ቀን ቀንሳቀሰ። "ሴት አጭቶ ጋብቻውን ያልፈፀመ፥ ቤት ሠርቶ ጣሪያውን ያልከደነ፥ ያረገዘች ፍየል ወይም ግመል ገዝቶ መውለዷን የሚጠባበቅ ሰው አይከተለኝ" በማለት ተከታዮቹን አዘዘ። ለዘመቻ ወጣ። ዐስር ወቅት ላይም እዚያው አካባቢ ከአንዲት መንደር ደረሱ። "እኔም አንችም ታዛዦች ነን" አላት _ለፀሐይዋ። "አላህ ሆይ! እንዳትጠልቅ አዘግይልን" በማለትም አላህን ለመነ። አላህ ድልን እስኪያቀዳጀው ድረስ ፀሐይዋ ሳትጠልቅ ቆየች። ምርኮውን ሰበሰበ። እሳቷ ልትበላው መጠች። አልበላችውም። "ከመካከላችሁ ምርኮ ደብቆ ያስቀረ ሰው አለ። ከእያንዳንዱ ጎሣ አንዳንድ ሰው እየመጣ ከኔ ጋር ቃልኪዳን ይጋባ" አለ። የአንድ ሰው እጅ ከእጁ ላይ ተጣብቆ ቀረ። "ከእናንተ መካከል ምርኮ የደበቀ አለ። የጎሣህ አባላት ከኔ ጋር ቃልኪዳን ይጋቡ" አለው። የሁለት ወይም የሦስት ሰው እጆች ከእጁ ጋር ተጣብቀው ቀሩ። "ምርኮ ደብቃችኋል" አላቸው። የሦስት ሰው ጭንቅላት የሚያክል ወርቅ ይዘው መጡ። ከምርኮው ጋር ቀላቀላቸው። እሳት ወረደችና ምርኮውን በላች። ከኛ በፊት ለማንም ምርኮ ሐላል (የተፈቀደ) አልነበረም። ከዚያም አላህ ደካማነታችንን በመገንዘብ ለኛ ሐላል (የተፈቀደ) አደረገልን።" (ቡኻሪና ሙስሊም)

ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች

1/ ቁርጡቢይ እንዳሉት፦ "ይህ ነቢይ ከተከታዮቹ በተጠቀሱት ሦት ሁኔታዎች ሥር የሚገኙትን እንዳይከተሉት ከልክሏል። ምክንያቱም እነኝህ ሰዎች ልቦናቸው በነኝህ ጎዳዮች የተንጠለጠለ በመሆኑ ወደኋላ እየተጎተተ ያስቸግራቸዋል። ለትግልና መስዋዕትነት የሚያስፈልገው ቆራጥነትና ብርታት ይጎድላቸዋል።
2/ የኚህ ነቢይ አባባል ግልጽ ነው። ለጂሃድ የሚንቀሳቀስ ሰው ከሌሎች ሐሳቦችና እንቅፋቶች ነፃ መሆን ይኖርበታል። በእውነተኛ ስሜትና ቆራጥነት መንቀሳቀስ እንዲችል።
3/ ግዑዛን ነገሮችና እንስሳት አንድን ነገር የመፈፀም ወይም ያለመፈፀም ምርጫ የላቸውም። በአላህ ትእዛዝ ሥር ብቻ ነው የሚንቀሳቀሱት። የሰው ልጆች ግን ለእንቅስቃሴያቸው ነፃነት ተሰጥቷቸዋል። ለእያንዳንዱ ድርጊታቸውም በኃላፊነት ይጠየቃሉ።
4/ ነቢያት ተአምራትን የመፈጸም ችሎታ አላቸው። ባለፉት ዘመናት የአንድ ምርኮ ከአላህ ዘንድ ተቀባይነት ማግኘት ምልክቱ እሳት ከሰማይ ወርዶ ያን ምርኮ መብላቷ ነበር። በኢስላም ግን አላህ ምርኮን ለነቢዩ ተከታዮች የተፈቀደ አድርጎታል። ይህ ለነቢዩ ሙሐመድ ከተሰጡ ልዩ ዕድሎች አንዱ ነው።

