Abu Umer Ibnu Sadik Manhaj Salaf Is My Way(መንሀጀ ሰለፍ መንገዴ ናት)

@abu_umer1


#ቁርአንእናሀዲስ
#ቅድሚያ_ለተውሂድ_እና_ለሱና
#የሰለፊይ_ኡስታዞች_ሙሀደራዎች




#የተለያዩ_ዲናዊ_ፅሁፎች
#የደጋግ_የቀደምቶች_ታሪክ

Abu Umer Ibnu Sadik Manhaj Salaf Is My Way(መንሀጀ ሰለፍ መንገዴ ናት)

24 Oct, 11:19


አላህ ባሪያውን መልካም ነገር ሲሻለት ልቡን ይሠብረዋል ከዚያም ወደ አላህ መመሻን መንገድ ይሠጠዋል።ተሠበርን ማለት በቃ ህይወት አበቃች ታጠረች ማለት አይደለም እንደውም መልካሙን ነገር እያሠብን እንድንጓዝ ጌታየ ብለን እሡን እንድናስታውስ የዋለልን ውለታ ነው
✍️Umu Imran

https://t.me/Abu_Umer1

Abu Umer Ibnu Sadik Manhaj Salaf Is My Way(መንሀጀ ሰለፍ መንገዴ ናት)

23 Oct, 06:38


የወንድ ልጅ ውበቱ ጺሙ ነው
የሴት ልጅ ውበት ደግሞ ኒቃቧ ነው
አራት ነጥብ እነዚህን አግልሎ ውበትን መፈለግ ከንቱ ድካም ነው።

Ibnu Menur

https://t.me/Abu_Umer1

Abu Umer Ibnu Sadik Manhaj Salaf Is My Way(መንሀጀ ሰለፍ መንገዴ ናት)

22 Oct, 18:36


ሼር ማድረግ እንዳይረሳ ባረከላህ ፊኩም

Abu Umer Ibnu Sadik Manhaj Salaf Is My Way(መንሀጀ ሰለፍ መንገዴ ናት)

22 Oct, 18:35


ትኩረት የሚሰጣቸው ጉዳዮች

ቢድዓን “ቢድአቱል ሀሰናህ” (መልካም ፈጠራ) እና “ቢድዓቱ ሰይአህ” (መጥፎ ፈጠራ) በሚል የከፈለ እርሱ ስህተተኛ ፣ ተሳሳች እና ለሚከተለው የረሱል ንግግር ተቃራኒ ነው፡

“ማንኛውም ቢድዓ ጥመት ነው”

ምክንያቱም ቢድዓ በሁሉም አይነት ቢሆን ጥመት እንደሆነ ረሱል ﷺ በዚህ ንግግራቸው ወሰኑ፡፡

ይህ ሰው ደግሞ “ሁሉም ቢድዓ ጥመት አይደለም ፣ ይልቁንም የቢድዓ መልካም አለው” እያለ ነው፡፡

ሀፊዝ ብን ረጀብ “ሸርህ አልአርበዒን” በተባለው ኪታባቸው የሚከተለውን ተናግረዋል ፡

“ሁሉም ቢድዓ ጥመት ነው” የሚለው የረሱል ﷺ ንግግር አጠቃላይ ከሆነው ንግግራቸው ውስጥ ነው፡፡ ከእርሱም አንድም ነገር ተቀንሶ የሚወጣ የለም፡፡ እርሱ ከዲን መሰረቶች ትልቅ የሆነ መሰረት ነው፡፡ “በዚህ ጉዳያችን ከእርሱ ያልሆነ አዲስን የፈጠረ ፣ እርሱ ተመላሽ ነው” የሚለው የረሱል ﷺ ንግግርም ተመሳሳይ ነው፡፡ ማንኛውም ከዲን መሰረት የሌለውን አዲስ ነገር የፈጠረ ከዚያም ወደ ዲኑ ያዛመደ እርሱ ወደርሱ ይመለስበታል፡፡ እርሱ ጥመት ነው፡፡ ዲን ከእርሱ የጸዳ ነው፡፡ ይህ ደግሞ በእምነት ጉዳዮችም ይሁን ወይም በተግባራት ፤ ከንግግር ግልጽም ይሁን ስወር ተመሳሳይ ነው”

'መልካም ቢድዓ አልለ' በማለት የተናገሩ ሰዎች በተራዊህ ሶላት ዙሪያ ኡመር 'ይህች ያማረች ቢድዓ ነች' በማለት የተናገረው ንግግር እንጅ ሌላ መረጃ የላቸውም፡፡

