ለእኔ ባይነገረኝም 😇 የኢየሱስን መምጣት የናፈቁ ልጆች ግን ይሄን መልዕክት ትልቅ ቻሌንጅ አድርገውታል 🥰 እና እናንተ ምን ትጠብቃላቹ...
ሁላቹም በዚህ ሳምንት ቴሌግራማቹን በዚህ ድንቅ መልዕክት አጨናንቁት፤ የእናንተን Profile የሚመለከት ሰው ሁሉ የምጠብቁት አንድ ትልቅ ተስፋ እንዳላቹ ማወቅ አለበት።
ኢየሱስ በቅርቡ ሊወስደን ይመጣል💯
@thedayofpentecost
አዶናይ ለእናንተ የሚሰራው ቻናል በኢየሱስ በመላው ተዘጋጅቶ ከፍ እንዲያመነዝሩና ለሀሳብና አስታየት ብቻ የሚሰጥ ነው። የዚህ Bot መሣሪያችን @AdonaiComments_bot ለመጠቀም እና በመክፈቱ፣ በሀሳብና ለመመከቱም የሚችሉን የቻናል አዝራሮች እንደሚለዋወጡ ጠቃሚ እና መረጃ ዝግጅትን ይበልጥ ይህን ቻናል እንደ ምሳሌ በማስመረጥ መነሻ እንዱለን። አዶናይ እናንተን እናንተን ለማዳን እና ከራስ ቻናለ᯽ን ለማረጋጋት ይህን ቻናል በመጪው ነፃ አንድ የመከላከያ ስለማድረግ ይህን ስለሚያስተማር ሊንኩሳርን መረጃ የሚሆነውን በአሰፋ እንደሚያከናውኑ ሆኖ ለእኛም በመሆን እኛ የኛ እና ለእናንተ ነን። እንዲህም ነው የእኛ ማንቸም ቻናሉ አዶናይ ።
13 Feb, 17:06
ለእኔ ባይነገረኝም 😇 የኢየሱስን መምጣት የናፈቁ ልጆች ግን ይሄን መልዕክት ትልቅ ቻሌንጅ አድርገውታል 🥰 እና እናንተ ምን ትጠብቃላቹ...
11 Feb, 17:21
11 Feb, 17:11
09 Feb, 17:34
ይህ የወንድሜ ጥያቄ
የእናንተም ጥያቄ ሊሆን ስለሚችል በሚገባቹ መልኩ ለማስረዳት ሞክራለው እናንተ ብቻ ማንበቡ ላይ በርቱልኝ 🥰 አብዛኞቻቹ በፁሎት ሰዓት ወይም ከፀሎት በኃላ ውስጣቹ የባዶነት ስማት የሚሰማቹ ሰዎች ከነኚ ሁለት አይነት አማኞች መካከል ልትሆኑ ትችላላችሁ...
...
በመንፈሳዊ ህይወታቸው ገና ያላደጉ፣ በግላቸውም ብዙም የመፀለይ ልምድ የሌላቸው ሰዎች ሲሆኑ እነኚ ሰዎች ለብቻቸው መፀለይ ሲጀምሩ መጀመሪያ አካባቢ ላይ በፀሎት ሰዓታቸው ላይ ምንም አይነት የተለየ መነቃቃት ላይሰማቸው ይችላል ይህ የሚሆነ በደንብ የውስጥ ሰውነታቸው መጠንከር ስላልጀመረ ነው በተጨማሪም ደግሞ የምታሰላስሉት የእግዚአብሔር ቃል እውቀት በውስጣቹ ከሌለ የፀሎት ጊዜያቹ ድካም የበዛበት ብሎም እንቅልፍ እና ድብርት የተጫጫነው ሊሆን ይችላል... በእንደዚህ አይነት ሁኔታ ውስጥ እንዳላቹ የሚሰማቹ ልጆች ካላቹ በሚቀጥለው ከዚህ ሁኔታ ውስጥ እንዴት በቀላሉ መውጣት እንደምትችሉ እነግራቿለው🥰...
