ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹 @amen122621 Channel on Telegram

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

@amen122621


እዚህ Channel ላይ ኦርቶዶክሳዊ ስብከት ፣መዝሙር ፣ኬነጥበቦች እና መፅሕፍት ይለቀቁበታል
"ጌታ ሆይ እናትህን ማን ብለን እንጥራት? እናት ብቻ እንዳንላት ድንግል ሆና አገኘናት ፣ ድንግል እንዳንላት ልጅ ታቅፋ አየናት። ጌታ ሆይ እናትህን ለመጥራት እንዲህ የሚያስቸግር ከሆነ አንተን ከቶ ምን ብለን እንጠራሃለን??"


ቅዱስ ኤፍሬም

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹 (Amharic)

እዚህ Channel ላይ ኦርቶዶክሳዊ ስብከት ፣ መዝሙር ፣ ኬነጥበቦች እና መፅሕፍት ይለቀቁበታል። ለእርስዎ መልእክት፣ ታላቅ ምሩፅን ያሳርፋል እና እየለቀቁ ለእርስዎ የሚልከኝ የእንቅስቃሴ እይቅና ስርዓት ላይ እንዲያደርጋት የመጣውን ከሆነ በእርስዎያት አወዳደርገው። ቅዱስ ኤፍሬም አሁን ተዘላለማዊ ተኮሯኛ በመንካት አድርገው ለበአሉት ሁኔታቸውን ስንሰማስ፣ በይሁዳ አዲስ አበባ ላይ በጀርሷን ያጋጠመችውን እልባት ይኖራል።

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

12 Feb, 19:57


🕊

† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን †

[  † እንኩዋን ለእናታችን "ቅድስት ማርያም እንተ ዕፍረት" እና "ቅዱስ አቡሊዲስ" ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ †  ]


[ †  🕊  ቅድስት ማርያም  🕊  † ]

ቅድስት ማርያም እንተ ዕፍረት ቅዱስ መጽሐፍ እንደሚለን በስምዖን ቤት የመድኃኔ ዓለምን እግር በእንባዋ አጥባለች:: በፀጉሯም አብሳ የ300 ብር ሽቱ ቀብታዋለች:: ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም የቀደመ ኀጢአቷን ይቅር ብሎ ከ36ቱ ቅዱሳት አንስት ደምሯታል:: [ሉቃ.፯፥፴፮-፶] (7:36-50)

+ ስለዚህች ቅድስት ሙሉ ታሪክ :-

፩. ትርጉዋሜ ወንጌልን
፪. ተአምረ ኢየሱስን
፫. ስንክሳርን እና
፬. መጽሐፈ ግንዘትን በማንበብ ማግኘት ይቻላል::

እንት ዕፍረት [ባለ ሽቱዋ ማለት ነው] ማርያም መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሚያስተምርበት ዘመን [በዘመነ ስብከቱ] የነበረችና ይህ ቀረሽ የማይሏት ቆንጆ ሴት ነበረች:: ግን መልክ የመልካም ነገሮች ምንጭ ሲሆን አይታይም::

በመልካቸው ማማር የጠፉና ያጠፉ ብዙ ሴቶችን ዓለማችን አስተናግዳለች:: ከክሊዎፓትራ እስከ ዘመናችን "ሞዴል" ነን ባዮች : እግዚአብሔር የሰጣቸውን ጸጋ የሰይጣን መደሰቻ : የገሃነም መንገድ አድርገውት ማየት [መስማት] እጅግ ያሳዝናል::

በአንጻሩ ደግሞ ብዙዎችን ያስደመመ መልካቸውን ንቀው : ሰማያዊ ሙሽርነትን የመረጡትን ቅዱሳቱን:- አርሴማን : ቴክላን : ጤቅላን : መሪናን : ጣጡስን : ሔራኒን : ኢራኒን : አትናስያን : ሶፍያን : ኢላርያን . . . ስናስብ ደስ ይለናል:: ዛሬም ጌታ በሚያውቀው ብዙ እናቶቻችን [እህቶቻችንም] ተመሳሳዩን በጐ ጐዳና መርጠው እየተጉዋዙ መሆኑን እናውቃለን::

ቅድስት ማርያምም ከፈጣሪዋ በተሰጣት ቁንጅና ክፋትን ትሠራ ዘንድ ሰይጣን ሲያገብራት "እሺ" ብላ የእሱ ወጥመድ ልትሆን ተራመደች:: ለዘመናትም ዓይነ-ዘማ : ልበ-ስስ የሆኑ ወንዶችን ወደ ኃጢአት ጐዳና ማረከች::

ለመልኩዋ ከነበራች ስስት የተነሳም ቶሎ ቶሎ ራሷን በመጽሔት [መስታውት ማለት ነው] ትመለከት ነበር:: መቼም አምላካችን ለሁሉም የመዳን ቀን ጥሪ አለውና [የሚያስተውለው ቢገኝ] ለማርያም ጥሪውን ላከላት:: ጥሪው ግን በስብከት : በመዝሙር : በመጽሐፍ . . . አልነበረም::

እንዳስለመደች ውበቷን ለመመልከት መስታውት ፊት ቆማ የራሷን ጸጉር : ግንባር : ዐይን : አፍንጫ : ጥርስ . . . እየተመለከተች ተደመመች:: ወዲያው ግን ይህ አካል አፈር እንደሚበላው የሚያስብ ልቡና መንፈስ ቅዱስ አምጥቶባት በጣም አዘነች:: የመኖር ተስፋዋ እንዳይቆረጥ ደግሞ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ዜና ሰማች::

መወሰን ነበረባትና ከሞት ወደ ሕይወት : ከጨለማ ወደ ብርሃን ልትሔድ ቆረጠች:: በአምላኩዋ ፊት የሚቀርቡም 3 ስጦታዎችን አዘጋጀች:: ሰይጣን ሊያጣት አልፈለገምና ወደ ክርስቶስ እንዳትደርስስ ብዙ መሰናክልን ፈጠረባት:: ግን ውሳኔዋ የእውነት ነበርና እያሳፈረችው ወደ አምላኩዋ ገሰገሰች::

የስምዖን ዘለምጽ በረኞችም ሊያስቀሰሯት አልተቻላቸውም:: ወደ ውስጥ ዘልቃ የያዘችውን ሁሉ ለመድኃኒታችን ሰዋች::

፩. ከውስጧ እንባዋን:
፪. ከአካሏ ጸጉሯን:
፫. ከንብረቷ ውድ የሆነውን ሽቱ አቀረበች::

ብዙ ወዳለችና ብዙ ኃጢአቷ ተሠርዮ ቅድስት እናታችን ሆነች:: ብዙ አዝማናትን ከሐዋርያት ጋር አገልግላም በዚህች ቀን ዐርፋለች::

" ቅዱስ አቡሊዲስ መምህረ ኩሉ ዓለም "

+ የዓለም ሁሉ መምህር:

¤ ባለ ብዙ ድርሳንና ተግሣጽ:
¤ የቤተ ክርስቲያን ምሰሶ:
¤ ፴፰ [38] ሕግጋትን የደነገገ:
¤ ስለ ቀናች እምነት የተጋደለ:
¤ መራራ ሞትን በደስታ የተቀበለ:
¤ የቀደመችዋ ሮም ሊቀ ዻዻሳት የነበረና:
¤ ሐዋርያትን የመሰለ አባት ነው::

+በ2ኛው መቶ ክ/ዘመን መጨረሻ አካባቢ ያበራው ይሀን ኮከብ ካቶሊካውያን ክደውታል:: እነርሱ "አቡሊዲስ የሚባል ዻዻስ አልነበረም" ቢሉም ምክንያታቸው ግን ከሰይጣን ነው:: ሃይማኖታቸውን ከመለወጣቸው 250 ዓመታት በፊት ስለተናገረባቸውና አንድ ባሕርይን ስላስተማረ መሆኑን ዓለም ያውቃል::

አባታችን ቅዱስ አቡሊዲስ የተገደለ የካቲት ፭ [5] ሲሆን የካቲት ፮ [6] ሥጋው የተገኘበት ነው::

አምላከ ቅዱሳን ከቅድስት ማርያም ንስሃዋን : ከአባ አቡሊዲስ ምሥጢረ ቅድስናውን ያድለን::

[  † የካቲት ፮ [ 6 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት  ]

፩. ቅድስት ማርያም እንተ ዕፍረት
፪. የዓለም ኁሉ መምሕር ቅዱስ አቡሊዲስ [ብዙ መንፈሳዊ ድርሳናትን የደረሰ ሊቀ ዻዻስና ሰማዕት]
፫. ቅዱሳን አቡቂርና ዮሐንስ [ሰማዕታት]
፬. ቅድስት አትናስያና ፫ [3] ቱ ሰማዕታት ልጆቿ [ቴዎድራ : ቴዎፍናና ቴዎዶክስያ]

[    † ወርኀዊ በዓላት    ]

፩. ቅድስት ደብረ ቁስቁዋም
፪. አባታችን አዳምና እናታችን ሔዋን
፫. አባታችን ኖኅና እናታችን ሐይከል
፬. ቅዱስ ኤልያስ ነቢይ
፭. ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሣርያ
፮. ቅዱስ ዮሴፍ አረጋዊ
፯. ቅድስት ሰሎሜ
፰. አባ አርከ ሥሉስ
፱. አባ ጽጌ ድንግል
፲. ቅድስት አርሴማ ድንግል

ከበረከተ ቅዱሳን ይክፈለን::

" . . . አንተ ራሴን ዘይት አልቀባኸኝም:: እርሷ ግን እግሬን ሽቱ ቀባች:: ስለዚህ እልሃለሁ : እጅግ ወዳለችና ብዙ ያለው ኃጢአቷ ተሰርዮላታል:: ጥቂት ግን የሚሰረይለት ጥቂት ይወዳል:: እርስዋንም:- 'ኃጢአትሽ ተሰርዮልሻል' አላት:: ከእርሱም ጋር በማዕድ ተቀምጠው የነበሩት በልባቸው:- 'ኃጢአትን እንኩዋ የሚያስተሰርይ ይህ ማነው' ይሉ ጀመር:: ሴቲቱንም:- 'እምነትሽ አድኖሻል: በሰላም ሒጂ' አላት::" [ሉቃ.፯፥፳፮] (7:46)

† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †

[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]


         †              †               †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖                   🕊                    💖

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

12 Feb, 19:23


እግዚአብሔር ቋንቋን የደበላለቀባቸው ህዝቡ ምን በማድረጋቸው ነው?

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

12 Feb, 18:33


አርሴማን ጥሩልኝ 🥺
ክፍል ፩
ልክ የዛሬ 15 አመት ነበረ ይህ ነገር  የሆነው ብዙ ጊዜ እግዚአብሔርን ለምን  ልጅ አልሰጠኸኝም ብለው ሲያማርሩ ብሎም ሆስፒታል ሄደው ሲፈላሰፉ አስተውላለሁ እኔና ባለቤቴ ግን አንድም ቀን እንኳን አማረን አናውቅም ልክ መስከረም 28 ቀን በተኛንበት እኔም ባሌም ተመሳሳይ ህልም አየን በጣም የምታምር እንደ ፀሃይ የምታበራዋ ባለዘንባባዋ እናቴ የሚያምር ወንድ ልጅ ይዛ ወደ ቤታችን ስትገባ ባሌ ያየውን ነገረኝ እኔም ስነግረው አላመነም ነበረ ወዲያው ተነሳንና.
.. see more

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

11 Feb, 21:16


🕊

† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን †

[  † እንኩዋን ለአባታችን "አባ ብሶይ ዼጥሮስ" እና "ቅዱስ ዕብሎይ" ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ †  ]

[   †   🕊  አክርጵዮስ   🕊  †   ]

በዚች ቀን የእስክንድሪያ አገር ሊቀ ጳጳሳት የከበረ አባት አክርጵዮስ አረፈ። እርሱም ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት አስረኛ ነው። ይህም አባት እግዚአብሄርን የሚፈራ ንፁህ ቅዱስ ነው ።

በእስክንድርያ አገርም ቄስ ሆኖ የሚያገለግል ነበር ከእርሱ በፊት የነበረ ሊቀ ጳጳሳት አባ ከላድያኖስ በአረፈ ጊዜ የእስክንድር አገር ህዝብና ኤጲስቆጶሳቱ መረጡት በወንጌላዊው ማርቆስ ወንበር ላይ ሊቀ ጵጵስና ሾሙት።

ከዚህም በኃላ እንደ ሀዋሪያት መልካም ጉዞን ተጓዘ የእግዚአብሄርን ሀይማኖት ህይወት የሆነ ህጉንም እያስተማረ ቅዱሳት መፅህፍትንም እያነበበላቸውና እያስተማራቸው መንጋዎቹን ይጠብቃቸው ነበር ሁል ጊዜም ይመለከታቸዋል አንድ የብር አላድን ወይም አንድ የወርቅ ዲናርን ጥሪት አላኖረም ከእለት ምግቡ ከቁርና ከሀሩር ስጋውን ከሚሸፈንበት ልብስ በቀር ምንም አላከማቸም።

በዚህም ተጋድሎ አስራ ሁለት አመት ኑሮ ጌታችንንም አገልግሎ በሰላም አረፈ።

[ †  🕊  ቅዱስ ዕብሎይ  🕊  † ]

አባ ዕብሎይ በቀደመ ሕይወቱ ለ፵ [ 40 ] ዓመታት በኀጢአት የኖረ: እግዚአብሔር ለንስሃ ሲጠራው "እሺ" ብሎ : ለ፵ [ 40 ] ዓመታት በንስሃ ሕይወት ተመላልሶ በበርሃ የተጋደለ: እንባው እንደጐርፍ ይፈስ የነበረ: አጋንንትንም ድል የነሳና ለፍሬ: ለትሩፋት የበቃ ቅዱስ አባት ነው:: እግዚአብሔርም ብዙ ቃል ኪዳን ገብቶለታል::

" ባርያ ሆኖ ያለ ኀጢአት: ጌታ ሆኖ ያለ ምሕረት የለምና ይቅር በለን !! " [የአባ ዕብሎይ የንስሃ ጸሎት]

[ † 🕊 አባ ብሶይ [ዼጥሮስ] 🕊 † ]

ብሶይ [ቢሾይ] በቤተ ክርስቲያን ታሪክ የተለመደ
የቅዱሳን ስም ነው:: በተለይ በምድረ ግብ በዚህ ስም ሰማዕታትም : ጻድቃንም ተጠርተውበታል:: ከእነዚህ ቅዱሳን [ከገዳማውያኑ] አንዱ የሆነው አባ ብሶይም [አንዳንዴ አባ ዼጥሮስም ይባላል] የዘመነ ጻድቃን ፍሬ ነው::

ቤተ ክርስቲያን የቅዱሳን ቤት ናት:: ያ ማለት ራሳቸውን ለክርስቶስ የለዩ ሰዎች ይኖሩባታል:: እነዚህ ሰዎች ከተለያየ ጐዳና እና ማንነት ሊመጡ ይችላሉ:: ቢያንስ ግን በንስሃ የታጠቡ መሆናቸው ወደ ተቀደሰው አንድነት እንዲገቡ ትልቅ መሠረት ይሆናቸዋል::

ቅዱሳንም አንዳንዶቹ ከእናታቸው ማኅጸን ሲመረጡ : ሌሎቹ ደግሞ ከኃጢአት ሕይወት የተመለሱ ሆነው ይታያሉ:: ደስ የሚለው ደግሞ በንስሃ ከታጠቡ በሁዋላ በፍጹም ልባቸው በመጋደላቸው እነሆ በሰማያዊ አክሊል ተከልለዋል::

አባ ብሶይ ዼጥሮስም ከኃጢአት ተመልሰው ለቅድስና ከበቁ ቀደምት አበው አንዱ ነው:: ቅዱሱ ተወልዶ ባደገባት ምድረ ግብጽ የታወቀ ሽፍታ : ዝሙተኛና ክፋቱ የተገለጠ ሰው ነበር:: ለብዙ ዘመናት በእንዲህ ካለ ግብሩ መላቀቅ ባይችል እግዚአብሔር ጥሪውን ላከለት::

የአምላካችን የጥሪ መንገዱ ብዙ ነውና ለእርሱ ደዌን ላከለት:: መቼም ወደድንም ጠላንም በሽታ ወደ እግዚአብሔር የሚያቀርብ ጥሩ ፈሊጥ [አጋጣሚ] ነው:: ዛሬም ቢሆን ዘለን : ዘለን ስንሰበርና የሐኪም መፍትሔ ሲጠፋ የግዳችን ወደ እግዚአብሔር ቤት [ወደ ጸበሉ] እንቀርባለንና:: አምላካችን ስለዚህ ጥበቡ ይክበር ይመስገን::

ቅዱስ አባት ብሶይም በሽፍትነትና በኃጢአት ኑሮ ሳለ ለሞት የሚያበቃ ደዌ ደርሶበት የአልጋ ቁራኛ ሆነ:: ኃይሉም ደከመ:: በእንዲህ እያለም በራዕዩ ያየው ነገር ፍጹም አስደነገጠው::

መላእክት ነፍሱን ወስደው መካነ ኩነኔን ካሳዩት በሁዋላ አለቀሰ::

ይልቁን ሌቦችና ዝሙተኞችን ከ፬ [4] ሲቆራርጣቸው ስላየ ፈጽሞ አዘነ : ተጸጸተ:: ፈጣሪውንም ዕድሜ ለንስሃ እንዲሰጠው ተማጸነ:: ጌታንም "አምላኬ ሆይ! ከበሽታየ ብታድነኝ : ዳግመኛ አልበድልህም:: ዓለምን ሁሉም ንቄ አገለግልሃለሁ" ሲል ተማጸነው::

እግዚአብሔርም ሰምቶት ፈጥኖ ፈወሰው:: አባ ብሶይም እንደ ቃሉ በፍጹም ልቡ ንስሃ ገብቶ መነነ:: በገዳመ አስቄጥስ [ግብጽ] ለ፴፰ [38] ዓመታት ሲኖር የላመ የጣመ በልቶ : ከሞቀ መኝታ ተኝቶ አያውቅም::

ሰውነቱን ይቀጣት ዘንድም እስከ ፴ [30] ቀን ያለ እህል ውሃ ይጾም ነበር:: በዘመኑ ሁሉም የሴት መልክን አላየም:: ንስሃን የሚወድ ጌታም ጸጋውን አብዝቶለት ብዙ ድርሳናትን ጽፏል:: የሚገርመው ደግሞ ከትህትናውና ቅድስናው የተነሳ የእያንዳንዱ ሰው ኃጢአት ተገልጦ ይታየው ነበር::

ቅዱሱ አባታችን ብሶይ ዼጥሮስ በንስሃና በቅድስና ሕይወት እንዲህ ተመላልሶ በዚህች ቀን ዐርፎ በገዳሙ ተቀብሯል:: የድካሙን ዋጋም አድልዎ ከሌለበት : ከእውነተኛው ፈራጅ ከመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተቀብሏል::

አምላከ ቅዱሳን ዕድሜ ለንስሃ : ዘመን ለፍስሐ
አይንሳን:: ከክብረ ቅዱሳንም ያካፍለን . . . አሜን !!

[  † የካቲት ፭ [ 5 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት  ]

፩. ቅዱስ አባ ዕብሎይ ገዳማዊ
፪. ቅዱስ አባ ብሶይ ጻድቅ
፫. አባ አክርዽዮስ
፬. ፵፱ "49" አረጋውያን ሰማዕታት [ፍልሠታቸው]
፭. ቅዱስ አሞኒና ሚስቱ ቅድስት ሙስያ [የታላቁ ዕብሎይ ወላጆች]
፮. አባ ኖብ ጻድቅ : መነሳንሱ ዘወርቅ

[   †  ወርሐዊ በዓላት   ]

፩. ቅዱስ ዼጥሮስ ሊቀ ሐዋርያት
፪. ቅዱስ ዻውሎስ ሐዋርያ
፫. አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ
፬. ቅዱስ ዮሐኒ ኢትዮዽያዊ
፭. ቅዱስ አሞኒ ዘናሒሶ

አምላክ በበረከታቸው ይባርከን::

" መቶ በግ ያለው : ከእነርሱም አንዱ ቢጠፋ ዘጠና ዘጠኙን በበርሃ ትቶ የጠፋውን እስኪያገኘው ድረስ ሊፈልገው የማይሔድ ከእናንተ ማን ነው? ባገኘውም ጊዜ ደስ ብሎት በጫንቃው ይሸከመዋል:: ወደ ቤትም በመጣ ጊዜ ወዳጆቹንና ጐረቤቶቹን በአንድነት ጠርቶ 'የጠፋውን በጌን አግኝቼዋለሁና ከእኔ ጋር ደስ ይበላችሁ' ይላቸዋል:: እላችሁአለሁ: እንዲሁ ንስሃ ከማያስፈልጋቸው ከዘጠና ዘጠኝ ጻድቃን ይልቅ ንስሃ በሚገባ በአንድ ኃጢአተኛ በሰማይ ደስታ ይሆናል።" [ሉቃ.፲፭፥፫-፯] (15:3-7)

† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †

[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]


         †              †               †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖                   🕊                    💖

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

10 Feb, 19:59


🕊

[  † እንኳን ለሐዋርያው ቅዱስ አጋቦስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †  ]

† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ! †

†  🕊 ቅዱስ አጋቦስ ሐዋርያ  🕊

† ከ፸፪ [ 72 ] ቱ አርድዕት አንዱ የሆነው ቅዱሱ ሐዋርያ ሃብተ-ትንቢት የተሠጠውና በዘመነ ሐዋርያት [በቀላውዴዎስ ቄሳር ጊዜ] በዓለም ላይ ከባድ ረሃብ እንደሚሆን ትንቢት የተናገረና በርካታ ክርስቲያኖችን ከረሃብና ከሞት የታደገ ትልቅ ሐዋርያ ነው:: [ሐዋ.፲፩፥፳፯ ] (11:27)

በቅዱስ ጳውሎስ ላይ የሚደርሰውን መከራ በመናገሩም "ሐዋርያ ትንቢት" ተብሏል:: በአገልግሎቱ ከአይሁድና ከአረማውያን ብዙዎችን ወደ ክርስትና በመሳቡ የተበሳጩ አይሁድም በዚህች ቀን ገድለውታል:: በተቀደሰ ሥጋው [መቃብሩ] ላይ ብርሃን ሲወርድ ያየች አይሁዳዊት ሴትም በክርስቶስ አምና ተሰውታለች::

††† የአባታችን በረከት ይደርብን::

[  † ካቲት ፬ [ 4 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት  ]

፩. ቅዱስ አጋቦስ ነቢይ: ሐዋርያና ሰማዕት
፪. አባ ዘካርያስ ትሩፈ ምግባር

[   † ወርኀዊ በዓላት   ]

፩. ቅዱስ ዮሐንስ ሐዋርያ ወልደ ነጎድጓድ
፪. ቅዱስ እንድርያስ ሐዋርያ
፫. ቅድስት ሶፊያ ሰማዕት
፬. ቅዱስ ዮሐንስ ዘሐራቅሊ

" በዚያም ወራት ነቢያት ከኢየሩሳሌም ወደ አንጾኪያ ወረዱ:: ከእነርሱም አጋቦስ የሚሉት አንድ ሰው ተነስቶ በዓለም ሁሉ ታላቅ ራብ ሊሆን እንዳለው በመንፈስ አመለከተ:: ይህም በቀላውዴዎስ ቄሣር ዘመን ሆነ::
ደቀ መዛሙርትም እያንዳንዳቸው: እንደ ችሎታቸው መጠን አዋጥተው በይሁዳ ለሚኖሩት ወንድሞች እርዳታን ይልኩ ዘንድ ወሰኑ:: እንዲህም ደግሞ አደረጉ:: በበርናባስና በሳውልም እጅ ወደ ሽማግሌዎቹ ሰደዱት::
"
† [ሐዋ. ፲፩፥፳፯]

" ስለ እኛ ትጸልዩ ዘንድ ይገባቹሃል: ለሁሉ መልካም ነገርን እንደምትወዱና እንደምትሹ እናምናለን:: " † [ዕብ. ፲፫፥፲፰]

† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †

[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]


         †              †               †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖                   🕊                    💖

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

10 Feb, 16:03


                        †                        

🕊  💖                     💖  🕊

[  ክርስቶስ ነጻነት አወጣን !  ]

🕊
                        †                        

❝ በነጻነት ልንኖር ክርስቶስ ነጻነት አወጣን ፤ እንግዲህ ጸንታችሁ ቁሙ እንደ ገናም በባርነት ቀንበር አትያዙ። ❞

[ ገላ . ፭ ፥ ፩  ]


💖  የ ነ ፍ ስ ነ ፃ ነ ት  💖   ]
                   ] [

     🕊    ምክረ ቅዱሳን   🕊

🕊 [ በብፁዕ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ ]


†                       †                        †
💖                    🕊                     💖

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

09 Feb, 21:28


🕊

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡

❖ እንኳን አደረሳችሁ ❖

የካቲት ፫ [ 3 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

[ †  🕊 ቅዱስ ማሪ ኤፍሬም ሶርያዊ 🕊 † ]

እንደ ቤተ ክርስቲያናችን ትውፊት ቅዱስ ኤፍሬም የተወለደው ንጽቢን በምትባል የሶርያ ግዛት ውስጥ በ፪፻፺፰ [298] / ፫፻፮ [306] ዓ/ም ነው:: ወላጆቹ በክርስቶስ የማያምኑ አላውያን ነበሩ:: [ምንም አንዳንድ ምንጮች ክርስቲያኖች ነበሩ
ቢሉም]

ቅዱሱ ተወልዶ ባደገባት ንጽቢን ዽዽስናን የተሾመ ቅዱስ ያዕቆብ የሚባል ታላቅ ሰው ነበር:: የሰማዕትነት: የሐዋርያነት: የጻድቅነትና የሊቅነት ግብር ያለው አባት ነው:: ታዲያ ቅዱስ ኤፍሬም ይሔ አባት ሁሌ ሲያስተምር ይሰማው ነበርና በስብከቱ ተማርኮ ደቀ መዝሙሩ ለመሆን በቃ::

ቅዱስ ኤፍሬም በቅዱስ ያዕቆብ እጅ ከተጠመቀ በሁዋላ ሙሉ የጣትነት ጊዜውን ያሳለፈው በትምሕርት ነው:: የሚገርመው መምሕሩ ቅዱስ ያዕቆብ ዘንጽቢን እመቤታችን ድንግል ማርያምን በፍጹም ልቡ የሚወድና ጠርቷት የማይጠግብ አባት ነውና ለልጁ ለቅዱስ ኤፍሬም ይሕንኑ አጥብቆ አስተምሮታል::

ቅዱስ ኤፍሬም ክርስትናን ሲመረምር የእመቤታችን ፍቅር ይበዛለት ጀመር:: ምክንያቱም እመ ብርሃንን ሳይወዱ ክርስትና የለምና:: እንደ እርሱ የሚወዳት የለም እስኪባል ድረስ ያገለግላት: ይገዛላትም ገባ::

እንዲህ እንደ ዛሬ የድንግል ማርያም ምስጋና በአንደበት እንጂ በመጽሐፍ አይገኝም ነበር:: እርሱ ግን ከወንጌለ ሉቃስ በስድስተኛው ወርን [ይዌድስዋን] እና ጸሎተ ማርያምን [ታዐብዮን] አውጥቶ በየዕለቱ በዕድሜዋ ልክ ፷፬ ፷፬ [ 64 64 ]ጊዜ ያመሰግናት ነበር::

በእንዲህ ያለ ግብር እያለ አርዮስ በመካዱ እርሱን ለማውገዝና ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን ለማጽናት በ ፫፻፲፯/፫፻፳፭ [ 317 / 325 ] ዓ/ም ፫፻፲፰ [318] ቱ ሊቃውንት በኒቅያ ሲሰበሰቡ አንዱ መምሕረ ኤፍሬም ቅዱስ ያዕቆብ ነበር:: በዚህ ምክንያት ቅዱስ ኤፍሬም ከሊቃውንቱ ትምሕርትና በረከትን አግኝቷል::

ከጉባዔ መልስ መንገድ ላይ በራዕይ የብርሃን ምሰሶ አይቶ "ጌታ ሆይ! ምንድን ነው?" ብሎ ቢጠይቅ "ይህማ ታላቁ ቅዱስ ባስልዮስ ነው" አለው:: እርሱም መምሕሩን ቅዱስ ያዕቆብን ተሰናብቶ ወደ ቅዱስ ባስልዮስ [ቂሣርያ] ወረደ:: ተገናኝተውም በአንድ ሌሊት ቁዋንቁዋ ተገልጦላቸው ሲጨዋወቱ አድረዋል::

በቦታው ብዙ ተአምራት ተደርጉዋል:: ቅዱስ ኤፍሬም ከታላቁ ባስልዮስ ከተማረ በሁዋላ ሃገረ ስብከት ተሰጥቶት ያስተምር ጀመር:: ሁል ጊዜ ታዲያ ጸሎቱ ይሔው ነበር:: "እመቤቴ ሆይ! ምስጋናሽ እንደ ሰማይ ከዋክብት: እንደ ባሕር አሽዋ በዝቶልኝ: እንደ እንጀራ ተመግቤው: እንደ ውሃ ጠጥቼው: እንደ ልብስም ተጐናጽፌው" እያለ ይመኝ ነበር::

አፍጣኒተ ረድኤት: ፈጻሚተ ፈቃድ እመ ብርሃንም በገሃድ ተገልጻ የልቡን ፈቃድ ፈጸመችለት:: ዛሬ ጸጋ በረከት የምናገኝበትን ውዳሴ ማርያምን ደረሰላት:: ሲደርስላትም እርሷ አእላፍ መላእክትን: ጻድቃን ሰማዕታትን አስከትላ ወርዳ: በፊቱም ተቀምጣ ሲሆን እርሱ ደግሞ ባጭር ታጥቆ: በፊቷ ቆሞ: በመንፈስ ቅዱስም ተቃኝቶ ነው::

ውዳሴዋን በ፯ [7] ቀናት ከደረሰላት በሁዋላ በብርሃን መስቀል ባርካው: ሊቀ ሊቃውንትም እንዲሆን ምስጢር ገልጣለት ዐረገች:: ከዚህ በኋላ በምስጢር ባሕር ውስጥ ዋኝቶ ፲፬ [14] ሺህ ድርሰቶችንም ደርሷል:: ዛሬ ሶርያ ውስጥ የምንሰማውን ዜማም የደረሰው ይህ ቅዱስ ነው::

እንዲያውም አንድ ቀን የምሥጢር ማዕበል ቢያማታው "አሃዝ እግዚኦ መዋግደ ጸጋከ" ብሎ ጸልዩዋል:: [የጸጋህን ማዕበል ያዝልኝ] እንደ ማለት ነው:: ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ በመጨረሻ ሕይወቱ ተክሪት በምትባል ሃገር ኤዺስ ቆዾስ ሆኖ ተሹሟል::

በጣፋጭ ስብከቱ ብዙዎችን ካለማመን መልሷል: የምዕመናንንም ሕይወት አጣፍጧል:: ለመናፍቃንና ለአርዮሳውያን ግን የማይጋፉት ግድግዳ ሆኖባቸው ኑሯል:: በዘመኑም ብዙ ተጋድሎ አፍርቷል: ተአምራትንም ሠርቷል:: በተወለደ በ፷፯ [67] ዓመቱ በ፫፻፷፭/፫፻፸፫ [365 / 373 ዓ/ም ዐርፎ ተቀብሯል::

ቅዱሱ ለሶርያ ብቻ ሳይሆን እመቤታችንን ለምንወድ የዓለም ክርስቲያኖች ሁሉ ሞገሳችን ሆኗል:: ስለዚህም እንዲህ እያልን እንጠራዋለን :-

፩. ቅዱስ ኤፍሬም
፪. ማሪ ኤፍሬም
፫. አፈ በረከት ኤፍሬም
፬. ሊቀ ሊቃውንት ኤፍሬም
፭. ጥዑመ ልሳን ኤፍሬም
፮. አበ ምዕመናን ኤፍሬም
፯. ርቱዐ ሃይማኖት ኤፍሬም . . . አባታችን አንተ ነህ::

❖ የካቲት ፫ ቀን ለቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ ዓመታዊ የፍልሠት በዓሉ ነው፡፡

ጽንዕት በድንግልና: ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ለቅዱስ ኤፍሬም የሰጠሽውን ጸጋውን: ክብሩን: አእምሮውን: ለብዎውን በልቡናችን ሳይብን: አሳድሪብን . . . አሜን::

[ † 🕊 አባ ያዕቆብ ገዳማዊ 🕊† ]

ነቢየ ጽድቅ ቅዱስ ዳዊት "ለስሒት መኑ ይሌብዋ- ስሕተትን ማን ያስተውላታል" [መዝ] ሲል የተናገረው ይፈጸም ዘንድ ይህ ታላቅ ቅዱስ ሰው በኃጢአት ብዙ ተፈተነ:: ወደ በርሃ ወጥቶ: በምናኔ ጸንቶ: በጾምና በጸሎት ተግቶ ዘመናትን ስላሳለፈ ሰይጣንን አሳፈረው::

ግን ደግሞ ክፉ ጠላት ባልጠረጠረው መንገድ መጥቶ መከራ ውስጥ ከተተው:: የአገረ ገዢው ልጅ ታማ "ፈውሳት" አሉት: ፈወሳት:: ወደ ቤቷ ስትመለስ ግን አመማት:: "ከአንተ ጋር ትቆይ" ብለው ትተዋት ቢሔዱ ከመለማመድ የተነሳ በዝሙት ወደቀ::

እንዳይገለጥበት ስለ ፈራም ገደላት:: በሆነው ነገር ተስፋ ቆርጦ ወደ ዓለም ሲመለስ: ቸር ፈጣሪ የሚናዝዝ አባትን ልኮ ንስሃ ሰጠው:: ጉድጓድ ምሶ: ድንጋይ ተንተርሶ ለ፴ [30] ዓመታት አለቀሰ:: እግዚአብሔርም ምሮት: የቀደመ ጸጋውን ቢመልስለት: ዝናምን አዝንሞ ሕዝቡን ከእልቂት ታድጓል:: በዚህች ዕለት ዐርፎም ለርስቱ በቅቷል::

[ † 🕊 ታላቁ አባ ዕብሎይ 🕊 † ]

ይህ ቅዱስ የአቡነ አቢብ ደቀ መዝሙር ሲሆን በዚህ ስም ከሚጠሩ ቅዱሳንም ቀዳሚው ነው:: ብዙ መጻሕፍት 'ርዕሰ ገዳማውያን' ይሉታል:: የቅዱሱ ተጋድሎ እጅግ ሰፊ ነው::

[ † የካቲት [ ፫ ] 3 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት † ]

፩. ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ [ አፈ በረከት-በዓለ ፍልሠቱ ]
፪. ቅዱስ አባ ዕብሎይ ገዳማዊ [ ሕይወቱ መላዕክትን የመሰለ ግብፃዊ አባት ]
፫. አባ ያዕቆብ መስተጋድል

[  † ወርኀዊ የቅዱሳን በዓላት ]

፩. በዓታ ለእግዝእትነ ማርያም ድንግል ወላዲተ አምላክ
፪. ቅዱሳን ኢያቄም ወሐና
፫. ቅዱሳን ሊቃነ ካህናት አበው [ ዘካርያስና ስምዖን ]
፬. አባ ሊባኖስ ዘመጣዕ
፭. አቡነ ዜና ማርቆስ
፮. አቡነ መድኃኒነ እግዚእ ዘደብረ በንኮል
፯. ቅዱስ ቄርሎስ ሊቅ [ ዓምደ ሃይማኖት ]


+ "ለምኑ ይሰጣችሁማል:: ፈልጉ ታገኙማላችሁ:: መዝጊያ አንኳኩ ይከፈትላችሁማል:: የሚለምነው ሁሉ ይቀበላልና:: የሚፈልገውም ያገኛል:: መዝጊያንም ለሚያንኳኳ ይከፈትለታል::" + [ማቴ.፯፥፯]

+ " የጻድቅ አፍ ጥበብን ያስተምራል:: አንደበቱም ፍርድን ይናገራል::የአምላኩ ሕግ በልቡ ውስጥ ነው:: በእርምጃውም አይሰናከልም::"  [መዝ.፴፯፥፴]

† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †

[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]


         †              †               †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖                   🕊                    💖

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

09 Feb, 17:21


🕊                        💖                      🕊

            [      ጾ መ ነ ነ ዌ !      ]

▬▬▬▬▬▬   ♱    ▬▬▬▬▬▬

❝ እግዚአብሔርም ከክፉ መንገዳቸው እንደ ተመለሱ በሥራቸውን አየ ፤ እግዚአብሔርም ያደርግባቸው ዘንድ በተናገረው ክፉ ነገር ተጸጽቶ አላደረገውም። ❞

[ ት.ዮናስ ፫፥፭ -፲ ]


[  እንኳን ለጾመ ነነዌ በሰላም አደረሳችሁ ! ]


🕊                       💖                     🕊

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

09 Feb, 16:05


🕊                        💖                      🕊


[ ታላቂቱ ከተማ !  ]


▬▬▬▬▬▬   ♱    ▬▬▬▬▬▬


❝ እግዚአብሔርም ከክፉ መንገዳቸው እንደ ተመለሱ በሥራቸውን አየ ፤ እግዚአብሔርም ያደርግባቸው ዘንድ በተናገረው ክፉ ነገር ተጸጽቶ አላደረገውም። ❞

[ ት.ዮናስ ፫፥፭ -፲ ]

🕊                       💖                     🕊

[       ታላቂቱ ከተማ !       ]

💖   ድንቅ ትምህርት  💖

[ በዲ/ን ሔኖክ ሐይሌ ]

[ እንኳን ለጾመ ነነዌ በሰላም አደረሳችሁ ! ]


🕊                       💖                     🕊

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

09 Feb, 10:22


                        †                           

🕊  💖  ቅዱስ አባ ጳውሊ  💖  🕊

                         🕊                         

❝  ሰላም ለአባ ጳውሊ ዘንጉሥ ወዓሊ ፤ ገዳማዊ ዘበአማን ኅሩይ ፤ ርዕሶሙ ለፈላስያን እለ በገዳም። ❞

ትርጉም  ፦

[ በበረሓ ላሉ ባሕታውያን [ መናንያን ] አለቃቸው ፤ በእውነት የተመረጠ ገዳማዊ ፤ የንጉሥ ሎሌ ለኾነ ለአባ ጳውሊ ሰላምታ ይገባል።

ከሰው ወገን ማንንም ማን አንድ ሳያይ በገዳም ውስጥ የተጠመደ ለኾነ ለጳውሊ ሰላምታ ይገባል ፤ በብዙ ወገን ደክሞ በብዙ ወገንም ተጋደለ ፤ ከሞቱም በኋላ በሕይወቱ እንደለመደው ለእግዚአብሔር የሰገደ ኾኖ ተገኘ። ]

[  ተአምኆ ቅዱሳን  ]

▬▬▬▬▬▬   ♱    ▬▬▬▬▬▬


[  †  🕊  እንኳን አደረሳችሁ  🕊  †  ]


🕊                        💖                      🕊

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

09 Feb, 09:07


💛
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬

🕊       [   ክብርት ሰንበት   ]        🕊


❝ አሁን ማንኛውም ቁርባኑ [ ሥጋውና ደሙ ] በተሠራበት ቤተ ክርስቲያኑ ጌታችን ስለማይለይ ፣ ሰንበትን እያከበርን መሆናችንን መናገር እንችላለን።

ይህች ሰንበት [ ቁርባን የተሠራባት ማንኛውም ዕለት ] እያከበርናት ያለነው ለምትመጣው ሰንበት ምሳሌ አድርገን አይደለም ፤ በመንግሥቱ ውስጥ ሆነን ሰንበታችንን [ ዕረፍታችን ክርስቶስን ] ፊት ለፊት የምናይባትን የምትመጣዋ ሰንበት መያዣ አድርገን እንጂ። ❞

[  ሊቅ ቀሲስ ታድሮስ  ]

🕊

❝ በነቢዩ በዳዊት መዝሙር በታወቀች በበዐላችን ቀን በእውነት ሃሌ ሉያ እንበል ፣ [ ይህች ቀን ያልታወቀች ያይደለች ] እግዚአብሔር ሥራውን ይሠራ ዘንድ የጀመረባት በእውነት የታወቀች ናት።

ወዮ ይህቺ ዕለት ቀዳሚት ናት ደኃራዊት አይደለችም ፣ ወዮ ይህቺ ዕለት ለዘላለሙ የምትሠለጥን [ ሰፋኒት ወይም ለዘላለም ጸንታ የምትኖር ] ደኃራዊት ናት ፤ ወዮ ይህቺ ዕለት ለአብርሃም ተገለጸች ፣ እርሱንም አስመኘች ፣ ትንቢትም አናገረች እርሱንም ደስ አሰኘች። ❞

†    🕊   ክብርት ሰንበት   🕊    †


🕊                       💖                     🕊

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

06 Feb, 12:33


💛
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬

[ የመርሐ-ግብር ማሳወቂያ ! ]

🕊

[ 💖 መንፈሳዊው መሰላል 💖 ]

እንደ እግዚአብሔር መልካም ፈቃድ ከፊታችን ሰኞ ጀምሮ በቀኑ መርሐ-ግብር የቅዱስ ዮሐንስ ክሊማኮስ [ ቅዱስ ዮሐንስ ዘሰዋስው ] ድርሳን ላይ "መንፈሳዊው መሰላል" በሚል ርዕስ የቀረበው ትምህርትና ድንቅ ምክር ለንባብ እንዲመች እየተመጠነ የሚቀርብ ይሆናል።

በመርሐ-ግብሩ ወደ እግዚአብሔር ለመድረስ ልንወጣ ስለሚገባን የቅድስና መሰላልና የንጽሕና ሕይወት ጉዞ አስደናቂ ትምህርቶችን የምናገኝበት ነው፡፡

[   🕊 መንፈሳዊው መሰላል 🕊  ]

- ተከታታይ መርሐ-ግብር
- ከፊታችን ሰኞ ጀምሮ
- ከቀኑ ፱ ሰዓት [ 09:00 ] ላይ


🕊                       💖                     🕊

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

05 Feb, 20:58


🕊

[  † እንኳን ለቅዱሳን ጻድቃነ ዴጌ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። †  ]

† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ! †

🕊  †   ጻድቃነ ዴጌ   †  🕊

† እነዚህ ጻድቃን ኢትዮዽያውያን ባይሆኑም ያበሩት በሃገራችን ነው:: ቅዱሳኑ በቁጥር ፫ ሺህ [3,000] : በዜግነት ሮማውያን ናቸው:: ከሺህ አዝማናት በፊት ከሮም ግዛት ተሰባስበው እንደ ተስዓቱ ቅዱሳን ወደ ኢትዮዽያ [አክሱም] መጥተዋል::

ቀጥለውም እዛው አካባቢ ወደሚገኝ ገዳም ገብተዋል:: ይህ ቦታ ለአክሱም ቅርብ ሲሆን በዘመነ ሐዋርያት የቅዱስ ማቴዎስ ወንጌላዊ በዓት ነበር:: የሐዋርያው በትረ መስቀልም እስካሁን አለች::

ጻድቃነ ዴጌ ሕጋቸው አንዲት : እርሷም ፍቅር ናት:: ለዘመናት በፍቅረ ክርስቶስ ታሥረው : ፍቅርን ለብሰው : በፍቅር ኑረዋል:: ሁሌም በ፳፱ [29] የጌታችንን ስም እየጠሩ ጽዋ ጠጥተዋል:: ስለ ፍቅራቸውም ጌታችን ፫ ሺህ ፩ኛ [3,001] ኛ ሆኖ : ነዳይ መስሎ አብሯቸው ጠጥቷል::

በመጨረሻም ፫ ሺው በአንድነት ተሠውረዋል::

† ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን:: እኛንም በወዳጆቹ ጸሎት ይማረን:: . . .አሜን !