በተጨማሪ የሚከተለውን ተናግረዋል ፡

ቀደምቶች ያላወገዟቸው በርካታ ነገሮች ተፈጥረዋል፡፡ ለምሳሌ ቁርዓንን በአንድ መጽሐፍ መሰብሰቡ ፤ ሐዲስ መጻፉና በጥራዝ ሆኖ መዘጋጀቱ ነው፡፡

ለዚህ ምላሽ ፡ እነዚህ ነገሮች አዲስ የተፈጠሩ ሳይሆኑ ፣ በሸሪዓ መሰረት ያላቸው ናቸው፡፡

“ያማረች ቢድዓ” በማለት ኡመር የተናገረው “ቢድዓቱ ሉገውያ” (ቋንቋዊ ቢድዓ) እንጅ ሸሪዓዊ ቢድዓን አይደለም የፈለገው፡፡ በሸሪዓ መሰረት ያለው ነገር ሁሉ ወደርሱ ይመለሳል፡፡

(የሸሪዓ መሰረት ኖሮት) “ይህ ነገር ቢድዓ ነው” ከተባለ ሸሪዓዊ ሳይሆን ቋንቋዊ ነው፡፡ ምክንያቱም ቢድዓ በሸሪዓ ወደርሱ የሚመለሱበት መሰረት የሌለው ነው፡፡

ቁርዓን በኪታብ ውስጥ መሰብሰቡ የሸሪዓ መሰረት አለው፡፡ ምክንያቱም ነብያችን ቁርዓን እንዲጻፍ አዘው ነበር፡፡ ይሁን እንጅ ቁርዓን በተለያዩ በሚጻፍባቸው ነገሮች (ለምሳሌ ፣ በቆዳ ፣ በጣውላ ..) ተበታትኖ ተጽፎ ስለነበር ሶሃቦች እርሱን ለመጠበቅ ሲሉ በአንድ መጽሐፍ ተሰባስቦ እንዲጻፍ አድርገዋል፡፡

ነብዩ ﷺ የተራዊህ ሶላትን የተወሰኑ ሌሊቶችን ለሶሃቦች ኢማም ሆነው አሰግደዋል፡፡ ከዚያም በእነርሱ ላይ ፈርድ ይሆናል ብለው በመስጋት ወደኋላ ቀሩ፡፡ ሶሃቦቹ ግን ነብዩ በሂዎት እያሉ ከሞቱም በኋላ የተበታተኑ ሆነው ስግደታቸውን ቀጠሉ፡፡ በመጨረሻ ኡመር በነብዩ ﷺ ጀርባ እንደሚሰግዱት ሁሉ በአንድ ኢማም ጀርባ ተሰባስበው እንዲሰግዱ አድርጓቸዋል፡፡ ይህ በዲን ቢድዓ አይደለም፡፡

በተመሳሳይ ሀዲስን በኪታብ መልኩ መጻፉ በሸሪዓ መሰረት አለው፡፡ የተወሰኑ ሶሃቦች ሐዲስ እንዲጻፍላቸው ሲፈለጉ ነብዩ ﷺ እንዲጻፍላቸው አዘዋል፡፡ ጥቅል በሆነ ሁኔታ እርሱን መጻፉ አደጋ የነበረው በረሱል ﷺ ዘመን ነበር፡፡ ምክንያቱም ከእርሱ ያልሆነው ከቁርዓን ጋር ይቀላቀላል ተብሎ ስለተፈራ፡፡ ከሞቱ በኋላ ግን ይህ ስጋት በመወገዱ ቁርዓን ከመሞታቸው በፊት በተሟላ ሁኔታ ተደራጀ፡፡ ሙስሊሞችን ከጥፋት ለመጠበቅ ሱናን በኪታብ ጠረዙ፡፡ ስለኢስላም እና ሙስሊሞች ለዋሉት ውለታ አላህ ጀዛቸውን ይክፈላቸው፡፡ የጌታቸውን መጽሐፍ የነብያቸውን ሱና ከጥፋትና ከቀልደኞች ጥፋት ጠበቁት፡፡

https://t.me/alateriqilhaq

https://t.me/Abu_Umer1
https://t.me/Abu_Umer1

كن على بصيرة

Abu Umer Ibnu Sadik Manhaj Salaf Is My Way(መንሀጀ ሰለፍ መንገዴ ናት)

22 Oct, 05:23


የመርካቶው ቃጠሎ ብዙ ሰዎችን ለአመታት የለፋበትን ንብረት ሀብት አውድሞባቸዋል። አላህ በተሻለ ይተካላቸው። እኛም አቅማችን በፈቀደው ልክ ልናግዛቸው ይገባል። ያልቻልን ደግሞ ዱአ እናድርግላቸው።

https://t.me/Abu_Umer1

Abu Umer Ibnu Sadik Manhaj Salaf Is My Way(መንሀጀ ሰለፍ መንገዴ ናት)