በፀሎት ውስጥ ወይም ከፀሎት በኋላ የባዶነት አይነት ስሜት የሚሰማቸው ሰዎች ከመጀመሪያዎቹ በተቃራኒ በመንፈስ አለም የጠየከሩ፣ ውስጣቸውም በመንፈስ ርሃብ የሚቃጠልባቸው ልጆች ሊሆኑ ይችላል እኔም ብዙ ጊዜ በዚህ አይነት ሁኔታ ውስጥ አልፌ ስለማውቅ ሁኔታ ይገባኛል፤ እንደ ጤና ባለሞያ ነገርዬው በምልክት ባስቀምጠው በቀላሉ ትረዱኛላቹ ☺️...ለምሳሌ የ 15 ቀን ፆም ፀሎት ይዛቹ በደንብ እየፀለያቹ እያለ የሆነ ሰዓት ላይ ውስጣቹ ባዶ ይሆናል ተነስታቹ መጽሐፍ ቅዱሳቹ ታነባላቹ አሁንም ግን ከዚያ ሁኔታ ውስጥ መውጣት ይከብዳቿል ፤ በቀን 2 እና 3 ሰዓታት ከጌታ ጋር ጊዜ አሳልፋቹ ስትወጡ እንዳሰባቹ የመንፈስ እርካታ ላይሰማቹ ይችላል... ይህ የሚሆነው አንደኛ የእግዚአብሔር ፍቃድ የሌለበትን የሆነ Mistake በህይወታቹ ከሰራቹ እግዚአብሔር በዚህ አይነት መልኩ ወደ ፍቃዱ እንድትመለሱ ሊያደርጋቹ ይችላል ፤ ሁለተኛው እና አብዛኛው ጊዜ በዚህ አይነት ሁኔታ ውስጥ የምትገቡበት ምክንያት ከልክ ያለፈ መንፈሳዊ ርሃብ ውስጥ በምቶኑበት ጊዜ ነው አለ አይደል በቃ እስከ ጥግ ድረስ ውስጣቹ የእግዚአብሔር ክብር ሲፈልግ የሚሰማቹ መንፈሳዊ ርሃብ አይነት ልክ ያዕቆብ አለቅህም ብሎ ከእግዚአብሔር ጋር ትግልን እንደገጠመው ማለት ነው 🔥እናንተም የምትፈልጉት እስካላገኛቹ ድረስ በምንም አይነት ሁኔታ ውስጥ መርካት አትፈልጉም በዚህም ምክንያት ከፀሎት በኋላ እንኳን ምንም እንዳልተቀበላቹ ሊሰማቹ ይችላል ነገር ግን ይህ ትግል የሆነ ከፍታ ላይ ሲያደርሳቹ ትናንት ያልረካቹበት ፀሎት ቀስ በቀስ የእናንተ መዋያ ይሆናል ።እወዳቿለሁ 🥰
07 Feb, 17:01
01 Feb, 17:09
29 Jan, 17:39
27 Jan, 17:25
እኔን ለመጣል ምን ያልፈነቀላቹት ድንጋይ አለ እኔ እንደው አሁንም በጌታዬ እቅፍ ውስጥ ነኝ 😇..
እንደኔ በግ መሆን እና እንደናንተ ተኩላነት ቢሆን ኖሮ ገና ዱሮ ነበር የሚያልቅልኝ ነገር ግን በእኔ እና በእናንተ መካከል አንድ እኔን የሚጠብቅ መልካም እረኛ አለ💪 እና ብዙ አትድከሙ ኢየሱስ የሚባል ጀግና እረኛ አለኝ 🥰 26 Jan, 17:29
ሰሞኑን የዘማሪ ሐዋሪያው ዮሃንስን አንድ መዝሙር እየሰማሁ ከእኔ አልፎ ለናንተም የማካፍለውን ትልቅ መልዕክት በውስጡ አገኘው...