🕊

[   † ጥር ፳፱ [ 29 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት   ]

፩. ጻድቃን ቅዱሳን ማሕበረ ዶጌ [ዴጌ ጻድቃን]
[አክሱም አካባቢ በቁጥር ወደ ፫ ሺህ [3,000] ሲሆኑ ከመድኃኔ ዓለም ጋር ማሕበር ይጠጡ የነበሩና በአንድ ላይ የተሠወሩ ቅዱሳን ናቸው]
፪. አባ ገብረ ናዝራዊ ዘቃውንት [ኢትዮዽያዊ]
፫. ቅድስት አክሳኒ ፈላሲት
፬. ቅዱስ ሰርያኮስ ሰማዕት
፭. አባ እስጢፋኖስ ገዳማዊ
፮. ከድሮዋ ሮም የተነሱ ቅዱሳት አንስት

[    † ወርሐዊ በዓላት    ]

፩. ቅድስት አርሴማ ሰማዕት
፪. ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ እናታችን
፫. ቅዱስ ዼጥሮስ ተፍፃሜተ ሰማዕት
፬. ቅዱስ ማርቆስ ዘቶርማቅ
፭. ቅዱስ ዘርዐ ክርስቶስ

" ጻድቃን ምድርን ይወርሳሉ:: በእርስዋም ለዘለዓለም ይኖራሉ:: የጻድቅ አፍ ጥበብን ያስተምራል:: አንደበቱም ፍርድን ይናገራል:: የአምላኩ ሕግ በልቡ ውስጥ ነው:: በእርምጃውም አይሰናከልም:: " † [መዝ.፴፮፥፳፱]

† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †

[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]


         †              †               †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖                   🕊                    💖

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

05 Feb, 19:52


ከሚቀበል ይልቅ የሚሰጥ ብፁዕ ነው ያለው ማነው?

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

05 Feb, 19:51


ከሚቀበል ይልቅ የሚሰጥ ብፁዕ ነው ያለው ማነው?

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

05 Feb, 18:51


ማኔ ቴቄል ፋሬስ ተብሎ የተጻፈበት ንጉሥ ማነው?

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

05 Feb, 16:28


💛
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬

🕊       [   ምክረ ቅዱሳን   ]        🕊

▷     "  የሚያበራ ንጽሕና !  "

[   💖   አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ   💖   ]

[                        🕊                        ]
-------------------------------------------------

❝ ወዳጆች ሆይ ፥ አሁን የእግዚአብሔር ልጆች ነን ፥ ምንም እንደምንሆን ገና አልተገለጠም። ዳሩ ግን ቢገለጥ እርሱ እንዳለ እናየዋለንና እርሱን እንድንመስል እናውቃለን።

በእርሱም ይህን ተስፋ የሚያደርግ ሁሉ እርሱ ንጹሕ እንደ ሆነ ራሱን ያነጻል። ❞

[   ፩ዮሐ.፫፥፪  ]


🕊                       💖                     🕊

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

05 Feb, 11:19


💛
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬


የቅዱስ መቃርዎስ ሕይወቱና ትምህርቱ ተፈጸመ !

🕊

አነሳስቶ ላስጀመረን ፥ አስጀምሮም ላስፈጸመን ለቅዱሳን ሁሉ አምላክ ለልዑል እግዚአብሔር ክብር ምስጋና ይሁን፡፡ የአባታችን የቅዱስ መቃርዮስ ምልጃና ጸሎቱ አይለየን፡፡

አሜን !


🕊                       💖                     🕊

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

05 Feb, 11:06


                          †                          

[    🕊    ገ ድ ለ   ቅ ዱ ሳ ን   🕊     ]

▬▬▬▬▬▬   †    ▬▬▬▬▬▬

[ ቅዱስ መቃርዮስ ካስተማረው ትምህርት ]

         [      የመጨረሻ ክፍል     ]

                         🕊  

[     ስለ እግዚአብሔር ቃል መስማት !    ]

🕊

❝ አባ መቃርዮስ ታላቁ እንዲህ አለ ፦ “በጌታ ቃል ደስ የሚልህ መሆኑ መልካም ነው ፣ ቃሉን ስትሰማ ግን ለመስማት ብቻ ሳይሆን ለመታዘዝና ለማድረግ እንድትችል ሆነህ እንድትማር ሁን ፤ የእግዚአብሔርን ቃል በሙሉ ኃይሉ የሚሰማ ሰው ለማድረግም ይማራልና፡፡

ብዙዎች የእግዚአብሔርን ቃል ሰምተዋል ፣ ሆኖም ግን በእግዚአብሔር ኃይልና በደስታ ሆነው አልሰሙትም ፤ ስለዚህም የሕይወት መሻሻልና ዕድገት አላመጡም፡፡

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንደዚህ ስላሉት ሰዎች እንዲህ ሲል አሰምቶ ተናግሯል ፦ "የሚሰማ ጆሮ ያለው መስማትን ይስማ፡፡" ሁሉም መስማትን ባያቆሙ ኖሮ እንደዚህ ብሎ ጆሮ ያለው መስማትን ይስማ ብሎ ደጋግሞ ባልተናገረ ነበር፡፡

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የዲያብሎስ ሥራ ነፍሳት የእግዚአብሔርን ቃል እንዳይሰሙና ሰምተው እንዳይድኑ መዋጋት መሆኑን ያውቃልና፡፡ ስለዚህም ጆሮ ያለው መስማትን ይስማ” አለ፡፡ የእግዚአብሔርን ቃል የሚሰሙ ለውጥና ዕድገት ያሳያሉና ፣ በነፍስና በሥጋ ፈቃዳትና በፍትወታት ሁሉ ላይም ድል አድራጊዎች ናቸውና፡፡

“ ነገር ግን ዲያብሎስ ነፍስን የእግዚአብሔርን ቃል በኃይል ከመስማት ቢያስቆማት [ቢያግዳት] መሻሻልና ማደግ አትችልም ፣ የሰውነት ፈቃዳትንና ፍትወታትን ለመዋጋትም መንገድ አታገኝም ፤ የእግዚአብሔር ቃል በውስጧ አይኖርባትምና፡፡ ጠላት በእርሷ ላይ ኃይል ቢጠቀም ከክፉ ፍትወታትና ከእኩያት ሕሊናት አንዳቸውንም ከእርሷ ለማባረር የምትችልበት መንገዱ ይጠፋባታል፡፡

ቃሉን ገንዘብ ያደረገች ነፍስ ግን ፍትወታት እኩያትንና ክፉ ሕሊናትን ከእርሷ በማባረር ብርቱ ናት ፣ ጠላት ዲያብሎስንም ከእርሷ ታስወጣዋለች ፣ እርሱም ኃፍረትን ተከናንቦ ፈጥኖ ተለይቷት ይሸሻል ፤ እንዲህ ተብሎ ተጽፏልና ፦ 'የእግዚአብሔር ቃል ሕያው ነውና ፣ የሚሠራም ሁለትም አፍ ካለው ሠይፍ ሁሉ ይልቅ የተሳለ ነው ፣ ነፍስንና መንፈስንም ጅማትንና ቅልጥምንም እስኪለይ ድረስ ይወጋል ፣ የልብንም ስሜትና ሃሳብ ይመረምራል፡፡'

“ሰው የእግዚአብሔርን ቃል መስማት ከቻለ እንዴት ክፉ ሃሳቦችን መቋቋምና ማባረር እንደሚችል ማየት እንችላለን ፣ የማይሰማ ከሆነ ግን ነፍስ ምንም ዓይነት ክፉ ሃሳቦችን ሳታባርር እንደ እርሳስ ትሆናለች፡፡ ስለዚህም ዲያብሎስ እንደዚህ ዓይነት ሰዎችን ይሳለቅባቸዋል ፤ እንደዚህ ያሉ ሰዎች ሕይወታቸውን በሙሉ በገዳምና በድንግልና ያሳለፉ ቢሆኑም እንኳ በምንም ነገር መለወጥና ማደግ አይችሉም፡፡ ከማርና ከማር ወለላ ይልቅ እጅግ በጣም ጣፋጭ የሆነውን የእግዚአብሔርን ጣፋጭነት ጣዕምም አላወቁትም ፣ በተጨማሪም ከምንም ነገር በላይ የሆነውንና የጻድቅ ሰው ልቡ ከአንበሳ ይልቅ ጀግና ነው' እንደ ተባለ ነፍስን ዕለት በዕለት የሚያበረታታትን ፣ ኃይል የሚሰጣትንና የሚያጸናትን የእግዚአብሔርን ኃይል አያውቁም፡፡

ልጆቼ ሆይ ! እውነተኛና ጻድቅ የሆነ ሰው ልብ እንዴት ጽኑና ጀግና እንደ ሆነ ታያላችሁን ? ምክንያቱም መንፈሳዊ ምግብን ለመቀበል ስለሚፈቅድለት ነው ፣ እርሱም የእግዚአብሔር ቃል ነው፡፡ ስለዚህም ምክንያት ለሰውነቱ ቀን በቀን ጥንካሬን ስለሚሰጠው ሥጋዊ ምግብን እንደሚወስድ ሰው ነፍሱ ጽኑዕና ደፋር ናት፡፡ ስለሆነም ለመብላትና ኃይል ጽንዕ የሚሆነውን ምግብ ለመውሰድ የማይፈልግ ከሆነ ሰውነቱ እየዛለ ይሄዳል፡፡

ጠላቶቹ ቢዋጉት በቀላሉ ያሽንፉታል፡፡ እናም ልጆቼ ሆይ ፣ በጠላቶቻችሁ ላይ ድል አድራጊዎች ትሆኑ ዘንድ እንዲህ ዓይነት ምግብ ለመመገብ ራሳችሁን አለማምዱ ፣ ይኸውም ቃለ እግዚአብሔር ነው ፤ ጠላቶቻቸውን ድል ለማድረግ የሚያስችላቸውን ኃይልና ድፍረት ያገኙበት የነበረውን ይህን መንፈሳዊ ምግብ መላ የሕይወት ዘመናቸውን አጋንንት ሳይመገቡ እንዲቀሩ ያደረጓቸው ቁጥራቸው በጣም ብዙ የሆነ መነኰሳትና ደናግል አሉና፡

ይህን ምግብ መመገብ ያልቻሉት ለምንድን ነው ? ምክንያቱ ልባቸው የቀና ስላልሆነና የልባቸውን ምኞት መቋቋም ስለማይችሉ ነው ፣ የዚህ ምክንያቱ ደግሞ ልባቸው የረከሰ ስለ ሆነና ስለ እግዚአብሔር ትንሽ እንኳ እውቀት ስለሌላቸው ነው:: ከዚህም የተነሣ ነፍሳቸውን ያበረቱ ዘንድ አጋንንት የተቀደሰ የሆነውን መንፈሳዊ ምግብ ይመገቡ ዘንድ አያሰናብቷቸውም፡፡

ስለዚህም ምክንያት መላ ሕይወታቸውን በፈሪነት ፣ ግራ በመጋባት ፣ በሥቃይ እና እርስ በእርስ በመወነጃጀልና በማመካኘት አጠፉት፡፡ ስለዚህ ተወዳጆች የሆናችሁ ልጆቼ ሆይ ፣ በሕይወት ትኖሩ ዘንድና በመድኃኒታችን በክርስቶስ ኢየሱስ ከእግዚአብሔር ጋር ሱቱፋን [ተሳታፊዎች] ሆናችሁ ትቆጠሩ ዘንድ ራሳችሁን ከዚህ መጥፎ ፍሬ ጠብቁ፡፡ ❞

🕊

አነሳስቶ ላስጀመረን ፥ አስጀምሮም ላስፈጸመን ለቅዱሳን ሁሉ አምላክ ለልዑል እግዚአብሔር ክብር ምስጋና ይሁን፡፡ የአባታችን የቅዱስ መቃርዮስ ምልጃና ጸሎቱ አይለየን፡፡

ይቆየን !


💖                      🕊                      💖

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

05 Feb, 06:28


ከሚቀበል ይልቅ የሚሰጥ ብፁዕ ነው ያለው ማነው?

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

19 Jan, 17:04


🕊

[    ከጌታ ፊት ምድር ተናወጠች  !   ]

❝ ባሕር አየች ሸሸችም ፥ ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ። ተራሮች እንደ ኮርማዎች ፥ ኮረብቶችም እንደ ጠቦቶች ዘለሉ።

አንቺ ባሕር የሸሸሽ ፥ አንቺም ዮርዳኖስ ወደ ኋላሽ የተመለስሽ ፥ ምን ሆናችኋል ?

እናንተም ተራሮች ፥ እንደ ኮርማዎች ፥ ኮረብቶችስ ፥ እንደ ጠቦቶች ለምን ዘለላችሁ ? ከያዕቆብ አምላክ ፊት ፥ ከጌታ ፊት ምድር ተናወጠች። ❞

[ መዝ.፻፲፬፥፬ ]


†       †       †
🕊                      💖                      🕊

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

19 Jan, 16:12


🕊

[ 💖 ORTHODOXY 💖 ]

†                       †                       †

ፕሬዝዳንት ፑቲንን ጨምሮ በርካታ ሩሲያውያን ጥምቀትን በተለያዩ ስፍራዎች አክብረዋል

ከ ፺ [ 90 ] ሚሊዮን በላይ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ያሏት ሩሲያም የጥምቀት በዓልን በድምቀት ከሚያከብሩ ሀገራት መካከል ተጠቃሽ ነች።

የሩሲያ ኦርቶዶክስ [ ምስራቃውያን ] እምነት ተከታዮች ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዮርዳኖስ ወንዝ መጠመቅን እና ምስጢረ ሥላሴን መሠረት በማድረግ በበረዶ ውሃ ውስጥ ራሳቸውን ሶስት ጊዜ ይነከራሉ።

†                       †                       †
💖                    🕊                     💖

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

19 Jan, 14:40


🕊                      💖                      🕊


❝ የእግዚአብሔር መንግሥት ጽድቅና ሰላም በመንፈስ ቅዱስም የሆነ ደስታ ናት እንጂ መብልና መጠጥ አይደለችምና። ❞ [ ሮሜ.፲፬፥፲፯ ]


🕊  ተ ዋ ሕ ዶ   ሰ ማ ያ ዊ ት  🕊  ]

      [  O R T H O D O X Y  !    ]


†                       †                       †
💖                    🕊                     💖

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

19 Jan, 07:55


†        †        †


❝ ያን ጊዜ ኢየሱስ በዮሐንስ ሊጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ መጣ። ❞ — [ ማቴዎስ ፫፥፲፫ ]

🕊                      💖                      🕊

እንኳን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ጥምቀት በሰላምና በጤና አደረሳችሁ

Congratulations on the baptism of our Lord and Savior Jesus Christ in peace and health

Baga gooftaa fi fayyisaa keenya Iyyasuus Kiristoos nagaa fi fayyaan cuuphame

እንኳዕ ጥምቀት ጎይታናን መድሓኒናን ኢየሱስ ክርስቶስ ብሰላምን ብጥዕናን ኣብጽሓና።

تهانينا على معمودية ربنا ومخلصنا يسوع المسيح بسلام وصحة
Félicitations pour le baptême de notre Seigneur et Sauveur Jésus-Christ dans la paix et la santé

Herzlichen Glückwunsch zur Taufe unseres Herrn und Erlösers Jesus Christus in Frieden und Gesundheit

[ TMC ]

🕊

🕊  ተ ዋ ሕ ዶ   ሰ ማ ያ ዊ ት  🕊  ]

      [  O R T H O D O X Y  !    ]


†                        †                        †
💖                     🕊                     💖

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

18 Jan, 21:04


ልደቱን ባከበረ ጊዜ ወለተ ሔሮድያዳ በዘፈን አጥምዳ አስማለችው:: እርሱም የታላቁን ነቢይ ራስ አስቆርጦ በወጪት አድርጐ ሰጣት:: አበው "እምሔሶ ለሔሮድስ ይብላዕ መሐላሁ - ሔሮድስ መሐላውን በበላ በተሻለው ነበር" ይላሉ:: የቅዱስ ዮሐንስ ራሱ በርራ ስትሔድ አካሉን ግን ደቀ መዛሙርቱ ቀብረውታል:: [ማቴ.፫፥፩ , ማር.፮፥፲፬ , ሉቃ.፫፥፩ , ዮሐ.፩፥፮]

- " አስማተ-ዮሐንስ መጥምቅ /የመጥምቁ ዮሐንስ ስሞች "

፩. ነቢይ
፪. ሐዋርያ
፫. ሰማዕት
፬. ጻድቅ
፭. ካሕን
፮. ባሕታዊ / ገዳማዊ
፯. መጥምቀ መለኮት
፰. ጸያሔ ፍኖት [መንገድ ጠራጊ]
፱. ድንግል
፲. ተንከተም [የብሉይና የሐዲስ መገናኛ ድልድይ]
፲፩. ቃለ አዋዲ [አዋጅ ነጋሪ]
፲፪. መምሕር ወመገሥጽ
፲፫. ዘየዐቢ እምኩሉ [ከሁሉ የሚበልጥ]

አምላከ ቅዱሳን በጥምቀቱ ይቀድሰን:: ከበረከተ ጥምቀቱም ያድለን::

🕊

[  † ጥር ፲፩ [ 11 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ በዓላት  ]

፩. በዓለ ኤጲፋንያ
፪. ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ
፫. አቡነ ሐራ ድንግል ጻድቅ
፬. አባ ወቅሪስ ገዳማዊ
፭. አባ ዮሐንስ ሊቀ ጳጳሳት
፮. ቅዱስ እንጣልዮስ ሰማዕት

[   †  ወርኀዊ በዓላት     ]

፩. ቅዱስ ያሬድ ካህን
፪. ማር ገላውዴዎስ ሰማዕት
፫. ቅዱስ ፋሲለደስ ሰማዕት
፬. ቅድስት ሐና ቡርክት

" ጌታ ኢየሱስም ከተጠመቀ በኋላ ወዲያው ከውኃ ወጣ:: እነሆም ሰማያት ተከፈቱ:: የእግዚአብሔርም መንፈስ እንደ ርግብ ሲወርድ: በእርሱ ላይም ሲመጣ አየ:: እነሆም ድምጽ ከሰማያት መጥቶ :- 'በእርሱ ደስ የሚለኝ: የምወደው ልጄ ይህ ነው' አለ::" [ማቴ. ፫፥፲፮]

† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †

[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]


         †              †               †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖                   🕊                    💖

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

18 Jan, 21:04


🕊

[  † እንኳን ለመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዓመታዊ የጥምቀት በዓል [ ኤጲፋንያ ] በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። †  ]

† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †

🕊  †  በዓለ ኤጲፋንያ  †    🕊

† "ኤጲፋንያ" የሚለው ቃል ከግሪክ [ጽርዕ] ልሳን የተወሰደ ሲሆን በቁሙ "አስተርእዮ: መገለጥ" ተብሎ ይተረጐማል:: በነገረ ድኅነት ምሥጢር ግን ኤጲፋንያ ማለት "የማይታይ መለኮት የታየበት: እሳተ መለኮት በተዋሐደው ሥጋ የተገለጠበት" እንደ ማለት ነው::

"ዘኢያስተርኢ ኅቡዕ እስመ አስተርአየ ለነ::
እሳት በላዒ አምላክነ::" እንዲል:: [አርኬ]

አንድም: ምሥጢር ሆኖ የቆየ አንድነቱ: ሦስትነቱ የተገለጠበት ቀን ነውና ዕለተ ጥምቀቱ ኤጲፋንያ ይሰኛል:: መድኃኒታችን ክርስቶስ አዳምንና ልጆቹን ያድን ዘንድ ከሰማያት ዙፋኑ ወርዶ: እንደ ሰውነቱ በሥጋ ማርያም ለ፴፫ [33] ዓመታት ተመላልሷል::

ጊዜው ሲደርስም በፈለገ ዮርዳኖስ: ከዮሐንስ ዘንድ ሊጠመቅ ሔደ:: መድኃኒታችን ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ የወረደው ጥር ፲ [10] ቀን አመሻሽ ላይ ሲሆን በፍጹም ትሕትና ተራ ሲጠብቅ አድሮ ሌሊት ፲ [10] ሰዓት ላይ ደረሰውና ሊጠመቅ ቀረበ::

አሥር ሰዓት መሆኑም ርግብ [መንፈስ ቅዱስ] ሲወርድ ሰዎች ሥጋዊት ርግብ ናት ብለው እንዳይጠራጠሩ ነው:: ርግብ በሌሊት መንቀሳቀስ አትችልምና::

መድኃኒታችን ወደ ቅዱስ ዮሐንስ ሲጠጋ አምላክነቱን ተረድቶ "እንዴት ፈጣሪየ ወደ እኔ ትመጣለህ? እንዴትስ በእኔ እጅ ትጠመቃለህ?" አለው:: ትህትና ለእናትና ልጅ ልማዳቸው ነውና:: ጌታ ግን "ጽድቅን ሁሉ ልንፈጽም ይገባል" ሲል እንዲያጠምቀው ፈቀደለት::

ቅዱስ ዮሐንስም "ስመ አብ በአንተ ሕልው ነው:: ስመ ወልድ ያንተ ነው:: ስመ መንፈስ ቅዱስም በአንተ ዘንድ ሕልው ነው:: በማን ስም አጠምቅሃለሁ?" ሲል ጠየቀው::

ጌታ "ወልዱ ለቡሩክ ከሣቴ ብርሃን ተሣሐለነ:: አንተ ካህኑ ለዓለም በከመ ሲመቱ ለመልከ ጼዴቅ" እያልክ አጥምቀኝ አለው:: ትርጉሙም "የቡሩክ አብ የባሕርይ ልጁ : ብርሃንን የምትገልጥ ሆይ ይቅር በለን! አንተ እንደ መልከ ጼዴቅ ሹመት የዓለም ካህኑ ነህና" እንደ ማለት ነው::

ከዚያም ጌታ ወደ ዮርዳኖስ ሲገባ ባሕር አይታ ደነገጠች : ሸሸችም:: [መዝ.፸፮፥፲፮ , ፲፩፥፫] ዮርዳኖስ ጨንቆት ግራ ቀኝ ተመላለሰ:: እሳተ መለኮት ቆሞበታልና ውኃው ፈላ:: በጌታ ትዕዛዝ ግን ጸና::

ጌታ ተጠምቆ: ሥርዓተ ጥምቀትን ሠርቶ: ዮርዳኖስን ብርህት ማሕጸን አድርጐ: የእዳ ደብዳቤአችንንም ቀዶ ከወጣ በኋላ ሰማያት ተከፈቱ:: ማለትም አዲስ ምሥጢር ተገለጠ::

አብ በደመና ሆኖ "የምወደው: የምወልደው: ሕልው ሆኜ ልመለክበት የመረጥኩት የባሕርይ ልጄ ይህ ነው!" ሲል በአካላዊ ቃሉ ፍጹም ተዋሕዶን መሰከረ:: መንፈስ ቅዱስም በአምሳለ ርግብ ወርዶ በራሱ ላይ ተቀመጠ:: ራሱንም ቆንጠጥ አድርጐ ያዘው:: በዚህም የሥላሴ አንድነቱ: ሦስትነቱ ታወቀ: ተገለጠ::

ቅዱስ ዮሐንስ "መጥምቀ መለኮት" የሚባልበትን ታላቁን ክብር ሲያገኝ ዮርዳኖስ የልጅነት መገኛ ቅዱስ ባሕር ሆነ::


🕊  † ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ †  🕊

ቅዱስ ወንጌል ላይ ቅዱስ ሉቃስ "ዘካርያስ ካህኑና ቅድስት ኤልሳቤጥ በሰውና በእግዚአብሔር ፊት ያለ ነቀፋ የሚኖሩ ጻድቃን ነበሩ" ይላቸዋል:: [ ሉቃ.፩፥፮ ]

እሊህ ቅዱሳን ባልና ሚስት ግን መካኖች በመሆናቸው ልጅ ሳይወልዱ ዘመናቸው አልፎ ነበር:: እንደ ቤተ ክርስቲያን ትውፊት ዕድሜአቸው የኤልሳቤጥ ፺ [90] የዘካርያስ ደግሞ ፻ [100] ደርሶ ነበር::

ፍጹም መታገሳቸውን የተመለከተ ጌታ ግን በስተ እርጅናቸው ከሰው ሁሉ በላይ የሆነ: ትንቢት ለብቻው የተነገረለት [ኢሳ.፵፥፫ , ሚል.፫፥፩] ታላቅ ነቢይን ይሰጣቸው ዘንድ መልአከ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤልን ላከላቸው::

ቅዱስ ዘካርያስ ሰው ነውና ከደስታ ብዛት በመከራከሩ ድዳ ሆነ:: ቅድስቲቷ ግን መስከረም ፳፮ [26] ቀን ታላቁን ሰው ጸንሳ ለ፮ [6] ወራት ራሷን ሠወረች:: በ፮ [6] ኛው ወር የፍጥረት ሁሉ ጌታ በተጸነሰ ጊዜ የአርያም ንግሥት ድንግል እመቤታችን ደጋ ደጋውን ወደ ኤልሳቤጥ መጣች:: ሁለቱ ቅዱሳት የእህትማማች ልጆች ናቸው::

የአምላክ እናቱ ስትደርስና "ሰላም" ስትላቸው መንፈስ ቅዱስ በእናትና ልጅ ወርዶ ኤልሳቤጥ በምስጋና: ዮሐንስ ደግሞ ገና በማሕጸን ሳለ በደስታ ዘለለ [ሰገደ]:: ከዚህ በኋላ ሰኔ ፴ [30] ተወልዶ: አባቱ ዘካርያስ "ዮሐንስ" ሲለው አንደበቱ ተፈትቶለታል::

ቅዱስ ዮሐንስ ከተወለደ ፪ ዓመት ከ፮ ወር በሆነው ጊዜ ሰብአ ሰገል በመምጣታቸው በእሥራኤል ምድር የሚገኙ ሕፃናትን ሔሮድስ ቁዝ አስፈጀ:: ትንሽ ቆይቶም አይሁድ ለሔሮድስ ስለ ቅዱሱ ሕፃን ነገሩት:: "ሲጸነስ የአባቱን አንደበት የዘጋ: ሲወለድ ደግሞ የከፈተ 'ዮሐንስ' የሚባል ሕፃን አለና እሱንም ግደል" አሉ::

እናቱ ቅድስት ኤልሳቤጥ ይዛው ስትሸሽ ካህኑን ዘካርያስን ግን በቤተ መቅደስ መካከል ገድለውታል:: አረጋይት ኤልሳቤጥም ሕፃኑን እያሳደገች በገዳመ ዚፋታ ለ፫ [፭] ዓመታት ቆይታለች:: ቅዱስ ዮሐንስ ፭ [፯] ዓመት ሲሞላው ግን እዚያው በበርሃ እናቱ ዐረፈች:: ከሰማይ ዘካርያስና ስምዖን ወርደው ቀበሯት::

ሕፃኑ ዮሐንስ ሲያለቅስ ድንግል ማርያም ስንት አገር አልፋ ሰማችው:: እርሷም ስደት ላይ ነበረችና:: ከጌታ ጋር በደመና ሒደው ድንግል አቅፋ አጽናናችው:: ጌታንም "እንውሰደው ይሆን?" አለችው:: ጌታችን ግን "ለአገልግሎት እስክጠራው እዚህ ይቆይ" አላት:: ባርካው: አጽናንታውም ተለያዩ::

ቅዱስ ዮሐንስ ከዚህ በኋላ በዚያ ቆላ የግመል ጠጉር ለብሶ: ጠፍር ታጥቆ ተባሕትዎውን ቀጠለ:: ለ፳፭ [፳፫] ዓመታትም በንጽሕና ሲኖር ከምድር አራዊትና ከሰማይ መላእክት በቀር ማንንም አላየም:: ይሕችን ዐመጸኛ ዓለምም አልቀመሳትም::

ከዚህ በኋላ ፴ [ 30 ] ዘመን ሲሞላው እግዚአብሔር ከሰማይ ተናገረው:: "ሒድ! የልጄን ጐዳና ጥረግ" አለው:: ነቢያት ስለዚህ ነገር ተናግረው ነበርና:: [ኢሳ.፵፥፫, ሚል.፫፥፩] አባቱ ዘካርያስም "ወአንተኒ ሕፃን ነቢየ ልዑል ትሰመይ: እስመ ተሐውር ቅድመ እግዚአብሔር ከመ ትጺሕ ፍኖቶ" [ሉቃ.፩፥፸፮] ብሎ መንገድ ጠራጊነቱን ተናግሮ ነበርና::

ቅዱስ ዮሐንስ በዚያ ጊዜ በኃይለ መንፈስ ቅዱስ እየገሰገሰ ከበርሃ ወደ ይሁዳ መጣ:: ያዩት ሁሉ ፈሩት: አከበሩት:: ቁመቱ ቀጥ ያለ: ጽሕሙ እንደ ተፈተለ ሐር የወረደ: ጸጉሩ የቁራ ያህል የጠቆረ: መልኩ የተሟላ: ግርማው የሚያስፈራ ገዳማዊ ነውና::

ፈጥኖም ሕዝቡን ለንስሐ ሰበከ: ለንስሐም በርካቶችን አጠመቃቸው:: በዚህ አገልግሎት ለ፮ ወራት ቆይቶ ጌታችን ወደ እርሱ ዘንድ መጣ:: ዮሐንስ ሰማይን ከነግሱ: ምድርን ከነልብሱ የያዘ ፈጣሪ "አጥምቀኝ" ብሎ ሲመጣ ደነገጠ:: የሚገባበትም ጠፋው::

" እንቢ ጌታየ ! አንተ አጥምቀኝ " አለው:: ጌታ ግን "ፈቅጄልሃለሁ" አለው: አጠመቀው:: በዚህ ምክንያት ይሔው እስከ ዛሬም "መጥምቀ መለኮት" ሲባል ይኖራል:: ቅዱስ ዮሐንስ በመጨረሻ ሔሮድስን ገሰጸው:: ንጉሡም ተቀይሞ ለ፯ ቀናት አሠረው::

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

18 Jan, 17:03


🕊                      💖                      🕊

❝ በነጻነት ልንኖር ክርስቶስ ነጻነት አወጣን ! ❞

[ ገላ.፭፥፩ ]

🕊                      💖                      🕊

[  ብርሃነ ጥምቀቱን በተቀደሰው ኦርቶዶክሳዊ ሕይወት ! ]

❝ ነገር ግን እላለሁ ፥ በመንፈስ ተመላለሱ ፥ የሥጋንም ምኞት ከቶ አትፈጽሙ። ... በመንፈስ ብትመሩ ግን ከሕግ በታች አይደላችሁም።

የሥጋ ሥራም የተገለጠ ነው እርሱም ዝሙት ፥ ርኵሰት ፥ መዳራት ፥ ጣዖትን ማምለክ ፥ ምዋርት ፥ ጥል ፥ ክርክር ፥ ቅንዓት ፥ ቁጣ ፥ አድመኛነት ፥ መለያየት ፥ መናፍቅነት ፥ ምቀኝነት ፥ መግደል ፥ ስካር ፥ ዘፋኝነት ፥ ይህንም የሚመስል ነው። አስቀድሜም እንዳልሁ ፥ እንደዚህ ያሉትን የሚያደርጉ የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም።

የመንፈስ ፍሬ ግን ፍቅር ፥ ደስታ ፥ ሰላም ፥ ትዕግሥት ፥ ቸርነት ፥ በጎነት ፥ እምነት ፥ የውሃት ፥ ራስን መግዛት ነው። ❞ [ ገላ.፭፥፲፮-፳፪ ]

🕊                      💖                      🕊

❝ በክርስቶስ ያለውን መልካሙን ኑሮአችሁን የሚሳደቡ ሰዎች ክፉን እንደምታደርጉ በሚያሙበት ነገር እንዲያፍሩ በጎ ሕሊና ይኑራችሁ። ❞ [ ፩ጴጥ.፫፥፲፮ ]


🕊                      💖                      🕊

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

18 Jan, 16:23


🕊                      💖                      🕊


❝ በተቀደሰ አሳሳም እርስ በርሳችሁ ሰላምታ ተሰጣጡ። የክርስቶስ አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ሰላምታ ያቀርቡላችኋል። ❞ [ ሮሜ.፲፮፥፲፮ ]


🕊  ተ ዋ ሕ ዶ   ሰ ማ ያ ዊ ት  🕊  ]

      [  O R T H O D O X Y  !    ]


†                        †                        †
💖                     🕊                     💖

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

09 Jan, 20:52


🕊

[  † እንኳን ለጻድቅ ሰው " ቅዱስ አቤል" እና " ቅዱስ ቴዎናስ ሊቅ " ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ †  ]

† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።

---------------------------------------------

🕊   †  ቅዱስ አቤል ጻድቅ †   🕊

- እግዚአብሔር አዳምን በ፯ ሃብታት አክብሮ በገነት ቢያኖረው "አትብላ" የተባለውን ዕፀ በለስ በላ:: በዚህም ከፈጣሪው ተጣልቶ: በሞተ ሥጋ ሞተ ነፍስ: በርደተ መቃብር ርደተ ገሃነም ተፈረደበት:: በሁዋላ ግን ንስሃ ስለ ገባ "ከ፭ ቀን ተኩል [5,500 ዘመን] በሁዋላ ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለሁ" የሚል ቃል ኪዳንን ሰጠው::

- አዳምና ሔዋን ከገነት ከወጡ በሁዋላ ወዲያው ሕገ ሰብሳብን [ የወንድና የሴት ሥርዓትን ] አልፈጸሙም:: ይልቁኑ ለ፲፬ ኢዮቤልዩ [ለ100 [98] ዓመታት] ንስሃ ገቡ: አለቀሱ እንጂ::

- አለቃቀሳቸውም እንደኛ በቤተ ፈት ልማድ ሳይሆን "እግዚአብሔርን ያህል ጌታ: ገነትን ታህል ቦታ በበደላችን አጣን" እያሉ ነበር:: "አልቦቱ ለአዳም ካልዕ ሕሊና ዘእንበለ ብካይ ላዕለ ኃጢአቱ" እንዲል:: [መቅድመ ወንጌል]

- እውነትን እንነጋገር ከተባለ እኛ ለወላጆቻችን አዳምና ሔዋን ተገቢውን ክብር እየሰጠናቸው አይደለም:: አንደበቱን የከፈተ "አስተማሪ" ሁሉ ኃጢአታቸውን እንጂ ክብራቸውን ሲናገር ሰምቼ አላውቅም:: ሌላው ይቅርና ማንም ሰው "ቅዱስ አዳምና ቅድስት ሔዋን" ብሎ ሲጠራቸው ገጥሞኝ አያውቅም::

- የሚገርመው ደግሞ እኛ እልፍ አእላፍ ኃጢአትን ተሸክመን እነርሱን ስለ አንዲቷ ኃጢአታቸው ስንወቅሳቸው መዋላችን ነው:: በእነርሱ ምክንያት ገነት ብትዘጋ: ዳግመኛ የተከፈተችው በፍጹም እንባና ንስሃቸው ነው::

- "ፍቅር ሰሐቦ ለወልድ ኃያል እመንበሩ ወአብጽሖ እስከ ለሞት" [ቅዳሴ ማርያም] እንዲል:: ጌታን ለሰውነት: ለሞት ያበቃው ፍቅረ አዳም መሆኑን ልንዘነጋ አይገባም::

†  በዚያውም ላይ አባታችን ቅዱስ አዳም :-
- በኩረ ኩሉ ፍጥረት
- በኩረ ነቢያት አበው
- በኩረ ሐዋርያት ወአርድእት
- በኩረ ጻድቃን ወሰማዕት
- በኩረ ደናግል ወመነኮሳት የሆነ ደግ ፍጥረት ነው:: ስለዚህም ቅዱሳን አዳምና ሔዋንን ልናከብራቸው በእጅጉ ይገባናል::

- ወደ ቀደመ ነገራችን እንመለስና ቅዱሳኑ አዳምና ሔዋን ንስሃቸውን ፈጽመው: ተስፋ ድኅነት ከተሰጣቸው በሁዋላ አብረው አደሩ:: በዚያች ሌሊትም ቃየንና ኤልዩድ [ሉድ] ተጸነሱ: በጊዜውም ተወለዱ::

- አሁንም ድጋሚ አብረው ቢያድሩ ቅዱስ አቤልና መንትያው አቅሌማ ተጸንሰው ተወለዱ:: ዓለምም በጊዜው እነዚ ፮ ሰዎች ይኖሩባት ነበር:: ምንም እንኩዋ እናታችን ቅድስት ሔዋን ብዙ መንትያዎችን ብትወልድም "ብዙ ተባዙ: ምድርንም ሙሉአት" ያለው የጌታ ቃል ይፈጸም ዘንድ ልጆቻቸውን ማጋባት ነበረባቸው::

- የመጀመሪያው የልጆች ጋብቻም በአቤልና በኤልዩድ: እንዲሁም በቃየንና በአቅሌማ መካከል እንዲሆን ተወሰነ:: አባታችን ቅዱስ አዳም ደግ ነቢይ ነውና ለማራራቅ ሲል ይህንን አደረገ:: ነገር ግን በውሳኔው እንደማይስማማ ቃየን ተናገረ::

- ምክንያቱ ደግሞ የአቤል መንትያ መልኩዋ የኔ ብጤ በመሆኗና የእርሱ መንትያ ኤልዩድ ግን እናቷን ቅድስት ሔዋንን የምትመስል ቆንዦ ስለ ነበረች "እኔ መንትያየን ነው የማገባ" የሚል ነበር::

- አቤል ግን የቱንም ቢሉት ከወላጆቹና ከፈጣሪው ትዕዛዝ የማይወጣ ደግ ሰው ነበር:: በጊዜውም መላእክት ባስተማሩት መሠረት ቅዱስ ሰው አዳም ለልጆቹ እርሻንና እንስሳት እርባታን አስተምሯቸው ነበርና ቃየን በግብርና: አቤል ደግሞ በበግ እረኝነት [እርባታ] ይኖሩ ነበር::

- ቅዱስ ሰው አቤል በቅንነቱና በታዛዥነቱ መንፈሰ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ሆነለት:: ሁሌም ስንጠራው "ጻድቅ" ብለን ነው:: ከጻድቃነ ብሊት [ብሉይ] አንዱ ሲሆን የዚህች ዓለም የመጀመሪያው ሟችና ሰማዕት ለመሆንም በቅቷል::

- በሴት ልጅ መልክ ምክንያት በዚህች ዓለም ጥላቻ "ሀ" ብሎ ጀመረ:: ምንም ሳያደርገው ቃየን ወንድሙ አቤልን ጠላው:: የጥላቻ አባቷ ዲያብሎስ ነውና የእርሱ ዘመድ ሆነ::

- ነገሮች ያላማሩት ቅዱሱ አባታቸው ግን በጐ መፍትሔ ሊሆናቸው: የቀናውንም ሥርዓት ሊያስተምራቸው "ለእግዚአብሔር መስዋዕትን አቅርቡ:: እግዚአብሔር መስዋዕቱን የተቀበለለት ኤልዩድን ያገባል" አላቸው:: "እሺ" ብለው መካነ ምስዋዕ አዘጋጁ::

- አቤል ከንጹሕ ልቡ እንዲህ አሰበ:: "እግዚአብሔር ንጹሐ ባሕርይ ነውና ንጹሕ ነገርን ይወዳል" አለ:: በዚህም ቀንዱ ያልከረከረውን: ጥፍሩ ያልዘረዘረውን: ጠጉሩ ያላረረውን: የ፩ ዓመት ነውር የሌለበትን ጠቦት አቀረበ::

- ቃየን ደግሞ ከክፉ ልቡ እንዲህ አሰበ:: "እግዚአብሔር አይበላ: አይጠጣ:: ጥሩ ነገር ብሰጠውስ ምን ያደርገዋል" ብሎ ዋግ የመታውን: ነቀዝ የበላውን እሕል [ሥርናይ] አቀረበ:: እዚህ ላይ አንድ ነገርን ልብ እንበል::

- እግዚአብሔር እንደ ሰው አይበላም: አይጠጣም:: ይህ እውነት ነው:: ግን እግዚአብሔር የአቤልን መስዋዕት የተቀበለው በጉን ፈልጐ: ወይ አቤል ቆንጆዋን ሴት እንዲያገባ አይደለም:: ምክንያቱም አቤል እንደሚገደልና በድንግልናው እንደሚሰዋ እርሱ ያውቃልና::

- ይልቁኑ እግዚአብሔርን የሚያስደስተው የስጦታው ምንነት ሳይሆን የሰጭው ማንነት ነውና እኛ ክርዳድ ሆነን ለእግዚአብሔር ስንዴ ልናቀርብለት አንችልም:: ምክንያቱም እግዚአብሔር ከእኛ ምንም ነገርን አይሻም:: ሰማይና ምድር: ፍጥረታት በሙሉ የእርሱ ናቸውና::

- ንጹሐ ባሕርይ ጌታ ከእኛ አንዲት ነገርን ብቻ ይሻል:: ይህቺም በንጹሕ ልቡና የምትቀርብ ንጹሕ አምልኮ ናት:: በዚህም የምንጠቀመው እኛ እንጂ እርሱ አይደለም::

- ፪ቱ ወንድማማቾች መስዋዕትን ሲያቀርቡለትም "ወነጸረ እግዚአብሔር ላዕለ አቤል ወላዕለ መስዋዕቱ" እንዲል እግዚአብለሔር ቃየንና መስዋዕቱን ትቶ መጀመሪያ ወደ አቤል: ቀጥሎም ወደ መስዋዕቱ ተመለከተ:: ማለትም አቤልና መስዋዕቱን ወደዳቸው::

- በዚህ ምክንያትም ቃየን ተበሳጨ:: ክፋትን እያሰበ ሲመላለስም ሰይጣን ተገናኝቶ ክፉውን መከረው:: በቁራ ተመስሎ ነፍሰ ገዳይነትን አስተማረው:: በዚህም ወደ ምድረ በዳ ወስዶ በድንጋይ ጭንቅላቱን መትቶ ገድሎት ሔደ::

- በዚህ ምክንያትም አቤል "በኩረ ምውታን - የመጀመሪያው ሟች" ተባለ:: "የዋሕ" የተባለበትም ምሥጢሩ ቂም እንደ ያዘበት: ክፋትን እንዳሰበበት እያወቀ እንደ በግ ተከትሎት መሔዱ ነው::

- ስለዚህም ነገር ለመድኃኒታችን ክርስቶስ ምሳሌው ሆነ:: አባ ሕርያቆስም እመቤታችንን ሲያመሰግናት "የውሃቱ ለአቤል ዘተቀትለ በአመጻ-በአመጻ የተገደለ የአቤል የውሃቱ: የየዋህነቱን ዋጋ የምታሰጭው አንቺ ነሽ" ብሏል::

+ቅዱስ አቤል ከተገደለ ከ፳፰ [28] ዓመታት በሁዋላ ነፍሱ ገነትን ተሳልማለች:: ስለ ቅዱሱ ግፍም እግዚአብሔር የቃየንን ዘሮች በጥፋት ውሃ ደምስሷቸዋል::


🕊  † ቅዱስ ቴዎናስ ሊቀ ዻዻሳት †  🕊

- ይህ ቅዱስ ሰው ተወልዶ ያደገው በእስክንድርያ [ግብጽ] ሲሆን ዘመኑም ፫ኛው መቶ ክ/ዘመን ነው:: እርሱ ትምሕርተ ቤተ ክርስቲያንን ተምሮ ጸጋው ቢበዛለት ከምዕመንነት ወደ ዲቁና: ከዲቁና ወደ ቅስና ማዕርግ ተሸጋገረ::

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

09 Jan, 20:52


- ቀጥሎም ለታላቅ ሃላፊነት ተመረጠ:: አባ መክሲሞስ ባረፈ ጊዜ የግብጽ ፲፮ኛ ፓትርያርክ ሆነ:: ግን ኃላፊነቱ ሠርግና ምላሽ [የተመቸ] አልነበረም:: ምክንያቱም እርሱ ሊቀ ዻዻሳት ሲሆን ዘመነ ሰማዕታት በመጀመሩ ክርስቲያኖች ተሰደዱ: ተጨፈጨፉ::

- አብያተ ክርስቲያናትም ተቃጥለው አለቁ:: በዚሀ ጊዜ ቅዱስ ቴዎናስ እየዞረ ሕዝቡን ያጸና ነበር:: በተለይም የእመቤታችንን ቤተ ክርስቲያን አንጾ ለሕዝቡ ያቆርብ: ያስተምር ነበር::

- በዘመነ ሲመቱ ተፍጻሜተ ሰማዕት ቅዱስ ዼጥሮስን ጨምሮ ብዙ አርድእትን አፍርቷል:: ሥልጣነ እግዚአብሔር ጋርዶት ስለ ነበር አገልግሎቱን ፈጽሞ በዚህ ቀን ዐርፏል::

የጻድቅ ሰው አቤል አምላከ የውሃቱን ይስጠን:: የዋሃንን ያብዛልን:: ከበረከቱም ይክፈለን::

🕊

[   † ጥር ፪ [ 2 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት  ]

፩. ቅዱስ አቤል ጻድቅ
፪. ቅዱስ ቴዎናስ ሊቀ ዻዻሳት
፫. ቅዱስ አላኒቆስ ሰማዕት
፬. ቅድስት ሳቤላ ነቢዪት
፭. ቅዳሴ ቤታ ለድንግል [በደብረ አባ ሲኖዳ]

[  †  ወርኀዊ በዓላት   ]

፩. ቅዱስ ታዴዎስ ሐዋርያ
፪. ቅዱስ ኢዮብ ጻድቅ ተአጋሲ
፫. ቅዱስ አባ ዻውሊ ገዳማዊ [ታላቁ]
፬. ቅዱስ ዮሐንስ ነቢይ [መጥምቀ መለኮት]
፭. ሊቁ አባ ሕርያቆስ
፮. ቅዱስ ሳዊሮስ ዘአንጾኪያ

" እምነትም ተስፋ ስለምናደርገው ነገር የሚያስረግጥ: የማናየውንም ነገር የሚያስረዳ ነው . . . አቤል ከቃየን ይልቅ የሚበልጥን መስዋዕት ለእግዚአብሔር በእምነት አቀረበ:: በዚህም እግዚአብሔር ስለ ስጦታው ሲመሰክር እርሱ ጻድቅ እንደ ሆነ ተመሰከረለት:: ሞቶም ሳለ በመስዋዕቱ እስከ አሁን ይናገራል::" [ዕብ.፲፩፥፩]

["አቤል" ማለት በስዕሉ ከፊት ያለው ወጣት ነው]

† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †

[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]


         †              †               †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖                   🕊                    💖

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

09 Jan, 17:21


🕊                        💖                       🕊   

                        

❝ የዓለም ሁሉ መድኃኒት የምትሆን ብላቴና እግሯ የተመላለሰበቱን ምድር እስም ዘንድ ማን በከፈለኝ : ይቅርታን የምታሰጥ ብላቴና ጥላዋ ይነካኝ ዘንድ ማን በከፈለኝ : የብርሃን ልጅ ወደሄደችበት እከተላት ዘንድ ማን በከፈለኝ : የእግሯንም ጫማ እሸከም ዘንድ ማን በከፈለኝ። ❞
          
                           🌼

[   🕊  አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ  🕊   ]



🕊                        💖                       🕊

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

09 Jan, 13:28


                        †                         

  [  🕊  መምጣቱ ድንቅ ነው !  🕊  ]

💖

❝ ኢየሩሳሌም ትላለች ፣ ንጉሤና አምላኬ ተወለደል ፣ በመለኮቱ ፍስሐ በቤተልሔም ተወለደ ፣ ... ኢየሩሳሌም አመሰገነችው ...