Umma Life
https://ummalife.com/MuslimEthio

ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1

Muslim ሙስሊም

12 Jan, 09:03


ምድር ላይ ከሚከሰቱ አደጋዎች የሚወሰዱ ትምህርቶች _ ኡስታዝ አህመድ አደም _ Hadis Amharic _ Ustaz ahmed adem _ #የመሬት_መንቀጥቀጥ.mp3

Muslim ሙስሊም

11 Jan, 10:10


#እውነተኝነት

#ክፍል_4

#ሐዲሥ 4 / 57

አቡ ሣቢት ሰህል ኢብኑ ሑነይፍ (ረ.ዐ) -አቡ ሰዒድ አቡል ወሊድም ይባላሉ፣ በድር ዘመቻ ላይ የተካፈሉ ሰው ናቸው- እንዳስተላለፉት ነቢዩ (ሶ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል፦ “ሰማዕትነትን አላህን በእውነት የተማጸነ፡ አላህ ወደ ሰማዕታት ደረጃ ያዘልቀዋል፤ ፍራሹ ላይ ቢሞትም እንኳ።” (ሙስሊም)

ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገር

1/ ወደ ታላቅ ደረጃ ለመዝለቅ የቀልብ እውነተኝነት ወሳኝ ነው። አንድን መልካም ተግባር ለመፈጸም ከልብ የተመኘ በተለያዩ ምክንያቶች መፈጸም ቢሳነውም እንኳ ምንዳውን ያገኛል።
2/ ሰማዕትነትን ከልብ መመኘት የተወደደ ነው።

Umma Life
https://ummalife.com/MuslimEthio

ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1

Muslim ሙስሊም

08 Jan, 13:25


#እውነተኝነት

#ክፍል_3

አላህ እንዲህ ብሏል፦
“እውነተኞች በኾኑ ኖሮ ለእነርሱ የተሻለ በኾነ ነበር።” (ሙሐመድ፡ 21)

#ሐዲሥ 4 / 56

አቡ ሱፍያን ሶኸር ኢብኑ ሐርብ (ረ.ዐ) ስለ ሂረቅል በተረኩት ረዥም ትረካቸው እንዳወሱት፦ ሂረቅል፦ “የሚያዛችሁ ነገር ምንድን ነው?” ሲል ጠየቃቸው -ነቢዩን (ሶ.ዐ.ወ) መሆኑ ነው። “እንዲህ አልኩት” ይላል አቡ ሱፍያን፦ “አላህን ብቻ አምልኩ። በርሱ ላይ ማንንም አታጋሩ። አባቶቻችሁ የሚሉትን ነገር ተዉ፤” ይላል። “ሶላት እንድንሰግድ፤ እውነት እንዲንናገር፤ ሐራም ከሆኑና ክብርን ከሚያጎድፉ ጸያፍ ተግባራት እንድንቆጠብና ዝምድናን እንድንቀጥል ያዘናል።”
(ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል)

ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች

1/ የአላህ መልዕክተኛ (ሶ.ዐ.ወ) እውነተኝነት ባሕሪያቸው እንደሆነና በዚህ ባሕሪያቸው ከሰዎች ዘንድ እንደሚታወቁ፤ ጠላትም እንደመሰከረላቸው ይህ ዘገባ ያመለክታል።
2/ የዚህ “ዲን” መሠረት አላህን በብቸኝነት ማምለክና በርሱ ላይ የትኛውንም አካል “አለማሻረክ” (አላማጋራት) ነው። ይህ ነው የመልካም ሥነ-ምግባር ሁሉ በላጭ።
3/ ሌሎችን በጭፍኑ የመከተል አደገኛነት -በተለይም በዲን ጉዳይ ላይ።