መልዕክቱ ከመናገሬ በፊት ግን አንድ ጥያቄ ልጠይቃቹ አሁን ላይ መኖራቹ ትርጉም ያለው ይመስላቿል ? ትርጉምስ አለው ካላቹን ህይወታቹ ትርጉም የኖረው ለእናንተ ነው ወይስ ለእግዚአብሔር ? ? ገና ሳትፈጠሩ በማህፀንም ሳይሰራቹ እግዚአብሔር እንድትኖሩለት ያሰበውን ያንን መኖር እየኖራቹ ከሆነ አዎ መኖራቹ በርግጥ አሁን ላይ ትርጉም አለው፤ ያሰበላቹን ሳይሆን ያሰባቹትን ፣ ፍቃዱን ሳይሆን ፍቃዳቹን ከኖራቹ ደግሞ ምንም ያህል እናንተ እየኖራቹ እንደሆነ ብታስቡም በእግዚአብሔር ዘንድ ግን ገና መኖር አልጀመራቹም፤ ሁላችንም በህይወታችን ውስጥ የምናገኛቸው ስኬቶችና ድሎች ትክክለኛ ትርጉም የሚኖራቸው ከእግዚአብሔር እንፃር ልክ ከሆኑ ብቻ ነው ካለዚያ ግን ድል ላይ ብዙ ድሎች ቢከመሩም እንኳን ሁል ጊዜ ተሸናፊዎች ነን።21 Jan, 16:53
አሁን ላይ ከጌታ ቤት ስትርቁ፣ ፀሎት ስታቆሙ እና በህይወታቹ ውስጥ የተሳሳተ ውሳኔ ስትወስኑ ልክ ናቹ ብለው ያጀቧቹ ሰዎች ነገ ላይ ስትጎዱ እና ስትደክሙ እናንተን ለማገዝ ማናቸውም አብረዋቹ አይቆሙም...
church ስትሄዱ የሚደብራቸው ሰዎች ካሉ እነርሱ ለማስደሰት ብላቹ Church ከምትቀሩ ለዘላለም እነርሱ እየደበራቹ ቢቀጥሉ ይሻላቸዋል፣ በመንፈሳዊ ህይወታቹም ስትበረቱና ፀሎት ስታበዙ ሙድ ለመያዝ የሚሞክሩ ጓደኞችም ካሏቹ እነርሱን ለመምሰል ብዙ አትጣጣሩ ተዋቸው ...
አንድ ወርቅ የያዘ ሰው ከዘጠና ዘጠኝ ድንጋይ ከያዙ ሰዎች ጋር አብሮ ቢሆንና ድንጋይ የያዙት ሰዎች ሙድ ቢይዙበት ይህ ሰው የግድ እነርሱን ለማስደሰት ብሎ የያዘውን ወርቅ መጣል ሳይሆን ያለበት እነርሱን ትቶ ወርቅ ከያዙ ሰዎች ጋር ነው መቀጠል ያለበት ካልሆነ ግን እነኚ ሰዎች በጊዜ ሂደት እነርሱ የያዙት ወርቅ እርሱ የያዘው ደግሞ ድንጋይ እንደሆነ አሳምነውት ትክክለኛውን ወርቅ ያስጥሉታል፤ Be Wise 😇 አሁን ያላቹበት ህይወት በጣም ውድ ነው፤ ሰዎች በዚህ ህይወት ላይ ሀሳብ እንዲሰጡበት አትፍቀዱላቸው።18 Jan, 17:17
አትሁኑ አላውቅም ነገር ግን በዚህ ሰዓት ከነኚ ሰዎች በላይ የት መዋል እንዳለባቸው በትክክል ያወቁ ሰዎች አይገኙም...
ብዙዎች በየ መጠጥ ቤቱና በየእርኩሰት ስፍራ ላይ በሚገኙበት በዚህ ሰዓት በጌታ እግሮች ስር ተንበርክኮ እንደመገኘት ያለ ትልቅ እድል የለም😭 የተወደዳቹ ጌታ በየቀኑ ኑሩበት ብሎ በእድሜያቹ ላይ ቀኖች ከተጨመረላቹ ላይቀር እነኛ ቀኖች እግሮቹ ስር ተንበርክካቹ የምታሳልፏቸው ቀኖቹ ይሁኑላቹ🔥 16 Jan, 17:08
ፍለጋ...ፍለጋ...ፍለጋ
ቀኞቼ ይለቁ አንተኑ ፍለጋ 😭
14 Jan, 17:10
እሷን ብቻ ይዘው ባንዴ ፀጥ የሚያደርጋትን ድንጋይ እየመረጡ በየአደባባዩ ትወገ ትወገ ብለው ሞቷን ደገሱላት......