21 Oct, 20:13


"አላህ ሆይ መርካቶ ላይ የተነሳውን እሳት በእዝነትህ ዝናብ በማዝነብ አስቁመው"

Abu Umer Ibnu Sadik Manhaj Salaf Is My Way(መንሀጀ ሰለፍ መንገዴ ናት)

21 Oct, 04:04


"እድለኛ ብሎ ማለት ቀኑን በቁርአን እና በዚክር የጀመረ ነው እድለ ቢስ ብሎ ማለት ደግሞ ቀኑን በዛዛታ እና በሀራም ወሬ የጀመረ ነው"

እና ከየትኞቹ ናቹህ? መልሱን ለእናንተ ተውኩት። ለማንኛውም ቁርአን ያልቀራቹ ቅሩ ለምን አንድ አያ አይሆንም።

https://t.me/Abu_Umer1

Abu Umer Ibnu Sadik Manhaj Salaf Is My Way(መንሀጀ ሰለፍ መንገዴ ናት)

20 Oct, 19:54


"በሌሎች የምንቃወመውን በራሳችን ሲሆን የማቀፍ ስራ የለንም በማንም ላይ ድንበር ማለፍ አልተፈቀደልንም ሸር በሸር አይመለስም  የአህለል ቢደአዎች (ኢኽዋኖች፣ኢብኑ መስኡዶች ፣ እነ ኢብኑ ሙነወር፣ሀጁሪዮች) ጥፋቶች በኢልም ኒቃሽ ይደረጉ እንጂ በሙሃተራ መሆን የለበትም ብዙ ጊዜ  ወጣ ያሉ ቃላቶች ሲሰነዘሩ እመለከታለው የሰው ወዳጅ ቢኖረንም የወንጀል ወዳጅ የለንም በኢልም በፈዋኢድ እናተኩር በልካችን እንኑር ምክሬ ለሁላችንም ነው።"
የኡስታዛችን አቡ አብዱራህማን ምክር ነው እናም ውድ ሰለፊዮች እኔንም እናንተንም ጨምሮ ያካተተ ምክር ነው። ስለዚህ ከአሁን በኃላ በቻልነው ልክ ከማይሆኑ እኛን ከማይመጥኑ ንግግሮች ምልልሶች መራቅ አለብን። በኛ ምክንያት ዲናችን መንሃጃችን ኡለሞቻችን ሊሰደቡብን አይገባም።

https://t.me/Abu_Umer1
https://t.me/Abu_Umer1

Abu Umer Ibnu Sadik Manhaj Salaf Is My Way(መንሀጀ ሰለፍ መንገዴ ናት)

20 Oct, 05:39


አንድ እብድ የሆነ አካል ተነስቶ በጥፊ ቢመታህ ብያናድህም ከራሱ እንዳልሆነ ስለምታቅ ይቅር ትለዋለህ።
👉ከጥቂት አመታት በፊት ሁሉም ሰለፍይ አንድ ነበር። ከዛም ፊትናው ተነሳ።
ፊትና እንደስሙ ፊትና ነው ሜዳ ላይ እንዳለች ዛፍ ወደ ሁሉም አቅጣጫ ያናውጥሃል።
አላህ ያዘነለትና ያገዘው ቶሎ ወደ ፅናት መጥቶ በነበረበት ይረጋል።
ሌላው በግዜአዊነት እየተንሳፈፈ ይቆያል።

👉አሁንም ብዙ የተንሳፈፉ ወንድሞችና እህቶች በዚ ሚድያ እያየን ነው።
ታዳ እንዴት ነው ሀቁ እኔዲገባቸው የምናደርጋቸው? ወይስ የባሰ ስሜታቸውን በመንካት ማደናበር ነው ያለብን።??

👉አየህ ወንድምህ ሲበድልም ሲበደልም እርዳው። ሲበደል አግዘው ገላግለው ሲበድል እጁን ያዘው። ነው

👉አንዳንዶቻችን መርዳት ባንችል ለመራቃቸው ሰበብ አንሁን።የግል ፕሮፋይላቸውን እየበረበርን ለአይን አናስጣው።

👉ኢስላማው ሀቁን እንጠብቅለት። ጀህል ካለበት እናስረዳው ሹብሃ ካለበት እንግለፅለት።

👉 አላማችን አንርሳ ። እሱም ሽርክን መዋጋትና ተውሂድን ማንገስ ነው።

👉በመጨረሻም ሙሉ ዲን ይዘን በአንድ እርስ አንገደብ። በተለይ እህቶች አላህን ፍሩ ሀቂቃ እናንተም ፊትና አይታመንላቹም።ቀልብ ተገለባባጭ ናት። ለነፍሳችን መጨነቅ ለወንድማችን ደሞ ማዘን ግዴታችን ነው።