Umma Life
https://ummalife.com/MuslimEthio

ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1

Muslim ሙስሊም

07 Jan, 10:38


#እውነተኝነት

#ክፍል_2

አላህ እንዲህ ብሏል፦
“እውነተኞች ወንዶችና እውነተኞች ሴቶችም” (አል-አሕዛብ፡ 35)

#ሐዲሥ 4 / 55

አቡ ሙሀመድ ሐሰን ኢብኑ ዐሊይ ኢብኑ አቢ ጧሊብ (ረ.ዐ) እንዲህ ሲሉ አስተላልፈዋል፦ ከአላህ መልዕክተኛ (ሶ.ዐ.ወ) ጠቃሚ ምክር ይዣለሁ፦ “የሚያጠራጥርህን ነገር በመተው የማያጠራጥርህን ያዝ። እውነት ውስጣዊ ሰላምና መረጋጋት ሲሆን፤ ሐሰት ደግሞ ጥርጣሬና የልቦና አለመረጋጋት ነው።”
(ቲርሚዚይ ዘግበውታል፡ ሐዲሱን “ሐሰን” ነውም ብለዋል)

ከሐዲሡ የምንማረው ቁምነገር

=› አሻሚ ነገሮችን በመተው ሐላል ወደሆኑ ነገሮች መዘንበል እጅግ ጠቃሚ ነው። ከአሻሚ ነገሮች የራቄ ዲኑንም፤ ክብሩንም ጠብቋልና።

Umma Life
https://ummalife.com/MuslimEthio

ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1

Muslim ሙስሊም

06 Jan, 08:20


#እውነተኝነት

#ክፍል_1

አላህ እንዲህ ሲል ተናግሯል፦

“እናንተ ያመናችሁ ሆይ! አላህን ፍሩ፤ ከእውነተኞቹም ጋር ኹኑ።” (አት-ተውባህ፡ 119)

#ሐዲሥ 4 / 54

ኢብኑ መስዑድ (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ (ሶ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል፦ “እውነት ወደ መልካም ተግባር ይመራል፤ መልካም ተግባር ደግሞ ወደ ጀንነት ይመራል። አንድ ሰው እውነት ይናገራል አላህ ዘንድ እውነተኛ የሚል እስኪጻፍ ድረስ። ሐሰት ደግሞ ወደ መጥፎ ተግባር ይመራል፤ መጥፎ ተግባር ደግሞ ወደ ጀሀነም ይመራል። አንድ ሰው ሐሰትን ይናገራል አላህ ዘንድ ሐሰተኛ ተብሎ እስኪጻፍ ድረስ።” (ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል)

ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች

1/ እውነት የመናገር ጠቃሚነት -እውነት የመልካም ነገሮች ሁሉ ምክንያት ነውና። ከሐሰት መጠንቀቅ -ሐሰት የመጥፎ ነገሮች ሁሉ ምንጭ ነውና። አንድን ባሕሪ የተላበሰ ሰው በዚያው ባሕሪው ሊጠራ ይገባል።
2/ ምንዳ ወይም ቅጣት የሰው ልጅ በሚሠራው መልካም ወይም መጥፎ ተግባር ላይ የተንተራሰ ነው።

Umma Life
https://ummalife.com/MuslimEthio

ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1

Muslim ሙስሊም

05 Jan, 09:51


#ትዕግሥት (#ሶብር)