ኢየሱስም አይቶ የድርሻውን ድንጋይ እንዲጥል ፈልገው ወደ እርሱ አመጧትና አንተስ ምን ትላለህ ? ብለው ጠየቁት፤ እርሱም ድንጋይ መወርወር ሲገባው ጥቂት ቃላት ወደ ከሳሾቿ ወርውሮ በድብቅ የሰሩትን ኃጢአት በግልፅ ገለጠባቸው ከዛም ድንጋይ ተሸክመው የመጡትን ሰዎች የሰሩትን ኃጢአት አሸክሟቸው ሸኛቸው ኃጢአቷን ይዛ የመጣችውን ሴት ግን የእርሱን ፅድቅ አካፍሏት በሰላም ሂጂ አላት.... የተወደዳቹ ሰዎች ስለናንተ ህይወት እድሉ ቢያገኙ ብዙ የሚያወሩት ይኖራቸዋል... ትወገር ፣ ትሙት
፣ ትጥፍ ፣ አይለፍላት ፣ አይሳካላት ፣ ብቻ ብዙ ነገር
ይላሉ ነገር ግን በእናንተ ህይወት ማንም ምንም ቢናገር መፍረድ እስካልቻለ ድረስ ምንም ማድረግ አይችልም፤ ለዚህ ነው ምን ይላሉ ሳይሆን ምን ይላል ብለን መጠበቅ የሚኖርብን።12 Jan, 17:35
10 Jan, 17:17
የውላቹ የተወደዳቹ እኛ አገልግሎታችን ለ Media ፍጆታ፣ ጌታን እንድናሳይበት የተሰጠንን መድረክ ደግሞ ለራስ ክብርና ለታይታ እንድናደርገው አይደለም የተጠራነው፤
መቼም ቢሆን ደግሞ የኛ ስህተት በታዋቂ ሰዎች ስለተደገፈ እና ህዝብ ስላጨበጨበለት ብቻ ትክክል አይሆንም፤ የሁላችንም ሀሳብ ልክ የሚሆነው ከእግዚአብሔር ቃል ጋር ከተስማማ ብቻ ነው ካለዚያ ልክ ናቸው ያልናቸው እውነታዎቻችን ሁሉ ስህተት ይሆናል፤ ክርስትናችንም ቢሆን የእውነት የሚሆነው ዘመን ከሚያመጣው ስልጣኔና በየዘመኑ ከሚነሳው የሰዎች ትምህርት በላይ በእግዚአብሔር እውነት ላይ ከተመሰረተ ብቻ ነው።07 Jan, 05:55
03 Jan, 17:26
💪🔥
..
...
😞🙇
ደግሞ ወደዛ ወደማቶዱት ህይወት ትመለሳላቹ... መድከም ትጀምራላቹ🙍 ያንን ትጋታቹን ትጥሉታላቹ፣ ኃጢአት Normal ይሆንባቿል ብቻ ብዙ
ነገር... አሁን በዚህ አይነት ድካም ውስጥ እያለፈ ያለ ሰው ካለ የምለው ነገር በደንብ ይገባዋል ብዬ አስባለሁ ፤ " ግን ለምንድነው ምደክመው ? " የብዙዎቻቹ ጥያቄ ነው እስቲ ላንዳፍታ ይሄ ጥያቄ በውስጣቹ የሚፈጠርባቹ ልጆች ጥቂት ጊዜ ወስዳቹ ዙሪያቹን
ተመልከቱ
...
የአባቴ ልጆች እናንተ አላስተዋላቹም እንጂ እኮ የእናንተ አድካሚዎች በዙሪያቹ ነው ያሉት
ለምሳሌ ጓደኞቻቹ ፣ የ social media አጠቃቀማቹ እና ሌላም
...