መምጣቱ ድንቅ ነው ፣ መወለዱም ድንቅ ነው ፣ ጥምቀቱም ድንቅ ነው ፣ ዮሐንስ ያጠመቀው አይቶም መመርመር ያልቻለው እርሱ ፣ በደስታና በሰላም በመጠመቁ ውኃ ተቀደሰች።

ዓለምን ያድነው ዘንድ [ አብ ] የበኵር ልጁን ወደ ዓለም ላከ ፣ በክርስቶስ ልደት ጥምቀት እና መገለጥ ምክንያት የሰላም ቃል በምድር ሁሉ ላይ ተዘራ።

ብዙ እረኞችም መጡ ድንጋይዋንም ከውኃ ጉድጓዱ አፍ መክፈት [ ወይም ማንሣት ] ተሳናቸው ፣ ከሰዎች ሥጋ ሊለብስ የሚገባው ከወገቡ ያለ ያዕቆብ እስኪመጣ ድረስ ፣ [ እሱ ድንጋዩን ] ከፍቶ መንጋውን አጠጣ። እንደዚሁም ብዙ ነቢያት መጡ ፣ ጥምቀትንም ሊገልጧት አልተቻላቸውም ፣ ታላቁ እረኛ ከሰማይ እስኪመጣ ድረስ ፣ ከፍቶ በውስጧ ብዙ ሕዝቦችን አጠመቀ ፣ የመድኃኒታችን ተአምራቱ ድንቅ ነው" በጎቹ በሚጠብቅባት በያዕቆብ በትር አምሳል ከእሤይ ሥር በትር እንደወጣች እሷም ማርያም ናት። በትር ትወጣለች አበባም [ ከርሷ ] ይወጣል ብሎ ስለተናገረውም ፣ እሱ [ በተዋሕዶ የከበረ ] ሥግው ቃል ነው ፣ እሱ የአምላክ ልጅ
ነው። ❞

🕊 ቅ ዱ ስ ያ ሬ ድ 🕊   ]

†                       †                        †
💖                    🕊                     💖

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

09 Jan, 09:16


🕊

እንኳን ለቀዳሜ ሰማዕት ቅዱስ እስጢፋኖስ ዓመታዊ የልደትና ሰማዕትነት ክብር ለተቀበለበት በዓሉ መታሰቢያ በሰላም አደረሳችሁ። 

[  እንደ መልአክ ፊት ሆኖ ፊቱን አዩት ! ]

💖

❝ የእግዚአብሔርም ቃል እየሰፋ ሄደ ፥ በኢየሩሳሌምም የደቀ መዛሙርት ቍጥር እጅግ እየበዛ ሄደ ፤ ከካህናትም ብዙ ሰዎች ለሃይማኖት የታዘዙ ሆኑ። እስጢፋኖስም ጸጋንና ኃይልን ተሞልቶ በሕዝቡ መካከል ድንቅንና ታላቅ ምልክትን ያደርግ ነበር።
...
በሸንጎም የተቀመጡት ሁሉ ትኵር ብለው ሲመለከቱት እንደ መልአክ ፊት ሆኖ ፊቱን አዩት። ❞ [ ሥራ.፮፥፯-፲፭ ]

❝ ከከተማም ወደ ውጭ አውጥተው ወገሩት። ምስክሮችም ልብሳቸውን ሳውል በሚሉት በአንድ ጎበዝ እግር አጠገብ አኖሩ። እስጢፋኖስም። ጌታ ኢየሱስ ሆይ ፥ ነፍሴን ተቀበል ብሎ ሲጠራ ይወግሩት ነበር።

ተንበርክኮም። ጌታ ሆይ ፥ ይህን ኃጢአት አትቍጠርባቸው ብሎ በታላቅ ድምፅ ጮኸ። ይህንም ብሎ አንቀላፋ። ❞
[ ሥራ.፯፥፶፰ ]
                        
🕊

❝ ሰማዕታት የዚችን አለም ጣዕም ናቁ ፤ ደማቸውንም ስለ እግዚአብሔር አፈሰሱ ፤ ስለመንግስተ ሠማያት መራራ ሞትን ታገሡ፡፡ ❞

[ ውዳሴ ማርያም ዘሐሙስ ]

🕊

❝ የሃይማኖት ምሰሶ ፥ የዲያቆናት አለቃ ፥ የሰማዕታት መጀመሪያ ለሆነ ለእስጢፋኖስ ሰላምታ ይገባል። የአብ ልጅ በቀኙ ተቀምጦ ሥላሴን በዓይኑ ያየ ፥ ተሟጋቾች ተከራክረው ያልረቱት ፥ ጥበብን በአንደበቱ የሚናገር ፥ የቃሉ ፍሬዎች እንደ አበባዎች የሚያምሩ ፥ በአይሁድ መካከል በአደባባይ ስለ ፈጣሪው ሰማዕትነትን የተቀበለ ፥ ሰማዕተ ወልድ ሰማዕተ ኢየሱስ ክርስቶስ እስጢፋኖስ ነው። ❞

[ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ]


💖                    🕊                     💖

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

08 Jan, 19:41


🕊

[   ጥር ፩ [ 1 ]    ]

[  † እንኩዋን ለቅዱስ " እስጢፋኖስ ሊቀ ዲያቆናት " እና " ለአክሚም ሰማዕታት " ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ †  ]

† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።

---------------------------------------------

† ቅዱስ እስጢፋኖስ ሊቀ ዲያቆናት ወቀዳሜ ሰማዕት † 

- በሕገ ወንጌል [ ክርስትና ] የመጀመሪያው ሊቀ ዲያቆናትና ቀዳሚው ሰማዕት ይህ ቅዱስ ነው:: ቅዱሱ በመጀመሪያው መቶ ክ/ዘመን አስገራሚ ማንነት ከነበራቸው እሥራኤላውያን አንዱ ነበር:: ይህስ እንደ ምን ነው ቢሉ :-

- የቅዱስ እስጢፋኖስ ወላጆቹ ስምዖንና ማርያም ይባላሉ:: [ ሌሎች ናቸው የሚሉም አሉ ] ገና ከልጅነቱ ቁም ነገር ወዳድ የነበረው ቅዱስ በሥርዓተ ኦሪት አድጐ እድሜው ሲደርስ ወደ ት ቤት ገባ:: የወቅቱ ታላቅ መምሕር ገማልያል ይባል ነበር:: ይህ ሰው በሐዋርያት ሥራ ምዕራፍ ፭፥፴፫ ላይ ተጠቅሷል::

- በትውፊት ትምሕርት ደግሞ ይህ ደግ [ ትልቅ ] ሰው በርካታ ቅዱሳንን [ እስጢፋኖስን : ዻውሎስን : ናትናኤልን : ኒቆዲሞስን . . .] አስተምሯል:: በጌታችን መዋዕለ ስብከት ጊዜም ከፈጣሪያችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ እየቀረበ ይጨዋወት ነበር:: በፍጻሜውም አምኗል::

- ወደ ቀደመ ነገራችን እንመለስና ቅዱስ እስጢፋኖስ ከዚህ ምሑር ዘንድ ተምሮ: ኦሪቱን ነቢያቱን ጠንቅቆ ወጣ:: ወቅቱ አስቸጋሪና ለኃጢአት ሕይወት የተመቸ ቢሆንም ቅዱሱ ግን የመሲህን መምጣት በጸሎትና በተስፋ ይጠባበቅ ነበር::

- በወቅቱ ደግሞ መጥምቁ ቅዱስ ዮሐንስ የንስሃ ጥምቀትን እየሰበከ መምጣቱን የተመለከተ ቅዱስ እስጢፋኖስ ነገሩን መረመረ:: ከእግዚአብሔር ሆኖ ቢያገኘው የመጥምቁ ዮሐንስ ደቀ መዝሙር ሆነ:: ለ፮ ወራትም በትጋት ቅዱስ ዮሐንስን አገለገለ::

- ለ፮ ወራት ከቅዱስ ዮሐንስ ዘንድ ከተማረ በሁዋላ ለስም አጠራሩ ስግደት ይድረሰውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተጠመቀ:: በወቅቱ የተደረገውን ታላቅ ተአምር ልብ ያለው ቅዱስ እስጢፋኖስ መምሕሩን ቅዱስ ዮሐንስን እንዲያስረዳው ጠየቀው::
"ከእኔ ይልቅ ከፈጣሪው አንደበት ይስማው" በሚል ላከው:: ቅዱሱም ከጌታ ዘንድ ሔዶ: እጅ ነስቶ ተማረ:: [ሉቃ.፯፥፲፰] በዚያውም የጌታ ደቀ መዝሙር ሆኖ ቀረ:: ጌታም ከ፸፪ቱ አርድእት አንዱ አድርጐት ለአገልግሎት ላከው:: አጋንንትም ተገዙለት:: [ሉቃ.፲፥፲፯]

- ቅዱስ እስጢፋኖስ ጌታችን መድኃኔ ዓለም ከዋለበት እየዋለ: ካደረበት እያደረ ወንጌልን ተማረ:: ምሥጢር አስተረጐመ:: ጌታ በፈቃዱ ስለ እኛ ሙቶ ከተነሳ በኋላ ሲያርግ ደቀ መዛሙርቱን በአንብሮ እድ ባርኳል:: በዚህ ጊዜም ቅዱሱ እንደ ወንድሞቹ ሐዋርያት ቅስናን [ዽዽስናን] ተሹሟል:: በበዓለ ሃምሳም መንፈስ ቅዱስ በወረደ ጊዜ ከ፸፪ቱ አርድእት የእርሱን ያህል ልሳን የበዛለት: ምሥጢርም የተገለጠለት የለም:: በፍጹም ድፍረትም ወንጌልን ይሰብክ ገባ::

በመጀመሪያይቱ ዘመን ቤተ ክርስቲያን ከማዕድ ሥርዓት ጋር በተያያዘ ፈተና ሲመጣ በመንፈስ ቅዱስ ምርጫ ፯ ዲያቆናት ሲመረጡ አንዱ እርሱ ነበር:: አልፎም የ፮ቱ ዲያቆናት አለቃ እና የ፰ሺው ማሕበር መሪ [አስተዳዳሪ] ሆኗል:: ፰ሺ ሰውን ከአጋንንት ፈተና መጠበቅ ምን ያህል ከባድ እንደ ሆነ ለማወቅ አባቶቻችንን መጠየቅ ነው::

- አንድን ሰው ተቆጣጥሮ ለድኅነት ማብቃት እንኳ እጅግ ፈተና ነው:: መጽሐፍ እንደሚል ግን 'መንፈስ ቅዱስ የሞላበት: ማሕደረ እግዚአብሔር' ነውና ለእርሱ ተቻለው:: [ ሐዋ.፮፥፭ ]  አንዳንዶቻችን ቅዱስ እስጢፋኖስ 'ሊቀ ዲያቆናት' ሲባል እንደ ዘመኑ ይመስለን ይሆናል:: እርሱ በመጀመሪያ ሐዋርያና ካህን ነው:: ዲቁናው ለእርሱ 'በራት ላይ ዳረጐት' ነው እንጂ እንዲሁ ዲያቆን ብቻ አይደለም::

- ቅዱስ እስጢፋኖስ ከጌታ ዕርገት በኋላ ለ ፩ ዓመት ያህል ፰ሺውን ማኅበር እየመራ: ወንጌልን እየሰበከ ቢጋደል ኦሪት 'እጠፋ እጠፋ': ወንጌል ደግሞ 'እሰፋ እሰፋ' አለች:: በዚህ ጊዜ 'ክርስትናን ለማጥፋት መፍትሔው ቅዱስ እስጢፋኖስን መግደል ነው' ብለው አይሁድ በማመናቸው ሊገልድሉት አስበውም አልቀሩ ገደሉት::

- እርሱ ግን ፊቱ እንደ እግዚአብሔር መልአክ እያበራ ፈጣሪውን በብዙ ነገር መሰለው:: በመጨረሻውም ስለ እነሱ ምሕረትን እየለመነ በድንጋይ ወገሩት:: ደቀ መዛሙርቱም ታላቅ ለቅሶን እያለቀሱ ቀበሩት::

🕊   †    ፍልሠት    †   🕊

- ቅዱስ እስጢፋኖስ ካረፈ ከ፫ መቶ ዓመታት በኋላ በኢየሩሳሌም የሚኖር አንድ ደግ ሰው ነበር:: ስሙም ሉክያኖስ ይባል ነበር:: በተደጋጋሚ በራዕይ ቅዱሱ እየተገለጠ "ሥጋየን አውጣ" ይለው ነበርና ሒዶ ለዻዻሱ ነገረው:: ዻዻሱም ደስ ብሎት ካህናትና ምዕመናንን ሰብስቦ ወደ አጸደ ገማልያል [ የመምሕሩ ርስት ነው ] ሔደ::

- ቦታውንም በቆፈሩ ጊዜ ታላቅ መነዋወጥ ሆነ:: መላእክት ሲያጥኑ በጐ መዓዛ ሸተተ:: ዝማሬ መላእክትም ተሰማ:: ሕዝቡና ዻዻሱም በቅዱስ እስጢፋኖስ ፊት ሰግደው: በታላቅ ዝማሬና በሐሴት ዐጽሙን ከዚያ አውጥተው: በጽርሐ ጽዮን [ በተቀደሰችው ቤት ] አኖሩት::

- እለ እስክንድሮስ የተባለ ደግ ሰውም ቤተ ክርስቲያን አንጾለት ወደዚያ አገቡት:: ከ፭ ዓመታት በኋላም እለ እስክንድሮስ ሲያርፍ በሳጥን አድርገው በቅዱሱ ጐን ስለ ፍቅሩ አኖሩት::ሚስቱ ወደ ሃገሯ ቁስጥንጥንያ ስትመለስ የባሏን ሥጋ መስሏት የቅዱስ እስጢፋኖስን ቅዱስ ሥጋ በመርከብ ጭና ወሰደችው:: መንገድ ላይ ከሳጥኑ ውስጥ ዝማሬ ሰምታ ብታየው ያመጣችው የቅዱሱን ሥጋ ነው:: እጅግ ደስ አላት: አምላክ ለዚህ አድሏታልና::

- እርሷም ወስዳ ለታላቁ ንጉሥ ቅዱስ ቆስጠንጢኖስ አስረከበች:: በከተማውም ታላቅ ሐሴት ተደረገ::ሥጋውን ሊያኖሩት በበቅሎ ጭነው ሲወስዱትም በቅሎዋ በሰው ልሳን ተናግራ ማረፊያውን አሳወቀች:: በዚያም ላይ ትልቅ ቤተ ክርስቲያን ታንጾለታል:: ቅዱስ እስጢፋኖስ ሲመቱ ጥቅምት ፲፯ [ 17 ] ፤ ዕረፍቱ ጥር ፩ [ 1] ፤ ፍልሠቱ ደግሞ መስከረም ፲፭ [ 15 ] ቀን ነው::


🕊  †  ሰማዕታተ አክሚም  †   🕊

- በቤተ ክርስቲያን የሐዲስ ኪዳን ታሪክ አሰቃቂ ጭፍጨፋ ከተካሔደባቸው አካባቢዎች አንዷ ሃገረ አክሚም ናት:: አክሚም ማለት የቀድሞ የግብጽ አውራጃ ናት:: በተለይ በ፫ኛው መቶ ክ ዘመን በርካታ ክርስቲያኖች በፍቅር ይኖሩባት ነበር::

- በከተማዋ ውስጥ የሚኖሩ ክርስቲያኖች ጥቡዓን: ታማኞች:ሥጋውን ደሙን የሚቀበሉና ዘወትር ቅዱስ ቃሉን ለመስማት የሚተጉ ነበሩ:: ለዚህም ደግሞ ከሊቀ ዻዻሱ አባ ብኑድያስ ጀምሮ ካህናቱ : ዲያቆናቱ : ንፍቅ ዲያቆናቱ : መጋቢዎቹ: አናጉንስጢሶቹ [ አንባቢዎቹ ] : መምሕራኑ : መሣፍንቱም ሳይቀር ለክርስቶስ ፍቅር የተጉ መሆናቸው አስተዋጽኦ ነበረው:: በተለይ ግን ፪ ወንድማማቾች የነበራቸው ቅድስና ብዙዎችን ስቧል:: እኒህ ቅዱሳን ዲዮስቆሮስና ሰከላብዮስ ይባላሉ::

- ከባለ ጸጋና ባለ ስልጣን ቤተሰብ ቢወለዱም ክርስትናቸው አልቀዘቀዘም:: የወጣትነት ስሜት ሳያሸንፋቸውም ወደ በርሃ ተጓዙ::

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

08 Jan, 19:41


- በዚያም በቅድስና ኑረው ለክህነት ማዕረግ በቅተዋል:: ቅዱሳኑ በገዳም ሳሉም መድኃኒታችን ክርስቶስ ተገልጦ "ወደ ትውልድ ሃገራችሁ አክሚም ተመለሱ:: ክብረ ሰማዕታት ይጠብቃቹሃል" አላቸው:: እነርሱም ደስ እያላቸው በፍጥነት ወደ አክሚም ወጡ::በዚያ ሰሞን የጌና ጾም ተፈጽሞ የአክሚም ክርስቲያኖች ለበዓለ ልደት ዝግጅት ሲያደርጉ በጠላት ሠራዊት ተከበቡ::ይህ ሠራዊት የተላከው ከርጉም ዲዮቅልጢያኖስ ሲሆን መሪው ደግሞ አርያኖስ ነው:: ዋናው ተልዕኮው ክርስቲያኖችን ለጣዖት ማሰገድ: እንቢ ካሉ ደግሞ መግደል ነው:: ክርስቲያኖቹ መከበባቸውን እያወቁ አልፈሩም::

- ታኅሳስ ፳፱ ቀንም ሁሉም የከተማዋ ክርስቲያኖች ወደ ቤተ ክርስቲያን ተሰበሰቡ:: በዚያም ሊቀ ዻዻሱ ሥርዓተ ቅዳሴን አደረሱ::

ሁሉም በተመስጦ ይጸልዩ ነበርና የክብር ባለቤት ክርስቶስ በገሃድ ተገለጠላቸው:: በዓይናቸው እያዩም ሥጋ ወደሙን አቀበላቸው:: ቅዳሴው ሲጠናቀቅ ግን አርያኖስና ሠራዊቱ ደርሰው ሁሉንም ክርስቲያኖች ያዛቸው::

- ክርስቶስን ክደው ከመገደል እንዲድኑ ተጠየቁ:: እነርሱ ግን በአንድ ድምጽ " አይሆንም " አሉ:: በዚያን ጊዜ ወታደሮቹ በክርስቲያኖች አንገት ላይ በሰይፍ ይጫወቱ ያዙ:: በተራ አሰልፈው ዻዻሱን : ካህናቱን : ዲያቆናቱን : አንባቢዎችን : መሣፍንቱን ሳይጨምር ከ፲፮ ሺህ [ 16,000 ] በላይ ክርስቲያኖች ደማቸው ፈሰሰ:: የቤተ ክርስቲያኑ ቅጥር ሞልቶ ደም ወደ ውጭ ፳ ክንድ ያህል ፈሰሰ::

በክርስቲያኖች ላይ ግፍ ተፈጸመ::አካባቢውም ያለ ወሬ ነጋሪ ቀረ:: ግድያው ለ፫ ቀናት ቀጥሎ ጥር ፩ አንድ ቀን ቅዱሳን ዲዮስቆሮስና ሰከላብዮስ ሲገደሉ ተጠናቀቀ::

† አምላከ ሰማዕታት ፍቅረ ሃይማኖታቸውን ያሳድርብን:: ከበረከታቸውም ይክፈለን:: †

🕊

[  † ጥር ፩ [ 1 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት  ]

፩. ቅዱስ እስጢፋኖስ ቀዳሜ ሰማዕት [ ሊቀ ዲያቆናት ]
፪. ቅዱሳን ሰማዕታተ አክሚም
፫. ቅዱሳን ዲዮስቆሮስ ወሰከላብዮስ
፬. ቅዱስ ለውንድዮስ ሰማዕት
፭. አባ መቃርስ ሊቀ ዻዻሳት

[  † ወርኀዊ የቅዱሳን በዓላት  ]

፩. ልደታ ለማርያም ድንግል እግዝእትነ
፪. ቅዱሳን ኢያቄም ወሐና
፫. ቅዱስ ራጉኤል ሊቀ መላዕክት
፬. ቅዱስ በርተሎሜዎስ ሐዋርያ
፭. ቅዱስ ሚልኪ ትሩፈ ምግባር

" እስጢፋኖስም ጸጋንና ኃይልን ተሞልቶ በሕዝቡ መካከል ድንቅንና ታላቅ ምልክትን ያደርግ ነበር . . . አንዳንዶቹ ተነስተው እስጢፋኖስን ይከራከሩት ነበር:: ይናገርበት የነበረውንም ጥበብና መንፈስ ይቃወሙ ዘንድ አልቻሉም:: በዚያን ጊዜ በሙሴ ላይ: በእግዚአብሔርም ላይ የስድብን ነገር ሲናገር ሰምተነዋል የሚሉ ሰዎችን አስነሱ . . . በሸንጐም የተቀመጡት ሁሉ ትኩር ብለው ሲመለከቱት እንደ መልአክ ፊት ሆኖ ፊቱን አዩት::" [ ሐዋ.፮፥፰-፲፭ ]

† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †

[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]


         †              †               †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖                   🕊                    💖

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

08 Jan, 09:02


▶️ Open የሚለውን ንኩ የፈለጋቹትን 📕ኦርቶዶክስሳዊ 📕ቁም ነገር ታገኙበታላችሁ።

1.ጉዞ ወደ እግዚአብሔር.....Open

2.ሕማማት......................Open

3.ቅዱስ አትናቲዎስ...........Open

4.አባቶችህን እወቅ...........Open

5.ሃይማኖተ አበው............Open

7.ትንሿ ቤተክርስቲያን.......Open

8.የብርሃን እናት...............Open

9.ማህሌተ ፅጌ................Open

10.የኤፍራጥስ ወንዝ.........Open

11.ተግባራዊ ክርስትና........Open

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

08 Jan, 07:55


የማንን መዝሙር ማዳመጥ ይፈልጋሉ?👇👇👇

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

08 Jan, 04:30


🕊

[  † እንኩዋን ለቅዱሳን ጻድቃን ወገዳማውያን "አባ ዮሐንስ" : "አባ ዘካርያስ ወአባ ዮሐንስ" ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ †  ]

† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።

---------------------------------------------

🕊  †  አባ ዮሐንስ ዘአስቄጥስ  †  🕊

- ገዳማዊ ሕይወት ጥንቱ ብሉይ ኪዳን ነው:: በቀዳሚነትም በደብር ቅዱስ አካባቢ ይኖሩ የነበሩ ደቂቀ ሴት እንደ ጀመሩት ይታመናል:: ሕይወቱ በጐላ: በተረዳ መንገድ የታየው ግን በታላቁ ጻድቅ ሄኖክ: ከዚያም በቅዱሱ ካህን መልከ ጼዴቅ አማካኝነት ነው::

- ቀጥሎም እነ ቅዱስ ኤልያስ ነቢይ: እነ ኤልሳዕ ደቀ መዝሙሩ ኑረውበታል:: በሐዲስ ኪዳን ደግሞ ሙሉ ሕይወቱን በገዳም [ በበርሃ ] ያሳለፈው መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ቅድሚያውን ይይዛል::

- ለስም አጠራሩ ስግደት ይሁንና መድኃኒታችን ክርስቶስ በገዳመ ቆረንቶስ ለ፵ ቀናት በትሕርምት ኑሮ ገዳማዊ ሕይወትን ቀድሷል: አስተምሯል:: በዘመነ ስብከቱም ያድርባት የነበረችው የደብረ ዘይቷ በዓቱ [ ኤሌዎን ዋሻ ] በራሷ ለዚህ ሕይወት ትልቅ ማሳያ ናት::

- ከጌታ ዕርገት በሁዋላም ክርስቲያኖቹ የዓለም ሁካታ ሲሰለቻቸው: አንድም በንጹሕና በተሸከፈ ልቡና ለፈጣሪያቸው መገዛትን ሲሹ ከከተማ ወጣ እያሉ ይኖሩ እንደ ነበር የታሪክ መዛግብት ያሳያሉ:: አኗኗራቸውም በቡድንም: በነጠላም ሊሆን ይችላል::

- ዋናው ነገር ግን በጾምና በጸሎት መትጋታቸው ነው:: ይሕም ሲያያዝ እስከ ፫ኛው መቶ ክ/ዘመን ደረሰ:: በዚህ ዘመን ግን አባ ዻውሊ የሚባል አንድ ንጹሕ ክርስቲያን ይሕንን ሕይወት ወደ ሌላ ደረጃ ከፍ አደረገው:: ለ፹ [ 80 ] ዓመታት ሰው ሳያይ ተጋድሎ "የባሕታውያን አባት" ተባለ:: ደንብ ያለው ተባሕትዎም ጀመረ::

- ይህ ከሆነ ከ ፳ [ 20 ] ዓመታት በሁዋላ ደግሞ አባ እንጦንስ የሚባሉ ደግ ክርስቲያን ይህንን ገዳማዊ ሕይወት በሌላ መንገድ አጣፈጡት:: በቅዱስ ሚካኤል አመንኩዋሽነት ገዳማዊ ሕይወት በምንኩስና ተቃኘ:: ስለዚህም አባ እንጦንስ የመነኮሳት አባት ተባሉ::

- እርሳቸውም ሕይወቱን ለማስፋፋት ከተለያዩ አሕጉር ደቀ መዛሙርትን እየተቀበሉ አመንኩሰዋል:: ቅዱሳን የአባ እንጦንስ ልጆችም ወደየ ሃገራቸው ተመልሰው: ሕይወቱን በተግባር አሳይተው ገዳማዊነትን አስፋፍተዋል::

- አባ እንጦንስ አባ መቃርስን: አባ መቃርስ አባ ዮሐንስን ወልደዋል:: አባ ዮሐንስም የታላቁ ገዳመ አስቄጥስ አበ ምኔት ሆነው በጸጋ አገልግለዋል:: አስቄጥስ በምድረ ግብጽ የሚገኝ: በስፋቱና ብዙ ቅዱሳንን በማፍራቱ ተወዳዳሪ የሌለው የዓለማችን ቁጥር አንድ ገዳም ነው::

- ሕይወተ ምንኩሰናም ወደ መላው ዓለም የተስፋፋ በዚህ ገዳም መናንያን አማካኝነት ነው:: በዚህ ገዳም ላይ የሚሾሙ አበው ደግሞ በብዛት መንፈስ ቅዱስ ያደረባቸውና አባታቸውን ቅዱስ መቃርስ ታላቁን የመሰሉ ናቸውና ኃላፊነቱ እጅግ ከባድ ነው::

- በ፭ኛው መቶ ክ/ዘመን በምድረ ግብጽ ተወልደው ያደጉት አባ ዮሐንስ ከመነኑባት ዕለት ጀምረው በፍጹም ተጸምዶና ተጋድሎ ለፈጣሪያቸው ስለ ተገዙ የታላቁ ገዳም አበ ምኔት ሊሆኑ ተገባቸው::

- በአበ ምኔትነት ዘመናቸውም መንጋውን ይጠብቁ ዘንድ ብዙ ደከሙ:: በተለይ ቅዱስ ቃሉን ያስተምሩ ዘንድ ተጉ:: ሕይወተ መላእክትንም ያሳዩ ዘንድ በቃል ብቻ ያይደለ በተግባር ሆነው ከመንፈሳዊ አብራካቸው ብዙ ቅዱሳንን ወለዱ::

- ከዋክብቱ አባ ገዐርጊ : አባ አብርሃም : አባ ሚናስ : አባ ዘካርያስ . . . የአባ ዮሐንስ ፍሬዎች ናቸውና:: ጻድቁ በዘመናቸው ብዙ ተአምራትን ሠርተዋል:: ከዕረፍታቸው በሁዋላ እንኩዋ መግነዛቸውና የልብሳቸው እራፊ ብዙ ድውያንን ፈውሷል::

- አንድ ጊዜም ለልጆቻቸው መነኮሳት ቤዛ ሆነው በበርበር [ አረማውያን ] ተማርከዋል:: በዚያም ክፉዎች ባሪያ ቢያደርጉዋቸው እግዚአብሔር ድንቅን ሠርቶ ወደ ገዳማቸው መልሷቸዋል:: ከብዙ ተጋድሎ በሁዋላም በ90 ዓመታቸው በዚህች ቀን ዐርፈው በበዓታቸው ተቀብረዋል::


🕊  † አባ ዘካርያስ ገዳማዊ  †  🕊

- ይሕም ቅዱስ የተነሳው በዚያው በዘመነ ጻድቃን ነው:: ምንም ክርስቲያን ቢሆንም በቀደመ ሕይወቱ ገንዘብ የሚጥመው ነጋዴ ነበር:: በንግድ ሥራውም ሃብታም መሆን ችሎ እንደ ነበር ዜና ሕይወቱ ይናገራል::

- እግዚአብሔር ሁሉም የሰው ልጆች ወደ መንግስተ ሰማያት ቢገቡ መልካም ፈቃዱ ነው:: ያ ብቻ አይደለም:: ለእያንዳንዱ ሰው የድኅነት ጥሪን በተለያየ መንገድ ያቀርብለታል:: ድምጹን ለሰማ ወደ ወንጌል ወደብ ያደርሰዋል::

- አንዳንዴ "እንቢ" ስንለው እንደ በጐ አባትነቱ በተግሣጹ ሊጠራንም ይችላል:: ተግሣጹም በደዌ: በአደጋና በመሰል መንገዶች ሊሆን ይችላል:: ዋናው ቁም ነገር ግን ጊዜው ሳያልፍብን: ቀኑም ሳይመሽብን ድምጹን መስማት: ለቃሉ መታዘዝ: ጥሪውንና ተግሣጹን አለማቃለል ነው::

- አባ ዘካርያስም የቅድስና ሕይወት ጥሪ የደረሰው ለሥጋ ገበያ ሲታትር ነበር:: አንድ ቀን ንብረቱን ይዞ ለንግድ መንገድ ላይ ሳለ ሽፍቶች ያዙት:: ሊያርዱት አጋድመውት ሳለ ግን የገዳመ ዻኩሚስ አበ ምኔት በሥፍራው ነበርና ጮኸባቸው::

- ቅዱሱ አበ ምኔት አካሉ በገድል ያለቀ ቢሆንም ድምጹ እንደ ነጐድጉዋድ ሲመጣ ገዳዮቹ ደንግጠው በረገጉ:: ዘካርያስም ከሞት ተረፈ:: እንደ ገና ሃብቱን ይዞ ወደ ከተማ ሲገባ በሃገረ ገዢው ተይዞ ሞት ተፈረደበት:: ከገንዘቡ መብዛት የተነሳ ዘራፊ መስሏቸው ነበርና:: በዚህ ጊዜም እግዚአብሔር በመኮንኑ ልብ ርሕራሔን ጨምሮ አዳነው::

- በዚያች ሌሊት ግን ነገሮችን ያስተዋለው ዘካርያስ የተፈጠሩት አጋጣሚወች የፈጣሪው ጥሪ እንደ ሆኑ አስተዋለ:: ወዲያውም ለዓይነ ሥጋ የሚያሳሳውን ያን ሁሉ ንብረቱን መጽውቶ በርሃ ገባ:: በደብረ አባ ዻኩሚስም መንኩሶ በዓት ወሰነ::

- ከዚያች ቀን ጀምሮም በፍጹም አምልኮ: በጾምና በጸሎት እግዚአብሔርን እያገለገለ ከርኩሳን መናፍስት ጋር ታገለ:: በእግሩም ወደ ኢየሩሳሌም ተጉዞ ቅዱሳት መካናትን ተሳለመ:: አንድ ጊዜም ሰይጣን ሰው መስሎ "አባትህ ሳልሞት ልየው እያለህ ነው" አለው:: ውስጡ ግን ፈቃደ ሥላሴ ነበረበትና "እሺ" ብሎ ሒዶ: አባቱን ቀብሮ ተመልሷል::

- ቅዱስ አባ ዘካርያስ ከብቃቱ የተነሳ የሚኖረው ከግሩማን አራዊት ጋር ነበር:: ሁሉንም አራዊትም ይመግባቸው ነበር:: በተለይ ደግሞ ዘንዶዎች ሰውን እንዳይጐዱ አዝዞ እርሱ ይመግባቸው ነበር:: የተጋድሎ ዘመኖቹን ከፈጸመ በሁዋላም በዚህች ቀን በክብር ዐርፏል::


🕊  †  አባ ዮሐንስ ብጹዕ  †  🕊

- ይህም ቅዱስ በተመሳሳይ የዘመነ ጻድቃን ቅዱሳን ፍሬ ነው:: "ኢትርአይ ገጻ : ወኢትስማዕ ድምጻ" በሚለው ሕገ ተባሕትዎ ለ40 ዓመታት ተወስኖ ኑሯል::

- ይህም ማለት አንድ ወንድ ከመነነ በሁዋላ ሴቶችን እንዲያይና ከእነርሱም ጋር እንዲያወራ አይፈቀድለትም:: ሴትም ብትመንን ሕጉ ያው ነው:: [ ዛሬ እየተደረገ ያለውን ግን ፈጣሪ ይመርምረው ]

- አባ ዮሐንስ ብጹዕም እንዲህ ባለ ፈሊጥ: ማለትም በጾምና በጸሎት: ከዓለም ተለይቶ: ከሴት ርቆ: ንጽሕ ጠብቆ ሲኖር አረጀ:: በጊዜው በከተማ የሚኖር አንድ መስፍን ወዳጅ ነበረው:: ይህ መስፍን ዘወትር ወደ ጻድቁ እየመጣ ይባረካል::

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

08 Jan, 04:30


- ሚስቱ ግን በረከቱን ሽታ ልታየው ብትሞክርም አልተሳካም:: ሕገ ምናኔ አይፈቅድምና:: በዚህ ነገር ፈጽማ ማዘኗን በጸጋ ያወቀው አባ ዮሐንስ ግን በራዕይ ወደ እርሷ መጣ:: "ሚ ሊተ ወለኪ ብእሲቶ - አንቺ ሆይ! ለምን ካላየሁህ እያልሽ ትዘበዝቢኛለሽ? እኔ ነቢይ ወይ ጻድቅ አይደለሁ" ብሏት ባርኯ ተሠወራት:: እርሷም ደስ ብሏት ለባሏ ነገረችው:: ባሏ ወደ ጻድቁ ሲሔድም ገና ሳይነጋገሩአባ ዮሐንስ ሳቅ ብሎ "ሚስትህ ደስ አላት አይደል?" ብሎታል:: ጻድቁ በ፺ [ 90 ] ዓመቱ በዚህች ቀን ዐርፎ ተቀብሯል::

አምላከ ጻድቃን ቅዱሳን ስለ ወዳጆቹ በጐ ምኞታችንን ይፈጽምልን:: ከበረከታቸውም ያድለን::

🕊

[  † ታሕሳስ ፴ [ 30 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት   ]

፩. አባ ዮሐንስ አበ ምኔት
፪. አባ ዘካርያስ ገዳማዊ
፫. አባ ዮሐንስ ብጹዕ
፬. ፻፵፬ ሺህ "144 ሺ" ሕጻናት [ ሔሮድስ የገደላቸው ]

[   † ወርኀዊ በዓላት   ]

፩. ቅዱስ ማርቆስ ሐዋርያ
፪. ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቀ መለኮት
፫. ቅዱስ ጐርጐርዮስ ነባቤ መለኮት
፬. ቅድስት ሶፍያ ሰማዕት
፭. አባ ሣሉሲ ክቡር ጻድቅ

" ስለዚህ የልቡናችሁን ወገብ ታጥቃችሁና በመጠን ኑራችሁ : ኢየሱስ ክርስቶስ ሲገለጥ የምታገኙትን ጸጋ ፈጽማችሁ ተስፋ አድርጉ:: እንደሚታዘዙ ልጆች ባለ ማወቃችሁ አስቀድሞ የኖራችሁበትን ምኞት አትከተሉ:: ዳሩ ግን 'እኔ ቅዱስ ነኝና ቅዱሳን ሁኑ' ተብሎ ስለ ተጻፈ የጠራችሁ ቅዱስ እንደ ሆነ እናንተ ደግሞ በኑሯችሁ ሁሉ ቅዱሳን ሁኑ::" [፩ዼጥ.፩፥፲፫]

† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †

[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]


         †              †               †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖                   🕊                    💖

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

07 Jan, 03:52


- በ፲፪ኛው መቶ ክ/ዘመን መጨረሻ ላይ በሃገራችን የነገሠው ቅዱስ ላሊበላ :-

- በብሥራተ መልአክ ተወልዷል :
- ቅዱሳት መጻሕፍትን ገና በልጅነቱ አጥንቷል :
- የንጉሥ ዘር ቢሆንም በጾምና ጸሎት : በትሕርምት አድጉዋል::

- በወንድሙ ቢገረፍም ቂም አልነበረውም:
- ስለ ወዳጆቹ ፍቅር መርዝ ጠጥቷል:
- በዙፋን ላይ የኢትዮዽያ ንጉሥ ሆኖ ቢቀመጥም እርሱስ አኗኗሩ ገዳማዊ ነበር:
- ከተባረከች ሚስቱ ቅድስት መስቀል ክብራ ጋር አንዲት ማዕድ ብቻ በቀን ይቀምሱ ነበር:: ለዛውም ለምለሙን ለነዳያን ሰጥተው እነርሱ የሚበሉት የእንጀራውን ቅርፍት [ ጠርዝ ] ብቻ ነበር::

- በአካለ ሥጋ ወደ ሰማያት ተነጥቆ ብዙ ምሥጢራትን አይቷል :
- በምሳሌውም ሃገረ ሮሃን [ ላስታን ] ገንብቷል:
- ዛሬም ድረስ ምስጢር የሆኑት ፍልፍል አብያተ መቃድስ የእጆቹ ሥራዎች ናቸው::

- ሥራውን ከፈጸመ በሁዋላ መንግሥቱን ለቅዱስ ነአኩቶ ለአብ አውርሶ : በመንኖ ጥሪትና በቅድስና ኑሮ አርፏል:: ጌታችን ስምህን ያከበረ : ዝክርህን የዘከረ: ከቤትህ ያደረውን : ከርስተ መንግስተ ሰማያት አካፍለዋለሁ ሲል ቃል ኪዳን ገብቶለታል:: ይህቺ ዕለት ቅዱሱ ንጉሥ የተወለደባት ናት::

- እኛን ስለ ወደደ ሰው የሆነ ጌታ ፍቅሩን ይሳልብን:: ከድንግል እናቱና ከልደቱ በረከትም ያሣትፈን::

🕊

ታሕሳስ ፳፱ [ 29 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

፩. ልደተ ክርስቶስ ስቡሕ
፪. ታኦዶኮስ [ ድንግል ማርያም ]
፫. ቅዱስ ኢያሱ ነቢይ [ ልደቱ ]
፬. ቅዱስ ላሊበላ [ ልደቱ ]
፭. አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ [ ልደታቸው ]
፮. ጻድቅ አቃርዮስ [ ንጉሠ ሮሃ ]
፯. ቅዱስ ቆሪል ገመላዊ
፰. ሰብአ ሰገል
፱. ዮሴፍና ሰሎሜ
፲. ቅዱሳን ሰማዕታተ አክሚም