#ክፍል_29

#ሐዲሥ 3 / 53

አቡ ኢብራሂም ዐብደላህ ኢብኑ አቡ አውፋ እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ ጠላትን ለመግጠም ከወጡባቸው ቀናት በአንዷ ፀሐይ ዘንበል እስክትል ድረስ ከጠበቁ በኋላ ከሰዎች መካከል በመቆም፦ "እናንተ ሰዎች ሆይ! ከጠላት መግጠምን አትመኙ፤ አላህን ሰላምን ለምኑት። ከገጠማችኋቸው ደግሞ ትዕግስት ይኑራችሁ። ጀነት ከሾተል ጥላ ሥር መሆኑን እወቁ።" ካሉ በኋላ፦ "ኪታብን ያወረድክ፥ ደመናን የምትነዳ፥ የከሓዲያንን ጥርቅም አሸናፊ የሆንከው አላህ ሆይ! አሸንፋቸው፤ በነርሱ ላይ ድልን አቀዳጀን።" ሲሉ አላህን ተማጸኑ። (ቡኻሪና ሙስሊም)

ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች

1/ ለጂሃድ ምንጊዜም ዝግጁ ሆኖ መገኘት። ኃይልን ማደራጀትና ጠላትን ፊት ለፊት መግጠም፥ ከኃጢአት መጽዳት፣ እውነተኛ ተውበትና ከልብ ወደ አላህ መመለስ ከጂሃድ ዝግጅት ውስጥ የሚካተቱ ናቸው።
2/ በጭንቀት ወቅት፥ በመከራ ሰዓት ዱዓ ማድረግ ሸሪዓዊ መሆኑ።
3/ ነቢዩ ለባልደረቦቻቸውና ለተከታዮቻቸው የነበራቸው ርኅራኄ።
4/ ከጠላት መግጠምን መመኘትን ነቢዩ መከልከላቸው።
5/ ጥንቁቅነትን፣ ቅንጅትንና ቁርጠኝነትን ችላ በማለት በቁሳዊ ኃይል ብቻ አለመመካት።
6/ "ሶብር" (ትዕግስት) ለጂሃድ ከሚያስፈልጉ ትጥቆችና መሣሪያዎች አንዱና ዓይነተኛው ነው።

Umma Life
https://ummalife.com/MuslimEthio

ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1

Muslim ሙስሊም

04 Jan, 07:59


#ትዕግሥት (#ሶብር)

#ክፍል_28

#ሐዲሥ 3 / 52

አቡ የሕያ ኡሰይድ ሑደይር እንዳስተላለፉት አንድ አንሷር ሰው፦ "የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! ለእገሌ ሹመት እንደሰጡት ለኔም ሹመት አይሰጡኝም?" ሲል ጠየቃቸው። "ከኔ በኋላ አድሏዊነት ይገጥሟቸዋል። "ሐውድ" ላይ እስክታገኙኝ ድረስ ትዕግስት ይኑራችሁ" አሉት። (ቡኻሪና ሙስሊም) "ሐውድ" አላህ ለነቢዩ ብቻ ጀነት ውስጥ ቃል የገባላቸው ምንጭ ነው።


ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች

1/ የነቢዩ ተአምር፤ ወደፊት ስለሚከሰቱ ሁኔታዎች መናገራቸው።
2/ ችሎታ ያለውና ለቦታው ብቁ የሆነ ተቀናቃኝ የሌለበት ሁኔታ እስካልሆነ ድረስ ሹመትን አለመፈለግ በላጭነት እንዳለው።
3/ የነቢዩ አርቆ አስተዋይነትና ለቦታው ብቃት የሌላቸው ሰዎች አለመሾማቸው።
4/ ብቃት የሌላቸው ሰዎች ከሥልጣን ኮርቻዎች ላይ በሚወጡበትና ነገሮች በሚበላሹበት ወቅት ትዕግስት እጅግ ጠቃሚ ነው።

Umma Life
https://ummalife.com/MuslimEthio

ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1

Muslim ሙስሊም

02 Jan, 09:48


#ትዕግሥት (#ሶብር)