የተወደዳቹ እንደ ወንድም የምትሰሙኝ ከሆነ አንድ ምክር ልምከራቹ፤ እንድትደክሙ ከሚያደርጓቹ ነገሮች መካከል ራሳቹን አርቁ በቃ ወስኑ ፤ አውቃለው ከለመዳቹት ነገር መለየቱ ያማል ነገር ግን እያመማቹም ቢሆን 01 Jan, 17:49
የእኔነቴም መጨረሻ ያሳደጉኝ እጆች ላይ ይሁንልኝ...
እኔ ቤት ጓደኛ ፣ ገንዘብና ዝና ካንተ እንፃር ሲታዩ ምን አይነት ዋጋ የላቸውም፤ ከፊት ቢሆን ከኃላ፣ መጨረሻም ላይም ቢሆን መጀመሪያ ላይ አንተ ካለ ብቻ ነው የኔ ህይወት ትርጉም የሚኖረው፤ የኔ አባት ዛሬ እንደ ልጅ እጠይቅሃለሁ ከእጆች መዳፍ እንዳልርቅ ጥብቅ አድርገህ በፍቅር ያዘኝና እጆችህ ላይ ዘመኔን ልጨርስ😭 31 Dec, 17:40
ምን አይነት ህይወት ልኑርልህ... እንደ ልጅ ከኔ የምትፈልገው ምንድነው እንድትሉት ይፈልጋል
፤ ከጌታ ጋር የሚኖራቹ ህብረትም ፍሬያማ የሚሆነው በእናንተ ፍላጎቶችና ጥያቄዎች ላይ ብቻ ሳይሆን በእርሱም የልብ ፍቃድ ላይ የሚመሰረት ከሆነ ነው።27 Dec, 17:19
"እኛም የሆነ ሰሞን እንዲህ ነበርን " ፣ "ብዙ አታካብድ/ አታካብጂ " ፣ "ትደርሳለህ ቀስ በል" የሚሉ ምክር መሳይ ቃላቶች ከቅርብ ከሚባሉ ሰዎች ትሰማላቹ...
እነኚን ወደ ኃላ የሚጎትቷቹን ድምፆች አልሰማ ብላቹ ይበልጥ ከፍ ስትሉ ደግሞ እነኛው ሰዎች እናንተን በአካል ማግኘት ስለማይችሉ በጎን ለሚያውቋቹ ሰዎች በመጥፎ ተግባር ስማቹን ለማጥፍት ይሞክራሉ፤ እንደዚህ ዓይነት ሰዎች የግድ የእነርሱ ማንነት ለማተለቅ ሲሉ የሌሎችን ማንነት ማኮሰስ እንዳለባቸው የሚያምኑ ሰዎች ናቸው፤ ኢየሱስንም በዘመኑ የጠራቢው ልጅ ፣ አጋንንት ያደረበት እብድ መሪ የሚሉት ሰዎች ነበሩ ጌታ ግን ለእነርሱ ትችትና ስላቅ ምላሽ ከመስጠት ይልቅ በሽተኞችን እየፈወሰና ሙታኖችን እያስነሳ እርስ በርሳቸው ግራ እንዲጋቡ ማድረግን ነበር የመረጠው፤ ዛሬም በእናንተ ህይወት ውስጥ እንደዚህ አይነት ባህሪ ያላቸው ሰዎች ካሉ በእነርሱ ላይ ኢየሱስ ካደረገው የተለየ ነገር ለማድረግ አትሞክሩ፤ የእናንተ ዝምታ ብቻ ለእነርሱ ትልቅ ጥያቄ ነው፤ ዝም ብላቹ ጉዟቹን ቀጥሉ።26 Dec, 18:49
24 Dec, 17:18
21 Dec, 17:07
19 Dec, 17:11
17 Dec, 17:52
13 Dec, 17:14
11 Dec, 17:32
07 Dec, 17:54
03 Dec, 17:26
ይስሃቅ በዛ ቤት ቢጠይቅ የማይሰጠው ቢፈልግ የማያገኘው ምንም ነገር አይኖርም፤ ነገር ግን ምንም ያህል በተአምር የተገኘ የቤቱ ብቸኛ ልጅ ቢሆንም ከእግዚአብሔር ድምፅ በላይ ግን ተሰሚነት የለውም...