ወርኀዊ በዓላት

፩. ቅዱስ ዼጥሮስ ተፍጻሜተ ሰማዕት
፪. ቅዱስ ማርቆስ ዘቶርማቅ
፫. ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ ኢትዮዽያዊት
፬. ቅዱስ ዘርዐ ክርስቶስ
፭. ቅድስት አርሴማ ድንግል

" እነሆ ለሕዝቡ ሁሉ የሚሆን ታላቅ ደስታ የምሥራች እነግራቹሃለሁና አትፍሩ:: ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት: እርሱም ክርስቶስ: ጌታ የሆነ ተወልዶላቹሃልና:: " [ ሉቃ.፪፥፲ ]

† ወስብሐት ለእግዚአብሔር  †


[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]

            †       †       †
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬

💖                🕊                   💖

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

07 Jan, 03:52


🕊

✞ እንኩዋን ለዓለም ሁሉ ጌታ "ኢየሱስ ክርስቶስ" ዓመታዊ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞

† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።

---------------------------------------------

🕊  †  ልደተ ክርስቶስ †  🕊

ዓለማትን : ዘመናትን : ፍጥረታትን ሁሉ የፈጠረ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ : ወልደ አምላክ ነው:: የእግዚአብሔር አብ የባሕርይ ልጁ ሲሆን ራሱም እግዚአብሔር ነው:: በባሕርየ ሥላሴ መበላለጥ የለምና ወልድ ክርስቶስ ከአብና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ትክክል ነው እንጂ አይበልጥምም : አያንስምም::

- እርሱ ቅድመ ዓለም የነበረ : ማዕከለ ዓለም ያለና ዓለምን አሳልፎ የሚኖር ጌታ ነው:: ቀዳማዊና ደኃራዊው : አልፋና ኦሜጋ እርሱ ነው:: [ዮሐ.፩፥፩ , ራዕ.፩ ] ሁሉ በእጁ የተያዘ ነው::

- እርሱ እውነተኛ አምላክ [ ሮሜ.፱፥፭ ] : የዘለዓለም አባት : የሰላምም አለቃ ነው:: [ ኢሳ.፱፥፮ ] ቅድመ ዓለም ሲሠለስ : ሲቀደስ ኑሮ ይህንን ዓለም ፈጠረ:: እርሱ ሁሉን ያስገኛል እንጂ ለእርሱ አስገኝ የለውም::

" አንድ ክርስቲያን ከሁሉ አስቀድሞ ሊያውቀው የሚገባ መሠረተ እምነት ይሔው ነው !! "

- መድኃኒታችን ክርስቶስን በዚህ መንገድ የማያምንና የማያመልክ ሁሉ እርሱ ክርስቲያን አይደለም:: ምንም ሥጋችንን ተዋሕዶ ብዙ የትሕትና ሥራዎችን ቢሠራም : ቢሰቀል : ቢሞትም እርሱ እግዚአብሔር ነውና ፍጹም አምላክ ፍጹምም ሰው ብለን ልናመልከው ይገባል::

- እንደ አርዮስ: ንስጥሮስና ልዮን የማይገቡ ነገሮችን መናገር ጐዳናው የሞት: መዳረሻውም ገሃነመ እሳት ነው:: እንኩዋን የክብር ባለቤት መድኅን ክርስቶስ ላይ በፍጡር ላይ እንኩዋ የማይገባ ነገርን የተናገረ ሁሉ የገሃነም ፍርድ አለበት::

" ለእርሱ የዓለም ፈጣሪ : ጌታና ቤዛ ለሆነው መድኅን ኢየሱስ ክርስቶስ ለዘለዓለም ምስጋና : ጌትነት : ውዳሴና አምልኮ ይሁን !! "

- እግዚአብሔር አዳምን በ፯ ሃብታት አክብሮ በገነት ቢያኖረው "አትብላ" የተባለውን ዕፀ በለስ በላ:: በዚህም ከፈጣሪው ተጣልቶ : በሞተ ሥጋ ሞተ ነፍስ : በርደተ መቃብር ርደተ ገሃነም ተፈረደበት:: በሁዋላ ግን ንስሃ ስለ ገባ " ከ፭ ቀን ተኩል [ 5,500 ዘመን ] በሁዋላ ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለሁ" የሚል ቃል ኪዳንን ሰጠው::

- ከዚህ በሁዋላ ለ ፭ ሺህ ፭ መቶ [ 5,500 ] ዘመናት ጊዜ ወደ ታች ይቆጠር ጀመር:: ስለ እግዚአብሔር ሰው መሆንና ዓለምን ማዳንም ትንቢት ይነገር : ሱባኤ ይቆጠር : ምሳሌም ይመሰል ገባ::

- ከአዳም እስከ ሙሴ [ ዘመነ አበው ] ምሳሌያት ይበዛሉ:: ከሙሴ እስከ ዳዊት [ ዘመነ መሣፍንት ] ምሳሌያቱ እየጐሉ መጥተዋል:: ከልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት እስከ ቅዱስ ሚልክያስ ድረስ [ በዘመነ ነቢያት / ነገሥት ] ግን ትንቢቶች ስለ ክርስቶስና ስለ ማደሪያ እናቱ እንደ ጐርፍ ፈሰዋል::

- ነቢያትም የመሲህን መምጣት እየጠበቁ በጾም: በጸሎትና በትሕርምት ኑረዋል:: እንባቸውንም አፍሰው ቅድመ እግዚአብሔር ደርሶላቸዋል::


🕊  †  ልደተ ክርስቶስ እምድንግል †  🕊

- "ጊዜው ሲደርስ አንባ ይፈርስ" እንዲሉ አበው መደኃኒታችን የጥልን ግድግዳ ያፈርስ ዘንድ: ከኃጢአትና ከሞት ቁራኝነት ይፈታን ዘንድ: ለሰዎች ቤዛ ይሆን ዘንድ: ትንቢተ ነቢያትን ይፈጽም ዘንድ: በቀጠሮ [ በ ፭ ቀን ተኩል ] ወደዚህ ዓለም መጣ::

- የሰማይና የምድር ጌታ በእንግድነት በመጣ ጊዜም እርሱን ለመቀበል በተገባ የተገኘች ንጽሕት ሙሽራ ድንግል ማርያም ሆነች:: ከእርሷ በቀር ለዚህ ክብር ሊበቃ የሚቻለው ፍጥረት: እንኩዋን ኃጢአት ካደከመው የሰው ልጅ ከንጹሐን መላእክት ወገን አልተገኘም::

- በጊዜውም መልአከ ትፍሥሕት ቅዱስ ገብርኤል መጋቢት ፳፱ [ 29 ] ቀን ወደ ድንግል ወርዶ የአምላክን ሰው የመሆን ዜና ከውዳሴና ከክብር ጋር ነገራት:: [ ሉቃ.፩፥፳፮ ] ድንግልም ለ9 ወራት ከ ፭ ቀናት ሰማይና ምድር የማይችሉትን መለኮትን ተሸከመች::

- ልክ ሙሴ በደብረ ሲና እንዳያት ዕጽ ድንግል ማርያምንም ባሕርየ መለኮቱ አላቃጠላትም:: ስለዚህም ነገር "ወላዲተ አምላክ: ታኦዶኮስ: ንጽሕተ ንጹሐን: ቅድስተ ቅዱሳን: ንግሥተ አርያም: የባሕርያችን መመኪያ . . ." እያልን እንጠራታለን::

- ግሩም ድንቅ ጌታን ጸንሳ ዘጠኝ ወራት እስኪፈጸሙ ድረስ ብዙ ተአምራትን ሠራች:: መላእክተ ብርሃን እየታጠቁ አገለገሏት: አመሰገኗት:: ልጇን አምላክ: እርሷን እመ አምላክ እያሉ ተገዙላት::

- ከዚያም በሮሙ ቄሣር በአውግስጦስ ዘመን ሰው ሁሉ ይቆጠር ዘንድ አዋጅ ወጥቷልና እመ ብርሃን ማርያም ከቅዱሳኑ ዘመዶቿ ዮሴፍና ሰሎሜ ጋር ወደ አባቷ ዳዊት ከተማ ወደ ቤተ ልሔም ሔደች::

- በዚያም ሳሉ የምትወልድበት ጊዜ ቢደርስ በፍጹም ድንግልና እንደ ጸነሰችው ሁሉ በፍጹም ድንግልና ወለደችው:: [ ኢሳ.፯፥፲፬ , ሕዝ.፵፬፥፩ ] ተፈትሖም አላገኛትም:: ልማደ አንስትም አልጐበኛትም:: ምጥም አልነበረባትም::

- ድንግል ማርያም ክርስቶስን በወለደች ጊዜ ልጇ አምላክ: እርሷም የአምላክ እናት መሆኗ ይታወቅ ዘንድ:-

፩. የብርሃን ጐርፍ ፈሰሰ:
፪. ፺፱ [ 99 ] ኙ ነገደ መላእክት ወርደው "ክብር ለእግዚአብሔር በአርያም" እያሉ ዘመሩ:
፫. ትጉሐን እረኞች በቅዱስ ገብርኤል መሪነት መጥተው ክብሩን ተካፈሉ :
፬. በሰማይም ልዩ ኮከብ ድንግልና ልጇ ተስለውበት ዝቅ ብሎ ታየ:
፭. ቅድስት ሰሎሜም በድፍረት የድንግልን ሆድ ዳስሳ እጇ ቢቃጠል እንደ ገና በተአምራት ድኖላታል::

- በጊዜውም በምሥራቅ የፋርስ: የባቢሎንና የሳባ ነገሥት አስቀድሞ ከበለዓም: በሁዋላም ከዠረደሸት በተረዱት መሠረት ኮከቡን በማየታቸው ታጥቀው ተነሱ::

- ከምሥራቅ አፍሪቃና ከእስያም በተመሳሳይ ኮከቡን በማየታቸው ፲፪ ነገሥታት በየግላቸው ፲ ፲ ሺህ ሠራዊትን እየያዙ ድንግልንና ንጉሥ ልጇን ፍለጋ ወጡ::

- ፲፪ቱ ነገሥታት ከነ ሠራዊታቸው ሲሔዱ ስንቃቸው በማለቁ ፱ ነገሥታት ተስፋ ቆርጠው ተመለሱ:: ፫ቱ ግን በፍጹም ጥብዓት ከ፴ሺ ሠራዊት ጋር በኮከብ እየተመሩ ኢየሩሳሌም ደረሱ::

- እነዚህም መሊኩ የኢትዮዽያ [ የሳባ ንጉሥ ተወራጅ ] : በዲዳስፋና መኑሲያ [ ማንቱሲማር ] ደግሞ የፋርስና የባቢሎን ነገሥታት ናቸው:: ወደ ኢየሩሳሌም ሲደርሱም ሔሮድስና ሠራዊቱ ታወኩ::

- እነርሱ ግን የቤተ ልሔምን ዜና ከጠየቁ በሁዋላ በጐል ድንግል ማርያምን : ክርስቶስን : ዮሴፍና ሰሎሜን አገኙ:: ለ፪ ዓመታት እነርሱን ፍለጋ ደክመዋል : ተንከራተዋልና ደስታቸው ወሰን አጣ::

- በእመቤታችንና በልጇ ፊት በደስታ ዘለሉ:: " አንፈርዓጹ ሰብአ ሰገል " እንዲል:: ወርቁን: እጣኑንና ከርቤውንም ገብረው: በግንባራቸው በፊቱ ሰገዱ:: ፫ ጊዜም እየወጡ እየገቡ ቢመለከቱት በኪነ ጥበቡ አንዴ እንደ ሕጻን : በ2ኛው እንደ ወጣት : በ ፫ኛው እንደ አረጋዊ ሆኖ ታይቷቸው ፈጽመው አድንቀዋል::

- ወደ ሃገራቸው ሲመለሱም " ወአስነቀቶሙ ሕብስተ ሰገም " እንዲል የገብስ ዳቦ ጋግራ ድንግል ለሰብአ ሰገል ሰጠቻቸው:: እነርሱም ይህንን እየተመገቡ የ፪ ዓመቱን መንገድ በ፵ ቀን ሲጨርሱት ዳቦው ግን ያ ሁሉ ሺህ ሰው ተመግቦት አላለቀም:: ተአምራትንም ሠርቷል::

" የልደቱ ነገር እንዲሁ ተተርኮ የሚያልቅ አይደለምና ይቆየን:: የከርሞ ሰውም ይበለን:: "


🕊  †  ቅዱስ ላል-ይበላ ንጉሥ †  🕊

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

06 Jan, 16:57


🕊                       

💖   እንኳን ለብርሃነ ልደቱ አደረሳችሁ  💖


[    " ብርሃንሽ መጥቶአልና ፥ የእግዚአብሔርም ክብር ወጥቶልሻልና ተነሺ ፥ አብሪ። "    ]

[ ኢሳ. ፷ ፥ ፩ - ፬ ] ]

💖                    🕊                     💖

❝ የሰማይ ሥርዓት በምድር ላይ ተሠራ። ቤተልሔም ሰማይን መሰለች : ስለ ፀሐይም በቅዱሳን ላይ የሚያበራ ለዘወትርም ጨለማ የማይቃወመው ኅልፈት ጥፋት የሌለበት ዕውነተኛ ፀሐይ በውስጧ ተገኘ።

የብርሃኑም ክበብ መምላትና መጉደልን ስለሚያፈራርቅ በጨረቃ ፈንታ በዕብራይስጥ ማሪሃም የተባለች የድንግልናዋም ምስጋና በሁሉ የመላ ነው። ለዘወትርም የማይጎድል እመቤታችን የተመረፀች ድንግል ማርያም ተገኘች : ስለ ከዋክብትም መላእክተ ብርሃን ታዩ።

ወደዚህ ማኅበር አንድነት እኖር ዘንድ ማን በከፈለኝ : ከመላእክት ጋር እንዳመሰግን : ካዋላጅቱም ጋር እንዳደንቅ : ከእረኞችም ጋር እንዳገለግል።

በረቱን እጅ እነሣ ዘንድ ማን በከፈለኝ : የሙታን ሕይወት የኃጥአንም ንጽሕና : የቅቡፃን ተስፋ የተጨነቁትንም የሚያድን ጌታ ወደተቀመጠበት።

የዓለም ሁሉ መድኃኒት የምትሆን ብላቴና እግሯ የተመላለሰበቱን ምድር እስም ዘንድ ማን በከፈለኝ።

ይቅርታን የምታሰጥ ብላቴና ጥላዋ ይነካኝ ዘንድ ማን በከፈለኝ። የብርሃን ልጅ ወደ ሄደችበት እከተላት ዘንድ ማን በከፈለኝ : የእግሯን ጫማ እሸከም ዘንድ ማን በከፈለኝ። ❞

🕊 አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ  🕊 ]


                †       †       †
†                       †                        †
💖                    🕊                     💖

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

04 Jan, 21:44


" መቶ በግ ያለው ከእነርሱም አንዱ ቢጠፋ ዘጠና ዘጠኙን በበርሃ ትቶ የጠፋውን እስኪያገኘው ድረስ ሊፈልገው የማይሔድ ከእናንተ ማን ነው? ባገኘውም ጊዜ ደስ ብሎት በጫንቃው ይሸከመዋል:: ወደ ቤትም በመጣ ጊዜ ወዳጆቹንና ጐረቤቶቹን በአንድነት ጠርቶ 'የጠፋውን በጌን አግኝቼዋለሁና ከእኔ ጋር ደስ ይበላችሁ' ይላቸዋል:: እላችሁአለሁ: እንዲሁ ንስሃ ከማያስፈልጋቸው ከዘጠና ዘጠኝ ጻድቃን ይልቅ ንስሃ በሚገባ በአንድ ኃጢአተኛ በሰማይ ደስታ ይሆናል::" [ሉቃ.፲፭፥፫-፯]

† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †

[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]


         †              †               †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖                   🕊                    💖

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

04 Jan, 21:44


🕊

[  ✞ እንኩዋን ለሰማዕቱ "አባ አብሳዲ" እና ለጻድቁ "አባ በግዑ" ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞  ]

† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን †

-------------------------------------------

🕊  †  ቅዱስ አባ አብሳዲ  †  🕊

- ቅዱሱን የመሰሉ አባቶች "መስተጋድላን" ይባላሉ በግዕዙ:: ለሃይማኖታቸው እስከ ደም ጠብታና እስከ መጨረሻዋ ህቅታ ድረስ መጋደላቸውን የሚያሳይ ነው:: መጋደል ጐዳናው ብዙ ዓይነት ነው::

- ከራሱ ጋር የሚጋደል አለ:: ከዓለም ጋር የሚጋደልም አለ:: የቅዱሳኑ ተጋድሎ ግን በዋነኝነት ከ፪ አካላት ጋር ነው:: በመጀመሪያ ፍትወታት እኩያትን [ ኃጣውዕን ] ከሚያመጡ አጋንንት ጋር ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ "ሃይማኖቸታችሁን ካዱ: ለጣዖትም ስገዱ" ከሚሉ ከሃድያን ጋር የሚደረግ ትግል ነው::

- በተለይ ፪ ኛው እስከ ሞት የሚያደርስ ውሳኔን ይጠይቃል:: የዚህን ቅዱስ ሕይወት ለመረዳት ግን አንድ ነገርን ልብ እንድትሉልኝ እፈልጋለሁ::

- ያለንበት ዘመን ክርስትና በራድ [ቀዝቃዛ] በመሆኑ የቀደሙ አባቶች የጸና ተጋድሎ አንዳንዴ ግራ ሲያጋባን ተመልክቻለሁ:: ቅዱሳኑ ሁሌም አንድ ነገርን እያሰቡ ይኖራሉ:: ይኼውም በዘመኑ በርካቶቻችን የረሳነው: ወይም ማስታወስ የማንፈልገው ነገር ይመስላል::

- ሰማያዊው አምላክ ከዙፋኑ ወርዶ በተዋሐደው ሥጋ በቃል ሊገለጽ የማይችል መከራን ስለ እኛ ተቀብሏል:: ክርስትና ማለት ቀራንዮን በልብ ውስጥ መሳል ነው:: ፍቅረ መስቀሉን: የጌታንም ውለታ የሚያስብ ማንኛውም ሰው: የትኛውም ዓይነት መከራ ቢመጣበት አይታወክም::

- ቅዱሳኑም የፍቅራቸውና የትእግስታቸው ምሥጢር ይኼው ነው:: ጌታችን "የሚወደኝ ቢኖር የሞቱን መስቀል ተሸክሞ ይከተለኝ" [ማቴ.፲፮፥፲፰] እንዳለው ቅዱሳኑ ይህንን ቃል በቃል ሲፈጽሙት እነሆ እንመለከታለን::


🕊  † ቅዱስ አባ አብሳዲ †  🕊

- ቅዱሱ ሰማዕት ተወልዶ ያደገው በምድረ ግብጽ : በ፫ ኛው መቶ ክ/ዘ ነው:: እንደርሱ በቅድስና ያጌጠ ባልንጀራም ነበረው:: ስሙም ቅዱስ አላኒቆስ ነበር::

- እኒህ ክርስቲያኖች በዚያ የመከራ ዘመን ግራ ቀኝ ሳይሉ ትምሕርተ ቤተ ክርስቲያንን ጠንቅቀው ተምረዋል:: በጐውን ጐዳና አጽንተው በመገኘታቸውም መንፈስ ቅዱስ ፪ቱንም በአንዴ ለእረኝነት ጠራቸው::

- ዽዽስና ከዚህ በፊት እንደ ተመለከትነው እዳ [ኃላፊነት] እንጂ ምድራዊ ክብርን ማጋበሻ መንገድ: ወይም የሥጋ ድሎትን መፍጠሪያ ዙፋን አይደለም:: ያም ሆኖ ምርጫው የመንፈስ ቅዱስ ሲሆን ደስ ያሰኛል::

- በእርግጥም የክርስቶስን መንጋ እንደሚገባ መምራትና በለመለመው የወንጌል መስክ ማሰማራት የሚያስገኘው ክብር በሰማያት ታላቅ ነው:: ያም ቢሆን ግን ከብዙ መከራ በሁዋላ እንጂ እንዲሁ በዋዛ አይደለም:: የእግአብሔር ጸጋውና መንግስቱ ያለ መከራ አትገኝምና::

- ቅዱሳኑ አባ አብሳዲና አባ አላኒቆስም ይህንን ኃላፊነት የተረዱ ነበርና ታጥቀው ሥራቸውን ጀመሩ:: እንደ ሐዋርያት ሥርዓትም ያላመነውን ማሳመን: ያመነውን በሃይማኖቱ ማጽናት: የጸናውን ደግሞ ለምሥጢራተ ቅድሳት [ሥጋ ወደሙ] ማብቃት የዘወትር ተግባራቸው ነበር::

- ቅዱሳኑ በዚህ ተጋድሏቸው ሳሉ ዜናቸው በየቦታው ተሰማ:: ነገር ግን ይህ ዝናቸው የወለደው መከራን ነበር:: በጊዜው አውሬው ዲዮቅልጢያኖስ ክርስቲያኖችን ከዋሉበት አላሳድር: ካደሩበትም አላውል ብሎ ነበር::

- ለክፋቱ እንዲመቸው በየሃገሩ ጨካኝ መኮንኖችን ሾመ:: በምድረ ግብጽም ፪ ገዢዎችን ሲያኖር አንዱ አርያኖስ [በሁዋላ አምኖ ሰማዕት ሆኗል] : ፪ኛው ደግሞ ሔርሜኔዎስ ይባላሉ::

- እነዚህ መኩዋንንት ግብጽን ለ፪ ተካፍለው: በሥራቸው ገዥዎችን ሹመው በግፍ ተግባራቸው ክርስቲያኖችን ይቀጡ ገቡ:: የስቃይ ተራው ደግሞ የ፪ቱ ቅዱሳን [አባ አብሳዲና አባ አላኒቆስ] ነበርና ተከሰሱ::

- ለፍርድ ይቀርቡ ዘንድም አርያኖስ በማዘዙ ወታደሮች መጡ:: ነገሮችን አስቀድሞ የሚያውቀው ቅዱስ አብሳዲም ምንም ስለ ክርስቶስ ለመሞት ቢቸኩልም መንጋውን እንዲሁ ሊበትን ግን አልወደደም::

- ስለዚህም ወታደሮችን "እባካችሁ ሕዝቡን ልሰናበት : አንድ ቀን ታገሱኝ" አላቸው:: ወታደሮቹ ከፊቱ የሚታየው ግርማው ደንቁዋቸው ነበርና ፈቀዱለት:: ቅዱሱም ከሕይወቱ የቀረችውን ፳፬ ሰዓት ይጠቀምባት ዘንድ ምዕመናን ልጆቹን ሁሉ ጠራ::

- ቅዳሴ ቀድሶ : ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ፈትቶ ለሁሉም አቀበላቸው:: [በጊዜው የማይቆርብ ክርስቲያን አልነበረምና]

- ከቅዳሴ መልስም የተፈጠረውን ሁሉ ነግሮ ወደ ክርስቶስ ሊሔድ እንደ ናፈቀ ነገራቸው:: ሊያስቀሩት እንደማይችሉ ሲረዱ ፈጽመው አዘኑ:: እርሱም በቀናችው እምነት እስከ ሞት ድረስ እንዲጸኑ አስተምሯቸው ከባልንጀራው ቅዱስ አላኒቆስ ጋር በወታደሮች እጅ ወደቀ::

- እነርሱም ቅዱሳኑን ወስደው በመኮንኑ አርያኖስ ፊት ለፍርድ አቀረቧቸው:: አርያኖስም የአባ አብሳዲ የፊቱ ግርማ ቢስበው ላለመግደል ወስኖ ሊያባብለው ወሰነ:: "አንተ ክቡር ሰው ነሕና ለንጉሡ ታዘዝ : ለጣዖትንም እጠን" አለው::

- ቅዱስ አላኒቆስ ግን "ክብሬ ክርስቶስ ነውና ፈጣሪየን በምንም ነገር አልለውጠውም" ሲል እቅጩን ነገረው:: እንደማያሳምነው ሲረዳም ከአባ አላኒቆስ ጋር ያሰቃዩአቸው ዘንድ አዘዘ::

- በምስክርነት አደባባይም በመንኮራኩር [አካልን የሚበጣጥስ ተሽከርካሪ ብረት ነው] አበራዩአቸው:: እግዚአብሔር ግን አዳናቸው:: እንደ ገና እሳት አስነድደው እዚያ ውስጥ ጨመሯቸው:: እሳቱም ግን ሊበላቸው አልቻለም::

- በመጨረሻም መኮንኑ አንገታቸው ይሰየፍ ዘንድ አዘዘ:: ከመሰየፋቸው በፊትም ቅዱሳኑ ጸሎትን አደረሱ:: አባ አብሳዲ ነጭ የቅዳሴ ልብሱን ለብሶ: ወደ ሰይፍ ቀረበ:: ወታደሮች ደግሞ ሁለቱን ቅዱሳን እንደታዘዙት ሰየፏቸው:: በክብርም ዐረፉ::


🕊  †  አባ በግዑ ጻድቅ  †  🕊

- እኒህ አባት በመካከለኛው ዘመን የሃገራችን ታሪክ ሰፊ ቦታን ይዘው ይገኛሉ:: ተጋድሏቸውን የፈጸሙት በደብረ ሐይቅ ነው:: ጻድቁ ብዙ ጊዜ የሁዋለኛው ዘመን ሙሴ ጸሊም ይባላሉ:: ብዙ የሕወታቸው ጐዳና ተመሳሳይ ነው::

- ልክ ቅዱስ ሙሴ ጸሊም ከኃጢአት ከሽፍትነት ሕይወት እንደ መጣው ሁሉ አባ በግዑም አስቸጋሪ ሰው እንደ ነበሩ ይነገርላቸዋል:: ከዚያ የከፋ የኃጢአት ኑሮ እግዚአብሔር ሲጠራቸው ግን ክሳደ ልቡናቸውን አላደነደኑም:: "እሺ" ብለው ንስሃ ገቡ እንጂ::

- ከዚያም በደብረ ሐይቅ [ወሎ] በፍጹም ተጋድሎ ኑረዋል:: ያዩ ሁሉም ፍጹም ያደንቁ ነበር:: ስትበላ: ስትጠጣ የኖረችውን ሰውነት ራሳቸውን ውሃ ለዘመናት በመከልከል ቀጥተዋታል:: ስለዚህም "ውሃ የማይጠጣው አባት" ይባሉም ነበር:: ጻድቁ ሲያርፉ ፈጣሪያቸው አክብሯቸዋል::

- አምላከ አበው ቅዱሳን አሠረ ፍኖታቸውን ይግለጽልን:: ከበረከታቸውም ያድለን::

🕊

[  † ታሕሳስ ፳፯ [ 27 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት   ]

፩. ቅዱስ አብሳዲ ሰማዕት
፪. አባ አላኒቆስ ሰማዕት
፫. አባ በግዑ ጻድቅ
፬. አባ ፊልዾስ

[   †  ወርኀዊ በዓላት   ]

፩. ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ
፪. አቡነ መብዓ ጽዮን ጻድቅ
፫. ቅዱስ መቃርስ [የመነኮሳት ሁሉ አለቃ]
፬. ቅዱስ ያዕቆብ ዘግሙድ
፭. ቅዱስ ገላውዴዎስ ሰማዕት [ንጉሠ ኢትዮዽያ]
፮. ቅዱስ ቢፋሞን ጻድቅና ሰማዕት
፯. ማር ቅዱስ ፊቅጦር ሰማዕት

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

04 Jan, 20:17


ቢሂለ አበው ( አባቶች ምን አሉ )

ልጄ ሆይ ማናቸውንም ነገር በምትፈፅምበት ጊዜ ሥራህን በፀሎት ጀምር። የምትሰራቸውን ሥራዎች ሁሉ በትምህርተ መስቀል ባርካቸው።

በምትበላም፣ በምትጠጣም ጊዜ፣ በምትተኛም፣ በምትነቃም ጊዜ፣ በቤት ውስጥም ሳለህ ይሁን በጎዳና፣ ማማተብን አትዘንጋ። የጌታህን ስቅለት አስታውሶ ከክፋት የሚጠብቅህ ይህን የመሰለ ጠባቂ ከቶ አታገኝም።

እርሱ ለምታደርጋቸው ድርጊቶችህ ሁሉ እንደ ግንብ ነው (ማስተዋልን ይሰጥኻል)። ማማተብን በስርዓት ይፈፅሙት ዘንድ የኢየሱስ ክርስቶስ ስቅለት ሁሌም በፊታቸው ይስሉ ዘንድ ለልጆችህ በጥንቃቄ አስተምራቸው።

#ሊቁ_ቅዱስ_ኤፍሬም_ሶርያዊ

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

04 Jan, 16:50


                       †                       

  [   🕊  ነ ገ ረ    ል ደ ቱ    🕊   ]  

🍒▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬🍒               

[     ነገረ ልደቱ በሊቃውንት !      ]
             

🕊                        💖                      🕊

❝ እሳትን ለብሷል ፣ በመጠቅለያ ጨርቅም ተጠቅልሏል ግን ደግሞ ከመታወቅ በላይ ነው  በዙፋን ላይ ተቀምጧል እንዲኹም በግርግም ተኝቷል ፤ ግን ደግሞ አይመረመርም በኪሩቤል ዠርባ ላይ ተቀምጧል እንዲኹም ጉልበቶች ተሸክመውታል ፤ ... እርሱን ይረዳው ያውቀው ዘንድ ማን ይችላል ❞

[ ቅዱስ ያዕቆብ ዘስሩግ ]

🕊

❝ ሰው ሆይ ! ሥጋ ያልነበረ እርሱ ለአንተ ብሎ ሥጋን ተዋሐደ ፤ ሰው ሆይ ! በመለኮቱ አይዳሠሥ የነበረ ነፍስን ሥጋን የተዋሐደ ቃል ለአንተ ብሎ ተዳሠሠ። በመለኮቱ ጥንት የሌለው እርሱ ጥንት ያለውን ፍጹም ሥጋ ተዋሐደ። ... እርሱ በድንግል ማኅፀን አደረ ሰማይን በደመና የሚሸፍን እርሱ በጨርቅ ተጠቀለለ ፤ የነገሥታት ንጉሥ በበረት ተጣለ። ❞

[ ቅዱስ አጢፎስ ዘቁስጥንጥንያ ]


🕊                        💖                      🕊
                             👇

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

04 Jan, 16:38


https://vm.tiktok.com/ZMkU2TTTS/

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

04 Jan, 12:07


                       †                        

🕊 በመጠቅለያ ጨርቅም ተጠቅልሏል 🕊 

💖

[   ቅዱሳን አባቶቻችን ስለ ጌታችን ልደት እንዲህ አሉ  ]

💖                     🕊                      💖

❝ የእግዚአብሔር የባሕርይ ልጅ ሲሆን ሰው ይባላል። ዳግመኛም የአዳም ልጅ ይባላል። ሰማያዊ ሲሆን በፈቃዱ ምድራዊ ሆነ። ❞

[ ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ ]


❝ እሳትን ለብሷል ፣ በመጠቅለያ ጨርቅም ተጠቅልሏል ግን ደግሞ ከመታወቅ በላይ ነው  በዙፋን ላይ ተቀምጧል እንዲኹም በግርግም ተኝቷል ፤ ግን ደግሞ አይመረመርም በኪሩቤል ዠርባ ላይ ተቀምጧል እንዲኹም ጉልበቶች ተሸክመውታል ፤ ... እርሱን ይረዳው ያውቀው ዘንድ ማን ይችላል ❞

[ ቅዱስ ያዕቆብ ዘስሩግ ]


❝ በመለኮቱ ጥንት በሌለው አስቀድሞ ዓለም ሳይፈጠር በመለኮቱ ከአብ በተወለደ ዳግመኛም እኛን ለማዳን በኋላ ዘመን ከቅድስት ድንግል ማርያም በተወለደ በእግዚአብሔር ልጅ እናምናለን። የቀኑ ቀጠሮ ሲደርስ እግዚአብሔር ልጁን ላከ ከድንግልም ተወለደ ብሎ ብፁዕ ሐዋርያ ቅዱስ ጳውሎስ እንዳስተማረን። ❞

[ ቅዱስ አትናቴዎስ ዘእስክንድርያ ]


❝ ሰው ሆይ ! ሥጋ ያልነበረ እርሱ ለአንተ ብሎ ሥጋን ተዋሐደ ፤ ሰው ሆይ ! በመለኮቱ አይዳሠሥ የነበረ ነፍስን ሥጋን የተዋሐደ ቃል ለአንተ ብሎ ተዳሠሠ። በመለኮቱ ጥንት የሌለው እርሱ ጥንት ያለውን ፍጹም ሥጋ ተዋሐደ። ... እርሱ በድንግል ማኅፀን አደረ ሰማይን በደመና የሚሸፍን እርሱ በጨርቅ ተጠቀለለ ፤ የነገሥታት ንጉሥ በበረት ተጣለ። ❞

[ ቅዱስ አጢፎስ ዘቁስጥንጥንያ ]


❝ የከበሩ መጻሕፍት ክርስቶስ ሰው እንደሆነ እንደሚነግሩን አምላክም እንደሆነ እንዲሁ እነርሱ ይነግሩናል። ግዙፍ እንደሆነ እንደሚነግሩን ረቂቅም እንደሆነ ፤ የእግዚአብሔር ቃልም እንደሆነ እርሱ ራሱም እግዚአብሔር እንደሆነ እንዲሁ ይነግሩናል። ከንጽሕት ድንግል ማርያም በኋላ ዘመን እንደተወለደ እንደሚነግሩን ቀድሞም ከአብ እንደተወለደ እንዲሁ ይነግሩናል። ❞

[ ቅዱስ ሄሬኔዎስ ዘኤዶም ]


†                        †                         †
💖                     🕊                      💖

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

02 Jan, 17:04


                       †                        

🕊  አስደናቂው የልደት ምስጢር  🕊 

💖

[  የአዳኛችንን በሥጋ መወለድ በተመለከተ በልደቱ ውስጥ ያለው አስደናቂ እና ጥልቅ መገለጥ  ]

💖                     🕊                     💖

❝ ምድርና በውስጧ ያለው ኹሉ በዚኽ ቀን ደስ ይበላቸው። በአሜኬላም ፈንታ ከአንተ ልደት በረከትን ታብቅል [ዘፍ.፫፥፲፰]። የሰው ዘር ራስ የኾነው አዳም በዚኽ ቀን ደስ ይበለው። ምክንያቱም ልክ እንደተመኘው መለኮትነትን ከልደትኽ ተቀብሏልና [ዘፍ.፫፥፭]።

በዚኽ ቀን ሔዋን ከአዳም ይልቅ ታመስግን። ምክንያቱም የመከራዋን ስቃይ የሚያስወግደው ሕፃን ከርሷ ወጥቶ አብርቷልና። [ዘፍ.፫፥፲፮]

በዚኽ ቀን ገነቱ ከዛፎቹ ጋር ሐሤት ያድርግ ምክንያቱም የተባረረው ወራሽ ባንተ በኩል ወደ መኖሪያው ወደ ዔደን [ ገነት ] ተመልሷልና። [ዘፍ.፫፥፳፫-፳፬]

በዚኽ ቀን በየምድር ዳርቻው የሚኖሩ አሕዛብ ምስጋና ይስጡ ፤ ምክንያቱም በተለያየ የአምልኮት ዐይነት ኹሉ ተበታትነው ነበር ፤ አኹን ግን ባንተ ተሰበሰቡ። [ዘፍ.፲፩፥፱]

በዚኽ ቀን ሰማይ ሐሤት ታድርግ ምድርም ደስ ይበላት። ምክንያቱም ጌታቸው ወርዶ ሰላምን በኹለቱ መኻhል አድርጓልና። [ኤፌ.፪፥፲፫-፲፰]

በዚኽ ቀን እንቡጡ ወጥቶ ምርኩዝ ኾኗልና። ላረጀው ዓለም በጣዖት አምልኮ ብዛትም ለጎበጠው ፤ በዚኽ ቀን ከዳዊት ቤት አበባ በቅሏል። ለተጠማውና ለተዋረደው ምድር ከወይኑ ያጠጣ ዘንድ [ ኢሳ.፲፩፥፩ ፤ ሮሜ.፲፭፥፲፪ ] በዚኽ ቀን ንስሩ [ ጌታ ] ተመለከተ እናም ጭልፊቶቹ ሸሹ፡፡ ርሱም የታደነችውን የደቂቀ ሰብእ ባሕርይ ርግቢቱን በጎዦው መልሶ አስቀመጠ ፤ በዚኽ ቀን ለርስቶቹ ይዘጋጅ ዘንድ ወራሹ ተቀስቅሷል፡፡ በጉልበት ይዟቸው ከቆየው ከዘራፊው መልሶ በመንጠቅ [ በማስጣል ] ፡፡

በዚኽ ቀን ተሰብሮ የነበረው እግር ቆሟል ወድቆ የነበረው ደካማ ቁርጭምጭሚቱም ብርታትን አግኝቷል፡፡ በዚኽ ቀን ከትውልድ የተማረኩት ሰላም ወርዶላቸዋል ፤ የከበረው ዕንቍም ርሱን ወደሚያውቁት በብርታት ተመልሷል፡፡ ❞

🕊 ቅዱስ ያዕቆብ ዘስሩግ  🕊 ]

💖                     🕊                     💖

ንጽሕት ድንግል ማርያም የታመነች አምላክን የወለደች ናት ለሰዎች ልጆችም ምሕረት አማላጅ ናት ኃጢአታችንን ያስተሠርይልን ዘንድ ወደ ልጅሽ ወደ ክርስቶስ ለምኝልን ቅድስት ሆይ ለምኝልን፡፡ ❞ [ ውዳሴ ማርያም ዘዓርብ ]

†                       †                        †
💖                    🕊                     💖

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

02 Jan, 10:06


                       †                        

  🕊     ቅዱስ አግናጥዮስ     🕊 

💖

❝ ክርስትያን ተብዬ ብቻ መጠራት የምፈልግ አይደለሁም ፤ ይልቁንም መሆንን እፈልጋለሁ ... ስጋዬን ለአውሬዎች ይስጡት በአውሬዎቹም ጥርስ ልፈጭ ፤ ንጹህ የክርስቶስ ህብስት ሆኜ ልገኝ ፤ ከአካሌም ምንም አያስቀሩ ፣ ምናልባት ለእናንተ ሥራ እንዳልሆንባችሁ፡፡ ❞

[ ቅዱስ አግናጥዮስ ዘአንጾክያ ለአራዊት ሊሰጥ ለሰማእትነት እየሄደ ሳለ ለሮሜ ሰዎች ከላከው መልእክት ]

🕊     

❝ በቅዱስ መስቀል አምሳያ ዘወትር ያለ ድካም ለጸሎት ለሚዘረጉትና በአሥር ጨካኝ ወታደሮች በብረት ሰንሰለት ታስረው ለተጎተቱት እጆችህ ሰላምታ ይገባል። ጵጵስናን ከቅዱስ ጴጥሮስ የተቀበልክ ሰማዕተ ክርስቶስ ቅዱስ አግናጥዮስ ሆይ ፣ ከታሰርኩበት የኃጢአት ሰንሰለት በተሰጠህ ሰማያዊ ሥልጣን ፍታኝ በብርሃን እጆችህም በፍጹም በረከት ባርከኝ። ❞

💖                    🕊                     💖

❝ ከቅዱሳን ሁሉ ጋር ስፋቱና ርዝመቱ ከፍታውም ጥልቅነቱም ምን ያህል መሆኑን ለማስተዋል ፥ ከመታወቅም የሚያልፈውን የክርስቶስን ፍቅር ለማወቅ ትበረቱ ዘንድ ፥ እስከ እግዚአብሔርም ፍጹም ሙላት ደርሳችሁ ትሞሉ ዘንድ። ❞ [ ኤፌ.፫፥፲፰ ]

[ የአባታችን የቅዱስ አግናጥዮስ የከበረች ጸሎቱና ምልጃው አይለየን። ከረከቱ ይክፈለን። ]


†                       †                        †
💖                    🕊                     💖

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

02 Jan, 07:45


                         †                         

🕊     ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት     🕊 

💖

❝ አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ሥላሴን በማመን ተተከለ [ ተገኘ ]። በማስተዋል ስሙት ፣ በጸጥታ እና በርጋታም ሆናችሁ አድምጡት። በጌታው የሠርግ ቀን [ በዕለተ ምጽዓት ] በመከራው ከሚገኘው ደስታ ትሳተፉ ዘንድ ፣ የነፍስ አባታችን ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ብላችሁ መጥራት ይቻላችሁ ዘንድ በመገዛት ፣ በማኅሌት እና ኅሊናን በመሰብሰብ በዐሉን አክብሩ። ❞

[ ገድለ ተክለ ሃይማኖት ]

🕊

እንኳን ለአቡነ ተክለ ሃይማኖት ለበዓለ ልደቱ መታሰቢ አደረሳችሁ።


†                       †                        †
💖                    🕊                     💖

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

01 Jan, 21:21


🕊

†  ታኅሳስ  ፳፬  [  24   ]  †

[  ✞ እንኩዋን ለቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት: ቅዱስ አግናጥዮስ እና ቅድስት አስቴር ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞   ]

† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። †

---------------------------------------------

🕊 ቅዱስ  ተክለ ሃይማኖት ሐዋርያዊ  🕊

†    ልደት   †

- መልካም ዛፍ መልካም ፍሬን ያፈራልና ተክለ ሃይማኖትን የወለዱት ደጋጉ : ጸጋ ዘአብ  ካህኑና  እግዚእ ኃረያ ናቸው:: እርሱ በክህነቱ: እርሷ በደግነቷ: በምጽዋቷ ጸንተው ቢኖሩ እግዚአብሔር ጣፋጭ ፍሬን ሰጥቷቸዋል::

- በዳሞቱ ገዢ በሞተለሚ አደጋ ቢደርስባቸው  ቅዱስ ሚካኤል : ጸጋ ዘአብን ከሞት: እግዚእ ኃረያን ከትድምርተ አረሚ [ ከአረማዊ ጋብቻ ] አድኗቸዋል:: በኋላም የቅዱሱን መወለድ አብስሯቸዋል::

- አቡነ ተክለ ሃይማኖት የጸነሱት መጋቢት ፳፬, በ፩ ሺህ ፪ መቶ ፮ [1206] (1196) ሲሆን የተወለዱት ታሕሳስ ፳፬ [24] , በ፲፻፯ [1207] (1197) ዓ/ም ነው:: በተወለዱበት ቀንም ብዙ ተአምራት ተገልጸዋል:: ቤታቸውም በበረከት ሞልቷል::

†  ዕድገት  †

- የጻድቁ የመጀመሪያ ስማቸው " ፍሥሃ_ጽዮን " ይሰኛል:: ይሕንን ስም ይዘው: አባታቸው ጸጋ ዘአብን ተከትለው አድገዋል:: በተለይ ቅዱሳት መጻሕፍትን [ብሉያት: ሐዲሳትን] ተምረዋል:: በሥጋዊው ጐዳናም ብርቱ አዳኝ እንደ ነበሩ ይነገራል:: ዲቁና ከወቅቱ ዻዻስ አባ ጌርሎስ  ተቀብለዋል::

†  መጠራት  †

- አንድ ቀን ፍሥሃ ጽዮን ለአደን ወጥቶ ሲያነጣጥር ድንገት ከሰማይ አስደንጋጭ ድምጽ ተሰማ:: የክብር ባለቤት  ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አእላፍ መላእክት እያመሰገኑ በሚካኤል ክንፍ ተቀምጦ ወረደ::