#ክፍል_27

#ሐዲሥ 3 / 51

ኢብኑ መስዑድ እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ፦ "ከኔ በኋላ አድሏዊነትና ተቀባይነት የሌላቸው የተሳሳቱ ጉዳዮች የሚከሰቱበት ሁኔታ ይኖራል" በማለት ተናገሩ። "የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! እንዲህ ዓይነት ሁኔታዎች በሚገጥሙን ወቅት ምን እንድናደርግ ያዙናል?" በማለት ጠየቋቸው። "ግዴታችሁን በመወጣት መብታችሁን ከአላህ ትጠይቃላችሁ።" ሲሉ መለሱ። (ቡኻሪና ሙስሊም)

ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች

1/ በአላህ ዕቅድና ፕላን የተፈፀሙ ሁኔታዎችን በጸጋ መቀበልና ማስተናገድ እንደሚገባ።
2/ ለአላህ ፍላጎት ተገዥነት።
3/ በኢስላማዊው ሥርዓት ውስጥ በታሪክ አጋጣሚ የሚከሠቱ ከኢስላም መንፈስ ያፈነገጡ የሙስሊም ኅብረተሰብ መሪዎችን ከሥልጣናቸው በአመጽ ለማውረድ መሞከር የባሰ ጥፋት የሚያስከትል ሆኖ ከተገኘ ችግሩን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ጥረት ማድረግና አላህንም ነገሮቹን መልካም በሆነ መልኩ ያስኬዳቸው ዘንድ መማጸን ተገቢ ነው።

Umma Life
https://ummalife.com/MuslimEthio

ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1

Muslim ሙስሊም

01 Jan, 09:15


#ትዕግሥት (#ሶብር)

#ክፍል_26

#ሐዲሥ 3 / 50

ኢብኑ ዐብባስ እንዲህ ሲሉ አስተላልፈዋል፦ ዑየይነህ ኢብኑ ሒስን (ወደ መዲና) በመምጣት ከወንድሙ ልጅ ከሑር ኢብኑ ቀይስ ዘንድ አረፈ። ሑር ዑመር ከሚያቀርባቸው ሰዎች አንዱ ነበር። የቁርአንን መልዕክት የመረዳት የላቀ ችሎታ ያላቸው ሰዎች _ወጣቶች ይሁኑ ሽማግሌዎች_ የዑመር ችሎት አባላትና አማካሪዎችም ነበሩ። "የወንድሜ ልጅ ሆይ! በዚህ አዛኝ (መሪ) ዘንድ ተደማጭነት ያለህ ሰው ነህና ከፊቱ መቅረብ እችል ዘንድ ፈቃድ ጠይቅልኝ" በማለት ዑየይነህ የወንድሙን ልጅ ይጠይቃል። ፈቃድ ጠየቀለት። ዑመር ፈቀዱለት። ዑመር ዘንድ በቀረበ ጊዜ፦ "በአላህ እምላለሁ! የኸጣብ ልጅ! በርከት ያለ ስጦታ አትሰጠንም፤ በፍትህ አትፈርድልንም" በማለት ተናገረ። ዑመር አለቅጥ ተቆጡ። ሊቀጡት እስኪከጅሉ። ሑር እንዲህ አላቸው፦ "የሙእሚኖች አሚር ሆይ! አላህ ለነቢዩ፦ "ገርን ጠባይ ያዝ፤ በመልካም እዘዝ፤ ባለጌዎችንም ተዋቸው" ብሏቸዋል። ይህ ሰው ደግሞ ከባለጌዎች አንዱ ነው።" ሑር ይህንን የቁርአን አንቀጽ ባነበበት ወቅት ዑመር ቁጣቸው በረደ። ዑመር የአላህ መጽሐፍ (መመሪያ) ቅንጣት የማይተላለፉ ሰው ነበሩ። (ቡኻሪ ዘግበውታል)

ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች

1/ የቁርአንን መልዕክትና መንፈስ የተረዱ ሰዎች የላቀ ደረጃ እዚህ ሐዲሥ ላይ ተጠቁሟል። ይህንን የክብር ደረጃ የተቸሩት የቁርአንን መልዕክት ተረድተው ወደ ተግባር የለወጡት ዑለሞች እንጅ ቁርአንን ለዓለማዊ ጥቅም ማካበቻ ያረጉት ክፍሎች አይደሉም።
2/ መሪዎችና አስተዳዳሪዎች መልካም አማካሪዎችን መያዝ እንዳለባቸው ይህ ሐዲሥ ይጠቁማል።

Umma Life
https://ummalife.com/MuslimEthio

ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1

Muslim ሙስሊም

31 Dec, 09:58


#ትዕግሥት (#ሶብር)

#ክፍል_25

#ሐዲሥ 3 / 49

አቡ ሁረይራ (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ (ሶ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋ፦ “በራሱ፣ በልጁና በገንዘቡ በኩል በሙእሚን ላይ መከራዎች ከመውረድ አይቦዝኑም፤ ከወንጀል የጸዳ ሆኖ አላህን እስኪገናኝ ድረስ።” (ቲርሚዚይ ዘግበውታል፡ ሐዲሱን “ሐሰኑን ሶሒሕ” ብለውታል)

ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች

1/ ሙእሚን በተለያዩ ችግሮችና መከራዎች ይፈተናል።
2/ ይህ ዘገባ መከራ ለሚደርስበት ሙእሚን ብስራትን አዝሏል።

Umma Life
https://ummalife.com/MuslimEthio

ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1

Muslim ሙስሊም

31 Dec, 09:10


ጀነት ገባ.mp3

Muslim ሙስሊም

30 Dec, 20:33


ሦስት ነገሮችን ከሰዎች ደብቅ .mp3

Muslim ሙስሊም

30 Dec, 09:08


ሒሳቡ ዛሬ ነው ርካሽ.mp3

Muslim ሙስሊም

30 Dec, 08:09


#ትዕግሥት (#ሶብር)

#ክፍል_24

#ሐዲሥ 3 / 48

አቡ ሁረይራ እንዳስተላለፉት አንድ ሰው ነቢዩን፦ "ምክር ይለግሱኝ" አላቸው። "አትቆጣ" አሉት። በተደጋጋሚ ጠየቃቸው። "አትቆጣ" የሚል ተደጋጋሚ ምላሽ ሰጡት። (ቡኻሪ ዘግበውታል)

ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች

1/ የቁጣ አጥፊነትና የሚያስከትለው ጉዳት።
2/ የቁጣ ውግዝነትና የመራቅ አስፈላጊነት።
3/ የተወገዘው ከዓለማዊ ጥቅምና ፍላጎት ጋር የተያያዘ እንደሆነ ብቻ ነው። ለአላህና ለዲኑ ሲባል የሚከሰት ቁጣ ሊወደስና ሊበረታታ ይገባል። ነቢዩ የአላህ ክልክሎች ሲደፈሩ ይቆጡ እንደነበር ይነገራል።

Umma Life
https://ummalife.com/MuslimEthio

ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1

Muslim ሙስሊም

29 Dec, 08:04


#ትዕግሥት (#ሶብር)

#ክፍል_23

#ሐዲሥ 3 / 47

ሙዓዝ ኢብኑ አነስ (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት ነቢዩ (ሶ.ዐ.ወ) እንዲህ ሲሉ ተናግረዋል፦ “መበቀል እየቻለ ቁጣውን የተቆጣጠረ ሰው አላህ የቂያማ ዕለት ከሰዎች መካከል ጥሪ ያቀርብለታል። ከሑረል-ዐይን ያሻውን እንዲመርጥም ይጋብዘዋል።” (አቡ ዳውድና ቲርሚዚይ ዘግበውታል፤ ሐዲሡን “ሐሰን” ነውም ብለዋል)

ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች

1/ ቁጣን የመቆጣጠር አስፈላጊነትና ጠቀሜታ።
2/ መበቀል እየቻሉ በይቅርታ ማለፍ ከፍተኛ ግምት ይሰጠዋል።

Umma Life
https://ummalife.com/MuslimEthio

ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1

Muslim ሙስሊም

28 Dec, 21:08


(4)የልብ መስፋትና መረጋጋትን ለማግኘት የሚረዱ ነገሮች ዝግጅት ኢማሙ ኢብኑል ቀይም ዛዱል መዓድ በተሰኘው ኪታባቸው በኡስታዝ አሕመድ ሸይኽ ኣደም@ዛዱል መዓድ-.mp3

Muslim ሙስሊም

26 Dec, 09:22


#ትዕግሥት (#ሶብር)

#ክፍል_22

#ሐዲሥ 3 / 46

ሱለይማን ኢብኑ ሱረድ (ረ.ዐ) እንዲህ ሲሉ አስተላልፈዋል፦ “ከነቢዩ (ሶ.ዐ.ወ) ጋር ተቀምጬ ነበር። ሁለት ሰዎች ይሰዳደባሉ። አንደኛው ፊቱ ቀልቷል። የደም ሥሩ ተግተርትሯል።” “አንዲት አባባል አውቃለሁ። እርሷን ቢናገር ቁጣው ይበርድለታል። “ከተረገመው ሰይጣን በአላህ እጠበቃለሁ።” ቢል ቁጣው ይወገድለታል” አሉ የአላህ መልዕክተኛ (ሶ.ዐ.ወ)። “ነቢዩ (ሶ.ዐ.ወ)፡ ከተረገመው ሰይጣን በአላህ ተጠበቅ” ብለውሃል” አሉት (ሰዎች)። (ቡኻሪና ሙስሊም)

ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች

1/ ይህ የሐዲስ ዘገባ ከሰባተኛው የቁርአን ምዕራፍ የ200ኛውን አንቀጽ መንፈስ ያንፀባርቃል። ቁጣን የሚያጭረው ሰይጣን ነው። በዲንም ሆነ በዱንያ የሚያስከትለውን ጉዳት ስለሚያውቅ። ስለዚህ ከዚህ የሰይጣን ተንኮል የአላህን ጥበቃ በመሻት መከላከል ያስፈልጋል።
2/ ነቢዩ (ሶ.ዐ.ወ) በእያንዳንዱ አጋጣሚ፣ ክስተትና ሁኔታ ተከታዮቻቸውን አቅጣጫ ለማስያዝና ለመምራት የነበራቸውን ጉጉት ይህ ዘገባ ያሳያል።

Umma Life
https://ummalife.com/MuslimEthio

ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1

Muslim ሙስሊም

25 Dec, 08:01


#ትዕግሥት (#ሶብር)

#ክፍል_21

#ሐዲሥ 3 / 45

አቡ ሁረይራ (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ (ሶ.ዐ.ወ) እንዲህ ሲሉ ተናግረዋል፦ “ኃይል ማለት ተፎካካሪዎቹን ታግሎ የሚያሸንፍ ሳይሆን፡ በቁጣ ወቅት ራሱን መቆጣጠር የሚችል ነው።” (ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል)

ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች

1/ ኢስላም በዘመነ-ድንቁርና (ጃሂሊያ) ኃይል ተሰጥቶት የነበረውን የተሳሳተ ትርጓሜ ውብ ወደሆነ ሥነ-ምግባራዊ ማኅበራዊ ትርጓሜ ለውጦታል።
2/ ራስን ታግሎ ማሸነፍ፡ መቆጣጠርና መምራት መቻል ጠላትን ከማንበርከክ ይበልጥ አስቸጋሪ ፈታኝ ነው።
3/ ከቁጣ መራቅ ተገቢ ነው። አካላዊ፣ አዕምሯዊና ማኅበራዊ ጉዳቶችን ስለሚያስከትል።

Umma Life
https://ummalife.com/MuslimEthio

ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1

1,113

subscribers

3,259

photos

331

videos