እዚህ ቤት ከይስሃቅ ይልቅ ለእግዚአብሔር ነበር ምን ላድርግልህ የሚባለው ፤ አብርሃም ለአምላኩ ለእግዚአብሔር እንኳን ልቡ የሚሳሳለትን ውዱን ይስሃቁን እንኳን ይሰጠዋል ለዛውም መስዋአት አድርጎ 💯 የተወደዳቹ የአባቴ ልጆች አሁን ላይ ብዙ ሰዎች በየቤታቸው አንድ ትኩረት የሚሰጡት ጉዳይ አላቸው አንዳንዱ ጋር ቤተሰቡ፣ ሌሎቹ ጋር ደግሞ ስራቸው እና ገንዘባቸው ዋና ጉዳያቸው ነው እንደ አብርሃም ያሉ ሰዎች ጋር ግን የእግዚአብሔር ነገር በጣም ከጓጉለት ነገር በላይ ትኩረትና ተሰሚነት አለው፤ ለካስ የእኛ ቤት ይስሃቅ ፤ ነገ ላይ ህዝብ የሚሆነው ከእግዚአብሔር በታች የሚሰማ ከሆነ ብቻ ነው።29 Nov, 17:21
ሰሞኑንን ጌታን አምርሬ አንድ ጥያቄ እየጠየኩት ነው...
ተጠቀምብኝ ብዬ 😭 እድሜ ከሰጠህኝ ላይቀር ፣ ካሰነበትከኝ ላይቀር ለክብርህ የሚሆን እቃ እድርገህ በሙሉ መልክህ ታይብኝ እያልኩት ነው ...
መኖርንማ ጌታን የማያውቁትም ይኖራሉ የኛ ኑሮ ግን ከስም ባለፈ እርሱን በማሳየት ሲኖር ነው ተኖረ ሚባለው፤ ካለዚያ በእድሜያችን ላይ የሚጨመሩልን ቀናቶች ዋጋ አይኖራቸውም። 17 Nov, 17:33
ይሄ መዝሙር ፀሎትም ጭምር ነው
መንፈስ ቅዱስ የግድ ታስፈልገኛለህ 🔥
14 Nov, 09:57
11 Nov, 17:05
“እግዚአብሔር
ዓለቴ፥ አምባዬ፥ መድኃኒቴ፥ አምላኬ፥ በእርሱም የምተማመንበት
ረዳቴ፥ መታመኛዬና የደኅንነቴ ቀንድ መጠጊያዬም ነው።” — መዝሙር
18፥
2
04 Nov, 17:15
02 Nov, 17:32
ይሄ ድምፅ ጥያቄዎቿን ሁሉ የሚመልስላት የምቶደው የመምህሯ ድምጽ ነበር
... ማርያም በጣም በሚያስፈራ በመቃብር ስፍራ አጥብቃ የፈለገችው የህይወቷ መምህር በመጨረሻ ራሱን በትንሳኤ አካል ገለጠላት
።30 Oct, 17:18
የህይወቴ ርዕስ ፣ የአገልግሎቴ ሁሉ ድምቀት የወጣትነቴ ውበት መንፈስ ቅዱስ ...
