ᴇʟɪᴀꜱ ᴍᴇꜱᴇʀᴇᴛ

@eliasmeseret


Journalist-at-large

ᴇʟɪᴀꜱ ᴍᴇꜱᴇʀᴇᴛ (Amharic)

የእነሱ የዳንኤል ሜስርት ድርጅት በሙሉ ሊሆን ይችላሉ። የትኩስ ምርጫዎችን በማስተዋወቅ ከግል የሆነ ድርጅትን ዘግተዋል። እነዚህ ድርጅቶችን ከእባኮት ጋር በማገኘት ወሰን በአንድ ላይ ያድርጉትን መስራት ይችላል። አቶ ኤልያስ መስራት የሚጠና ጽሑፉን ይዞ ፀሐይ አልጠበቀም። ኤልያስ ከተጋለፍ እስኪያል እና በማስተዋወቅ በጽሑፍ ተመጣጣሪነት መስራትን ካስብ እንዲህ ነበር። ድርጅቶችን ከእንቅስቃሴ ካስቁ እና በቁጥጥራን አላቅነው። የመጀመሩበት ጊዜ ነገ በቅፅል ለመቀነስ ወደ በላይ ያስመሰሉትን ፊልም ወደቀምሯተር በማድረግ እንደሚከተሉ እና ተቆረጡ። አቶ ኤልያስ ግንባረማ ከተጋለፉ አንደበት ሌላ ጊዜ ሊቀመጡት እንችላለን።

ᴇʟɪᴀꜱ ᴍᴇꜱᴇʀᴇᴛ

19 Oct, 16:38


https://youtu.be/f9FMRVCKYk0?si=DEkkCUS-gyKO-swT

ᴇʟɪᴀꜱ ᴍᴇꜱᴇʀᴇᴛ

18 Oct, 15:25


#ከፍተኛትኩረት በደቡባዊ የሀገራችን ክፍል በቅርብ አመታት ታይቶ የማይታወቅ የወባ ወረርሽኝ ተከስቶ ህዝብ እየረገፈ ነው

በአካባቢው ያሉ የጤና ባለሙያዎች እንደነገሩኝ በወላይታ፣ በከምባታ፣ በጉራጌ ዞኖች እንዲሁም በምስራቅ ወለጋ እና ዙርያው ወረርሽኙ ተባብሷል።

ፈጣን ትኩረት ያሻዋል፣ መሠረት ሚድያ በምሽት ዜናው ሁኔታውን በስፋት ይዳስሳል።

@EliasMeseret

ᴇʟɪᴀꜱ ᴍᴇꜱᴇʀᴇᴛ

16 Oct, 14:53


ከወንድም ጌጡ ተመስገን እና ጓድ ታደለ አሰፋ ጋር በአፍሪካን ኢምፓክት አዋርድ ፕሮግራም

Was fun.

@EliasMeseret

ᴇʟɪᴀꜱ ᴍᴇꜱᴇʀᴇᴛ

15 Oct, 17:15


#ለግልፅነት ከሚሰራበት ቦታ ተባሮ እና የሚኖርበት ቤት እንደሚፈርስ ሲነገረው ራሱን ስላጠፋው አዲሱ ካሳሁን ትናንት አንድ መረጃ እና የድጋፍ ጥሪ አቅርቤ ነበር

እስከ አሁኑ ሰአት ድረስ ብቻ 520,000 ብር (አምስት መቶ ሀያ ሺህ ብር) በባለቤቱ የቀጥታ የባንክ አካውንት ድጋፍ ተደርጎላታል።

ድጋፍ ላደረጋችሁ እንዲሁም መረጃውን በአካውንታችሁ እና ገፃችሁ መልሳችሁ ሼር ላደረጋችሁ ሁሉ ምስጋና ይድረሳችሁ።

@EliasMeseret

ᴇʟɪᴀꜱ ᴍᴇꜱᴇʀᴇᴛ

15 Oct, 15:51


ህዝቡ በጣም ገቢው አድጎ ስለበለፀገ አምና በሳንቲሞች ይጨምር የነበረው የትራንስፖርት ዋጋ አሁን እስከ እጥፍ በሚሆን ጭማሪ አሳይቷል...

የመዓት ግዜ!