- የወጣቱን አዳኝ ፍርሃቱን አርቆ ጌታችን ተናገረ:

" ከዛሬ ጀምሮ ስምህ ተክለ ሃይማኖት [ ተክለ ሥላሴ ] ይሁን:: አራዊትን ሳይሆን ነፍሳትን ታድናለህ:: ዘወትር ካንተ ጋር ነኝ" ብሎ በግርማ ዐረገ:: ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከዚህ ጊዜ በኋላሰዓትን አላጠፉም:: ንብረታቸውን ለነዳያን በትነው በትር ብቻ ይዘው ቤታቸው እንደ ተከፈተ ወደ ምናኔ ወጡ::

†   አገልግሎት   †

- ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከዻዻሱ ቅስና ተቀብለው የወንጌል አገልግሎትን ጀመሩ:: በመጀመሪያ ስብከታቸው እዚያው ሽዋ [ ጽላልሽ ] አካባቢ ብቻ በ ፲ ሺ የሚቆጠሩ ሰዎችን አሳምነው አጠመቁ:: ያንጊዜ ኢትዮዽያ ፪ መልክ ነበራት::

፩. ዮዲት [ ጉዲት ] በፈጠረችው ጣጣና በእስላሞች ተጽዕኖ ወደ ደቡብ አካባቢ ያለው ነዋሪ አንድም ሃይማኖቱን ክዷል: ወይም በባዕድ አምልኮ ተጠምዷል::

፪. ደግሞ በዛግዌ ነገሥታት ጥረት ክርስትናና ምናኔ ተነቃቅቶ ነበር::

- ግማሹ ሃገር በጨለመበት ወቅት የደረሱት  ሐዲስ ሐዋርያ አባ ተክለ ሃይማኖት በወጣት ጉልበታቸውና በኃይለ መንፈስ ቅዱስ ብዙ ቦታዎችን አደረሱ:: ሕዝቡን: መሣፍንቱን ወደ ሃይማኖት መልሰው: ማርያኖችን [ ጠንቁዋዮችን ] አጥፍተዋል::

†  ገዳማዊ ሕይወት   †

- ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት በወንጌል ብርሃን ኢትዮዽያን ከማብራታቸው ባለፈ ገዳማዊ ሕይወትንም አስፋፍተዋል:: እርሳቸው ከሁሉ የተሻሉ ሳሉም በ ፫ ገዳማት በረድዕነት አገልግለዋል::

- እነዚህም በአቡነ በጸሎተ ሚካኤል ገዳም ለ፲፪ ዓመታት: በአቡነ ኢየሱስ ሞዐ ዘሐይቅ ገዳም ለ ፯ ዓመታት: በደብረ ዳሞ ከአቡነ ዮሐኒ  ጋር ለ ፯ ዓመታት: በአጠቃላይ ለ፳፮ ዓመታት አገልግለዋል::

- በአቡነ ኢየሱስ ሞዐ ከመነኮሱ በኋላም ወደ ምድረ ሽዋ ዞረሬ ተመልሰው በአንዲት በዓት ውስጥ ለ ፳፪ ዓመታት ቆመው ጸልየዋል:: በተሰበረ እግራቸውም ፮ ጦሮችን በግራና በቀኝ ተክለው ለ ፯ ዓመታት ጸልየዋል::

†  ስድስት ክንፍ   †

- ኢትዮዽያዊው ጻድቅና ሐዋርያ ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከኢትዮዽያ ወደ ኢየሩሳሌም ተጉዘው ከቅዱሳት መካናት ተባርከዋል:: ጻድቁ ምድረ እሥራኤል  የገቡት በየመንገዱ መንፈሳዊ ዘርን እየዘሩ: እያስተማሩና እያሳመኑ ነበር::

- የወቅቱ ሊቀ ዻዻሳት አባ ሚካኤል  ጋርም ተገናኝተው ቡራኬን ተሰጣጥተዋል:: ዋናው ጉዳይ ግን ከዚህ በኋላ ነው:: ጻድቁ እመቤታችንና ጌታችን ከጽንሰታቸው እስከ ዕርገታቸው የረገጧቸውን ቦታዎች ሲመለከቱ በፍጹም ተደሞ እንባቸው ይፈስ ነበር::

- ምክንያቱም እግዚአብሔር ስላበቃቸው ተክለ ሃይማኖት የሚያዩት ቦታውን አልነበረም:: በገሃድ :-

- በቤተ መቅደስ ብስራቱን
- በቤተ ልሔም ልደቱን
- በቤተ ዮሴፍ ግዝረቱን
- በፈለገ ዮርዳኖስ ጥምቀቱን
- በቤተ አልዓዛር ተአምራቱን ይመለከቱ ነበር::

- የጉብኝታቸው የመጨረሻ ክፍል ወደሆነው  ቀራንዮ ደርሰው ጌታቸውን እንደ ተሰቀለ ሆኖ ቢመለከቱት ከዓይናቸው ይፈስ የነበረው ቁጡ እንባ መልኩን ቀየረና ዓይናቸው ጠፋ:: በዚያች ቅጽበት ስም አጠራሯ የከበረ  እመቤታችን ድንግል ማርያም ፈጥና ደርሳ ጻድቁን ወደሰማይ አሳረገቻቸው::

†  በዚያም :-

- የብርሃን ዐይን ተቀብለው
- ፮ ክንፍ አብቅለው
- የወርቅ ካባ ላንቃ ለብሰው
- ማዕጠንተ ወርቁን ይዘው
- ከ፳፬ቱ ካህናተ ሰማይም ተደምረው
- ሥላሴን በአንድነቱና ሦስትነቱ ተመልክተው
- "ስብሐት ወክብር ለሥሉስ ቅዱስ ይደሉ" ብለው መንበረ ጸባኦትን አጥነው ወደ መሬት ተመልሰዋል::

†  ተአምራት   †

- የጻድቁ ተአምራት እንደ ሰማይ ከዋክብት የበዛ ነው::

- ሙት አንስተዋል
- ድውያንን ፈውሰዋል
- አጋንንትን አሳደዋል
- እሳትን ጨብጠዋል
- በክንፍ በረዋል
- ደመናን ዙፋን አድርገዋል::

- ብዙ ደቀ መዛሙርትን አፍርተው ደብረ ሊባኖስን መሥርተዋል:: በዚያም ሴትና ወንድ መነኮሳት እንደ ሕጻናት አብረው ኑረዋል:: በዘመናቸው ሰይጣን ታሥሯልና::

†   ዕረፍት    †

- ጻድቅ: ሰማዕትና ሐዋርያ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ብርሃን ሆነው መከራን በብዙ ተቀብለው: አእላፍ ፍሬን አፍርተው: በተወለዱ በ፺፱ [99] ዓመት: ከ ፰ [8] ወር: ከ ፩ [1] ቀናቸው ነሐሴ ፳፬ [24] , በ፲፻፫፮ [1306] [1296] ዓ/ም ዐርፈዋል:: ጌታ: ድንግል ማርያምና ቅዱሳን ከሰማይ ወርደው ተቀብለዋቸዋል:: ፲ ትውልድ የሚያስምር ቃል ኪዳንም ተቀብለዋል::

† የጻድቁ አባታችን ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት የቅድስናና የክብር ስሞች :-

፩. ተክለ አብ: ተክለ ወልድ: ተክለ መንፈስ ቅዱስ
፪. ፍስሐ ፅዮን
፫. ሐዲስ ሐዋርያ
፬. መምሕረ ትሩፋት
፭. ካህነ ሠማይ
፮. ምድራዊ መልዐክ
፯. እለ ስድስቱ ክነፊሁ [ባለስድስት ክንፍ]
፰. ጻድቅ ገዳማዊ
፱. ትሩፈ ምግባር
፲. ሰማዕት
፲፩. የኢትዮዽያ መነኮሳት አለቃ
፲፪. ፀሐይ ዘበፀጋ
፲፫. የኢትዮዽያ ብርሃኑዋ
፲፬. ብእሴ እግዚአብሔር [የእግዚአብሔር ሰው]
፲፭. መናኒ
፲፮. ኤዺስ ቆዾስ [እጨጌ]

እነዚህ የአባታችን ስሞች እንደዘመኑ ሰው ለመሞጋገስ የወጡ ሳይሆኑ ሁሉም በትክክል ሥራዎቹንና ለቤተ ክርስቲያን የሆነላትን የሚያዘክሩ ናቸው:

🕊  †  ቅዱስ አግናጥዮስ  †  🕊

ይህ ቅዱስ ሰው ከመንፈስ ቅዱስ ጸጋ የጠገበ በመሆኑ በመላው ዓለም ዝነኛ ነው:: እርሱ :-

- በክርስቶስ እጅ ተባርኩዋል
- ፈጣሪውን ፊት ለፊት አይቷል
- ሐዋርያትን አገልግሏል
- ከምሥጢር አባት ከዮሐንስ ወንጌላዊ እግር ተምሯል
- ስለ ክርስትና ለአንበሶች ተጥሎ በመገደሉ "ምጥው ለአንበሳ" ይባላል::

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

01 Jan, 21:21


- ቅዱስ አግናጥዮስ የተወለደው በክርስቶስ አምላካችን መዋዕለ ስብከት [በ፴ ዓ/ም አካባቢ] እንደ ሆነ ይታመናል:: በትውፊትም በማቴ.፲፰፥፩] ላይ ያለው ሕጻን እርሱ ነው ይባላል::

- ሐዋርያት ከመካከላቸው ማን እንደሚበልጥ ሲጠይቁት አንድ ሕጻንን [ አግናጥዮስን ] ከመሃል አቁሞ "ካልተመለሳችሁ: እንደዚህም ሕጻን ካልሆናችሁ ከቶውንም ወደ እግዚአብሔር መንግስት አትገቡም" ብሏቸዋል::

- ከጌታ ዕርገት በሁዋላም ሐዋርያት ለወንጌል ሲፋጠኑ ሕጻኑ ቅዱስ አግናጥዮስ እየተከተለ አገልግሏል: ተምሯል:: ኢየሩሳሌም በጥጦስ አስባስያኖስ ቄሣር በጠፋችበት ዓመት [በ፸ ዓ/ም] ቅዱሱ የአንጾኪያ ሊቀ ዻዻሳት ሆኖ ተሹሟል::

- ከዚህ በሁዋላም ለ ፪ እና ፫ አሠርት ዓመታት ከወንጌላዊ ዮሐንስ ጋር አብሮ ወንጌልን ሰብኩዋል:: የዚህ ቅዱስ ተጋድሎ ጫፍ የደረሰው ከ ፻ ዓ/ም በሁዋላ ሁሉም ሐዋርያት ሰማዕት በመሆናቸውና ትልቁን ኃላፊነት እርሱ በመሸከሙ ነው:: የወቅቷን ቤተ ክርስቲያን ከቅዱሳኑ ቀሌምንጦስ ዘሮምና ፖሊካርፐስ ዘሰርምኔስ ጋር ሆኖ እስከ ደም ጠብታ ጠብቁዋል::

- ከዚህ በሁዋላ ቅዱስ አግናጥዮስ ለዘመናት ወንጌልን እየሰበከ በሕይወቱና በትምሕርቱ አስተማረ:: ብዙ መልእክቶችን [ ድርሳናትንም ] ጻፈ:: በመጨረሻው ግን በጠራብሎስ ቄሣር ተይዞ: በብረት ሰንሰለት ታስሮ: ከአንጾኪያ [ ሶርያ ] ወደ ሮም [ ጣልያን ] ተወሰደ::

- ደሙ እስኪፈስም ገረፉት:: ዛሬ በሮም ከተማ ግማሽ አካሉ ፈርሶ በሚታየው ስታዲየም [ በአባቶቻችን አጠራር ተያጥሮን ] እንዲገደል ተወሰነበት:: በወቅቱ ባደረገው ንግግርም ቄሣሩና ሕዝቡ ድፍረቱን አደነቁ:: በመጨረሻም ለአንበሳ እንዲሰጥ ተደርጐ በዚህች ቀን ሰማዕት ሆነ::

🕊  †  ቅድስት አስቴር   †   🕊 

- ይህቺ ቅድስት እናት :-

- እሥራኤል በባቢሎን ምርኮ ሳሉ የነበረች
- አባቷ አሚናዳብ ባለ መኖሩ በአጐቷ መርዶክዮስ እጅ ያደገች
- እጅግ ውብ በመሆኗ የአርጤክስስ ሚስት [ ንግሥት ] ለመሆን የበቃች
- ራሷን መስዋዕት አድርጋ ወገኖቿን አይሁድን ከሞት ያተረፈች
- ለመርዶክዮስ ክብርን: ለአማሌቃዊው ሐማ ደግሞ ስቅላትን ያስፈረደች እና
- እግዚአብሔር ሞገስ የሆናት እናት ናት::
- ዛሬ ዕረፍቷ ነው::

አምላከ ቅዱሳን ወዳጆቹን ባጸናበት ቅዱስ መንፈሱ እኛንም ያጽናን:: ከበረከታቸውም ይክፈለን::

🕊

[   † ታሕሳስ ፳፬ [ 24 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት   ]

፩. ቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት
፪. ቅዱሳን ጸጋ ዘአብና እግዚእ ኃረያ
፫. ቅዱስ አግናጥዮስ ሐዋርያ
፬. ቅድስት አስቴር
፭. አባ ፊሎንጐስ ሊቀ ዻዻሳት
፮. አባ ዻውሊ ጻድቅ
፯. ጻድቃን ቅዱሳን ዘከዲህ

[   † ወርኀዊ በዓላት   ]

፩. ቅዱስ ቶማስ ዘመርዐስ
፪. አቡነ ዘዮሐንስ ጻድቅ ዘክብራን
፫. ቅዱስ አጋቢጦስ [ ጻድቅ ኤዺስቆዾስ ]
፬. ቅዱስ አብላርዮስ ታላቁ
፭. ፳፬ "24ቱ" ካኅናተ ሰማይ [ ሱራፌል ]
፮. ቅዱስ አባ ሙሴ ጸሊም [ ኢትዮዽያዊ ]
፯. ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ

" ንግሥቲቱም አስቴር መልሳ:- 'ንጉሥ ሆይ ! በአንተ ዘንድ ሞገስን አግኝቼ እንደ ሆነ: ንጉሡንም ደስ ቢያሰኘው: ሕይወቴ በልመናዬ: ሕዝቤም በመሻቴ ይሰጠኝ:: እኔና ሕዝቤ ለመጥፋትና ለመገደል: ለመደምሰስም ተሸጠናልና::" [አስቴር.፯፥፫]

† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †

[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]


         †              †               †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖                   🕊                    💖

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

01 Jan, 20:02


የአእላፋት ዝማሬ የሚደረግበት ቀን እና ሰአት መቼ እንደሆነ በ ጃን ያሬድ የቴለግራም ቻናል ላይ ተለቋል!
መግለጫ ለማየት join በሉ

@yeaelafat_zmare

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

01 Jan, 19:23


🌿🌿🌿መንፈሳዊ ጥያቄዎች 🍀🍀




1, ሰንበት ማለት ምን ማለት ነው ?
2, ሰንበት በብሉይ ቅዳሜ, በሐዲስ እሁድ ለምን ሆነ?
3, አእማደ ሚሥጢራት ለምን ሚሥጢር ተባለ?
4, 10ሩን የቅድስና ማዕረጋት ዘርዝሩ?
5, ሚሥጢር ማለት ምን ማለት ነው ?
6, ሚሥጢረ ሥጋዌ ማለት ምን ማለት ነው?


መልስ ለማግኘት👇👇👇

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

25 Dec, 20:30


የአእላፋት መዝሙር ጥናት ተጀመረ!!!

እንዳልዘምር የሚከለክለኝ ምንድን ነው?

አዲስ የአእላፋት መርሙራት ተለቀዋል!

መዝሙሮቹን በቴለግራም ለማጥናት JOIN በሉ!

@yeaelafat_zmare

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

25 Dec, 20:02


ከሚከተሉት ውስጥ የማይደገመው የቤተ ክርስቲያን ምሥጢር የቱ ነው??

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

25 Dec, 19:20


የማንን መዝሙር ማዳመጥ ይፈልጋሉ 👇

ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ

👤 ሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ

👤 ሊቀ መዘምራን . ኪነጥበብ ወ/ቂርቆስ

👤 ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ

👤 ቀሲስ እንግዳወርቅ በቀለ

👤 ዘማሪ ዲያቆን አቤል መክብብ

👤 ዘማሪት ምርትነሽ ጥላሁን

👤 ዘማሪ| በሱፍቃድ አንድአርጋቸው

👤 ዘማሪት ሲስተር ሊዲያ ታደሰ

👤 ዘማሪ ዳግማዊ ደርቤ

👤 ዘማሪት ፋንቱ ወልዴ

👤 ዘማሪ ዲያቆን ብርሃኑ በቀለ

👤ዘማሪት አዜብ ከበደ

👤 ዘማሪ ዲያቆን ሙሉቀን ከበደ

👤 ዘማሪት ፋሲካ ድንቁ

👤 ዘማሪት ሰላማዊት በርታ

የሁሉንም ዘማሪዎች ለማግኘት🎚

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

25 Dec, 17:18


💛
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬

🕊       [   ምክረ ቅዱሳን   ]        🕊


▷   "  ም ን   ት ፈ ል ጋ ላ ች ሁ ? ! "


💖  በቅዱስ ዮሐንስ-አፈወርቅ  💖 ] 

[                        🕊                        ]
-------------------------------------------------

❝ ኢየሱስም ዘወር ብሎ ሲከተሉትም አይቶ። ምን ትፈልጋላችሁ ? አላቸው። ❞

[  ዮሐ . ፩ ፥ ፴፰  ]


🕊                       💖                     🕊

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

25 Dec, 15:13


                       †                        

🕊  አስደናቂው የልደት ምስጢር  🕊 

💖

[  የአዳኛችንን በሥጋ መወለድ በተመለከተ በልደቱ ውስጥ ያለው አስደናቂ እና ጥልቅ መገለጥ  ]

💖                     🕊                     💖

❝ ርሱ እሳትን ለብሷል ፥ በመጠቅለያ ጨርቅም ተጠቅልሏል፡፡ ግን ደግሞ ከመታወቅ በላይ ነው፡፡ በዙፋን ላይ ተቀምጧል እንዲኹም በግርግም ተኝቷል !

ደግሞ አይመረመርም በኪሩቤል ዠርባ ላይ ተቀምጧል እንዲኹም ጉልበቶች ተሸክመውታል ፣ እናም በዚያ ምክንያት ርሱ ታላቅ ነው ፥ ርሱ የተፈጠሩ ፍጥረታትን ያላውሳቸዋል። እንዲኹም ርሱ አካለ ሥጋን ተዋሕዷል እናም እነርሱ ድንቁን ይናገራሉ፡፡ ርሱ ወገኖችን ያኖራቸዋል ርሱ እንዲኹም ወተት ይጠባል ! ርሱን ይረዳው ያውቀው ዘንድ ማን ይችላል ?

ርሱ ዝናብን ያዘንባል ፥ ርሱ ደግሞ ጡት ይጠባል ፥ እናም ድንቁን ተመልከቱ ርሱ ልዑል እና አስፈሪ ነው ርሱም የሚቀኝለት ነው : እነሆ ድንቁ ፣ ሰማይ ለእርሱ እጅግ ያንሰዋል እናም ርሱ መኖሪያን ፈለገ ፡ እነሆ እንዴት ያለጸጋ ነው !

ሱራፌል ራሳቸውን ይሽፍናሉ [ ይጋርዳሉ ] ፣ ዮሴፍ ይሰግዳል አንዳች ድንቅ በዚኽ አለና ፤ ሥልጣናት ተዘርግተዋል ሰዎችም ደካሞች ናቸው ፤ ያስተውል ዘንድ ማን ይችላል ? ❞

🕊 ቅዱስ ያዕቆብ ዘስሩግ  🕊 ]

💖

ንጹሐን ከሆኑ መላእክት ጋር በፍጹም ደስታ ደስ ተሰኝተን እናመስግን " በሰማይም ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን በምድርም ዕርቅ ይሁን " እንበል ክብርና ምስጋና ጌትነት ያለው እርሱ አንቺን ወዷልና ቅድስት ሆይ ለምኝልን፡፡ ❞ [ የማክሰኞ ውዳሴ ማርያም ]

†                       †                        †
💖                    🕊                     💖

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

25 Dec, 12:57


                          †                          

[    🕊    ገ ድ ለ   ቅ ዱ ሳ ን   🕊     ]

▬▬▬▬▬▬   †    ▬▬▬▬▬▬

[ ቅዱስ መቃርዮስ ካስተማረው ትምህርት ]

[               ክፍል  ስድሳ አንድ               ]

                         🕊  

[ ስለ እግዚአብሔር መግቦት አስተማረ ! ]

🕊

❝  በአንድ ወቅት ከአኃው ጋር አዝመራ በመሰብሰብ ሥራ ላይ አብሮ ተሰማርቶ እየሠራ ሳለ ፣ አንድ ተኩላ አፉን ከፍቶ በዓይኖቹ ወደ ሰማይ ወደ ጌታ አንጋጦ ትክ ብሎ እያየ በታላቅ ጩኸት ጮኸ፡፡

ቅዱስ መቃርዮስም ቆመና በዓይኖቹ ዕንባ እየወረደ ፊቱ ፈገግ አለ፡፡ አኃው ባዩት ጊዜም ተደነቁ፡፡ ከእግሩ ላይ ወድቀው ፦ “ አባታችን ሆይ ፣ ዓይኖችህ ዕንባ እያፈሰሱ ትኩር ብለህ ስታይ የነበረው ለምን እንደ ነበር ትነግረን ዘንድ እንለምንሃለን” አሉት፡፡ እርሱም ከዕንባ ጋር አትኩሮ እየተመለከተ ሳለ በእርሱ ካደረው የእግዚአብሔር ጸጋ የተነሣ ፊቱ እንደ ብርሃን ጸዳል እንደ እሳት ያበራ ነበር፡፡

እርሱም ፦ “ ይህ ተኩላ ምን ብሎ እንደ ጮኸ አልሰማችሁምን? ” አላቸው፡፡ እነርሱም ፦ “ ምንድን ነበር አባታችን? ” አሉት፡፡ እርሱም ፦ “ሰውን ወዳጅ ወደ ሆነው ፣ ብቻውን አዛኝና ርኅሩህ ወደ ሆነው ፣ ስፍር ቁጥር የሌለው የምሕረት መዝገብ ወዳለው ወደ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሚያስፈልገኝ ነገር የማትንከባከበኝና የምበላውን የማትሰጠኝ ከሆነ ቢያንስ እንኳ ለምን እንደምሠቃይ ንገረኝ ፤ የፈጠርከኝ አንተው ነህ' ሲል ጮኸ፡፡

ሥጋ በል የሆኑ አራዊት ስለ እግዚአብሔር መግቦትና ደግነት ይህን ያህል መረዳት ካላቸውና ወደ እርሱ ከጮኹና እርሱም እነርሱን ሁሉንም የሚመግባቸው ከሆነ ባለ አእምሮ ለሆንነው ለእኛማ በማይገደበውና በማይለካው ምሕረቱና ርኅራሄው እንዴት አያስብልንም? የሚያስፈልገንንስ እንዴት አይሰጠንም? እንዴትስ አይንከባከበንም?

ብሩህና ብርሃናዊ የሆነው የተሰወረውን የሚገልጠው ታላቁ አባት አባ መቃርዮስ እነዚህን ነገሮች ለአኃው እየነገራቸው ሳለ ተኩላው አፉን በመገረም ዓይነት ሁኔታ ሆኖ ቆመ:: ከዚያም በኋላ አውሬው እግዚአብሔር ምግቡን ወዳዘጋጀለት ቦታ ሄደ፡፡

አኃውም ሁሉም ከእግሩ ሥር ወድቀው የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ የሆነውን አባት አከበሩ፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስንም አመሰገኑ፡፡
..  ❞

🕊

የአባታችን የቅዱስ መቃርዮስ ምልጃና ጸሎቱ አይለየን፡፡

ይቆየን !


†                       †                         †
💖                    🕊                     💖

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

25 Dec, 10:48


🕊                      †                        🕊

[ ተዋሕዶ ፍጽምት የቅዱሳን ሃይማኖት ]
▬▬▬▬▬▬   †    ▬▬▬▬▬▬

[   ፍጹም ሰው ሁኖ ተወለደ !  ]

🕊

▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬

❝ እስከዚህች ቀን ድረስ ትሩፋት የሠሩ ሐዋርያት ፤ ሰማዕታት ሁሉ እንደ አመኑት እምነት እንዲህ እኔ አምናለሁ ፤ ቃል ሥጋ ሆኖዋልና መናፍቃንም እንደ ተናገሩት በዕሩቅ ብእሲ አላደረምና

በእርሱ ፈቃድ በአባቱና በመንፈስ ቅዱስ ፈቃድ ከቅድስት ድንግል ማርያም ሥጋን ተዋሐደ እንጂ እርሱ ባወቀ መለወጥ በሌለባት በእመቤታችን ማሕፀን ሥጋን ፈጥሮ ተዋሐደ

የጥልቅ ጥልቅ በሆነው ውስጥ ያለውን ያውቅ ዘንድ ከሰው ወገን ማንም ማን አይችልም ሁሉን የፈጠረ አምላክ የአብ አካላዊ ቃል ፍጹም ሰው ሁኖ ተወለደ እንደ ተጻፈ። [ ገላ.፬፥፬ ]

የሠላሳ ዘመን ጐልማሳ ለመሆን እስኪደርስ ድረስ ሕፃን በመሆን ሥርዓተ ሕፃናትን ፈጸመ ፥ ሁሉ የተፈጠረበት የእግዚአብሔር ቃል ይህ ነው ፤ ሥልጣን ሁሉ ገንዘቡ ሲሆን በራሱ ፈቃድ ብቻ ለአይሁድ ራሱን አሳልፎ ሰጠ። [ዮሐ.፩፥፩-፲፬ ። ሉቃ.፪፥፳፯-፵፪ ና ፡ ፶፫ ። ፫፥፳፫።

ዳግመኛ አስነሣት ዘንድ እኔ ሰውነቴን ለበጎች [ ለምእመናን ] ቤዛ አድርጌ ለሕማም ፤ ለሞት እሰጣታለሁ ከእኔ ማንም ሊወስዳት አይችልም ፥ ሰውነቴን ለሕማም ለሞት ልሰጣት ላስነሣትም ሥልጣን አለኝ ብሎ እንደ ተናገረ እርሱ አንዱ እግዚአብሔር ቃል ብቻ በማይመረመር ምሥጢር ሰው በመሆኑ ተሰቀለ። [ዮሐ.፲፥፲፰ ና ፲፱ ] ❞

[    ቅዱስ ጎርጎርዮስ  ዘእንዚናዙ    ]

▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬

ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፤ ወለወላዲቱ ድንግል ፤ ወለመስቀሉ ክቡር። አሜን።


†                         †                         †
💖                      🕊                      💖

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

24 Dec, 21:35


🕊

[  ✞ እንኩዋን ለኃያል "መሥፍነ እሥራኤል ቅዱስ ጌዴዎን" እና "ማርያም እህተ ሙሴ" ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞  ]

†  በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።  †

---------------------------------------------

🕊   †  ኃያል ጌዴዎን   †   🕊

- እግዚአብሔር ሰማይንና ምድርን: ፳፪ [22] ቱን ሥነ ፍጥረትን ፈጥሮ አዳምን ገዢ አደረገው:: አክሎም በነፍስ ሕያው አድርጐ: በመንፈስ ቅዱስ አክብሮ: ነቢይና ካህን አድርጐ: ካንዲት ዕፀ በለስ በቀር በፍጥረት ሁሉ ላይ አሰለጠነው::

- አባታችን አዳም ግን ስሕተት አግኝቶት ከገነት ወጣ:: መከራና ፍዳም አገኘው:: በሁዋላም ለ፻ [100] ዓመት አልቅሶ ንስሃ ገባ:: ጌታም ንስሃውን ተቀብሎ "ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለሁ" የሚል ተስፋ ድህነትን ሰጠው::

- ስለዚህም ምክንያት ለ፭ ሺህ ፭ መቶ [5500] ዓመታት ትንቢት ሲነገር: ሱባኤ ወደ ታች ሲቆጠር: ምሳሌም ሲመሰል ኖረ:: ከደግ ፍጥረት አዳም እስከ ኖኅ ድረስ: የሴት ልጆች እግዚአብሔርን በንጽሕና ሁነው በደብር ቅዱስ አመለኩ::

- ትንሽ ቆይተው ግን ስለተቀላቀሉ ከቃየን ልጆች ጋር በማየ ድምሳሴ ጠፉ:: በጻድቅ ሰው ኖኅ የተጀመረው ትውልድም እግዚአብሔርን ለመዘንጋት ጊዜ አልፈጀበትም:: ነገር ግን ከሴም ዘር ቅንና ጻድቅ ሰው አብርሃም ተገኘ::

- ከእርሱም ይስሐቅ: ከዚያም ያዕቆብ [ደጋጉ] ተገኙ:: ያዕቆብም "እሥራኤል" ተብሎ: በልጆቹ "ሕዝበ እግዚአብሔር" የተባለ ነገድ ተመሠረተ:: በተስፋይቱ ምድር በከነዓን እንዳይኖሩም ረሃብ ምድረ ግብጽ አወረዳቸው::

- በዚያም ለ፪ መቶ ፲፭  [2015] ዓመታት በጭንቅ የባርነትን ሕይወትን አሳለፉ:: እግዚአብሔርም ስለ ወዳጁ አብርሃም ሲል እሥራኤልን አሰባቸው:: የዋሕና ጻድቅ ሰው ሙሴን አስነስቶ እሥራኤልን ከግብጽ ባርነት አዳናቸው::

- ይኸውም በጸናች እጅ: በበረታችም ክንድ: በ፱ መቅሰፍት: በ፲ኛ ሞተ በኩር: በ፲፩ኛ ስጥመት ግብጻውያንን አጥፍቶ ነው:: በየመንገዱም ጠላቶቻቸውን እየተበቀለላቸው ነው:: ከዚህ ዘመን ጀምሮም እሥራኤል በመሳፍንትና በካህናት የሚተዳደሩ ሆኑ::

- አስቀድሞ ሙሴ በምስፍና: አሮን በክህነት መሯቸው:: ቀጥሎም በቅዱስ ሙሴ ኢያሱ: በአሮን አልዓዛር ተተኩ:: እንዲህ እንዲህ እያለም ከኃያል ሰው ጌዴዎን ደረሱ:: ይኸውም ከዓለም ፍጥረት ፬ ሺህ ፩ መቶ ፶፩ [4151] ዓመታት በሁዋላ መሆኑ ነው::

- በጊዜው እሥራኤል ጣዖትን እያመለኩ እግዚአብሕርን ስላሳዘኑት ለጠላቶቻቸው አሳልፎ ይሰጣቸው ነበር:: የአካባቢው መንግስታት እነ አሞን: አማሌቅ: ኢሎፍሊ ስንኩዋ ያኔ ዛሬም ቢሆን እንደምትመለከቱት ዶሮና ጥሬ ናቸው::

- ከክርስቶስ ልደት ፩ ሺህ ፫ መቶ ፵፱ [1349] ዓመታት በፊትም በእሥራኤል ላይ ምድያማውያን [ይህቺ ሃገር የኢትዮዽያ ግዛት ነበረች ይባላል] በጠላትነት ተነስተውባቸው ተጨነቁ::

- አምላካችን እግዚአብሔርም ሊያድናቸው ወዶ መልአኩን ወደ ጌዴዎን ላከው:: ቅዱስ መልአክም ወደ እርሱ ቀርቦ "ኃያል የእግአብሔር ሰው" ሲል ጠራው:: ጌዴዎን ግን "ባሮች ስንሆን ምን ኃይል አለን!" ሲል መለሰለት::

- መልአኩም "እግዚአብሔር ካንተ ጋር ነውና ሒድ! እሥራኤልን ከምድያም እጅ አድናቸው" አለው:: ጌዴዎን ምልልሱን ቀጠለ:: "እግዚአብሔር ከእኔ ጋር መሆኑን በምን አውቃለሁ?" ሲል ጠየቀው::

- ጌዴዎን ይህንን ያለው ፈጣሪውን ተጠራጥሮት አይደለም:: ይልቁኑ ጥበበ እግዚአብሔር ይገለጥ ዘንድና በሁዋለኛው ዘመን የሚፈጸመውን ምሥጢረ ሥጋዌ ሊያስረዳ እንጂ::

- መልአኩም መስፍኑ የሰዋውን መስዋዕት አሳረገለት:: ቀጥሎም ጌዴዎን "ጸምር [ብዝት ጨርቅ] ልዘርጋ:: ጠል [ዝናብ] በጸምሩ ላይ ይውረድ:: ዳር ዳሩ ግን ይቡስ [ደረቅ] ይሁን" አለ:: በጠዋትም እንዳለው ሆኖ አገኘው::

- በጸምሩ ላይ የወረደውን ጠል ጨምቆ በመንቀል ሞልቶ ቢጠጣው ሰማያዊ ኃይል ወረደለት:: ጥያቄውን አሁንም ቀጠለ:: "ጌታ ሆይ! እንደ ገናም ነገሩ ይቀየርልኝ:: ጠል በጸምሩ ላይ አይውረድ:: ዳር ዳሩ ግን ይውረድበት" አለ::

- እንዳለውም ሆነ:: ይህ ሁሉ ምሳሌ ነው:: ለጊዜው ጸምር የእሥራኤል: ጠል የረድኤት: ምድር የአህዛብ ምሳሌ ነው:: ጠል በጸምር እንጂ በምድር ላይ እንዳልወረደ ረድኤተ እግዚአብሔር ለእሥራኤል እንጂ ለአሕዛብ ያለ መደረጉ ምሳሌ ነው::

- አንድም ምሳሌውን ይለውጧል:: ጠል የሚለውን ብቻ እንቀይረውና ጠል የመቅሰፍት ምሳሌ: በ፪ኛው ጠል በምድር ላይ እንጂ በጸምር ላይ እንዳልወረደ: መቅሰፍቱም እሥራኤልን ትቶ በአሕዛብ ላይ ወርዷልና:: [ይህ ጊዜአዊ ምሥጢሩ ነው::]

- አማናዊ ምሥጢሩ ግን ወደ ሐዲስ ኪዳን ያመጣናል:: ጸምር የእመቤታችን: ጠል የጌታ ምሳሌ:: ጠል በጸምር እንጂ በምድር ላይ አለመውረዱ ጌታ ከድንግል ማርያም ብቻ መወለዱን ያሳያል::

- በ፪ኛው ምሳሌ ደግሞ ጠል የፍዳ: የመርገም ምሳሌ ይሆናል:: ጠል በምድር ላይ እንጂ በጸምር ላይ አለመውረዱ ድንግል ማርያም ፍዳ መርገም የሌለባት ንጽሕት መሆኗን ያሳያል::

- ይህ ሁሉ የተደረገለት ጌዴዎንም በወገኖቹ መካከል አዋጅ አስነግሮ ፴፪ [32] ሺ ሠራዊትን ሰበሰበ:: ግን እግዚአብሔር የእሥራኤላውያንን ክፋት [ማለትም በራሳችን ኃይል አሸነፍን] እንደሚሉ ያውቃልና "የፈራ ይመለስ በል" አለው::

- ፳፪ ሺ [22,000] ሠራዊት ፈርቶ ተመለሰ:: ምክንያቱም የምድያም ሠራዊት ከ፻ [100,000]  ሺ በላይ ነበርና:: አሁንም "፲ ሺው [10,000] ብዙ ነው:: ወደ ወንዝ አውርደህ ለያቸው" አለው:: ጌዴዎንም ወደ ወንዝ አውርዶ "ውሃ ጠጡ" አላቸው::

- ከ፲ ሺው ፫ [10,300] መቶው በእጃቸው እየጠለፉ ሲጠጡ ፱ ሺህ ፯ መቶ [9,700] ያህል ሰራዊት ግን ተጐንብሰው በአፋቸው ጠጡ:: በዚህም "ሌሎቹን [የተጐነበሱትን] አስመልሰህ በ፫ መቶው [300] ው ተዋጋ" ተባለ::

- እርሱም ፫ መቶ [300] ውን ተከታዮቹን ይዞ: መለከትና መብራት በሸክላ ይዞ በምድያም ሠራዊት አካባቢ አደረ:: በዚያች ሌሊትም ጌዴዎንና ሠራዊቱ በምድያም መካከል ገብተው እንስራቸውን ሰበሩ::

- መለከቱንም ነፉ:: እንደ አንበሳም "ኃይል ዘእግዚአብሔር: ኩዊናት ዘጌዴዎን - ኃይልን ከእግዚአብሔር: ጦርን ከጌዴዎን" እያሉ ገጠሙ::

- በድንጋጤ የተመቱት ምድያማውያንም እርስ በርሳቸው ተዋግተው በአንድ ሌሊት ብቻ መቶ ሁለት ሺህ [102,000] ሠራዊት አለቀባቸው:: ቀሪዎቹም ወገኖቻቸው አፈሩ:: እሥራኤል ግን በፈጣሪያቸው ኃይል ተፈሩ:: ጌዴዎንም ለ ፵ [40] ዓመታት እሥራኤልን አስተዳድሮ በዚህች ቀን ዐርፏል:: [መሣ.፮፥፩ - ፰፥፴፭] [6:1---8:35]


🕊  † ማርያም እህተ ሙሴ †   🕊

ይህች እናት የሊቀ ነቢያት ቅዱስ ሙሴና የሊቀ ካህናቱ ቅዱስ አሮን ትልቅ እህት ስትሆን ወላጆቿ እንበረምና ዮካብድ ይባላሉ:: እሥራኤል ከግብጽ ባርነት እንዲወጡ የእርሷን ያህል አስተዋጽኦ ያደረገች ሴት የለችም::

- ከመነሻውም ቅዱስ ሙሴን የጠበቀች: በሕግ በሥርዓት እንዲያድግ ከእናቱ ጋር ያገናኘች: ወገኖቿ ከግብጽ ሲወጡም ሴቶችን የመራች እናት ናት:: ወንድሞቿን ሙሴንና አሮንንም ታገለገላቸው ነበር:: በተለይ እግዚአብሔር ባሕረ ኤርትራን የብስ ሲያደርጋት ከበሮን አንስታ "ንሴብሖ ለእግዚአብሔር" ብላ ፈጣሪዋን አመስግናለች:: [ዘጸ.፲፭፥፳] [15:20]

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

24 Dec, 21:35


- አንድ ጊዜም "ኢትዮዽያዊቷን ሲፓራን ለምን አገባህ" በሚል ስለ ተናገረችው እግዚአብሔር ተቆጥቶ በለምጽ መቷታል:: [ዘኁ.፲፪፥፩] [12:1] ቆይቶም በቅዱሱ ምልጃ ምሯታል:: ማርያም በመንገድ ሳሉ: ወደ ርስት ሳይደርሱ ዐርፋ ተቀብራለች:: [ዘኁ.፳፥፩] [20:1]

አምላከ ኃያላን መንፈሳዊ ኃይልን ልኮ ጠላትን ያድክምልን:: ከወዳጆቹ በረከትም ይክፈለን::

🕊

[ † ታሕሳስ ፲፮ [ 16 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት  ]

፩. ቅዱስ ጌዴዎን ኃያል
፪. ማርያም እህተ ሙሴ

[   † ወርኀዊ በዓላት   ]

፩. ኪዳነ ምሕረት [የሰባቱ ኪዳናት ማሕተም]
፪. ቅድስት ኤልሳቤጥ [የመጥምቁ ዮሐንስ እናት]
፫. ቅዱስ ገብረ ማርያም ጻድቅ ንጉሠ ኢትዮዽያ
፬. ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌሉ ዘወርቅ
፭. ቅዱስ አኖሬዎስ ጻድቅ
፮. አባ ዳንኤል ገዳማዊ
፯. አባ አቡናፍር ገዳማዊ

" እንግዲህ ምን እላለሁ? ስለ ጌዴዎንና ስለ ባርቅ: ስለ ሶምሶንም: ስለ ዮፍታሔም: ስለ ዳዊትና ስለ ሳሙኤልም: ስለ ነቢያትም እንዳልተርክ ጊዜ ያጥርብኛልና:: እነርሱ በእምነት መንግሥታትን ድል ነሡ:: ጽድቅንም አደረጉ . . ." [ዕብ.፲፩፥፴፪]

† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †

[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]


         †              †               †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖                   🕊                    💖

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

24 Dec, 20:35


የአእላፋት መዝሙር ጥናት ተጀመረ!!!

እንዳልዘምር የሚከለክለኝ ምንድን ነው?

አዲስ የአእላፋት መርሙራት ተለቀዋል!

መዝሙሮቹን በቴለግራም ለማጥናት JOIN በሉ!

@yeaelafat_zmare

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

08 Dec, 02:51


በጊዜው መጽሐፈ ቅዳሴ ባለ መደራጀቱ ሥጋውን ደሙን ሲፈትቱ ፈጣሪ እንዳመለከታቸው ይጸልዩ ነበር:: ቅዱሱ ግን የጌታንና የሐዋርያትን ቅዳሴ ዛሬ በምናየው መንገድ አደራጅቶ ጽፎታል:: በስሙ የሚጠራና "ቀሌምንጦስ" የሚባል መጽሐፉም [፰ ክፍሎች አሉት] ከ፹፩ዱ [አሥራው] መጻሕፍት ተቆጥሮለታል::

ቅዱሱ ሐዋርያ እንዲህ ሲመላለስ ኖሮ በ2ኛው መቶ ክ/ዘመን መጀመሪያ አካባቢ በጠራብሎስ እጅ ወደቀ:: ንጉሡም "ክርስትናን አስተምረሃል" በሚል ብዙ አሰቃይቶ: ከትልቅ ድንጋይ ጋር አስሮ ባሕር ውስጥ አስጥሞታል:: በዚህም ዐርፏል::

ሁሌ ግን በዓመት በዓመት ባሕሩ እየተከፈለላቸው: ምዕመናን እየገቡ ከቅዱስ አካሉ ይባረካሉ:: ቅዱሱን ብዙ ጊዜ "ቀሌምንጦስ ዘሮም" የምንለው "ቀሌምንጦስ ዘእስክንድርያ" የሚባል መናፍቅ ስላለ ከእርሱ ለመለየት ነው::
የቅዱሱ ክብር በእውነት ታላቅ ነው!