👉እህቶች ግዜቹን እየመነዘራቹ ለግለሰቦች አትበትኑት።

ibn Taymiyyah

https://t.me/Abu_Umer1

Abu Umer Ibnu Sadik Manhaj Salaf Is My Way(መንሀጀ ሰለፍ መንገዴ ናት)

19 Oct, 09:07


ከውጭ በተለይም ከአረብ ሃገር ወደ ኢትዮ የምትገቡ ወገኖች በተለይ እህቶች አዲስ አበባ ቦሌ ኤርፖርት ላይ እባካችሁ ጥንቃቄ አድርጉ …ደጋግመን እያሳወቅን ነው ግን ብዙዎቻችሁ አትሰሙም ስትነገሩ

የራሳችሁ የምታውቁት ሰው ቤተሰብ ካልሆነ ማንንም ሰው አትቅረቡ ልሸኛችሁ ቢላችሁ አምናችሁ መኪና ላይ አትግቡ

አሁን ላይ ደግሞ አረብኛ ተናጋሪ ሴቶችን አሰማርተው ነው እየዘረፉ ያሉት ባለፈው አንድ ሳምንት ብቻ አራት እህቶች ሙሉ ሻንጣና ንብረታቸውን በዚህ መንገድ ተዘርፈዋል

አረብኛ ስለተናገሩ ብቻ አትመኑ…ተናግረናል

መል ዕክቱን ለሌሎችም ሼር በማድረግ አስተላልፉ በጎነት ለራስ ነው

ኮፒ
https://t.me/Abu_Umer1
https://t.me/Abu_Umer1

Abu Umer Ibnu Sadik Manhaj Salaf Is My Way(መንሀጀ ሰለፍ መንገዴ ናት)

18 Oct, 13:19


ረሱል (ዐለይሂ_ሰላም) ስሰግድ እንዳያችሁኝ ስገዱ አሉ ስግደታቸውን ስናይ ውስጡ ላይ ...التحيات لله የሚልን አገኘን ቱርጉሙንም ስንጠይቅ «ዝቅዝቅ ማለት ለአሏህ ብቻ ነው» ተባልን!
እንዲህ ብለው ለነገሩንም ሰዎች ዝቅዝቅ ሲባልላቸው አየን! ዝቅዝቅ ማለት ለአላህ ብቻ ነው አላላቹህንም ወይ ብለን ስንጠይቃቸው?!
ወልዮችን አትደፋፈር ውሃብይ አሉን!
መልሳችን ግን አዎ ለአላህ ብቻ የሚገባውን አምልኮ ከሱ ውጭ ላለ ሲሰጥ አይተን መቃወማችን ውሃቢይ የሚስብለን ከሆነ ውሃብይ ነን።
لأن الوهاب وهبنا التوحيد

Mubarak Sabir

https://t.me/Abu_Umer1
https://t.me/Abu_Umer1

Abu Umer Ibnu Sadik Manhaj Salaf Is My Way(መንሀጀ ሰለፍ መንገዴ ናት)

17 Oct, 20:21


ወላሂ
👉 ሼህ ሁሴን አስ_ስልጢን በጥሞና አላዳመጥኳቸውም የሓዲስ ጥናትን ቢጣፍጠኝ እንጂ።

👉ሼህ አብዱልሃሚድን በጥሞና አላዳመጥኳቸውም በመንሃጅ ፀንቶ መሞት ቢናፍቀኝ እንጂ።

👉ሼህ ሐሰን ገላፍ በጥሞና አላዳመጥኳቸውም ትልቅ ሆኜ ዝቅ ማለትን ብያምረኝ እንጂ።

👉ኡስታዝ ሙሃመድ ኪርማኒን በጥሞና አላዳመጥኩትም አውቄ ያወኩትን ለትውልድ ማስተማርን ቢናፍቀኝ እንጂ።

👉ኡስታዝ በሃሩ ተካን በጥሞና አላዳመጥኩትም ዳኢ ሆኜ  በፅናት የነብያት ዳእዋን ማሰራጨት ብያጓጓኝ እንጂ።

👉ኡስታዝ ሻሚል በጥሞና አላዳመጥኩትም ከሚድያ ፊትና ርቄ ለአላህ ብዬ ማስተማርን ብያምረኝ እንጂ።


ሁሉም የሰለፍያ አይነታዎች ልዩ መለያ አላቹኮ
አላህ ያቆያቹ በዱንያም በአኺራ አይለያያቹ።
እኛንም የናንተን ቦታ የምንተካ ያርገን።

https://t.me/Sunna_tube
https://t.me/Sunna_tube
https://t.me/Sunna_tube
https://t.me/Sunna_tube
https://t.me/Sunna_tube
https://t.me/Sunna_tube
https://t.me/Sunna_tube