@EliasMeseret

ᴇʟɪᴀꜱ ᴍᴇꜱᴇʀᴇᴛ

14 Oct, 14:42


‼️ ከሁለት ሰአት በፊት ያጋራሁት የድጋፍ ጥሪ የባንክ አካውንት ቁጥር እንደማይሰራ (inactive እንደነበር) በገለፃችሁት መሰረት አሁን ተስተካክሏል

ᴇʟɪᴀꜱ ᴍᴇꜱᴇʀᴇᴛ

14 Oct, 12:46


አዲሱ ካሳሁን በአዲስ አበባ ከተማ ከኡራኤል ቤተክርስቲያን ወደ አትላስ ሆቴል በሚወስደው መንገድ አካባቢ በሚገኘው 'በፀጋህ ሆስፒታል' ፊት ለፊት ባለ አንድ ግቢ ነዋሪ ነበር።

አዲሱ ነጠላ ከሚሸጥበት ኡራኤል ቤተከርስቲያን አካባቢ ስራ እንዳይሰራ ሶስት ግዜ በደንብ አስከባሪዎች ተባሮ እና ንብረቱም ተወስዶበት እንደነበር ባለቤቱ እንዲሁም ጓደኞቹ ይናገራሉ።

ከዚህም በተጨማሪ ከአምስት ቀን በፊት ምሽት ወደ ቤቱ ሲገባ ተከራይቶ የሚኖርበት ቤት በነጋታው ጠዋት እንደሚፈርስ ሲነገረው ተስፋ በመቁረጥ ስሜት እዛው ግቢ ውስጥ ራሱን እንዳጠፋ ባለቤቱ በእንባ እየታጠበች ነግራኛለች።

"የዛን እለት ብዙ ሲጨናነቅ ነበር፣ ቤት ሲያጠያይቅ 13 ሺህ እና 15 ሺህ ሲሉት ነበር፣ በዛ ላይ ቤተሰብ ያለው አናከራይም እያሉት። ሊነጋጋ ሲል ራሱን አጥፍቶ አግኝተነዋል፣ አሁን የት እንደምሄድ እና ምን እንደማረግ እንዳለብኝ አላውቅም" በማለት ነግራኛለች።

የሁለት የልጅ አባት የሆነው አዲሱ (አንደኛው ገና 5 ወሩ ነው) ባሳለፍነው አርብ እለት ስድስት ሰአት ላይ በኡራኤል ቤተክርስቲያን ቀብሩ ተፈፅሟል።

ባለቤቱን እማኑሽ ፈንታን በቻልነው አቅማችን እንደግፍ፣ ለማስጀመርያ እንዲሆን እኔም በግሌ የአቅሜን ድጋፍ አደርጋለሁ።

እማኑሽ ፈንታ
ስልክ: +251920660393

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
1000334824652

ᴇʟɪᴀꜱ ᴍᴇꜱᴇʀᴇᴛ

14 Oct, 03:16


የዘንድሮው የአፍሪካ ኢምፓክት አዋርድ ስነ ስርአት ሜሪላንድ በሚገኘውና ኢትዮጵያዊያን በባለቤትነት በሚያስተዳድሩት ሜትሮ ፖይንትስ ሆቴል ዛሬ፣ እሁድ ኦክቶበር 13/2024 ምሽት በደማቅ ዝግጅት እየተካሄደ ነው፣ እኛም በስፍራው ተገኝተናል

በአሜሪካ ዋሽንግተን ዲሲ የተመሰረተውና ለትርፍ ያልተቋቋመው ኖቫ ኮኔክሽን ያዘጋጀው የ2024 አፍሪካ ኢምፓክት አዋርድ የዘንድሮ የክብር የሽልማት ሥነ ስርዓት እየተከናወነ ነው።

ይህ አመታዊ የእውቅና ሽልማት ስነ ስርአት በአሜሪካና በአፍሪካ በሙያቸው ታላቅ ሥራ የሰሩ ግለሰቦችን ለማክበር የተዘጋጀ ነው።

በየአመቱ ከስፖርት፣ ከስነ ጥበብና ከስራ ፈጠራ ዘርፎች ለማህበረሰቦቻቸው ላበረከቱት አስተዋፅኦና ለለውጥ ላደረጉት የላቀ ተሳትፎ ከየዘርፉ ተመርጠው የሚሸለሙበት መድረክ ነው።

አፍሪካ ኢምፓክት አዋርድ እስካሁን ለአራት ጊዜያት ተካሂዷል። ዘንድሮም በተለያዩ ዘርፎች ለአምስት ተፅዕኖ ፈጣሪ ኢትዮጵያዊያንን የክብር እውቅና እየሰጠ ይገኛል።