† አምላከ ሐዋርያት ወሰማዕት በመከራቸው ከመከራ ይሰውረን:: በረከታቸውንም ያብዛልን::

🕊

[   † ኅዳር ፳፱ [ 29 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት   ]

፩. ቅዱሳን ሰማዕታተ ክርስቶስ [ሁሉም]
፪. ቅዱስ ጴጥሮስ ተፍጻሜተ ሰማዕት
፫. ቅዱስ ቀሌምንጦስ ሐዋርያ [ዘሮም]

[   † ወርኀዊ በዓላት    ]

፩. የፈጣሪያችን ኢየሱስ ክርስቶስ ልደት
፪. ቅዱስ ማርቆስ ዘቶርማቅ
፫. ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ ኢትዮጵያዊት
፬. ቅዱስ ዘርዐ ክርስቶስ
፭. ቅድስት አርሴማ ድንግል

† " አቤቱ አሕዛብ ወደ ርስትህ ገቡ:: የቅድስናህንም መቅደስ አረከሱ:: ኢየሩሳሌምንም እንደ መደብ አደረጉአት:: የባሪያዎችህንም በድኖች ለሰማይ ወፎች አደረጉ:: የጻድቃንህንም ሥጋ ለምድር አራዊት:: ደማቸውንም በኢየሩሳሌም ዙሪያ እንደ ውኃ አፈሰሱ:: የሚቀብራቸውም አጡ::" † [መዝ.፸፰፥፩]

† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †

[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]


         †              †               †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖                   🕊                    💖

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

08 Dec, 02:51


🕊

[  † እንኳን ለአእላፍ ሰማዕታት : ቅዱስ ጴጥሮስ እና ቅዱስ ቀሌምንጦስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። †  ]

† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †


🕊  †  ቅዱሳን ሰማዕታት  †   🕊

† ቤተ ክርስቲያን ዛሬ [ኅዳር ፳፱ [29] የሁሉንም ሰማዕታት በዓል ታከብራለች:: አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ [ቅዱሱ ሊቅ] በመጽሐፈ ሰዓታት ሰማዕታትን :-

"መስተጋድላን ከዋክብት ብሩሃን::
ማኅትዊሃ ለቤተ ክርስቲያን::" ይላቸዋል::

በ፫ኛው መቶ ክ/ዘመን የሮም መንግስት ዓለምን የሚያስተዳድረው በሁለት ከተሞች: ማለትም በራሷ በሮምና በአንጾኪያ ነበር:: የወቅቱ ንጉሥ ኑማርያኖስ ሲሆን የቤተ መንግስቱ ልዑላንና የጦር አለቆች ቅዱሳኑ :- - ፋሲለደስ: - ገላውዴዎስ: - ፊቅጦር: - መቃርስ: - አባዲር: - ቴዎድሮስ [ሦስቱም] : - አውሳብዮስ: - ዮስጦስ: - አቦሊ: ሌሎቹም ነበሩ::

ሴቶቹ ደግሞ ቅዱሳቱ :- - ማርታ: - ሶፍያ: - ኢራኢ: - ታኡክልያ: ሌሎቹም ነበሩ:: ለእነዚህ ሁሉ የበላይ ደግሞ ቅዱስ ፋሲለደስ ነበር:: ወቅቱ ከፋርስ: ከቁዝና ከበርበር ጦርነት የሚበዛበት ነበርና ባጋጣሚ ንጉሡ ኑማርያኖስ በሰልፍ መካከል ተመትቶ ወደቀ [ሞተ]::

የሮም መንግስትም ባዶ ሆነች:: ዙፋኑን መያዝ ለቅዱስ ፋሲለደስም ሆነ ለሌሎቹ ቅዱሳን ቀላል ነበር:: ግን እነሱ ዝም ብለው ጠላትን ለመዋጋት ወጡ::

በዘመኑ ደግሞ በግብጽ የፍየል እረኛ የነበረና ከልጅነቱ ሰይጣን የሚያናግረው አንድ አግሪጳዳ የሚሉት ጉልበተኛ ሰው ነበር:: ንጉሡ ከወለዳቸው ልጆች ሁለቱ ሴቶች ክፉዎች ነበሩና ትንሿ አግሪጳዳን ማንም በሌለበት አንግሣ ጠበቀቻቸው:: ስሙንም ዲዮቅልጢያኖስ አለችው::

በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ከሰይጣን ቀጥሎ እንደዚህ የከፋ ስም የለም:: የዓለም ክርስቲያኖችን የጨፈጨፈ ሰው ነው:: ትልቋ ደግሞ የትንሿን አይታ መክስምያኖስ የሚባል አውሬ አግብታ አነገሠችው:: ዓለምም በእነዚህ ጨካኝ ሰዎች እጅ ወደቀች::

ሠራዊቱ ሁሉ በሚሊየን ይቆጠራሉ:: የተደረገውን ሲያዩ ተበሳጩ:: ይህንን የተመለከተው ቅዱሱ ፋሲለደስ ግን ልዑላኑንና አለቆችን ሰብስቦ:- "ይህ ዓለም ከነ ክብሩ ጠፊ ነው:: ስለዚህ የተሻለውን የክርስቶስን መንግስት እንምረጥ" አላቸው:: ሁሉም እንደ አንድ ልብ መካሪ ደስ ተሰኝተው ምድራዊ ክብራቸውን ሊተው ወሰኑ::

ቀጥለውም በአንድ ቤት ተሰብስበው ይጾሙ: ይጸልዩ ገቡ:: ወደ ውጪ የሚወጡት ለምጽዋት ብቻ ነበር:: ከሃዲውም ይህንን ሲያይ የልብ ልብ ተሰማው:: ከድሮ ያሰበውንና ክርስቲያኖችን የማጥፋቱን እቅድ ሊፈጽም ምክንያት አገኘ::

አባ አጋግዮስ በሚባል መነኩሴ ምክንያት "አብያተ ክርስቲያናት ይትዐጸዋ: አብያተ ጣዖታት ይትረኀዋ - ቤተ ክርስቲያኖች ይዘጉ: ቤተ ጣዖቶችም ይከፈቱ" አለ:: አጵሎን: አርዳሚስ የሚባሉ ጣዖቶችንም አቆመ::

በዚህ አዋጅ ምክንያትም የክርስቲያኖች ሰቆቃ ጀመረ::

- ምድር በደም ታጠበች::
- ቅዱሳኑ ቀባሪ አጡ::
- እኩሉ ተገደለ:: እኩሉ ተቃጠለ:: እኩሉ ታሠረ:: እኩሉም ተሰደደ::

የቤተ ክርስቲያን ታሪክ የተጻፈው በብራናና በብዕር አይደለም:: ይልቁኑ እንደ ቀለም የሰማዕታት ደማቸው: እንደ ብዕር አጥንታቸው: ቆዳቸው እንደ ብራና ሆኖ ተጽፏል እንጂ:: ሰማዕታት ለሃይማኖታቸው የከፈሉት ዋጋ እጅግ ታላቅ ነው::

ስለዚህም "ተጋዳዮች: የሚያበሩ ኮከቦች: የቤተ ክርስቲያን ሻማዎች" ተብለው: እነሱ እየቀለጡ አብርተዋል:: ሰማዕትነት በብሉይ ኪዳን የጀመረና እስከ ዳግም ምጽዐተ ክርስቶስም የሚቀጥል ቢሆንም "ዘመነ ሰማዕታት" የሚባለው ከ፻፶ እስከ ፫፻፲፪ ዓ/ም ድረስ ያለው ዘመን ነው::

በተለይ ግን ከ፪፻፸ ዎቹ እስከ ፫፻፲፪ ዓ/ም ድረስ ያሉ ዓመታት እጅግ የከፉ ነበሩና: የአርባ ሰባት ሚሊየን [ ፵፯ ሚሊየን] ክርስቲያኖች ደም በምድር ላይ ፈሷል:: የሰማዕታት ምሥጢራቸው ቃለ ወንጌል: የጌታ ስብከትና ሕይወት እንጂ ሌላ አይደለም:: [ማቴ.፲፥፲፮, ማር.፲፫፥፱, ሉቃ.፲፪፥፬, ዮሐ.፲፮፥፩, ሮሜ.፰፥፴፭, ራዕይ.፪፥፱]

የቅዱሳን ሰማዕታት መነሻቸው ቅዱስ እስጢፋኖስ ሲሆን ፍጻሜአቸው ደግሞ ቅዱስ ጴጥሮስ ሊቀ ጳጳሳት ነው::


🕊  † ቅዱስ ጴጥሮስ ሰማዕት †  🕊

† ይህ ቅዱስ የሚታወቀው "ተፍጻሜተ ሰማዕት [የሰማዕታት መጨረሻ]" በሚለው ስሙ ነው::
ይሕስ እንደ ምን ነው ቢሉ :-

የቅዱሱ ሃገረ ሙላዱ ግብጽ ናት:: ዘመኑም ፫ኛው መቶ ክ/ዘመን ነው:: ወላጆቹ ካህን ቴዎድሮስና ቡርክት ሶፍያ ልጅ አጥተው ሐምሌ ፭ ቀን ወደ ፈጣሪ ቢማጸኑ በራዕይ ጴጥሮስ ወጳውሎስ ተገልጠው ብሥራትን ለሶፍያ ነገሯት:: በወለደችው ጊዜም በራዕዩ መሠረት "ጴጥሮስ" አለችው::

ሰባት ዓመት በሆነው ጊዜም ለቤተ እግዚአብሔር ሰጥተው በሊቀ ጳጳሳቱ ቅዱስ ቴዎናስ እጅ አደገና በወጣትነቱ ሊቅ: ጥዑመ ቃልና በጐ ሰው ሆነ:: ዲቁናና ቅስናን ተሹሞ ሲያገለግል ቅዱስ ቴዎናስ በማረፉ ቅዱስ ጴጥሮስን የግብጽ ፲፯ኛ ፓትርያርክ አድርገው ሾሙት::

ዘመኑ ደግሞ እጅግ ጭንቅ ነበር:: ክርስቲያኖች በተገኙበት ስለሚገደሉ: አብያተ ክርስቲያናትም ስለ ተቃጠሉ የቅዱሱ መከራ የበዛ ነበር:: ለ፲፬ ዓመታት በፍጹም ትጋት ከመንጋው ጋር ተጨነቀ::

አርዮስን [ተማሪው ነበር] አውግዞ ለየው:: ከጌታ ጋርም ብዙ ጊዜ ተነጋገረ:: ብዙ ተአምራትንም ሠራ:: በዚህ ሁሉ ጊዜ አንድም ቀን በመንበረ ጵጵስናው ላይ አልተቀመጠም:: በኋላ ግን ጨካኙ ንጉሥ እንዲገደል አዘዘ::

ሕዝቡ "ከእሱ በፊት እኛን ግደሉን" በማለታቸው ሁከት እንዳይነሳ ቅዱስ ጴጥሮስ ተደብቆ ሔደና በፈቃዱ ለወታደሮች ተሰጠ:: በዚያች ሌሊትም የእርሱ ደም የግፍ ማብቂያ እንዲሆን እያለቀሰ ጮኸ:: ከሰማይም "አሜን! ይሁን!" የሚል ቃል መጣ:: ያን ጊዜ የእርሱ አንገት ተሰየፈ:: ዘመነ ሰማዕታትም አለፈ::


🕊  † ቅዱስ ቀሌምንጦስ ዘሮም †  🕊

† የዚህ ቅዱስ ሐዋርያ ስሙ እንደ ምን ያምር! እንደ ምንስ ይከብር! ለቤተ ክርስቲያን ትልቁ ድልድዩዋ ነውና:: ቅዱስ ቀሌምንጦስ የቅዱስ ቀውስጦስና የቅድስት አክሮስያ ልጅ ሲሆን ወንድምም ነበረው::

አባትና እናቱም የሮም መሳፍንት: በስብከተ ቅዱስ ጴጥሮስ ሊቀ ሐዋርያት ያመኑ: ገንዘባቸውን በምጽዋት የጨረሱ የመጀመሪያዎቹ የሮም ክርስቲያኖች ናቸው:: ልጆቻቸው [ቀሌምንጦስና ወንድሙ] በመርዝ ቢሞቱባቸው በአምላከ ጴጥሮስ ተማጽነው ተነስተውላቸዋል::

አንድ ጊዜ ቀውስጦስ በሌለበት አንድ ሰው አክሮስያን ስላስቸገራት ልጆቿን ይዛ ተሰዳለች:: በመንገድም መርከባቸው ተሰብሮ ቅዱስ ቀሌምንጦስ በስባሪው ግብጽ ደርሷል:: በዚያም ቅዱስ ጴጥሮስን አግኝቶት የሊቀ ሐዋርያት ደቀ መዝሙሩ ሆኗል::

ቅዱስ ጴጥሮስንም ተከትሎ ለአገልግሎት ብዙ አሕጉራትን ዙሯል:: ብዙ ምሥጢራትንም ተካፍሏል:: የቅዱሳን ሐዋርያትን ዜናም ከቅዱስ ሉቃስ [ግብረ ሐዋርያት] ቀጥሎ የጻፈ እርሱ ነው::

ቅዱሳን ሐዋርያት ሙሉ ቀኖናቸውን ለቅዱስ ቀሌምንጦስ ሲሰጡት ቅዱስ ጴጥሮስ ደግሞ ሰብአ ሰገል ለክርስቶስ ያመጡትን ወርቅ: እጣን: ከርቤውን አስረክቦታል:: በተለይ ሁሉም ሐዋርያት ባረፉ ጊዜ እርሱ ቤተ ክርስቲያንን ተረከበ:: በሮም ሁለተኛው ፓትርያርክ ሆነ::

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

07 Dec, 15:40


                       †                       

  [  🕊  ድምፀ ተዋሕዶ   🕊  ]  

🍒▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬🍒               

[  ሕይወት የሚገኝባቸው የቅድስት ቤተክርስቲያን መንፈሳዊ ትምህርቶች በሊቃውንተ ቤተክርስቲያን በድምፅ ይቀርባሉ።  ]

[   ሳምንታዊ መርሐ-ግብር   ]

🕊             
             
❝ የእግዚአብሔር ሕግ ፍጹም ነው ፤ ነፍስን ይመልሳል ፤ የእግዚአብሔር ምስክር የታመነ ነው ፤ ሕፃናትን ጠቢባን ያደርጋል።

የእግዚአብሔር ሥርዓት ቅን ነው ፥ ልብንም ደስ ያሰኛል ፤ የእግዚአብሔር ትእዛዝ ብሩህ ነው ፥ ዓይንንም ያበራል። ❞

[ መዝ . ፲፱ ፥ ፯  ]

▬▬▬▬▬▬   †    ▬▬▬▬▬▬

[  ❝ የእግዚአብሔር ሕግ ፍጹም ነው ! ❞  ]

               [   ክፍል - ፴፱ -    ]

          💖   ድንቅ ትምህርት  💖

[ በመምህራችን በቀሲስ ኅብረት የሺጥላ ]

የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ፥ ከመከራም ሥጋት ያርፋል። ❞ [ ምሳ.፩፥፴፫ ]

         †              †               †
▬▬▬▬ ▬▬▬▬▬ ▬▬▬▬
                        👇

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

07 Dec, 08:41


📍የመስቀል ምልክቱን ንኩት እና መንፈሳዊ እና ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶችን ምክሮችን የያዘ የቴሌግራም ቻናል ይቀላቀሉ ።
👇👇
እግዚአብሔር በአንድም በሌላም መንገድ ያስተምራል። ኑ አብረን እንማር።👇👇

🌑🌑███🌑🌑
🌑🌑███🌑🌑
█████████
█████████
🌑🌑███🌑🌑
🌑🌑███🌑🌑
🌑🌑███🌑🌑
🌑🌑███🌑🌑
🌑🌑███🌑🌑

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

07 Dec, 08:10


💛

🕊     ቅ ዱ ስ አ ማ ኑ ኤ ል     🕊

❝ ሰላም ለአስተርእዮቱ በሥጋ
ዘአስተርአየ ገሃድ ከመ የሀበነ ጸጋ ❞

[  በግልጽ ጸጋን ያድለን ዘንድ በሥጋ የተገለጠ ለኾነ ለእርሱ አገላለጥ ሰላምታ ይገባል ]

▬▬▬▬▬▬   †    ▬▬▬▬▬▬

❝ ስለዚህ ጌታ ራሱ ምልክት ይሰጣችኋል ፤ እነሆ ፥ ድንግል ትፀንሳለች ፥ ወንድ ልጅም ትወልዳለች ፥ ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች። ❞

[ ኢሳ.፯፥፲፬ ]

" Therefore the Lord himself shall give you a sign; Behold, a virgin shall conceive, and bear a son, and shall call his name Immanuel."

[ Isaiah 7:14 ]


🕊                        💖                     🕊
                             👇

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

06 Dec, 21:35


🕊

✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞

†  እንኩዋን ለአበው ቅዱሳን "አባ ሊቃኖስ ወአባ ሰረባሞን ሰማዕት" ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ †

" ኅዳር ፳፰ [ 28 ] "


🕊  †  አባ ሊቃኖስ ዘደብረ ቆናጽል  †   🕊

ጻድቁ ገድላቸውን የፈጸሙት በኢትዮዽያ ቢሆንም ሃገረ ሙላዳቸው የጥንቱ የሮም ግዛት የሆነችው ታናሽ እስያ ናት:: አባ ሊቃኖስ ከዘጠኙ [ተስዓቱ] ቅዱሳን አንዱ ናቸው:: ዘጠኙ ቅዱሳን ተወልደው ያደጉት ምንም በአንድ የሮም ግዛት ሥር ቢሆንም መነሻ ቦታቸው ግን የተለያየ ነው::

ሁሉንም አንድ ያደረጋቸው መንፈስ ቅዱስ በኪነ ጥበቡ ነው:: በምክንያት ደረጃ እንግለጸው ከተባለ ደግሞ የአንድነታቸው ምሥጢር :-

፩. የቀናች ሃይማኖታቸው ተዋሕዶ
፪. ዓላማ [የእግዚአብሔር መንግስት] እና
፫. ገዳማዊ ሕይወት ነው::

አባ ሊቃኖስን ጨምሮ ሁሉም ቅዱሳን ዘራቸው ከቤተ መንግስት ነው:: እነርሱ ግን ምድራዊውን ክብር ንቀው ሰማያዊውን ክብር ገንዘብ ማድረግን መርጠዋል:: አስቀድመው ቅዱሳት መጻሕፍትን ያጠኑት አበው በተለያየ ጊዜ እየመነኑ ከሮም ግዛት ወደ ግብጽ በርሃዎች ወርደዋል::

በምናኔ ቅድሚያውን አባ ዸንጠሌዎንና አቡነ አረጋዊ ይይዛሉ:: ዘመኑ የተዋሕዶ አማኞች የሚሰደዱበት ፭ኛው መቶ ክ/ዘመን ነበርና እምነትን ላለመለወጥ ዘጠኙ ቅዱሳን ስደትን መረጡ::

በወቅቱ ደግሞ ለስደት መጠለያ የምትሆንና ከኢትዮዽያ የተሻለች ሃገር አልነበረችም:: ስለዚህም በ፬ መቶ ፸ ዎቹ ዓ/ም አልዓሜዳ በኢትዮዽያ ነግሦ ሳለ ቅዱሳኑ በአረጋዊ መሪነት መጡ::

ንጉሡም ሲጀመር የእግዚአብሔር እንግዳ ስለሆኑ: ሲቀጥል ደግሞ ቅድስናቸውን ተመልክቶ መልካም አቀባበልን አደረገላቸው:: ማረፊያ ትሆናቸውም ዘንድ አክሱም ውስጥ አንዲት ቦታን ወስኖ ሰጣቸው:: ይህች ቦታ ቤተ ቀጢን ትባላለች::

አባ ሊቃኖስና ፰ቱ ቅዱሳን ወደ ሃገራችን እንደ ገቡ የመጀመሪያ ሥራቸው ቋንቋን መማር ነበር::

ልሳነ ግዕዝን በወጉ ተምረው እዛው አክሱም አካባቢ ሥራቸውን አንድ አሉ:: በወቅቱ በአቡነ ሰላማ: በአብርሃ ወአጽብሐና በአቡነ ሙሴ ቀዳማዊ የተቀጣጠለው ክርስትና በተወሰነ መንገድ ተቀዛቅዞ ነበርና እነ አባ ሊቃኖስ እንደ ገና አቀጣጠሉት::

ሕዝቡን በራሱ ልሳን ለክርስትና ይነቃቃ ዘንድ ሰበኩት::የካደውን እየመለሱ: የቀዘቀዘውን እያሟሟቁ ለዓመታት ወንጌልን ሰበኩ:: ቀጣዩ ሥራቸው ደግሞ መጻሕፍትን መተርጐም ሆነ::

ከሃገራቸው ያመጧቸውን ቅዱሳት መጻሕፍት ተከፋፍለው ወደ ግዕዝ ልሳን ተረጐሟቸው:: በዚህም ለሃገራችን ትልቁን ውለታ ዋሉ:: ይህ ሁሉ ሲሆን እነ አባ ሊቃኖስ የሚመገቡትም ሆነ የሚጸልዩት በማኅበር ነበር:: በመካከላቸውም ፍጹም ፍቅር ነበር:: ጸጋ እግዚአብሔር አልተለያቸውም::

የነ አባ ሊቃኖስ ቀጣዩ ተግባራቸው ደግሞ ገዳማዊ ሕይወትን ማስፋፋት ሆነ:: ይህንን ለማድረግ ግን የግድ መለያየት አስፈለጋቸው:: እያንዳንዱም መንፈስ ቅዱስ ወደ መራው ቦታ ሔደ::

- ዸንጠሌዎን በጾማዕት:
- ገሪማ በመደራ:
- አረጋዊ በዳሞ
- ጽሕማ በጸድያ
- አባ ይምዓታ በገርዓልታ
- ሌሎችም በሌላ ቦታ ገዳማትን መሠረቱ::

ልክ እንደ ባልንጀሮቻቸው ፰ቱ ቅዱሳን አባ ሊቃኖስም ከጻድቅነታቸው ባሻገር ለሃገራችን ትልቅ ባለውለታ ናቸው::በነገራችን ላይ 'አባ ሊቃኖስ' የመጀመሪያ ስማቸው ሳይሆን በትምሕርታቸው [በእውቀታቸው] የተደመመ የአክሱም ሕዝብ ያወጣላቸው ስም ነው::

ሊቃኖስን 'ሊቁ አባት' ማለት ነው ብለው የተረጐሙልን አበው አሉና:: ይሕስ በምን ይታወቃል ቢሉ :- ፱ኙ ቅዱሳን የማኅበር አገልግሎታቸውን ፈጽመው ወደየ ራሳቸው ገዳማት ሲሔዱ አባ ዸንጠሌዎንና አባ ሊቃኖስ እዚያው አክሱም አካባቢ በመቅረታቸው ይሏል::

ምክንያቱም ሕዝቡና ንጉሡ ፪ቱን አበው "አትራቁን" ብለው ለምነዋቸው ነበርና:: በዚህም የተነሳ አባ ዸንጠሌዎን ከአክሱም ከተማ በላይ ባለች ጾማዕት [እንዳባ ዸንጠሌዎን] በሚሏት ተራራ ላይ ሲያርፉ: አባ ሊቃኖስ ደግሞ ከዚያው ከጾማዕት ፩ ኪሎ ሜትር ርቆ በሚገኘው ደብረ ቆናጽል [የቀበሮዎችተራራ] ላይ ዐርፈዋል::

በመካከላቸው ደግሞ የቅድስት ማርያም መግደላዊት ቤተ ክርስቲያን ይገኛል:: አባ ሊቃኖስ በአታቸውን ካደራጁና ገዳም ካነጹ በኋላ ደቀ መዛሙርትን አፈሩ: አስተማሩ::

እጅግ ከበዛው ተጋድሏቸው ባልተናነሰ መንገድ ለ፳፩ ዓመታት ያህል ከተራራው እየተነሱ ወንጌልን ሰብከዋል:: መጽሐፍ ቅዱስና ሌሎች መጻሕፍትንም ከሱርስት [የሶርያ ልሳን] እና ከጽርዕ [የግሪክ ልሳን] ተርጉመዋል::

ሁልጊዜም ለአገልግሎት ሲወጡ በትረ ሙሴአቸውን አይለዩም ነበር:: ሲሰብኩም: ሲጸልዩም ተደግፈውባት ነበር:: ታዲያ ከዘመን ብዛት የእጃቸው መዳፍ መነደሉን አበው :-"ወበእሒዘ በትር ዘተሰቁረ ዕዱ" ሲሉ ይናገራሉ::

ዳግመኛ ማታ ማታ ለጸሎት እጆቻቸውን ሲያነሱ እንደ ፋና ቦግ ብለው ሲያበሩ ይታዩ ነበር:: ጻድቁ አባ ሊቃኖስ ሥሙር በሆነ ሕይወታቸው በእግዚአብሔር ብቻ ሳይሆን በነገሥታቱና በሕዝቡ ዘንድም ሞገስን አግኝተዋል:: ዛሬም ድረስ የአክሱም ሕዝብ ከልቡ ያከብራቸዋል::

አንድ ወቅትም ሳይገባን [በቸርነቱ] ሒደን ገዳማቸውን ተመልከተናል:: አበው እንደሚሉት በደብረ ቆናጽል ላይ ያለው ደን የብዙ ሥውራን መኖሪያ ነው:: ለ፩ ሺህ ፭ መቶ ዓመታት ተከብሮ ቢኖርም በ፲፱፻፳፰ቱ የጣልያን ወረራ ግን እንዳልነበረ ሆኖ ነበር::

ዛሬም በቀድሞ ገጽታው አይደለም:: በገዳሙም ያገኘነው አንድ አባትን ነው::

ዐይናችን ግን ብዙ ነገሮችን ተመልክቶ አድንቋል:: እንደ ሰማነውም ዛሬም መካነ ቅዱሳን በመሆኑ የጽዮን አገልጋዮችም ማረፊያ ነው:: ጻድቁ አባ ሊቃኖስ ያረፉት ሕዳር ፳፰ ቀን ነው::

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

06 Dec, 21:35


🕊  † ቅዱስ ሰረባሞን ሰማዕት †  🕊

ቅዱሱ ሰው የዘመነ ሰማዕታት ፍሬ ሲሆን የቅዱሳን ሐዋርያት ዘመድ ነው:: እርሱ ተወልዶ ያደገው በ፫ኛው መቶ ክ/ዘመን በኢየሩሳሌም ነው:: የዘር ሐረጉ ሲቆጠርም በቀጥታ ከሊቀ ዲያቆናት ቅዱስ እስጢፋኖስና ከስምዖን ቀለዮዻ ይደርሳል::

በልጅነቱ ያደገው በሥርዓተ ኦሪት ነው:: ወጣት በሆነ ጊዜ ግን ፈጣሪ በሰጠው ሕሊና ተመራምሮ በክርስትና ለመኖር ወሰነ:: የወቅቱን የኢየሩሳሌም ኤዺስ ቆዾስ ሒዶ "አጥምቀኝ" ቢለው "ልጄ! ደስ ይለኝ ነበር:: ግን ወገኖችህ አይሁድ ይገድሉኛል" ሲል መለሰለት::

አክሎም "ወደ ግብጽ ሒደህ ግን ብትመጠመቅ የተሻለ ነው" ስላለው ከኢየሩሳሌም ግብጽ ገባ:: ግብጽ ደርሶ: ከቅዱስ ቴዎናስ [፲፮ኛ ፓትርያርክ] ክርስትናን ተምሮ ተጠመቀ::ቀጥሎም ወደ ገዳም ገብቶ ከመጀመሪያዎቹ መነኮሳት አንዱ ሆነ:: ምናኔን ከአባ እንጦንስ ተምሮ ስም አጠራሩ ከፍ አለ::

በተጋድሎውና በንጽሕናው ስለ ወደዱትም የኒቅዮስ ዻዻስ አደረጉት:: በዘመነ ሲመቱም ጣዖት አምልኮን ከአካባቢው አጥፍቷል:: ስለዚህ ፈንታም በዲዮቅልጢያኖስ ተይዞ በዚህች ቀን ተገድሏል:: ሲገደልም ልክ እንደ ቅድመ አያቱ ቅዱስ እስጢፋኖስ ፊቱ ያበራ ነበር::

አምላከ አበው ቅዱሳን መዓዛ ቅድስናቸውን
ያሳድርብን::ከበረከታቸውም ይክፈለን::

 🕊

[ ኅዳር ፳፰ [ 28 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]

፩. አባ ሊቃኖስ ጻድቅ [ከተስዓቱ ቅዱሳን]
፪. ቅዱስ ሰረባሞን ሰማዕት

[ ወርኀዊ የቅዱሳን በዓላት ]

፩. አማኑኤል ቸር አምላካችን
፪. ቅዱሳን አበው /አብርሃም: ይስሐቅና ያዕቆብ/
፫. ቅዱስ እንድራኒቆስና ሚስቱ ቅድስት አትናስያ
፬. ቅድስት ዓመተ ክክርስቶስ
፭. ቅዱስ ቴዎድሮስ ሮማዊ [ሰማዕት]

" ጻድቃን ምድርን ይወርሳሉ:: በእርስዋም ለዘለዓለም ይኖራሉ:: የጻድቅ አፍ ጥበብን ያስተምራል:: አንደበቱም ፍርድን ይናገራል:: የአምላኩ ሕግ በልቡ ውስጥ ነው::በእርምጃውም አይሰናከልም::" [መዝ.፴፮፥፳፱]

† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †

[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]


         †              †               †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖                   🕊                    💖

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

05 Dec, 17:11


💛
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬

🕊     ም ክ ረ     ቅ ዱ ሳ ን     🕊

▷ ❝ ለራስ የሚሰጥ ያልተገባ ክብር ! ❞


💖  አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ    ] 💖

[                        🕊                        ]
---------------------------------------------------

- ከንቱ ውዳሴን የሚያስወድድ ሰይጣን !

❝ እንግዲህ ምጽዋት ስታደርግ ፥ ግብዞች በሰው ዘንድ ሊከበሩ በምኩራብ በመንገድም እንደሚያደርጉ በፊትህ መለከት አታስነፋ ፤ እውነት እላችኋለሁ ፥ ዋጋቸውን ተቀብለዋል።

አንተ ግን ምጽዋት ስታደርግ ምጽዋትህ በስውር እንዲሆን ቀኝህ የምትሠራውን ግራህ አትወቅ ፤ በስውር የሚያይ አባትህም በግልጥ ይከፍልሃል።  ❞

[ ማቴ . ፮ ፥ ፪ ]


🕊                        💖                     🕊
                             👇

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

05 Dec, 15:27


                         †                        

  [      🕊   ፍኖተ ቅዱሳን    🕊      ]

[ የቅዱሳን አባቶቻችን የቅድስናና የተጋድሎ ሕይወት ]

▬▬▬▬▬▬   †    ▬▬▬▬▬▬

[  ሁል ጊዜ በትጋትና በጥንቃቄ መሆን እንደሚገባ !  ]

🕊

"  ሦስት የዲያብሎስ ኃይሎች .... ! "
........

- አበው እንዲህ አሉ ፡- ❝ ከማንኛውም ኃጢአት ፊት የሚሄዱት የዲያብሎስ ኃይሎች ሦስት ናቸው ፣ እነዚህም ዝንጋኤግዴለሽነት እና ምኞት ናቸው::

ዝንጋኤ [ መዘንጋት ] በሚመጣበት በማንኛውም ጊዜ ሁሉ ግዴለሽነትን ይወልዳል ፣ ከግዴለሽነት ደግሞ ምኞት ይከተላል ፣ ምኞት ደግሞ ሰውን እንዲወድቅ ያደርገዋል፡፡

ነፍስ ጠላትን በትጋት ነቅታ የምትጠብቅ ከሆነ ግን ለሰይጣን መግቢያ ቀዳዳ አትሰጠውም ፣ ካልተመኘች በክርስቶስ ቸርነት ከመውደቅ ትጠበቃለች። ❞


የአባቶቻችን ጸሎትና በረከት ይደርብን፡፡


†                       †                         †
💖                    🕊                     💖

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

05 Dec, 13:30


✟ እንዳልዘምር የሚከለክለኝ ምንድን ነው?



📎 https://t.me/+1rCQMEj6K2kzM2E8
📎 https://t.me/+1rCQMEj6K2kzM2E8

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

05 Dec, 12:49


                          †                          

[    🕊    ገ ድ ለ   ቅ ዱ ሳ ን   🕊     ]

▬▬▬▬▬▬   †    ▬▬▬▬▬▬

[ ቅዱስ መቃርዮስ ካስተማረው ትምህርት ]

[             ክፍል  ሃምሳ               ]

                         🕊  

    [            ስለ ትሕትና !           ]

🕊

❝  አባ ወቅሪስ እንዲህ አለ ፡- “ኣባ መቃርዮስን ልጎበኘው ሄድኩና ፦ 'በሕይወት ለመኖር የሚጠቅመኝን አንድ ቃል ንገረኝ' አልሁት፡፡ እርሱም ፦ 'ብነገርህ ሰምተኸኝ ታደርገዋለህ?' አለኝ፡፡ እኔም እምነቴና ፍቅሬ ከአንተ የተሰወሩ አይደሉም አልሁት::

አባ መቃርዮስም እንዲህ አለኝ ፦ 'በእውነት እኔ የመልካም ምግባር ሕይወት ይጎድለኛል ፤ አንተ ግን ጥሩ ነህ፡፡ ነገር ግን የዚህ ዓለም ትምህርት የሚያመጣውን ክብርና ዝና አውልቀህ ብትጥልና የቀራጩን ትሕትና ብትላበስ በሕይወት ትኖራለህ::'

እነዚህን ነገሮች በተናገረኝ ጊዜ ሃሳቦቼ ሁሉ በንነው ጠፉ ፣ ይቅርታውን በጠየቅሁትም ጊዜ በላዬ ላይ ከጸለየልኝ በኋላ አሰናበተኝ፡፡ የውስጤ ሃሳቦች ሁሉ ከእግዚአብሔር ሰው ከአባ መቃርዮስ የተሰወሩ እንዳልሆኑ ተረዳሁ ፣ ወደ እርሱ በሄድሁ ጊዜም ሁሉ እንዳዳምጠው ከሚያደርገኝ ከጸጋው የተነሣ እርዳለሁ ፣ ለእኔም ትሕትናን የምለማመድበት አጋጣሚ ነበር፡፡ ❞

የአባታችን የቅዱስ መቃርዮስ ምልጃና ጸሎቱ አይለየን፡፡

ይቆየን !


†                       †                         †
💖                    🕊                     💖

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

05 Dec, 02:44


🕊  † የናግራን ሰማዕታት †   🕊

በ፮ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ናግራን [የአሁኗ የመን] የክርስቲያኖች ሃገር ነበረች:: የሳባ ግዛትን የእኛ ነገሥታት ሲተዋት የተተካው ፊንሐስ ደግሞ ጨካኝ አይሁዳዊ ነበርና ናግራንን ሊያጠፋት ተመኘ:: ቀጥሎም "ሃገራችሁን ልጐብኝ" ብሎ በማታለል ገባ::

ወዲያውም ሕዝቡንና ካህናትን ሰብስቦ "ክርስቶስን ካዱ" አላቸው:: ጽኑ ክርስቲያኖች ግን "አይደረግም" አሉት:: እርሱም ሊያስፈራራቸው አስቦ ፬ ሺህ ያህል ካህናት: ዲያቆናትና ምሑራንን ጨፈጨፋቸው::

ይሕንን አድርጐ "አሁንሳ?" አላቸው:: ሕዝቡ ግን አሁንም "ከክርስቶስ ፍቅር የሚለየን የለም" አሉት:: [ሮሜ.፰፥፭] ጨካኙ ፊንሐስም እንደ ገና ከሕዝቡ መካከል ከ፬ ሺህ ፩ መቶ በላይ የሚሆኑትን ጨፈጨፈ::

ታላቁን ቅዱስ ሒሩትንም [የሕዝቡ መሪ ነው] ብዙ አሰቃይቶ ሰየፈው:: ሚስቱን ቅድስት ድማሕንም ፪ ሴት ልጆቿን ሰይፈው የልጆቿን ደም አጠጧት:: ከዚያም ሰየፏት:: ይሕንን የተመለከቱ የናግራን ክርስቲያኖች ግን ስለ መፍራት ፈንታ በፈቃዳቸው እየተሯሯጡ ወደ እሳትና ሰይፍ ተሽቀዳደሙ::

ከተማዋም እየነደደችና ደም እየፈሰሰባት ለ፵ ቀናት ቆየች:: ይሕንን የሰማው ቅዱሱ አፄ ካሌብም ደርሶ የተረፉትን ሲታደግ ፊንሐስን ከነ ወታደሮቹ አጥፍቶታል::

አምላከ አበው ወሰማዕት ጣዕመ ፍቅራቸውን: ክብራቸውን: ጸጋ በረከታቸውንም ይክፈለን::

🕊

[  † ኅዳር ፳፮ [ 26 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት   ]

፩. አቡነ ኢየሱስ ሞዐ ዘሐይቅ
፪. አቡነ ሃብተ ማርያም ንጹሕ
፫. ቅዱሳን ሰማዕታተ ናግራን
፬. ቅዱስ ሒሩት አረጋዊ
፭. ቅዱሳን ቢላርያኖስ: ኪልቅያና ታቱስብያ [ሰማዕታት]
፮. ቅዱስ ጐርጐርዮስ ዘደሴተ ሰንሲላ
፯. ቅድስት ዮስቴና ቡርክት

[    † ወርሐዊ በዓላት    ]

፩. ቅዱስ ቶማስ ሐዋርያ
፪. ቅዱስ አቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን

" እግዚአብሔር ፍርድን ይወድዳልና:: ቅዱሳኑንም አይጥላቸውምና:: ለዘለዓለምም ይጠብቃቸዋል . . . ጻድቃን ምድርን ይወርሳሉ:: በእርስዋም ለዘላለም ይኖራሉ:: የጻድቅ አፍ ጥበብን ያስተምራል:: አንደበቱም ፍርድን ይናገራል:: የአምላኩ ሕግ በልቡ ውስጥ ነው:: በእርምጃውም አይሰናከልም::" [መዝ.፴፮፥፳፰-፴፩]

† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †

[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]


         †              †               †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖                   🕊                    💖

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

05 Dec, 02:44


🕊

✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞

† ኅዳር ፳፮ [ 26 ] †


🕊 † አቡነ ኢየሱስ ሞዐ ዘሐይቅ † 🕊

እግዚአብሔር በ፲፫ኛው መቶ ክ/ዘ እነ አቡነ ኢየሱስ ሞዐን ባያስነሳ ኑሮ ምናልባትም ዛሬ የኢትዮዽያ ቤተ ክርስቲያንን በምናያት መንገድ ላናገኛት እንችል ነበር:: እውነተኛ አባቶቻችን ፈጽሞ ከሚቆረቁራቸው ነገር አንዱ የጻድቅና ሐዋርያዊ አባት አቡነ ኢየሱስ ሞዐ መዘንጋት ነው::

እርሳቸው ፍሬ ሃይማኖት ሆነው ከጽድቅ ፍሬአቸው አዕላፍ ቅዱሳንን ወልደው ሃገራችን በወንጌል ትምሕርትና በገዳማዊ ሕይወት እንድታሸበርቅ አድርገዋል:: እስኪ በዕለተ ዕረፍታቸው ስለ ጻድቁ ጥቂት ነገሮችን እናንሳ::

አቡነ ኢየሱስ ሞዐ ዘሐይቅ የተወለዱት ጐንደር: የድሮው ስማዳ [ዳኅና] አካባቢ ሲሆን ወላጆቻቸው ዘክርስቶስና እግዚእ ክብራ ይባላሉ:: የተወለዱት በ1210 ዓ/ም ነው:: ነገር ግን አንዳንድ ምንጮች በ1196 ዓ/ም ያደርጉታል::

ጻድቁ ከክርስቲያን ወላጆቻቸው ጋር እንደሚገባ አድገዋል:: በልጅነታቸው በብዛት ወላጆቻቸውን ያግዙ ነበር:: በትርፍ ጊዜአቸው ደግሞ ትምሕርተ ሃይማኖትንና ሥርዓቱን ያጠኑ ነበር:: በ1240 ዓ/ም ግን [ማለትም ፴ ዓመት ሲሞላቸው] ይሕቺን ዓለም ይተዋት ዘንድ አሰቡ::

አስበውም አልቀሩ ፈጣሪን እየለመኑ ደብረ ዳሕሞ ገቡ:: በወቅቱ ዳሞ የትምሕርት: የምናኔ ማዕከል ከመሆኑ ባሻገር የአቡነ አረጋዊ ፭ኛ የቆብ ልጅ ካልዕ ዮሐኒ ነበሩና የእርሳቸው ደቀ መዝሙር ሆኑ::

አቡነ ኢየሱስ ሞዐ በደብረ ዳሞ በነበራቸው ቆይታ ቀን ቀን ሲታዘዙ: ሲፈጩ: ውሃ ሲቀዱ ውለው ሌሊት እኩሉን በጸሎት በስግደትና የቀረውን ሰዓት ደግሞ ቅዱሳት መጻሕፍትን በመገልበጥ አሳለፉ::

በመጨረሻም ልብሰ ምንኩስናን ለበሱ:: ይህን ጊዜ ፴፯ ዓመታቸው ሲሆን ዘመኑም 1247 ዓ/ም ነው:: ወዲያውም በዳሞ ሳሉ መልአከ ሰላም ቅዱስ ገብርኤል ተገልጦ "ወደ ወሎ ሐይቅ ሒድ: ብዙ የምትሠራው አለና" አላቸው::

በአንዴም ከዳሞ [ትግራይ] ነጥቆ ሐይቅ እስጢፋኖስ [ወሎ] አደረሳቸው:: በዚያም ለ፯ ዓመታት በዼጥሮስ ወዻውሎስ ቤተ መቅደስ በተጋድሎ: በስብከተ ወንጌል: በማዕጠንትና ሐይቁ ውስጥ ሰጥሞ በመጸለይ ኖሩ::

ቅድስናቸውን የተመለከቱ አበውም በግድ አበ ምኔት አድርገው ሾሟቸው:: ይህ ነው እንግዲህ በኢትዮዽያ ቤተ ክርስቲያን ላይ ትልቁ መሠረት የተጣለበት አጋጣሚ:: ነገሩ እንዲህ ነው :-

ስም አጠራሯ የከፋ ዮዲት ጉዲት ለ፵ ዓመታት ሃገሪቱን እንዳልነበረች ብታደርጋት ክርስትና ተዳከመ:: ባዕድ አምልኮም ነገሠ:: አቡነ ኢየሱስ ሞዐ [ትርጉሙ ኢየሱስ ክርስቶስ አሸነፈ ማለት ነው] ደግሞ ሃይማኖታቸው የቀና ከ፰ መቶ በላይ ክርስቲያኖችን ሰበሰቡ::

በሃገሪቱ ትልቅና የመጀመሪያው ሊባል የሚችል ቤተ መጻሕፍት አደራጁ:: እነዚያን አርድእት በቅድስናና በትምሕርት አብስለው አመነኮሱና "ሒዱ! ሃገሪቱን ታበሩ ዘንድ ተጋደሉ" ብለው አሰናበቷቸው::

ክእነዚህ መካከልም ታላላቁን አቡነ ተክለ ሃይማኖትን: አቡነ በጸሎተ ሚካኤልን እና የሁዋላውን ፍሬ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫን መጥቀስ እንችላለን:: በዚህም ምክንያት ጻድቁ "ወላዴ አእላፍ ቅዱሳን - አእላፍ ቅዱሳንን የወለደ" ሲባሉ ይኖራሉ::

ጻድቁ ከዚህ በተጨማሪ የወቅቱን ንጉሥ አፄ ይኩኖ አምላክን በማስተማር ለሃገርና ለቤተ ክርስቲያን ጠቃሚ ሰው አድርገዋል:: በግላቸው ሐይቅ ውስጥ ገብተው ሲጸልዩ የብርሃን ምሰሶ ይወርድላቸው ነበር:: ሐይቅ እስጢፋኖስ ገዳምንም ከጠፋ ከ፫ መቶ ዓመታት በሁዋላ አቅንተዋል::

እንዲህ ለቤተ ክርስቲያን ሲተጉ: በተለይ በአበ ምኔትነት በቆዩባቸው ፵፭ ዓመታት ለዓይናቸው እንቅልፍን አላስመኙትም:: ጐድናቸውም ከምኝታ ጋር ተገናኝቶ አያውቅም::
"እንዘ የኀሊ ዘበሰማያት ዐስቦ::
መጠነ ዓመታት ሃምሳ ኢሰከበ በገቦ::" እንዲል::

ከዚህ በሁዋላ የሚያርፉበት ዕለት ቢደርስ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወርዶ ቃል ኪዳን ሰጥቷቸዋል:: በተወለዱ በ፹፪ [82] ዓመታቸው [በ፹፮ [86] ዓመታቸው የሚልም አለ] በ1282 ዓ/ም በዕለተ ሰንበት ዐርፈው ተቀብረዋል:: "ጻድቁ ስም አጠራራቸው እጅግ የከበረ ነው!!"