በዘመኔ ካላንተ ህልውና ካላንተ መገኘት የምኖርባቸው ቀኖች አይደሉም ሰዓታት አይኑሩኝ28 Oct, 17:36
26 Oct, 17:14
24 Oct, 17:26
23 Oct, 22:53
አልዋሽህም ደና ነኝ ብዬ 😔
አልዋሽህም ብርቱ ነኝ ብዬ
እንደገና ስራኝ እንደገና
እንደገና ዳሰኝ እንደገና 😥
23 Oct, 17:36
መጠቀም ሰዎችን ግራ ለማጋባት ካልሆነ በቀር ሌላ አላማ የለውም።
22 Oct, 17:25
ያየኽውን እንደሚያይ ለዛም ራሱን እንደሚለይ ግብ የሆነ ያንተ ክብር ከነብሱም ጋር የማይማከር ስራኝ እንደዚህ እንደ ክቡር እቃ ላየኽው ለመጨረሻው ዝናብ እንድበቃ ስራኝ እንደዚህ እንደ ክብሩ እቃ ላየኽው ለክብር ቀን እንድበቃ 😭
20 Oct, 17:16
እግዚአብሔር ለዚህ ነው በእርሱ ብቻ የሚመለስ ጥያቄ በእያንዳንዳችን ህይወት ውስጥ ያስቀመጠው፤ ሀና ቤት ለረጅም ጊዜ ጥያቄ የነበረው ሳሙኤል የሆነ ቀን እግዚአብሔር በዛ ቤት እንዳለ እንደተናገረ ሁሉ
እናንተም ቤት መፍትሄ ያጣቹባቸው ጥያቄዎቻቹ አንድ ቀን እግዚአብሔር እንዳለ በግልፅ ይናገራሉ።19 Oct, 17:54
17 Oct, 17:15
ነገር ግን ይሳቅን አገኛለው ብሎ አጋር ጋር የሄደው አብርሃም ከአጋር ማግኘት የቻለው የተጠበቀውን ይሳቅን ሳይሆን ያልታሰበውን እስማኤልን ነበር ....
ለካስ የተስፍው ቃል ባለቤት ይስሀቅ ያለው ያረጀቺው ሳራ ጋር እንጂ ወጣቷ አጋር ጋር አልነበረም ፤ አብርሃም ተሸወደ 😊 የተወደዳቹ እግዚአብሔር የእናንተን ይሳቅ ጠብቃቹት እንጂ አቋራጭ መንገድ ተጠቅማቹ እንድታገኙት በፍፁም አይፈልግም፤ ጌታ የነገራቹን ቃል የሚፈፅምበት የራሱ ጊዜ አለው እናንተ ብቻ የተባላቹትን በተባላቹት ስፍራ ላይ ሆናቹ ጠብቁ
።14 Oct, 17:37
09 Oct, 17:09
ትናንት ይሁዳ ላላወቀው የኢየሱስ ሰውነት ሰላሳ ዲናር ዋጋ ሲሰጠው ማሪያም ግን ሰላሳ ዲናር ለተሰጠው ሰውነት እግሮች ከሶስት መቶ ዲናር በላይ
የሚያወጣውን ውድ ሽቶ አፈሰሰችበት ፤ የተወደዳቹ ዛሬ አንድ ጥያቄ ልጠይቃቹ በእናንተ ህይወት ውስጥ ለኢየሱስ ዋጋ ስጡት ብትባሉ ስንት ትሰጡት ይሆን ለእግሮቹስ ምን የሚሰበር ነገር ይሆራቿል ? ከእርሱ ጋር መዋልና እግሩቹ ስር መቆየት በፍፁም ኪሳራ አይደለም እንደ ማርያምም ውዱን አልባስጥሮስ ሽቶ እግሮቹ ላይ መስበርም ማባከን አይደለም፤ በመንፈስ ቅዱስ በኩል የጌታ ዋጋ እየገባቹ ሲመጣ እናንተ ህይወት ውስጥ ትናንት ላይ ትልቅ ቦታ የነበራቸው ነገሮች ቀስ በቀስ ዋጋ እያጡ ይመጣሉ።06 Oct, 17:18
ዛሬስ እኛን ምን ይሆን የወሰደን ተጠቀሙበት ብሎ የሰጠን ገንዘብ ወይስ አገልግሉበት ብሎ የሰጠን መድረክ ? የቱ ይሆን ?
