ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ሰራተኞች በሙሉ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ቀዳማዊ መሠረታዊ የሠራተኛ ማህበር (EAGPBTU) ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ መሠረታዊ የሠራተኛ ማህበር (EAGBTU) ጋር ታሪካዊ ዉህደት ባደረገ ማግስት የመጀመሪያዉን የመክፈቻ የምክር ቤት ጉባኤውን አደረገ።
አዲስ አበባ ፣ ኢትዮጵያ ጥቅምት 10 ቀን 2017 ዓ.ም
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ቀዳማዊ መሠረታዊ የሠራተኛ ማህበር ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ መሠረታዊ የሠራተኛ ማኅበር ጋር ያደረገዉን ታሪካዊ ውህደት ተከትሎ የመጀመሪያዉን የምክር ቤት ጉባኤ በተሳካ ሁኔታ ጥቅምት 7 እና 8 ቀን 2017 ዓ.ም ያደረገ ሲሆን ይህም ሠራተኛ ማህበሩ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ሰራተኞችን ውክልና እና ድምጽ ለማጎልበት የሚያደርገውን ጥረት አዲስ ምዕራፍ የሚያመለክት ነው።
ጥቅምት 7 እና 8 በኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና መስሪያ ቤት የተካሄደው የሁለት ቀናት ጉባኤ ከሁለቱም የቀድሞ ማህበራት የተውጣጡ እና አሁን በአንድ አመራር የተዋሃዱ መሪዎችን አሳትፏል። ቀዳሚ አጀንዳው የሰራተኞችን ጉዳይ ለመፍታት ስትራቴጂ በመቅረጽ እና የሰራተኞችን ጥቅም ማስጠበቅ፣ እንከን የለሽ ሽግግርን ማረጋገጥ እና ለቀጣይ ተግባራት መሰረት መጣል ላይ ያተኮረ ነበር።
የመጀመሪያ ቀን አዲስ የተቋቋመው ምክር ቤት በመተዳደሪያ ደንቡ መሠረት ማህበሩን በቅንነት፣በታማኝነት እንዲሁም በታላቅ የአደራ ስሜት እንዲመሩ አቶ መገርሳ አስፋው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ቀዳማዊ መሠረታዊ የሠራተኛ ማህበር ፕሬዝደንት ሆነው እንዲያገለግሉ በምክር ቤቱ ሙሉ ድምፅ መርጧል። ከዚህም በመቀጠል ፕሬዝደንት መገርሳ አስፋው በመተዳደሪያ ደንቡ መሠረት ሶስት የአብራሪ ሰራተኞችን ጨምሮ 12 (አስራ ሁለት) አባላት ያሉትን የስራ አስፈፃሚ አካላትን ፤ እንዲሁም 3 (ሶስት) አባላትን ያቀፈ የስራ ሂደት ገምጋሚ አካላትን ለምክር ቤቱ በማቅረብ አፀድቀዋል።
ከዚህም በማስከተል አቶ መገርሳ እና የምክር ቤት ቡድናቸው ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና የስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው እና WST ማናጅመንት ጋር ወደተዘጋጀው የምሳ እና የትዉውቅ መርሀ ግብር በክብር ተጋብዘዋል። በመርሀ ግብሩ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ቀዳማዊ መሠረታዊ የሠራተኛ ማህበር የስራ አስፈፃሚ አካላት እንዲሁም የምክር ቤት አባላት ከድርጅቱ የስራ አስፈፃሚ አካላት ጋር ትዉውቅ ያደረጉ ሲሆን ቀጣዩን የስራ ዘመን የሰራተኛ መብት ፣ጥቅማ ጥቅም እና የስራ ዋስትና በሚረጋገጥበት እንዲሁም አመቺ የስራ ሁኔታ በሚፈጠርበት አግባብ ላይ በመነጋገር እና በመደራደር ዉጤት ተኮር የሆነ ስራ በጋራ ለመስራት የኢትዮጲያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው እና የኢትዮጲያ አየር መንገድ ግሩፕ ቀዳማዊ መሠረታዊ የሠራተኛ ማህበር ፕሬዝደንት አቶ መገርሳ አስፋዉ በቅርበት ለመስራት ያላቸውን ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል።