🕊 † አቡነ ሃብተ ማርያም ጻድቅ †  🕊

እኒህ ጻድቅ ደግሞ የሃገራችን ኮከበ ገዳም ናቸው:: "ጽድቅና ትሩፋት እንደ ሃብተ ማርያም" እንዲሉ አበው:: ባሕር ከሆነ ጣዕመ ሕይወታቸው ጥቂቱን ለበረከት እንካፈል::

ጻድቁ መካነ ሙላዳቸው ሽዋ [የራውዕይ] ውስጥ ሲሆን አባታቸው ፍሬ ቡሩክ: እናታቸው ደግሞ ቅድስት ዮስቴና ትባላለች:: በተለይ ቅድስት ዮስቴና እጅግ ደመ ግቡ: ምጽዋትን ወዳጅ: ቡርክት ሴት ነበረች:: እንዲያውም ከጻድቁ መወለድ በፊት መንና ጭው ካለ በርሃ ገብታ ነበር::

ግን የበቃ ግኁስ አግኝቷት "ከማሕጸንሽ ደግ የሥላሴ ባርያ አለና ተመለሽ" ብሏት እንደ ገና ተመልሳለች:: ጻድቁን ወልዳ አሳድጋም እንደ ገና መንና በተጋድሎ ኑራ ፯ አክሊላትን ተቀብላ ዐርፋለች::

ወደ ጻድቁ ዜና ሕይወት ስንመለስ አቡነ ሃብተ ማርያም ገና ሕጻን እያሉ ከእናታቸው ጋር ቆመው ሲያስቀድሱ "እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ" ሲባል ይሰማሉ:: ይሕችን ጸሎት በሕጻን አንደበታቸው ይዘው ሌሊት ሌሊት እየተነሱ "ማረን እባክህን?" እያሉ ይሰግዱ ነበር::

የ፭ ዓመት ሕጻን እንዲህ ሲያደርግ ማየቱ በእውነት ይደንቃል:: ትንሽ ከፍ ብለው በእረኝነት ሳሉም ፍጹም ተሐራሚና ጸዋሚ ነበሩ:: ጸጋው ስለ በዛላቸውም ልጅ ሆነው ብዙ ተአምራትን ሰርተዋል:: የፈጣሪውን ስም ያቃለውን አንድ እረኛም በዓየር ላይ ሰቅለው አውለውታል::

ከዚያ ግን ለአካለ መጠን ሲደርሱ ወደ ት/ቤት ገብተው: መጻሕፍትንም አጥንተው መንነዋል:: በአባ መልከ ጼዴቅ እጅ ከመነኮሱ በሁዋላ የሠሩትን ትሩፋትና የነበራቸውን ተጋድሎ ግን የኔ ብጤ ደካማ ሰው ሊዘረዝረው አይችልም::

- ባሕር ውስጥ ሰጥመው ፭ መቶ ጊዜ ይሰግዳሉ::
- በየቀኑ ፬ቱን ወንጌልና 150 መዝሙረ ዳዊትን ይጸልያሉ:: [መጽሐፍ ቅዱስን ማንበብ ታላቅ ጸሎት ነው]
- በ፵ ቀናት: ቀጥሎም በ፹ ቀን አንዴ ብቻ ይመገባሉ::
- ምግባቸው ደግሞ ሣርና ቅጠል ብቻ ነው::

- በየዕለቱ ያለ ማስታጐል ማዕጠንት ያሳርጋሉ:: [ካህን ናቸውና]
- ዘወትር በንጽሕና ቅዱስ ሥጋውን ይበላሉ: ክቡር ደሙን ይጠጣሉ::
- በፍጹም በልባቸው ውስጥ ቂምን: መከፋትን አላሳደሩም::

በእነዚህና በሌሎች ትሩፋቶቻቸው ደስ የተሰኘ ጌታም ለጻድቁ የእሳትና የብርሃን ሠረገላን ሰጥቷቸው በዚያ እየበረሩ ኢየሩሳሌም ይሔዱ ነበር:: ከብዙ የተጋድሎ ዘመናት በሁዋላም የክብር ባለቤት መድኃኒታችን ክርስቶስ አዕላፍ መላእክትን አስከተትሎ መጥቶ አላቸው::

"ስለ እኔ ረሃብና ጥምን ስለ ታገስክ : ስለ ምናኔሕ : ስለ ተባረከ ምንኩስናህ : ስለ ንጹሕ ድንግልናህ : ቂምና በቀልን ስላለመያዝህ : ስለ ንጹሕ ክህነትህና ማዕጠንትህ : ቅዱስ ወንጌልን በፍቅር ስለ ማንበብህ ፯ አክሊላትን እሰጥሃለሁ::"

"በሰማይም ከመጥምቁ ዮሐንስ ጐን: ፭ መቶ የእንቁ ምሰሶዎች ያሉበትን አዳራሽ ሰጥቼሃለሁ:: በስምህ የሚለምኑ: በቃል ኪዳንህ የሚማጸኑትንም ሁሉ እንድምርልህ 'አማንየ! በርእስየ!' ብዬሃለሁ" አላቸው::

ቅዱሳን መላእክትም "ሃብተ ማርያም ወንድማችን" ሲሉ አቀፏቸው:: ጌታ ግን በዚያች ሰዓት አንድም ሦስትም ሆኖ ታያቸውና አቅፎ 3 ጊዜ ሳማቸው:: ከፍቅሩ ጽናትም የተነሳ ነፍሳቸው ከሥጋቸው ተለየች:: በዝማሬም ወሰዷት::"

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

04 Dec, 16:41


💛
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬

🕊     ም ክ ረ     ቅ ዱ ሳ ን     🕊

▷   ❝   የጭካኔ  ሕይወት  !   ❞


💖  አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ    ] 💖

[                        🕊                        ]
---------------------------------------------------

- በሰዎች ላይ የሚፈጸም ጭካኔ
- በእግዚአብሔር ላይ የሚፈጸም ጭካኔ


❝ ዛሬ ድምጹን ብትሰሙት ፥ በማስመረር እንደሆነ ልባችሁን እልከኛ አታድርጉ። ሰምተው ያስመረሩት እነማን ነበሩ ? ❞

[ ዕብ . ፫ ፥ ፲፭ ]


🕊                        💖                     🕊
                             👇

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

04 Dec, 15:13


                         †                        

  [      🕊   ፍኖተ ቅዱሳን    🕊      ]

[ የቅዱሳን አባቶቻችን የቅድስናና የተጋድሎ ሕይወት ]

▬▬▬▬▬▬   †    ▬▬▬▬▬▬

[  ሁል ጊዜ በትጋትና በጥንቃቄ መሆን እንደሚገባ !  ]

🕊

❝  አይ አይደለም ፣ ዛሬ ንስሐ እገባለሁ ! ❞
........

- አንድ አረጋዊ እንዲህ አለ ፦ " ወደ ንጉሥ የቀረበን ሰው ጠላቱ ሊያገኘውና ሊጎዳው እንደማይችለው ሁሉ ወደ እግዚአብሔር የቀረበን ሰውም ዲያብሎስ ምንም ሊያደርገው አይችልም። ነገር ግን ብዙ ጊዜ ራሳችንን ከፍ ስለምናደርግና ድካማችንን ስለማናውቅ ጠላት እኛን ወደ ታች ለመጣልና ወደ አሳፋሪ ነውሮችም ለማውረድ አይቸገርም።


- አንድ አባት ክፉ ሃሳቦች በኅሊናው ፦ " ዛሬ ተዝናና ፣ ደስም ይበልህ ፣ ነገ ንስሐ ትገባለህ" ሲሉት እርሱ ግን መልሶ ፦ " አይ አይደለም ፣ ዛሬ ንስሐ እገባለሁ ፣ ነገ ደግሞ የእግዚአብሔር ፈቃድ ይሁን" አለ።


የአባቶቻችን ጸሎትና በረከት ይደርብን፡፡


†                       †                         †
💖                    🕊                     💖

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

15 Nov, 09:50


❤️ የማንን መዝሙር ማዳመጥ ይፈልጋሉ 👇

👤 ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ

👤 ሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ

👤 ሊቀ መዘምራን . ኪነጥበብ ወ/ቂርቆስ

👤 ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ

👤 ቀሲስ እንግዳወርቅ በቀለ

👤 ዘማሪ ዲያቆን አቤል መክብብ

👤 ዘማሪት ምርትነሽ ጥላሁን

👤 ዘማሪ| በሱፍቃድ አንድአርጋቸው

👤 ዘማሪት ሲስተር ሊዲያ ታደሰ

👤 ዘማሪ ዳግማዊ ደርቤ

👤 ዘማሪት ፋንቱ ወልዴ

👤 ዘማሪ ዲያቆን ብርሃኑ በቀለ

👤 ዘማሪት አዜብ ከበደ

👤 ዘማሪ ዲያቆን ሙሉቀን ከበደ

👤 ዘማሪት ፋሲካ ድንቁ

👤 ዘማሪት ሰላማዊት በርታ

🔗የሁሉንም ዘማሪዎች ለማግኘት🎚
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

15 Nov, 08:52


✥● የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አባትና እናት ማን ይባላሉ❓️

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

14 Nov, 21:36


የእመ ብርሃንን ስዕለ አድኅኖ በአበባ ተከባ: በብርሃንም ተውጣ ተመለከቱ:: በዚህ ምክንያትም ዛሬ በጣፋጭነቱ የሚታወቀውን ማኅሌተ ጽጌን ፻፶ ዓርኬ አድርግው ደረሱ:: እስከ ዕለተ ዕረፍታቸውም እመቤታችንና ልጇን በገዳማቸው [ወለቃ አካባቢ የሚገኝ] ሲያመሰግኑ ኑረዋል:: ጻድቁ ያረፉት ጥቅምት ፳፯ ሲሆን ዛሬ የቃል ኪዳን በዓላቸው ነው::

ቸሩ መድኃኔ ዓለም የድንግል እናቱን ስደት አስቦ ከመንግስተ ሰማያት ስደት ይሠውረን:: ከስደቱ በረከትም ያድለን::

🕊

[  † ኅዳር ፮ [ 6 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት  ]

፩. ቅድስት ደብረ ቁስቁዋም [ሚጠታ ለማርያም]
፪. ቅዱስ ዮሴፍ አረጋዊ
፫. ቅድስት ሰሎሜ ቡርክት
፬. ቅዱስ ዮሳ [ ወልደ ዮሴፍ ]
፭. ቅዱስ ቴዎፍሎስ ሊቅ
፮. አባ ጽጌ ድንግል ዘወለቃ
፯. አባ ፊልክስ ዘሮሜ

[  † ወርኀዊ የቅዱሳን በዓላት ]

፩. ቅድስት ደብረ ቁስቁዋም
፪. አባታችን አዳምና እናታችን ሔዋን
፫. አባታችን ኖኅና እናታችን ሐይከል
፬. ቅዱስ ኤልያስ ነቢይ
፭. ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሣርያ
፮. ቅዱስ ዮሴፍ አረጋዊ
፯. ቅድስት ሰሎሜ
፰. አባ አርከ ሥሉስ
፱. አባ ጽጌ ድንግል
፲. ቅድስት አርሴማ ድንግል

" ዘንዶውም ሴቲቱ በወለደች ጊዜ ሕጻኗን እንዲበላ ልትወልድ ባላት ሴት ፊት ቆመ:: አሕዛብንም ሁሉ በብረት ዘንግ ይገዛቸው ዘንድ ያለውን ልጅ: ወንድ ልጅ ወለደች:: ልጇም ወደ እግዚአብሔርና ወደ ዙፋኑ ተነጠቀ:: ሴቲቱም ሺህ ከሁለት መቶ ስድሳ ቀን በዚያ እንዲመግቧት በእግዚአብሔር ተዘጋጅቶላት ወደ ነበረው ሥፍራ ወደ በረሃ ሸሸች::" [ራዕይ.፲፪፥፬-፯]

† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †

[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]

         †              †               †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖                   🕊                    💖

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

14 Nov, 21:36


🕊

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡

🕊  †  ኅዳር ፮ [ 6 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት  †  🕊


🌹በዓለ ደብረ ቁስቁዋም🌹

የአርያም ንግሥት: የፍጥረታት ሁሉ እመቤት ድንግል ማርያም የባሕርይ አምላክ ልጇን አዝላ ወደ ምድረ ግብፅ ወርዳለች:: በወንጌል ላይ [ማቴ.፪፥፩-፲፰] እንደተጻፈው ጌታችን በተወለደ በ፪ ዓመቱ የጥበብ ሰዎች [ሰብአ ሰገል] ወደ ቤተ ልሔም መጥተው ሰግደውለት ወርቅ: እጣን: ከርቤውን ገበሩ: አገቡለት::

ንጉሥ ተወልዷል መባሉን የሰማ ሔሮድስ መቶ አርባ አራት ሺህ [144,000] ሕጻናትን ሲፈጅ በቅዱስ ገብርኤል ትዕዛዝ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ፩ አምላክ ልጇን አዝላ: በአንዲት አህያ ጥቂት ስንቅ ቁዋጥራ: ከዮሴፍና ከሰሎሜ ጋር ስደት ወጣች::

ከገሊላ ተነስታ በጭንቅ: በመከራ: በረሃብና በጥም: በሐዘንና በድካም: በላበትና በእንባ ተጉዛ በዚሕች ቀን ምድረ ግብፅ ገብታለች::

- የአምላክ እናቱ እሳትን አዝላ በብርድ ተንገላታለች::
- ለእኛ የሕይወት እንጀራን ተሸክማ እርሷ ተራበች::
- የሕይወትን ውሃ ተሸክማ ተጠማች::
- የሕይወት ልብስን ተሸክማ ተራቆተች::
- የሕይወት ፍስሐን ተሸክማ አዘነች::
- እመ አምላክ ተራበች: ተጠማች: ታረዘች: ደከመች: አዘነች: አለቀሰች: እግሯ ደማ: ተንገላታች::

ለሚገባው ይሕ ሁሉ የተደረገው ለእኛ ድኅነት ነው:: በእውነት ይህንን እያወቀ ለድንግል ማርያም ክብር የማይሰጥ ሰይጣን ብቻ ነው:: አራዊት: ዕፀዋትና ድንጋዮች እንኳ ለአመላክ እናት ክብር ይሰጣሉ::

አረጋዊው ቅዱስ ዮሴፍና ቅድስት ሰሎሜ ደግሞ የክብር ክብር ይገባቸዋል:: ከአምላክ እናት ከድንግል ማርያምና ከቸር ልጇ ጋር መከራ መቀበልን መርጠዋልና::

"መድኃኔ ዓለም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለምን ተሰደደ? ለምን ስደቱን ወደ ግብፅና ኢትዮዽያ አደረገ?"

፩. ትንቢቱን ይፈጽም ዘንድ:: በፈጣን ደመና ወደ ግብፅ እንደሚወርድ ተነግሯልና [ኢሳ.፲፱፥፩, ዕን.፫፥፯]

፪. ምሳሌውን ለመፈጸም:: የሥጋ አባቶቹ እነ አብርሃም: ያዕቆብ [እሥራኤል] : ኤርምያስ ወደዚያው ተሰደዋልና::

፫. ከግብፅ ጣዖት አምልኮን ያጠፋ ዘንድ:: [ኢሳ.፲፱፥፩]

፬. የግብፅና የኢትዮዽያ ገዳማትን ይቀድስ ዘንድ::

፭. ሰው መሆኑ በአማን እንጂ ምትሐት እንዳልሆነ ለማጠየቅ:: [ሰው ባይሆን ኑሮ አይሰደድም ነበር:: ሔሮድስ ቢያገኘው ደግሞ ሊገድለው አይችልም:: ያለ ፈቃዱና ያለ ዕለተ ዐርብ ደሙ አይፈስምና::]

፮. ስደትን ለሰማዕታት ባርኮ ለመስጠት:: እና

፯. የአዳምን ስደት በስደቱ ለመካስ ነው::

እመ ብርሃን ድንግል ማርያም ለ፫ ዓመታት ከ፮ ወራት [ወይም ለ፵፪ ወራት] በስደት የቆየችባቸው ቦታዎች አሉ:: ድንግል ማርያም ከርጉም ሔሮድስ ስትሸሽ መጀመሪያ የሔደችው ከገሊላ ወደ ሶርያ ደንበር [ደብረ ሊባኖስ] ነው::

በዚያ የሸሸጋት ቅዱስ ጊጋር መስፍኑ በሔሮድስ ሲገደል ወደ ምድረ ግብጽ ወረደች:: በግብጽም ለብዙ ጊዜ ከአንዱ ወደ ሌላው ስትሸሽ ቆየች::
"እንዘ ከመ በግዕት ግድፍት አመ ሳኮይኪ ውስተ ምድረ በዳ" እንዲል:: [እሴብሕ ጸጋኪ]

ቀጥላም በሰሜኑ የሃገራችን ክፍል ገብታ ደብረ ቢዘን ላይ [አሁን ኤርትራ ውስጥ ነው] ዐረፈች:: ከደብረ ቢዘን በደብረ ዳሙ: አክሱም: ደብር ዓባይ: ዋልድባ አድርጋ እየባረከች ጣና ደርሳለች:: በጣና ገዳማትም: በተለይ በጣና ቂርቆስ ለ፻ ቀናት ቆይታ ቀጥታ በጐጃም ወደ ሽዋ ሒዳ ደብረ ሊባኖስን ቀድሳለች::

ቀጥላም እስከ ደብረ ወገግና ደብረ ሐዘሎ ደርሳለች:: በእግሯ ያልደረሰችባቸውን የሃገራችን ክፍሎች በደመና ተጭና ዐይታ ባርካቸዋለች:: ከልጇም በአሥራትነት ተቀብላለች:: ሔሮድስ መሞቱን መልአከ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል የነገራትም እዚሁ ኢትደዮዽያ ውስጥ መሆኑን ትውፊት ያሳያል::

እመ ብርሃንም ከሃገራችን ሰዎች [ከሰብአ ኦፌር] የተቀበለችውን ስንቅና ስጦታ በ፭ ግመሎች ጭና ከቅዱሳኑ ዮሴፍና ሰሎሜ ጋር በዚህች ቀን ደብረ ቁስቁዋም ውስጥ ገብተው ከድካም ዐርፈዋል:: ሐሴትንም አድርገዋል::

ዳግመኛም ከክርስቶስ ስደት ፬፻ ዓመታት በኋላ በዚህች ቀን የግብጿ ደብረ ቁስቁዋም ታንጻ ተቀድሳለች:: የቅዱሳን ማደሪያም ሁናለች:: ይህስ እንደ ምን ነው ቢሉ:-

ለስም አጠራሩ ጌትነት ይሁንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በ፫፻፺ዎቹ አካባቢ ድንግል እናቱን: ቅዱሳን ሐዋርያትን: አእላፍ መላእክትን: ጻድቃን ሰማዕታትን: አስከትሎ ወረደ::

የወቅቱ የግብጽ ፓትርያርክ ቅዱስ ቴዎፍሎስና ሊቁ ቅዱስ ቄርሎስ ቤተ ክርስቲያኑን አንጸው: ሕዝቡን ሰብስበው ይጠብቁት ነበርና ወርዶ ቀድሶላቸው ታላቅ ደስታ ሁኗል::

ስደቷን መሳተፍን ሽተው አበው :-

"እመ ኀሎኩ በጐይዮቱ ውእተ መዋዕለ:
እምተመነይኩ ኪያሁ በዘባንየ ሐዚለ:
ወበልሳንየ እልሐስ ዘአእጋሪሁ ጸበለ:
ወከመ አዕርፍ ምስሌሁ በትረ ዮሴፍ ኀበ ተተክለ:
ለወልደ ማርያም በሐጸ ፍቅሩ ልቡናየ ቆስለ::" እንዳሉ:: [ሰቆቃወ ድንግል]
እኛም እመ ብርሃንን ልንሻት ያስፈልገናል::

ይህቺ ቀን ለእኛ ለክርስቲያኖች ሁሉ እጅግ የደስታ ቀን ነውና ሐሴትን እናድርግ:: የሰማይና የምድር ጌታ ለእኛ ሲል ካደረገው ስደቱ በዚህች ቀን ተመልሷልና:: ስደቷን አስበን ካዘንን: መመለሷን አስበን ደስ ልንሰኝ ይገባልና::

"አብርሒ አብርሒ ናዝሬት ሃገሩ:
ንጉሥኪ በጽሐ ዘምስለ ማርያም መጾሩ" ልንልም ይገባል::


+" 🌷አባ ጽጌ ድንግል ዘወለቃ 🌷 "+

ጻድቁ አቡነ ጽጌ ድንግል በ፲፬ኛው መቶ ክ/ዘመን የነበሩ ሊቅና ገዳማዊ ናቸው:: የዘር ሐረጋቸው ምንም ከቤተ እሥራኤል እንደሚመዘዝ ቢታወቅም ኢትዮዽያዊ ናቸው:: አስቀድመው አይሁዳዊ በመሆናቸው ኢየሱስ ክርስቶስንና ድንግል እናቱን አያምኑም ነበር::

የተማሩትም ብሉይ ኪዳንን ብቻ ነበር:: በጊዜውም "ክርስቶስ አልተወለደም: ትክክለኛው እምነት ይሁዲ ነው" እያሉ ከክርስቲያኖች ጋር ይከራከሩ ነበሩ:: አንድ ቀን ግን ከታላቁ ሊቅና ገዳማዊ አቡነ ዜና ማርቆስ ጋር ተገናኙ::

ጻድቁን ስላልቻሏቸው ተሸንፈው በክርስቶስ አመኑ:: አቡነ ዜና ማርቆስም አስተምረው ክርስትና ሲያነሷቸው /ሲያጠምቁዋቸው 'ጽጌ ድንግል' አሏቸው:: ሲመነኩሱም 'ጽጌ ብርሃን' ተብለዋል:: ቀጥለውም በጾምና በጸሎት ሲጋደሉ: እመቤታችንንም ሲለምኑ ምሥጢር ተገለጠላቸው::

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

14 Nov, 16:45


🔔


[  እ ና ታ ች ን ቤ ተ ክ ር ስ ቲ ያ ን !  ]


†               †                 †


በሐሰተኛ መንፈስና አሠራር ቅድስት ቤተክርስቲያንን እየፈተኑና ምዕመናንን እያጎሳቆሉ ስለሚገኙ ሐሰተኛ አጥማቂያን እግዚአብሔር ቢፈቅድና ብንኖር ተከታታይ መርሐ-ግብር ከቀጣይ ሳምንት ጀምሮ የሚቀርብ ይሆናል !

ይከታተሉ !



                †       †       †
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

14 Nov, 16:00


                           †                           

      [   🕊 ድንግል ሆይ ፦  🕊    ]  

🌼▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬🌼

🌹    ተፈጸመ ናሁ ማሕሌተ ጽጌ     🌹

🕊

❝ ሕብረ ሐመልሚል ቀይሕ ወጸአድዒድ አርአያ ኰሰኰስ ዘብሩር ተአምርኪ ንጹሕ በአምሳለ ወርቅ ግቡር ተፈጸመ ናሁ ማሕሌተ ጽጌ ሥሙር አስምኪ ቦቱ ንግሥተ ሰማያት ወምድር ከመ በሕጽንኪ ያሰምክ ፍቁር ❞


[ የሚያብረቀርቅ ቀይና ነጭ ቀለም ያለው አርአያው የብር ዝንጒርጒር ጠቃጠቆ የኾነ ንጹሕ ተአምርሽ በወርቅ አምሳል የተሠራ ነው ፤ እነሆ የተወደደ [ መልካም ] ማሕሌተ ጽጌ ደረሰ ተፈጸመ ፤ የሰማይና የምድር ንግሥት ማርያም ሆይ የተወደደ ልጅሽ በጒያሽ [ በዕቅፍሽ ] እንዲጠጋ [ እንዲደገፍ ፣ እንዲንተራስ ] በርሱ ዐማጽኚ፡፡ ]

[ አባ ጽጌ ድንግል [ ማህሌተ ጽጌ ] ]

🕊

❝ እመቤቴ ማርያም ሆይ በመገዛት አመሰግንሻለሁ:: በመማጸንም አገንሻለሁ። አንቺ የሊቀ ካህናቱ መሠውያ ሁነሻልና ልጅሽም በእውነት ለሚመገበው የሕይወት ምግብ ነው::

ሕፃንሽ ከልብ ለሚያዳምጠው ምክሩ ጣፋጭ ነው። ቁጣ የሌለብሽ ርኅሩኅ ሆይ ወደ አንቺ እጸልያለሁ ፤ በመማለድም ወደ አንቺ እለምናለሁ:: በኵርሽ /ልጅሽ ክርስቶስ/ አካሔዴን ወደ ጽድቅ መንገድ ያቅና ስምሽን በማስታወስ በጠራሁት ጊዜም በእውነት ይነጋግረኝ።

አንቺም ለዚህ ለአገልጋይ የሚጠቅመውን ስጠው በሥልጣንህ እርዳው ፤ በእጅህም አጽናው ፤ ከሚያስፈራው የሕይወት ጠላቱም መፈራትን አጐናጽፈው በይው:: ለዘለዓለሙ አሜን:: ❞


" ሱላማጢስ ሆይ ተመለሺ ! " [መሓ. ፯:፩]


💖                     🕊                    💖

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

14 Nov, 13:33


ኦርቶዶክሳዊ ቻናል/ግሩፕ ያላችሁ ከ7k በላይ Promotion ውስጥ መግባት የምትፈልጉ ሳያመልጣችሁ


    👇👇👇
@Maryamn_27

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

14 Nov, 13:08


                          †                          

[    🕊    ገ ድ ለ   ቅ ዱ ሳ ን   🕊     ]

▬▬▬▬▬▬   †    ▬▬▬▬▬▬

[  የአባታችን የቅዱስ መቃርዮስ የተጋድሎ ሕይወቱና ትምህርቱ  ]

[         ክፍል  ሠላሳ ስምንት          ]

💛

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡

[  የአንድን ባለ ሥልጣን ልጅ ከበሽታዋ እንደ ፈወሳት  !   ]

                         🕊                         

❝ ስለ አባ መቃርዮስ እንዲህ ተባለ ፦ “ የአንጾኪያ ባለ ሥልጣን [ የንጉሥ አማካሪ ] የሆነ አጋቶኒከስ የተባለ ሰው አባ መቃርዮስ በጌታችን በመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሽተኞችን የመፈወስ ታላቅ ስጦታ እንዳለው በሰማ ጊዜ በርኲስ መንፈስ ተይዛ የምትሰቃየውን ልጁን ይጸልይላት ዘንድ ወደ አባ መቃርዮስ ላካት:: በዚህም ቀን አባ መቃርዮስ ማታ ላይ ኅብስት ሊቀምስ ሳለ ከደቀ መዛሙርቱ አንዱ መጣና “በልሳነ ዮናኒ የሚናገር አንድ ሰው መጥቷል ፣ እርሱም አለባበሱ የመኳንንት አለባበስ ይመስላል፡፡ ከእርሱም ጋር አሳዛኝና የተጎዳ የሚመስል ሕፃን አብሮት አለ፡፡ እነርሱም ከአንተ ይባረኩ ዘንድ ይፈልጋሉ” አለው::

እርሱም ፦ “ወደ እኔ እንዲገቡ እዘዛቸው” አለው፡፡ እነርሱም ሲገቡ ቅዱስ መቃርዮስ ተቀበላቸው ፣ ግብራቸውን ሁሉ በመንፈስ ቅዱስ አወቀው፡፡ ረዱን ፦ “በሰላም ሂድ” ካለው በኋላ አብረው ተቀምጠው ሳለ ያን ሰው ፦ “ምን ትሻለህ?” አለው:: እርሱም ፦ “ይህ ሕፃን ልጄ ነው ፣ በእርሱ ላይ የሰይጣናት አለቃ አለበት ፣ ራሱ ሲናገር እኔ ከሰይጣናት ሠራዊት አለቃ ነኝ ይላል፡፡ በየጊዜው ይጥለዋል ፣ ያሰቃየዋልም፡፡ በሀገራችን ወዳሉ ብዙ ቅዱሳን ወስደነው ነበር ፣ ያድኑት ዘንድ ግን አልቻሉም፡፡ ከልብሱ ይራቆታል ፣ ሰውነቱንም ይነክሳል ፣ ስለዚህም ይህን ጨርቅ አለበስሁት አለው::”

ቅዱስ አባታችን መቃርስም ፦ “ይህች ልጅ ሴት ስትሆን ወደዚህ ገዳም ይዘሃት ትገባ ዘንድ እንዴት ደፈርክ ? ይህም ብቻ አልበቃህም ፣ ጸጋ መንፈስ ቅዱስን ዋሽተሃልና ፤ እርሷ የአንጾኪያው ገዥ ልጅ ስትሆን ከአንተ ጋር በስውር ወደዚህ አመጣሃት” አለው:: ያም ሰው ይህን በሰማ ጊዜ ፈራ ፣ በቅዱስ መቃርዮስ እግር ፊትም መሬት ላይ ወደቀ፡፡ ቅዱስ መቃርዮስም ፦ “ተነሥ አይዞህ አትፍራ ፣ እንዳትዋሽም ተጠንቀቅ” አለው:: እርሱም ፦ “ጌታዬና አባቴ ሆይ ይቅር ትለኝ ዘንድ እለምንሃለሁ ፣ እኔ ምስኪን የሆንኩ የዚህች ልጅ አገልጋይዋ ነኝና ፣ እንደ ታዘዝኩ እንዲሁ አደረግሁ ፤ እኔ ለእግዚአብሔርና ለጌቶቼ ታዛዥ ነኝና" አለው:: ቅዱስ መቃርዮስም ዘይት ያመጡለት ዘንድ አዘዘ ፤ በዘይቱም ላይ ጸልዮ በልጅቷ ጆሮ ዙሪያ ዘይቱን በመስቀል ምልክት እያደረገ ቀባት ፣ ያን ጊዜም ዳነች፡፡

ቅዱስ መቃርዮስም ፦ “ተነሥና ወደ ሀገርህ ሂድ ፣ አብረውህ ካሉት ከወንዶችና ከሴቶች ብዛት የተነሳ ይህን ሌሊት በዚህ ገዳም አትደር፡፡ ወደ ግብጽ ሄዳችሁ በቅርብ በምታገኙት ቦታ እደሩ፡፡ የልጅቷ ወላጆች በቅዱሳን ላይ ስላላቸው እምነትና በቀናች ሃይማኖት ውስጥ በመሆናቸው እነሆ እግዚአብሔር መዳንን ሰጥቷታል” አለው፡፡ ያን ጊዜም ያ ሰው ከበአት ርቀው ከቆሙት ከዚያች ልጅ አገልጋዮች ውስጥ አንዱን ጠራው:: እርሱም በውስጡ አራት መቶ ዲናር ያለው ሳጥን ወደ ቅዱስ መቃርዮስ አመጣለት፡፡

ያ ሰውም ፦ “አባቴ ሆይ ፣ ይህን መጠኑ አራት መቶ ዲናር የሆነ የጌታዬን በረከት ትቀበል ዘንድና ገንዘቡን ለአኃው ለሚያስፈልጋቸው ነገሮችና ቅድስናህ ለወደደው ነገር ያውለው ዘንድ እለምንሃለሁ" አለው:: ቅዱስ መቃርዮስም እንዲህ አለው ፡- “የእግዚአብሔር ጸጋ በገንዘብ በብርና በወርቅ ፈጽሞ አይገኝም ፤ እኒህ በዚህ ያሉ ድሆች የሆኑ መነኰሳትም ወርቅና ብር አይፈልጉም ፣ እነርሱ ወደዚህ የመጡት ስለ እግዚአብሔር ነውና እምነታቸውም በእርሱ ላይ ነውና ፣ እርሱም በሚያስፈልጋቸው ነገር ሁሉ ያስብላቸዋል፡፡ አንተም ገንዘብህን ያዝና ወደ ላከህ ሰው በሰላም ሂድ፡፡” ይህም ሰው ከተባረከ በኋላ ቅዱስ መቃርዮስ እንዳዘዘው ያን ሌሊት በዚያ ገዳም ሳያድር ወጥቶ ወደ ግብጽ ሄደ፡፡ እናት አባቷም በመቃርስ ጸሎትና አማላጅነት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያደረገውን ተአምር በተመለከቱ ጊዜ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን አመሰገኑት፡፡ ❞

የአባታችን የቅዱስ መቃርዮስ ምልጃና ጸሎቱ አይለየን፡፡

ይቆየን !


†                       †                         †
💖                    🕊                     💖

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

14 Nov, 07:09


🕊  💖  ▬▬    †    ▬▬  💖  🕊

[ ተዋሕዶ ፍጽምት የቅዱሳን ሃይማኖት ]
▬▬▬▬▬▬   †    ▬▬▬▬▬▬

[   ❝  ከአንቺ ግን .... !  ❞  ]

🕊

❝ እግዚአብሔር ዐሥሩን ቃላት በእጁ የጻፈባቸውን ሁለቱን ጽላት በደብረ ሲና ሰጠ ከአንቺም እግዚአብሔር ቅዱስ ጽላትን ፈጠረ ይኸውም ሥጋው ነው። [ዘፀአ.፴፬፥፳፰-፴]

ከደብረ ሲና እሳት ጨለማ መጣ ፤ ከአንቺ ግን ሰው የሆነ አምላክ ተገኘልን፡፡

በደብረ ሲና በአይሁድ ላይ ድንጋፄ ሀውክ ተደረገ ፤ በአንቺም በአይሁድ በሄሮድስ በዲያብሎስና በሠራዊቱ ላይ ጽኑ ድንጋፄ ተደረገ፡፡ [ዘፀአ.፳፥፲፰ ፡፡ ዕብ.፲፪፥፲፱]  ❞

[      ቅዱስ ኤፍሬም      ]



†                       †                         †
💖                    🕊                     💖

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

04 Nov, 16:56


                          †                          

💖  [   ጋብቻ ቅዱስ !  ] 💖


[ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያንን እንደ ወደዳት ! ]

🕊

❝ ዳሩ ግን ቤተ ክርስቲያን ለክርስቶስ እንደምትገዛ እንዲሁ ሚስቶች ደግሞ በሁሉ ለባሎቻቸው ይገዙ።

ባሎች ሆይ ፥ ክርስቶስ ደግሞ ቤተ ክርስቲያንን እንደ ወደዳት ሚስቶቻችሁን ውደዱ ፤ በውኃ መታጠብና ከቃሉ ጋር አንጽቶ እንዲቀድሳት ስለ እርስዋ ራሱን አሳልፎ ሰጠ ፤ እድፈት ወይም የፊት መጨማደድ ወይም እንዲህ ያለ ነገር ሳይሆንባት ቅድስትና ያለ ነውር ትሆን ዘንድ ክብርት የሆነችን ቤተ ክርስቲያን ለራሱ እንዲያቀርብ ፈለገ።

እንዲሁም ባሎች ደግሞ እንደ ገዛ ሥጋቸው አድርገው የገዛ ሚስቶቻቸውን ሊወዱአቸው ይገባቸዋል። የገዛ ሚስቱን የሚወድ ራሱን ይወዳል፤ ❞

[ ኤፌ.፭ ፥ ፳፬ ]

🕊                      💖                      🕊

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

04 Nov, 15:54


                          †                          

💖  [    የትሕርምት ሕይወት !    ]  💖

🕊                      💖                      🕊

[     በፈተና መጽናትን በተመለከተ  !    ]

ጸጋ ሊሰጣቸሁ ሲል መከራ ይመጣባችኋል !

" ወንድሜ ሆይ ጠላትህ በአንተ ላይ ከሚያስበው ሐሳብ የተነሣ አትታወክ፡፡ ይህ የጦርነት መጀመሪያ ነው፡፡

ወንድሜ ሆይ በዝናብ ጊዜ ከሚሞላው ሐይቅ ተማር፡፡ ዝናቡ በጣለና ውኃው ሐይቁን በሚሞላበት ጊዜ መጀመሪያ ላይ ውኃው ይደፈርሳል፡፡ ነገር ግን የዝናቡ ጊዜ ሲያልፍ በቆይታ ሐይቁ መጠኑ ከመጨመሩ በላይ እንደ መስታወት ጥርት ብሎ በውስጡ የሚመላለሱት ዐሣትን ያሳየናል።

ስለዚህ ተወዳጆች ሆይ በመከራ ምክንያት ልባችሁ አይዛል። ጸጋ ሊሰጣቸሁ ሲል መከራ ይመጣባችኋልና መከራ ካለፈ በኋላ በጸጋው ይሞላችኋል ፤ ጽድቃችሁም በሰው ሁሉ ፊት የተገለጠ ይሆናል፡፡

ስለዚህ በመከራ ጽኑ፡፡ ወደ አምላክህም ፦ “ነፍሴ መከራን ጠግባለችና ፥ ሕይወቴም ወደ ሲኦል ቀርባለች .... አቤቱ መቅሠፍትህ በላዬ አለፈ ፥ ግርማህም አስደነገጠኝ፡፡ ሁልጊዜ እንደ ውኃ ከበቡኝ ፥ በአንድነትም ያዙኝ” [መዝ.፹፰፥፩-፲፯] በማለት አሳስቡ፡፡  እንዲሁም ፦ “በእግዚአብሔር ቃሉን አመሰግናለሁ ፣ በእግዚአብሔር ታመንሁ አልፈራም ሰው ምን ያደርገኛል” [መዝ.፶፮፥፬] በማለት ጸልይ፡፡ "

[  ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ  ]


🕊                        💖                    🕊

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

04 Nov, 13:24


                          †                          

[    🕊    ገ ድ ለ   ቅ ዱ ሳ ን   🕊     ]

▬▬▬▬▬▬   †    ▬▬▬▬▬▬

[  የአባታችን የቅዱስ መቃርዮስ የተጋድሎ ሕይወቱና ትምህርቱ  ]

[               ክፍል  ሠላሳ አንድ             ]

💛

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡

[ አባ መቃርዮስ በአት ውስጥ ሌባ እንደ ገባ ! ]

                         🕊                         

❝ አንድ ጊዜ አባ መቃርዮስ ከበዓቱ ውጪ እያለ ሌባ መጣና ያለውን ንብረት ሁሉ በግመል ላይ ይጭን ጀመር፡፡

አባ መቃርዮስም ሲመጣ የቀረውን ንብረት በመጫን ሌባውን ረዳው፡፡ ሌባውም እቃውን ሁሉ ጭኖ ሲያበቃ ግመሏን ሊያስነሣት ሞከረ ፤ ነገር ግን ለመነሣት እምቢ አለችው፡፡ አባ መቃርዮስም ወደ በኣቱ ገብቶ አንዲት የተረሳች መኮትኮቻ አመጣና ፦ "ወንድሜ ግመሏ ይህንም መውሰድ ፈልጋ ይሆናል" ብሎ ጫነለት፡፡ ከዚያም አባ መቃርዮስ ግመሏን እንድትነሣ አዘዛት ፤ ግመሏም ትዕዛዙን አክብራ በመነሣት ትንሽ እንደ ተራመደች መልሳ ተቀመጠች፡፡ ከዚያም በኋላ ግን እቃው ሁሉ እስኪወርድ ድረስ አልነሣም አለች፡፡ ❞

የአባታችን የቅዱስ መቃርዮስ ምልጃና ጸሎቱ አይለየን፡፡

ይቆየን !


†                       †                         †
💖                    🕊                     💖

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

04 Nov, 09:51


🕊                      †                        🕊

[ ተዋሕዶ ፍጽምት የቅዱሳን ሃይማኖት ]
▬▬▬▬▬▬   †    ▬▬▬▬▬▬

[  ❝  በዚህ በአንድ አካል ይመጣል ! ❞  ]

🕊

❝ ዓለምን ሁሉ ፈጥሮ የሚገዛ የሚታየውን ፥ የማይታየውንም ሁሉ በፈጠረው በአንድ አምላክ በአብ እናምናለን።

ከአብ በተወለደ በአንድ በእግዚአብሔር ልጅ በአንዱ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ እናምናለን ፥ ቅድመ ዓለም ከአብ ባሕርይ ከተወለደ ፥ በኋላ ዘመንም በግብረ መንፈስ ቅዱስ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ተወለደ።

ነፍስ ፤ ሥጋ ፥ ልብ ፥ ዕውቀት ፥ ከኃጢአት ብቻ በቀር ለሰው ያለው ሁሉ ገንዘቡ የሚሆን ፍጹም ሰው ሆነ

በዘርዓ ብእሲ የተወለደ አይደለም ፥ በሰው ሁሉ እንደ ሚያድርም አላደረበትም ፤ እርሱ ሥጋን ነሥቶ ለእርሱ ለብቻው ገንዘብ አደረገው እንጂ ፥ በተዋሕዶም አንድ አደረገው እንጂ። አድሮ እንደ ተናገረባቸው እንደ ነቢያት ሁሉ አይደለም ፤ ፍጹም ሰው ሆነ እንጂ ፥ ቃል ሥጋ ሆነ ፤ አልተለወጠም ፥ መለኮቱን ሰው ወደመሆን አልለወጠውም ፥ ከመለኮት ጋር ጽኑዕ አንድነቱን በተዋሕዶ አደረገ እንጂ።

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አንድ ነው ፥ ፈጣሪ ነው ፥ ንጉሥ ነው ፥ በሥጋ ሞቶ የተነሣ እርሱ ነው ፥ በዚህ አንድ አካል ወደ ሰማይ ዐረገ ፥ ዳግመኛም በሕያዋን በሙታን ይፈርድ ዘንድ በዚህ በአንድ አካል ይመጣል። ❞

[      ቅዱስ ኤጲፋንዮስ      ]

ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፤ ወለወላዲቱ ድንግል ፤ ወለመስቀሉ ክቡር። አሜን።


†                       †                         †
💖                    🕊                     💖

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

03 Nov, 19:56


🕊

✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞

[  "እንኩዋን ለታላቁ "ጻድቅና ሰማዕት አቡነ አቢብ": "አባ ዕብሎይ" እና "ቅዱስ ዮልዮስ ሰማዕት" ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ"  ]


†  🕊  አቡነ አቢብ [ አባ ቡላ ]  🕊  †

ይህን ታላቅ ቅዱስ በምን እንመስለዋለን!

- እኛ ኃጥአን ጣዕመ ዜናውን: ነገረ ሕይወቱን ሰምተን ደስ ተሰኝተናል !

- ቅዱሱ አባታችን :- "ቡላ - የእግዚአብሔር አገልጋይ" ብለን እንጠራሃለን::

- ዳግመኛም "አቢብ - የብዙኃን አባት" ብለን እንጠራሃለን::

- እርሱ ቅሉ አባትነትህ አንተን ለመሰሉ ቅዱሳን ቢሆንም እኛን ኃጥአንን ቸል እንደማትለንም እናውቃለን::

- አባ! ማነው እንዳንተ የክርስቶስን ሕማማት የተሳተፈ!

- ማን ነው እንዳንተ በፈጣሪው ፍቅር ብዙ መከራዎችን የተቀበለ!

- ማንስ ነው እንዳንተ በአንዲት ጉርሻ አማልዶ ርስትን የሚያወርስ!