የዘንድሮ ተሸላሚዎች አርቲስት አስቴር አወቀ፣ ጋዜጠኛ መአዛ ብሩ፣ አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ፣ ወ/ሮ ሬቤካ ሀይሌ እና አትሌት ትግስት አሰፋ ናቸው።

ለግብዣው ዶ/ር ጋሻው አበዛን አመሰግናለሁ።

@EliasMeseret

ᴇʟɪᴀꜱ ᴍᴇꜱᴇʀᴇᴛ

11 Oct, 19:55


https://www.facebook.com/100068497307887/posts/pfbid0Zw69kGWvZPuH9u6VDRtGMvbKAncR76Rnb4jBE3CvLoLxQhvR7JqBKpe7ozvTchANl/

ᴇʟɪᴀꜱ ᴍᴇꜱᴇʀᴇᴛ

11 Oct, 17:38


#FactCheck ኢትዮጵያ የምግብ ሉዓላዊነትን በማረጋገጥ ሂደት ከአፍሪካ 2ኛ ደረጃ ሆነች በሚል የተሰራጨው መረጃ የተሳሳተ ነው

ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ጨምሮ በርካታ የመንግስት ሚድያዎች፣ የግብርና ሚኒስቴር እንዲሁም የማህበራዊ ትስስር ገጽ ተጠቃሚዎች “ኢትዮጵያ የምግብ ሉዓላዊነትን በማረጋገጥ ሂደት ከአፍሪካ 2ኛ ደረጃ ሆነች” የሚል መረጃ አጋርተዋል።

ይህን መረጃ ያጋሩት ሚድያዎች እና ግለሰቦች እንደ መረጃ ምንጭነት የተጠቀሙትም ኢን ኦን አፍሪካ (IOA) የተሰኘ ድረ-ገጽ ነው፡ https://www.inonafrica.com/ 

ይህ በደቡብ አፍሪካ እአአ በ 2007 ዓ/ም የተመሰረተ ተቋም በአፍሪካ ጉዳዮች ላይ ጥናቶችን በማድረግ የሚታወቅ ነው።

ይሁን እንጂ ኢትዮጵያ ቼክ እየተሰራጨ የሚገኘውን መረጃ በተመለከተ የኢን ኦን አፍሪካን ድረ-ገጽን እንዲሁም የማህበራዊ ትስስር ገጾቹን የተመለከተ ሲሆን የተባለው ሪፖርት በድርጅቱ የመረጃ ቋቶች ላይ እንደሌሉ አረጋግጧል።

እየተጋራ በሚገኘው ስክሪን ቅጂው የላይኛው ክፍል ላይ የሚገኙ ጽሁፎች እና ምስሎች ከተቋሙ ትክክለኛ ድረ-ገጽ ጋር ተመሳሳይነት ቢኖራቸውም ሪፖርቱ ግን ትክክለኛው የ ‘IOA’ ድረ-ገጽ ላይ እንደሌለ አረጋግጠናል።

በተጨማሪም ከመረጃው ጋር እየተጋራ የሚገኘው የስክሪን ቅጂ የፊደል አቀማመጥ/ፎንት ስህተቶች የሚታዩበት መሆኑንም ተመልክተናል።

ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት መረጃውን በፌስቡክ ገጹ ካጋራ ከሰዓታት በኋላ መልሶ ማጥፋቱንም ተመልክተናል።

ከሰሞኑ ተመሳስለው የተዘጋጁ ሀሰተኛ ስክሪን ቅጂዎች በስፋት እየተሰራጩ እና በርካቶችን ለስህተት እየዳረጉ ይገኛሉ። በመሆኑም መሰል ስክሪን ቅጂዎችን አምነን መረጃዎችን ከማጋራታችን በፊት ተገቢውን ማጣራት እናድርግ።

Via Ethiopia Check

ᴇʟɪᴀꜱ ᴍᴇꜱᴇʀᴇᴛ

10 Oct, 22:05


በዛሬው እለት በአለም አቀፍ ደረጃ ታስቦ የዋለውን የአእምሮ ጤና ቀን ምክንያት በማድረግ ከክሊኒካል ሳይኮሎጂስት ዶ/ር አወቀ ምህረቱ ጋር በመሠረት ሚድያ ቆይታ አድርጌ ነበር

ከራስን ማጥፋት ጀምሮ እስከ የአእምሮ መቃወስ ያሉ ብዙ ስለማይነገርላቸው ነገር ግን ህዝቡን በከፍተኛ ደረጃ እየጎዱ ስላሉ ጉዳዮች አውርተናል

https://youtu.be/zh8I3sgXGC0?si=Lzh_EnUavzu7ufPy

ᴇʟɪᴀꜱ ᴍᴇꜱᴇʀᴇᴛ

10 Oct, 14:53


Facts matter.