ውጤት ተኮር የአመራር ስልት በመከተል የሚታወቁት አቶ መገርሳ አስፋዉ የሁለቱን ማህበራት ዉህደት እዉን ለማድረግ ቁልፍ ሚና የተጫወቱትን የቀድሞ የማሕበሩ አመራሮችን ያመሰገኑ ሲሆን በዚሁ ቀን ከቀትር በኋላ ዉሎ የማህበሩ የስራ አስፈፃሚ አባላት በተገኙበት በቅርቡ ማህበራችን ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ መሠረታዊ የሠራተኛ ማህበር ጋር ያደረገዉን የዉህደት ስምምነትን አስመልክቶ ይፋዊ ጋዜጤዊ መግለጫ ሰጥቷል።
ሁለተኛ ቀን ማለትም ጥቅምት 8 ቀን 2017 ዓ.ም ምክር ቤቱ እና የስራ አስፈፃሚው መልሶ የተገናኘ ሲሆን በወሳኝ ኹነቶች ላይ ውይይት አድርጓል። ምቹ የስራ ሁኔታን ለመፍጠር፣የሰራተኛ መብትን ለማስጠበቅ፣የሰራተኞች ጥቅማ ጥቅም ለማሳደግ እና የስራ ደህንነትን ለማረጋገጥ ትኩረት ተሰጥቷል። በዉይይቱ መክፈቻ የማህበሩ ፕሬዝደንት አቶ መገርሳ አስፋዉ ለአስራ ሁለቱ የስራ አስፈፃሚ አካላት የስራ ድርሻ ክፍፍል ያደረጉ ሲሆን በተሰጣቸው የስራ ኀላፊነት በ ኮርፖሬት ደረጃ መዳሰስ ያለባቸዉን የሠራተኛ የወል ጉዳዮች ላይ ከድርጅቱ የበላይ አካላት ጋር በመነጋገር እና በመደራደር አመርቂ ውጤት እንዲያስመዘግቡ በፅኑ አሳስበዋል። አቶ መገርሳ አስፋዉ አክለውም በመጪዎቹ ሶስተ ወራት መሠራት ስለሚገባቸው የሠራተኛው የወል ጉዳዮች እንዲሁም በዲቪዥን ደረጃ ስለሚፈቱ ጉዳዮች የትኩረት አቅጣጫወችን አስቀምጠው ማብራሪያ ሰተዉበታል። በዚህም መሠረት የወል ጉዳዮች ተብለው ለተዘረዘሩት አንኳር ነጥቦች ሶስት አባላትን የያዘ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ስራ እንዲገባ ተደርጓል ፤ ከዚህ በተጨማሪ በ ዲቪዥን ደረጃ ለሚፈቱ ጉዳዮች የማህበሩን ምክትል ፕሬዝደንት እና ጀነራል ሰክሬተሪን ጨምሮ ሁለት ሁለት አባላትን የያዘ ታስክ ፎርስ በመጪወቹ ሣምንታት በሁሉም የድርጅቱ ከፍተኛ ስራ አስፈፃሚ የሚመሩ ክፍሎች ጋር ጉዳዮቹ መፍትሔ በሚያገኙበት አግባብ ዉይይት እንዲደረግ አቅጣጫ ተሰትዋል። የእነዚህን ጉዳዮች አስፈላጊነት ከግምት ውስጥ በማስገባት የተቋቋሙት ግብረ ሃይሎች የሰራተኛ ማህበሩን ስትራቴጂካዊ ግቦችን በተቻለ መጠን በአጭር ጊዜ ውስጥ ተግባራዊ ለማድረግ አዲሱ አመራር ተጨባጭ ውጤት ለማምጣት ቁርጠኛ ነው ብለዋል አቶ መገርሳ።
ፕሬዝደንቱ ስለ ማህበሩ የወደፊት ተስፋ ያላቸውን ስሜት ገልፀው፣ ይህ ውህደት ሰራተኞቻችንን የሚወክል ጠንካራ የመደራደር አቅም ያለው አመራር ፈጥሯል ፤ ይህም የሁሉም ሰራተኞች የስራ ደህንነትና ጥቅማ ጥቅምን ለማሻሻል እና ለመጠበቅ ትልቅ እርምጃ እንደሚወስድ ገልጸዋል።
በመጨረሻም የማህበሩ ፕሬዝደንት አቶ መገርሳ አስፋው የስራ አስፈፃሚ አካላቱን እንዲሁም የምክር ቤት አባላቱን ከተከበረዉ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሠራተኞች የተጣለበትን ታላቅ አደራ በብቃት እና በቁርጠኝነት እንዲወጣ የአደራ መልእክታቸውን አሰተላልፈዋል።
ለበለጠ መረጃ ከታች ባለው አድራሻ ይጎብኙን:
Mr. Motolomi Bitena
EAGPBTU Executive and Communication officer
Phone: +251901224581
Building a Strong Future Together!!
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ቀዳማዊ መሠረታዊ የሠራተኛ ማህበር!!!
Ethiopian Airlines Group Primary Basic Trade Union (EAGPBTU)