- የፍጡራንን እንተወውና በፈጣሪ አንደበት ተመስግነሃልና ቅዱሱ አባታችን ላንተ ክብር: ምስጋናና ስግደት በጸጋ ይገባሃል እንላለን::

†    ልደት    †

አባታችን አቡነ አቢብ የተወለደው በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን መጨረሻ አካባቢ ሲሆን ሃገረ ሙላዱ ሮሜ ናት:: ወላጆቹ ቅዱስ አብርሃምና ቅድስት ሐሪክ እጅግ ጽኑ ክርስቲያኖች ነበሩ:: ልጅ ግን አልነበራቸውም:: ዘመነ ሰማዕታት ደርሶ ስደት በሆነ ጊዜ እነርሱም በርሃ ገቡ::

በዚያም ሳሉ በቅዱስ መልአክ ብሥራት ሐሪክ ጸንሳ ብሩሕ የሆነ ልጅ ወለደች:: ቅዱሱ ሕጻን ሲጸነስ ማንም ሳይተክለው የበቀለው ዛፍ ላይ መልአኩ እንዲህ የሚል የብርሃን ጽሑፍ ጽፎበት ወላጆቹ ዐይተዋል::
"ቡላ ገብሩ ለእግዚአብሔር: ወቅዱሱ ለአምላከ ያዕቆብ: ዘየኀድር ውስተ ጽዮን"

†     ጥምቀት     †

ቅዱሱ ሕጻን ከተወለደ በሁዋላ ሳይጠመቅ ለ ፩ ዓመት ቆየ::
ምክንያቱም ዘመኑ የጭንቅ ነውና ካህናትን እንኩዋን በዱር በከተማም ማግኘት አይቻልም ነበር:: እመቤታችን ግን ወደ ሮሙ ሊቀ ዻዻሳት አባ ሰለባስትርዮስ ሒዳ "አጥምቀው" አለችው::

ወደ በርሐ ወርዶ ሊያጠምቀው ሲል ሕጻኑ ተነስቶ: እጆቹንም ዘርግቶ:- "አሐዱ አብ ቅዱስ: አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውዕቱ መንፈስ ቅዱስ" ብሎ አመስግኖ ተጠመቀ:: ከሰማይም ሕብስትና ጽዋዕ ወርዶላቸው ሊቀ ዻዻሳቱ ቀድሶ ሁሉንም አቆረባቸው:: የሕጻኑ ወላጆች "ለልጃችን ስም አውጣልን" ቢሉት "ቡላ" ብሎ ሰየመው:: እነርሱም ምሥጢሩን ያውቁ ነበርና አደነቁ::

†   ሰማዕትነት   †

የቅዱሱ ቡላ ወላጆች ለ፲ ዓመታት አሳድገውት ድንገት ሕዳር ፯ ቀን ተከታትለው ዐረፉ:: ሕጻኑን የማሳደግ ኃላፊነትን የአካባቢው ሰዎች ሆነ:: ሕጻኑ ቡላ ምንም የ፲ ዓመት ሕጻን ቢሆንም ያለ ማቁዋረጥ ሲጾም: ሲጸልይ ክፉ መኮንን "ለጣዖት ስገዱ" እያለ መጣ::

በዚህ ጊዜ በሕጻን አንደበቱ አምልኮተ ክርስቶስን ሰበከ:: በዚህ የተበሳጨ መኮንኑ ስቃያትን አዘዘበት:: በጅራፍ ገረፉት: በዘንግ ደበደቡት: ቆዳውን ገፈፉት: በመጋዝ ቆራርጠውም ጣሉት:: ነገር ግን ኃይለ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ነበርና 2 ጊዜ ከሞት ተነሳ:: በመጨረሻ ግን ሚያዝያ ፲፰ ቀን ተከልሎ ሰማዕት ሆኗል::

†   ገዳማዊ ሕይወት     †

ቅዱስ ቡላ ሰማዕትነቱን ከፈጸመ በሁዋላ ቅዱስ ሚካኤል በአክሊላት አክብሮ ወስዶ በገነት አኖረው:: ከሰማዕታትም ጋር ደመረው:: በዚያም ቡላ ቅዱስ ጊዮርጊስን ተመልክቶ ተደነቀ:: መንፈሳዊ ቅንዐትን ቀንቷልና "እባክህን ወደ ዓለም መልሰኝና ስለ ፍቅርህ እንደ ገና ልጋደል" ሲል ጌታን ለመነ::

ጌታችን ግን "ወዳጄ ቡላ! እንግዲህስ ሰማዕትነቱ ይበቃሃል::
ሱታፌ ጻድቃንን ታገኝ ዘንድ ግን ፈቃዴ ነውና ሒድ" አለው:: ቅዱስ ሚካኤልም የቅዱስ ቡላን ነፍስ ከሥጋው ጋር አዋሕዶ: ልብሰ መነኮሳትንም አልብሶ ግብጽ በርሃ ውስጥ አኖረው::

†    ተጋድሎ    †

አባ ቡላ ወደ በርሃ ከገባ ጀምሮ ዐርብ ዐርብ የጌታን ሕማማት እያሰበ ራሱን ያሰቃይ ገባ:: ራሱን ይገርፋል: ፊቱን በጥፊ ይመታል: ሥጋውን እየቆረጠ ለአራዊት ይሰጣል: ከትልቅ ዛፍ ላይ ተሰቅሎ ወደ ታች ይወረወራል::

በጭንቅላቱ ተተክሎ ለብዙ ጊዜ ጸልዮ ጭንቅላቱ ይፈሳል:: ሌላም ብዙ መከራዎችን የጌታን ሕማማት እያሰበ ይቀበላል:: ስለ ጌታ ፍቅርም ምንም ነገር ሳይቀምስ ለ፵፪ ዓመታት ጹሟል:: ጌታችንም ስለ ክብሩ ዘወትር ይገለጥለት ነበር::

የሚታየውም እንደ ተወለደ: እንደ ተጠመቀ: እንደ ተሰቀለ: እንደ ተነሳ: እንዳረገ እየሆነ ነበር:: አንድ ቀንም ጌታችን መጥቶ "ወዳጄ ቡላ! እንዳንተ ስለ እኔ ስም መከራ የተቀበለ ሰው የለም:: አንተም የብዙዎች አባት ነሕና ስምህ አቢብ [ሃቢብ] ይሁን" አለው::

"እስከ ይቤሎ አምላክ ቃለ አኮቴት ማሕዘኔ:
ረሰይከኑ ለባሕቲትከ ኩነኔ:
ዘመጠነዝ ታጻሙ ነፍስከ በቅኔ" እንዲል::

†     ዕረፍት     †

አቡነ አቢብ ታላቁ ዕብሎን ጨምሮ በርካታ ደቀ መዛሙርትን አፈራ:: ከእመቤታችን ጋርም ዕለት ዕለት እየተጨዋወተ ዘለቀ:: በተጋድሎ ሕይወቱም ከ፲ ጊዜ በላይ ሙቶ ተነስቷል:: በዚህች ቀን ሲያርፍ ገዳሙ በመላእክት ተሞላ::

ጌታም ከድንግል እናቱ ጋር መጥቶ "ወዳጄ ቡላ! ስምህን የጠራውን: መታሰቢያህን ያደረገውን እምርልሃለሁ:: አቅም ቢያጣ "አምላከ አቢብ ማረኝ" ብሎ ፫ ጊዜ በዕለተ ዕረፍትህ የሚለምነኝን: በስምሕ እንኩዋ ቁራሽ የሚበላውን ሁሉ እምርልሃለሁ" ብሎት ነፍሱን በክብር አሳረገ: በሰማይም ዕልልታ ተደረገ::


†  🕊  ታላቁ አባ ዕብሎይ 🕊  † 

ይህ ቅዱስ የአቡነ አቢብ ደቀ መዝሙር ሲሆን በዚህ ስም ከሚጠሩ ቅዱሳንም ቀዳሚው ነው:: ብዙ መጻሕፍት "ርዕሰ ገዳማውያን" ይሉታል:: የቅዱሱ ተጋድሎ እጅግ ሰፊ በመሆኑ በዕለተ ዕረፍቱ [የካቲት ፫ ቀን] እንመለከተዋለንና የዚያ ሰው ይበለን::


†   🕊 ቅዱስ ዮልዮስ ሰማዕት 🕊  †

ከሁሉ አስቀደሞ ስለ ሰማዕታት ዜና ሲሰማ ለዚህ ቅዱስ አንክሮ [አድናቆት]: ክብርና የጸጋ ውዳሴ ይገባዋል:: ምክንያቱም ገድለ ሰማዕታትን የጻፈልን እርሱ ነውና:: ነገር ግን መጻፍ ሲባል: ነገሮች እንዲህ እንደ እኛው ዘመን ቀላል እንዳይመስሏችሁ:: ቅዱሱ ዜና ሰማዕታትን ለማዘጋጀት ሃብቱን: ንብረቱን: ቤተሰቦቹንና ሕይወቱንም ሰውቷል::

ይህስ እንደ ምን ነው ቢሉ :-

በመጨረሻው ዘመነ ሰማዕታት [በ፫ኛው መቶ ክ/ዘ] ዓለም በደመ ሰማዕታት ስትሞላ እንኩዋን የሰማዕታቱን ዜና የሚጽፍ: ሥጋቸውን እንኩዋ የሚቀብር አልተገኘም:: "ወኃጥኡ ዘይቀብሮሙ - የሚቀብራቸውም አጡ" እንዳለ ቅዱስ ዳዊት:: [መዝ.፸፰፥፫]

እግዚአብሔር ግን ስለ ወዳጆቹ ሰማዕታት ይህንን ቅዱስ አስነሳ:: ቅዱስ ዮልዮስ በዘመኑ ደግ ክርስቲያን: ትዳርና ልጆች ያሉት: እጅግ ባለ ጸጋና ፫ መቶ አገልጋዮች ያሉት: ምጽዋትንም የሚወድ ሰው ነበር::

በወቅቱ የክርስቲያኖች በየመንገዱ ወድቀው መታየታቸው ዕረፍት ቢነሳው ከቤተሰቦቹ ጋር መክሮ መልካም ግን ደግሞ ከባድ ውሳኔን አስተላለፈ:: ውሳኔውንም ታጥቆ ይተገብረው ጀመር::
በእውነት ድንቅ ሰው ነው:: በምን እንመስለዋለን! እርሱን የፈጠረውን ጌታ "ዕጹብ ዕጹብ" ብለን ከማድነቅ በቀር::

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

03 Nov, 19:56


ሰማዕታቱም ስለ ደግነቱ የሚመልሱለት ቢያጡ ዝም ብለው ይመርቁት ነበር::+እንዲህ: እንዲህ እያለ ዘመነ ሰማዕታት ሊፈጸም ወራት ቀሩት:: በዚህ ጊዜ ለሰማዕትነት ከመነሳሳቱ የተነሳ ጌታችንን ተማጸነ:: ጌታችንም ተገልጾለት "ሒድና ሰማዕት ሁን: ፈቅጄልሃለሁ" አለው:: እርሱም ደስ እያለው ዜና ሰማዕታቱን ለሁነኛ ሰው ሰጥቶ: ሃብት ንብረቱን ለነዳያን አካፈለ::

ቀጥሎም ቤተሰቦቹንና አገልጋዮቹን ጨምሮ ወደ ሃገረ ገምኑዲ ሔደ:: በመኮንኑ ፊት የክርስቶስን አምላክነት ቢመሰክር ፈጽመው አሰቃዩት:: በማግስቱም ወታደሮቹ ለጣዖት ካልሰገድክ ሲሉት "ቆዩማ ላሳያችሁ" ብሎ በጸሎቱ ጣዖታትን ከነ ካህናቶቻቸው ምድር ተከፍታ እንድትውጣቸው አደረገ:: በተአምሩም መኮንኑና ሠራዊቱ አምነው ተከተሉት::

በፍጻሜውም በሌላ ሃገር መኮንኑ ቅዱስ ዮልዮስን ከቤተሰቡና ከ፩ ሺህ ፭ መቶ ያህል ተከታዮቹ ጋር: ፪ቱን የሃገረ ገዥዎች ጨምሮ አንገታቸውን አሰይፏቸዋል::

አምላከ ጻድቃን ወሰማዕት በቃል ኪዳናቸው እንዲምረን ቸርነቱ ይርዳን:: በረከታቸውንም አትርፎ ይስጠን::

🕊

[  †  ጥቅምት ፳፭ [ 25 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት  ]

፩. አቡነ አቢብ [አባ ቡላ]
፪. አባ ዕብሎይ ገዳማዊ
፫. ቅዱስ ዮልዮስ ሰማዕት
፬. ቅዱሳን አብርሃምና ሐሪክ
፭. ቅዱሳን አሞኒና ሙስያ [የታላቁ ዕብሎ ወላጆች]

[    † ወርሐዊ በዓላት   ]

፩. ቅዱስ መርቆሬዎስ ሰማዕት
፪. ቅድስት ቴክላ ሐዋርያዊት
፫. ቅዱስ አበከረዙን ሰማዕት
፬. ቅዱስ ዱማድዮስ ሶርያዊ
፭. ቅዱስ አቡፋና ጻድቅ
፮. ታላቁ አባ ቢጻርዮን

" እኔን መከተል የሚወድ ቢኖር ራሱን ይካድ:: መስቀሉንም ተሸክሞ ይከተለኝ:: ነፍሱን ሊያድን የሚወድ ሁሉ ያጠፋታል:: ስለ እኔ ግን ነፍሱን የሚያጠፋ ሁሉ ያገኛታል:: " [ማቴ.፲፮፥፳፬]

† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †

[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]

         †              †               †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖                   🕊                    💖

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

03 Nov, 15:54


                       †                       

  [  🕊  ድምፀ ተዋሕዶ   🕊  ]  

🍒▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬🍒               

[  ሕይወት የሚገኝባቸው የቅድስት ቤተክርስቲያን መንፈሳዊ ትምህርቶች በሊቃውንተ ቤተክርስቲያን በድምፅ ይቀርባሉ።  ]

[   ሳምንታዊ መርሐ-ግብር   ]

🕊             
             
❝ የእግዚአብሔር ሕግ ፍጹም ነው ፤ ነፍስን ይመልሳል ፤ የእግዚአብሔር ምስክር የታመነ ነው ፤ ሕፃናትን ጠቢባን ያደርጋል።

የእግዚአብሔር ሥርዓት ቅን ነው ፥ ልብንም ደስ ያሰኛል ፤ የእግዚአብሔር ትእዛዝ ብሩህ ነው ፥ ዓይንንም ያበራል። ❞

[ መዝ . ፲፱ ፥ ፯  ]

▬▬▬▬▬▬   †    ▬▬▬▬▬▬

[  ❝ የእግዚአብሔር ሕግ ፍጹም ነው ! ❞  ]

               [   ክፍል - ፴፩ -    ]

          💖   ድንቅ ትምህርት  💖

[ በመምህራችን በቀሲስ ኅብረት የሺጥላ ]

የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ፥ ከመከራም ሥጋት ያርፋል። ❞ [ ምሳ.፩፥፴፫ ]

         †              †               †
▬▬▬▬ ▬▬▬▬▬ ▬▬▬▬
                        👇

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

03 Nov, 12:14


                       †                        

   [       ለጥያቄዎ ምላሽ !        ]

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡


[ " እግዚአብሔር ይፍታችሁ! ብቻ አይበቃም ? " ]

[  ከምዕመናን የቀረበ ጥያቄ  ]
                                
🍒

" ከቅዳሴ በኋላም ሆነ ከጉባኤ በኋላ የሚያሳርጉት ካህን "እግዚአብሔር ይፍታችሁ" ይሉናል፡፡ እኛም ፦ ስናውቅ በድፍረት ሳናውቅ በስሕተት ከሠራነው የኃጢአት ማሠሪያ እንደምንፈታ እናምናለን፡፡ በመሆኑም ኃጢአታችንን ለንስሓ አባታችን ሳንናዘዝ ሥጋ ወደሙ ብንቀበል ምናለበት? በጉባኤው ላይ "እግዚአብሔር ይፍታችሁ" የተባለው አይበቃም?"

------------------------------------------------

[  የቅድስት ቤተክርስቲያን መልስ  ]

አባቶች ካህናት ከቅዱሳን ሐዋርያት ጀምሮ ሲያያዝ በመጣው መዓርገ ክህነት መሠረት የመፍታትና የማሠር ሥልጣን አላቸው። [ማቴ. ፲፮፥፲፱ ፤ ፲፰፥፲፰] ጌታችን ለደቀ መዛሙርቱ ፦ "እነሆም እኔ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ፡፡" ማለቱ የሚያረጋግጥልን ይህንኑ ነው፡፡ [ማቴ.፳፰፥፳] በመሆኑም እነርሱ አዝዘው ኃጢአቱን ይቅር ያሉለት ሰው ሁሉ ኃጢአቱ ይቀርለታል ፣ የያዙበትም ሰው እንዲሁ ይያዝበታል፡፡ ይህም ኃጢአቱን ላስተሠረዩለት ሰው ይሠረይለታል ፤ ላላስተሠረዩለት ሰው ደግሞ አይሠረይለትም ማለት ነው። [ዮሐ፳፥፳፫]

በዚህም መሠረት የመጥምቀ መለኮት የቅዱስ ዮሐንስን የንስሐ ስብከት ሰምተው በዮርዳኖስ የተሰበሰቡ ሁሉ ኃጢአታቸውን ለቅዱስ ዮሐንስ ይናዘዙ እንደነበረ እኛም ኃጢአታችንን ለካህኑ እንናዘዛለን [ማቴ.፫፡፮] ካህኑም ኃጢአቱን ሰምተው ቀኖና ይሰጡናል፡፡ ቀኖናው ጾም ወይም ስግደት ወይም ምጽዋት ሊሆን ይችላል፡፡ በዚህ ዓይነት የተሰጠንን ቀኖናም ከፈጸምን በኋላ ወደ ካህኑ ስንመለስ "እግዚአብሔር ይፍታችሁ" ይሉናል፡፡ በዚህን ጊዜም ከኃጢአት ማሰሪያ ሁሉ የተፈታን እንሆናለን፡፡ ከዚህም የምንማረው ኃጢአትን ለንስሓ አባት መናዘዝ ግዴታ መሆኑን ነው፡፡

ይኸንን ይዘን ወደ ጥያቄው መንፈስ ስንመጣ እርስ በርሱ የሚጋጭ ይመስለን ይሆናል፡፡ ነገር ግን ለእኛ ይምሰለን እንጂ አባቶቻችን እርስ በርሱ የሚጋጭ ምንም ነገር አልሠሩልንም፡፡ ምክንያቱም በእነርሱ አድሮ ሥራ የሠራው መንፈስ ቅዱስ ነውና። እንግዲህ ከቅዳሴም ሆነ ከጉባኤ በኋላ "እግዚአብሔር ይፍታችሁ" ስንባል የምንፈታው እግዚአብሔር ከሚያውቀው እኛ ግን ከማናውቀው ኃጢአት ሲሆን ፣ በተጨማሪም የሰው ልጅ ከበደል ስለማይነጻ በየደቂቃውና በየሰዓቱ ከምንፈጽመውና አስታውሰነው ከማንናዘዘው ኃጢአት ነው፡፡ አባቶቻችን ካህናት ሲያሳርጉ "ሰይጣን ከሸመቀው / ከዓይነ ሥጋ እና ከአይነ ልቡና ከሰወረው/ መንፈስ ቅዱስ ግን ካወቀው ኃጢአት እግዚአብሔር ይፍታችሁ" የሚሉት ለዚህ ነው።

ተሳስተንም ይሁን በድፍረት ስለሠራነው እና ስለምናውቀው ኃጢአት ግን የግድ መናዘዝ አለብን፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር፡፡

ይቆየን !

†                       †                       †
💖                    🕊                    💖

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

01 Nov, 17:31


                           †                           

  [  🕊 ገዢን የወለድሽ ንግሥቴ 🕊  ]  

🌼▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬🌼

❝ እመቤቴ ማርያም ሆይ ገዢን የወለድሽ ንግሥቴ አንቺ ነሽ። የክብርሽን እጅ መንሻ ከተርሴስ ዕንቊን ከሕንደኬም ጽሩይ ወርቅን ያመጣሉ::

ድንግል ሆይ እኔ ገናናነትሽን ሰባኪ ሆንሁ:: በፍጹም ምስጋና ፈጽሜ ከፍ ከፍ አደርግሻለሁ:: የተመረጥሽ ሆይ አገልጋይሽን የሚያውክ የክፋት ነፋስን ጸጥ አድርጊው። የሕይወቴን ልምላሜ እንደወይራ ቅጠል እንዳያጠወልገው ፤ እንደ ገዢም እንዳይመጣብኝ ይቅርታሽን ላኪልኝ ርኅሩኅ የሆነ ረዳትነትሽም አይለይኝ። ❞

🕊

[  እንዚራ ስብሐት   ]


💖                    🕊                    💖

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

01 Nov, 16:11


                          †                          

💖  [    የትሕርምት ሕይወት !    ]  💖

🕊                      💖                      🕊

[     ትእግስትን በተመለከተ  !   - ፫ -    ]

ከአንተ ይልቅ ንጉሥ ሆኖ ሳለ !

❝ ወዳጄ ሆይ ! ስለ ጌታ ብለህ አገልግሎትህን በትዕግሥት መፈጸም ሲገባህ እንደ መዋረድ የምታስብ ከሆነ ከአንተ ይልቅ ንጉሥ ሆኖ ሳለ ራሱን ዝቅ በማድረግ እኛን ማገልገሉን እንደ ስድብ መቍጠር ያለበት እርሱ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነበር፡፡

አንተ ይህን ለእርሱ ማገልገልን ከንቱ ድካም ነው አልህ፡፡ በዚህ ተግባርህም ሃኬተኞችን መሰልህ፡፡ ለኃጢአተኞችና ለሃኬተኞች ወዮላቸው። ስለ ጌታችን ብለን መከራን መታገሥ ካልቻልን ስለምን ታዲያ ከዚህ ዓለም ተለየን ?

ተወዳጆች ሆይ ! ስለ ጌታችን ብሎ መከራን የማይታገሥ ማን ነው? ተወዳጆች ሆይ ከእናንተ የሚጠበቀው ጥቂት እንደሆነ የምታገኙት ግን ታላቅ እንደሆነ ልብ በሉ፡፡ እኛ ትዕግሥትን ገንዘብ አድርገን የእግዚአብሔርን ፈቃድ ስንፈጽም እርሱ ለእኛ የገባውን ቃል ኪዳን ይጠብቃል፡፡ "እስከ መጨረሻው የሚጸና እርሱ ይድናል" ይላልና ቃሉ መዳናችንን በትዕግሥት እንፈጽም፡፡ ❞

[  ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ  ]


🕊                        💖                    🕊

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

01 Nov, 12:44


                          †                          

[    🕊    ገ ድ ለ   ቅ ዱ ሳ ን   🕊     ]

▬▬▬▬▬▬   †    ▬▬▬▬▬▬

[  የአባታችን የቅዱስ መቃርዮስ የተጋድሎ ሕይወቱና ትምህርቱ  ]

[                ክፍል  ሠላሳ               ]

💛

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡

[ ከአኃው መካከል ፍቅረ ነዋይ ያደረበት አንድ እኁ ! ]

                         🕊                         

❝ ብዙ በሽተኞች ወደ እርሱ ይመጡ ስለ ነበር የሕሙማን ቤት ተዘጋጀ፡፡ ብዙ በሽተኞች ከተለያዩ አገራት እየመጡ ለበሽተኞች በተዘጋጀው ቤት ሆነው እግዚአብሔር በእርሱ አማካኝነት ይፈውሳቸው ዘንድ በተስፋ ይጠባበቁ ነበር፡፡ በየቀኑም በዘይት ላይ እየጸለየ ይቀባቸውና ይፈውሳቸው ነበር፡፡ ከአኃው መካከል ዮሐንስ የተባለውን አንዱን ለድውያን በመላላክ ያገለግል ዘንድ መደበው፡፡ ምእመናን ሰዎችም ለበሽተኞች አገልግሎት ይሆን ዘንድ ብር እያዋጡ የሚሰጡት ሆኑ፡፡ ያ እኁም ሰይጣናዊና ጽኑ ደዌ የሆነውን የገንዘብ ፍቅር በልቡናው ተቀበለና ገንዘብ መውደድ ጀመረ፡፡ ለበሽተኞች ከሚዋጣው ገንዘብም መደበቅ ጀመረ፡፡

አባት መቃርዮስም የሚያደርገውን ነገር ሁሉ በመንፈስ ያይ ነበር ፣ ሆኖም ለብዙ ጊዜ ታገሠው፡፡ ከረጅም ጊዜ በኋላ ወደ እርሱ ጠራውና ፦ "ዮሐንስ ሆይ ፣ ሰይጣን በላይህ ላይ በአፍቅሮ ንዋይ ነግሦብሃል" አለውና ይህን ፆር ከውስጡ ያርቅ ዘንድ መከረው ፣ ገሠጸውም፡፡ እርሱ ግን የአባቱን ምክር አልሰማም ፣ ይልቁንም አብዝቶ በጣም ብዙ ብር ይሰበስብ ጀመር፡፡ ቅዱስ መቃርስ ባረፈ በአሥራ አምስተኛው ዓመት እግዚአብሔር በላዩ ላይ ከባድ ደዌን አመጣበት፡፡ በሰውነቱ ላይ ጤነኛ የሆነና የመርፌ መውጊያ እንኳ ያህል ሕይወት ያለው ጤነኛ አካል አልተገኘም፡፡ በዚህ ሁኔታ ተሰቃይቶ ሞተ፡፡

በሌላ ጊዜ ድቀት ያገኘው አንድ ወጣት የሆነ መነኩሴ  ወደ አባ መቃርዮስ መጣና ፦ " አባቴ ሆይ ፣ ኃጢአቴን ይቅር በለኝ በኃጢአት እንደ ወደቅሁ አንተ ታውቃለህና ፣ ነገር ግን እግዚአብሔር ኃጢአቴን ይቅር ይለኝ ዘንድ ስለ እኔ ጸልይልኝ" አለው፡፡ ቅዱስ መቃርዮስም ፦ "ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ኃጢአትህን ይቅር ሊልህ እንደሚችል በፍጹም ልብህ እመን ፣ የእርሱ ምሕረትና ቸርነት ዘመን የማይገድበው ወሰን የሌለው ነውና እርሱ ኃጢአትህን ይቅር ይበልህ ፣ ዳግመኛም እንዳትበድል ሁን" አለው፡፡ ❞

የአባታችን የቅዱስ መቃርዮስ ምልጃና ጸሎቱ አይለየን፡፡

ይቆየን !


†                       †                         †
💖                    🕊                     💖

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

01 Nov, 08:57


                       †                       

🕊  †  ቅዱስ ዑራኤል  †  🕊  ]

🕊

በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ትውፊት መሠረት ከ፯ [ 7 ]ቱ ሊቃነ መላእክት አንዱ የሆነው ቅዱስ ዑራኤል :-

፩. ድንግል ማርያም በአካለ ሥጋ እያለች ወደ ሰማይ አሳርጉዋታል:: በሠረገላ ብርሃን ጭኖ: በክንፎቹም ተሸክሞ: አስቅድሞ ገነትን ቀጥሎም ሲዖልን አስጐብኝቷታል:: በዚህም ምክንያት እመ ብርሃን ስለ ኃጥአን የምታለቅስ: የምትለምንና የምትማልድ ሆናለች:: ለምናም አልቀረች የምሕረት ቃል ኪዳን ተቀብላለች::

፪. ቅዱሱ መልአክ እመ ብርሃንን በስደቷ ጊዜ ወደ ኢትዮዽያ መርቶ አምጥቷታል:: በክንፉ ተሸክሞ: በ፬ አቅጣጫ አዙሮ አሳይቶ አሥራት እንድትቀበል አድርጉዋል::

፫. ጌታችን በተሰቀለ ጊዜ ደሙን በጽዋዕ አድርጐ በኢትዮዽያ ወንዞች ላይ አፍስሷል::

፬. ለብዙ ቅዱሳን [ አባ ጊዮርጊስን ጨምሮ ] ጽዋዐ ልቡናን አጠጥቷል::

አምላከ ቅዱሳን ስለ ወዳጆቹ በጐ ምኞታችንን
ይፈጽምልን:: ከበረከታቸውም ያድለን::


💖                     🕊                     💖

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

01 Nov, 01:58


✞ አምላከ ቅዱስ ሉቃስ ምሥጢሩን: ፍቅሩን: ጥበቡን ይግለጽልን:: ከሐዋርያው በረከትም ያሳትፈን::

🕊

[   † ጥቅምት ፳፪ [ 22 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት  ]

፩. ቅዱስ ሉቃስ ወንጌላዊ ሐዋርያ
፪. ቅዱስ ሲላስ አረጋዊ [የቅዱስ ሉቃስ ረድእ]
፫. ቅዱስ ታኦፊላ
፬. ፬፻፸፯ "477" ሰማዕታት [የቅዱስ ሉቃስ ማሕበር]

[  †  ወርሐዊ በዓላት   ]

፩. ቅዱስ ዑራኤል መላእክ
፪. ቅዱስ ደቅሲዮስ [የእመቤታችን ወዳጅ]
፫. አባ እንጦኒ [የመነኮሳት አባት]
፬. አባ ጳውሊ
፭. ቅዱስ ዮልዮስ ሰማዕት

" የከበርህ ቴዎፍሎስ ሆይ! ከመጀመሪያው በዓይን ያዩትና የቃሉ አገልጋዮች የሆኑት እንዳስተላለፉልን: በእኛ ዘንድ ስለ ተፈጸመው ነገር ብዙዎች ታሪክን በየተራው ለማዘጋጀት ስለ ሞከሩ: እኔ ደግሞ ስለ ተማርከው ቃል እርግጡን እንድታውቅ: በጥንቃቄ ሁሉን ከመጀመሪያው ተከትዬ በየተራው ልጽፍልህ መልካም ሆኖ ታየኝ:: " [ሉቃ.፩፥፩]

† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †

[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]

         †              †               †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖                   🕊                    💖

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

01 Nov, 01:58


🕊

✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ✞

✞ ጥቅምት ፳፪ [ 22 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ✞


†  🕊  ቅዱስ ሉቃስ ወንጌላዊ  🕊  † 

✞ ቅዱስ ሉቃስ :-

- ሐዋርያ ነው
- ወንጌላዊ ነው
- ሰማዕት ነው
- ዓቃቤ ሥራይ [ዶክተር] ነው
- የጥበብ ሰው [ሰዓሊ] ነው

- ዘጋቢ [የሐዋርያትን ዜና ሕይወት የጻፈ] ነው:: ይሕስ እንደምን ነው ቢሉ :-

በመጀመሪያው መቶ ክ/ዘመን መነሻ አካባቢ: በተወደደች የጌታ ዓመት ከእሥራኤላውያን ወገኖቹ ቅዱስ ሉቃስ ተወልዷል:: ያደገውም መቄዶንያ አካባቢ ነው:: ጌታችን ተጠምቆ ማስተማር ሲጀምር ከተከተሉት የ፭ ገበያ ሕዝብ መካከል ፻፳ውን ለቤተሰብነት መምረጡ ይታወቃል::

ታዲያ እንዲጠቅም አውቆ ቅዱስ ሉቃስን ከ፸፪ቱ አርድእት ደምሮታል:: ቅዱስ ሉቃስ ጌታን ከተከተለ በኋላ ለ፫ ዓመት ከ፫ ወር: ከዋለበት እየዋለ: ካደረበትም እያደረ የቃሉን ትምሕርት: የእጆቹን ተአምራት በጥሞና ይከታተል ነበር::

ጌታችን ለዓለም ድኅነት ተሰቅሎ: ሙቶ: ከተነሳ በኋላ ስለዚህ ቅዱስ የሚናገር አንድ የወንጌል ክፍል እናገኛለን:: በሉቃስ ወንጌል ምዕራፍ ፳፬ ላይ ከምናያቸው የኤማሁስ መንገደኞች አንዱ ይህ ቅዱስ እንደ ሆነ አባቶች አስተምረውናል::

በእርግጥ 'ቀለዮዻ' የሚለው ስም በዘመኑ የብዙዎች መጠሪያ ቢሆንም እርሱም ጌታን ከመከተሉ በፊት በዚህ ስም ይጠራ እንደ ነበር ይታመናል:: በወቅቱ ታዲያ ፪ቱ ደቀ መዛሙርት [ሉቃስና ኒቆዲሞስ] ወደ ኤማሁስ ሲሔዱ ጌታ መንገድ ላይ ተገልጦ እያጫወታቸው አብሮ ተጉዟል::

እነርሱም ማንነቱን አላወቁምና ስለ ራሱ ለራሱ እየሰበኩለት ተጉዘዋል:: ከሐዘናቸው ብዛት ማስተዋል ተስኗቸው: ቀቢጸ ተስፋም ወሯቸው ነበርና መድኃኒታችን ክርስቶስ የነቢያትን ትንቢት ተረጐመላቸው::

በዚህ ጊዜም ከነገሩ ማማር: ከምሥጢሩ መሥመር ጋር እየገረማቸው ልቦናቸው ይቃጠል [ይቀልጥባቸው] ነበር:: "አኮኑ ይነድደነ ልበነ" እንዲል:: ወደ ኤማሁስ ሲደርሱ ግን ደጐች ናቸውና "በቤት ካላደርክ: ራት ካልበላህ" ብለው ግድ አሉት::

በማዕድ ሰዓት ግን ቡራኬውን ሰጥቷቸው: ቸር አምላክነቱን ገልጦላቸው ተሰወራቸው:: እነርሱም በሐሴት ከኤማሁት ተመልሰው እየሮጡ ኢየሩሳሌም ደርሰው ትንሳኤውን ሰበኩ::

የመንገዱ ርዝመትም አልታወቃቸውም ነበር:: ከዚህ በኋላ ቅዱስ ሉቃስ እንደ ሐዋርያቱ መጽሐፈ ኪዳንን: ትምሕርተ ኅቡዓትን ተምሮ: መንፈስ ቅዱስን ተቀብሎ ለስብከተ ወንጌል ወጥቷል::


†   🕊   ቅዱሱ ዶክተር  🕊    †

✞ በትውፊት ትምሕርት እንደ ተማርነው ቅዱስ ሉቃስ ጌታን ከመከተሉ በፊት ሥራው ሐኪምነት [ዶክተር] ነበር:: በዚህም አበው "አቃቤ ሥራይ / ባለ መድኃኒት" ይሉታል:: በተሰጠው ሙያም ብዙዎችን አገልግሏል::

የጌታ ደቀ መዝሙር ከሆነ በኋላ ደግሞ "አቃቤ ሥራይ ዘነፍስ-የነፍስ ሐኪም" ተብሏል:: እንዲያውም አባቶቻችን ሐዋርያትን ያክማቸው ነበር ይባላል:: ምክንያቱም ቅዱሳን ሐዋርያት አብዛኞቹ በሽተኞች ነበርና ነው:: ከደግነታቸው የተነሳም እልፍ አእላፍ ድውያንን በተአምራት ሲፈውሱ እነርሱ ግን በስቃይ ይኖሩ ነበር::

ሕመማቸው ሲጠናባቸው ግን ቅዱሱ ዶክተር ሉቃስ ይራዳቸው ነበር:: ይሕንንም ቅዱስ ዻውሎስ በቆላስይስ መልእክቱ ላይ "የተወደደው ባለ መድኃኒቱ ሉቃስ: ዴማስም ሰላምታ ያቀርቡላቹሃል" ሲል ገልጾታል:: [ቆላ.፬፥፲፬]


†   🕊   ዘጋቢው ሐዋርያ  🕊   †

ቅዱስ ሉቃስ እንደ ዛሬው ነገሮች ምቹ ባልነበሩበት ዘመን እጅግ አድካሚ የሆነ ጉዞ አድርጐ የሐዋርያትን ዜና ሕይወት ዘግቦልናል:: ልክ ወንጌሉን ለታኦፊላ [ቴዎፍሎስ] ደቀ መዝሙሩ እንደ ጻፈለት ግብረ ሐዋርያትንም ለእርሱ በትረካ መልክ አቅርቦለታል::

ሲጽፍለትም "ሰማሁ" እያለ ሳይሆን: አብሮ እያለ ያየውንና የተሳተፈበትን ነው:: አተራረኩም በአንደኛና በ፫ኛ መደብ አድርጐ እያቀያየረ ነው:: ማለትም አንዳንዴ "እኛ" እያለ ሌላ ጊዜ ደግሞ "እነርሱ" እያለ ነበር የሚተርክለት::

መጽሐፉም ፳፰ ምዕራፎች ሲኖሩት በጌታ ዕርገት ጀምሮ በኢየሩሳሌምና በአሕዛብ የነበረውን ስብከተ ወንጌል ገልጦ: የቅዱስ ዻውሎስን ጉዞዎች በሰፊው ዳስሶ ይጠናቀቃል::


†  🕊  ወንጌላዊው ሐዋርያ 🕊   †

ቅዱስ ሉቃስ ወንጌልን እንዲጽፉ ከተመረጡ [ከተፈቀደላቸው] ሐዋርያት አንዱ ነው:: በቤተ ክርስቲያንም "ዘላሕም" እየተባለ ይጠራል:: ለዚህም ምክንያቱ :-

፩. ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በበረት: በላምና በአህያ መካከል መወለዱን በመጻፉ
፪. ጌታችንን "መግዝአ ላሕም-የሚታረድ ሜልገች [ላም]" ብሎ በመግለጹ እና
፫. ከ፬ቱ እንስሳ [ኪሩቤል] አንዱ [ገጸ ላሕም] ይራዳው: ይጠብቀውም ስለ ነበር ነው::

ቅዱስ ሉቃስ ወንጌሉን የጻፈው ጌታ ባረገ በ፳፪ኛው ዓመት ሲሆን ይኼውም በ፶፮ ዓ/ም አካባቢ ማለት ነው:: ሲጽፍም ብቻውን አልነበረም:: ልክ ቅዱስ ማርቆስ ወንጌሉን የጻፈው ከሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ ዼጥሮስ ጋር እንደ ሆነው ሁሉ: ቅዱስ ሉቃስም የጻፈው ከብርሃነ ዓለም ቅዱስ ዻውሎስ ጋር ነው:: ምክንያቱም ለረዥም ዓመታት አብረው ለስብከተ ወንጌል ተጉዘዋልና::

ቅዱስ ሉቃስ ወንጌሉን ሲጽፍ በነ ዘካርያስ ቤተሰብ ጀምሮ: ብሥራተ ገብርኤልን: ክብረ ድንግል ማርያምን: የጌታን ልደት: እድገት: መጠመቅ: ማስተማር: መሰቀል: መሞት: መነሳትና ማረግ በቅደም ተከተል ይተርክልናል::


†  🕊 ጥበበኛው [ሰዓሊው] ሐዋርያ 🕊  †

ቅዱስ ሉቃስን ለየት ከሚያደርጉት ነገሮች ሌላኛው ደግሞ ጐበዝ ሰዓሊ የነበረ መሆኑ ነው:: በሐዲስ ኪዳንም የመጀመሪያውን የእመቤታችንን ስዕል [ምስለ ፍቁር ወልዳን] የሳለው እሱ ነው::

አንድ ቀን የአምላክ እናት ባለችበት ከጌታ አስፈቅዶ የሳላት ስዕለ አድኅኖ ሥጋን የለበሰች: ከፊቷ ወዝ የሚወጣ: የምታለቅስ: ስትወጋ የምትደማና ድውያንን የምትፈውስ ሆና ተገኝታለች:: ይህች ስዕል ዛሬ ሃገራችን ኢትዮዽያ ውስጥ አለች ይባላል::


†   🕊  ሰማዕቱ ሐዋርያ  🕊   †

ቅዱስ ሉቃስ እንዲህ ባለ ሕይወት ሲመላለስ በትጋት [ያለ ዕረፍት] ወንጌልን እየሰበከ ነበር:: በ፷፮ እና በ፷፯ ዓ/ም ብርሃናተ ዓለም ዼጥሮስ ወዻውሎስ በኔሮን ቄሣር እጅ ሲገደሉ የሮም ግዛት ክርስቲያኖች ኃላፊነት በእርሱ ላይ ነበረ::

ከወንጌሉና ግብረ ሐዋርያቱ ባለፈ በመልእክታት: አንድም እየዞረ ክርስቲያኖችን አጸና: አሕዛብንም አሳመነ:: ከጥቂት ጊዜ በኋላ ግን ዝናውን የሰማው ኔሮን ሊገድለው ፈለገ:: በዚህ ጊዜ ቅዱስ ሉቃስ ከደቀ መዛሙርቱ መካከል ሲላስ የሚባለውን ሽማግሌ መርጦ መጽሐፎቹን ሁሉ አስረከበው::

በድፍረትም ወደ ኔሮን ቄሣር ቀርቦ ተናገረው:: ንጉሡም "ክርስቶስን አምልኩ የምትል ቀኝ እጅህ መቆረጥ አለባት" ብሎ እጁን ከትክሻው በሰይፍ ለይቶ መሬት ላይ ጣለው:: ሁሉ ሰው ሲደነግጥ ቅዱሱ ተጐንብሶ የወደቀች እጁን አነሳትና እንደ ነበረችው አደረጋት::

በዚያ የነበሩ አሕዛብም "ግሩም" አሉ:: መልሶ ግን "አሁን እጄ ሥራዋን ስለ ጨረሰች አልፈልጋትም" ብሎ እንደ ገና ለይቶ ጣላት::
"ከመ ያርኢ ኃይለ ቅድመ ኔሮን ወተዓይኑ:
አስተላጸቃ ወሌለያ ለምትርት የማኑ:
እስመ ላዕሌሁ ተሰውጠ ለክርስቶስ ስልጣኑ::" እንዲል::

በዚህ ጊዜም ይህንን ድንቅ ያዩ ፬፻፸፯  ያህል አሕዛብ በክርስቶስ አምነው አብረውት ተሰይፈዋል:: የስብከት ዘመኑም ከ፴፮ ዓመታት በላይ ነው::

ኦርቶዶክሳዊነት 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

31 Oct, 15:48


                          †                          

💖  [    የትሕርምት ሕይወት !    ]  💖

🕊                      💖                      🕊

[     ትእግስትን በተመለከተ  !   - ፪ -    ]

ሥቃዩን ሁሉ ታግሠው ኖሩ  !

" የቀደሙ አባቶቻችን ጻድቃን ቅዱሳን በእምነታቸው የእሳቱን እቶን አቀዘቀዙት፡፡ በዚያም በባዕድ ሀገር ባርነቱን ፣ መከራውን ፣ ሥቃዩን ሁሉ ታግሠው ኖሩ፡፡

እኛ ጥቂቱን መከራ እንኳ ያለመታገሣችን ምክንያቱ እምነታችን ጎዶሎ ስለሆነ ነው፡፡ በዚህም ምክንያት ትዕግሥት ከእኛ ዘንድ የራቀ ሆነ፡፡

አንተ የሰውን ገንዘብ ብታጠፋ እምነትንም ብታጎድል ወደ ወኅኒ ቤት ትጣላለህ በዚያም መከራን ትቀበላለህ፡፡ እንዲሁ በእግዚአብሔር ባትታመንና ወደ ድፍረት ኃጢአት ብትገባ በነፍስህ ጽኑ መከራን ትቀበላለህ፡፡

ስለዚህ በእግዚአብሔር አምላክህ ዘንድ ዋጋ እንዳታጣ ትዕግሥትን ገንዘብህ አድርገህ ተመላለስ፡፡ አስቀድመህ የፈጸምከውም የጽድቅ ሥራ ዋጋ እንዳያጣ ወደ ኋላ አትመልከት፡፡ በሕይወትህም ለእግዚአብሔር የምትቀና በሰው ዘንድ የታመንህ ሁን፡፡ "

[  ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ  ]


🕊                        💖                    🕊

8,839

subscribers

3,767

photos

212

videos