ሙሉ ዜናውን ኢትዮጵያ ቼክ ላይ ያንብቡ: https://www.facebook.com/100068497307887/posts/pfbid02xnTj89oS98WCLQAohDKcMDSDAkp5G7n9wbyzKsBvww4rReKVnQVWRC7HmZDxmjAWl/

@EliasMeseret

ᴇʟɪᴀꜱ ᴍᴇꜱᴇʀᴇᴛ

09 Oct, 09:23


አሻም የህዝብ ድምፅ!

@EliasMeseret

ᴇʟɪᴀꜱ ᴍᴇꜱᴇʀᴇᴛ

08 Oct, 18:27


በዚህ አካሄድ አውሮፕላን መግዛት ሳያዋጣ አይቀርም

Totally insane!

@EliasMeseret

ᴇʟɪᴀꜱ ᴍᴇꜱᴇʀᴇᴛ

04 Oct, 22:56


እንኳን ለደማቁ የእሬቻ በአል አደረሳችሁ፣ አደረሰን!

Baga Irreecha Baranaa Geenye!

መልካም በአል!

@EliasMeseret

ᴇʟɪᴀꜱ ᴍᴇꜱᴇʀᴇᴛ

30 Sep, 22:04


የሰሞኑን የብር መዳከምን (የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን) ተከትሎ ገበያ ላይ ያልጨመረ ነገር የለም ቢባል ማጋነን አይሆንም

ይህ አልበቃ ብሎ የመንግስት ተቋማት ህዝብ ላይ እልህ እየተወጡ ይመስል ተራ በተራ እስከ 700 ፐርሰንት ጭማሪ ያረጉ አሉ።

ኢሚግሬሽን፣ ንግድ ባንክ፣ ኤሌክትሪክ፣ ውሀ፣ ቴሌ፣ አየር መንገድ፣ የመኪና ቦሎ እና መንጃ ፈቃድ፣ የትራፊክ ቅጣት... ከሰሞኑ ደግሞ የዳኝነት ክፍያ እንኳን ጭማሪ ይደረግበታል። የኔ ጥያቄ:

አንደኛ፣ ጭማሪ ሲደረግ ነባራዊ የህዝብን አቅም እና ችግር ማገናዘብ የለበትም ወይ?

ሁለተኛ፣ በሌላው አለም እንደምናየው progressive የሆነ የ10%፣ የ20%... ወዘተ እያለ ጭማሪ ይደረጋል እንጂ ሲፈልግ የ150%፣ ሲያሻው የ700% ጭማሪ ማድረግ ማለት ነው?

ሶስተኛ ደግሞ አንድ ሰሞን ሲወራ የነበረውን ጥቂት የሆነ የደሞዝ ጭማሪ እንኳን ተግባራዊ ሳያደርጉ ህዝብ ላይ ሸክም መጫን ለምን ተፈልጎ ይሆን?

እውነት ይሄ ነገር አንድ ወዳጄ እንዳለኝ "መንግስት ከህዝብ ጋር እልህ ተጋብቶ እየቀጣው ነው" ያለው እውነት ይሆን እንዴ?

ዝመት ሲባል ዘምቶ ለሚቆም፣ ደግፍ ሲባል በሚሊዮኖች ወጥቶ ለሚሰለፍ፣ ሀገርህ ተደፈረ ሲባል "ኢትዮጵያን!" ብሎ ለሚዘምት ግን ይህ አይገባውም።

@EliasMeseret

ᴇʟɪᴀꜱ ᴍᴇꜱᴇʀᴇᴛ

30 Sep, 17:59


#ለግልፅነት በትናንትናው እለት ለእታገኝ አየናቸው ያጋራሁትን የድጋፍ ጥሪ ተከትሎ ከ 375,000 ብር በላይ በቀጥታ በንግድ ባንክ አካውንቷ ተሰብስቧል። አንድ ዶክተርም ለታማሚው ልጅ ህክምና ለመስጠት ፈቃደኛ ሆነዋል።

ድጋፍ በማድረግ ለተካፈላችሁ በሙሉ ከፍ ያለ ምስጋና ይድረሳችሁ።