አሁን ላይ ሰይጣን ከወሰደብን ነገር ይልቅ ትናንት ከጌታ ተቀብለነው ዛሬ ላይ እኛን የወሰደን ነገር ይበልጣል። ሰለሞን ጥበብን ፣ ሳምሶን ሀይልን ፣ ይሁዳ ደግሞ ደቀ-መዝሙርነት የተቀበሉት ከጌታ ነበር ነገር ግን ሁሉም የተሰጣቸውን ነገር እንዴት መጠቀም እንዳለባቸው ባለማወቃቸው ምክንያት ኃላ ላይ የተሰጣቸው ስጦታ ከሰጪ እንደበለጠባቸው መጽሐፍ ይነግረናል፤ እናንተ ቤት ግን ሰጪው ንጉስ ይሁን🔥04 Oct, 17:15
ነገር ግን ለአሁን የ Airdrop ጉዳይ አግባብ ነው ወይስ አይደለም ማለቱን ትተን ከጀርባ በወጣቱ ልብ ላይ እየሰሩትን ያለውን ስራ በጥቂቱ እንመልከት...
እንደምታውቁት ገንዘብ የሁላችንም ደካማ ጎን ነው በተለይ ለወጣቶች ታዲያ በዚህ ደካማ ጎናችን በኩል መጥተው የያዝነውን እውነት ቀስ በቀስ በገንዘባቸው እያባበሉ እየነጠቁን እንደሆነ ስንቶቻቹ አስተውላቿል ? አሁን ብዙዎቻቹ በቀላሉ ገንዘብ ብንሰራ ችግሩ ምኑ ጋር ነው ልትሉኝ ትችላላችሁ እኔም በቀላል መንገድ ገንዘብ ማግኘት ስህተት ነው እያልኳቹ አይደለም ነገር ግን እንዲህ መስቀል በሚዘቀዝቁ እና በጌታ ስራ ላይ በሚቀልዱ ድርጅቶች ስር ሆኖ ታፕ ታፕ እያደረጉ ገንዘብ መሰብሰብ ለጭለማው መንግስት ድጋፍ እንደመስጠት ነው የሚቆጠረው፤ እነኚ ድርጅቶች ለጊዜው የሆነ ገንዘብ ሊሰጧቹ ይችላሉ ነገር ግን ከገንዘቡ ባለፈ ዋናው አላማቸው እናንተ ለመጨረሻው ዘመን ያላቹን ንቃት ማጥፋትና የጌታን መምጣት እንድትረሱት ማድረግ ነው፤ ስለዚህ እንደ መንፈሳዊ ሰው በዚህ ጉዳይ ላይ ቆም ብላቹ አስቡበት።29 Sep, 17:31
ጌታ በሌለበት መዋል ስታበዙ፣ ከፍቃዱ መስመር ስትርቁ የሚሰማቹን ፍርሃት
ውደዱት።27 Sep, 17:32
፤
ታዲያ በመጨረሻ ልጅ የትናንቱን ጥፍት እየሰበ ከወሰነው ባርነት ይልቅ አባት ልጅነቱን እያሰበ የወሰነው ክብር በልጦ ተገኘ
።እናንተ ትናንት ላይ ያጠፋቹትን ጥፍት እያሰባቹ ለራሳቹ ከሰጣቹት ስፍራ በላይ ጌታ ልጅነታቹን እያሰበ ያዘጋጀላቹ ያ የክብር ስፍራ ይበልጣል።
18 Sep, 17:56
ሰራቂዎች
፥ ብዙ በኃጢአት እንድትወድቁ የሚፈልጉ ሀሳቦች ቢኖሩም ከሁሉም በላይ ግን ፀንታቹ እንድትቆሙ የሚያደርጋቹ የምህረት እጅ እንዳለ አትርሱ ፤ በዚህ ሰዓት ደክማቹ፣ አቅም አታቹ ይሄን መልዕክቴኝ የምታነቡ የአባቴ ልጆች ካላቹ
እግዚአብሔር የደከሙበትን ልጆቹን ወደ እርሱ የሚጠራበት ምህረት የሚባል የፍቅር ቋንቋ እንዳለው ልነገራቹ ፈልጋለው።14 Sep, 17:39
ይሄን መዝሙር በሰማሁ ቁጥር በመንፈስ እነካለሁ🔥
ምን አይነት መንፈስ የሞላበት መልዕክት ነው
🥰