Abu Umer Ibnu Sadik Manhaj Salaf Is My Way(መንሀጀ ሰለፍ መንገዴ ናት)

16 Oct, 17:34


👉  ከጭንቅ መውጫው መንገድ

     ኢብኑል ጀውዚ ረሂመሁላሁ እንዲህ ይላል :-

" ነገሩ ከብዶኝ ተጠበብኩኝ የማይላቀቅ የሆነ ጭንቀት ያዘኝ , በምችለው ዘዴና አቅም ከዚህ ጭንቅ ለመውጣት የምችለውን ሁሉ ማሰብ ጀመርኩ ። ምንም መውጫ እንደሌለ አየሁ ። በዚህን ጊዜ እንዲህ የሚለው የአላህ ቃል መጣልኝ :–
" አላህን የፈራ ሰው ከጭንቅ ሁሉ መውጫ ያደርግለታል " 
      ከዚያም አላህን መፍራት የጭንቅ ሁሉ መውጫ መሆኑን አወቁኝ ። በምችለው ሁሉ አላህን መፍራት ጀመርኩ ። ከጭንቄም መውጫ አገኘሁ ። ለሰው ልጅ ማሰብም ሆነ መመካት ያለበት የአላህን ትእዛዝ በመፈፀም ላይ ነው
ይህ ለሱ የተዘጋን ሁሉ ለማስከፈት ሰበቡ ነው "

ሰይዱል ኻጢር ገፅ ( 63 )

https://t.me/bahruteka

https://t.me/Abu_Umer1
https://t.me/Abu_Umer1

Abu Umer Ibnu Sadik Manhaj Salaf Is My Way(መንሀጀ ሰለፍ መንገዴ ናት)

16 Oct, 14:28


ሰለምቴዎችን በሰለምቴነታቸው የሚሳደብ ሰው የተሸከመው ጭንቅላት ሳይሆን ድንጋይ መሆኑን ይመን። በመንሃጃቸው በአቂዳቸው ላይ ክፍተት ሲያዩ ሰለምቴ እያሉ ይሳደባሉ። ከቀድሞቶች አንዱ እንዲህ ብሎ ነበር"ከሙብተዲኦች አቅል ያለውን አይቼ አላውቅም" አዎ ሙብተዲኦች አቅል የላቸውም። አቅል ቢኖራቸው ኖሮ ሰለምቴ እያሉ ሙእሚን ወንድም እና እህቶቻቸውን ባላነወሩ ነበር።

https://t.me/Abu_Umer1

Abu Umer Ibnu Sadik Manhaj Salaf Is My Way(መንሀጀ ሰለፍ መንገዴ ናት)

15 Oct, 18:39


"አቂዳቸው መንሃጃቸው ተስተካክሎ ነገር ግን አህላቅ የሌላቸው ሰዎች በተወሰነ መልክ ሰለፎችን ተፃረዋል ያም በስነ ምግባር ብልሹነት ነው። ስለዚህ አኽላቅ ማሳመር ላይ ከአቂዳ እና መንሃጅ ቀጥሎ ትኩረት ሊደረግበት ይገባል።"

https://t.me/Abu_Umer1

Abu Umer Ibnu Sadik Manhaj Salaf Is My Way(መንሀጀ ሰለፍ መንገዴ ናት)

14 Oct, 19:13


የቂን…

የቂን ማለት ዙርያህ ሁሉ በተስፋ አስቆራጭና ድቅድቅ ጨለማ የተሞላ ቢሆንም አላህ ያሰብኩትን ሁሉ ያሳካልኛል ብሎ ማሰብ ነው።

https://t.me/Abu_Umer1

Abu Umer Ibnu Sadik Manhaj Salaf Is My Way(መንሀጀ ሰለፍ መንገዴ ናት)

13 Oct, 11:31


      ➡️   የምቀኝነት ክርፋት ግሳት

     በየአንዳንዱ ሰው ውስጥ ምቀኝነት አለ ። አላህን የሚፈራው ታግሎ ይደብቀዋል ። ወራዳ ግን በአሳፋሪ ሁኔታ ግልፅ ያደርገዋል ። በዚህም ማንነቱን አገር ያውቀዋል ።
     በሚሊኒየሙ ፕሮግራም ሲንጨረጨር የነበረው የሙነወር ልጅ በብስጭት በሚወራጩ ጣቶቹ የሞነጫጨረውን አንድ ወንድም ፎርዋርድ አድርጎልኝ ነበር ። በጣም የሚገርመው ይህ ሙንጭርጭር የተለጠፈው ኦክቶበር 10 መሆኑንም እስክሪን ሻት አድርጎ ልኮልኛል ። ለኛ የፕሮግራሙ መሸጋሸግ አስፈላጊነት የተነገረንና የለጠፍነው ኦክቶበር 11 ነው ። ታዲያ የሙነወር ልጅ ኦክቶበር 10 ላይ ስለፕሮግራሙ መስተጓጎል ያወራው በጥንቁልና ይሆን ወይስ እንዲስተጓጎል ካደረጉት አካላት ጋር ግንኙነት ነበረው ?  መልሱን ለራሱ ።
    የለጠፈበትን ቀን በሚቀጥለው ሊንክ ገብተው ይመልከቱ : –  👇👇👇👇👇👇👇👇
https://drive.google.com/file/d/1MMHa5GFqsFig27MDOEvvdWf81Q1ykjz9/view?usp=drivesdk
     አንድ ፅሑፍ መች እንደተለጠፈ ለማወቅ እስክሪኑ ላይ ፁሑፉን ትንሽ ወደታች ካደረጉት በኋላ በመጠኑ ተጭኖ ወደ ላይ ሲደረግ ከላይ ጫፍ ላይ ይመጣል ።
      የሙነወር ልጅ ውስጡ ታምቆ ሲያስጨንቀውና አብጦ ሊፈነዳ የደረሰውን የምቀኝነት ክርፋት በማግሳት ሲያወጣው ካነሳቸው ነጥቦች ውስጥ ገና ከርእሱ እንዲህ ይላል : – 
    " እዩኝ ፣ እዩኝ ማለት ደብቁኝ ፣ ደብቁኝ ማለት ያመጣል " ።
      ይህ አገላለፅ " ሸማተተል አዕዳእ " ( የጠላት መዘባበት ) ይባላል ። ለመሆኑ የሙነወር ልጅ ጠላትነቱ ለባሕሩ ወይስ ለዳዕዋው ? በምኑ ነው እየተዘባበተ ያለው ? ሌላው የተውሒድ ዳዕዋ አለ ብሎ ማስተዋወቅ እዩልኝ ማለት ነው ? ደብቁኝ የሚያሰኝ አሳፋሪ ስራ ስላልሰራን እንድንል የሚያደርገን ነገር የለም ። ይልቁንም ይበልጥ ወደፊት ነው የምንሄደው አላህ ካለ በውጤቱ ታየዋለህ ። የበለጥ ለመበሳጨት ተዘጋጅ !!!
   በዚህ ነጥብ ላይ ብዙ በማለት አንባቢያንን ማሰልችት አልፈልግ ። 
     በመቀጠል ጥቂት ነጥቦችን ብታስተውሉ ብሎ ምክር በሚል ልብስ የተሸፈነ የማንነቱ ማሳያ መክሮችን እንዲህ እያለ ይዘረዝራል ። ከእነዚህ ውስጥ : –
  – 2ተኛ ላይ ምክር በሚመስል መልኩ ብዙ ከሞነጨረ በኋላ ውስጡ ያለውን የተደበቀ ማንነቱን ሲገልፅ እንዲህ ይላል : –
    " ብዙ ሰው ያላቸው አካላት ጋር ትከሻ እየተለካኩ ሲንገዳገዱ ከማዘን በአቅም ልክ ማሰብ ይሻላል "
     ይህ እንግዲህ ነሲሓዎች ሚሊኒየም አዳራሽ ላይ ረመዳን መግቢያ አካባቢ አሕባሾችን ፣ ሱፍዮችን ፣ የኢኽዋን መሪዮችን የክብር እንግዳ አድርገው ጠርተው እነዚህን አካላት ዑለሞቻችን ፣ ዶክተራችን እያሉ ያሞካሹበትን ፕሮግራም ለማስታወስ ያደረገው ነው ። ለመሆኑ ከእነዚህ አካላት ጋር ትከሻ ስንለካካ የት ሆነህ ነበር ያየኸን ? የአቅም መለኪያህ ብዛት መሆኑን ማሳየትህን ከዚህ ነው የምትጀምረው ። የተከታይ ብዛት መኖር አቅም አፈርጥሞ የፈለጉትን ማድረግ እንዲቻል የያደርጋል በሚል ስሌት ነው ተከታይ ለማብዛት መከራህን እያየህ ያለኸው !!! ለመሆኑ ነሲሓዎች አንተ በምትለው መድረክ ላይ የክብር እንግዳ ብለው በጠሩት አካል የተዋጣላቸው ለማኞች ናቸው እኔ ካለሁበት አካባቢ በአንድ ቀን 8 ሚሊየን ብር ሰብስቧል ሲባሉ አድንቀሃቸው ነበር ማለት ነው?  ዛሬ ስለአቅማቸው እያወራህ አድናቂ ተከታያቸው መሆንህን የምትገልፀው ። ወይስ ከነበርክበት አቋም ወርደህ እነርሱ ሰፈር እንትገባ ያደረገህ የሰለፍዮች ምስኪንነትና የእነርሱ በልመና ያካበቱት ሀብት ነው ? የኛ ሀገር አቀፍ የዳዕዋ ፕሮግራም በሀገሪቱ ዋና መዲና ላይ በሚሊኒየም አዳራሽ ለማድረግ መከራየት ለምን በዚህ መልኩ አስጨነቀህ ? እውነት የኛ አቅምና የተከታይ ማነስ አሳስቦህ ወይስ ነሲሓዎች እንዴት ተደፈሩ የሚል ስሜት ? አሁንም መልሱ ለራስህ ትቼዋለሁ ።
     እይታህ እርስ በርሱ የሚጋጭ መሆኑ እዚህ ጋር ተከታያችን ትንሽ ሰለሆነ አቅም እንደሌለን እየነገርከን መልሰህ ደግሞ ስለኛ ተከታዮች ብዛት ሊቀንስ እንደሚችል ትተነብያለህ ።!!!
  –  4ተኛ ላይ እንዲህ ይላል : –
          "  ኢኽላሳችሁን ፈትሹ ፣ የቀስድ መበላሸት ብዙ ነገር ያበላሻ "
      አቶ ኢብኑ ሙነወር አንተና አምሳያዎች ደጋግማችሁ ሰዎች የሆነ ሰራ በሰሩ ቁጥር ዘላችሁ ኢኽላስ የሌለው መሆኑን ለማሳየት ትጥራላችሁ ኧረ እንደውም መሀላ ሁሉ ይቃጣችኋል !!! ለመሆኑ በሰው ንያ ውስጥ ስላለ ነገር በዚህ መልኩ መቀባጠር የሩቅ ሚስጢር አውቃለሁ ማለት እንደሆነና ተውሒድን የሚያበላሽ መሆኑን ረስታችሁት ነው ወይስ የኪታቡ ተውሒድን መትን እንኳን አልቀራችሁም ? 
    – ወደ ማጠቃለያ አካባቢ ካነሳቸው ሁለት ነጥቦች ውስጥ መጀመሪያ ላይ እንዲህ ይላል : –  " አንድ ነገርአስረግጬ ልንገራችሁ ። ቁጥራችሁ አሁን ካለውም የበለጠ እያነሰ ነው የሚሄደው "
      ሱብሃነላህ የቁጥር ማነስና መብዛት እዚህ ድረስ ነው የሚያስጨንቅህ ? ቅድም ቁጥራችሁ ትንሽ ነው አቅም የላችሁም ከነሲሓዎች ጋር ትከሻ አትለካኩ እነርሱ ብዙ ተከታይ አላቸው ስትል ነበር ። አሁን ደግሞ የኛ ቁጥር መብዛ ምን ያክል እያስጨነቀህ መሆኑና ህልም ቀንሶ ማየት እንደሆነ በዚህ ልክ እየነገርከን ነው ። በመጀመሪያ ደረጃ ወደ ፊት ስለሚሆነው ነገር አስረግጬ ልንገራችሁ ብለህ የሩቅ ሚስጢር መናገርህን መቀጠልህ ከተውሒድ አስተምሮ ርቀህ ነሲሓዎች ስፈር መግባት በእንደነዚህ አይነት ትላልቅ የዐቂዳ ግድፈቶች ውስጥ እንድትዘፈቅ እንዴት እንዳደረገህ ተመልከት !!! ቢያንስ ተውበት አድርገህ ተመለስ ። ሌላው ከሚቀጥለው ነጥብ ጋር ስለሚመሳሰል አንድ ላይ እመልሰዋለሁ ።
    – ከማጠቃለያ ነጥቦቹ ሁለተኛው አሁንም ከብዛት ጋር በተገናኘ እንዲህ ይላል : –
    " በሆይሆይታ ያሰለፋችኋቸው መንጋዎች ወደ ቀልባቸው ሲመለሱ እናንተ ከምትሾፉሩት የስሜት ባቡር እየተንጠባጠቡ ይወርዳሉ ።
     ይህ እያብከነከነው ያለውን ቁጥራቸው በዛ የሚለው የምቀኝነት እብጠት ክርፋት ያገሳህበት የመጨረሻ ሀሳብ ነው ። አሁንም በቁጭትህ ሙት እኛ ከቁጥር ጋር ግንኙነት የለንም ። አንተ የስሜት ባቡር ያልከው የሱና መርከብ ላይ ያሉ ሰዎች አላህ ያጠብቃቸውና ሳይሆን ቀርቶ ዛሬውኑ ከሱናው መርከብ ወርደው ባንተ የስሜት ባቡር ላይ ቢሳፈሩ ምንም አይመስለንም ። የአላህ መልእክተኛ የመካ አጋሪያኖች በስምምነቱ ላይ ከኛ ሰልሞ ወደናንተ የሄደውን ወደኛ ትመልሳላችሁ ከናንተ ከፍሮ ወደኛ የመጣውን ግን አንመልስም ሲሉዋችው የሰጡትን መልስ ነው ላንተም የምሰጥህ ።
     የአላህ መልእክተኛ እንዲህ ነበር ያሉት " አላህ ከእዝነቱ ያባረረው ሰው ወደኛ ቢመጣ ምን ያደርግልናል ከእነርሱ ወደኛ መጥቶ የሚመለሰው ግን አላህ መውጫ ያደርግለታል "።
     ልክ እንደዚሁ ዛሬ ከሱናው መርከብ ተንጠባጥቦ ወርዶ ወደ ቢዳዓው ባቡራችሁ የተሳፈረ ለኛ ምን ያደርግልናል ። የቂያማ ቀን ነብይ ሆኖ አንድ ሰው ሳይከተለው ብቻውን የሚመጣ መኖሩን የአላህ መልእከተኛ የነገሩን የሱና ሰዎች ነንና ይህ ለኛ ምናችንም አይደለም ።
      በመጨረሻም ይህን ስሜታችሁን አይተው ነው ኢኽዋንና ነሲሓዎች የተጫወቱባችሁ ። ለማንኛውም ከገባችሁበት የምቀኝነት አሮንቋ አላህ ያውጣችሁ የሚለው ዱዓችን ነው ።
   
http://t.me/bahruteka

Abu Umer Ibnu Sadik Manhaj Salaf Is My Way(መንሀጀ ሰለፍ መንገዴ ናት)

12 Oct, 17:53


🔹 የአላህ ጥበብ እያደር ግልፅ ይሆናል

    ለኮንፈረሱ የመግቢያ ትኬት የተላከላችሁ
ወንድሞች የተሸጠው በአካውንቱ አስገብታችሁ ቀሪው ትኬት እናንተው ዘንድ አድርጉት ። በፕሮግራሙ መራዘም በተለያዩ ቅድመ ሁኔታዎች የወጣው የተወሰነ ገንዘብ ቢከስርም አብዛኛዎቹ አላህ ካለ የምንጠቀምባቸው ይሆናል ። ለአዳራሹ ተከፈለው ላይ የተወሰነ እዳ ይኑር እንጂ ፕሮግራሞች ሲስተካከሉ እንደምንጠቀምበት ነግረውናል ። ባጠቃላይ በፕሮግራሙ መራዘም የተገኙ ድሎችና የአላህ ሒክማ እኛ አሁን ያየናቸው ያሉ ሲሆን ወደፊት ደግሞ አብረን የምናየው ይሆናል ። 
       የአላህ መልእክተኛ 1400 ሶሓቦችን ለዛው በአላህ ትእዛዝ ወደ መካ ዑምራ ሊያደርጉ ሐርመው ይዘው መጥተው ለዘንድሮ ተመለስ በሚቀጥለው አመት ታደርጋለህ መባሉ በሶሓቦች ስነልቦና ላይ ያሳደረው ተፅኖና እናስታውስ ። ወደ መካ እየተመለሱ ሳሉ ድል መሆኑ በወሕይ ከመነገሩ ጀምሮ መካ እስከተከፈተና የተውሒድ ባንዲራ ከየአቅጣጫው ከፍ ብሎ እየተውለበለበ ወደ ካዕባ ሲያመሩ ሙሉ በሙሉ ሒክማው ለሁሉም ፍንትው ማለቱን ስናይ የድሉና የጥበቡ ውጤት በተስፋ እንድንጠብቅ ያደርገናል ።
      መርሳት የሌለብን አላህ ያለ ሒክማ ምንም ነገር የማይሰራ መሆኑንና  ሒክማውን ለባሮቹ በየደረጃው እንደየአስፈላጊነቱ ግልፅ የሚያደርግ መሆኑን ነው ።

http://t.me/bahruteka

https://t.me/Abu_Umer1
https://t.me/Abu_Umer1

1,721

subscribers

287

photos

48

videos